#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ለቤት ወጪ እያልኩ ከምሰጣት ገንዘብ ላይ እያብቃቃች ልዩ ልዩ ተጨማሪ የማድ ቤት ቁሳቁሶች ገዛች፡፡ ዕቃዎቹ ሳይሆኑ ቁጠባዋ አስደሰተኝ።
የወዲያነሽ' ዛሬ የማድረው ወላጆቼ ቤት ነው፡፡ ስለዚህ እንዳትሠጊ ትፈሪያለሽ እንዴ?» ብያት በምሄድበት ጊዜ «ለእኔ ብለህ እኮ ተሠቃየህ ወይ አበሳህ» በማለት ራሷን ታማርራለች፡፡
ከዋል አደር የወህኒ ቤቱን ሕይወቷን እየረሳች አዲሱን ኑሮ ተላመደች::
ፈገግታዋ" ለዛና ጨዋታዋ ቀስ በቀስ ጎረፈ፡፡ እኔ ግን ወላጆቼ እንዳሰቡትና
እንደ ተመኙት ሳይሆን፣ ማንም ሳያውቅና ሳይሰማ፣ ጠላ ሳይጠመቅ፣ ጠጅና
ፍሪዳ ሳይጣል፣ ድንኳን ሳይተከል፣ ዕልልታና ሆታው ሳይቀልጥ፣ ጉልበት ስማ ሳልመረቅ፣ ከአንዱ የመከራ ጊዜ ጓደኛዬ በስተቀር ሚዜ ሳልመርጥና
ሳልመለምል፣ ሞላ ጎደለ ብዬ ሳልማስን፣ የእኔ ናት ብዬ ያመንኩባትንና ሕሊናዬ
ሙሉ በሙሉ የተቀበላትን የወዲያነሽን የኑሮ ጓደኛዪ ኣድርጌ ጎጆ ወጣሁ፡፡
ወደዱም ጠሉም የወዲያነሽ የሕይወቴ ምሰሶ ሆና በይፋ ብቅ የምትልበት ብሩህ
ቀን መምጣቱ አይቀርም፡፡
የተከራየነው የጉልላት አጎት ቤት አርጀትጀት ያለ በመሆኑ ግድግዳው
ላይ የተለጠፉት የአዲስ ዘመንና የሰንደቅ ዓላማችን ጋዜጦች ተገሽላልጠው ፀሐይ
እንዳጠቃው የሙዝ ቅጠል ዐልፎ ዐልፎ ተሽመልምለዋል። ምርጊቱ ላይ ተለጥፈው የተጋደሙት የጤፍ ጭዶች ይታያሉ፡፡ ያም ሆነ ይህ የወዲያነሽ
አብራኝ ስላለችና አብሬያት ስላለሁ ያለሁትና ያለችው በፍቅር ውብ እልፍኝ
ውስጥ ነው፡፡ ከፋ ሲለኝና ሐሳብ ሲያስጨንቀኝ ግን «የሕይወት ጥቀርሻ» ማለቴ አይቀረም፡፡
ምንጊዜም ቢሆን ጉልላትና የወዲያነሽ ባንድ ላይ ተቀምጠውም ሆነ ቆመው ሲያወሩ ደስ ይላሉ። የናቴ ልጅ እንኳ እንደ ጋሼ ጉልላት አይሆንልኝም፣ ጋሼ ጉልላት! ጋሼ ጉልላት ያንጀት ናቸው» ትላለች፡፡
ዓርብ ማታ ነበር፡፡ የወዲያነሽ ከተፈታች 17 ቀን ሆኗታል፡፡ ጉልላት ጀምሮልኝ የነበረውን ሐሳብ «ያም ሆነ ይህ ያለፈው ሁሉ ዐልፏል። የመጪውን ጊዜ ኑሮ ለማስተካከል ከባድ ጥረት ያስፈልጋል» አለና ዝም አለ። ዝም የማለትም
አመል አለበት። ይህን ተናግሮ እንደ ጨረሰ ሐሳቡን እያሰላሰልኩና እየሸነሸንኩ
በማሰብ በቆምኩባት መሬት ላይ የተተከልኩ ይመስል ውልፍት ሳልል ብዙ
ደቂቃዎች ቆየሁ፡፡ የሰበሰቡን አራት ማዕዘን አግዳሚ ዕንጨት እንደያዝኩ ትንሽ ቀና ብል ምሥራቃዊውን የበጋ ሰማይ ባዘቶ የሚመስል ደመና እዚህና እዚያ ጉች ጉች ብለውበታል። በውስጡ በሚከናወነው የአየር ግፊት ሜክንያት ደመናው ተለዋዋጭ ቅርፆች እየሰራ ወደ ምእራብ ተጓዘ።ደመናው ወደ ምእራብ በገሠገሠ ቁጥር የተለያየ ውበትና መጠን ያላቸው ከወክብት ወደ ምስራቅ የሚጓዙ ይመስላሉ ደመናው ጥርግ ብሎ ከሄደ በኋላ ግን እንደ ነባር አቀማመጣቸው በየነበሩበት ቀጥ ብለው ይቀራሉ።የእኔም ሐሳብ ይጓዝ ይክነፍ ይመጥቅ ይውዘገዘግና አንዲት ተራ የሐሳብ ድንበር ሳያገኝ ቀጥ ይላል።
የእናቱን ጡት እያነፈነፈ እንደሚፈልግ የውሻ ቡችላ ሐሳብ ሲያነፈፍ የቆየው ጉልላት እንግዲህ» ብሉ ንግግሩን ጀመር ሲያደርግ ወደ እርሱ መለስ ብዬ ማዳመጥ ጀመርኩ። በሕይወት ውስጥ ባሉት የኑሮ ጐዳናዎች በምትጓዝበት ጊዜ የሚያጋጥሙህን ፈተናዎችና ትግሎች ሁሉ ሳትሸሽና ሳታመነታ መታገል ይገባሃል፡፡ በዕንባዋ የሚረጥቡት ዐይኖቿ ያሳዝኑኛል፡፡ሥቃይዋ ይመረኛል' ማለት በቂ አይደለም፡፡ ማዘን ቢሉህ ማዘን አይምሰልህ።አንድ ምጽዋት ሰጪ ሃይማኖተኛ የሰማይ በር ያስከፍትልኛል ለሠራሁት ኃጢአት መደምሰሻ ይሆንልኛል ብሎ ለአንድ ለማኝ ቁራሽ ሲሰጥ ያዝናል፤ ያን በማድረጉ የራሱን የማይታይ ሥውር ጥቅም ጨመረ እንጂ ለማኙን ከራሱ
ጋር አላስተካከለውም፡፡ አድርግም ቢባል እሺ አይልም፡፡ አንተ ግን ከዚህ የተለየህ
ሁን። አሁን በምትኖርበት ኅብረተሰብ ውስጥ የመልካም ኑሮዋ ጀንበር
እንድትወጣና እንድትጠልቅ የምታደርጋት አንተ መሆንህን ዕወቅ።
«እኔም ራሲ ማን መሆኔን ለማወቅ የምችለውና ምግባሬን አሻግሬ
በማየት እኔነቴን ለማወቅ የምበቃው የአንተን የትግል አረማመድና ውጤት
እየተመለከትኩ ነው» ብሎ በእኔ ላይ ሙሉ እምነትና ተስፋ እንዳለው ለማረጋገጥ ረጋ ባለ ሁኔታ ምራቁን ውጦ ዝም እለ፡፡ እንደገና ከወደ ምሥራቅ የመጣው ደመና የከዋክብቱን ብርሃን እየጋረደው ሲሄድ አካባቢያችን ግራጫ ጨለማ አለበሰው።
በየወዲያነሽ ሕይወት ላይ የደረሰውን የመጥፎ ልማድ ውጤት ሁሉ በማስወገድ ሌላ አዲስ ትርጉምና ይዞታ እንዲያገኝ ለማድረግ የገባሁትን የተግባር ቃል አሳጥፈውም፡፡ መሸከም የሚገባኝን ቀንበር ከዛሬ ጀምሬ እሸከማለሁ፡፡ ሆኖም
ድል ማድረግ አለብህ ማለት ሳይሆን የሚጠብቀኝን ተቃውሞና የቤተሰብ መራር አንካሰላንትያ እንድታውቅልኝ ያስፈልጋል” አልኩና እንደ አዲስ ትክል የቤት ምሰሶ ቀጥ ብዬ ቆምኩ፡፡
ጉልላት ራሱን እየነቀነቀ ወደ ቤት ገባ፡፡ ተከትዬው ገባሁና አጠገቡ ተቀመጥኩ፡፡ የወዲያነሽ የጣደችው ሻይ እየተንተከተከ እንፋሎቱ አየር ውስጥ እየገባ ይዋጣል፡፡ እሷ እንገቷን ደፍታ በጎድጓዳ ሳህን ውስጥ የሻይ ስኒ ታጥባለች፡፡
አሮጊቷ ሠራተኛ ትንሽ ራቅ ብለው ጉልበታቸውን ኣቅፈው ያንጎላጃሉ፡፡
በጣም ጫን ሲላቸው ለሰስተኛ ንፋስ እንደምታወዛውዛት መቃ ወደ ጎን ወይንም ወደ ፊት ጠንቀስ ይሉና ደንገጥ ብለው ቀና ሲሉ ትናንሽ ዐይኖቻቸው ብልጭ ብለው ይከደናሉ፡፡ ሻዩ ተቀድቶ ቀረበልን፡፡
ጉልላት እንፋሎቱ እየተነነ የሚወጣውን ሻይ እየተመለከተ «እኔ እኮ የምልህ» ብሎ ንግግር ጀመረ የሁለታችን ጠንካራ ፍቅርና አንድነት ብዙ ነገር መጀመርና መፈጸም የሚችል መሆን አለበት፡፡ ከእንግዲህ ወዲህ እብራችሁ
መታገልና የሚያጋጥማችሁ የጋራ መሰናክል ሁሉ ሽንጣችሁን ገትራችሁ
መቋቋም እንጂ መሽሽና ያላግባብ ማፈግፈግ የእናንተ ድርሻ መሆን የለበትም፡፡
በተለይም አንተ እሷን እያጠናከር ክና ሳትነጠል ለአዲስ ዘላቂ ግብ
የሚገሠግሥ እውነተኛ ዓላማ እንዳለሁ አሳይ። አንተ በኑሮህ እና በትምህርትህ
ምክንያት የተሻለ ዕውቀትና ችሎታ አለህ፡፡ ምሳሌዩ ቅር እንዳያሰኝህ እጂ
ቀላዋጭ የሚቀላውጠው የአስቀልዋጩን ያህል ስለሌለው ወይም በግልጽ በሥውር ስለ ተነጠቀ ነው፡፡ ያም ሆነ ይህ አግዛት፣ አብራህ ትሠለፋለች::
ዓርማህን በፅናት ለመትከል ካልተጣጣርህና አካባቢህንም ለመለወጥ እምነትህን ካላስፋፋህ የጥንቱ ልማድ እንደ ክፉ አውሬ አሳዶ ይበላሃል። የበሰለ ሕሊና ያለው ሰው የምትሰኘውም ብዙዎችን ላስቸገረ ከባድ ጥያቄ መልስ ለማግኘት ስትል ከራስህ አልፈህ በተግባር የሚተባበሩህን መልካም ሰዎች በማፍራት ለዘላቂ መፍትሔ ስትታገል ነው፡፡ የዚህን የአሁኑን ሕይወት ቅርፅና ይዘት መለወጥ ያስፈልጋል። አሮጌውንና ለሕዝብ የማይጠቅመውን ነገር ሁሉ እያፈራረሱ በአዲስ የአኗኗር ስልት መተካት ይገባል፡፡ ግን አፈጻጸሙ እንደ አወራሩ ቀላል አይደለም» ብሎ በንግግሩ መኻል በረድ ያለችውን ሻይ መጠጣት ጀመረ፡፡
የወዲያነሽ ጉልላት ስለ እኔና ስለ እርሷ እንደ ተናገረ ስለ ገባት የመጨነቅ ሁኔታ ፊቷን ወረረው:: በስኒው ውስጥ የቀረችውን ሻይ ጨለጠና
የወዲያነሽን አሻግሮ እያየ «አንቺም ከእንግዲህ ወዲህ ነቃ ነቃ በይ! ይኸ ዐይን እስኪያብጥ እያለቀሱ አጉል መተከዝ በፍፁም አይጠቅማችሁም፡፡ ምንም እንኳ እንዳንቺ ወህኒ ቤት ገብተን ባንታሰርም እኛም ያንችኑ ያህል ከውጪ ሆነን ተሠቃይተናል። ሐሞትሽን ኮስተር አድርገሽ ለመታገል ከበረታሽ መልካሟ
የቤትሽ እመቤት አንቺ ብቻ ነሽ» ብሎ ጠበል እንዳልጠቀመው በሽተኛ ሻይ
እንዳስሞላለት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ለቤት ወጪ እያልኩ ከምሰጣት ገንዘብ ላይ እያብቃቃች ልዩ ልዩ ተጨማሪ የማድ ቤት ቁሳቁሶች ገዛች፡፡ ዕቃዎቹ ሳይሆኑ ቁጠባዋ አስደሰተኝ።
የወዲያነሽ' ዛሬ የማድረው ወላጆቼ ቤት ነው፡፡ ስለዚህ እንዳትሠጊ ትፈሪያለሽ እንዴ?» ብያት በምሄድበት ጊዜ «ለእኔ ብለህ እኮ ተሠቃየህ ወይ አበሳህ» በማለት ራሷን ታማርራለች፡፡
ከዋል አደር የወህኒ ቤቱን ሕይወቷን እየረሳች አዲሱን ኑሮ ተላመደች::
ፈገግታዋ" ለዛና ጨዋታዋ ቀስ በቀስ ጎረፈ፡፡ እኔ ግን ወላጆቼ እንዳሰቡትና
እንደ ተመኙት ሳይሆን፣ ማንም ሳያውቅና ሳይሰማ፣ ጠላ ሳይጠመቅ፣ ጠጅና
ፍሪዳ ሳይጣል፣ ድንኳን ሳይተከል፣ ዕልልታና ሆታው ሳይቀልጥ፣ ጉልበት ስማ ሳልመረቅ፣ ከአንዱ የመከራ ጊዜ ጓደኛዬ በስተቀር ሚዜ ሳልመርጥና
ሳልመለምል፣ ሞላ ጎደለ ብዬ ሳልማስን፣ የእኔ ናት ብዬ ያመንኩባትንና ሕሊናዬ
ሙሉ በሙሉ የተቀበላትን የወዲያነሽን የኑሮ ጓደኛዪ ኣድርጌ ጎጆ ወጣሁ፡፡
ወደዱም ጠሉም የወዲያነሽ የሕይወቴ ምሰሶ ሆና በይፋ ብቅ የምትልበት ብሩህ
ቀን መምጣቱ አይቀርም፡፡
የተከራየነው የጉልላት አጎት ቤት አርጀትጀት ያለ በመሆኑ ግድግዳው
ላይ የተለጠፉት የአዲስ ዘመንና የሰንደቅ ዓላማችን ጋዜጦች ተገሽላልጠው ፀሐይ
እንዳጠቃው የሙዝ ቅጠል ዐልፎ ዐልፎ ተሽመልምለዋል። ምርጊቱ ላይ ተለጥፈው የተጋደሙት የጤፍ ጭዶች ይታያሉ፡፡ ያም ሆነ ይህ የወዲያነሽ
አብራኝ ስላለችና አብሬያት ስላለሁ ያለሁትና ያለችው በፍቅር ውብ እልፍኝ
ውስጥ ነው፡፡ ከፋ ሲለኝና ሐሳብ ሲያስጨንቀኝ ግን «የሕይወት ጥቀርሻ» ማለቴ አይቀረም፡፡
ምንጊዜም ቢሆን ጉልላትና የወዲያነሽ ባንድ ላይ ተቀምጠውም ሆነ ቆመው ሲያወሩ ደስ ይላሉ። የናቴ ልጅ እንኳ እንደ ጋሼ ጉልላት አይሆንልኝም፣ ጋሼ ጉልላት! ጋሼ ጉልላት ያንጀት ናቸው» ትላለች፡፡
ዓርብ ማታ ነበር፡፡ የወዲያነሽ ከተፈታች 17 ቀን ሆኗታል፡፡ ጉልላት ጀምሮልኝ የነበረውን ሐሳብ «ያም ሆነ ይህ ያለፈው ሁሉ ዐልፏል። የመጪውን ጊዜ ኑሮ ለማስተካከል ከባድ ጥረት ያስፈልጋል» አለና ዝም አለ። ዝም የማለትም
አመል አለበት። ይህን ተናግሮ እንደ ጨረሰ ሐሳቡን እያሰላሰልኩና እየሸነሸንኩ
በማሰብ በቆምኩባት መሬት ላይ የተተከልኩ ይመስል ውልፍት ሳልል ብዙ
ደቂቃዎች ቆየሁ፡፡ የሰበሰቡን አራት ማዕዘን አግዳሚ ዕንጨት እንደያዝኩ ትንሽ ቀና ብል ምሥራቃዊውን የበጋ ሰማይ ባዘቶ የሚመስል ደመና እዚህና እዚያ ጉች ጉች ብለውበታል። በውስጡ በሚከናወነው የአየር ግፊት ሜክንያት ደመናው ተለዋዋጭ ቅርፆች እየሰራ ወደ ምእራብ ተጓዘ።ደመናው ወደ ምእራብ በገሠገሠ ቁጥር የተለያየ ውበትና መጠን ያላቸው ከወክብት ወደ ምስራቅ የሚጓዙ ይመስላሉ ደመናው ጥርግ ብሎ ከሄደ በኋላ ግን እንደ ነባር አቀማመጣቸው በየነበሩበት ቀጥ ብለው ይቀራሉ።የእኔም ሐሳብ ይጓዝ ይክነፍ ይመጥቅ ይውዘገዘግና አንዲት ተራ የሐሳብ ድንበር ሳያገኝ ቀጥ ይላል።
የእናቱን ጡት እያነፈነፈ እንደሚፈልግ የውሻ ቡችላ ሐሳብ ሲያነፈፍ የቆየው ጉልላት እንግዲህ» ብሉ ንግግሩን ጀመር ሲያደርግ ወደ እርሱ መለስ ብዬ ማዳመጥ ጀመርኩ። በሕይወት ውስጥ ባሉት የኑሮ ጐዳናዎች በምትጓዝበት ጊዜ የሚያጋጥሙህን ፈተናዎችና ትግሎች ሁሉ ሳትሸሽና ሳታመነታ መታገል ይገባሃል፡፡ በዕንባዋ የሚረጥቡት ዐይኖቿ ያሳዝኑኛል፡፡ሥቃይዋ ይመረኛል' ማለት በቂ አይደለም፡፡ ማዘን ቢሉህ ማዘን አይምሰልህ።አንድ ምጽዋት ሰጪ ሃይማኖተኛ የሰማይ በር ያስከፍትልኛል ለሠራሁት ኃጢአት መደምሰሻ ይሆንልኛል ብሎ ለአንድ ለማኝ ቁራሽ ሲሰጥ ያዝናል፤ ያን በማድረጉ የራሱን የማይታይ ሥውር ጥቅም ጨመረ እንጂ ለማኙን ከራሱ
ጋር አላስተካከለውም፡፡ አድርግም ቢባል እሺ አይልም፡፡ አንተ ግን ከዚህ የተለየህ
ሁን። አሁን በምትኖርበት ኅብረተሰብ ውስጥ የመልካም ኑሮዋ ጀንበር
እንድትወጣና እንድትጠልቅ የምታደርጋት አንተ መሆንህን ዕወቅ።
«እኔም ራሲ ማን መሆኔን ለማወቅ የምችለውና ምግባሬን አሻግሬ
በማየት እኔነቴን ለማወቅ የምበቃው የአንተን የትግል አረማመድና ውጤት
እየተመለከትኩ ነው» ብሎ በእኔ ላይ ሙሉ እምነትና ተስፋ እንዳለው ለማረጋገጥ ረጋ ባለ ሁኔታ ምራቁን ውጦ ዝም እለ፡፡ እንደገና ከወደ ምሥራቅ የመጣው ደመና የከዋክብቱን ብርሃን እየጋረደው ሲሄድ አካባቢያችን ግራጫ ጨለማ አለበሰው።
በየወዲያነሽ ሕይወት ላይ የደረሰውን የመጥፎ ልማድ ውጤት ሁሉ በማስወገድ ሌላ አዲስ ትርጉምና ይዞታ እንዲያገኝ ለማድረግ የገባሁትን የተግባር ቃል አሳጥፈውም፡፡ መሸከም የሚገባኝን ቀንበር ከዛሬ ጀምሬ እሸከማለሁ፡፡ ሆኖም
ድል ማድረግ አለብህ ማለት ሳይሆን የሚጠብቀኝን ተቃውሞና የቤተሰብ መራር አንካሰላንትያ እንድታውቅልኝ ያስፈልጋል” አልኩና እንደ አዲስ ትክል የቤት ምሰሶ ቀጥ ብዬ ቆምኩ፡፡
ጉልላት ራሱን እየነቀነቀ ወደ ቤት ገባ፡፡ ተከትዬው ገባሁና አጠገቡ ተቀመጥኩ፡፡ የወዲያነሽ የጣደችው ሻይ እየተንተከተከ እንፋሎቱ አየር ውስጥ እየገባ ይዋጣል፡፡ እሷ እንገቷን ደፍታ በጎድጓዳ ሳህን ውስጥ የሻይ ስኒ ታጥባለች፡፡
አሮጊቷ ሠራተኛ ትንሽ ራቅ ብለው ጉልበታቸውን ኣቅፈው ያንጎላጃሉ፡፡
በጣም ጫን ሲላቸው ለሰስተኛ ንፋስ እንደምታወዛውዛት መቃ ወደ ጎን ወይንም ወደ ፊት ጠንቀስ ይሉና ደንገጥ ብለው ቀና ሲሉ ትናንሽ ዐይኖቻቸው ብልጭ ብለው ይከደናሉ፡፡ ሻዩ ተቀድቶ ቀረበልን፡፡
ጉልላት እንፋሎቱ እየተነነ የሚወጣውን ሻይ እየተመለከተ «እኔ እኮ የምልህ» ብሎ ንግግር ጀመረ የሁለታችን ጠንካራ ፍቅርና አንድነት ብዙ ነገር መጀመርና መፈጸም የሚችል መሆን አለበት፡፡ ከእንግዲህ ወዲህ እብራችሁ
መታገልና የሚያጋጥማችሁ የጋራ መሰናክል ሁሉ ሽንጣችሁን ገትራችሁ
መቋቋም እንጂ መሽሽና ያላግባብ ማፈግፈግ የእናንተ ድርሻ መሆን የለበትም፡፡
በተለይም አንተ እሷን እያጠናከር ክና ሳትነጠል ለአዲስ ዘላቂ ግብ
የሚገሠግሥ እውነተኛ ዓላማ እንዳለሁ አሳይ። አንተ በኑሮህ እና በትምህርትህ
ምክንያት የተሻለ ዕውቀትና ችሎታ አለህ፡፡ ምሳሌዩ ቅር እንዳያሰኝህ እጂ
ቀላዋጭ የሚቀላውጠው የአስቀልዋጩን ያህል ስለሌለው ወይም በግልጽ በሥውር ስለ ተነጠቀ ነው፡፡ ያም ሆነ ይህ አግዛት፣ አብራህ ትሠለፋለች::
ዓርማህን በፅናት ለመትከል ካልተጣጣርህና አካባቢህንም ለመለወጥ እምነትህን ካላስፋፋህ የጥንቱ ልማድ እንደ ክፉ አውሬ አሳዶ ይበላሃል። የበሰለ ሕሊና ያለው ሰው የምትሰኘውም ብዙዎችን ላስቸገረ ከባድ ጥያቄ መልስ ለማግኘት ስትል ከራስህ አልፈህ በተግባር የሚተባበሩህን መልካም ሰዎች በማፍራት ለዘላቂ መፍትሔ ስትታገል ነው፡፡ የዚህን የአሁኑን ሕይወት ቅርፅና ይዘት መለወጥ ያስፈልጋል። አሮጌውንና ለሕዝብ የማይጠቅመውን ነገር ሁሉ እያፈራረሱ በአዲስ የአኗኗር ስልት መተካት ይገባል፡፡ ግን አፈጻጸሙ እንደ አወራሩ ቀላል አይደለም» ብሎ በንግግሩ መኻል በረድ ያለችውን ሻይ መጠጣት ጀመረ፡፡
የወዲያነሽ ጉልላት ስለ እኔና ስለ እርሷ እንደ ተናገረ ስለ ገባት የመጨነቅ ሁኔታ ፊቷን ወረረው:: በስኒው ውስጥ የቀረችውን ሻይ ጨለጠና
የወዲያነሽን አሻግሮ እያየ «አንቺም ከእንግዲህ ወዲህ ነቃ ነቃ በይ! ይኸ ዐይን እስኪያብጥ እያለቀሱ አጉል መተከዝ በፍፁም አይጠቅማችሁም፡፡ ምንም እንኳ እንዳንቺ ወህኒ ቤት ገብተን ባንታሰርም እኛም ያንችኑ ያህል ከውጪ ሆነን ተሠቃይተናል። ሐሞትሽን ኮስተር አድርገሽ ለመታገል ከበረታሽ መልካሟ
የቤትሽ እመቤት አንቺ ብቻ ነሽ» ብሎ ጠበል እንዳልጠቀመው በሽተኛ ሻይ
እንዳስሞላለት
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...በደሳሳዋ ጎጆ ውስጥ ከወዲያ ማዶ ጥጉን ይዞ ተቀምጧል። ጋቢውን
አፍንጫው ድረስ ተከናንቦ አረቄውን ይጨልጣል። የሚያውቀው ሰው
ድንገት መጥቶ እንዳያየው እየተጠራጠረ ዐይኑን ብቻ በጋቢው አልሽፈነም እንጂ ሁለመናው ጋቢ ለብሶ እሱነቱን ለማወቅ እጅግ አስቸጋሪ ነበር፡፡ ከፊት ለፊቱ የተገተረውን የአረቄ ጠርሙስ አንገት አሁንም አሁንም እያነቀ በብርጭቆው ውስጥ ከደፈቀው በኋላ እንደ ጠላ አናቱ
ድረስ እየሞላ ቁልቁል ያንደቀድቀዋል፡፡ ጎንቻ ቦሩ በሌብነት ያገኘውን ገንዘብ እንደ ልቡ እየተምነሸነሸበት ነው። የዐይኑ ሲሳይ ዓለሚቱ፥ የልቡ ትኩሳት ዓለሚቱ፣ የስሜቱ ረመጥ ዓለሚቱን በተስፋ እየተመኘ፣ ዐይን ዐይኖቿን በማየት ብቻ ርካታ እያገኘ ስለሚውል ከዚያች ቤት ጠፍቶ አያውቅም፡፡ በውርርድ ከዚያች ቤት አይታጣም። ዋ! የአይን ፍቅር ክፉ...
ጎንቻን ክፉኛ ለክፎት የጎጆዋ ጠባቂ የዓለሚቱ ፍቅር የቁም እስረኛ ሆኖ
ተተብትቧል።
ጎንቻ የቶላን ከብቶች ሰርቆ እጅ ከፍንጅ በመያዙ ከፍተኛ የውርደት ስሜት ተሰምቶታል።የዘረፋቸውን ከብቶች ሳይቸበችባቸው በመቅረቱ በቀል እና ቁጭት ሲያተክኑት ሰንብተዋል። የቶላ ሁኔታ እጅግ አድርጎ አንገብግቦታል፡፡ በህይወቱ ሙሉ የዚያን አይነቱ ክፉ ቅሌት ደርሶበት አያውቅም ነበረና ያንን በአደባባይ ያጋለጠውን፣ ለገበያ በወጣ ህዝብ መሀል የለበሰው ጋቢ በአየር ላይ ብን እስከሚል ድረስ እየወደቀ እየተነሳ እንዲፈረጥጥ ያደረገውን ሰው ለመበቀል ሌላ የወንጀል ጥንስስ ሌላ የውንብድና ስራ ለመፈፀም ተመኘ፡፡ ሌብነቱ የወለደውን ቅሌት ሌብነቱ ያስከተለበትን ውርደት ለማካካስ የሰው ህይወት ማጥፋትን የሰው ጉሮሮ ፈጥርቆ
የመግደል ምኞትን አሳደረበትና የበቀል ካራ በልቡ መሳል ጀመረ፡፡
ቶላ ንብረቱን ለማዳን፣ ትዳሩን ለመታደግና ባሳደጋቸው ከብቶቹ አንገት
ላይ ካራ እንዳይገባባቸው መሯሯጡ በጎንቻ ዘንድ ይቅር የማያስብል
ወንጀል ሆኖ ተገኘና ህይወቱን ሊቀጥፈው በሆዱ ማለ፡፡ ይህን በሚያስብበት ጊዜ ደግሞ የዓለሚቱ ነገር አለና ልቡ ለሁለት ተከፈለ።ግድያ ከፈፀመ አረቄ ቤት ሄዶ ዐይን ዐይኖቿን በማየት የአይን ፍቅሩን መወጣት አይችልምና ልቡ ፈራ። ዓለሚቱ በላይነህ ጠይም የሚያጓጓ መልክ እና ቁመና ያላት የአረቄ ሻጫ የወይዘሮ ባንችይደሩ ልጅ ስትሆን የሁለት ልጆች እናትና ባለትዳር ነች። ዓለሚቱ እናቷን በስራ ለመርዳት ምንጊዜም ከቤታቸው አትጠፋም፡፡ በተለይ መልከ ቀናነቷ የብዙ
ዎቹን ጠጪዎች አይን ስለሚስብ ለገበያቸው መድራት ዓለሚቱ አይነተኛ ምክንያት ነበረች፡፡ ጎንቻ ግን ይህንን ሁሉ አያውቅም ነበር፡፡ ባለትዳር መሆኗን ሳያውቅ በፍቅር ወደቀ፡፡ ያውም በህይወቱ ውስጥ የመጀመሪያው በሆነው የሴት ልጅ ፍቅር ጎንቻ በቶላ ከብቶች ስርቆት ላይ ተይዞ ከደነበረ ጊዜ ጀምሮ በፍፁም ያልቀናው ቢሆንም አረቄ የሚጠጣበት ገንዘብ ግን አላጣም፡፡ ጠዋትና ማታ ከዚያች አረቄ ቤት ውስጥ በመመሸግ በቋሚ ደንበኛነቱ የወይዘሮ ባንቺደሩን ልብ መማረክ ቻለ፡፡ ከዚያም
ዓለሚቱን ቀስ በቀስ እየቀረባት እየተላመዳት ሄደ። አንደበቱን እያፍታታ
የዐይን ፍቅር እስረኛነቱ ቀስ በቀስ እየለቀቀው ድፍረት እያገኘ ያጨዋውታት አልፎ አልፎም ይጋብዛት ጀመር፡፡ እናቷም ቋሚ ደምበኛቸው በመሆኑና ተጋባዦችን ይዞ እየመጣ ገበያቸውን ስላሟሟቀላቸው ለጎንቻ ልዩ አክብሮት እየሰጡት ሄዱ፡፡ በዚህም ምክንያት ዓለሚቱ ቀስ በቀስ ጎንቻን እየቀረበችው መጣች፡፡
ጎንቻ በውበቷ ተማርኮና በፍቅሯ ተለክፎ በመሰቃየት ላይ መሆኑን አላወቀችም ነበር፡፡ እየዋለ ሊያደር ግን ሁኔታዎች ግልፅ እየሆኑ መጡ። በሚያገኘው የስርቆሽ ገንዘብ ለዓለሚቱ ሽቶ፣ቅባት፣ ጌጣጌጥ እየገዛ በድብቅ በገፀበረከትነት ያቀርብላት ጀመር፡፡ ይህ ሁኔታ እየተደጋገመ ሲሄድ የጎንቻ ውለታ
እየከበዳት መጣ፡፡ ቀንና ለሊት ስለሱ ማስብ ጀመረች። ከዚያም ቀስ በቀስ በሱ ላይ መንደድ የጀመረው የፍቅር እሳት እሷንም ሊገርፋት ወላፈኑ በሷም ላይ ተሻግሮ ሊለበልባት እየዳዳው መሆኑ ታወቃት አረቄ ጠጥተው በሞቅታ ውስጥ መጎሻሸሙ፣መተሻሸቱ፣ መላፋቱ እየተዘወተረ ሄደ። ባሏ እርሻ ስለሚውል ዓለሚቱን እንደ ልቡ ለማጫወት
ተመቸው። ዓለሚቱ ባለትዳር መሆኗን
ፍቅሩን ሊያቀዘቅዘው እነደማይችል በመሀላ አረጋገጠላትና በስርቆሽ ለመቀማመስ ተፈቃቀዱ ከዚያም መዳራቱ መላፋቱ የደረጃ እድገቱን ጠበቀና በዚያው በእናቷ ጎጆ በጓዳ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ጨርቅ ለመጋፈፍ በቁ፡፡ ቀስ በቀስ እንቁላል በእግሩ ይሄዳል ነውና ቀስ በቀስ በስውር
በምስኪኑ ባሏ በገበየው ቆጥ ላይ እንደ ዶሮ መስፈር ጀመሩ።
ዓለሚቱ የስርቆሽ ቅምሻው የበለጠ እየጣፈጣት ሲመጣ ጎንቻም በጣፋጫ
ዓለሚቱ ልቡ ተሰወረች…ከዛ በኋላማ ምን ይጠየቃል? ጎንቻ አባወራ ቀረሽ ቅናት እና ፍቅር ያግለበልበው ጀመር፡፡ “የምጣዱ እያለ የእንቅቡ ተንጣጣ” እንዲሉ በፍቅር ከመቃጠሉ የተነሳ የሁለት ልጆች አባትና
የሰማንያ ባሏ ገበየሁ እያለ በዓላሚቱ የሚቀናው ጎንቻ፣ ለዓለሚቱ አሳቢው ጎንቻ፣ ስለዓለሚቱ አድራጊ ፈጣሪው ጎንቻ ሆነና አረፈው። ዓለሚቱም የጎንቻን ድንግልና ከወሰደች በኋላ ትኩስ ጉልበቱ አዲስ የጉርምስና ጠረኑ ቁመናው በልቧ እያደላ ፍቅሯን ለባሏ መሰሰት ጀመረች።
ያለወትሮዋ ንጭንጭ፣ ጭቅጭቅ አመጣች፡፡ ከገበየሁ ሰርቃ ፍቅርን
ለጎንቻ በገፍ መመገብ ጀመረች። ጎንቻም እየተሰረቀ የሚሰጠው ፍቅር ከሚገባው በላይ ጣፈጠውና ገበየሁን የፍቅሩ ተሻሚ አድርጎ መቁጠር ጀመረ። ፍቅሩን ለብቻው በመመገብ ብቻውን ለመጥገብ ፈለገ፡፡ ተስገበገበ፡፡ መቼም የሰው ልጅ በተፈጥሮ ራስ ወዳድ ነውና ጎንቻ ራሱን በጣም
ወደደ። ምርጥ ምርጡን ለግሉ ብቻ ተመኘ፡፡ ከገበየሁ አስበልጣ እንድትወደው ዓለሚቱን እያንበሸበሻት ልቧን እየሰለበው ሄደ፡፡ የሚገዛላት
የጆሮ ጉትቻ የእግር አልቦ የሱዳን ሽቶ ቀሚስ ለጉድ ሆነ፡፡ ግን ምን ዋጋ አለው? ጌጣጌጡ ሽቶው ሁሉ በብዛት በእናቷ ሙዳይና በሳጥን ውስጥ ተቀምጦ እየዛገ እየተበላሸ ሄደ እንጂ ልታጌጥበት ልትደምቅበት አልቻለችም፡፡ ብታጌጥበት፣ ብታምርበት፣ብትታይበት ደግሞ መዘዝ ይዞ እንደሚመጣ ገመተች፡፡ ባሏ ገበየሁ “ከየት መጣ? እንዴት ሊሆን ቻለ?”
እያለ ሊጠይቅና ጥርጣሬ ውስጥ ሊገባ ነው፡፡ ስለዚህ ይሄንን እንድታምር፣ እንድታጌጥ፣ እንድትደምቅና እንድትሽቀረቀር ስትፈልግ ደንቃራ፣
ምቀኛ የሆነባትን ባሏን እየጠላችው መጣች። በዚህ ላይ ጎንቻ ችሮታው በገፍ ፍቅሩ በእጥፍ እየጨመረ በመሄድ ላይ ነበረና በገበየሁ የድህነት ትዳር ሰንሰለት የፊጥኝ ታስራ የኖረችበትን ጊዜ እያማረረች፣ የምትፈልገውን ማድረግ ባለመቻሏ ትዳሯን የበለጠ እየጠላች፣ ገበየሁን ከልቧ እያስወጣች በምትኩ ጎንቻን እያስገባች መሄዷን ቀጠለች ...
የገበየሁ ጣፋጭነት ወደ ምሬት ሊለወጥ ጎንቻ ወደር የሌለው ጣፋጭነቱንና የበላይነቱን እያረጋገጠ ሄደ።አዲስ እየተወደደ አሮጌው እየተጠላ ይሄዳልና ገበየሁ ተጠላና ጎንቻ ተወደደ። ለትዳሩ ቀን ከለሊት ደፋ ቀና የሚለው ጉዱን ያላወቀው ገበየሁ በጎንቻ በጥባጭነት ንፁህ ትዳሩ እየደፈረስ መጣ:: ባለቤቱ ያልተለመደውን ጭቅጭቋንና ንጭንጫን እያባባስችው ሄደች
“ስማ! ልጆቼን ብዬ በልጆቼ ታስሬ እንጂ ላንተ ገረድ ሆኜ የምቀመጥ ሴት አልነበርኩም! የፈለኩትን ለብሼ! በፈለኩት አጊጬ! ጓደኞቼን በልጬ
እንጂ ከጓደኞቼ በታች ሆኜ የምኖር ሰው እንዳልነበርኩ ማወቅ ይኖርብሀል!አንተ ግን ይሄ ሁሉ አይገባህም!” ይሄ የመረረ ንግግር ይሄ ታይቶ የማይታወቅ የሚስቱ ፀባይ መለወጥ ያሳሰበው ባል ሚስቱ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...በደሳሳዋ ጎጆ ውስጥ ከወዲያ ማዶ ጥጉን ይዞ ተቀምጧል። ጋቢውን
አፍንጫው ድረስ ተከናንቦ አረቄውን ይጨልጣል። የሚያውቀው ሰው
ድንገት መጥቶ እንዳያየው እየተጠራጠረ ዐይኑን ብቻ በጋቢው አልሽፈነም እንጂ ሁለመናው ጋቢ ለብሶ እሱነቱን ለማወቅ እጅግ አስቸጋሪ ነበር፡፡ ከፊት ለፊቱ የተገተረውን የአረቄ ጠርሙስ አንገት አሁንም አሁንም እያነቀ በብርጭቆው ውስጥ ከደፈቀው በኋላ እንደ ጠላ አናቱ
ድረስ እየሞላ ቁልቁል ያንደቀድቀዋል፡፡ ጎንቻ ቦሩ በሌብነት ያገኘውን ገንዘብ እንደ ልቡ እየተምነሸነሸበት ነው። የዐይኑ ሲሳይ ዓለሚቱ፥ የልቡ ትኩሳት ዓለሚቱ፣ የስሜቱ ረመጥ ዓለሚቱን በተስፋ እየተመኘ፣ ዐይን ዐይኖቿን በማየት ብቻ ርካታ እያገኘ ስለሚውል ከዚያች ቤት ጠፍቶ አያውቅም፡፡ በውርርድ ከዚያች ቤት አይታጣም። ዋ! የአይን ፍቅር ክፉ...
ጎንቻን ክፉኛ ለክፎት የጎጆዋ ጠባቂ የዓለሚቱ ፍቅር የቁም እስረኛ ሆኖ
ተተብትቧል።
ጎንቻ የቶላን ከብቶች ሰርቆ እጅ ከፍንጅ በመያዙ ከፍተኛ የውርደት ስሜት ተሰምቶታል።የዘረፋቸውን ከብቶች ሳይቸበችባቸው በመቅረቱ በቀል እና ቁጭት ሲያተክኑት ሰንብተዋል። የቶላ ሁኔታ እጅግ አድርጎ አንገብግቦታል፡፡ በህይወቱ ሙሉ የዚያን አይነቱ ክፉ ቅሌት ደርሶበት አያውቅም ነበረና ያንን በአደባባይ ያጋለጠውን፣ ለገበያ በወጣ ህዝብ መሀል የለበሰው ጋቢ በአየር ላይ ብን እስከሚል ድረስ እየወደቀ እየተነሳ እንዲፈረጥጥ ያደረገውን ሰው ለመበቀል ሌላ የወንጀል ጥንስስ ሌላ የውንብድና ስራ ለመፈፀም ተመኘ፡፡ ሌብነቱ የወለደውን ቅሌት ሌብነቱ ያስከተለበትን ውርደት ለማካካስ የሰው ህይወት ማጥፋትን የሰው ጉሮሮ ፈጥርቆ
የመግደል ምኞትን አሳደረበትና የበቀል ካራ በልቡ መሳል ጀመረ፡፡
ቶላ ንብረቱን ለማዳን፣ ትዳሩን ለመታደግና ባሳደጋቸው ከብቶቹ አንገት
ላይ ካራ እንዳይገባባቸው መሯሯጡ በጎንቻ ዘንድ ይቅር የማያስብል
ወንጀል ሆኖ ተገኘና ህይወቱን ሊቀጥፈው በሆዱ ማለ፡፡ ይህን በሚያስብበት ጊዜ ደግሞ የዓለሚቱ ነገር አለና ልቡ ለሁለት ተከፈለ።ግድያ ከፈፀመ አረቄ ቤት ሄዶ ዐይን ዐይኖቿን በማየት የአይን ፍቅሩን መወጣት አይችልምና ልቡ ፈራ። ዓለሚቱ በላይነህ ጠይም የሚያጓጓ መልክ እና ቁመና ያላት የአረቄ ሻጫ የወይዘሮ ባንችይደሩ ልጅ ስትሆን የሁለት ልጆች እናትና ባለትዳር ነች። ዓለሚቱ እናቷን በስራ ለመርዳት ምንጊዜም ከቤታቸው አትጠፋም፡፡ በተለይ መልከ ቀናነቷ የብዙ
ዎቹን ጠጪዎች አይን ስለሚስብ ለገበያቸው መድራት ዓለሚቱ አይነተኛ ምክንያት ነበረች፡፡ ጎንቻ ግን ይህንን ሁሉ አያውቅም ነበር፡፡ ባለትዳር መሆኗን ሳያውቅ በፍቅር ወደቀ፡፡ ያውም በህይወቱ ውስጥ የመጀመሪያው በሆነው የሴት ልጅ ፍቅር ጎንቻ በቶላ ከብቶች ስርቆት ላይ ተይዞ ከደነበረ ጊዜ ጀምሮ በፍፁም ያልቀናው ቢሆንም አረቄ የሚጠጣበት ገንዘብ ግን አላጣም፡፡ ጠዋትና ማታ ከዚያች አረቄ ቤት ውስጥ በመመሸግ በቋሚ ደንበኛነቱ የወይዘሮ ባንቺደሩን ልብ መማረክ ቻለ፡፡ ከዚያም
ዓለሚቱን ቀስ በቀስ እየቀረባት እየተላመዳት ሄደ። አንደበቱን እያፍታታ
የዐይን ፍቅር እስረኛነቱ ቀስ በቀስ እየለቀቀው ድፍረት እያገኘ ያጨዋውታት አልፎ አልፎም ይጋብዛት ጀመር፡፡ እናቷም ቋሚ ደምበኛቸው በመሆኑና ተጋባዦችን ይዞ እየመጣ ገበያቸውን ስላሟሟቀላቸው ለጎንቻ ልዩ አክብሮት እየሰጡት ሄዱ፡፡ በዚህም ምክንያት ዓለሚቱ ቀስ በቀስ ጎንቻን እየቀረበችው መጣች፡፡
ጎንቻ በውበቷ ተማርኮና በፍቅሯ ተለክፎ በመሰቃየት ላይ መሆኑን አላወቀችም ነበር፡፡ እየዋለ ሊያደር ግን ሁኔታዎች ግልፅ እየሆኑ መጡ። በሚያገኘው የስርቆሽ ገንዘብ ለዓለሚቱ ሽቶ፣ቅባት፣ ጌጣጌጥ እየገዛ በድብቅ በገፀበረከትነት ያቀርብላት ጀመር፡፡ ይህ ሁኔታ እየተደጋገመ ሲሄድ የጎንቻ ውለታ
እየከበዳት መጣ፡፡ ቀንና ለሊት ስለሱ ማስብ ጀመረች። ከዚያም ቀስ በቀስ በሱ ላይ መንደድ የጀመረው የፍቅር እሳት እሷንም ሊገርፋት ወላፈኑ በሷም ላይ ተሻግሮ ሊለበልባት እየዳዳው መሆኑ ታወቃት አረቄ ጠጥተው በሞቅታ ውስጥ መጎሻሸሙ፣መተሻሸቱ፣ መላፋቱ እየተዘወተረ ሄደ። ባሏ እርሻ ስለሚውል ዓለሚቱን እንደ ልቡ ለማጫወት
ተመቸው። ዓለሚቱ ባለትዳር መሆኗን
ፍቅሩን ሊያቀዘቅዘው እነደማይችል በመሀላ አረጋገጠላትና በስርቆሽ ለመቀማመስ ተፈቃቀዱ ከዚያም መዳራቱ መላፋቱ የደረጃ እድገቱን ጠበቀና በዚያው በእናቷ ጎጆ በጓዳ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ጨርቅ ለመጋፈፍ በቁ፡፡ ቀስ በቀስ እንቁላል በእግሩ ይሄዳል ነውና ቀስ በቀስ በስውር
በምስኪኑ ባሏ በገበየው ቆጥ ላይ እንደ ዶሮ መስፈር ጀመሩ።
ዓለሚቱ የስርቆሽ ቅምሻው የበለጠ እየጣፈጣት ሲመጣ ጎንቻም በጣፋጫ
ዓለሚቱ ልቡ ተሰወረች…ከዛ በኋላማ ምን ይጠየቃል? ጎንቻ አባወራ ቀረሽ ቅናት እና ፍቅር ያግለበልበው ጀመር፡፡ “የምጣዱ እያለ የእንቅቡ ተንጣጣ” እንዲሉ በፍቅር ከመቃጠሉ የተነሳ የሁለት ልጆች አባትና
የሰማንያ ባሏ ገበየሁ እያለ በዓላሚቱ የሚቀናው ጎንቻ፣ ለዓለሚቱ አሳቢው ጎንቻ፣ ስለዓለሚቱ አድራጊ ፈጣሪው ጎንቻ ሆነና አረፈው። ዓለሚቱም የጎንቻን ድንግልና ከወሰደች በኋላ ትኩስ ጉልበቱ አዲስ የጉርምስና ጠረኑ ቁመናው በልቧ እያደላ ፍቅሯን ለባሏ መሰሰት ጀመረች።
ያለወትሮዋ ንጭንጭ፣ ጭቅጭቅ አመጣች፡፡ ከገበየሁ ሰርቃ ፍቅርን
ለጎንቻ በገፍ መመገብ ጀመረች። ጎንቻም እየተሰረቀ የሚሰጠው ፍቅር ከሚገባው በላይ ጣፈጠውና ገበየሁን የፍቅሩ ተሻሚ አድርጎ መቁጠር ጀመረ። ፍቅሩን ለብቻው በመመገብ ብቻውን ለመጥገብ ፈለገ፡፡ ተስገበገበ፡፡ መቼም የሰው ልጅ በተፈጥሮ ራስ ወዳድ ነውና ጎንቻ ራሱን በጣም
ወደደ። ምርጥ ምርጡን ለግሉ ብቻ ተመኘ፡፡ ከገበየሁ አስበልጣ እንድትወደው ዓለሚቱን እያንበሸበሻት ልቧን እየሰለበው ሄደ፡፡ የሚገዛላት
የጆሮ ጉትቻ የእግር አልቦ የሱዳን ሽቶ ቀሚስ ለጉድ ሆነ፡፡ ግን ምን ዋጋ አለው? ጌጣጌጡ ሽቶው ሁሉ በብዛት በእናቷ ሙዳይና በሳጥን ውስጥ ተቀምጦ እየዛገ እየተበላሸ ሄደ እንጂ ልታጌጥበት ልትደምቅበት አልቻለችም፡፡ ብታጌጥበት፣ ብታምርበት፣ብትታይበት ደግሞ መዘዝ ይዞ እንደሚመጣ ገመተች፡፡ ባሏ ገበየሁ “ከየት መጣ? እንዴት ሊሆን ቻለ?”
እያለ ሊጠይቅና ጥርጣሬ ውስጥ ሊገባ ነው፡፡ ስለዚህ ይሄንን እንድታምር፣ እንድታጌጥ፣ እንድትደምቅና እንድትሽቀረቀር ስትፈልግ ደንቃራ፣
ምቀኛ የሆነባትን ባሏን እየጠላችው መጣች። በዚህ ላይ ጎንቻ ችሮታው በገፍ ፍቅሩ በእጥፍ እየጨመረ በመሄድ ላይ ነበረና በገበየሁ የድህነት ትዳር ሰንሰለት የፊጥኝ ታስራ የኖረችበትን ጊዜ እያማረረች፣ የምትፈልገውን ማድረግ ባለመቻሏ ትዳሯን የበለጠ እየጠላች፣ ገበየሁን ከልቧ እያስወጣች በምትኩ ጎንቻን እያስገባች መሄዷን ቀጠለች ...
የገበየሁ ጣፋጭነት ወደ ምሬት ሊለወጥ ጎንቻ ወደር የሌለው ጣፋጭነቱንና የበላይነቱን እያረጋገጠ ሄደ።አዲስ እየተወደደ አሮጌው እየተጠላ ይሄዳልና ገበየሁ ተጠላና ጎንቻ ተወደደ። ለትዳሩ ቀን ከለሊት ደፋ ቀና የሚለው ጉዱን ያላወቀው ገበየሁ በጎንቻ በጥባጭነት ንፁህ ትዳሩ እየደፈረስ መጣ:: ባለቤቱ ያልተለመደውን ጭቅጭቋንና ንጭንጫን እያባባስችው ሄደች
“ስማ! ልጆቼን ብዬ በልጆቼ ታስሬ እንጂ ላንተ ገረድ ሆኜ የምቀመጥ ሴት አልነበርኩም! የፈለኩትን ለብሼ! በፈለኩት አጊጬ! ጓደኞቼን በልጬ
እንጂ ከጓደኞቼ በታች ሆኜ የምኖር ሰው እንዳልነበርኩ ማወቅ ይኖርብሀል!አንተ ግን ይሄ ሁሉ አይገባህም!” ይሄ የመረረ ንግግር ይሄ ታይቶ የማይታወቅ የሚስቱ ፀባይ መለወጥ ያሳሰበው ባል ሚስቱ
#ያልታበሱ_እንባዎች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...ባርናባስ የሔዋንን ሁለት እጆች ግጥም እድርጎ ይዟል። ሸዋዬ የአገኘችውን ነገር ሁሉ እያነሳች ትደበድባታለች። ሔዋን ኡኡ ድረሱልኝ እያለች ትጮሀለች።
እጆቿን ከባርናባስ ለማስለቀቅ ትታገላለች። እሱ ደግሞ እንዳታመልጠው ጥርሱን
ንክስ እያረገ ሀይሉን ያጠነክራል። ሸዋዬ አሁንም ትደበድባታለች፡፡ ሔዋንም ትጮሀለች፡፡ ይህ ሁሉ ሲሆን በርካታ ሰው ዙሪያውን ከብቦ ይመለከታል። ግን
“ማንም ሊገላግል አያስብም፡፡ አስቻለው ሊገላግል እየፈለግን ደግሞ መሮጥ ያቅተዋል። ይለፋል ግን አይችልም፡፡ ከያዘው ነገር ራሱን እንድምንም አላቅቆ ወደ
ድብድቡ ቦታ ሊሮጥ ሲል ድንገት ከእንቅልፉ ብንን አለ፡፡ «በስመ አብ ወወልድ መንፈስ ቅዱስ..." ብሎ ከተንጋለለበት ቀና በማለት ፊቱን በሁለት እጆቹ ሽፍን አድርጎ ወደ ፊት ወደ እግሮቹ ድፍት አለ ዝግንን አለው ደርጊቱን ያየው
በቅዠት እንዳልሆነ ሁሉ ሔዋን አሁንም በዚያው ሁኔታ ውስጥ
ሆና ትታየው ጀመር። አሳዘነችው። ከዚያ በኋላ መተኛት አልፈለገም
ከአልጋው ላይ ፈጠን ብሎ ወረደና ልብሱን ለባበሰ።
ምን ሊያግርን እንደሆነ ሳይታወቀው በቀጥታ ወደ ሸዋዬ ቤት መሄድ ፈለገ። ቤቱን ቆለፈና ከግቢ ወጥቶ ቁልቅል ወደሸዋዬ ቤት አቅጣጫ ወረደ ልክ በሸዋዬ ቤት አቅጣጫ ስምንተኛ መንገድ ላይ ሲደርስ መንገድ ላይ ቀጥ ብሎ ቆመና በቀኝ አቅጣጫ ያለውን የወይዘሮ ዘነቡን ግቢ በርቀት ይመለከተው ጀመር በሀሳቡ ሸዋዬ ቤት ገባ ሸዋዬንና በርናባስ ፍራሽ ላይ ቁጭ ብለው
ጫት ሲቅሙ ሔዋን ደሞ በከሰል
ላይ ጀበና ጥዳ የሁለቱ ብና አፋይ ሆና ሁሉም በአንድ ላይ እንደ ስዕል ታዩት።ልቡ ወደዚያው ቤት ሂድ ሂድ አለው። ነገር ግን ድንገት ዘው ቢል ሊፈጠር የሚችለው ሁኔታ ታየው፡፡ ከሁሉም በላይ ሔዋን ትሳቀቅበታለች !
በዚያ ምትክ ከንፈሩን ንክስ አድርጎ ራሱን በቁጭት ወዘወዘ።
በዚሁ ሁኔታ ጥቂት ቆየና ሳይወድ በግድ ሃሳቡን ለወጠ፡፡ በቃ ወደ ሸዋዩ ቤት መግባት አልፈለገም፡፡ ግን ደግሞ ወዴት እንደሚሄድ ጨነቀው ቤቱም ሰለቸው ወደ አንድ ቡና ቤት አይሄድ ነገር እዚያ ሄዶ የሚገጥመው ነገር ለመንፈሱ
አይመቸውም። ግራ ሲገባው ቁልቁል ወደ ከተማዋ ዳርቻ ይራመድ ጀመር ቁርጥ ያለ አድራሻ የለውም። ብቻ መሄድ ብቻ መራመድ፡፡ ብሎ ብሎ ከከተማው ወጣና ወደ እሮሬሳ ገበሬ ማህበር አዋሳኝ ላይ ደረሰ።እያደር ደግሞ
የገጠሩ ሽታ አማለለው፡፡ አሁንም ወደፊት ሊራመድ መሰነና ርምጃውን ቀጠለ። በዚያ መንገድ ላይ በርካታ የገጠር ነዋሪዎች ወደ ከተማ ያመራሉ።ከከተማ ወደ ገጠር ይሄዳሉ፡፡ አስቻለውም ርምጃውን ዝም ብሎ ወደ ፊት ቀጠለ፡፡በልቡ ግን አንድ ነገር ያስላስሳል ዐወደፊት ሐምሌ ላይ የሚጠብቀውን ዝውውርና
ከሔዋን ጋር ስለሚኖረው ግንኙነት። 'ለመሆኑ' ይላል በሀሳቡ። ብዛወር የሐዩ ጉዳይ እንዴት ሊሆን ነው? ይዢያት ልሄድ ወይስ ትቻት? ይልና እንደገና
የታፈሡና የበልሁ ወደ ክብረ መንግስት የመሄድ ዕቅድ ይመጣበታል። ሄደውስ
ይሳካላቸው ይሆን? ወይስ የሔዩ እናትና አባት ሽዋዬ በፃፈችላቸው ደብዳቤ ምክንያት ሁኔታው አስግቷቸው ያንገራግሩ ይሆን እሺ ቢሉም ሰርግ ድግስ ምናምን ሊሉ ይችላሉ። ያ እስከሚሆን ጊዜ ይፈጃል፡፡ ዞሮ ዞሮ ላልተወሰነ ጊዜ
ከሒዩ ጋር መራራቀ አይቀርም፡፡» በማለት ራሱን እንደማረጋጋት አይነት እንግዲህ የሆነው ይሁን ብቻ ሰላምና ጤና ትሁንልኝ፡፡» እያለ አምላኩን ይማፀናል፡፡
ሳያውቀው ብዙ ተጉዟል በለየለት ገጠር ውስጥ ገብቶ ከዲላ ከተማ በግምት ሁለት ኪሎ ሜትር ያህል ርቋል። ከሀሳቡ ብንን በማለት ባለበት ቦታ ላይ ቆሞ ዓይኑን ወደ ቀኝ አቅጣጫ ጣል ሲያደርግ ዙሪያዋን በረጃጅም ዛፎች
የቸከበበችና፣ ሰፋ ያለች ደስ የምትል ገላጣ ሜዳ ታየችው፡፡ ከግጦሽ ከፍ ያለ የእድገት ደረጃ ላይ በደረሰ ለምለም ሳር ተሸፍናለች። በውስጧ አልፎ አልፎ
የደረቁ ጉቶዎች ጉብ ጉብ ብለው ይታያሉ፡ ወደዚያው ታጠፈና ሜዳዋ መሀል ገብቶ ከአንድ ጉቶ ላይ ቁጭ አለ፡፡ ዙሪያውን ሲመለከት ጥቅጥቅ ያለ ጫካ ነው፡፡ ዛፎች ደግሞ ረጃጅም፡ ወደ መሬት ሲያይ ያ ለምለም ሳር፡፡ በአፍንጫው የሚገባው አየር በራሱ የተለየ መዓዛ ያለው፡፡ መንፈስ የሚያድስ፡፡ እጆቹን በደረቱ ላይ አቆላልፎ ወደ ዛፎቹ ሲያይ ከአንዱ ወደ ሌላው እየተዘዋወሩ የሚንጫጬ ወፎች
ቀልቡን ሳቡት ከወፎቹ የጫጫታ ድግግሞሽ የተነሳ የወፍ ድምፅ ፂው ስትል ሲኮንድ አታልፍም:: የድምጻቸው ልዩነት ውበትና ህበሩ በጭንቅ በጥበብ ከተቀመረ
ዘመናዊ ሙዚቃ የበለጠ ስሜት ይማርካል፡፡
«እናንት ወፎች» አለ አስቻለው ሁኔታቸው ሁለ ግርም ብሎት፡፡ ዛፋ ሁሉ የሁላችሁ ለኔ ብቻ ባይ ስግብግብ በመሀላችሁ የለም
አዛዥ የላችሁ ገልማጭ ጠላት የላችሁ ምቀኛ ኑሮአችሁ በራሳችሁ፣ ውሸት አታውቁ ቅጥፈት ክፉ አቶለሙ ክፉ አትናገሩ አትቀየሙ አታስቀይሙ ጨኸታችሁ አይገደብ ጫጫታችሁ አይመዘገብ ቂም አታውቁ በቀል፤ በእናንተ ዘንድ ዛቻ የለ
ማስፈራራት፤ ፍርሀት የለ ጭንቀት፣ በዚች ምድር ሰላም ልትኖሩ የተፈጠራችሁ ሰላማዊ ፍጡሮች! በማለት ብቻውን ሲነጋገር ከቆየ በኋሳ ሀሳቡን ወደ ሰው ልጅ ባህሪና አኗኗር መለስ ሲያደርገው ጭራሽ አስጠላው።
«ያልታደለ ፍጡር»አለ በስጨት ባለ አነጋገር፡፡ ታየው የሰው ልጅ
ክፋቱና ተንኮሉ፣ ቂምና በቀሉ፣ ሸርና ምቀኝነቱ፤ ጠበና ጭቅጭቁ፣ ከሁሉም በላይ
እብሪቱና ጭካኔው፡ በቃሉም ይገልፀው ጀመር «የአሳር ሽክም የተጫነ መከረኛ ፍጡር፥ ሰው! የቱንም ያህል ቢማር ቢመራመር ከራሱ ጋር መታረቅ ያቃተው
ደካማ ፍጡር፡ ሰው ፈጣሪው ራሱ እሱን በመፍጠሩ የተፀፀተበት ብቸኛ እንስሳ ሰው!» ካለ በኋላ ራሱን ወዝወዝ አድርጎ ወደ መሬት ጎንበስ አለና ያን የለመለመ
ሳር ልብ ብሎ ይመለከተው ጀመር፡፡ ከሩቅ ሲያዩት ልምላሜ ያምራል:: ስሩ ሲታይ ግን ብዙ ጥቃንጥት አለበት፡፡ የደረቁ ቅጠሎችና ጭራሮዎች እንዲሁም ልዩ ልዩ በርካታ ነገሮች ስር ስሩን ትብትብ እድርገው ይዘውታል። ይህ ሁኔታ ሔዋንን አስታወየው፡፡
«አንተ ለምለም ሳርና የኔዋ ሔዋን እንድ ናቸሁ፡ ከሩቅ ሲያዩአቸሁ ውብ ናችሁ:: ፍጹም የደላችሁ ትመስላላችሁ፡፡ ሥር ሥራችሁንና ውስጥ ውስጣችሁን ግን ብዙ ችግር አለባችሁ፡፡ ሳትጠሩት የመጣባችሁ፣ ሳትፈልጉት የተዳበላችሁ፡፡ አቁሳይ ጥገኛ አለባችሁ፡፡ አንተን የጭራሮና የቅጠል ርጋፊዎች ስርህን ተብትበው እንደ ያዘህ ሁሉ የኔዋ ሔዋንም የአፈቀረ ልቧን የሚወ,ጋ የስሜት እሾህ ኣለባት፡፡
ለመውደድና ለመወደድ የተፈጠረች ቆንጆ ነበረች:: ግን እሾሁ ጋሬጣው በዛባትና
መንፈሷ ቆሰለ፡፡ በአፈቀረች ተሰቃየች። ማልቀስና መተከዝ ዕጣ ፋንታዋ ሆነ።
እያለ ሲያስብ በዚያው ያ ቅዠት ውስጥ ያየው ሁኔታ ትዝ አለው፡፡ ድንግጥ ብሎ እንደ መደንበር አረገና በተቀመጠበት ጉቶ ላይ ብድግ አለ ሳያስበው በዚያ
በለመለመ ሳር ላያ ይዘዋወር ጀመር፡፡
እጆቹን በጀርባው ላይ አጣምሮ ጎንበስ በማለት በግምት ከአስር: እስከ አስራ አምስት ርምጃዎችን ከተራመደ በኋላ በግራ በኩል ወደ መንገዱ ዞር ብሎ ሲያይ አንድ ለየት ያለ ነገር አየ፡፡ በመንገዱ ላይ ሰዎች አሁንም ወደ ላይ ወደ ታችም አቅጣጫ ይሄዳሉ፡፡ ነገር ግን መንገደኛ፣ ለየት ባለ እኳኋን አንዲት በጀርባዋ ጓዝ የያዘች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...ባርናባስ የሔዋንን ሁለት እጆች ግጥም እድርጎ ይዟል። ሸዋዬ የአገኘችውን ነገር ሁሉ እያነሳች ትደበድባታለች። ሔዋን ኡኡ ድረሱልኝ እያለች ትጮሀለች።
እጆቿን ከባርናባስ ለማስለቀቅ ትታገላለች። እሱ ደግሞ እንዳታመልጠው ጥርሱን
ንክስ እያረገ ሀይሉን ያጠነክራል። ሸዋዬ አሁንም ትደበድባታለች፡፡ ሔዋንም ትጮሀለች፡፡ ይህ ሁሉ ሲሆን በርካታ ሰው ዙሪያውን ከብቦ ይመለከታል። ግን
“ማንም ሊገላግል አያስብም፡፡ አስቻለው ሊገላግል እየፈለግን ደግሞ መሮጥ ያቅተዋል። ይለፋል ግን አይችልም፡፡ ከያዘው ነገር ራሱን እንድምንም አላቅቆ ወደ
ድብድቡ ቦታ ሊሮጥ ሲል ድንገት ከእንቅልፉ ብንን አለ፡፡ «በስመ አብ ወወልድ መንፈስ ቅዱስ..." ብሎ ከተንጋለለበት ቀና በማለት ፊቱን በሁለት እጆቹ ሽፍን አድርጎ ወደ ፊት ወደ እግሮቹ ድፍት አለ ዝግንን አለው ደርጊቱን ያየው
በቅዠት እንዳልሆነ ሁሉ ሔዋን አሁንም በዚያው ሁኔታ ውስጥ
ሆና ትታየው ጀመር። አሳዘነችው። ከዚያ በኋላ መተኛት አልፈለገም
ከአልጋው ላይ ፈጠን ብሎ ወረደና ልብሱን ለባበሰ።
ምን ሊያግርን እንደሆነ ሳይታወቀው በቀጥታ ወደ ሸዋዬ ቤት መሄድ ፈለገ። ቤቱን ቆለፈና ከግቢ ወጥቶ ቁልቅል ወደሸዋዬ ቤት አቅጣጫ ወረደ ልክ በሸዋዬ ቤት አቅጣጫ ስምንተኛ መንገድ ላይ ሲደርስ መንገድ ላይ ቀጥ ብሎ ቆመና በቀኝ አቅጣጫ ያለውን የወይዘሮ ዘነቡን ግቢ በርቀት ይመለከተው ጀመር በሀሳቡ ሸዋዬ ቤት ገባ ሸዋዬንና በርናባስ ፍራሽ ላይ ቁጭ ብለው
ጫት ሲቅሙ ሔዋን ደሞ በከሰል
ላይ ጀበና ጥዳ የሁለቱ ብና አፋይ ሆና ሁሉም በአንድ ላይ እንደ ስዕል ታዩት።ልቡ ወደዚያው ቤት ሂድ ሂድ አለው። ነገር ግን ድንገት ዘው ቢል ሊፈጠር የሚችለው ሁኔታ ታየው፡፡ ከሁሉም በላይ ሔዋን ትሳቀቅበታለች !
በዚያ ምትክ ከንፈሩን ንክስ አድርጎ ራሱን በቁጭት ወዘወዘ።
በዚሁ ሁኔታ ጥቂት ቆየና ሳይወድ በግድ ሃሳቡን ለወጠ፡፡ በቃ ወደ ሸዋዩ ቤት መግባት አልፈለገም፡፡ ግን ደግሞ ወዴት እንደሚሄድ ጨነቀው ቤቱም ሰለቸው ወደ አንድ ቡና ቤት አይሄድ ነገር እዚያ ሄዶ የሚገጥመው ነገር ለመንፈሱ
አይመቸውም። ግራ ሲገባው ቁልቁል ወደ ከተማዋ ዳርቻ ይራመድ ጀመር ቁርጥ ያለ አድራሻ የለውም። ብቻ መሄድ ብቻ መራመድ፡፡ ብሎ ብሎ ከከተማው ወጣና ወደ እሮሬሳ ገበሬ ማህበር አዋሳኝ ላይ ደረሰ።እያደር ደግሞ
የገጠሩ ሽታ አማለለው፡፡ አሁንም ወደፊት ሊራመድ መሰነና ርምጃውን ቀጠለ። በዚያ መንገድ ላይ በርካታ የገጠር ነዋሪዎች ወደ ከተማ ያመራሉ።ከከተማ ወደ ገጠር ይሄዳሉ፡፡ አስቻለውም ርምጃውን ዝም ብሎ ወደ ፊት ቀጠለ፡፡በልቡ ግን አንድ ነገር ያስላስሳል ዐወደፊት ሐምሌ ላይ የሚጠብቀውን ዝውውርና
ከሔዋን ጋር ስለሚኖረው ግንኙነት። 'ለመሆኑ' ይላል በሀሳቡ። ብዛወር የሐዩ ጉዳይ እንዴት ሊሆን ነው? ይዢያት ልሄድ ወይስ ትቻት? ይልና እንደገና
የታፈሡና የበልሁ ወደ ክብረ መንግስት የመሄድ ዕቅድ ይመጣበታል። ሄደውስ
ይሳካላቸው ይሆን? ወይስ የሔዩ እናትና አባት ሽዋዬ በፃፈችላቸው ደብዳቤ ምክንያት ሁኔታው አስግቷቸው ያንገራግሩ ይሆን እሺ ቢሉም ሰርግ ድግስ ምናምን ሊሉ ይችላሉ። ያ እስከሚሆን ጊዜ ይፈጃል፡፡ ዞሮ ዞሮ ላልተወሰነ ጊዜ
ከሒዩ ጋር መራራቀ አይቀርም፡፡» በማለት ራሱን እንደማረጋጋት አይነት እንግዲህ የሆነው ይሁን ብቻ ሰላምና ጤና ትሁንልኝ፡፡» እያለ አምላኩን ይማፀናል፡፡
ሳያውቀው ብዙ ተጉዟል በለየለት ገጠር ውስጥ ገብቶ ከዲላ ከተማ በግምት ሁለት ኪሎ ሜትር ያህል ርቋል። ከሀሳቡ ብንን በማለት ባለበት ቦታ ላይ ቆሞ ዓይኑን ወደ ቀኝ አቅጣጫ ጣል ሲያደርግ ዙሪያዋን በረጃጅም ዛፎች
የቸከበበችና፣ ሰፋ ያለች ደስ የምትል ገላጣ ሜዳ ታየችው፡፡ ከግጦሽ ከፍ ያለ የእድገት ደረጃ ላይ በደረሰ ለምለም ሳር ተሸፍናለች። በውስጧ አልፎ አልፎ
የደረቁ ጉቶዎች ጉብ ጉብ ብለው ይታያሉ፡ ወደዚያው ታጠፈና ሜዳዋ መሀል ገብቶ ከአንድ ጉቶ ላይ ቁጭ አለ፡፡ ዙሪያውን ሲመለከት ጥቅጥቅ ያለ ጫካ ነው፡፡ ዛፎች ደግሞ ረጃጅም፡ ወደ መሬት ሲያይ ያ ለምለም ሳር፡፡ በአፍንጫው የሚገባው አየር በራሱ የተለየ መዓዛ ያለው፡፡ መንፈስ የሚያድስ፡፡ እጆቹን በደረቱ ላይ አቆላልፎ ወደ ዛፎቹ ሲያይ ከአንዱ ወደ ሌላው እየተዘዋወሩ የሚንጫጬ ወፎች
ቀልቡን ሳቡት ከወፎቹ የጫጫታ ድግግሞሽ የተነሳ የወፍ ድምፅ ፂው ስትል ሲኮንድ አታልፍም:: የድምጻቸው ልዩነት ውበትና ህበሩ በጭንቅ በጥበብ ከተቀመረ
ዘመናዊ ሙዚቃ የበለጠ ስሜት ይማርካል፡፡
«እናንት ወፎች» አለ አስቻለው ሁኔታቸው ሁለ ግርም ብሎት፡፡ ዛፋ ሁሉ የሁላችሁ ለኔ ብቻ ባይ ስግብግብ በመሀላችሁ የለም
አዛዥ የላችሁ ገልማጭ ጠላት የላችሁ ምቀኛ ኑሮአችሁ በራሳችሁ፣ ውሸት አታውቁ ቅጥፈት ክፉ አቶለሙ ክፉ አትናገሩ አትቀየሙ አታስቀይሙ ጨኸታችሁ አይገደብ ጫጫታችሁ አይመዘገብ ቂም አታውቁ በቀል፤ በእናንተ ዘንድ ዛቻ የለ
ማስፈራራት፤ ፍርሀት የለ ጭንቀት፣ በዚች ምድር ሰላም ልትኖሩ የተፈጠራችሁ ሰላማዊ ፍጡሮች! በማለት ብቻውን ሲነጋገር ከቆየ በኋሳ ሀሳቡን ወደ ሰው ልጅ ባህሪና አኗኗር መለስ ሲያደርገው ጭራሽ አስጠላው።
«ያልታደለ ፍጡር»አለ በስጨት ባለ አነጋገር፡፡ ታየው የሰው ልጅ
ክፋቱና ተንኮሉ፣ ቂምና በቀሉ፣ ሸርና ምቀኝነቱ፤ ጠበና ጭቅጭቁ፣ ከሁሉም በላይ
እብሪቱና ጭካኔው፡ በቃሉም ይገልፀው ጀመር «የአሳር ሽክም የተጫነ መከረኛ ፍጡር፥ ሰው! የቱንም ያህል ቢማር ቢመራመር ከራሱ ጋር መታረቅ ያቃተው
ደካማ ፍጡር፡ ሰው ፈጣሪው ራሱ እሱን በመፍጠሩ የተፀፀተበት ብቸኛ እንስሳ ሰው!» ካለ በኋላ ራሱን ወዝወዝ አድርጎ ወደ መሬት ጎንበስ አለና ያን የለመለመ
ሳር ልብ ብሎ ይመለከተው ጀመር፡፡ ከሩቅ ሲያዩት ልምላሜ ያምራል:: ስሩ ሲታይ ግን ብዙ ጥቃንጥት አለበት፡፡ የደረቁ ቅጠሎችና ጭራሮዎች እንዲሁም ልዩ ልዩ በርካታ ነገሮች ስር ስሩን ትብትብ እድርገው ይዘውታል። ይህ ሁኔታ ሔዋንን አስታወየው፡፡
«አንተ ለምለም ሳርና የኔዋ ሔዋን እንድ ናቸሁ፡ ከሩቅ ሲያዩአቸሁ ውብ ናችሁ:: ፍጹም የደላችሁ ትመስላላችሁ፡፡ ሥር ሥራችሁንና ውስጥ ውስጣችሁን ግን ብዙ ችግር አለባችሁ፡፡ ሳትጠሩት የመጣባችሁ፣ ሳትፈልጉት የተዳበላችሁ፡፡ አቁሳይ ጥገኛ አለባችሁ፡፡ አንተን የጭራሮና የቅጠል ርጋፊዎች ስርህን ተብትበው እንደ ያዘህ ሁሉ የኔዋ ሔዋንም የአፈቀረ ልቧን የሚወ,ጋ የስሜት እሾህ ኣለባት፡፡
ለመውደድና ለመወደድ የተፈጠረች ቆንጆ ነበረች:: ግን እሾሁ ጋሬጣው በዛባትና
መንፈሷ ቆሰለ፡፡ በአፈቀረች ተሰቃየች። ማልቀስና መተከዝ ዕጣ ፋንታዋ ሆነ።
እያለ ሲያስብ በዚያው ያ ቅዠት ውስጥ ያየው ሁኔታ ትዝ አለው፡፡ ድንግጥ ብሎ እንደ መደንበር አረገና በተቀመጠበት ጉቶ ላይ ብድግ አለ ሳያስበው በዚያ
በለመለመ ሳር ላያ ይዘዋወር ጀመር፡፡
እጆቹን በጀርባው ላይ አጣምሮ ጎንበስ በማለት በግምት ከአስር: እስከ አስራ አምስት ርምጃዎችን ከተራመደ በኋላ በግራ በኩል ወደ መንገዱ ዞር ብሎ ሲያይ አንድ ለየት ያለ ነገር አየ፡፡ በመንገዱ ላይ ሰዎች አሁንም ወደ ላይ ወደ ታችም አቅጣጫ ይሄዳሉ፡፡ ነገር ግን መንገደኛ፣ ለየት ባለ እኳኋን አንዲት በጀርባዋ ጓዝ የያዘች
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
... አየ ወለቴ ጠጋ ብየ ባጥናናሁሽ፡፡ እኔ አልረሳሁሽም። የሩቅ ቅርብ ሁኜ ስላንቺ አስባለሁ። ምንግዝየም ኸልቤ አትጠፊም አለ።..
ከለቅሶው በኋላ፣ ሕዝቡ ወደ መኻል ግንብ ለስንብት ሲሄድ አብሮ ሄደ። በግርግሩ መሃል ከነአብርሃ ጋር በመጠፋፋቱ፣ ከተሰናዳው የእዝን ግብር ከሕዝቡ ጋር መካፈል ሆዱ እንቢ ብሎት፣ በሰዎች ተከልሎ ምንትዋብና ኢያሱን እጅ ነስቶ አልፎ ወርቄ ቤት ሄዶ ውጭ ተቀምጦ ጠበቃቸው።
እነወርቄ እንደተመለሱ፣ አብርሃ ለብቻው ከተፍ አለ። “የት ኸዳችሁ
ነው የተጠፋፋን? ወዲህ ብል ወዲያ ብል አጣኋችሁ” አላቸው።
ሁሉም የነበሩበትን ቦታ ከተነጋገሩ በኋላ፣ ውስጥ ገብተው ወርቄ
ምሳ አቀረበች። በልተው ሲጨርሱ፣ ጠላ እየተጎነጩ ስለ ቀኑ ውሎ ማውጋት ጀመሩ።
“መቼም ሰዉ ሁሉ ሚያወራው ስለ እቴጌ ጥንካሬ ነው” አለ፣
አብርሃ። “ቀብሩን ሆነ የቅጥር ልቅሶውን እንዴት አርገው እንዳዘጋጁት ይገርማል ። ባላባቱ፣ ካህናቱና ሊቃውንቱ፣ “በርግጥም በካፋ አልሞቱም ሲሉ ነበር አሉ” አላቸው።
ጥላዬ ዝም አለ። ምንትዋብ በልጅነቷ ባሏን በማጣቷ ጉዳቷ
ተሰምቶታል። አጠገቧ ሆኖ ሊያጽናናት ባይችልም፣ ደብረ ወርቅ መመለስ ከብዶታል። በሩቅም ቢሆን ሐዘኗን መካፈል መርጧል።ምንም ቢሆን ወለቴ እኮ አብሮ አደጌ ናት። ኑሯችን እየቅል ቢሆንም በዕዘኗ ሆነ በደስታዋ የሩቅ ቅርብ ሁኜ መካፈል አለብኝ አለ፣ ለራሱ።
በሌላ በኩል አለቃ ሔኖክን ደግሞ ሳያያቸው ማረፋቸው አሳዘነው።
ደብረ ወርቅ በነበረበት ወቅት ስለእሳቸው ሲያስብ፣ የተማረውን ሁሉ ሊያወራቸው ሲመኝ ቆይቶ፣ እንደ አባት የሚያያቸውን መምህሩን ሞት ስለነጠቀው ከፋው። በሌላ በኩል ወርቄ ወላጆቿ መጥተውላት አጠገቧ
በመሆናቸው ደስ አለው። አርባቸውን ሳላወጣ አልኸድም አለ፣ ለራሱ።
ወርቄ፣ ሐሳብ ውስጥ እንደገባ አስተዋለች። ደብረ ወርቅ እስኪመለስ ድረስ የቀድሞ ቤቱ መክረም እንደሚችል ነገረችው።
አብርሃ፣ ጥላዬን ከስድስት ዓመት በኋላ፣ በማግኘቱ ደስታው መጠን
አጥቶ ነበርና፣ “ኸኔ ዘንድ ይቆያል” አላት።
እኔማ ያው ቤቱ አለ ብየ እንጂ” አለች ወርቄ፣ ጥላዬን እያየች።
“ኸብረሃም ዘንድ እየተጫወትን እንከርማለን። ኸናንተም አልለይም።አልሰማሁ ሁኘ አለቃን ሳልቀብራቸው ቀርቸ እኼው ዛሬ እንጉሥ ለቅሶ ለመድረስ በቃሁ። እንዳው አለቃን ከዛሬ ነገ አያቸዋለሁ ስል አመለጡኝ” አላት።
ወርቄ በዐይኗ ውሃ ሞላ።
“ተይ ልዤ ጠሐይ ላይ ውለሽ መጥተሽ። መቀበል ነው እንጂ ሌላ ምን ማረግ ይቻላል?” አሏት እናቷ።
አብርሃ፣ ትኩር ብሎ አያትና፣ “የአለቃ ሞት ሁላችንንም ነው የጎዳ።መጥናናት ነው እንጂ ሌላ ምን እናረጋለን። ሞት እንደሁ ያለ ነው” አላት።
“የአለቃን ነፍስ በገነት ያኑርልን። የጃንሆይንም ነፍስ እዝጊሃር
ይማር” አሉ፣ የወርቄ አባት።
“አሜን” አሉ፣ ሁለም።
“እቴጌም ቢሆኑ አሳዘኑኝ በልዥነታቸው ባላቸውን አጥተው። ዕጣ ፈንታቸው እንደኔ የሙት ሚስት መሆኑ ያሳዝናል” አለች ወርቄ ለምንትዋብም ለራሷም በማዘን።
ሁሉም አንገታቸውን ደፍተው ዝም አሉ።
አብርሃ፣ እኔማ ትምርቱስ እንዴት ሁኖለት ይሆን እያልሁ ሳስብ”
አለው ጥላዬን፣ ቤቱን የከበበውን የትካዜ ድባብ ለመቀየር።
“ትምርቱማ... ያው ኸዝኽ አንድ ዓመት አርጌ ማልነበር ወደ ደብረ
ወርቅ ማርያም የኸድሁት? ኸዛ ያገኘዃቸው መምህር... ሊቀጠበብት አዳሙ እንዴት ያሉ ሰው መሰሉህ። አለቃ ሔኖክ እሳቸው ዘንድ ስለላኩኝ እንዳመሰገንዃቸው አለሁ። ያው... ኸዝኸ እንደኸድሁ ሥጋ
ለባሾችን ሠራሁ።”
“ሰዎችን ማለቱ ነው” ሲል አብራራ አብርሃ፣ የወርቄ ወላጆች ግር
ሲላቸው አይቶ።
“ቤተስኪያን አካባቢ ያሉ ቀሳውስት፣ መነኮሳት... መምህር
የመሳሰሉትን ማለቴ ነው” አለ፣ ጥላዬ። “ታስታውሳለህ አለቃ ሔኖክ...ነፍሳቸውን ይማርና... ስዠምር ጥቁር ቀለም ብቻ ነው ምትጠቀመው ሲለኝ? ኋላ ሌሎች ዓይነት ቀለሞችም ተጠቅሜያለሁ።”
“ራስህ እያዘጋጀህ?"
ኋላ! ራስህ ነህ እንጂ ሌላ ማን ያዘጋጅልሀል? እና ... የቤተክህነት
ሰዎችን ስትሥል፣ የልብሳቸውን ሆነ የካባቸውን ቀለም አሳምረህ
ትሠራለህ። ጥምጥማቸውንም እንዲሁ ትክክል አርገህ ትሥላለህ። ንድፉ እንዳይንጋደድብህም ትጠነቃቃለህ። የልብሳቸውንና የካባቸውንም ዕጥፋት ሳይቀር ነው በጥንቃቄ ምትሠራው።”
“ስንታቸውን ሣልህ በል?”
“ምን አለፋህ ብዙዎቹን ሥያለሁ። የዠመርሁት በአንድ መነኩሴ
ነበር። መነኩሴው ሲያዩት ደስ አላቸው። ማስታወሻ ብየ ሰጠኋቸው።ሁለተኛ ሊቀጠበብት አዳሙን ነበር የሣልሁት። እሳቸውም እንደዝሁ ደስ አላቸው። እንዲህ እያልሁ ወደሚቀጥለው ተሻገርሁ።”
“ምን ሠራህ?”
“ጻድቃንን ሣልሁ። አቡነ ተክለሃይማኖትን፣ ቅዱስ ያሬድን፣ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስን፣ አቡነ ኪሮስን፣ እናታችንን ክርስቶስ ሣምራን የመሰሉትን ሣልሁ።”
“የሁሉን መልክ አውቃችሁ ነው ምትሥሉ?” ሲሉ ጣልቃ ገቡ፣
የወርቄ አባት።
“የለ... የለ... እነሱን ስንሥል መልካቸውን ስለማናውቅ... የተሰወሩ ስላለባቸውም ... ታሪካቸውን፣ ታምራቸውንና ገድላቸውን ጠንቅቀን
አውቀን ነው ምንሥል። እነሱን ለመሣል ኸመነሣታችን በፊት
ታሪካቸውንና ገድላቸውን ለማወቅ ንባብ አድርገን ነው ምንሥላቸው።
ሥጋ ወደሙን ተቀብለን ስንሠራ ደሞ ትክክለኛ መልካቸው
ይገለጥልናል” አላቸው፣ ጥላዬ።
“እህ” አሉ የወርቄ አባት፣ እንደገባቸው ለማሳወቅ ራሳቸውን
እየነቀነቁ።
“እንደ ቅኔ ነው በለኛ! እኛም እኮ ክብረ ነገሥት፣ ገድላት፣ ድርሳናት
ወንጌል... መጽሐፍ ቅዱስ... ኻላወቅን ቅኔ አንቆጥርም” አለው
አብርሃ።
“አውቀው የለ። ደሞ ሰማዕታትን ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ እንደ መርቆርዮርስና ገላውዲዮስ የመሳሰሉትን ሣልሁ። ሰማዕታት ቤተክሲያን ውስጥ ሲሣሉ በግራ በኩል ነው ሚሣሉ። ሁሉም ሚሣሉበት ቦታ ቦታ አላቸው። ሚሣሉበት ቀለምም እንደዝሁ ይለያያል። ሰማዕታት ለጌታችን ለክርስቶስ ፍቅር ሲሉ፣ ስለአዳኝነቱ ሲመሰክሩ አንገታቸው
በሠይፍ ተቀልቶ፣ ወይ ከእሳት እቶን ተጥለው ማዶል የሞቱት? እናም ያነን ያፈሰሱትን ደም ለመዘከር በቀይ ቀለም ይሣላሉ። መላዕክት የመንፈስ ቅዱስ ሕይወት በነሱ ላይ ስላደረ... ብርሃንና ተስፋ ሰጪዐስለሆኑ፣ እነሱን ለመሣል ምትጠቀመው ቀለም ደማቅ መሆን አለበት።
ደማቅ ቀለም የተስፋ ምልክት ነው። ጻድቃን.. ይኸን ዓለም ንቀው በጽድቅ ኖረው ያለፉ አባቶቻችን ደሞ ፈዘዝ ባለ ቀለም ይሣላሉ።ድንግል ማርያም ደሞ ልብሷ ከላይ በሰማያዊ፣ ከውስጥ በቀይና ምትከናነበው ደሞ በአረንጓዴ ቀለሞች ይሣላል። ምትሥለው ሥዕል
እንደ ተሣዩ ማንነትና ታሪክ ምትመርጠው ቀለም ይለያያል። ሰማያዊ መንፈሳዊ ንፅህናን ያሳያል፤ ነጭ እንደምታውቀው ብርሃን ነው፤ ብጫ
ደሞ የዠግንነት ምልክት ነው።”
“ዘይገርም!” አለ፣ አብርሃ።
“ምን አለፋህ መላዕክትን... ሰባቱን ሊቃነ መላዕክት... እነቅዱስ ገብርኤልንም ሣልሁ” ሲል ቀጠለ ጥላዬ። “መላዕክት እንደምታውቀው መከሠቻ አላቸው። ሚከሠቱበት መንገድም ይለያያል...”
“መከሠቻ?” አሉ፣ ሁሉን በጥሞና ሲያዳምጡ የቆዩት የወርቄ እናት።
“ኣዎ መገለጫ ማለቴ ነው።”
“እንዴት እንዴት ሁነው ነው ሚገለጡ?”
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
... አየ ወለቴ ጠጋ ብየ ባጥናናሁሽ፡፡ እኔ አልረሳሁሽም። የሩቅ ቅርብ ሁኜ ስላንቺ አስባለሁ። ምንግዝየም ኸልቤ አትጠፊም አለ።..
ከለቅሶው በኋላ፣ ሕዝቡ ወደ መኻል ግንብ ለስንብት ሲሄድ አብሮ ሄደ። በግርግሩ መሃል ከነአብርሃ ጋር በመጠፋፋቱ፣ ከተሰናዳው የእዝን ግብር ከሕዝቡ ጋር መካፈል ሆዱ እንቢ ብሎት፣ በሰዎች ተከልሎ ምንትዋብና ኢያሱን እጅ ነስቶ አልፎ ወርቄ ቤት ሄዶ ውጭ ተቀምጦ ጠበቃቸው።
እነወርቄ እንደተመለሱ፣ አብርሃ ለብቻው ከተፍ አለ። “የት ኸዳችሁ
ነው የተጠፋፋን? ወዲህ ብል ወዲያ ብል አጣኋችሁ” አላቸው።
ሁሉም የነበሩበትን ቦታ ከተነጋገሩ በኋላ፣ ውስጥ ገብተው ወርቄ
ምሳ አቀረበች። በልተው ሲጨርሱ፣ ጠላ እየተጎነጩ ስለ ቀኑ ውሎ ማውጋት ጀመሩ።
“መቼም ሰዉ ሁሉ ሚያወራው ስለ እቴጌ ጥንካሬ ነው” አለ፣
አብርሃ። “ቀብሩን ሆነ የቅጥር ልቅሶውን እንዴት አርገው እንዳዘጋጁት ይገርማል ። ባላባቱ፣ ካህናቱና ሊቃውንቱ፣ “በርግጥም በካፋ አልሞቱም ሲሉ ነበር አሉ” አላቸው።
ጥላዬ ዝም አለ። ምንትዋብ በልጅነቷ ባሏን በማጣቷ ጉዳቷ
ተሰምቶታል። አጠገቧ ሆኖ ሊያጽናናት ባይችልም፣ ደብረ ወርቅ መመለስ ከብዶታል። በሩቅም ቢሆን ሐዘኗን መካፈል መርጧል።ምንም ቢሆን ወለቴ እኮ አብሮ አደጌ ናት። ኑሯችን እየቅል ቢሆንም በዕዘኗ ሆነ በደስታዋ የሩቅ ቅርብ ሁኜ መካፈል አለብኝ አለ፣ ለራሱ።
በሌላ በኩል አለቃ ሔኖክን ደግሞ ሳያያቸው ማረፋቸው አሳዘነው።
ደብረ ወርቅ በነበረበት ወቅት ስለእሳቸው ሲያስብ፣ የተማረውን ሁሉ ሊያወራቸው ሲመኝ ቆይቶ፣ እንደ አባት የሚያያቸውን መምህሩን ሞት ስለነጠቀው ከፋው። በሌላ በኩል ወርቄ ወላጆቿ መጥተውላት አጠገቧ
በመሆናቸው ደስ አለው። አርባቸውን ሳላወጣ አልኸድም አለ፣ ለራሱ።
ወርቄ፣ ሐሳብ ውስጥ እንደገባ አስተዋለች። ደብረ ወርቅ እስኪመለስ ድረስ የቀድሞ ቤቱ መክረም እንደሚችል ነገረችው።
አብርሃ፣ ጥላዬን ከስድስት ዓመት በኋላ፣ በማግኘቱ ደስታው መጠን
አጥቶ ነበርና፣ “ኸኔ ዘንድ ይቆያል” አላት።
እኔማ ያው ቤቱ አለ ብየ እንጂ” አለች ወርቄ፣ ጥላዬን እያየች።
“ኸብረሃም ዘንድ እየተጫወትን እንከርማለን። ኸናንተም አልለይም።አልሰማሁ ሁኘ አለቃን ሳልቀብራቸው ቀርቸ እኼው ዛሬ እንጉሥ ለቅሶ ለመድረስ በቃሁ። እንዳው አለቃን ከዛሬ ነገ አያቸዋለሁ ስል አመለጡኝ” አላት።
ወርቄ በዐይኗ ውሃ ሞላ።
“ተይ ልዤ ጠሐይ ላይ ውለሽ መጥተሽ። መቀበል ነው እንጂ ሌላ ምን ማረግ ይቻላል?” አሏት እናቷ።
አብርሃ፣ ትኩር ብሎ አያትና፣ “የአለቃ ሞት ሁላችንንም ነው የጎዳ።መጥናናት ነው እንጂ ሌላ ምን እናረጋለን። ሞት እንደሁ ያለ ነው” አላት።
“የአለቃን ነፍስ በገነት ያኑርልን። የጃንሆይንም ነፍስ እዝጊሃር
ይማር” አሉ፣ የወርቄ አባት።
“አሜን” አሉ፣ ሁለም።
“እቴጌም ቢሆኑ አሳዘኑኝ በልዥነታቸው ባላቸውን አጥተው። ዕጣ ፈንታቸው እንደኔ የሙት ሚስት መሆኑ ያሳዝናል” አለች ወርቄ ለምንትዋብም ለራሷም በማዘን።
ሁሉም አንገታቸውን ደፍተው ዝም አሉ።
አብርሃ፣ እኔማ ትምርቱስ እንዴት ሁኖለት ይሆን እያልሁ ሳስብ”
አለው ጥላዬን፣ ቤቱን የከበበውን የትካዜ ድባብ ለመቀየር።
“ትምርቱማ... ያው ኸዝኽ አንድ ዓመት አርጌ ማልነበር ወደ ደብረ
ወርቅ ማርያም የኸድሁት? ኸዛ ያገኘዃቸው መምህር... ሊቀጠበብት አዳሙ እንዴት ያሉ ሰው መሰሉህ። አለቃ ሔኖክ እሳቸው ዘንድ ስለላኩኝ እንዳመሰገንዃቸው አለሁ። ያው... ኸዝኸ እንደኸድሁ ሥጋ
ለባሾችን ሠራሁ።”
“ሰዎችን ማለቱ ነው” ሲል አብራራ አብርሃ፣ የወርቄ ወላጆች ግር
ሲላቸው አይቶ።
“ቤተስኪያን አካባቢ ያሉ ቀሳውስት፣ መነኮሳት... መምህር
የመሳሰሉትን ማለቴ ነው” አለ፣ ጥላዬ። “ታስታውሳለህ አለቃ ሔኖክ...ነፍሳቸውን ይማርና... ስዠምር ጥቁር ቀለም ብቻ ነው ምትጠቀመው ሲለኝ? ኋላ ሌሎች ዓይነት ቀለሞችም ተጠቅሜያለሁ።”
“ራስህ እያዘጋጀህ?"
ኋላ! ራስህ ነህ እንጂ ሌላ ማን ያዘጋጅልሀል? እና ... የቤተክህነት
ሰዎችን ስትሥል፣ የልብሳቸውን ሆነ የካባቸውን ቀለም አሳምረህ
ትሠራለህ። ጥምጥማቸውንም እንዲሁ ትክክል አርገህ ትሥላለህ። ንድፉ እንዳይንጋደድብህም ትጠነቃቃለህ። የልብሳቸውንና የካባቸውንም ዕጥፋት ሳይቀር ነው በጥንቃቄ ምትሠራው።”
“ስንታቸውን ሣልህ በል?”
“ምን አለፋህ ብዙዎቹን ሥያለሁ። የዠመርሁት በአንድ መነኩሴ
ነበር። መነኩሴው ሲያዩት ደስ አላቸው። ማስታወሻ ብየ ሰጠኋቸው።ሁለተኛ ሊቀጠበብት አዳሙን ነበር የሣልሁት። እሳቸውም እንደዝሁ ደስ አላቸው። እንዲህ እያልሁ ወደሚቀጥለው ተሻገርሁ።”
“ምን ሠራህ?”
“ጻድቃንን ሣልሁ። አቡነ ተክለሃይማኖትን፣ ቅዱስ ያሬድን፣ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስን፣ አቡነ ኪሮስን፣ እናታችንን ክርስቶስ ሣምራን የመሰሉትን ሣልሁ።”
“የሁሉን መልክ አውቃችሁ ነው ምትሥሉ?” ሲሉ ጣልቃ ገቡ፣
የወርቄ አባት።
“የለ... የለ... እነሱን ስንሥል መልካቸውን ስለማናውቅ... የተሰወሩ ስላለባቸውም ... ታሪካቸውን፣ ታምራቸውንና ገድላቸውን ጠንቅቀን
አውቀን ነው ምንሥል። እነሱን ለመሣል ኸመነሣታችን በፊት
ታሪካቸውንና ገድላቸውን ለማወቅ ንባብ አድርገን ነው ምንሥላቸው።
ሥጋ ወደሙን ተቀብለን ስንሠራ ደሞ ትክክለኛ መልካቸው
ይገለጥልናል” አላቸው፣ ጥላዬ።
“እህ” አሉ የወርቄ አባት፣ እንደገባቸው ለማሳወቅ ራሳቸውን
እየነቀነቁ።
“እንደ ቅኔ ነው በለኛ! እኛም እኮ ክብረ ነገሥት፣ ገድላት፣ ድርሳናት
ወንጌል... መጽሐፍ ቅዱስ... ኻላወቅን ቅኔ አንቆጥርም” አለው
አብርሃ።
“አውቀው የለ። ደሞ ሰማዕታትን ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ እንደ መርቆርዮርስና ገላውዲዮስ የመሳሰሉትን ሣልሁ። ሰማዕታት ቤተክሲያን ውስጥ ሲሣሉ በግራ በኩል ነው ሚሣሉ። ሁሉም ሚሣሉበት ቦታ ቦታ አላቸው። ሚሣሉበት ቀለምም እንደዝሁ ይለያያል። ሰማዕታት ለጌታችን ለክርስቶስ ፍቅር ሲሉ፣ ስለአዳኝነቱ ሲመሰክሩ አንገታቸው
በሠይፍ ተቀልቶ፣ ወይ ከእሳት እቶን ተጥለው ማዶል የሞቱት? እናም ያነን ያፈሰሱትን ደም ለመዘከር በቀይ ቀለም ይሣላሉ። መላዕክት የመንፈስ ቅዱስ ሕይወት በነሱ ላይ ስላደረ... ብርሃንና ተስፋ ሰጪዐስለሆኑ፣ እነሱን ለመሣል ምትጠቀመው ቀለም ደማቅ መሆን አለበት።
ደማቅ ቀለም የተስፋ ምልክት ነው። ጻድቃን.. ይኸን ዓለም ንቀው በጽድቅ ኖረው ያለፉ አባቶቻችን ደሞ ፈዘዝ ባለ ቀለም ይሣላሉ።ድንግል ማርያም ደሞ ልብሷ ከላይ በሰማያዊ፣ ከውስጥ በቀይና ምትከናነበው ደሞ በአረንጓዴ ቀለሞች ይሣላል። ምትሥለው ሥዕል
እንደ ተሣዩ ማንነትና ታሪክ ምትመርጠው ቀለም ይለያያል። ሰማያዊ መንፈሳዊ ንፅህናን ያሳያል፤ ነጭ እንደምታውቀው ብርሃን ነው፤ ብጫ
ደሞ የዠግንነት ምልክት ነው።”
“ዘይገርም!” አለ፣ አብርሃ።
“ምን አለፋህ መላዕክትን... ሰባቱን ሊቃነ መላዕክት... እነቅዱስ ገብርኤልንም ሣልሁ” ሲል ቀጠለ ጥላዬ። “መላዕክት እንደምታውቀው መከሠቻ አላቸው። ሚከሠቱበት መንገድም ይለያያል...”
“መከሠቻ?” አሉ፣ ሁሉን በጥሞና ሲያዳምጡ የቆዩት የወርቄ እናት።
“ኣዎ መገለጫ ማለቴ ነው።”
“እንዴት እንዴት ሁነው ነው ሚገለጡ?”
#ትኩሳት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
...ስለነሱ ስትነግሪኝ ለምን ልቤ እንደሚጠፋ ልንገርሽ»
«ለምንድነው?»
«ከነገርሽኝ ነገሩን አወቅኩት ማለት ነው። ካወቅኩት ደሞ
አያስፈራኝም፡፡ ጭለማ ሲሆን፣ ምን ይመጣብኝ ይሆን? በማለት
እፈራለሁ እንጂ፡ በብርሀን ካየሁት ማንም ሰው ቢሆን አያስፈራኝም፡፡ ማለቴ ሳላውቀው አንድ ሰው ይተኛሽ ይሆን? ብዬ እፈራለሁ እንጂ፣ እያወቅኩ ከሆነ፣ አስር ሰው ቢተኛሽም አልፈራም፡፡
እያወቅኩት ከተደረገ ድርጊቱ የኔ ሆነ ማለት ነው፡፡ የኔ ከሆነ
ሊጎዳኝ አይችልም .. እንዴት እንደተኙሽ ስትነግሪኝ፣ እኔ እነሱን
ሆኜ ተኛሁሽ፣ ተወስዶብኝ የነበረውን ገላሽን፣ ቃላትን መለሱልኝ ማለት ነው። ... ስለዚህ ነው የተኙሽ ወንዶች ቁጥር እንደመብዛቱ መጠን የኔ ደስታ የሚበዛው፡፡»
«አልገባኝም»
«አየሽ፣ ማንም አልተኛሽም ማለት ያስፈራኛል፡፡ ጭለማ ውስጥ
ነኝ ማለት ነው። .. አንድ ሰው ተኝቶኛል ብትይ፡ ትንሽ ይሻለኛል። ግን አሁንም አንድ ሰው ደብቀሽኝ ሊሆን ይችላል። አራት ወንድ ተኛኝ ብትይ የበለጠ ይሻላል። ምክንያቱም የደበቅሽኝ ነገር
የለም ማለት ነው። ስለዚህ መፍራት አያስፈልገኝም፤ ምክንያቱም የተወሰደብኝ ሁሉ ተመልሶልኝ አቅፌዋለሁ ማለት ነው፡፡»
«ገባኝ። አንድ ጥያቄ፡፡»
«ምን?»
«እኔም እነሱም ያው ነን ካልክ፣ ምን እንዳረጉኝ ባታውቅስ ምን
ልዩነት ያመጣል?»
«ይህን አትጠይቂኝ። ላስረዳሽ አልችልም፡፡ እኔም ራሴ
አይገባኝም፡፡ ምናልባት እኔም እነሱም ያው ለመሆን የምንችለው፣ እነሱ ያረጉትን ካወቅኩ ብቻ ይሆናል፡፡»
ዝም ዝም ሆነ፡፡ ታችኛ ከንፈሯን እየነከለች ስታስብ ቆየች
«ልንገርህ?» አለች
«ምን?»
«እኔ በበኩሌ ሌላ ሆኖ ነው የሚታየኝ»
እንዴት ሆኖ ነው ሚታይሽ?»
“በጭራሽ በሽታ አልያዘህም፡፡ እንደሌላ ወንድ ነህ»
ሌሎች ወንዶች ከሌላ ጋር ተኝተሽ ነይልኝ ይሉሻል?»
« አይሉኝም
እኔም የሚሉሽ አልመሰለኝም
«ስማኝ እንግዲህ:: ክርክሩን ተውና አድምጠኝ። በግብረ ስጋ
በኩል ስለሴቶች ታውቃለህ እንጂ፣ በጥቅሉ ስለ ሴቶች ምን
ታውቃለህ? እነሱ ካልነገሩሀ ስለነሱ ለማወቅ አትችልም፡፡ እነሱ ደሞ የውስጡን አይነግሩህም። ለምሳሌ፣ አንተ እኔን ከሌሎች እየተቀበልክ እንደምትደሰትብኝ ለሰው ትነግራለህ ይመስልሀል? ለማንም አትናገርም። ሌሎችም ወንዶች ውስጣዊውን ምስጢር አይነግሩህም፡፡
ስለዚህ ሴት ካልሆንክ ወንዶችን በዚህ በኩል ልታውቃቸው
አትችልም። እኔ ልንገርህ
“ብዙ ጋብቻዎች መቀዝቀዝ ሲጀምሩ፣ ሴትዮዋ ተስፋ
ትቆርጥና ውሽማ ትይዛለች። ባልየው ሲያውቅ ምን እንደሚያደርግ ታውቃለህ? ለጊዜው ይናደዳል፣ ይደበድባታል፣ እንፋታ ይላል።
በኋላ ግን ታርቀው ይቅርታ ያደርግላትና፣ በጣም ሊወዳት
ይጀምራል። ቀዝቅዞ የነበረው ጋብቻ ይሞቃል፣ ይታደሳል። ለምን? ሴትዮዋ ሌላ ወንድ ጋ ስለሄደች ነው
መንገድ ዳር ውጣና ጎረምሶቹን ሴት ሲያድኑ እያቸው።
ሴትዮዋ በጣም ጨዋ ከመሰለቻቸው፣ ምንም ቆንጆ ብትሆን አይከተሏትም፡፡ ትንሽ በመጠኑ ስድ ብጤ ከሆነች ግን
አስተያየቷ፣ አረማመዷ፣ ወይም አለባበሷ በቂ ልቅነት ካሳየ
ጎረምሶቹ ይሻሟታል። በቀላሉ ሊያገኙዋት ስለሚችሉ ብቻ
እንዳይመስልህ፡፡ ዋናው ምክንያት ሌላ ነው። ባለጌ ከመሰለች፣
እንግዲያው ብዙ ወንድ ኣውቃለች ማለት ነው:: ለዚህ ነው
የሚሻሟት
«እየው፣ የሰው ልጅ ፍጥረቱ እንደዚህ ነው:: አንድ የለመድከው ሰው ሊለይህ የሆነ እንደሆነ ልትወደው ትጀምራለህ።
ለህይወትህ የሚያስፈራ በሽታ የያዘህ የመሰለህ እንደሆነ፣ በፊት
ከምንም የማትቆጥራትን ህይወትህን በሀይል ልትወዳት ትጀምራለህ
ሀኪም ጨው እንዳትበላ ያዘዘህ : እንደሆነ፣ ጨው ምንኛ ግሩም
ቅመም እንደሆነ ትገነዘባለህ ሴትህ ወደሌላ የሄደችብህ
እንደሆነ፣ እንዴት ቆንጆ እንደሆነች እንደ አዲስ ሊታይህ ይጀምራል
በራሲ የሚያጋጥመኝን ለምን አልነግርህም? በዚህ ሰሞን
ከማያቸው ወንዶች ሁለቱ እንዴት እንደሚሆኑ ላጫውትህ፡፡ ሁለቱም
ያው ናቸው። ስለዚህ ስለአንዱ ልንገርህ፡፡ ማርሴል ይባላል። በጣም ቆንጆ ነው። ብዙ ሴት ያወቀ ወጣት ነው። ማታ ከእራት በኋላ ካንተ እንደተለየሁ፣ በቀጥታ ወደሱ የሄድኩ እንደሆነ፣ ንፁህ ነኝ፣ የማንም ላብ አልነካኝም፣ ጠረኔ የራሴ ነው፡፡ ልብሴን አስወልቆ ያቅፈኛል! በደምብ ያስደስተኛል፡፡ አንዳንዴ ታድያ፣ ካንተ እንደትለየሁ በቀጥታ ወደሱ እልሄድም፡፡ በፊት ሌላጋ እደርሳለሁ። እና እሱጋ ስሄድ የሌላ ወንድ ላብ ነክቶኛል፣ ጠረኔ የብቻዬ ሳይሆን ከጎረምሳ ጠረን ጋር ተቀላቅሏል። አሁንም ልብሴን ያስወልቀኝና ያቅፈኛል፤ ግን እንደነብር ይሆናል፣ ይጨፈልቀኛል፣ ይነክሰኛል።
ስለሌላ ወንድ አንነጋገርም ግን ሌላጋ እንደነበርኩ በማወቁ የበለጠ እንደሚጣፍጠው ግልፅ ነው፡፡ ይታይሀል?"
«በሚገባ! እና እኔ እንዲህ የምሆንበት ምክንያቱ ምን
ይመስልሻል?» ቀላል ነው። አንደኛ፣ ሌላ ወንድ ከተኛኝ ቆንጆ ነኝ ማለት ነው። ብዙዎች ከተኙኝ እጅግ በጣም ቆንጆ ነኝ፡፡ ስለዚህ የቀለጠ ትፈልገኛለህ፡፡ ሁለተኛ፣ ሌላው ተኝቶኝ አንተ ቀጥለህ ከተኛኸኝ፣ ከሱ ቀምተህ ወሰድከኝ ማለት ነው:: እኔ በሀይል ቆንጆ ሆኜ ከሌሎቹ ሁሉ ቀምተህ ከወሰድከኝ፣ ከሌሎቹ ሁሉ የበለጠ ወንድ ነህ።በወንድነት ከሁሉ በላይ ሆንክ፣ ስለዚህ ደስ ይልሀል፡፡ በጣም ደስ ይልሀል። ወንዶች ሁላችሁም እንደሱ ናችሁ። ግን አየችኝ..
«ግን ምን?» አልኳት
አብዛኛዎቹ ወንዶች ውጪውን ጎበዝ ቢመስሉም ውስጡን ፈሪ
ናቸው፡፡ የውስጥ ስሜታቸውን አይተው መቀበል ይፈራሉ። ስለዚህ ከራሳቸው ይደብቁታል። ሁሉም ወንድ አብዛኛው ወንድ ልበል የራሱን ሴት ሌሎች ሲቀምሱበትና እሱ ነጥቋቸው መልሶ የራሱ ሲያረጋት፣ የበለጠ ወንድነት ይሰማዋል። በሀይል ደስ ይለዋል። ግን ይህን እንደ ጉድ አርጎ ስለሚቆጥረውና ስለሚያፍርበት፣ እያየውም
አውቆ አይኑን ይጨፍናል። ስለዚህ ያስመስላል፤ ያስመስላል፡
ያስመስላል። አቤት ስንት ማስመሰል አለ!
«እዚህ ላይ ነው አንተን ከልቤ የማደንቅህ፡፡ እቺን
ያህል አትፈራም። ወደነብስህ ውስጥ አትኩረህ ትመለከታለህ፡፡ እዚያ ውስጥ ምንም ቀፋፊ ነገር ብታይ አይንህን አትጨፍንም፡፡ ስለዚህ ያለማስመሰል ትኖራለህ ውስጣዊውን ኑሮ ማለቴ ነው። እንግዲህ ወደ ውስጥህ ተመለከትክ፣ ውስጥህ እኔን ሌሎች ቢተኙኝ ከነሱ
ቀምተህ ስትተኛኝ ደስ እንደሚለው ነገረህ። ስለዚህ እኔን 'ሂጂ ወንዶችሽ ጋ አልከኝ። ሄድኩ፡፡ ተመለስኩ። ተደሰትክብኝ፡፡ ወንድ
ነህ። አንተ እውነተኛ ወንድ የሆንከውን ያህል እኔ እውነተኛ ሴት ሆኜ እንደሆነ እጅግ ኩራት ይሰማኛል።»
«አንቺ እንደምትይኝ ከሆንኩ፣ አንቺም እንደኔ አይነት ነሽ።
ልክ እንደኔ አይነት! አብዛኛዎቹ ሴቶች፣ ፍቅር ከያዘኝ ወንድ ጋር
ብቻ ነው ግብረ ስጋ ደስ የሚለኝ ይላሉ። ይህም ማስመሰል፣
ማስመሰል፣ ማስመሰል ነው። አንቺ ግን ለራስሽ አትዋሺም። ቆንጆ ወጣት ሆኖ ቆንጆ ወንድ እያቀያየሩ መደሰት እንዴት ያለ ገነት ነው!' ትያለሽ። እኔኮ አልችልም፣ ቆንጆ ወንድ ሳይ አያስችለኝም፣ቁንጅናውን መንካት መዳሰስ አለብኝ፣ በወጣትነቱ መደሰት አለብኝ ትያለሽ
“አንድ ቀን አንድ ነገር አልሽኝ። አስከመቼም አልረሳውም፡፡»
«ምን አልኩህ?»
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
...ስለነሱ ስትነግሪኝ ለምን ልቤ እንደሚጠፋ ልንገርሽ»
«ለምንድነው?»
«ከነገርሽኝ ነገሩን አወቅኩት ማለት ነው። ካወቅኩት ደሞ
አያስፈራኝም፡፡ ጭለማ ሲሆን፣ ምን ይመጣብኝ ይሆን? በማለት
እፈራለሁ እንጂ፡ በብርሀን ካየሁት ማንም ሰው ቢሆን አያስፈራኝም፡፡ ማለቴ ሳላውቀው አንድ ሰው ይተኛሽ ይሆን? ብዬ እፈራለሁ እንጂ፣ እያወቅኩ ከሆነ፣ አስር ሰው ቢተኛሽም አልፈራም፡፡
እያወቅኩት ከተደረገ ድርጊቱ የኔ ሆነ ማለት ነው፡፡ የኔ ከሆነ
ሊጎዳኝ አይችልም .. እንዴት እንደተኙሽ ስትነግሪኝ፣ እኔ እነሱን
ሆኜ ተኛሁሽ፣ ተወስዶብኝ የነበረውን ገላሽን፣ ቃላትን መለሱልኝ ማለት ነው። ... ስለዚህ ነው የተኙሽ ወንዶች ቁጥር እንደመብዛቱ መጠን የኔ ደስታ የሚበዛው፡፡»
«አልገባኝም»
«አየሽ፣ ማንም አልተኛሽም ማለት ያስፈራኛል፡፡ ጭለማ ውስጥ
ነኝ ማለት ነው። .. አንድ ሰው ተኝቶኛል ብትይ፡ ትንሽ ይሻለኛል። ግን አሁንም አንድ ሰው ደብቀሽኝ ሊሆን ይችላል። አራት ወንድ ተኛኝ ብትይ የበለጠ ይሻላል። ምክንያቱም የደበቅሽኝ ነገር
የለም ማለት ነው። ስለዚህ መፍራት አያስፈልገኝም፤ ምክንያቱም የተወሰደብኝ ሁሉ ተመልሶልኝ አቅፌዋለሁ ማለት ነው፡፡»
«ገባኝ። አንድ ጥያቄ፡፡»
«ምን?»
«እኔም እነሱም ያው ነን ካልክ፣ ምን እንዳረጉኝ ባታውቅስ ምን
ልዩነት ያመጣል?»
«ይህን አትጠይቂኝ። ላስረዳሽ አልችልም፡፡ እኔም ራሴ
አይገባኝም፡፡ ምናልባት እኔም እነሱም ያው ለመሆን የምንችለው፣ እነሱ ያረጉትን ካወቅኩ ብቻ ይሆናል፡፡»
ዝም ዝም ሆነ፡፡ ታችኛ ከንፈሯን እየነከለች ስታስብ ቆየች
«ልንገርህ?» አለች
«ምን?»
«እኔ በበኩሌ ሌላ ሆኖ ነው የሚታየኝ»
እንዴት ሆኖ ነው ሚታይሽ?»
“በጭራሽ በሽታ አልያዘህም፡፡ እንደሌላ ወንድ ነህ»
ሌሎች ወንዶች ከሌላ ጋር ተኝተሽ ነይልኝ ይሉሻል?»
« አይሉኝም
እኔም የሚሉሽ አልመሰለኝም
«ስማኝ እንግዲህ:: ክርክሩን ተውና አድምጠኝ። በግብረ ስጋ
በኩል ስለሴቶች ታውቃለህ እንጂ፣ በጥቅሉ ስለ ሴቶች ምን
ታውቃለህ? እነሱ ካልነገሩሀ ስለነሱ ለማወቅ አትችልም፡፡ እነሱ ደሞ የውስጡን አይነግሩህም። ለምሳሌ፣ አንተ እኔን ከሌሎች እየተቀበልክ እንደምትደሰትብኝ ለሰው ትነግራለህ ይመስልሀል? ለማንም አትናገርም። ሌሎችም ወንዶች ውስጣዊውን ምስጢር አይነግሩህም፡፡
ስለዚህ ሴት ካልሆንክ ወንዶችን በዚህ በኩል ልታውቃቸው
አትችልም። እኔ ልንገርህ
“ብዙ ጋብቻዎች መቀዝቀዝ ሲጀምሩ፣ ሴትዮዋ ተስፋ
ትቆርጥና ውሽማ ትይዛለች። ባልየው ሲያውቅ ምን እንደሚያደርግ ታውቃለህ? ለጊዜው ይናደዳል፣ ይደበድባታል፣ እንፋታ ይላል።
በኋላ ግን ታርቀው ይቅርታ ያደርግላትና፣ በጣም ሊወዳት
ይጀምራል። ቀዝቅዞ የነበረው ጋብቻ ይሞቃል፣ ይታደሳል። ለምን? ሴትዮዋ ሌላ ወንድ ጋ ስለሄደች ነው
መንገድ ዳር ውጣና ጎረምሶቹን ሴት ሲያድኑ እያቸው።
ሴትዮዋ በጣም ጨዋ ከመሰለቻቸው፣ ምንም ቆንጆ ብትሆን አይከተሏትም፡፡ ትንሽ በመጠኑ ስድ ብጤ ከሆነች ግን
አስተያየቷ፣ አረማመዷ፣ ወይም አለባበሷ በቂ ልቅነት ካሳየ
ጎረምሶቹ ይሻሟታል። በቀላሉ ሊያገኙዋት ስለሚችሉ ብቻ
እንዳይመስልህ፡፡ ዋናው ምክንያት ሌላ ነው። ባለጌ ከመሰለች፣
እንግዲያው ብዙ ወንድ ኣውቃለች ማለት ነው:: ለዚህ ነው
የሚሻሟት
«እየው፣ የሰው ልጅ ፍጥረቱ እንደዚህ ነው:: አንድ የለመድከው ሰው ሊለይህ የሆነ እንደሆነ ልትወደው ትጀምራለህ።
ለህይወትህ የሚያስፈራ በሽታ የያዘህ የመሰለህ እንደሆነ፣ በፊት
ከምንም የማትቆጥራትን ህይወትህን በሀይል ልትወዳት ትጀምራለህ
ሀኪም ጨው እንዳትበላ ያዘዘህ : እንደሆነ፣ ጨው ምንኛ ግሩም
ቅመም እንደሆነ ትገነዘባለህ ሴትህ ወደሌላ የሄደችብህ
እንደሆነ፣ እንዴት ቆንጆ እንደሆነች እንደ አዲስ ሊታይህ ይጀምራል
በራሲ የሚያጋጥመኝን ለምን አልነግርህም? በዚህ ሰሞን
ከማያቸው ወንዶች ሁለቱ እንዴት እንደሚሆኑ ላጫውትህ፡፡ ሁለቱም
ያው ናቸው። ስለዚህ ስለአንዱ ልንገርህ፡፡ ማርሴል ይባላል። በጣም ቆንጆ ነው። ብዙ ሴት ያወቀ ወጣት ነው። ማታ ከእራት በኋላ ካንተ እንደተለየሁ፣ በቀጥታ ወደሱ የሄድኩ እንደሆነ፣ ንፁህ ነኝ፣ የማንም ላብ አልነካኝም፣ ጠረኔ የራሴ ነው፡፡ ልብሴን አስወልቆ ያቅፈኛል! በደምብ ያስደስተኛል፡፡ አንዳንዴ ታድያ፣ ካንተ እንደትለየሁ በቀጥታ ወደሱ እልሄድም፡፡ በፊት ሌላጋ እደርሳለሁ። እና እሱጋ ስሄድ የሌላ ወንድ ላብ ነክቶኛል፣ ጠረኔ የብቻዬ ሳይሆን ከጎረምሳ ጠረን ጋር ተቀላቅሏል። አሁንም ልብሴን ያስወልቀኝና ያቅፈኛል፤ ግን እንደነብር ይሆናል፣ ይጨፈልቀኛል፣ ይነክሰኛል።
ስለሌላ ወንድ አንነጋገርም ግን ሌላጋ እንደነበርኩ በማወቁ የበለጠ እንደሚጣፍጠው ግልፅ ነው፡፡ ይታይሀል?"
«በሚገባ! እና እኔ እንዲህ የምሆንበት ምክንያቱ ምን
ይመስልሻል?» ቀላል ነው። አንደኛ፣ ሌላ ወንድ ከተኛኝ ቆንጆ ነኝ ማለት ነው። ብዙዎች ከተኙኝ እጅግ በጣም ቆንጆ ነኝ፡፡ ስለዚህ የቀለጠ ትፈልገኛለህ፡፡ ሁለተኛ፣ ሌላው ተኝቶኝ አንተ ቀጥለህ ከተኛኸኝ፣ ከሱ ቀምተህ ወሰድከኝ ማለት ነው:: እኔ በሀይል ቆንጆ ሆኜ ከሌሎቹ ሁሉ ቀምተህ ከወሰድከኝ፣ ከሌሎቹ ሁሉ የበለጠ ወንድ ነህ።በወንድነት ከሁሉ በላይ ሆንክ፣ ስለዚህ ደስ ይልሀል፡፡ በጣም ደስ ይልሀል። ወንዶች ሁላችሁም እንደሱ ናችሁ። ግን አየችኝ..
«ግን ምን?» አልኳት
አብዛኛዎቹ ወንዶች ውጪውን ጎበዝ ቢመስሉም ውስጡን ፈሪ
ናቸው፡፡ የውስጥ ስሜታቸውን አይተው መቀበል ይፈራሉ። ስለዚህ ከራሳቸው ይደብቁታል። ሁሉም ወንድ አብዛኛው ወንድ ልበል የራሱን ሴት ሌሎች ሲቀምሱበትና እሱ ነጥቋቸው መልሶ የራሱ ሲያረጋት፣ የበለጠ ወንድነት ይሰማዋል። በሀይል ደስ ይለዋል። ግን ይህን እንደ ጉድ አርጎ ስለሚቆጥረውና ስለሚያፍርበት፣ እያየውም
አውቆ አይኑን ይጨፍናል። ስለዚህ ያስመስላል፤ ያስመስላል፡
ያስመስላል። አቤት ስንት ማስመሰል አለ!
«እዚህ ላይ ነው አንተን ከልቤ የማደንቅህ፡፡ እቺን
ያህል አትፈራም። ወደነብስህ ውስጥ አትኩረህ ትመለከታለህ፡፡ እዚያ ውስጥ ምንም ቀፋፊ ነገር ብታይ አይንህን አትጨፍንም፡፡ ስለዚህ ያለማስመሰል ትኖራለህ ውስጣዊውን ኑሮ ማለቴ ነው። እንግዲህ ወደ ውስጥህ ተመለከትክ፣ ውስጥህ እኔን ሌሎች ቢተኙኝ ከነሱ
ቀምተህ ስትተኛኝ ደስ እንደሚለው ነገረህ። ስለዚህ እኔን 'ሂጂ ወንዶችሽ ጋ አልከኝ። ሄድኩ፡፡ ተመለስኩ። ተደሰትክብኝ፡፡ ወንድ
ነህ። አንተ እውነተኛ ወንድ የሆንከውን ያህል እኔ እውነተኛ ሴት ሆኜ እንደሆነ እጅግ ኩራት ይሰማኛል።»
«አንቺ እንደምትይኝ ከሆንኩ፣ አንቺም እንደኔ አይነት ነሽ።
ልክ እንደኔ አይነት! አብዛኛዎቹ ሴቶች፣ ፍቅር ከያዘኝ ወንድ ጋር
ብቻ ነው ግብረ ስጋ ደስ የሚለኝ ይላሉ። ይህም ማስመሰል፣
ማስመሰል፣ ማስመሰል ነው። አንቺ ግን ለራስሽ አትዋሺም። ቆንጆ ወጣት ሆኖ ቆንጆ ወንድ እያቀያየሩ መደሰት እንዴት ያለ ገነት ነው!' ትያለሽ። እኔኮ አልችልም፣ ቆንጆ ወንድ ሳይ አያስችለኝም፣ቁንጅናውን መንካት መዳሰስ አለብኝ፣ በወጣትነቱ መደሰት አለብኝ ትያለሽ
“አንድ ቀን አንድ ነገር አልሽኝ። አስከመቼም አልረሳውም፡፡»
«ምን አልኩህ?»
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....ጠዋት ግን በተቻለ እንግዳውን ለመቦጥቦጥ አቅዷል፡፡.
ሚስተር ቴናድዬ ገና ጎሕ ሳይቀድ ከመኝታው ተነስቶ ወደ እንግዳ
መቀበያ ሥፍራ ሄደ፡፡ ሻማ አብርቶ የእንግዳውን ሂሳብ ያሰላል፡፡ ሚስቱ ከአጠገቡ አጎንብሳ ቆማለች:: ሂሣቡን ሲያሰላና ቁጥሮችን ሲጽፍ በዓይንዋ
ትከተለዋለች፡፡ ግን አሳብ አይለዋወጡም፡፡ ከቤት ውስጥ ድምፅ ተሰማ አንድ ሰው ክፍሎችን ይጠርጋል፡፡
ከአንድ ሩብ ሰዓት በኋላ ሚስተር ቴናድዬ ሂሣቡን አስልቶ ጨረሰ::
ከዚያም ክፍሉን ለቅቆ ወጣ፡፡ እርሱ ልክ ሲወጣ እንግዳው እርሱ ከነበረበት ክፍል ገባ። ሚስተር ቴናድዬ ብዙ አልራቀም፥ ሚስቱ ክፍሉ ውስጥ ሆና ታየዋለች:: እንግዳው እቃውን በእጁ ይዞ ነው ከክፍሉ የገባው::
«ምነው ቶሎ ተነሱ!» አለች ሚስስ ቴናድዬ፤ «ገና ሳይነጋ ሊሄዱ
ነው እንዴ?»
እንግዳው አሳብ የገባው መሰለ፡፡ መልስ ቶሎ አልሰጠም:: ቆይቶ
ግን «አዎን እሜቴ፤ መሄድ አለብኝ» አለ፡፡ወደ ሌላ «አገር ማለፍዎ ነው? ሞንትፌርሜ ውስጥ ሥራ የለዎትም
ማለት ነው?» ስትል ጠየቀች::
«የለም፧ ስለመሸብኝ ነው ያደርኩት እንጂ እዚህ የተለየ ጉዳይ
የለኝም» ካለ በኋላ ሂሣቡ ስንት እንደሆነ ጠየቀ፡፡
ሚስስ ቴናድዬ የቃል መልስ ሳትሰጠው ባልተቤትዋ ያዘጋጀውን
ሂሣብ ኣንስታ ሰጠችው::
መንገደኛው ወረቀቱን በማገላበጥ ሂሣቡን ተመለከተ፤ ግን ወረቀቱ
ላይ ያፍጥጥ እንጂ አሳቡ ሌላ ቦታ ነበር::
«እሜቴ» አለ፧ «ሞንትፌርሜ ውስጥ የንግድ ሥራ እንቅስቃሴ
እንዴት ነው?» ሲል ጠየቃት::
«ምንም አይደል» ብላ መለሰችለት በመገረም::፡ እርስዋ የጠበቀችው ሌላ ጥያቄ ነበር፡፡ «ክቡርነትዎ እንደሚያውቀው መቼም ጊዜው እስከዚህም የሚያስደስት አይደለም:: ከተማዋ ውስጥ ብዙ ብር ያላቸው ሰዎች በጣት የሚቆጠሩ ናቸው:: ከተማዋም እንደሚያዩዋት በጣም አነስተኛ ከተማ ናት፡፡ እንደ እርስዎ ያለ ሀብታም እንግዳ የሚያጋጥመን አልፎ አልፎ ነው፡፡
ወጪያችን ግን በጣም ብዙ ነው:: ያቺ ትንሽ ልጅ እንኳን ብዙ ታስወጣናለች»
በማለት ችግርዋን ደረደረች::
«ከእርስዋ ብትገላገሉስ?» አለ ነገሩን በማናናቅና በማንቋሸሽ፡፡
«ከማን? ከኮዜት?»
«አዎን፡፡»
የሴትዮዋ ፊት እንደማታ ጨረቃ ወገግ አለ፡፡
«አይ ጌታዬ! ውሰዷት፤ የትም አድርሷት፤ ቢፈልጉ እንደ ምግብ
ብሏት፤ እንደ ውሃ ጠጧት ብቻ ውሰዷት እንጂ እንደፈለጉ ያድርጓት፡፡እምዬ ማርያም ከእርስዋ ብትገላግለኝ ሻማ አበራታለሁ:»
«ተስማምቻለሁ፡፡»
«ይቀልዳሉ መሰለኝ፣ አሁን እውነት ከልብዎ ነው? ይዘዋት ይሄዳሉ?»
«አሁኑኑ እወስዳታሁ፤ ልጅትዋን ይጥሯት፡፡»
«ኮዜት!» ስትል ሚስስ ቴናድዬ ተጣራች::
«ልጅትዋ እስክትመጣ ሂሣቡን ላጠናቅቅ ስንት ነበር?»
ሂሣቡን ከወረቀቱ ላይ አየ:: ግን የመገረም ምልክት አላሳየም::
«ሃያ ሦስት ፍራንክ?»
በዚህ ጊዜ ሚስተር ቴናድዬ ከክፍሉ ውስጥ ገባ፡፡
«የለም ጌታው፤ ያለብህ ሃያ ስድስት ሱስ ብቻ ነው» አለ፡፡
«ሃያ ስድስት ሱስ» ስትል ሴትዮዋ ጮኸች::
«የክፍሉ ኪራይ ሃያ ሰስ ሲሆን የእራት ሂሣብ ስድስት ሱስ ነው::
ስለልጅትዋ ግን እኔና አንተ እንነጋገራለን፡፡ አንቺ ደግሞ ጉዳዩን ለእኛ ብትተይው ይሻላል፡፡»
ሚስስ ቴናድዬ በባልዋ ሁኔታ ተገርማ መልስ ሳትሰጥ ከክፍሉ
ወጥታ ሄደች::
ባለቤቱ እንደወጣች «ምነው ቆምክ? እስቲ አንዴ ቁጭ በል» በማለት ወንበር አቀረበለት:: መንገደኛው ቁጭ አለ፡፡ ሚስተር ቴናድዬ ግን አልተቀመጠም፡፡
«ጌታው» አለ ሚስተር ቴናድዬ ፤ «መቼም ይህቺ ልጅ በጣም
የማደንቃትና የምወዳት ናት፡፡»
እንግዳው ሰውዬ አተኩሮ በማፍጠጥ ተመለከተው::
«የምን ልጅ?»
ሚስተር ቴናድዬ ቀጠለ፡፡
«የእርስዋ ነገር አይሆንልኝም፤ ይህቺን ልጅ በጣም ነው የማደንቃት!»
«የትኛዋን ልጅ ነው የምትለው?» ሲል እንግዳው ጠየቀ፡፡
«ውይ አልገባህም እንዴ! ይህቺ የኛይቱ ትንሽዋ ኮዜት ናታ! እና
አሁን አንተ ልትወስድብን ትፈልጋለህ! እኔ መቼም በዚህ አልስማማም::ከሄደች እጅግ በጣም ትናፍቀኛለች፡፡ ከሕፃንነትዋ ጀምሮ ኣብራን ስለኖረች
የእርስዋ ነገር አይሆንልንም እርግጥ ነው ብዙ ታስወጣናለች፤ ብዙ ጥፋትም ታጠፋለች:፡ እኛ ደግሞ የተትረፈረፈ ሀብት የለንም፡፡ ሆኖም አንድ ጊዜ
ታማ አራት መቶ ፍራንክ ለመድኃኒት አስወጥታኛለች፡፡ ለሰማዩ ጌታ ስል ይህን ያህል ወጪ በማውጣታችን አልተማረርንም፡፡ እናትም አባት
የላትም፡፡ እኔ ግን እንደ አባትም እንደ እናትም ሁኜ አሳደግኋት:: አሁን ቢሆን ለእኔና ለእርስዋ የሚሆን የእለት እንጀራ ኣላጣም፡፡ ስለዚህ ይህቺ ልጅ እንድትሄድብኝ አልፈልግም:: መቼም የምለው ነገር ይገባሃል፡፡ ልጅትዋን
እንወዳታለን፡፡ ባለቤቴ አንዳንዴ ችኩል ናት:: ነገር ግን እርስዋም ብትሆን ልጅትዋን ትወዳታለች፡፡ እንደ ራሳችን ልጅ ነው የምናያት፡፡»
ሚስተር ቴናድዬ ይህን ሁሉ ሲለፈልፍ እንግዳው መንገደኛ ዓይኑን ከተናጋሪው ዓይን አላነሳም:: ሰውዬው ንግግሩን ቀጠለ፡፡
«ይቅርታ አድርግልኝና ማንም ሰው ቢሆን ልጁን ለማያውቀው ሰው
አንስቶ አይሰጥም፡፡ ልክ አይደለሁም? መቼም አንተ እንዲሁ ሲያዩህ የጨዋ
ልጅ እንደሆንክ ታስታውቃለህ፡፡ ሀብትም የተረፈህ ትመስላለህ፡፡ ልጅትዋን ልውሰዳት ስትል ስለልጅትዋ ብለህ እንደሆነ ማወቅ ይኖርብኛል፡፡ ገባህ
አይደለም? ለእርስዋ ስል ስሜቴን ልግታ፤ ጥቅሜን መስዋዕት ላድርግ ብል እንኳን የት እንደምትወስዳት ማወቅ አለብኝ:: ሌላው ቢቀር የወደፊት
አድራሻዋ የት እንደሚሆንና ከማን ጋር እንደምትኖር ባውቅ እየተመላለስኩ እጠይቃታለሁ፡፡ አሁን ለምሳሌ ስምህን እንኳን አላውቅምና ልጅትዋን ማን
ወሰዳት ተብዬ ብጠየቅ ምን እላለሁ? ነገር ግን ልጅትዋን ልውሰዳት የምትለው ለሕፃንዋ ብለህ እንደሆነ አውቃለሁ፡፡ ሌላው ቢቀር ፓስፖርትህን
ወይም የመታወቂያ ወረቀትህን እንኳን ማየት አለብኝ፡፡»
መንገደኛው አሁንም ዓይኑን ከዓይኑ ሳያነሳ የሚቀጥለውን መለሰ፡፡
ሚስተር ቴናድዬ፤ ሰዎች ከፓሪስ ከተማ ወጣ ባሉ ቁጥር የመታወቂያ ወረቀት አይዙም
ኮዜትን ከወሰድኳት እወስዳታለሁ፤ በቃ:: ሌላ አጀብ አያስፈልገውም፡ ለዚህ ማን እንደሆንክ፤ የት እንደምኖር፤ ልጅትዋ ወደፊት የት እንደምትኖር ማወቅ አያስፈልግህም፡፡ እንዲያውም እግርዋ ከዚህ ቤት ከወጣ ዳግም እንድታይዋት አልፈልግም፡፡ በዚህ ትስማማለህ? እሺ ወይም
ሰውየው ከባድ ሰው እንደሆነ ሕሊናው ጠረጠረ፡፡ ማታ ከጠጪዎች ጋር ቢጠጣ፤ ቢስቅና ቢያሽካካም ከመጀመሪያ እስከመጨረሻ ሰውየውን
አጢኖታል፡፡ ማምሻውን ዓይኑ ከኮዜት ዓይን ላይ እንዳላነሳ ልብ ብሉአል፡፡ለምን ወደዳት? ይህ ሰው ማነው? ይኸ ሁሉ ብር ተሸክሞ ሳለ ምነው አዳፋ ልብስ ለበሰ? እነዚህንና የመሳሰሉትን ጥያቄዎች አንስቶ መልስ
ለማግኘት ባለመቻሉ ተበሳጭቶ ነው ያመሽው:: አያትዋ ነው? ታዲያ ለምን ራሱን አያስተዋውቅም? አባትዋ ሊሆን አይችልም! መቼም ማንም
በሆን መብቱን አይሸሽግም፡፡ ታዲያ ይህ ሰው ማነው? ነገር ግን ሰውየው ትልቅ ሰው እንደሆነና ለመታወቅ የማይፈልገው ደግሞ በአንድ ምከንያት መሆኑን አልተጠራጠረም፡፡ ከእንግዳው ጋር ጨዋታ ሲጀምር የተደበቀ
ምስጢር መኖሩን ልቦናው አውቋል፡፡ ስለዚህ የሰውዬው ቆራጥ መልስ አላብረከረከውም፡፡ ነገር ቶሎ የሚገባው ሰው ስለሆነ ያልጠበቀው መልስ ቢመጣም አልተረበሸም፡፡ እንዲያውም እድሌ አሁን ነው ሲል አሰበ። ወዲያው ፍርጥም ብሉ ቴናድዬ ተናገረ::
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....ጠዋት ግን በተቻለ እንግዳውን ለመቦጥቦጥ አቅዷል፡፡.
ሚስተር ቴናድዬ ገና ጎሕ ሳይቀድ ከመኝታው ተነስቶ ወደ እንግዳ
መቀበያ ሥፍራ ሄደ፡፡ ሻማ አብርቶ የእንግዳውን ሂሳብ ያሰላል፡፡ ሚስቱ ከአጠገቡ አጎንብሳ ቆማለች:: ሂሣቡን ሲያሰላና ቁጥሮችን ሲጽፍ በዓይንዋ
ትከተለዋለች፡፡ ግን አሳብ አይለዋወጡም፡፡ ከቤት ውስጥ ድምፅ ተሰማ አንድ ሰው ክፍሎችን ይጠርጋል፡፡
ከአንድ ሩብ ሰዓት በኋላ ሚስተር ቴናድዬ ሂሣቡን አስልቶ ጨረሰ::
ከዚያም ክፍሉን ለቅቆ ወጣ፡፡ እርሱ ልክ ሲወጣ እንግዳው እርሱ ከነበረበት ክፍል ገባ። ሚስተር ቴናድዬ ብዙ አልራቀም፥ ሚስቱ ክፍሉ ውስጥ ሆና ታየዋለች:: እንግዳው እቃውን በእጁ ይዞ ነው ከክፍሉ የገባው::
«ምነው ቶሎ ተነሱ!» አለች ሚስስ ቴናድዬ፤ «ገና ሳይነጋ ሊሄዱ
ነው እንዴ?»
እንግዳው አሳብ የገባው መሰለ፡፡ መልስ ቶሎ አልሰጠም:: ቆይቶ
ግን «አዎን እሜቴ፤ መሄድ አለብኝ» አለ፡፡ወደ ሌላ «አገር ማለፍዎ ነው? ሞንትፌርሜ ውስጥ ሥራ የለዎትም
ማለት ነው?» ስትል ጠየቀች::
«የለም፧ ስለመሸብኝ ነው ያደርኩት እንጂ እዚህ የተለየ ጉዳይ
የለኝም» ካለ በኋላ ሂሣቡ ስንት እንደሆነ ጠየቀ፡፡
ሚስስ ቴናድዬ የቃል መልስ ሳትሰጠው ባልተቤትዋ ያዘጋጀውን
ሂሣብ ኣንስታ ሰጠችው::
መንገደኛው ወረቀቱን በማገላበጥ ሂሣቡን ተመለከተ፤ ግን ወረቀቱ
ላይ ያፍጥጥ እንጂ አሳቡ ሌላ ቦታ ነበር::
«እሜቴ» አለ፧ «ሞንትፌርሜ ውስጥ የንግድ ሥራ እንቅስቃሴ
እንዴት ነው?» ሲል ጠየቃት::
«ምንም አይደል» ብላ መለሰችለት በመገረም::፡ እርስዋ የጠበቀችው ሌላ ጥያቄ ነበር፡፡ «ክቡርነትዎ እንደሚያውቀው መቼም ጊዜው እስከዚህም የሚያስደስት አይደለም:: ከተማዋ ውስጥ ብዙ ብር ያላቸው ሰዎች በጣት የሚቆጠሩ ናቸው:: ከተማዋም እንደሚያዩዋት በጣም አነስተኛ ከተማ ናት፡፡ እንደ እርስዎ ያለ ሀብታም እንግዳ የሚያጋጥመን አልፎ አልፎ ነው፡፡
ወጪያችን ግን በጣም ብዙ ነው:: ያቺ ትንሽ ልጅ እንኳን ብዙ ታስወጣናለች»
በማለት ችግርዋን ደረደረች::
«ከእርስዋ ብትገላገሉስ?» አለ ነገሩን በማናናቅና በማንቋሸሽ፡፡
«ከማን? ከኮዜት?»
«አዎን፡፡»
የሴትዮዋ ፊት እንደማታ ጨረቃ ወገግ አለ፡፡
«አይ ጌታዬ! ውሰዷት፤ የትም አድርሷት፤ ቢፈልጉ እንደ ምግብ
ብሏት፤ እንደ ውሃ ጠጧት ብቻ ውሰዷት እንጂ እንደፈለጉ ያድርጓት፡፡እምዬ ማርያም ከእርስዋ ብትገላግለኝ ሻማ አበራታለሁ:»
«ተስማምቻለሁ፡፡»
«ይቀልዳሉ መሰለኝ፣ አሁን እውነት ከልብዎ ነው? ይዘዋት ይሄዳሉ?»
«አሁኑኑ እወስዳታሁ፤ ልጅትዋን ይጥሯት፡፡»
«ኮዜት!» ስትል ሚስስ ቴናድዬ ተጣራች::
«ልጅትዋ እስክትመጣ ሂሣቡን ላጠናቅቅ ስንት ነበር?»
ሂሣቡን ከወረቀቱ ላይ አየ:: ግን የመገረም ምልክት አላሳየም::
«ሃያ ሦስት ፍራንክ?»
በዚህ ጊዜ ሚስተር ቴናድዬ ከክፍሉ ውስጥ ገባ፡፡
«የለም ጌታው፤ ያለብህ ሃያ ስድስት ሱስ ብቻ ነው» አለ፡፡
«ሃያ ስድስት ሱስ» ስትል ሴትዮዋ ጮኸች::
«የክፍሉ ኪራይ ሃያ ሰስ ሲሆን የእራት ሂሣብ ስድስት ሱስ ነው::
ስለልጅትዋ ግን እኔና አንተ እንነጋገራለን፡፡ አንቺ ደግሞ ጉዳዩን ለእኛ ብትተይው ይሻላል፡፡»
ሚስስ ቴናድዬ በባልዋ ሁኔታ ተገርማ መልስ ሳትሰጥ ከክፍሉ
ወጥታ ሄደች::
ባለቤቱ እንደወጣች «ምነው ቆምክ? እስቲ አንዴ ቁጭ በል» በማለት ወንበር አቀረበለት:: መንገደኛው ቁጭ አለ፡፡ ሚስተር ቴናድዬ ግን አልተቀመጠም፡፡
«ጌታው» አለ ሚስተር ቴናድዬ ፤ «መቼም ይህቺ ልጅ በጣም
የማደንቃትና የምወዳት ናት፡፡»
እንግዳው ሰውዬ አተኩሮ በማፍጠጥ ተመለከተው::
«የምን ልጅ?»
ሚስተር ቴናድዬ ቀጠለ፡፡
«የእርስዋ ነገር አይሆንልኝም፤ ይህቺን ልጅ በጣም ነው የማደንቃት!»
«የትኛዋን ልጅ ነው የምትለው?» ሲል እንግዳው ጠየቀ፡፡
«ውይ አልገባህም እንዴ! ይህቺ የኛይቱ ትንሽዋ ኮዜት ናታ! እና
አሁን አንተ ልትወስድብን ትፈልጋለህ! እኔ መቼም በዚህ አልስማማም::ከሄደች እጅግ በጣም ትናፍቀኛለች፡፡ ከሕፃንነትዋ ጀምሮ ኣብራን ስለኖረች
የእርስዋ ነገር አይሆንልንም እርግጥ ነው ብዙ ታስወጣናለች፤ ብዙ ጥፋትም ታጠፋለች:፡ እኛ ደግሞ የተትረፈረፈ ሀብት የለንም፡፡ ሆኖም አንድ ጊዜ
ታማ አራት መቶ ፍራንክ ለመድኃኒት አስወጥታኛለች፡፡ ለሰማዩ ጌታ ስል ይህን ያህል ወጪ በማውጣታችን አልተማረርንም፡፡ እናትም አባት
የላትም፡፡ እኔ ግን እንደ አባትም እንደ እናትም ሁኜ አሳደግኋት:: አሁን ቢሆን ለእኔና ለእርስዋ የሚሆን የእለት እንጀራ ኣላጣም፡፡ ስለዚህ ይህቺ ልጅ እንድትሄድብኝ አልፈልግም:: መቼም የምለው ነገር ይገባሃል፡፡ ልጅትዋን
እንወዳታለን፡፡ ባለቤቴ አንዳንዴ ችኩል ናት:: ነገር ግን እርስዋም ብትሆን ልጅትዋን ትወዳታለች፡፡ እንደ ራሳችን ልጅ ነው የምናያት፡፡»
ሚስተር ቴናድዬ ይህን ሁሉ ሲለፈልፍ እንግዳው መንገደኛ ዓይኑን ከተናጋሪው ዓይን አላነሳም:: ሰውዬው ንግግሩን ቀጠለ፡፡
«ይቅርታ አድርግልኝና ማንም ሰው ቢሆን ልጁን ለማያውቀው ሰው
አንስቶ አይሰጥም፡፡ ልክ አይደለሁም? መቼም አንተ እንዲሁ ሲያዩህ የጨዋ
ልጅ እንደሆንክ ታስታውቃለህ፡፡ ሀብትም የተረፈህ ትመስላለህ፡፡ ልጅትዋን ልውሰዳት ስትል ስለልጅትዋ ብለህ እንደሆነ ማወቅ ይኖርብኛል፡፡ ገባህ
አይደለም? ለእርስዋ ስል ስሜቴን ልግታ፤ ጥቅሜን መስዋዕት ላድርግ ብል እንኳን የት እንደምትወስዳት ማወቅ አለብኝ:: ሌላው ቢቀር የወደፊት
አድራሻዋ የት እንደሚሆንና ከማን ጋር እንደምትኖር ባውቅ እየተመላለስኩ እጠይቃታለሁ፡፡ አሁን ለምሳሌ ስምህን እንኳን አላውቅምና ልጅትዋን ማን
ወሰዳት ተብዬ ብጠየቅ ምን እላለሁ? ነገር ግን ልጅትዋን ልውሰዳት የምትለው ለሕፃንዋ ብለህ እንደሆነ አውቃለሁ፡፡ ሌላው ቢቀር ፓስፖርትህን
ወይም የመታወቂያ ወረቀትህን እንኳን ማየት አለብኝ፡፡»
መንገደኛው አሁንም ዓይኑን ከዓይኑ ሳያነሳ የሚቀጥለውን መለሰ፡፡
ሚስተር ቴናድዬ፤ ሰዎች ከፓሪስ ከተማ ወጣ ባሉ ቁጥር የመታወቂያ ወረቀት አይዙም
ኮዜትን ከወሰድኳት እወስዳታለሁ፤ በቃ:: ሌላ አጀብ አያስፈልገውም፡ ለዚህ ማን እንደሆንክ፤ የት እንደምኖር፤ ልጅትዋ ወደፊት የት እንደምትኖር ማወቅ አያስፈልግህም፡፡ እንዲያውም እግርዋ ከዚህ ቤት ከወጣ ዳግም እንድታይዋት አልፈልግም፡፡ በዚህ ትስማማለህ? እሺ ወይም
ሰውየው ከባድ ሰው እንደሆነ ሕሊናው ጠረጠረ፡፡ ማታ ከጠጪዎች ጋር ቢጠጣ፤ ቢስቅና ቢያሽካካም ከመጀመሪያ እስከመጨረሻ ሰውየውን
አጢኖታል፡፡ ማምሻውን ዓይኑ ከኮዜት ዓይን ላይ እንዳላነሳ ልብ ብሉአል፡፡ለምን ወደዳት? ይህ ሰው ማነው? ይኸ ሁሉ ብር ተሸክሞ ሳለ ምነው አዳፋ ልብስ ለበሰ? እነዚህንና የመሳሰሉትን ጥያቄዎች አንስቶ መልስ
ለማግኘት ባለመቻሉ ተበሳጭቶ ነው ያመሽው:: አያትዋ ነው? ታዲያ ለምን ራሱን አያስተዋውቅም? አባትዋ ሊሆን አይችልም! መቼም ማንም
በሆን መብቱን አይሸሽግም፡፡ ታዲያ ይህ ሰው ማነው? ነገር ግን ሰውየው ትልቅ ሰው እንደሆነና ለመታወቅ የማይፈልገው ደግሞ በአንድ ምከንያት መሆኑን አልተጠራጠረም፡፡ ከእንግዳው ጋር ጨዋታ ሲጀምር የተደበቀ
ምስጢር መኖሩን ልቦናው አውቋል፡፡ ስለዚህ የሰውዬው ቆራጥ መልስ አላብረከረከውም፡፡ ነገር ቶሎ የሚገባው ሰው ስለሆነ ያልጠበቀው መልስ ቢመጣም አልተረበሸም፡፡ እንዲያውም እድሌ አሁን ነው ሲል አሰበ። ወዲያው ፍርጥም ብሉ ቴናድዬ ተናገረ::
#ገረገራ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
...ብችል ሀገር፣ ካልቻልሁ ግን ከተማ መለወጥ እንዳለብኝ ወስኜ ልጄን ጠቅልያለሁ ዓይኔን ጨፍኜ ስለ መጥፊያ አማራጮቼ ሳስብ ቆየሁና፣ ልጄን አቅፌ ቀና ስል በሰዉ ተከብቢያለሁ፡ እየቆየ ትንፋሽ እስከሚያጥረኝ ድረስ በዳስ የነበረዉ እድምተኛ ሁሉ እየመጣ ተኮደኮደ፡ ሁሉም
የቅድሙን የጃሪምን ሁኔታ ተመልክቷልና፣ አንድ አንድ እያለ መጥቶ መኝታ ክፍሉን እጭቅ ብሎበታል፡ የጃሪም መኝታ ክፍል ከሳሎኑ ጋር አንድ ግድግዳ የሚጋራ እና በሩም ሰፋ ያለ በመሆኑም ፣ ከዉስጥ የተረፈዉ
ሰዉ በዋናዉ ሳሎን ሆኖ ትከሻ ለትከሻ እየተጋፋ በበራፉ በኩል ቱናትን በዓይኑ ይወጋል። ያሽሟጥጣል፡ ከሩቅም ከቅርብም፣ ሹክሹክታ
ይሰማኛል፡
“እንዲህ ናት እዴ ለካ?” አለች አንደኛዋ በለሆሳስ፣ ግን ደግሞ
እንዲሰማኝ አድርጋ
“ጭንቅላቷ ደግሞ ምንድነዉ የሚ ያህለዉ?” ስትል ተቀበለቻት ሌላኛዋ፣ ገንፎ ያላመጠችበት ጥርሷን ለሳቅ እያገጠጠችዉ፡፡
“ገዳም ቅብጥርሴ ይላሉ እንዴ ቄሱ ደግሞ? ሆ! ሲጀመር ልክስክስነቷ መስሎኝ እዲንህ ያለ ልጅ ያስታቀፋት! መኝታዋን እንኳን በወጉ ለማድረግ ያላስቻላትን፣ እንዴት ብላ ነዉ ለገዳም ማዕረግ ትበቃለች ብለዉ የጠበቋት?”
“ጉድ እኮ ነዉ! ኧረ የሕጻኗን ዓይን ተመለከቺልኝ: እንዴት ነዉ ደግሞ
የምታቃስተዉ በናትሽ? አይ ይቺ ልጅማ አትተርፍም። ምናለች በዪኝ
ኋላ፤ የሳምንት ዕድሜ እንኳን አይኖራትም”
“የልጇ አባት ግን የትኛዉ ነዉ፤ ያ ከጎኗ ተቀምጦ የነበረዉ ጅላጅል ነዉ እዳትዪኝ ብቻ
ነዉ እንጂ እሸቴ ይባላል አሉ: ከሴተኛ አዳሪ ጭን አይጠፋም ሲሉ ሰምቻለሁ”
“ሂጅ ሂጅ ሂጅ… በስመ አብ!”
“ይቺን የመሰለች ልጅ ወስዶ እዚያ ምን እንደጣላት ላምን አልችልም
መቼም”
“አንቺ ደግሞ፣ሙሉ አድርጎ የፈጠረዉ ሰዉ አለ ብለሽ ነዉ? እንጂ እሷንም አታያትም? እኔ ነኝ የምትል ቆንጆ ደፍራ በዉብርስት አጠገብ ታልፋለች? ቆንጆ የሚለዉ ቃል እኮ አይበቃትም: ታዲያ ምን ዋጋ አለዉ? በአልጋ ሲለምኗት አፈር ሆና አረፈቺዋ! የቆንጆ ልክስክስ እሷን አየን”
“እግዚአብሔር ሲጣላ ደግሞ እንዴት እንደሚቀጣ አየሽልኝ አይደል?”
“አመንሽ? ባለፈዉ ለጃሪም እህቱ አይደለችም ስልሽ፣ እንዲያ
ስትሟገችኝ አልነበር? ይኼዉ ዛሬ ከራሱ አፍ ሰምተሽ እንኳን ለአፍ
እላፊሽ እፈሪ ተዋርደሻል''
“ኧረ እሱስ ደገቆኛል: እህቱ አይደለችም ማለት ነዉ በቃ?”
“እሷ ብቻ ናት ወንድሜ ስትለዉ የምትሰማዉ እንጂ፣ የእሷ እህትነት ከእሱ አፍ ተሰምቶ አይታወቅም ነዉ የሚባለዉ። እንዲያዉም ይኼ ግቢ
ከነቤቱ የእናት የአባቱ ነዉ አሉ እኮ: ከእነእናቷ አስወጣታለሁ እያለ ሲዝት የሰሙት ሰዎች ናቸዉ የነገሩኝ በእናትም በአባትም አይገናኙም አሉ
አሮጊቷ ራሱ በገዛ ርስቱ ላይ ተደላድላ ለመኖር ስትል እናት መሰለች እንጂ፣ የእናትነት ምልክቱ የላትም”
“ አንዴ... በየከተማዉ በየገጠሩ ሲንከራተቱ ኖረዉ ቅርብ ጊዜ
አደለም እንዴ ወደዚህ የመጡት?''
“እኮ! ድንገት ዱብ ብለዉ ነዉ አሉ አሁን ባለቤት የመሰሉት''
“እኔ አሁንም ላምን አልቻልሁም:: ጭራሽ አሮጊቷ የጃሪም እናት
አይደለችም ማለት ነዉ?''
“እየነገርሁሽ!”
“ይገርማል”
“የእሱ ይገርምሻል እንዴ አንቺ? ዝማምን ታዉቂያት የለ?''
“ዝማም ዝማም… ዝማም የዚችን እህት ማለትሽ ነዉ ወይስ ሌላ?”
“ወይ እህት እቴ: እኔማ ገና ትናንት አይደል እንዴ የምሰማዉ ?
“ምኑን? ”
“እህቷ አይደለችም''
“እርፍ! እሷም?”
“አይደለችም”
አንድ አንድ ብሎ እየገባ ቤቱን ጥቅጥቅ ብሎበት የነበረዉ እንግዳ ሁሉ፣ የቻለዉን ያህል ልጄን ተጠቋቁሞባት ሲበቃዉ፣ ቀስ በቀስ ስለ ወጣ በቤቱ
የቀረዉ ሰዉ ቀነሰ፡ ቀለል ማለቱን ተጠቅሜ ሐሜተኛ ሴቶቹን ዞሬ
በዓይኔ አጣበርኋቸዉ፡ ትኩር ብዬ ስመለከታቸዉ ልክ በድምፃቸዉ
እንደ ጠረጠርሁት እነዚያዉ ተናግሮ አናጋሪዎች ናቸዉ፡ ከአራት ወር በፊት፣ በታዕካ ነገሥት ገዳም ከእመዋ ጋር ቆይቼ ስወጣ መንገዴ ላይ ቆመዉ እህቱ ናት እህቱ አይደለችም እያሉ የተወራረዱብኝ ሴቶች ናቸዉ ምንም አላልኋቸዉም በዚያም ላይ፣ ልቤ ቆሟል ወዴት እንደምሄድ ባላዉቀዉም፣ ልጄን ይዤ ብን ብዬ ከመጥፋት ዉጪ ምንም ምርጫ አይታየኝም ጨክኛለሁ እንግዳዉ ከዳሱ እየተንጠባጠበ ወጥቶ ወጥቶ፣ ጥቂት ሰዎች ቀርተዉበታል፡ የመስኮቱን መጋረጃ በስሱ ገለጥ አድርጌ አሳልፌ ስቆጥር
እመዋ፣ ባልቻ፣ እሸቴ እና ጥቂት የቅርብ ዘመዶቻችን ብቻ ቅስማቸዉ ድቅቅ ብሎ ይታዩኛል፡ እርስ በእርስም አያወሩም: የደስታ ጫፍ እንቀምስበታለን ያሉት ቀን በብላሽ ቀርቶባቸዉ ከፍቷቸዋል፡ እኔ እርግጥ ወደምጠፋበት ለመጥፋት ከአሁን የተመቸ ጊዜ አላገኝም፡ ነገር ግን ጨቅላ ልጅ ይዤ በእግሬ ልሂድ ብል የት እደርሳለሁ? ያዉም ጨቅላዋ ቱናት ሆና፡ በዚያ ላይ፣ መጀመሪያ ወደ ምስጢራዊዋ ቤት ሄጄ
አንድ አንድ ነገሮችን መያዝ ይኖርብኛል ደግነቱ ዕድሜ ለሲራክ ፯ የብዙ ሀገራት ፓስፖርት በተለያየ ማንነት ወጥቶልኛል፡ ከሀገር መዉጣቴ ካልቀረ፣ ቢያንስ ፓስፖርቶቼን መያዝ አለብኝ ያለ ገንዘብም
የሚሆን ነገር የለም ዞሮ ዞሮ ወዲያ ወዲህ ማለቴ ላይቀር ነዉ።
እንደዚያ ከሆነ ደግሞ መኪናዬ የግድ ታስፈልገኛለች: አሁን የት
እንዳለች ግን አላዉቅም: ምክንያቱም ከነዳኋት ቆይቻለሁ፡ ሆስፒታል ከገባሁ ጀምሮ ታናሽ እህቴ እንድትጠቀምበት ፈቅጄላት እሷ ይዛት ስለሰነበተች፣ ምናልባትም ዳሱ ሲሠራ ቦታ እንዳታጣብብ ብላ፣ በጎረቤት
ግቢ ወይም የሆነ መንገድ ዳር አቁማት ይሆናል፡ በእርግጥ፣ የኔ ብቻ ሳይሆን የማንም መኪና በግቢዉ የለም።
የራሴን መኪና ማግኘቱ ቀላል አለመሆኑን እንዳወቅሁ፣ አልፎ አልፎ መኪና በማልይዘበት አጋጣሚ አገልግሎት የሚያደርግልኝን የታክሲ ደንበኛዬን ደዉዬ ጠራሁት። ወዲያዉኑ፣ ጥላዬን ጠብቄ በጀርባ በኩል
ወዳለችዋ ጠባብ የግቢያችን በር ሰተት አልሁ ሽሽት መሸነፍ መሆኑን ባዉቅም፣ ለልጄ ስል የትም ብሄድ አይገደኝም: ቢቻል ቢቻል ላሳክማት፣ ከሰዉ አፍ ላተርፋት ይገባል፡ ከዚህ በኋላ ማንም እንዲያይብኝ
አልፈልግም ማንም በልጄ ጤና እንዲሳለቅ አልፈቅድለትም።
እንዲያዉስ ገዳምሽ ናት ብለዉኝ የለ የንስሐ አባቴ? ታዲያ ወደ ገዳሜ መግባት አለብኛ! ልበል እንግዲህ ልጄ ዉስጥ ገብቼ ልመንኩስ፡፡
የሚጠበቅብኝን የአመክሮ ጊዜ እንደሆነ በሆስፒታል ቆይታዬ ተወጥቼዋለሁ
ምናልባት ቱናት፣ ከዝቋላ ወይ ከደብረ ሊባኖስ ገዳም የምትለየዉ የራሷ ትክለኛ ስለ ሌላት ብቻ ነዉ፡ ወፍጮም ሆነ እህል የሚገብርላት የለም
እንጂ፣ እሷም ሆነ ዝቋላ የእግዚአብሔር መኖሪያዎች እንደሆኑ ግን አልጠራጠርም ስለዚህ በከተማ የገደምኋትን ገዳም የሚቸግራት ነገር
እንዳይኖር ከፈለግሁ በከተማ ማገልገሉን እገደድበታለሁ
ከከተማም ደህና ሕክምና የምታገኝበት፣ ደህና ከተማ መምረጥ አለብኝ፡
አንዴ ከመነኮሱ በኋላ ደግሞ ዞሮ ማየት እንደ ሌለ አዉቃለሁ፡ አምሮቴ፣ ትዳሬ፣ ሥራዬ፣ ወዳጆቼ፣ ዘመዶቼ የሚሉትን ሁሉ መተዉ ቀዳሚዉ የገዳማዉያን ሕግ መሆኑን አዉቃለሁ ዞሮ አለማየት ፈታኝ ቢሆንም፣ የቀረዉ ይቀራል እንጂ ይኼኛዉን ሕግ ግን አልሽረዉም፡፡ በፍጹም!
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
...ብችል ሀገር፣ ካልቻልሁ ግን ከተማ መለወጥ እንዳለብኝ ወስኜ ልጄን ጠቅልያለሁ ዓይኔን ጨፍኜ ስለ መጥፊያ አማራጮቼ ሳስብ ቆየሁና፣ ልጄን አቅፌ ቀና ስል በሰዉ ተከብቢያለሁ፡ እየቆየ ትንፋሽ እስከሚያጥረኝ ድረስ በዳስ የነበረዉ እድምተኛ ሁሉ እየመጣ ተኮደኮደ፡ ሁሉም
የቅድሙን የጃሪምን ሁኔታ ተመልክቷልና፣ አንድ አንድ እያለ መጥቶ መኝታ ክፍሉን እጭቅ ብሎበታል፡ የጃሪም መኝታ ክፍል ከሳሎኑ ጋር አንድ ግድግዳ የሚጋራ እና በሩም ሰፋ ያለ በመሆኑም ፣ ከዉስጥ የተረፈዉ
ሰዉ በዋናዉ ሳሎን ሆኖ ትከሻ ለትከሻ እየተጋፋ በበራፉ በኩል ቱናትን በዓይኑ ይወጋል። ያሽሟጥጣል፡ ከሩቅም ከቅርብም፣ ሹክሹክታ
ይሰማኛል፡
“እንዲህ ናት እዴ ለካ?” አለች አንደኛዋ በለሆሳስ፣ ግን ደግሞ
እንዲሰማኝ አድርጋ
“ጭንቅላቷ ደግሞ ምንድነዉ የሚ ያህለዉ?” ስትል ተቀበለቻት ሌላኛዋ፣ ገንፎ ያላመጠችበት ጥርሷን ለሳቅ እያገጠጠችዉ፡፡
“ገዳም ቅብጥርሴ ይላሉ እንዴ ቄሱ ደግሞ? ሆ! ሲጀመር ልክስክስነቷ መስሎኝ እዲንህ ያለ ልጅ ያስታቀፋት! መኝታዋን እንኳን በወጉ ለማድረግ ያላስቻላትን፣ እንዴት ብላ ነዉ ለገዳም ማዕረግ ትበቃለች ብለዉ የጠበቋት?”
“ጉድ እኮ ነዉ! ኧረ የሕጻኗን ዓይን ተመለከቺልኝ: እንዴት ነዉ ደግሞ
የምታቃስተዉ በናትሽ? አይ ይቺ ልጅማ አትተርፍም። ምናለች በዪኝ
ኋላ፤ የሳምንት ዕድሜ እንኳን አይኖራትም”
“የልጇ አባት ግን የትኛዉ ነዉ፤ ያ ከጎኗ ተቀምጦ የነበረዉ ጅላጅል ነዉ እዳትዪኝ ብቻ
ነዉ እንጂ እሸቴ ይባላል አሉ: ከሴተኛ አዳሪ ጭን አይጠፋም ሲሉ ሰምቻለሁ”
“ሂጅ ሂጅ ሂጅ… በስመ አብ!”
“ይቺን የመሰለች ልጅ ወስዶ እዚያ ምን እንደጣላት ላምን አልችልም
መቼም”
“አንቺ ደግሞ፣ሙሉ አድርጎ የፈጠረዉ ሰዉ አለ ብለሽ ነዉ? እንጂ እሷንም አታያትም? እኔ ነኝ የምትል ቆንጆ ደፍራ በዉብርስት አጠገብ ታልፋለች? ቆንጆ የሚለዉ ቃል እኮ አይበቃትም: ታዲያ ምን ዋጋ አለዉ? በአልጋ ሲለምኗት አፈር ሆና አረፈቺዋ! የቆንጆ ልክስክስ እሷን አየን”
“እግዚአብሔር ሲጣላ ደግሞ እንዴት እንደሚቀጣ አየሽልኝ አይደል?”
“አመንሽ? ባለፈዉ ለጃሪም እህቱ አይደለችም ስልሽ፣ እንዲያ
ስትሟገችኝ አልነበር? ይኼዉ ዛሬ ከራሱ አፍ ሰምተሽ እንኳን ለአፍ
እላፊሽ እፈሪ ተዋርደሻል''
“ኧረ እሱስ ደገቆኛል: እህቱ አይደለችም ማለት ነዉ በቃ?”
“እሷ ብቻ ናት ወንድሜ ስትለዉ የምትሰማዉ እንጂ፣ የእሷ እህትነት ከእሱ አፍ ተሰምቶ አይታወቅም ነዉ የሚባለዉ። እንዲያዉም ይኼ ግቢ
ከነቤቱ የእናት የአባቱ ነዉ አሉ እኮ: ከእነእናቷ አስወጣታለሁ እያለ ሲዝት የሰሙት ሰዎች ናቸዉ የነገሩኝ በእናትም በአባትም አይገናኙም አሉ
አሮጊቷ ራሱ በገዛ ርስቱ ላይ ተደላድላ ለመኖር ስትል እናት መሰለች እንጂ፣ የእናትነት ምልክቱ የላትም”
“ አንዴ... በየከተማዉ በየገጠሩ ሲንከራተቱ ኖረዉ ቅርብ ጊዜ
አደለም እንዴ ወደዚህ የመጡት?''
“እኮ! ድንገት ዱብ ብለዉ ነዉ አሉ አሁን ባለቤት የመሰሉት''
“እኔ አሁንም ላምን አልቻልሁም:: ጭራሽ አሮጊቷ የጃሪም እናት
አይደለችም ማለት ነዉ?''
“እየነገርሁሽ!”
“ይገርማል”
“የእሱ ይገርምሻል እንዴ አንቺ? ዝማምን ታዉቂያት የለ?''
“ዝማም ዝማም… ዝማም የዚችን እህት ማለትሽ ነዉ ወይስ ሌላ?”
“ወይ እህት እቴ: እኔማ ገና ትናንት አይደል እንዴ የምሰማዉ ?
“ምኑን? ”
“እህቷ አይደለችም''
“እርፍ! እሷም?”
“አይደለችም”
አንድ አንድ ብሎ እየገባ ቤቱን ጥቅጥቅ ብሎበት የነበረዉ እንግዳ ሁሉ፣ የቻለዉን ያህል ልጄን ተጠቋቁሞባት ሲበቃዉ፣ ቀስ በቀስ ስለ ወጣ በቤቱ
የቀረዉ ሰዉ ቀነሰ፡ ቀለል ማለቱን ተጠቅሜ ሐሜተኛ ሴቶቹን ዞሬ
በዓይኔ አጣበርኋቸዉ፡ ትኩር ብዬ ስመለከታቸዉ ልክ በድምፃቸዉ
እንደ ጠረጠርሁት እነዚያዉ ተናግሮ አናጋሪዎች ናቸዉ፡ ከአራት ወር በፊት፣ በታዕካ ነገሥት ገዳም ከእመዋ ጋር ቆይቼ ስወጣ መንገዴ ላይ ቆመዉ እህቱ ናት እህቱ አይደለችም እያሉ የተወራረዱብኝ ሴቶች ናቸዉ ምንም አላልኋቸዉም በዚያም ላይ፣ ልቤ ቆሟል ወዴት እንደምሄድ ባላዉቀዉም፣ ልጄን ይዤ ብን ብዬ ከመጥፋት ዉጪ ምንም ምርጫ አይታየኝም ጨክኛለሁ እንግዳዉ ከዳሱ እየተንጠባጠበ ወጥቶ ወጥቶ፣ ጥቂት ሰዎች ቀርተዉበታል፡ የመስኮቱን መጋረጃ በስሱ ገለጥ አድርጌ አሳልፌ ስቆጥር
እመዋ፣ ባልቻ፣ እሸቴ እና ጥቂት የቅርብ ዘመዶቻችን ብቻ ቅስማቸዉ ድቅቅ ብሎ ይታዩኛል፡ እርስ በእርስም አያወሩም: የደስታ ጫፍ እንቀምስበታለን ያሉት ቀን በብላሽ ቀርቶባቸዉ ከፍቷቸዋል፡ እኔ እርግጥ ወደምጠፋበት ለመጥፋት ከአሁን የተመቸ ጊዜ አላገኝም፡ ነገር ግን ጨቅላ ልጅ ይዤ በእግሬ ልሂድ ብል የት እደርሳለሁ? ያዉም ጨቅላዋ ቱናት ሆና፡ በዚያ ላይ፣ መጀመሪያ ወደ ምስጢራዊዋ ቤት ሄጄ
አንድ አንድ ነገሮችን መያዝ ይኖርብኛል ደግነቱ ዕድሜ ለሲራክ ፯ የብዙ ሀገራት ፓስፖርት በተለያየ ማንነት ወጥቶልኛል፡ ከሀገር መዉጣቴ ካልቀረ፣ ቢያንስ ፓስፖርቶቼን መያዝ አለብኝ ያለ ገንዘብም
የሚሆን ነገር የለም ዞሮ ዞሮ ወዲያ ወዲህ ማለቴ ላይቀር ነዉ።
እንደዚያ ከሆነ ደግሞ መኪናዬ የግድ ታስፈልገኛለች: አሁን የት
እንዳለች ግን አላዉቅም: ምክንያቱም ከነዳኋት ቆይቻለሁ፡ ሆስፒታል ከገባሁ ጀምሮ ታናሽ እህቴ እንድትጠቀምበት ፈቅጄላት እሷ ይዛት ስለሰነበተች፣ ምናልባትም ዳሱ ሲሠራ ቦታ እንዳታጣብብ ብላ፣ በጎረቤት
ግቢ ወይም የሆነ መንገድ ዳር አቁማት ይሆናል፡ በእርግጥ፣ የኔ ብቻ ሳይሆን የማንም መኪና በግቢዉ የለም።
የራሴን መኪና ማግኘቱ ቀላል አለመሆኑን እንዳወቅሁ፣ አልፎ አልፎ መኪና በማልይዘበት አጋጣሚ አገልግሎት የሚያደርግልኝን የታክሲ ደንበኛዬን ደዉዬ ጠራሁት። ወዲያዉኑ፣ ጥላዬን ጠብቄ በጀርባ በኩል
ወዳለችዋ ጠባብ የግቢያችን በር ሰተት አልሁ ሽሽት መሸነፍ መሆኑን ባዉቅም፣ ለልጄ ስል የትም ብሄድ አይገደኝም: ቢቻል ቢቻል ላሳክማት፣ ከሰዉ አፍ ላተርፋት ይገባል፡ ከዚህ በኋላ ማንም እንዲያይብኝ
አልፈልግም ማንም በልጄ ጤና እንዲሳለቅ አልፈቅድለትም።
እንዲያዉስ ገዳምሽ ናት ብለዉኝ የለ የንስሐ አባቴ? ታዲያ ወደ ገዳሜ መግባት አለብኛ! ልበል እንግዲህ ልጄ ዉስጥ ገብቼ ልመንኩስ፡፡
የሚጠበቅብኝን የአመክሮ ጊዜ እንደሆነ በሆስፒታል ቆይታዬ ተወጥቼዋለሁ
ምናልባት ቱናት፣ ከዝቋላ ወይ ከደብረ ሊባኖስ ገዳም የምትለየዉ የራሷ ትክለኛ ስለ ሌላት ብቻ ነዉ፡ ወፍጮም ሆነ እህል የሚገብርላት የለም
እንጂ፣ እሷም ሆነ ዝቋላ የእግዚአብሔር መኖሪያዎች እንደሆኑ ግን አልጠራጠርም ስለዚህ በከተማ የገደምኋትን ገዳም የሚቸግራት ነገር
እንዳይኖር ከፈለግሁ በከተማ ማገልገሉን እገደድበታለሁ
ከከተማም ደህና ሕክምና የምታገኝበት፣ ደህና ከተማ መምረጥ አለብኝ፡
አንዴ ከመነኮሱ በኋላ ደግሞ ዞሮ ማየት እንደ ሌለ አዉቃለሁ፡ አምሮቴ፣ ትዳሬ፣ ሥራዬ፣ ወዳጆቼ፣ ዘመዶቼ የሚሉትን ሁሉ መተዉ ቀዳሚዉ የገዳማዉያን ሕግ መሆኑን አዉቃለሁ ዞሮ አለማየት ፈታኝ ቢሆንም፣ የቀረዉ ይቀራል እንጂ ይኼኛዉን ሕግ ግን አልሽረዉም፡፡ በፍጹም!
#ሳቤላ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
አንድ ጊዜ ከተናገረች የማትመለሰው ሚስ ካርላይል ፥ ቤቷን ለቃ ሚስተር
ካርላይል የቀጠራቸውን ሠራተኞች አሰናብታ ፒተርንና ሁለት ሠራተኞቿን ይዛ
ጓዟን ሁሉ ጠቅልላ ኢስት ሊን ገባች " ሚስተር ዲል አድራጎቷ የማይባ መሆኑን
ሊያስረዳት ቢሞክርም አልተቀበለችውም
ሚስተር ካርላይልና ሚስቱ በተጋቡ በአንድ ወራቸው ዓርብ ቀን ማታ ወደ
ቤታቸው ተመለሱ " መምጣታቸው አስቀድሞ ታውቆ ስለ ነበር ሚስ ካርላይል ከበረንዳው ቁማ ስትጠብቅ አንድ የሚያምር ሠረገላ በአራት ፈረሶች እየተሳበ ዘለቀ።
ሚስ ካርላይል የሠረገላውን ማማርና ትልቅነት ዐይታ በንዴት ከንፈሯን መጠጠች " ጠቆር ያለ ደስ የሚል የሐር ቀሚስ ለብሳ አዲስ ባርኔጣ ደፍታ ነበር » በአንድ ወር ውስጥ ቁጣዋ በረዶላታል የሚሻለው የሚቻላትን ሁሉ አድርጋ ሙሽሮቹን በደስታ መቀበል መሆኑን አስባና አምና ተዘጋጅታ ጠበቀቻቸው ሚስተር ካርላይል ከሳቤላ ጋር ሆኖ ደረጃዎቹን ወጣ "
“ መጥተሻል እንዴ ኮርነሊያ ? እሰይ ጎሽ ! እንደ ምን ሰነበትሽ ሳቤላ .. እኅቴ ናት ” ብሎ አስተዋወቃት
ሳቤላ እጅዋን ስትዘረጋላት ኮርነሊያ መልካም ፈዷ ሆኖ የጣቶቿን ጫፍ ነካ አደረገችላትና
“ደኅና ነሽ እመቤት ? '' አለቻት በሚቆረቁር ድምፅ
ሚስተር ካርላይል አንድ ላይ ተዋቸውና ከሠረገላው ዕቃ እንዳይቀር ለመቆጣጠር ወጣ ሚስ ካርላይል ወደ ሳሎን ገብታ ሳቤላን '' በይ እንግዲህ እመቤት. .ከፎቅ ወጥተሽ ከራት በፊት የመንገድ ልብስሽን ብትቀይሪው አይሻልም? አለቻት"
ኣመሰግናለሁ፤ ወዶ ክፍሌ እሔዳለሁ ራት ግን አያስፈልገኝም " እመንገድ በልተናል ”
ታዲያ ምን ብትቀምሺ ይሻልሻል ? ” አለች ሚስ ካርላይል
“ ሻይ ባገኝ ከሆነማ » በጣም አምሮኛል "
“ ሻይ ? ” አለች ካርላይል በመገረም “ ሻይ አሁን ! የፈላ ውሀ መኖሩንም አላውቅም ከሌሊቱ አምስት ሰዓት ላይ ሻይ ከጠጣሽ የአንዲት ቅፅበት እንኳን ዕንቅልፍ ሳታገኝ ይነጋል ”
" አዬ .. እንግዲያውስ ግድ የለም ይቅርብኝ » አስፈላጊነቱም እስከዚህ አይደለምና ባላስቸግር ይሻላል " ” ከመተላለፊያው ላይ ከማርቨል ጋር ፊት ለፊት ተጋጠሙ " ምንም ቃል ሳይለዋወጡ ተፋጠጡ " ማርቨል አለባበስ ዐዋቂ ነበረች አሁንም ባለ አምስት ደረጃ ቀሚስ አጥልቃ ዐይነርግቧን አድርጋ ዣንጥላዋን ይዛ ሽክ ብላ አምሮባት ነበር " ይህ ሲሆን ሳቤላ ቬን ከተቀመጠችበት እየተንሰቀሰቀች ዕንባዋን ታወርደው ጀመር ሆድ ባሳት ወደ ቤቷ ወደ ኢስት ሊን የተመለሰች አልመስላት አለ " ሚስተር ካርላይል ገባና ሁኔታዋን ተመለከተ "
“ ሳቤላ !” አላት ነግሩ ገርሞት ወደ እሷ አየተጠጋ “የኔ ፍቅር"
ምን ነካሽ?”
“ ደከመኝ መሰለኝ ” አለችው ዝግ ብላ ወደዚህ ቤት ተመልሶ መምጣቱ አባባን አስታወሰኝ የትኛው እንዶፈደሆነ አላውቀውም አሁንስ ወደ መኝታዬ ብሔድ ደስ ይለኝ ነበር።
ሚስተር ካርላይልም አላወቀውም ሚስ ካርላይል መጣችና እዚያ
ከቤተ መጻሕፍቱ ጐን ያሉት ምርጥ ክፍሎች ናቸው" እኔ ልውስዳት ? ” አለች "
ሚስተር ካርላይል ግን ራሱ መሔድን መረጠና ለሳቤላ እጁን ዘረጋላት " እሷም በሚስ ካርላይል ፊት ስታልፍ ፊቷን በዐይነ ርግቧ ጋረደች
ሲገቡ ቀንዲሎች አልተለኮሱም ክፍሉ ይቀፋል ይቀዘቅዛል
“ነገሩ ሁሉ እንዶ ተዘበራረቀ ነውሳ? የተደረገ ዝግጅት የለም አለ ሚስተር ካርላይል “ አሽከሮቼ የጻፍኩላቸው ደብዳቤ በደንብ ስለ አልገባቸው ነገ ማታ የምንመጣ መስሏቸው ነው " "
“ አርኪባልድ ” አለች ሳቤላ የራስ መሸፈኛዋን ያወለቀች በጣም ድክም ብሎኛል ደግሞ ምንም ደስ አላለኝም እንግዲህ ወደ ሳሎን ባልወርድና ልብሴን አወላልቄ ብተኛስ ? ”
ቀና ብሎ አያትና ፈግ አለ ባልወርድሳ አልሽ? ከገዛ ቤትሽ መመለስሺን ረሳሺው ? እንዳፈቀደሽ እንጂ የደስታ ቤት እንደሚሆንልሽ አምናለሁ ..የኔ
ፍቅር እንዲሆንልሽም የምችለውን ሁሉ አደርጋለሁ ” አላት ።
ከሱ ላይ ድግፍ ብላ ጩኻ ስትንሰቀለቅ ብስጭቷን ብትክትክ ማለቷን በትዕግሥት ችሎ እያባበለ ፡ ቀና ብሎ የሚያየው ፊቷን እየሳመ ያረጋጋትና ያጽናናት
ጀመር የሱ ፍላጐት ይች ከእጅ የባችውን ውብ አበባ ተንከባክቦ ለመያዝ ነበር ነገር ግን ራሱን ከእኅቱ የበላይነት ማላቀቅ ካልቻለ ዓላማው ግቡን እንዳይስት ሊያ
ሠጋው ይችላል ሳቤላ ባልዋን እንደምታፈቅረው በደንብ ብታውቅም በደግነቱና ባለውለታዋ በመሆኑ ለማፍቀር እንድትበቃም ትመኝ ነበር ።
“ ምን ትቀምሽ ... ሳቤላ ? ” አላት ሚስተር ካርላይል “ ሻይ ይምጣልሽ ?
“ተወው ... አመስግናለሁ ” አለችው የሚስ ካርላይልን መልስ በማስታወስ"
“ የለም አንድ ነገር መቅመስ አለብሽ » ከሠረገላው ውስጥ ሳለን የምጠጣው ነገር ባገኘሁ ስትይ ነበር "
“ውሃ ይበቃኛል ይሻለኛል ማለቴ ነው እሱንም ማርቨል ትሰጠኛለች''
ሚስተር ካርላይል ወጥቶ ሲሔድ የሳቤላ ደንገጡር አንጀቷ እርር ብሎ ተናዳ ለምቦጯን ጥላ ምላሷ እየተንቀጠቀጠ የእመቤቷን ልብስ አወለቀችላት "
የጋብቻዉ ዕለት የሚንከባከብ ከፍተኛ ማዕረግ ያለው የወንድ ሎሌ ባለመኖሩ ከዚያ ቀን ጀምሮ ንዴቷ ሲጠራቀም ሰንብቷል " ያለፈው ቅሬታ እንዳይበቃት
ከቤት ብትመጣ ደግሞ እሷ እንደምታውቀው እንደ ታላላቅ መኳንንት ቤት የሠለጠኑ
የልፍኝ አሽከሮች የቤት አዛዥና የምግብ አሳላፊዎች አለመኖራቸውን ስታውቅ የባሰውን ተናደዶች " በተጨማሪ ከሚስ ካርላይል ጋር ተጋጨች » ማርቨል የእመቤቷን ልብስ የያዘ አንድ አነስተኛ ጥቅል ተሸክሞ የሚያስገባ አሽከር ቀብረር እያለች ስትጣራ ሚስ ካርላይል አገኘቻትና ራሷ ተሸክማ እንድታስባው ነገረቻት "ማርቭል የባሰውን እሳት ሆነች ሴትዬዋ ማን መሆንዋን አስቀድማ በማወቋ ተወቻት እንጂ
ማርቨል ዕቃውን አንሥታ ራሷ ላይ ልትወረውረው ቃጥቷት ነበር "
ሌላስ ምን ቀረ እሜቴ ? - አለች ማርቨል ዕቃውን አስገባችና "
ምንም አለች ሳቤላ “ልትሔጂ ትችያለሽ "
ሳቤላ የቤት ውስጥ የሙቀት ልብሷን ደራርባ የሙቀት ጫማ አድርጋ መጽሐፍ ይዛ ተቀመጠች ማርቨል እጅ ነሥታ ወደ መኝታዋ ሔደች » ሚስተር ካርላይል
ከሳቤላ ዘንድ ወጥቶ እኅቱን ፍለጋ ሔዶ። ራት የምትበላ እሷው ብቻ መሆኗን ስታውቅ በተለይ የዛንለት ቀደም ብላ መብላት አሰኛት " ሚስተር ካርላይል ሲገባ አንድ
የዶሮ ክንፍ ይዛ ስትግተግት ሚስ ካርላይልን አገኛት።
“ኮርነሊያ ”አላት " “ እኔ ነገሩ ሁሉ አልገባኝም " የኔን አሽከሮች አላየኋቸውም " ያንቺን ግን አያቸዋለሁ " የኔዎቹ የት ነው ያሉት ? ''
"ሔዱ ! ”
ሔዱ ? ለምን ? በጣም ጥሩ አሽhሮች መስለውኝ ነበር ።"
“ እንዴታ ! ለጥረታቸውስ ወግ አለው ! እንዴ በውድ ልብሶች የሚሽቀረቀሩ ስለቤት አያያዝ ምንም ግድ የሌላቸው ደንታ ቢሶች ኦሽከር ብሎ ዝም ነበሩ”
ትላለህ ? ዳሩ አንተ ምኑን ታውቀዋለህ? እኔስ ትርፍ ስለሆኑ አሰናበትኳቸው ወደ ፊትም ቢሆን አርኪባልድ . . . በቤት ውስጥ ጣጣ እንዳትገባ " በል አሁን ከሱ ምላስ ሥጋ ቁረጥልኝ አለችው "
“ ግን ምን አጠፉ ? ” አላት ያዘዘችውን ሥጋ እየቆረጠላት "
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
አንድ ጊዜ ከተናገረች የማትመለሰው ሚስ ካርላይል ፥ ቤቷን ለቃ ሚስተር
ካርላይል የቀጠራቸውን ሠራተኞች አሰናብታ ፒተርንና ሁለት ሠራተኞቿን ይዛ
ጓዟን ሁሉ ጠቅልላ ኢስት ሊን ገባች " ሚስተር ዲል አድራጎቷ የማይባ መሆኑን
ሊያስረዳት ቢሞክርም አልተቀበለችውም
ሚስተር ካርላይልና ሚስቱ በተጋቡ በአንድ ወራቸው ዓርብ ቀን ማታ ወደ
ቤታቸው ተመለሱ " መምጣታቸው አስቀድሞ ታውቆ ስለ ነበር ሚስ ካርላይል ከበረንዳው ቁማ ስትጠብቅ አንድ የሚያምር ሠረገላ በአራት ፈረሶች እየተሳበ ዘለቀ።
ሚስ ካርላይል የሠረገላውን ማማርና ትልቅነት ዐይታ በንዴት ከንፈሯን መጠጠች " ጠቆር ያለ ደስ የሚል የሐር ቀሚስ ለብሳ አዲስ ባርኔጣ ደፍታ ነበር » በአንድ ወር ውስጥ ቁጣዋ በረዶላታል የሚሻለው የሚቻላትን ሁሉ አድርጋ ሙሽሮቹን በደስታ መቀበል መሆኑን አስባና አምና ተዘጋጅታ ጠበቀቻቸው ሚስተር ካርላይል ከሳቤላ ጋር ሆኖ ደረጃዎቹን ወጣ "
“ መጥተሻል እንዴ ኮርነሊያ ? እሰይ ጎሽ ! እንደ ምን ሰነበትሽ ሳቤላ .. እኅቴ ናት ” ብሎ አስተዋወቃት
ሳቤላ እጅዋን ስትዘረጋላት ኮርነሊያ መልካም ፈዷ ሆኖ የጣቶቿን ጫፍ ነካ አደረገችላትና
“ደኅና ነሽ እመቤት ? '' አለቻት በሚቆረቁር ድምፅ
ሚስተር ካርላይል አንድ ላይ ተዋቸውና ከሠረገላው ዕቃ እንዳይቀር ለመቆጣጠር ወጣ ሚስ ካርላይል ወደ ሳሎን ገብታ ሳቤላን '' በይ እንግዲህ እመቤት. .ከፎቅ ወጥተሽ ከራት በፊት የመንገድ ልብስሽን ብትቀይሪው አይሻልም? አለቻት"
ኣመሰግናለሁ፤ ወዶ ክፍሌ እሔዳለሁ ራት ግን አያስፈልገኝም " እመንገድ በልተናል ”
ታዲያ ምን ብትቀምሺ ይሻልሻል ? ” አለች ሚስ ካርላይል
“ ሻይ ባገኝ ከሆነማ » በጣም አምሮኛል "
“ ሻይ ? ” አለች ካርላይል በመገረም “ ሻይ አሁን ! የፈላ ውሀ መኖሩንም አላውቅም ከሌሊቱ አምስት ሰዓት ላይ ሻይ ከጠጣሽ የአንዲት ቅፅበት እንኳን ዕንቅልፍ ሳታገኝ ይነጋል ”
" አዬ .. እንግዲያውስ ግድ የለም ይቅርብኝ » አስፈላጊነቱም እስከዚህ አይደለምና ባላስቸግር ይሻላል " ” ከመተላለፊያው ላይ ከማርቨል ጋር ፊት ለፊት ተጋጠሙ " ምንም ቃል ሳይለዋወጡ ተፋጠጡ " ማርቨል አለባበስ ዐዋቂ ነበረች አሁንም ባለ አምስት ደረጃ ቀሚስ አጥልቃ ዐይነርግቧን አድርጋ ዣንጥላዋን ይዛ ሽክ ብላ አምሮባት ነበር " ይህ ሲሆን ሳቤላ ቬን ከተቀመጠችበት እየተንሰቀሰቀች ዕንባዋን ታወርደው ጀመር ሆድ ባሳት ወደ ቤቷ ወደ ኢስት ሊን የተመለሰች አልመስላት አለ " ሚስተር ካርላይል ገባና ሁኔታዋን ተመለከተ "
“ ሳቤላ !” አላት ነግሩ ገርሞት ወደ እሷ አየተጠጋ “የኔ ፍቅር"
ምን ነካሽ?”
“ ደከመኝ መሰለኝ ” አለችው ዝግ ብላ ወደዚህ ቤት ተመልሶ መምጣቱ አባባን አስታወሰኝ የትኛው እንዶፈደሆነ አላውቀውም አሁንስ ወደ መኝታዬ ብሔድ ደስ ይለኝ ነበር።
ሚስተር ካርላይልም አላወቀውም ሚስ ካርላይል መጣችና እዚያ
ከቤተ መጻሕፍቱ ጐን ያሉት ምርጥ ክፍሎች ናቸው" እኔ ልውስዳት ? ” አለች "
ሚስተር ካርላይል ግን ራሱ መሔድን መረጠና ለሳቤላ እጁን ዘረጋላት " እሷም በሚስ ካርላይል ፊት ስታልፍ ፊቷን በዐይነ ርግቧ ጋረደች
ሲገቡ ቀንዲሎች አልተለኮሱም ክፍሉ ይቀፋል ይቀዘቅዛል
“ነገሩ ሁሉ እንዶ ተዘበራረቀ ነውሳ? የተደረገ ዝግጅት የለም አለ ሚስተር ካርላይል “ አሽከሮቼ የጻፍኩላቸው ደብዳቤ በደንብ ስለ አልገባቸው ነገ ማታ የምንመጣ መስሏቸው ነው " "
“ አርኪባልድ ” አለች ሳቤላ የራስ መሸፈኛዋን ያወለቀች በጣም ድክም ብሎኛል ደግሞ ምንም ደስ አላለኝም እንግዲህ ወደ ሳሎን ባልወርድና ልብሴን አወላልቄ ብተኛስ ? ”
ቀና ብሎ አያትና ፈግ አለ ባልወርድሳ አልሽ? ከገዛ ቤትሽ መመለስሺን ረሳሺው ? እንዳፈቀደሽ እንጂ የደስታ ቤት እንደሚሆንልሽ አምናለሁ ..የኔ
ፍቅር እንዲሆንልሽም የምችለውን ሁሉ አደርጋለሁ ” አላት ።
ከሱ ላይ ድግፍ ብላ ጩኻ ስትንሰቀለቅ ብስጭቷን ብትክትክ ማለቷን በትዕግሥት ችሎ እያባበለ ፡ ቀና ብሎ የሚያየው ፊቷን እየሳመ ያረጋጋትና ያጽናናት
ጀመር የሱ ፍላጐት ይች ከእጅ የባችውን ውብ አበባ ተንከባክቦ ለመያዝ ነበር ነገር ግን ራሱን ከእኅቱ የበላይነት ማላቀቅ ካልቻለ ዓላማው ግቡን እንዳይስት ሊያ
ሠጋው ይችላል ሳቤላ ባልዋን እንደምታፈቅረው በደንብ ብታውቅም በደግነቱና ባለውለታዋ በመሆኑ ለማፍቀር እንድትበቃም ትመኝ ነበር ።
“ ምን ትቀምሽ ... ሳቤላ ? ” አላት ሚስተር ካርላይል “ ሻይ ይምጣልሽ ?
“ተወው ... አመስግናለሁ ” አለችው የሚስ ካርላይልን መልስ በማስታወስ"
“ የለም አንድ ነገር መቅመስ አለብሽ » ከሠረገላው ውስጥ ሳለን የምጠጣው ነገር ባገኘሁ ስትይ ነበር "
“ውሃ ይበቃኛል ይሻለኛል ማለቴ ነው እሱንም ማርቨል ትሰጠኛለች''
ሚስተር ካርላይል ወጥቶ ሲሔድ የሳቤላ ደንገጡር አንጀቷ እርር ብሎ ተናዳ ለምቦጯን ጥላ ምላሷ እየተንቀጠቀጠ የእመቤቷን ልብስ አወለቀችላት "
የጋብቻዉ ዕለት የሚንከባከብ ከፍተኛ ማዕረግ ያለው የወንድ ሎሌ ባለመኖሩ ከዚያ ቀን ጀምሮ ንዴቷ ሲጠራቀም ሰንብቷል " ያለፈው ቅሬታ እንዳይበቃት
ከቤት ብትመጣ ደግሞ እሷ እንደምታውቀው እንደ ታላላቅ መኳንንት ቤት የሠለጠኑ
የልፍኝ አሽከሮች የቤት አዛዥና የምግብ አሳላፊዎች አለመኖራቸውን ስታውቅ የባሰውን ተናደዶች " በተጨማሪ ከሚስ ካርላይል ጋር ተጋጨች » ማርቨል የእመቤቷን ልብስ የያዘ አንድ አነስተኛ ጥቅል ተሸክሞ የሚያስገባ አሽከር ቀብረር እያለች ስትጣራ ሚስ ካርላይል አገኘቻትና ራሷ ተሸክማ እንድታስባው ነገረቻት "ማርቭል የባሰውን እሳት ሆነች ሴትዬዋ ማን መሆንዋን አስቀድማ በማወቋ ተወቻት እንጂ
ማርቨል ዕቃውን አንሥታ ራሷ ላይ ልትወረውረው ቃጥቷት ነበር "
ሌላስ ምን ቀረ እሜቴ ? - አለች ማርቨል ዕቃውን አስገባችና "
ምንም አለች ሳቤላ “ልትሔጂ ትችያለሽ "
ሳቤላ የቤት ውስጥ የሙቀት ልብሷን ደራርባ የሙቀት ጫማ አድርጋ መጽሐፍ ይዛ ተቀመጠች ማርቨል እጅ ነሥታ ወደ መኝታዋ ሔደች » ሚስተር ካርላይል
ከሳቤላ ዘንድ ወጥቶ እኅቱን ፍለጋ ሔዶ። ራት የምትበላ እሷው ብቻ መሆኗን ስታውቅ በተለይ የዛንለት ቀደም ብላ መብላት አሰኛት " ሚስተር ካርላይል ሲገባ አንድ
የዶሮ ክንፍ ይዛ ስትግተግት ሚስ ካርላይልን አገኛት።
“ኮርነሊያ ”አላት " “ እኔ ነገሩ ሁሉ አልገባኝም " የኔን አሽከሮች አላየኋቸውም " ያንቺን ግን አያቸዋለሁ " የኔዎቹ የት ነው ያሉት ? ''
"ሔዱ ! ”
ሔዱ ? ለምን ? በጣም ጥሩ አሽhሮች መስለውኝ ነበር ።"
“ እንዴታ ! ለጥረታቸውስ ወግ አለው ! እንዴ በውድ ልብሶች የሚሽቀረቀሩ ስለቤት አያያዝ ምንም ግድ የሌላቸው ደንታ ቢሶች ኦሽከር ብሎ ዝም ነበሩ”
ትላለህ ? ዳሩ አንተ ምኑን ታውቀዋለህ? እኔስ ትርፍ ስለሆኑ አሰናበትኳቸው ወደ ፊትም ቢሆን አርኪባልድ . . . በቤት ውስጥ ጣጣ እንዳትገባ " በል አሁን ከሱ ምላስ ሥጋ ቁረጥልኝ አለችው "
“ ግን ምን አጠፉ ? ” አላት ያዘዘችውን ሥጋ እየቆረጠላት "
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
.....የሚያንቀጠቅጥ ሀሳብ መጣብኝı ኬሪ ወይም ኮሪ የሆነ ነገር ሊሰብሩ ቢችሉ ቅጣቱ ምን ሊሆን እንደሚችል!.
እናታችን ቃሏን በመጠበቅ መንትዮቹ ከተኙ በኋላ ወደ ክፍላችን መጣች::በጣም ቆንጆ ከመሆኗ የተነሳ ልቤ በኩራት፣ በአድናቆትና በትንሹ በቅናት
አበጠ የለበሰችው ልብስ ጆሮዎቿ ላይ በረጅሙ ከተንጠለጠሉትና ከሚያበሩት የአልማዝና ኤሜራልድ የጆሮ ጌጦች ጋር አብሮ ያንፀባርቃል። ጠረኗ
በምስራቅ ያለ በጨረቃ ብርሀን የደመቀ ሽቶ ሽቶ የሚሽት የአትክልት ስፍራን አስታወሰኝ፡፡ ክሪስ ፍዝዝ ብሎ እሷ ላይ ማፍጠጡ ምንም አያስገርምም::
በከባዱ ተነፈስኩ፡ አምላኬ እባክህ አንድ ቀን… እንደ እሷ እንድመስልና ወንዶች እጅግ የሚያደንቁት ገባ ያለ ወገብ እንዲኖረኝ አድርግ።
ስትራመድ ግራና ቀኝ ያለው የልብሷ ዘርፍ እንደ ክንፍ ከፍና ዝቅ እያለ ለመጀመሪያ ጊዜ ከዚያ ደብዛዛ ብርሃን ካለው ክፍል ወጣን፡ የእናታችንን ኮቴ
እየተከተልን በሰሜን አቅጣጫ ባሉት ጨለማማ ሰፊ አዳራሾች በኩል መሄድ ጀመርን፡ “ልጅ እያለሁ ትልልቅ ሰዎች ሲደንሱ ለማየት ወላጆቼ ሳያውቁ
የምደበቅበት ቦታ ነበር” ስትል አንሾካሾከች: “ለሁለታችሁ ይጠባችኋል። ግን ተደብቃችሁ ልታዩ የምትችሉበት ቦታ ያ ብቻ ነው: በምንም አይነት ሁኔታ ቢሆን አንድም ድምፅ እንደማታሰሙ እንደገና ቃል እንድትገቡልኝ
እፈልጋለሁ እንቅልፋችሁ ከመጣ ቀስ ብላችሁ ሳትታዩ ወደ ክፍላችሁ ሂዱ እንዴት እዚያ እንደምትደርሱ አስታውሱ:” መንትዮቹ ድንገት ከእንቅልቻቸው ነቅተው ፍርሀት እንዳይስማቸው ከአንድ ሰዓት የበለጠ
እንዳንቆይ አስጠነቀቀችን፡ ምናልባትም እኛን ፍለጋ ሊወጡና አዳራሹ ውስጥ ወዲያ ወዲህ ሊሉ ይችሉ ይሆናል። እንደዚያ ካደረጉ ምን ሊፈጠር
እንደሚችል እግዚአብሔር ብቻ ነው የሚያውቀው።
በሚስጥር ከስሩ በሮች ያሉት ትልቅ ጠረጴዛ ስር ገባን፡ የማይመችና በጣም ጠባብ ነው፡ ግን ከጀርባው ባለው መስኮት መስል ክፍተት በደንብ መመልከት
እንችላለን፡
እናታችን በፀጥታ ሹልክ አለች።
እኛ ካለንበት በታች ራቅ ብሎ በሚያምር ሁኔታ በሻማ ብርሀን ያጌጠ ክፍል ተመለከትን፡ በህይወቴ እንደዚህ የበዙ ሻማዎች አንድ ላይ ሲበሩ አይቼ
አላውቅም! የሻማዎቹ ሽታ እንዲሁም ብርሃኑ ሴቶቹ ያደረጓቸው ጌጣጌጦች
ላይ ሲያርፍ ያለው ማንፀባረቅ ምትሀታዊና ፊልም ላይ ሲንዴሬላና ልዑሉ የደነሱበትን ቦታ ይመስል ነበር።
በመቶ የሚቆጠሩ እንደ ሀብታም የለበሱ ሰዎች እየሳቁና እያወሩ ነው: ጥግ ላይ ደግሞ ለማመን የሚከብድ የገና ዛፍ ተቀምጧል እጅግ በጣም ትልቅ ሲሆን ባለቀለም ጌጣጌጦች ተደርገውበታል፡ ላዩ ላይ የተደረጉት በመቶዎች
የሚቆጠሩ ወርቃማ መብራቶች አይን ያፈዛሉ በዳንሱ ክፍል ውስጥ ወጣ ገባ እያሉ በትሪዎች ላይ ምግብ ይዘው ትልቅ ጠረጴዛ ላይ ይደረድራሉ፡ ሁሉም
ነገር ውብ፣ የሚያምርና የሚያስደንቅ ነበር ... እናም ከተቆለፈ በር ውጪ ደስተኛ ህይወት መኖሩን ማወቅ ጥሩ ነው።
"ካቲ…” ክሪስ በጆሮዬ እያንሾካሾከ “ከዚያ ጥርት ካለው መጠጥ አንድ ጊዜ ፉት ለማለት ነፍሴን ለሰይጣን እሸጣለሁ” አለ።
የእኔም ሀሳብ ነበር ...
እንደዛሬ ርሀብ፣ ጥማትና መከልከል ተሰምቶኝ አያውቅም: ሆኖም ግን ሁለታችንም ታላቅ ሀብት ሊገዛውና ሊያስገኘው በሚችለው ድምቀት ተገረምን፡ ጥንዶች የሚደንሱበት ወለል በሰም ተወልውሎ እንደ መስተዋት
ያንፀባርቃል፡ ትልልቅ ወርቃማ ፍሬሞች ያሏቸው በክፍሉ ውስጥ ያሉት መስታዎቶች የዳንሰኞቹን ምስል ሲያንፀባርቁ ሲታይ የትኛው እውነተኛ ምስል እንደሆነ እንኳ ለመለየት ያስቸግር ነበር።
እኔና ክሪስ ወጣትና ቆንጆ በሆኑት ጥንዶች ላይ አፍጥጠን ነበር፡ ስለ
ልብሳቸው፣ የፀጉር አሰራራቸውና ስላላቸው ግንኙነት በመገመት አስተያየት እንሰጥ ነበር ከሁሉም በላይ ግን የትኩረት ማዕከል የነበረችውን እናታችንን እያየን ነበር፡ በአብዛኛው ከአንድ ረጅም፣መልከመልካም፣ ጥቁር ፀጉርና ረጅም ፂም ካለው ሰው ጋር እየደነሰች ነበር: የምትበላውንና የምትጠጣውንም
ያመጣላት እሱ ነበር ምግቡን ይዛ ሶፋ ላይ ተቀምጠው መብላት ጀመሩ።በጣም ተጠጋግተው እንደተቀመጡ አሰብኩ። በፍጥነት አይኖቼን ከእነርሱ መልሼ ከትልልቆቹ ጠረጴዛዎች ኀላ ወደ ቆሙት ሶስት ምግብ አብሳዮች
አተኮርኩ አሁንም ምግብ እየሰሩ ነው የምግቦቹ ሽታ ወደኛ ደርሶ የምራቅ እጢዎቻችንን በኃይል እንዲሰሩ አደረጋቸው፡
ከጊዜ ወደ ጊዜ እናታችን ከዚያ ሰው ጋር ትሰወራለች የት ነው የሚሄዱት?ምንድነው የሚሰሩት? እየተሳሳሙ ነው? ፍቅር ይዟታል? ካለንበት ከዚያ ርቀት ላይ ሆነን እንኳ ሰውየው በእናታችን እንደተማረከ መናገር እችላለሁ:
አይኑን ከፊቷ ላይ መንቀል አልቻለም፧ እጆቹም እሷን ከመንካት መከልከል
አልቻለም::
ቀስ ባለ ሙዚቃ ሲደንሱ፣ ጉንጯ ጉንጩን እስኪነካ ድረስ አስጠግቶ ይዟት ነበር ዳንሱን ሲጨርሱ እጁን ትከሻዎቿ ወይም ወገቧ ላይ ያደርጋል። አንድ ጊዜ እንደውም ጡቷን እስከ መንካት ሳይቀር ደፍሯል።
አሁን ይህንን መልከ መልካም ፊቱን በጥፊ ትለዋለች ብዬ አሰብኩ። ምክንያቱም እኔ ብሆን እንደዚያ ነበር የማደርገው: እሷ ግን ዞር አለችና ሳቀች ከዚያ ገፋ አደረገችውና በአደባባይ እንደዚያ እንዳያደርግ ማስጠንቀቂያ
ሊሆን ይችላል የሆነ ነገር አለችው: እሱም ፈገግ ብሎ እጇን ያዘና ወደ ከንፈሩ አስጠጋው ከዚያ አይኖቻቸው ረጅምና ትርጉም ያለው እይታ ተለዋወጡ:
ወይም እንደዚያ እንደሆነ አሰብኩ
“ክሪስ እናታችንን ከዚያ ሰው ጋር አየሀት?”
“አዎ አይቻቸዋለሁ ልክ እንደ አባታችን ረጅም ነው።”
“አሁን ያደረገውን አይተሀል?”
“ልክ እንደሌሎቹ እየበሉና እየጠጡ፣ እየሳቁና እያወሩ እንዲሁም እየደነሱ ነው: አስቢው ካቲ… እናታችን ያንን ሁሉ ገንዘብ ስትወርስ እንደዚህ አይነት
ድግሶች ለገና እና ለልደቶቻችን እንደግሳለን፡ አሁን ያየናቸውን እንግዶች ወደፊት እናገኛቸው ይሆናል። ግላድስተን ላሉት ጓደኞቻችን የግብዣ ወረቀት
እንልክላቸዋለን፡ አቤት! የወረስነውን ሲመለከቱ በጣም ነው የሚገረሙት"አለ፡፡
ወዲያው አያታችን ወደ ዳንስ ክፍሉ ገባች: ወደ ግራም ወደ ቀኝም አልተመለከተችም ለማንምም ፈገግታ አላሳየችም
ቀሚሷ ግራጫ አልነበረም።
እኛን ለማስደነቅ ያ ብቻውን በቂ ነበር ፀጉሯ በሚገባ ተሰርቷል። አንገቷ፣ጆሮዎቿ ክንዶቿና ጣቶቿ በአልማዝና በሩቢ ጌጣጌጦች አሸብርቀዋል።ያቺ አስደናቂ ንጉሳዊ ግርማ ሞገስ ያላት ሴት በየቀኑ የምትጎበኘን አስፈሪ
አያታችን መሆኗን ማን ያምናል?
ፈቃደኛ ባንሆንም አሁንም አሁንም በሹክሹክታ “እጅግ አስደናቂ ሆናለች '' ብለን አመንን
“አዎ በጣም አስገራሚ”
የዚህን ጊዜ ነው የማናውቀውን ወንድ አያታችንን ያየነው!
ወደ ታች መመልከቴ ትንፋሼን ቀጥ አደረገው ያየሁት ሰው በጣም አባቴን ይመስላል አባታችን እስከሚያረጅ ድረስ በህይወት ቢኖር ኖሮ ይህን ሰው
እንደሚመስል ማየት ይቻላል በሚገፋ ወንበር ላይ ተቀምጦ ነበር። ቶክሲዶ ለብሷል። ሸሚዙ ጥቁር ቁልፍ ያለበት ነጭ ሸሚዝ ነበር፡ የሳሳው ወርቃማ ፀጉሩ ነጭ ወደ መሆን ሄዶ፣ በብርሃን ሲታይ ብርማ መስሎ ያንፀባርቃል።
ቆዳው ደግሞ የተደበቅንበት ቦታ ላይ ሆነን በሩቅ እያየነው ስለሆነ ሊሆን ይችላል፣ አልተጨማደደም: እኔና ክሪስ በመደንገጥና በመገረም አንድ ጊዜ ካየነው ጀምሮ አይኖችንን ወዴትም አላንቀሳቀስንም፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
.....የሚያንቀጠቅጥ ሀሳብ መጣብኝı ኬሪ ወይም ኮሪ የሆነ ነገር ሊሰብሩ ቢችሉ ቅጣቱ ምን ሊሆን እንደሚችል!.
እናታችን ቃሏን በመጠበቅ መንትዮቹ ከተኙ በኋላ ወደ ክፍላችን መጣች::በጣም ቆንጆ ከመሆኗ የተነሳ ልቤ በኩራት፣ በአድናቆትና በትንሹ በቅናት
አበጠ የለበሰችው ልብስ ጆሮዎቿ ላይ በረጅሙ ከተንጠለጠሉትና ከሚያበሩት የአልማዝና ኤሜራልድ የጆሮ ጌጦች ጋር አብሮ ያንፀባርቃል። ጠረኗ
በምስራቅ ያለ በጨረቃ ብርሀን የደመቀ ሽቶ ሽቶ የሚሽት የአትክልት ስፍራን አስታወሰኝ፡፡ ክሪስ ፍዝዝ ብሎ እሷ ላይ ማፍጠጡ ምንም አያስገርምም::
በከባዱ ተነፈስኩ፡ አምላኬ እባክህ አንድ ቀን… እንደ እሷ እንድመስልና ወንዶች እጅግ የሚያደንቁት ገባ ያለ ወገብ እንዲኖረኝ አድርግ።
ስትራመድ ግራና ቀኝ ያለው የልብሷ ዘርፍ እንደ ክንፍ ከፍና ዝቅ እያለ ለመጀመሪያ ጊዜ ከዚያ ደብዛዛ ብርሃን ካለው ክፍል ወጣን፡ የእናታችንን ኮቴ
እየተከተልን በሰሜን አቅጣጫ ባሉት ጨለማማ ሰፊ አዳራሾች በኩል መሄድ ጀመርን፡ “ልጅ እያለሁ ትልልቅ ሰዎች ሲደንሱ ለማየት ወላጆቼ ሳያውቁ
የምደበቅበት ቦታ ነበር” ስትል አንሾካሾከች: “ለሁለታችሁ ይጠባችኋል። ግን ተደብቃችሁ ልታዩ የምትችሉበት ቦታ ያ ብቻ ነው: በምንም አይነት ሁኔታ ቢሆን አንድም ድምፅ እንደማታሰሙ እንደገና ቃል እንድትገቡልኝ
እፈልጋለሁ እንቅልፋችሁ ከመጣ ቀስ ብላችሁ ሳትታዩ ወደ ክፍላችሁ ሂዱ እንዴት እዚያ እንደምትደርሱ አስታውሱ:” መንትዮቹ ድንገት ከእንቅልቻቸው ነቅተው ፍርሀት እንዳይስማቸው ከአንድ ሰዓት የበለጠ
እንዳንቆይ አስጠነቀቀችን፡ ምናልባትም እኛን ፍለጋ ሊወጡና አዳራሹ ውስጥ ወዲያ ወዲህ ሊሉ ይችሉ ይሆናል። እንደዚያ ካደረጉ ምን ሊፈጠር
እንደሚችል እግዚአብሔር ብቻ ነው የሚያውቀው።
በሚስጥር ከስሩ በሮች ያሉት ትልቅ ጠረጴዛ ስር ገባን፡ የማይመችና በጣም ጠባብ ነው፡ ግን ከጀርባው ባለው መስኮት መስል ክፍተት በደንብ መመልከት
እንችላለን፡
እናታችን በፀጥታ ሹልክ አለች።
እኛ ካለንበት በታች ራቅ ብሎ በሚያምር ሁኔታ በሻማ ብርሀን ያጌጠ ክፍል ተመለከትን፡ በህይወቴ እንደዚህ የበዙ ሻማዎች አንድ ላይ ሲበሩ አይቼ
አላውቅም! የሻማዎቹ ሽታ እንዲሁም ብርሃኑ ሴቶቹ ያደረጓቸው ጌጣጌጦች
ላይ ሲያርፍ ያለው ማንፀባረቅ ምትሀታዊና ፊልም ላይ ሲንዴሬላና ልዑሉ የደነሱበትን ቦታ ይመስል ነበር።
በመቶ የሚቆጠሩ እንደ ሀብታም የለበሱ ሰዎች እየሳቁና እያወሩ ነው: ጥግ ላይ ደግሞ ለማመን የሚከብድ የገና ዛፍ ተቀምጧል እጅግ በጣም ትልቅ ሲሆን ባለቀለም ጌጣጌጦች ተደርገውበታል፡ ላዩ ላይ የተደረጉት በመቶዎች
የሚቆጠሩ ወርቃማ መብራቶች አይን ያፈዛሉ በዳንሱ ክፍል ውስጥ ወጣ ገባ እያሉ በትሪዎች ላይ ምግብ ይዘው ትልቅ ጠረጴዛ ላይ ይደረድራሉ፡ ሁሉም
ነገር ውብ፣ የሚያምርና የሚያስደንቅ ነበር ... እናም ከተቆለፈ በር ውጪ ደስተኛ ህይወት መኖሩን ማወቅ ጥሩ ነው።
"ካቲ…” ክሪስ በጆሮዬ እያንሾካሾከ “ከዚያ ጥርት ካለው መጠጥ አንድ ጊዜ ፉት ለማለት ነፍሴን ለሰይጣን እሸጣለሁ” አለ።
የእኔም ሀሳብ ነበር ...
እንደዛሬ ርሀብ፣ ጥማትና መከልከል ተሰምቶኝ አያውቅም: ሆኖም ግን ሁለታችንም ታላቅ ሀብት ሊገዛውና ሊያስገኘው በሚችለው ድምቀት ተገረምን፡ ጥንዶች የሚደንሱበት ወለል በሰም ተወልውሎ እንደ መስተዋት
ያንፀባርቃል፡ ትልልቅ ወርቃማ ፍሬሞች ያሏቸው በክፍሉ ውስጥ ያሉት መስታዎቶች የዳንሰኞቹን ምስል ሲያንፀባርቁ ሲታይ የትኛው እውነተኛ ምስል እንደሆነ እንኳ ለመለየት ያስቸግር ነበር።
እኔና ክሪስ ወጣትና ቆንጆ በሆኑት ጥንዶች ላይ አፍጥጠን ነበር፡ ስለ
ልብሳቸው፣ የፀጉር አሰራራቸውና ስላላቸው ግንኙነት በመገመት አስተያየት እንሰጥ ነበር ከሁሉም በላይ ግን የትኩረት ማዕከል የነበረችውን እናታችንን እያየን ነበር፡ በአብዛኛው ከአንድ ረጅም፣መልከመልካም፣ ጥቁር ፀጉርና ረጅም ፂም ካለው ሰው ጋር እየደነሰች ነበር: የምትበላውንና የምትጠጣውንም
ያመጣላት እሱ ነበር ምግቡን ይዛ ሶፋ ላይ ተቀምጠው መብላት ጀመሩ።በጣም ተጠጋግተው እንደተቀመጡ አሰብኩ። በፍጥነት አይኖቼን ከእነርሱ መልሼ ከትልልቆቹ ጠረጴዛዎች ኀላ ወደ ቆሙት ሶስት ምግብ አብሳዮች
አተኮርኩ አሁንም ምግብ እየሰሩ ነው የምግቦቹ ሽታ ወደኛ ደርሶ የምራቅ እጢዎቻችንን በኃይል እንዲሰሩ አደረጋቸው፡
ከጊዜ ወደ ጊዜ እናታችን ከዚያ ሰው ጋር ትሰወራለች የት ነው የሚሄዱት?ምንድነው የሚሰሩት? እየተሳሳሙ ነው? ፍቅር ይዟታል? ካለንበት ከዚያ ርቀት ላይ ሆነን እንኳ ሰውየው በእናታችን እንደተማረከ መናገር እችላለሁ:
አይኑን ከፊቷ ላይ መንቀል አልቻለም፧ እጆቹም እሷን ከመንካት መከልከል
አልቻለም::
ቀስ ባለ ሙዚቃ ሲደንሱ፣ ጉንጯ ጉንጩን እስኪነካ ድረስ አስጠግቶ ይዟት ነበር ዳንሱን ሲጨርሱ እጁን ትከሻዎቿ ወይም ወገቧ ላይ ያደርጋል። አንድ ጊዜ እንደውም ጡቷን እስከ መንካት ሳይቀር ደፍሯል።
አሁን ይህንን መልከ መልካም ፊቱን በጥፊ ትለዋለች ብዬ አሰብኩ። ምክንያቱም እኔ ብሆን እንደዚያ ነበር የማደርገው: እሷ ግን ዞር አለችና ሳቀች ከዚያ ገፋ አደረገችውና በአደባባይ እንደዚያ እንዳያደርግ ማስጠንቀቂያ
ሊሆን ይችላል የሆነ ነገር አለችው: እሱም ፈገግ ብሎ እጇን ያዘና ወደ ከንፈሩ አስጠጋው ከዚያ አይኖቻቸው ረጅምና ትርጉም ያለው እይታ ተለዋወጡ:
ወይም እንደዚያ እንደሆነ አሰብኩ
“ክሪስ እናታችንን ከዚያ ሰው ጋር አየሀት?”
“አዎ አይቻቸዋለሁ ልክ እንደ አባታችን ረጅም ነው።”
“አሁን ያደረገውን አይተሀል?”
“ልክ እንደሌሎቹ እየበሉና እየጠጡ፣ እየሳቁና እያወሩ እንዲሁም እየደነሱ ነው: አስቢው ካቲ… እናታችን ያንን ሁሉ ገንዘብ ስትወርስ እንደዚህ አይነት
ድግሶች ለገና እና ለልደቶቻችን እንደግሳለን፡ አሁን ያየናቸውን እንግዶች ወደፊት እናገኛቸው ይሆናል። ግላድስተን ላሉት ጓደኞቻችን የግብዣ ወረቀት
እንልክላቸዋለን፡ አቤት! የወረስነውን ሲመለከቱ በጣም ነው የሚገረሙት"አለ፡፡
ወዲያው አያታችን ወደ ዳንስ ክፍሉ ገባች: ወደ ግራም ወደ ቀኝም አልተመለከተችም ለማንምም ፈገግታ አላሳየችም
ቀሚሷ ግራጫ አልነበረም።
እኛን ለማስደነቅ ያ ብቻውን በቂ ነበር ፀጉሯ በሚገባ ተሰርቷል። አንገቷ፣ጆሮዎቿ ክንዶቿና ጣቶቿ በአልማዝና በሩቢ ጌጣጌጦች አሸብርቀዋል።ያቺ አስደናቂ ንጉሳዊ ግርማ ሞገስ ያላት ሴት በየቀኑ የምትጎበኘን አስፈሪ
አያታችን መሆኗን ማን ያምናል?
ፈቃደኛ ባንሆንም አሁንም አሁንም በሹክሹክታ “እጅግ አስደናቂ ሆናለች '' ብለን አመንን
“አዎ በጣም አስገራሚ”
የዚህን ጊዜ ነው የማናውቀውን ወንድ አያታችንን ያየነው!
ወደ ታች መመልከቴ ትንፋሼን ቀጥ አደረገው ያየሁት ሰው በጣም አባቴን ይመስላል አባታችን እስከሚያረጅ ድረስ በህይወት ቢኖር ኖሮ ይህን ሰው
እንደሚመስል ማየት ይቻላል በሚገፋ ወንበር ላይ ተቀምጦ ነበር። ቶክሲዶ ለብሷል። ሸሚዙ ጥቁር ቁልፍ ያለበት ነጭ ሸሚዝ ነበር፡ የሳሳው ወርቃማ ፀጉሩ ነጭ ወደ መሆን ሄዶ፣ በብርሃን ሲታይ ብርማ መስሎ ያንፀባርቃል።
ቆዳው ደግሞ የተደበቅንበት ቦታ ላይ ሆነን በሩቅ እያየነው ስለሆነ ሊሆን ይችላል፣ አልተጨማደደም: እኔና ክሪስ በመደንገጥና በመገረም አንድ ጊዜ ካየነው ጀምሮ አይኖችንን ወዴትም አላንቀሳቀስንም፡
#ጠላፊዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
የበረራ መሃንዲሱ ኤዲ ዲከን የስማይ በራሪ ጀልባውን የሚያየው
ጥንቃቄ የሚፈልግ ነገር አድርጎ ነው፡፡ የአይሮፕላኑ መሳሪያዎች ገና በቅጡ
ያልዳበሩ መሆናቸውንና በአትላንቲክ ውቅያኖስ በምሽት በሚደረገው በረራ
ወቅት ያልተጠበቀ አደጋ ሊደርስ እንደሚችል ተሳፋሪዎቹ የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ያውቃል፡፡ ሆኖም ኤዲ የካፒቴኑ የመሾፈር ብቃት፣ የአይሮፕላኑ ሰራተኞች ከልብ መስራትና የአሜሪካ ኢንጂነሪንግ የደረሰበት ደረጃ ተዳምረው አይሮፕላኑን በሰላም አሜሪካ እንደሚያደርሱት ይተማመናል።
ይህ ጉዞም እስካሁን ካደረጋቸው ጉዞዎች ሁሉ አስፈሪ ሆኖበታል፡በተሳፋሪዎች ስም ዝርዝር ውስጥ ቶም ሉተር የሚባል ሰው መኖሩን አይቷል፡፡ ተሳፋሪዎቹ አንድ በአንድ አይሮፕላኑ ላይ ሲሳፈሩ ከእነዚህ ውስጥ ካሮል አንን ያገታት ቶም ሉተር የቱ ይሆን? አለ በሆዱ¨
አዕምሮውን ወጥሮ የያዘውን የካሮል አንን ጉዳይ ለጥቂት ጊዜም ቢሆን ትቶ አይሮፕላኑን ለበረራ ለማዘጋጀት ተነሳ፡፡ የአይሮፕላኑ የተለያዩ መሳሪያዎች የሚሰሩና የማይሰሩ መሆናቸውን መፈተሽ፣ አራቱን ግዙፍ ሞተሮች መቆጣጠር ከሚሰራቸው ስራዎች ውስጥ አንዳንዶቹ ናቸው፡ አይሮፕላኑ ተነስቶ በጥሩ ሁኔታ መብረር ከጀመረ በኋላ ብዙም የሚሰራው ነገር አይኖርም፡፡ በዚህ ጊዜ የአይሮፕላኑ ፍጥነትና
የሞተሮቹ ሙቀት መጠን
በትክክል መስራቱንና ነዳጁን መቆጣጠር
ይሆናል። ሆኖም አዕምሮው እንደገና ወደ ካሮል አን እየሄደበት ተቸገረ፡፡
ካሮል አን በሚቀጥሉት ሃያ አራት ሰዓት ውስጥ በእነዚህ አረመኔዎች እጅ በተለይም ከጠጡ ምን ሊደርስባት እንደሚችል አይታወቅም:
እነዚህ ሰዎች ምንድነው
ከእሱ የሚፈልጉት? የስራ ጓደኞቹ የተቸገረበትን ነገር እንዳያውቁበት መጠንቀቅ አለበት፡፡ ሁሉም ግዴታውን
ለመወጣት ተፍ ተፍ ስለሚል ላያውቁበት ይችላሉ፡ ካፒቴን ቤከርና ረዳት ካፒቴን ጆኒ ዶት የአይሮፕላኑ ጋቢና ውስጥ ተመቻችተው ተቀምጠዋል
ከተሳፋሪዎች ክፍል የሚመጣው ብርሃን ፓይለቶቹን እንዳያስቸግራቸው
ማታ ማታ ወፍራም መጋረጃ ይጋረዳል፡ ማፖችንና መሳሪያዎች በመጠቀም
አይሮፕላኑን ትክክለኛውን አቅጣጫ እንዲይዝ የሚያደርገው ናቪጌተሩ ጃክ
አሽፎርድ ማፑ ላይ አፍጥጧል፡
ይህን አይሮፕላን ከሌሎች አይሮፕላኖች የሚለየው አይሮፕላኑ መሬት
ሳይወርድ ዘይት የሚያፈስን የሞተር ክፍል ጥገናን የመሳሰሉ ቀላል የጥገና
ስራዎችን መስራት ማስቻሉ ነው፡፡ ቀጥሎ የሚገኘው ቦታ የሬዲዮ ኦፕሬተሩ
የቤን ቶምሰን ሲሆን ከእሱ ኋላ ደግሞ የኤዲ የስራ ቦታ ይገኛል።
ኤዲ ጀርባቸውን ለእሱ ሰጥተው በተመስጦ የሚሰሩ ጓደኖቹ የእሱን
ጭንቀትና ፍርሃት ባለማስተዋላቸው ተረጋጋ:: ለጊዜው ማንነቱ ያልታወቀው ሚስተር ሉተር እኔ ነኝ እንዲል ለማድረግ ፍላጎት አደረበት፡፡
በተሳፋሪዎች ክፍል መተላለፊያ መንጎራደድ ፈለገና ከመቀመጫው ተነስቶ ‹‹እስቲ አንድ ቼክ የማደርገው ነገር አለ›› ብሎ ለናቪጌተሩ ነገረና ደረጃውን
ወርዶ ሄደ፡፡ የሆነ ሰው ለምን ቼክ ማድረግ እንደፈለገ ቢጠይቀው ዝም ብሎ እንደሚያልፍ ወስኗል፡፡
ኤዲ በመተላለፊያው ላይ ቀስ ብሎ ተራመደ፡ ኒክና ዴቪ ለተሳፋሪዎች ምግብና መጠጥ እያደሉ ነው፡፡ ተሳፋሪዎቹ በተለያዩ ቋንቋዎች ያወራሉ፡፡
የተወሰኑ ሰዎች ካርታ ጨዋታ አጧጡፈዋል፡ ከተሳፋሪዎቹ መካከል ታዋቂ ሰዎች ቢያይም ሃሳቡ ስለተበታተነበት እነማን እንደሆኑ መለየት አልቻለም፡፡እያንዳንዱ ሰው ላይ ተራ በተራ ቢያፈጥም ማንም ሰው ‹ቶም ሉተር እኔ
ነኝ›› አላለውም፡፡ ማየት የፈለገውን ነገር እንደነገሩ አይቶ በሩን ሲዘጋ አንድ
አስራ አራት አመት የሚሆነው ልጅ የሚሰራውን በተመስጦ ሲመለከት አየና
ፈገግ አለ፡፡
የፓይለቶቹን ጋቢና ማየት ይቻላል?›› ሲል ጠየቀው ልጁ፡
‹‹ይቻላል›› አለ ኤዲ፡ በዚህ ሰዓት ማንም እንዲያስቸግረው ባይፈልግም ተሳፋሪውን በትህትና ማናገር አለበት፡
‹በጣም አመሰግናለሁ›› አለ ልጁ፡
‹‹ወደ መቀመጫህ ተመለስና ጥቂት ጊዜ ቆይቼ እጠራሃለሁ›› አለው
ልጁ በኤዲ መልስ ግራ ቢጋባም ራሱን በእሺታ ነቀነቀና ፈጠን ብሎ
ሄደ፡፡
ኤዲ በመተላለፊያው ላይ እየተንጎራደደ አንድ ሰው እንዲያናግረው ጠበቀ፡፡ የሚያናግረው ሰው አለመኖሩን ሲረዳ ሰውየው ሰው የማይኖርበትን
አጋጣሚ እየጠበቀ መሆኑን ገመተ፡ አስተናጋጁን ሉተር የተባለው ሰው የቱጋ እንደተቀመጠ መጠየቅ ይችላል፡፡ ነገር ግን ለምንህ ነው የምትጠይቀው?› ብሎ ቢለው ምን መልስ እንደሚሰጥ አያውቅም በዚህ ጊዜ የስራ ባልደረቦቹ በእሱ ላይ ምንም አይነት ጥርጣሬ እንዲያድርባቸ
የሚያደርግ ነገር ማድረግ የለበትም፡፡
ልጁ ከአባትና ከእናቱ ጋር ነው የተቀመጠው፡፡ ኤዲም ‹‹ማሙሽ አሁን ና›› ሲል ተጣራ፡ አባትና እናቱም በመቀበል ራሳቸውን ነቀነቁ። አንዲት ጸጉረ ረጅም ልጅ የልጁ እህት ሳትሆን አትቀርም ሞቅ ያለ ፈገግታ
ስትመግበው ልቡ ደንገጥ አለ፡፡ ልጅቷ ስትስቅ ታምራለች፡
‹‹ማነው ስምህ ማሙሽ?›› አለው፡
‹‹ፔርሲ ኦክሰንፎርድ›› አለ፡
‹‹እኔ ኤዲ ዲኪን እባላለሁ፡፡ የበረራ መሀንዲስ ነኝ፡፡ ሞተሮቹን በትክክል መስራታቸውን መከታተል ነው ስራዬ››
የመጨረሻው ደረጃ ላይ ደረሱ፡ ‹‹ይሄ ሁሉ ደውልና መሳሪያ ምን ያደርጋል?››
‹‹የሽክርክሪቱን ፍጥነት፣ የሞተሩን የሙቀት መጠን እና የነዳጁን ቅልቅል ይቆጣጠራል፡፡›› ለልጁ በይበልጥ እንዲገባው ‹‹እዚህ ወንበር ላይ
ቁጭ በል›› አለው፡ ፔርሲም ቁጭ አለ፡፡ ‹‹ይሄ ደውል የቁጥር ሁለት ሞተርን የሙቀት መጠን ያሳያል፡ አሁን ሙቀቱ ከፍ ብሏል፡ ትንሽ ማቀዝቀዝ ያስፈልጋል፡››
‹‹እንዴት ነው ይሄን የምታደርገው?››
‹‹እጀታውን ያዝና ትንሽ ወደታች ግፋው ይህን ያህል ይበቃል፡ አሁን ተጨማሪ አየር እየገባ ነው ከትንሽ ደቂቃ በኋላ የሙቀት መጠኑ ሲወርድ
ታያለህ፡፡ ፊዚክስ ተምረሃል?›› ሲል ጠየቀው ኤዲ፡፡
‹‹እኔ የምማረው ዘመናዊ ትምህርት ቤት ውስጥ አይደለም›› አለ ፔርሲ፣ ‹‹ትምህርት ቤቱ ላቲንና ግሪክ ቋንቋዎች ላይ ነው በይበልጥ ትኩረት የሚያደርገው፡፡ ሳይንስ ላይ እስከዚህም ነው፡፡››
‹‹ሌሎቹ የስራ ባልደረቦችህስ ምንድነው ስራቸው?››
‹ዋናው ትልቅ ስራ ያለበት ናቪጌተሩ ነው፤ ቻርቱ ላይ ያፈጠጠው ጃክ አሽፎርድ ይባላል አይሮፕላኑ የት እንዳለ የሚቆጣጠረው እሱ ነው! በተለይ መሃል አትላንቲክ ላይ ስንበር፡፡››
ጃክ ካቀረቀረበት ቀና ብሎ ፈገግ አለ፡፡ ‹‹አይሮፕላኑ እየበረረ የሚገኝበትን ቦታ የሚጠቁመንን መሳሪያ የሚቆጣጠረው ጃክ ሲሆን አንዳንድ ጊዜ ከባህር በላይ ሲበር ቦታውን ማወቅ አስቸጋሪ የሚሆንበት ጊዜ አለ፡፡››
ጃክም ስለስራው ሲናገር ‹‹ብመጀመሪያ መሳሪያውን በመጠቀም በመስታወት እያየህ አንድ ኮከብ ፈልገህ ኮከቡ በአድማስ ላይ ትክክል እስኪመጣ ጠብቀህ የመስታወቱን አንግል ታስተካክላለህ›› አለ፡
‹‹ይሄማ ቀላል ነው›› አለ ፔርሲ፡፡
‹‹ይሄ በቲዮሪ ደረጃ ነው›› አለ ጃክ እየሳቀ ‹‹የዚህ የጉዞ መስመር ችግር ጠቅላላ በረራውን ድፍን ባለ ደመና ልንጓዝ የምንችልበት አጋጣሚ
የሚፈጠርበት ጊዜ መኖሩ ነው፡፡ የተነሳህበትን ነጥብ ካወቅህና በተመሳሳይ
አቅጣጫ የምትጓዝ ከሆንክ ልትሳሳትበት የምትችልበት አጋጣሚ ባይኖርም
ይሄ የሚሆነው ግን ነፋስ በሌለበት ጊዜ ነው፡፡ሀይለኛ ንፋስ በሚኖርበት ጊዜ
አይሮፕላኑን ወዲህና ወዲያ የሚያላጋው ስለሆነ መስመር ጠብቆ መጓዝ
አስቸጋሪ ነው:፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
የበረራ መሃንዲሱ ኤዲ ዲከን የስማይ በራሪ ጀልባውን የሚያየው
ጥንቃቄ የሚፈልግ ነገር አድርጎ ነው፡፡ የአይሮፕላኑ መሳሪያዎች ገና በቅጡ
ያልዳበሩ መሆናቸውንና በአትላንቲክ ውቅያኖስ በምሽት በሚደረገው በረራ
ወቅት ያልተጠበቀ አደጋ ሊደርስ እንደሚችል ተሳፋሪዎቹ የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ያውቃል፡፡ ሆኖም ኤዲ የካፒቴኑ የመሾፈር ብቃት፣ የአይሮፕላኑ ሰራተኞች ከልብ መስራትና የአሜሪካ ኢንጂነሪንግ የደረሰበት ደረጃ ተዳምረው አይሮፕላኑን በሰላም አሜሪካ እንደሚያደርሱት ይተማመናል።
ይህ ጉዞም እስካሁን ካደረጋቸው ጉዞዎች ሁሉ አስፈሪ ሆኖበታል፡በተሳፋሪዎች ስም ዝርዝር ውስጥ ቶም ሉተር የሚባል ሰው መኖሩን አይቷል፡፡ ተሳፋሪዎቹ አንድ በአንድ አይሮፕላኑ ላይ ሲሳፈሩ ከእነዚህ ውስጥ ካሮል አንን ያገታት ቶም ሉተር የቱ ይሆን? አለ በሆዱ¨
አዕምሮውን ወጥሮ የያዘውን የካሮል አንን ጉዳይ ለጥቂት ጊዜም ቢሆን ትቶ አይሮፕላኑን ለበረራ ለማዘጋጀት ተነሳ፡፡ የአይሮፕላኑ የተለያዩ መሳሪያዎች የሚሰሩና የማይሰሩ መሆናቸውን መፈተሽ፣ አራቱን ግዙፍ ሞተሮች መቆጣጠር ከሚሰራቸው ስራዎች ውስጥ አንዳንዶቹ ናቸው፡ አይሮፕላኑ ተነስቶ በጥሩ ሁኔታ መብረር ከጀመረ በኋላ ብዙም የሚሰራው ነገር አይኖርም፡፡ በዚህ ጊዜ የአይሮፕላኑ ፍጥነትና
የሞተሮቹ ሙቀት መጠን
በትክክል መስራቱንና ነዳጁን መቆጣጠር
ይሆናል። ሆኖም አዕምሮው እንደገና ወደ ካሮል አን እየሄደበት ተቸገረ፡፡
ካሮል አን በሚቀጥሉት ሃያ አራት ሰዓት ውስጥ በእነዚህ አረመኔዎች እጅ በተለይም ከጠጡ ምን ሊደርስባት እንደሚችል አይታወቅም:
እነዚህ ሰዎች ምንድነው
ከእሱ የሚፈልጉት? የስራ ጓደኞቹ የተቸገረበትን ነገር እንዳያውቁበት መጠንቀቅ አለበት፡፡ ሁሉም ግዴታውን
ለመወጣት ተፍ ተፍ ስለሚል ላያውቁበት ይችላሉ፡ ካፒቴን ቤከርና ረዳት ካፒቴን ጆኒ ዶት የአይሮፕላኑ ጋቢና ውስጥ ተመቻችተው ተቀምጠዋል
ከተሳፋሪዎች ክፍል የሚመጣው ብርሃን ፓይለቶቹን እንዳያስቸግራቸው
ማታ ማታ ወፍራም መጋረጃ ይጋረዳል፡ ማፖችንና መሳሪያዎች በመጠቀም
አይሮፕላኑን ትክክለኛውን አቅጣጫ እንዲይዝ የሚያደርገው ናቪጌተሩ ጃክ
አሽፎርድ ማፑ ላይ አፍጥጧል፡
ይህን አይሮፕላን ከሌሎች አይሮፕላኖች የሚለየው አይሮፕላኑ መሬት
ሳይወርድ ዘይት የሚያፈስን የሞተር ክፍል ጥገናን የመሳሰሉ ቀላል የጥገና
ስራዎችን መስራት ማስቻሉ ነው፡፡ ቀጥሎ የሚገኘው ቦታ የሬዲዮ ኦፕሬተሩ
የቤን ቶምሰን ሲሆን ከእሱ ኋላ ደግሞ የኤዲ የስራ ቦታ ይገኛል።
ኤዲ ጀርባቸውን ለእሱ ሰጥተው በተመስጦ የሚሰሩ ጓደኖቹ የእሱን
ጭንቀትና ፍርሃት ባለማስተዋላቸው ተረጋጋ:: ለጊዜው ማንነቱ ያልታወቀው ሚስተር ሉተር እኔ ነኝ እንዲል ለማድረግ ፍላጎት አደረበት፡፡
በተሳፋሪዎች ክፍል መተላለፊያ መንጎራደድ ፈለገና ከመቀመጫው ተነስቶ ‹‹እስቲ አንድ ቼክ የማደርገው ነገር አለ›› ብሎ ለናቪጌተሩ ነገረና ደረጃውን
ወርዶ ሄደ፡፡ የሆነ ሰው ለምን ቼክ ማድረግ እንደፈለገ ቢጠይቀው ዝም ብሎ እንደሚያልፍ ወስኗል፡፡
ኤዲ በመተላለፊያው ላይ ቀስ ብሎ ተራመደ፡ ኒክና ዴቪ ለተሳፋሪዎች ምግብና መጠጥ እያደሉ ነው፡፡ ተሳፋሪዎቹ በተለያዩ ቋንቋዎች ያወራሉ፡፡
የተወሰኑ ሰዎች ካርታ ጨዋታ አጧጡፈዋል፡ ከተሳፋሪዎቹ መካከል ታዋቂ ሰዎች ቢያይም ሃሳቡ ስለተበታተነበት እነማን እንደሆኑ መለየት አልቻለም፡፡እያንዳንዱ ሰው ላይ ተራ በተራ ቢያፈጥም ማንም ሰው ‹ቶም ሉተር እኔ
ነኝ›› አላለውም፡፡ ማየት የፈለገውን ነገር እንደነገሩ አይቶ በሩን ሲዘጋ አንድ
አስራ አራት አመት የሚሆነው ልጅ የሚሰራውን በተመስጦ ሲመለከት አየና
ፈገግ አለ፡፡
የፓይለቶቹን ጋቢና ማየት ይቻላል?›› ሲል ጠየቀው ልጁ፡
‹‹ይቻላል›› አለ ኤዲ፡ በዚህ ሰዓት ማንም እንዲያስቸግረው ባይፈልግም ተሳፋሪውን በትህትና ማናገር አለበት፡
‹በጣም አመሰግናለሁ›› አለ ልጁ፡
‹‹ወደ መቀመጫህ ተመለስና ጥቂት ጊዜ ቆይቼ እጠራሃለሁ›› አለው
ልጁ በኤዲ መልስ ግራ ቢጋባም ራሱን በእሺታ ነቀነቀና ፈጠን ብሎ
ሄደ፡፡
ኤዲ በመተላለፊያው ላይ እየተንጎራደደ አንድ ሰው እንዲያናግረው ጠበቀ፡፡ የሚያናግረው ሰው አለመኖሩን ሲረዳ ሰውየው ሰው የማይኖርበትን
አጋጣሚ እየጠበቀ መሆኑን ገመተ፡ አስተናጋጁን ሉተር የተባለው ሰው የቱጋ እንደተቀመጠ መጠየቅ ይችላል፡፡ ነገር ግን ለምንህ ነው የምትጠይቀው?› ብሎ ቢለው ምን መልስ እንደሚሰጥ አያውቅም በዚህ ጊዜ የስራ ባልደረቦቹ በእሱ ላይ ምንም አይነት ጥርጣሬ እንዲያድርባቸ
የሚያደርግ ነገር ማድረግ የለበትም፡፡
ልጁ ከአባትና ከእናቱ ጋር ነው የተቀመጠው፡፡ ኤዲም ‹‹ማሙሽ አሁን ና›› ሲል ተጣራ፡ አባትና እናቱም በመቀበል ራሳቸውን ነቀነቁ። አንዲት ጸጉረ ረጅም ልጅ የልጁ እህት ሳትሆን አትቀርም ሞቅ ያለ ፈገግታ
ስትመግበው ልቡ ደንገጥ አለ፡፡ ልጅቷ ስትስቅ ታምራለች፡
‹‹ማነው ስምህ ማሙሽ?›› አለው፡
‹‹ፔርሲ ኦክሰንፎርድ›› አለ፡
‹‹እኔ ኤዲ ዲኪን እባላለሁ፡፡ የበረራ መሀንዲስ ነኝ፡፡ ሞተሮቹን በትክክል መስራታቸውን መከታተል ነው ስራዬ››
የመጨረሻው ደረጃ ላይ ደረሱ፡ ‹‹ይሄ ሁሉ ደውልና መሳሪያ ምን ያደርጋል?››
‹‹የሽክርክሪቱን ፍጥነት፣ የሞተሩን የሙቀት መጠን እና የነዳጁን ቅልቅል ይቆጣጠራል፡፡›› ለልጁ በይበልጥ እንዲገባው ‹‹እዚህ ወንበር ላይ
ቁጭ በል›› አለው፡ ፔርሲም ቁጭ አለ፡፡ ‹‹ይሄ ደውል የቁጥር ሁለት ሞተርን የሙቀት መጠን ያሳያል፡ አሁን ሙቀቱ ከፍ ብሏል፡ ትንሽ ማቀዝቀዝ ያስፈልጋል፡››
‹‹እንዴት ነው ይሄን የምታደርገው?››
‹‹እጀታውን ያዝና ትንሽ ወደታች ግፋው ይህን ያህል ይበቃል፡ አሁን ተጨማሪ አየር እየገባ ነው ከትንሽ ደቂቃ በኋላ የሙቀት መጠኑ ሲወርድ
ታያለህ፡፡ ፊዚክስ ተምረሃል?›› ሲል ጠየቀው ኤዲ፡፡
‹‹እኔ የምማረው ዘመናዊ ትምህርት ቤት ውስጥ አይደለም›› አለ ፔርሲ፣ ‹‹ትምህርት ቤቱ ላቲንና ግሪክ ቋንቋዎች ላይ ነው በይበልጥ ትኩረት የሚያደርገው፡፡ ሳይንስ ላይ እስከዚህም ነው፡፡››
‹‹ሌሎቹ የስራ ባልደረቦችህስ ምንድነው ስራቸው?››
‹ዋናው ትልቅ ስራ ያለበት ናቪጌተሩ ነው፤ ቻርቱ ላይ ያፈጠጠው ጃክ አሽፎርድ ይባላል አይሮፕላኑ የት እንዳለ የሚቆጣጠረው እሱ ነው! በተለይ መሃል አትላንቲክ ላይ ስንበር፡፡››
ጃክ ካቀረቀረበት ቀና ብሎ ፈገግ አለ፡፡ ‹‹አይሮፕላኑ እየበረረ የሚገኝበትን ቦታ የሚጠቁመንን መሳሪያ የሚቆጣጠረው ጃክ ሲሆን አንዳንድ ጊዜ ከባህር በላይ ሲበር ቦታውን ማወቅ አስቸጋሪ የሚሆንበት ጊዜ አለ፡፡››
ጃክም ስለስራው ሲናገር ‹‹ብመጀመሪያ መሳሪያውን በመጠቀም በመስታወት እያየህ አንድ ኮከብ ፈልገህ ኮከቡ በአድማስ ላይ ትክክል እስኪመጣ ጠብቀህ የመስታወቱን አንግል ታስተካክላለህ›› አለ፡
‹‹ይሄማ ቀላል ነው›› አለ ፔርሲ፡፡
‹‹ይሄ በቲዮሪ ደረጃ ነው›› አለ ጃክ እየሳቀ ‹‹የዚህ የጉዞ መስመር ችግር ጠቅላላ በረራውን ድፍን ባለ ደመና ልንጓዝ የምንችልበት አጋጣሚ
የሚፈጠርበት ጊዜ መኖሩ ነው፡፡ የተነሳህበትን ነጥብ ካወቅህና በተመሳሳይ
አቅጣጫ የምትጓዝ ከሆንክ ልትሳሳትበት የምትችልበት አጋጣሚ ባይኖርም
ይሄ የሚሆነው ግን ነፋስ በሌለበት ጊዜ ነው፡፡ሀይለኛ ንፋስ በሚኖርበት ጊዜ
አይሮፕላኑን ወዲህና ወዲያ የሚያላጋው ስለሆነ መስመር ጠብቆ መጓዝ
አስቸጋሪ ነው:፡
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ከሉ ሆራ ጎይቲ አንተነህን ሐመር ካደረሳት በኋላ አስር ቀን በማይሞላ ጊዜ ተመልሶ እንደሚመጣና እሱ አዲሳባ ለተወሰኑ ቀናት
ሲቆይ ካርለት ደግሞ ወደ ሐመር ለመሄድ እቅድ ነበራቸው፡፡ ከሎ ሆራ ግን የውሃ ሽታ ሆነባት፡፡
“ምን ነካው?” እያለች ብዙ አሰበች ካርለት: ደህንነታቸውንና
ያጋጠመውን ችግር ግን ማወቂያ አንዳችም የመገናኛ እድል
አልነበራትም፡ ስልክ ደብዳቤ ፋክስ ኢሜል.. አንዳቸውንም የሉም: ሐመር ውስጥ መገናኛ ዘዴው “ላልሰማው አሰማ" የሚለው ዘዴ ነው:: መንገደኛ ሲገናኝ በርኮቶው ላይ ቁጭ ይልና ሰዉ ከብቱ
ቀየው. ሰላም መሆኑን በጥሞና ይነጋገራል: አዲስ ነገር ደስታ ችግር ግጭት ካለ ያየው ላላየው ይነግራል፡፡ ወይንም የሰማው ከሆነ ሰማሁ ብሎ ያወራል፡፡
አስቸኳይና ጊዜ የማይሰጥ
ማህበረሰቡን የሚጎዳ ችግር ካለ ግን ሁለት እጃቸውን ያቆላልፉና ከትንፋሻቸው የሚወጣውን
አየር የእጅ ጣታቸውን ከፈት ከደን በማድረግ ድምፅ ይፈጥራሉ፡፡ የሰማው ላልሰማው በተመሳሳይ መልኩ እየነፋ ያስተላልፋል፡፡ ያን
ጊዜ ዋናው መንገድ ላይ የሚሄድ ሐመር ሁሉ ጫካ ጫካውን አድፍጦ እየተጓዘ ባለ ጠበንጃው ጠበንጃውን ባለ ጦሩ ጦሩን… ሁሉም ያለውን እየያዘ እየተሰበሰበ መንደሩን የሚጠብቁ እነ እከሌ እከሌ ከብቶች ዘንድ እነ እከሌ እነ እከሌ እየተባለ አሳሾች,ሸማቂዎች
ሰላዮች ይመደቡና የመጣባቸውን ችግር በጋራ
ይጋፈጣሉ፡፡ ሰላም ሲሆንም አንዱ ለሌላው እያሰማ ወደ እለት የኑሮውን ይመለሳል፡፡ በሐመር ይኸ ነው ለዘመናት የቆየው መገናኛ:
“ምናልባት መኪናዋ ተበላሽታ ይሆን? ወይንስ መንገዱ ተበላሽቶ ድልድይ ተሰብሮ…" እያለችም አሰበች ካርለት መልስ ግን
አጣች! መላ ምት ብቻ:: ስለዚ አዲሳባ ተቀምጣ ከምትጨነቅ መሄዱን መረጠች፡፡
በምን እንደምትሄድ ግን ጨነቃት። በትራንስፖርት መኪና መሄዱን አሰበች እንዲያውም እስካሁን በትራንስፖርት መኪና
ከተማ ውስጥ ካልሆነ በስተቀር ሄዳ አታውቅም፡ ችግሩ ግን ጓዟ
ብዙ ነው፡
እዚሆ ሆኜ በሃሳብ ከመጨነቅ መሄዱ ይሻለኛል ካለስራ አዲሳባ መቀመጡ ደግሞ ራሱን የቻለ ትልቅ ችግር ነው' ብላ
አሰበች: ለጊዜው የሚያስፈልጋትን ብቻ ይዛ ሌላውን ሌላ ጊዜ ከሎ
እንዲወስድላት ብታደርግ እንደሚሻላት አመነች፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።፡።
ካርለት ታክሲ ተኮናትራ መርካቶ የክፍለሃገር አውቶብስ መናኸሪያ ስትደርስ የሚተራመሰው ሰው ለጉድ ነው: ሆንኮንግና
ህንድ አገር ግን እንዲያ ያለውን ትርምስ ስለለመደችው አልተገረመችም፡፡ ባለታክሲው ደንበኛዋ ነው፡ ታክሲዋን ወደ ዜድ ሙዚቃ ቤት አቅራቢያ አቆሞ ጓዟን ተከፋፍለው መንገዱ አቆራርጠው ከሚተራመሰው ህዝብ መካከልም አልፈው በሰፊው በር በኩል ወደ መናኸሪያው ገቡ፡
“ድሬዳዋ ደሴ ለቀምት በካቻማሊ በዋሊያ" እያሉ
ሰውን የሚጎትቱት እሷንም ጎነታተሏት! ያስፈራሉ። ስነ ስርዓቱ ቅጥ የለውም
ለዝርፊያና ቅሚያ አመች ነው: አለንጋ የያዙት ዘበኞች
ስርዓቱን ለማስጠበቅ ከአቅም በላይ ሆኖባቸዋል፡፡ መንደኛው ግን እራሱን ይጠብቃል። ካርለት ሻንጣዋን በትከሻዋ አንጠልጥላ በሁለት
እጅዋ ከፊት ለፊቷ አጥብቃ ይዛ ገባች፡፡ ታክሲ ነጂው
የሚያዣብቡትን ይክላከላል፡፡ እንደ ሽንት ቤት ዝንብ ግር ብለው
ይመጡና እሱን ሲያዩ ገለል ይሉላታል
“አርባምንጭ አንደኛ አርባምንጭ
ሁለተኛ ከሚለው
አውቶበስ ዘንድ ደረሰ! ለመስቀል የሚጓዘው መንገደኛ ከአውቶብሉ
በስተኋላ አቧል። “ትኬት ይኖራል?” ታክሲ ሾፌሩ ካርኒ ቆራጮችን
በየተራ ጠየቃቸው: “አልቋል ባክህ ገለል ገለል በሉ ካለበለዚያእቃችሁ አይገመትም• አይጫንም፤ ስለዚህ ማርፈዳችሁን እወቁ…" አለ እንደኛው ካርኒ ቆራጭ በስጨት ብሎ። አንድ ብልጣ ብልጥ
ለእራሱ እየተጠጋ “እስኪ እሽ በሉ ማርፈዱ የሚጎዳን እኛን ነው…"አለ፡፡ መስማማት የለም። ሁሉም እቃውን ጭኖ ፊት አካባቢ
ተቀምጦ ለመጓዝ ጓጉቷል፡፡ ደሞ መስቀል ነው። የዓመቱ መገናኛ ዓውዳመት! ካርኒ ቆራጩ አኩሩፎ “ያውላችሁ" ብሎ ወጣና ተደናግጣ ከቆመችው ካርለት ጎን ቆመ:: አየችው አያት! ታለትንሽ ጊዜ ተያዩ፡፡
ካኪ ካፖርት ሁለት ጥራዝ ካርኒ ጭንቅላቱ ላይ ደግሞ
ፎጣ ጠምጥሟል፡ ፊቱ ምጥጥ ያለ ጠይም መልከ መልካም ግን ነገረኛ መሳይ ነው። ሲያናግሩት አይናገርም:: ከመሰላቸት ወይም ከኩራት ይሁን እግዜር ይወቀው
"አርባምንጭ ዘላቂ ምንም ትኬት የለም ለሷ ነበር”
አለው ታክሲ ሾፌሩ ጠጋ ብሎ። አላናገረውም! ካርለትን ግን እንደገና አያትና፦
ነገርኩህ አይደለም የኔ ወንድም አልቋል" አለና የሚያስብ መሰለ: እስኪ አንዴ የት ነው እባካችሁ ሁለት ትኬት ገዝቶ አንድ
ወንበር ላይ መቀመጥ እፈልጋለሁ ያለ ሰው ነበር”
“የታል?" አለ ታክሲ ሾፌሩ: ካርለት! ነገሩን ለማጣራት
ፈለገች በእንግሊዘኛ የሚገልፅላት ግን ጠፋ።
ዩ ዌት" አላት ታክሲ ሾፌሩ ለከት ባጣ እንግሊዘኛ::
“ቆይ ግዴለም እኔ አናግረዋለሁ ብሎ እቃውን እየገመተ መጫን ተጀመረ ከዚያም የአትወብሱ
በር ሲከፈት ግፊያው
ያስፈራል፡፡ ሽማግሌዎች, ህፃን የያዙ ሴቶች….. እየተወረወሩ በግፊያው እየተሽቀነጠሩ ጉልበት ያለው እየበረቃቀሰ ገባ ካርለት ገረማት፡፡
“ሁሌም እንዲህ ይሆን ወይንስ ዛሬ ብቻ? ነፍስ እስኪጠፋ ነው የሚጠበቀው? ምናለ በወንበር ቁጥር ወይንም በሌላ ዘዴ የማንም መብት ሳይነካ መንገደኛው ቢስተናገድ' ብላ አዘነች፡፡
“እስኪ ነይ እቃሽ እላይ ይውጣ ጫንላት” አለ ካርኒ
ቆራጩ በምልክት። ካርለት ተከትላው አውቶቡስ ውስጥ ገባች፡፡መንገደኛው ገና ተረጋግቶ አልተቀመጠም። ሲገባ ከነበረው ትርምስ
ግን ይሻላል፡፡
“የኔ ወንድም አንተ ነህ አይደለም ሁለት ትኬት
የያዝኸው?"
“አዎን! እኔ ነኝ። አንዱ ጎን ካልተቀመጥሁ' ብሎ ለምን
አያፈጥብኝ: እኔ ደልቶኝ መሰለው ሁለት ትኬት መግዛቴ፡ ሰላም ፈልጌ ነው መሳቀቅ ጠልቼ ነው. አሁን ግን ሰላም ነው አስበህ
ልትጠይቀኝ በመምጣትህ አመሰግናለሁ። ለዚህ አይደል እኔስ ቀደም
ብዬ አደራ ማለቴ አለው ፂሙን በቀኝ እጁ ቁልቁል እሞዠቀ፡፡
የለም አመጣጤ ለሌላ ነው። ይህች የሰው አገር ሰው ናት… እባክህ ተባበራት ብዙም አታስቸግርህም። ገንዘቡን ተቀብያት እሰጥሃለሁ።”
ኖ የለም እኔ አፓርታይድ አይደለሁ ጥቁር ነጭ የምል!መሳቀቅ መጨነቅ ስለማልፈልግ ብቻ ነው። ይህንን ደግሞ አስረድቻችሁ ተስማምተናል በጭራሽ አጠገቤ ሰው አይቀመጥም፡"
“…እባክህ ተባበራት መስሪያ ቤታችን እኮ ይህን ጉዞ ሲያዘጋጅ ገንዘብ ማግኘት ብቻ ሳይሆን ህዝቡንም ለመርዳት ነው"
አለው።
“ይኸ እኮ ነው የጠላሁት። ሰላም ለማግኘት ብዬ ገንዘቤን አውጥቼ ያላሰብሁት አተካራ ገዛሁበት: ጭቅጭቅ አልፈልግም እሽ!
ገንዘቤን! ያው ቦታዋ” አለ: ካርለት ሰላሣ ሁለት ብር ከአስር ሣንቲም ከፈለችው: ለታክሲ ሾፌሩም ኪራዩን ከጉርሻ ጋር ስትሰጠው በደስታ ፊቱ በርቶ ተሰናብቷት ሄደ፡
አጠገቧ የተቀመጠው ሰው አንድ አነስ ያለች ጀሪካን አንድ በመጠኑ ከትንሽዋ ጀሪካን ከፍ ያለ እንደ ህጻን በእቅፉ ይዟል። ሰፊ
ኮት የወታደር ቦት ጫማ ተጫምቷል! ፀጉሩ ዞማ ነው አበጣጠሩ ግን ለከት የለውም! ፊቱ ከፊሉ በፂሙ ተሸፍኗል! ከንፈሩ
አይታይም…
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ከሉ ሆራ ጎይቲ አንተነህን ሐመር ካደረሳት በኋላ አስር ቀን በማይሞላ ጊዜ ተመልሶ እንደሚመጣና እሱ አዲሳባ ለተወሰኑ ቀናት
ሲቆይ ካርለት ደግሞ ወደ ሐመር ለመሄድ እቅድ ነበራቸው፡፡ ከሎ ሆራ ግን የውሃ ሽታ ሆነባት፡፡
“ምን ነካው?” እያለች ብዙ አሰበች ካርለት: ደህንነታቸውንና
ያጋጠመውን ችግር ግን ማወቂያ አንዳችም የመገናኛ እድል
አልነበራትም፡ ስልክ ደብዳቤ ፋክስ ኢሜል.. አንዳቸውንም የሉም: ሐመር ውስጥ መገናኛ ዘዴው “ላልሰማው አሰማ" የሚለው ዘዴ ነው:: መንገደኛ ሲገናኝ በርኮቶው ላይ ቁጭ ይልና ሰዉ ከብቱ
ቀየው. ሰላም መሆኑን በጥሞና ይነጋገራል: አዲስ ነገር ደስታ ችግር ግጭት ካለ ያየው ላላየው ይነግራል፡፡ ወይንም የሰማው ከሆነ ሰማሁ ብሎ ያወራል፡፡
አስቸኳይና ጊዜ የማይሰጥ
ማህበረሰቡን የሚጎዳ ችግር ካለ ግን ሁለት እጃቸውን ያቆላልፉና ከትንፋሻቸው የሚወጣውን
አየር የእጅ ጣታቸውን ከፈት ከደን በማድረግ ድምፅ ይፈጥራሉ፡፡ የሰማው ላልሰማው በተመሳሳይ መልኩ እየነፋ ያስተላልፋል፡፡ ያን
ጊዜ ዋናው መንገድ ላይ የሚሄድ ሐመር ሁሉ ጫካ ጫካውን አድፍጦ እየተጓዘ ባለ ጠበንጃው ጠበንጃውን ባለ ጦሩ ጦሩን… ሁሉም ያለውን እየያዘ እየተሰበሰበ መንደሩን የሚጠብቁ እነ እከሌ እከሌ ከብቶች ዘንድ እነ እከሌ እነ እከሌ እየተባለ አሳሾች,ሸማቂዎች
ሰላዮች ይመደቡና የመጣባቸውን ችግር በጋራ
ይጋፈጣሉ፡፡ ሰላም ሲሆንም አንዱ ለሌላው እያሰማ ወደ እለት የኑሮውን ይመለሳል፡፡ በሐመር ይኸ ነው ለዘመናት የቆየው መገናኛ:
“ምናልባት መኪናዋ ተበላሽታ ይሆን? ወይንስ መንገዱ ተበላሽቶ ድልድይ ተሰብሮ…" እያለችም አሰበች ካርለት መልስ ግን
አጣች! መላ ምት ብቻ:: ስለዚ አዲሳባ ተቀምጣ ከምትጨነቅ መሄዱን መረጠች፡፡
በምን እንደምትሄድ ግን ጨነቃት። በትራንስፖርት መኪና መሄዱን አሰበች እንዲያውም እስካሁን በትራንስፖርት መኪና
ከተማ ውስጥ ካልሆነ በስተቀር ሄዳ አታውቅም፡ ችግሩ ግን ጓዟ
ብዙ ነው፡
እዚሆ ሆኜ በሃሳብ ከመጨነቅ መሄዱ ይሻለኛል ካለስራ አዲሳባ መቀመጡ ደግሞ ራሱን የቻለ ትልቅ ችግር ነው' ብላ
አሰበች: ለጊዜው የሚያስፈልጋትን ብቻ ይዛ ሌላውን ሌላ ጊዜ ከሎ
እንዲወስድላት ብታደርግ እንደሚሻላት አመነች፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።፡።
ካርለት ታክሲ ተኮናትራ መርካቶ የክፍለሃገር አውቶብስ መናኸሪያ ስትደርስ የሚተራመሰው ሰው ለጉድ ነው: ሆንኮንግና
ህንድ አገር ግን እንዲያ ያለውን ትርምስ ስለለመደችው አልተገረመችም፡፡ ባለታክሲው ደንበኛዋ ነው፡ ታክሲዋን ወደ ዜድ ሙዚቃ ቤት አቅራቢያ አቆሞ ጓዟን ተከፋፍለው መንገዱ አቆራርጠው ከሚተራመሰው ህዝብ መካከልም አልፈው በሰፊው በር በኩል ወደ መናኸሪያው ገቡ፡
“ድሬዳዋ ደሴ ለቀምት በካቻማሊ በዋሊያ" እያሉ
ሰውን የሚጎትቱት እሷንም ጎነታተሏት! ያስፈራሉ። ስነ ስርዓቱ ቅጥ የለውም
ለዝርፊያና ቅሚያ አመች ነው: አለንጋ የያዙት ዘበኞች
ስርዓቱን ለማስጠበቅ ከአቅም በላይ ሆኖባቸዋል፡፡ መንደኛው ግን እራሱን ይጠብቃል። ካርለት ሻንጣዋን በትከሻዋ አንጠልጥላ በሁለት
እጅዋ ከፊት ለፊቷ አጥብቃ ይዛ ገባች፡፡ ታክሲ ነጂው
የሚያዣብቡትን ይክላከላል፡፡ እንደ ሽንት ቤት ዝንብ ግር ብለው
ይመጡና እሱን ሲያዩ ገለል ይሉላታል
“አርባምንጭ አንደኛ አርባምንጭ
ሁለተኛ ከሚለው
አውቶበስ ዘንድ ደረሰ! ለመስቀል የሚጓዘው መንገደኛ ከአውቶብሉ
በስተኋላ አቧል። “ትኬት ይኖራል?” ታክሲ ሾፌሩ ካርኒ ቆራጮችን
በየተራ ጠየቃቸው: “አልቋል ባክህ ገለል ገለል በሉ ካለበለዚያእቃችሁ አይገመትም• አይጫንም፤ ስለዚህ ማርፈዳችሁን እወቁ…" አለ እንደኛው ካርኒ ቆራጭ በስጨት ብሎ። አንድ ብልጣ ብልጥ
ለእራሱ እየተጠጋ “እስኪ እሽ በሉ ማርፈዱ የሚጎዳን እኛን ነው…"አለ፡፡ መስማማት የለም። ሁሉም እቃውን ጭኖ ፊት አካባቢ
ተቀምጦ ለመጓዝ ጓጉቷል፡፡ ደሞ መስቀል ነው። የዓመቱ መገናኛ ዓውዳመት! ካርኒ ቆራጩ አኩሩፎ “ያውላችሁ" ብሎ ወጣና ተደናግጣ ከቆመችው ካርለት ጎን ቆመ:: አየችው አያት! ታለትንሽ ጊዜ ተያዩ፡፡
ካኪ ካፖርት ሁለት ጥራዝ ካርኒ ጭንቅላቱ ላይ ደግሞ
ፎጣ ጠምጥሟል፡ ፊቱ ምጥጥ ያለ ጠይም መልከ መልካም ግን ነገረኛ መሳይ ነው። ሲያናግሩት አይናገርም:: ከመሰላቸት ወይም ከኩራት ይሁን እግዜር ይወቀው
"አርባምንጭ ዘላቂ ምንም ትኬት የለም ለሷ ነበር”
አለው ታክሲ ሾፌሩ ጠጋ ብሎ። አላናገረውም! ካርለትን ግን እንደገና አያትና፦
ነገርኩህ አይደለም የኔ ወንድም አልቋል" አለና የሚያስብ መሰለ: እስኪ አንዴ የት ነው እባካችሁ ሁለት ትኬት ገዝቶ አንድ
ወንበር ላይ መቀመጥ እፈልጋለሁ ያለ ሰው ነበር”
“የታል?" አለ ታክሲ ሾፌሩ: ካርለት! ነገሩን ለማጣራት
ፈለገች በእንግሊዘኛ የሚገልፅላት ግን ጠፋ።
ዩ ዌት" አላት ታክሲ ሾፌሩ ለከት ባጣ እንግሊዘኛ::
“ቆይ ግዴለም እኔ አናግረዋለሁ ብሎ እቃውን እየገመተ መጫን ተጀመረ ከዚያም የአትወብሱ
በር ሲከፈት ግፊያው
ያስፈራል፡፡ ሽማግሌዎች, ህፃን የያዙ ሴቶች….. እየተወረወሩ በግፊያው እየተሽቀነጠሩ ጉልበት ያለው እየበረቃቀሰ ገባ ካርለት ገረማት፡፡
“ሁሌም እንዲህ ይሆን ወይንስ ዛሬ ብቻ? ነፍስ እስኪጠፋ ነው የሚጠበቀው? ምናለ በወንበር ቁጥር ወይንም በሌላ ዘዴ የማንም መብት ሳይነካ መንገደኛው ቢስተናገድ' ብላ አዘነች፡፡
“እስኪ ነይ እቃሽ እላይ ይውጣ ጫንላት” አለ ካርኒ
ቆራጩ በምልክት። ካርለት ተከትላው አውቶቡስ ውስጥ ገባች፡፡መንገደኛው ገና ተረጋግቶ አልተቀመጠም። ሲገባ ከነበረው ትርምስ
ግን ይሻላል፡፡
“የኔ ወንድም አንተ ነህ አይደለም ሁለት ትኬት
የያዝኸው?"
“አዎን! እኔ ነኝ። አንዱ ጎን ካልተቀመጥሁ' ብሎ ለምን
አያፈጥብኝ: እኔ ደልቶኝ መሰለው ሁለት ትኬት መግዛቴ፡ ሰላም ፈልጌ ነው መሳቀቅ ጠልቼ ነው. አሁን ግን ሰላም ነው አስበህ
ልትጠይቀኝ በመምጣትህ አመሰግናለሁ። ለዚህ አይደል እኔስ ቀደም
ብዬ አደራ ማለቴ አለው ፂሙን በቀኝ እጁ ቁልቁል እሞዠቀ፡፡
የለም አመጣጤ ለሌላ ነው። ይህች የሰው አገር ሰው ናት… እባክህ ተባበራት ብዙም አታስቸግርህም። ገንዘቡን ተቀብያት እሰጥሃለሁ።”
ኖ የለም እኔ አፓርታይድ አይደለሁ ጥቁር ነጭ የምል!መሳቀቅ መጨነቅ ስለማልፈልግ ብቻ ነው። ይህንን ደግሞ አስረድቻችሁ ተስማምተናል በጭራሽ አጠገቤ ሰው አይቀመጥም፡"
“…እባክህ ተባበራት መስሪያ ቤታችን እኮ ይህን ጉዞ ሲያዘጋጅ ገንዘብ ማግኘት ብቻ ሳይሆን ህዝቡንም ለመርዳት ነው"
አለው።
“ይኸ እኮ ነው የጠላሁት። ሰላም ለማግኘት ብዬ ገንዘቤን አውጥቼ ያላሰብሁት አተካራ ገዛሁበት: ጭቅጭቅ አልፈልግም እሽ!
ገንዘቤን! ያው ቦታዋ” አለ: ካርለት ሰላሣ ሁለት ብር ከአስር ሣንቲም ከፈለችው: ለታክሲ ሾፌሩም ኪራዩን ከጉርሻ ጋር ስትሰጠው በደስታ ፊቱ በርቶ ተሰናብቷት ሄደ፡
አጠገቧ የተቀመጠው ሰው አንድ አነስ ያለች ጀሪካን አንድ በመጠኑ ከትንሽዋ ጀሪካን ከፍ ያለ እንደ ህጻን በእቅፉ ይዟል። ሰፊ
ኮት የወታደር ቦት ጫማ ተጫምቷል! ፀጉሩ ዞማ ነው አበጣጠሩ ግን ለከት የለውም! ፊቱ ከፊሉ በፂሙ ተሸፍኗል! ከንፈሩ
አይታይም…
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
ስበሳጭ ጀርባዬን ይበላኛል...የበላኝን ቦታ ለማከክ እጄን በወገቤ አዙሬ አሽከረክራለሁ፤ ግን ደግሞ አልደርስበትም.. በትከሻዬ በኩል አጠማዝዤ ሞክራለሁ፤ ትርፉ ድካም ነው። ከእከኬ ስቃይ እራሴን ለማስታገስ እገዛ መፈለጌ ያበሳጨኛል ደካማነቴንና ማድረግ የማልችላቸው ነገሮች ብዛት ያስጨንቀኛል...ጀርባዬን በላኝ እከኩልኝ ብዬ የሰው እገዛ ላለመጠየቅ ልብሴን አወልቅና ከሻካራ ግድግዳ ጋር እራሴን አፋትጋለሁ... ቢያቆስለኝም ያስተነፋሰኛል። ቢያንስ ገበናዬ ጠብቄያለሁ፡፡
አለመቻሌንም በሚስጥር በውስጤ አፍኜ ይዘዋለሁ፡፡አዎ አንዳንዴ ህይወት በዛ መጠን ትጨክንብኛለች በዛ መጠንም ታሰቃየኛለች፡፡
ዛሬ እርግጥ አልተበሳጨሁም ፤ግን ደግሞ በጣም ተጨንቄያለሁ፡፡ ጊዜው ጨለምለም ብሎል...አንድ ሰአት ከሩብ አካባቢ ነው›፡፡ ጀማሪ ማፊያ ይመስል ተጀባብኜ ወደሰፈር ተጠጋሁ...፡፡
እየተንቀጠቀጥኩ ነው ፡፡መቼስ ብርድ ብቻ አይመስለኝም እንደዚህ ውስጤ ገብቶ እያንቀጠቀጠኝ ያለው ።ኳስ እንጫወትበት የነበረው ሜዳ ባለአራት ፎቅ ህንፃ ተገማሽሮ ቆሞበታል። መቼስ ደፍረው ጠጠርና አሸዋ አምጥተው የሠፈሩ ሰው እያየ ሲሚንቶ አውርደው ፤ቀስበቀስ የገነቡት ሳይሆን ድንገት ከእለታት በአንድ ቀን ሁሉም የሰፈር ጎረምሳ ሆነ አሮጊት መተኛታቸውን አረጋግጠው ከሆነ ቦታ ጭነው መተው የተከተሉት ነው የሚመስለው። ወደቤታችን አየተቃረብኩ ስመጣ እግሬ እየተሳሰረ አስቸገረኝ፤ መራመድ ሁሉ አቃተኝ።
የውጩ ፍሬንች ዶር በአዲስ ከመቀየሩ ውጭ ቤታችን ከውጭ ያለው እይታ በፊት እንዳነበረ ነው።አለፍ ብዬ ሄድኩና ኮርነር ጋር ስደርስ ጨለማን ተገን አድርጌ ቆምኩ፡፡ ፊቴን ወደ በራፋችን አነጣጠርኩ
፡፡ ...ምንድነው የምጠብቀው..?.ማን እንዲወጣ ወይ ማን እንዲገባ ነው ? ልጄን አሁን የማየት እድል አለኝ ይሆን?በዚህ ጨለማ ምን ልትሰራ ትወጣለች...?ምን አልባት አክስቴ...አዎ ምንአልባት እሷን ነው ላይ የምችለው...፡፡ባላናግራትም ላያት ምኞቴ ነው፡፡ ሶስት ሰአት ድረስ እዛው በቆምኩበት ደንዝዤለሁ… የጨው ሀውልት እንደሆነችው ልክ እንደ ሎጥ ሚስት እኔም የበረዶ ሀውልት ከመሆኔ በፊት ወደ ሆቴሌ ልመለስ ወስኜ እግሬን ሳንቀሳቅስ ስልኬ ተንጫረረ ።በደነዘዘ እጄ አወጣሁና አየሁት ..የደዋዪን ማንነት ሳይ ከሰውነቴ ላይ በረዶ የሠራው ቅዝቃዜ በቅፅበት የረገፈ ይመስል ሙቀት ተሠማኝ ።ልጄ ነች።እንዴ አይታኝ ይሆን እንዴ? ዙሪያ ገባዬን ተገላምጬ ተመለከትኩ።ምንም የለም፡፡ስልኩን አነሳሁት
"ሄሎ የእኔ ልዕልት"
"አባዬ እንዴት ነህ..?ምን እየሠራህ ነው?"
"ስለአንቺ እያሰብኩ"
"ታድዬ" ታድዬ አባባሏ ልቤን ስንጥቅ አድርጎ ቃላቱ በስንጥቁ እየተንጠባጠበ ወደውስጤ ሲዘልቅ ተሠማኝ።
"ምን እየሠራሽ ነው...?ነገ ዝግጅት ስላለብሽ በጊዜ አትተኚም እንዴ?
"እነቴቴ እንደዛ ብለው አጠፋፍተው በጊዜ ተኙ።እኔ ግን ክፍሌ ከገባሁ ብኃላ ከመተኛቴ በፊት መስኮቴን ከፍቼ ጨረቃን ሳያት አንተ ትዝ አልከኝ...እና ደወልኩልህ"
ቀና ብዬ ምትላትን ጨረቃ አያየኋት… ግማሽ ቅርፅ፤ግማሽ ውበት፡፡
"ልጄ እውነትሽን ነው ..ታምራለች"
"ማን ነች የምታምረው አባዬ"
"ያልሻት ጨረቃ ነቻ..አይኖቼን አንጋጥጬ እያየኋት ነው… ግማሽ ብትሆንም ልክ እንደአንቺ ታምራለች"
"አባዬ ዛሬ ከጎኔ ሆነህ እቅፍ አድርጌህ ብተኛ ደስ ይለኝ ነበር"
"እንግዲያው መስኮቱን ክፍት አድርጊና ለጥ በይ ..እኔ በርሬ እመጣና በመስኮት ክፍልሽ ገብቼ እቅፍ አደርግሻለሁ..ግን ከተኛሽ በኃላ ነው የምመጣው"
"አባዬ ደስ የሚል ጫወታ ነው ...በቃ ሳልዘጋው ነው የምተኛው..ነገ ከዝግጅቱ በኃላ ደውልልሀለሁ.ወድሀለሁ።››
"እኔም ወድሻለሁ "ስልኩ ተዘጋ..
የእኔም ወደሆቴሌ የመመለስ አፒታይቴም አብሮ ተዘጋ፤
"ምን ላድርግ?"ከሀያ ደቂቃ በላይ ባለሁበት ቦታ ተገትሬ ማሰብ እንኳን አቅቶኝ ደንዝዤ ቆየሁ።ወደጓሮ ሄድኩ ..፡፡.ካልተቀየረች አንድ ወደጊቢ ዘሎ መግቢያ ምቹ ቦታ ነበረች..አዎ አገኘኋት።ዙሪያ ገባውን ዞር ዞር ብዬ ሰው አለመኖሩ አረጋገጥኩና እንደምንም ተንጠላጥዬ ዘልዬ ግቢውስጥ ገባሁ። ድሮ የሀይእስኩል ተማሪ እያለሁ በተለያየ ምክንያት ውጭ ሳመሽና በራፍ ሲዘጋብኝ በዚህ ዘዴ ነበር ወደ ውስጥ የምገባው..፡፡ይሄው የዛን ጊዜው ልምድ ለዛሬ ረዳኝ።
የውጭ መብራት ስለጠፍ ግቢው በፀጥታና በጭለማ ተውጧል።ኮቴዬን ሳላሰማ ቀስ ብዬ ወደልጄ ክፍል ማለት ወደእኔ የድሮ ክፍል አመራሁ...፡፡ወይ የእኔ ማር እንዳልኳት መስኮቱን ከፍታ ነው የተኛችው። እንደምንም ተንጠላጠልኩና መስኮቱ ላይ ወጣሁ ..ደግነቱ መስኮቱ አጠር ስለሚል በተለይ ከእኔ ቁመት አንፃር አልተቸገርኩም፡፡ በቀላሉ ወደላይ ወጣሁና እግሬን አሽከርክሬ ወደውስጥ ገባሁ፡፡ ልጄን እንዳላስደነግጣት ተጠንቅቄ ወደማብሪያ ማጥፊያው አመራሁ..፡፡አብዛኛውን ዕድሜዬን የኖርኩበት ቤት መሆኑ ነገሮች የት የት እንደሆኑ በቀላሉ ለመለየት ረድቶኛል ። መብራቱን አበራሁ።ልጄ እንዴት አድጋለች..ደግሞ አተኛኞ ልክ እንደናቷ ዝርግትግት ብላ ነው።በቅርቤ ያገኘኋት ኩርሲ መቀመጫ ወደአልጋዎ አስጠጋሁና ቁጭ አልኩ ...፡፡ጭንቅላቴን ሸፍኜበት የነበረውን ኮፍያ ከላዬ ላይ ገፍፌ ጣልኩት።አይኔ ላይ ሰክቼ የነበረውን መነፅር አወለቅኩና በአቅራቢዬ ያለ ትንሽ ጠረጰዛ ላይ አስቀመጥኩ። ሙሉ ትኩረቴን ወደልጄ ሰበሰብኩ።እጆቼን በእርጋታ ወደጭንቅላቷ ሰደድኩ .."ቀስ ብዬ ስዳብሳት አይኖቾን ገለጠች...፡፡ደነገጥኩና እጄን ሰበሰብኩ...እሪ ብላ የምትጮህ መሠሎኝ ፈራሁ። ምን ላድርግ...?ፈጠን ብዬ ዘልዬ እንደአመጣጤ ልውጣ እንዴ?ብዙ ነገር አስቤ አንድንም ሳላደርግ
"አባዬ....ህልም አይደለም አይደል..?"አለችኝ፡፡
"አይደለም የእኔ ማር ...››በተኛችበት ጉንጮቾን ሞጨሞጭኳት...እሷም እጇቾን በአንገቴ ዙሪያ ጠመጠመችና ግንባሬን፤ጉንጬን ፤አገጬን ምንም የቀራት ቦታ የለም...ሙሉ በሙሉ ንቁ ሆና አልጋዎ መካከል ቁጭ አለች።
"አባዬ እኔ እኮ እመጣለሁ ስትለኝ በህልሜ መስሎኝ ነው ቶሎ የተኛሁት።
"በጣም ስለናፈቅሺኝና ..ነገ የደረጃ ተማሪ ሆነሽ ልትሸለሚ ስለሆነ እኔ አባትሽ በጣም ኩራት ስለተሰማኝ እንዴ ተደብቄም ቢሆን በዚህ ቀን ልጄን ካላየኋት እኔ ምን አይነት አባት ነኝ ?ብዬ ነው በዚህ ለሊት ሹልክ ብዬ ክፍልሽ የተገኘሁት።
"አባቴ ውድድድ ነው የማደርግህ...አሁን አቅፍቅፍ ብለን እንተኛ"
"ግን አቴቴ ለሊት ልታይሽ ብትመጣስ?"
"አትመጣም ..ደግሞ እኮ ከውስጥ ተቀርቅሯል ..ብትመጣም ገና ስታንኳኳ ቶሎ ብለህ በመስኮት ትሄዳለህ"
"ምን አይነት ብልጥ ልጅ ነው ያለኝ"አልኩና ከላይ የለበስኩትን ጃኬት በማውለቅ ጠረጳዛ ላይ አኑሬ አልጋ ላይ ወጣሁ..ይሄ አልጋ የእኔና የእናትሽ እንደነበር ታውቂያለሽ?"
"አዎ …ለዛ እኮነው ክፍሌንም አልጋዬንም የምወደው"
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
ስበሳጭ ጀርባዬን ይበላኛል...የበላኝን ቦታ ለማከክ እጄን በወገቤ አዙሬ አሽከረክራለሁ፤ ግን ደግሞ አልደርስበትም.. በትከሻዬ በኩል አጠማዝዤ ሞክራለሁ፤ ትርፉ ድካም ነው። ከእከኬ ስቃይ እራሴን ለማስታገስ እገዛ መፈለጌ ያበሳጨኛል ደካማነቴንና ማድረግ የማልችላቸው ነገሮች ብዛት ያስጨንቀኛል...ጀርባዬን በላኝ እከኩልኝ ብዬ የሰው እገዛ ላለመጠየቅ ልብሴን አወልቅና ከሻካራ ግድግዳ ጋር እራሴን አፋትጋለሁ... ቢያቆስለኝም ያስተነፋሰኛል። ቢያንስ ገበናዬ ጠብቄያለሁ፡፡
አለመቻሌንም በሚስጥር በውስጤ አፍኜ ይዘዋለሁ፡፡አዎ አንዳንዴ ህይወት በዛ መጠን ትጨክንብኛለች በዛ መጠንም ታሰቃየኛለች፡፡
ዛሬ እርግጥ አልተበሳጨሁም ፤ግን ደግሞ በጣም ተጨንቄያለሁ፡፡ ጊዜው ጨለምለም ብሎል...አንድ ሰአት ከሩብ አካባቢ ነው›፡፡ ጀማሪ ማፊያ ይመስል ተጀባብኜ ወደሰፈር ተጠጋሁ...፡፡
እየተንቀጠቀጥኩ ነው ፡፡መቼስ ብርድ ብቻ አይመስለኝም እንደዚህ ውስጤ ገብቶ እያንቀጠቀጠኝ ያለው ።ኳስ እንጫወትበት የነበረው ሜዳ ባለአራት ፎቅ ህንፃ ተገማሽሮ ቆሞበታል። መቼስ ደፍረው ጠጠርና አሸዋ አምጥተው የሠፈሩ ሰው እያየ ሲሚንቶ አውርደው ፤ቀስበቀስ የገነቡት ሳይሆን ድንገት ከእለታት በአንድ ቀን ሁሉም የሰፈር ጎረምሳ ሆነ አሮጊት መተኛታቸውን አረጋግጠው ከሆነ ቦታ ጭነው መተው የተከተሉት ነው የሚመስለው። ወደቤታችን አየተቃረብኩ ስመጣ እግሬ እየተሳሰረ አስቸገረኝ፤ መራመድ ሁሉ አቃተኝ።
የውጩ ፍሬንች ዶር በአዲስ ከመቀየሩ ውጭ ቤታችን ከውጭ ያለው እይታ በፊት እንዳነበረ ነው።አለፍ ብዬ ሄድኩና ኮርነር ጋር ስደርስ ጨለማን ተገን አድርጌ ቆምኩ፡፡ ፊቴን ወደ በራፋችን አነጣጠርኩ
፡፡ ...ምንድነው የምጠብቀው..?.ማን እንዲወጣ ወይ ማን እንዲገባ ነው ? ልጄን አሁን የማየት እድል አለኝ ይሆን?በዚህ ጨለማ ምን ልትሰራ ትወጣለች...?ምን አልባት አክስቴ...አዎ ምንአልባት እሷን ነው ላይ የምችለው...፡፡ባላናግራትም ላያት ምኞቴ ነው፡፡ ሶስት ሰአት ድረስ እዛው በቆምኩበት ደንዝዤለሁ… የጨው ሀውልት እንደሆነችው ልክ እንደ ሎጥ ሚስት እኔም የበረዶ ሀውልት ከመሆኔ በፊት ወደ ሆቴሌ ልመለስ ወስኜ እግሬን ሳንቀሳቅስ ስልኬ ተንጫረረ ።በደነዘዘ እጄ አወጣሁና አየሁት ..የደዋዪን ማንነት ሳይ ከሰውነቴ ላይ በረዶ የሠራው ቅዝቃዜ በቅፅበት የረገፈ ይመስል ሙቀት ተሠማኝ ።ልጄ ነች።እንዴ አይታኝ ይሆን እንዴ? ዙሪያ ገባዬን ተገላምጬ ተመለከትኩ።ምንም የለም፡፡ስልኩን አነሳሁት
"ሄሎ የእኔ ልዕልት"
"አባዬ እንዴት ነህ..?ምን እየሠራህ ነው?"
"ስለአንቺ እያሰብኩ"
"ታድዬ" ታድዬ አባባሏ ልቤን ስንጥቅ አድርጎ ቃላቱ በስንጥቁ እየተንጠባጠበ ወደውስጤ ሲዘልቅ ተሠማኝ።
"ምን እየሠራሽ ነው...?ነገ ዝግጅት ስላለብሽ በጊዜ አትተኚም እንዴ?
"እነቴቴ እንደዛ ብለው አጠፋፍተው በጊዜ ተኙ።እኔ ግን ክፍሌ ከገባሁ ብኃላ ከመተኛቴ በፊት መስኮቴን ከፍቼ ጨረቃን ሳያት አንተ ትዝ አልከኝ...እና ደወልኩልህ"
ቀና ብዬ ምትላትን ጨረቃ አያየኋት… ግማሽ ቅርፅ፤ግማሽ ውበት፡፡
"ልጄ እውነትሽን ነው ..ታምራለች"
"ማን ነች የምታምረው አባዬ"
"ያልሻት ጨረቃ ነቻ..አይኖቼን አንጋጥጬ እያየኋት ነው… ግማሽ ብትሆንም ልክ እንደአንቺ ታምራለች"
"አባዬ ዛሬ ከጎኔ ሆነህ እቅፍ አድርጌህ ብተኛ ደስ ይለኝ ነበር"
"እንግዲያው መስኮቱን ክፍት አድርጊና ለጥ በይ ..እኔ በርሬ እመጣና በመስኮት ክፍልሽ ገብቼ እቅፍ አደርግሻለሁ..ግን ከተኛሽ በኃላ ነው የምመጣው"
"አባዬ ደስ የሚል ጫወታ ነው ...በቃ ሳልዘጋው ነው የምተኛው..ነገ ከዝግጅቱ በኃላ ደውልልሀለሁ.ወድሀለሁ።››
"እኔም ወድሻለሁ "ስልኩ ተዘጋ..
የእኔም ወደሆቴሌ የመመለስ አፒታይቴም አብሮ ተዘጋ፤
"ምን ላድርግ?"ከሀያ ደቂቃ በላይ ባለሁበት ቦታ ተገትሬ ማሰብ እንኳን አቅቶኝ ደንዝዤ ቆየሁ።ወደጓሮ ሄድኩ ..፡፡.ካልተቀየረች አንድ ወደጊቢ ዘሎ መግቢያ ምቹ ቦታ ነበረች..አዎ አገኘኋት።ዙሪያ ገባውን ዞር ዞር ብዬ ሰው አለመኖሩ አረጋገጥኩና እንደምንም ተንጠላጥዬ ዘልዬ ግቢውስጥ ገባሁ። ድሮ የሀይእስኩል ተማሪ እያለሁ በተለያየ ምክንያት ውጭ ሳመሽና በራፍ ሲዘጋብኝ በዚህ ዘዴ ነበር ወደ ውስጥ የምገባው..፡፡ይሄው የዛን ጊዜው ልምድ ለዛሬ ረዳኝ።
የውጭ መብራት ስለጠፍ ግቢው በፀጥታና በጭለማ ተውጧል።ኮቴዬን ሳላሰማ ቀስ ብዬ ወደልጄ ክፍል ማለት ወደእኔ የድሮ ክፍል አመራሁ...፡፡ወይ የእኔ ማር እንዳልኳት መስኮቱን ከፍታ ነው የተኛችው። እንደምንም ተንጠላጠልኩና መስኮቱ ላይ ወጣሁ ..ደግነቱ መስኮቱ አጠር ስለሚል በተለይ ከእኔ ቁመት አንፃር አልተቸገርኩም፡፡ በቀላሉ ወደላይ ወጣሁና እግሬን አሽከርክሬ ወደውስጥ ገባሁ፡፡ ልጄን እንዳላስደነግጣት ተጠንቅቄ ወደማብሪያ ማጥፊያው አመራሁ..፡፡አብዛኛውን ዕድሜዬን የኖርኩበት ቤት መሆኑ ነገሮች የት የት እንደሆኑ በቀላሉ ለመለየት ረድቶኛል ። መብራቱን አበራሁ።ልጄ እንዴት አድጋለች..ደግሞ አተኛኞ ልክ እንደናቷ ዝርግትግት ብላ ነው።በቅርቤ ያገኘኋት ኩርሲ መቀመጫ ወደአልጋዎ አስጠጋሁና ቁጭ አልኩ ...፡፡ጭንቅላቴን ሸፍኜበት የነበረውን ኮፍያ ከላዬ ላይ ገፍፌ ጣልኩት።አይኔ ላይ ሰክቼ የነበረውን መነፅር አወለቅኩና በአቅራቢዬ ያለ ትንሽ ጠረጰዛ ላይ አስቀመጥኩ። ሙሉ ትኩረቴን ወደልጄ ሰበሰብኩ።እጆቼን በእርጋታ ወደጭንቅላቷ ሰደድኩ .."ቀስ ብዬ ስዳብሳት አይኖቾን ገለጠች...፡፡ደነገጥኩና እጄን ሰበሰብኩ...እሪ ብላ የምትጮህ መሠሎኝ ፈራሁ። ምን ላድርግ...?ፈጠን ብዬ ዘልዬ እንደአመጣጤ ልውጣ እንዴ?ብዙ ነገር አስቤ አንድንም ሳላደርግ
"አባዬ....ህልም አይደለም አይደል..?"አለችኝ፡፡
"አይደለም የእኔ ማር ...››በተኛችበት ጉንጮቾን ሞጨሞጭኳት...እሷም እጇቾን በአንገቴ ዙሪያ ጠመጠመችና ግንባሬን፤ጉንጬን ፤አገጬን ምንም የቀራት ቦታ የለም...ሙሉ በሙሉ ንቁ ሆና አልጋዎ መካከል ቁጭ አለች።
"አባዬ እኔ እኮ እመጣለሁ ስትለኝ በህልሜ መስሎኝ ነው ቶሎ የተኛሁት።
"በጣም ስለናፈቅሺኝና ..ነገ የደረጃ ተማሪ ሆነሽ ልትሸለሚ ስለሆነ እኔ አባትሽ በጣም ኩራት ስለተሰማኝ እንዴ ተደብቄም ቢሆን በዚህ ቀን ልጄን ካላየኋት እኔ ምን አይነት አባት ነኝ ?ብዬ ነው በዚህ ለሊት ሹልክ ብዬ ክፍልሽ የተገኘሁት።
"አባቴ ውድድድ ነው የማደርግህ...አሁን አቅፍቅፍ ብለን እንተኛ"
"ግን አቴቴ ለሊት ልታይሽ ብትመጣስ?"
"አትመጣም ..ደግሞ እኮ ከውስጥ ተቀርቅሯል ..ብትመጣም ገና ስታንኳኳ ቶሎ ብለህ በመስኮት ትሄዳለህ"
"ምን አይነት ብልጥ ልጅ ነው ያለኝ"አልኩና ከላይ የለበስኩትን ጃኬት በማውለቅ ጠረጳዛ ላይ አኑሬ አልጋ ላይ ወጣሁ..ይሄ አልጋ የእኔና የእናትሽ እንደነበር ታውቂያለሽ?"
"አዎ …ለዛ እኮነው ክፍሌንም አልጋዬንም የምወደው"
#ባል_አስይዞ_ቁማር
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
ሰዓቱ 11.10 ነው።22 አንድ ካፌ ውስጥ ቁጭ ብላለች።ብቻዋን ነው ያለችው...ስልኳን አወጣችና ደወለች።
‹‹ሀይ ቃልዬ እንዴት ነህ?››
‹‹አለሁ ልዩ ደህና ነሽ?››
‹‹አለሁ ...ከስራ አልወጣህም እንዴ?››
‹‹ወጥቼያለሁ ..መገናኛ ነኝ።››
"ለምን መክሰስ አልጋብዝህም 22 ነው ያለሁት"
"ደስ ይለኝ ነበር.. ግን አሁን ጊፍቲ ደውላ ሰፈር እየጠበቅኩህ ነው ስላለቺኝ ወደእዛው ልሄድ ነው"እንደዛ ያላት አውቆ ነው…ልዩ እንገናኝ ካለችው ጊፍቲንም ይዟት ሊሄድ ስለፈለገ ነው…
"ሰፈር ማለት አንተ ቤት ?"
‹‹አዎ"
‹‹ለምን ይዘሀት አትመጣም..እንደውም አሪፍ ነው?"
አንዳሰበው ስለሆነለት ፈገግ አለ"ልጠይቃትና መልሼ ልደውልልሽ"
"እሺ ቃልዬ...እዛው ቁጭ ብዬ ጠብቃለሁ"አለችውና ስልኩ ተዘጋ። ከጨጓራዋ አካባቢ የተነሳ ቃጠሎ ጉሮሮዋ ድረስ ሲሰማት ታወቀት፡፡
ቃል የልዩን ስልክ እንደዘጋ ወደ ጊፍቲ ደወለ፡፡
‹‹ሄሎ ቃለዬ..፡፡››
‹‹አለሁልሽ ጊፍቲ.ላግኝሽ?››
‹‹ደስ ይለኛል..መክሰስ ልትጋብዘኝ ነው ወይስ እራት?››
‹‹አይ መክስ ነው.. ግን ጋባዡ እኔ አይደለሁም.›
‹‹ችግር የለውም እኔ ጋብዝሀለው››
‹‹አይ ጋባዥ አለን›
‹‹ማን?››
ልዩ ደውላልኝ ነበረ ..ልጋብዛችሁ ስላልች ነው የደወልኩልሽ››
ቅሬታዋን መደበቅ አልቻለችም‹‹ቃል ግን እሷ ልጅ…››አንጠልጥላ ተወችው፡፡
‹‹እሷ ልጅ ምን…?››
‹‹እኔ እንጃ ነገረ ስራዋ አያምረኝም…ሌላ አላማ ያላት ይመስለኛል››
እንዳልገባው ሆነ‹ሌላ አላማ ስትይ..?››
‹‹ያው ማለቴ ምትወድህ ይመስለኛል..››
ደስ አለው…..አዎ ቅናት እየጀመራት ነው ሲል አሰበ..‹‹ብትወደኝ ምን ችግር አለው? ጓደኛዬ አይደለች..››
‹‹ቃል ደግሞ… እንደዛ ለማለት ፈልጌ አይደለም.ምታፈቅርህ ይመስለኛል.ደግሞ ይመስለኛል አይደለም እርግጠኛ ነኝ…››
‹‹አረ ተይ .እኔ ምንም እንደዛ አይነት ስሜት አላየሁባትም.ደግሞ ፍቅረኛዬ እንደሆንሽ ነግሬታለሁ እኮ››
ቢሆንም ተጠንቀቃት.ለማንኛውም የት ነህ ልምጣ.››ያለበትን ቦታ ነገራትና በፈግታ ስልኩን ዘግቶ ለልዩ እንደሚመጡ ለመናገር ደወለላት፡፡
"ይህቺ ጊፋቲ የምትባል ሴት እንዴት ላስወግዳት?"ልዩ እራሷን ጠየቀች... ...ስልኳ ተንጫረረ ..ቃል ነው.. ቀና መልስ እንዲመልስላት በውስጧ እየፀለየች አነሳችው፡፡
"እሺ ቃል?"
"15 20 ደቂቃ እናስጠብቅሻለን።
"ችግር የለውም አንድ ሰዓትም ቢሆን እጠብቃችኋለው"አለችና በደስታ ያለችበትን ካፌ ስም ነግራቸው ስልኳን ዘጋችው፡፡
በራሷ ሁኔታ መገረም ጀመረች"ወይ ጉዴ.. አንድ ሰዓትም ቢሆን እጠብቃችኃለው"ስል አሁን መድህኔ ቢሰማ ጭንቅላቱን ይዞ ነው የሚጮኸው...›አለች እንዲህ ልትል የቻለችበት ምክንያት 5 ደቂቃ አረፈድክ ብላ ብዙ ቀን ጮኸበታለች...አስር ደቂቃ አርፍዶ ቀጠሮውን ሰርዛ ጥላው የሄደችበትም ቀናቶች ጥቂት አይደሉም።
እንዳሉትም ከ20 ደቂቃ በኃላ እጅ ለእጅ ተያይዘው ፊቷ ተከሰቱ፡..መጀመሪያ ልክ እንደረጅም ጊዜ የልብ ጓደኛዋ እሷ ላይ ተጠመጠመችባት ..አገላብጣ ጉንጮቾን ሳመቻት...ጊፍቲ ያልጠበቀችው አይነት አቀባበል ስለሆነ ግር እንዳላት ከሁኔታዎ ያስታውቃል...እሷ እራሷ ለምን እንደዛ ኦቨር አክት እንዳደረገች አልገባትም ‹‹...ምን አልባት የይሁዳን መሳም ይሆናል የሳምኳት..››ስትል እራሷን ታዘበች፡፡.ቃልን ከእሷ መለስ ባለ ሰላምታ ሰላም አለችውና ሁለቱም ከፊት ለፊቷ ወንበር ስበው ሊቀመጡ ሲሉ‹‹..አይ ቆይ እንውጣ"አለቻቸው፡፡
"ምነው ታሳፍሪኛለሽ ..መክሰስ ትጋብዘናለች ብዬ እኮ ነው ይዤት የመጣሁት..መክሰሱ ቢቀር ቢያንስ ሻይ ጋብዢን እንጂ"ሲል ቀለደ
"አይ የመክሰሱን ሰዓትማ አሳለፍችሁት አሁን የእራት ሰዓት ነው...እራት የሚገኝበት ቤት እንሂድ.."
‹‹እሱ የተሻለና የተቀደሰ ሀሳብ ነው"አለች ጊፍቲ ...
ተያይዘው ወጡና መኪናዋ ውስጥ ገቡ… ወደ ዪሆሚያ ክትፎ ቤት ይዛቸው ሄደች ...እዛ ገብተው እስፔሻል ክትፎቸውን አዘው ቀላል ጫወታዎችን እየተጫወቱ ..በልተው ሲያጠናቅቁ አንድ ሰዓት ከሩብ ሆኖ ነበር። ሂሳብ ልትከፍል ስትጠይቅ ተከፍሏል አሏት...ልቆጣጠረው የማትችለው ንዴት ተናነቃት፡፡..
‹‹ማን ነው የከፈለው ...?››ፊት ለፊቷ ያሉት ቃልና ጊፍቲ ላይ አፈጠጠችባቸው።ሁለቱም ደንግጠው እርስ በርስ ተያዩ ..."አረ ተረጋጊ እኛ አልከፈልንም"አለት ቃል።
"ማን ነው የከፈለው?"አስተናጋጅን ጠርታ ጠየቀችው፡፡
"ጋሽ መድህኔ ነው"
ተረጋጋች"እሱ ደግሞ ከእዚህ ቤት አይጠፍም" ስትል በውስጧ አልጎመጎመች፡
"መድህኔ ማን ነው?"ብላ ጠየቀቻት
‹‹ እስቲ አሁን ሆነ ብላ እኔን ለማሳቀቅ ካልሆነ የመድህኔ ማንነት ምን ይረባታል..? በውስጧ ነው ምታወራው…ቀና ብላ ቃልን ስታየው እሱም የመድህኔን ማንነት ለማወቅ የጓጓ መሆኑን በሚያሳብቅ አስተያየት ነው እያየት ያለው..ለተጠየቀችው ጥያቄ መልስ ከመመለስ ውጭ ሌላ ምርጫ እንደሌላት ግልፅ ሆነላት፡፡ምን ብላ ትመልስ…ግራ ገባት" መድህኔ ጓደኛዬ...ማለቴ ፍቅረኛዬ ነው"አለች፡፡
‹‹የት አለ አስተዋውቂና አረ ጥሪው"ጊፍቲ አሽቃበጠች….፡፡
ልዩ አሁንም የሆነ ነገር ለማድረግ ከአባቱ ፍቃድ እንደሚፈልግ ህፃን በቆረጣ ቃልን አየችው፡፡
ቃልም ልክ ከዚህ በፊት መድሀኒ የተባለወን ስም እንዳልሰማ በማስመሰል "አዎ ጥሪውና እናመስግነው...በዛውም እንተዋወቀዋለን"አላት
"ደወለችለት"
"አንተ የት ነህ?"
"ውስጥ ነኝ ..እጄን እየታጠብኩ"
‹‹ታዲያ ሰላም አትለንም እንዴ?"
‹‹መጣሁ"ከ3 ደቂቃ በኃላ መድህኔ እንደወትሮ ዝንጥ ብሎ በሱፍ እንደታነቀ ፊት ለፊታችን ገጭ አለ...
‹‹ተዋወቁት መድህኔ ማለት እሱ ነው"በየተራ እየጨበጠ ተዋወቃቸው..
"ስለተዋወቅኩህ ደስ ብሎኛል...ልዩ ግን ይሄን የመሰለ ሸበላ ባል እንዳለሽ ለምን እስከዛሬ ደበቅሽኝ?"አለቻት ልዩ ተሸማቀች፡፡ የጊፍቲን ንግግር ለሚሰማ ሰው የሁለቱ ትውውቅና የጓደኝነት ታሪክ አመታትን ያስቆጠረ ነው ሚመስለው? ልዩ ከውስጧ እየታገለች ዝም አለች
..ቃል ‹‹ቁጭ በላ›› አለው ቦታ እያመቻቸለት
"ቆይ ጓደኞቼን ተሠናብቼ ልምጣ ››አለ
ልዩ ግን መድሀኔ ተመልሶ እንዲመጣና እንዲቀላቀላቸው ስላልፈለገች..."አይ ለምን እኛም እኮ ልንወጣ ነው"አለችው፡
"እኮ 2 ደቂቃ ብቻ ጠብቁኝና አብረን እንወጣለን ..እንዴ ክትፎ በልቶ ደግሞ አንድ ሁለት ሳይባል ቢገባ ጥሩ አይደለም...እራት እኔ አይደል የጋበዝኮችሁ አንቺና ጓደኞችሽ ደግሞ መጠጥ ትጋብዙኛላችሁ ...››ብሎ መልስ ሳይጠብቅ ዞሮ ሄደ...ሳታስበው እንደውም ጥሩ ሀሳብ ነው..
ወደእነ ቃል ዞራ "ሰዎች እንግዲህ ቻሉት.. መድህኔ ካለ አለ ነው "አለች
ጊፍቲ"እንዲህ አይነት ድንገተኛ ግብዣ ተገኝቶ ነው...ጭፈራ ቤት ብንሄድ ደግሞ እንዴት ደስ ይለኛል መሰለሽ" ስትል ተቅለብልባ መለሰችላት..ቃል ዞር ብሎ አያትና"በቃ አንቺና ጭፈራ መች ነው የምትለያዩት"አለ፡፡
"ጭፈራ ትወጂያለሽ እንዴ?"ልዩ ነች ጠያቂዋ፡
"አትጠይቂኝ… ጭፈራ ከመውደዴ የተነሳ አንድ አመት ዲጄ ሆኜ ሰርቼያለሁ... "
‹‹አንግዲያው ከመድህኔ ጋር በጠም ትጣጣማለችሁ ማለት ነው›ሥትል ከኃላዋ መድህኔ መጣና በምንድነው የምንጣጣመው? ››ሲል ያልተዘጋጀችበትን ድንገተኛ ጥያቄ ጠየቀቻት፡፡…
‹‹ በቅርቡ ልታየው አይደል ››በማለት ድፍን ያለ መልስ መለስችለትና ተያይዘን ወጡ ...
✨ይቀጥላል✨
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
ሰዓቱ 11.10 ነው።22 አንድ ካፌ ውስጥ ቁጭ ብላለች።ብቻዋን ነው ያለችው...ስልኳን አወጣችና ደወለች።
‹‹ሀይ ቃልዬ እንዴት ነህ?››
‹‹አለሁ ልዩ ደህና ነሽ?››
‹‹አለሁ ...ከስራ አልወጣህም እንዴ?››
‹‹ወጥቼያለሁ ..መገናኛ ነኝ።››
"ለምን መክሰስ አልጋብዝህም 22 ነው ያለሁት"
"ደስ ይለኝ ነበር.. ግን አሁን ጊፍቲ ደውላ ሰፈር እየጠበቅኩህ ነው ስላለቺኝ ወደእዛው ልሄድ ነው"እንደዛ ያላት አውቆ ነው…ልዩ እንገናኝ ካለችው ጊፍቲንም ይዟት ሊሄድ ስለፈለገ ነው…
"ሰፈር ማለት አንተ ቤት ?"
‹‹አዎ"
‹‹ለምን ይዘሀት አትመጣም..እንደውም አሪፍ ነው?"
አንዳሰበው ስለሆነለት ፈገግ አለ"ልጠይቃትና መልሼ ልደውልልሽ"
"እሺ ቃልዬ...እዛው ቁጭ ብዬ ጠብቃለሁ"አለችውና ስልኩ ተዘጋ። ከጨጓራዋ አካባቢ የተነሳ ቃጠሎ ጉሮሮዋ ድረስ ሲሰማት ታወቀት፡፡
ቃል የልዩን ስልክ እንደዘጋ ወደ ጊፍቲ ደወለ፡፡
‹‹ሄሎ ቃለዬ..፡፡››
‹‹አለሁልሽ ጊፍቲ.ላግኝሽ?››
‹‹ደስ ይለኛል..መክሰስ ልትጋብዘኝ ነው ወይስ እራት?››
‹‹አይ መክስ ነው.. ግን ጋባዡ እኔ አይደለሁም.›
‹‹ችግር የለውም እኔ ጋብዝሀለው››
‹‹አይ ጋባዥ አለን›
‹‹ማን?››
ልዩ ደውላልኝ ነበረ ..ልጋብዛችሁ ስላልች ነው የደወልኩልሽ››
ቅሬታዋን መደበቅ አልቻለችም‹‹ቃል ግን እሷ ልጅ…››አንጠልጥላ ተወችው፡፡
‹‹እሷ ልጅ ምን…?››
‹‹እኔ እንጃ ነገረ ስራዋ አያምረኝም…ሌላ አላማ ያላት ይመስለኛል››
እንዳልገባው ሆነ‹ሌላ አላማ ስትይ..?››
‹‹ያው ማለቴ ምትወድህ ይመስለኛል..››
ደስ አለው…..አዎ ቅናት እየጀመራት ነው ሲል አሰበ..‹‹ብትወደኝ ምን ችግር አለው? ጓደኛዬ አይደለች..››
‹‹ቃል ደግሞ… እንደዛ ለማለት ፈልጌ አይደለም.ምታፈቅርህ ይመስለኛል.ደግሞ ይመስለኛል አይደለም እርግጠኛ ነኝ…››
‹‹አረ ተይ .እኔ ምንም እንደዛ አይነት ስሜት አላየሁባትም.ደግሞ ፍቅረኛዬ እንደሆንሽ ነግሬታለሁ እኮ››
ቢሆንም ተጠንቀቃት.ለማንኛውም የት ነህ ልምጣ.››ያለበትን ቦታ ነገራትና በፈግታ ስልኩን ዘግቶ ለልዩ እንደሚመጡ ለመናገር ደወለላት፡፡
"ይህቺ ጊፋቲ የምትባል ሴት እንዴት ላስወግዳት?"ልዩ እራሷን ጠየቀች... ...ስልኳ ተንጫረረ ..ቃል ነው.. ቀና መልስ እንዲመልስላት በውስጧ እየፀለየች አነሳችው፡፡
"እሺ ቃል?"
"15 20 ደቂቃ እናስጠብቅሻለን።
"ችግር የለውም አንድ ሰዓትም ቢሆን እጠብቃችኋለው"አለችና በደስታ ያለችበትን ካፌ ስም ነግራቸው ስልኳን ዘጋችው፡፡
በራሷ ሁኔታ መገረም ጀመረች"ወይ ጉዴ.. አንድ ሰዓትም ቢሆን እጠብቃችኃለው"ስል አሁን መድህኔ ቢሰማ ጭንቅላቱን ይዞ ነው የሚጮኸው...›አለች እንዲህ ልትል የቻለችበት ምክንያት 5 ደቂቃ አረፈድክ ብላ ብዙ ቀን ጮኸበታለች...አስር ደቂቃ አርፍዶ ቀጠሮውን ሰርዛ ጥላው የሄደችበትም ቀናቶች ጥቂት አይደሉም።
እንዳሉትም ከ20 ደቂቃ በኃላ እጅ ለእጅ ተያይዘው ፊቷ ተከሰቱ፡..መጀመሪያ ልክ እንደረጅም ጊዜ የልብ ጓደኛዋ እሷ ላይ ተጠመጠመችባት ..አገላብጣ ጉንጮቾን ሳመቻት...ጊፍቲ ያልጠበቀችው አይነት አቀባበል ስለሆነ ግር እንዳላት ከሁኔታዎ ያስታውቃል...እሷ እራሷ ለምን እንደዛ ኦቨር አክት እንዳደረገች አልገባትም ‹‹...ምን አልባት የይሁዳን መሳም ይሆናል የሳምኳት..››ስትል እራሷን ታዘበች፡፡.ቃልን ከእሷ መለስ ባለ ሰላምታ ሰላም አለችውና ሁለቱም ከፊት ለፊቷ ወንበር ስበው ሊቀመጡ ሲሉ‹‹..አይ ቆይ እንውጣ"አለቻቸው፡፡
"ምነው ታሳፍሪኛለሽ ..መክሰስ ትጋብዘናለች ብዬ እኮ ነው ይዤት የመጣሁት..መክሰሱ ቢቀር ቢያንስ ሻይ ጋብዢን እንጂ"ሲል ቀለደ
"አይ የመክሰሱን ሰዓትማ አሳለፍችሁት አሁን የእራት ሰዓት ነው...እራት የሚገኝበት ቤት እንሂድ.."
‹‹እሱ የተሻለና የተቀደሰ ሀሳብ ነው"አለች ጊፍቲ ...
ተያይዘው ወጡና መኪናዋ ውስጥ ገቡ… ወደ ዪሆሚያ ክትፎ ቤት ይዛቸው ሄደች ...እዛ ገብተው እስፔሻል ክትፎቸውን አዘው ቀላል ጫወታዎችን እየተጫወቱ ..በልተው ሲያጠናቅቁ አንድ ሰዓት ከሩብ ሆኖ ነበር። ሂሳብ ልትከፍል ስትጠይቅ ተከፍሏል አሏት...ልቆጣጠረው የማትችለው ንዴት ተናነቃት፡፡..
‹‹ማን ነው የከፈለው ...?››ፊት ለፊቷ ያሉት ቃልና ጊፍቲ ላይ አፈጠጠችባቸው።ሁለቱም ደንግጠው እርስ በርስ ተያዩ ..."አረ ተረጋጊ እኛ አልከፈልንም"አለት ቃል።
"ማን ነው የከፈለው?"አስተናጋጅን ጠርታ ጠየቀችው፡፡
"ጋሽ መድህኔ ነው"
ተረጋጋች"እሱ ደግሞ ከእዚህ ቤት አይጠፍም" ስትል በውስጧ አልጎመጎመች፡
"መድህኔ ማን ነው?"ብላ ጠየቀቻት
‹‹ እስቲ አሁን ሆነ ብላ እኔን ለማሳቀቅ ካልሆነ የመድህኔ ማንነት ምን ይረባታል..? በውስጧ ነው ምታወራው…ቀና ብላ ቃልን ስታየው እሱም የመድህኔን ማንነት ለማወቅ የጓጓ መሆኑን በሚያሳብቅ አስተያየት ነው እያየት ያለው..ለተጠየቀችው ጥያቄ መልስ ከመመለስ ውጭ ሌላ ምርጫ እንደሌላት ግልፅ ሆነላት፡፡ምን ብላ ትመልስ…ግራ ገባት" መድህኔ ጓደኛዬ...ማለቴ ፍቅረኛዬ ነው"አለች፡፡
‹‹የት አለ አስተዋውቂና አረ ጥሪው"ጊፍቲ አሽቃበጠች….፡፡
ልዩ አሁንም የሆነ ነገር ለማድረግ ከአባቱ ፍቃድ እንደሚፈልግ ህፃን በቆረጣ ቃልን አየችው፡፡
ቃልም ልክ ከዚህ በፊት መድሀኒ የተባለወን ስም እንዳልሰማ በማስመሰል "አዎ ጥሪውና እናመስግነው...በዛውም እንተዋወቀዋለን"አላት
"ደወለችለት"
"አንተ የት ነህ?"
"ውስጥ ነኝ ..እጄን እየታጠብኩ"
‹‹ታዲያ ሰላም አትለንም እንዴ?"
‹‹መጣሁ"ከ3 ደቂቃ በኃላ መድህኔ እንደወትሮ ዝንጥ ብሎ በሱፍ እንደታነቀ ፊት ለፊታችን ገጭ አለ...
‹‹ተዋወቁት መድህኔ ማለት እሱ ነው"በየተራ እየጨበጠ ተዋወቃቸው..
"ስለተዋወቅኩህ ደስ ብሎኛል...ልዩ ግን ይሄን የመሰለ ሸበላ ባል እንዳለሽ ለምን እስከዛሬ ደበቅሽኝ?"አለቻት ልዩ ተሸማቀች፡፡ የጊፍቲን ንግግር ለሚሰማ ሰው የሁለቱ ትውውቅና የጓደኝነት ታሪክ አመታትን ያስቆጠረ ነው ሚመስለው? ልዩ ከውስጧ እየታገለች ዝም አለች
..ቃል ‹‹ቁጭ በላ›› አለው ቦታ እያመቻቸለት
"ቆይ ጓደኞቼን ተሠናብቼ ልምጣ ››አለ
ልዩ ግን መድሀኔ ተመልሶ እንዲመጣና እንዲቀላቀላቸው ስላልፈለገች..."አይ ለምን እኛም እኮ ልንወጣ ነው"አለችው፡
"እኮ 2 ደቂቃ ብቻ ጠብቁኝና አብረን እንወጣለን ..እንዴ ክትፎ በልቶ ደግሞ አንድ ሁለት ሳይባል ቢገባ ጥሩ አይደለም...እራት እኔ አይደል የጋበዝኮችሁ አንቺና ጓደኞችሽ ደግሞ መጠጥ ትጋብዙኛላችሁ ...››ብሎ መልስ ሳይጠብቅ ዞሮ ሄደ...ሳታስበው እንደውም ጥሩ ሀሳብ ነው..
ወደእነ ቃል ዞራ "ሰዎች እንግዲህ ቻሉት.. መድህኔ ካለ አለ ነው "አለች
ጊፍቲ"እንዲህ አይነት ድንገተኛ ግብዣ ተገኝቶ ነው...ጭፈራ ቤት ብንሄድ ደግሞ እንዴት ደስ ይለኛል መሰለሽ" ስትል ተቅለብልባ መለሰችላት..ቃል ዞር ብሎ አያትና"በቃ አንቺና ጭፈራ መች ነው የምትለያዩት"አለ፡፡
"ጭፈራ ትወጂያለሽ እንዴ?"ልዩ ነች ጠያቂዋ፡
"አትጠይቂኝ… ጭፈራ ከመውደዴ የተነሳ አንድ አመት ዲጄ ሆኜ ሰርቼያለሁ... "
‹‹አንግዲያው ከመድህኔ ጋር በጠም ትጣጣማለችሁ ማለት ነው›ሥትል ከኃላዋ መድህኔ መጣና በምንድነው የምንጣጣመው? ››ሲል ያልተዘጋጀችበትን ድንገተኛ ጥያቄ ጠየቀቻት፡፡…
‹‹ በቅርቡ ልታየው አይደል ››በማለት ድፍን ያለ መልስ መለስችለትና ተያይዘን ወጡ ...
✨ይቀጥላል✨
#ታምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
/
ዙሪያቸውን ሲያዩ ነግቷል …ቢያንስ 12 ሰዓት ሆኗል….ሁለቱም ከተጣበቁበት ተላቀው ልብሳቸውን ከየወዳደቀበት በመለቃቀም መልበስ ጀመሩ ..ኬድሮን መጀመሪያ ቀሚሷን አንስታ አጠለቀች….ቀጥሎ ፓንቷን ስታነሳ ቦታው ላይ የተወሰነ የተበታተነ ድንጋዬች በደም ነጠብጣብ ቀልመዋል…አንዱን ድንጋይ አነሳችና ሱሪውን ለብሶ ጨርሶ ቲሸርቱን በመልበስ ላይ ወደአለው አንድሪው ተጠጋችና በእጆቹ አስጨበጣችው.. በአካባቢው የተሰበሰቡትን ሰዎችን ከቁብ ሳትቆጥር ጉንጩን ሳመችና አጀቡን ሰንጥቃ በተረጋጋና በሰከነ ሁኔታ ወደድንኳኑ ተመለሰች….ስትደርስ ንስሯ ሻንጣው ላይ ቁጭ ብሎ የትዝብት በመሰለ አስተያየት እየተመከለታት ነበር ..ቶሎ ብላ አገልግሏን አነሳችና ትከሻዋ ላይ አንጠለጠለች፡፡ ንስሩን ገፈትራ አስነስታ ሻንጣውንም አነሳች‹‹ጀግናዬ በል ቶሎ እንሂድ ››አለችው ንስሯን፡፡
ጊዜ አላጠፋም….ክንፉን ዘረጋና ወደላይ ከፍ ብሎ አንጠለጠላት..እይታዋን አንድሪውን ጥላ ወደመጣችበት አቅጣጫ ስታማትር እሱ ከፊት እየመራ ሌሎች ከኃላ እየተከተሉት እሷ ወዳለችበት አቅጣጫ እየሮጠ ነው፡፡በመቶ ሜትር ከፍታ ላይ ሆና እጇን ለስንብት አውለበለበችለት…. ጥላው እንዳትሄድ በእጁም እየተወራጨ በእግሮቹ መሬቱን እየተመተመ፤ በአንደበቱም ጉሮሮው እስኪሰነጠቅ እየጮኸ ተማፀናት…ልቧ ራርቶ ልትመለስ አልቻለችም….ሶስት መቶ ሜትር ከፍታ ላይ ስትደርስ ተስፋ ቆርጦ መሬት ላይ ዝርፍጥ አለ…..ከዛ ከእይታው ተሰወረች .፡፡
አምስት ሰዓት አካባቢ ከበረሩ በኃላ ነው ኬንያ ድንበር ሞምባሳ ወደብ ተጠግቶ ከሚገኝ ኢንዲያና ውቅያኖስ ውስጥ የጣላት፡፡እሱ አገልግሏንና ሻንጣውን ይዞ ወደ ዳር በረረና ዋኝታ ጨርሳ ሰእስክትመጣ ዛፍ ላይ በመቀመጥ እረፍት በመውሰድ ይጠብቃት ጀመር፡፡
የተለየ ምሽተና የተለየ ለሊት ነበር ያሳለፈችው….እና በወሲብ ወቅት የወራዛውን ላቧን መሬት ላይ ስትንከባለል በአቧራ የቆሸሸና ሰውነቷን ድንግልናዋን ስታስረክብ በጭኗ መካከል ተንሻሮ የተንጣበጠበ ደሟን በኢንድያና ውቅያኖስ ጨዋማ ውሀ እያጠበችውና እያፀዳአቸው ነው……አሁን ትናንት የነበረችውን ኬድሮንን አይደለችም….ሴት ከመሆኗ ጋር ተያይዞ ሌላ የሆነ የተከፈተላት የኃይል በር እንዳለ እየተሰማት ነው…..አንድሪውን ወዳዋለች…..ከእሱ ጋር በፈፀመችው ነገር ምንም አይነት ፀፀት እየተሰማት አይደለም…እንደውም በተቃራኒው የተለየ አይነት እርካታን የመሞላትና የመባረክ ስሜት ነው እየተሰማት ያለው…..ለምን ተጨማሪ ጊዜ ከእሱ ጋር እዳላሳለፈች አታውቅም…..የማትቆጣጣረው ኃይል በአስቸካይ አካባቢውን ለቃ እንድትወጣ አስገድዷታል…እንጂማ ቢያንስ አንድ ተጨማሪ ቀንና አንድ ተጨማሪ ወሲብ ከአንድሪው ጋር ቢኖራት ፍፅም ደስተኛ ትሆን ነበር፡፡
የሰውነቷንም ሆነ የሀሳቧንም ቆሻሻ እዛው ኢንዲያና ውቅያኖስ ላይ ካራገፈች በኃላ ወደወደቡ ዳር ወጥታ ንስሯ ወዳለበት ቦታ ሄደችና እሱ ባለበት ዛፍ ስር ቁጭ አለች…..ከላይ ካለበት የዛፉ ጫፍ ሻንጣውን እና አገልግሉን ይዞ በሮ በመውረድ ከጎኗ አረፈ…..ሻንጣዋን ከፈተችና ሌላ ቀሚሰ በማውጣት የለበሰችውንና የረጠበውን ቀሚስ በማውለቅ ደህናውን ለበሰችና እርጥቡን ጨምቃ የግንዱ ቅርንጫፍ ላይ አሰጣችው፡፡
ከዛ አገልግሉን ወደራሷ አስጠጋችና እናቷ ከቆጠረችላት ገና ግማሹን እንኳን ያልተበላለት ጩኮ ከፈተችና ለመብላት ተዘጋጀች…ንስሯ አፍጥጦ ሲያያት ነበር ‹‹..ወይ ይቅርታ አንተም ለካ እርቦሀል….››ብላ ሄደህ የሚታደን ነገር ፈልገህ ተመገብ …ታዲያ ከ30 ደቂቃ በላይ እንዳትቆይ….››አለችው
ልክ እንደ ሰው ያለችውን በፅሞና ሰምቶ በአየር ላይ ተንሳፈፈና ሰማዩን ሰንጥቆ ከእይታዋ ተሰወረ…..እሷም ጩኮዋን እየቆረሰች በኮዳዋ በያዘችው ውሀ እየማገች መመገብ ጀመረች…እስክትጠግብ ከበላች በኃላ .. ግንዱን ተደግፋ ጋደም ብላ ስለአንድሪው እያሰበች የንስሯን መምጣት እየተጠባበቀች ነው….20 ደቂቃ በኃላ ንስሯ በመንቁሩ የሆነ ቦርሳ ነገር አንጠልጥሎ መጣ ፤ግራ ገባት… ስሯ አረፈ….
‹‹የሚበላ ይዘህ ና አልኩህ እንጂ ቦርሳ አልኩህ?››
እጇ ላይ አስቀመጠላት…..የሚያምር አነስተኛ የእጅ ቦርሳ ነው፡፡ተቀበለችውና ከፈተችው…የሚያብረቀርቁና አይን ላይ ብዙ አይንት ቀላማትን ሚረጩ ሁለት የእጅ መዳፍ ያህል መጠን የሚሆኑ ጌጦች ናቸው››
‹‹ምንድናቸው…?››ንስሯን ጠየቀችው…፡፡
አእምሮውን ከፈተላት…አልማዝ እንደሆነ አወቀች፡፡
‹ከየት አመጣኸው?››
ባህሩ መሀከል …የመርከብ ዘራፊዎች እርስ በርስ እየተገዳደሉ አንድ ሌላውን ሲዘርፍ ከመሀከላቸው ነጥቆ እንዳመጣ ምስሉን በአእምሮዋ ልኮ እንድታውቀው አደረጋት፡፡
‹‹ስንት ያወጣል……?››
‹‹የአንድ ሻንጣ ብር ምስሉን በእምሮዋ አሳያት……እስከዚህን ዕድሜዋ ድረስ ስለገንዘብ እስባም ሆነ ተጨንቃ አታውቅም…አሁን ግን እልማዙን ስታይ ሆነ ስለሚያወጣው ገንዘብ ንስሯ ሲነግራት የተለየ ስሜት ነው የተሰማት…ምን አልባት ይሄ ሴት ከመሆኟ ገራ በውስጧ በቅሎ ያደገ አዲስ ስሜት ሳይሆን እንደማይቀር ገመተች፡፡ብር የሚያስገኛቸውን ነገሮች አንድ በአንድ ማጣጣም ቀጣይ ተግባሮ እንደሚሆን አለመች፡፡
‹‹በል አሁን ወደሀገራችን እንሂድ….የእማዬ ቡና ናፍቆኛል››አለችው፡፡
አንጠልጥሎት በአየር ላይ አዋላትና ዞሮ ከጀርባዋ ተጣበቀ.. ከኬንያ ወደ ኢትዬጵያ አቅጣጫውን አስተካክሎ መብረር ጀመረ፡፡
✨ይቀጥላል✨
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
/
ዙሪያቸውን ሲያዩ ነግቷል …ቢያንስ 12 ሰዓት ሆኗል….ሁለቱም ከተጣበቁበት ተላቀው ልብሳቸውን ከየወዳደቀበት በመለቃቀም መልበስ ጀመሩ ..ኬድሮን መጀመሪያ ቀሚሷን አንስታ አጠለቀች….ቀጥሎ ፓንቷን ስታነሳ ቦታው ላይ የተወሰነ የተበታተነ ድንጋዬች በደም ነጠብጣብ ቀልመዋል…አንዱን ድንጋይ አነሳችና ሱሪውን ለብሶ ጨርሶ ቲሸርቱን በመልበስ ላይ ወደአለው አንድሪው ተጠጋችና በእጆቹ አስጨበጣችው.. በአካባቢው የተሰበሰቡትን ሰዎችን ከቁብ ሳትቆጥር ጉንጩን ሳመችና አጀቡን ሰንጥቃ በተረጋጋና በሰከነ ሁኔታ ወደድንኳኑ ተመለሰች….ስትደርስ ንስሯ ሻንጣው ላይ ቁጭ ብሎ የትዝብት በመሰለ አስተያየት እየተመከለታት ነበር ..ቶሎ ብላ አገልግሏን አነሳችና ትከሻዋ ላይ አንጠለጠለች፡፡ ንስሩን ገፈትራ አስነስታ ሻንጣውንም አነሳች‹‹ጀግናዬ በል ቶሎ እንሂድ ››አለችው ንስሯን፡፡
ጊዜ አላጠፋም….ክንፉን ዘረጋና ወደላይ ከፍ ብሎ አንጠለጠላት..እይታዋን አንድሪውን ጥላ ወደመጣችበት አቅጣጫ ስታማትር እሱ ከፊት እየመራ ሌሎች ከኃላ እየተከተሉት እሷ ወዳለችበት አቅጣጫ እየሮጠ ነው፡፡በመቶ ሜትር ከፍታ ላይ ሆና እጇን ለስንብት አውለበለበችለት…. ጥላው እንዳትሄድ በእጁም እየተወራጨ በእግሮቹ መሬቱን እየተመተመ፤ በአንደበቱም ጉሮሮው እስኪሰነጠቅ እየጮኸ ተማፀናት…ልቧ ራርቶ ልትመለስ አልቻለችም….ሶስት መቶ ሜትር ከፍታ ላይ ስትደርስ ተስፋ ቆርጦ መሬት ላይ ዝርፍጥ አለ…..ከዛ ከእይታው ተሰወረች .፡፡
አምስት ሰዓት አካባቢ ከበረሩ በኃላ ነው ኬንያ ድንበር ሞምባሳ ወደብ ተጠግቶ ከሚገኝ ኢንዲያና ውቅያኖስ ውስጥ የጣላት፡፡እሱ አገልግሏንና ሻንጣውን ይዞ ወደ ዳር በረረና ዋኝታ ጨርሳ ሰእስክትመጣ ዛፍ ላይ በመቀመጥ እረፍት በመውሰድ ይጠብቃት ጀመር፡፡
የተለየ ምሽተና የተለየ ለሊት ነበር ያሳለፈችው….እና በወሲብ ወቅት የወራዛውን ላቧን መሬት ላይ ስትንከባለል በአቧራ የቆሸሸና ሰውነቷን ድንግልናዋን ስታስረክብ በጭኗ መካከል ተንሻሮ የተንጣበጠበ ደሟን በኢንድያና ውቅያኖስ ጨዋማ ውሀ እያጠበችውና እያፀዳአቸው ነው……አሁን ትናንት የነበረችውን ኬድሮንን አይደለችም….ሴት ከመሆኗ ጋር ተያይዞ ሌላ የሆነ የተከፈተላት የኃይል በር እንዳለ እየተሰማት ነው…..አንድሪውን ወዳዋለች…..ከእሱ ጋር በፈፀመችው ነገር ምንም አይነት ፀፀት እየተሰማት አይደለም…እንደውም በተቃራኒው የተለየ አይነት እርካታን የመሞላትና የመባረክ ስሜት ነው እየተሰማት ያለው…..ለምን ተጨማሪ ጊዜ ከእሱ ጋር እዳላሳለፈች አታውቅም…..የማትቆጣጣረው ኃይል በአስቸካይ አካባቢውን ለቃ እንድትወጣ አስገድዷታል…እንጂማ ቢያንስ አንድ ተጨማሪ ቀንና አንድ ተጨማሪ ወሲብ ከአንድሪው ጋር ቢኖራት ፍፅም ደስተኛ ትሆን ነበር፡፡
የሰውነቷንም ሆነ የሀሳቧንም ቆሻሻ እዛው ኢንዲያና ውቅያኖስ ላይ ካራገፈች በኃላ ወደወደቡ ዳር ወጥታ ንስሯ ወዳለበት ቦታ ሄደችና እሱ ባለበት ዛፍ ስር ቁጭ አለች…..ከላይ ካለበት የዛፉ ጫፍ ሻንጣውን እና አገልግሉን ይዞ በሮ በመውረድ ከጎኗ አረፈ…..ሻንጣዋን ከፈተችና ሌላ ቀሚሰ በማውጣት የለበሰችውንና የረጠበውን ቀሚስ በማውለቅ ደህናውን ለበሰችና እርጥቡን ጨምቃ የግንዱ ቅርንጫፍ ላይ አሰጣችው፡፡
ከዛ አገልግሉን ወደራሷ አስጠጋችና እናቷ ከቆጠረችላት ገና ግማሹን እንኳን ያልተበላለት ጩኮ ከፈተችና ለመብላት ተዘጋጀች…ንስሯ አፍጥጦ ሲያያት ነበር ‹‹..ወይ ይቅርታ አንተም ለካ እርቦሀል….››ብላ ሄደህ የሚታደን ነገር ፈልገህ ተመገብ …ታዲያ ከ30 ደቂቃ በላይ እንዳትቆይ….››አለችው
ልክ እንደ ሰው ያለችውን በፅሞና ሰምቶ በአየር ላይ ተንሳፈፈና ሰማዩን ሰንጥቆ ከእይታዋ ተሰወረ…..እሷም ጩኮዋን እየቆረሰች በኮዳዋ በያዘችው ውሀ እየማገች መመገብ ጀመረች…እስክትጠግብ ከበላች በኃላ .. ግንዱን ተደግፋ ጋደም ብላ ስለአንድሪው እያሰበች የንስሯን መምጣት እየተጠባበቀች ነው….20 ደቂቃ በኃላ ንስሯ በመንቁሩ የሆነ ቦርሳ ነገር አንጠልጥሎ መጣ ፤ግራ ገባት… ስሯ አረፈ….
‹‹የሚበላ ይዘህ ና አልኩህ እንጂ ቦርሳ አልኩህ?››
እጇ ላይ አስቀመጠላት…..የሚያምር አነስተኛ የእጅ ቦርሳ ነው፡፡ተቀበለችውና ከፈተችው…የሚያብረቀርቁና አይን ላይ ብዙ አይንት ቀላማትን ሚረጩ ሁለት የእጅ መዳፍ ያህል መጠን የሚሆኑ ጌጦች ናቸው››
‹‹ምንድናቸው…?››ንስሯን ጠየቀችው…፡፡
አእምሮውን ከፈተላት…አልማዝ እንደሆነ አወቀች፡፡
‹ከየት አመጣኸው?››
ባህሩ መሀከል …የመርከብ ዘራፊዎች እርስ በርስ እየተገዳደሉ አንድ ሌላውን ሲዘርፍ ከመሀከላቸው ነጥቆ እንዳመጣ ምስሉን በአእምሮዋ ልኮ እንድታውቀው አደረጋት፡፡
‹‹ስንት ያወጣል……?››
‹‹የአንድ ሻንጣ ብር ምስሉን በእምሮዋ አሳያት……እስከዚህን ዕድሜዋ ድረስ ስለገንዘብ እስባም ሆነ ተጨንቃ አታውቅም…አሁን ግን እልማዙን ስታይ ሆነ ስለሚያወጣው ገንዘብ ንስሯ ሲነግራት የተለየ ስሜት ነው የተሰማት…ምን አልባት ይሄ ሴት ከመሆኟ ገራ በውስጧ በቅሎ ያደገ አዲስ ስሜት ሳይሆን እንደማይቀር ገመተች፡፡ብር የሚያስገኛቸውን ነገሮች አንድ በአንድ ማጣጣም ቀጣይ ተግባሮ እንደሚሆን አለመች፡፡
‹‹በል አሁን ወደሀገራችን እንሂድ….የእማዬ ቡና ናፍቆኛል››አለችው፡፡
አንጠልጥሎት በአየር ላይ አዋላትና ዞሮ ከጀርባዋ ተጣበቀ.. ከኬንያ ወደ ኢትዬጵያ አቅጣጫውን አስተካክሎ መብረር ጀመረ፡፡
✨ይቀጥላል✨
#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
እሁድ ከቀኑ ዘጠኝ ሠዓት
ሁሴን ከነጋ ከትንግርት ጋር አልተያዩም፡፡ ማታ ሲጠጡና ሲጫወቱ እስከ ስምንት ሠዓት ነበር የቆዩት፡፡ ከዛ በኋላ ነው ብቻውን መሆን እንደሚፈልግ የተናገረው ነገር ከምሩ ሳይሆን በወቅቱ ተበሳጭቶ ስለነበር ገልፆላት ይቅርታ እንድታደርግለት ከለመናት በኋላ የመጨረሻ ዕድሉን የመሞከሪያ ቀኑንም አብራው እንድትሆን አሳምኗት ሊተኛ ወደ መኝታ ክፍሉ እየተንገዳገደ የሄደው፡፡
ከእንቅልፉ ሲነቃ ሠባት ሠዓት ሆኖ ነበር፡፡ በርግጎ በመነሳት ከክፍሉ ወጥቶ የትንግርትን ክፍል ሲያይ እሷም አልተነሳችም፡፡ ከዛ ያደረገው ነገር ቢኖር አስተናጋጁን ጠርቶ ምግብ እና የምትጠጣው ነገር ክፍሏ ድረስ እንዲወስዱላት ማድረግ ነበር፡፡ እሱም ለራሱ ሻወር ከወሠደ በኋላ ምሳውን በልቶ ወደ ከተማ ወጣና ዞር ዞር ብሎ ሲመለስ ትንግርት እንደተኛች አገኛት፡፡ ክፍሉ ገብቶ የተዝረከረኩና የተበታተኑ የግል ዕቃዎቹን ሠብስቦ በሻንጣው ውስጥ ጨመራቸው፡፡ ወደ ሆቴሉ እንግዳ መቀበያ ክፍልም ሄዶ ያለበትን ሂሳብ ዘጋ፡፡ ዛሬ ከበፊት ቀናት ይልቅ የመዝናናት የደስታ ስሜት እየተሠማው ነው፡፡ ሠዓቱን ተመለከተ፤ ዘጠኝ ተኩል ሆኗል፡፡
በመካከለኛ ኃይል የትንግርትን በር አንኳኳ፡
ኳ..ኳ..ኳ..ኳ..ኳ
‹‹ማነው?"
‹‹በሕይወት አለሽ? የበከትሽ መስሎኝ ነበር፡፡››
‹‹አንተም አልበከትክ .. ጠብቀኝ መጣሁ፡፡››
ከውጭ እንደተገተረ የተወሠኑ ደቂቃዎች አስጠበቀችው፡፡በዝግታ በሩ ተከፈተና ‹‹ግባ›› አለችው፡፡ ገባ፡፡ መልሳ በራፉን ዘጋችው፡፡ ከሻወር ነው የምትወጣው፡፡ገና ልብሷን
አለበሰችም፡፡ መሀከላዊ ሠውነቷን በፎጣ ጠቅልላዋለች፡፡አብዛኛው የላይና የታች አካሏ እንደተራቆተ ነው፡፡ ለመጀመሪያ ቀን ያያት ይመስል ዓይኖቹን ተከለባት፡፡ ከእሷ ጋር ያሳለፋቸው የፍቅር ጊዜያቶች፣የቆዳዋ ልስላሴ፣የሠውነቷ ጠረን፣የከናፍሮቿ ጣዕም፣ጠቅላላ ትዝታው የፍቅር ረሃቡን ቀሠቀሱበት፡፡ የቡና ቤት ሕይወቷን ካቋረጠች ስምንት ወር ሞላት ያ ማለት ከእሱ ጋርም ጾታዊ ግንኙነት ማድረግ ካቆሙ ስምንት ወር አለፏቸዋል ማለት ነው፡፡ያ የሆነው ደግሞ እሷም ፊት ስለነሳችው እሱም ስለፈራት ነው!፡፡
‹‹ምነው አትናገርም እንዴ?››
‹‹እንዲህ ቆንጆ ሆነሽ አይቼሽ አላውቅም..›› አላት አስቦበት አይደለም በድንገት ነው ቃላቶቹ ከአንደበቱ ተስፈንጥረው የወጡት ፡፡
ተንጨፍርሮ ውሃ የቋጠረ ፀጉሯን በፎጣ እያደረቀች‹‹ምን አልባት ያየኸኝም ዛሬ ገና ብቻ ሳይሆን አይቀርም!!›› መለሠችለት ፡፡
‹‹አይደለም፤ካገኘሁሽ ቀን ጀምሮ በጥልቀት አይሻለሁ፤ ቆንጆ እንደሆንሽም
አውቃለሁ፤አሁን ለማለት የፈለኩት ግን የተለየሽ ሆነሻል ማለቴ ነው፡፡ዞማ ፀጉርሽ ተንጨፍርሮ ወዲህና ወዲያ መዘበራረቁ፤የአይኖችሽ ቅንድቦች አበጥ…
አበጥ ማለታቸው፣የፊትሽ ወዝ ጥራቱ፣ደረትሽ
ላይ ያለው ሀብል፣የጡቶችሽ
መቀሰር፣ያገለደምሽው ፎጣ፣ ወጣ ወጣ ያሉ
ዳሌዎችሽ፣በትንሹ የተጋለጠው ባትሽ፣ የእግሮችሽ ጣቶች፣በቃ እነዚህ ሁሉ በአንድ ላይ በግልፅ ሳያቸው ምን ዓይነት ስሜት እንደፈጠሩብኝ ታውቂያለሽ? ምነው
ሠዓሊ በሆንኩ ነው ያሰኘኝ፡፡›› ያለ ምንም
ፍራቻና መሳቀቅ ፊት ለፊቱ ልብሶቿን እየለበሠች ንግግሯን ቀጠለች
<<አቶ ጋዜጠኛው! እነዚህን የመሰሉ ውብ የፍቅር
ዓረፍተ ነገሮች ያለቦታቸው አታባክናቸው፡፡ ነው
ወይንስ በኋላ እሷን ስታገኛት ምን ማለት
እንዳለብህ እየተለማመድክብኝ ነው? >>
‹‹ካገኘኋትማ አትበይ! ለምን እንደዚህ ደስ ያለኝ ይመስልሻል፤ ዘጠና ዘጠኝ ፐርሠንት ያቺ ጠይም አንባቢ የእኔዋ ምስጢር እንደሆነች እርግጠኛ ነኝ፡፡ ግን አመንሽም አላመንሽም ስለ አንቺ የተናገርኩት ከምሬ ነው››
ቀሚሷን ከስር አጥልቃ ዳሌዋን ካለበሰች በኋላ ከላይ ያለውን ፎጣ አንስታ አልጋ ላይ ወረወረችና በገረሜታ ቆሞ የሚያወራትን ሁሴንን ተመለከተችው፤እናም ከወገቧ በላይ እንደተራቆተች አልጋው ጠርዝ ላይ ቁጭ አለችና እሱንም ስባ ከጎኗ አስቀመጠችው፡፡ ግራ በመጋባት ዝም ብሎ ተጎተተላት፡፡
‹‹እስቲ ንገረኝ... ቆይ እኔ ላንተ ምንህ ነኝ?››
‹‹አልገባኝም?››
‹‹ብዙ ጊዜ የእኔ ነገር በቀላሉ እንደማይገባህ አውቃለሁ፡፡ ለማለት የፈለግኩት እኔ ላንተ የድሮ የቡና ቤት የወሲብ ደንበኛህ ነኝ? ... የድሮ ፍቅረኛህ ነኝ? ... ወይስ ጓደኛህ ነኝ?...
ወይንስ በቃ ዝም ብሎ በሆነ አጋጣሚ የምታውቀኝ አንድ ተራ ግለሠብ ነኝ?››
ዝም ብሎ የጎንዬሽ ተመለከታት፡፡ በመጀመሪያ ጥያቄዎቿ እንደወትሮው የቀልድና የሽሙጥ መስለውት ነበር፡፡ አይኖቿን ሲያነባቸው ግን ትናንትና ማታ ስላለፈ የፍቅር ሕይወቷ ስትተርክለት ያስተዋለውን አይነት ስቃይ አነበባቸው እናም ጥያቄዎቿን በጥሞና አጤናቸው፡፡
‹‹ትክክለኛ መልስ ነው የምትፈልጊው?››
‹‹ለስሜቴ ቅንጣትም ሳትጨነቅ ትክክለኛ የሚሠማህን››
ለደቂቃዎች እንደመቆዘም አለና መናገር ጀመረ፡፡ ‹‹እንግዲያው እውነቱን ንገረኝ ካልሽ አንቺ ምኔ እንደሆንሽ ከአሁን በፊት አስቤው አላውቅም፡፡ ግን በእርግጠኝነት የማውቀው አንድ ነገር ቢኖር ዘወትር ካንቺ ጎን መሆን መፈለጌን ነው፡፡ሁል ጊዜ ስበሳጭ፣በሕይወቴ
የሆነ ነገር ሲመሠቃቀልብኝና ማደርገው ነገር ግራ ሲገባኝ፣መጨፈር ወይም ማልቀስ ሲያሠኘኝ፣አጠገቤ ማግኘት የምፈልገው ብቸኛዋ ሠው አንቺ መሆንሽን በእርግጠኝነት አውቃለሁ፡፡ይሄ ስሜቴና ፍላጎቴ የጓደኝነት ይሁን የፍቅር ... ብቻ ትክክለኛ ስሜቱን አላውቅም፡፡ በቃ ይሄው ነው፡፡›› በማለት ንግግሩን ጨርሶ ቀና ሲል ከሚንከባለሉ ዓይኖቿ እንባዋ እየተንጠባጠበ ደረቷ ላይ አርፎ በጡቶቿ መሃከል ሲንኳለል ተመለከተ፡፡
‹‹ምን ያስለቅስሻል ... ምን የሚያስለቅስ ነገር ተናገርኩ?›› በማለት ይበልጥ ተጠጋትና ቀኝ እጁን ትከሻዋ ላይ ጣል አድርጎ ሊያባብላት ፈለገ፡፡
‹‹ምንም ክፉ ነገር አልተናገርክም፡፡ እንደውም በተቃራኒው መስማት የምፈልገውን ነገር ስለነገርከኝ ደስ ብሎኝ ነው ያለቀስኩት፡፡ እኔም ስላንተ የሚሠማኝን ነገር ሁሉ ዝርግፍ አድርጌ ብነግርህ ደስ ይለኝ ነበር ...ግን አልችልም በፍፁም አልችልም›› ሠዓቷን ተመለከተች ፡፡
ዘጠኝ ሠዓት ሆኗል፡፡
‹‹ይሄውልህ አሁን ዘጠኝ ሠዓት ነው፡፡ ወደ ቀጠሮህ ቦታ ለመሄድ የቀረን አንድ ሠዓት ብቻ ነው፡፡ ከዛ በኋላ ነገሮች ሁሉ መልካቸውን ይቀይራሉ ፤እንዳልከው እሷ ሆና ካገኘሀት እንደዚህ እንደዛሬው አንድ ቤርጎ ጎን ለጎን ለዛውም ግማሽ እርቃን ሆኜ ማውራት ይቅርና በአደባባይና በካፌ እንኳን የመገናኘት ዕድላችን በእሷ በጎ ፍቃደኝነት የሚወሰን ይሆናል፡፡ ባታገኛትም የተለየ ታሪክ አይኖረውም፤ምክንያቱም እኔ ከዚህ በፊት ደጋግሜ በፍቅር እጦት እንደተሠባበርኩ አንተም ትሠበራለህ፤ከዛ በኃላ አንተ ትጠፋና በድንህ ብቻ ይቀር ይሆናል፤ከበድንህ ጋር
ደግሞ እንደከዚህ ቀደሙ ያለ ግንኙነት ሊቀጥል አይችልም ...>>
‹‹ምን እያወራሽ ነው?የሲኦል ፍራቻ በልቤ ውስጤ እየበተንሽ እኮ ነው
‹‹እኔም በጣም ስለፈራሁ ነዋ፡፡ ከፍራቻዬ ጥልቀት የተነሳ እየተንቀጠቀጥኩ አይታይህም?››
‹‹መንቀጥቀጥሽ ይሠማኛል፤ግን ተረጋጊ በእኛ ግንኙነት መካከል ምንም የሚቀየር ነገር አይኖርም፡፡›› እርግጠኛ ባይሆንም በወቅቱ ማለት የሚችለው እንደዚህ ነበር፡፡
‹‹እንድረጋጋ...ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ.... ማለት ከዛሬ ወዲህ መቼም የማይደገም… በቃ...መሠናበቻ ...›› ንግግሯን መጨረስ አልቻም ሳግ አቋረጣት፡፡
‹‹የመሠናበቻ ምን? ... ንገሪኝ፡፡››
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
እሁድ ከቀኑ ዘጠኝ ሠዓት
ሁሴን ከነጋ ከትንግርት ጋር አልተያዩም፡፡ ማታ ሲጠጡና ሲጫወቱ እስከ ስምንት ሠዓት ነበር የቆዩት፡፡ ከዛ በኋላ ነው ብቻውን መሆን እንደሚፈልግ የተናገረው ነገር ከምሩ ሳይሆን በወቅቱ ተበሳጭቶ ስለነበር ገልፆላት ይቅርታ እንድታደርግለት ከለመናት በኋላ የመጨረሻ ዕድሉን የመሞከሪያ ቀኑንም አብራው እንድትሆን አሳምኗት ሊተኛ ወደ መኝታ ክፍሉ እየተንገዳገደ የሄደው፡፡
ከእንቅልፉ ሲነቃ ሠባት ሠዓት ሆኖ ነበር፡፡ በርግጎ በመነሳት ከክፍሉ ወጥቶ የትንግርትን ክፍል ሲያይ እሷም አልተነሳችም፡፡ ከዛ ያደረገው ነገር ቢኖር አስተናጋጁን ጠርቶ ምግብ እና የምትጠጣው ነገር ክፍሏ ድረስ እንዲወስዱላት ማድረግ ነበር፡፡ እሱም ለራሱ ሻወር ከወሠደ በኋላ ምሳውን በልቶ ወደ ከተማ ወጣና ዞር ዞር ብሎ ሲመለስ ትንግርት እንደተኛች አገኛት፡፡ ክፍሉ ገብቶ የተዝረከረኩና የተበታተኑ የግል ዕቃዎቹን ሠብስቦ በሻንጣው ውስጥ ጨመራቸው፡፡ ወደ ሆቴሉ እንግዳ መቀበያ ክፍልም ሄዶ ያለበትን ሂሳብ ዘጋ፡፡ ዛሬ ከበፊት ቀናት ይልቅ የመዝናናት የደስታ ስሜት እየተሠማው ነው፡፡ ሠዓቱን ተመለከተ፤ ዘጠኝ ተኩል ሆኗል፡፡
በመካከለኛ ኃይል የትንግርትን በር አንኳኳ፡
ኳ..ኳ..ኳ..ኳ..ኳ
‹‹ማነው?"
‹‹በሕይወት አለሽ? የበከትሽ መስሎኝ ነበር፡፡››
‹‹አንተም አልበከትክ .. ጠብቀኝ መጣሁ፡፡››
ከውጭ እንደተገተረ የተወሠኑ ደቂቃዎች አስጠበቀችው፡፡በዝግታ በሩ ተከፈተና ‹‹ግባ›› አለችው፡፡ ገባ፡፡ መልሳ በራፉን ዘጋችው፡፡ ከሻወር ነው የምትወጣው፡፡ገና ልብሷን
አለበሰችም፡፡ መሀከላዊ ሠውነቷን በፎጣ ጠቅልላዋለች፡፡አብዛኛው የላይና የታች አካሏ እንደተራቆተ ነው፡፡ ለመጀመሪያ ቀን ያያት ይመስል ዓይኖቹን ተከለባት፡፡ ከእሷ ጋር ያሳለፋቸው የፍቅር ጊዜያቶች፣የቆዳዋ ልስላሴ፣የሠውነቷ ጠረን፣የከናፍሮቿ ጣዕም፣ጠቅላላ ትዝታው የፍቅር ረሃቡን ቀሠቀሱበት፡፡ የቡና ቤት ሕይወቷን ካቋረጠች ስምንት ወር ሞላት ያ ማለት ከእሱ ጋርም ጾታዊ ግንኙነት ማድረግ ካቆሙ ስምንት ወር አለፏቸዋል ማለት ነው፡፡ያ የሆነው ደግሞ እሷም ፊት ስለነሳችው እሱም ስለፈራት ነው!፡፡
‹‹ምነው አትናገርም እንዴ?››
‹‹እንዲህ ቆንጆ ሆነሽ አይቼሽ አላውቅም..›› አላት አስቦበት አይደለም በድንገት ነው ቃላቶቹ ከአንደበቱ ተስፈንጥረው የወጡት ፡፡
ተንጨፍርሮ ውሃ የቋጠረ ፀጉሯን በፎጣ እያደረቀች‹‹ምን አልባት ያየኸኝም ዛሬ ገና ብቻ ሳይሆን አይቀርም!!›› መለሠችለት ፡፡
‹‹አይደለም፤ካገኘሁሽ ቀን ጀምሮ በጥልቀት አይሻለሁ፤ ቆንጆ እንደሆንሽም
አውቃለሁ፤አሁን ለማለት የፈለኩት ግን የተለየሽ ሆነሻል ማለቴ ነው፡፡ዞማ ፀጉርሽ ተንጨፍርሮ ወዲህና ወዲያ መዘበራረቁ፤የአይኖችሽ ቅንድቦች አበጥ…
አበጥ ማለታቸው፣የፊትሽ ወዝ ጥራቱ፣ደረትሽ
ላይ ያለው ሀብል፣የጡቶችሽ
መቀሰር፣ያገለደምሽው ፎጣ፣ ወጣ ወጣ ያሉ
ዳሌዎችሽ፣በትንሹ የተጋለጠው ባትሽ፣ የእግሮችሽ ጣቶች፣በቃ እነዚህ ሁሉ በአንድ ላይ በግልፅ ሳያቸው ምን ዓይነት ስሜት እንደፈጠሩብኝ ታውቂያለሽ? ምነው
ሠዓሊ በሆንኩ ነው ያሰኘኝ፡፡›› ያለ ምንም
ፍራቻና መሳቀቅ ፊት ለፊቱ ልብሶቿን እየለበሠች ንግግሯን ቀጠለች
<<አቶ ጋዜጠኛው! እነዚህን የመሰሉ ውብ የፍቅር
ዓረፍተ ነገሮች ያለቦታቸው አታባክናቸው፡፡ ነው
ወይንስ በኋላ እሷን ስታገኛት ምን ማለት
እንዳለብህ እየተለማመድክብኝ ነው? >>
‹‹ካገኘኋትማ አትበይ! ለምን እንደዚህ ደስ ያለኝ ይመስልሻል፤ ዘጠና ዘጠኝ ፐርሠንት ያቺ ጠይም አንባቢ የእኔዋ ምስጢር እንደሆነች እርግጠኛ ነኝ፡፡ ግን አመንሽም አላመንሽም ስለ አንቺ የተናገርኩት ከምሬ ነው››
ቀሚሷን ከስር አጥልቃ ዳሌዋን ካለበሰች በኋላ ከላይ ያለውን ፎጣ አንስታ አልጋ ላይ ወረወረችና በገረሜታ ቆሞ የሚያወራትን ሁሴንን ተመለከተችው፤እናም ከወገቧ በላይ እንደተራቆተች አልጋው ጠርዝ ላይ ቁጭ አለችና እሱንም ስባ ከጎኗ አስቀመጠችው፡፡ ግራ በመጋባት ዝም ብሎ ተጎተተላት፡፡
‹‹እስቲ ንገረኝ... ቆይ እኔ ላንተ ምንህ ነኝ?››
‹‹አልገባኝም?››
‹‹ብዙ ጊዜ የእኔ ነገር በቀላሉ እንደማይገባህ አውቃለሁ፡፡ ለማለት የፈለግኩት እኔ ላንተ የድሮ የቡና ቤት የወሲብ ደንበኛህ ነኝ? ... የድሮ ፍቅረኛህ ነኝ? ... ወይስ ጓደኛህ ነኝ?...
ወይንስ በቃ ዝም ብሎ በሆነ አጋጣሚ የምታውቀኝ አንድ ተራ ግለሠብ ነኝ?››
ዝም ብሎ የጎንዬሽ ተመለከታት፡፡ በመጀመሪያ ጥያቄዎቿ እንደወትሮው የቀልድና የሽሙጥ መስለውት ነበር፡፡ አይኖቿን ሲያነባቸው ግን ትናንትና ማታ ስላለፈ የፍቅር ሕይወቷ ስትተርክለት ያስተዋለውን አይነት ስቃይ አነበባቸው እናም ጥያቄዎቿን በጥሞና አጤናቸው፡፡
‹‹ትክክለኛ መልስ ነው የምትፈልጊው?››
‹‹ለስሜቴ ቅንጣትም ሳትጨነቅ ትክክለኛ የሚሠማህን››
ለደቂቃዎች እንደመቆዘም አለና መናገር ጀመረ፡፡ ‹‹እንግዲያው እውነቱን ንገረኝ ካልሽ አንቺ ምኔ እንደሆንሽ ከአሁን በፊት አስቤው አላውቅም፡፡ ግን በእርግጠኝነት የማውቀው አንድ ነገር ቢኖር ዘወትር ካንቺ ጎን መሆን መፈለጌን ነው፡፡ሁል ጊዜ ስበሳጭ፣በሕይወቴ
የሆነ ነገር ሲመሠቃቀልብኝና ማደርገው ነገር ግራ ሲገባኝ፣መጨፈር ወይም ማልቀስ ሲያሠኘኝ፣አጠገቤ ማግኘት የምፈልገው ብቸኛዋ ሠው አንቺ መሆንሽን በእርግጠኝነት አውቃለሁ፡፡ይሄ ስሜቴና ፍላጎቴ የጓደኝነት ይሁን የፍቅር ... ብቻ ትክክለኛ ስሜቱን አላውቅም፡፡ በቃ ይሄው ነው፡፡›› በማለት ንግግሩን ጨርሶ ቀና ሲል ከሚንከባለሉ ዓይኖቿ እንባዋ እየተንጠባጠበ ደረቷ ላይ አርፎ በጡቶቿ መሃከል ሲንኳለል ተመለከተ፡፡
‹‹ምን ያስለቅስሻል ... ምን የሚያስለቅስ ነገር ተናገርኩ?›› በማለት ይበልጥ ተጠጋትና ቀኝ እጁን ትከሻዋ ላይ ጣል አድርጎ ሊያባብላት ፈለገ፡፡
‹‹ምንም ክፉ ነገር አልተናገርክም፡፡ እንደውም በተቃራኒው መስማት የምፈልገውን ነገር ስለነገርከኝ ደስ ብሎኝ ነው ያለቀስኩት፡፡ እኔም ስላንተ የሚሠማኝን ነገር ሁሉ ዝርግፍ አድርጌ ብነግርህ ደስ ይለኝ ነበር ...ግን አልችልም በፍፁም አልችልም›› ሠዓቷን ተመለከተች ፡፡
ዘጠኝ ሠዓት ሆኗል፡፡
‹‹ይሄውልህ አሁን ዘጠኝ ሠዓት ነው፡፡ ወደ ቀጠሮህ ቦታ ለመሄድ የቀረን አንድ ሠዓት ብቻ ነው፡፡ ከዛ በኋላ ነገሮች ሁሉ መልካቸውን ይቀይራሉ ፤እንዳልከው እሷ ሆና ካገኘሀት እንደዚህ እንደዛሬው አንድ ቤርጎ ጎን ለጎን ለዛውም ግማሽ እርቃን ሆኜ ማውራት ይቅርና በአደባባይና በካፌ እንኳን የመገናኘት ዕድላችን በእሷ በጎ ፍቃደኝነት የሚወሰን ይሆናል፡፡ ባታገኛትም የተለየ ታሪክ አይኖረውም፤ምክንያቱም እኔ ከዚህ በፊት ደጋግሜ በፍቅር እጦት እንደተሠባበርኩ አንተም ትሠበራለህ፤ከዛ በኃላ አንተ ትጠፋና በድንህ ብቻ ይቀር ይሆናል፤ከበድንህ ጋር
ደግሞ እንደከዚህ ቀደሙ ያለ ግንኙነት ሊቀጥል አይችልም ...>>
‹‹ምን እያወራሽ ነው?የሲኦል ፍራቻ በልቤ ውስጤ እየበተንሽ እኮ ነው
‹‹እኔም በጣም ስለፈራሁ ነዋ፡፡ ከፍራቻዬ ጥልቀት የተነሳ እየተንቀጠቀጥኩ አይታይህም?››
‹‹መንቀጥቀጥሽ ይሠማኛል፤ግን ተረጋጊ በእኛ ግንኙነት መካከል ምንም የሚቀየር ነገር አይኖርም፡፡›› እርግጠኛ ባይሆንም በወቅቱ ማለት የሚችለው እንደዚህ ነበር፡፡
‹‹እንድረጋጋ...ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ.... ማለት ከዛሬ ወዲህ መቼም የማይደገም… በቃ...መሠናበቻ ...›› ንግግሯን መጨረስ አልቻም ሳግ አቋረጣት፡፡
‹‹የመሠናበቻ ምን? ... ንገሪኝ፡፡››
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
"ውይ ለመክሰስ ሆቴል...?ሰርቼ ልጋብዝሽ የምትለኝ መስሎኝ ነበር።"
‹‹ደስ ይለኝ ነበር...ግን ካገዝሽኝ ነው..."
"ይቻላል"
ሁለቱም የየራሳቸውን ቢራ ይዘው በእሱ መሪነት ወደ ኪችን.አመሩ።
ኪችኑ በእጅጉ የተደራጀና የሚያምር ነው። ፍሪጁን ከፈተና ተመለከተ...
"ምን እንስራ"በራሱ መወሰን አቅቶት ጠየቃት።
"እኔ እንጃ...ምን አለህ?"አለችና ወደእሱ ተጠግታ ያለውን ነገር ተመለከተች...ብዙ ምርጫ አላቸው...የምትፈልገውን ነገር እየመረጠች ከፍሪጁ ማውጣት ጀመረች፡፡ እሱም ወደውጭ ሊወጣ አስቦ የለበሰውን ጃኬት አወለቀና ሽርጥ ለበሰ..ለእሷም ተመሳሳይ ሽርጥ ሰጣት።በ30 ደቂቃ ውስጥ ሶስት የተለያየ የምግብ አይነት ተጋግዘው በመስራት ሳሎን የምግብ ጠረጴዛ ላይ አቀረቡ..በልተው ሲጨርሱ አንድ ሰዓት አልፎ ነበር።
"አሁን በላሁ ጠጣሁ...ወደማድርበት ቤርጎዬ ልትመልሰኝ ትችላለህ?›› አለችው። ሞባይሉን በማውጣት ሰዓቱን አየና"እንዴ ገና አንድ ሰዓት እኮ ነው...ባይሆን አንድ ወዳጄ ከፈረንሳይ ያመጣልኝ ልዩ ወይን አለኝ...እሱን ላምጣና መጠጥ እንቀይር››አለና እሺታዋንም ሳይጠብቅ መቀመጫውን ለቆ ወደመኝታ ቤቱ በመሄድ ይዞ መጣና የቢራ ጠርሙሶችን ከፊታቸው በማንሳት በወይን ብርጭቆ ተካውና ተደላድሎ ቁጭ አለ፡፡:
"በቀደም ለታ ግን ማደሪያ ቦታ ስጠይቅህ ለምን ቤትህን አራተኛ ምርጫ አድርገህ አላቀረብክልኝም ነበር?"ስትል.ያላሰበውን ድንገተኛ ጥያቄ ጠየቀችው።
"እኔ እንጃ...ምን አልባት እንደዛ ብልሽ ሌላ ነገር ታስቢያለሽ ብዬ.ፈርቼ ይሆናል"አላት፡፡
"እንዴት ሌላ ነገር አስባለሁ?"
"ብታስቢም እኮ አይፈረድብሽም...በጥልቀት አታውቂኝም"
"ለነገሩ እውነትህን ነው፤እሺ አሁን ብዙ ብር ከምትዝቅበት የማሳጅ ስራ ራስህን ለምን እንዳገለልክ ንገረኝ? "ቅድም ጀምረው ወዳቋረጡት የጫወታ ርእስ መለሰችው፡፡
የወይኑን ብርጭቆ አነሳና ውስጡ ያለውን ከጨለጠ በኃላ መልሶ አስቀምጦ አንገቱን አቀረቀረ፡፡››
"ምነው ከባድ ጥያቄ ነው እንዴ የጠየኩህ?" በረጅሙ ተነፈሰ፡፡
"ከከባድም በላይ..አየሽ ቅድም ስለስራው ሳስረዳሽ ልክ እንደሀሺሽ ነው ብዬሽ ነበር አይደል። በመጀመሪያ ሁሉ ነገር አስደሳችና ልብን ስውር የሚያደርግ ነበር። አገልግሎቱን ለማግኘት የሚመጡት ሴቶች ሊነኳቸው የሚያሳሱ የሰውነታቸው ቆዳ እንደሀር ጨርቅ የለሠለሠ፤ የፊታቸው ውበት የመላእክት የመሰለ ፤ጠረናቸው ጭንቅላት አዙሮ ጭናቸው ስር የመድፋት ኃይል ያለው፤ የህልም አለም ንግስቶች ናቸው። ታዲያ እነሱን እርቃን አስወልቀሽ ከላይ ከጭንቅላታቸው እስከታች የእግር ጥፍራቸው መላ ሰውነታቸውን አፍተልትለሽ ዳብሰሽና አሽተሽ፤በስሜት ሲወራጩና በደስታ እንባቸው ሲንጠባጠብ አይተሽ...ለምነውና በአይናቸው ተለማምጠው እርቃንሽን ከእርቃናቸው እንድታዋህጂ ለምነውሽ...አርክተሻቸውና.ረክተሽ፤አስደስተውሽና ተደስተሽ፤ አስለቅሰሻቸውና አልቅሰሽ ከዛ ደግሞ ረብጣ ብር የእጅሽ መዳፍ ላይ አስጨብጠው..በመፍለቅለቅ ጉንጭሽን ወይም ከንፈርሽን ስመው በሳምንቱ እንደሚመለሱ ምለውና ተገዝተው ይሄዳሉ...;
‹‹ስራው እስከዚህ ይሄዳል ማለት ነው"
"አዎ ምነው የፈረምሽውን ውል በቅጡ አላነበብሽውም እንዴ...ደንበኛ ምንም ነገር ጠይቆ መከልከል የለበትም ይላል እኮ.ያ ማለት ደግሞ ስራው ከነገርኩሽም በላይ ይሄዳል ማለት ነው.."
"እና አሁን አንድ የማላውቀው ሰው መጥቶ እንድትወጪልኝ እፈልጋለሁ ካለኝ..ዝም ብዬ እከፍትለታለሁ ማለት ነው።"
‹‹አይ ዝም ብለሽማ አትከፍቺለትም ...አንቺ ያለሽበት ቦታ አገልግሎትሽን ፈልጎ የሚመጣው ግለሰብ በየሄደበት ዝም ብለው የሚከፍቱለት ቁጥር ስፍር የሌላቸው አንዳንዴም ካንቺ በላይ ለጋ፤ ካንቺ በላይ ፀሀይ የመሰሉ ውብ የሆኑ ሴቶች አሉት...እንደዛ ካደረግሽ ደብሮት የመጣውን ሰውዬ ጭራሽ አሳብደሽ ነው የምትልኪው››
‹‹እና ምንድነው ማድረግ የሚጠበቅብኝ ?››በከፍተኛ መገረም ጠየቀችው።
እጅሽ ሰውነቱ ላይ ሲያርፍ ልስላሴውና ሙቀቱ ቆዳውን ሳይሆን ልቡ ላይ ሊሰማው ያስፈልጋል....መሳም ኖሮብሽ ከሳምሽው ከከንፈሮችሽ የሚመነጨው ሙቀት ወደ ጭንቅላቱ ሄዶ በቢሊዬን የሚቆጠሩትን የኒሮን ሴሎችን ከተኙበት መቀስቀስና መደነስ እንዲችሉ ማድረግ አለብሽ... ልብሶችሽን ፊቱ ስታወልቂ አይኖቹ ቆዳሽን ሰንጥቀው ውስጥሽ በመግባት ነፍስሽን ጭምር ለመቆረጣጠም እስኪመኝ መቃተት መቻል አለበት። ጭንሽን ከፍተሽለት ብልቱ ብልትሽን ሰንጥቆ ከገባ አካሉ መጥፋት፤አእምሮ መሰወር፤ነፍሱ በአየር ላይ እየተንሳፈፈች ትዕይንቱን መታዘብ አለባት።ሰውዬው ካንቺ በፊት ከመቶ ሴቶች ጋር ለአንድ ሺኛ ጊዜ ወሲብ አድርጎ የሚያውቅ ከሆነ .. እንዴ ከዚህ በፊት ወሲብ አድርጌ አውቅ ነበር እንዴ ..?ብሎ እስኪጠይቅና እስኪወነባበድ ድረስ ህልም ውስጥ እንዲገባ ማድረግ ይጠበቅብሻል... የስራው ከባድነት ደግሞ ሰውዬው በሳምንት ወይም በወራት ልዩነት ደጋግሞ ቢመጣ በተመሳሳይ ብቃት ግን ደግሞ ፍፁም ባልተደጋገመ 10 የተለያየ መንገድ ማስተናገድ ይጠበቅብሻል፡፡
"የሚያወራውን ሁሉ የምታዳምጠው ሁሉንም የስሜት ህዋሳቶቿን ከፋፍታ ነበር...እየጠጣችው ያለው መጠጥ እየሠማችው ካለው ወሬ ጋር ተዳምሮ ሙቀትና ንዝረት ለቀቀባት
"የምትነግረኝ ነገር ሁሉ ግን እውነት ነው?ማለቴ እንደዚህ አይነት ነገር አለ?"
"አዎ አለ"
"ወይ በፈጣሪ..ታዲያ እኔ ምን ላደርግ ነው? እንደው ፍቃደኛ ሆኜ የተጠየቅኩትን ለማድረግ ፈለኩ ልበል…ግን በየትኛው ብቃቴ ነው አንተ ባወራህልኝ መጠን በአየር ላይ የሚያንሳፍፍ ወሲብ መፈፀም የምችለው..?
"አይዞሽ ...አንቺ ብቻ ከልብሽ ተቀባይ ሁኚ እንጂ…በቂ ስልጠና ይሰጥሻል...ከዛ የተወሰነ የስራ ልምድ በኋላ እርግጠኛ ነኝ ከነገርኩሽም በላይ የተካንሽ ትሆኚያለሽ"
"እንዴት እርግጠኛ ሆንክ?"ብላ ልትጠይቀው ፈለገችና ብዙ በተናገረች ቁጥር ይበልጥ ራሷን እያጋለጠችና ወደ ሽብር ውስጥ እየገባች ስለመጣች መልሳ ዋጠችው።
"እሺ ይሄን ለጊዜው ተውና ..የጀመርክልኝን የራስህን ታሪክ ቀጥልልኝ"
"አጠር ላድርገውና በተደጋጋሚ ጊዜ ከሚመላለሱ ደንበኞቼ መካከል ከአንዷ ጋር የተለየ ግንኙነት ነበረኝ፣ለነገሩ ከአንዷ ጋር ብቻ አልነበረም ከአምስት ከስድስቱ ጋር በይው። ግን ስራ እንዳቆም ስላስገደደቺኝ አንዷ ብቻ ላውራሽ።
የባለስልጣን ሚስት ነች። ባሏ የሆነ መስሪያ ቤት ሚኒስትር ዲኤታ ነው። ያው በስራውም በራሱ ጉዳይም በጣም እረፍት የሌለው ከወር ውስጥ ግማሹን ቤቱ
የማያድር...በሚያድርባቸው ጥቂት ቀናትም እኩለ ለሊት ገብቶ ወፍ ሲንጫጫ የሚወጣ አይነት አባወራ ነው። ሚስቱ የፈለገችውን ያህል ብር ይሰጣታል። በዛ ላይ በእሷ ስም የተከፈተ ግዙፍ ድርጅት አላቸው። የት ገባህ የት ወጣህ እንዳትለው ያንን በማስተዳደር ቢዚ ሊያደርጋት ሞክሮ ነበር። ይሄ እቅድ ለተወሰነ አመት ቢሰራለትም ቀስ በቀስ ሴትዬዋን ለድብርትና ለጭንቀት እያጋለጣት መጣ ...ከዛ በአንድ ወዳጇ ገፋፊነት እኛ ጋር ትመጣለች..አጋጣሚ ሆኖ እኔ ጋር ተላከች። በመጀመሪያዎቹ ሶስት አራት ዙሮች እንደማንኛውም ኖርማል ማሳጅ የተለመደውን አገልግሎት እያገኘች ነበር የምትሄደው...ከዛ ነገሮች በሂደት እድገት ሲያሳዩ ከስድስት ወር የደንበኝነት መመላለስ በኃላ ጥልቅ የሆነ ፍቅር ውስጥ ገባች...
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
"ውይ ለመክሰስ ሆቴል...?ሰርቼ ልጋብዝሽ የምትለኝ መስሎኝ ነበር።"
‹‹ደስ ይለኝ ነበር...ግን ካገዝሽኝ ነው..."
"ይቻላል"
ሁለቱም የየራሳቸውን ቢራ ይዘው በእሱ መሪነት ወደ ኪችን.አመሩ።
ኪችኑ በእጅጉ የተደራጀና የሚያምር ነው። ፍሪጁን ከፈተና ተመለከተ...
"ምን እንስራ"በራሱ መወሰን አቅቶት ጠየቃት።
"እኔ እንጃ...ምን አለህ?"አለችና ወደእሱ ተጠግታ ያለውን ነገር ተመለከተች...ብዙ ምርጫ አላቸው...የምትፈልገውን ነገር እየመረጠች ከፍሪጁ ማውጣት ጀመረች፡፡ እሱም ወደውጭ ሊወጣ አስቦ የለበሰውን ጃኬት አወለቀና ሽርጥ ለበሰ..ለእሷም ተመሳሳይ ሽርጥ ሰጣት።በ30 ደቂቃ ውስጥ ሶስት የተለያየ የምግብ አይነት ተጋግዘው በመስራት ሳሎን የምግብ ጠረጴዛ ላይ አቀረቡ..በልተው ሲጨርሱ አንድ ሰዓት አልፎ ነበር።
"አሁን በላሁ ጠጣሁ...ወደማድርበት ቤርጎዬ ልትመልሰኝ ትችላለህ?›› አለችው። ሞባይሉን በማውጣት ሰዓቱን አየና"እንዴ ገና አንድ ሰዓት እኮ ነው...ባይሆን አንድ ወዳጄ ከፈረንሳይ ያመጣልኝ ልዩ ወይን አለኝ...እሱን ላምጣና መጠጥ እንቀይር››አለና እሺታዋንም ሳይጠብቅ መቀመጫውን ለቆ ወደመኝታ ቤቱ በመሄድ ይዞ መጣና የቢራ ጠርሙሶችን ከፊታቸው በማንሳት በወይን ብርጭቆ ተካውና ተደላድሎ ቁጭ አለ፡፡:
"በቀደም ለታ ግን ማደሪያ ቦታ ስጠይቅህ ለምን ቤትህን አራተኛ ምርጫ አድርገህ አላቀረብክልኝም ነበር?"ስትል.ያላሰበውን ድንገተኛ ጥያቄ ጠየቀችው።
"እኔ እንጃ...ምን አልባት እንደዛ ብልሽ ሌላ ነገር ታስቢያለሽ ብዬ.ፈርቼ ይሆናል"አላት፡፡
"እንዴት ሌላ ነገር አስባለሁ?"
"ብታስቢም እኮ አይፈረድብሽም...በጥልቀት አታውቂኝም"
"ለነገሩ እውነትህን ነው፤እሺ አሁን ብዙ ብር ከምትዝቅበት የማሳጅ ስራ ራስህን ለምን እንዳገለልክ ንገረኝ? "ቅድም ጀምረው ወዳቋረጡት የጫወታ ርእስ መለሰችው፡፡
የወይኑን ብርጭቆ አነሳና ውስጡ ያለውን ከጨለጠ በኃላ መልሶ አስቀምጦ አንገቱን አቀረቀረ፡፡››
"ምነው ከባድ ጥያቄ ነው እንዴ የጠየኩህ?" በረጅሙ ተነፈሰ፡፡
"ከከባድም በላይ..አየሽ ቅድም ስለስራው ሳስረዳሽ ልክ እንደሀሺሽ ነው ብዬሽ ነበር አይደል። በመጀመሪያ ሁሉ ነገር አስደሳችና ልብን ስውር የሚያደርግ ነበር። አገልግሎቱን ለማግኘት የሚመጡት ሴቶች ሊነኳቸው የሚያሳሱ የሰውነታቸው ቆዳ እንደሀር ጨርቅ የለሠለሠ፤ የፊታቸው ውበት የመላእክት የመሰለ ፤ጠረናቸው ጭንቅላት አዙሮ ጭናቸው ስር የመድፋት ኃይል ያለው፤ የህልም አለም ንግስቶች ናቸው። ታዲያ እነሱን እርቃን አስወልቀሽ ከላይ ከጭንቅላታቸው እስከታች የእግር ጥፍራቸው መላ ሰውነታቸውን አፍተልትለሽ ዳብሰሽና አሽተሽ፤በስሜት ሲወራጩና በደስታ እንባቸው ሲንጠባጠብ አይተሽ...ለምነውና በአይናቸው ተለማምጠው እርቃንሽን ከእርቃናቸው እንድታዋህጂ ለምነውሽ...አርክተሻቸውና.ረክተሽ፤አስደስተውሽና ተደስተሽ፤ አስለቅሰሻቸውና አልቅሰሽ ከዛ ደግሞ ረብጣ ብር የእጅሽ መዳፍ ላይ አስጨብጠው..በመፍለቅለቅ ጉንጭሽን ወይም ከንፈርሽን ስመው በሳምንቱ እንደሚመለሱ ምለውና ተገዝተው ይሄዳሉ...;
‹‹ስራው እስከዚህ ይሄዳል ማለት ነው"
"አዎ ምነው የፈረምሽውን ውል በቅጡ አላነበብሽውም እንዴ...ደንበኛ ምንም ነገር ጠይቆ መከልከል የለበትም ይላል እኮ.ያ ማለት ደግሞ ስራው ከነገርኩሽም በላይ ይሄዳል ማለት ነው.."
"እና አሁን አንድ የማላውቀው ሰው መጥቶ እንድትወጪልኝ እፈልጋለሁ ካለኝ..ዝም ብዬ እከፍትለታለሁ ማለት ነው።"
‹‹አይ ዝም ብለሽማ አትከፍቺለትም ...አንቺ ያለሽበት ቦታ አገልግሎትሽን ፈልጎ የሚመጣው ግለሰብ በየሄደበት ዝም ብለው የሚከፍቱለት ቁጥር ስፍር የሌላቸው አንዳንዴም ካንቺ በላይ ለጋ፤ ካንቺ በላይ ፀሀይ የመሰሉ ውብ የሆኑ ሴቶች አሉት...እንደዛ ካደረግሽ ደብሮት የመጣውን ሰውዬ ጭራሽ አሳብደሽ ነው የምትልኪው››
‹‹እና ምንድነው ማድረግ የሚጠበቅብኝ ?››በከፍተኛ መገረም ጠየቀችው።
እጅሽ ሰውነቱ ላይ ሲያርፍ ልስላሴውና ሙቀቱ ቆዳውን ሳይሆን ልቡ ላይ ሊሰማው ያስፈልጋል....መሳም ኖሮብሽ ከሳምሽው ከከንፈሮችሽ የሚመነጨው ሙቀት ወደ ጭንቅላቱ ሄዶ በቢሊዬን የሚቆጠሩትን የኒሮን ሴሎችን ከተኙበት መቀስቀስና መደነስ እንዲችሉ ማድረግ አለብሽ... ልብሶችሽን ፊቱ ስታወልቂ አይኖቹ ቆዳሽን ሰንጥቀው ውስጥሽ በመግባት ነፍስሽን ጭምር ለመቆረጣጠም እስኪመኝ መቃተት መቻል አለበት። ጭንሽን ከፍተሽለት ብልቱ ብልትሽን ሰንጥቆ ከገባ አካሉ መጥፋት፤አእምሮ መሰወር፤ነፍሱ በአየር ላይ እየተንሳፈፈች ትዕይንቱን መታዘብ አለባት።ሰውዬው ካንቺ በፊት ከመቶ ሴቶች ጋር ለአንድ ሺኛ ጊዜ ወሲብ አድርጎ የሚያውቅ ከሆነ .. እንዴ ከዚህ በፊት ወሲብ አድርጌ አውቅ ነበር እንዴ ..?ብሎ እስኪጠይቅና እስኪወነባበድ ድረስ ህልም ውስጥ እንዲገባ ማድረግ ይጠበቅብሻል... የስራው ከባድነት ደግሞ ሰውዬው በሳምንት ወይም በወራት ልዩነት ደጋግሞ ቢመጣ በተመሳሳይ ብቃት ግን ደግሞ ፍፁም ባልተደጋገመ 10 የተለያየ መንገድ ማስተናገድ ይጠበቅብሻል፡፡
"የሚያወራውን ሁሉ የምታዳምጠው ሁሉንም የስሜት ህዋሳቶቿን ከፋፍታ ነበር...እየጠጣችው ያለው መጠጥ እየሠማችው ካለው ወሬ ጋር ተዳምሮ ሙቀትና ንዝረት ለቀቀባት
"የምትነግረኝ ነገር ሁሉ ግን እውነት ነው?ማለቴ እንደዚህ አይነት ነገር አለ?"
"አዎ አለ"
"ወይ በፈጣሪ..ታዲያ እኔ ምን ላደርግ ነው? እንደው ፍቃደኛ ሆኜ የተጠየቅኩትን ለማድረግ ፈለኩ ልበል…ግን በየትኛው ብቃቴ ነው አንተ ባወራህልኝ መጠን በአየር ላይ የሚያንሳፍፍ ወሲብ መፈፀም የምችለው..?
"አይዞሽ ...አንቺ ብቻ ከልብሽ ተቀባይ ሁኚ እንጂ…በቂ ስልጠና ይሰጥሻል...ከዛ የተወሰነ የስራ ልምድ በኋላ እርግጠኛ ነኝ ከነገርኩሽም በላይ የተካንሽ ትሆኚያለሽ"
"እንዴት እርግጠኛ ሆንክ?"ብላ ልትጠይቀው ፈለገችና ብዙ በተናገረች ቁጥር ይበልጥ ራሷን እያጋለጠችና ወደ ሽብር ውስጥ እየገባች ስለመጣች መልሳ ዋጠችው።
"እሺ ይሄን ለጊዜው ተውና ..የጀመርክልኝን የራስህን ታሪክ ቀጥልልኝ"
"አጠር ላድርገውና በተደጋጋሚ ጊዜ ከሚመላለሱ ደንበኞቼ መካከል ከአንዷ ጋር የተለየ ግንኙነት ነበረኝ፣ለነገሩ ከአንዷ ጋር ብቻ አልነበረም ከአምስት ከስድስቱ ጋር በይው። ግን ስራ እንዳቆም ስላስገደደቺኝ አንዷ ብቻ ላውራሽ።
የባለስልጣን ሚስት ነች። ባሏ የሆነ መስሪያ ቤት ሚኒስትር ዲኤታ ነው። ያው በስራውም በራሱ ጉዳይም በጣም እረፍት የሌለው ከወር ውስጥ ግማሹን ቤቱ
የማያድር...በሚያድርባቸው ጥቂት ቀናትም እኩለ ለሊት ገብቶ ወፍ ሲንጫጫ የሚወጣ አይነት አባወራ ነው። ሚስቱ የፈለገችውን ያህል ብር ይሰጣታል። በዛ ላይ በእሷ ስም የተከፈተ ግዙፍ ድርጅት አላቸው። የት ገባህ የት ወጣህ እንዳትለው ያንን በማስተዳደር ቢዚ ሊያደርጋት ሞክሮ ነበር። ይሄ እቅድ ለተወሰነ አመት ቢሰራለትም ቀስ በቀስ ሴትዬዋን ለድብርትና ለጭንቀት እያጋለጣት መጣ ...ከዛ በአንድ ወዳጇ ገፋፊነት እኛ ጋር ትመጣለች..አጋጣሚ ሆኖ እኔ ጋር ተላከች። በመጀመሪያዎቹ ሶስት አራት ዙሮች እንደማንኛውም ኖርማል ማሳጅ የተለመደውን አገልግሎት እያገኘች ነበር የምትሄደው...ከዛ ነገሮች በሂደት እድገት ሲያሳዩ ከስድስት ወር የደንበኝነት መመላለስ በኃላ ጥልቅ የሆነ ፍቅር ውስጥ ገባች...
ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፡
፡
ልጅም ቶሎ ያንጠለጠለውን የእጅ ቦርሳ ጠረጴዛ ላይ አደረገና ከብር የተሠራ የሚመስል ሁለት የእጅ ብራስሌት መጀመሪያ ምስራቅ እጅ ላይ ቀጥሎ ናኦል እጅ ላይ አጠለቀና ከኪሱ ስልኩን አውጥቶ በማብራት ሲነካካ እጃቸው ላይ ያጠለቀላቸው ብራስሌት ቀለሙን ከብራማነት ወደ ደማቅ ሰማያዊነት ቀየረ።ዝም ብሎ ሁኔታውን ሲከታተል የነበረው ዳግላስ መናገር ጀመረ
"አሁን እንግደህ እህታችሁን እኔ ሳልሆን ለእናንተ ማመጣላችሁ ..እናንተ ናችሁ ለእኔ የምታመጡልኝ..." ብሎ ኑሀሚ የእሱን ሰው ገድላ ከሌላ ከእሱ ሰው ጋር እንደኮበለለች...እስከአሁንም በመላው አማዞን ደን ውስጥ ቢያስፈልጋት ሊያገኛት እንዳልቻለ...እሷን መሞቷን ካላረጋገጠ ወይም በህይወት እጅ ካላስገባት የሰላም እንቅልፍ እንደማይወስደው..ወንድሟን ያስመጣበት ምክንያት ተሳክቶላት እንኳን ማምለጥ ብትችል ለወንድሟ ደህንነት ስትል በፍቃዷ መልሳ እጅ እንድትሰጥ አቅዶ ያደረገው እንደሆነ አብራርቶ ከአሁን ሰዓት በኃላ እዛው እሱ የሚኖርበት ወለል ላይ የራሳቸው ክፍል እንደሚሰጣቸው እና እጃቸው ላይ በተጠለቀላቸው አንባር ሙሉ የ24 ሰዓት ክትትል እንደሚደረግላቸው ነገራቸው። እሷ መጥታ በፍቃዷ እጇን እስክትሰጥ ወይንም መሞቷ እስኪረጋገጥ ድረስ ከክፍላቸው መውጣት እንደማይችሉ...ፀባያቸውን እስካሳመሩና ችግር ለመፍጠር እስካልሞከሩ ድረስ የሚፈልጉት ነገር እንደሚያሟላላቸው አብራርቶላቸው.. ወደክፍላቸው እንዲወስዳቸው አዘዘ...።የታዘዘውም ታጣቂ እየጎተ ወሰዶ አንድ ለቀቅ ያለ ሻወርና ማንበቢያ ክፍል ያለው ባለአንድ ክፍል ቤት ውስጥ አስገብቶ ከውጭ ዘጋባቸው..
እቤት ውስጥ ከገብ በኃላ እንኳን ናኦል እና ምስራቅ ለረጅም ደቂቃ ደንዝዘውና ፈዘው ማህል ወለል ላይ በዝምታ ተገትረው ነበር።
ናኦል እንባ እየተናነቀው"ምስራቅ ምን ውስጥ ነው የገባነው..?ይሄ ሰውዬ ተጫወተብን"አላት ።
ምስራቅም ወደእሱ ተንደረደረችና አቀፈችው ።አንገቱ ስር ሽጉጥ ብላ በጆሮው "አትደንግጥ...እቅድ አለኝ"አለችው።
ዝም አለ...ከዚህ ለመውጣት ምን አይነት ተአምራዊ ዕቅድ ሊኖራት እንደሚችል ምንም ሊገለፅለት አልቻለም።ቢሆንም ከሞስራቅ ጋር ባሳለፋቸው በርካታ አመታት ብዙ ተአምር መሳይ ነገሮችን ስትከውንና ደጋግሞም ሲሳካላት ታዝቦልና የተናገረችው ነገር ንቆ ሊያልፈው አልደፈረም።...
ብራዚል/አማዞን ደን ውስጥ
አካባቢው ድቅድቅ ጨለማ ነው፡፡ጨረቃዋም በሰማይ ላይ ብርሀን አልፈነጠቀችም፡፡ከዋክብቱም የከሰሙ መስለዋል ፡፡ኑሀሚ ካርሎስ የሰራላት የአንጨት ርብራብ አልጋ ላይ ተኝታ የእጇ ጥዝጣዜ ታዳምጣለች፡፡እርግጥ ከትናንቱ የተሻ ጤንነት ላይ ብትገኝም ሰውነቷ ግን ሙሉ በሙሉ እደዛለ ነው፡፡በህይወቷ በእንዲህ አይነት ደካማንትና አቅመ ቢስነት ተሰምቷት አያውቅም፡፡ ካርሎስ በሶስት ቀን ውስጥ ሙሉ በሙሉ እደምታገግም ነግሯት ነበር ፡፡ አሁን አሁን ያለችበት ሁኔታ ስታስበው በሶስት ወር ተሽሏት ከዚህ አካባቢ የምትንቀሳቀስ እየመሰላት አይደለም፡፡ያም ሆኖ ግን ትናንትና ጉሮሮዋን ፈጥርቆ ነፍሷን ሊነጥቃት የነበረው ሲኦላዊ ህመም ዛሬ በሙሉ አቅሙ የለም፡፡ያ የሆነው ደግሞ ካርሎስ እጇ ላይ ባሰረለት የባህል መድሀኒት ምክንያት ነው፡፡
እንደምንም አንገቷን ወደ ዳር ሸርተት አድርጋ አየችው፡፡ እዛው ርብራብ አልጋ ጎን ባለ ጠፍጣፍ ድንጋይ ላይ ተቀምጦ አንገቱን በካኔቴራው ሙሉ በሙሉ ሸፍኖ የእንጨት አልጋውን ቋሚ ተደግፎ ጨልጥ ያለ እንቅልፍ ተኝቷል፡፡ አሳዘናት፡፡ቢቻላት ኩርምት ብሎ በተቀመጠበት እንቅልፍ የወሰደውን ይሄን መልካም ሰው ጎትታ ወደራሷ ስባ እሷ የተኛችበት የእንጨት ርብራብ ላይ ከጎኗ ሽጉጥ አድርጋው ብትተኛ ደስ ይላት ነበር ፡፡
ወዲያው ሀሳቧን ሳትጨርስ ነጎድጓድ በሰማዩ አንፀባራቂ ብርሀን እየረጨ ያንቧርቅ ጀመር፡፡የሚያስፈራ ደራጎናዊ ድምፅ አካባቢውን ያናጋው ጀመር፡፡ ኑሀሚ እንኳን በእንደዚህ አይነት ሁኔታ እንደዚህ አይነት ቦታ ሆና ይቅርና በሀገሯ ሰማይ ስር በገዛ ቤቷ እያለች ሳይቀር እንዲህ አይነት ነጎድጎድ በጣም ነው የሚያስፈራት፡፡፡እንደምንም ደካማ እጃን አንቀሳቀሰችና ትከሻው ላይ አኑራ በመወዝወዝ..‹‹ካርሎስ ካርሎስ›› ስትል ጠራችው፡፡
በርግጎ ተነሳ‹‹..ምን …አመመሽ እንዴ?››
‹‹አይ ነጎድጎድ ፈራለሁ››
ከተቀመጠበት ተነሳና ወደእሷ ተንቀሳቀሰ….ርብራቡ ጠርዝ ላይ ከጎኗ ተቀመጠና እጆቿን በእጆቹ ውስጥ አስገብቶ ያሻሽላት ጀመር፡፡ከእሱ ሰውነት ወደእሷ እየተላለፈ ያለው ሙቀት ብቻ ሳይሆን ብርታትና ጥንካሬ ጭምር ነው፡፡
በድጋሚ‹‹በጣም እኮ ነው የፈረሁት››አለችው፡፡
‹‹አይዞሽ…ስጋታችን፤ፍረሀቶችንና እና ጥርጣሬዎቻችን ሰው በመሆናችን የተሰጡን ፀጋዎች ናቸው፡፡ካለበለዚያማ እህያና በቅሎ መሰል አይነት ስሜቶች ስለሌላቸው ከእኛ የተሻሉ እደለኞች ናቸው ልንል መሆኑ ነው?፡፡››
‹‹እሱስ እውትህን ነው››አለችና ይበልጥ ተለጠፈችበት
ወዲያው ሰማዩን አግቶ ይዞ የነበረውን ዝናብ ዘረገፈው፡፡የተሰራችው ጊዜያዊ ጎጆ ሙሉ በሙሉ በዛ ድቅድቅ ጨለማ የሚወርደውን የዝናብ ውሀ አግዳ ለማስቀረት ጥንካሬው አልነበራትም፡፡ሁለቱም በ5 ደቂቃ ውስጥ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ በዝናብ ራሱ፡፡እሷ ከህመሙና የሰውነት ጥንካሬዋ በመዳከሙ የተነሳ ዝናቡንና ቅዝቃዜውን መቋቋም ስላልቻለች ትዘፈዘፈች፣ካርሎስ የሚያደርገው ጠፋበት፡፡ ሙሉ በሙሉ ወደእንጨት አልጋው ወጣና ከእሷ ተስተካክሎ ተኛ…አቀፋትና ወደራሱ አስጠግቶ ከሰውነቱ ለጠፋት፡፡የናፈቀውን የእናቱን ጡት እንዳገኘ ህፃን ልጥፍ አለችበት፡፡የተሻለ ምቾት ተሰማት፡፡ከዝናብ ውርጅብኝ የምትሸሸግበት መጠለያ ዋሻ ያገኘች አይነት ስሜት ተሰማት፡፡ እጆቹን በረጠበ ልብሷ ስር ሰቅስቆ በማስገባት ሰውነቷን ላይ አሳረፈና ይዳብሳት ጀመር..፡፡ከዛ ቀስ እያለ ከንፈሩን ከንፋሯ ላይ አሳረፈና በቀስታ ይመጣት ጀመር፡፡አሁን ከውስጧ እየተቀጣጠለ ያለው ሙቀት ወደላይኛው የሰውነት ቆዳ በመድረስ ከላይ የሚያርፋባትን ዝናብ የሚያስከትልባትን ቅዝቃዜ እያተነ የሚያስወግድላት እየመሰላት ነው፡፡ጭልጥ ያለ ምናባዊ ህልም ውስጥ ነው የገባችው፡፡ከንፈራቸው ሳይላቀቅ ዝናቡም ከመቆሙ በፊት እሷ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወሰዳት፡፡
ስትነቃ ጎጆዋ በጥዋት የደመቀ የፀሀይ ፈንጣቂ አድምቋታል፡፡ሁሉ ነገር ብሩህ ፣ ሁሉ ነገር ዳማቅ ሆኖ ነው እየታየ ያለው፡፡እራሷን ለማንቀሳቀስ ሞከረች፡፡ አሁንም ሰውነቷ እንደተሳሰረ ነው፡፡ወደ ጎን አንገቷን መልሳ ተመለከተች፡፡ ለሊት ጎኗ ተኝቶ የነበረው ጉብል አሁን የለም፡፡አይኖቾን ብታንከራትትም ጎጆው ባዶ ነው፡፡ አንደምንም እራሷን አበረታታ ከተኛችበት ተነሳች፡፡ ዱላ መሰል እንጨት ተደግፋ እንደምንም እግሮቾን እየጎተተች ወደጎጆዋ በራፍ ሄደች፡፡ፊት ለፊቷ ያለው አማዞን ወንዝ እየተገማሸረ ጥሩ አቋም ላይ አንዳለ የማራቶን ራጭ ወደፊት እየገሰገሰ ነው፡፡አካባቢውን የሞሉት ውብና ማራኪ ወፎች ወዲህና ወዲያ አክሮባት እየሰሩ ይዝናናሉ.. አይኖቾን አሩቅ ስታማትር ካርሎስ በ500 ሜትር ርቀት በፓንት ብቻ አማዞን ወንዝ ውስጥ ጠልቆ ገብቶ ዓሳ ላመስገረ ሲዳክር ተመከተችው፡፡ፈገግ አለችና ወደ ውስጥ ተመለሰች፡፡ወደ ሻንጣቸው ተጠጋች ፡፡ውሀ የማያሳገባውን የሻንጣ ዚፕ ከፍታ ውስጥ ያለውን የካርሎስን ማስታወሻ ደብተር ከእነእስኪሪብቶው አወጣች፡፡እዛው መሬት ይዛ ተቀመጠችና ለመፅሀፍ ተዘጋጀች፡፡
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፡
፡
ልጅም ቶሎ ያንጠለጠለውን የእጅ ቦርሳ ጠረጴዛ ላይ አደረገና ከብር የተሠራ የሚመስል ሁለት የእጅ ብራስሌት መጀመሪያ ምስራቅ እጅ ላይ ቀጥሎ ናኦል እጅ ላይ አጠለቀና ከኪሱ ስልኩን አውጥቶ በማብራት ሲነካካ እጃቸው ላይ ያጠለቀላቸው ብራስሌት ቀለሙን ከብራማነት ወደ ደማቅ ሰማያዊነት ቀየረ።ዝም ብሎ ሁኔታውን ሲከታተል የነበረው ዳግላስ መናገር ጀመረ
"አሁን እንግደህ እህታችሁን እኔ ሳልሆን ለእናንተ ማመጣላችሁ ..እናንተ ናችሁ ለእኔ የምታመጡልኝ..." ብሎ ኑሀሚ የእሱን ሰው ገድላ ከሌላ ከእሱ ሰው ጋር እንደኮበለለች...እስከአሁንም በመላው አማዞን ደን ውስጥ ቢያስፈልጋት ሊያገኛት እንዳልቻለ...እሷን መሞቷን ካላረጋገጠ ወይም በህይወት እጅ ካላስገባት የሰላም እንቅልፍ እንደማይወስደው..ወንድሟን ያስመጣበት ምክንያት ተሳክቶላት እንኳን ማምለጥ ብትችል ለወንድሟ ደህንነት ስትል በፍቃዷ መልሳ እጅ እንድትሰጥ አቅዶ ያደረገው እንደሆነ አብራርቶ ከአሁን ሰዓት በኃላ እዛው እሱ የሚኖርበት ወለል ላይ የራሳቸው ክፍል እንደሚሰጣቸው እና እጃቸው ላይ በተጠለቀላቸው አንባር ሙሉ የ24 ሰዓት ክትትል እንደሚደረግላቸው ነገራቸው። እሷ መጥታ በፍቃዷ እጇን እስክትሰጥ ወይንም መሞቷ እስኪረጋገጥ ድረስ ከክፍላቸው መውጣት እንደማይችሉ...ፀባያቸውን እስካሳመሩና ችግር ለመፍጠር እስካልሞከሩ ድረስ የሚፈልጉት ነገር እንደሚያሟላላቸው አብራርቶላቸው.. ወደክፍላቸው እንዲወስዳቸው አዘዘ...።የታዘዘውም ታጣቂ እየጎተ ወሰዶ አንድ ለቀቅ ያለ ሻወርና ማንበቢያ ክፍል ያለው ባለአንድ ክፍል ቤት ውስጥ አስገብቶ ከውጭ ዘጋባቸው..
እቤት ውስጥ ከገብ በኃላ እንኳን ናኦል እና ምስራቅ ለረጅም ደቂቃ ደንዝዘውና ፈዘው ማህል ወለል ላይ በዝምታ ተገትረው ነበር።
ናኦል እንባ እየተናነቀው"ምስራቅ ምን ውስጥ ነው የገባነው..?ይሄ ሰውዬ ተጫወተብን"አላት ።
ምስራቅም ወደእሱ ተንደረደረችና አቀፈችው ።አንገቱ ስር ሽጉጥ ብላ በጆሮው "አትደንግጥ...እቅድ አለኝ"አለችው።
ዝም አለ...ከዚህ ለመውጣት ምን አይነት ተአምራዊ ዕቅድ ሊኖራት እንደሚችል ምንም ሊገለፅለት አልቻለም።ቢሆንም ከሞስራቅ ጋር ባሳለፋቸው በርካታ አመታት ብዙ ተአምር መሳይ ነገሮችን ስትከውንና ደጋግሞም ሲሳካላት ታዝቦልና የተናገረችው ነገር ንቆ ሊያልፈው አልደፈረም።...
ብራዚል/አማዞን ደን ውስጥ
አካባቢው ድቅድቅ ጨለማ ነው፡፡ጨረቃዋም በሰማይ ላይ ብርሀን አልፈነጠቀችም፡፡ከዋክብቱም የከሰሙ መስለዋል ፡፡ኑሀሚ ካርሎስ የሰራላት የአንጨት ርብራብ አልጋ ላይ ተኝታ የእጇ ጥዝጣዜ ታዳምጣለች፡፡እርግጥ ከትናንቱ የተሻ ጤንነት ላይ ብትገኝም ሰውነቷ ግን ሙሉ በሙሉ እደዛለ ነው፡፡በህይወቷ በእንዲህ አይነት ደካማንትና አቅመ ቢስነት ተሰምቷት አያውቅም፡፡ ካርሎስ በሶስት ቀን ውስጥ ሙሉ በሙሉ እደምታገግም ነግሯት ነበር ፡፡ አሁን አሁን ያለችበት ሁኔታ ስታስበው በሶስት ወር ተሽሏት ከዚህ አካባቢ የምትንቀሳቀስ እየመሰላት አይደለም፡፡ያም ሆኖ ግን ትናንትና ጉሮሮዋን ፈጥርቆ ነፍሷን ሊነጥቃት የነበረው ሲኦላዊ ህመም ዛሬ በሙሉ አቅሙ የለም፡፡ያ የሆነው ደግሞ ካርሎስ እጇ ላይ ባሰረለት የባህል መድሀኒት ምክንያት ነው፡፡
እንደምንም አንገቷን ወደ ዳር ሸርተት አድርጋ አየችው፡፡ እዛው ርብራብ አልጋ ጎን ባለ ጠፍጣፍ ድንጋይ ላይ ተቀምጦ አንገቱን በካኔቴራው ሙሉ በሙሉ ሸፍኖ የእንጨት አልጋውን ቋሚ ተደግፎ ጨልጥ ያለ እንቅልፍ ተኝቷል፡፡ አሳዘናት፡፡ቢቻላት ኩርምት ብሎ በተቀመጠበት እንቅልፍ የወሰደውን ይሄን መልካም ሰው ጎትታ ወደራሷ ስባ እሷ የተኛችበት የእንጨት ርብራብ ላይ ከጎኗ ሽጉጥ አድርጋው ብትተኛ ደስ ይላት ነበር ፡፡
ወዲያው ሀሳቧን ሳትጨርስ ነጎድጓድ በሰማዩ አንፀባራቂ ብርሀን እየረጨ ያንቧርቅ ጀመር፡፡የሚያስፈራ ደራጎናዊ ድምፅ አካባቢውን ያናጋው ጀመር፡፡ ኑሀሚ እንኳን በእንደዚህ አይነት ሁኔታ እንደዚህ አይነት ቦታ ሆና ይቅርና በሀገሯ ሰማይ ስር በገዛ ቤቷ እያለች ሳይቀር እንዲህ አይነት ነጎድጎድ በጣም ነው የሚያስፈራት፡፡፡እንደምንም ደካማ እጃን አንቀሳቀሰችና ትከሻው ላይ አኑራ በመወዝወዝ..‹‹ካርሎስ ካርሎስ›› ስትል ጠራችው፡፡
በርግጎ ተነሳ‹‹..ምን …አመመሽ እንዴ?››
‹‹አይ ነጎድጎድ ፈራለሁ››
ከተቀመጠበት ተነሳና ወደእሷ ተንቀሳቀሰ….ርብራቡ ጠርዝ ላይ ከጎኗ ተቀመጠና እጆቿን በእጆቹ ውስጥ አስገብቶ ያሻሽላት ጀመር፡፡ከእሱ ሰውነት ወደእሷ እየተላለፈ ያለው ሙቀት ብቻ ሳይሆን ብርታትና ጥንካሬ ጭምር ነው፡፡
በድጋሚ‹‹በጣም እኮ ነው የፈረሁት››አለችው፡፡
‹‹አይዞሽ…ስጋታችን፤ፍረሀቶችንና እና ጥርጣሬዎቻችን ሰው በመሆናችን የተሰጡን ፀጋዎች ናቸው፡፡ካለበለዚያማ እህያና በቅሎ መሰል አይነት ስሜቶች ስለሌላቸው ከእኛ የተሻሉ እደለኞች ናቸው ልንል መሆኑ ነው?፡፡››
‹‹እሱስ እውትህን ነው››አለችና ይበልጥ ተለጠፈችበት
ወዲያው ሰማዩን አግቶ ይዞ የነበረውን ዝናብ ዘረገፈው፡፡የተሰራችው ጊዜያዊ ጎጆ ሙሉ በሙሉ በዛ ድቅድቅ ጨለማ የሚወርደውን የዝናብ ውሀ አግዳ ለማስቀረት ጥንካሬው አልነበራትም፡፡ሁለቱም በ5 ደቂቃ ውስጥ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ በዝናብ ራሱ፡፡እሷ ከህመሙና የሰውነት ጥንካሬዋ በመዳከሙ የተነሳ ዝናቡንና ቅዝቃዜውን መቋቋም ስላልቻለች ትዘፈዘፈች፣ካርሎስ የሚያደርገው ጠፋበት፡፡ ሙሉ በሙሉ ወደእንጨት አልጋው ወጣና ከእሷ ተስተካክሎ ተኛ…አቀፋትና ወደራሱ አስጠግቶ ከሰውነቱ ለጠፋት፡፡የናፈቀውን የእናቱን ጡት እንዳገኘ ህፃን ልጥፍ አለችበት፡፡የተሻለ ምቾት ተሰማት፡፡ከዝናብ ውርጅብኝ የምትሸሸግበት መጠለያ ዋሻ ያገኘች አይነት ስሜት ተሰማት፡፡ እጆቹን በረጠበ ልብሷ ስር ሰቅስቆ በማስገባት ሰውነቷን ላይ አሳረፈና ይዳብሳት ጀመር..፡፡ከዛ ቀስ እያለ ከንፈሩን ከንፋሯ ላይ አሳረፈና በቀስታ ይመጣት ጀመር፡፡አሁን ከውስጧ እየተቀጣጠለ ያለው ሙቀት ወደላይኛው የሰውነት ቆዳ በመድረስ ከላይ የሚያርፋባትን ዝናብ የሚያስከትልባትን ቅዝቃዜ እያተነ የሚያስወግድላት እየመሰላት ነው፡፡ጭልጥ ያለ ምናባዊ ህልም ውስጥ ነው የገባችው፡፡ከንፈራቸው ሳይላቀቅ ዝናቡም ከመቆሙ በፊት እሷ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወሰዳት፡፡
ስትነቃ ጎጆዋ በጥዋት የደመቀ የፀሀይ ፈንጣቂ አድምቋታል፡፡ሁሉ ነገር ብሩህ ፣ ሁሉ ነገር ዳማቅ ሆኖ ነው እየታየ ያለው፡፡እራሷን ለማንቀሳቀስ ሞከረች፡፡ አሁንም ሰውነቷ እንደተሳሰረ ነው፡፡ወደ ጎን አንገቷን መልሳ ተመለከተች፡፡ ለሊት ጎኗ ተኝቶ የነበረው ጉብል አሁን የለም፡፡አይኖቾን ብታንከራትትም ጎጆው ባዶ ነው፡፡ አንደምንም እራሷን አበረታታ ከተኛችበት ተነሳች፡፡ ዱላ መሰል እንጨት ተደግፋ እንደምንም እግሮቾን እየጎተተች ወደጎጆዋ በራፍ ሄደች፡፡ፊት ለፊቷ ያለው አማዞን ወንዝ እየተገማሸረ ጥሩ አቋም ላይ አንዳለ የማራቶን ራጭ ወደፊት እየገሰገሰ ነው፡፡አካባቢውን የሞሉት ውብና ማራኪ ወፎች ወዲህና ወዲያ አክሮባት እየሰሩ ይዝናናሉ.. አይኖቾን አሩቅ ስታማትር ካርሎስ በ500 ሜትር ርቀት በፓንት ብቻ አማዞን ወንዝ ውስጥ ጠልቆ ገብቶ ዓሳ ላመስገረ ሲዳክር ተመከተችው፡፡ፈገግ አለችና ወደ ውስጥ ተመለሰች፡፡ወደ ሻንጣቸው ተጠጋች ፡፡ውሀ የማያሳገባውን የሻንጣ ዚፕ ከፍታ ውስጥ ያለውን የካርሎስን ማስታወሻ ደብተር ከእነእስኪሪብቶው አወጣች፡፡እዛው መሬት ይዛ ተቀመጠችና ለመፅሀፍ ተዘጋጀች፡፡
#ጉዞ_በፀሎት
(አቃቂ እና ቦሌ)
:
:
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ተካ አቶ ኃይለልኡል ባዘዙት መሰረት ሽጉጡን ሙሉ ጥይት ሞልቶ ወገቡ ላይ ከሸጎጠ በኃላ አጉሊ መሳሪያ ያዘና ማንን ሳያስከትል ቀጥታ መኪና ውስጥ ገብቶ ወደ ቃሊቲ ነዳው….የሰውዬውን ጥርጣሬ ምንም አልተዋጠለትም…‹‹ልጅቷ ስንት አማራጭ እያላት እንዴት እዛ ጭንቁርቁስ ቤት ከጭርቁስቁስ ሰዎች ጋር ለመቆየት ታስባለች? ››ሲል እራሱን ጠየቀ፡፡ ሊዋጥለት አልቻም…፡፡
በፀሎት ከጠፋችበት ቀን አንስቶ በመላ ሀገሪቱ ፍላጋ የተሰማሩትን በመቶ የሚቆጠሩ ግለሰቦችን የሚመራው ..መረጃ የሚቀበለው አዲስ ቦታ ስምሪት የሚሰጠው እሱ ነው፡፡እና የእሱ እቅድ የሆነ ቦታ መኖሯን በሆነ መንገድ ቀድሞ ቢደርስበት እንደምንም ብሎ የራሱ ሰው በሚስጥር እንዲያገኛት አድርጎ በእጅ አዙር 5 ሚሊዬኑን የሽልማት ገንዘብ ለመቀባበል አቅዶ ከልቡ እየሰራ ነበር...እርግጥ እንደዚህ እያደረገ መሆኑን ቀድመው ቢደርሱበት ያለምንም ማቅማማት ግንባሩን በጥይት እንደሚነድሉት እርግጠኛ ነው…ግን በህይወት የተሻለ ነገር ማግኘት ሪስክ መውሰድ የግድ እንደሆነ የሚያምን ስለሆነ ነገሩን ልክ እንደቁማር ነው ያየው..‹‹ወይ በላለሁ..ወይ ደግሞ እበላለው››ብሎ ነበር ውሳኔ ላይ ደርሶ በተግባር ሲንቀሳቀስ የከረመው፡፡…አሁን ሰውዬው እንደሚሉት ልጅቷ የገመቱት ቦታ የምትገኝ ከሆነ ያ ሁ እቅዱ ውሀ በላው ማለት ነው፡፡ቦታውን ራሳቸው ቀድመው አውቀው ስለነገሩት ሽልማት የሚሰጡበት ምንም ምክንያት የለም….መኪናውን ወደእዛ ሲያሽከረክር በውስጡ በፀሎት የተባለው ቤት በፍፅም እንዳትገኝ እየፀለየ ነበር፡፡እንደደረሰ ከመንገድ ማዶ አስፓልት ጠርዝ ላይ መኪናውን ፓርክ አደረገና የመኪናው መስኮት በከፊል ከፍቶ ማጊሊያ መነፅሩን ወደእነ አቶ ለሜቻ ግቢ አነጣጠረና ገቢ ወጪውን መመልከትና በመሀከልም የተለየ ነገር ያገኘ ሲመስለው በሞባይሉ ፎቶ ማንሳት ጀመረ…
ስራ የጀመረው ከጥዋቱ 5 ሰዓት አካባቢ ቢሆንም እሰከ 10 ሰዓት ሁለት ሶስት ጊዜ አሮጊት ሴት ስትወጣ ስትገባ ከማየት ውጭ በግቢው ውስጥ አይን የሚስብ ምንም አይነት እንቅስቃሴ አልነበረም…ሰዓቱ እየረዘመ ሲሄድ ተስፋ እየቆረጠና እየተሰላቸ መጣ…ለዛሬ ይበቃኛል ብሎ 11 ሰዓት ላይ አካባቢውን ለቆ ወደቤቱ ሄደ ..
በማግስቱ በጥዋት ማለዳ አንድ ሰዓት ላይ ነበር የመጣው፣እና ሁለት ሰዓት ላይ የሚፈልገውን አገኘ ..ደጋግሞ ፎቶ አነሳው…በቤቱ አንድ ሴት ልጅ ብቻ እንዳላቸው አጣርቷል ..አሁን እየገቡ እየወጡ ያሉት ግን በተቀራራቢ እድሜ ላይ የሚገኙ ሁለት ወጣቶች ናቸው፡፡አንደኛዋ የቤቱ ልጅ እንደሆነች እርግጠኛ ነው…ሁለተኛዋ ግን የሚፈልጋት የባለፀጋው ቅምጥል ልጅ ትሁን አትሁን መለየት አልቻለም…የለበሰችው ልብስ የተለመደ አይነት ነው..በዛ ላይ ፊቷን ጭንቅላቷን ጭምር በሻርፕ ሸፍናለች…ዝም ብሎ ከመኪናው በመውረድና በእግሩ ወደ አጥሩ በመጠጋት ከቅርብ ርቀት በርከት ያለ ፎቶ አነሳና ለአቶ ኃይለ ልኡል ላከላቸው፡፡
አቶ ኃይለልኡል በዚህ ጊዜ ከባለቤታቸው ጋር በሰለሞን በሚሾፈር መኪና ከቢሾፍቱ ወደአዲስ አበባ እየተመለሱ ነበር፡፡ስልካቸው ድምፅ ሲያሰማ ከኪሳቸው አወጡና ተመለከቱት..መልዕክት መሆኑን ሲያዩ ከፈቱት…አይናቸው ተጉረጠረጠ….
‹‹እራሷ ነች ..ልጄ እራሷ ነች….ከጎናቸው ያለችው ሚሳታቸው ላይ ተጠመጠሙና ጉንጮቾን አገላብጠው ይስሙ ጀመር››
‹‹እንዴ ኃይሌ ምን ተፈጠረ..?ምን ተገኘ..አረ ንገረኝ?››
‹‹ይሄውልሽ..እንቺ እይው..ፊቷን ብትሸፋፈንም እራሷ ነች፡፡››ወይዘሮ ስንዱ ስልኩን ከባላቸው እጅ ተቀበሉና አፍጥጠው ተመለከቱ…..ከባላቸው በበለጠ በመደነቅ ኡኡ.አሉ…መኪናዋን በእልልታ አደባላለቁት…ሰለሞን የነገሩ ውል ስላልገባው መሪውን ጠመዘዘና የመንገዱን ዳር አስይዞ መኪናዋን አቆማት…በራፉን ከፍተው ወረዱ….እሱም ተከትሏቸው ወረደ‹‹አረ ለእኔም ንገሩኝ ምንድነው? እንዲህ የሚያስፈነጥዝ ደስታ፡፡››
‹‹ልጃችን የት እንዳለች አወቅን..እያት ተመልከት››ስልኩን ከሚስታቸው ተቀበሉና ለሰለሞን አቀበሉት..አንድ ፊቷ በቅጡ የማይታይ ወጣት ፎቶ ነው…ግን በፀሎት እንደሆነች ወዲያው ነው ያወቃት..ሙሉ ፊቷን ሳያይ እሷ እንደሆነች አንዴት እንዳወቀ አልገባውም…››
‹‹አየህ …ልጃችን እራሷ ነች…ሰው እንዳይለያት ነው ፊቷን የሸፋፈነችው……››
‹‹ለመሆኑ የት ነው ያለችው?››ጠየቀ ሰሎሞን፡፡
‹‹የት እዳለች ቆይ ነግራችኃላው››ብለው ስልኩን ተቀበሉና ደወሉ
‹‹ሄሎ….ፎቶው ደርሶኛል፡፡››
‹‹አዎ ሳስበው እሷ ትመስለኛለች››
‹‹አዎ እሷ እራሷነች…ከቦታው እንዳትንቀሳቀስ..እዛው ጠብቀን…ከቢሾፍቱ እየተመለስን ስለሆነ ከ15 ደቂቃ በኃላ ያለህበት እንደርሳለን››
‹‹ወጥታ ከሄደችስ…?ላስቁማት››
‹‹አይ..ልጄን ቀጥታ እኔው ነኝ የማገኛት..እንዳታስቆማት ትደነግጥብኛለች…ከቤት ከወጣች ዝም ብለህ በርቀት እየተከታተልክ ያለችበትን ታሳውቀኛለህ፡››
‹‹እሺ..ጌታዬ እንዳሉት አደርጋለው››
‹‹ጎበዝ ..እንዳስደሰትከኝ አስደስትሀለው…ቆንጆ ጉርሻ ይጠብቅሀል ››
‹‹እሺ ጌታዬ››ስልኩን ዘጉና‹‹በሉ ጊዜ አናባክን ..ግቡና እንሂድ››
‹‹እንዴ የት አንዳለች ንገረን እንጂ……?››ወ.ሮ ስንዱ ጠየቁ
‹‹ስንድ ልጃችን ሰዎቹ ጋር ነው ያለችው….››
‹‹የትኞቹ ሰዎች››
‹‹እነአቶ ለሜቻ ጋር..ማለቴ የልብ ለጋሾ ቤተሰብ ጋር ነው ያለችው››
‹‹ወይ ጉዴ….አሁን ምንድነው የምናደርገው?››እያሉ ወደመኪናው ገቡ፡፡ አቶ ኃይለልኡልም ተከትለዋቸው ገቡ….ሰለሞን በሰማው ያልተጠበቀ ነገር ግራ እንደተጋባና ምን ማድረግ እንዳለበት እያሰላሰለ ገቢና ገባ፡፡ መኪናውን አንቀሳቀሳት…ባልና ሚስቶቹ በደስታ ሰክረው እሱን ከቁብ ሳይቆጥሩት እርስ በርስ በፈንጠዝያ ሲጎሻሸምና ሲሳሳሙ እሱ ምን ማድረግ እንዳለበትና ይሄንን ያለጊዜው ያጋጠመውን ነገር እንዴት እንደሚፈታ እያሰላሰለ ነበር የሚነዳው….
አቃቂ አቶ ለሜቻ ቤት ለመድረስ 500 ሜትር ያህል ሲቀራቸው የመኪናውን መሪ ወደግራ ጠመዘዘና ፊት ለፊት ከሚታየው ሆቴል ይዞቸው ገባ..ባልና ሚስቶቹ በድንጋጤ እርስ በርስ ተያዩ
‹‹ሰለሞን…ምን እያደረክ ነው?››አቶ ኃይለልኡል ጠየቁ፡፡
‹መነጋገር አለብን››
‹‹ስለምን?››
‹‹አሁን ልጃቹህ ጋር ከመሄዳችሁ በፊት አረፍ ብለን መነጋገር አለብን››
‹‹ምን መነጋገር ያስፈልጋል…?በቃ እኔና እናቷ ሄደን ልጃችንን ወደቤት ይዘን እንሄዳለን….እንደምታየው አሁን ሁሉ ነገር ውብ እና የተስተካለከለ ነው..አይዞህ
አታስብ…ከንተጋር ያለንን ነገር እንቀጥላለን..ከሶስት ቀን በኃላም ወደአልከው ቦታ ትወስደናለህ››
መኪናውን አቆመና ሞተሩን አጥፍቶ ወደኃላ ዞረ..ፊት ለፊት እያያቸው‹‹ይሄ ነገር እንደምታስብት ቀላል ይመስላችኃላ?››
‹‹ማለት?››
‹‹አሁን ያለችበት ቤት ሄደችሁ በማንኳኳት..ነይ ልጄ በቃ አግኝተንሻል አሁን ወደቤትሽ ተመለሺ ብትሏት ..እሺ ብላ በደስታ ዘላ የምትጠመጠምባችሁ ይመስላችኃላ…እምቢ መሄድ አልፈልግም ብትል ምን ታደርጋላችሁ ?በግድ በጎረምሳ አሳዝላችሁ መኪና ውስጥ በመክተት ወደቤት ትወስዷታላችሁ….?ከዛስ..?አንድ ክፍል ውስጥ ቆልፋችሁባት በራፍ ላይ ሁለት ጠብደል ጠባቂ ታቆማላችሁ?እስኪ ንገሩኝ ምንድነው የምደርጉት?››
(አቃቂ እና ቦሌ)
:
:
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ተካ አቶ ኃይለልኡል ባዘዙት መሰረት ሽጉጡን ሙሉ ጥይት ሞልቶ ወገቡ ላይ ከሸጎጠ በኃላ አጉሊ መሳሪያ ያዘና ማንን ሳያስከትል ቀጥታ መኪና ውስጥ ገብቶ ወደ ቃሊቲ ነዳው….የሰውዬውን ጥርጣሬ ምንም አልተዋጠለትም…‹‹ልጅቷ ስንት አማራጭ እያላት እንዴት እዛ ጭንቁርቁስ ቤት ከጭርቁስቁስ ሰዎች ጋር ለመቆየት ታስባለች? ››ሲል እራሱን ጠየቀ፡፡ ሊዋጥለት አልቻም…፡፡
በፀሎት ከጠፋችበት ቀን አንስቶ በመላ ሀገሪቱ ፍላጋ የተሰማሩትን በመቶ የሚቆጠሩ ግለሰቦችን የሚመራው ..መረጃ የሚቀበለው አዲስ ቦታ ስምሪት የሚሰጠው እሱ ነው፡፡እና የእሱ እቅድ የሆነ ቦታ መኖሯን በሆነ መንገድ ቀድሞ ቢደርስበት እንደምንም ብሎ የራሱ ሰው በሚስጥር እንዲያገኛት አድርጎ በእጅ አዙር 5 ሚሊዬኑን የሽልማት ገንዘብ ለመቀባበል አቅዶ ከልቡ እየሰራ ነበር...እርግጥ እንደዚህ እያደረገ መሆኑን ቀድመው ቢደርሱበት ያለምንም ማቅማማት ግንባሩን በጥይት እንደሚነድሉት እርግጠኛ ነው…ግን በህይወት የተሻለ ነገር ማግኘት ሪስክ መውሰድ የግድ እንደሆነ የሚያምን ስለሆነ ነገሩን ልክ እንደቁማር ነው ያየው..‹‹ወይ በላለሁ..ወይ ደግሞ እበላለው››ብሎ ነበር ውሳኔ ላይ ደርሶ በተግባር ሲንቀሳቀስ የከረመው፡፡…አሁን ሰውዬው እንደሚሉት ልጅቷ የገመቱት ቦታ የምትገኝ ከሆነ ያ ሁ እቅዱ ውሀ በላው ማለት ነው፡፡ቦታውን ራሳቸው ቀድመው አውቀው ስለነገሩት ሽልማት የሚሰጡበት ምንም ምክንያት የለም….መኪናውን ወደእዛ ሲያሽከረክር በውስጡ በፀሎት የተባለው ቤት በፍፅም እንዳትገኝ እየፀለየ ነበር፡፡እንደደረሰ ከመንገድ ማዶ አስፓልት ጠርዝ ላይ መኪናውን ፓርክ አደረገና የመኪናው መስኮት በከፊል ከፍቶ ማጊሊያ መነፅሩን ወደእነ አቶ ለሜቻ ግቢ አነጣጠረና ገቢ ወጪውን መመልከትና በመሀከልም የተለየ ነገር ያገኘ ሲመስለው በሞባይሉ ፎቶ ማንሳት ጀመረ…
ስራ የጀመረው ከጥዋቱ 5 ሰዓት አካባቢ ቢሆንም እሰከ 10 ሰዓት ሁለት ሶስት ጊዜ አሮጊት ሴት ስትወጣ ስትገባ ከማየት ውጭ በግቢው ውስጥ አይን የሚስብ ምንም አይነት እንቅስቃሴ አልነበረም…ሰዓቱ እየረዘመ ሲሄድ ተስፋ እየቆረጠና እየተሰላቸ መጣ…ለዛሬ ይበቃኛል ብሎ 11 ሰዓት ላይ አካባቢውን ለቆ ወደቤቱ ሄደ ..
በማግስቱ በጥዋት ማለዳ አንድ ሰዓት ላይ ነበር የመጣው፣እና ሁለት ሰዓት ላይ የሚፈልገውን አገኘ ..ደጋግሞ ፎቶ አነሳው…በቤቱ አንድ ሴት ልጅ ብቻ እንዳላቸው አጣርቷል ..አሁን እየገቡ እየወጡ ያሉት ግን በተቀራራቢ እድሜ ላይ የሚገኙ ሁለት ወጣቶች ናቸው፡፡አንደኛዋ የቤቱ ልጅ እንደሆነች እርግጠኛ ነው…ሁለተኛዋ ግን የሚፈልጋት የባለፀጋው ቅምጥል ልጅ ትሁን አትሁን መለየት አልቻለም…የለበሰችው ልብስ የተለመደ አይነት ነው..በዛ ላይ ፊቷን ጭንቅላቷን ጭምር በሻርፕ ሸፍናለች…ዝም ብሎ ከመኪናው በመውረድና በእግሩ ወደ አጥሩ በመጠጋት ከቅርብ ርቀት በርከት ያለ ፎቶ አነሳና ለአቶ ኃይለ ልኡል ላከላቸው፡፡
አቶ ኃይለልኡል በዚህ ጊዜ ከባለቤታቸው ጋር በሰለሞን በሚሾፈር መኪና ከቢሾፍቱ ወደአዲስ አበባ እየተመለሱ ነበር፡፡ስልካቸው ድምፅ ሲያሰማ ከኪሳቸው አወጡና ተመለከቱት..መልዕክት መሆኑን ሲያዩ ከፈቱት…አይናቸው ተጉረጠረጠ….
‹‹እራሷ ነች ..ልጄ እራሷ ነች….ከጎናቸው ያለችው ሚሳታቸው ላይ ተጠመጠሙና ጉንጮቾን አገላብጠው ይስሙ ጀመር››
‹‹እንዴ ኃይሌ ምን ተፈጠረ..?ምን ተገኘ..አረ ንገረኝ?››
‹‹ይሄውልሽ..እንቺ እይው..ፊቷን ብትሸፋፈንም እራሷ ነች፡፡››ወይዘሮ ስንዱ ስልኩን ከባላቸው እጅ ተቀበሉና አፍጥጠው ተመለከቱ…..ከባላቸው በበለጠ በመደነቅ ኡኡ.አሉ…መኪናዋን በእልልታ አደባላለቁት…ሰለሞን የነገሩ ውል ስላልገባው መሪውን ጠመዘዘና የመንገዱን ዳር አስይዞ መኪናዋን አቆማት…በራፉን ከፍተው ወረዱ….እሱም ተከትሏቸው ወረደ‹‹አረ ለእኔም ንገሩኝ ምንድነው? እንዲህ የሚያስፈነጥዝ ደስታ፡፡››
‹‹ልጃችን የት እንዳለች አወቅን..እያት ተመልከት››ስልኩን ከሚስታቸው ተቀበሉና ለሰለሞን አቀበሉት..አንድ ፊቷ በቅጡ የማይታይ ወጣት ፎቶ ነው…ግን በፀሎት እንደሆነች ወዲያው ነው ያወቃት..ሙሉ ፊቷን ሳያይ እሷ እንደሆነች አንዴት እንዳወቀ አልገባውም…››
‹‹አየህ …ልጃችን እራሷ ነች…ሰው እንዳይለያት ነው ፊቷን የሸፋፈነችው……››
‹‹ለመሆኑ የት ነው ያለችው?››ጠየቀ ሰሎሞን፡፡
‹‹የት እዳለች ቆይ ነግራችኃላው››ብለው ስልኩን ተቀበሉና ደወሉ
‹‹ሄሎ….ፎቶው ደርሶኛል፡፡››
‹‹አዎ ሳስበው እሷ ትመስለኛለች››
‹‹አዎ እሷ እራሷነች…ከቦታው እንዳትንቀሳቀስ..እዛው ጠብቀን…ከቢሾፍቱ እየተመለስን ስለሆነ ከ15 ደቂቃ በኃላ ያለህበት እንደርሳለን››
‹‹ወጥታ ከሄደችስ…?ላስቁማት››
‹‹አይ..ልጄን ቀጥታ እኔው ነኝ የማገኛት..እንዳታስቆማት ትደነግጥብኛለች…ከቤት ከወጣች ዝም ብለህ በርቀት እየተከታተልክ ያለችበትን ታሳውቀኛለህ፡››
‹‹እሺ..ጌታዬ እንዳሉት አደርጋለው››
‹‹ጎበዝ ..እንዳስደሰትከኝ አስደስትሀለው…ቆንጆ ጉርሻ ይጠብቅሀል ››
‹‹እሺ ጌታዬ››ስልኩን ዘጉና‹‹በሉ ጊዜ አናባክን ..ግቡና እንሂድ››
‹‹እንዴ የት አንዳለች ንገረን እንጂ……?››ወ.ሮ ስንዱ ጠየቁ
‹‹ስንድ ልጃችን ሰዎቹ ጋር ነው ያለችው….››
‹‹የትኞቹ ሰዎች››
‹‹እነአቶ ለሜቻ ጋር..ማለቴ የልብ ለጋሾ ቤተሰብ ጋር ነው ያለችው››
‹‹ወይ ጉዴ….አሁን ምንድነው የምናደርገው?››እያሉ ወደመኪናው ገቡ፡፡ አቶ ኃይለልኡልም ተከትለዋቸው ገቡ….ሰለሞን በሰማው ያልተጠበቀ ነገር ግራ እንደተጋባና ምን ማድረግ እንዳለበት እያሰላሰለ ገቢና ገባ፡፡ መኪናውን አንቀሳቀሳት…ባልና ሚስቶቹ በደስታ ሰክረው እሱን ከቁብ ሳይቆጥሩት እርስ በርስ በፈንጠዝያ ሲጎሻሸምና ሲሳሳሙ እሱ ምን ማድረግ እንዳለበትና ይሄንን ያለጊዜው ያጋጠመውን ነገር እንዴት እንደሚፈታ እያሰላሰለ ነበር የሚነዳው….
አቃቂ አቶ ለሜቻ ቤት ለመድረስ 500 ሜትር ያህል ሲቀራቸው የመኪናውን መሪ ወደግራ ጠመዘዘና ፊት ለፊት ከሚታየው ሆቴል ይዞቸው ገባ..ባልና ሚስቶቹ በድንጋጤ እርስ በርስ ተያዩ
‹‹ሰለሞን…ምን እያደረክ ነው?››አቶ ኃይለልኡል ጠየቁ፡፡
‹መነጋገር አለብን››
‹‹ስለምን?››
‹‹አሁን ልጃቹህ ጋር ከመሄዳችሁ በፊት አረፍ ብለን መነጋገር አለብን››
‹‹ምን መነጋገር ያስፈልጋል…?በቃ እኔና እናቷ ሄደን ልጃችንን ወደቤት ይዘን እንሄዳለን….እንደምታየው አሁን ሁሉ ነገር ውብ እና የተስተካለከለ ነው..አይዞህ
አታስብ…ከንተጋር ያለንን ነገር እንቀጥላለን..ከሶስት ቀን በኃላም ወደአልከው ቦታ ትወስደናለህ››
መኪናውን አቆመና ሞተሩን አጥፍቶ ወደኃላ ዞረ..ፊት ለፊት እያያቸው‹‹ይሄ ነገር እንደምታስብት ቀላል ይመስላችኃላ?››
‹‹ማለት?››
‹‹አሁን ያለችበት ቤት ሄደችሁ በማንኳኳት..ነይ ልጄ በቃ አግኝተንሻል አሁን ወደቤትሽ ተመለሺ ብትሏት ..እሺ ብላ በደስታ ዘላ የምትጠመጠምባችሁ ይመስላችኃላ…እምቢ መሄድ አልፈልግም ብትል ምን ታደርጋላችሁ ?በግድ በጎረምሳ አሳዝላችሁ መኪና ውስጥ በመክተት ወደቤት ትወስዷታላችሁ….?ከዛስ..?አንድ ክፍል ውስጥ ቆልፋችሁባት በራፍ ላይ ሁለት ጠብደል ጠባቂ ታቆማላችሁ?እስኪ ንገሩኝ ምንድነው የምደርጉት?››
#የድንግሊቷ_አፍቃሪዎች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
====================
ኩማንደር አለማየሁ የአላዛርን ስልክ ተቀብሎ እሷን ወደማረፊያ ክፍል ከላካት በኃላ ጥልቅ ትዝታ ውስጥ ነው የተዘፈቀው፡፡ከእሷ ጋር ብቻ ሳይሆን ከሌሎች ሁለት ጓደኞቹ ጋር የነበረው የልጅነት እና የወጣትነት ትዝታ በብዙ ውጣ ውረዶች የተሞላ፤ደስታንም ሀዘንንም በውስጡ ያጨቀ ነበር፡፡አዎ አለማየሁ እንደሚያስታውሰው ሰሎሜ ለሶስቱ ወንዶች ልክ እንደጨረቃቸው ነበረች፡፡እነሱ ደግሞ በዙሪያዋ እየተሸከረከሩ ውበቷን የሚያጎሉላት ፍንጥርጣሪ ከዋክብቶች፡፡እናም ሰሎሜ ሶስቱንም ጓደኞቾን የምትወድበት የራሷ የሆነ የተለየ ምክንያት እንደነበራት ይገምታል፡፡ለምሳሌ አላዛርን በውበቱና በልስልስ ባህሪው…እሱን በኮሚክነቱና በድፍረቱ ሁሴንን በጉብዝናው እና በብልሀቱ ፡፡
አሌክስ ፤አላዛር እና ሁሴን ከልጅነታቸው ጀምሮ በእሷ ምክንያት ችግር ውስጥ እንደገቡ ነበር፡፡አረ ከእነሱም አልፎ ወላጆቻቸውን ጨምሮ በተደጋጋሚ ጊዜ ችግር ውስጥ ገብተው እንደሚያውቀው ያስታውሳል፡፡አንድ ጊዜ የዘጠኝ አመት ገዳማ ልጆችና የሁለተኛ ክፍል ተማሪ እንደሉ ነበር፡፡ጊዜው የበልግ ዝናብ በሚዘንብበት ወቅት ስለሆነ መስኩ ጠቅላላ ውሀ ባቆሩ መሬቶችና ጭቃ ባላቆጡ መንገዶች የተሞላ ነበር፡፡ታዲያ የትምህርት ቤት የእረፍት ጊዜ ደውል ከተደወለ በኋላ ሰሎሜ ከእነሱ ተነጥላ ሳያዮት ሾልካ ትሔዳች፡፡እደዛ ያደረገችው ሽንቷ ወጥሯት ስለነበረ ወደ ሽንት ቤት ነበር፡፡ስትመለስ ግን ጎረምሳ ጎረምሳ ከሚጫወቱ የስድስተኛ ክፍል ሴት ተማሪዎች እጅ ትወድቃለች፡፡ሴቶቹ እድሜያቸው አስራዎቹ ቤት የገባና በቁጥርም ሶስት ነበሩ፡፡ዙሪያዋን ከበዋት ጆሮዋን እየቆነጠጡ ውሀ ያቆረ ሜዳ ውስጥ በባዶ እግሯቾ ገብታ እያንቦረጨቀች መዝሙር እንድትዘምርላቸው አስገደዷት፡፡
እንዳሏት እየዘለለች ስትዘምር በጭቃ የላቆጠው እና ውሀ ያቆረው መሬት እየተፈናጠረ የለበሰችውን ሙሉ ነጭ ቀሚስ እንዳልነበረ አበላሸባት…፡፡ከዛም አልፏ ፊቷና ጸጉሯ ላይ ሳይቀር ተፈነጣትጥሮባት.. በጭቃ የተሰራች አሻንጉሊት አስመሰሏት ነበር …በንዴትና በፍርሀት እንባዋ እየረገፈ ያሏትን ስታደርግ ቆየች..ልጆቹ የትምህርት ቤት የእርፍት ጊዜ ማለቁን የሚያበስር ደውል ሲደወል ነበር ጥለዋት የሄዱት …ከዛ ምን ታድርግ ተማሪዎች ሁሉ ወደክፍል ከገቡ በኃላ እያለቀሰች ሄዳ ክፍላቸው ጀርባ ባለ መቀመጫ ተቀመጠች፡፡እንደዛ ጨቅይታና ልብሷ ጠቅላላ ተበላሽቶ እንዴት ወደክፍል ትግባ..?አስተማሪውስ ምን ይላታል?፡፡ ወደቤት እንዳትሄድ ደግሞ ቦርሳዋ ክፍል ውስጥ ነበር፡፡
በዚያን ቀን እሱን ጨምሮ ሁለቱ ጓደኞቾ እረፍትን ጨምሮ ክፍል ውስጥ ባለመኖሯ እንዴት ተደናግጠው እንደነበረ ትዝ ይለዋል፡፡‹‹የት ሄደች?››የሶስቱም ጥያቄ ነበር፡፡የሚቀርቧትን ሴቶች ሁሉ ቢጠይቁ አይተናታል የሚል ሰው አላገኙም፡፡…አስተማሪ መጥቶ ክፍለጊዜው ከመጀመሩ በፊት እሷን ፍለጋ ክፍሉን ለቀው በመውጣት የትምህርት ቤቱን አጥር ጊቢ በሳምሶማ ሩጫ ማሳስ ጀመሩ፡፡በስተመጨረሻ ከክፍላቸው ጀርባ እንዳልሆነች ሆና አገኞት፡፡….ሶስቱም ነበር አብረዋት ያለቀሱት፡፡በዛን ወቅት ሲያያት የተሰማውን ድንጋጤና ንዴት ትዝ አለውና ፈገግ አለ ና ወደ ትዝታው ተመለሰ፡፡
በወቅቱ ወደ ቧንቧ ወሰዷት ..ፊቷንና፤ ፀጉሯን እና እግሮቾንም በማጣብ የአንዳቸውን ጃኬት አለበሷት…ሶስቱም ወደክፍላቸው ገብተው የእሷን እና የራሳቸውን ቦርሳ ጭምር በመያዝ ወጡና እሷን መሀከል አድርገው በማፅናናት ወደቤት ነበር ይዘዋት የሄድት፡፡
ከዛ ምሽቱን ሙሉ በወላጆቻቸው ተገደው ወደቤት እስኪገቡ ድረስ ‹‹እንዴት አድርገን ነው የእኛን ንግስት ያስለቀሷትን ሴቶች በእጥፍ የምናስለቅሳቸው?›› ብለው ሲማከሩና እቅዶች ሲነድፉ አመሹ ፡፡
የእነሱን ሰሎሜን ያቆሸሾትና ያስለቀሷት ልጆቹ ሰሚራ፤ ሳራና፤ ሰላም ይባለሉ እንደነበር አሁን ድረስ ስማቸውን ከነመልካቸው ያስታውሰዋል፡፡
‹‹እኛ ሶስት ነን አይደል?››ሲል ነበር አለማየሁ ጓደኞቹን የጠየቀው፡፡
‹‹አዎ››መለሱለት፡፡
‹‹እሺ ሰሎሜን ያስለቀሷትም ሴቶች ሶስት ናቸው››
‹‹አዎ ትክክል ሶስት ትላልቅ ሴቶች ናቸው››መለሱለት፡፡
‹‹ጥሩ..አንዳ እንድ እንከፋፈላቸዋለን››አለ አለማየሁ፡፡
አላዛር ተቃወመ‹‹አይሆንም እኔ አልስማማም››
‹‹ለምንድነው ማትስማማው?››
‹‹እኔ ከሰሎሜ ውጭ ሌላ ሴት አልፈልግም…..የእኔን ድርሻም ከፈለጋችሁ ተካፈሉና ውሰዷት››ሲል ነበር አቋሙን ያሳወቀው፡፡
‹‹አንተ ጀዝባ የሆንክ ልጅ …የምንካፈላቸው እኮ የእኛ ልናደርጋቸው አይደለም.. ልናሰቃያቸውና ልናስለቅሳቸው ነው…ለሰሎሜ ልንበቀልላት ነው፡፡››
ሁሴን ‹‹ገባኝ..ለመበቀል ግን ለምን መከፋፈል አስፈለገ?››ሲል ጠየቀ
‹‹‹ለእያንዳንዳችን የደረሰችንን ሴት የሆነ ዘዴ ፈልገን በተማሪ ፊት እንድታፍር ፤ እንድታለቅስና እንድትፀፀት እናደርጋታላን፡፡ታዲያ ከሶስታችን በጣም በአስቂኝና አስደናቂ መንገድ ተጠቅሞ ማስለቀስ የቻላ የበለጠ ሰሎሜን ያፈቅራታል ማለት ነው፡፡››እንደዚህ አይነት ሀሳብና እቅድ በዛ እድሜ እንዴት ማመንጨት እንደቻለ ዛሬም ሲያስበው በራሱ ይገረማል፡፡
ሁሴን‹‹ተስማምቼለው…እኔ ከሁለታችሁም በላይ ጂኒዬስ ስለሆኑክ ካሁኑ መሸነፋችሁን እመኑ››ሲል ጎረረ፡፡
‹‹ሞኞ በትምህርት ጎበዝ ሆንክ ማለት በእንደዚህ አይነት ነገርም ጎበዝ ነህ ማለት አይደለም?››ሲል ነበር የመለሰለት፡፡
በክርክራቸው የተሰላቸው አላዘር‹‹እባካችሁ አትጨቃጨቁብኝ. .አሁን እንዴት አድርገን ነው ሴቶቹን ምንካፈላቸው››ሲል ግራ የገባውን ነገር ጠየቀ፡፡
‹‹እጣ እንጥላለን›› ብለው ተስማሙና በዛው መሰረት ተከፋፈሉ…ለሁሉም የአንድ ሰምንት ጊዜ ተሰጣቸው፡፡
ይሄ ውይይት በተደረገ በአራተኛው ቀን ሰላም በምትባለው ልጅ ላይ የመጀመሪያው ጥቃት ደረሰባት፡፡ሁሴን ለመጀመሪያ ሁለት ቀናት ልጆቹን ስር ስራቸው እየሄደ የሆነ ቦታ ተቀምጠው ሲያወሩ በሆነ ከለላ እየተደበቀ የሚያወሩትን በመስማት መረጃ ሰበሰበ፡፡በሶስተኛው ቀን እንደምንም ወደስድስተኛ ክፍል ሾልኮ ገባና ከሰላም ቦርሳ ውስጥ አንድ ደብተር በመስረቅ ወደቤቱ ይዞ ሄዳ፡፡ከዛ ለሁለት ሰዓት ያህል ፊደል አጣጣሏንና የእጅ ፅሁፏን ሲለማመድ ቆየ..ከዛ እርግጠኛ ሲሆን ያሰበውን ወደማድረግ ተሸጋገረ፡፡
በእሷ ስም ለአንዱ የክፍሏ ልጅ ደብዳቤ ፃፈ፡፡
ውድ ወንድይራድ…..እንዴት ነህ..?እኔ የአንተ ፅጌረዳ ከአንተ ሀሳብና ናፍቆት በስተቀር ሰላም ነኝ፡፡ይሄንን ደብዳቤ የፃፍኩልህ ምን ያህል እንደማፈቅርህ ፊት ለፊትህ ቆሜ ልነግርህ መድፈር ስላቃተኝ ነው፡፡ታውቃለህ ደግሞ እነዛ አስጠሊታ ሁለት ጓደኞቼ ሁል ግዜ እንደተጣበቁብኝ ነው…ሲያስጠሉ፡፡ውዴ ከአሁን በኋላ አንተን ካገኘሁ እነሱ አያስፈልጉኝም…ድሮውም እንደመደበሪያ ነበር የምጠቀምባቸው፡፡ውዴ በእርግጠኝነት አንተም እንደምታፈቅረኝ አውቃለሁ…እንደእኔ አይነት ቆንጆ እንዴት ላታፈቅር ትችላለህ?፡፡ለማንኛውም መልስህን በጉጉት እጠብቃለው፡፡ደግሞ የመልሱን ደብዳቤ ስትሰጠኝ አነዛ ቅናታም ጓደኞቼ እንዳያዩህ ተጠንቀቅ፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
====================
ኩማንደር አለማየሁ የአላዛርን ስልክ ተቀብሎ እሷን ወደማረፊያ ክፍል ከላካት በኃላ ጥልቅ ትዝታ ውስጥ ነው የተዘፈቀው፡፡ከእሷ ጋር ብቻ ሳይሆን ከሌሎች ሁለት ጓደኞቹ ጋር የነበረው የልጅነት እና የወጣትነት ትዝታ በብዙ ውጣ ውረዶች የተሞላ፤ደስታንም ሀዘንንም በውስጡ ያጨቀ ነበር፡፡አዎ አለማየሁ እንደሚያስታውሰው ሰሎሜ ለሶስቱ ወንዶች ልክ እንደጨረቃቸው ነበረች፡፡እነሱ ደግሞ በዙሪያዋ እየተሸከረከሩ ውበቷን የሚያጎሉላት ፍንጥርጣሪ ከዋክብቶች፡፡እናም ሰሎሜ ሶስቱንም ጓደኞቾን የምትወድበት የራሷ የሆነ የተለየ ምክንያት እንደነበራት ይገምታል፡፡ለምሳሌ አላዛርን በውበቱና በልስልስ ባህሪው…እሱን በኮሚክነቱና በድፍረቱ ሁሴንን በጉብዝናው እና በብልሀቱ ፡፡
አሌክስ ፤አላዛር እና ሁሴን ከልጅነታቸው ጀምሮ በእሷ ምክንያት ችግር ውስጥ እንደገቡ ነበር፡፡አረ ከእነሱም አልፎ ወላጆቻቸውን ጨምሮ በተደጋጋሚ ጊዜ ችግር ውስጥ ገብተው እንደሚያውቀው ያስታውሳል፡፡አንድ ጊዜ የዘጠኝ አመት ገዳማ ልጆችና የሁለተኛ ክፍል ተማሪ እንደሉ ነበር፡፡ጊዜው የበልግ ዝናብ በሚዘንብበት ወቅት ስለሆነ መስኩ ጠቅላላ ውሀ ባቆሩ መሬቶችና ጭቃ ባላቆጡ መንገዶች የተሞላ ነበር፡፡ታዲያ የትምህርት ቤት የእረፍት ጊዜ ደውል ከተደወለ በኋላ ሰሎሜ ከእነሱ ተነጥላ ሳያዮት ሾልካ ትሔዳች፡፡እደዛ ያደረገችው ሽንቷ ወጥሯት ስለነበረ ወደ ሽንት ቤት ነበር፡፡ስትመለስ ግን ጎረምሳ ጎረምሳ ከሚጫወቱ የስድስተኛ ክፍል ሴት ተማሪዎች እጅ ትወድቃለች፡፡ሴቶቹ እድሜያቸው አስራዎቹ ቤት የገባና በቁጥርም ሶስት ነበሩ፡፡ዙሪያዋን ከበዋት ጆሮዋን እየቆነጠጡ ውሀ ያቆረ ሜዳ ውስጥ በባዶ እግሯቾ ገብታ እያንቦረጨቀች መዝሙር እንድትዘምርላቸው አስገደዷት፡፡
እንዳሏት እየዘለለች ስትዘምር በጭቃ የላቆጠው እና ውሀ ያቆረው መሬት እየተፈናጠረ የለበሰችውን ሙሉ ነጭ ቀሚስ እንዳልነበረ አበላሸባት…፡፡ከዛም አልፏ ፊቷና ጸጉሯ ላይ ሳይቀር ተፈነጣትጥሮባት.. በጭቃ የተሰራች አሻንጉሊት አስመሰሏት ነበር …በንዴትና በፍርሀት እንባዋ እየረገፈ ያሏትን ስታደርግ ቆየች..ልጆቹ የትምህርት ቤት የእርፍት ጊዜ ማለቁን የሚያበስር ደውል ሲደወል ነበር ጥለዋት የሄዱት …ከዛ ምን ታድርግ ተማሪዎች ሁሉ ወደክፍል ከገቡ በኃላ እያለቀሰች ሄዳ ክፍላቸው ጀርባ ባለ መቀመጫ ተቀመጠች፡፡እንደዛ ጨቅይታና ልብሷ ጠቅላላ ተበላሽቶ እንዴት ወደክፍል ትግባ..?አስተማሪውስ ምን ይላታል?፡፡ ወደቤት እንዳትሄድ ደግሞ ቦርሳዋ ክፍል ውስጥ ነበር፡፡
በዚያን ቀን እሱን ጨምሮ ሁለቱ ጓደኞቾ እረፍትን ጨምሮ ክፍል ውስጥ ባለመኖሯ እንዴት ተደናግጠው እንደነበረ ትዝ ይለዋል፡፡‹‹የት ሄደች?››የሶስቱም ጥያቄ ነበር፡፡የሚቀርቧትን ሴቶች ሁሉ ቢጠይቁ አይተናታል የሚል ሰው አላገኙም፡፡…አስተማሪ መጥቶ ክፍለጊዜው ከመጀመሩ በፊት እሷን ፍለጋ ክፍሉን ለቀው በመውጣት የትምህርት ቤቱን አጥር ጊቢ በሳምሶማ ሩጫ ማሳስ ጀመሩ፡፡በስተመጨረሻ ከክፍላቸው ጀርባ እንዳልሆነች ሆና አገኞት፡፡….ሶስቱም ነበር አብረዋት ያለቀሱት፡፡በዛን ወቅት ሲያያት የተሰማውን ድንጋጤና ንዴት ትዝ አለውና ፈገግ አለ ና ወደ ትዝታው ተመለሰ፡፡
በወቅቱ ወደ ቧንቧ ወሰዷት ..ፊቷንና፤ ፀጉሯን እና እግሮቾንም በማጣብ የአንዳቸውን ጃኬት አለበሷት…ሶስቱም ወደክፍላቸው ገብተው የእሷን እና የራሳቸውን ቦርሳ ጭምር በመያዝ ወጡና እሷን መሀከል አድርገው በማፅናናት ወደቤት ነበር ይዘዋት የሄድት፡፡
ከዛ ምሽቱን ሙሉ በወላጆቻቸው ተገደው ወደቤት እስኪገቡ ድረስ ‹‹እንዴት አድርገን ነው የእኛን ንግስት ያስለቀሷትን ሴቶች በእጥፍ የምናስለቅሳቸው?›› ብለው ሲማከሩና እቅዶች ሲነድፉ አመሹ ፡፡
የእነሱን ሰሎሜን ያቆሸሾትና ያስለቀሷት ልጆቹ ሰሚራ፤ ሳራና፤ ሰላም ይባለሉ እንደነበር አሁን ድረስ ስማቸውን ከነመልካቸው ያስታውሰዋል፡፡
‹‹እኛ ሶስት ነን አይደል?››ሲል ነበር አለማየሁ ጓደኞቹን የጠየቀው፡፡
‹‹አዎ››መለሱለት፡፡
‹‹እሺ ሰሎሜን ያስለቀሷትም ሴቶች ሶስት ናቸው››
‹‹አዎ ትክክል ሶስት ትላልቅ ሴቶች ናቸው››መለሱለት፡፡
‹‹ጥሩ..አንዳ እንድ እንከፋፈላቸዋለን››አለ አለማየሁ፡፡
አላዛር ተቃወመ‹‹አይሆንም እኔ አልስማማም››
‹‹ለምንድነው ማትስማማው?››
‹‹እኔ ከሰሎሜ ውጭ ሌላ ሴት አልፈልግም…..የእኔን ድርሻም ከፈለጋችሁ ተካፈሉና ውሰዷት››ሲል ነበር አቋሙን ያሳወቀው፡፡
‹‹አንተ ጀዝባ የሆንክ ልጅ …የምንካፈላቸው እኮ የእኛ ልናደርጋቸው አይደለም.. ልናሰቃያቸውና ልናስለቅሳቸው ነው…ለሰሎሜ ልንበቀልላት ነው፡፡››
ሁሴን ‹‹ገባኝ..ለመበቀል ግን ለምን መከፋፈል አስፈለገ?››ሲል ጠየቀ
‹‹‹ለእያንዳንዳችን የደረሰችንን ሴት የሆነ ዘዴ ፈልገን በተማሪ ፊት እንድታፍር ፤ እንድታለቅስና እንድትፀፀት እናደርጋታላን፡፡ታዲያ ከሶስታችን በጣም በአስቂኝና አስደናቂ መንገድ ተጠቅሞ ማስለቀስ የቻላ የበለጠ ሰሎሜን ያፈቅራታል ማለት ነው፡፡››እንደዚህ አይነት ሀሳብና እቅድ በዛ እድሜ እንዴት ማመንጨት እንደቻለ ዛሬም ሲያስበው በራሱ ይገረማል፡፡
ሁሴን‹‹ተስማምቼለው…እኔ ከሁለታችሁም በላይ ጂኒዬስ ስለሆኑክ ካሁኑ መሸነፋችሁን እመኑ››ሲል ጎረረ፡፡
‹‹ሞኞ በትምህርት ጎበዝ ሆንክ ማለት በእንደዚህ አይነት ነገርም ጎበዝ ነህ ማለት አይደለም?››ሲል ነበር የመለሰለት፡፡
በክርክራቸው የተሰላቸው አላዘር‹‹እባካችሁ አትጨቃጨቁብኝ. .አሁን እንዴት አድርገን ነው ሴቶቹን ምንካፈላቸው››ሲል ግራ የገባውን ነገር ጠየቀ፡፡
‹‹እጣ እንጥላለን›› ብለው ተስማሙና በዛው መሰረት ተከፋፈሉ…ለሁሉም የአንድ ሰምንት ጊዜ ተሰጣቸው፡፡
ይሄ ውይይት በተደረገ በአራተኛው ቀን ሰላም በምትባለው ልጅ ላይ የመጀመሪያው ጥቃት ደረሰባት፡፡ሁሴን ለመጀመሪያ ሁለት ቀናት ልጆቹን ስር ስራቸው እየሄደ የሆነ ቦታ ተቀምጠው ሲያወሩ በሆነ ከለላ እየተደበቀ የሚያወሩትን በመስማት መረጃ ሰበሰበ፡፡በሶስተኛው ቀን እንደምንም ወደስድስተኛ ክፍል ሾልኮ ገባና ከሰላም ቦርሳ ውስጥ አንድ ደብተር በመስረቅ ወደቤቱ ይዞ ሄዳ፡፡ከዛ ለሁለት ሰዓት ያህል ፊደል አጣጣሏንና የእጅ ፅሁፏን ሲለማመድ ቆየ..ከዛ እርግጠኛ ሲሆን ያሰበውን ወደማድረግ ተሸጋገረ፡፡
በእሷ ስም ለአንዱ የክፍሏ ልጅ ደብዳቤ ፃፈ፡፡
ውድ ወንድይራድ…..እንዴት ነህ..?እኔ የአንተ ፅጌረዳ ከአንተ ሀሳብና ናፍቆት በስተቀር ሰላም ነኝ፡፡ይሄንን ደብዳቤ የፃፍኩልህ ምን ያህል እንደማፈቅርህ ፊት ለፊትህ ቆሜ ልነግርህ መድፈር ስላቃተኝ ነው፡፡ታውቃለህ ደግሞ እነዛ አስጠሊታ ሁለት ጓደኞቼ ሁል ግዜ እንደተጣበቁብኝ ነው…ሲያስጠሉ፡፡ውዴ ከአሁን በኋላ አንተን ካገኘሁ እነሱ አያስፈልጉኝም…ድሮውም እንደመደበሪያ ነበር የምጠቀምባቸው፡፡ውዴ በእርግጠኝነት አንተም እንደምታፈቅረኝ አውቃለሁ…እንደእኔ አይነት ቆንጆ እንዴት ላታፈቅር ትችላለህ?፡፡ለማንኛውም መልስህን በጉጉት እጠብቃለው፡፡ደግሞ የመልሱን ደብዳቤ ስትሰጠኝ አነዛ ቅናታም ጓደኞቼ እንዳያዩህ ተጠንቀቅ፡፡
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
/////
ዘሚካኤል ስቲዲዬ ቆይቶ ገና ወደቤት እንደገባ ነበር ስልኩ የጠራው፡፡
የደወለችለት አዲስ አለም ነበረች፡፡የጠበቀው ሚካኤል ይደውልልኛል ብሎ ነበር ፡፡ከአባቱ ጋር የሚገናኙበትን ቀን ከወህኒ ቤቱ አስተዳዳሪ ጋር ተነጋግሮ እንደሚደውልለት ነገሮት ነበር፡፡እና ይሄን ቀን በፍርሀትና በጉጉት ነበር እየጠበቀ ያለው፡፡ስለአባቱ ዜና ለመስማት፡፡ስልኩን አነሳው፡፡
‹‹ሄሎ አዲስ እንዴት ነሽ?››
‹‹ሰላም ነኝ አንተስ?››
‹‹እኔ በጣም ደህና ነኝ…ሚካኤል ይደውልልኛል ብዬ እየጠበቅኩ ነበር፡፡››
‹‹ይደውልልሀል..አሁን ኩማንደሩ ቀጥሮት ሊያገኘው ሄዶል …ከእሱ እንደጨረሰ እርግጠኛ ነኝ ይደውልልሀል፡፡…አታስብ ኩማንደሩ ደግሞ ያንተ አድናቂ ስለሆነ ከአባታችሁ እንድትገናኙ ሁኔታውን ያመቻቻል….በዛ እርግጠኛ ነኝ፡፡››አለችው
‹‹ጥሩ ታዲያ አንቺ ሰላም ነሽ?››
‹‹በጣም ሰላም ነኝ…ግን አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ ነበር››
‹‹ምን?››
‹‹ከፀዲ ጋር እንዴት ናችሁ?››
ያልጠበቀውን ጥያቄ ነው የጠየቀችው‹‹በጣም አሪፍ ነን…ከቦንጋ ከተመለስን በኋላ በአካል ባንገናኝም በስልክ ግን በቀን ሁለት ሶስት ጊዜ እንደዋወላለን…እንደውም የፊታችን ቅዳሜና እሁድ ከከተማ ወጣ ብለን ለማሳለፍ ተነጋግረናል፡፡
ግን ምነው ጠየቅሺኝ?››
‹‹ግልፅ ሆነህ ንገረኝ…ስለእሷ ምን ታስባለህ..ማለቴ አሁንም በፊት እንደነገርከኝ ታፈቅራታለህ?››
‹‹እንዴ!እንዴት በአንድ ወር ፍቅሩ ይተናል ብለሽ አሰብሽ? እንደውም ጥሩ ነገር አነሳሽልኝ…የሆነ ቀን አመቻችቼ ካንቺ ጋር መነጋገር እፈልግ ነበር..እኔ ላገባት እፍልጋለው..በቅርብ ቀን..እና እንዴት ጠይቄ ላሳምናት የሚለውን ከእኔ ይልቅ አንቺ ስለምታውቂ እንድታማክሪኝ እፈልጋለው፡፡››
‹‹እንግዲያው እንደዛ ከሆነ ሳይረፍድብህ ፍጠን››
‹‹አልገባኝም?››
‹‹ያንተን ልጅ አርግዛለች..››
የሰማውን ነገር ማመን አልቻለም…በደስታ ጮኸ…
‹‹ማለት…በፈጣሪ እየዋሸሺኝ አይደለም አይደል? ››
‹‹አርግዛለች..ለእኔም አልነገረችኝም ፡፡
በአጋጣሚ አንድ የግል ሆስፒታል ካርድ ክፍል የምትሰራ ወዳጅ ነበረችኝ …አሁን ከደቂቃዎች በፊት ደውላ ጓደኛሽ ፀንሳ እኛ ሆስፒታል ለማስወረድ መጥታ ነበር…ብላ ነገረችኝ፡፡መጀመሪያ አላመንኩም ነበር..በኋላ ግን ሆስፒታሉ ድረስ ሄጄ በሌላ መንገድ እራሷ መሆኗን አረጋግጬያለው…ልታስወርደው ለተነገወዲያ ቀጠሮ አሲይዛለች….ቀጥታ ላናግራት ፍልጌ ነበር….ጭራሽ እልክ ትጋባለች ብዬ ስለፈራሁ ምንም ልላት አልቻልኩም…አንተ ምታደርገው ነገር ካለ ሞክር››
‹‹ወይኔ በፈጣሪ..ለእኔ አረገዘችልኝ…..››በበቃ ቻው አዲስ አንቺ አትጨነቂ እኔ አስተካክለዋለው፡፡
የአዲስን ስልክ ከዘጋ በኃላ ቀጥታ ልብሶቹ በሻንጣ መክተት ነው የጀመረው፡፡ሁለት ሻንጣ ልብስና በወሳኝ የሚፈልጋቸውን ነገሮች ሰበሰበና አፓርታማውን ለቆ ወጣ …ቀጥታ ወደአዳማ ነው የነዳው፡፡
ፀአዳ ቤት ሲደርስ በራፏ ዝግ ነበር..ሊደውልላት አልፈለገም ፡፡ሻንጣውን አወረደና በራፏ በረንዳ ላይ አድርጎ እሱ መኪናው ውስጥ ሆኖ መጠበቅ ጀመረ…ከምሽቱ አንድ ሰአት ስትመጣ እሱ መኪና ውስጥ ሻንጣው በረንዳ ላይ ሆኖ ስታየው ፍፁም ነው ግራ የተጋባችው…ምስር እሱ መሆኑን ስታውቅ ከእናቷ ተነጥላ ወደእሱ መሮጥ ስትጀምር እሱም ፈጥኖ ከመኪናው ወረደና እጇቹን እንደክንፍ ዘርግቶ ጠበቃት…ተጠምጥማበት በደስታ ጉንጩን ትስመው ጀመር…
ወደቤት እንደገቡ ፀደይ‹‹ምንድነው ጉዱ?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹ምንም ..ለጥቂት ሳምንታት እረፍት ስለሆንኩ እዚህ ከእናንተ ጋር ለመቆየት ወስኜ ነው፡፡››
‹‹እዚህ ከእኛ ጋር?››
‹‹አዎ ከእናንተ ጋር››
ህፃኖ ምስር ‹‹ታድለን…ታድለን›› እያለች መጨፈር ጀመረች፡፡
ፀአዳ ልጇ ምስር ፊት ምንም ማለት አልቻለችም.‹‹እንግዲያው እደቤትህ ዘና በል…እኔ ልብስ ልቀይር ››አለችና መኝታ ቤት ገባች፡፡ከዛ እራት ሰርታ በሉና ከሶስት ሰዓት በኃላ ምስርን አስተኝተው ነበር እንደአዲስ ጭቅጭቁን የጀመሩት፡፡
‹‹ምን እየሰራህ ነው?››
‹‹እንደምታገቢኝ ቃል ገብተሸ ቀለበት እስክታስሪልኝ ድረስ ከዚህ ቤት ወጥቼ ወደቤቴ አልመለስም››ሲል ቁርጡን ፍርጥም ብሎ ነገራት፡
‹‹ጭራሽ ማግባት? እየቀለድክ ነው፡፡››
‹‹በፍፅም …ብቀልድ ነው እንደዚህ አይነት እርምጃ የወሰድኩት፡፡››
‹‹ስማ..እኔ ካንተ ጋብቻ ፍቅር ምናምን አልፈልግም››
‹‹ታዲያ ምንድንው ምትፈልጊው?››
ትኩር ብላ አየችው….
‹‹ንገሪኝ ከእኔ ምንድነው የምትፈልጊው….. ?››
‹‹ካንተ ወሲብ ብቻ ይበቃኛል….ማለቴ እስከአሁን የደረግነውን ለማለት ነው …ደግሞ አሁንም እናድረግ እያልኩህ አይደለም፡፡››
በንግግሯ ሆድን እስኪያመው ሳቀ…በመሀል ስልክ ተደወለለት ..ከወንድሙ ነበር…በጉጉት አነሳው‹‹እሺ ሚካኤል ደህና አመሸህ?››
‹‹ሰላም ነኝ…ነገ ጥዋት ሶስት ሰዓት ላይ አዳማ መገኘት ትችላለህ?››
‹‹ምነው ?አባዬን እንድናገኝ ፈቀዱልን እንዴ?››
‹‹አዎ በጣም ደስ የሚለው ደግሞ አንድ ላይ እንድናገኘው ነው ያመቻቹልን ቅር ካላለህ አዲስንና ቅዱስንም ይዘናቸው እንሄዳለን››
‹‹አረ ቅር አይለኝም ጥሩ ሀሳብ …ግን አባዬ እኔን ለማናገር ፍቃደኛ የሚሆን ይመስልሀል?››ሰሞኑን ሲብሰለሰልበት የነበረውን ስጋቱን አንስቶ ጠየቀው፡፡
‹‹ትቀልዳለህ እንዴ…ከመሞቱ በፊት ማግኘት የሚፈልገው ብቸኛ ነገር እኮ አንተን ማናገር ነው…በደስታ ነው የሚያነባው….እንኳን በአካል አግኝተሀው አባዬ ብለህ ስጠራው ሰምቶ ይቅርና ባለፈው ፎቶህን ሳሳየው እንዴት እያገላበጠ ሲስምና ሲያለቅስ እንደነበረ እኔ ነኝ የማውቀው…በል በዛ እርግጠኛ ሁን..ምንም አትጨናነቅ፡፡››
‹‹ምን ያስፈልገዋል…?ማለት ምን ይዤለት ልሂድ?››
‹‹የሚያስፈልገወን ነገር ሁሉ አዘጋጅተናል…አንተ ደግሞ ሚፈልገውን ነገር እንጠይቀውና በሚቀጥለው ዙር ትወስድለታለህ…ደግሞ ደስ የሚለው ከቦንጋ ያመጣችሁትን ከዶ/ሩ ጋር ያደረጋችሁትን ውይይት ለኩማንደሩ አሰምቼው በጣም ነው ያዘነው..እናም አባዬን ከሌሎች እስረኞች ጋር ተቀላቅሎ እንዲኖር ወስነዋል…››
‹‹በጣም የሚያስደስት ነገር ነው እየነገርከኝ ያለሀው..ወንድሜ በጣም ጥሩ ሰው እንደሆንክ ታውቃለህ አይደል… በጣም ነው የምኮራብህ፡፡››
ሚካኤልም እንባ እየተናነቀው‹‹እኔም በጣም ነው የምኮራብህ››አለው
‹‹በቃ እሺ …...ሶስት ሰዓት ነው ያልከኝ አይደል?፡፡››
‹‹አዎ…መድረስ ትችላለህ አይደል…?››
‹‹በደንብ እንጂ ሁለት ተኩል ደርሼ ደውልልሀለው››
‹‹ጥሩ በቃ ደህና እደር››ስልኩን ዘጋ፡፡
ንግግራቸውን ሁሉ በገረሜታ ስትሰማ የነበረችው ፀደይ‹‹እርግጠኛ ነህ ግን ሁለት ተኩል ትደርሳለህ?››ስትል በፈገግታ አሾፈችበት፡፡
‹‹ትቆጪኛለሽ ብዬ ነው እንጂ እዚህ ነኝ ልለው ነበረ››
‹‹ልፋ ቢልህ ነው ….ግን ለእናንተ ደስ ብሎኛል››
‹‹ማለት?››
‹‹አንተና ወንድምህ እንዲህ እየተደዋወላችሁ በሰላም ማውራት መቻላችሁ ትልቅ ነገር ነው…አረ እንደውም ከመነጋጋርም አልፋችሁ መሞጋገስ ጀምራችኃል››
‹‹እድሜ ለአንቺ ….ባንቺ ቀናነትና ጥረት ነው ለዚህ የበቃነው….››
‹‹እኔን ማሞገሱን እንኳን ለሌላ ጊዜ አቆየው..በነገራችን ላይ የአባትህ ጉዳይ ላይ ይግባኝ ለመጠየቅ ሚቻል ከአሆነ አንድ ጎበዝ ጠበቃ አግኝኝቼ ሁኔታውን አስረድቼው ነበር….››
‹‹በእውነት ..ታዲያ ምን አለሽ?››
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
/////
ዘሚካኤል ስቲዲዬ ቆይቶ ገና ወደቤት እንደገባ ነበር ስልኩ የጠራው፡፡
የደወለችለት አዲስ አለም ነበረች፡፡የጠበቀው ሚካኤል ይደውልልኛል ብሎ ነበር ፡፡ከአባቱ ጋር የሚገናኙበትን ቀን ከወህኒ ቤቱ አስተዳዳሪ ጋር ተነጋግሮ እንደሚደውልለት ነገሮት ነበር፡፡እና ይሄን ቀን በፍርሀትና በጉጉት ነበር እየጠበቀ ያለው፡፡ስለአባቱ ዜና ለመስማት፡፡ስልኩን አነሳው፡፡
‹‹ሄሎ አዲስ እንዴት ነሽ?››
‹‹ሰላም ነኝ አንተስ?››
‹‹እኔ በጣም ደህና ነኝ…ሚካኤል ይደውልልኛል ብዬ እየጠበቅኩ ነበር፡፡››
‹‹ይደውልልሀል..አሁን ኩማንደሩ ቀጥሮት ሊያገኘው ሄዶል …ከእሱ እንደጨረሰ እርግጠኛ ነኝ ይደውልልሀል፡፡…አታስብ ኩማንደሩ ደግሞ ያንተ አድናቂ ስለሆነ ከአባታችሁ እንድትገናኙ ሁኔታውን ያመቻቻል….በዛ እርግጠኛ ነኝ፡፡››አለችው
‹‹ጥሩ ታዲያ አንቺ ሰላም ነሽ?››
‹‹በጣም ሰላም ነኝ…ግን አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ ነበር››
‹‹ምን?››
‹‹ከፀዲ ጋር እንዴት ናችሁ?››
ያልጠበቀውን ጥያቄ ነው የጠየቀችው‹‹በጣም አሪፍ ነን…ከቦንጋ ከተመለስን በኋላ በአካል ባንገናኝም በስልክ ግን በቀን ሁለት ሶስት ጊዜ እንደዋወላለን…እንደውም የፊታችን ቅዳሜና እሁድ ከከተማ ወጣ ብለን ለማሳለፍ ተነጋግረናል፡፡
ግን ምነው ጠየቅሺኝ?››
‹‹ግልፅ ሆነህ ንገረኝ…ስለእሷ ምን ታስባለህ..ማለቴ አሁንም በፊት እንደነገርከኝ ታፈቅራታለህ?››
‹‹እንዴ!እንዴት በአንድ ወር ፍቅሩ ይተናል ብለሽ አሰብሽ? እንደውም ጥሩ ነገር አነሳሽልኝ…የሆነ ቀን አመቻችቼ ካንቺ ጋር መነጋገር እፈልግ ነበር..እኔ ላገባት እፍልጋለው..በቅርብ ቀን..እና እንዴት ጠይቄ ላሳምናት የሚለውን ከእኔ ይልቅ አንቺ ስለምታውቂ እንድታማክሪኝ እፈልጋለው፡፡››
‹‹እንግዲያው እንደዛ ከሆነ ሳይረፍድብህ ፍጠን››
‹‹አልገባኝም?››
‹‹ያንተን ልጅ አርግዛለች..››
የሰማውን ነገር ማመን አልቻለም…በደስታ ጮኸ…
‹‹ማለት…በፈጣሪ እየዋሸሺኝ አይደለም አይደል? ››
‹‹አርግዛለች..ለእኔም አልነገረችኝም ፡፡
በአጋጣሚ አንድ የግል ሆስፒታል ካርድ ክፍል የምትሰራ ወዳጅ ነበረችኝ …አሁን ከደቂቃዎች በፊት ደውላ ጓደኛሽ ፀንሳ እኛ ሆስፒታል ለማስወረድ መጥታ ነበር…ብላ ነገረችኝ፡፡መጀመሪያ አላመንኩም ነበር..በኋላ ግን ሆስፒታሉ ድረስ ሄጄ በሌላ መንገድ እራሷ መሆኗን አረጋግጬያለው…ልታስወርደው ለተነገወዲያ ቀጠሮ አሲይዛለች….ቀጥታ ላናግራት ፍልጌ ነበር….ጭራሽ እልክ ትጋባለች ብዬ ስለፈራሁ ምንም ልላት አልቻልኩም…አንተ ምታደርገው ነገር ካለ ሞክር››
‹‹ወይኔ በፈጣሪ..ለእኔ አረገዘችልኝ…..››በበቃ ቻው አዲስ አንቺ አትጨነቂ እኔ አስተካክለዋለው፡፡
የአዲስን ስልክ ከዘጋ በኃላ ቀጥታ ልብሶቹ በሻንጣ መክተት ነው የጀመረው፡፡ሁለት ሻንጣ ልብስና በወሳኝ የሚፈልጋቸውን ነገሮች ሰበሰበና አፓርታማውን ለቆ ወጣ …ቀጥታ ወደአዳማ ነው የነዳው፡፡
ፀአዳ ቤት ሲደርስ በራፏ ዝግ ነበር..ሊደውልላት አልፈለገም ፡፡ሻንጣውን አወረደና በራፏ በረንዳ ላይ አድርጎ እሱ መኪናው ውስጥ ሆኖ መጠበቅ ጀመረ…ከምሽቱ አንድ ሰአት ስትመጣ እሱ መኪና ውስጥ ሻንጣው በረንዳ ላይ ሆኖ ስታየው ፍፁም ነው ግራ የተጋባችው…ምስር እሱ መሆኑን ስታውቅ ከእናቷ ተነጥላ ወደእሱ መሮጥ ስትጀምር እሱም ፈጥኖ ከመኪናው ወረደና እጇቹን እንደክንፍ ዘርግቶ ጠበቃት…ተጠምጥማበት በደስታ ጉንጩን ትስመው ጀመር…
ወደቤት እንደገቡ ፀደይ‹‹ምንድነው ጉዱ?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹ምንም ..ለጥቂት ሳምንታት እረፍት ስለሆንኩ እዚህ ከእናንተ ጋር ለመቆየት ወስኜ ነው፡፡››
‹‹እዚህ ከእኛ ጋር?››
‹‹አዎ ከእናንተ ጋር››
ህፃኖ ምስር ‹‹ታድለን…ታድለን›› እያለች መጨፈር ጀመረች፡፡
ፀአዳ ልጇ ምስር ፊት ምንም ማለት አልቻለችም.‹‹እንግዲያው እደቤትህ ዘና በል…እኔ ልብስ ልቀይር ››አለችና መኝታ ቤት ገባች፡፡ከዛ እራት ሰርታ በሉና ከሶስት ሰዓት በኃላ ምስርን አስተኝተው ነበር እንደአዲስ ጭቅጭቁን የጀመሩት፡፡
‹‹ምን እየሰራህ ነው?››
‹‹እንደምታገቢኝ ቃል ገብተሸ ቀለበት እስክታስሪልኝ ድረስ ከዚህ ቤት ወጥቼ ወደቤቴ አልመለስም››ሲል ቁርጡን ፍርጥም ብሎ ነገራት፡
‹‹ጭራሽ ማግባት? እየቀለድክ ነው፡፡››
‹‹በፍፅም …ብቀልድ ነው እንደዚህ አይነት እርምጃ የወሰድኩት፡፡››
‹‹ስማ..እኔ ካንተ ጋብቻ ፍቅር ምናምን አልፈልግም››
‹‹ታዲያ ምንድንው ምትፈልጊው?››
ትኩር ብላ አየችው….
‹‹ንገሪኝ ከእኔ ምንድነው የምትፈልጊው….. ?››
‹‹ካንተ ወሲብ ብቻ ይበቃኛል….ማለቴ እስከአሁን የደረግነውን ለማለት ነው …ደግሞ አሁንም እናድረግ እያልኩህ አይደለም፡፡››
በንግግሯ ሆድን እስኪያመው ሳቀ…በመሀል ስልክ ተደወለለት ..ከወንድሙ ነበር…በጉጉት አነሳው‹‹እሺ ሚካኤል ደህና አመሸህ?››
‹‹ሰላም ነኝ…ነገ ጥዋት ሶስት ሰዓት ላይ አዳማ መገኘት ትችላለህ?››
‹‹ምነው ?አባዬን እንድናገኝ ፈቀዱልን እንዴ?››
‹‹አዎ በጣም ደስ የሚለው ደግሞ አንድ ላይ እንድናገኘው ነው ያመቻቹልን ቅር ካላለህ አዲስንና ቅዱስንም ይዘናቸው እንሄዳለን››
‹‹አረ ቅር አይለኝም ጥሩ ሀሳብ …ግን አባዬ እኔን ለማናገር ፍቃደኛ የሚሆን ይመስልሀል?››ሰሞኑን ሲብሰለሰልበት የነበረውን ስጋቱን አንስቶ ጠየቀው፡፡
‹‹ትቀልዳለህ እንዴ…ከመሞቱ በፊት ማግኘት የሚፈልገው ብቸኛ ነገር እኮ አንተን ማናገር ነው…በደስታ ነው የሚያነባው….እንኳን በአካል አግኝተሀው አባዬ ብለህ ስጠራው ሰምቶ ይቅርና ባለፈው ፎቶህን ሳሳየው እንዴት እያገላበጠ ሲስምና ሲያለቅስ እንደነበረ እኔ ነኝ የማውቀው…በል በዛ እርግጠኛ ሁን..ምንም አትጨናነቅ፡፡››
‹‹ምን ያስፈልገዋል…?ማለት ምን ይዤለት ልሂድ?››
‹‹የሚያስፈልገወን ነገር ሁሉ አዘጋጅተናል…አንተ ደግሞ ሚፈልገውን ነገር እንጠይቀውና በሚቀጥለው ዙር ትወስድለታለህ…ደግሞ ደስ የሚለው ከቦንጋ ያመጣችሁትን ከዶ/ሩ ጋር ያደረጋችሁትን ውይይት ለኩማንደሩ አሰምቼው በጣም ነው ያዘነው..እናም አባዬን ከሌሎች እስረኞች ጋር ተቀላቅሎ እንዲኖር ወስነዋል…››
‹‹በጣም የሚያስደስት ነገር ነው እየነገርከኝ ያለሀው..ወንድሜ በጣም ጥሩ ሰው እንደሆንክ ታውቃለህ አይደል… በጣም ነው የምኮራብህ፡፡››
ሚካኤልም እንባ እየተናነቀው‹‹እኔም በጣም ነው የምኮራብህ››አለው
‹‹በቃ እሺ …...ሶስት ሰዓት ነው ያልከኝ አይደል?፡፡››
‹‹አዎ…መድረስ ትችላለህ አይደል…?››
‹‹በደንብ እንጂ ሁለት ተኩል ደርሼ ደውልልሀለው››
‹‹ጥሩ በቃ ደህና እደር››ስልኩን ዘጋ፡፡
ንግግራቸውን ሁሉ በገረሜታ ስትሰማ የነበረችው ፀደይ‹‹እርግጠኛ ነህ ግን ሁለት ተኩል ትደርሳለህ?››ስትል በፈገግታ አሾፈችበት፡፡
‹‹ትቆጪኛለሽ ብዬ ነው እንጂ እዚህ ነኝ ልለው ነበረ››
‹‹ልፋ ቢልህ ነው ….ግን ለእናንተ ደስ ብሎኛል››
‹‹ማለት?››
‹‹አንተና ወንድምህ እንዲህ እየተደዋወላችሁ በሰላም ማውራት መቻላችሁ ትልቅ ነገር ነው…አረ እንደውም ከመነጋጋርም አልፋችሁ መሞጋገስ ጀምራችኃል››
‹‹እድሜ ለአንቺ ….ባንቺ ቀናነትና ጥረት ነው ለዚህ የበቃነው….››
‹‹እኔን ማሞገሱን እንኳን ለሌላ ጊዜ አቆየው..በነገራችን ላይ የአባትህ ጉዳይ ላይ ይግባኝ ለመጠየቅ ሚቻል ከአሆነ አንድ ጎበዝ ጠበቃ አግኝኝቼ ሁኔታውን አስረድቼው ነበር….››
‹‹በእውነት ..ታዲያ ምን አለሽ?››