#ትኩሳት
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
ሲልቪ
ላይ ላዩን
..ተመስገን ክፍል ውስጥ ቁጭ ብዬ ስሰራ አንዳንዴ ውቢቱ ሲልቪ ትመጣና «Salut Castro noire» ትለኛለች። («ሰላም፣ ጥቁር ካስትሮ») (ፂም ስላለኝ ነው፡፡)
«Que la paix soit avec toi Scheherazade Blanche» እላታለሁ
(«ሰላም ላንቺ ይሁን፣ ፃእዳይቱ ሻህራዝድ ሆይ»)
ትስቃለች። በምስራቃውያን አነጋገር እንቀጥላለን። ቀልድ
ነው። ከሲልቪ ጋር ሁልጊዜ ቀልድ ነው:: እውነተኛ ፈረንሳዊት ናት፣ ስለምንም ነገር ቢሆን «Moi je men fous!» ነው የምትለው
(«እኔ ስለዚህ ነገር ደንታ የለኝም»)
ታድያ ደስ ትላለች። ሰፊ አፏ
ሳሙኝ ሳሙኝ ይላል፡፡ አብረሀት ስትሆን ሳቅ ቀልድ ታበዛለህ፣
«ዠማንፉቲዝሟ» ይጋባብሀል፤ ስለምንም ነገር ደንቴ አይኖርህም
አንድ ቀን ግን
«ምንድነው ሁልጊዜ ስትፅፍ የማገኝህ?» አለችና ደብተሬን
አየችው:: የምን ፅህፈት ነው ይሄ? ያገራችሁ ነው?» አለችኝ
«አዎን»
«ምኑም አይገባም»
«ቀላል ነው፡፡ ሁለት መቶ አርባ የሚሆኑ ፊደላት አሉት»
«Quel horreur! (ኧረ የጉድ ያለህ!) እንግዲያው አታስረዳኝ
ይቅርብኝ .. ምንድነው ምትፅፈው?»
«ምንም አይደለም»
«ልብወለድ ነው?»
«ብጤ ነው»
«እንዴት ማለት ብጤ?»
«እንዴት ልበልሽ? ልብወለድ ነው፣ ግን ፈጥሬው አይደለም፣
ያየሁትን የሰማሁትን ነገር ሰብስቤ ቅርጹን እለዋውጣለሁ እንጂ፣
ላንባቢ እንዲጥም»
«ቆይ ቆይ፡፡ አሁን መፃፍ አለብህ ወይስ ለጊዜው ልትተወው
ትችላለህ»
«ልተወው እችላለሁ»
«እንግዲያው ከዚህ እንሂድና ቡና ልጋብዝህ:: እና ስለድርሰት
እናውራ። ይስማማሀል?»
«በደምብ ነዋ! ቆንጆ ሴት ቡና ስትጋብዘኝ ሁልጊዜ
ይስማማኛል»
«Malin Castro noir va!» («ሂድ ወድያ! ፎሌ ጥቁር ካስትሮ!»)
Deux Chevaux መኪናዋ ውስጥ ከገባን በኋላ
«ኤክስ ውስጥ የምወደው ካፌ የለኝም፡፡ ማርሰይ እንሂድ?»
አለችኝ
እየቀለድን እየሳቅን ደጋግማ «Moi, u sais je m en fous!»
እያለች፣ በሆዴ ውበቷን እያደነቅኩ፣ ማርሰይ ደረስን፡፡ የንግድ ሳይሆን የግል የመደሰቻ ልዩ ልዩ አይነት ጀልባዎች ከተደረደሩበት ወደብ አጠገብ አንድ ካፌ ገብተን ቢራ ካዘዝን በኋላ፣ ጉልህ ሰማያዊ
አይኖቿ በፈገግታ እያዩኝ
«ንገረኛ ስለምትፅፈው» አለችኝ
«ምን ልንገርሽ?»
«ስለሰዎቹ፣ ስለጊዜው፣ ስለግንኙነታቸው፣ ማን ማንን እንደ
ሚወድ፣ ማንስ ማንን እንደሚጠላ፣ መፅሀፍህ አንዴት እንደ ሚጀመር፣ አሁን የት እንደደረሰ፣ በኋላ እንዴት እንደሚያልቅ፣
ምን ምን ነገር እንደሚያስቸግርህ፣ መፅሀፍህ ምን እንዲል እንደ
ምትፈልገው፣ ሁሉን ንገረኝ
ቆንጆ ስለሆነች ይሁን፣ አጠያየቁን ስላወቀችበት ይሁን ወይ ሌላ ያልተገለፀልኝ ምክንያት ይኑር እንጃ፣ ስለመፅሀፌ ሁሉን
ነገርኳት። ለማንም ነግሬ የማላውቀውን ለሷ አጫወትኳት፡፡ ችግሩን ደስታውን፣ ብስጭቱን፣ የድል አድራጊነት ስሜቱን፣ ምንም
ሳልደብቅ አዋየኋት። ፈረንሳይኛው ሲያስቸግረኝ ልክ ልናገረው
የፈለግኩትን ቃላት ታቀብለኛለች፣ ምክንያቱም ሀሳቤ ቃላቱን
ቀድሞ ደርሷት ይቆያል። አንዳንድ ቦታ አንድ ሀሳብ ተናግሬ
ጨርሼ ሌላ ሀሳብ አልመጣልህ ሲለኝ አንድ ጥያቄ ትጠይቀኛለች
እሱን ጥያቄ ስመልስ፣ ሌላ ሀሳብ ይመጣልኝና እቀጥላለሁ፡፡ እንደዚህ ብዙ ካወራሁ በኋላ
«ይገርምሻል፣ ይህን ለማንም ነግሬ አላውቅም» አልኳት
«Jen suis lattee» አለችኝ (ክብር ይሰማኛል።)
«እኔ እውነቴን ነው»
«እኔም እውነቴን ነው»
«አሁን ተራሽን አውሪልኝ
«ቆይ» አለችና ከያዘችው የመፃህፍት ቦርሳ አንድ አስር የሚሆኑ ባንድ በኩል ብቻ በታይፕ የተፃፈባቸው ነጠላ ወረቀቶች ሰጠችኝ።
አንብበው አለችኝ፡፡ አነበብኩት፡፡ አጭር ልብ ወለድ ታሪክ ነው።
ስጨርስ ምን ይመስልሀል?» አለችኝ
«አንቺ ነሽ የፃፍሽው?» አልኳት
«አዎን» አለችኝ
«አዝናለሁ። ጥሩ ታሪክ አይደለም»
«ምንድነው የጎደለው?»
«እርግጠኛ አይደለሁም። አየሽ፣ አንድ ሰው የሚወዳትን ሴት
ሊገድል ይችል ይሆናል፡፡ ግን ባስር ገፅ ውስጥ ይህን መናገር
የሚቻል አይመስለኝም፡፡ ቢያንስ ቢያንስ ሁለት መቶ ገፅ
ያስፈልገዋል»
«ይህንንም አንብብ እስቲብላ ሌላ አስራ ሶስት ገፅ ሰጠችኝ።
አነበብኩት። ግሩም ታሪክ ነበር፡፡
«ይህንንም አንቺ ነሽ የፃፍሽው?»
«አዎን»
«ታሪክ ይሉሻል ይሄ ነው! ይህን ጊ ደ ሞፓሳን ራሱ ነው የፃፈው ቢሉኝ አምናለሁ» አልኳት
ጉልህ ሰማያዊ አይኖቿ ልዩ አስተያየት ሰጡኝ፣ እንደማቀፍ ያለ
አስተያየት፣ ሙቀት ያለው አስተያየት
«Merci»አለችኝ
«Je ten prie (ኧረ ምንም አይደለም) ይህን የመሰለ ለመፃፍ
ስትችዪ፣ እንዴት አርገሽ የቅድሙን ፃፍሽው?» አልኳት
መሳቅ ጀመረች (ጥርሶቿ ትክክል ሆነው ነጫጭ ናቸው። ነጭ
የፈረንጅ ጥርስ ብዙ እይታይም) «እኔ እንጃ አለችኝ «በምፅፍበት
ሰአት ሁሉም እኩል ጥሩ ሆኖ ይሰማኛል። ካንድ ሁለት ወር በኋላ
ሳነበው ነው እውነተኛው ዋጋው የሚታየኝ»
«ይሄ መጥፎው መቼ ነው የተፃፈው?»
«ካንድ አመት ተኩል በፊት
«እንግዲያው መጥፎ መሆኑ
ድሮ ገብቶሻል። ለምን
እስነበብሽኝ?»
«ላውቅህ ስለፈለግኩ። ማንም ሰው ቢሆን፣ እንደምፅፍ ካወቀ
ወይም እንዲያውቅ ከፈለግኩ፣ መጀመሪያ መጥፎ ታሪኬን
አስነብሰዋለሁ። አንብቦት ጥሩ ነው ካለ በቃው። ሁለተኛ እኔ
የፃፍኩትን አያነብም። እስካሁን ለአንድ ስምንት ሰው አስነብቤያለሁ።
አንተና አንድ የፓሪስ ጓደኛዬ ብቻ ናችሁ መጥፎውን መጥፎ
ያላችሁት። ስለዚህ ሁለታችሁ ብቻ ናችሁ ጥሩውን ያነሰሳችሁ»
«ሌላ የፃፍሽው አለ?»
«ሃያ ሶስት አለኝ፡፡ አስራ አንዱ ጥሩ ይመስሉኛል። ሰባቱ
በጣም መጥፎ ነው:: አምስቱ ግን ጥሩም አይደል፣ መጥፎም
ኣይደል እንደኔ እስተያየት። ስለዚህ አንተ እነዚህን አምስት
አንብበህ ምን እንደሚመስልህ ብትነግረኝ፣ ተስፋ የሌለውን
እጥለውና ተስፋ ያለውን እየመከርከኝ አሻሽለዋለሁ»
«ክብር ይሰማኛል፣ ግን ልመክርሽ መቻሌን እንጂ
«ትችላለህ። ታግዘኛለህ? »
«ከቻልኩማ በደስታ! አሁን ስለራስሽ ንገሪኝ፡፡ ቅድም እኔ
እንደነገርኩሽ»
ነገረችኝ፡፡ የምንፅፍበት ቋንቋ ተለያየ 'ንጂ ሙከራችን፤
ችግራችን፣ አስተያየታችን በጣም ይመሳሰላል፡፡ ስንወያይ መሸ፡፡
«እማውቃት ጥሩ ርካሽ ምግብ ቤት አለች» ብላ ሳን ሻርል
ባቡር ጣቢያ አጠገብ ወስዳ እራት ጋበዘችኝ። በፈረንሳይ ደምብ ከምግቡ ጋር አንድ ጠርሙስ ወይን ጠጣን፡፡ ሲኒማ ላስገባሽ አልኳት፡፡ ሁለታችንም እንደዚህ ልንጨዋወት የምንችልበት ጊዜ
መቼ ተመልሶ እንደሚመጣ አይታወቅም አለችኝ፡፡ እውነትሽን ነው አልኳት
ወደ ወደቡ ተመልሰን በእግር እየተዘዋወርን ወሬያችንን ቀጠልን። በተርታ የቆሙ ጀልባዎች የሚወዛወዙበት ውሀ ውስጥ የማርሰይ መብራት ይጫወታል። የባህር ሽታ ይዞ ከባህር በኩል የሚመጣው ነፋስ ቅዝቅዝ ያለ ሆኖ ይለሰልሳል። እንደኛው እያወሩ
የሚዘዋወሩ ሰዎች አሉ፤ አብዛኛዎቹ ተቃቅፈዋል፡፡ መንሽራሽር ሲበቃን አንድ ካፌ ገብተን ቁጭ ብለን ቢራ አዘዝን
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
ሲልቪ
ላይ ላዩን
..ተመስገን ክፍል ውስጥ ቁጭ ብዬ ስሰራ አንዳንዴ ውቢቱ ሲልቪ ትመጣና «Salut Castro noire» ትለኛለች። («ሰላም፣ ጥቁር ካስትሮ») (ፂም ስላለኝ ነው፡፡)
«Que la paix soit avec toi Scheherazade Blanche» እላታለሁ
(«ሰላም ላንቺ ይሁን፣ ፃእዳይቱ ሻህራዝድ ሆይ»)
ትስቃለች። በምስራቃውያን አነጋገር እንቀጥላለን። ቀልድ
ነው። ከሲልቪ ጋር ሁልጊዜ ቀልድ ነው:: እውነተኛ ፈረንሳዊት ናት፣ ስለምንም ነገር ቢሆን «Moi je men fous!» ነው የምትለው
(«እኔ ስለዚህ ነገር ደንታ የለኝም»)
ታድያ ደስ ትላለች። ሰፊ አፏ
ሳሙኝ ሳሙኝ ይላል፡፡ አብረሀት ስትሆን ሳቅ ቀልድ ታበዛለህ፣
«ዠማንፉቲዝሟ» ይጋባብሀል፤ ስለምንም ነገር ደንቴ አይኖርህም
አንድ ቀን ግን
«ምንድነው ሁልጊዜ ስትፅፍ የማገኝህ?» አለችና ደብተሬን
አየችው:: የምን ፅህፈት ነው ይሄ? ያገራችሁ ነው?» አለችኝ
«አዎን»
«ምኑም አይገባም»
«ቀላል ነው፡፡ ሁለት መቶ አርባ የሚሆኑ ፊደላት አሉት»
«Quel horreur! (ኧረ የጉድ ያለህ!) እንግዲያው አታስረዳኝ
ይቅርብኝ .. ምንድነው ምትፅፈው?»
«ምንም አይደለም»
«ልብወለድ ነው?»
«ብጤ ነው»
«እንዴት ማለት ብጤ?»
«እንዴት ልበልሽ? ልብወለድ ነው፣ ግን ፈጥሬው አይደለም፣
ያየሁትን የሰማሁትን ነገር ሰብስቤ ቅርጹን እለዋውጣለሁ እንጂ፣
ላንባቢ እንዲጥም»
«ቆይ ቆይ፡፡ አሁን መፃፍ አለብህ ወይስ ለጊዜው ልትተወው
ትችላለህ»
«ልተወው እችላለሁ»
«እንግዲያው ከዚህ እንሂድና ቡና ልጋብዝህ:: እና ስለድርሰት
እናውራ። ይስማማሀል?»
«በደምብ ነዋ! ቆንጆ ሴት ቡና ስትጋብዘኝ ሁልጊዜ
ይስማማኛል»
«Malin Castro noir va!» («ሂድ ወድያ! ፎሌ ጥቁር ካስትሮ!»)
Deux Chevaux መኪናዋ ውስጥ ከገባን በኋላ
«ኤክስ ውስጥ የምወደው ካፌ የለኝም፡፡ ማርሰይ እንሂድ?»
አለችኝ
እየቀለድን እየሳቅን ደጋግማ «Moi, u sais je m en fous!»
እያለች፣ በሆዴ ውበቷን እያደነቅኩ፣ ማርሰይ ደረስን፡፡ የንግድ ሳይሆን የግል የመደሰቻ ልዩ ልዩ አይነት ጀልባዎች ከተደረደሩበት ወደብ አጠገብ አንድ ካፌ ገብተን ቢራ ካዘዝን በኋላ፣ ጉልህ ሰማያዊ
አይኖቿ በፈገግታ እያዩኝ
«ንገረኛ ስለምትፅፈው» አለችኝ
«ምን ልንገርሽ?»
«ስለሰዎቹ፣ ስለጊዜው፣ ስለግንኙነታቸው፣ ማን ማንን እንደ
ሚወድ፣ ማንስ ማንን እንደሚጠላ፣ መፅሀፍህ አንዴት እንደ ሚጀመር፣ አሁን የት እንደደረሰ፣ በኋላ እንዴት እንደሚያልቅ፣
ምን ምን ነገር እንደሚያስቸግርህ፣ መፅሀፍህ ምን እንዲል እንደ
ምትፈልገው፣ ሁሉን ንገረኝ
ቆንጆ ስለሆነች ይሁን፣ አጠያየቁን ስላወቀችበት ይሁን ወይ ሌላ ያልተገለፀልኝ ምክንያት ይኑር እንጃ፣ ስለመፅሀፌ ሁሉን
ነገርኳት። ለማንም ነግሬ የማላውቀውን ለሷ አጫወትኳት፡፡ ችግሩን ደስታውን፣ ብስጭቱን፣ የድል አድራጊነት ስሜቱን፣ ምንም
ሳልደብቅ አዋየኋት። ፈረንሳይኛው ሲያስቸግረኝ ልክ ልናገረው
የፈለግኩትን ቃላት ታቀብለኛለች፣ ምክንያቱም ሀሳቤ ቃላቱን
ቀድሞ ደርሷት ይቆያል። አንዳንድ ቦታ አንድ ሀሳብ ተናግሬ
ጨርሼ ሌላ ሀሳብ አልመጣልህ ሲለኝ አንድ ጥያቄ ትጠይቀኛለች
እሱን ጥያቄ ስመልስ፣ ሌላ ሀሳብ ይመጣልኝና እቀጥላለሁ፡፡ እንደዚህ ብዙ ካወራሁ በኋላ
«ይገርምሻል፣ ይህን ለማንም ነግሬ አላውቅም» አልኳት
«Jen suis lattee» አለችኝ (ክብር ይሰማኛል።)
«እኔ እውነቴን ነው»
«እኔም እውነቴን ነው»
«አሁን ተራሽን አውሪልኝ
«ቆይ» አለችና ከያዘችው የመፃህፍት ቦርሳ አንድ አስር የሚሆኑ ባንድ በኩል ብቻ በታይፕ የተፃፈባቸው ነጠላ ወረቀቶች ሰጠችኝ።
አንብበው አለችኝ፡፡ አነበብኩት፡፡ አጭር ልብ ወለድ ታሪክ ነው።
ስጨርስ ምን ይመስልሀል?» አለችኝ
«አንቺ ነሽ የፃፍሽው?» አልኳት
«አዎን» አለችኝ
«አዝናለሁ። ጥሩ ታሪክ አይደለም»
«ምንድነው የጎደለው?»
«እርግጠኛ አይደለሁም። አየሽ፣ አንድ ሰው የሚወዳትን ሴት
ሊገድል ይችል ይሆናል፡፡ ግን ባስር ገፅ ውስጥ ይህን መናገር
የሚቻል አይመስለኝም፡፡ ቢያንስ ቢያንስ ሁለት መቶ ገፅ
ያስፈልገዋል»
«ይህንንም አንብብ እስቲብላ ሌላ አስራ ሶስት ገፅ ሰጠችኝ።
አነበብኩት። ግሩም ታሪክ ነበር፡፡
«ይህንንም አንቺ ነሽ የፃፍሽው?»
«አዎን»
«ታሪክ ይሉሻል ይሄ ነው! ይህን ጊ ደ ሞፓሳን ራሱ ነው የፃፈው ቢሉኝ አምናለሁ» አልኳት
ጉልህ ሰማያዊ አይኖቿ ልዩ አስተያየት ሰጡኝ፣ እንደማቀፍ ያለ
አስተያየት፣ ሙቀት ያለው አስተያየት
«Merci»አለችኝ
«Je ten prie (ኧረ ምንም አይደለም) ይህን የመሰለ ለመፃፍ
ስትችዪ፣ እንዴት አርገሽ የቅድሙን ፃፍሽው?» አልኳት
መሳቅ ጀመረች (ጥርሶቿ ትክክል ሆነው ነጫጭ ናቸው። ነጭ
የፈረንጅ ጥርስ ብዙ እይታይም) «እኔ እንጃ አለችኝ «በምፅፍበት
ሰአት ሁሉም እኩል ጥሩ ሆኖ ይሰማኛል። ካንድ ሁለት ወር በኋላ
ሳነበው ነው እውነተኛው ዋጋው የሚታየኝ»
«ይሄ መጥፎው መቼ ነው የተፃፈው?»
«ካንድ አመት ተኩል በፊት
«እንግዲያው መጥፎ መሆኑ
ድሮ ገብቶሻል። ለምን
እስነበብሽኝ?»
«ላውቅህ ስለፈለግኩ። ማንም ሰው ቢሆን፣ እንደምፅፍ ካወቀ
ወይም እንዲያውቅ ከፈለግኩ፣ መጀመሪያ መጥፎ ታሪኬን
አስነብሰዋለሁ። አንብቦት ጥሩ ነው ካለ በቃው። ሁለተኛ እኔ
የፃፍኩትን አያነብም። እስካሁን ለአንድ ስምንት ሰው አስነብቤያለሁ።
አንተና አንድ የፓሪስ ጓደኛዬ ብቻ ናችሁ መጥፎውን መጥፎ
ያላችሁት። ስለዚህ ሁለታችሁ ብቻ ናችሁ ጥሩውን ያነሰሳችሁ»
«ሌላ የፃፍሽው አለ?»
«ሃያ ሶስት አለኝ፡፡ አስራ አንዱ ጥሩ ይመስሉኛል። ሰባቱ
በጣም መጥፎ ነው:: አምስቱ ግን ጥሩም አይደል፣ መጥፎም
ኣይደል እንደኔ እስተያየት። ስለዚህ አንተ እነዚህን አምስት
አንብበህ ምን እንደሚመስልህ ብትነግረኝ፣ ተስፋ የሌለውን
እጥለውና ተስፋ ያለውን እየመከርከኝ አሻሽለዋለሁ»
«ክብር ይሰማኛል፣ ግን ልመክርሽ መቻሌን እንጂ
«ትችላለህ። ታግዘኛለህ? »
«ከቻልኩማ በደስታ! አሁን ስለራስሽ ንገሪኝ፡፡ ቅድም እኔ
እንደነገርኩሽ»
ነገረችኝ፡፡ የምንፅፍበት ቋንቋ ተለያየ 'ንጂ ሙከራችን፤
ችግራችን፣ አስተያየታችን በጣም ይመሳሰላል፡፡ ስንወያይ መሸ፡፡
«እማውቃት ጥሩ ርካሽ ምግብ ቤት አለች» ብላ ሳን ሻርል
ባቡር ጣቢያ አጠገብ ወስዳ እራት ጋበዘችኝ። በፈረንሳይ ደምብ ከምግቡ ጋር አንድ ጠርሙስ ወይን ጠጣን፡፡ ሲኒማ ላስገባሽ አልኳት፡፡ ሁለታችንም እንደዚህ ልንጨዋወት የምንችልበት ጊዜ
መቼ ተመልሶ እንደሚመጣ አይታወቅም አለችኝ፡፡ እውነትሽን ነው አልኳት
ወደ ወደቡ ተመልሰን በእግር እየተዘዋወርን ወሬያችንን ቀጠልን። በተርታ የቆሙ ጀልባዎች የሚወዛወዙበት ውሀ ውስጥ የማርሰይ መብራት ይጫወታል። የባህር ሽታ ይዞ ከባህር በኩል የሚመጣው ነፋስ ቅዝቅዝ ያለ ሆኖ ይለሰልሳል። እንደኛው እያወሩ
የሚዘዋወሩ ሰዎች አሉ፤ አብዛኛዎቹ ተቃቅፈዋል፡፡ መንሽራሽር ሲበቃን አንድ ካፌ ገብተን ቁጭ ብለን ቢራ አዘዝን
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...ለአሥራ ዘጠኝ ዓመት እስር ቤት ውስጥ ሲቀመጥ ኣንድ ቀን እንኳን እንባ አልወጣውም::
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ከቤተክርስቲያን አናት ላይ የተሰቀለው ሰዓት ስምንት ሰዓት ሲደውል ዣን ቫልዣ ከእንቅልፉ እንደገና ነቃ፡፡ ከአራት ሰዓት በላይ ጥሩ እንቅልፍ ወስዶት ተኝቷል፡፡ ድካሙ ሁሉ ወጣለት:: ለዚህን ያህል ጊዜ የእረፍት ሰዓት ኣግኝቶ አያውቅም፡፡ ዓይኑን ገልጦ በአካባቢው በሰፈነው ጨለማ
ዘልቆ ለማየት ሞከረ፡፡ ለማየት ባለመቻሉ እንደገና እንቅልፍ እንዲወስደው ዓይኖቹን ጨፈነ፡፡
ቀኑን ሙሉ አእምሮ በብዙ ነገሮች ተበጥብጦ ከዋለና የተለያዩ ነገሮች ከተመላለሱበት አንድ ጊዜ እንጂ ሁለት ጊዜ እንቅልፍ ሊወስድ እንደማይችል
ሁሉ ዣን ቫልዣንም ሊወስደው አልቻለም:: እንቅልፍ መጀመሪያ ሲመጣ ያዳፋል፡፡ ሁለተኛ ግን ቢለማመጡትም በዓይን አይዞርም:: እንደገና እንቅልፍ
ሊወስደው ስላልቻላ ማሰብ ጀመረ::
ብዙ ዓይነት አሳብ ከኀሊናው ውስጥ ገባ፡፡ ግን ሌሎቹን ሁሉ እየዋጠ እርሱ ብቻ እየተመላለሰ ያስቸገረው አንድ አሳብ ነበር፡፡ እነዚያ መዳም ማግልዋር ከጠረጴዛው ላይ የደረደሩዋቸው የሚያማምሩ ስድስት ከብር
የተሠሩ ሣህኖችና ትልቅ የብር ጭልፋ በዓይኑ ዞሩ፡፡ በጣም ወዷቸዋል:: አጠገቡ ከጳጳሱ ትራስጌ በኩል ቡፌ ውስጥ ሴትዬዋ ሲያስቀምጧቸው
አይቶአል፡፡ ከብር የተሠሩ ጥንታዊ ቅርስ በመሆናቸው ከነጭልፋው እስካ 200 ፍራንክ እንደሚያወጡ ያውቃል፡፡
ኅሊናው ከወዲያ ወዲህ እየዋለለ አንድ ሰዓት አለፈ፡፡ በአሳብ እየዋተቱ አንድ ሰዓት ማሳለፍ፤ ያውም ሌሊት በጨለማ ምን ያህል ረጅም እንደሆነ
የደረሰበት ያውቀዋል፡፡ የቤተክርስቲያኑ ሰዓት ደወል ዘጠኝ ሰዓት መሆኑን አበሰረ:: ዓይኑን በድንገት ገልጦ ከአልጋው ዘልሉ ወረደ:: ስልቻውን በእጁ
እየዳሰሰ ፈለገና እንደያዘው ከአልጋው ጠርዝ ቁጭ አለ፡፡ ሳያውቀው ብዙ ተቀመጠ፡፡ ሰዓቱ በየአሥራ አምስት ደቂቃና ግማሽ ሰዓት ደወል እየደወለ ባይቀሰቅሰውማ እስኪነጋ ድረስ በተቀመጠ፡፡ ደወሉ «አይዞህ፣ በርታ» የሚለው መሰለው::
ተነስቶ ቆመ፤ ለመራመድ ግን አመነታ:: አንድ እርምጃ ወደፊት
ተራምዶ አዳመጠ፡፡ ሁሉም ነገር ጸጥ ብሎአል:: ቀስ ብሎ በጥንቃቄ ወደ መስኮቱ ተጠጋ፡፡ ሌሊቱ ጥቅጥቅ ባለ ጨለማ የተዋጠ ኣልነበረም:: ጨረቃ
በሩቁ ትታያለች:: ሆኖም ደመና ዞሮባታል፡፡ ደመና ጨረቃዋን በጋረዳት ቁጥር ቤቱ ትንሽ ጨለም ይላል፡፡ ውጪው በደምብ ሲታይ እቤት ውስጥ ግን ያንገዳግዳል፡፡ መስኮቱ አጠገብ ደርሶ መስኮቱን ሲመለከት በቀላሉ
እንደሚከፈት ስለተገነዘበ ከፈተው:: ሆኖም ኃይለኛ ብርድ ስለገባ መልሶ ዘጋው:: መስኮቱ መስታወት ስለነበር እንደተዘጋ ግቢውን ቃኘ፡፡ ግቢው
በአነስተኛ ግምብ መከለሉን ተመለከተ:: ከግምቡ ውጭ ረጃጅም ዛፎች ነበሩ፡፡ በሁለት ዛፎች መካከል ያለውን ርቀት ሲያጤን ርቀታቸው ተመሳሳይ
ሆኖ ስላየው ምናልባት ማዘጋጃ ቤቱ የተከላቸው ዛፎች መሆናቸውን በመገመት ከአጥሩ ውጭ ያለው መንገድ አውራ ጎዳና መሆን አለበት ብሎ ደመደመ::
ወደ ውሳኔ አሳብ እንደደረሰ ሰው በቆራጥነት ወደ አልጋው ተመለሰ፡፡ አቆማዳውን አንስቶ ከፈተውና ከውስጠ ምናምን ፈለገ፡፡ ኣንድ ነገር አውጥቶ
አልጋው ላይ አስቀመጠ፡፡ ጫማውን ኪሱ ውስጥ ከተተ፡፡ ኣልጋው ላይ ካስቀመጠው እቃ ሌላ የተቀሩትን እሳስሮ ትከሻው ላይ አኖረ፡፡ ቆቡን አጠለቀና ዱላውን ፈልጎ ከያዘ በኋላ ያሰረውን እቃ ከመስኮቱ ሥር
አስቀመጠው:: ወደ ኣልጋው ተመልሶ ያስቀመጠውን እቃ አነሳ:: እቃው ከአንድ ጫፍ እንደ ጦር የሾለ፣ ከሌላው ጫፍ ቋር ያለው ወፍራም ብረት ነበር፡፡ በዚያ ጨለማ ብረቱ ለምን ሥራ እንደተዘጋጀ ለመለየት አስቸጋሪ
ነበር፡፡ ዱላ ነው ወይስ እቃ ማንሻ? አይታወቅም:: ቀን እንኳን ቢሆን
የማዕድን ሠራተኞች መቆፈሪያ ነው ለማለት ያስችላል፡፡ በዚያን ጊዜ ቱሉን ከተባለ ቦታ አካባቢ በሚገኙ ከፍተኛ ኮረብታዎች ላይ ድንጋይ እንዲፈልጡ
የተፈረደባቸው ወንጀለኞች ይቀጠሩ ነበር፡፡ ወንጀለኞቹ ብዙውን ጊዜ የዚያን ዓይነት ብረት የመሰለ መፍለጫ ይይዛሉ፡፡
ዣን ቫልዣ ያን ብረት በቀኝ እጁ ያዘ፡፡ ትንፋሹን ውጦ በዝግታ
ተራመደ:: ወደ ጳጳሱ መኝታ ቤት አመራ:: ወደ በሩ ሲጠጋ አለመቀርቀሩን ተመለከተ፡፡ «አባታችን በራቸውን ሳይቆልፉ ነው የሚተኙት» አለ በልቡ፡፡
ዣን ቫልዣ ጆሮውን አቅንቶ አዳመጠ፡፡ ድምፅ የሚሉት ነገር
የለም:: በሩን ከፈት አድርጎ ሲፈራ ሲቸር በጣቶቹ ጫፍ ቀስ ብሎ ገፋው::ጥንቃቄው ከድመት ይበልጣል:: በሩ ምንም ድምፅ ሳያሰማና ለመንቀሳቀሱ
እንኳን በሚያጠራጥር ሁኔታ በዝግታ በመገፋቱ ከመጀመሪያው ይበልጥ ጥቂት ከፈት አለ፡
ለጥቂት ጊዜ ከበሩ አጠገብ ቆም አለ፡፡ አሁን ግን በይበልጥ ድፍረቱ
ስለተሰባሰበለት ከቀድሞ በበለጠ ጉልበት በሩን ገፋ አደረገው:: በዚህ ጊዜ የበሩ ማያያገዥ የዛገ ብረት ረዘም ያለ የሚሰቀጥጥ ድምፅ አሰማ፡፡
ልቡ የተሰነጠቀ መሰለው:: እንደ እንጨት ደርቆ ከቆመበት ሐውልት
ይመስል ሳይንቀሳቀስ ለጥቂት ጊዜ ተገተረ:: ለመነቃነቅ አቅም አነሰው ድፍረትም አልነበረውም:: ጥቂት ደቂቃዎች አለፉ:: በሩ ወለል ብሎ ተከፍቷል:: ወደ ክፍሉ ተመለከተ:: የተንቀሳቀሰ ነገር የለም:: አዳመጠ፤ የሚንቀሳቀስ ወይም ድምፅ የሚሰጥ ነገር አሁንም ከጆሮው ኣልገባም::
የበሩ ድምፅ ማንንም አልቀሰቀሰም ማለት ነው::
የመጀመሪያው አደጋ አለፈ:: ልቡ ግን በጣም ፈርቷል ፤ ሆኖም
አላወላወለም:: የፈለገውን ቶሎ ለመጨረስ ቁርጥ አሳብ አደረገ፡፡ በአንድ እርምጃ ከክፍለ ውስጥ ገባ፡፡ ክፍሉ ውስጥ ጸጥታ ሰፍኖበታል፡፡ ዣን ቫልገዣ ከወንበርና ጠረጴዛ ጋር እንዳይጋጭ እየተጠነቀቀ ወደፊት ተራመደ::ጳጳሱ ክፍለ ውስጥ ጥግ ይዘው ተኝተው በኃይል ሲተነፍሱ አዳመጠ፡፡በድንገት ቆም አለ:: ከጳጳሰ አልጋ አጠገብ ደርሷል፡፡
ቶሉ የደረሰ መሰለው::አንዳንድ ጊዜ ተፈጥሮ የምንሠራውን ሥራ ለማራገብ ከእኛ ጋር ታብራለች:: ለግማሽ ሰዓት ያህል ደመና ጨረቃን በመጋረድዋ አካባቢው
ጨልሞ ነበር፡፡ አሁን ግን ልክ እንደተማከረ ሰው ዣን ቫልዣ ከጳጳሱ አልጋ አጠገብ እንደቆመ ደመና ለጨረቃ ቦታዋን ለቀቀች:: የጨረቃ ብርሃን በመስኮት በኩል ዘልቆ በመግባት ከጳጳሱ የገረጣ ፊት ላይ አበራ:: ጭልጥ
አድርጎ እንቅልፍ ወስዷቸዋል። የሌሊቱ ብርድ ከባድ ስለነበር ወፈር ያለ የሌሊት ልብስ ለብሰው በጀርባቸው ተዘርረው ነው የተኙት፡፡ ስንት ደግ ሥራ የሠራው ታማኙና ነዳያን የሳሙት እጃቸው ካልጋው ጠርዝ አልፎ ወደመሬት ተንጠልጥሎአል፡፡ ሌላው እጃቸው ከደረታቸው ላይ በማረፉ
የጵጵስና ቀለበታቸው ያበራል፡፡ እዚያ ተጋድመው ሲያይዋቸው መላ አካላቸው የተስፋ ፣ የደስታና የእርካታ ማኅደር እንደሆነ ይናገራል:: በቃላት ለመግለጽ የሚያዳግት የማይታይ ብርሃን ከግንባራቸው ላይ አርፎአል፡፡
የጨረቃው በሰማይ ላይ መንጣለል፤ የምድር በከፊል የተኛች መምሰል ፤ የግቢው አትክልት እርጭ ማለትና የቤቱና የዚያች ሰዓት ፀጥታ እኚህ መለኮት የቀረባቸውን ሰው «አክብሩ አትድፈሯቸው» የሚያሰኝ
ነበር፡፡ ዓይናቸውን ጨፍነው እንደተኙ የነበራቸው ግርማ ሞገስና ለተስፋ ምንጭ የሆነውና በጨርቅ ያልተሽፈነው ግንባራቸው ሲያዩት በፍርሃት የሚያርበደብድ ነበር፡፡
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...ለአሥራ ዘጠኝ ዓመት እስር ቤት ውስጥ ሲቀመጥ ኣንድ ቀን እንኳን እንባ አልወጣውም::
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ከቤተክርስቲያን አናት ላይ የተሰቀለው ሰዓት ስምንት ሰዓት ሲደውል ዣን ቫልዣ ከእንቅልፉ እንደገና ነቃ፡፡ ከአራት ሰዓት በላይ ጥሩ እንቅልፍ ወስዶት ተኝቷል፡፡ ድካሙ ሁሉ ወጣለት:: ለዚህን ያህል ጊዜ የእረፍት ሰዓት ኣግኝቶ አያውቅም፡፡ ዓይኑን ገልጦ በአካባቢው በሰፈነው ጨለማ
ዘልቆ ለማየት ሞከረ፡፡ ለማየት ባለመቻሉ እንደገና እንቅልፍ እንዲወስደው ዓይኖቹን ጨፈነ፡፡
ቀኑን ሙሉ አእምሮ በብዙ ነገሮች ተበጥብጦ ከዋለና የተለያዩ ነገሮች ከተመላለሱበት አንድ ጊዜ እንጂ ሁለት ጊዜ እንቅልፍ ሊወስድ እንደማይችል
ሁሉ ዣን ቫልዣንም ሊወስደው አልቻለም:: እንቅልፍ መጀመሪያ ሲመጣ ያዳፋል፡፡ ሁለተኛ ግን ቢለማመጡትም በዓይን አይዞርም:: እንደገና እንቅልፍ
ሊወስደው ስላልቻላ ማሰብ ጀመረ::
ብዙ ዓይነት አሳብ ከኀሊናው ውስጥ ገባ፡፡ ግን ሌሎቹን ሁሉ እየዋጠ እርሱ ብቻ እየተመላለሰ ያስቸገረው አንድ አሳብ ነበር፡፡ እነዚያ መዳም ማግልዋር ከጠረጴዛው ላይ የደረደሩዋቸው የሚያማምሩ ስድስት ከብር
የተሠሩ ሣህኖችና ትልቅ የብር ጭልፋ በዓይኑ ዞሩ፡፡ በጣም ወዷቸዋል:: አጠገቡ ከጳጳሱ ትራስጌ በኩል ቡፌ ውስጥ ሴትዬዋ ሲያስቀምጧቸው
አይቶአል፡፡ ከብር የተሠሩ ጥንታዊ ቅርስ በመሆናቸው ከነጭልፋው እስካ 200 ፍራንክ እንደሚያወጡ ያውቃል፡፡
ኅሊናው ከወዲያ ወዲህ እየዋለለ አንድ ሰዓት አለፈ፡፡ በአሳብ እየዋተቱ አንድ ሰዓት ማሳለፍ፤ ያውም ሌሊት በጨለማ ምን ያህል ረጅም እንደሆነ
የደረሰበት ያውቀዋል፡፡ የቤተክርስቲያኑ ሰዓት ደወል ዘጠኝ ሰዓት መሆኑን አበሰረ:: ዓይኑን በድንገት ገልጦ ከአልጋው ዘልሉ ወረደ:: ስልቻውን በእጁ
እየዳሰሰ ፈለገና እንደያዘው ከአልጋው ጠርዝ ቁጭ አለ፡፡ ሳያውቀው ብዙ ተቀመጠ፡፡ ሰዓቱ በየአሥራ አምስት ደቂቃና ግማሽ ሰዓት ደወል እየደወለ ባይቀሰቅሰውማ እስኪነጋ ድረስ በተቀመጠ፡፡ ደወሉ «አይዞህ፣ በርታ» የሚለው መሰለው::
ተነስቶ ቆመ፤ ለመራመድ ግን አመነታ:: አንድ እርምጃ ወደፊት
ተራምዶ አዳመጠ፡፡ ሁሉም ነገር ጸጥ ብሎአል:: ቀስ ብሎ በጥንቃቄ ወደ መስኮቱ ተጠጋ፡፡ ሌሊቱ ጥቅጥቅ ባለ ጨለማ የተዋጠ ኣልነበረም:: ጨረቃ
በሩቁ ትታያለች:: ሆኖም ደመና ዞሮባታል፡፡ ደመና ጨረቃዋን በጋረዳት ቁጥር ቤቱ ትንሽ ጨለም ይላል፡፡ ውጪው በደምብ ሲታይ እቤት ውስጥ ግን ያንገዳግዳል፡፡ መስኮቱ አጠገብ ደርሶ መስኮቱን ሲመለከት በቀላሉ
እንደሚከፈት ስለተገነዘበ ከፈተው:: ሆኖም ኃይለኛ ብርድ ስለገባ መልሶ ዘጋው:: መስኮቱ መስታወት ስለነበር እንደተዘጋ ግቢውን ቃኘ፡፡ ግቢው
በአነስተኛ ግምብ መከለሉን ተመለከተ:: ከግምቡ ውጭ ረጃጅም ዛፎች ነበሩ፡፡ በሁለት ዛፎች መካከል ያለውን ርቀት ሲያጤን ርቀታቸው ተመሳሳይ
ሆኖ ስላየው ምናልባት ማዘጋጃ ቤቱ የተከላቸው ዛፎች መሆናቸውን በመገመት ከአጥሩ ውጭ ያለው መንገድ አውራ ጎዳና መሆን አለበት ብሎ ደመደመ::
ወደ ውሳኔ አሳብ እንደደረሰ ሰው በቆራጥነት ወደ አልጋው ተመለሰ፡፡ አቆማዳውን አንስቶ ከፈተውና ከውስጠ ምናምን ፈለገ፡፡ ኣንድ ነገር አውጥቶ
አልጋው ላይ አስቀመጠ፡፡ ጫማውን ኪሱ ውስጥ ከተተ፡፡ ኣልጋው ላይ ካስቀመጠው እቃ ሌላ የተቀሩትን እሳስሮ ትከሻው ላይ አኖረ፡፡ ቆቡን አጠለቀና ዱላውን ፈልጎ ከያዘ በኋላ ያሰረውን እቃ ከመስኮቱ ሥር
አስቀመጠው:: ወደ ኣልጋው ተመልሶ ያስቀመጠውን እቃ አነሳ:: እቃው ከአንድ ጫፍ እንደ ጦር የሾለ፣ ከሌላው ጫፍ ቋር ያለው ወፍራም ብረት ነበር፡፡ በዚያ ጨለማ ብረቱ ለምን ሥራ እንደተዘጋጀ ለመለየት አስቸጋሪ
ነበር፡፡ ዱላ ነው ወይስ እቃ ማንሻ? አይታወቅም:: ቀን እንኳን ቢሆን
የማዕድን ሠራተኞች መቆፈሪያ ነው ለማለት ያስችላል፡፡ በዚያን ጊዜ ቱሉን ከተባለ ቦታ አካባቢ በሚገኙ ከፍተኛ ኮረብታዎች ላይ ድንጋይ እንዲፈልጡ
የተፈረደባቸው ወንጀለኞች ይቀጠሩ ነበር፡፡ ወንጀለኞቹ ብዙውን ጊዜ የዚያን ዓይነት ብረት የመሰለ መፍለጫ ይይዛሉ፡፡
ዣን ቫልዣ ያን ብረት በቀኝ እጁ ያዘ፡፡ ትንፋሹን ውጦ በዝግታ
ተራመደ:: ወደ ጳጳሱ መኝታ ቤት አመራ:: ወደ በሩ ሲጠጋ አለመቀርቀሩን ተመለከተ፡፡ «አባታችን በራቸውን ሳይቆልፉ ነው የሚተኙት» አለ በልቡ፡፡
ዣን ቫልዣ ጆሮውን አቅንቶ አዳመጠ፡፡ ድምፅ የሚሉት ነገር
የለም:: በሩን ከፈት አድርጎ ሲፈራ ሲቸር በጣቶቹ ጫፍ ቀስ ብሎ ገፋው::ጥንቃቄው ከድመት ይበልጣል:: በሩ ምንም ድምፅ ሳያሰማና ለመንቀሳቀሱ
እንኳን በሚያጠራጥር ሁኔታ በዝግታ በመገፋቱ ከመጀመሪያው ይበልጥ ጥቂት ከፈት አለ፡
ለጥቂት ጊዜ ከበሩ አጠገብ ቆም አለ፡፡ አሁን ግን በይበልጥ ድፍረቱ
ስለተሰባሰበለት ከቀድሞ በበለጠ ጉልበት በሩን ገፋ አደረገው:: በዚህ ጊዜ የበሩ ማያያገዥ የዛገ ብረት ረዘም ያለ የሚሰቀጥጥ ድምፅ አሰማ፡፡
ልቡ የተሰነጠቀ መሰለው:: እንደ እንጨት ደርቆ ከቆመበት ሐውልት
ይመስል ሳይንቀሳቀስ ለጥቂት ጊዜ ተገተረ:: ለመነቃነቅ አቅም አነሰው ድፍረትም አልነበረውም:: ጥቂት ደቂቃዎች አለፉ:: በሩ ወለል ብሎ ተከፍቷል:: ወደ ክፍሉ ተመለከተ:: የተንቀሳቀሰ ነገር የለም:: አዳመጠ፤ የሚንቀሳቀስ ወይም ድምፅ የሚሰጥ ነገር አሁንም ከጆሮው ኣልገባም::
የበሩ ድምፅ ማንንም አልቀሰቀሰም ማለት ነው::
የመጀመሪያው አደጋ አለፈ:: ልቡ ግን በጣም ፈርቷል ፤ ሆኖም
አላወላወለም:: የፈለገውን ቶሎ ለመጨረስ ቁርጥ አሳብ አደረገ፡፡ በአንድ እርምጃ ከክፍለ ውስጥ ገባ፡፡ ክፍሉ ውስጥ ጸጥታ ሰፍኖበታል፡፡ ዣን ቫልገዣ ከወንበርና ጠረጴዛ ጋር እንዳይጋጭ እየተጠነቀቀ ወደፊት ተራመደ::ጳጳሱ ክፍለ ውስጥ ጥግ ይዘው ተኝተው በኃይል ሲተነፍሱ አዳመጠ፡፡በድንገት ቆም አለ:: ከጳጳሰ አልጋ አጠገብ ደርሷል፡፡
ቶሉ የደረሰ መሰለው::አንዳንድ ጊዜ ተፈጥሮ የምንሠራውን ሥራ ለማራገብ ከእኛ ጋር ታብራለች:: ለግማሽ ሰዓት ያህል ደመና ጨረቃን በመጋረድዋ አካባቢው
ጨልሞ ነበር፡፡ አሁን ግን ልክ እንደተማከረ ሰው ዣን ቫልዣ ከጳጳሱ አልጋ አጠገብ እንደቆመ ደመና ለጨረቃ ቦታዋን ለቀቀች:: የጨረቃ ብርሃን በመስኮት በኩል ዘልቆ በመግባት ከጳጳሱ የገረጣ ፊት ላይ አበራ:: ጭልጥ
አድርጎ እንቅልፍ ወስዷቸዋል። የሌሊቱ ብርድ ከባድ ስለነበር ወፈር ያለ የሌሊት ልብስ ለብሰው በጀርባቸው ተዘርረው ነው የተኙት፡፡ ስንት ደግ ሥራ የሠራው ታማኙና ነዳያን የሳሙት እጃቸው ካልጋው ጠርዝ አልፎ ወደመሬት ተንጠልጥሎአል፡፡ ሌላው እጃቸው ከደረታቸው ላይ በማረፉ
የጵጵስና ቀለበታቸው ያበራል፡፡ እዚያ ተጋድመው ሲያይዋቸው መላ አካላቸው የተስፋ ፣ የደስታና የእርካታ ማኅደር እንደሆነ ይናገራል:: በቃላት ለመግለጽ የሚያዳግት የማይታይ ብርሃን ከግንባራቸው ላይ አርፎአል፡፡
የጨረቃው በሰማይ ላይ መንጣለል፤ የምድር በከፊል የተኛች መምሰል ፤ የግቢው አትክልት እርጭ ማለትና የቤቱና የዚያች ሰዓት ፀጥታ እኚህ መለኮት የቀረባቸውን ሰው «አክብሩ አትድፈሯቸው» የሚያሰኝ
ነበር፡፡ ዓይናቸውን ጨፍነው እንደተኙ የነበራቸው ግርማ ሞገስና ለተስፋ ምንጭ የሆነውና በጨርቅ ያልተሽፈነው ግንባራቸው ሲያዩት በፍርሃት የሚያርበደብድ ነበር፡፡
#ገረገራ
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
“እንዴት ነህ ጃ?” አልሁት፣ ከተንጋለልሁበት መነሳት የእረጥብ አራስ ያህል እያቃተኝ፡፡ ያቆላመጥሁት ራሱ አልመሰለኝም ማን ብዬ ነዉ ግን የጠራሁት? እንደ እህት ጃ ነዉ ወይስ እንደ ቀበሌ ጃሪም ብዬ? እንጃልኝ
ብቻ።
“ጭራሽ አልጋዬ ላይ?”
"በይ አልጋዬን ልቀቂልኝ ያለ በሚመስል ዓይኑ ጠቅ አድርጎኝ ሲቆም፣ ብድግ ብዬ ከአልጋዉ ላይ ወርጄለት ወደ ራሴ ክፍል ሄድሁ። ምን እንዳለኝ እንኳን ልብ ያልሁት በኋላ ሻንጣዎቹን ወደ ዉጪ ማመላለስ ሲጀምር ነበር።
የእመዋ ቤት ጎስቆል ያለች ብትሆንም፣ አሠራሯ ሁልጊዜም
ያስገርመኛል። ክብ አይሏት፣ አራት ማዕዘን አይሏት፣ የግንብ አይሏት፣
የጭቃ አይሏት፣ ብቻ ግን ሁሉንም ትመስላለች። በዚያ ላይ የሞቀች
ናት፡፡ እኔም፣ ምንም እንኳን ከቤተሰባችን ጋር አባታችንን እየተከተልሁ በዞርሁበት ክፍለ ሀገር የኖርሁባቸዉ ቤቶች ሁሉ የነበረኝ ትዝታ ባይለቀኝም፣ በቅጡ ነፍስ ያወቅሁባት ቤት ናትና እንደዚችኛዋ የሚሆንልኝ ቤት ግን የለም፡፡ ጠባብ ብትመስልም ለእኛ ግን ጠብባን አታዉቅም። በዚች ቤት ሁላችንም የየራሳችን ክፍል አለን፡፡ በእርግጥ በዚች ቤት ያለንን ክፍል መጀመሪያ የያዝነዉ እንደ ዋዛ፣ በሽሚያ ነበር።
ትዝ ይለኛል፤ መጨረሻ ከነበርንበት ከተማ ቀይረን ወደ'ዚች ቤት ልንገባ ደጁን የረገጥነዉ ኅዳር 29፣ ሐሙስ ቀን ነበር።
“በሉ እንግዲህ” አለችን እመዋ፣ ልክ ወደ'ዚች ቤት በራፍ
ከመድረሳችን፣ ቤቷ ወዳሏት ክፍሎች እየለቀቀችን፡፡ “መቼም እንግዲህ አድገናል ብላችኋል። ለየብቻ ማደሩን ከሆነ የጓጓችሁለት ይኸዉ እንዳሻችሁ ሞክሩት ደግሞ። በሉ፤ ኮተቶቻችሁን በየክፍላችሁ አስገቡ”
“በየክፍላችሁ?” አልሁኝ እኔ፣ እንክት ብዬ፡ ያደግነዉ አንድ ሰፊ
ምንጣፍ መሀል ወለሉ ላይ አንጥፈን፣ ተቃቅፈን እየተኛን ነዉ። እየተኛን አልሁ እንጂ፣ የሌሊቱን እኩሌታ እንኳን የምናሳልፈዉ እንዲሁ እንዳዉካካን ነበር። ለወጉ መብራቱን እናጠፋፋና፣ ልብሳችንንም ለዋዉጠን በዚያ ሀገር በሚያህለዉ ምንጣፍ ላይ በጎን በጎናችን እንሆናለን። ከዚያ ተረቡ፣ አሽሙሩ፣ ቀልዱ፣ ተረቱ፣ እንቆቅልሹ፣ እንካ ስላንቲያዉ፣ መሳሳቁ፣ መላፋቱ ይመጣል። ያልሆነዉ ምን አለ? ዛሬ ተረኛ እኔ የሆንሁ እንደሆነ፤ አንዴ በቃል ተረብ፣ ቀጥለዉ በልፊያ፣
ቀጥለዉ ቁንጥጫ ሁሉም ይረባረቡብኛል። ታዲያ ያሉኝን ቢሉኝስ ወንድሞቼንና እህቶቼን ላኮርፋቸዉ? ኧረ በጭራሽ! እንዲያዉም አሁን አሁን ሳስበዉ፣ ተረባቸዉን እና ልፊያቸዉን ሁሉ ለመከላከል አደርገዉ
የነበረዉ መፍጨርጨር ሁሉ ሳይጠቅመኝ አልቀረም። ቢያንስ ቢያንስ ንግግሬ እና ጡንቻዬን አዳብሮልኛል። በዚያም ላይ እኮ እኔ በተራዬ የቀመስኋትን ሁሉ፣ እነሱም በየተራቸዉ ይቀምሷታል።
“በየክፍላችሁ? አረ ምን ዓይነት፣ የማን ሐሳብ ነዉ ግን ይኼ?” አልኋት እመዋን፣ ሆዴን ባር ባር እያለዉ።
“ቀርፋፎ! ይልቅ ተመርጦ ሳያልቅብሽ ክፍልሽን አትመርጪም?” አለችኝ
ኣንደኛዋ እህቴ፣ የራሷን ክፍል መርጣ ማንም እንዳይነካባት ቆልፋዉ ወደኔ እየተመለሰች።
ብቻዬን እንደ ቀረሁ አስተዋልሁ። ሁሉም ይሻለኛል የሚለዉን ክፍል
ተሻምቷል። እኔ እዚህ በትዝታ ወዲያ ወዲህ ስል፣ እንደ ዱሯችን
እንድንተኛ እንድመካከራቸዉ እንኳን የሚሆን አፍታ ሳይታገሱኝ መስኮት ያላቸዉን እና በመስኮት በኩል አሻግሮ ለማየት የሚያመቹትን ክፍሎች ሁሉ ተሽቀዳድመዉባቸዋል፡፡ በተለይ የጃሪም ደግሞ ልዩ ነዉ፡፡ ከመስኮት በተጨማሪ፣ በዚህ በኩል ወደ ዋናዉ ሳሎን የሚያስገባ እና በዚያ በኩል
ደግሞ ወደ ዉጪ የሚያስወጣ በር ያለዉን፣ ሰፊዉን ክፍል ነዉ ተሻምቶ የያዘዉ።
ምንም አማራጭ ስላጣሁ እነሱ ያያዟቸዉን ክፍሎች እየተዟዟርሁ
ስመለከት ቆይቼ፣ ያሉኝን ኮተቶች ሁሉ እየጎተትሁ ወደ ተተወችልኝ
ምራጫ ክፍል አስገባሁባት። ያም ሆኖ ግን እምብዛም አልከፋኝም ነበር። ምክንያቱም፣ ዞሮ ዞሮ ወንድሞቼ እና እህቶቼ ናቸዉ። ለስሙ ክፍሉ የየራሳቸዉ ቢባልም፣ መቼም በፈለግሁት ክፍል እንዳላድር የሚከለክለኝ
አይኖርም፡፡ እነሱም ለጊዜዉ መስሏቸዉ ነዉ እንጂ፣ በዚህ ምርጫቸዉ እንደሚጸጸቱ ገምቻለሁ። ለአንድ ወይም ላኹለት አዳር ለየብቻ ከሞከሩት
በኋላ ወደ መሀል ወለል መጥተዉ እንደ ዱሯችን አብረን እንተኛ
ማለታቸዉ አይቀርም፡፡ ይኼን ይኼን ሳስብ ትንሽ ቀለል ብሎኝ የነበረ ቢሆንም፣ ዉሎ አድሮ የሆነዉ ግን እንደ ጠበቅሁት አይደለም።
ይኼዉ በእንደዚያ ያለ ሁኔታ የያዝነዉ ክፍል አሁንም ድረስ ድርሻችን እንደሆነ አለ። የኋላ በኋላም ቢሆን፣ ጨክነን የየራሳችንን ቤት ስላልሠራን፣ በዚሁ ቤት ያለዉ ክፍላችን እንደ ተጠበቀ አለ። በርግጥ ገሚሶቹ ወንድሞቼ ወጣ ገባ እያሉ የኪራይ ቤት ኑሮ የሞካከሩ አሉ።
የሆነዉ ሆኖ፣ አሁን የየራሳችንን ሥራ ከያዝን እና የየራሳችን ኃላፊዎች ሆነናል ካልን በኋላም የምንኖረዉ እዚሁ ግቢ ነዉ። ቀን የየራሳችንን ሥራ ስንከዉን ዉለን አዳራችንም በየራሳችን ክፍል፣ በየራሳችን አልጋ ሆኗል። በእርግጥ እኔ ከሌሎቹ በተለየ መልኩ፣ ክፍት ባገኘሁት አልጋ
ሁሉ ነዉ የምተኛዉ። እንዲያዉም ብዙ ጊዜ ክፍት ሳይሆንም ጭምር፣ ጠጋ በሉልኝ ብዬ አብሬ የምተኛበት ጊዜ አለኝ። እያየኋቸዉም እንኳን
ደርሰዉ ንፍቅ በሚሉኝ ሰዓት ስስቴን የማስታግሰዉ፣ እነሱን እቅፍ አድርጌ ትንፋሻቸዉን ስምግ ያደርሁ እንደሆነ ብቻ ነዉ። እንደ ነፍሴ በምሳሳላቸዉ እህቶቼ እና ወንድሞቼ አልጋ ላይ ብተኛ፣ ነዉሩ ምን ላይ እንደሆነ አሁንም አይገባኝም፡፡ በእርግጥ ማንም ከልክሎኝ አያዉቅም ነበር። እኔ እንዲያዉም ደስ የሚላቸዉ ነበር የሚመስለኝ።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ማጉረምረም አመጡ፡፡ አንዳንዶች እንደ ጨዋታ እያስመስሉ፣ አንዳንዶች ደግሞ የሆነች የጀመሯት ነገር አልሳካ ያለቻቸዉ
እንደሆነ፣ ቀድመዉ የሚያላክኩት ወደኔ ሆኗል። የእነሱ ማለት የእኔም ነዉ እያልሁ ባደረስኝ ክፍል ሁሉ ስንት እና ስንት ልብስ እና ጌጣጌጥ ያኖርሁ ቢሆንም፣ አሁን ግን እሱን ጭምር ብላሽ አስቀርተዉብኛል።
“ምነዉ ሻንጣህን ሸካከፍህ፣ ንብረት እያሸሽህ ነዉ'ንዴ ወንድሜ?” አልሁት፣ በእኔ ቤት ቀልጄ ሞቼ ልቤ ዉልቅ እያለ፡፡ ይኼም አልበቃ ብሎኝ እኮ ጥርሴን ለፈገግታ አግጥጨዋለሁ ሳላስበዉ ነፍሰ ጡር እንደሆንሁ፣ ሕይወቴ ምስቅልቅሉ እንደወጣ፣ የእሱ የወንድምነት ምክር
እንደሚያስፈልገኝ ልነግረዉ በልቤ ወስኛለሁ። በመሆኑም የመጨረሻ
ሻንጣዉን አንጠልጥሎ ወደ በሩ ሲጣደፍ ተከተልሁት። ለካንስ ሌላ
ደልዳላ ሰዉ ደግሞ ከበሩ በእዳሪ ሆኖ እየተቀበለ ወደ መኪናዉ
እያጓጓዘለት ኖሯል። ልብ ባልለዉ እንጂ፣ ከልብሶቹ ሌላም የእኔ ናቸዉ የሚላቸዉን እቃዎች ከሳሎን ሳይቀር ለቃቅሞ በመኪናዉ ቀርቅቦ አስጭኖ ጨርሷል። አልጋዉን ራሱ ከምን ጊዜዉ እንዳወጣዉ አላየሁትም።
“ምን እያደረግህ ነዉ አንተ?” አልሁት፣ ልሳቅ አልሳቅ በሚል ቃና።
“ቻዉ!” አለኝ፣ ጥያቄዬን እንዳልሰማ ሁሉ የመኪናዉን የጋቢና በር ከፍቶ እየገባ፡፡
“አንተ ጃሪም! ቆይ እንጂ ወዴት ... ምን እየሆንህ ነዉ?” አልሁት፣
ተንደርደሬ ከፊት ለፊቱ መንገዱን ዘግቼ እየቆምሁበት።
“አይበቃንም ብለሽ ነዉ?”
“ምኑ ነዉ የሚበቃን?”
“ዉሽቱ ሁላ! ለጥቅማችሁ ስትሉ ጠብ እርግፍ አላችሁ እንጂ፣ እኔ እኮ ከዚህ ቤተሰብ አይደለሁም። እናትሽም እናቴ፣ አንቺም እህቴ፣
ዘመዶችሽም ምኔም አይደላችሁም በቃ”
“ምንድነዉ የምታወራዉ?”
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
“እንዴት ነህ ጃ?” አልሁት፣ ከተንጋለልሁበት መነሳት የእረጥብ አራስ ያህል እያቃተኝ፡፡ ያቆላመጥሁት ራሱ አልመሰለኝም ማን ብዬ ነዉ ግን የጠራሁት? እንደ እህት ጃ ነዉ ወይስ እንደ ቀበሌ ጃሪም ብዬ? እንጃልኝ
ብቻ።
“ጭራሽ አልጋዬ ላይ?”
"በይ አልጋዬን ልቀቂልኝ ያለ በሚመስል ዓይኑ ጠቅ አድርጎኝ ሲቆም፣ ብድግ ብዬ ከአልጋዉ ላይ ወርጄለት ወደ ራሴ ክፍል ሄድሁ። ምን እንዳለኝ እንኳን ልብ ያልሁት በኋላ ሻንጣዎቹን ወደ ዉጪ ማመላለስ ሲጀምር ነበር።
የእመዋ ቤት ጎስቆል ያለች ብትሆንም፣ አሠራሯ ሁልጊዜም
ያስገርመኛል። ክብ አይሏት፣ አራት ማዕዘን አይሏት፣ የግንብ አይሏት፣
የጭቃ አይሏት፣ ብቻ ግን ሁሉንም ትመስላለች። በዚያ ላይ የሞቀች
ናት፡፡ እኔም፣ ምንም እንኳን ከቤተሰባችን ጋር አባታችንን እየተከተልሁ በዞርሁበት ክፍለ ሀገር የኖርሁባቸዉ ቤቶች ሁሉ የነበረኝ ትዝታ ባይለቀኝም፣ በቅጡ ነፍስ ያወቅሁባት ቤት ናትና እንደዚችኛዋ የሚሆንልኝ ቤት ግን የለም፡፡ ጠባብ ብትመስልም ለእኛ ግን ጠብባን አታዉቅም። በዚች ቤት ሁላችንም የየራሳችን ክፍል አለን፡፡ በእርግጥ በዚች ቤት ያለንን ክፍል መጀመሪያ የያዝነዉ እንደ ዋዛ፣ በሽሚያ ነበር።
ትዝ ይለኛል፤ መጨረሻ ከነበርንበት ከተማ ቀይረን ወደ'ዚች ቤት ልንገባ ደጁን የረገጥነዉ ኅዳር 29፣ ሐሙስ ቀን ነበር።
“በሉ እንግዲህ” አለችን እመዋ፣ ልክ ወደ'ዚች ቤት በራፍ
ከመድረሳችን፣ ቤቷ ወዳሏት ክፍሎች እየለቀቀችን፡፡ “መቼም እንግዲህ አድገናል ብላችኋል። ለየብቻ ማደሩን ከሆነ የጓጓችሁለት ይኸዉ እንዳሻችሁ ሞክሩት ደግሞ። በሉ፤ ኮተቶቻችሁን በየክፍላችሁ አስገቡ”
“በየክፍላችሁ?” አልሁኝ እኔ፣ እንክት ብዬ፡ ያደግነዉ አንድ ሰፊ
ምንጣፍ መሀል ወለሉ ላይ አንጥፈን፣ ተቃቅፈን እየተኛን ነዉ። እየተኛን አልሁ እንጂ፣ የሌሊቱን እኩሌታ እንኳን የምናሳልፈዉ እንዲሁ እንዳዉካካን ነበር። ለወጉ መብራቱን እናጠፋፋና፣ ልብሳችንንም ለዋዉጠን በዚያ ሀገር በሚያህለዉ ምንጣፍ ላይ በጎን በጎናችን እንሆናለን። ከዚያ ተረቡ፣ አሽሙሩ፣ ቀልዱ፣ ተረቱ፣ እንቆቅልሹ፣ እንካ ስላንቲያዉ፣ መሳሳቁ፣ መላፋቱ ይመጣል። ያልሆነዉ ምን አለ? ዛሬ ተረኛ እኔ የሆንሁ እንደሆነ፤ አንዴ በቃል ተረብ፣ ቀጥለዉ በልፊያ፣
ቀጥለዉ ቁንጥጫ ሁሉም ይረባረቡብኛል። ታዲያ ያሉኝን ቢሉኝስ ወንድሞቼንና እህቶቼን ላኮርፋቸዉ? ኧረ በጭራሽ! እንዲያዉም አሁን አሁን ሳስበዉ፣ ተረባቸዉን እና ልፊያቸዉን ሁሉ ለመከላከል አደርገዉ
የነበረዉ መፍጨርጨር ሁሉ ሳይጠቅመኝ አልቀረም። ቢያንስ ቢያንስ ንግግሬ እና ጡንቻዬን አዳብሮልኛል። በዚያም ላይ እኮ እኔ በተራዬ የቀመስኋትን ሁሉ፣ እነሱም በየተራቸዉ ይቀምሷታል።
“በየክፍላችሁ? አረ ምን ዓይነት፣ የማን ሐሳብ ነዉ ግን ይኼ?” አልኋት እመዋን፣ ሆዴን ባር ባር እያለዉ።
“ቀርፋፎ! ይልቅ ተመርጦ ሳያልቅብሽ ክፍልሽን አትመርጪም?” አለችኝ
ኣንደኛዋ እህቴ፣ የራሷን ክፍል መርጣ ማንም እንዳይነካባት ቆልፋዉ ወደኔ እየተመለሰች።
ብቻዬን እንደ ቀረሁ አስተዋልሁ። ሁሉም ይሻለኛል የሚለዉን ክፍል
ተሻምቷል። እኔ እዚህ በትዝታ ወዲያ ወዲህ ስል፣ እንደ ዱሯችን
እንድንተኛ እንድመካከራቸዉ እንኳን የሚሆን አፍታ ሳይታገሱኝ መስኮት ያላቸዉን እና በመስኮት በኩል አሻግሮ ለማየት የሚያመቹትን ክፍሎች ሁሉ ተሽቀዳድመዉባቸዋል፡፡ በተለይ የጃሪም ደግሞ ልዩ ነዉ፡፡ ከመስኮት በተጨማሪ፣ በዚህ በኩል ወደ ዋናዉ ሳሎን የሚያስገባ እና በዚያ በኩል
ደግሞ ወደ ዉጪ የሚያስወጣ በር ያለዉን፣ ሰፊዉን ክፍል ነዉ ተሻምቶ የያዘዉ።
ምንም አማራጭ ስላጣሁ እነሱ ያያዟቸዉን ክፍሎች እየተዟዟርሁ
ስመለከት ቆይቼ፣ ያሉኝን ኮተቶች ሁሉ እየጎተትሁ ወደ ተተወችልኝ
ምራጫ ክፍል አስገባሁባት። ያም ሆኖ ግን እምብዛም አልከፋኝም ነበር። ምክንያቱም፣ ዞሮ ዞሮ ወንድሞቼ እና እህቶቼ ናቸዉ። ለስሙ ክፍሉ የየራሳቸዉ ቢባልም፣ መቼም በፈለግሁት ክፍል እንዳላድር የሚከለክለኝ
አይኖርም፡፡ እነሱም ለጊዜዉ መስሏቸዉ ነዉ እንጂ፣ በዚህ ምርጫቸዉ እንደሚጸጸቱ ገምቻለሁ። ለአንድ ወይም ላኹለት አዳር ለየብቻ ከሞከሩት
በኋላ ወደ መሀል ወለል መጥተዉ እንደ ዱሯችን አብረን እንተኛ
ማለታቸዉ አይቀርም፡፡ ይኼን ይኼን ሳስብ ትንሽ ቀለል ብሎኝ የነበረ ቢሆንም፣ ዉሎ አድሮ የሆነዉ ግን እንደ ጠበቅሁት አይደለም።
ይኼዉ በእንደዚያ ያለ ሁኔታ የያዝነዉ ክፍል አሁንም ድረስ ድርሻችን እንደሆነ አለ። የኋላ በኋላም ቢሆን፣ ጨክነን የየራሳችንን ቤት ስላልሠራን፣ በዚሁ ቤት ያለዉ ክፍላችን እንደ ተጠበቀ አለ። በርግጥ ገሚሶቹ ወንድሞቼ ወጣ ገባ እያሉ የኪራይ ቤት ኑሮ የሞካከሩ አሉ።
የሆነዉ ሆኖ፣ አሁን የየራሳችንን ሥራ ከያዝን እና የየራሳችን ኃላፊዎች ሆነናል ካልን በኋላም የምንኖረዉ እዚሁ ግቢ ነዉ። ቀን የየራሳችንን ሥራ ስንከዉን ዉለን አዳራችንም በየራሳችን ክፍል፣ በየራሳችን አልጋ ሆኗል። በእርግጥ እኔ ከሌሎቹ በተለየ መልኩ፣ ክፍት ባገኘሁት አልጋ
ሁሉ ነዉ የምተኛዉ። እንዲያዉም ብዙ ጊዜ ክፍት ሳይሆንም ጭምር፣ ጠጋ በሉልኝ ብዬ አብሬ የምተኛበት ጊዜ አለኝ። እያየኋቸዉም እንኳን
ደርሰዉ ንፍቅ በሚሉኝ ሰዓት ስስቴን የማስታግሰዉ፣ እነሱን እቅፍ አድርጌ ትንፋሻቸዉን ስምግ ያደርሁ እንደሆነ ብቻ ነዉ። እንደ ነፍሴ በምሳሳላቸዉ እህቶቼ እና ወንድሞቼ አልጋ ላይ ብተኛ፣ ነዉሩ ምን ላይ እንደሆነ አሁንም አይገባኝም፡፡ በእርግጥ ማንም ከልክሎኝ አያዉቅም ነበር። እኔ እንዲያዉም ደስ የሚላቸዉ ነበር የሚመስለኝ።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ማጉረምረም አመጡ፡፡ አንዳንዶች እንደ ጨዋታ እያስመስሉ፣ አንዳንዶች ደግሞ የሆነች የጀመሯት ነገር አልሳካ ያለቻቸዉ
እንደሆነ፣ ቀድመዉ የሚያላክኩት ወደኔ ሆኗል። የእነሱ ማለት የእኔም ነዉ እያልሁ ባደረስኝ ክፍል ሁሉ ስንት እና ስንት ልብስ እና ጌጣጌጥ ያኖርሁ ቢሆንም፣ አሁን ግን እሱን ጭምር ብላሽ አስቀርተዉብኛል።
“ምነዉ ሻንጣህን ሸካከፍህ፣ ንብረት እያሸሽህ ነዉ'ንዴ ወንድሜ?” አልሁት፣ በእኔ ቤት ቀልጄ ሞቼ ልቤ ዉልቅ እያለ፡፡ ይኼም አልበቃ ብሎኝ እኮ ጥርሴን ለፈገግታ አግጥጨዋለሁ ሳላስበዉ ነፍሰ ጡር እንደሆንሁ፣ ሕይወቴ ምስቅልቅሉ እንደወጣ፣ የእሱ የወንድምነት ምክር
እንደሚያስፈልገኝ ልነግረዉ በልቤ ወስኛለሁ። በመሆኑም የመጨረሻ
ሻንጣዉን አንጠልጥሎ ወደ በሩ ሲጣደፍ ተከተልሁት። ለካንስ ሌላ
ደልዳላ ሰዉ ደግሞ ከበሩ በእዳሪ ሆኖ እየተቀበለ ወደ መኪናዉ
እያጓጓዘለት ኖሯል። ልብ ባልለዉ እንጂ፣ ከልብሶቹ ሌላም የእኔ ናቸዉ የሚላቸዉን እቃዎች ከሳሎን ሳይቀር ለቃቅሞ በመኪናዉ ቀርቅቦ አስጭኖ ጨርሷል። አልጋዉን ራሱ ከምን ጊዜዉ እንዳወጣዉ አላየሁትም።
“ምን እያደረግህ ነዉ አንተ?” አልሁት፣ ልሳቅ አልሳቅ በሚል ቃና።
“ቻዉ!” አለኝ፣ ጥያቄዬን እንዳልሰማ ሁሉ የመኪናዉን የጋቢና በር ከፍቶ እየገባ፡፡
“አንተ ጃሪም! ቆይ እንጂ ወዴት ... ምን እየሆንህ ነዉ?” አልሁት፣
ተንደርደሬ ከፊት ለፊቱ መንገዱን ዘግቼ እየቆምሁበት።
“አይበቃንም ብለሽ ነዉ?”
“ምኑ ነዉ የሚበቃን?”
“ዉሽቱ ሁላ! ለጥቅማችሁ ስትሉ ጠብ እርግፍ አላችሁ እንጂ፣ እኔ እኮ ከዚህ ቤተሰብ አይደለሁም። እናትሽም እናቴ፣ አንቺም እህቴ፣
ዘመዶችሽም ምኔም አይደላችሁም በቃ”
“ምንድነዉ የምታወራዉ?”
#ሳቤላ
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
... ሚሲዝ ሔር እሳቷን አስነድዳ ወንበሯን አስጠጋችና አግሮቿን ከምድጃውጠርዝ ዘርግታ ስትሞቅ ባርባራ ግን አሁንም ሐሳቧ እንደ ተበተነ ልቧ እንደ ተሰቀለ ነበር " በመጨረሻ ከልብስ መስቀያው አንድ የሱፍ ያንገት ልብስ አውርዳ ከትከሻዋ ደረበችና ወጥታ ሔደች የግቢውን የአግር መንገድ ይዛ በቀጥታ ሔዳ ከብረቱ በር ስትደርስ ቆም ብላ ወደ ሕዝቡ ጐዳና ትመለከት ጀመር " ነገር ግን ያ ጐዳና በዚያ ሰዓትና ቦታ፡እንደ ሌላው ጊዜ ሕዝብ አልነበረበትም!ጸጥ ብሎ ነበር
የግንቦት መጀመሪያ ላይ ስለ ነበረ በጣም ቀዝቃዛ ይሁን እንጂ ጸጥ ያለ አስደሳች የጨረቃ ምሽት ነበር።
“ ከቶ መቸ....ይመለስ ይሆን ? አለች ባርባራ ከበሩ ተደግፋ ብቻዋን ስታወራ (እሱ የሌለበት ሕይወት ምን ሕይወት ነው ! አሁን በነዚህ ጥቂት ቀኖች ውስጥ ምን ያህል ተጨነቅሁ ? እንደ ኮርኒሊያ አባባል ከሆነ ለአንድ ቀን ብቻ ነበር የሔደው " ለመሆኑ ወደዚያ ምን ጉዳይ ቢኖረው ነው የሔደው ?
የእግር ዳና ከጆሮዋ ጥልቅ አለ በዚያ ሰዓትና ቦታ ማንም መንገደኛ እንዲያያት አልፈለገችም ስለዚህ ወደ ኋላዋ ምልስ ብላ ከዛፎቹ ጥላ ሥር ተከለለች "
የኮቴው ድምፅ እየቀረበ ሲመጣ ከዚያ በፊት የምታውቀው አረጋጥ መሆኑን ለየችው ስሜቷ ተለዋወጠ ዐይኖቿ በሩ ጉንጮቿ ፍም መሰሉየደም ሥሮቿ
ከደስታዋ ብዛት ነዘሩ እንዳትታይ ተጠንቅቃ በበሩ ቁልቁል ስትመለከት አንድ ረጅም ሰውዬ ከወደ ዌስት ሊን ሲመጣ አየች " የኋሊት ሽሽት አለች እውነተኛ
ፍቅር ድንጉጥ ነው " የባርባራ ሔር ሌሎች ተስጥዎች ያፈቀደውን ቢባሉም ፍቅሯ
ግን ልባዊና ጥልቅ ነበር ከበሩ ሲደርስ ይገባል ብላ ስትጠብቀው ዐልፎ የሚሔድ ይመስል ወደ በሩ እንኳን ዞር ብሎ አላየም " ባርባራ ሐሞቷ ፍስስ አለ እንደገና
ወደበሩ ተጠግታ ፍዝዝ ብላ በጕጒት መመልከት ጀመረች።
በርግጥም ስለሷ ምንም ሳያስብ ወደሷ ዘወር ሳይል ዐልፎ ወደፊቱ ሲገሠግሥ ስታይ በዚያች ቅጽበት በመጣበት የስሜት ግፊት «አርኪባልድ» ብላ ጠራችው።
« ባርባራ ... ሌቦችና ሕገ ወጥ አዳኞች እንዳይቡ እየጠበቅሽ ነው እንዴ ? እንደምነሽ ? » አለ
«እንደምነህ?» አለችው በአንድ በኩል በሩን ከፍታ ይዛ ስታስገባው በሌላ በኩል ደግሞ ከሱ ጋር እጅ ለእጅ ስትጨባበጥ እየገነፈለ ያስጨነቃትን ስሜት ለማመቅ ከራሷ ጋር እየተናነቀች » « መቸ መጣህ ? » አለችው " « አሁን በሁለት ሰዓቱ ባቡር መድረሴ ነው " ላንዳፍታ ከቢሮ ገባሁና አሁን ደግሞ ሚስተር ቦሻምን ለአንድ ጉዳይ ስለምፈልገው ወደሱ እየሔድኩ ነው " በይ ስመለስ እገባ ይሆናል " አሁን ግን ቸኩያለሁ አመሰግናለሁ " »
አዬ አባባና ሚስተር ስፒርነርም ከዚያ ስለአሉ ' ከነሱ ጋር ቆይተው ወደዚህ ለመምጣት በጣም ይመሽብሃል “ እነሱ እንዶሆኑ ከአምስትና ከስድስት ሰዓት በፊት
አይላቀቁም " »
« እነሱ እዚያ ካሉስ ከሚስተር ቦሻም ጋር ያለኝ ጉዳይ የግል ስለሆነ ለነገ ማስተላለፌ ነው » የያዘችውን በር ተቀብሎ ዘጋውና ክንዷን በክንዱ ይዞ ወደቤት
አመሩ እሱ ይህን ያህል የሚቀርባትና የሚይዛት በምንም ስሜታዊ ግፊት ሳይሆን
ከልማዳዊው ትሕትና በመነሣት ማክበሩ ነበር ባርባራ ሔር ግን ክንዷን ከክንዱ አቆላልፋ ጐን ለጐን ሆነው እያነጋገራት ሲሔዱ ኤደን ገነት ውስጥ እንደ ገባች ሆና ሀይሰማት ነበር "
«ታዲያስ ባርባራ ... ... ... በነዚህ ጥቂት ቀኖች ውስጥ እንዴት ሰነበታችሁ?
« መሔድህን ሳንሰማ ምን ነገር ነው ድንገት ብድግ አድርጎ የወሰደህ ? »
« ተናርሺው እኮ ባርባራ!...... ... አንድ ያልታሰበ የሥራ ጉዳይ ተፈጠረ ሔድኩ »
« ኮርኒሊያ ግን ለአንድ ቀን ብቻ መሔድን ነበር የነገረችኝ»
« አለችሽ እንዴ ? ለንደን ከደረስኰ በኋላ ብዙ የምፈጽማቸው ነገሮች
ገጠሙኝና ቆየሁ " ሚስዝ ሔር እንደምን ስነበቱ ? »
« እሷ ያው ናት እኔስ ግማሾቹ በሽታዎቿን በሐሳቧ የፈጠረቻቸው ይመስሉኛል " አሁን በግድ እየተነሣች ብትንቀሳቀስ ይሻላት ነበር " ምንድነው ከሱ ጠቅለህ የያዝከው ? »
« ሚሲዝ ሔርን እንጂ አንቺን ስለማይመለከት አትጠይቂኝ " »
« ለእማማ ያመጣህላት ነገር ነው ማለት ነው አርኪባልድ ? »
« አዎን ' አንድ ገጠሬ ለንደን ከደረሰ ለወዳጆቹ ምን ስጦታ ይዞላቸው እንደሚመለስ ነው የሚያስበው " የጥንት ወጉ ይኸ ነበር " »
« እና አሁን በርግጥ ለእማማ ያመጣህላት ነው? »
« ምነው እየነገርኩሽ …. ባርባራ ላንቺም እንድ ነገር አምጥቼልሻለሁ»
« ምን አመጣልኝ ? » አለችው ፊቷ እንዳመሉ እየቀላ ቀልዱን ይሁን እውነቱን እስክታውቅ ድረስ ሐሳቧ በጕጒት እየተንጓለለ "
« ቀስ በይ እኮ አትቸኩይ !ምን እንደሆነማ ልታይው አይደል » አላትና የያዘውን ጥቅል አጠገባቸው ከነበረ ከአንድ ያትክልት ቦታ ወንበር ላይ አስቀመጠና ኪሶቹን ሁሉ ቢዳብስ አጣ "
« ባርባራ ... ካንዱ ሳልጥለው ቀረሁ ብለሽ ? » አለና እንደገና
ኪሶቹን ሁሉ ፈለገ አራገፈ " በመጨረሻ አንድ ያልታሰበ ኪስ ውስጥ አንድ ነገር ጐረበጠው
«አይ እዚህ አለ መሰለኝ ። ግን እዚህ ምን አመጣው ? » አለና አንዲት ትንሽ ሣጥን አውጥቶ በመክፈት ከውስጧ አንድ ረጂም የወርቅ ሐብል አንሥቶ ባንገቷ አጠለቀላት ከሐብሉ ጋር ባንድ በኰል ጌጥ በሌላ በኩል የጥቃቅን መታስቢያዎች ለመያዣ የሚያገለግል ትንሽ የወርቅ ሙዳይ ተያይዞ ነበር ።
ልቧ በኃይል ሲመታ የፊቷ ቅላት እንደ ልቧ አመታት ቦግ እልም ይል ጀመር አንዲት የምስጋና ቃል እንኳን መተንፈስ አልቻለችም " ሚስተር ካርላይል ያኖረውን ጥቅል አንሥቶ ወደ ሚስዝ ሔር ዘንድ ገባ። ሻማ ባይያያዝም በክፍሉ ሲነድ የነበረው እሳት ቦግ ብሎ በርቶ ነበርዠ።
« መቸም እንዳይሥቁብኝ» አለ ያመጣውን ጥቅል እየፈታ እስከዚህም የረባ ስጦታ አይደለም ብቻ ብዙ ጊዜ ሲመኙት እሰማ ስለ ነበር ከአንድ ሱቅ መስኮት ላይ አይቼ በአየር የሚሞላ መከዳ ነው ያመጣሁለዎ » ብሎ ሰጣት » በመጋደምና በመቀመጥ ሰውነቷ ያለቀው ሚሲዝ ሔር እንደዚያ ያለ ዕቃ ለንደን እንደሚገኝ
ከመስማቷ በቀር ከነማየቷም አታስታውሰውም እንደ ጓጓች ተቀበለችውና በምስጋና ትክ ብላ ተመለከተችው "
« አንዴት ብዬ ነው የማመሰግንህ? » አለችው የደስታ ዕንባ እየተናነቃት
« አስበህ ስለ አመጣሀልኝ አመሰግንሃለሁ»
« አሁን ለባርባራ ስነግራት ነበር " ወደ ለንደን ከሔድን ለወዳጆቻችን ምን ይዘን መመለስ እንደሚገባን ማሰብ እንጀምራለን ባርባራንስ እንዴት እንዳሳመርኳት አዩዋት አይደል ? » አላት ሚስተር ካርላይል "
ባርባራ ሐብሉን ካንገቷ ቶሎ አወለቀችና ከናቷ ፊት አኖረችው "
«አቤት እንዴት ያምራል ልጄ!መቸም ለዚህ ያወጣኸው ገንዘብ ልክ አይኖረውም»
« ኧረ እሱስ ጥቂት ነው ፍሬም የለው» አለ ሚስተር ካርላይል እንደ መሳቅ ብሎ " « እንዴት እንደገዛሁት ላጫውታችሁ የጅ ስዓቴ ማሰሪያ እየተፊታ አስ
ቸገረኝና ወደ አንድ ወርቅ ሠሪ ዘንድ ጎራ ብዬ ነበር በዚያ ብዙ አይነት ሐብሎች ተሰቅለው ሳይ ኮርነሊያና ባርባራ አብረውኝወደ ሊንቦራ ሔደው በነበረ ጊዜ ባርባራ የጠፋባትን ሐብል አስታወሱኝ " ስለዚህ ለባርባራ አንገት የሚስማማውን መርጬ
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
... ሚሲዝ ሔር እሳቷን አስነድዳ ወንበሯን አስጠጋችና አግሮቿን ከምድጃውጠርዝ ዘርግታ ስትሞቅ ባርባራ ግን አሁንም ሐሳቧ እንደ ተበተነ ልቧ እንደ ተሰቀለ ነበር " በመጨረሻ ከልብስ መስቀያው አንድ የሱፍ ያንገት ልብስ አውርዳ ከትከሻዋ ደረበችና ወጥታ ሔደች የግቢውን የአግር መንገድ ይዛ በቀጥታ ሔዳ ከብረቱ በር ስትደርስ ቆም ብላ ወደ ሕዝቡ ጐዳና ትመለከት ጀመር " ነገር ግን ያ ጐዳና በዚያ ሰዓትና ቦታ፡እንደ ሌላው ጊዜ ሕዝብ አልነበረበትም!ጸጥ ብሎ ነበር
የግንቦት መጀመሪያ ላይ ስለ ነበረ በጣም ቀዝቃዛ ይሁን እንጂ ጸጥ ያለ አስደሳች የጨረቃ ምሽት ነበር።
“ ከቶ መቸ....ይመለስ ይሆን ? አለች ባርባራ ከበሩ ተደግፋ ብቻዋን ስታወራ (እሱ የሌለበት ሕይወት ምን ሕይወት ነው ! አሁን በነዚህ ጥቂት ቀኖች ውስጥ ምን ያህል ተጨነቅሁ ? እንደ ኮርኒሊያ አባባል ከሆነ ለአንድ ቀን ብቻ ነበር የሔደው " ለመሆኑ ወደዚያ ምን ጉዳይ ቢኖረው ነው የሔደው ?
የእግር ዳና ከጆሮዋ ጥልቅ አለ በዚያ ሰዓትና ቦታ ማንም መንገደኛ እንዲያያት አልፈለገችም ስለዚህ ወደ ኋላዋ ምልስ ብላ ከዛፎቹ ጥላ ሥር ተከለለች "
የኮቴው ድምፅ እየቀረበ ሲመጣ ከዚያ በፊት የምታውቀው አረጋጥ መሆኑን ለየችው ስሜቷ ተለዋወጠ ዐይኖቿ በሩ ጉንጮቿ ፍም መሰሉየደም ሥሮቿ
ከደስታዋ ብዛት ነዘሩ እንዳትታይ ተጠንቅቃ በበሩ ቁልቁል ስትመለከት አንድ ረጅም ሰውዬ ከወደ ዌስት ሊን ሲመጣ አየች " የኋሊት ሽሽት አለች እውነተኛ
ፍቅር ድንጉጥ ነው " የባርባራ ሔር ሌሎች ተስጥዎች ያፈቀደውን ቢባሉም ፍቅሯ
ግን ልባዊና ጥልቅ ነበር ከበሩ ሲደርስ ይገባል ብላ ስትጠብቀው ዐልፎ የሚሔድ ይመስል ወደ በሩ እንኳን ዞር ብሎ አላየም " ባርባራ ሐሞቷ ፍስስ አለ እንደገና
ወደበሩ ተጠግታ ፍዝዝ ብላ በጕጒት መመልከት ጀመረች።
በርግጥም ስለሷ ምንም ሳያስብ ወደሷ ዘወር ሳይል ዐልፎ ወደፊቱ ሲገሠግሥ ስታይ በዚያች ቅጽበት በመጣበት የስሜት ግፊት «አርኪባልድ» ብላ ጠራችው።
« ባርባራ ... ሌቦችና ሕገ ወጥ አዳኞች እንዳይቡ እየጠበቅሽ ነው እንዴ ? እንደምነሽ ? » አለ
«እንደምነህ?» አለችው በአንድ በኩል በሩን ከፍታ ይዛ ስታስገባው በሌላ በኩል ደግሞ ከሱ ጋር እጅ ለእጅ ስትጨባበጥ እየገነፈለ ያስጨነቃትን ስሜት ለማመቅ ከራሷ ጋር እየተናነቀች » « መቸ መጣህ ? » አለችው " « አሁን በሁለት ሰዓቱ ባቡር መድረሴ ነው " ላንዳፍታ ከቢሮ ገባሁና አሁን ደግሞ ሚስተር ቦሻምን ለአንድ ጉዳይ ስለምፈልገው ወደሱ እየሔድኩ ነው " በይ ስመለስ እገባ ይሆናል " አሁን ግን ቸኩያለሁ አመሰግናለሁ " »
አዬ አባባና ሚስተር ስፒርነርም ከዚያ ስለአሉ ' ከነሱ ጋር ቆይተው ወደዚህ ለመምጣት በጣም ይመሽብሃል “ እነሱ እንዶሆኑ ከአምስትና ከስድስት ሰዓት በፊት
አይላቀቁም " »
« እነሱ እዚያ ካሉስ ከሚስተር ቦሻም ጋር ያለኝ ጉዳይ የግል ስለሆነ ለነገ ማስተላለፌ ነው » የያዘችውን በር ተቀብሎ ዘጋውና ክንዷን በክንዱ ይዞ ወደቤት
አመሩ እሱ ይህን ያህል የሚቀርባትና የሚይዛት በምንም ስሜታዊ ግፊት ሳይሆን
ከልማዳዊው ትሕትና በመነሣት ማክበሩ ነበር ባርባራ ሔር ግን ክንዷን ከክንዱ አቆላልፋ ጐን ለጐን ሆነው እያነጋገራት ሲሔዱ ኤደን ገነት ውስጥ እንደ ገባች ሆና ሀይሰማት ነበር "
«ታዲያስ ባርባራ ... ... ... በነዚህ ጥቂት ቀኖች ውስጥ እንዴት ሰነበታችሁ?
« መሔድህን ሳንሰማ ምን ነገር ነው ድንገት ብድግ አድርጎ የወሰደህ ? »
« ተናርሺው እኮ ባርባራ!...... ... አንድ ያልታሰበ የሥራ ጉዳይ ተፈጠረ ሔድኩ »
« ኮርኒሊያ ግን ለአንድ ቀን ብቻ መሔድን ነበር የነገረችኝ»
« አለችሽ እንዴ ? ለንደን ከደረስኰ በኋላ ብዙ የምፈጽማቸው ነገሮች
ገጠሙኝና ቆየሁ " ሚስዝ ሔር እንደምን ስነበቱ ? »
« እሷ ያው ናት እኔስ ግማሾቹ በሽታዎቿን በሐሳቧ የፈጠረቻቸው ይመስሉኛል " አሁን በግድ እየተነሣች ብትንቀሳቀስ ይሻላት ነበር " ምንድነው ከሱ ጠቅለህ የያዝከው ? »
« ሚሲዝ ሔርን እንጂ አንቺን ስለማይመለከት አትጠይቂኝ " »
« ለእማማ ያመጣህላት ነገር ነው ማለት ነው አርኪባልድ ? »
« አዎን ' አንድ ገጠሬ ለንደን ከደረሰ ለወዳጆቹ ምን ስጦታ ይዞላቸው እንደሚመለስ ነው የሚያስበው " የጥንት ወጉ ይኸ ነበር " »
« እና አሁን በርግጥ ለእማማ ያመጣህላት ነው? »
« ምነው እየነገርኩሽ …. ባርባራ ላንቺም እንድ ነገር አምጥቼልሻለሁ»
« ምን አመጣልኝ ? » አለችው ፊቷ እንዳመሉ እየቀላ ቀልዱን ይሁን እውነቱን እስክታውቅ ድረስ ሐሳቧ በጕጒት እየተንጓለለ "
« ቀስ በይ እኮ አትቸኩይ !ምን እንደሆነማ ልታይው አይደል » አላትና የያዘውን ጥቅል አጠገባቸው ከነበረ ከአንድ ያትክልት ቦታ ወንበር ላይ አስቀመጠና ኪሶቹን ሁሉ ቢዳብስ አጣ "
« ባርባራ ... ካንዱ ሳልጥለው ቀረሁ ብለሽ ? » አለና እንደገና
ኪሶቹን ሁሉ ፈለገ አራገፈ " በመጨረሻ አንድ ያልታሰበ ኪስ ውስጥ አንድ ነገር ጐረበጠው
«አይ እዚህ አለ መሰለኝ ። ግን እዚህ ምን አመጣው ? » አለና አንዲት ትንሽ ሣጥን አውጥቶ በመክፈት ከውስጧ አንድ ረጂም የወርቅ ሐብል አንሥቶ ባንገቷ አጠለቀላት ከሐብሉ ጋር ባንድ በኰል ጌጥ በሌላ በኩል የጥቃቅን መታስቢያዎች ለመያዣ የሚያገለግል ትንሽ የወርቅ ሙዳይ ተያይዞ ነበር ።
ልቧ በኃይል ሲመታ የፊቷ ቅላት እንደ ልቧ አመታት ቦግ እልም ይል ጀመር አንዲት የምስጋና ቃል እንኳን መተንፈስ አልቻለችም " ሚስተር ካርላይል ያኖረውን ጥቅል አንሥቶ ወደ ሚስዝ ሔር ዘንድ ገባ። ሻማ ባይያያዝም በክፍሉ ሲነድ የነበረው እሳት ቦግ ብሎ በርቶ ነበርዠ።
« መቸም እንዳይሥቁብኝ» አለ ያመጣውን ጥቅል እየፈታ እስከዚህም የረባ ስጦታ አይደለም ብቻ ብዙ ጊዜ ሲመኙት እሰማ ስለ ነበር ከአንድ ሱቅ መስኮት ላይ አይቼ በአየር የሚሞላ መከዳ ነው ያመጣሁለዎ » ብሎ ሰጣት » በመጋደምና በመቀመጥ ሰውነቷ ያለቀው ሚሲዝ ሔር እንደዚያ ያለ ዕቃ ለንደን እንደሚገኝ
ከመስማቷ በቀር ከነማየቷም አታስታውሰውም እንደ ጓጓች ተቀበለችውና በምስጋና ትክ ብላ ተመለከተችው "
« አንዴት ብዬ ነው የማመሰግንህ? » አለችው የደስታ ዕንባ እየተናነቃት
« አስበህ ስለ አመጣሀልኝ አመሰግንሃለሁ»
« አሁን ለባርባራ ስነግራት ነበር " ወደ ለንደን ከሔድን ለወዳጆቻችን ምን ይዘን መመለስ እንደሚገባን ማሰብ እንጀምራለን ባርባራንስ እንዴት እንዳሳመርኳት አዩዋት አይደል ? » አላት ሚስተር ካርላይል "
ባርባራ ሐብሉን ካንገቷ ቶሎ አወለቀችና ከናቷ ፊት አኖረችው "
«አቤት እንዴት ያምራል ልጄ!መቸም ለዚህ ያወጣኸው ገንዘብ ልክ አይኖረውም»
« ኧረ እሱስ ጥቂት ነው ፍሬም የለው» አለ ሚስተር ካርላይል እንደ መሳቅ ብሎ " « እንዴት እንደገዛሁት ላጫውታችሁ የጅ ስዓቴ ማሰሪያ እየተፊታ አስ
ቸገረኝና ወደ አንድ ወርቅ ሠሪ ዘንድ ጎራ ብዬ ነበር በዚያ ብዙ አይነት ሐብሎች ተሰቅለው ሳይ ኮርነሊያና ባርባራ አብረውኝወደ ሊንቦራ ሔደው በነበረ ጊዜ ባርባራ የጠፋባትን ሐብል አስታወሱኝ " ስለዚህ ለባርባራ አንገት የሚስማማውን መርጬ
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
...ሳሎን ሶፋ ላይ እንድንቀመጥ አደረገች። እናቴ ወፍራሙን ፖስታ ሳትከፍተው ገና ማልቀስ ጀመረች ከዚያ በዝግታ የደብዳቤ መክፈቻ አመጣችና በሚንቀጠቀጡ እጆቿ ሦስት ወረቀቶችን ከፖስታ ውስጥ አውጥታ ደጋግማ አነበበቻቸው: እያነበበች እያለ እምባዋ የተቀባችውን ሜካፕ እያበለሻሸ ቀስ እያለ በጉንጮቿ ይወርድ ነበር።
እያየኋት ለስላሳና ማራኪ ገፅታዋ ወዲያው ወደሚያስፈራ ኮስታራነት
እየተቀየረ አፈጠጠችብን፡ ያኔም ቀዝቃዛ ብርድ ታች አከርካሪዬ ድረስ ደርሶ አንቀጠቀጠኝ ከዚያ ልክ ደብዳቤው ላይ ለተፃፈ የሆነ ጥያቄ መልስ የምትሰጥ ይመስል በሚንቀጠቀጡ እጆቿ ወደያዘቻቸው ወረቀቶች እንደገና
ደግሞ ወደ መስኮቱ ተመለከተች
እናታችን እንግዳ የሆነ ፀባይ እያሳየችን በመሆኑ ስለተደናገርን ባልተለመደ ሁኔታ ዝም አልን፡ የእናታችንን ምላስ የቆለፈና አይኖቿን ያደነደነው ባለሶስት ገፅ ደብዳቤ ሳይጨመር እንኳን አባት የሌለበት ቤታችን በበቂ ሁኔታ
አስፈራርቶን ነበር ለምን ይሆን እንደዚህ እንግዳ በሆነ አይን የምትመለከተን?
በመጨረሻ ጉሮሮዋን አፀዳችና በተለመደው ለስላሳና ሞቃት ድምፅ ሳይሆን የእሷ በማይመስል ቀዝቃዛ ድምፅ መናገር ጀመረች: “አያታችሁ በመጨረሻ
ለደብዳቤዬ መልስ ፅፋልኛለች: የፃፍኩላት እነዚያ ሁሉ ደብዳቤዎች ላይ...በቃ ተስማምታለች: ሄደን ከእሷ ጋር እንድንኖር ተስማምታለች” አለች።
መልካሙን ዜና ለመስማት ስንጠብቀው የነበረ በመሆኑ ልንደሰት ይገባን ነበር ግን አልተደሰትንም: እናታችን በድጋሚ ወደዚያ ዝምታዋ ተመለሰችና
እዚያው እንደተቀመጠች እኛ ላይ ማፍጠጥ ቀጠለች ምን ሆና ነው? የልብስ ማስጫ ገመድ ላይ የተቀመጡ ወፎች የምንመስል አራት እንግዳ ፍጥረታት
አይደለንም፧ የእሷ ልጆች እንደሆንን አታውቅም?
“ክሪስቶፈር፣ ካቲ፣ አስራ አራትና አስራ ሁለት ዓመት ዕድሜ ላይ ስለሆናችሁ የምለውን ለመረዳት፣ ለመተባበርና እናታችሁን ካለችበት ተስፋ መቁረጥ ለማውጣት በቂ እድሜ ላይ ናችሁ።” መናገሯን ቆም አድርጋ ጣቷን ጉሮሮዋ
ላይ አድረገችና በጭንቀት በከባዱ ተነፈሰች: ለማልቀስ የደረሰች ትመስላለች
ባል የሌላት ምስኪኗ እናቴ በጣም፣ እጅግ በጣም አሳዘነችኝ፡፡
“እማዬ ሁሉም መልካም ነው? አልኳት።
“አዎ ውዴ ሁሉ መልካም” ብላ ፈገግ ለማለት ሞከረች: “ነፍሱን ይማረውና አባትሽ ረጅም እድሜ እንደሚኖርና በቂ የሆነ ንብረት እንደሚያጠራቅም ያስብ ነበር፡ ገንዘብ እንዴት መስራት እንደሚቻል ከሚያውቁ ሰዎች መሀል ስለመጣ እድሜ ቢሰጠው ኖሮ ያቀደውን በትክክል እንደሚፈፅም ምንም
ጥርጣሬ አልነበረኝም ሰዎች ሁልጊዜ መጥፎ ነገሮች ሌሎች ሰዎች ላይ እንጂ እነርሱ ላይ እንደማይደርስ አድርገው የሚያምኑበት መንገድ አላቸው
አደጋዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ አንገምትም። በወጣትነት መሞት እንዳለ አንጠብቅም አባታችሁና እኔ አብረን እንደምናረጅ እናስብ ነበር። በአንድ ቀን አብረን ከመሞታችን በፊትም የልጅ ልጆቻችንን እንደምናይ ተስፋ ነበረን::አንደኛችንም፣ ብቻችንን ቀርተን በሌላኛችን ሞት እናዝናለን ብለን አስበን አናውቅም ነበር።
እንደገና በጭንቀት ተነፈሰች “ከዛሬ ቀድመን እየኖርን እንደነበር መናገርh እፈልጋለሁ። ማለቴ ከወደፊታችን ላይ እንኳን ገንዘብ እንበደር ነበር፧ ከማግኘታችን በፊት እናጠፋ ነበር። በዚህ ጉዳይ ላይ እሱን እንዳትወቅሱት: ስለ ድህነት በደንብ ያውቅ ነበር። እኔ ግን ስለ ድህነት ብዙም ስለማላውቅ
ጥፋቱ የኔ ነበር። እንዴት ያሞላቅቀኝ እንደነበር ታውቃላችሁ። ይህንን ቤት
ስንገዛ እንኳን የሚያስፈልጉን ሶስት መኝታ ክፍሎች ያሉት ቤት ነው ብሎኝ ነበር። እኔ ግን አራት ካልሆኑ አልኩት። አራትም በቂ አይመስለኝም ነበር።
“ተመልከቱ፣ ይህ ቤት የሰላሳ ዓመት የባንክ ዕዳ አለበት። ውስጡ ያሉት የትኞቹም ዕቃዎች የእኛ አይደሉም መኪኖቹም፣ ወጥቤት ያሉት ዕቃዎችም
ሆኑ የልብስ ማጠቢያው ክፍል ውስጥ ያሉት የትኞቹም ነገሮች ሙሉ ዋጋ የተከፈለባቸው አይደሉም”
ፈራን… ደነገጥን፡ ፊቷ ቀልቶ መናገሯን ቆም አደረገችና አይኖቿ የእሷ ውበት አምሳያ የሆነውን የሚያምረውን ክፍል መቃኘት ጀመሩ የሚያምሩት ቅንድቦቿ በመጓጓት አይነት ተኮሳተሩ። “አባታችሁ ተይ እንዳይለኝ ይወደኝ
ነበር ስለሚወደኝም ያሞላቅቀኝ ነበር። እኔም እንዴት ላሳምነው እንደምችል አውቅ ነበር። በመጨረሻ እነዚያ የቅንጦት ነገሮች አስፈላጊዎቻችን እየሆኑ
መጡና እጅ ሰጠ፡ ሁለታችንም ፍላጎቶቻችንን ለማሳካት መንገዶች ነበሩን።
እንግዳ በሆነ ድምጿ የምትናገረውን ከመቀጠሏ በፊት ፊቷ ከባዶ ትዝታዎቿ በአንዱ የተዋጠ መሰለ፡ “አሁን ሁሉም ውብ ነገሮቻችን ተወስደዋል። በህግ ቋንቋ ሁኔታው መውረስ ይባላል የገዛችሁትን ነገር ዋጋውን ከፍላችሁ ለመጨረስ በቂ ገንዘብ ከሌላችሁ እነሱ እንደዚያ ነው የሚደረጉት። ለምሳሌ ያንን ሶፋ ውሰዱ፤ ከሶስት ዓመት በፊት ዋጋው ስምንት መቶ ዶላር ነበር።
ሁሉንም ከፍለን የቀረን አንድ መቶ ዶላር ብቻ ነው: ግን በቃ ይወስዱታል።
ሁሉም ነገር ላይ የከፈልነውን ጭምር እናጣለን ይሄ ደግሞ ህጋዊ አሰራር ነው። የምናጣው እቃዎቹንና ቤቱን ብቻ አይደለም መኪናቹንም ጭምር ነው። ከልብሶቻችንና ከአሻንጉሊቶቻችሁ በስተቀር ሁሉንም እናጣለን ማለት
ነው። የጋብቻ ቀለበቴን እንድወሰደው ፈቅደውልኛል። እኔ ደግሞ ስንተጫጭ የሰጠኝን የአልማዝ ቀለበት ደብቄዋለሁ ስለዚህ እነሱ ለማረጋገጥ ሲመጡ
ለአንደኛቸውም እንኳን የቃልኪዳን ቀለበት እንዳለኝ እንዳትናገሩ፡"
“እነሱ” ማን እንደሆኑ ማናችንም አልጠየቅንም መጠየቅም አልመጣልኝም። ካለፈ በኋላ ደግሞ አስፈላጊ አልነበረም።
ከክሪስቶፈር ጋር ተያየን: ለመረዳት በመፈለግ ውስጥ እንዳልሰምጥ
እየታገልኩ ነበር። እውነታው ግን በትልልቅ ሰዎች የሞትና የዕዳ አለም ውስጥ እየሰመጥኩ መሆኑ ነው። ወንድሜ እጁን ዘርግቶ ያዘኝና ባልተለመደ ወንድማዊ የማረጋገጫ ምልክት ጣቶቼን ጨመቅ አደረጋቸው።
ለማንበብ ቀላል የሆንኩ የንፋስ መጥረጊያ ነኝ አንዴ ዋና አጥቂዬ የሆነው ወንድሜ እንኳን ሊያፅናናኝ የሚፈልገው? ምን ያህል ትልቅ ሰው እንደሆንኩ
ለማረጋገጥና እነሱ ሁሉንም ነገር በመውሰዳቸው ምክንያት የተሰማኝን ፍርሀትና ደካማነት ላለማሳየት ፈገግ ለማለት ሞከርኩ። የትኛዋም ትንሽ
ልጅ በእኔ ክፍል ውስጥ እንድትኖርም ሆነ እኔ አልጋ ላይ እንድትተኛና እኔ በምወዳቸው ነገሮች እንድትጫወት፣ አሻንጉሊቶቼን እንድትነካም ሆነ
በሙዚቃ ሳጥኔ እንድትጫወት አልፈልግም እነዚያንም ይወስዱብኝ ይሆን?
እናቴ የእኔንና የወንድሜን ሁኔታ በቅርበት እየተመለከተች ነበር። ከዚያ እንደገና በቀድሞው ጣፋጭ አነጋገሯ “ልባችሁ አይሰበር፤ እኔ ስነግራችሁ
እንደሚመስለው ያህል መጥፎ አይደለም: አሁንም ገና ትንንሽ ልጆች መሆናችሁን ረስቼ ሀሳብ የለሽ በመሆኔ ይቅር በሉኝ። መጥፎውን ዜና በመጀመሪያ የነገርኳችሁ ጥሩውን ወደ ኋላ አስቀርቼ ነው አሁን ትንፋሻችሁን
ያዙ! ወላጆቼ እጅግ ሀብታሞች እንደሆኑ ስነግራችሁ አታምኑኝም: መካከለኛ ኑሮ የሚኖሩ ሀብታሞች እንዳይመስሏችሁ፤ በማይታመን አይነት በጣም በጣም ሀብታሞች ናቸው! ቨርጂኒያ ውስጥ በሚገኝ ግዙፍ ቤት ውስጥ ነው የሚኖሩት። እንደዚያ አይነት ቤት ከዚህ በፊት አይታችሁ አታውቁም
የተወለድኩትና ያደግኩት እዚያ ነው ያንን ቤ ትዚህ ጋር ስታነፃፅሩት ይሄኛው እንደ ትንሽ ጎጆ ነው
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
...ሳሎን ሶፋ ላይ እንድንቀመጥ አደረገች። እናቴ ወፍራሙን ፖስታ ሳትከፍተው ገና ማልቀስ ጀመረች ከዚያ በዝግታ የደብዳቤ መክፈቻ አመጣችና በሚንቀጠቀጡ እጆቿ ሦስት ወረቀቶችን ከፖስታ ውስጥ አውጥታ ደጋግማ አነበበቻቸው: እያነበበች እያለ እምባዋ የተቀባችውን ሜካፕ እያበለሻሸ ቀስ እያለ በጉንጮቿ ይወርድ ነበር።
እያየኋት ለስላሳና ማራኪ ገፅታዋ ወዲያው ወደሚያስፈራ ኮስታራነት
እየተቀየረ አፈጠጠችብን፡ ያኔም ቀዝቃዛ ብርድ ታች አከርካሪዬ ድረስ ደርሶ አንቀጠቀጠኝ ከዚያ ልክ ደብዳቤው ላይ ለተፃፈ የሆነ ጥያቄ መልስ የምትሰጥ ይመስል በሚንቀጠቀጡ እጆቿ ወደያዘቻቸው ወረቀቶች እንደገና
ደግሞ ወደ መስኮቱ ተመለከተች
እናታችን እንግዳ የሆነ ፀባይ እያሳየችን በመሆኑ ስለተደናገርን ባልተለመደ ሁኔታ ዝም አልን፡ የእናታችንን ምላስ የቆለፈና አይኖቿን ያደነደነው ባለሶስት ገፅ ደብዳቤ ሳይጨመር እንኳን አባት የሌለበት ቤታችን በበቂ ሁኔታ
አስፈራርቶን ነበር ለምን ይሆን እንደዚህ እንግዳ በሆነ አይን የምትመለከተን?
በመጨረሻ ጉሮሮዋን አፀዳችና በተለመደው ለስላሳና ሞቃት ድምፅ ሳይሆን የእሷ በማይመስል ቀዝቃዛ ድምፅ መናገር ጀመረች: “አያታችሁ በመጨረሻ
ለደብዳቤዬ መልስ ፅፋልኛለች: የፃፍኩላት እነዚያ ሁሉ ደብዳቤዎች ላይ...በቃ ተስማምታለች: ሄደን ከእሷ ጋር እንድንኖር ተስማምታለች” አለች።
መልካሙን ዜና ለመስማት ስንጠብቀው የነበረ በመሆኑ ልንደሰት ይገባን ነበር ግን አልተደሰትንም: እናታችን በድጋሚ ወደዚያ ዝምታዋ ተመለሰችና
እዚያው እንደተቀመጠች እኛ ላይ ማፍጠጥ ቀጠለች ምን ሆና ነው? የልብስ ማስጫ ገመድ ላይ የተቀመጡ ወፎች የምንመስል አራት እንግዳ ፍጥረታት
አይደለንም፧ የእሷ ልጆች እንደሆንን አታውቅም?
“ክሪስቶፈር፣ ካቲ፣ አስራ አራትና አስራ ሁለት ዓመት ዕድሜ ላይ ስለሆናችሁ የምለውን ለመረዳት፣ ለመተባበርና እናታችሁን ካለችበት ተስፋ መቁረጥ ለማውጣት በቂ እድሜ ላይ ናችሁ።” መናገሯን ቆም አድርጋ ጣቷን ጉሮሮዋ
ላይ አድረገችና በጭንቀት በከባዱ ተነፈሰች: ለማልቀስ የደረሰች ትመስላለች
ባል የሌላት ምስኪኗ እናቴ በጣም፣ እጅግ በጣም አሳዘነችኝ፡፡
“እማዬ ሁሉም መልካም ነው? አልኳት።
“አዎ ውዴ ሁሉ መልካም” ብላ ፈገግ ለማለት ሞከረች: “ነፍሱን ይማረውና አባትሽ ረጅም እድሜ እንደሚኖርና በቂ የሆነ ንብረት እንደሚያጠራቅም ያስብ ነበር፡ ገንዘብ እንዴት መስራት እንደሚቻል ከሚያውቁ ሰዎች መሀል ስለመጣ እድሜ ቢሰጠው ኖሮ ያቀደውን በትክክል እንደሚፈፅም ምንም
ጥርጣሬ አልነበረኝም ሰዎች ሁልጊዜ መጥፎ ነገሮች ሌሎች ሰዎች ላይ እንጂ እነርሱ ላይ እንደማይደርስ አድርገው የሚያምኑበት መንገድ አላቸው
አደጋዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ አንገምትም። በወጣትነት መሞት እንዳለ አንጠብቅም አባታችሁና እኔ አብረን እንደምናረጅ እናስብ ነበር። በአንድ ቀን አብረን ከመሞታችን በፊትም የልጅ ልጆቻችንን እንደምናይ ተስፋ ነበረን::አንደኛችንም፣ ብቻችንን ቀርተን በሌላኛችን ሞት እናዝናለን ብለን አስበን አናውቅም ነበር።
እንደገና በጭንቀት ተነፈሰች “ከዛሬ ቀድመን እየኖርን እንደነበር መናገርh እፈልጋለሁ። ማለቴ ከወደፊታችን ላይ እንኳን ገንዘብ እንበደር ነበር፧ ከማግኘታችን በፊት እናጠፋ ነበር። በዚህ ጉዳይ ላይ እሱን እንዳትወቅሱት: ስለ ድህነት በደንብ ያውቅ ነበር። እኔ ግን ስለ ድህነት ብዙም ስለማላውቅ
ጥፋቱ የኔ ነበር። እንዴት ያሞላቅቀኝ እንደነበር ታውቃላችሁ። ይህንን ቤት
ስንገዛ እንኳን የሚያስፈልጉን ሶስት መኝታ ክፍሎች ያሉት ቤት ነው ብሎኝ ነበር። እኔ ግን አራት ካልሆኑ አልኩት። አራትም በቂ አይመስለኝም ነበር።
“ተመልከቱ፣ ይህ ቤት የሰላሳ ዓመት የባንክ ዕዳ አለበት። ውስጡ ያሉት የትኞቹም ዕቃዎች የእኛ አይደሉም መኪኖቹም፣ ወጥቤት ያሉት ዕቃዎችም
ሆኑ የልብስ ማጠቢያው ክፍል ውስጥ ያሉት የትኞቹም ነገሮች ሙሉ ዋጋ የተከፈለባቸው አይደሉም”
ፈራን… ደነገጥን፡ ፊቷ ቀልቶ መናገሯን ቆም አደረገችና አይኖቿ የእሷ ውበት አምሳያ የሆነውን የሚያምረውን ክፍል መቃኘት ጀመሩ የሚያምሩት ቅንድቦቿ በመጓጓት አይነት ተኮሳተሩ። “አባታችሁ ተይ እንዳይለኝ ይወደኝ
ነበር ስለሚወደኝም ያሞላቅቀኝ ነበር። እኔም እንዴት ላሳምነው እንደምችል አውቅ ነበር። በመጨረሻ እነዚያ የቅንጦት ነገሮች አስፈላጊዎቻችን እየሆኑ
መጡና እጅ ሰጠ፡ ሁለታችንም ፍላጎቶቻችንን ለማሳካት መንገዶች ነበሩን።
እንግዳ በሆነ ድምጿ የምትናገረውን ከመቀጠሏ በፊት ፊቷ ከባዶ ትዝታዎቿ በአንዱ የተዋጠ መሰለ፡ “አሁን ሁሉም ውብ ነገሮቻችን ተወስደዋል። በህግ ቋንቋ ሁኔታው መውረስ ይባላል የገዛችሁትን ነገር ዋጋውን ከፍላችሁ ለመጨረስ በቂ ገንዘብ ከሌላችሁ እነሱ እንደዚያ ነው የሚደረጉት። ለምሳሌ ያንን ሶፋ ውሰዱ፤ ከሶስት ዓመት በፊት ዋጋው ስምንት መቶ ዶላር ነበር።
ሁሉንም ከፍለን የቀረን አንድ መቶ ዶላር ብቻ ነው: ግን በቃ ይወስዱታል።
ሁሉም ነገር ላይ የከፈልነውን ጭምር እናጣለን ይሄ ደግሞ ህጋዊ አሰራር ነው። የምናጣው እቃዎቹንና ቤቱን ብቻ አይደለም መኪናቹንም ጭምር ነው። ከልብሶቻችንና ከአሻንጉሊቶቻችሁ በስተቀር ሁሉንም እናጣለን ማለት
ነው። የጋብቻ ቀለበቴን እንድወሰደው ፈቅደውልኛል። እኔ ደግሞ ስንተጫጭ የሰጠኝን የአልማዝ ቀለበት ደብቄዋለሁ ስለዚህ እነሱ ለማረጋገጥ ሲመጡ
ለአንደኛቸውም እንኳን የቃልኪዳን ቀለበት እንዳለኝ እንዳትናገሩ፡"
“እነሱ” ማን እንደሆኑ ማናችንም አልጠየቅንም መጠየቅም አልመጣልኝም። ካለፈ በኋላ ደግሞ አስፈላጊ አልነበረም።
ከክሪስቶፈር ጋር ተያየን: ለመረዳት በመፈለግ ውስጥ እንዳልሰምጥ
እየታገልኩ ነበር። እውነታው ግን በትልልቅ ሰዎች የሞትና የዕዳ አለም ውስጥ እየሰመጥኩ መሆኑ ነው። ወንድሜ እጁን ዘርግቶ ያዘኝና ባልተለመደ ወንድማዊ የማረጋገጫ ምልክት ጣቶቼን ጨመቅ አደረጋቸው።
ለማንበብ ቀላል የሆንኩ የንፋስ መጥረጊያ ነኝ አንዴ ዋና አጥቂዬ የሆነው ወንድሜ እንኳን ሊያፅናናኝ የሚፈልገው? ምን ያህል ትልቅ ሰው እንደሆንኩ
ለማረጋገጥና እነሱ ሁሉንም ነገር በመውሰዳቸው ምክንያት የተሰማኝን ፍርሀትና ደካማነት ላለማሳየት ፈገግ ለማለት ሞከርኩ። የትኛዋም ትንሽ
ልጅ በእኔ ክፍል ውስጥ እንድትኖርም ሆነ እኔ አልጋ ላይ እንድትተኛና እኔ በምወዳቸው ነገሮች እንድትጫወት፣ አሻንጉሊቶቼን እንድትነካም ሆነ
በሙዚቃ ሳጥኔ እንድትጫወት አልፈልግም እነዚያንም ይወስዱብኝ ይሆን?
እናቴ የእኔንና የወንድሜን ሁኔታ በቅርበት እየተመለከተች ነበር። ከዚያ እንደገና በቀድሞው ጣፋጭ አነጋገሯ “ልባችሁ አይሰበር፤ እኔ ስነግራችሁ
እንደሚመስለው ያህል መጥፎ አይደለም: አሁንም ገና ትንንሽ ልጆች መሆናችሁን ረስቼ ሀሳብ የለሽ በመሆኔ ይቅር በሉኝ። መጥፎውን ዜና በመጀመሪያ የነገርኳችሁ ጥሩውን ወደ ኋላ አስቀርቼ ነው አሁን ትንፋሻችሁን
ያዙ! ወላጆቼ እጅግ ሀብታሞች እንደሆኑ ስነግራችሁ አታምኑኝም: መካከለኛ ኑሮ የሚኖሩ ሀብታሞች እንዳይመስሏችሁ፤ በማይታመን አይነት በጣም በጣም ሀብታሞች ናቸው! ቨርጂኒያ ውስጥ በሚገኝ ግዙፍ ቤት ውስጥ ነው የሚኖሩት። እንደዚያ አይነት ቤት ከዚህ በፊት አይታችሁ አታውቁም
የተወለድኩትና ያደግኩት እዚያ ነው ያንን ቤ ትዚህ ጋር ስታነፃፅሩት ይሄኛው እንደ ትንሽ ጎጆ ነው
#ጠላፊዎቹ
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
...ይህንን ማሰቡ በራሱ አንቀጠቀጣት፡፡ ወደ ክፍሏ ተመለሰችና ራሷን አረጋግታ ለአባቷ የምትለውን ነገር አሰላሰለች፡፡ ረጋ ማለት አለባት፡፡ እምባ እንደማያሳዝናቸውና ቁጣ ለስድብ እንደሚጋብዛቸው ታውቃለች፡፡ ምራቁን እንደዋጠ ሰው ነው መናገር ያለባት፡፡ ተጨቃጫቂ ከሆነች ቁጣቸውን ይቀሰቅስባቸውና ፍርሃት ተሰምቷት ያሰበችውን ከመናገር ልትታቀብ ትችላለች፡.
እንዴት ብላ ትጀምር? ስለ ወደፊቱ አንድ ነገር ለመናገር መብት
አለኝ?.ትበል።
አይደለም ይሄ ጥሩ አይደለም፡፡ ለአንቺ ህይወት ሀላፊው እኔ ነኝ፧ እኔ ነኝ መወሰን ያለብኝ ይሏታል፡
ምናልባትም ስለአሜሪካ ጉዞ ላናግርህ› ብትል ይሻል ይሆን?
‹ምንም የምንነጋገረው የለም› ይሏት ይሆናል፡
አጀማመሯ ተቃውሞ የማይቀሰቅስ መሆን አለበት፡፡
‹አንድ ነገር ልጠይቅህ› ልትላቸው ወሰነች፡፡ ለዚህም እሺ› ይሏታል፡ ከዚያ በኋላስ? ቁጣቸውን ሳትቀሰቅስ እቅዷ ጋ እንዴት ትጠጋ፡፡ባለፈው ጦርነት የጦር ሰራዊቱ ውስጥ ነበርክ ትበላቸው ይሆን? ፈረንሳይ ውስጥ መዋጋታቸውን ታውቃለች፡፡ እናታችንስ ነበረችበት?› ትበል ይሆን?እናታቸው የቆሰሉ የአሜሪካ ወታደሮችን በፈቃደኝነት ለማከም ለንደን ውስጥ
አገራዊ ግዴታቸውን ተወጥተዋል፡፡ በመጨረሻም ሁለታችሁም ሀገራችሁን አገልግላችኋል፧ መቼም እኔም ይህን ለማድረግ እንደምፈልግ ልትረዱት ይገባል፣› ማለት ሊኖርባት ነው።
ይህን የአገር ማገልገልን መርህ የሚቀበሉ ቢሆን እንኳን ሌላ ተቃውሟቸውን ሊቀሰቅስ የሚችለውንም ነገር አሰበች፡፡ ጦር ሰራዊቱን እስክትቀላቀል ዘመድ ጋ መቆየት ትችላለች፡ ይህም ለተወሰኑ ቀናት ነው፡፡አሁን አስራ ዘጠኝ አመቷ ነው፡ በዚህ እድሜ ላይ ያሉ ሴት ወጣቶች በቀን
ስድስት ሰዓት ይሰራሉ፡፡ መኪና ለመንዳት፣ ለትዳርም ሆነ ወህኒ ለመውረድ
እድሜዋ ይፈቅድላታል፡ እንግሊዝ ውስጥ እንዳትቆይ የማይፈቅዱበት
ምንም ምክንያት የለም፡
አሁን ያሰበችው ነገር ትክክል እንደሆነ ገመተች። የሚያስፈልጋት ድፍረት ብቻ ነው፡
አባቷ ከንግድ ድርጅታቸው ኃላፊ ጋር እየተወያዩ ነው፡፡ ማርጋሬት ከክፍሏ ወጣች፡ ደረጃውን ስትወርድ በፍርሃት እግሮቿ ራዱ፡፡
አባቷ ለሚቃወማቸው ንዴታቸው የከረረ ሲሆን ቅጣታቸውም የከፋ
ነው፡፡ በሰባት አመቷ አልጋ ላይ በመሽናቷ አሻንጉሊቷን ተነጥቃለች፡፡የአስራ አንድ አመት ልጅ ሳለች አንድ እንግዳ አንጓጣ ቀኑን ሙሉ ፊቷን ወደ ግድግዳ አዙራ እንድትቆይ አድርገዋታል፡ አንድ ጊዜ ተናደው ድመቷን
ከፎቅ በመስኮት ወርውረውባታል፡
አሁን እንግሊዝ ውስጥ
እንደምትቀርና ናዚዎችን እንደምትዋጋ ለአባቷ ብትናገር ምን ያደርጋሉ?
ደረጃውን በፍጥነት ወረደች፤ ነገር ግን የንባብ ክፍላቸው ጋ ስትደርስ
ፍርሃት ዋጣት፡፡ ሲናደዱ፣ ፊታቸው ሲቀላና አይናቸው ሲጎለጎል ታያት፤ጉልበቶቿ ተብረከረኩ፡፡ ራሷን ለማረጋጋት ሞከረች፡፡
አባቷ ያሉበት ክፍል በር ላይ ስትደርስ ቤት ጠባቂዋ ሚስስ አለን አዳራሹን አቋርጣ መጣች፡ ሚስስ አለን የቤት ሰራተኞች አለቃ ስትሆ በስሯ ያሉትን ሰራተኞች አሽቆጥቁጣ ነው የምታስተዳድረው፡፡ ቤተሰቡን በሙሉ ስለምትወድ አገር ለቀው መሄዳቸው በጣም አሳዝኗታል“ የእንጀራ ገመድ ተበጠሰ ማለት ነው፡፡ ለማርጋሬት ያሳየችው ፈገግታ በእምባ የታጀበ ነበር፡፡
ማርጋሬትም ሚስስ አለንን ስታይ ልቧ ተነካ፡፡ ወዲያውኑም የመጥፋት
ዕቅዷ በአዕምሮዋ ውስጥ ቅርፅ እየያዘ መጣ፡፡ ከሚስስ አለን ገንዘብ ትበደርና ቤቱን አሁኑኑ ለቃ የአስር ሰዓት ከሃምሳ ደቂቃውን ባቡር ተሳፍራ ወደ ለንደን ትሄዳለች፧ በአክስቷ በካትሪን ቤት ሌሊቱን ታሳልፍና በጧት የምድር ጦር መምሪያን ትቀላቀላለች፡፡ አባቷ ሲደርሱ እሷ ሰራዊቱን ስለምትቀላቀል ምንም ማድረግ አይችሉም፡፡
‹እቅዱ በጣም አደገኛና ድፍረት የሚጠይቅ በመሆኑ ሊሳካ አይችልም ብላ ሃሳቧን ከመለወጧ በፊት ‹‹ኦ ሚስስ አለን ትንሽ ገንዘብ ትስጪኛለሽ?
አንድ ነገር ገበያ ሄጄ ልገዛ አስቤ ነበር፤ አባባን ደግሞ መረበሽ አልፈለኩም በስራ ተጠምዷል፣›› አለቻት፡
ሚስስ አለን ሳታመነታ ‹‹እሺ እመቤቴ ምን ያህል ነው የሚፈልጉት? ማርጋሬት ወደ ለንደን ለመጓዝ የባቡሩን ዋጋ አታውቀውም፡፡ ትኬት
ገዝታ አታውቅም፡፡
እንዲያው በግምት ‹‹አንድ ፓውንድ ይበቃኛል›› አለቸ
ወዲያው በሃሳቧ ላደርገው ነው?› አለች፡፡
ሚስስ አለን ከቦርሳዋ ውስጥ ሁለት የአስር ሽልንግ ኖቶት አወጣች
ብትጠይቃት ዕድሜዋን ሙሉ ያጠራቀመችውን ገንዘብ ትሰጣት ነበር፡
ማርጋሬት ገንዘቡን እየተንቀጠቀጠች ተቀበለች፡፡ ይሄ የነፃነቴ ትኬት ይሆን ይሆናል› ስትል አሰበች፡፡ ፍርሃት ልቧን ቢያርደውም እንደ እሳ
የሚንቀለቀል ተስፋ ልቧ ውስጥ ተጫረ፡፡
ሚስስ አለን አገር ለቀው መሄዳቸው አሳዝኗት የማርጋሬትን እጅ
ጭምቅ አደረገች፡፡
‹‹ክፉ ቀን ነው የመጣብን እመቤት ማርጋሬት ለሁላችንም›› አለችና
ሽበት የወረረውን ጭንቅላቷን በሃዘን እየወዘወዘች ወደ ማድቤቷ ሮጠች።
ማርጋሬት በመረበሽ ዙሪያውን ቃኘች፤ አንድም ሰው አይታይም፡፡ ልቧ
ይደልቃል፧ ትንፋሿ ቁርጥ ቁርጥ ይላል፡፡ከተጠራጠረች እቅዷ አፈር ድሜ መብላቱ ነው፡፡ ኮቷን ለመልበስ ጊዜ ሳታጠፋ ገንዘቧን በእጇ ጨብጣ በፊት ለፊቱ በር ወጥታ ሄደች፡፡
የባቡር ጣቢያው ከቤታቸው ሁለት ኪሎ ሜትር ያህል ይርቃል፡፡በመንገድ ላይ የአባቷ ሮልስ ሮይስ መኪና ከኋላ የሚመጣ እየመሰላት
ትደነብራለች፡፡ ምን እንዳደረገች እንዴት ሊያውቁ ይችላሉ? መጥፋቷ ቢያንስ ከራት ሰዓት በፊት ሊታወቅ አይችልም፡፡ ሚስስ አለን ገበያ መሄዷን ትነግራቸዋለች፡፡
ባቡር ጣቢያ ቶሎ ደረሰች ቲኬት ገዝታ ብዙ ገንዘብ ተርፏታል፡ የሴቶች መቆያ ክፍል ገብታ የግርግዳ ሰዓቱን አየች፡
ባቡሩ ዘግይቷል፡
አስር ሰዓት ከሃምሳ አምስት ሆነ ከዚያም አስራ አንድ እያለ አስራ አንድ ከአምስት ሆነ፡ በዚህ ጊዜ ማርጋሬት ከመፍራቷ የተነሳ እቅዷን ሰርዛ ወደ ቤቷ በመመለስ ጭንቀቷን ማስወገድ እንደሚሻል ተሰማት፡፡
ባቡሩ አስራ አንድ ሰዓት ከአስራ አራት ደቂቃ ላይ መጣ፡፡ አባቷ በአካባቢው አይታዩም፡፡
ማርጋሬት ልቧ በጉሮሮዋ ተወትፎ ባቡር ላይ ተሳፈረችና መስኮቱ ጋ
ቆማ ‹አባቴ በመጨረሻው ደቂቃ ላይ መጥቶ ይወስደኛል› ስትል ተጨነቀች፡፡
በመጨረሻም ባቡሩ ተንቀሳቀሰ፡፡
ማምለጧን ማመን አቃታት፡፡
ባቡሩ ፍጥነቱን ሲጨምር የመጀመሪያው የደስታ ፍንጣቂ በልቧ ተጫረ፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ባቡሩ ጣቢያውን ለቆ ተጓዘ፡፡ ማርጋሬት
መንደሩ ወደ ኋላ ሲጓዝ ስትመለከት ልቧ በድል አድራጊነት ሲግል
ተሰማት፤ አደረገችው፤ አመለጠች፡፡
ወዲያው ጉልበቷ በድካም ተብረከረከ፡፡ መቀመጫ
ዙሪያውን ሲማትር ባቡሩ ሙሉ መሆኑን ለመጀመሪያ ጊዜ ተገነዘበች፡:ሁሉም ወንበሮች ተይዘዋል፤ አንደኛ ማዕረግም ቢሆን፡፡
ወለሉ ላይም የተቀመጡ ወታደሮች ነበሩ፡፡ እሷ ግን እንደቆመች ቀረች፡ ጉዞዋ ቅዠት ቢመስልም በልቧ የሚሰማት ደስታ አልቀነሰም፡፡
በየጣቢያው ባቡሩ ውስጥ ሰዎች ይጠቀጠቃሉ፡ ሪዲንግ ከተማ ላይ
ባቡሩ ሶስት ሰዓት ተገተረና አረፈው፡፡
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
...ይህንን ማሰቡ በራሱ አንቀጠቀጣት፡፡ ወደ ክፍሏ ተመለሰችና ራሷን አረጋግታ ለአባቷ የምትለውን ነገር አሰላሰለች፡፡ ረጋ ማለት አለባት፡፡ እምባ እንደማያሳዝናቸውና ቁጣ ለስድብ እንደሚጋብዛቸው ታውቃለች፡፡ ምራቁን እንደዋጠ ሰው ነው መናገር ያለባት፡፡ ተጨቃጫቂ ከሆነች ቁጣቸውን ይቀሰቅስባቸውና ፍርሃት ተሰምቷት ያሰበችውን ከመናገር ልትታቀብ ትችላለች፡.
እንዴት ብላ ትጀምር? ስለ ወደፊቱ አንድ ነገር ለመናገር መብት
አለኝ?.ትበል።
አይደለም ይሄ ጥሩ አይደለም፡፡ ለአንቺ ህይወት ሀላፊው እኔ ነኝ፧ እኔ ነኝ መወሰን ያለብኝ ይሏታል፡
ምናልባትም ስለአሜሪካ ጉዞ ላናግርህ› ብትል ይሻል ይሆን?
‹ምንም የምንነጋገረው የለም› ይሏት ይሆናል፡
አጀማመሯ ተቃውሞ የማይቀሰቅስ መሆን አለበት፡፡
‹አንድ ነገር ልጠይቅህ› ልትላቸው ወሰነች፡፡ ለዚህም እሺ› ይሏታል፡ ከዚያ በኋላስ? ቁጣቸውን ሳትቀሰቅስ እቅዷ ጋ እንዴት ትጠጋ፡፡ባለፈው ጦርነት የጦር ሰራዊቱ ውስጥ ነበርክ ትበላቸው ይሆን? ፈረንሳይ ውስጥ መዋጋታቸውን ታውቃለች፡፡ እናታችንስ ነበረችበት?› ትበል ይሆን?እናታቸው የቆሰሉ የአሜሪካ ወታደሮችን በፈቃደኝነት ለማከም ለንደን ውስጥ
አገራዊ ግዴታቸውን ተወጥተዋል፡፡ በመጨረሻም ሁለታችሁም ሀገራችሁን አገልግላችኋል፧ መቼም እኔም ይህን ለማድረግ እንደምፈልግ ልትረዱት ይገባል፣› ማለት ሊኖርባት ነው።
ይህን የአገር ማገልገልን መርህ የሚቀበሉ ቢሆን እንኳን ሌላ ተቃውሟቸውን ሊቀሰቅስ የሚችለውንም ነገር አሰበች፡፡ ጦር ሰራዊቱን እስክትቀላቀል ዘመድ ጋ መቆየት ትችላለች፡ ይህም ለተወሰኑ ቀናት ነው፡፡አሁን አስራ ዘጠኝ አመቷ ነው፡ በዚህ እድሜ ላይ ያሉ ሴት ወጣቶች በቀን
ስድስት ሰዓት ይሰራሉ፡፡ መኪና ለመንዳት፣ ለትዳርም ሆነ ወህኒ ለመውረድ
እድሜዋ ይፈቅድላታል፡ እንግሊዝ ውስጥ እንዳትቆይ የማይፈቅዱበት
ምንም ምክንያት የለም፡
አሁን ያሰበችው ነገር ትክክል እንደሆነ ገመተች። የሚያስፈልጋት ድፍረት ብቻ ነው፡
አባቷ ከንግድ ድርጅታቸው ኃላፊ ጋር እየተወያዩ ነው፡፡ ማርጋሬት ከክፍሏ ወጣች፡ ደረጃውን ስትወርድ በፍርሃት እግሮቿ ራዱ፡፡
አባቷ ለሚቃወማቸው ንዴታቸው የከረረ ሲሆን ቅጣታቸውም የከፋ
ነው፡፡ በሰባት አመቷ አልጋ ላይ በመሽናቷ አሻንጉሊቷን ተነጥቃለች፡፡የአስራ አንድ አመት ልጅ ሳለች አንድ እንግዳ አንጓጣ ቀኑን ሙሉ ፊቷን ወደ ግድግዳ አዙራ እንድትቆይ አድርገዋታል፡ አንድ ጊዜ ተናደው ድመቷን
ከፎቅ በመስኮት ወርውረውባታል፡
አሁን እንግሊዝ ውስጥ
እንደምትቀርና ናዚዎችን እንደምትዋጋ ለአባቷ ብትናገር ምን ያደርጋሉ?
ደረጃውን በፍጥነት ወረደች፤ ነገር ግን የንባብ ክፍላቸው ጋ ስትደርስ
ፍርሃት ዋጣት፡፡ ሲናደዱ፣ ፊታቸው ሲቀላና አይናቸው ሲጎለጎል ታያት፤ጉልበቶቿ ተብረከረኩ፡፡ ራሷን ለማረጋጋት ሞከረች፡፡
አባቷ ያሉበት ክፍል በር ላይ ስትደርስ ቤት ጠባቂዋ ሚስስ አለን አዳራሹን አቋርጣ መጣች፡ ሚስስ አለን የቤት ሰራተኞች አለቃ ስትሆ በስሯ ያሉትን ሰራተኞች አሽቆጥቁጣ ነው የምታስተዳድረው፡፡ ቤተሰቡን በሙሉ ስለምትወድ አገር ለቀው መሄዳቸው በጣም አሳዝኗታል“ የእንጀራ ገመድ ተበጠሰ ማለት ነው፡፡ ለማርጋሬት ያሳየችው ፈገግታ በእምባ የታጀበ ነበር፡፡
ማርጋሬትም ሚስስ አለንን ስታይ ልቧ ተነካ፡፡ ወዲያውኑም የመጥፋት
ዕቅዷ በአዕምሮዋ ውስጥ ቅርፅ እየያዘ መጣ፡፡ ከሚስስ አለን ገንዘብ ትበደርና ቤቱን አሁኑኑ ለቃ የአስር ሰዓት ከሃምሳ ደቂቃውን ባቡር ተሳፍራ ወደ ለንደን ትሄዳለች፧ በአክስቷ በካትሪን ቤት ሌሊቱን ታሳልፍና በጧት የምድር ጦር መምሪያን ትቀላቀላለች፡፡ አባቷ ሲደርሱ እሷ ሰራዊቱን ስለምትቀላቀል ምንም ማድረግ አይችሉም፡፡
‹እቅዱ በጣም አደገኛና ድፍረት የሚጠይቅ በመሆኑ ሊሳካ አይችልም ብላ ሃሳቧን ከመለወጧ በፊት ‹‹ኦ ሚስስ አለን ትንሽ ገንዘብ ትስጪኛለሽ?
አንድ ነገር ገበያ ሄጄ ልገዛ አስቤ ነበር፤ አባባን ደግሞ መረበሽ አልፈለኩም በስራ ተጠምዷል፣›› አለቻት፡
ሚስስ አለን ሳታመነታ ‹‹እሺ እመቤቴ ምን ያህል ነው የሚፈልጉት? ማርጋሬት ወደ ለንደን ለመጓዝ የባቡሩን ዋጋ አታውቀውም፡፡ ትኬት
ገዝታ አታውቅም፡፡
እንዲያው በግምት ‹‹አንድ ፓውንድ ይበቃኛል›› አለቸ
ወዲያው በሃሳቧ ላደርገው ነው?› አለች፡፡
ሚስስ አለን ከቦርሳዋ ውስጥ ሁለት የአስር ሽልንግ ኖቶት አወጣች
ብትጠይቃት ዕድሜዋን ሙሉ ያጠራቀመችውን ገንዘብ ትሰጣት ነበር፡
ማርጋሬት ገንዘቡን እየተንቀጠቀጠች ተቀበለች፡፡ ይሄ የነፃነቴ ትኬት ይሆን ይሆናል› ስትል አሰበች፡፡ ፍርሃት ልቧን ቢያርደውም እንደ እሳ
የሚንቀለቀል ተስፋ ልቧ ውስጥ ተጫረ፡፡
ሚስስ አለን አገር ለቀው መሄዳቸው አሳዝኗት የማርጋሬትን እጅ
ጭምቅ አደረገች፡፡
‹‹ክፉ ቀን ነው የመጣብን እመቤት ማርጋሬት ለሁላችንም›› አለችና
ሽበት የወረረውን ጭንቅላቷን በሃዘን እየወዘወዘች ወደ ማድቤቷ ሮጠች።
ማርጋሬት በመረበሽ ዙሪያውን ቃኘች፤ አንድም ሰው አይታይም፡፡ ልቧ
ይደልቃል፧ ትንፋሿ ቁርጥ ቁርጥ ይላል፡፡ከተጠራጠረች እቅዷ አፈር ድሜ መብላቱ ነው፡፡ ኮቷን ለመልበስ ጊዜ ሳታጠፋ ገንዘቧን በእጇ ጨብጣ በፊት ለፊቱ በር ወጥታ ሄደች፡፡
የባቡር ጣቢያው ከቤታቸው ሁለት ኪሎ ሜትር ያህል ይርቃል፡፡በመንገድ ላይ የአባቷ ሮልስ ሮይስ መኪና ከኋላ የሚመጣ እየመሰላት
ትደነብራለች፡፡ ምን እንዳደረገች እንዴት ሊያውቁ ይችላሉ? መጥፋቷ ቢያንስ ከራት ሰዓት በፊት ሊታወቅ አይችልም፡፡ ሚስስ አለን ገበያ መሄዷን ትነግራቸዋለች፡፡
ባቡር ጣቢያ ቶሎ ደረሰች ቲኬት ገዝታ ብዙ ገንዘብ ተርፏታል፡ የሴቶች መቆያ ክፍል ገብታ የግርግዳ ሰዓቱን አየች፡
ባቡሩ ዘግይቷል፡
አስር ሰዓት ከሃምሳ አምስት ሆነ ከዚያም አስራ አንድ እያለ አስራ አንድ ከአምስት ሆነ፡ በዚህ ጊዜ ማርጋሬት ከመፍራቷ የተነሳ እቅዷን ሰርዛ ወደ ቤቷ በመመለስ ጭንቀቷን ማስወገድ እንደሚሻል ተሰማት፡፡
ባቡሩ አስራ አንድ ሰዓት ከአስራ አራት ደቂቃ ላይ መጣ፡፡ አባቷ በአካባቢው አይታዩም፡፡
ማርጋሬት ልቧ በጉሮሮዋ ተወትፎ ባቡር ላይ ተሳፈረችና መስኮቱ ጋ
ቆማ ‹አባቴ በመጨረሻው ደቂቃ ላይ መጥቶ ይወስደኛል› ስትል ተጨነቀች፡፡
በመጨረሻም ባቡሩ ተንቀሳቀሰ፡፡
ማምለጧን ማመን አቃታት፡፡
ባቡሩ ፍጥነቱን ሲጨምር የመጀመሪያው የደስታ ፍንጣቂ በልቧ ተጫረ፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ባቡሩ ጣቢያውን ለቆ ተጓዘ፡፡ ማርጋሬት
መንደሩ ወደ ኋላ ሲጓዝ ስትመለከት ልቧ በድል አድራጊነት ሲግል
ተሰማት፤ አደረገችው፤ አመለጠች፡፡
ወዲያው ጉልበቷ በድካም ተብረከረከ፡፡ መቀመጫ
ዙሪያውን ሲማትር ባቡሩ ሙሉ መሆኑን ለመጀመሪያ ጊዜ ተገነዘበች፡:ሁሉም ወንበሮች ተይዘዋል፤ አንደኛ ማዕረግም ቢሆን፡፡
ወለሉ ላይም የተቀመጡ ወታደሮች ነበሩ፡፡ እሷ ግን እንደቆመች ቀረች፡ ጉዞዋ ቅዠት ቢመስልም በልቧ የሚሰማት ደስታ አልቀነሰም፡፡
በየጣቢያው ባቡሩ ውስጥ ሰዎች ይጠቀጠቃሉ፡ ሪዲንግ ከተማ ላይ
ባቡሩ ሶስት ሰዓት ተገተረና አረፈው፡፡
#ከቡስካ_በስተጀርባ
#ድንግል_ውበት
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ከሎ ከተቀመጠበት ስፍራ ላይ ጕልበቱን ሰብሰብ አድርጎ በመታቀፍ ከንፈሩን እያኘከ የሚተነፍገውን የወይጦ በረሃ የእፅዋት
ሽታ ይምጋል ከየጉድባው ወጥተው ድብልቅልቅ በሚያደርግ ድምፅ የሚያገሱት አንበሶች፣ በቀጭንና ወፍራም ድምፅ ጨለማን ተገን አድርገው ድምፃቸውን በነፃነት የሚያስተጋቡትን የአራዊት
ትርምስ እያዳመጡ ሁለቱም በሐሳብ ተውጠው ቆዩ"
ከዋክብት ሰማዩ ላይ ሆጨጭ ብለው ብርሃናቸውን ብልጭ
ድርግም ሲያደርጉ፣ ገና የተወለደች ጨረቃ ካለአቅሟ ግዙፉን
ጨለማ ከዝሆን ጋር እንደሚታገል ዝንብ በብርሃን ድል ለማድረግ
ከተራራው አናት ወደ መሃል ሰማይ ስትገሰግስ፣ በበረት የታጎሩት ከብቶች እያመነዠኩ ሲያቃስቱ፣ ካርለትም ሆዷ እየተሸበረ፣
በምትፈጥረው ወኔ ግን እራሷን እየደለለች እንደ ከብቶች ላይ ላይ
እየተነፈሰች ታቃስታለች።
የወይጦ በርሃ በተለይም በቀትር ላይ ሙቀቱ እንደ ደመራ እሳት ይጋረፋል" የአራዊቱና የእፅዋቱ አካል ሳይቀር በሙቀቱ ስለሚቀረና አካባቢው ለየት ባለ ሽታ ይታፈናል" በዚህ ወቅት እንግዳ ሰው እንደ
ውሻ እያለከለከ የሚስበው አየር ፍለጋ አፍንጫውን እንደ አንቴና አቁሞ ያንጋጥጣል። ሆኖም ግን የፀሀይ ማኅበረሰብ፣ ሰጎን፣ አንበሳ፣ የሜዳ ፍየል፣ ጉርኑክና የመሳሰሉት እንስሳት በደስታ ተዝናንተው
ይኖሩበታል።
የወይጦ በረሃ ግለት እየቀነሰ ሲመጣ የፀማይ ማኅበረሰብ አባላት
ከማሳ፣ ከወንዝ፣ ከከብት ጥበቃ፣ ከአደን፣ ከማር ቆረጣ፣ከመንገድ...
ወደየመንደሩ ሲከት፣ ከተለመደው ውጭ ነጭ መኪና፣ ጸጕሯ ረዘም ያለ ነጭ ሴት፣ ልብስ የለበሰ ጠይም ከተሜ መንደራቸው
ውስጥ ድንኳን ከትመው አገኛቸው" በዚያን ወቅት፣ ድፍን የፀማይ ኗሪ ስልክና ሌላ መገናኛ ባይኖርም የሰማው ላልሰማው መልእክቱን በቃል እያስተላለፈ፣ ቤት ለቤት የሚውሉ ሽማግሌና ባልቴቶች ሳይቀሩ «ነጭ በቆሎ» የመሰለችውንና ብልጭልጭ ቅራቅንቦ
የተቀረቀበባትን መኪና፣ ለማየት ጎረፉ።
በካርለት ጸጕርና እጅ ላይ ብዙ የፀማይ «ተመራማሪ» እጆች አረፉበት እንደ አንበሳ ጐፈሬ የለሰለሰ ጸጕር፣ እንደ እብነ በረድ የነጣና የለሰለሰ ገላ፣ የትንባሆ አጢያሽ የመሰለ ጥርስ ሲመለከቱ፣
«ይህች ሰው ምንድ ናት?» ብለው ሲደነቁ ቆዩ። ከመካከል አንዱ፣
«ፈረንጅ ናት» አለ፣ ነቃ ያለው።
«ፈረንጅ...ኡ» አሉ፣ በአድናቆት አፋቸውን እየያዙ“
«አሃ ፈረንጅማ ከሆነች ያች በፍየልና ማር ከነጋዴ
የምንለውጣት የሽጉጥ ጥይት የመሰለችው የፈረንጅ መድኃኒት ትኖራለች» ተባባሉ እርስ በእርሳቸው ከሎ ሆራ ፀማይኛ አይችልም
አንዳንድ ፀማዮች ግን ሐመርኛ ስለሚችሉ መድኃኒቷን እንድትሰጠን
ጠይቅልን አሉት፥ ለምልክት አንድ የ«ቴትራሳይhሊን» እንክብል እያሳዩት" ፀማዮች ካርለትና ከሎ ቋንቋቸውን ባለመቻላቸው በተለይ
ሴቶችና ጎረምሶች ግራ ገብቷቸዋል፣ «ሆሆይ ለካ እናንተዬ ፀማይኛም የማይችል ሰው አለ!» ብለው ተሳልቀዋል።
በዚህ መልክ ራቁታቸውን የሆኑ ሕፃናት፣ ጎረምሳና አዋቂ ወንዶች ግልድም ያገለደሙ፣ ከወገባቸው በታች የለበሱት ቆዳ
መሬት ለመሬት የሚጎተት ትንሽ እንጨት ያለበት ሴቶች ካርለትን እንደ ጉድ ተመለከቷት እሷም እነሱን በተመስጦ እየተመለከተች
የሁለት ወገን ጉዶች ካለ ቋንቋ በጥቅሻ ሲነጋገሩ፣ አንዱ ሌላውን ለመግባባት ሲጣጣር ቆይተው የምሽቱ የአራዊት ትርምስና ጨለማ
ሳያሸብራቸው በየአቅጣጫው በመሄድ ቀስ በቀስ ተበታተኑባት"።
ካርለት፣ hአዲስ አበባው ሒልተን ሆቴል ወደ አርባ ምንጩ በቀለ ሞላ ሆቴል፣ ከአርባ ምንጩ ሆቴል ወደ ድንኳን አዳር እየወረደች
የምትበላውም መጠኑና ዓይነቱ በጣም እየቀነሰ
ቢመጣም፣ በጣም የተቸገረችበት ጉዳይ ሌላ ነበር። እስከ አሁን
እንዳስተዋለችው ፀማይ መንደር ውስጥም ሆነ መንገድ ላይ ሽንት ቤት አላየችም። ለመጸዳዳት ወደ ጫካ ሲገቡ ተመልhታለች" እሷ ደግሞ ጫካ ሄዳ መጸዳዳቱን ሕሊናዋ ሊቀበለው አልቻለም" በጕዞዋ ባሳለፈችው ቆይታ በሶፍት እየተጸዳዳች በማቃጠል፣ እየተጠቀመች
ነው። ሐመር ስትሄድ ግን በዚሁ መልክ መቀጠል የሚቻላት አይሆንም" ሽንት ቤት አስቆፍራ እንዳትጠቀም ለአካባቢው እንግዳ ሁኔታ በመፍጠሯ መልካም ግንኙነት ላይኖራት ነው“ ስለዚህ ሊታይ
በማይችልና መጠነኛ ጥልቀት ባለው ጉድጓድ መጠቀሙን እያሰበችበት ነው።
በእርግጥ እንኳን ካደጉበት ባህል ውጭ ላተወሰነ ጊዜ
ከተከታተሉት ባህልን ለየት ወዳለ ሲገባ የመጨነቅ ስሜት መፈጠሩ
የነበረ ነውና ካርለትም የኢንግላንድ ዘመናዊነት፣ የለንደን ከተማ፣
ማንችስተር የሚገኙት አያቶቿ፣ የወንድና ሴት ጓደኞቿ፣ መዝናኛዎች፣ የጭፈራ ቦታዎች ቀርተው ራቁታቸውን ከሚሄዱ ጥቋቁር ሰዎች፣ ከከብቶች በረት፣ ከፍየልና በጎች ጋጥ አካባቢ መሆንዋ
ሕልም እንጂ እውን ሊመስላት አልቻለም።
ካርለት ወደ ኢትዮጵያ ለጥናት ከመምጣቷ በፊት የአገር ቤቱን ሕይወት ለመለማመድ ወደ ስፓኝ በመሄድ «የስፓኝ በር» ተብላ በምትታወቀው የሁልቫ ከተማ የበጋ መዝናኛዋን በማድረግና ከወንድ ጓደኛዋ ጋር በብርቱካንና የሱፍ ማሳ አቅራቢያ ተቀምጣ ፀሐይ ላይ ብዙ መቆየት፣ ብርድና፣ ብቸኝነትን ለመለማመድ ሞካክራ ነበር።ያን ጊዜ የወደፊት የጥናት ቦታዋ በአሥር እጅ ከዚያ ሊለይ
እንደሚችል ብትገምትም አሁን ግን ዘጠና ዘጠኝ እጅ ያላሰበችውና
ያልገመተችው ዓይነት ሆነባት"
ካርለት እንዲህ በሐሳብ ጉና ስትንጨዋለል፣ እያንቋረረ
የሚከፈተውን የከሎን ጕሮሮ ስትሰማ ከሰመመኗ ተመለሰች።ከዚያም ዓይኗንና ሕሊናዋን ወደ እሱ መለሰች።፣
እስከ አሁን ከከሎ ጋር ባደረገችው ቆይታ ካላናገሩት የማይናገረው ጥቁሩ ወጣት በራሱ ፍላጎትና አነሳሽነት፣ ሊያወጋት መዘጋጀቱ ሳያስደንቃት አልቀረም።
«ሚንጊ ነኝ» አለ ከሎ ድንገት።
«ምን?» አለች ካርለት፥ የጠቀሰው ቃል አልገባሽ ብሏት
«ሚንጊ ማለት በሐመር ቋንቋ ገፊ ማለት ነው» አሁንም የባሰ ተደነጋገረችI ስለዚህ፣ እንዲግባቡ ለማድረግ ገለጻውን ሰፋ አድርጎ ጀመረ።
«ሕፃን ልጅ በሽማግሌዎች ፈቃድ ይወለዳል።»
«ካለ ሽማግሌ ፈቃድ መውለድ አይቻልም? ለመውለድ የሽማግሌዎችን ፈቃድ እንዴት ይጠየቃል? ሽማግሌ የተባሉት ልዩ
ችሎታ ያላቸው ሰዎች ናቸው?» ካርለት ልጅ ለመውለድ ሲያስፈልግ የሐኪም፣ ካስፈለገም የሥነአእምሮ ጠቢብ ምክር
ሊጠየቅ እንደሚችል ታውቃለች" ይህም ቢሆን ችግር ያለባቸውና
በማኅበራዊ ጠንቅ ውስጥ እንዳይዘፈቁ የሰጉ ሰዎች የሚፈጽሙት እንጂ ለማንኛውም ዜጋ የተደነገገ ሕግ አይደለም" ሆኖም፣ ሽማግሌ የተባሉት ለየት ያለ ችሎታ ያላቸው ይሆናሉ ብላ ገመተች።
«አንችን ለማስረዳት ለኔ ከባድ ነው" በኋላ ቀስ በቀስ
ልታውቂው ትችያለሽ ሽማግሌ የተባሉት ግን በዕድሜና በልምድ
ተደማጭነት ያላቸው ሲሆኑ ማንም የሐመር ማኅበረሰብ ሴት ባሏ ጥሎሽ ጥሎ እሱ ዘንድ ካመጣት በኋላ አንድ ቅል አሸዋና አንድ ቅል
ወተት ይዛ ወደ ክልሉ ሽማግሎች ዘንድ ትሄድና ትመረቃለች"ከዚያም ወተቷን ትሰጥና አሸዋውን የያዘውን ቅል ቤቷ አምጥታ
ግርግም ላይ ታንጠለጥለዋለች" ከዚያ፣ ከባሏ ጋር የግብረሥጋ
ግንኙነት አድርጋ ፅንስ ከፀነሰች፣ ወደ ሽማግሎች ሄዳ መፀነሷን ታስታውቃለች። አንዴ መፀነሷን ሽማግሎች ከሰሙ፣ ባሏና እሷ
ፅንሱ አድጎ ከተወለደ በኋላ ጥርስ ማብቀል እስኪጀምር ድረስ የግብረ ሥጋ ግንኙነት አይፈጽሙም።»
#ድንግል_ውበት
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ከሎ ከተቀመጠበት ስፍራ ላይ ጕልበቱን ሰብሰብ አድርጎ በመታቀፍ ከንፈሩን እያኘከ የሚተነፍገውን የወይጦ በረሃ የእፅዋት
ሽታ ይምጋል ከየጉድባው ወጥተው ድብልቅልቅ በሚያደርግ ድምፅ የሚያገሱት አንበሶች፣ በቀጭንና ወፍራም ድምፅ ጨለማን ተገን አድርገው ድምፃቸውን በነፃነት የሚያስተጋቡትን የአራዊት
ትርምስ እያዳመጡ ሁለቱም በሐሳብ ተውጠው ቆዩ"
ከዋክብት ሰማዩ ላይ ሆጨጭ ብለው ብርሃናቸውን ብልጭ
ድርግም ሲያደርጉ፣ ገና የተወለደች ጨረቃ ካለአቅሟ ግዙፉን
ጨለማ ከዝሆን ጋር እንደሚታገል ዝንብ በብርሃን ድል ለማድረግ
ከተራራው አናት ወደ መሃል ሰማይ ስትገሰግስ፣ በበረት የታጎሩት ከብቶች እያመነዠኩ ሲያቃስቱ፣ ካርለትም ሆዷ እየተሸበረ፣
በምትፈጥረው ወኔ ግን እራሷን እየደለለች እንደ ከብቶች ላይ ላይ
እየተነፈሰች ታቃስታለች።
የወይጦ በርሃ በተለይም በቀትር ላይ ሙቀቱ እንደ ደመራ እሳት ይጋረፋል" የአራዊቱና የእፅዋቱ አካል ሳይቀር በሙቀቱ ስለሚቀረና አካባቢው ለየት ባለ ሽታ ይታፈናል" በዚህ ወቅት እንግዳ ሰው እንደ
ውሻ እያለከለከ የሚስበው አየር ፍለጋ አፍንጫውን እንደ አንቴና አቁሞ ያንጋጥጣል። ሆኖም ግን የፀሀይ ማኅበረሰብ፣ ሰጎን፣ አንበሳ፣ የሜዳ ፍየል፣ ጉርኑክና የመሳሰሉት እንስሳት በደስታ ተዝናንተው
ይኖሩበታል።
የወይጦ በረሃ ግለት እየቀነሰ ሲመጣ የፀማይ ማኅበረሰብ አባላት
ከማሳ፣ ከወንዝ፣ ከከብት ጥበቃ፣ ከአደን፣ ከማር ቆረጣ፣ከመንገድ...
ወደየመንደሩ ሲከት፣ ከተለመደው ውጭ ነጭ መኪና፣ ጸጕሯ ረዘም ያለ ነጭ ሴት፣ ልብስ የለበሰ ጠይም ከተሜ መንደራቸው
ውስጥ ድንኳን ከትመው አገኛቸው" በዚያን ወቅት፣ ድፍን የፀማይ ኗሪ ስልክና ሌላ መገናኛ ባይኖርም የሰማው ላልሰማው መልእክቱን በቃል እያስተላለፈ፣ ቤት ለቤት የሚውሉ ሽማግሌና ባልቴቶች ሳይቀሩ «ነጭ በቆሎ» የመሰለችውንና ብልጭልጭ ቅራቅንቦ
የተቀረቀበባትን መኪና፣ ለማየት ጎረፉ።
በካርለት ጸጕርና እጅ ላይ ብዙ የፀማይ «ተመራማሪ» እጆች አረፉበት እንደ አንበሳ ጐፈሬ የለሰለሰ ጸጕር፣ እንደ እብነ በረድ የነጣና የለሰለሰ ገላ፣ የትንባሆ አጢያሽ የመሰለ ጥርስ ሲመለከቱ፣
«ይህች ሰው ምንድ ናት?» ብለው ሲደነቁ ቆዩ። ከመካከል አንዱ፣
«ፈረንጅ ናት» አለ፣ ነቃ ያለው።
«ፈረንጅ...ኡ» አሉ፣ በአድናቆት አፋቸውን እየያዙ“
«አሃ ፈረንጅማ ከሆነች ያች በፍየልና ማር ከነጋዴ
የምንለውጣት የሽጉጥ ጥይት የመሰለችው የፈረንጅ መድኃኒት ትኖራለች» ተባባሉ እርስ በእርሳቸው ከሎ ሆራ ፀማይኛ አይችልም
አንዳንድ ፀማዮች ግን ሐመርኛ ስለሚችሉ መድኃኒቷን እንድትሰጠን
ጠይቅልን አሉት፥ ለምልክት አንድ የ«ቴትራሳይhሊን» እንክብል እያሳዩት" ፀማዮች ካርለትና ከሎ ቋንቋቸውን ባለመቻላቸው በተለይ
ሴቶችና ጎረምሶች ግራ ገብቷቸዋል፣ «ሆሆይ ለካ እናንተዬ ፀማይኛም የማይችል ሰው አለ!» ብለው ተሳልቀዋል።
በዚህ መልክ ራቁታቸውን የሆኑ ሕፃናት፣ ጎረምሳና አዋቂ ወንዶች ግልድም ያገለደሙ፣ ከወገባቸው በታች የለበሱት ቆዳ
መሬት ለመሬት የሚጎተት ትንሽ እንጨት ያለበት ሴቶች ካርለትን እንደ ጉድ ተመለከቷት እሷም እነሱን በተመስጦ እየተመለከተች
የሁለት ወገን ጉዶች ካለ ቋንቋ በጥቅሻ ሲነጋገሩ፣ አንዱ ሌላውን ለመግባባት ሲጣጣር ቆይተው የምሽቱ የአራዊት ትርምስና ጨለማ
ሳያሸብራቸው በየአቅጣጫው በመሄድ ቀስ በቀስ ተበታተኑባት"።
ካርለት፣ hአዲስ አበባው ሒልተን ሆቴል ወደ አርባ ምንጩ በቀለ ሞላ ሆቴል፣ ከአርባ ምንጩ ሆቴል ወደ ድንኳን አዳር እየወረደች
የምትበላውም መጠኑና ዓይነቱ በጣም እየቀነሰ
ቢመጣም፣ በጣም የተቸገረችበት ጉዳይ ሌላ ነበር። እስከ አሁን
እንዳስተዋለችው ፀማይ መንደር ውስጥም ሆነ መንገድ ላይ ሽንት ቤት አላየችም። ለመጸዳዳት ወደ ጫካ ሲገቡ ተመልhታለች" እሷ ደግሞ ጫካ ሄዳ መጸዳዳቱን ሕሊናዋ ሊቀበለው አልቻለም" በጕዞዋ ባሳለፈችው ቆይታ በሶፍት እየተጸዳዳች በማቃጠል፣ እየተጠቀመች
ነው። ሐመር ስትሄድ ግን በዚሁ መልክ መቀጠል የሚቻላት አይሆንም" ሽንት ቤት አስቆፍራ እንዳትጠቀም ለአካባቢው እንግዳ ሁኔታ በመፍጠሯ መልካም ግንኙነት ላይኖራት ነው“ ስለዚህ ሊታይ
በማይችልና መጠነኛ ጥልቀት ባለው ጉድጓድ መጠቀሙን እያሰበችበት ነው።
በእርግጥ እንኳን ካደጉበት ባህል ውጭ ላተወሰነ ጊዜ
ከተከታተሉት ባህልን ለየት ወዳለ ሲገባ የመጨነቅ ስሜት መፈጠሩ
የነበረ ነውና ካርለትም የኢንግላንድ ዘመናዊነት፣ የለንደን ከተማ፣
ማንችስተር የሚገኙት አያቶቿ፣ የወንድና ሴት ጓደኞቿ፣ መዝናኛዎች፣ የጭፈራ ቦታዎች ቀርተው ራቁታቸውን ከሚሄዱ ጥቋቁር ሰዎች፣ ከከብቶች በረት፣ ከፍየልና በጎች ጋጥ አካባቢ መሆንዋ
ሕልም እንጂ እውን ሊመስላት አልቻለም።
ካርለት ወደ ኢትዮጵያ ለጥናት ከመምጣቷ በፊት የአገር ቤቱን ሕይወት ለመለማመድ ወደ ስፓኝ በመሄድ «የስፓኝ በር» ተብላ በምትታወቀው የሁልቫ ከተማ የበጋ መዝናኛዋን በማድረግና ከወንድ ጓደኛዋ ጋር በብርቱካንና የሱፍ ማሳ አቅራቢያ ተቀምጣ ፀሐይ ላይ ብዙ መቆየት፣ ብርድና፣ ብቸኝነትን ለመለማመድ ሞካክራ ነበር።ያን ጊዜ የወደፊት የጥናት ቦታዋ በአሥር እጅ ከዚያ ሊለይ
እንደሚችል ብትገምትም አሁን ግን ዘጠና ዘጠኝ እጅ ያላሰበችውና
ያልገመተችው ዓይነት ሆነባት"
ካርለት እንዲህ በሐሳብ ጉና ስትንጨዋለል፣ እያንቋረረ
የሚከፈተውን የከሎን ጕሮሮ ስትሰማ ከሰመመኗ ተመለሰች።ከዚያም ዓይኗንና ሕሊናዋን ወደ እሱ መለሰች።፣
እስከ አሁን ከከሎ ጋር ባደረገችው ቆይታ ካላናገሩት የማይናገረው ጥቁሩ ወጣት በራሱ ፍላጎትና አነሳሽነት፣ ሊያወጋት መዘጋጀቱ ሳያስደንቃት አልቀረም።
«ሚንጊ ነኝ» አለ ከሎ ድንገት።
«ምን?» አለች ካርለት፥ የጠቀሰው ቃል አልገባሽ ብሏት
«ሚንጊ ማለት በሐመር ቋንቋ ገፊ ማለት ነው» አሁንም የባሰ ተደነጋገረችI ስለዚህ፣ እንዲግባቡ ለማድረግ ገለጻውን ሰፋ አድርጎ ጀመረ።
«ሕፃን ልጅ በሽማግሌዎች ፈቃድ ይወለዳል።»
«ካለ ሽማግሌ ፈቃድ መውለድ አይቻልም? ለመውለድ የሽማግሌዎችን ፈቃድ እንዴት ይጠየቃል? ሽማግሌ የተባሉት ልዩ
ችሎታ ያላቸው ሰዎች ናቸው?» ካርለት ልጅ ለመውለድ ሲያስፈልግ የሐኪም፣ ካስፈለገም የሥነአእምሮ ጠቢብ ምክር
ሊጠየቅ እንደሚችል ታውቃለች" ይህም ቢሆን ችግር ያለባቸውና
በማኅበራዊ ጠንቅ ውስጥ እንዳይዘፈቁ የሰጉ ሰዎች የሚፈጽሙት እንጂ ለማንኛውም ዜጋ የተደነገገ ሕግ አይደለም" ሆኖም፣ ሽማግሌ የተባሉት ለየት ያለ ችሎታ ያላቸው ይሆናሉ ብላ ገመተች።
«አንችን ለማስረዳት ለኔ ከባድ ነው" በኋላ ቀስ በቀስ
ልታውቂው ትችያለሽ ሽማግሌ የተባሉት ግን በዕድሜና በልምድ
ተደማጭነት ያላቸው ሲሆኑ ማንም የሐመር ማኅበረሰብ ሴት ባሏ ጥሎሽ ጥሎ እሱ ዘንድ ካመጣት በኋላ አንድ ቅል አሸዋና አንድ ቅል
ወተት ይዛ ወደ ክልሉ ሽማግሎች ዘንድ ትሄድና ትመረቃለች"ከዚያም ወተቷን ትሰጥና አሸዋውን የያዘውን ቅል ቤቷ አምጥታ
ግርግም ላይ ታንጠለጥለዋለች" ከዚያ፣ ከባሏ ጋር የግብረሥጋ
ግንኙነት አድርጋ ፅንስ ከፀነሰች፣ ወደ ሽማግሎች ሄዳ መፀነሷን ታስታውቃለች። አንዴ መፀነሷን ሽማግሎች ከሰሙ፣ ባሏና እሷ
ፅንሱ አድጎ ከተወለደ በኋላ ጥርስ ማብቀል እስኪጀምር ድረስ የግብረ ሥጋ ግንኙነት አይፈጽሙም።»
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታሰ
እድላችን ነው: አሁን መነሳት ያለበት ጥያቂ አይደለም።
መልሉ የተሰጠ ጥያቄ ጥያቂ ሊሆን አይችልም
ይልቅስ ሁሉንም በፀጋ ተቀብሎ መኖር ነው" ለምን በምን. ላይ ያተኮረ
ሃሳብ ሃሳብ እንዳላት ሊገባው አልቻለም ስለዚህ ደስታው እየኮለመነ ግራ መጋባቱ እያየለ ሄደ።
“ልታነጋግሪኝ የፈለግሽው ምንድን ነው? ፈገግ ለማለት
እየሞከረ በጥሞና ጠየቃት:
“...እንደውሻ ቢያላዝኑ ሰሚ በሌለባት ምድር ለምን
ተወለድሁ! መወለዴን ሳስበው ይቆጨኛል! መሞቴም ያበሽቀኛል፤
ለምን ተወለድኩና ለምንስ ደግሞ እሞታለሁ። ስወለድም ለሞት
የምኖረውም ለሞት... አይኖችዋ ድንገት በእንባ ተጥለቀለቁና ቁልቁል ተደፋ: ያን ጊዜ ጨነቀው፡
የሚለበልበው እንባዋ
የማያውቃት ልጅ ድንገት እቤቱ መምጣቷ ብቻ አንሷት እንደበደላት ሁሉ ስታለቅስበት የሚይዘው የሚጨብጠው ጠፋው።
“የኔ እህት የሶራ ገልቻ ቤት የብሶት መወጫ የበደል
ማራገፊያ ነው ያለሽ ማን ነው?... ደግሞስ እንዲህ ስታለቅሺ ሰው ቢመጣ ምን ይላል? ልቅሶ ካማረሽ ብሶትሽን ማካፈል ከፈለግሽ...”ብሎ በውስጡ የተፈጠረውን ሃሳብ በአእምሮ አዘጋጅቶ ከመቋጨቱ በፊት አናጠባቸው:
“ወኔ ቢስ! ይህን ስትል አታፍርም አይደል! እልህ
ውስጥህ አይንጠውም አይደል! እዚች ሃገር መወለዴ እድሌ መሆኑ ጠፍቶኝ የጠየቅህ ይመስልሃል? እንዴት ያስጨነቀኝ ጥያቂ መለስህልኝ ባክህ ጅል!" ብላ በእልክ እያለቀሰች በስርዓት የተጠቀለለ ፀጉሯን ነጨችው።
“ቆይ እስኪ እንዴ
እኔ አልበደልኩሽ የኔ እህት: አይጥ በበላ ዳዋ ተመታ እንዲሉ ካለበደሌ..."
ዝም በል! ደሞ አልበደልኩሽ ይላል” በለባጣ ሳቅ ተፍለቀለቀች። ጥርሶችዋ ያምራሉ! እያለቀሰች እንኳን አይኖችዋ
ያንፀባርቃሉ በጣቶችዋ
የምትበትነውኀፀጉሯም ውበቷን አላጎደለውም:
“ጤነኛ ነሽ? ለመሆኑ ከማን ጋር ለምን እንደምትነጋገሪ
ታውቂያለሽ?" አላት ትንሽ መረር ኮስተር ብሎ።
እሷ ግን “እብድ መሰልኩህ? እልኸኛ በመሆኔ በማስመሰያ ግብረገባዊነት በውስጤ የሚንተከተከውን ሃሳቤን ሳላፍን እንደ እሳተ ጎሞራ ፈንድቶ ሲወጣ እየለበለበኝ የሚፈሰው እንባዬን,
ስሜቴን በማካፈሌ እብድ በለኛ! ለነገሩ ማን መርምሮኝ ጤንነቴን
አውቀዋለሁ። አመመኝ ስል አውልቂ እባላለሁ... በሽታዬ ይገኛል እፈወሳለሁ ስል ጭኖቼ ተበርግደው ቆሻሻ ይደፉብኛል” ብላ
በትዝብትና ጥላቻ አየችው።
ከሴት ልጅ የምትፈልጉት ይህን ነው አይደል?!" ቀሚሷን ወደ ላይ ገለበችው:: ፈጣን አይኑ በለስላሳ ጭኖችዋ አልፎ
በለበሰችው ስስ ፓንት ያለውን ነገር ተመለከተ:
“...ይህን እንካ ብልህ እብድ ነሽ! አትለኝም ነበር። ከሃሣቤ ይልቅ ሳያስረዱህ የምታውቀው የስሜት ለሃጭህን የምታዝረከርከው
የሴት ልጅ ጭን ስታይ ነው አይደል!... ብሽቅ! አለችውና
ጭንቅላቷን ያዘች
“..እኔ ምንህም አይደለሁም. የአንተ እህት ግን ጓደኛዬ ናት። እንደ ሎሚ ተመጣ የምትጣል! ጭኖችዋን ለስሜት ሳይሆን ለገንዘብ የምትከፍት! የማታውቀውን ጠረን የምትታጠን... ለመሆኑ ስለእሷና ስለጓደኞችዋ አስበህ አዝነህ... ታውቃለህ? እህትህ ለተጠማው ወንድ ሁሉ በገንዘብ ተገዝታ የምትጠጣ መጠጥ
ተመልሳ ደግሞ እንደ ሽንት ቆሻሻ ላይ የምትሸና ጉድፍ መሆኗን ታውቃለህ?"
እህትህ' ስትል ነደደውና
ሶራ በጥሞና ሲያዳምጣት እንዳልቆዬ ሁሉ እህትህ
“የማን እህት?... የኔ... የኔ እህት?…" አፈጠጠባት: በንቀት እያየችው ቆየችና ረጋ ብላ፦
“ጠባብ በአብራh ክፋይ የምታምን ቂል. ሸርሙጣ እህት የለኝም እያልክ ያን የበከተ እምነትህን በመግለፅ ልትኮፈስ ይሆናል።''
“የኔ እህት ልትሰድቢኝ'ኮ…"
“ዝም በል አንተ?” ባረቀችበት።
“የተማርከው! እንደ ባንዲራ እየዘመራችሁ ወደላይ ስቀሉኝና አየሩ ላይ ልውለብለብ ንፁህ አየር ነፍሴን ያስደስታት የነዳያንን
ጩኸት ወደማልሰማበት ፉከታቸውን ወደማላይበት! ወደላይ ሽቅብ ልውጣ... ባይ ነህ አይደል! እንደ ብዙዎቹ ምስኪን ያገራችን
ምሁራን፡
“የኛ መማር ከድሃው Uዝብ በተለየ ደሴት ውስጥ ለመኖር ነው። የተማርነውን
ንድፈ ሃሳብ ኮሯጆችን ውስጥ ከተን አንጨምርበት አኝከን አንትፋው ስንውጠው አንታይ!... ብቻ
ተሸክመነው እላይ ወጥተን መውለብለብ ንግግሯን ገታ አድርጋ አየችው አያት፡ ተያዩ ምን እንደሚላት ጠፋው: ውጭልኝ ለማለትም ወኔ አጣ: እሷ ግን ቤቱን ደግማ አማተረች:: አይኗ
ከምኝታው ራስጌ ካለው ኮመዲኖ ባለው የሚማርh ፍሬም ላይ አረፈ።
“ምንድን ነው ይሄ?” ብላ ፈገግ እያለች በንቀት አየችው:
“የቱ?” አላት ወደራስጌው እየተመለከተ
"ዲግሪ ስትቀበል የተነሳኸው ፎቶ! አለችና ሳቀችበት።
“አያምርም! አየ አስተያየት አየ መልክ... አቤት ኩራት!
አሁንም የምፀት ሣቋን ለቀቀችው።
“...ምን ሰራሁበት ብለህ ነው ከራስጌህ ያስቀመጥከው?
መካኒክ የመካኒክነት ሙያ ንድፈ ሃሳብ በመማሩ መፍቻዎቹን ደረቱ
ላይ ደርድሮ ፎቶ ቢነሳ ምንድነው ትርጉሙ? ጉራ ብቻ! ሥራበት አዲስ ቅርፅ አዲስ ምርት አምርትበት ጠቅመህ ተጠቀምበት
የተባለውን መፍቻ እንደሰራው ሁሉ ደረቱ ላይ ደርድሮ ፎቶውን ገጭ አድርጎ ግድግዳው ላይ ቢሰቅለው ወይንም እንዳንተ ኮሚዲኖው ላይ ቢያስቀምጠው ፍችው ምንድነው?
ሶራ ተቁነጠነጠ ቀዝቃዛ ላብ በጆሮ ግንዱ ስር ተንቆረቆረ: “...ሌሎች የፈጠሩትን ለማወቅህ ሌሎች ያሉትን ለመስማትህ የተቀበልከውን መተማመኛ
የደረሰህን ለማዳረስ ቃለ መሃላ የፈፀምክበትን ጥቁር ጨርቅና ወረቀት ለሰራኸው ቁም ነገር ለፈፀምከው የስው ልጅ መልካም ተግባር እንደተሰጠህ ሁሉ ቀለሙ በሚጮህ ፍሬም ውስጥ ከተህ ለእይታ ዳረግኸው፡
“ማንነትህ እንዲታወቅ... ያልተማረ እንዳትባል... በሃሣብህ ጨቅላነት የናቀህ ፎቶህን አይቶ እንዲያከብርህ እንደ ፋሲካ ዶሮ አልጋህ ላይ ልታርዳት የምታመጣት ሴት ኧረ የተማረ ይግደለኝ
ብላ በንድፈ ሃሳብ ሞረድ በተሳለው ምላስህ ሳትፈራገጥ
እንድትታረድልህ... ነው አይደል! ዲግሪ የተቀበልክበትን ፎቶ ራስጌህ ያስቀመጥኸው:
“ስትሰራ ህዝቡን ስትረዳ.. የተነሳኸውማ ምን ማስታወሻ አለህ? ማረሻ የያዘና ባዶ እጁን የቆመ ሁለቱም አንዳች ሥራ
እስካልሰሩ ድረስ ምን ለውጥ አላቸው?
“ለመሆኑ ለምን እዚች አገር ተወለድሁ? ከኬንያ
ከታንዛንያ... ያነሰች ደሃ ተብላ በምትናቅ፤ እምትኮራበት ታሪክ
አንጂ ቤሳ ቤስቲኒ ስልጣኔ በሌለባት ሃገር ለምን ተፈጠርሁ ብለህ
ቀንተህ ታውቃለህ ከርሳም ጀብ ድሮ ጅብ ሆዱ ከሞላ በየት አገር ነው የሚቀናው: ሆዱ ከሞላ ባገኘው የቀበሮ ጉድጓድ ገብቶ መጋደም ነው: ክርፋቱ አይሸተው ጥንብ ነው ብሎ አይጠየፍ ስለ ማደሪያው አያስብ…
“በእንዳንተና እኔ አይነት ግዴለሾች ግን ችግር ችግር
እየተከመረ ዋጠን በህሊናና እጆቻችን ሰርተን ከመጠቀም ይልቅ
የህይወት ከርፋት ውስጥ ተጠቅልለን ማልቀስ መጮህ... እጣ ፈንታችን ሆነ" አላችና በሐዘን አንገቷን አቀረቀረች᎓ እንባዋ ዱብ
ዱብ ሲል ታየው: የመጣችበት ጉዳይና የምትናገርበት ምክንያት
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታሰ
እድላችን ነው: አሁን መነሳት ያለበት ጥያቂ አይደለም።
መልሉ የተሰጠ ጥያቄ ጥያቂ ሊሆን አይችልም
ይልቅስ ሁሉንም በፀጋ ተቀብሎ መኖር ነው" ለምን በምን. ላይ ያተኮረ
ሃሳብ ሃሳብ እንዳላት ሊገባው አልቻለም ስለዚህ ደስታው እየኮለመነ ግራ መጋባቱ እያየለ ሄደ።
“ልታነጋግሪኝ የፈለግሽው ምንድን ነው? ፈገግ ለማለት
እየሞከረ በጥሞና ጠየቃት:
“...እንደውሻ ቢያላዝኑ ሰሚ በሌለባት ምድር ለምን
ተወለድሁ! መወለዴን ሳስበው ይቆጨኛል! መሞቴም ያበሽቀኛል፤
ለምን ተወለድኩና ለምንስ ደግሞ እሞታለሁ። ስወለድም ለሞት
የምኖረውም ለሞት... አይኖችዋ ድንገት በእንባ ተጥለቀለቁና ቁልቁል ተደፋ: ያን ጊዜ ጨነቀው፡
የሚለበልበው እንባዋ
የማያውቃት ልጅ ድንገት እቤቱ መምጣቷ ብቻ አንሷት እንደበደላት ሁሉ ስታለቅስበት የሚይዘው የሚጨብጠው ጠፋው።
“የኔ እህት የሶራ ገልቻ ቤት የብሶት መወጫ የበደል
ማራገፊያ ነው ያለሽ ማን ነው?... ደግሞስ እንዲህ ስታለቅሺ ሰው ቢመጣ ምን ይላል? ልቅሶ ካማረሽ ብሶትሽን ማካፈል ከፈለግሽ...”ብሎ በውስጡ የተፈጠረውን ሃሳብ በአእምሮ አዘጋጅቶ ከመቋጨቱ በፊት አናጠባቸው:
“ወኔ ቢስ! ይህን ስትል አታፍርም አይደል! እልህ
ውስጥህ አይንጠውም አይደል! እዚች ሃገር መወለዴ እድሌ መሆኑ ጠፍቶኝ የጠየቅህ ይመስልሃል? እንዴት ያስጨነቀኝ ጥያቂ መለስህልኝ ባክህ ጅል!" ብላ በእልክ እያለቀሰች በስርዓት የተጠቀለለ ፀጉሯን ነጨችው።
“ቆይ እስኪ እንዴ
እኔ አልበደልኩሽ የኔ እህት: አይጥ በበላ ዳዋ ተመታ እንዲሉ ካለበደሌ..."
ዝም በል! ደሞ አልበደልኩሽ ይላል” በለባጣ ሳቅ ተፍለቀለቀች። ጥርሶችዋ ያምራሉ! እያለቀሰች እንኳን አይኖችዋ
ያንፀባርቃሉ በጣቶችዋ
የምትበትነውኀፀጉሯም ውበቷን አላጎደለውም:
“ጤነኛ ነሽ? ለመሆኑ ከማን ጋር ለምን እንደምትነጋገሪ
ታውቂያለሽ?" አላት ትንሽ መረር ኮስተር ብሎ።
እሷ ግን “እብድ መሰልኩህ? እልኸኛ በመሆኔ በማስመሰያ ግብረገባዊነት በውስጤ የሚንተከተከውን ሃሳቤን ሳላፍን እንደ እሳተ ጎሞራ ፈንድቶ ሲወጣ እየለበለበኝ የሚፈሰው እንባዬን,
ስሜቴን በማካፈሌ እብድ በለኛ! ለነገሩ ማን መርምሮኝ ጤንነቴን
አውቀዋለሁ። አመመኝ ስል አውልቂ እባላለሁ... በሽታዬ ይገኛል እፈወሳለሁ ስል ጭኖቼ ተበርግደው ቆሻሻ ይደፉብኛል” ብላ
በትዝብትና ጥላቻ አየችው።
ከሴት ልጅ የምትፈልጉት ይህን ነው አይደል?!" ቀሚሷን ወደ ላይ ገለበችው:: ፈጣን አይኑ በለስላሳ ጭኖችዋ አልፎ
በለበሰችው ስስ ፓንት ያለውን ነገር ተመለከተ:
“...ይህን እንካ ብልህ እብድ ነሽ! አትለኝም ነበር። ከሃሣቤ ይልቅ ሳያስረዱህ የምታውቀው የስሜት ለሃጭህን የምታዝረከርከው
የሴት ልጅ ጭን ስታይ ነው አይደል!... ብሽቅ! አለችውና
ጭንቅላቷን ያዘች
“..እኔ ምንህም አይደለሁም. የአንተ እህት ግን ጓደኛዬ ናት። እንደ ሎሚ ተመጣ የምትጣል! ጭኖችዋን ለስሜት ሳይሆን ለገንዘብ የምትከፍት! የማታውቀውን ጠረን የምትታጠን... ለመሆኑ ስለእሷና ስለጓደኞችዋ አስበህ አዝነህ... ታውቃለህ? እህትህ ለተጠማው ወንድ ሁሉ በገንዘብ ተገዝታ የምትጠጣ መጠጥ
ተመልሳ ደግሞ እንደ ሽንት ቆሻሻ ላይ የምትሸና ጉድፍ መሆኗን ታውቃለህ?"
እህትህ' ስትል ነደደውና
ሶራ በጥሞና ሲያዳምጣት እንዳልቆዬ ሁሉ እህትህ
“የማን እህት?... የኔ... የኔ እህት?…" አፈጠጠባት: በንቀት እያየችው ቆየችና ረጋ ብላ፦
“ጠባብ በአብራh ክፋይ የምታምን ቂል. ሸርሙጣ እህት የለኝም እያልክ ያን የበከተ እምነትህን በመግለፅ ልትኮፈስ ይሆናል።''
“የኔ እህት ልትሰድቢኝ'ኮ…"
“ዝም በል አንተ?” ባረቀችበት።
“የተማርከው! እንደ ባንዲራ እየዘመራችሁ ወደላይ ስቀሉኝና አየሩ ላይ ልውለብለብ ንፁህ አየር ነፍሴን ያስደስታት የነዳያንን
ጩኸት ወደማልሰማበት ፉከታቸውን ወደማላይበት! ወደላይ ሽቅብ ልውጣ... ባይ ነህ አይደል! እንደ ብዙዎቹ ምስኪን ያገራችን
ምሁራን፡
“የኛ መማር ከድሃው Uዝብ በተለየ ደሴት ውስጥ ለመኖር ነው። የተማርነውን
ንድፈ ሃሳብ ኮሯጆችን ውስጥ ከተን አንጨምርበት አኝከን አንትፋው ስንውጠው አንታይ!... ብቻ
ተሸክመነው እላይ ወጥተን መውለብለብ ንግግሯን ገታ አድርጋ አየችው አያት፡ ተያዩ ምን እንደሚላት ጠፋው: ውጭልኝ ለማለትም ወኔ አጣ: እሷ ግን ቤቱን ደግማ አማተረች:: አይኗ
ከምኝታው ራስጌ ካለው ኮመዲኖ ባለው የሚማርh ፍሬም ላይ አረፈ።
“ምንድን ነው ይሄ?” ብላ ፈገግ እያለች በንቀት አየችው:
“የቱ?” አላት ወደራስጌው እየተመለከተ
"ዲግሪ ስትቀበል የተነሳኸው ፎቶ! አለችና ሳቀችበት።
“አያምርም! አየ አስተያየት አየ መልክ... አቤት ኩራት!
አሁንም የምፀት ሣቋን ለቀቀችው።
“...ምን ሰራሁበት ብለህ ነው ከራስጌህ ያስቀመጥከው?
መካኒክ የመካኒክነት ሙያ ንድፈ ሃሳብ በመማሩ መፍቻዎቹን ደረቱ
ላይ ደርድሮ ፎቶ ቢነሳ ምንድነው ትርጉሙ? ጉራ ብቻ! ሥራበት አዲስ ቅርፅ አዲስ ምርት አምርትበት ጠቅመህ ተጠቀምበት
የተባለውን መፍቻ እንደሰራው ሁሉ ደረቱ ላይ ደርድሮ ፎቶውን ገጭ አድርጎ ግድግዳው ላይ ቢሰቅለው ወይንም እንዳንተ ኮሚዲኖው ላይ ቢያስቀምጠው ፍችው ምንድነው?
ሶራ ተቁነጠነጠ ቀዝቃዛ ላብ በጆሮ ግንዱ ስር ተንቆረቆረ: “...ሌሎች የፈጠሩትን ለማወቅህ ሌሎች ያሉትን ለመስማትህ የተቀበልከውን መተማመኛ
የደረሰህን ለማዳረስ ቃለ መሃላ የፈፀምክበትን ጥቁር ጨርቅና ወረቀት ለሰራኸው ቁም ነገር ለፈፀምከው የስው ልጅ መልካም ተግባር እንደተሰጠህ ሁሉ ቀለሙ በሚጮህ ፍሬም ውስጥ ከተህ ለእይታ ዳረግኸው፡
“ማንነትህ እንዲታወቅ... ያልተማረ እንዳትባል... በሃሣብህ ጨቅላነት የናቀህ ፎቶህን አይቶ እንዲያከብርህ እንደ ፋሲካ ዶሮ አልጋህ ላይ ልታርዳት የምታመጣት ሴት ኧረ የተማረ ይግደለኝ
ብላ በንድፈ ሃሳብ ሞረድ በተሳለው ምላስህ ሳትፈራገጥ
እንድትታረድልህ... ነው አይደል! ዲግሪ የተቀበልክበትን ፎቶ ራስጌህ ያስቀመጥኸው:
“ስትሰራ ህዝቡን ስትረዳ.. የተነሳኸውማ ምን ማስታወሻ አለህ? ማረሻ የያዘና ባዶ እጁን የቆመ ሁለቱም አንዳች ሥራ
እስካልሰሩ ድረስ ምን ለውጥ አላቸው?
“ለመሆኑ ለምን እዚች አገር ተወለድሁ? ከኬንያ
ከታንዛንያ... ያነሰች ደሃ ተብላ በምትናቅ፤ እምትኮራበት ታሪክ
አንጂ ቤሳ ቤስቲኒ ስልጣኔ በሌለባት ሃገር ለምን ተፈጠርሁ ብለህ
ቀንተህ ታውቃለህ ከርሳም ጀብ ድሮ ጅብ ሆዱ ከሞላ በየት አገር ነው የሚቀናው: ሆዱ ከሞላ ባገኘው የቀበሮ ጉድጓድ ገብቶ መጋደም ነው: ክርፋቱ አይሸተው ጥንብ ነው ብሎ አይጠየፍ ስለ ማደሪያው አያስብ…
“በእንዳንተና እኔ አይነት ግዴለሾች ግን ችግር ችግር
እየተከመረ ዋጠን በህሊናና እጆቻችን ሰርተን ከመጠቀም ይልቅ
የህይወት ከርፋት ውስጥ ተጠቅልለን ማልቀስ መጮህ... እጣ ፈንታችን ሆነ" አላችና በሐዘን አንገቷን አቀረቀረች᎓ እንባዋ ዱብ
ዱብ ሲል ታየው: የመጣችበት ጉዳይና የምትናገርበት ምክንያት
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ
፡
፡
#ዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፡
፡
#ክፍል_አራት
////
እንዳትሰማኝ ድምፄን ዝቅ አድርጌ‹‹የእውነት አድናቂሽ ነኝ"አልኩ ..እውነቴን ነው ግማሽ ጠርሙስ ውስኪ ብቻዋን ገልብጣ ገድገድ ሳትል ...እኔ ገና በግማሽ ብርጭቆ ጉልበቴ እየተብረከረከ ነው።
ተነሳሁና የተከፈቱ መስኮቶችን መዘጋጋት ጀመርኩ..ማብራቶችን አጠፍሁ፡፡ የሴትዬዎን ግማሽ ጠርሙስ ውስኪ ይዤ ወጣሁና የሆቴሉን በራፍ ቆልፌ ቁልፉን በጥንቃቄ ሚስጥር ኪሴ ውስጥ ሽጉጬ ወደ አልጋ ክፍል አመራሁ...አቀብያት በዛው ወደ ቤቴ ሄዳለሁ ሞባይሌን አውጥቼ ሰዓት ሳይ 7፡40 ይላል።
ደረስኩና አንኳኳሁ...
‹‹ግባ ክፍት ነው››
የሚል ድምፅ ስሰማ ቀስ ብዬ በራፍን ወደ ውስጥ ገፋ አደረኩትና ውስኪ ጠርሙስ የያዘ እጄን አስቀድሜ አንገቴን አሰገግኩ፡ መሀል ወለል ላይ ቆማ ተበትኖ ጀርባዋ ላይ የተኛውን ፀጉሯን አንድ ላይ ጠቅልላ እያሰረችው ነው..ቅድም ለብሳ የነበረውን ጅንስ ሱሪ አውልቃ ስስ የለሊት ቢጃማ ቀሚስ ለብሳለች...፡፡ ቢጃማው ሮዝ ቀለም ሲኖረው አጭር እና በቀላሉ አይን ውስጥ የሚመሰግ ነው...አስተውሎ ላየው ቀሚስ ሳይሆን ቁምጣ ነው የሚመስለው..እና ያ የሚንቀጠቀጥ እና ሊፈርጥ የደረሰ ዳሌዋ በከፊል እርቃን ነው...፡፡
"በራፍ ላይ ተገትረህ ታድራለህ ወይስ ትገባለህ ?"
"እ እሺ ገባለሁ ››አልኩና ወደውስጥ ገብቼ ጠርሙሱን ጠረጴዛ ላይ አስቀምጬ ለመውጣት ዞር ስል እሷ ከቦታዋ ተንቀሳቅሳ ወደበራፍ እያመራች ነው፡፡
‹‹...ብርድ አስመታሀኝ ››"በሚል ሰበብ ክፍት ጥዬ የመጣሁትን በራፍ ዘጋችና ቆለፈችው፡፡
"ቆይ እኔ ሳልወጣ?"አልኩ ደንግጬ፡፡
"ትንሽ አጣጣኝ እና ትሄዳለህ.. ያውልህ ብርጭቆ…
"ቅዳልኝ" የንግግሯ ቃና ወደ ትዕዛዝ ያዘነበለ ነው.፡፡
ግራ በመጋባትና በመርበትበት እንዳለቺኝ አደረኩና እዛው ጠረጴዛ ጎን ያለ ደረቅ ወንበር ላይ ቁጭ አልኩ..፡፡እሷም ወደእኔ መጣችና ብርጭቆዋን አንስታ አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጠች ...፡፡አቀማመጧ በእኔ ትክክል ነው...፡፡አይኔ ወደታች ወደተጋለጠው ጭኗ እየተንሸራተተ አስቸገረኝ ፡፡...እሷ የእኔን ሁኔታ ከቁብም የቆጠረች አይመስልም፡፡ጭኗ እንደሴቶች ጭን ልል እና ለስላሳ አይደለም…፡፡እንደስፖርተኛ የዳበረ እና ፈርጣማ ነው፡፡ሲነኩት ትንቡክ የሚል አይነት ሳይሆን ሲነካ ጭፍልቅ የሚያደርግ አይነት፡፡
"አሁን ጋሼ እንዲህ ከእንግዳ ጋር በውድቅት ለሊት ቤርጎ ውስጥ ገብቼ ዘና ስል ቢያየኝ ምን ይለኛል? ጓደኞቼስ ቢያዩ ተረባቸውን እችለዋለሁ?››
በዝምታ ውስጥ ሆና የቀዳሁላትን ጠጥታ ጨረሰችና ከተቀመጠችበት ተነስታ እራሷ ለራሷ ቀዳች ፡፡..ልትቀዳ ስትል ታከከቺኝ..እናም ደግሞ የተቀባችው ሽቶ ያለፍላጎቴ በአፍንጫዬ ሰርጎ ገባ...እና እየጠጣሁ ካለሁት መጠጥ ጋር ተጋግዞ አነቃቃኝ...፡፡
ወደቦታዋ ተመልሳ ተቀመጠች ፡፡አቀማመጧ ግን እንደቅድሙ እግሮቿን አጣምራ ሳይሆን ፈርክክ አድርጋ ከፍታ ነው፡፡ ...እና በክፍተቱ አይንን ሚያጥበረብር ቀይ ፓንት አየሁ..፡፡ለምን አየህ ?ብላ ተነስታ የምታንቀኝ መስሎኝ ከመርበትበቴ የተነሳ ብርጭቆ ውስጥ ያለችውን መጠጥ በአንድ ትንፍሽ ገርገጭ አድርጌ አጋባኋት፡፡
"በቃ እግዜር ይስጥልኝ አሁን መሸብኝ ልሂድ..›› ለማለት አስቤ ገና አፌን ሳልከፋት ከተቀመጠችበት ተነስታ በድጋሚ ቀዳችልኝ፡፡ ..ለመናገር የተከፈተ አፌን ቀስ ብዬ ዘጋሁትና አንዴ መጠጡን አንዴ እሷን እያፈራረቅኩ ማየት ጀመርኩ።"አሁን ብዥ እያለብኝ ነው..፡፡ሞባይሌን አወጣሁና ሰዓት ተመለከትኩ...8:18 ይላል።
"ምነው መሸብህ እንዴ?"
"አይ አንቺን እንቅልፍ ነሳሁሽ ብዬ ነው"
"ጥሩ አስመሳይ ነህ"አለችኝ.፡፡
‹‹እስቲ በጌታ አሁን እንዲህ ይባላል?››አንገቴን በእፍረት ከማቀርቀር ውጭ ምንም መልስ አልሰጠኋትም፡፡ከተቀመጠችበት ተነሳችና ወደሻንጣዋ በመሄድ መጎርጎር ጀመረች‹‹...ምን ልትሰጠኝ ነው?"ብዬ ሳሰላስል ክሬም ቅባት አወጣችና አልጋ ላይ ወረወረች..መቀመጫዋን ወደ እኔ ፊቷን በተቃራኒው ወደግድግዳው አዞረችና በቆመችበት አጭሩን የለሊት ቀሚሷን ሞሽልቃ አወለቀች።አይኖቼን ጨፈንኩ..ገለጥኩ...መልሼ ጨፈንኩ...ቅድም በስሱ ካየሁት ቀይ ፓንት በስተቀር ምንም የጨርቅ ዘር በሰውነቷ አልቀረም....፡፡ጡቶቾ እንደሩሲያ አስፈሪ ሚሳዬሎች ጫፋቸውን ወደእኔ ቀስረው ልቤን አራዷት ብላችሁ ደስ ይለኝ ነበር፡፡ ግን እየታዩኝ አይደለም፡፡ፐ!! ከኃላዋ የሚታየው የሰውነቷ ቅርፅ ግን ከአንገቷ በላይ ያለውን መልኳን በሁለት ሶስት እጥፍ ይበልጣል።
ዘለህ ተጠምጠምባት የሚል ስሜት ከሁሉም የስሜት ህዎሳቶቼ ተሰባስቦ ጉሮሮዬ ላይ ተወተፈብኝ... እጇቼ ገላዋን ለመዳሰስ አይኖቼ ከግራ ወደቀኝ እያገላበጠ መላ ሰውነቷን በምስጠት ለመመልከት፤ አፍንጫዬ አንገቷ ስር ተደፍቶ ጠረኗን ወደውስጥ መማግ፤ጆሮዎቼ አፍ አካባቢ ተለጥፈው ከአንደበቷ የሚወጣውን ሹክሹክታ በፅሞና ለማዳመጥ እና እንትኔ ደግሞ ጭኖቾን ፈልቅቆ ወደ ውስጠቷ መስመጥ ፈለገ(ውይ እንትኔ ለካ የስሜት ህዋሳቴ አይደለም...ነው እንዴ?)
ዘፍ ብላ በሆዷ አልጋው ላይ ተኛች...አሁን በህይወቴ በአካልም በፊልምም ጭምር ካየኋቸው ባለ እርቃን ሴቶች ሁሉ ተወዳዳሪ የሌላት ፍፅም አማላይ ሆና ታየችኝ፡፡.. ፀጉሯ ብትን ብሎ ከፊል ጀርባዋን እና የተንተራሰችበትን ትራስ ሸፍኖታል..፡፡ከዛ ወረድ ስንል ልምጥ ብሎ የሚታየው ወገቧ የሩብ ጨረቃን ቅርፅ ይዞ አይንን ያፈዛል ፡፡..ከዛ ሽቅብ ወደላይ ስንወጣ መቀመጫዋ ቀይ ፅጌረዳ አበባ የሸፈናቸው ግዙፍ መንታ ተራሮች ይመስላሉ፡፡..ከዛ በመነሳት ለሁለት ተከፍለው የተዘረጉት እግሮቾ ለምለም መስክ ላይ የተዘረጋ የአክሱም ሀውልትን ይመስላሉ...እጣቶቾ ደግሞ....
"ትንሽ እሸኝና ትሄዳለህ.."የሚለው ንግግሯ ስለውበቷ ተቀኝቼ ሳልጨርስ ከሀሳቤ አናጠበኝ።
" ሎሺኑን ተጠቀምና እሸኝ.."ደገመችልኝ።
"እሸኝ ማለት ምን ማለት ነው..?እንዴት ነው የማሻት..?የሚታሽና የማይታሽ የሠውነት ክፍል ይኖራት ይሆን ?ካሸዋትስ በኃላ የሚከተል ነገር ይኖራል..?በሰከንድ ውስጥ በምናቤ ብልጭ ድርግም ያሉ ወሳኝ ጥያቄዎች ናቸው..፡፡እጆቼን ሰበሰብኩና ወደአልጋው ተራመድኩ፡፡ ጠርዝ ላይ ተመቻችቼ ተቀመጥኩ..፡፡ጃርባዋን ያለበሰውን ፀጉሯን ሰበሰብኩና ወደትራሱ አሻገርኩት...እና ሎሺኑን አነሳሁና ጨመቅ ጨመቅ አድርጌ እጄ ላይ አፈሰስኩና ከትከሻዋ ጀመርኩ...፡፡ይህ ሰውነት ከዚህ በፊት እንደማውቃቸው የሴት ገላዎች የሀር ጨርቅ አይነት ልስላሴ የለውም..፡፡በዳበሩ ጡንቻዎች የተገነባና በጠንካራ ቆዳ የተሸፈነ ልዩ አይነት ሰውነት ነው፡፡ቢሆንም ሲያሹት እጅን ሙልጭ ሙልጭ እያደረገ ቢፈታተንም ደስ ይላል፡፡ ‹‹ አዎ ትግስት ካለኝ ተገልብጣ በጀርባዋ ስትተኛና ከፊት ለፊቷ ያለውን የሰውነት ክፍሏን እንዳሻት ስትመቻችልኝ ቀስ ብዬ ልክ እንደዚህ ሎሺን ጡቶቾን አሸት አሸት እያደረኩ ከውስጣቸው ፍቅር እንዲያመነጩ አስገድዳቸዋለሁ፡፡›› ስል በአይነ ህሊናዬ በመሳል ጎመዣሁ..ምራቄን ገርገጭ እያደረግኩ ዋጥኩ ።
፡
፡
#ዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፡
፡
#ክፍል_አራት
////
እንዳትሰማኝ ድምፄን ዝቅ አድርጌ‹‹የእውነት አድናቂሽ ነኝ"አልኩ ..እውነቴን ነው ግማሽ ጠርሙስ ውስኪ ብቻዋን ገልብጣ ገድገድ ሳትል ...እኔ ገና በግማሽ ብርጭቆ ጉልበቴ እየተብረከረከ ነው።
ተነሳሁና የተከፈቱ መስኮቶችን መዘጋጋት ጀመርኩ..ማብራቶችን አጠፍሁ፡፡ የሴትዬዎን ግማሽ ጠርሙስ ውስኪ ይዤ ወጣሁና የሆቴሉን በራፍ ቆልፌ ቁልፉን በጥንቃቄ ሚስጥር ኪሴ ውስጥ ሽጉጬ ወደ አልጋ ክፍል አመራሁ...አቀብያት በዛው ወደ ቤቴ ሄዳለሁ ሞባይሌን አውጥቼ ሰዓት ሳይ 7፡40 ይላል።
ደረስኩና አንኳኳሁ...
‹‹ግባ ክፍት ነው››
የሚል ድምፅ ስሰማ ቀስ ብዬ በራፍን ወደ ውስጥ ገፋ አደረኩትና ውስኪ ጠርሙስ የያዘ እጄን አስቀድሜ አንገቴን አሰገግኩ፡ መሀል ወለል ላይ ቆማ ተበትኖ ጀርባዋ ላይ የተኛውን ፀጉሯን አንድ ላይ ጠቅልላ እያሰረችው ነው..ቅድም ለብሳ የነበረውን ጅንስ ሱሪ አውልቃ ስስ የለሊት ቢጃማ ቀሚስ ለብሳለች...፡፡ ቢጃማው ሮዝ ቀለም ሲኖረው አጭር እና በቀላሉ አይን ውስጥ የሚመሰግ ነው...አስተውሎ ላየው ቀሚስ ሳይሆን ቁምጣ ነው የሚመስለው..እና ያ የሚንቀጠቀጥ እና ሊፈርጥ የደረሰ ዳሌዋ በከፊል እርቃን ነው...፡፡
"በራፍ ላይ ተገትረህ ታድራለህ ወይስ ትገባለህ ?"
"እ እሺ ገባለሁ ››አልኩና ወደውስጥ ገብቼ ጠርሙሱን ጠረጴዛ ላይ አስቀምጬ ለመውጣት ዞር ስል እሷ ከቦታዋ ተንቀሳቅሳ ወደበራፍ እያመራች ነው፡፡
‹‹...ብርድ አስመታሀኝ ››"በሚል ሰበብ ክፍት ጥዬ የመጣሁትን በራፍ ዘጋችና ቆለፈችው፡፡
"ቆይ እኔ ሳልወጣ?"አልኩ ደንግጬ፡፡
"ትንሽ አጣጣኝ እና ትሄዳለህ.. ያውልህ ብርጭቆ…
"ቅዳልኝ" የንግግሯ ቃና ወደ ትዕዛዝ ያዘነበለ ነው.፡፡
ግራ በመጋባትና በመርበትበት እንዳለቺኝ አደረኩና እዛው ጠረጴዛ ጎን ያለ ደረቅ ወንበር ላይ ቁጭ አልኩ..፡፡እሷም ወደእኔ መጣችና ብርጭቆዋን አንስታ አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጠች ...፡፡አቀማመጧ በእኔ ትክክል ነው...፡፡አይኔ ወደታች ወደተጋለጠው ጭኗ እየተንሸራተተ አስቸገረኝ ፡፡...እሷ የእኔን ሁኔታ ከቁብም የቆጠረች አይመስልም፡፡ጭኗ እንደሴቶች ጭን ልል እና ለስላሳ አይደለም…፡፡እንደስፖርተኛ የዳበረ እና ፈርጣማ ነው፡፡ሲነኩት ትንቡክ የሚል አይነት ሳይሆን ሲነካ ጭፍልቅ የሚያደርግ አይነት፡፡
"አሁን ጋሼ እንዲህ ከእንግዳ ጋር በውድቅት ለሊት ቤርጎ ውስጥ ገብቼ ዘና ስል ቢያየኝ ምን ይለኛል? ጓደኞቼስ ቢያዩ ተረባቸውን እችለዋለሁ?››
በዝምታ ውስጥ ሆና የቀዳሁላትን ጠጥታ ጨረሰችና ከተቀመጠችበት ተነስታ እራሷ ለራሷ ቀዳች ፡፡..ልትቀዳ ስትል ታከከቺኝ..እናም ደግሞ የተቀባችው ሽቶ ያለፍላጎቴ በአፍንጫዬ ሰርጎ ገባ...እና እየጠጣሁ ካለሁት መጠጥ ጋር ተጋግዞ አነቃቃኝ...፡፡
ወደቦታዋ ተመልሳ ተቀመጠች ፡፡አቀማመጧ ግን እንደቅድሙ እግሮቿን አጣምራ ሳይሆን ፈርክክ አድርጋ ከፍታ ነው፡፡ ...እና በክፍተቱ አይንን ሚያጥበረብር ቀይ ፓንት አየሁ..፡፡ለምን አየህ ?ብላ ተነስታ የምታንቀኝ መስሎኝ ከመርበትበቴ የተነሳ ብርጭቆ ውስጥ ያለችውን መጠጥ በአንድ ትንፍሽ ገርገጭ አድርጌ አጋባኋት፡፡
"በቃ እግዜር ይስጥልኝ አሁን መሸብኝ ልሂድ..›› ለማለት አስቤ ገና አፌን ሳልከፋት ከተቀመጠችበት ተነስታ በድጋሚ ቀዳችልኝ፡፡ ..ለመናገር የተከፈተ አፌን ቀስ ብዬ ዘጋሁትና አንዴ መጠጡን አንዴ እሷን እያፈራረቅኩ ማየት ጀመርኩ።"አሁን ብዥ እያለብኝ ነው..፡፡ሞባይሌን አወጣሁና ሰዓት ተመለከትኩ...8:18 ይላል።
"ምነው መሸብህ እንዴ?"
"አይ አንቺን እንቅልፍ ነሳሁሽ ብዬ ነው"
"ጥሩ አስመሳይ ነህ"አለችኝ.፡፡
‹‹እስቲ በጌታ አሁን እንዲህ ይባላል?››አንገቴን በእፍረት ከማቀርቀር ውጭ ምንም መልስ አልሰጠኋትም፡፡ከተቀመጠችበት ተነሳችና ወደሻንጣዋ በመሄድ መጎርጎር ጀመረች‹‹...ምን ልትሰጠኝ ነው?"ብዬ ሳሰላስል ክሬም ቅባት አወጣችና አልጋ ላይ ወረወረች..መቀመጫዋን ወደ እኔ ፊቷን በተቃራኒው ወደግድግዳው አዞረችና በቆመችበት አጭሩን የለሊት ቀሚሷን ሞሽልቃ አወለቀች።አይኖቼን ጨፈንኩ..ገለጥኩ...መልሼ ጨፈንኩ...ቅድም በስሱ ካየሁት ቀይ ፓንት በስተቀር ምንም የጨርቅ ዘር በሰውነቷ አልቀረም....፡፡ጡቶቾ እንደሩሲያ አስፈሪ ሚሳዬሎች ጫፋቸውን ወደእኔ ቀስረው ልቤን አራዷት ብላችሁ ደስ ይለኝ ነበር፡፡ ግን እየታዩኝ አይደለም፡፡ፐ!! ከኃላዋ የሚታየው የሰውነቷ ቅርፅ ግን ከአንገቷ በላይ ያለውን መልኳን በሁለት ሶስት እጥፍ ይበልጣል።
ዘለህ ተጠምጠምባት የሚል ስሜት ከሁሉም የስሜት ህዎሳቶቼ ተሰባስቦ ጉሮሮዬ ላይ ተወተፈብኝ... እጇቼ ገላዋን ለመዳሰስ አይኖቼ ከግራ ወደቀኝ እያገላበጠ መላ ሰውነቷን በምስጠት ለመመልከት፤ አፍንጫዬ አንገቷ ስር ተደፍቶ ጠረኗን ወደውስጥ መማግ፤ጆሮዎቼ አፍ አካባቢ ተለጥፈው ከአንደበቷ የሚወጣውን ሹክሹክታ በፅሞና ለማዳመጥ እና እንትኔ ደግሞ ጭኖቾን ፈልቅቆ ወደ ውስጠቷ መስመጥ ፈለገ(ውይ እንትኔ ለካ የስሜት ህዋሳቴ አይደለም...ነው እንዴ?)
ዘፍ ብላ በሆዷ አልጋው ላይ ተኛች...አሁን በህይወቴ በአካልም በፊልምም ጭምር ካየኋቸው ባለ እርቃን ሴቶች ሁሉ ተወዳዳሪ የሌላት ፍፅም አማላይ ሆና ታየችኝ፡፡.. ፀጉሯ ብትን ብሎ ከፊል ጀርባዋን እና የተንተራሰችበትን ትራስ ሸፍኖታል..፡፡ከዛ ወረድ ስንል ልምጥ ብሎ የሚታየው ወገቧ የሩብ ጨረቃን ቅርፅ ይዞ አይንን ያፈዛል ፡፡..ከዛ ሽቅብ ወደላይ ስንወጣ መቀመጫዋ ቀይ ፅጌረዳ አበባ የሸፈናቸው ግዙፍ መንታ ተራሮች ይመስላሉ፡፡..ከዛ በመነሳት ለሁለት ተከፍለው የተዘረጉት እግሮቾ ለምለም መስክ ላይ የተዘረጋ የአክሱም ሀውልትን ይመስላሉ...እጣቶቾ ደግሞ....
"ትንሽ እሸኝና ትሄዳለህ.."የሚለው ንግግሯ ስለውበቷ ተቀኝቼ ሳልጨርስ ከሀሳቤ አናጠበኝ።
" ሎሺኑን ተጠቀምና እሸኝ.."ደገመችልኝ።
"እሸኝ ማለት ምን ማለት ነው..?እንዴት ነው የማሻት..?የሚታሽና የማይታሽ የሠውነት ክፍል ይኖራት ይሆን ?ካሸዋትስ በኃላ የሚከተል ነገር ይኖራል..?በሰከንድ ውስጥ በምናቤ ብልጭ ድርግም ያሉ ወሳኝ ጥያቄዎች ናቸው..፡፡እጆቼን ሰበሰብኩና ወደአልጋው ተራመድኩ፡፡ ጠርዝ ላይ ተመቻችቼ ተቀመጥኩ..፡፡ጃርባዋን ያለበሰውን ፀጉሯን ሰበሰብኩና ወደትራሱ አሻገርኩት...እና ሎሺኑን አነሳሁና ጨመቅ ጨመቅ አድርጌ እጄ ላይ አፈሰስኩና ከትከሻዋ ጀመርኩ...፡፡ይህ ሰውነት ከዚህ በፊት እንደማውቃቸው የሴት ገላዎች የሀር ጨርቅ አይነት ልስላሴ የለውም..፡፡በዳበሩ ጡንቻዎች የተገነባና በጠንካራ ቆዳ የተሸፈነ ልዩ አይነት ሰውነት ነው፡፡ቢሆንም ሲያሹት እጅን ሙልጭ ሙልጭ እያደረገ ቢፈታተንም ደስ ይላል፡፡ ‹‹ አዎ ትግስት ካለኝ ተገልብጣ በጀርባዋ ስትተኛና ከፊት ለፊቷ ያለውን የሰውነት ክፍሏን እንዳሻት ስትመቻችልኝ ቀስ ብዬ ልክ እንደዚህ ሎሺን ጡቶቾን አሸት አሸት እያደረኩ ከውስጣቸው ፍቅር እንዲያመነጩ አስገድዳቸዋለሁ፡፡›› ስል በአይነ ህሊናዬ በመሳል ጎመዣሁ..ምራቄን ገርገጭ እያደረግኩ ዋጥኩ ።
#የዘርሲዎች_ፍቅር
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
፡
፡
#ክፍል_አራት
ዘርሲዎች ግማሽ ክብ ሰርተው ከመንደሩ ራቅ ብላ ዙሪያ ገቡን ከምታሳየው
የግራር ዛፍ ስርቁጭ ብለዋል ጩሉሌዎች
አንገታቸውን ቁልቁል ደፋ አድርገው በዛ ዙሪያ ያንዣብባሉ: ነፋሱ
ቅጠሎችን ጎንበስ ቀና እያደረገ ይነፍሳል
ከፊት ለፊታቸው ርጥብ
ቅጠል ተነጥፏል መሃል ላይ ጎረምሶች የተጠበሰውን የፍየል ስጋ እየቆራረጡ የፍሪንባውን ሥጋ በእድሜ ለገፉትና በጀግንነታደው ለሚታወቁት ለሌሎች ደግሞ ከተለያየውደ የስጋ አይነት እፊት ለፊታቸው ካለው ቅጠል አስቀመጡ" ህፃናት ጨዋታቸውን አቁመው ራቅ ብለው ሲቁለጨለጩ ቆይተው እደላው አልቆ መብሉ ሲጀመር ወደየአባቶቻቸው ጉያ ተሸጉጠው ዳረጎታቸውን እየተቀበሉ ከአጥንት ጋር መታገል ጀመሩ በመጨረሻ የሚበላው ከተበላ: ቀሪውን ደግሞ ጎረምሶቹ ካቀለጣጠፉት በኋላ ወጣቶቹ ቅጠሉን ሰብስበው ጥለው
ከስብሰባው አካባቢ ርቀው ሄዱ።
የሽማግሎች አለቃ ጦራቸውን ይዘው ከተቀመጡበት ተነስተው
ከፈርሱ እግራቸውን ቀባ አድርገው ወዲህ ወዲያ ወዲያ ወዲህ አሉና፣
"የአባት ደንብ ጥሩ ነው" በልክ መብላት የአባቶቻችን ባህል ነው አባቶቻችን የራበውና የጠገበ ትክክል ፍርድ አይሰጥም ይሉ
ነበር" የጠገበ ወንድ ሴት ማለት ነው መሳቅ ቧልት ይወዳል ከብቶችን አይፈቅድም ጫካውን አይቃኝም ከጓደኞቹ ጋር
አይመክርም መዝለል አይችልም መቀመጥና ማንጎላጀት ይወዳል
ትክክለኛ ፍርድ በዚህ ምክንያት አይሰጥም ይሉ ነበር አባቶቻችን" ሽማግሌው እቱፍ: እቱፍ
ብለው የጦሩን ዘንግ በምራቃቸው ቀባ ቀባ እያደረጉ ሽማግሎችን:
የአባታቸውን አገር አድማስ እየተዟዟሩ አይተው
አባቶቼ የራበውም ከጠገበ አይሻልም ይሉ ነበር የራበው ሰው ሰነፍ ነው
ሲኖረው አያውቅበትም
የወደቀችው ጀንበር:
የጠፋችው ጨረቃ ተመልሰው የሚመጡ
አይመስሉትም እንደ
አጋሰስ ፈረስ ዘመዶቹ ለመቋቋሚያ የሰጡትን ፍየሉንም፥ በጉንም
ከብቱንም: እህሉንም ብቻውን እየበላ ነገን ዘንግቶ: ልጆቼ: የአባቴ
ምክር ሳይል ሁሉን ያሟጥጥና የሚያልበው ሲያጣ የሚበላው
ሲቸግረው ሰውን: መሬቷን: ቦርጆን: አባቶቹን ይራገማል" ሆዱን
ለመሙላት ይቀማል ይዋሻል … ፍቅር አያውቅም ዘመድ ወገን አይለይም
አያስተውልም፤ ጨካኝ ነው
በዚህ ምክንያት
አባቶቻችን የራበው ሰው ትክክል አይፈርድም ይሉ ነበር አባቶቻችን ትክክል ናቸው ወንድሞቼ ጥጋብ ልቦናን ያዛባል ረሃብ ደግሞ ተስፋ መቁረጥንና ጥላቻን ያመጣል ከሁሉም የሚከፋው ደግሞ ሁለቱም ያስዋሻሉ" ብለው በርኮታቸው ላይ ቁጭ አሉ
ዝምታው ቀጠለ ሐመር ላይ ተረትን ሽማግሌ ለሌላው ማስታወስ እንጂ አይጨርሰውም የሰሙት እኩል: የፈፀሙት እኩል … ስለሆነ ተረት ጨራሽ አዳማጭ የለውም"
"በሉ ተናገሩ?" አሉ ሽማግሌው ከጥቂት ቆይታ በኋላ ጥሩ ነው! ከወደ መሃል አንዱ ድምፅ አሰሙ ገልመጥ ብሎ ያዬ የለም ሁሉም ግን አባባላቸውን በጆሮው ቀልቧል።
"ጥሩ ነው!- በአካል ተለይተውን ነፍሶቻቸው ደንቡን ጥበቃ አብረውን ላሉት ወንድሞቻችን ተገቢው ደንብ የሚሰራበት
ቀን ይመረጥ ልጆቻቸውና ሚስቶቻቸው በየበረሃው የአሉትን ተባት በግና ፍየሎች ከብቶችን ያስመጡ" በየመንደሩ ለሚኖሩት ዘመድ ጓደኞችም ጥሪ ይላክ ለዚያ ደሞ ዛሬ ቀኑ ተቆርጦ ቋጠሮ ይዘጋጅ አሉ።
የሽማግሎች አለቃ ሌላ ኃሳብ አለመኖሩን በዝምታደ ጠበቁና አንድ ጎረምሳ ጠርተው ልጥ አምጣ አንተ" አሉት ልጡ መጣ
"ስንት ላይ ይቋጠር?"
"መከን ተቢ" አሉ አንድ ሽማግሌ በስተግራ በኩል
ከተቀመጡት ሰላሳ ለማለት ልጡ ሰላሳ ላይ ተቋጥሮ ለሟቹ ታናሽ ወንድም
ተሰጠው" የሽማግሎች አለቃ አንዱን ችግር
በመቋጨታቸው
"ባይሮ ኢሜ" አሉ ሽማግሎችን እግዜር
ይስጣችሁ ለማለት
"በሉ ቀጥሉ?" አሉ የስብሰባው መሪ
"ጥሩ ነው!" አለ ልጅ እግሩና የአባቱን ጠላት ገሎ በቅርቡ
ከሽማግሌዎች ጋር ለመቀመጥ እድል ያገኘው ሰለምቤ፤ "ጥሩ ነው!
ታለውሻ በቀር አባቶቻችን ከአውሬ ጋር አልኖሩም እና ካርለቴ ይዛብን የመጣችውን አውሬ በጥይት አጉኖ ራቅ አድርጎ መቅበር ነው "አለ ገና የጎረምሳነት ባህሪው ሙሉ በሙሉ ያልቀዘቀዘለት ወጣቱ ሽማግሌ አለመብሰሉ በአነጋገሩ ፍጥጥ ብሎ እየታየበት።
"ጥሩ ነው! አውሬ ማለት ከብት የሚበላ ችግር የሚፈጥር ነው የነጯ ሐመር የካርለቴ አራት እግር አውሬ ሳይሆን መሂና
ነው የሚባል አባቶቻችን ደሞ መሂና የሚባል አውሬ አለ አላሉንም ደሞስ የካርለቴ መሂና እንደ ፈረስ እየጫነን ገበያ እያመላለሰን ነው እና መኖሩ ምን ጎዳ! አሉ ግራሯን የተደገፉት አንድ ዐይና
የአባት ደንብ እየሻርን ያ ይጎዳል ይሄ ይጠቅማል
ካልንማ ይህች አገርና ይህ ህዝብ መዓት ይመጣበታል" በነሱ ጊዜ ያልነበረ አውሬ አሁንም መኖር የለበትም " አሉ አገጫቸውን በግራ
እጃቸው ደግፈው የቆዩት ሽማግሌ ከዚያ ክርክሩ ከተለያዬ አቅጣጫ
መቅረቡ ቀጠለ
በአባቶቻችን ደንብ ፍየል ቢመጣ ፍየል ጋጥ: ከብት
ቢመጣ ከብቶች በረት ሰው ቢመጣ ወደ ሰዎች መኖሪያ ጎጆ ይገባል እህ እንዲህ እስተሆነ ድረስ የካርለቴ መሂና የሚገባ
ፍየሎች ጋጥ ነው? ከከብቶች በረት ነው? ወይንስ ከሰዎች ጋር ጎጆ
ውስጥ! መቼም ተውሾች ጋር እየተሯሯጠ አውሬና ጠላት ይከላከላል
አይባል ይኑር ከተባለ ወገኑ ከማን ነው? ተከብቶቹ ወይንስ ከእኛ! አሉ ከወደመሀል መፋቂያቸውን ሲያኝኩ የቆዩት ሽማግሌ
"ጥሩ ነው የሁላችሁም አስተያየት አዲስ ነገር መምጣቱ ይኸው ሁለት ሶስት ቦታ ከፋፍሎ አጨቃጨቀን ያልነበረ ነገር
ሲመጣ ያልነበረ ችግር ይፈጥራል ነጯ ሐመር የእኛ የሆነች እንግዳ ናት መሂና ያለችውን አውሬ ዱካውን ለማጥፋት በጥይትና ጦር
ደብድበን እንቅበረው ብንል እሷን እናሳዝናት ይሆናል"
ባይሆን አውሬሽን ካመጣሽበት ጫካ ጥለሽ ነይ ብንላት አይሻልም
ወንድሞቼ!" አሉ። አንተነህ ይመር ጋልታምቤ ጎን የተቀመጡት ሽማግሌ
ተው! ተው! ይህችን ሰው ተማበራችን አታውጧት! እሷ
ሐመር ናት የሐመር ልጃገረድ ተቀብላማ እንደ እህቶችዋ የፍየል ቆዳ ለብሳ ለዘመዷ ለከሎ ከብት
የአባቷን ትክክለኛ ደንብ
ዝላይ ተገርፋ … እንዴት እንዴት ነው እንደውጭ ሰው ይከፋታል ማለት! ከአባትሽ ባህልና ደንብ ውጭ ያመጣሽው አውሬ ቦርጆን ያስከፋል የአባቶቻችንንም ነፍስ ያሳዝናል እነሱ ተቆጥተው ዝናብ ከሚያጠፉብን በሽታ ከሚልኩብን አውሬሽን ቀብረነው እንረፍ
ብንላት በፍጡም አይከፋትም ወዲያውስ ከሽማግሌ ቃል ወጥታ የት ልትደርስ ኧረ አይከፋትም!" አሉ የዘርሲዎች አለቃ ከዚያ ለረጅም ጊዜ ዝምታ ሰፍኖ ቆየ
"ጥሩ ነው! እንዳላችሁትም
ነጯ ሐመር የእኛ ናት, የእኛ
ያልሆነውን ግን ዝም ብለን ብንለቀው ምን እንደሚያመጣ አናውቅም ሲቆይ ልጆቻችንን እሷን ጨምሮ: እኛን ይተናኮስ
አይተናኮስ ሳናውቅ እናጥፋው እስከተባባልን
ድረስ በኋላ ለቀን
ከምናሳድድ እዚሁ ገራም መስሎ አጠገባችን እንዳለ አድብቶ በጥይት ማጎን ነው የሚበጀው ካለበለዚያ
እኮ አስተውላችሁት እንደሁ
አላውቅም እንጂ አጉረምርሞ አጉረምርሞ ሰውነቱ የጋለ እንደሆን
እንደ ጥይት ከተፈተለከ
ድንጋይ አይል ውሃ ... ማን ጀግና ያቆመዋል! ስለዚህ ሳይደነብር አዋዝተው ጎረምሶች በክላሽ ጥይት
ሆድቃውን እንዲነድሉት ማድረግ ነው"" እንዳሉ
"ይህስ እውነት ነው! በቀደም ሳላየው ሩም … ብሎ ባጠገቤ ቢያልፍ የድምፁ ወላፈን እንዴት አሽቀንጥሮ ወረወረኝ መሰላችሁ ተዚያ ንዴቱ ይሁን ድንጋጤው ሰማይ እሆን ምድር ጠፋኝ!" አሉ ሌላው አዛውንት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
፡
፡
#ክፍል_አራት
ዘርሲዎች ግማሽ ክብ ሰርተው ከመንደሩ ራቅ ብላ ዙሪያ ገቡን ከምታሳየው
የግራር ዛፍ ስርቁጭ ብለዋል ጩሉሌዎች
አንገታቸውን ቁልቁል ደፋ አድርገው በዛ ዙሪያ ያንዣብባሉ: ነፋሱ
ቅጠሎችን ጎንበስ ቀና እያደረገ ይነፍሳል
ከፊት ለፊታቸው ርጥብ
ቅጠል ተነጥፏል መሃል ላይ ጎረምሶች የተጠበሰውን የፍየል ስጋ እየቆራረጡ የፍሪንባውን ሥጋ በእድሜ ለገፉትና በጀግንነታደው ለሚታወቁት ለሌሎች ደግሞ ከተለያየውደ የስጋ አይነት እፊት ለፊታቸው ካለው ቅጠል አስቀመጡ" ህፃናት ጨዋታቸውን አቁመው ራቅ ብለው ሲቁለጨለጩ ቆይተው እደላው አልቆ መብሉ ሲጀመር ወደየአባቶቻቸው ጉያ ተሸጉጠው ዳረጎታቸውን እየተቀበሉ ከአጥንት ጋር መታገል ጀመሩ በመጨረሻ የሚበላው ከተበላ: ቀሪውን ደግሞ ጎረምሶቹ ካቀለጣጠፉት በኋላ ወጣቶቹ ቅጠሉን ሰብስበው ጥለው
ከስብሰባው አካባቢ ርቀው ሄዱ።
የሽማግሎች አለቃ ጦራቸውን ይዘው ከተቀመጡበት ተነስተው
ከፈርሱ እግራቸውን ቀባ አድርገው ወዲህ ወዲያ ወዲያ ወዲህ አሉና፣
"የአባት ደንብ ጥሩ ነው" በልክ መብላት የአባቶቻችን ባህል ነው አባቶቻችን የራበውና የጠገበ ትክክል ፍርድ አይሰጥም ይሉ
ነበር" የጠገበ ወንድ ሴት ማለት ነው መሳቅ ቧልት ይወዳል ከብቶችን አይፈቅድም ጫካውን አይቃኝም ከጓደኞቹ ጋር
አይመክርም መዝለል አይችልም መቀመጥና ማንጎላጀት ይወዳል
ትክክለኛ ፍርድ በዚህ ምክንያት አይሰጥም ይሉ ነበር አባቶቻችን" ሽማግሌው እቱፍ: እቱፍ
ብለው የጦሩን ዘንግ በምራቃቸው ቀባ ቀባ እያደረጉ ሽማግሎችን:
የአባታቸውን አገር አድማስ እየተዟዟሩ አይተው
አባቶቼ የራበውም ከጠገበ አይሻልም ይሉ ነበር የራበው ሰው ሰነፍ ነው
ሲኖረው አያውቅበትም
የወደቀችው ጀንበር:
የጠፋችው ጨረቃ ተመልሰው የሚመጡ
አይመስሉትም እንደ
አጋሰስ ፈረስ ዘመዶቹ ለመቋቋሚያ የሰጡትን ፍየሉንም፥ በጉንም
ከብቱንም: እህሉንም ብቻውን እየበላ ነገን ዘንግቶ: ልጆቼ: የአባቴ
ምክር ሳይል ሁሉን ያሟጥጥና የሚያልበው ሲያጣ የሚበላው
ሲቸግረው ሰውን: መሬቷን: ቦርጆን: አባቶቹን ይራገማል" ሆዱን
ለመሙላት ይቀማል ይዋሻል … ፍቅር አያውቅም ዘመድ ወገን አይለይም
አያስተውልም፤ ጨካኝ ነው
በዚህ ምክንያት
አባቶቻችን የራበው ሰው ትክክል አይፈርድም ይሉ ነበር አባቶቻችን ትክክል ናቸው ወንድሞቼ ጥጋብ ልቦናን ያዛባል ረሃብ ደግሞ ተስፋ መቁረጥንና ጥላቻን ያመጣል ከሁሉም የሚከፋው ደግሞ ሁለቱም ያስዋሻሉ" ብለው በርኮታቸው ላይ ቁጭ አሉ
ዝምታው ቀጠለ ሐመር ላይ ተረትን ሽማግሌ ለሌላው ማስታወስ እንጂ አይጨርሰውም የሰሙት እኩል: የፈፀሙት እኩል … ስለሆነ ተረት ጨራሽ አዳማጭ የለውም"
"በሉ ተናገሩ?" አሉ ሽማግሌው ከጥቂት ቆይታ በኋላ ጥሩ ነው! ከወደ መሃል አንዱ ድምፅ አሰሙ ገልመጥ ብሎ ያዬ የለም ሁሉም ግን አባባላቸውን በጆሮው ቀልቧል።
"ጥሩ ነው!- በአካል ተለይተውን ነፍሶቻቸው ደንቡን ጥበቃ አብረውን ላሉት ወንድሞቻችን ተገቢው ደንብ የሚሰራበት
ቀን ይመረጥ ልጆቻቸውና ሚስቶቻቸው በየበረሃው የአሉትን ተባት በግና ፍየሎች ከብቶችን ያስመጡ" በየመንደሩ ለሚኖሩት ዘመድ ጓደኞችም ጥሪ ይላክ ለዚያ ደሞ ዛሬ ቀኑ ተቆርጦ ቋጠሮ ይዘጋጅ አሉ።
የሽማግሎች አለቃ ሌላ ኃሳብ አለመኖሩን በዝምታደ ጠበቁና አንድ ጎረምሳ ጠርተው ልጥ አምጣ አንተ" አሉት ልጡ መጣ
"ስንት ላይ ይቋጠር?"
"መከን ተቢ" አሉ አንድ ሽማግሌ በስተግራ በኩል
ከተቀመጡት ሰላሳ ለማለት ልጡ ሰላሳ ላይ ተቋጥሮ ለሟቹ ታናሽ ወንድም
ተሰጠው" የሽማግሎች አለቃ አንዱን ችግር
በመቋጨታቸው
"ባይሮ ኢሜ" አሉ ሽማግሎችን እግዜር
ይስጣችሁ ለማለት
"በሉ ቀጥሉ?" አሉ የስብሰባው መሪ
"ጥሩ ነው!" አለ ልጅ እግሩና የአባቱን ጠላት ገሎ በቅርቡ
ከሽማግሌዎች ጋር ለመቀመጥ እድል ያገኘው ሰለምቤ፤ "ጥሩ ነው!
ታለውሻ በቀር አባቶቻችን ከአውሬ ጋር አልኖሩም እና ካርለቴ ይዛብን የመጣችውን አውሬ በጥይት አጉኖ ራቅ አድርጎ መቅበር ነው "አለ ገና የጎረምሳነት ባህሪው ሙሉ በሙሉ ያልቀዘቀዘለት ወጣቱ ሽማግሌ አለመብሰሉ በአነጋገሩ ፍጥጥ ብሎ እየታየበት።
"ጥሩ ነው! አውሬ ማለት ከብት የሚበላ ችግር የሚፈጥር ነው የነጯ ሐመር የካርለቴ አራት እግር አውሬ ሳይሆን መሂና
ነው የሚባል አባቶቻችን ደሞ መሂና የሚባል አውሬ አለ አላሉንም ደሞስ የካርለቴ መሂና እንደ ፈረስ እየጫነን ገበያ እያመላለሰን ነው እና መኖሩ ምን ጎዳ! አሉ ግራሯን የተደገፉት አንድ ዐይና
የአባት ደንብ እየሻርን ያ ይጎዳል ይሄ ይጠቅማል
ካልንማ ይህች አገርና ይህ ህዝብ መዓት ይመጣበታል" በነሱ ጊዜ ያልነበረ አውሬ አሁንም መኖር የለበትም " አሉ አገጫቸውን በግራ
እጃቸው ደግፈው የቆዩት ሽማግሌ ከዚያ ክርክሩ ከተለያዬ አቅጣጫ
መቅረቡ ቀጠለ
በአባቶቻችን ደንብ ፍየል ቢመጣ ፍየል ጋጥ: ከብት
ቢመጣ ከብቶች በረት ሰው ቢመጣ ወደ ሰዎች መኖሪያ ጎጆ ይገባል እህ እንዲህ እስተሆነ ድረስ የካርለቴ መሂና የሚገባ
ፍየሎች ጋጥ ነው? ከከብቶች በረት ነው? ወይንስ ከሰዎች ጋር ጎጆ
ውስጥ! መቼም ተውሾች ጋር እየተሯሯጠ አውሬና ጠላት ይከላከላል
አይባል ይኑር ከተባለ ወገኑ ከማን ነው? ተከብቶቹ ወይንስ ከእኛ! አሉ ከወደመሀል መፋቂያቸውን ሲያኝኩ የቆዩት ሽማግሌ
"ጥሩ ነው የሁላችሁም አስተያየት አዲስ ነገር መምጣቱ ይኸው ሁለት ሶስት ቦታ ከፋፍሎ አጨቃጨቀን ያልነበረ ነገር
ሲመጣ ያልነበረ ችግር ይፈጥራል ነጯ ሐመር የእኛ የሆነች እንግዳ ናት መሂና ያለችውን አውሬ ዱካውን ለማጥፋት በጥይትና ጦር
ደብድበን እንቅበረው ብንል እሷን እናሳዝናት ይሆናል"
ባይሆን አውሬሽን ካመጣሽበት ጫካ ጥለሽ ነይ ብንላት አይሻልም
ወንድሞቼ!" አሉ። አንተነህ ይመር ጋልታምቤ ጎን የተቀመጡት ሽማግሌ
ተው! ተው! ይህችን ሰው ተማበራችን አታውጧት! እሷ
ሐመር ናት የሐመር ልጃገረድ ተቀብላማ እንደ እህቶችዋ የፍየል ቆዳ ለብሳ ለዘመዷ ለከሎ ከብት
የአባቷን ትክክለኛ ደንብ
ዝላይ ተገርፋ … እንዴት እንዴት ነው እንደውጭ ሰው ይከፋታል ማለት! ከአባትሽ ባህልና ደንብ ውጭ ያመጣሽው አውሬ ቦርጆን ያስከፋል የአባቶቻችንንም ነፍስ ያሳዝናል እነሱ ተቆጥተው ዝናብ ከሚያጠፉብን በሽታ ከሚልኩብን አውሬሽን ቀብረነው እንረፍ
ብንላት በፍጡም አይከፋትም ወዲያውስ ከሽማግሌ ቃል ወጥታ የት ልትደርስ ኧረ አይከፋትም!" አሉ የዘርሲዎች አለቃ ከዚያ ለረጅም ጊዜ ዝምታ ሰፍኖ ቆየ
"ጥሩ ነው! እንዳላችሁትም
ነጯ ሐመር የእኛ ናት, የእኛ
ያልሆነውን ግን ዝም ብለን ብንለቀው ምን እንደሚያመጣ አናውቅም ሲቆይ ልጆቻችንን እሷን ጨምሮ: እኛን ይተናኮስ
አይተናኮስ ሳናውቅ እናጥፋው እስከተባባልን
ድረስ በኋላ ለቀን
ከምናሳድድ እዚሁ ገራም መስሎ አጠገባችን እንዳለ አድብቶ በጥይት ማጎን ነው የሚበጀው ካለበለዚያ
እኮ አስተውላችሁት እንደሁ
አላውቅም እንጂ አጉረምርሞ አጉረምርሞ ሰውነቱ የጋለ እንደሆን
እንደ ጥይት ከተፈተለከ
ድንጋይ አይል ውሃ ... ማን ጀግና ያቆመዋል! ስለዚህ ሳይደነብር አዋዝተው ጎረምሶች በክላሽ ጥይት
ሆድቃውን እንዲነድሉት ማድረግ ነው"" እንዳሉ
"ይህስ እውነት ነው! በቀደም ሳላየው ሩም … ብሎ ባጠገቤ ቢያልፍ የድምፁ ወላፈን እንዴት አሽቀንጥሮ ወረወረኝ መሰላችሁ ተዚያ ንዴቱ ይሁን ድንጋጤው ሰማይ እሆን ምድር ጠፋኝ!" አሉ ሌላው አዛውንት
#ባል_አስይዞ_ቁማር
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ስንት ሰዓት እንደተኛች አታውቅም፡፡ ፍፁም ሰላማዊና ህልም አልባ እንቅልፍ ነበር። ነቃች።ከአልጋ ወረደች።ቀለል ብሏታል። ወደፊት ለፊተኛው ክፍል ስትገባ ባዶ ነው፡፡ እንደውም ተዘግቷል። ‹‹ባዶ ቤት ጥሎኝ የት ሄደ...?፡፡››ቅር አለት፡፡የቤቱን ዙሪያ ገባ ስትቃኝ መሀል ጠረጴዛ ላይ ወረቀት አየች፡፡ ወደእዛ ሄደችና አነሳችው… አነበበችው"
ይቅርታ ስምሽን አላወቅኩትም ለማንኛውም
አስቸኮይ ስራ ስላጋጠመኝ ወጥቼያለሁ..
ሳልመጣ የምትሄጂ ከሆነ መኝታ ቤት ኮመዲኖ ላይ የታክሲ ብር አስቀምጪልሻለሁ።
ቤቱን ቆልፊና ፊት ለፊት ለአከራዮ ስጪልኝ።
በይ እግዜር ይማርሽ...አመሰግናለሁ።
አንብባ ስትጨርስ‹‹በቃ..? ››ስትል ጠየቀች፡፡
‹‹አይ እስክትመጣ አልሄድም..››ስትል ቃል አውጥታ ተናገረች… .አጠገቧ ያገኘችው ወንበር ላይ ተቀመጠች፡፡
‹‹ስሜ ልዩ ነው፡፡››ይሰማት ይመስል በድጋሚ ጮክ ብላ ተናገረች፡፡
"ደግሞ እንዴት ይሄን ሁሉ ነገር አድርጎልኝ ሳላመሰግነው እሄዳለሁ..?እንደውም ጥሩ ምክንያት አገኘሁ ለእማዬ ደውዬ እንግራተና እዚሁ አድራለሁ..ከዛ የሚፈጠረውን አያለሁ››አለች ድንገት ከመቀመጫዋ ተነሳችና….ወደመኝታ ቤት ተመልሳ ገባች.. እንዳለው ኮመዲኖው ላይ ብር አስቀምጦላታል…አነሳችውና ቆጠረችው፡፡ ሶስት መቶ ብር ነው። ኮመዲኖ የታችኛው ቁልፍ እላዩ ላይ እንደተንጠለጠለ ነው፡፡ የምታውቀወ ግን የምትጠላውና የመትጠየፈው ቢሆንም ደግሞ ልትቆጣጠረው የማትችለው ኃይል በውስጧ ሲሰርግ ታወቃት.... የተጣባት የሌብነት መንፈስ አንበረከካት፡፡ ቁልፉን አሽከረከረችው… ተከፈተላት፡፡ ውስጡ ብዙ ሰነዶችና አንድ ላፕቶፕ አለ."ያለምንም ማቅማማት ላፕቶፑን አነሳችውና ፤300ብር በእጇ ጨምድዳ ይዛ መኝታ ቤቱን ለቃ ወጣች….እንዳለት ቤቱን ቆለፈችና ቁልፉን ለአሮጊቷ ሰጥታቸው ሰፈሩን በላዳ ለቃ ወጣች፡፡
መሄድ የነበረባ ወደጦር ኃይሎች ነበር ..ከዛ ወደትምህርት ቤቷ ሄዳ ግቢው ወስጥ ያቆመቻትን መኪና ይዛ ነበር ወደሳሪስ መሄድ የሚገባት ግን አሁን እንደዛ ማድረግ አልቻለችም ቀጥታ…ላፕቶፑን በደረቷ ላይ ለጥፋ ከካሳንቺስ እስከሳሪስ እያለቀስች ነበር የደረስችው...ልክ ላፕቶፕ ካልሰረቅሽ ህይወትሽን ታጪያለሽ ብለው በግዳጅ እንዳሰረቋት ነገር ነው ሁኔታዋ የሚመስለው፡፡
‹‹አሁን ለዚህ ልጅ በዚህ ደግነቱ እንዲህ መዘረፍ ይገበዋል…?.እኔስ ዘራፊና ሌባ መሆን ይገባኝ ነበር…?አረ ጌታ ሆይ እውነት በመንበርህ ካለህ አንድ ነገር አድርግ..ነው ወይስ የሌባ ፀሎት አንተ ጋር ምንም እርባን የለውም…ምንም ሌባ ብሆነ እኮ ያው አንተው ነህ የፈጠርከኝ››ስትል አምርራ ወደፈጣሪዋ አጉረመረመች፡፡
///
እቤት እንደደረሰች በራፍን የከፈተላት ዘበኛ በድንጋጤ ጭንቅላቱን ያዘ፡፡ በረንዳ ስታፀዳ የነበረችው የቤት ሰራተኛም መወልወያዋን በቁማ ጥላ‹‹ እትዬ..ልዩ ተጎድታለች..እትዬ ልዩ ተፈንክታልሽ መጣች....››እያላች ወደግዙፍ ባለሁለት ፎቅ ህንፃ ገባች..እሷ የሳሎን በረንዳ ላይ ስደርስ እቤት ውስጥ የነበሩት ቤተሰቦቾ በጠቅላላ በእናቷ ፊት መሪነት እየተንጋጉ ዙሪያዋን ከበቧት፡፡
…እናቷ እሪታዋን ለቀቀችው..‹‹ወይኔ ልጄን ይሄው ገደሏት…ወይኔ ምነው እመቤቴ ..?ምነው አንቺም ልጅ አለሽ …የአንድ ብቸኛ ልጅ እናት መሆን ፈተናውና መሳቀቁ ምን ያህል ጥልቅ እንደሆነ ካንቺ በላይ የሚያውቀው የለም… ታዲያ ምን አለ ብትሰሚኝ ››ልክ የሞተችና ሬሳዋን ተሸክመውላቸው የመጡ ነው ያስመሰሉት፡፡
አዛኙም አሽቃባጩም በአንድነት ከበቧትና አፋፍሰው ልክ መራመድ እንደማትችል ወደውስጥ ይዘዋት ገቡ፡፡ እሷም ሲደጋግፏት ያልነበረ ህመሟ ከያለበት ተሰብሰቦ ሰፈረባት፡፡ ጭንቅላቷ ላይ የሆነ ቋጥኝ የተጫነባት ይመስል ውጥርጥር አድርጓታል፡፤ የጭንቅላቷ እብጠት ጥዝጣዜ ነርቯን ነካት
‹‹….እዛ ልጅ ጋር ይሄን ያህል ያለመመኝ እቤቴ ስገባ ለምን ተደበላለቀብኝ፡፡››እራሷን ጠየቀች፡፡
‹‹በሉ እዛ ደክተር ጋ ደውሉለት….በአስቸኮይ መጥቶ ይያተና ካልሆነ ሆስፒታል እንወስዳታለን.››እናቷ ናቸው በለቅሶ የታጀበ ትዕዛዝ የሚየዥጎደጉዱት፡፡
አንደኛ ፎቅ ላይ ወደሚገኘው የተንጣለለው መኝታ ቤቷ አስገቧት
….‹‹.ዞር በሉላት በቃ አታጨናንቋት….››ብለው አስተኞት፡፡
‹‹ለመሆኑ መንግስት ባለበት ሀገር ከማን ተጣልተሸ ነው..?››በቀጣይ የጠየቋት ጥያቄ ነው
‹ግን በአሁኑ ወቅት ኢትዬጵያ ውስጥ እንዲህ አይነት ጥያቄ ይጠየቃል..? መንግስት እያለ ምን የማይደረግ ነገር አለ..?ግድያ ፣አስገድዶ መድፈር፣ከገዛ መንደር መፈናቀል…ነገሩ እንዚህ ሁሉ ወንጀሎች መንግስት ባለባቸው በማንኘኛቸውም ሀገሮች ይፈፀማሉ… በአሜሪካም ጭመር….አንዳንዴ እንደውም መንግስት እራሱ በእጅ አዙር ያስፈፅማቸዋል …አንተ እያለህልን እንዴት እንዲባል?እናቴ ግን ምን ታደርግ ሳሪስ ላይ ተቀምጣ ስለእነዚህ ነገሮች በወሬ እንኳን ብትሰማ ከምታየው የቱርክ ፊልም ጋር ስለሚምታታባት እውነት ይሁን ውሸት ትዝም አይሏት….ለነገሩ እኔም እንደእሷው ነኝ…አሁን እራሱ ስለእንደዚህ አይነት ጠንከር ያለ ነገር እንዴት ማሰብ እንደቻልኩ አላውቅም...ምን አልባት ጭንቅላቴን ሲነርቱት የሆኑ አንቀላፍተው የነበሩ ነርቮችን አነቁብኝ ይሆን እንዴ…?ኸረ አያድርገው…ጌታ ሆይ ስለፖለቲካና ዲሞክራሲ ሚበሉ ህልሞች የሚያስብ የእምሮዬን ክፍሎችን መቼም ንቁ እንዳይሆኑ እማፀንሀለሁ›› ስትል ፀለየች..መቼስ ይሄንንንም እንደሌሎች ፀሎቶቿ ችላ እንደማይልባ አየተማመነች፡፡
እናቷ እሷን መጨቅጨቃቸውን ቀጥለዋል‹‹ዩኒቨርሲቲ አመፅ ተነስቶ ነው…? ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተሸ ነበር እንዴ?ምን ተከስቷ ነው?›
እናቷ የማትመልሳቸውን አያሌ ጥያቄዎች ያዥጎደጉድባታል…. ዩኒቨርሲቲ ያሏት.. ጥዋት ከቤት ቁርስ በልታ ዩኒቨርሲቲ ክላስ አለኝ ብላ በመውጣቷ ነው ፡፡ደግሞም ሄዳ ነበር….ልዩ የምትማረው ዪኒቲ ዪኒቨርሲቲ ነው..መኪናዋን ይዛ ወደእዛ ነበር የተጎዘችው..አንድ ክላስ እንደተማረች ግን የተለመደ ድብርቷ ተቀሰቀሰባትና መኪናዋን እዛው ግቢ ውስጥ እንዳቆመች፤ስልኳን እንኳን እዛው መኪናዋ ውስጥ ቻርጅ እንደሰካች በእግሯ ከግቢው ወጣች ፡፡
በተክሲ ስትዲዬም ድረስ ከስቴዲዬም ደግሞ መገናኛ ሄዳ ነው እንግዲህ ያ ታክሲ ላይ ያጋጠማት ታሪክ የተፈጠረው..እንደዛም ስለሆነ ከወትሮ በተለየ ፀፀትና ንዴት አልተሰማትም ነበር፡፡በጣም ልዩ በሆነ አጋጣሚ ከተለየ እና ተአምራዊ ከሆነ ልጅ ጋር ነበር ያገናኛት.. ምን ያደርጋል? አፈፃፀሙን አበላሸችው… የማትፈልገውን ላፕቶፕ ሰርቃ ያንን የመሰለ አጋጣሚ በማጨመላለቋ እራሷን ተጠይፋለች፡፡አሁን በሰውነቷ ካለው ቁስል በላይ ክፉኛ እየጠዘጠዛት ያለው ይሄ ነው፡፡
..‹‹ግን ወድጄ ነው እንዴ እንደዛ ያደረኩት?››ስትል እራሷን ለማፅናናት ሞከረች፡፡
ሁሉም መኝታ ቤቷን ለቀው እንዲወጡ ተደረገና በክፍሉ እናቷና እሷ ብቻ ቀሩ፡፡
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ስንት ሰዓት እንደተኛች አታውቅም፡፡ ፍፁም ሰላማዊና ህልም አልባ እንቅልፍ ነበር። ነቃች።ከአልጋ ወረደች።ቀለል ብሏታል። ወደፊት ለፊተኛው ክፍል ስትገባ ባዶ ነው፡፡ እንደውም ተዘግቷል። ‹‹ባዶ ቤት ጥሎኝ የት ሄደ...?፡፡››ቅር አለት፡፡የቤቱን ዙሪያ ገባ ስትቃኝ መሀል ጠረጴዛ ላይ ወረቀት አየች፡፡ ወደእዛ ሄደችና አነሳችው… አነበበችው"
ይቅርታ ስምሽን አላወቅኩትም ለማንኛውም
አስቸኮይ ስራ ስላጋጠመኝ ወጥቼያለሁ..
ሳልመጣ የምትሄጂ ከሆነ መኝታ ቤት ኮመዲኖ ላይ የታክሲ ብር አስቀምጪልሻለሁ።
ቤቱን ቆልፊና ፊት ለፊት ለአከራዮ ስጪልኝ።
በይ እግዜር ይማርሽ...አመሰግናለሁ።
አንብባ ስትጨርስ‹‹በቃ..? ››ስትል ጠየቀች፡፡
‹‹አይ እስክትመጣ አልሄድም..››ስትል ቃል አውጥታ ተናገረች… .አጠገቧ ያገኘችው ወንበር ላይ ተቀመጠች፡፡
‹‹ስሜ ልዩ ነው፡፡››ይሰማት ይመስል በድጋሚ ጮክ ብላ ተናገረች፡፡
"ደግሞ እንዴት ይሄን ሁሉ ነገር አድርጎልኝ ሳላመሰግነው እሄዳለሁ..?እንደውም ጥሩ ምክንያት አገኘሁ ለእማዬ ደውዬ እንግራተና እዚሁ አድራለሁ..ከዛ የሚፈጠረውን አያለሁ››አለች ድንገት ከመቀመጫዋ ተነሳችና….ወደመኝታ ቤት ተመልሳ ገባች.. እንዳለው ኮመዲኖው ላይ ብር አስቀምጦላታል…አነሳችውና ቆጠረችው፡፡ ሶስት መቶ ብር ነው። ኮመዲኖ የታችኛው ቁልፍ እላዩ ላይ እንደተንጠለጠለ ነው፡፡ የምታውቀወ ግን የምትጠላውና የመትጠየፈው ቢሆንም ደግሞ ልትቆጣጠረው የማትችለው ኃይል በውስጧ ሲሰርግ ታወቃት.... የተጣባት የሌብነት መንፈስ አንበረከካት፡፡ ቁልፉን አሽከረከረችው… ተከፈተላት፡፡ ውስጡ ብዙ ሰነዶችና አንድ ላፕቶፕ አለ."ያለምንም ማቅማማት ላፕቶፑን አነሳችውና ፤300ብር በእጇ ጨምድዳ ይዛ መኝታ ቤቱን ለቃ ወጣች….እንዳለት ቤቱን ቆለፈችና ቁልፉን ለአሮጊቷ ሰጥታቸው ሰፈሩን በላዳ ለቃ ወጣች፡፡
መሄድ የነበረባ ወደጦር ኃይሎች ነበር ..ከዛ ወደትምህርት ቤቷ ሄዳ ግቢው ወስጥ ያቆመቻትን መኪና ይዛ ነበር ወደሳሪስ መሄድ የሚገባት ግን አሁን እንደዛ ማድረግ አልቻለችም ቀጥታ…ላፕቶፑን በደረቷ ላይ ለጥፋ ከካሳንቺስ እስከሳሪስ እያለቀስች ነበር የደረስችው...ልክ ላፕቶፕ ካልሰረቅሽ ህይወትሽን ታጪያለሽ ብለው በግዳጅ እንዳሰረቋት ነገር ነው ሁኔታዋ የሚመስለው፡፡
‹‹አሁን ለዚህ ልጅ በዚህ ደግነቱ እንዲህ መዘረፍ ይገበዋል…?.እኔስ ዘራፊና ሌባ መሆን ይገባኝ ነበር…?አረ ጌታ ሆይ እውነት በመንበርህ ካለህ አንድ ነገር አድርግ..ነው ወይስ የሌባ ፀሎት አንተ ጋር ምንም እርባን የለውም…ምንም ሌባ ብሆነ እኮ ያው አንተው ነህ የፈጠርከኝ››ስትል አምርራ ወደፈጣሪዋ አጉረመረመች፡፡
///
እቤት እንደደረሰች በራፍን የከፈተላት ዘበኛ በድንጋጤ ጭንቅላቱን ያዘ፡፡ በረንዳ ስታፀዳ የነበረችው የቤት ሰራተኛም መወልወያዋን በቁማ ጥላ‹‹ እትዬ..ልዩ ተጎድታለች..እትዬ ልዩ ተፈንክታልሽ መጣች....››እያላች ወደግዙፍ ባለሁለት ፎቅ ህንፃ ገባች..እሷ የሳሎን በረንዳ ላይ ስደርስ እቤት ውስጥ የነበሩት ቤተሰቦቾ በጠቅላላ በእናቷ ፊት መሪነት እየተንጋጉ ዙሪያዋን ከበቧት፡፡
…እናቷ እሪታዋን ለቀቀችው..‹‹ወይኔ ልጄን ይሄው ገደሏት…ወይኔ ምነው እመቤቴ ..?ምነው አንቺም ልጅ አለሽ …የአንድ ብቸኛ ልጅ እናት መሆን ፈተናውና መሳቀቁ ምን ያህል ጥልቅ እንደሆነ ካንቺ በላይ የሚያውቀው የለም… ታዲያ ምን አለ ብትሰሚኝ ››ልክ የሞተችና ሬሳዋን ተሸክመውላቸው የመጡ ነው ያስመሰሉት፡፡
አዛኙም አሽቃባጩም በአንድነት ከበቧትና አፋፍሰው ልክ መራመድ እንደማትችል ወደውስጥ ይዘዋት ገቡ፡፡ እሷም ሲደጋግፏት ያልነበረ ህመሟ ከያለበት ተሰብሰቦ ሰፈረባት፡፡ ጭንቅላቷ ላይ የሆነ ቋጥኝ የተጫነባት ይመስል ውጥርጥር አድርጓታል፡፤ የጭንቅላቷ እብጠት ጥዝጣዜ ነርቯን ነካት
‹‹….እዛ ልጅ ጋር ይሄን ያህል ያለመመኝ እቤቴ ስገባ ለምን ተደበላለቀብኝ፡፡››እራሷን ጠየቀች፡፡
‹‹በሉ እዛ ደክተር ጋ ደውሉለት….በአስቸኮይ መጥቶ ይያተና ካልሆነ ሆስፒታል እንወስዳታለን.››እናቷ ናቸው በለቅሶ የታጀበ ትዕዛዝ የሚየዥጎደጉዱት፡፡
አንደኛ ፎቅ ላይ ወደሚገኘው የተንጣለለው መኝታ ቤቷ አስገቧት
….‹‹.ዞር በሉላት በቃ አታጨናንቋት….››ብለው አስተኞት፡፡
‹‹ለመሆኑ መንግስት ባለበት ሀገር ከማን ተጣልተሸ ነው..?››በቀጣይ የጠየቋት ጥያቄ ነው
‹ግን በአሁኑ ወቅት ኢትዬጵያ ውስጥ እንዲህ አይነት ጥያቄ ይጠየቃል..? መንግስት እያለ ምን የማይደረግ ነገር አለ..?ግድያ ፣አስገድዶ መድፈር፣ከገዛ መንደር መፈናቀል…ነገሩ እንዚህ ሁሉ ወንጀሎች መንግስት ባለባቸው በማንኘኛቸውም ሀገሮች ይፈፀማሉ… በአሜሪካም ጭመር….አንዳንዴ እንደውም መንግስት እራሱ በእጅ አዙር ያስፈፅማቸዋል …አንተ እያለህልን እንዴት እንዲባል?እናቴ ግን ምን ታደርግ ሳሪስ ላይ ተቀምጣ ስለእነዚህ ነገሮች በወሬ እንኳን ብትሰማ ከምታየው የቱርክ ፊልም ጋር ስለሚምታታባት እውነት ይሁን ውሸት ትዝም አይሏት….ለነገሩ እኔም እንደእሷው ነኝ…አሁን እራሱ ስለእንደዚህ አይነት ጠንከር ያለ ነገር እንዴት ማሰብ እንደቻልኩ አላውቅም...ምን አልባት ጭንቅላቴን ሲነርቱት የሆኑ አንቀላፍተው የነበሩ ነርቮችን አነቁብኝ ይሆን እንዴ…?ኸረ አያድርገው…ጌታ ሆይ ስለፖለቲካና ዲሞክራሲ ሚበሉ ህልሞች የሚያስብ የእምሮዬን ክፍሎችን መቼም ንቁ እንዳይሆኑ እማፀንሀለሁ›› ስትል ፀለየች..መቼስ ይሄንንንም እንደሌሎች ፀሎቶቿ ችላ እንደማይልባ አየተማመነች፡፡
እናቷ እሷን መጨቅጨቃቸውን ቀጥለዋል‹‹ዩኒቨርሲቲ አመፅ ተነስቶ ነው…? ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተሸ ነበር እንዴ?ምን ተከስቷ ነው?›
እናቷ የማትመልሳቸውን አያሌ ጥያቄዎች ያዥጎደጉድባታል…. ዩኒቨርሲቲ ያሏት.. ጥዋት ከቤት ቁርስ በልታ ዩኒቨርሲቲ ክላስ አለኝ ብላ በመውጣቷ ነው ፡፡ደግሞም ሄዳ ነበር….ልዩ የምትማረው ዪኒቲ ዪኒቨርሲቲ ነው..መኪናዋን ይዛ ወደእዛ ነበር የተጎዘችው..አንድ ክላስ እንደተማረች ግን የተለመደ ድብርቷ ተቀሰቀሰባትና መኪናዋን እዛው ግቢ ውስጥ እንዳቆመች፤ስልኳን እንኳን እዛው መኪናዋ ውስጥ ቻርጅ እንደሰካች በእግሯ ከግቢው ወጣች ፡፡
በተክሲ ስትዲዬም ድረስ ከስቴዲዬም ደግሞ መገናኛ ሄዳ ነው እንግዲህ ያ ታክሲ ላይ ያጋጠማት ታሪክ የተፈጠረው..እንደዛም ስለሆነ ከወትሮ በተለየ ፀፀትና ንዴት አልተሰማትም ነበር፡፡በጣም ልዩ በሆነ አጋጣሚ ከተለየ እና ተአምራዊ ከሆነ ልጅ ጋር ነበር ያገናኛት.. ምን ያደርጋል? አፈፃፀሙን አበላሸችው… የማትፈልገውን ላፕቶፕ ሰርቃ ያንን የመሰለ አጋጣሚ በማጨመላለቋ እራሷን ተጠይፋለች፡፡አሁን በሰውነቷ ካለው ቁስል በላይ ክፉኛ እየጠዘጠዛት ያለው ይሄ ነው፡፡
..‹‹ግን ወድጄ ነው እንዴ እንደዛ ያደረኩት?››ስትል እራሷን ለማፅናናት ሞከረች፡፡
ሁሉም መኝታ ቤቷን ለቀው እንዲወጡ ተደረገና በክፍሉ እናቷና እሷ ብቻ ቀሩ፡፡
#ህያብ
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በኤርሚ
ነሀሴ መጨረሻ ላይ ውጤት መጣ ተባለና አየን ጥሩ ውጤት ነው ያመጣሁት ግን ሩቅ ሀገር ነው የመደቡኝ ጎንደር ዩንቨርስቲ በምፈልገው ዲፓርትመንት(ህክምና)
እናቴን እና ልጄን ትቼ እንዴት ችዬ ይህን ያክል እርቃለሁ.. ትምህርቴን መተው እናቴን እንደመቅበር ነው። ሁላችንም ቢከብደንም ግዴታ ሄጄ መማር አለብኝ።
.....
ስራ ቦታዋ ሄጄ ለእናቴ ስነግራት እልልታዋን አቀለጠችው። ደንበኞቿ ምን እንደተፈጠረ ሲጠይቁኝ ነገርኳቸው እንኳን ደስ ያለሽ እያሉ እናቴን አቀፏት..... ከሁኔታቸው እኔ ሳልሆን እናቴ ውጤት የመጣላት ነበር የሚመስለው....
......
ቤት ውስጥ ጎረቤቶቻችንና አንዳንድ የእናቴ ወዳጆች በተገኙበት መጠነኛ የሽኝት ዝግጅት ተደረገልኝ። ልለያት እንደሆነ ያላወቀችው ልጄም ከኔ እኩል ፍንድቅድቅ ብላለች። እንግዶች በልተው ማዕዱ ከፍ ካለ በኋላ እናቴ ወደ መሀል ወጣችና
"አንዴ ፀጥታ...." ብላ ጨብጨብ ስታደርግ ሁሉም ሰው ባንዴ ዝምምም አለ።
"በህይወቴ እንደዛሬ የተደሰትኩበት ቀን የለም ... ልጄ ዩንቨርስቲ ገባችልኝ። ይሄ ከምንም በላይ ትልቁ ህልሜ ነው። እዛ ሄዳ በስኬት እንደምትመለስ እተማመንባታለሁ። ትልቅ ነገርም ባይሆን ይሄን ስጦታ በእናንተ ፊት እሰጣታለሁ" ወደኔ መጥታ ጉንጬን አገላብጣ ከሳመችኝ በኋላ የተጠቀለለውን ስጦታ ሰጠችኝና"ክፈቺው..." አለችኝ። የተጠቀለለበትን ወረቀት ስከፍተው ሞባይል ከነ ቻርጀሩ ብቅ አለ። አላመንኩም እናቴ ለኔ የእጅ ስልክ ገዛችልኝ... በዚያን ጊዜ አብዛኛው ሰው ባለ ሞባይል እየሆነ ቢሆንም እኔ ይኖረኛል ብዬ ግን አላሰብኩም ነበር።
"አመሰግናለሁ እናቴ.... ደግሞ ቃል እገባልሻለሁ... አኮራሻለሁ"
"እተማመንብሻለሁ የኔ ጀግና.... ሳትሳቀቂ በናፈቅሺን ሰዓት መደወል ብቻ ነው...."ወደ ደረቷ ወስዳ ጥብቅ አድርጋ አቀፈችኝ። ይሄን እቅፍ እኮ ስወደው..............
ቃል ባትናገር እንኳን በእቅፏ ብቻ ብዙ መልዕክት የምታስተላልፍልኝ ይመስለኛል።
"በርቺ....
ባንቺ እተማመናለሁ....
እኔ አለሁልሽ...
እወድሻለሁ......." ብቻ ስታቅፈኝ ከዚህም በላይ ብዙ የምትለኝ ይመስለኛል።
..............
የምወዳት ልጄን እና እናቴን ተሰናብቼ ወደ አፄ ፋሲል ሀገር ጥንታዊቷ ጎንደር ተጓዝኩ ።
..........
ምዝገባ እና ሌሎች ፕሮሰሶች አልቀው ትምህርት የምንጀምርበት ቀን ደረሰ...... የመጀመሪያ ቀን እንደመሆኑ አብዛኛው ተማሪ ቀድሞ ክፍል ተገኝቷል ከነኛ መሀል አንዷ እኔ ነኝ።
.....
ከደቂቃዎች በኋላ
"ይሄ ሸበላ ብቻ እንዳይሆን የሚያስተምረን" ከኋላዬ ያለችው ልጅ ወደ ጆሮዬ ተጠግታ አንሾካሾከችልኝ። ከንግግሯ እኩል ቀና ብዬ ወደ ፊት ለፊቴ አየሁ..... " ዋው ውበት ..... ዋው ቁመና.... ዋው ደረት...." ብዙ ዋው የሚያስብሉ ነገሮችን ያሟላ ሸበላ ሰው.....
......
"እሺ ዛሬ ብዙም የምንማረው ነገር አይኖረንም እርስ በርሳችን እንተዋወቅና ኮርስ አውትላይን እሰጣችኋለሁ...... እምም ከፊት ልጀምር ስምሽን አስተዋውቂን እስኪ...." ምኑ ነው ምን አለ እስከምረጋጋ እንኳን ሌላ ሰው ቢጠይቅ
"ህያብ በዛብህ እባላለሁ የመጣሁት ከአዲስ አበባ" ጣቱን ከኔ ቀጥሎ ወዳለችው ልጅ ጠቆመ
"መቅደስ ገዛህኝ..... ከሀዋሳ
ተፈሪ ይልማ...... ከደሴ
አብሳላት አበበ.... ከአዳማ
የትናዬት ዘመረ..... ከአዲስ አበባ......" ሁሉም ስማቸውን እና የመጡበትን ከተማ ተናገሩ ሁላችንንም ከሰማ በኋላ
" የኔ ስም ደግሞ ዮናታን ይባላል የ...." ከዚህ በኋላ ያለውን አልሰማሁትም .... ዮናታን.... ዮኒ ስሙ ደስ ይላል መልኩም ደስ ይላል። ሳላውቀው ስለሱ ብዙ አሰብኩ.... እጄ ላይ ያረፈ ወረቀት ከሀሳቤ አነቃኝ
"ያልኩትን ሰምተሽኛል ህያብ" ድንብርብሬ ወቶ አይን አይኑን አየው ጀመር እሱም ትንሽ ካየኝ በኋላ
" ተወካይ እስክትመርጡ ድረስ አንቺ ተወካይ ሆነሽ እነኝህን ወረቀቶች ለሁሉም አዳርሺ...." መልሴን ሳይጠብቅ ክፍሉን ለቆ ወጣ። እንዴ ቆይ ደግሞ ስሜን እንዴት ባንዴ ያዘው..... ይገርማል
........
" እና እኔንም አፈዘዘኝ እያልሽኝ ነው" አለችኝ ከፊት ለፊቴ መጥታ
"ይቅርታ እህቴ ምን......"
."ቅድም አልሰማሽኝም የትናየት.... የትናዬት ነው ስሜ"
"እሺ የትናዬት የምትይው አልገባኝም"
"ቀስ ብሎ ይገባሻል ለማንኛውም የራሴን ልውሰድ." አንዱን ወረቀት አንስታ እየተቆናጠረች ከክፍሉ ወጣች።
"ወይ አምላኬ ስንት አይነት ሰው አለ" ብዬ ስዞር ሁሉም አፍጠው የሚያዩኝ እኔን ነው።
ህይወት ልክ በምኞታችን ውስጥ እንዳሰብናት ቀላልና ጣፋጭ አይደለችም። ልንመራት ያወጣነውን እቅድ አስጥላ በራሷ ምህዋር ላይ ታሽከረክረናለች። እምቢ ብለን ብናስቸግራት እንኳን ወይ ከራሳችን እቅድ ወይም ሽክርክሪቱ ከሚያመጣው ነገር ሳንቋደስ ሜዳ ላይ እንቀራለን።
ዩንቨርስቲ መግባትን ሳስብ የሚታየኝ ጠንክሮ መማርና መማር ብቻ ነበር። ግቢ ውስጥ ሆኜ ከትምህርቴ የበለጠ ቦታ እሰጠዋለሁ ብዬ የማስበው ምንም ነገር አልነበረም። የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ እያለሁ የሆነ ሰው መጥቶ ይህን ጥያቄ ቢጠይቀኝ በመጠየቁ ልናደድበት እችል ነበር። ዛሬ ግን ያን እምነቴን የትላንት እቅዴን ሊያከሽፍ የሚችል ፍቅር ያዘኝ። ያውም ውድድር የበዛበት ፍቅር.....
አብሬው ልሁን ብዬ ባስብ እንኳን ከሱ እኔን አለማፍቀር ውጪ ከደርዘን በላይ ሴቶች ጋር መጋፈጥ ይኖርብኛል..... ያውም እኔ የማውቃቸው ብቻ።
ያለኝ አማራጭ አንድ ብቻ ነው ቢከብደኝም ስሜቴን አምቄ መያዝ እና በሰላም ትምህርቴን መቀጠል። ምንም ሳይተነፍሱ ሁሉንም በልብ መያዝ ከምንም በላይ ህመም ነው.... በተለይ ደግሞ ፍቅር ሲሆን...
ብዙ ጊዜ ይሄን አስባለሁ ለእናቴ ይሄ አይገባትም አይደል? ... ስኬቴን ለምትናፍቅ እናቴ ስል ከመጋፈጥ ይልቅ መሸሽን መርጫለሁ። የምሸሽበት ምክንያት ዋናው ቁም ነገሩ እኮ ማፍቀሬ አይደለም ፍቅር በየትኛውም ጊዜ እና ሁኔታ ውስጥ ሊከሰት የሚችል ስሜት ነው። ችግሩ ለዚህ ፍቅር ስል ብፋለም ለትምህርት የሚሆን ነፃ አይምሮ ላገኝ እችላለው ወይ? የበለጠው ችግር ደግሞ ያፈቀርኩት ሰው ሁሉንም ቀማሽ መሆኑ ነው።
፧፧፧፧፧፧
ከዛን ቀን ጀምሮ ማለትም ከመጀመሪያ የትምህርት ቀናችን ጀምሮ በዮኒ ፍቅር ተለክፊያለሁ። ፍቅር እንደያዘኝ እንኳን እያወኩ ላለማመን ከራሴ ጋር ለወራት ተከራክሪያለሁ። የትናዬት በየቀኑ እኔን ማስበርገግ ስራዬ ብላ ከያዘች ቆይታለች። በተለይ ዮናታን አስተምሮን ሲወጣ ወይ ከጎኔ ናት ወይም ከፊት ለፊቴ.... እልፍ ጊዜ እኮ አብረው አይቻቸዋለሁ... ብዙ ጊዜ ቢሮው ስትገባ ያዩዋት ነግረውኛል...... እኔ ደግሞ በተቃራኒው ከሱ ጋር የሚያገናኘን ድልድይ ሁላ ላፈርስ የምሞክር ሰው ነኝ። ለምን ይሄን ያክል የቤት ስራ እንደሆንኩባት አላውቅም። አሁን ግን መሮኛል ፀብ ላለመፍጠር እያልኩ እንደፈሪ መታየት መሮኛል።
ዛሬም እንደለመደችው ከጥሩ ትወና ጋር የአሽሙር ንግግሯን ተናግራኝ ከክፍሉ ወጣች። ብሽቅ ብዬ ወረቀቶቼን ሰብስቤ ተከትያት እየወጣሁ እያለ አንድ ሰው ከኋላዬ ያዘኝ። ዞር ስል ቢኒ ነው ከተማሪዎች ሁሉ የተለየው ዝምተኛ ልጅ።
"አቤት ቢኒ" አልኩት ኮስተር ብዬ... ግንባሬን አይቶ እጁን ከክንዴ ላይ አነሳ እና
"ይቅርታ ህያብ.... ጣልቃ ልገባ ፈልጌ አይደለም ግን እኔ የታየኝን አንድ ነገር ልበልሽ..."
"ምን"
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በኤርሚ
ነሀሴ መጨረሻ ላይ ውጤት መጣ ተባለና አየን ጥሩ ውጤት ነው ያመጣሁት ግን ሩቅ ሀገር ነው የመደቡኝ ጎንደር ዩንቨርስቲ በምፈልገው ዲፓርትመንት(ህክምና)
እናቴን እና ልጄን ትቼ እንዴት ችዬ ይህን ያክል እርቃለሁ.. ትምህርቴን መተው እናቴን እንደመቅበር ነው። ሁላችንም ቢከብደንም ግዴታ ሄጄ መማር አለብኝ።
.....
ስራ ቦታዋ ሄጄ ለእናቴ ስነግራት እልልታዋን አቀለጠችው። ደንበኞቿ ምን እንደተፈጠረ ሲጠይቁኝ ነገርኳቸው እንኳን ደስ ያለሽ እያሉ እናቴን አቀፏት..... ከሁኔታቸው እኔ ሳልሆን እናቴ ውጤት የመጣላት ነበር የሚመስለው....
......
ቤት ውስጥ ጎረቤቶቻችንና አንዳንድ የእናቴ ወዳጆች በተገኙበት መጠነኛ የሽኝት ዝግጅት ተደረገልኝ። ልለያት እንደሆነ ያላወቀችው ልጄም ከኔ እኩል ፍንድቅድቅ ብላለች። እንግዶች በልተው ማዕዱ ከፍ ካለ በኋላ እናቴ ወደ መሀል ወጣችና
"አንዴ ፀጥታ...." ብላ ጨብጨብ ስታደርግ ሁሉም ሰው ባንዴ ዝምምም አለ።
"በህይወቴ እንደዛሬ የተደሰትኩበት ቀን የለም ... ልጄ ዩንቨርስቲ ገባችልኝ። ይሄ ከምንም በላይ ትልቁ ህልሜ ነው። እዛ ሄዳ በስኬት እንደምትመለስ እተማመንባታለሁ። ትልቅ ነገርም ባይሆን ይሄን ስጦታ በእናንተ ፊት እሰጣታለሁ" ወደኔ መጥታ ጉንጬን አገላብጣ ከሳመችኝ በኋላ የተጠቀለለውን ስጦታ ሰጠችኝና"ክፈቺው..." አለችኝ። የተጠቀለለበትን ወረቀት ስከፍተው ሞባይል ከነ ቻርጀሩ ብቅ አለ። አላመንኩም እናቴ ለኔ የእጅ ስልክ ገዛችልኝ... በዚያን ጊዜ አብዛኛው ሰው ባለ ሞባይል እየሆነ ቢሆንም እኔ ይኖረኛል ብዬ ግን አላሰብኩም ነበር።
"አመሰግናለሁ እናቴ.... ደግሞ ቃል እገባልሻለሁ... አኮራሻለሁ"
"እተማመንብሻለሁ የኔ ጀግና.... ሳትሳቀቂ በናፈቅሺን ሰዓት መደወል ብቻ ነው...."ወደ ደረቷ ወስዳ ጥብቅ አድርጋ አቀፈችኝ። ይሄን እቅፍ እኮ ስወደው..............
ቃል ባትናገር እንኳን በእቅፏ ብቻ ብዙ መልዕክት የምታስተላልፍልኝ ይመስለኛል።
"በርቺ....
ባንቺ እተማመናለሁ....
እኔ አለሁልሽ...
እወድሻለሁ......." ብቻ ስታቅፈኝ ከዚህም በላይ ብዙ የምትለኝ ይመስለኛል።
..............
የምወዳት ልጄን እና እናቴን ተሰናብቼ ወደ አፄ ፋሲል ሀገር ጥንታዊቷ ጎንደር ተጓዝኩ ።
..........
ምዝገባ እና ሌሎች ፕሮሰሶች አልቀው ትምህርት የምንጀምርበት ቀን ደረሰ...... የመጀመሪያ ቀን እንደመሆኑ አብዛኛው ተማሪ ቀድሞ ክፍል ተገኝቷል ከነኛ መሀል አንዷ እኔ ነኝ።
.....
ከደቂቃዎች በኋላ
"ይሄ ሸበላ ብቻ እንዳይሆን የሚያስተምረን" ከኋላዬ ያለችው ልጅ ወደ ጆሮዬ ተጠግታ አንሾካሾከችልኝ። ከንግግሯ እኩል ቀና ብዬ ወደ ፊት ለፊቴ አየሁ..... " ዋው ውበት ..... ዋው ቁመና.... ዋው ደረት...." ብዙ ዋው የሚያስብሉ ነገሮችን ያሟላ ሸበላ ሰው.....
......
"እሺ ዛሬ ብዙም የምንማረው ነገር አይኖረንም እርስ በርሳችን እንተዋወቅና ኮርስ አውትላይን እሰጣችኋለሁ...... እምም ከፊት ልጀምር ስምሽን አስተዋውቂን እስኪ...." ምኑ ነው ምን አለ እስከምረጋጋ እንኳን ሌላ ሰው ቢጠይቅ
"ህያብ በዛብህ እባላለሁ የመጣሁት ከአዲስ አበባ" ጣቱን ከኔ ቀጥሎ ወዳለችው ልጅ ጠቆመ
"መቅደስ ገዛህኝ..... ከሀዋሳ
ተፈሪ ይልማ...... ከደሴ
አብሳላት አበበ.... ከአዳማ
የትናዬት ዘመረ..... ከአዲስ አበባ......" ሁሉም ስማቸውን እና የመጡበትን ከተማ ተናገሩ ሁላችንንም ከሰማ በኋላ
" የኔ ስም ደግሞ ዮናታን ይባላል የ...." ከዚህ በኋላ ያለውን አልሰማሁትም .... ዮናታን.... ዮኒ ስሙ ደስ ይላል መልኩም ደስ ይላል። ሳላውቀው ስለሱ ብዙ አሰብኩ.... እጄ ላይ ያረፈ ወረቀት ከሀሳቤ አነቃኝ
"ያልኩትን ሰምተሽኛል ህያብ" ድንብርብሬ ወቶ አይን አይኑን አየው ጀመር እሱም ትንሽ ካየኝ በኋላ
" ተወካይ እስክትመርጡ ድረስ አንቺ ተወካይ ሆነሽ እነኝህን ወረቀቶች ለሁሉም አዳርሺ...." መልሴን ሳይጠብቅ ክፍሉን ለቆ ወጣ። እንዴ ቆይ ደግሞ ስሜን እንዴት ባንዴ ያዘው..... ይገርማል
........
" እና እኔንም አፈዘዘኝ እያልሽኝ ነው" አለችኝ ከፊት ለፊቴ መጥታ
"ይቅርታ እህቴ ምን......"
."ቅድም አልሰማሽኝም የትናየት.... የትናዬት ነው ስሜ"
"እሺ የትናዬት የምትይው አልገባኝም"
"ቀስ ብሎ ይገባሻል ለማንኛውም የራሴን ልውሰድ." አንዱን ወረቀት አንስታ እየተቆናጠረች ከክፍሉ ወጣች።
"ወይ አምላኬ ስንት አይነት ሰው አለ" ብዬ ስዞር ሁሉም አፍጠው የሚያዩኝ እኔን ነው።
ህይወት ልክ በምኞታችን ውስጥ እንዳሰብናት ቀላልና ጣፋጭ አይደለችም። ልንመራት ያወጣነውን እቅድ አስጥላ በራሷ ምህዋር ላይ ታሽከረክረናለች። እምቢ ብለን ብናስቸግራት እንኳን ወይ ከራሳችን እቅድ ወይም ሽክርክሪቱ ከሚያመጣው ነገር ሳንቋደስ ሜዳ ላይ እንቀራለን።
ዩንቨርስቲ መግባትን ሳስብ የሚታየኝ ጠንክሮ መማርና መማር ብቻ ነበር። ግቢ ውስጥ ሆኜ ከትምህርቴ የበለጠ ቦታ እሰጠዋለሁ ብዬ የማስበው ምንም ነገር አልነበረም። የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ እያለሁ የሆነ ሰው መጥቶ ይህን ጥያቄ ቢጠይቀኝ በመጠየቁ ልናደድበት እችል ነበር። ዛሬ ግን ያን እምነቴን የትላንት እቅዴን ሊያከሽፍ የሚችል ፍቅር ያዘኝ። ያውም ውድድር የበዛበት ፍቅር.....
አብሬው ልሁን ብዬ ባስብ እንኳን ከሱ እኔን አለማፍቀር ውጪ ከደርዘን በላይ ሴቶች ጋር መጋፈጥ ይኖርብኛል..... ያውም እኔ የማውቃቸው ብቻ።
ያለኝ አማራጭ አንድ ብቻ ነው ቢከብደኝም ስሜቴን አምቄ መያዝ እና በሰላም ትምህርቴን መቀጠል። ምንም ሳይተነፍሱ ሁሉንም በልብ መያዝ ከምንም በላይ ህመም ነው.... በተለይ ደግሞ ፍቅር ሲሆን...
ብዙ ጊዜ ይሄን አስባለሁ ለእናቴ ይሄ አይገባትም አይደል? ... ስኬቴን ለምትናፍቅ እናቴ ስል ከመጋፈጥ ይልቅ መሸሽን መርጫለሁ። የምሸሽበት ምክንያት ዋናው ቁም ነገሩ እኮ ማፍቀሬ አይደለም ፍቅር በየትኛውም ጊዜ እና ሁኔታ ውስጥ ሊከሰት የሚችል ስሜት ነው። ችግሩ ለዚህ ፍቅር ስል ብፋለም ለትምህርት የሚሆን ነፃ አይምሮ ላገኝ እችላለው ወይ? የበለጠው ችግር ደግሞ ያፈቀርኩት ሰው ሁሉንም ቀማሽ መሆኑ ነው።
፧፧፧፧፧፧
ከዛን ቀን ጀምሮ ማለትም ከመጀመሪያ የትምህርት ቀናችን ጀምሮ በዮኒ ፍቅር ተለክፊያለሁ። ፍቅር እንደያዘኝ እንኳን እያወኩ ላለማመን ከራሴ ጋር ለወራት ተከራክሪያለሁ። የትናዬት በየቀኑ እኔን ማስበርገግ ስራዬ ብላ ከያዘች ቆይታለች። በተለይ ዮናታን አስተምሮን ሲወጣ ወይ ከጎኔ ናት ወይም ከፊት ለፊቴ.... እልፍ ጊዜ እኮ አብረው አይቻቸዋለሁ... ብዙ ጊዜ ቢሮው ስትገባ ያዩዋት ነግረውኛል...... እኔ ደግሞ በተቃራኒው ከሱ ጋር የሚያገናኘን ድልድይ ሁላ ላፈርስ የምሞክር ሰው ነኝ። ለምን ይሄን ያክል የቤት ስራ እንደሆንኩባት አላውቅም። አሁን ግን መሮኛል ፀብ ላለመፍጠር እያልኩ እንደፈሪ መታየት መሮኛል።
ዛሬም እንደለመደችው ከጥሩ ትወና ጋር የአሽሙር ንግግሯን ተናግራኝ ከክፍሉ ወጣች። ብሽቅ ብዬ ወረቀቶቼን ሰብስቤ ተከትያት እየወጣሁ እያለ አንድ ሰው ከኋላዬ ያዘኝ። ዞር ስል ቢኒ ነው ከተማሪዎች ሁሉ የተለየው ዝምተኛ ልጅ።
"አቤት ቢኒ" አልኩት ኮስተር ብዬ... ግንባሬን አይቶ እጁን ከክንዴ ላይ አነሳ እና
"ይቅርታ ህያብ.... ጣልቃ ልገባ ፈልጌ አይደለም ግን እኔ የታየኝን አንድ ነገር ልበልሽ..."
"ምን"
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
///
የሚሰቀጥጥ የድንጋጤ ጩኸት…‹እስቲ ምን መሆኔ ነው..…?ይሄ እንደሚከሰት እንዴት ቀድሜ ሳላስብ ……?ወንዙ ውስጥ ዘልዬ ስገባ እሱን ፍለጋ አይደለ እንዴ ….? እና ላገኘው እንደምችል እና ሊያዝለኝ ወይም ሊያቅፈኝ እንደሚችል እንዴት ሳልገምት…..…? ገምቼስ ከሆነ አሁን እንዲህ ለገዛ እራሴ እስኪሰቀጥጠኝ ድረስ መጮኼ ምን የሚሉት ቅብጠት ነው……? ››
ብላ እሯሷን በሯሷ ታዘበች፡፡
እንግዳው ሰው ግን ጩኸቷን ከቁብ አልቆጠረም ..እንደዛው በጀርባው እንዳዘላት ወንዙን መሀል በቁመቱ በመሰንጠቅ ከነበሩበት ሁለት መቶ ሜትር ያህል ርቀት ይዞት ተሰፈነጠረ ….ከፍራቻ ይሁን ከፍቅር አታውቅም ጥምጥም አለችበት….ዞሮ ተመለሰና ልብሷ ያለበት ቦታ ሲደርስ ወደዳር በመጠጋት ድንጋዩን በእጁ ይዞ እረፍት ወሰደ… ከዛው ከውሀ ውስጥ ሳይወጡ እሷም አንገቱ ላይ ተንጠልጥላ እንደተጣበቀችበት ማውራት ጀመሩ
‹‹ምን አይነት ሰይጣን ነህ….…?››
‹‹ቆንጆ ሰይጣን…?››መለሰላት፡፡
‹‹ሂድ ከዚህ …እንዴት እንዲህ ታስደነግጠኛለህ ?››የኩርፊያ በሚመስል የድምጽ ቅላፄ ገሰፀችው፡፡
‹‹ደነገጥሽ እንዴ የእኔ ፍቅር..…?ደግሞ እንዲህ ድንቅ የዋና ችሎታ እያለሽ ነው ሳምንት ሙሉ ስትግደረደሪ የነበረው…?››
‹‹መዋኛት አልችልም መች አልኩህ..…? አልፈልግም እንጂ ፡፡››
‹‹ ዛሬ ታዲያ ምን ተገኘ…?››
‹‹ውሀ ልቀዳ ነዋ…››
መልሷን እንደሰማ ሳቁን ለቀቀው፡፡ ..ደነገጠች‹‹ ..ምን ተሳሳትኩ..…?››መለስ ብላ ከአንደበቷ የወጣውን ንግግር አሰበች…‹‹ውይ ምን አይነት ቀሺም ነኝ…?፡፡››አለች
ጄሪካኗን እዛ ዳር ጥላ ልብሷን አውልቃ ወንዙ መሀከል ገብታ ውስጥ ለውስጥ እየተሹለከለከች እየዋኘች አግኝቷት ዉሀ ልቀዳ ነው ብላ መመለሷ እንኳን ለእሱ ለእሷም አስቂኝ ነው፡፡
‹‹የቀረው መስሎሽ ደነግጠሽ ነው አይደል….…?ከአንደበትሽ መስማት ደስ ስለሚለኝ ነው እንጂ እኮ ከፈለግኩ ከልብሽ ማንበብ እችላለሁ…ያው ስለማፈቅርሽ ልብሽን ሰርስሬ በመግባት ልሰልልሽ አልፈልግም….››
‹‹ምን ታስፈራራኛለህ…ከቻልክ አድርገው››ፎከረችበት፡
‹‹እንግዴያው ገባሁ… ወንዙ ውስጥ የገባሽው መዋኘት ፈልገሽ ሳይሆን ስለቀረሁብሽ ደንግጠሸ ነው… እኔን ፍለጋ ነው ሳታስቢበት በደመነፍስ የገባሽው››
‹‹እንዴ ጥንቅር ብለህ ቅራ ….ምንድነው ሚያስደነግጠኝ…?›››
‹‹ብታምኚ ምን አለበት… እኔ እንደወደድኩሽ አንቺም ወደሺኛል…››
‹‹አሁን ወሬ አታብዛ..እንዴት አድርጌ ነው አንተን ልወድህ የምችለው……?››
‹‹ምን ማለት ነው…?››
‹‹ሰው ሁን ሰይጣን እንኳን መለየት አልቻልኩም፡፡ወይ ምን ይታወቃል ብዙ ሰው ጨፍጭፈህ በወንጀል የምትፈለገ የመንግሰት ታዳኝ ልትሆንም ትችላለህ፡ አይ እንደዛ አይደለም ብለህ እራስህን መከላከል የምትፈልግ ከሆነ እስኪ ከተማ ውስጥ አግኘኝና ልደነቅ…ወይንም ደግሞ ቤትህ ውሰደኝ…››
‹‹እስኪ ምን ማለቴ ነው ለሳምንት የማውቀውን ሰው ከታማ አግኘኝ ምለው....?እሺ አግኝቶኝ ምን ያድርገኝ….…?እቤትህ ውሰደኝ ማለትስ… …?ይሄኛውማ ባስ ያለ ዕብደት ነው›ሥትል በውስጧ
በእፍረትን በቁጭት ተብሰለሰለች፡
እሱ ንግግሩን ቀጠለ…‹‹እንደዛ ካደረግኩ ብቻ ነው እዳማፈቀርሺኝ የምታምኚው…?››
‹‹ማምነው ሳይሆን..ምን አልባት ላፈቅርህ የምሞክረው››አለችው ..፡
እውነቱ ግን ከተማ ባያገኛትም ወይም እቤቱ ፍቃደኛ ሆኗ ባይወስዳትም ..አንዴ በመጨራሻው አቅሟ አፍቅራዋለች…. ምንም ሚቀንስ ምንም ሚጨምር ነገር የለም….፡፡
እሱ ግን አላሳፈራትም ..ውስጧን አንብቦ ይመስላል ‹‹እሺ ሰሞኑን እቤቴ ወስድሻለሁ...አሁን ግን አንቺን ማዘሉ ከበደኝ ….ውረጂልኝ››አላት…
በጣም ነው የደነገጠችው፡፡.ለካ ይሄን ሁሉ የምትቀደው አጆቾን በአንገቱ ዙሬያ ጠምጥማ በጀርባው በኩል ከእርቃን ሰውነቱ ላይ እንደተጣበቀች ነበር…በርግጋ እጆቾን ከአንገቱ አላቀቀችና በጀርባዋ ወደኃላ ወንዙ ላይ ተዘረረች….፡፡
‹‹ለዚህ እኮ ነው ምወድሽ…ፐ በተለይ እርቃንሽን ውብ ነሽ››ብሏት ጭርሽ አሳፈራት፡፡
እዛው ወንዝ ውስጥ ጥላው ወጣችና ጀሪካኑን ወደወንዙ መሀል ወረወረችለት…‹‹ወሬውን ተውና ልብሴን እስክለብስ ድረስ ሙላልኝ…››አለችው፡፡
‹‹ታዛዥ ነኝ የእኔ እመቤት ..››…..ብሎ ተስፈንጥሮ ጄሪካኑን ቀለበና ይቀዳላት ጀመረ ..እሷም ብስብስ ያለውን ቀሚሷን ካስቀመጠችበት ቦታ አነሳችና ለበሰችው፡፡
ተንዘፈዘፈች..፡፡በለሊት መዋኘት ውሀ ውስጥ ይሞቃል….ችግሩ ከወንዙ ውስጥ ሲወጡ ነው፡፡አየሩ ቀዝቃዛ ስለሆነ እንኳን እርጥብ ልብስ ደርበውበት ይቅርና ደረቅም ልብስ ቢለብሱበት መብረዱ አይቀርም ነበር….፡፡
ጄሪካኑን ሞልቶ ወደ ዳር አወጣላትና አቀበላት…ተቀበለችውና አንጠልጥላ ከፍ ያለ የግንድ ጉማጅ ላይ በማስቀመጥ ዞራ በጀርባዋ በፎጣው አዘለችና ስትጨርስ‹‹በል ቻው››አለችው
በቀዝቃዛው አየርና በረጠበቅ ልብሷ ምክንያት ሰውነቷ ሲንዘፈዘፍ ታዝቦፈኲ ‹‹ከቀሚስሽ ላይ ውሀው እኮ እየተንጠፈጠፈ ነው››አላት፡፡
‹‹ቅድም አንሸራቶኝ እኮ ወንዙ ውስጥ ከነ ልብሴ ገባሁ…...ለዛ እኮ ነው መግባቴ ካልቀረ ልዋኝ ብዬ የቀጠልኩበት..››አለችው እፍረት እየተሰማት፡፡
‹‹ግን እኮ ተንሸራተሽ ሳይሆን ዘለሽ ስትገቢ ነው ያየሁት››ብሎት እርፍ
‹‹እና እንኳን ዘለልኳ…. በራሴ ቀሚስ ምን አገባህ?››
የሌባ አይነ ደረቅ መልሶ ልብ አድርቅ ቢጤ ሆነችበት…እንደውሸታምና ቀልማዳ ሴት ሆና በእሱ መገመት አትፈልግም..እሱ ደግሞ ካለ ባህሪው ምንም አይነት ሽራፊ ውሸት ሰምቶ እንዳልሰማ አውቆ እንዳላወቀ ማለፍ አይሆንለትም፡፡
‹‹አትበሳጪ …ባይሆን ቀሚስሽን ላድረቅልሽ››
‹‹እንዴት አድርገህ ነው የምታደርቅልኝ…? ››
‹‹እስኪ ጠጋ በይ››
‹‹ለምንድነው የምጠጋው..››
‹‹ግድ የለሽም እኔ ከወንዙ ከምወጣ አንቼ ጠጋ በይ››
‹‹…ምን ታማጣለህ?›› በሚል እልክ ተጠጋችለት ….እጁን ሰነዘረና ውሀ የሚንጠፈጠፍበትን የቀሚሷን ጠርዝ ጨበጠው…. ማመን አልቻለችም ….ችስስስስስ በማለት እየተነነ ፍም የሞላበት ጊርጊራ ውስጥ እጣን ሲጨመር የሚወጣ አይነት ጭስ ለአንድ ደቂቃ ያህል ከልብሷ ተነነ …. እናም ኩርምት እስኪል ድረስ ቀሚሷ ደረቀ ..አፏን በአድናቆት ከፍታ ምን እንደምትናገር ግራ ገብቷኝ እያለ ተስፈንጥሮ ውሀ ውስጥ ሰምጦ እንደወትሮው ተሰወረባት…..
✨ይቀጥላል✨
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
///
የሚሰቀጥጥ የድንጋጤ ጩኸት…‹እስቲ ምን መሆኔ ነው..…?ይሄ እንደሚከሰት እንዴት ቀድሜ ሳላስብ ……?ወንዙ ውስጥ ዘልዬ ስገባ እሱን ፍለጋ አይደለ እንዴ ….? እና ላገኘው እንደምችል እና ሊያዝለኝ ወይም ሊያቅፈኝ እንደሚችል እንዴት ሳልገምት…..…? ገምቼስ ከሆነ አሁን እንዲህ ለገዛ እራሴ እስኪሰቀጥጠኝ ድረስ መጮኼ ምን የሚሉት ቅብጠት ነው……? ››
ብላ እሯሷን በሯሷ ታዘበች፡፡
እንግዳው ሰው ግን ጩኸቷን ከቁብ አልቆጠረም ..እንደዛው በጀርባው እንዳዘላት ወንዙን መሀል በቁመቱ በመሰንጠቅ ከነበሩበት ሁለት መቶ ሜትር ያህል ርቀት ይዞት ተሰፈነጠረ ….ከፍራቻ ይሁን ከፍቅር አታውቅም ጥምጥም አለችበት….ዞሮ ተመለሰና ልብሷ ያለበት ቦታ ሲደርስ ወደዳር በመጠጋት ድንጋዩን በእጁ ይዞ እረፍት ወሰደ… ከዛው ከውሀ ውስጥ ሳይወጡ እሷም አንገቱ ላይ ተንጠልጥላ እንደተጣበቀችበት ማውራት ጀመሩ
‹‹ምን አይነት ሰይጣን ነህ….…?››
‹‹ቆንጆ ሰይጣን…?››መለሰላት፡፡
‹‹ሂድ ከዚህ …እንዴት እንዲህ ታስደነግጠኛለህ ?››የኩርፊያ በሚመስል የድምጽ ቅላፄ ገሰፀችው፡፡
‹‹ደነገጥሽ እንዴ የእኔ ፍቅር..…?ደግሞ እንዲህ ድንቅ የዋና ችሎታ እያለሽ ነው ሳምንት ሙሉ ስትግደረደሪ የነበረው…?››
‹‹መዋኛት አልችልም መች አልኩህ..…? አልፈልግም እንጂ ፡፡››
‹‹ ዛሬ ታዲያ ምን ተገኘ…?››
‹‹ውሀ ልቀዳ ነዋ…››
መልሷን እንደሰማ ሳቁን ለቀቀው፡፡ ..ደነገጠች‹‹ ..ምን ተሳሳትኩ..…?››መለስ ብላ ከአንደበቷ የወጣውን ንግግር አሰበች…‹‹ውይ ምን አይነት ቀሺም ነኝ…?፡፡››አለች
ጄሪካኗን እዛ ዳር ጥላ ልብሷን አውልቃ ወንዙ መሀከል ገብታ ውስጥ ለውስጥ እየተሹለከለከች እየዋኘች አግኝቷት ዉሀ ልቀዳ ነው ብላ መመለሷ እንኳን ለእሱ ለእሷም አስቂኝ ነው፡፡
‹‹የቀረው መስሎሽ ደነግጠሽ ነው አይደል….…?ከአንደበትሽ መስማት ደስ ስለሚለኝ ነው እንጂ እኮ ከፈለግኩ ከልብሽ ማንበብ እችላለሁ…ያው ስለማፈቅርሽ ልብሽን ሰርስሬ በመግባት ልሰልልሽ አልፈልግም….››
‹‹ምን ታስፈራራኛለህ…ከቻልክ አድርገው››ፎከረችበት፡
‹‹እንግዴያው ገባሁ… ወንዙ ውስጥ የገባሽው መዋኘት ፈልገሽ ሳይሆን ስለቀረሁብሽ ደንግጠሸ ነው… እኔን ፍለጋ ነው ሳታስቢበት በደመነፍስ የገባሽው››
‹‹እንዴ ጥንቅር ብለህ ቅራ ….ምንድነው ሚያስደነግጠኝ…?›››
‹‹ብታምኚ ምን አለበት… እኔ እንደወደድኩሽ አንቺም ወደሺኛል…››
‹‹አሁን ወሬ አታብዛ..እንዴት አድርጌ ነው አንተን ልወድህ የምችለው……?››
‹‹ምን ማለት ነው…?››
‹‹ሰው ሁን ሰይጣን እንኳን መለየት አልቻልኩም፡፡ወይ ምን ይታወቃል ብዙ ሰው ጨፍጭፈህ በወንጀል የምትፈለገ የመንግሰት ታዳኝ ልትሆንም ትችላለህ፡ አይ እንደዛ አይደለም ብለህ እራስህን መከላከል የምትፈልግ ከሆነ እስኪ ከተማ ውስጥ አግኘኝና ልደነቅ…ወይንም ደግሞ ቤትህ ውሰደኝ…››
‹‹እስኪ ምን ማለቴ ነው ለሳምንት የማውቀውን ሰው ከታማ አግኘኝ ምለው....?እሺ አግኝቶኝ ምን ያድርገኝ….…?እቤትህ ውሰደኝ ማለትስ… …?ይሄኛውማ ባስ ያለ ዕብደት ነው›ሥትል በውስጧ
በእፍረትን በቁጭት ተብሰለሰለች፡
እሱ ንግግሩን ቀጠለ…‹‹እንደዛ ካደረግኩ ብቻ ነው እዳማፈቀርሺኝ የምታምኚው…?››
‹‹ማምነው ሳይሆን..ምን አልባት ላፈቅርህ የምሞክረው››አለችው ..፡
እውነቱ ግን ከተማ ባያገኛትም ወይም እቤቱ ፍቃደኛ ሆኗ ባይወስዳትም ..አንዴ በመጨራሻው አቅሟ አፍቅራዋለች…. ምንም ሚቀንስ ምንም ሚጨምር ነገር የለም….፡፡
እሱ ግን አላሳፈራትም ..ውስጧን አንብቦ ይመስላል ‹‹እሺ ሰሞኑን እቤቴ ወስድሻለሁ...አሁን ግን አንቺን ማዘሉ ከበደኝ ….ውረጂልኝ››አላት…
በጣም ነው የደነገጠችው፡፡.ለካ ይሄን ሁሉ የምትቀደው አጆቾን በአንገቱ ዙሬያ ጠምጥማ በጀርባው በኩል ከእርቃን ሰውነቱ ላይ እንደተጣበቀች ነበር…በርግጋ እጆቾን ከአንገቱ አላቀቀችና በጀርባዋ ወደኃላ ወንዙ ላይ ተዘረረች….፡፡
‹‹ለዚህ እኮ ነው ምወድሽ…ፐ በተለይ እርቃንሽን ውብ ነሽ››ብሏት ጭርሽ አሳፈራት፡፡
እዛው ወንዝ ውስጥ ጥላው ወጣችና ጀሪካኑን ወደወንዙ መሀል ወረወረችለት…‹‹ወሬውን ተውና ልብሴን እስክለብስ ድረስ ሙላልኝ…››አለችው፡፡
‹‹ታዛዥ ነኝ የእኔ እመቤት ..››…..ብሎ ተስፈንጥሮ ጄሪካኑን ቀለበና ይቀዳላት ጀመረ ..እሷም ብስብስ ያለውን ቀሚሷን ካስቀመጠችበት ቦታ አነሳችና ለበሰችው፡፡
ተንዘፈዘፈች..፡፡በለሊት መዋኘት ውሀ ውስጥ ይሞቃል….ችግሩ ከወንዙ ውስጥ ሲወጡ ነው፡፡አየሩ ቀዝቃዛ ስለሆነ እንኳን እርጥብ ልብስ ደርበውበት ይቅርና ደረቅም ልብስ ቢለብሱበት መብረዱ አይቀርም ነበር….፡፡
ጄሪካኑን ሞልቶ ወደ ዳር አወጣላትና አቀበላት…ተቀበለችውና አንጠልጥላ ከፍ ያለ የግንድ ጉማጅ ላይ በማስቀመጥ ዞራ በጀርባዋ በፎጣው አዘለችና ስትጨርስ‹‹በል ቻው››አለችው
በቀዝቃዛው አየርና በረጠበቅ ልብሷ ምክንያት ሰውነቷ ሲንዘፈዘፍ ታዝቦፈኲ ‹‹ከቀሚስሽ ላይ ውሀው እኮ እየተንጠፈጠፈ ነው››አላት፡፡
‹‹ቅድም አንሸራቶኝ እኮ ወንዙ ውስጥ ከነ ልብሴ ገባሁ…...ለዛ እኮ ነው መግባቴ ካልቀረ ልዋኝ ብዬ የቀጠልኩበት..››አለችው እፍረት እየተሰማት፡፡
‹‹ግን እኮ ተንሸራተሽ ሳይሆን ዘለሽ ስትገቢ ነው ያየሁት››ብሎት እርፍ
‹‹እና እንኳን ዘለልኳ…. በራሴ ቀሚስ ምን አገባህ?››
የሌባ አይነ ደረቅ መልሶ ልብ አድርቅ ቢጤ ሆነችበት…እንደውሸታምና ቀልማዳ ሴት ሆና በእሱ መገመት አትፈልግም..እሱ ደግሞ ካለ ባህሪው ምንም አይነት ሽራፊ ውሸት ሰምቶ እንዳልሰማ አውቆ እንዳላወቀ ማለፍ አይሆንለትም፡፡
‹‹አትበሳጪ …ባይሆን ቀሚስሽን ላድረቅልሽ››
‹‹እንዴት አድርገህ ነው የምታደርቅልኝ…? ››
‹‹እስኪ ጠጋ በይ››
‹‹ለምንድነው የምጠጋው..››
‹‹ግድ የለሽም እኔ ከወንዙ ከምወጣ አንቼ ጠጋ በይ››
‹‹…ምን ታማጣለህ?›› በሚል እልክ ተጠጋችለት ….እጁን ሰነዘረና ውሀ የሚንጠፈጠፍበትን የቀሚሷን ጠርዝ ጨበጠው…. ማመን አልቻለችም ….ችስስስስስ በማለት እየተነነ ፍም የሞላበት ጊርጊራ ውስጥ እጣን ሲጨመር የሚወጣ አይነት ጭስ ለአንድ ደቂቃ ያህል ከልብሷ ተነነ …. እናም ኩርምት እስኪል ድረስ ቀሚሷ ደረቀ ..አፏን በአድናቆት ከፍታ ምን እንደምትናገር ግራ ገብቷኝ እያለ ተስፈንጥሮ ውሀ ውስጥ ሰምጦ እንደወትሮው ተሰወረባት…..
✨ይቀጥላል✨
#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
.....‹‹ሁላችንስ ሸርሙጦች አይደለን? እሷ ሸርሙጣ መሆኗን በአዋጅ ያስነገረች የአደባባይ ሸርሙጣ ስትሆን እኔ እና አንቺ ደግሞ ጓሮ ለጓሮ ከሠው ተሸሽገን በሚሥጥ የምንወሰብ ሸርሙጦች ነን፡፡ አሁንም እኮ የመጣሽው እንድንሸረሙጥ ፈልገሽ መሠለኝ >>
ሠውነቷ ተንቀጠቀጠባት፣የጨጓራዋ ቁስለት ሲለበልባት ይሰማታል፡፡ በትንግርት ጉዳይ ብዙ ጊዜ ተጨቃጭቀዋል፡፡ ለቀናቶች በተደጋጋሚ ተኮራርፈውም ያውቃሉ እስከአሁ የተለወጠ ነገር ባይኖርም፡፡ ብዙ ጊዜ እርግፍ አድርጋ ልትተወው ታስብና መሸነፍ ደግሞ ያስጠላታል.... እልህ ትገባለች፡፡‹‹እና ተመልስ እንድሄድልህ ትፈልጋለህ?››
‹‹እንደፈለግሽ፡፡››...
መሄድ አልፈለገችም፡፡ የምትወደውን ገላ፣በፍቅር የምትሰቃይለትን ሠውነት፣የምትራብለትን ትንፋሽ አይኗ እያየ አለሌ ለምትላት ትንግርት አስረክባ ወደ ቤት ሄዳ የሠላም እንቅልፍ እንደማትተኛ ስለገባት እዚሁ ቆይታ እውነታውን በመጋፈጥ ለመፋለም ወሰነች፡፡በዚህ ቅፅበት ነበር መለስ ብሎ የነበረው የሳሎን በር በድንገት ተበርግዶ የተከፈተው፡፡
እንደመንገዳገድ ብላ ቆመች ትንግርት ነች፡፡ ከላይ ከደረቷ እስከ እምብርቷ ከስር ደግሞ ከመቀመጫዋ ብዙም የማይረዝም እራፊ ጨርቅ እላይዋ ላይ ጣል አድርጋለች፣ ከትከሻዋ አልፎ ወደ መቀመጫዋ የሚጠጋውን እንደ ሀር የሚጠቁረ ፀጉሯን በትግሬዎች ባህላዊ ሹሩባ አሰራር ተሰርታ አሽሞንሙናዋለች፡፡ ጎላ ጎላ ያሉ አይኖቿን በኩል ይበልጥ ደምቀዋል፡፡ በተረፈ ፊቷ ንፁህ ነው፡፡ በሜካፕ አልተጨማለቀም፡፡ በአጠቃላይ እርቃኗን የቀረች ክንፍ አልባ በሰው አካል ውስጥ ሰርጋ የምትንቀሳቀስ መንፈስ መስላለች፡፡
ሁሴን አስተውሏት ምራቁን ዋጠ፡፡ ትንግርት ሁለቱንም በደከሙ አይኖቿ እያፈራረቀች አየችና ፍርፍር ብላ ሳቀች፡፡ ‹‹ኪ.ኪ.. ኪ...
እንደምንም ተረጋግታ መናገር ጀመረ፡፡‹‹ጋሼ ጋዜ..ጠኛው፤ ዛሬ ደግሞ ሁለታ..ችንም በአንድ ጊዜ አሠኘንህ?›› አለች በተኮለታተፈ አንደበት፡፡
ከዚህ በፊት ሁለቱ በአካል ተገናኝተው ባያውቁም አንደኛዋ ስለሌላዋ ታሪክ በደንብ ያውቃሉ፡፡ ትንግርት ኤደንን በሩቅ አይታት ታውቃለች፡፡ ኤደን ግን የትንግርትን መልክ ስታይ የመጀመሪያ ጊዜዋ ነው፡፡ ደነገጠች..ዘወትር ሸርሙጣ ብላ የምታንቋሽሻት ጣውንቷ የዚህን ያህል አፍዛዥ ውበት አላት ብላ ገምታ አታውቅም ነበር፡፡
ሁሴን‹‹ቁጭ በይ›› አላት፡፡ተንደርድራ ከጎኑ ሄዳ ተቀመጠችና ጉንጩን ሳመችው፡፡ ኤደን ላለማየት ፊቷን ወደ ሌላ አቅጣጫ አዞረች፤
እራሷን ለመቆጣጠር ከፍተኛ ትንቅንቅ ላይ
‹‹እሺ እህት... ደህና ነሽ?›› ትንግርት ነበረች የሽሙጥ ይሁን የትህትና ባለየለት ቃና ሠላምታ ለኤደን የሠነዘረችው፡፡ አልመለሠችላትም፡፡
የኋላ በር ተከፈተና ፎዚያ ገባች፡፡ ግራ በተጋባ ሁኔታ እንግዶቹን እያፈራረቀች ከቃኘች በኋላ በመርበትበት ለሁለቱም ሠላምታ አቀረበች፡፡ ሁለቱ በአንድ ቀን በአንድ ላይ ሲመጡ ስትመለከት ይሄ የመጀመሪያ ቀን ገጠመኟ ነው፡፡
‹‹ሃይ..›› አለቻት ትንግርት፡፡ ኤደን በዝምታዋ እንደቀጠለች ነው፡፡
ፎዚያ‹‹እራት ላቅርብ?››ብላ ወደ ሁሴን በመዞር ጠየቀች፡፡
‹‹አቅርቢ፡፡›› መለሰላት፡፡
‹‹ጋዜጠኛው.... ሳልጠግብ ነው የመጣሁት፤ መጠጥ እፈልጋለሁ፡፡›› ትንግርት ነች ጠያቂዋ፡፡
‹‹ኦኬ›› በማለት ከተቀመጠበት ተነሳና ሙሉ የውስኪ ጠርሙስ ከሦስት ብርጭቆ ጋር ይዞ በመምጣት በየተራ ለሁሉም እስከ ድርበብ ቀዳላቸው፡፡ ለሁለቱ ሴቶች አድሎ ለራሱም ይዞ ወደ መቀመጫው ተመለሰ፡፡ ቀድማ መጠጣት የጀመረችው ኤደን ነበረች፡፡ በአንድ ትንፋሽ ግማሹን ማገችው፡፡
ትንግርት በመገረም‹‹እንዴ...?››. አለች፡፡
‹‹ምን ሆነሻል?›› በግልምጫ ጠየቀች ኤደን፡፡
‹‹የቤት ልጆችም እንዲህ ትጠጣላችሁ እንዴ?››
‹‹ከሸርሙጦች ነው የተማርኩት፡፡›› የመልስ ምት ሠነዘረች፡፡
‹‹ሠካራምነቱ ብቻ ነው… ወይስ ሽርሙጥናውንም? ፡፡››
ኤደን ሌላ መልስ ለመመለስ ስታሞጠሙጥ ፎዚያ የምግብ ሠሀኖችን ይዛ ገባችና ጠረጴዛ ላይ ኮለኮለችው፡፡ ትንግርትም ከተቀመጠችበት ሶፋ ተንደርድራ በመነሳት ወደ ምግብ ጠረጴዛው እየሄደች ‹‹ጋዜጣኛው... ካልበላሁ ለሊቱን በደንብ ላስደስትህ አቅም አይኖረኝም›› አለችው፡፡
ምንም አልመለሰላትም፡፡ የእንካ ሠላምታው ተሳታፊ ላለመሆን ወስኖ በዝምታ እንደተሸበበ ወደ ምግብ ጠረጴዛው ቀረበ፡፡
‹‹እመቤት እንብላ እንጂ፡፡›› አለቻት ትንግርት ወደ ኤደን በፈገግታ እየተመለከተች፡፡
ከግልምጫ ውጪ መልስ አልመለሰችላትም፡፡ ይልቅስ መጠጡን ከብርጭቆ አጋባችና ሁለተኛውን ሞልታ ቀዳች፡፡
‹‹እራት አትበይም እንዴ?›› ሁሴን ጠየቃት፡፡
‹‹ነገር አጥግቦኛል›› መለሠችለት፡፡
‹‹የእኔ እህት አንድ ምክር ልለግስሽ.. ለዘመኑ ወንድ እንዲህ በግነሽ አትችይም፡፡ ወንዱ ሁሉ ንፋስ ሆኗል፡፡ እንደ አነፋፈሱ አብረሽ ካልነፈስሽ ዕድሜሽ አጭር ይሆናል፡፡ የሠብለወንጌልና የበዛብህ አይነት በድንግልና እስከ መቃብር ድረስ ተማምኖ የመዝለቅን አይነት ፍቅር በዚህ ዘመን እየፈለግሽ ከሆነ በእውነት አንቺ ገና ከእንቅልፍሽ ያልነቃሽ ህልመኛ ነሸ፡፡››
‹‹ይሄንን ፍልስፍና…ማስተርስሽን በሽርሙጥና ስትሰሪ ነው ያስተማሩሽ?››
‹‹ይሆናል .. አንቺን ከማስረዳት በእርግማን የፈራረሰችውን ባቢሎን መልሶ መገንባት ይቀላል፤አርፌ እራቴን ብበላ ይበጀኛል፡፡›› በማለት መብላቱ ላይ አተኮረች፡፡
ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኃላ ሁሴንና ትንግርት ምግባቸውን ተመግበው ወደ በፊት መቀመጫቸው በመመለስ መጠጡን
ተያያዙት፡፡ ትንግርትና ኤደን በመጠጥ እኔ እበልጥ እኔ እበልጥ የሚፎካከሩ ይመስላል፡፡ ሁሴንም በተመስጦ እየኮመኮመ ይመለከታቸዋል፡፡ በመሀከል ኤደን መተኛት እንደምትፈልግ መጠጥ ባሠከረውና በተኮላተፈ አፏ ተናገረች፡፡
‹‹ያው ግቢና ተኚ ››በማለት ከሱ መኝታ ክፍል ቀጥሎ ያለውን ሌላ መኝታ ክፍል ጠቆማት፡፡
‹‹ምን ማለትህ ነው?››
‹‹እንዴት ምን ማለት?››
ትንግርት ሳቅ አፈናትና እጆቿን አደራርባ አፏን ከደነች፡፡
‹‹አንተስ?››ኤደን ነች አሁንም ጠያቂዋ፡፡
‹‹እኔማ መኝታ ክፍሌ ተኛለሁ፡፡››
‹‹እንዴ ነችና ልጅት! ... እሷስ?››
‹‹እሷ ደግሞ ካንቺ ፊት ለፊት ካለው መኝታ ቤት ትተኛለች፡፡››
ትንግርት ጣልቃ ገባች፡፡ ‹‹ብሬን ግን ከች ነው፡፡››
እጁን ወደ ኪሱ ሠደደና ድፍን አምስት የመቶ ብር ወረቀቶች አውጥቶ ሠጣት፡፡
‹‹እግዜር ይስጥልኝ የእኔ እህት፡፡ ማታ አንዱ ጎረምሳ ስብርብሬን አውጥቶኝ ስለነበር ድክም ብሎኝ ነበር፡፡ አንቺ ባትመጪ ደግሞ ጋሼ ጋዜጠኛው በእዛ በምታውቂው ጠንካራ ዕቃው ሲሠነጣጥቀኝ ነበር የሚያድረው፡፡››
በማለት የሠጣትን ብር ጨምድዳ ቦርሳዋ ውስጥ ከታ እየተወላገደች ወደ ተመደበላት መኝታ ክፍል አመራች፡፡ በራፉ ላይ እንደደረሰች የረሳችው ነገር እንዳለ ፊቷን መልሳ ‹‹አንተ ጋዜጠኛ… ለምን ግን ያቺ ደራሲህንም ሳትጠራት? ሦስት ብንሆን ደግሞ ቤትህ ይበልጥ ይደምቅልህ ነበር!››
‹‹ጠርቼያታለሁ...እሷ እዚህ ውስጥ ነው ያለችው፡፡›› አላት በጣቱ ወደ ልቡ እየጠቆመ፡፡
‹‹ታድላለች....ልብህ ውስጥ ካለችማ እሷ ነች ማለት ነው አብራህ የምታድረው፡፡ እመቤት ኤደን አየሽ.. እኔ እና አንቺ ስንፎካከር ሌላዋ ጩልሌ ቀማችን፡፡ ለምን ግን ተስማምተን ለሁለት አናገባውም?››
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
.....‹‹ሁላችንስ ሸርሙጦች አይደለን? እሷ ሸርሙጣ መሆኗን በአዋጅ ያስነገረች የአደባባይ ሸርሙጣ ስትሆን እኔ እና አንቺ ደግሞ ጓሮ ለጓሮ ከሠው ተሸሽገን በሚሥጥ የምንወሰብ ሸርሙጦች ነን፡፡ አሁንም እኮ የመጣሽው እንድንሸረሙጥ ፈልገሽ መሠለኝ >>
ሠውነቷ ተንቀጠቀጠባት፣የጨጓራዋ ቁስለት ሲለበልባት ይሰማታል፡፡ በትንግርት ጉዳይ ብዙ ጊዜ ተጨቃጭቀዋል፡፡ ለቀናቶች በተደጋጋሚ ተኮራርፈውም ያውቃሉ እስከአሁ የተለወጠ ነገር ባይኖርም፡፡ ብዙ ጊዜ እርግፍ አድርጋ ልትተወው ታስብና መሸነፍ ደግሞ ያስጠላታል.... እልህ ትገባለች፡፡‹‹እና ተመልስ እንድሄድልህ ትፈልጋለህ?››
‹‹እንደፈለግሽ፡፡››...
መሄድ አልፈለገችም፡፡ የምትወደውን ገላ፣በፍቅር የምትሰቃይለትን ሠውነት፣የምትራብለትን ትንፋሽ አይኗ እያየ አለሌ ለምትላት ትንግርት አስረክባ ወደ ቤት ሄዳ የሠላም እንቅልፍ እንደማትተኛ ስለገባት እዚሁ ቆይታ እውነታውን በመጋፈጥ ለመፋለም ወሰነች፡፡በዚህ ቅፅበት ነበር መለስ ብሎ የነበረው የሳሎን በር በድንገት ተበርግዶ የተከፈተው፡፡
እንደመንገዳገድ ብላ ቆመች ትንግርት ነች፡፡ ከላይ ከደረቷ እስከ እምብርቷ ከስር ደግሞ ከመቀመጫዋ ብዙም የማይረዝም እራፊ ጨርቅ እላይዋ ላይ ጣል አድርጋለች፣ ከትከሻዋ አልፎ ወደ መቀመጫዋ የሚጠጋውን እንደ ሀር የሚጠቁረ ፀጉሯን በትግሬዎች ባህላዊ ሹሩባ አሰራር ተሰርታ አሽሞንሙናዋለች፡፡ ጎላ ጎላ ያሉ አይኖቿን በኩል ይበልጥ ደምቀዋል፡፡ በተረፈ ፊቷ ንፁህ ነው፡፡ በሜካፕ አልተጨማለቀም፡፡ በአጠቃላይ እርቃኗን የቀረች ክንፍ አልባ በሰው አካል ውስጥ ሰርጋ የምትንቀሳቀስ መንፈስ መስላለች፡፡
ሁሴን አስተውሏት ምራቁን ዋጠ፡፡ ትንግርት ሁለቱንም በደከሙ አይኖቿ እያፈራረቀች አየችና ፍርፍር ብላ ሳቀች፡፡ ‹‹ኪ.ኪ.. ኪ...
እንደምንም ተረጋግታ መናገር ጀመረ፡፡‹‹ጋሼ ጋዜ..ጠኛው፤ ዛሬ ደግሞ ሁለታ..ችንም በአንድ ጊዜ አሠኘንህ?›› አለች በተኮለታተፈ አንደበት፡፡
ከዚህ በፊት ሁለቱ በአካል ተገናኝተው ባያውቁም አንደኛዋ ስለሌላዋ ታሪክ በደንብ ያውቃሉ፡፡ ትንግርት ኤደንን በሩቅ አይታት ታውቃለች፡፡ ኤደን ግን የትንግርትን መልክ ስታይ የመጀመሪያ ጊዜዋ ነው፡፡ ደነገጠች..ዘወትር ሸርሙጣ ብላ የምታንቋሽሻት ጣውንቷ የዚህን ያህል አፍዛዥ ውበት አላት ብላ ገምታ አታውቅም ነበር፡፡
ሁሴን‹‹ቁጭ በይ›› አላት፡፡ተንደርድራ ከጎኑ ሄዳ ተቀመጠችና ጉንጩን ሳመችው፡፡ ኤደን ላለማየት ፊቷን ወደ ሌላ አቅጣጫ አዞረች፤
እራሷን ለመቆጣጠር ከፍተኛ ትንቅንቅ ላይ
‹‹እሺ እህት... ደህና ነሽ?›› ትንግርት ነበረች የሽሙጥ ይሁን የትህትና ባለየለት ቃና ሠላምታ ለኤደን የሠነዘረችው፡፡ አልመለሠችላትም፡፡
የኋላ በር ተከፈተና ፎዚያ ገባች፡፡ ግራ በተጋባ ሁኔታ እንግዶቹን እያፈራረቀች ከቃኘች በኋላ በመርበትበት ለሁለቱም ሠላምታ አቀረበች፡፡ ሁለቱ በአንድ ቀን በአንድ ላይ ሲመጡ ስትመለከት ይሄ የመጀመሪያ ቀን ገጠመኟ ነው፡፡
‹‹ሃይ..›› አለቻት ትንግርት፡፡ ኤደን በዝምታዋ እንደቀጠለች ነው፡፡
ፎዚያ‹‹እራት ላቅርብ?››ብላ ወደ ሁሴን በመዞር ጠየቀች፡፡
‹‹አቅርቢ፡፡›› መለሰላት፡፡
‹‹ጋዜጠኛው.... ሳልጠግብ ነው የመጣሁት፤ መጠጥ እፈልጋለሁ፡፡›› ትንግርት ነች ጠያቂዋ፡፡
‹‹ኦኬ›› በማለት ከተቀመጠበት ተነሳና ሙሉ የውስኪ ጠርሙስ ከሦስት ብርጭቆ ጋር ይዞ በመምጣት በየተራ ለሁሉም እስከ ድርበብ ቀዳላቸው፡፡ ለሁለቱ ሴቶች አድሎ ለራሱም ይዞ ወደ መቀመጫው ተመለሰ፡፡ ቀድማ መጠጣት የጀመረችው ኤደን ነበረች፡፡ በአንድ ትንፋሽ ግማሹን ማገችው፡፡
ትንግርት በመገረም‹‹እንዴ...?››. አለች፡፡
‹‹ምን ሆነሻል?›› በግልምጫ ጠየቀች ኤደን፡፡
‹‹የቤት ልጆችም እንዲህ ትጠጣላችሁ እንዴ?››
‹‹ከሸርሙጦች ነው የተማርኩት፡፡›› የመልስ ምት ሠነዘረች፡፡
‹‹ሠካራምነቱ ብቻ ነው… ወይስ ሽርሙጥናውንም? ፡፡››
ኤደን ሌላ መልስ ለመመለስ ስታሞጠሙጥ ፎዚያ የምግብ ሠሀኖችን ይዛ ገባችና ጠረጴዛ ላይ ኮለኮለችው፡፡ ትንግርትም ከተቀመጠችበት ሶፋ ተንደርድራ በመነሳት ወደ ምግብ ጠረጴዛው እየሄደች ‹‹ጋዜጣኛው... ካልበላሁ ለሊቱን በደንብ ላስደስትህ አቅም አይኖረኝም›› አለችው፡፡
ምንም አልመለሰላትም፡፡ የእንካ ሠላምታው ተሳታፊ ላለመሆን ወስኖ በዝምታ እንደተሸበበ ወደ ምግብ ጠረጴዛው ቀረበ፡፡
‹‹እመቤት እንብላ እንጂ፡፡›› አለቻት ትንግርት ወደ ኤደን በፈገግታ እየተመለከተች፡፡
ከግልምጫ ውጪ መልስ አልመለሰችላትም፡፡ ይልቅስ መጠጡን ከብርጭቆ አጋባችና ሁለተኛውን ሞልታ ቀዳች፡፡
‹‹እራት አትበይም እንዴ?›› ሁሴን ጠየቃት፡፡
‹‹ነገር አጥግቦኛል›› መለሠችለት፡፡
‹‹የእኔ እህት አንድ ምክር ልለግስሽ.. ለዘመኑ ወንድ እንዲህ በግነሽ አትችይም፡፡ ወንዱ ሁሉ ንፋስ ሆኗል፡፡ እንደ አነፋፈሱ አብረሽ ካልነፈስሽ ዕድሜሽ አጭር ይሆናል፡፡ የሠብለወንጌልና የበዛብህ አይነት በድንግልና እስከ መቃብር ድረስ ተማምኖ የመዝለቅን አይነት ፍቅር በዚህ ዘመን እየፈለግሽ ከሆነ በእውነት አንቺ ገና ከእንቅልፍሽ ያልነቃሽ ህልመኛ ነሸ፡፡››
‹‹ይሄንን ፍልስፍና…ማስተርስሽን በሽርሙጥና ስትሰሪ ነው ያስተማሩሽ?››
‹‹ይሆናል .. አንቺን ከማስረዳት በእርግማን የፈራረሰችውን ባቢሎን መልሶ መገንባት ይቀላል፤አርፌ እራቴን ብበላ ይበጀኛል፡፡›› በማለት መብላቱ ላይ አተኮረች፡፡
ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኃላ ሁሴንና ትንግርት ምግባቸውን ተመግበው ወደ በፊት መቀመጫቸው በመመለስ መጠጡን
ተያያዙት፡፡ ትንግርትና ኤደን በመጠጥ እኔ እበልጥ እኔ እበልጥ የሚፎካከሩ ይመስላል፡፡ ሁሴንም በተመስጦ እየኮመኮመ ይመለከታቸዋል፡፡ በመሀከል ኤደን መተኛት እንደምትፈልግ መጠጥ ባሠከረውና በተኮላተፈ አፏ ተናገረች፡፡
‹‹ያው ግቢና ተኚ ››በማለት ከሱ መኝታ ክፍል ቀጥሎ ያለውን ሌላ መኝታ ክፍል ጠቆማት፡፡
‹‹ምን ማለትህ ነው?››
‹‹እንዴት ምን ማለት?››
ትንግርት ሳቅ አፈናትና እጆቿን አደራርባ አፏን ከደነች፡፡
‹‹አንተስ?››ኤደን ነች አሁንም ጠያቂዋ፡፡
‹‹እኔማ መኝታ ክፍሌ ተኛለሁ፡፡››
‹‹እንዴ ነችና ልጅት! ... እሷስ?››
‹‹እሷ ደግሞ ካንቺ ፊት ለፊት ካለው መኝታ ቤት ትተኛለች፡፡››
ትንግርት ጣልቃ ገባች፡፡ ‹‹ብሬን ግን ከች ነው፡፡››
እጁን ወደ ኪሱ ሠደደና ድፍን አምስት የመቶ ብር ወረቀቶች አውጥቶ ሠጣት፡፡
‹‹እግዜር ይስጥልኝ የእኔ እህት፡፡ ማታ አንዱ ጎረምሳ ስብርብሬን አውጥቶኝ ስለነበር ድክም ብሎኝ ነበር፡፡ አንቺ ባትመጪ ደግሞ ጋሼ ጋዜጠኛው በእዛ በምታውቂው ጠንካራ ዕቃው ሲሠነጣጥቀኝ ነበር የሚያድረው፡፡››
በማለት የሠጣትን ብር ጨምድዳ ቦርሳዋ ውስጥ ከታ እየተወላገደች ወደ ተመደበላት መኝታ ክፍል አመራች፡፡ በራፉ ላይ እንደደረሰች የረሳችው ነገር እንዳለ ፊቷን መልሳ ‹‹አንተ ጋዜጠኛ… ለምን ግን ያቺ ደራሲህንም ሳትጠራት? ሦስት ብንሆን ደግሞ ቤትህ ይበልጥ ይደምቅልህ ነበር!››
‹‹ጠርቼያታለሁ...እሷ እዚህ ውስጥ ነው ያለችው፡፡›› አላት በጣቱ ወደ ልቡ እየጠቆመ፡፡
‹‹ታድላለች....ልብህ ውስጥ ካለችማ እሷ ነች ማለት ነው አብራህ የምታድረው፡፡ እመቤት ኤደን አየሽ.. እኔ እና አንቺ ስንፎካከር ሌላዋ ጩልሌ ቀማችን፡፡ ለምን ግን ተስማምተን ለሁለት አናገባውም?››
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ለሀለቃዋ ትብለጥ ፍቅረኛዋ መሞቱ ድብርት ውስጥ እንደከታት ተናግራ የአንድ ወር ፍቃድ ወሰደች፡፡እረፍቷን ጨርሳ ተመልሳ ከመግባቷ በፊት መጽሀፉም አልቆ እስከወዲያኛው ይገላግላት ይሆናል፡፡አዎ ተስፋዋ ያ ነው፡፡
ሳባ እረፍት ከወሰደች በኋላ ቤት መዋል ጀመረች፡፡ራሷን መቆጣጠር እስኪያቅታት ድረስም ኃይለኛ መደበትና ጭንቀት ውስጥ ገባች፡፡እርግጥ ይሄ
የመደበት ችግር አሁን ፍቅረኛዋ ስለሞተ ወይም እሷ ራሷ ስላስገደለችው ድንገት የተከሰተባት በሽታ አይደለም…ከእሷ ጋር ሶስት አራት አመት በደባልነት ኖሯል…ቢያንስ በስድስት ወር አንዴ የሆነ ምክንያት ፈልጎ ይቀሰቀስባታል፡፡
ይተወኛል ብላ ለ15 ቀን ከቤቷ ሳትወጣ እረፍት ለማድረግ ብትሞክርም ነገሮች ግን እየባሱባት መጡ..በዚህም ምክንያት የስነ-ልቦና ባለሞያ እንድታናግር አንድ ወዳጇ ጨቀጨቃትና በሀሳቡ ተሰማምታ የጠቆማት ሆስፒታል ሄደች፡፡
በተቻላት መጠን ጥሩ አለባበስ ለብሳ ፤ከወትሮዋ በተሻለ ነቃ ለማለት፤ የተቻላትን ጥረት አድርጋ በጠዋት ተነስታ መኪናዋን አስነስታ በተሰጣት አድራሻ ሄደች፡፡ቀድማ ደውላ ቀጠሮ አስይዛ ስለነበረ.እንደሄደች ነበር ነርሷ የተወሰኑ ፎርሞችን እንድትሞላ በማድረግ ወደ ዶክተሩ እንድትገባ ያደረገቻት፡፡
ብዙ ጊዜ ለህክምና ወደተለያዩ የከተማዋ ስመጥር ሆስፒታሎች ሄዳ አገልግሎት አግኝታ ታውቃለች…አሁንም የገባችበት የዶክተሩ ምርመራ ክፍል ከዚህ በፊት ከምታውቃቸውና ከጎበኘቻቸው ብዙም የተለየ አይደለም…ግን በራፉን ከፍታ ወደውስጥ እንደገባች ፈዛለች፡፡ለውስጧ ጥልቅ ድረስ እስኪሰማት ድረስ ደንዝዛለች፡፡
‹‹ጤና ይስጥልኝ አረፍ በይ›› ሲላት ሁሉ አልሰማችውም.አይኗን አይኖቹ ላይ ተክላ በቆመችበት ቅዝዝ ብላ እየተመለከተችው ነው፡፡
እጁ ላይ ያለውን የእሷን ካርድ እየተመለከተ ‹‹ወይዘሪት ሳባ….አረፍ በይ››ሲላት እንደምንም ከመደንዘዝ ለመንቃት እየሞከረች እግሯን የመጎተት ያህል አንቀሳቀሰችና እንድትቀመጥ በተነገራት ወንበር ላይ ተቀመጠች፡፡
‹‹እሺ ሳባ ዶ/ር ጀማል እባላለሁ.››ሲል ራሱን አስተዋወቃት፡፡
ዝም አለችው
‹‹እስኪ ስለራስሽ ጥቂት ንገሪኝ›› አላት፡፡
‹‹ግራ ገባት..ሀኪም ቤት ለስነ-ልቦና ህክምና የመጣች ሳይሆን የሆነ ካፌ ውስጥ ቁጭ ብላ የሆነ አማላይ ወንድ ወንበሯን ተጋርቶ ሊጀነጅናት ሙከራ እያደረገ እሷ ደግሞ እየተግደረደረችና እየተሸኮረመመች ያለች ነው የመሰላት፡፡
‹‹ስለእኔ ምን?››
‹‹ስለ ማንኛውም ነገር….ሳባ ማን ነች?ምንድነው የምትወደው? ምንድነው የምትሰራው? ፡፡››
‹‹ስራዬ የሆነ የግል ድርጅት ውስጥ ተቀጥሬ ነው ምሰራው…ተቀጥሬ እንኳን ማለት ይከብዳል…በኮሚሽን ነው የምሰራው፡፡የምኖረው ብቻዬን ነው…ማለት አንድ ዘበኛ እና ተመላላሽ የቤት ሰራተኛ አለኝ... ጥሩ ኑሮ እኖራለው፡፡ግን ደግሞ ብቸኛ እና ደስታ የራቀኝ ሰው ነኝ..ሁሉ ነገር እየሰለቸኝ ነው…ለምን እንደምኖር እራሱ ግራ እየጋባኝ ነው፡፡››ሁሉን ነገር ተወችና ቀጥታ ወደ መደምደሚያው በመሻገር አሁን ሰላለችበት ሁኔታ ወደማብራራቱ ተስፈነጠረች፡፡
‹‹ጥሩ…. እንዲህ አይነት ስሜት ይሰማሽ የጀመረው ከመቼ ጀምሮ ነው?››
‹‹ሶስት አራት አመት..ግን የከፋ የሆነው ከሀያ ቀን በፊት ጀምሮ ነው፡፡፡››
‹‹በቅርብ በህይወትሽ የተከሰተ ጠንከር ያለ ነገር ነበር?››
‹‹አዎ ለአንድ አመት ፍቅረኛዬ የነበረ ሰው ቀለበት እያሰረልኝ ሳለ እኔ የማላውቃት ልጅ ፍቅረኛው ሆና በጠርሙስ ጭንቅላቱን ከፈለችውና ሞተ…ከዛ ወዲህ ይመስለኛል ነገሮች እየባሱ የሄዱት፡፡››የታሪኩን ግማሽ እውነት ነገረችው፡፡
‹‹ገባኝ….ግን የትኛው ነው በጣም ያመመሽ…?››ሲል ጠየቃት
‹‹ከምንና ከምኑ?››
‹‹ከፍቅረኛሽ ሞትና….ከመከዳትሽ?››
ደነገጠች…እንዲህ ፈፅሞ አስባ አታውቅም..‹‹መከዳት…ስለፍቅረኛው ማለትህ ነው?››
‹‹አዎ››
ዝም አለች..ምን እንደምትመልስ ግራ ገባት፡፡ሳባ ልክ እንደጓደኛሽ ቁጠሪኝ ….ነፃ ሁኚ፡፡
‹‹አይ ፋሲልን .ማለቴ ፍቅረኛዬን በተመለከተ የሚሰማኝ ስሜት ግራ የተጋባ ነው…ሞቱ ይሄን ያህል ይረብሸኛል ብዬ ፈፅሞ አስቤ አላውቅም ነበር….የእኔና የእሱ ግንኙነት በተወሰኑ የጋራ ጥቅሞች ላይ የተመሰረተ ነበር…ፍቅረኛውን በተመለከተ ምንም የሚሰማኝ ነገር የለም..በእርግጥ እስከመጨረሻው ቀን ምንም የማውቀው ነገር አልነበረም..ባውቅም በእኔ ላይ ማግጦብኛል ብዬ የምበሳጭበት ምክንያት አይታየኝም...እኔም ታምኜለት አላውቅም እሱም ይታመንልኛል የሚል እምነት አልነበረኝም..እውነቱን ለመናገር እንዲታመንልኝም ፍላጎቱ አልነበረኝም.. በአጠቃላይ ስለፍቅረኛው ማወቄ ምንም ትርጉም የሰጠኝ አይመስለኝም፡፡››
‹‹ምን አልባት ትዳሩን ትፈልጊው ነበር…?በእሱ ሞት ምክንያት በመበላሸቱ ተበሳጭተሻል?››
‹‹በተአምር እንደዛ አይነት ፍላጎት አልነበረኝም...ቀለበቱን ሲያደርግልኝ ድንገት ሳያማክረኝ ነበር ያደረገው...ማማከር ሳይሆን ስለወደፊታችን አውርተን እንኳን አናውቅም...እንዳገባው ሲጠይቀኝ በጣም ብዙ በሚያውቁት ሰዎች ፊት ስለሆነ እሱን ላለማሸማቀቅ እና ግርግር ላለመፍጠር ነበር ጣቴን የዘረጋሁለት..እና መቼም ላገባው እቅድ አልነበረኝም፡፡ግን የገረመኝ በመሞቱ በውስጤ ቅሬታ ተፈጥሯል …ፈፅሞ ልረሳው አልቻልኩም…ከእሱ የማጣው አንድ ብቸኛ ነገር ወሲብ ነው….ያንን ደግሞ ካሰብኩበት ከሌላ ሰው በቀላሉ ማግኘት እችላለሁ…ያው የእሱን ያህል ሊሆን ባይችልም ማለቴ ነው..እና ለምን ከአዕምሮዬ ላወጣው እንዳልቻልኩ አልገባኝም፡››
‹‹ግን እሱ ብቻ ነው የሚያስጨንቅሽ? ማለቴ እሱ በህይወት እያለስ ሌላ ምቾት የሚነሳሽ ጉዳይ ነበር?››
‹‹እየተጠነቀቀች እራሷን ከመጠን በላይ ላለማጋለጥ እየጣረች ከሁለት ሰዓት በላይ ከዶ/ሩ ጋር አወራች….በጊዜያዊነት የሚያረጋጓትን ሁለት መድሀኒቶችን መውሰድ ከሚገባት የተወሰነ ምክር ጋር ለግሷት ለሳምንት ሌላ ቀጠሮ ሰጥቷት አሰናበታት….
በመምጣቷ ተደስታለች …በዶ/ሩ መስተንግዶ ተደስታለች..ልቧ ለምን እንደደነገጠባት አልገባትም…ያምራል…ከአይኖቹ የሚረጫቸው ብርሀን የሰውን ልብ በቀላሉ ይሰረስራሉ፡፡ንግግሩ እርጋታ የተለባሰና እንዲያወሩ የሚያበረታታ ነው፡፡ በዛ የተነሳ በቆይታዋ ተደስታለችም…የተወሰነ ቀለል የማለት ስሜትም እየተሰማት ነው..ትንሽ ቅር ያላት ቀጠሮ ከሳምንት በኋላ መሆኑ ነው፡፡ ከሁለት ወይም ከሶስት ቀን በኋላ መልሳ ብታገኘው ደስ ይላት ነበር.ደግነቱ ችግር ካለና የተለየ ስሜት ከተሰማት እንድትደውልለት ነግሯት ቁጥሩን ሰጥቷታል፡፡መኪናዋን ራሷ እያሽረከረች ቀጥታ ወደቤቷ ሄደች..አዲሱ ዘበኛዋ በራፉን ከፈተና ወደ ውስጥ አስገባት..፡፡ይሄንን ዘበኛ ከቀጠረች አስር ቀን ቢሆነው ነው፡፡የመጀመሪያውን ዘበኛ ያሰናበተችው የመጀመሪየውን ዘበኛ ከእሷ ጋር አስተዋውቋት ያስቀጠረው ፋሲል ስለነበረ ነው፡፡ከእሱ ጋር የሚያገናኛት ምንም አይነት ትዝታ አትፈልግም፡፡ደግሞ ምን አይነት ሚስጥራዊ ግንኙነት እንዳላቸው ስለማታውቅና በዛም ጥርጣሬ ስለነበራት ያልሰራበትን የሶስት ወር ደሞዙን ሰጥታ አሰናበተችው፡፡
ከዛም እንደተለመደው መኝታ ቤቷ ገባችና ራሷን ሸሸገች..
💫ይቀጥላል💫
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ለሀለቃዋ ትብለጥ ፍቅረኛዋ መሞቱ ድብርት ውስጥ እንደከታት ተናግራ የአንድ ወር ፍቃድ ወሰደች፡፡እረፍቷን ጨርሳ ተመልሳ ከመግባቷ በፊት መጽሀፉም አልቆ እስከወዲያኛው ይገላግላት ይሆናል፡፡አዎ ተስፋዋ ያ ነው፡፡
ሳባ እረፍት ከወሰደች በኋላ ቤት መዋል ጀመረች፡፡ራሷን መቆጣጠር እስኪያቅታት ድረስም ኃይለኛ መደበትና ጭንቀት ውስጥ ገባች፡፡እርግጥ ይሄ
የመደበት ችግር አሁን ፍቅረኛዋ ስለሞተ ወይም እሷ ራሷ ስላስገደለችው ድንገት የተከሰተባት በሽታ አይደለም…ከእሷ ጋር ሶስት አራት አመት በደባልነት ኖሯል…ቢያንስ በስድስት ወር አንዴ የሆነ ምክንያት ፈልጎ ይቀሰቀስባታል፡፡
ይተወኛል ብላ ለ15 ቀን ከቤቷ ሳትወጣ እረፍት ለማድረግ ብትሞክርም ነገሮች ግን እየባሱባት መጡ..በዚህም ምክንያት የስነ-ልቦና ባለሞያ እንድታናግር አንድ ወዳጇ ጨቀጨቃትና በሀሳቡ ተሰማምታ የጠቆማት ሆስፒታል ሄደች፡፡
በተቻላት መጠን ጥሩ አለባበስ ለብሳ ፤ከወትሮዋ በተሻለ ነቃ ለማለት፤ የተቻላትን ጥረት አድርጋ በጠዋት ተነስታ መኪናዋን አስነስታ በተሰጣት አድራሻ ሄደች፡፡ቀድማ ደውላ ቀጠሮ አስይዛ ስለነበረ.እንደሄደች ነበር ነርሷ የተወሰኑ ፎርሞችን እንድትሞላ በማድረግ ወደ ዶክተሩ እንድትገባ ያደረገቻት፡፡
ብዙ ጊዜ ለህክምና ወደተለያዩ የከተማዋ ስመጥር ሆስፒታሎች ሄዳ አገልግሎት አግኝታ ታውቃለች…አሁንም የገባችበት የዶክተሩ ምርመራ ክፍል ከዚህ በፊት ከምታውቃቸውና ከጎበኘቻቸው ብዙም የተለየ አይደለም…ግን በራፉን ከፍታ ወደውስጥ እንደገባች ፈዛለች፡፡ለውስጧ ጥልቅ ድረስ እስኪሰማት ድረስ ደንዝዛለች፡፡
‹‹ጤና ይስጥልኝ አረፍ በይ›› ሲላት ሁሉ አልሰማችውም.አይኗን አይኖቹ ላይ ተክላ በቆመችበት ቅዝዝ ብላ እየተመለከተችው ነው፡፡
እጁ ላይ ያለውን የእሷን ካርድ እየተመለከተ ‹‹ወይዘሪት ሳባ….አረፍ በይ››ሲላት እንደምንም ከመደንዘዝ ለመንቃት እየሞከረች እግሯን የመጎተት ያህል አንቀሳቀሰችና እንድትቀመጥ በተነገራት ወንበር ላይ ተቀመጠች፡፡
‹‹እሺ ሳባ ዶ/ር ጀማል እባላለሁ.››ሲል ራሱን አስተዋወቃት፡፡
ዝም አለችው
‹‹እስኪ ስለራስሽ ጥቂት ንገሪኝ›› አላት፡፡
‹‹ግራ ገባት..ሀኪም ቤት ለስነ-ልቦና ህክምና የመጣች ሳይሆን የሆነ ካፌ ውስጥ ቁጭ ብላ የሆነ አማላይ ወንድ ወንበሯን ተጋርቶ ሊጀነጅናት ሙከራ እያደረገ እሷ ደግሞ እየተግደረደረችና እየተሸኮረመመች ያለች ነው የመሰላት፡፡
‹‹ስለእኔ ምን?››
‹‹ስለ ማንኛውም ነገር….ሳባ ማን ነች?ምንድነው የምትወደው? ምንድነው የምትሰራው? ፡፡››
‹‹ስራዬ የሆነ የግል ድርጅት ውስጥ ተቀጥሬ ነው ምሰራው…ተቀጥሬ እንኳን ማለት ይከብዳል…በኮሚሽን ነው የምሰራው፡፡የምኖረው ብቻዬን ነው…ማለት አንድ ዘበኛ እና ተመላላሽ የቤት ሰራተኛ አለኝ... ጥሩ ኑሮ እኖራለው፡፡ግን ደግሞ ብቸኛ እና ደስታ የራቀኝ ሰው ነኝ..ሁሉ ነገር እየሰለቸኝ ነው…ለምን እንደምኖር እራሱ ግራ እየጋባኝ ነው፡፡››ሁሉን ነገር ተወችና ቀጥታ ወደ መደምደሚያው በመሻገር አሁን ሰላለችበት ሁኔታ ወደማብራራቱ ተስፈነጠረች፡፡
‹‹ጥሩ…. እንዲህ አይነት ስሜት ይሰማሽ የጀመረው ከመቼ ጀምሮ ነው?››
‹‹ሶስት አራት አመት..ግን የከፋ የሆነው ከሀያ ቀን በፊት ጀምሮ ነው፡፡፡››
‹‹በቅርብ በህይወትሽ የተከሰተ ጠንከር ያለ ነገር ነበር?››
‹‹አዎ ለአንድ አመት ፍቅረኛዬ የነበረ ሰው ቀለበት እያሰረልኝ ሳለ እኔ የማላውቃት ልጅ ፍቅረኛው ሆና በጠርሙስ ጭንቅላቱን ከፈለችውና ሞተ…ከዛ ወዲህ ይመስለኛል ነገሮች እየባሱ የሄዱት፡፡››የታሪኩን ግማሽ እውነት ነገረችው፡፡
‹‹ገባኝ….ግን የትኛው ነው በጣም ያመመሽ…?››ሲል ጠየቃት
‹‹ከምንና ከምኑ?››
‹‹ከፍቅረኛሽ ሞትና….ከመከዳትሽ?››
ደነገጠች…እንዲህ ፈፅሞ አስባ አታውቅም..‹‹መከዳት…ስለፍቅረኛው ማለትህ ነው?››
‹‹አዎ››
ዝም አለች..ምን እንደምትመልስ ግራ ገባት፡፡ሳባ ልክ እንደጓደኛሽ ቁጠሪኝ ….ነፃ ሁኚ፡፡
‹‹አይ ፋሲልን .ማለቴ ፍቅረኛዬን በተመለከተ የሚሰማኝ ስሜት ግራ የተጋባ ነው…ሞቱ ይሄን ያህል ይረብሸኛል ብዬ ፈፅሞ አስቤ አላውቅም ነበር….የእኔና የእሱ ግንኙነት በተወሰኑ የጋራ ጥቅሞች ላይ የተመሰረተ ነበር…ፍቅረኛውን በተመለከተ ምንም የሚሰማኝ ነገር የለም..በእርግጥ እስከመጨረሻው ቀን ምንም የማውቀው ነገር አልነበረም..ባውቅም በእኔ ላይ ማግጦብኛል ብዬ የምበሳጭበት ምክንያት አይታየኝም...እኔም ታምኜለት አላውቅም እሱም ይታመንልኛል የሚል እምነት አልነበረኝም..እውነቱን ለመናገር እንዲታመንልኝም ፍላጎቱ አልነበረኝም.. በአጠቃላይ ስለፍቅረኛው ማወቄ ምንም ትርጉም የሰጠኝ አይመስለኝም፡፡››
‹‹ምን አልባት ትዳሩን ትፈልጊው ነበር…?በእሱ ሞት ምክንያት በመበላሸቱ ተበሳጭተሻል?››
‹‹በተአምር እንደዛ አይነት ፍላጎት አልነበረኝም...ቀለበቱን ሲያደርግልኝ ድንገት ሳያማክረኝ ነበር ያደረገው...ማማከር ሳይሆን ስለወደፊታችን አውርተን እንኳን አናውቅም...እንዳገባው ሲጠይቀኝ በጣም ብዙ በሚያውቁት ሰዎች ፊት ስለሆነ እሱን ላለማሸማቀቅ እና ግርግር ላለመፍጠር ነበር ጣቴን የዘረጋሁለት..እና መቼም ላገባው እቅድ አልነበረኝም፡፡ግን የገረመኝ በመሞቱ በውስጤ ቅሬታ ተፈጥሯል …ፈፅሞ ልረሳው አልቻልኩም…ከእሱ የማጣው አንድ ብቸኛ ነገር ወሲብ ነው….ያንን ደግሞ ካሰብኩበት ከሌላ ሰው በቀላሉ ማግኘት እችላለሁ…ያው የእሱን ያህል ሊሆን ባይችልም ማለቴ ነው..እና ለምን ከአዕምሮዬ ላወጣው እንዳልቻልኩ አልገባኝም፡››
‹‹ግን እሱ ብቻ ነው የሚያስጨንቅሽ? ማለቴ እሱ በህይወት እያለስ ሌላ ምቾት የሚነሳሽ ጉዳይ ነበር?››
‹‹እየተጠነቀቀች እራሷን ከመጠን በላይ ላለማጋለጥ እየጣረች ከሁለት ሰዓት በላይ ከዶ/ሩ ጋር አወራች….በጊዜያዊነት የሚያረጋጓትን ሁለት መድሀኒቶችን መውሰድ ከሚገባት የተወሰነ ምክር ጋር ለግሷት ለሳምንት ሌላ ቀጠሮ ሰጥቷት አሰናበታት….
በመምጣቷ ተደስታለች …በዶ/ሩ መስተንግዶ ተደስታለች..ልቧ ለምን እንደደነገጠባት አልገባትም…ያምራል…ከአይኖቹ የሚረጫቸው ብርሀን የሰውን ልብ በቀላሉ ይሰረስራሉ፡፡ንግግሩ እርጋታ የተለባሰና እንዲያወሩ የሚያበረታታ ነው፡፡ በዛ የተነሳ በቆይታዋ ተደስታለችም…የተወሰነ ቀለል የማለት ስሜትም እየተሰማት ነው..ትንሽ ቅር ያላት ቀጠሮ ከሳምንት በኋላ መሆኑ ነው፡፡ ከሁለት ወይም ከሶስት ቀን በኋላ መልሳ ብታገኘው ደስ ይላት ነበር.ደግነቱ ችግር ካለና የተለየ ስሜት ከተሰማት እንድትደውልለት ነግሯት ቁጥሩን ሰጥቷታል፡፡መኪናዋን ራሷ እያሽረከረች ቀጥታ ወደቤቷ ሄደች..አዲሱ ዘበኛዋ በራፉን ከፈተና ወደ ውስጥ አስገባት..፡፡ይሄንን ዘበኛ ከቀጠረች አስር ቀን ቢሆነው ነው፡፡የመጀመሪያውን ዘበኛ ያሰናበተችው የመጀመሪየውን ዘበኛ ከእሷ ጋር አስተዋውቋት ያስቀጠረው ፋሲል ስለነበረ ነው፡፡ከእሱ ጋር የሚያገናኛት ምንም አይነት ትዝታ አትፈልግም፡፡ደግሞ ምን አይነት ሚስጥራዊ ግንኙነት እንዳላቸው ስለማታውቅና በዛም ጥርጣሬ ስለነበራት ያልሰራበትን የሶስት ወር ደሞዙን ሰጥታ አሰናበተችው፡፡
ከዛም እንደተለመደው መኝታ ቤቷ ገባችና ራሷን ሸሸገች..
💫ይቀጥላል💫
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
#ኢትዬጵያዊቷ_ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
:
:
#ክፍል_አራት
:
:
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ፔሩ/ኢኩኤቶስ
ኑሀሚ በተኛችበት አጨንቁራ በመስታወቱ አሻግራ እያየችው ነው፡፡የህይወት አዙሪት ከየት ወስዶ የት ላይ እንደወረወራት አሰበችና እጅግ ተገረመች፡፡ስለእሱ እና ስለገጠመኞቾ እያመላለሰች በማሰብ ላይ ሳለች ድንገት ወደሀገር ቤት የሚያበር የሀሳብ ሀዲድ በአእምሮዋ ተዘረጋ….ጭንቅሏቷን ትራሷ ላይ አመቻቸችና በተዝናኖት ተኝታ በተዘረጋው ሀዲድ ወደሀገር ቤት በትዝታ ፍስስ አለች፡፡ ኑሀሚ የተደላደለ እና የተረጋጋ የሚባል ህይወት የኖረችው እስከ 9 ዓመቷ ድረስ ብቻ ነበር፡፡ ከዛ በጥምቀት ሰሞን በእለተ ከተራ የዘጠኝ አመቷን የልደት በአል ሊከበርላት ድግስ ተደግሶ፤ ኬክ ታዞ፤ ሻማ ተገዝቶና ፤እቤቱ በዲኮሬሽን አሸብርቆ ባለበት ቀን እናትና አባቷ ተቃቅፈው በተኙበት ሞተው ተገኙ፡፡በምትወዳት የልደት ቀኗ በጥምቀት ቀን ጥር 11 በህይወቷ በጣም ልብ ሰባሪው ሀዘን ደረሰባት፡፡ከዛ በኃላ ህይወት ለእሷ ቀላል ሆና አታውቅም፡፡ከዛ በኃላ በአለም ላይ በ10 ደቂቃ ታላቋ ከሆነ ከመንትያ ወንድሟ በስተቀር ምንም ነገር አልነበራትም….ከዛ በኋላ አመት በመጣ ቁጥር በጥምቀት ወቅት ህዝበ- ክርስቲያኑ በየጎዳናው ተቦት ተከትለው ሲዘምሩና ሲጨፍሩ የወላጆቾን ሬሳ ተከትለው ሙሾ የሚያወርዱ ለቀስተኞች ነው የሚመስሏት…በቃ ከዛ በኃላ ሕይወት በአጠቃላይ ሁሉ ነገር አስከፊ ሁሉ ነገር አስጠዩ ነበር የሆነባት፡፡ይህ በጥልቅ ሀዘንና ብቸኝነት አጥንት የሚሰነጣጥቅ ችግር ለእሷ ብቻ ሳይሆን ለወንድሟም ጭምር ነበር፡፡ስለወንድሟ ትዝ ሲላት ከተጋደመችበት ተስፈንጥራ ተነሳችና ስልኳን በማንሳት ወደ ሀገር ቤት ደወለች…ወንድሟ ጋር፡፡
‹‹ሄሎ ናኦል…እንዴት ነህ?››
‹‹አለሁልሽ እህቴ…እንዴት ነሽ…?.ሁሉ ነገር አሪፍ ነው?፡፡››
‹‹ሰላም ነኝ.. ዛሬ ከፔሩ አንተ ወደምትወዳት ብራዚል እየበረርኩ ነበር… ግን የአየር ፀባዩ ተበላሸና ሳንደርስ አንድ የምታምር ለብራዚል ድንበር ቅርብ የሆነች የፔሩ ከተማ ለማረፍ ተገደድን፡፡››
ወንድሟ በሰማው ዜና በጣም ደነገጠ‹‹እንዴት ….?ምን አይነት ቦታ ነው ያረፋችሁት ..?ፕሌኑ ሰላም ነው?››
‹‹አረ ሁሉ ነገር አሪፍ ነው…፡፡››
‹‹እና እንዴት ልትሆኑ ነው?››
‹‹በቃ ምን እንሆናለን..አሁን ቤርጎ ይዤ አረፍ ብዬ ነው እየደወልኩልህ ያለሁት፡፡ነገ የአየር ፀባዩ ከተሻሻለ እንቀጥላለን፡፡ከለበለዚያ የዝግጅቱ አስተባባሪዎች በሚሰጡት ትዕዛዝ መሰረት የምናደርገውን እናያለን፡፡››
‹‹አህቴ እራስሽን ጠብቂ ደግሞ በጣም ናፍቀሺኛል….ጨርሰሽ እስክትመጪ ቸኩያለሁ፡፡..ሶስት ወር እንደዚህ ረጂም መሆኑን አላውቅም ነበር››ሲል ተናዘዘላት፡፡
‹‹ለምን ይዋሻል..ከዚህ በፊት እኮ ሶስት አመት ሙሉ ተለያይተን ነበር››
‹‹የዛን ጊዜ እኮ እኔ ራሴ ሀይለኛ ወከባ ላይ ነበርኩ…የአዲስአበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት አለ..በዛ ላይ በምታውቂው ስራ ሀለቃችን ምስራቅ ከወዲህ ወዲያ ታሽከረክረኝ ነበር…ከዚህ ሁሉ መዋከብ በተረፈቺኝ ብጣቂ ጊዜ ብቻ ነበር አንቺን መናፈቅ የምችለው፡፡አሁን ግን ስለአንቺ ከማሰብ ውጭ ሌላ ምን ስራ አለኝ?››ሲል ተናዘዘላት፡፡
‹‹ስለናፈቅኩህ ደሰስ ብሎኛ፤ቻለው ከአንድ ወር በታች ነው የቀረኝ…እና ደግሞ እንዲህ ዞር ስል የምናፍቅህ ከሆነ ስርህ እያለው አታበሳጨኝም ማለት ነው፡፡››
‹‹አረ አንቺ ብቻ ነይልኝ እንጂ ቀና ብዬም አላይሽም፡፡››ሲል ቃል ገባላት፡፡
‹‹ነግሬሀለው… አሁን የተናገርከውን ሪከርድ አድርጌዋለው፡፡››
‹‹ችግር የለውም እውነቴ ነው፡፡››
‹‹ምስራቅ ደህና ነች..?››ስትል ሌላ ጥያቄ ጠየቀችው፡፡
‹‹ያው ታውቂያለሽ ..እሷ ካልፈለገች አላገኛትም..ግን ደህና መሆኗን አውቃለሁ፡፡››ሲል እሷ ብቻ ሳትሆን ምስራቅም እንደናፈቀችው በሚያሳብቅ የድምፅ ቅላፄ መለሰላት፡፡ምስራቅ ማለት በሁለቱም ህይወት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ ያላት…የደህንነት መስራቤት ውስጥ የምትሰራ ሲኒዬር ሰላይና ለአመታት ሀለቃቸው የነበረች የ43 ዓመት ሴት ነች፡፡
‹‹በል ቸው ..ልተኛ ደክሞኛል ነገ ደውልልሀለው፡፡››አለችው፡፡
‹‹ቸው እህቴ …ውድድ ነው የማደርግሽ››ስልኩ ተዘጋ፡፡
አልጋውን ለቃ ወረደችና ወደ ፍሪጁ በመሄድ ሌላ የቆርቆሮ መጠጥ አወጣችና ከፍታ እየተጎነጨች ወደውጭ ወጣች፡፡ዳግላስ አሁንም ላፕቶፑ ላይ አቀርቅሮ ውዝግብ ውስጥ እንደገባ ነው፡፡የአማዞን ወንዝ ከበረንዳው አሻግረው ሲያያዩ እንደእባብ ተጠምዝዞ ሽብልል እያለ ሲፈስ ይታያል፡፡ትኩረቷን ወደዳግላስ መለሰችና‹‹እሺ አዲስ ነገር አለ?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹የተወሰነ ነገር እየገባኝ ነው፡፡ሳይንቲስት ነኝ፡፡አዎ ኬሚስት ነኝ፡፡እዚህ አማዞን ጫካ ውስጥ በሚገኝ የኮኬይ መቀመሚያ ላብ ውስጥ እሰራ ነበር፡፡አሁንም እንዴት እንደሚቀመም ፕሮሰሱን ሁሉም ትዝ ብሎኛል፡፡ግን ከዛ በፊት የት ነበርኩ..?የት ነው የተማርኩት? ቤተሰቦቼ የት ናቸው…?ሚስትና ልጆች አሉኝ…?እንዴት እዚህ ነገር ውስጥ ልገባ ቻልኩ?አሁንስ ፔሩ ምን ስሰራ ነበር..?የተሸከምኩትን ሻንጣ ሙሉ ዶላር ከየት አመጣሁት? ለምንስ ተሸከምኩት?አሁንስ ወደብራዚል ለምንድነው እየሄድኩ ያለሁት?ቀደም ብለሽ አንቺ ለጠይቅሺኝ ለእነዚህ ሁሉ ጥያቄዎች ሚሆን መልስ ግን እስከአሁን አላገኘሁም፡፡››
‹‹በቃ ላፕቶፑን ዝጋና ተነስ… ወደ ውስጥ እንግባ …ምን አልባት ለጠየቅካቸው ጥያቄዎች ሁሉ የሚሆኑ መልሶችን አረፍ ብለህ እንቅልፍ ከተኛህ በኃላ ትዝ ሊሉህ ይችላሉ፡፡ዶላሩ ላልከው ግን ምን አልባት ለአመታት ለሰራህላቸው ስራ የከፈሉህ ደሞዝ ሊሆን ይችላል፡፡ምን አልባት ከእነሱ ጋር በሰላም ተለያይተህ ሰላማዊና ኖርማል ህይወት ለመኖር ወደ ሀገርህና ቤተሰቦች በመጓዝ ላይ ትሆናለህ፡፡በል አሁን እኩለ ለሊት ሆነ ፤አረፍ እንበልና ነገ ከነገወዲያ የሚሆነውን እናያለን..ምን አልባትም እኮ ለእነዚህ ሁሉ ጥቄዎችህ መልስ የሚሰጥህ ሰው አየር ማረፊያ ቆሞ እየጠበቀህ ሊሆንም ይችላል፡፡››
‹‹አዎ እኔም ተስፋ ማደርገው እንደዛ ነው፡፡››አለና እንዳለችው ላፕቶፑን በመዝጋት መቀመጫውን ለቆ ተነሳ፡፡ ..ተያይዘው ወደ ውስጥ ገቡን ወደበረንዳ የሚያስወጣውን በራፍ በመዝጋት በየአልጋቸው ላይ ተቀመጡ፡፡
‹‹ታውቂያለሽ ከሌላ ፕላኔት ድንገት ተንሸራትቼ የወደቅኩና ያለቦታዬ ከማላውቃቸውና ከማይመስሉኝ ፍጡሮች ጋር የተቀላቀልኩ እየመሰለኝ ነው፡፡››አላት
በንግግሩ አሳዘናት‹‹አይዞኝ…..እንዳልኩህ አሁን መጨነቁን አቁምና ለማረፍ ሞክር…ጥዋት የሚሆነውን እናደርጋለን፡፡›› ብላ አልጋዋ ላይ ወጣችና ተሸፋፍና ለመተኛት መከረች፡፡ፈፅሞ እንቅልፍ ይወስደኛል ብላ አላሰበችም ነበር፡፡ግን ወዲያው ነበር ጭልጥ ያለ እንቅልፍ የወሰዳት፡፡ማለዳ 12፡40 አካባቢ ከእንቅልፏ ባና አይኗን ስትገልጥ ዳግላስ ስትተኛ ተቀምጦበት በነበረበት ቦታ ተቀምጦ ነው ያገኘችው፡፡
‹‹ምነው አልተኛህም እንዴ?››ስትል በመገረም ጠየቀችው፡፡
‹‹አይ አልተኛሁም፡››
‹‹እና እዛው የተቀመጥክበት ቦታ አነጋኸው …. ?››
( በአመዞን ደን ውስጥ)
:
:
#ክፍል_አራት
:
:
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ፔሩ/ኢኩኤቶስ
ኑሀሚ በተኛችበት አጨንቁራ በመስታወቱ አሻግራ እያየችው ነው፡፡የህይወት አዙሪት ከየት ወስዶ የት ላይ እንደወረወራት አሰበችና እጅግ ተገረመች፡፡ስለእሱ እና ስለገጠመኞቾ እያመላለሰች በማሰብ ላይ ሳለች ድንገት ወደሀገር ቤት የሚያበር የሀሳብ ሀዲድ በአእምሮዋ ተዘረጋ….ጭንቅሏቷን ትራሷ ላይ አመቻቸችና በተዝናኖት ተኝታ በተዘረጋው ሀዲድ ወደሀገር ቤት በትዝታ ፍስስ አለች፡፡ ኑሀሚ የተደላደለ እና የተረጋጋ የሚባል ህይወት የኖረችው እስከ 9 ዓመቷ ድረስ ብቻ ነበር፡፡ ከዛ በጥምቀት ሰሞን በእለተ ከተራ የዘጠኝ አመቷን የልደት በአል ሊከበርላት ድግስ ተደግሶ፤ ኬክ ታዞ፤ ሻማ ተገዝቶና ፤እቤቱ በዲኮሬሽን አሸብርቆ ባለበት ቀን እናትና አባቷ ተቃቅፈው በተኙበት ሞተው ተገኙ፡፡በምትወዳት የልደት ቀኗ በጥምቀት ቀን ጥር 11 በህይወቷ በጣም ልብ ሰባሪው ሀዘን ደረሰባት፡፡ከዛ በኃላ ህይወት ለእሷ ቀላል ሆና አታውቅም፡፡ከዛ በኃላ በአለም ላይ በ10 ደቂቃ ታላቋ ከሆነ ከመንትያ ወንድሟ በስተቀር ምንም ነገር አልነበራትም….ከዛ በኋላ አመት በመጣ ቁጥር በጥምቀት ወቅት ህዝበ- ክርስቲያኑ በየጎዳናው ተቦት ተከትለው ሲዘምሩና ሲጨፍሩ የወላጆቾን ሬሳ ተከትለው ሙሾ የሚያወርዱ ለቀስተኞች ነው የሚመስሏት…በቃ ከዛ በኃላ ሕይወት በአጠቃላይ ሁሉ ነገር አስከፊ ሁሉ ነገር አስጠዩ ነበር የሆነባት፡፡ይህ በጥልቅ ሀዘንና ብቸኝነት አጥንት የሚሰነጣጥቅ ችግር ለእሷ ብቻ ሳይሆን ለወንድሟም ጭምር ነበር፡፡ስለወንድሟ ትዝ ሲላት ከተጋደመችበት ተስፈንጥራ ተነሳችና ስልኳን በማንሳት ወደ ሀገር ቤት ደወለች…ወንድሟ ጋር፡፡
‹‹ሄሎ ናኦል…እንዴት ነህ?››
‹‹አለሁልሽ እህቴ…እንዴት ነሽ…?.ሁሉ ነገር አሪፍ ነው?፡፡››
‹‹ሰላም ነኝ.. ዛሬ ከፔሩ አንተ ወደምትወዳት ብራዚል እየበረርኩ ነበር… ግን የአየር ፀባዩ ተበላሸና ሳንደርስ አንድ የምታምር ለብራዚል ድንበር ቅርብ የሆነች የፔሩ ከተማ ለማረፍ ተገደድን፡፡››
ወንድሟ በሰማው ዜና በጣም ደነገጠ‹‹እንዴት ….?ምን አይነት ቦታ ነው ያረፋችሁት ..?ፕሌኑ ሰላም ነው?››
‹‹አረ ሁሉ ነገር አሪፍ ነው…፡፡››
‹‹እና እንዴት ልትሆኑ ነው?››
‹‹በቃ ምን እንሆናለን..አሁን ቤርጎ ይዤ አረፍ ብዬ ነው እየደወልኩልህ ያለሁት፡፡ነገ የአየር ፀባዩ ከተሻሻለ እንቀጥላለን፡፡ከለበለዚያ የዝግጅቱ አስተባባሪዎች በሚሰጡት ትዕዛዝ መሰረት የምናደርገውን እናያለን፡፡››
‹‹አህቴ እራስሽን ጠብቂ ደግሞ በጣም ናፍቀሺኛል….ጨርሰሽ እስክትመጪ ቸኩያለሁ፡፡..ሶስት ወር እንደዚህ ረጂም መሆኑን አላውቅም ነበር››ሲል ተናዘዘላት፡፡
‹‹ለምን ይዋሻል..ከዚህ በፊት እኮ ሶስት አመት ሙሉ ተለያይተን ነበር››
‹‹የዛን ጊዜ እኮ እኔ ራሴ ሀይለኛ ወከባ ላይ ነበርኩ…የአዲስአበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት አለ..በዛ ላይ በምታውቂው ስራ ሀለቃችን ምስራቅ ከወዲህ ወዲያ ታሽከረክረኝ ነበር…ከዚህ ሁሉ መዋከብ በተረፈቺኝ ብጣቂ ጊዜ ብቻ ነበር አንቺን መናፈቅ የምችለው፡፡አሁን ግን ስለአንቺ ከማሰብ ውጭ ሌላ ምን ስራ አለኝ?››ሲል ተናዘዘላት፡፡
‹‹ስለናፈቅኩህ ደሰስ ብሎኛ፤ቻለው ከአንድ ወር በታች ነው የቀረኝ…እና ደግሞ እንዲህ ዞር ስል የምናፍቅህ ከሆነ ስርህ እያለው አታበሳጨኝም ማለት ነው፡፡››
‹‹አረ አንቺ ብቻ ነይልኝ እንጂ ቀና ብዬም አላይሽም፡፡››ሲል ቃል ገባላት፡፡
‹‹ነግሬሀለው… አሁን የተናገርከውን ሪከርድ አድርጌዋለው፡፡››
‹‹ችግር የለውም እውነቴ ነው፡፡››
‹‹ምስራቅ ደህና ነች..?››ስትል ሌላ ጥያቄ ጠየቀችው፡፡
‹‹ያው ታውቂያለሽ ..እሷ ካልፈለገች አላገኛትም..ግን ደህና መሆኗን አውቃለሁ፡፡››ሲል እሷ ብቻ ሳትሆን ምስራቅም እንደናፈቀችው በሚያሳብቅ የድምፅ ቅላፄ መለሰላት፡፡ምስራቅ ማለት በሁለቱም ህይወት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ ያላት…የደህንነት መስራቤት ውስጥ የምትሰራ ሲኒዬር ሰላይና ለአመታት ሀለቃቸው የነበረች የ43 ዓመት ሴት ነች፡፡
‹‹በል ቸው ..ልተኛ ደክሞኛል ነገ ደውልልሀለው፡፡››አለችው፡፡
‹‹ቸው እህቴ …ውድድ ነው የማደርግሽ››ስልኩ ተዘጋ፡፡
አልጋውን ለቃ ወረደችና ወደ ፍሪጁ በመሄድ ሌላ የቆርቆሮ መጠጥ አወጣችና ከፍታ እየተጎነጨች ወደውጭ ወጣች፡፡ዳግላስ አሁንም ላፕቶፑ ላይ አቀርቅሮ ውዝግብ ውስጥ እንደገባ ነው፡፡የአማዞን ወንዝ ከበረንዳው አሻግረው ሲያያዩ እንደእባብ ተጠምዝዞ ሽብልል እያለ ሲፈስ ይታያል፡፡ትኩረቷን ወደዳግላስ መለሰችና‹‹እሺ አዲስ ነገር አለ?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹የተወሰነ ነገር እየገባኝ ነው፡፡ሳይንቲስት ነኝ፡፡አዎ ኬሚስት ነኝ፡፡እዚህ አማዞን ጫካ ውስጥ በሚገኝ የኮኬይ መቀመሚያ ላብ ውስጥ እሰራ ነበር፡፡አሁንም እንዴት እንደሚቀመም ፕሮሰሱን ሁሉም ትዝ ብሎኛል፡፡ግን ከዛ በፊት የት ነበርኩ..?የት ነው የተማርኩት? ቤተሰቦቼ የት ናቸው…?ሚስትና ልጆች አሉኝ…?እንዴት እዚህ ነገር ውስጥ ልገባ ቻልኩ?አሁንስ ፔሩ ምን ስሰራ ነበር..?የተሸከምኩትን ሻንጣ ሙሉ ዶላር ከየት አመጣሁት? ለምንስ ተሸከምኩት?አሁንስ ወደብራዚል ለምንድነው እየሄድኩ ያለሁት?ቀደም ብለሽ አንቺ ለጠይቅሺኝ ለእነዚህ ሁሉ ጥያቄዎች ሚሆን መልስ ግን እስከአሁን አላገኘሁም፡፡››
‹‹በቃ ላፕቶፑን ዝጋና ተነስ… ወደ ውስጥ እንግባ …ምን አልባት ለጠየቅካቸው ጥያቄዎች ሁሉ የሚሆኑ መልሶችን አረፍ ብለህ እንቅልፍ ከተኛህ በኃላ ትዝ ሊሉህ ይችላሉ፡፡ዶላሩ ላልከው ግን ምን አልባት ለአመታት ለሰራህላቸው ስራ የከፈሉህ ደሞዝ ሊሆን ይችላል፡፡ምን አልባት ከእነሱ ጋር በሰላም ተለያይተህ ሰላማዊና ኖርማል ህይወት ለመኖር ወደ ሀገርህና ቤተሰቦች በመጓዝ ላይ ትሆናለህ፡፡በል አሁን እኩለ ለሊት ሆነ ፤አረፍ እንበልና ነገ ከነገወዲያ የሚሆነውን እናያለን..ምን አልባትም እኮ ለእነዚህ ሁሉ ጥቄዎችህ መልስ የሚሰጥህ ሰው አየር ማረፊያ ቆሞ እየጠበቀህ ሊሆንም ይችላል፡፡››
‹‹አዎ እኔም ተስፋ ማደርገው እንደዛ ነው፡፡››አለና እንዳለችው ላፕቶፑን በመዝጋት መቀመጫውን ለቆ ተነሳ፡፡ ..ተያይዘው ወደ ውስጥ ገቡን ወደበረንዳ የሚያስወጣውን በራፍ በመዝጋት በየአልጋቸው ላይ ተቀመጡ፡፡
‹‹ታውቂያለሽ ከሌላ ፕላኔት ድንገት ተንሸራትቼ የወደቅኩና ያለቦታዬ ከማላውቃቸውና ከማይመስሉኝ ፍጡሮች ጋር የተቀላቀልኩ እየመሰለኝ ነው፡፡››አላት
በንግግሩ አሳዘናት‹‹አይዞኝ…..እንዳልኩህ አሁን መጨነቁን አቁምና ለማረፍ ሞክር…ጥዋት የሚሆነውን እናደርጋለን፡፡›› ብላ አልጋዋ ላይ ወጣችና ተሸፋፍና ለመተኛት መከረች፡፡ፈፅሞ እንቅልፍ ይወስደኛል ብላ አላሰበችም ነበር፡፡ግን ወዲያው ነበር ጭልጥ ያለ እንቅልፍ የወሰዳት፡፡ማለዳ 12፡40 አካባቢ ከእንቅልፏ ባና አይኗን ስትገልጥ ዳግላስ ስትተኛ ተቀምጦበት በነበረበት ቦታ ተቀምጦ ነው ያገኘችው፡፡
‹‹ምነው አልተኛህም እንዴ?››ስትል በመገረም ጠየቀችው፡፡
‹‹አይ አልተኛሁም፡››
‹‹እና እዛው የተቀመጥክበት ቦታ አነጋኸው …. ?››
#ጉዞ_በፀሎት
(አቃቂ እና ቦሌ)
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
በፀሎት ከጠፋች ከአንድ ሰዓት በኃላ ነበር አባትዬው ዜናውን የሰሙት፡፡በመጀመሪያ የቤቱ ሰው ሁሉ ያሰበው የተለመደው የልብ በሽተዋ ተነስቷባት ተዝለፍልፋ የሆነ ቦታ ወድቃ ይሆናል ተብሎ ነበር ፡፡ለአንድ ሰዓት ያህል ጋርዶቹ ፤ ዘበኞቹና አስተናጋጆቹ ሳይቀር የቤቱ ጥጋጥግ ከ50 በላይ ክፍሎች አንድ በአንድ እየከፈቱ አንድም ቦታ ሳይቀር ፈልገው ጅባት ካሉ በኃላ ነበር የጋርዶቹ ሀላቃ ፈራ ተባ እያለ የአቶ ኃይለመለኮትን መኝታ ቤት ያንኳኳው….በለሊት ልብሳቸው ሆነው የልጃቸውን የልደት በዓል ምክንያት በድካም የዛለ ሰውነታቸውን አልጋ ላይ አሳርፈው ገና እንቅልፍ እንዳሸለባቸው ነበር በራፋቸው የተንኳኳው…በመጀመሪያ በህልማቸው መስሏቸው ነበር፡፡ በኋላ ግን የምርም ክፍላቸው እየተንኳኳ መኆኑን ገባቸውና እየተነጫነጩ አልጋቸውን ለቀው በንዴት ውስጥ ሆነው በራፉ ሊከፍቱ እየሄዱ ባሉበት ቅፅበት ከመኝታ ቤታቸው ቀጥሎ ካለው ከፍል ውስጥ ያሉት ወ.ሮ ስንዱ ድምፅ ሰምተውና ደንግጠው ክፍላቸውን ከፍተው እየወጡ ነበር፡፡ ሁለቱም በአንድ ጊዜ እያንኳኳ ያለው ጋርድ ላይ አፈጠጡበት፡፡
‹‹ምን ተፈጥሮ ነው?››
‹‹ጋሼ..እንዴት እንደሆነ አናውቅም…..ልጆቹ እየተከታተሏት ነበር….››ለማስረዳት አስቦ መንተባተብ ጀመረ..፡፡
‹‹ምን እያወራህ ነው?››
‹‹በፀሎት..››
‹‹በፀሎት ..ልጄ ምን ሆነች..?አመማት እንዴ…?የልብ ህመሟ ተቀሰቀሰባት?››እናትዬው በመርበትበት በጥያቄ አጣደፉት፡፡
‹‹አይ አላመማትም…ላለፉት አንድ ሰዓት ውስጥ ስንፈልጋት ነበር…የለችም…››
‹‹የለችም ማለት…….?››
‹‹ጓደኞቾ ደብቀው ይዘዋት ሄደው መሰለኝ…. ግቢው ውስጥ የለችም፡፡››
‹‹እንዴ ..ይሄ ምን ማለት ነው..?ያን ሁሉ ጠብደል ጎረምሳ በጠባቂነት የቀጠርኩት እንዲህ አይነት ነገር እንዲከሰት ነው እንዴ…?ሰውዬ የእያንዳንዳችሁን ግንባር በሽጉጥ ሳልነድልላችሁ ልጄን ካለችበት ፈልጉና አስረክቡኝ…፡፡››በመራር ንግግር ቀድሞም የደነገጠውን ሰውዬ ይበልጥ ፍርሀት ለቀቁበት፡፡
‹‹እሺ ጌታዬ… ሁሉም ሰው እየፈለጋት ነው፣ይሄንን ነገር እርሶም በሰዓቱ መስማት አለቦት ብዬ ነው ቀድሜ ያሳወቅኳት…››
‹‹ወይኔ ልጄን..ይሄ የእነሱ ሳይሆን ያንተ ጥፋት ነው…››እናትዬው ቁጣቸውን ወደባላቸው አዞሩት፡፡
‹‹ይሄ ደግሞ ምን ማለት ነው?››ባልና ሚስቶች የተለመደውን ጭቅጭቃቸውን ቀጠሉ፡፡
‹‹ልጄን እንደከብት እረኛ ቀጥረህባት ስታጨናንቃት ነው ለዚህ ያበቃችው፡፡››
‹‹ሴትዬ እስኪ አሁን ተይኝ….እኔ ለራሴ ግራ ገብቶኛል ይበልጥ ግራ አታጋቢኝ.››አሉን ፊት ለፊት እየሄደ ያለውን ጋርድ ተከትለው ኮሪደሩን አቆርጠው መሄድ ጀመሩ..፡፡ወ.ሮ ስንዱም ማጉረምረማቸውን በለቅሶ አጅበው የለበሱትን ቢጃማ እንኳን ሳይቀይሩ ከኋላ መከተል ጀመሩ…፡፡በፀሎት ግን ለሊቱን ሙሉ ብትፈለግ ..በየወዳጅ ዘመድ ቤት ቢደወል…በከተማ አውራ ጎዳናዎች ከሰላሳ በላይ መኪኖችን ተሰማርቶ ብትፈለግ ድኩዋን ለማግኘት አልተቻለም…
በስተመጨረሻ የግቢው ካሜራ ቅጂ ለሁለተኛ ጊዜ በዝግታ ሲታይ ነው እራሷን በአለባበሶ ቀይራ ብቻዋን በሞተር ሳይክል ግቢውን ለቃ እንደወጣች የታወቀው፡፡ይሄ ደግሞ በቤተሰቡ ላይ የነበረውን ድንጋጤና ፍራቻ ይበልጥ አናረው..ምክንቱም አወጣጧ አስባባት መሆኑን ስለተረዱ….፡፡ከዛ አባትዬው አቶ ኃይለመለኮት ያላቸውን ተሰሚነትና ከመንግስት ሰዎች ጋር ያላቸውን ትስስር በመጠቀም ለእያንዳንዱ ፖሊስና ትራፊክ ፖሊስ ፎቶዋና የሞተር አይነትና ታርጋ ቁጥሩ ተበትኖ እንድትፈለግ መመሪያ እንዲተላለፍ ተደረገ ፡፡
በማግስቱም ምንም ፍንጭ ሳይገኝ በመንጋቱ እቤቱ ሁሉ በወዳጅ ዘመድ ተጨናነቀ፡፡..ወላጆቹ በስጋትና ፍራቻ ብቻ ሳይሆን በሰው ትንፋሽም መፈናፈኛ አጣ…አቶ ኃይለመለኮት ሲጨንቃቸው ከአጀቡ ተነጥለው ቀጥታ ወደልጃቸው መኝታ ቤት ገቡና ከውስጥ ዘግታው አልጋዋ ጠርዝ ላይ ቁጭ ብለው ግድግዳው ላይ የተለጠፈውን ግዙፍ የልጃቸውን ፎቶ እየተመለከቱ በትካዜ መንሳፈፍ ጀመሩ....እንባቸው መቆጣጠር አልተቻላቸውም…እንደህፃን ልጅ ነው ተንሰቅስቀው ያለቀሱት….በህይወታቸው እንዲህ አይነት ለቅሶ መቼ እንዳለቀሱ ፍጹም ትዝ አይላቸውም….አዎ ልጃቸው የልብ ንቅለተከላ በተደረገላት ጊዜ በህይወታቸው በጣም ያዘኑበትና የተጨናነቁበት ጊዜ ነበር…በቀሪ ህይወታቸውም መቼም ተመሳሳይ ሀዘን ውስጥ እገባለሁ የሚል ግምት አልነበራቸውም….ግን ተሳስተው ነበረ..አሁን ያሉበት ጭንቀትና ስጋት ከዛን ጊዜም ከፍ ያለ ነው…. ፡፡ልጃቸው አንድ ነገር ብትሆን ምን እንደሚሆኑ ምንም የሚያውቁት ነገር የለም..፡፡ግን በእርግጠኝነት ሌላ ኃይለመለኮት እንደሚሆኑ ሳይታለም የተፈታ ነው..ምን አልባት አብደው ጨርቃቸውን ሊጥሉ ይችሉ ይሆናል...ወይንም ንዴታምና አውሬ አይነት ሰው ሊሆኑ ይችላሉ ….ልባቸው ፍስስ እያለባቸው ነው….አይናቸውን ከወዲህ ወዲያ እያሽከረከሩ የልጃቸውን እቃዎች በስስት ሲቃኙ አይናቸው አንድ ፖስታ ላይ አረፈ..በድንጋጤ ተነሱና ወደእዛው ተራመድ፡፡ አነሱት… ሁለት ነው…፡፡ከላዩ ላይ የተፀፈውን አነበቡት..፣አንደኛው ለአባዬ ይላል…ሁለተኛውን አዩት ለእማዬ ይላል…እሱን ጠረጴዛው ላይ መልሰው አስቀመጡና ለእሷቸው የተጻፈውን ይዘው ወደአልጋ ጠርዝ ተመላሱና ፖስታውን ቀደው ወረቀቱን በማውጣት ማንበብ ጀመሩ፡፡
አባዬ….እንዴት እንደምወድህ ታውቃለህ አይደል? በጣም ነው የምወድህ..ግን ሁሌ ትናፍቀኛለህ…፡፡ሁሌ እሩቅ ውጭ ሀገር ያለህ ነው የሚመስለኝ….እቤት እያለህ እራሱ የሌለህ መስሎ ነው የሚሰማኝ…እርግጥ አንተ ሁሉ ነገር ተሟልቶልኝ በቅምጥል የምኖር ደስተኛ
ልጅ ነው የምመስልህ…እየቀያየርኩ ምነዳችወ ከሶስት በላይ ዘማናዊ መኪናዎች አሉኝ፣በወር ከመቶ ሺ ብር በላይ በእጄ ይሰጠኛል….በየሄድኩበት እየሄዱ የሚጠብቁኝ ቁጥራቸውን የማላውቃቸው ጋርዶች አሉኝ……በአመት ሁለትና ሶስት ጊዜ የፈለኩትን ውጭ ሀገር ሄጂ እዝናናለሁ…በአጠቃላይ ኑሮዬ ለአብዛኛው ኢትዬጵያዊ በተረት አለም እንኳን ሰምቶት የማያውቀው የህልም አለም አይነት ነው…ግን እኔ በእድሜዬ እናትና አባቴ ሲሳሳሙ አይቼ የማላውቅ ልጅ እንደሆኑክ ማንም አያውቅም..አረ መሳሳሙ ይቅር አንድ መኝታ ቤት ውስጥ አብረው ሲያድሩ አይቼ አላውቅም… አይገርምም…..፡፡
አባዬ ልጅ ሆኜ እርግቤ እያልክ ነበር የምትጠራኝ..እርግቤ ስትልኝ እንዴት እንደምደሰት አታውቅም ፡፡የእውነትም ያንተ ነጭ እርግብ ሆኜ አድማሱን ሰንጥቄ በሰማይ መብረር የምችልና ጨረቃ ጋር ደርሼ ከዋክብቶችን ጨብጬ ምጫወትባቸው ይመስለኝ ነበር…በቃ ትንሽ መልአክ እንደሆንኩ እንዲሰማኝ ነበር የምታደርገው..ግን አባዬ አንተ ያልተረዳኸውነ ነገር እኔ ከ19 ዓመቴ በኋላ ማለቴ የሌላ ሴት ከሰውነቴ ካወሀድኩ ጀምሮ እኔ እኔን አይደለሁም…..ትዝ ይልሀል እርግቤ አትበለኝ በስሜ ጥራኝ ብዬ ያስተውኩህ እራሴው ነኝ..ለምን ብለህ ጠይቀኸኝ ግን አታውቅም..ምን አልባት ዝም ብዬ እርግቤ የሚለው ሰም ደስ ስለማይለኝ መስሎህ ሊሆን ይችላል እንደዛ ግን አይደለም….ከልብ ነቅለ-ተከላ ከተደረገልኝ በኃላ ክንፏ የተሰበረባት መብረር የማትችል እና በየጓሮ የምትንፏቀቅ እርግብ እንደሆንኩ እየተሰማኝ ስለመጣ ነው ያስቆምኩህ..ለአንድ ልጅ እኮ በሰማይ እንዳሻት እንድትበር የሚያደርጋት የአባቷ ፍቅር ቀኝ ክንፍ እና የእናቷ ፍቅር ግራ ክንፍ ሲሆናት ነው….የወላጆቾ ፍቅር ነው እንድትበር የሚያደርጋት….ያ እንደሌለኝ ስረዳ ነው ስሙ ያስጠላኝ፡፡ለምን
(አቃቂ እና ቦሌ)
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
በፀሎት ከጠፋች ከአንድ ሰዓት በኃላ ነበር አባትዬው ዜናውን የሰሙት፡፡በመጀመሪያ የቤቱ ሰው ሁሉ ያሰበው የተለመደው የልብ በሽተዋ ተነስቷባት ተዝለፍልፋ የሆነ ቦታ ወድቃ ይሆናል ተብሎ ነበር ፡፡ለአንድ ሰዓት ያህል ጋርዶቹ ፤ ዘበኞቹና አስተናጋጆቹ ሳይቀር የቤቱ ጥጋጥግ ከ50 በላይ ክፍሎች አንድ በአንድ እየከፈቱ አንድም ቦታ ሳይቀር ፈልገው ጅባት ካሉ በኃላ ነበር የጋርዶቹ ሀላቃ ፈራ ተባ እያለ የአቶ ኃይለመለኮትን መኝታ ቤት ያንኳኳው….በለሊት ልብሳቸው ሆነው የልጃቸውን የልደት በዓል ምክንያት በድካም የዛለ ሰውነታቸውን አልጋ ላይ አሳርፈው ገና እንቅልፍ እንዳሸለባቸው ነበር በራፋቸው የተንኳኳው…በመጀመሪያ በህልማቸው መስሏቸው ነበር፡፡ በኋላ ግን የምርም ክፍላቸው እየተንኳኳ መኆኑን ገባቸውና እየተነጫነጩ አልጋቸውን ለቀው በንዴት ውስጥ ሆነው በራፉ ሊከፍቱ እየሄዱ ባሉበት ቅፅበት ከመኝታ ቤታቸው ቀጥሎ ካለው ከፍል ውስጥ ያሉት ወ.ሮ ስንዱ ድምፅ ሰምተውና ደንግጠው ክፍላቸውን ከፍተው እየወጡ ነበር፡፡ ሁለቱም በአንድ ጊዜ እያንኳኳ ያለው ጋርድ ላይ አፈጠጡበት፡፡
‹‹ምን ተፈጥሮ ነው?››
‹‹ጋሼ..እንዴት እንደሆነ አናውቅም…..ልጆቹ እየተከታተሏት ነበር….››ለማስረዳት አስቦ መንተባተብ ጀመረ..፡፡
‹‹ምን እያወራህ ነው?››
‹‹በፀሎት..››
‹‹በፀሎት ..ልጄ ምን ሆነች..?አመማት እንዴ…?የልብ ህመሟ ተቀሰቀሰባት?››እናትዬው በመርበትበት በጥያቄ አጣደፉት፡፡
‹‹አይ አላመማትም…ላለፉት አንድ ሰዓት ውስጥ ስንፈልጋት ነበር…የለችም…››
‹‹የለችም ማለት…….?››
‹‹ጓደኞቾ ደብቀው ይዘዋት ሄደው መሰለኝ…. ግቢው ውስጥ የለችም፡፡››
‹‹እንዴ ..ይሄ ምን ማለት ነው..?ያን ሁሉ ጠብደል ጎረምሳ በጠባቂነት የቀጠርኩት እንዲህ አይነት ነገር እንዲከሰት ነው እንዴ…?ሰውዬ የእያንዳንዳችሁን ግንባር በሽጉጥ ሳልነድልላችሁ ልጄን ካለችበት ፈልጉና አስረክቡኝ…፡፡››በመራር ንግግር ቀድሞም የደነገጠውን ሰውዬ ይበልጥ ፍርሀት ለቀቁበት፡፡
‹‹እሺ ጌታዬ… ሁሉም ሰው እየፈለጋት ነው፣ይሄንን ነገር እርሶም በሰዓቱ መስማት አለቦት ብዬ ነው ቀድሜ ያሳወቅኳት…››
‹‹ወይኔ ልጄን..ይሄ የእነሱ ሳይሆን ያንተ ጥፋት ነው…››እናትዬው ቁጣቸውን ወደባላቸው አዞሩት፡፡
‹‹ይሄ ደግሞ ምን ማለት ነው?››ባልና ሚስቶች የተለመደውን ጭቅጭቃቸውን ቀጠሉ፡፡
‹‹ልጄን እንደከብት እረኛ ቀጥረህባት ስታጨናንቃት ነው ለዚህ ያበቃችው፡፡››
‹‹ሴትዬ እስኪ አሁን ተይኝ….እኔ ለራሴ ግራ ገብቶኛል ይበልጥ ግራ አታጋቢኝ.››አሉን ፊት ለፊት እየሄደ ያለውን ጋርድ ተከትለው ኮሪደሩን አቆርጠው መሄድ ጀመሩ..፡፡ወ.ሮ ስንዱም ማጉረምረማቸውን በለቅሶ አጅበው የለበሱትን ቢጃማ እንኳን ሳይቀይሩ ከኋላ መከተል ጀመሩ…፡፡በፀሎት ግን ለሊቱን ሙሉ ብትፈለግ ..በየወዳጅ ዘመድ ቤት ቢደወል…በከተማ አውራ ጎዳናዎች ከሰላሳ በላይ መኪኖችን ተሰማርቶ ብትፈለግ ድኩዋን ለማግኘት አልተቻለም…
በስተመጨረሻ የግቢው ካሜራ ቅጂ ለሁለተኛ ጊዜ በዝግታ ሲታይ ነው እራሷን በአለባበሶ ቀይራ ብቻዋን በሞተር ሳይክል ግቢውን ለቃ እንደወጣች የታወቀው፡፡ይሄ ደግሞ በቤተሰቡ ላይ የነበረውን ድንጋጤና ፍራቻ ይበልጥ አናረው..ምክንቱም አወጣጧ አስባባት መሆኑን ስለተረዱ….፡፡ከዛ አባትዬው አቶ ኃይለመለኮት ያላቸውን ተሰሚነትና ከመንግስት ሰዎች ጋር ያላቸውን ትስስር በመጠቀም ለእያንዳንዱ ፖሊስና ትራፊክ ፖሊስ ፎቶዋና የሞተር አይነትና ታርጋ ቁጥሩ ተበትኖ እንድትፈለግ መመሪያ እንዲተላለፍ ተደረገ ፡፡
በማግስቱም ምንም ፍንጭ ሳይገኝ በመንጋቱ እቤቱ ሁሉ በወዳጅ ዘመድ ተጨናነቀ፡፡..ወላጆቹ በስጋትና ፍራቻ ብቻ ሳይሆን በሰው ትንፋሽም መፈናፈኛ አጣ…አቶ ኃይለመለኮት ሲጨንቃቸው ከአጀቡ ተነጥለው ቀጥታ ወደልጃቸው መኝታ ቤት ገቡና ከውስጥ ዘግታው አልጋዋ ጠርዝ ላይ ቁጭ ብለው ግድግዳው ላይ የተለጠፈውን ግዙፍ የልጃቸውን ፎቶ እየተመለከቱ በትካዜ መንሳፈፍ ጀመሩ....እንባቸው መቆጣጠር አልተቻላቸውም…እንደህፃን ልጅ ነው ተንሰቅስቀው ያለቀሱት….በህይወታቸው እንዲህ አይነት ለቅሶ መቼ እንዳለቀሱ ፍጹም ትዝ አይላቸውም….አዎ ልጃቸው የልብ ንቅለተከላ በተደረገላት ጊዜ በህይወታቸው በጣም ያዘኑበትና የተጨናነቁበት ጊዜ ነበር…በቀሪ ህይወታቸውም መቼም ተመሳሳይ ሀዘን ውስጥ እገባለሁ የሚል ግምት አልነበራቸውም….ግን ተሳስተው ነበረ..አሁን ያሉበት ጭንቀትና ስጋት ከዛን ጊዜም ከፍ ያለ ነው…. ፡፡ልጃቸው አንድ ነገር ብትሆን ምን እንደሚሆኑ ምንም የሚያውቁት ነገር የለም..፡፡ግን በእርግጠኝነት ሌላ ኃይለመለኮት እንደሚሆኑ ሳይታለም የተፈታ ነው..ምን አልባት አብደው ጨርቃቸውን ሊጥሉ ይችሉ ይሆናል...ወይንም ንዴታምና አውሬ አይነት ሰው ሊሆኑ ይችላሉ ….ልባቸው ፍስስ እያለባቸው ነው….አይናቸውን ከወዲህ ወዲያ እያሽከረከሩ የልጃቸውን እቃዎች በስስት ሲቃኙ አይናቸው አንድ ፖስታ ላይ አረፈ..በድንጋጤ ተነሱና ወደእዛው ተራመድ፡፡ አነሱት… ሁለት ነው…፡፡ከላዩ ላይ የተፀፈውን አነበቡት..፣አንደኛው ለአባዬ ይላል…ሁለተኛውን አዩት ለእማዬ ይላል…እሱን ጠረጴዛው ላይ መልሰው አስቀመጡና ለእሷቸው የተጻፈውን ይዘው ወደአልጋ ጠርዝ ተመላሱና ፖስታውን ቀደው ወረቀቱን በማውጣት ማንበብ ጀመሩ፡፡
አባዬ….እንዴት እንደምወድህ ታውቃለህ አይደል? በጣም ነው የምወድህ..ግን ሁሌ ትናፍቀኛለህ…፡፡ሁሌ እሩቅ ውጭ ሀገር ያለህ ነው የሚመስለኝ….እቤት እያለህ እራሱ የሌለህ መስሎ ነው የሚሰማኝ…እርግጥ አንተ ሁሉ ነገር ተሟልቶልኝ በቅምጥል የምኖር ደስተኛ
ልጅ ነው የምመስልህ…እየቀያየርኩ ምነዳችወ ከሶስት በላይ ዘማናዊ መኪናዎች አሉኝ፣በወር ከመቶ ሺ ብር በላይ በእጄ ይሰጠኛል….በየሄድኩበት እየሄዱ የሚጠብቁኝ ቁጥራቸውን የማላውቃቸው ጋርዶች አሉኝ……በአመት ሁለትና ሶስት ጊዜ የፈለኩትን ውጭ ሀገር ሄጂ እዝናናለሁ…በአጠቃላይ ኑሮዬ ለአብዛኛው ኢትዬጵያዊ በተረት አለም እንኳን ሰምቶት የማያውቀው የህልም አለም አይነት ነው…ግን እኔ በእድሜዬ እናትና አባቴ ሲሳሳሙ አይቼ የማላውቅ ልጅ እንደሆኑክ ማንም አያውቅም..አረ መሳሳሙ ይቅር አንድ መኝታ ቤት ውስጥ አብረው ሲያድሩ አይቼ አላውቅም… አይገርምም…..፡፡
አባዬ ልጅ ሆኜ እርግቤ እያልክ ነበር የምትጠራኝ..እርግቤ ስትልኝ እንዴት እንደምደሰት አታውቅም ፡፡የእውነትም ያንተ ነጭ እርግብ ሆኜ አድማሱን ሰንጥቄ በሰማይ መብረር የምችልና ጨረቃ ጋር ደርሼ ከዋክብቶችን ጨብጬ ምጫወትባቸው ይመስለኝ ነበር…በቃ ትንሽ መልአክ እንደሆንኩ እንዲሰማኝ ነበር የምታደርገው..ግን አባዬ አንተ ያልተረዳኸውነ ነገር እኔ ከ19 ዓመቴ በኋላ ማለቴ የሌላ ሴት ከሰውነቴ ካወሀድኩ ጀምሮ እኔ እኔን አይደለሁም…..ትዝ ይልሀል እርግቤ አትበለኝ በስሜ ጥራኝ ብዬ ያስተውኩህ እራሴው ነኝ..ለምን ብለህ ጠይቀኸኝ ግን አታውቅም..ምን አልባት ዝም ብዬ እርግቤ የሚለው ሰም ደስ ስለማይለኝ መስሎህ ሊሆን ይችላል እንደዛ ግን አይደለም….ከልብ ነቅለ-ተከላ ከተደረገልኝ በኃላ ክንፏ የተሰበረባት መብረር የማትችል እና በየጓሮ የምትንፏቀቅ እርግብ እንደሆንኩ እየተሰማኝ ስለመጣ ነው ያስቆምኩህ..ለአንድ ልጅ እኮ በሰማይ እንዳሻት እንድትበር የሚያደርጋት የአባቷ ፍቅር ቀኝ ክንፍ እና የእናቷ ፍቅር ግራ ክንፍ ሲሆናት ነው….የወላጆቾ ፍቅር ነው እንድትበር የሚያደርጋት….ያ እንደሌለኝ ስረዳ ነው ስሙ ያስጠላኝ፡፡ለምን
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ተመስገን
ከጠፋች በኋላ፤ ብቻ ሳይሆን ከእድላዊት ጋርም ከትምህርት ቤት መጥተው ምሳቸውን ከበሉበት ቀን አንስቶ ወደ ትምህርት ቤት ለመሄድ አይደለም አስቦትም አያውቅም፡፡
ወደ ትምህርት ቤትም አልሄደም፡፡ ትዳር የሚባል ሳያስብ እናት አባቱን እየረዳ የግብርና ስራውን ሌት ከቀን እየተጋ መዋሉን ተያይዞታል፡፡
ከሚወዳት እህቱ እድላዊት ውጪ የቅርብ ጓደኛዬ የሚለው ሴትም ይሁን ወንድ ለግዜው አልነበረውም፡፡ አንድ ቀን በስራ ምክንያት ከሰፈሩ ልጅ ያሬድ ጋር ይገናኛል፡፡ ታዲያ ተመስገንና ያሬድ ከዚህ በፊት ከእግዚአብሔር ሰላምታ በስተቀር የጠበቀ ግንኙነት አልነበራቸውም፡፡
ያሬድ ተመስገንንም ይሁን ቤተሰቦቹን በደንብ ጠንቅቆ ያውቃቸዋል፡፡ በጥሩ ቤተሰብ ያደገና ከቤተሰቦቹ ጋር የሚኖር ገና ታዳጊ ወጣት ሆኖ በራሱ ፈቃድ
ትምህርቱን አቋርጦ ወደ ግብርናው ከተሰማራ ሰንበትበት ብሏል፡፡
ከተመስገን ጋር ግንኙነታቸው ከእግዚአብሔር ሰላምታ አልፎ ወደ መቀራረብ ደረሰ ፤ አልፎ አልፎም ስራ በመተጋገዝ መረዳዳት ጀምረዋል፡፡
ተመስገን እንደ እህቱ የሚሆንለት ባያገኝም ለእሱ የሚሆንና የሚያበረታታው የቅርብ ጓደኛ በማግኘቱ ደስተኛ አድርጎታል፡፡
ከእለታት አንድ ቀን እነያሬድ ቤት የሽንብራ ቆሎ እየፈጩ ፤ ከስንዴው ጠላ ጎንጨት እያሉ የወደፊት ምኞታቸውና አላማቸውን ይጫወታሉ፡፡
"ለወደፊት ምን ለመስራት አስበሃል?" ብሎ ጠየቀው ተመስገን፡፡
"እኔ ለቀጣይ ያስብኩት አሁን የጀመርኩትን ቤት ስጨርስ ቤተሰቦቼ ትምህርትህን ከተወህ ማግባት አለብህ እያሉኝ ስለሆነ ለማግባት አቅጃለሁ፡፡ ብሎት አንተስ ምን አስበሃል? አለው ያሬድ፡፡
ተመስገን የወደፊት ምኞትና እቅዱ ከጓደኛው ያሬድ የተለየና ተቃራኒ ነው፡፡ "እኔ እንኳን እህቴን እስከማገኝ ድረስ ትዳር የመያዝ ሃሳብና ፍላጎት የለኝም"፡፡
ቤተሰቦቸን እየረዳሁ ለራሴም ትንሽ እያጠራቀምኩ ለመኖር ነው የማስበው አለ፡፡
ያሬድ የተመስገንን እቅድ ሲሰማ እህቱን በፊትም እደሚወዳት ስለሚያቅ ለምን አታገባም ብሎም አልጠይቀውም..፡፡
አርምዴ
ባለቤታቸው ከሞተ በኋላ፤ ሌላ ባል አላገቡም፡፡ ወደ ውጭ ወጥተው ጎንበስ ቀና ብለው መስራት አይችሉም፡፡
ልጃቸው ሰርቶ የሚሰጣቸውን እህል አብስለው ለመብላት ያልተቸገሩ የስልሳ ዓመት የእድሜ ባለፀጋ ናቸው፡፡ የአርምዴ እናት ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
ቀኑ እንደመምሸት ብሎ ለዓይን ያዝ አድርጓል፡፡ ኩራዝ ለመለኮስ ከምድጃቸው እሳት ለማቀጣጠል ይታገላሉ፡፡
አይናቸው ተርገበገበባቸው፡፡ ዛሬ ደግሞ በምሽት ምን ሊያሳየኝ ነው ፡፡ አይኔ የሚርገበገበው እያሉ የውጭ በር ተንኳኳ
እሳት ማቀጣጠሉን ተወት አርገው ወደ ውጭ ወጡ፡፡ ልጃቸው አርምዴ እድላዊትን አዝሎ ገባ፡፡ ደነገጡ፡፡
"ውይ! በሞትኩት ልጄ ምን ሆና ነው? ብለው ጠየቁት፡፡
እረኞች ጫካ ውስጥ መሬት ለመሬት ጎትተዋት ነው፡፡
"እና በጣም ጎድተዋታል" ?
"አዎ! ይዣትም ስመጣ ለማናገር ብሞክርም ማናገር አልቻለችም"፡፡
"ታዲያ ከየት እንደመጣችም አልነገረችህም"?
"አልነገረችኝም ፡፡ ጩኸት ሰምቼ እየሮጥሁ ሲሄድ ጥለዋት ተበታተኑ፡፡ እሷም ተጎድታ ስለነበር አላናገረችኝም፡፡ እንዴው እግዚአብሔር ድረስላት ሲለኝ ነው እንጂ ዛሬ አደን የሔድኩት ይገሏት ነበር፡፡
"አሁን ምን እንስጣት? ነው ትንሽ ትተኛ? ድካሟ እስከ ሚያልፍላት አሉ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
ወደ አስተኛት ፍራሽ ላይ ተጠጋ፡፡ እድላዊት አይኖቿን አንከራተተች፡፡ ግራና ቀኝ ተቁለጨለጨች፡፡
አርምዴ የእድላዊትን አይኖች መንከራተትና በእንባ መሞላት አየ፡፡ እሱም ከየት መጣ ሳይባል አይኖቹ በእንባ ተሞሉ፡፡
እድላዊት አርምዴን የምትመለከተው ውሃ ስጠኝ ለማለት ነበር፡፡ ግን መናገር አቅቷታል፡፡
አቶ አርምዴ ውሃ መፈለጓን የተረዳት አይመስልም፡፡ አንጀቱ እንደነብሰጡር ተላወሰ፡፡ እንባ እየተናነቀው "ምን ልስጥሽ " አላት፡፡
እድላዊት መናገር አልቻለችም፡፡ በእጇ ውሃ እንደ ጠማት አመለከተችው፡፡
አቶ አርምዴ በምልክት የገለፀችውን ሳያደናግረው ተረዳት፡፡ ውሃ ቀድቶ ሰጣት፡፡
ውሃው ወደ ውስጥ መግባቱን ትቶ ግራና ቀኝ በአፏ ወደ ውጭ ፈሰሰ፡፡
እድላዊት በውሃ ጥም የተነሳ ቶንሲሏ ወርዷል፡፡ አቶ አርምዴ የባሰ ተጨነቀ
"ውይ በሞትኩት ልጄን ውሃ አልወርድላት አለ ? ቶንሲሏ ወርዶ ይሆናል አሉ፤ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
"እና ምን ይሻላል? መድሃኒት በቅርብ አይገኝም? አለ ፤ አቶ አርምዴ፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ የሃበሻ መድሃኒት ሊያቀምሷት መድሃኒቱን እንዲያመጣላቸው ልጃቸውን እንዳይልኩት መድሃኒቱ ሲቆረጥ ስሙ መጠራት የለበትም፡፡ እራሳቸው ለመቁረጥ ቆይ እስቲ መጣሁ ብለው ወደ ጓሮ ሄዱ፡፡
ለቶንሲል መድሃኒት የሚሆነውን ሰባት የጌሾ ቀንበጥ ቆርጠው አመጡ፡፡ ለእድላዊት እንድታኝከው ሰጧት፡፡
እድላዊት መናገር ቢያቅታትም መስማት ትችላለች፡፡ የተሰጠችውን የቶንሲል መድሃኒት አኝኪው ስለተባለች ብቻ
እየመረራት ቢሆንም ጨክና አኘከችው፡፡
በውሃ ጥም ምራቋ ደርቋል፡፡ ከንፈሮቿም ኩበት መስለዋል፡፡ ምላሷ ብቻ ብቅ ጥልቅ ይላል፡፡ ነብሷ ልትወጣ ደረሰች፡፡ ሰውነቷ በላብ ተዘፈቀ፡፡ ልቧ ተጨነቀች፡፡ በጀመረችው የምልክት ቋንቋ ውሃ ስጡኝ ብላ በእጇ አመለከተች፡፡
አቶ አርምዴ የእድላዊት ነገር አሁንም ግራ ገባው፡፡ ከሸንበቆ ላይ ቀጭን ሸንበቆ ተከርክሞ እድላዊት በሸንበቆው አማካኝነት ውሃ እንድትቀምስ ተደረገ፡፡
ለእድላዊት እንጀራ እንዳይሰጧት ችላ አትበላም፡፡ ምን እንደሚሰጧት ጨነቃቸው፡፡ የእድላዊት ነገር አንጀታቸውን በላው፡፡
በደከመ አቅማቸውም ቢሆን ትንሽ ገንፎ አገንፍተው እንድትቀምስ አደረጉ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
እድላዊት የተሰራላትን ገንፎ ለመድሃኒት ያህል ቀመሰች፡፡ ወ/ሮ በሰልፏ ለቶንሲሏ ሌላ መዳኒት ዝንጅብል እንድታኝክበት ሰጧት፡፡
"ለቶንሲል ጥሩ ነው፡፡ ለነገ በደንብ ይሻልሻል፡፡ አይዞሽ እያሉ ልጃቸው ያሰረላትን ጨርቅ ከቁስሏ ላይ ፈቱላት፡፡ ለብ ባለ ውሃ አጠቡላት፡፡ ያበጠውን እግርና እጇንም በቅባት አሹላት፡፡ የተላላጠውን ቁስሏንም በነጠላ ጨርቅ ተኩሰው መኝታ ላይ ጋደም እንድትል አደረጉ፡፡
አቶ አርምዴ የሚደረግላትን ካደረገ በኋላ ወደ ቤቱ ሄደ፡፡ አድሮ በነጋታው ጥዋት እድላዊት እንዴት እንዳደረች ለመጠየቅ ከመኝታው ተነስቶ ሲመጣ እናቱ የቤቱን በር ከፍተው ሲወጡ ደረሰ፡፡
የእግዚአብሔር ሰላምታ ተለዋውጠው "ደግሞ ማታ እመለሳለሁ ብለህ ሳትመጣ ቀረህ በሰላም ነው ያልተመለስከው? አሉት ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
"ለመምጣት አስቤ ነበር፡፡ ግን ቤቱንና ከብቶቹን ትቼ እንዳልመጣ አውሬ እንኳን ቢገባ የሚሰማ ስላልነበረ ቀረሁ"፡፡ እንዴት አደረች ልጅቷ?ተሸሏት አላደረችም? አለ፡፡
የእድላዊት ስቃይና መከራ ከአንጀቱ ገብቶ ሳይወጣ አንጀቱ እያለቀሰላት እህል እንኳን አልወርድ ብሎት ለአደን ሲሄድ በቀመሰው ቁራሽ እንጀራ ነበር፡፡ እራት ሳይቀምስ ያደረው፡፡
ከአሁን አሁን ያማት ይሆን ? እያሉ ሌሊቱን ሙሉ እንቅልፍ ሳይወስዳቸው አይደለም በዓይናቸው ሳይዞር ነበር ያደሩት ወ/ሮ በሰልፏም፡፡
"ሰላም አድራለች፡፡ ብቻ ሌሊቱን ሲያቃዧት ነው ያደረው፡፡ አሟት ይሆን ብየ ሌሊት ተነስቼ ሳያት ከቅዠት በስተቀር ምንም አላየሁባትም፡፡ ከነጋም አልቀሰቀስኳትም፡፡ ቅዝቃዜ ስላለ ትንሽ ትተኛ ብየ ነው፡፡ እስኪ አሁን አንተ ከመጣህ ቀስቅሳትና እንዴት እንዳደረች ጠይቃት አሉ፡፡ ቤታቸውን ለመጥረግ የቤት መጥረጊያ ቅጠል ለማምጣት ወደ ውጭ እየወጡ፡፡
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ተመስገን
ከጠፋች በኋላ፤ ብቻ ሳይሆን ከእድላዊት ጋርም ከትምህርት ቤት መጥተው ምሳቸውን ከበሉበት ቀን አንስቶ ወደ ትምህርት ቤት ለመሄድ አይደለም አስቦትም አያውቅም፡፡
ወደ ትምህርት ቤትም አልሄደም፡፡ ትዳር የሚባል ሳያስብ እናት አባቱን እየረዳ የግብርና ስራውን ሌት ከቀን እየተጋ መዋሉን ተያይዞታል፡፡
ከሚወዳት እህቱ እድላዊት ውጪ የቅርብ ጓደኛዬ የሚለው ሴትም ይሁን ወንድ ለግዜው አልነበረውም፡፡ አንድ ቀን በስራ ምክንያት ከሰፈሩ ልጅ ያሬድ ጋር ይገናኛል፡፡ ታዲያ ተመስገንና ያሬድ ከዚህ በፊት ከእግዚአብሔር ሰላምታ በስተቀር የጠበቀ ግንኙነት አልነበራቸውም፡፡
ያሬድ ተመስገንንም ይሁን ቤተሰቦቹን በደንብ ጠንቅቆ ያውቃቸዋል፡፡ በጥሩ ቤተሰብ ያደገና ከቤተሰቦቹ ጋር የሚኖር ገና ታዳጊ ወጣት ሆኖ በራሱ ፈቃድ
ትምህርቱን አቋርጦ ወደ ግብርናው ከተሰማራ ሰንበትበት ብሏል፡፡
ከተመስገን ጋር ግንኙነታቸው ከእግዚአብሔር ሰላምታ አልፎ ወደ መቀራረብ ደረሰ ፤ አልፎ አልፎም ስራ በመተጋገዝ መረዳዳት ጀምረዋል፡፡
ተመስገን እንደ እህቱ የሚሆንለት ባያገኝም ለእሱ የሚሆንና የሚያበረታታው የቅርብ ጓደኛ በማግኘቱ ደስተኛ አድርጎታል፡፡
ከእለታት አንድ ቀን እነያሬድ ቤት የሽንብራ ቆሎ እየፈጩ ፤ ከስንዴው ጠላ ጎንጨት እያሉ የወደፊት ምኞታቸውና አላማቸውን ይጫወታሉ፡፡
"ለወደፊት ምን ለመስራት አስበሃል?" ብሎ ጠየቀው ተመስገን፡፡
"እኔ ለቀጣይ ያስብኩት አሁን የጀመርኩትን ቤት ስጨርስ ቤተሰቦቼ ትምህርትህን ከተወህ ማግባት አለብህ እያሉኝ ስለሆነ ለማግባት አቅጃለሁ፡፡ ብሎት አንተስ ምን አስበሃል? አለው ያሬድ፡፡
ተመስገን የወደፊት ምኞትና እቅዱ ከጓደኛው ያሬድ የተለየና ተቃራኒ ነው፡፡ "እኔ እንኳን እህቴን እስከማገኝ ድረስ ትዳር የመያዝ ሃሳብና ፍላጎት የለኝም"፡፡
ቤተሰቦቸን እየረዳሁ ለራሴም ትንሽ እያጠራቀምኩ ለመኖር ነው የማስበው አለ፡፡
ያሬድ የተመስገንን እቅድ ሲሰማ እህቱን በፊትም እደሚወዳት ስለሚያቅ ለምን አታገባም ብሎም አልጠይቀውም..፡፡
አርምዴ
ባለቤታቸው ከሞተ በኋላ፤ ሌላ ባል አላገቡም፡፡ ወደ ውጭ ወጥተው ጎንበስ ቀና ብለው መስራት አይችሉም፡፡
ልጃቸው ሰርቶ የሚሰጣቸውን እህል አብስለው ለመብላት ያልተቸገሩ የስልሳ ዓመት የእድሜ ባለፀጋ ናቸው፡፡ የአርምዴ እናት ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
ቀኑ እንደመምሸት ብሎ ለዓይን ያዝ አድርጓል፡፡ ኩራዝ ለመለኮስ ከምድጃቸው እሳት ለማቀጣጠል ይታገላሉ፡፡
አይናቸው ተርገበገበባቸው፡፡ ዛሬ ደግሞ በምሽት ምን ሊያሳየኝ ነው ፡፡ አይኔ የሚርገበገበው እያሉ የውጭ በር ተንኳኳ
እሳት ማቀጣጠሉን ተወት አርገው ወደ ውጭ ወጡ፡፡ ልጃቸው አርምዴ እድላዊትን አዝሎ ገባ፡፡ ደነገጡ፡፡
"ውይ! በሞትኩት ልጄ ምን ሆና ነው? ብለው ጠየቁት፡፡
እረኞች ጫካ ውስጥ መሬት ለመሬት ጎትተዋት ነው፡፡
"እና በጣም ጎድተዋታል" ?
"አዎ! ይዣትም ስመጣ ለማናገር ብሞክርም ማናገር አልቻለችም"፡፡
"ታዲያ ከየት እንደመጣችም አልነገረችህም"?
"አልነገረችኝም ፡፡ ጩኸት ሰምቼ እየሮጥሁ ሲሄድ ጥለዋት ተበታተኑ፡፡ እሷም ተጎድታ ስለነበር አላናገረችኝም፡፡ እንዴው እግዚአብሔር ድረስላት ሲለኝ ነው እንጂ ዛሬ አደን የሔድኩት ይገሏት ነበር፡፡
"አሁን ምን እንስጣት? ነው ትንሽ ትተኛ? ድካሟ እስከ ሚያልፍላት አሉ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
ወደ አስተኛት ፍራሽ ላይ ተጠጋ፡፡ እድላዊት አይኖቿን አንከራተተች፡፡ ግራና ቀኝ ተቁለጨለጨች፡፡
አርምዴ የእድላዊትን አይኖች መንከራተትና በእንባ መሞላት አየ፡፡ እሱም ከየት መጣ ሳይባል አይኖቹ በእንባ ተሞሉ፡፡
እድላዊት አርምዴን የምትመለከተው ውሃ ስጠኝ ለማለት ነበር፡፡ ግን መናገር አቅቷታል፡፡
አቶ አርምዴ ውሃ መፈለጓን የተረዳት አይመስልም፡፡ አንጀቱ እንደነብሰጡር ተላወሰ፡፡ እንባ እየተናነቀው "ምን ልስጥሽ " አላት፡፡
እድላዊት መናገር አልቻለችም፡፡ በእጇ ውሃ እንደ ጠማት አመለከተችው፡፡
አቶ አርምዴ በምልክት የገለፀችውን ሳያደናግረው ተረዳት፡፡ ውሃ ቀድቶ ሰጣት፡፡
ውሃው ወደ ውስጥ መግባቱን ትቶ ግራና ቀኝ በአፏ ወደ ውጭ ፈሰሰ፡፡
እድላዊት በውሃ ጥም የተነሳ ቶንሲሏ ወርዷል፡፡ አቶ አርምዴ የባሰ ተጨነቀ
"ውይ በሞትኩት ልጄን ውሃ አልወርድላት አለ ? ቶንሲሏ ወርዶ ይሆናል አሉ፤ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
"እና ምን ይሻላል? መድሃኒት በቅርብ አይገኝም? አለ ፤ አቶ አርምዴ፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ የሃበሻ መድሃኒት ሊያቀምሷት መድሃኒቱን እንዲያመጣላቸው ልጃቸውን እንዳይልኩት መድሃኒቱ ሲቆረጥ ስሙ መጠራት የለበትም፡፡ እራሳቸው ለመቁረጥ ቆይ እስቲ መጣሁ ብለው ወደ ጓሮ ሄዱ፡፡
ለቶንሲል መድሃኒት የሚሆነውን ሰባት የጌሾ ቀንበጥ ቆርጠው አመጡ፡፡ ለእድላዊት እንድታኝከው ሰጧት፡፡
እድላዊት መናገር ቢያቅታትም መስማት ትችላለች፡፡ የተሰጠችውን የቶንሲል መድሃኒት አኝኪው ስለተባለች ብቻ
እየመረራት ቢሆንም ጨክና አኘከችው፡፡
በውሃ ጥም ምራቋ ደርቋል፡፡ ከንፈሮቿም ኩበት መስለዋል፡፡ ምላሷ ብቻ ብቅ ጥልቅ ይላል፡፡ ነብሷ ልትወጣ ደረሰች፡፡ ሰውነቷ በላብ ተዘፈቀ፡፡ ልቧ ተጨነቀች፡፡ በጀመረችው የምልክት ቋንቋ ውሃ ስጡኝ ብላ በእጇ አመለከተች፡፡
አቶ አርምዴ የእድላዊት ነገር አሁንም ግራ ገባው፡፡ ከሸንበቆ ላይ ቀጭን ሸንበቆ ተከርክሞ እድላዊት በሸንበቆው አማካኝነት ውሃ እንድትቀምስ ተደረገ፡፡
ለእድላዊት እንጀራ እንዳይሰጧት ችላ አትበላም፡፡ ምን እንደሚሰጧት ጨነቃቸው፡፡ የእድላዊት ነገር አንጀታቸውን በላው፡፡
በደከመ አቅማቸውም ቢሆን ትንሽ ገንፎ አገንፍተው እንድትቀምስ አደረጉ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
እድላዊት የተሰራላትን ገንፎ ለመድሃኒት ያህል ቀመሰች፡፡ ወ/ሮ በሰልፏ ለቶንሲሏ ሌላ መዳኒት ዝንጅብል እንድታኝክበት ሰጧት፡፡
"ለቶንሲል ጥሩ ነው፡፡ ለነገ በደንብ ይሻልሻል፡፡ አይዞሽ እያሉ ልጃቸው ያሰረላትን ጨርቅ ከቁስሏ ላይ ፈቱላት፡፡ ለብ ባለ ውሃ አጠቡላት፡፡ ያበጠውን እግርና እጇንም በቅባት አሹላት፡፡ የተላላጠውን ቁስሏንም በነጠላ ጨርቅ ተኩሰው መኝታ ላይ ጋደም እንድትል አደረጉ፡፡
አቶ አርምዴ የሚደረግላትን ካደረገ በኋላ ወደ ቤቱ ሄደ፡፡ አድሮ በነጋታው ጥዋት እድላዊት እንዴት እንዳደረች ለመጠየቅ ከመኝታው ተነስቶ ሲመጣ እናቱ የቤቱን በር ከፍተው ሲወጡ ደረሰ፡፡
የእግዚአብሔር ሰላምታ ተለዋውጠው "ደግሞ ማታ እመለሳለሁ ብለህ ሳትመጣ ቀረህ በሰላም ነው ያልተመለስከው? አሉት ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
"ለመምጣት አስቤ ነበር፡፡ ግን ቤቱንና ከብቶቹን ትቼ እንዳልመጣ አውሬ እንኳን ቢገባ የሚሰማ ስላልነበረ ቀረሁ"፡፡ እንዴት አደረች ልጅቷ?ተሸሏት አላደረችም? አለ፡፡
የእድላዊት ስቃይና መከራ ከአንጀቱ ገብቶ ሳይወጣ አንጀቱ እያለቀሰላት እህል እንኳን አልወርድ ብሎት ለአደን ሲሄድ በቀመሰው ቁራሽ እንጀራ ነበር፡፡ እራት ሳይቀምስ ያደረው፡፡
ከአሁን አሁን ያማት ይሆን ? እያሉ ሌሊቱን ሙሉ እንቅልፍ ሳይወስዳቸው አይደለም በዓይናቸው ሳይዞር ነበር ያደሩት ወ/ሮ በሰልፏም፡፡
"ሰላም አድራለች፡፡ ብቻ ሌሊቱን ሲያቃዧት ነው ያደረው፡፡ አሟት ይሆን ብየ ሌሊት ተነስቼ ሳያት ከቅዠት በስተቀር ምንም አላየሁባትም፡፡ ከነጋም አልቀሰቀስኳትም፡፡ ቅዝቃዜ ስላለ ትንሽ ትተኛ ብየ ነው፡፡ እስኪ አሁን አንተ ከመጣህ ቀስቅሳትና እንዴት እንዳደረች ጠይቃት አሉ፡፡ ቤታቸውን ለመጥረግ የቤት መጥረጊያ ቅጠል ለማምጣት ወደ ውጭ እየወጡ፡፡
#የድንግሊቷ_አፍቃሪዎች
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
================
አለማየሁ ልቡ ላይ አዲስ እና ያልተጠበቀ ፍቅር በቅሏል…የአስካለ ምስልም በተለይ ወሬዋና ሳቋ ከምናቡ ለደቂቃም ሊሰወር አልቻለም፡፡ለዘላለም ከሰሎሜ ውጭ ሌላ ሰው ሊያፍቀር ሚችል አይመስለውም ነበር…ግን ሆነ፡፡እርግጥ ለሁለቱ ያለው ፍቅር ፍፅም ተመሳሳይ አይደለም….ይሄኛው አዲሱ ፍቅሩ የሚያንቀዠቅዝ አይነት ነው፡፡የወሲብ ርሀብ ያለበት የተክለፈለፈ ፍቅር፡፡የሰሎሜ ግን የተረጋጋና ጥልቅ ነው፡፡ስስትና እና ተስፋ ያቆሙት ዘላለማዊ መሳይ ነው፡፡
ከአስካለ ጋር ባሳለፈ በሁለተኛው ቀን ወደአላዛር ሄደና‹‹አባትህ እንዴት ናቸው?››ሲል ጠየቀው፡፡
‹‹ያው ድኖ አይደል ወደቤት የገባው…ምን ይሆናል?››ሲል ድርቅ ያለ መልስ መለሰለት፡፡
‹‹አሁን እንዴት እንደሆኑ ደውለህ ጠየቅክ?››
‹‹ለምን ብዬ ጠይቃለሁ?››
‹‹በትክክል መጠየቅ ይገባሀል…›››
‹‹የትናንቱንም እንዴት እንዳደረኩት ግራ እየገባኝ ነው››
‹‹እንደውም ተነስ እንሂድና አይተናቸው እንምጣ፡፡››
አላዛር ግራ በመጋባት አፍጥጦ ሲያየው ከቆየ በኃላ፡፡‹‹ሰላም ነህ ግን?››ሲል ጠየቀው፡፡
‹‹ምነው…ምኔ ነው ሰላም አልመስል ያለህ ?››ሲል መልሶ ጠየቀው፡፡
‹‹ የምናገረው አይገባህም እንዴ? ትናንት በዛ ለሊት ለእሱ ስል ራሴም ተንከራትቼ እናንተንም ሳንከራተት ማደሬ እራሱ እየቆጨኝ ነው ..ጭራሽ ዛሬም ደግሜ ቤት ሄጄ እንድጠይቀው ትፈልጋለህ?፡፡››
‹‹ተወው በኃላ እንዳትፀፀት …ላንተው ብዬ ነው፡፡እኔ አባቴ ጠጪም ሌባም ፤ቁማርተኛም ..ምንም ሆኖ ምንም በህይወት ቢኖርልኝ እንዴት እንደምደሰት ልትገምት አትችልም፡፡በዚህ አለም ላይ እንደቤተሰብ ወሳኝ ነገር የለም፡፡ከፋም ለማም በጨለማ ቀናቶችህ አብረውህ የሚንከራተቱት እነሱ ናቸው፡፡..ቤተሰብ በህይወት መንገድ ወሳኙ አጋር እንደሆነ አውቃለው፡፡የገንዘብ ችግር ቢኖርብህ ቤተሰብ ካለህ ታልፈዋለ…ክፉኛ ብትታመም ቤተሰብ ካለህ ህመምህን ቻል አድርገህ በቀላሉ ማገገም ትችላለህ …ሀገርህ ፈርሳ ስደት ላይ ብትሆን እራሱ ቤተሰብህ ከጎንህ ካለ እንደምንም እየተደጋገፍክ ያንን ክፉ ቀን ታልፈዋለህ፡፡››
‹‹ገባኝ…የእኔ ቤተሰብ እናቴና እህቶቼ ናቸው፡፡በተጨማሪ ደግሞ እናንተ ወንድሞቼ አላችሁልኝ…እርግጥ እናቴ የለችም….ሁለት እህቶቼ ግን አሁንም አሉልኝ..እነሱ በቂዬ ናቸው፡፡ለእኔ አባቴ ከእናቴ ቀድሞ ነው የሞተው…አሁን እሱን ሳይ በድን አካሉ ብቻ ነው ሲንቀሳቀስ የማየው..ነፍሱ ውስጡ የለችም፡፡››
አለማየሁ ሊያሳምነው ስላልቻለ ተበሳጨ‹‹በቃ ቸው..ድሮም አንተ ከጠመምክ መመለሻ የለህም››አለውና ፊቱን አዙሮ መራመድ ጀመረ፡፡
‹‹ቆይ አትሂድ..ና እንካ››አለና እጁን ወደባንኮኒው በመስደድ ብር በእጁ አስጨበጠው፡፡
‹‹ምንድነው?››
‹‹ማኪያቶ ልጋብዝህ ነበር …መውጣት አልቻልኩም..ስለዚህ ብቻህን ጠጣ››አለው፡፡
አለማየሁም‹‹አመሰግናለሁ፡፡››ብሎት የሰጠውን ብር በእጁ እያሻሸ አካባቢውን ለቆ ሄደ ..የእሱ ሀሳብ አላዛርን አሳምኖ አባቱ ቤት አብሮት መሄድ ነበር፡፡፡ያንን የፈለገው ያችን ውብ የጓደኛውን አባት ሚስት ዳግመኛ ለማየት ነው፡፡ከትናንትናው ምሽት ጀምሮ ፈፅሞ ከምናቡ ሊያሸሻት አልተቻለውም፡፡የአላዛር መገገም ግን እቅዱን ሁሉ ገደል ከተተበት፡፡
ከአላዛር ሱቅ ከራቀ በኃላ መዳፉን ፈልቅቆ ሲያየው ድፍን መቶ ብር ነው፡፡ስልኩን አወጣ ..ሰሎሜ ጋር ለመደወል ነው የፈለገው፡፡መቶ ብር ካለው ወይ ይዟት ሲኒማ ቤት ይገባል ወይ ደግሞ አንድ ካፌ ቁጭ ብለው ማኪያቶ እየተጎነጩ ዘና ይላሉ፡፡እቅዱ እንደዛ ነው፡፡
‹‹ሄሎ ››
‹‹ምነው? አሁን ተለይተሀኝ ሄደህ አሁን ናፈቅኩህ እንዴ?››
‹‹ውይ ሰው ጠፍቶ አንቺ ትናፍቂኛለሽ…..?ጉረኛ ነሽ››
‹‹እመን …..››
‹‹ለምን ብዬ ነው የማምነው?››
‹‹እሺ ለምን ፈለከኝ?››
‹‹ምን እየሰራሽ ነው…?አመድ በኪሴ ስላለ ዘና ላድርግሽ ብዬ ነው…››
‹‹አንድ ጥብስ የማይገዛ ብር ይዘህ..ዘና ላድርግሽ ብዬ ነው ስትል ትንሽ አይሸምምህም?››
‹‹አንቺ ምስጋና ቢስ…ይሄኔ በኪስሽ አምስት ብር የለም…አሁን ትወጪያለሽ ወይስ አትወጪም?››
‹‹አዝናለሁ እቴቴ...ዘመዶቾ ጋር እንሂድ ብላኝ ለመሄድ እየተዘጋጀን ነው፡፡››
‹‹የት ?ሰንዳፋ?››
‹‹አዎ…ምነው መሄድ ትፈልጋለህ እንዴ?››
‹‹አይ ይለፈኝ…ግን ታድራላችሁ እንዴ?››
‹‹አዎ… ነገ ነው ምንመጣው፡፡››
‹‹እሺ መልካም መንገድ፡፡››
‹‹አንተ ደግሞ በጊዜ ወደቤት ግባ …እቴቴ እንዳታዘርፈኝ እያለች ነው ፡፡››
‹‹እሺ …አታስቢ በያት፡፡››ብሎ ስልኩን ዘጋውና ተቀያሪ ሀሳብ ማብላላት ጀመረ…ወዲያው ነው መሳጭ የሆነ ሀሳብ ብልጭ ያለለት‹‹ መንገድ ተሻገረና ወደአትክልት መሸጫ ሱቅ ሄደ ..አንድ ኪሎ ሙዝ ገዛ፡፡ ታክሲ ውስጥ ገባ ፡፡ቀጥታ ወደአላዛር አባት ሰፈር ነው የሄደው፡፡ደረሰና የውጪውን በራፍ አንኳኳ…፡፡
ከተወሰነ ጥበቃ በኃላ ተከፈተለት…
ይህቺን ሴት ለሁለተኛ ጊዜ ሲያያት ይበልጥ አምራና ውብ ሆና ነው የታየችው፡፡አስካለ ፈፅሞ አየዋለሁ ብላ ያልጠበቀችው ስለሆነ በጣም ነው የደነገጠችው፡፡
በዝምታ አፍጥጣ ስታየው ግራ ተጋባና ‹‹ምነው አላወቅሺኝም እንዴ?››ሲል ጠየቃት፡፡
በራፉን ጋርዳ እንደቆመች‹‹ይቅርታ እንዲህ በቅርቡ ደግሜ አይሀለው ብዬ ስላልገመትኩ ነው…እንጂማ አንተን እንዴት እረሳሀለው፡››አለችው ፡፡
በጥቁር ፔስታል የያዘውን ሙዝ እንድታይ እያወዛወዘ፡፡‹‹ጋሼን ለመጠየቅ ነው የመጣሁት››አላት፡፡
‹‹ግባ…ና ግባ››አለችና በራፉን ለቀቀችለትና ቀድማው ወደውስጥ መራመድ ጀመረች ፡፡ከኃላዋ ተከተላት፡፡ገቡ፡፡
‹‹ቁጭ በል፡፡››ሙዙን አቀበላትና ፈራ ተባ እያለ ቁጭ አለ፡፡
‹‹አሁን የእውነት ሰውዬው እሷቸውን ልጠይቅ እንደመጣው ያምኑኛል?››ሲል ከዚህ በፊት ያላሰበውን ነገር አሰበ‹‹አይ አላዛር ነው የላከኝ ..ስራ ላይ ስለሆንኩ ሰላም መሆኑን እይልኝ ሳለለኝ ነው የመጣሁት፡፡››እለዋለው ሲል ወሰና ተረጋጋ፡፡ሙዙን ተቀበለችውና ጠረጴዛ ላይ አስቀምጣ..ከፊት ለፊቱ ሄዳ ተቀመጠች፡፡
‹‹ጋሼ ተኝተዋል እንዴ?››ፈራ ተባ እያለ ጠየቃት፡፡
‹‹‹የሉም ስራ ገብተዋል››
በረጅሙ ተነፈሰ‹‹እንደዛ ነው…በደንብ ተሻሏቸዋል ማለት ነው?››
‹‹አዎ በደንብ ተሽሏቸዋል፡፡አተነፋፈስህ ግን ባለመኖራቸው ደስ ያለህ ይመስላል››አለችው፡፡ የውስጡን ስላነበበችበት አፈረ፡፡
‹‹አይ..ያው አለ አይደለ..ከድሮም ጀምሮ እፈራቸዋለው…ለዛ ነው፡፡››
‹‹ታዲያ ይሄን ያህል የሚያጨናንቅህ ከሆነ ለምን መጣህ?››ብላ ሲፈራው የቆየውን ከባድ ጥያቄ ጠየቀችው፡፡
‹‹ያው አላዛር ስራ ላይ ስለሆነ መጥቶ ሊጠይቃቸው አልቻለም…እይልኝ ብሎ ስላስቸገረኝ ነው››ከደቂቃ በፊት ያቀናበረውን ምክንያት ነገራት፡፡
ፈገግ አለች….
‹‹ምነው?››
‹‹አይ …እኔ ደግሞ እኔን ለማየት የመጣህ መስሎኝ ደስ ብሎኝ ነበር?››ስትል ያልጠበቀውን አማላይ አይነት መልስ ሰጠችው፡፡
‹‹እሱማ ..ያው እግረመንገዴን አንቺንም ማየትና እንዴት እንደሆንሽ ማወቅ ስለፈለኩ ነው የመጣሁት፡፡››ሲል በከፊል አመነላት፡፡
‹‹ስለመጣህ ደስ ብሎኛል…መጣው ተጫወት›› ብላ ወደውስጥ ገባችና ..ሻይ ጥዳ….ተመለሰች፡፡
ሞባይሉን አወጣና ሰዓቱን ተመለከተ..5፡20 ይላል፡፡‹‹ምሳ ሰዓት እየቀረበ ነው….››አላት፡፡
‹‹አዎ ..ምነው እርቦሀል ላቅርብ እንዴ?››
‹‹አይ!! ማለቴ ጋሼ አሁን ለምሳ ይመጣሉ ለማለት ነው፡፡››
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
================
አለማየሁ ልቡ ላይ አዲስ እና ያልተጠበቀ ፍቅር በቅሏል…የአስካለ ምስልም በተለይ ወሬዋና ሳቋ ከምናቡ ለደቂቃም ሊሰወር አልቻለም፡፡ለዘላለም ከሰሎሜ ውጭ ሌላ ሰው ሊያፍቀር ሚችል አይመስለውም ነበር…ግን ሆነ፡፡እርግጥ ለሁለቱ ያለው ፍቅር ፍፅም ተመሳሳይ አይደለም….ይሄኛው አዲሱ ፍቅሩ የሚያንቀዠቅዝ አይነት ነው፡፡የወሲብ ርሀብ ያለበት የተክለፈለፈ ፍቅር፡፡የሰሎሜ ግን የተረጋጋና ጥልቅ ነው፡፡ስስትና እና ተስፋ ያቆሙት ዘላለማዊ መሳይ ነው፡፡
ከአስካለ ጋር ባሳለፈ በሁለተኛው ቀን ወደአላዛር ሄደና‹‹አባትህ እንዴት ናቸው?››ሲል ጠየቀው፡፡
‹‹ያው ድኖ አይደል ወደቤት የገባው…ምን ይሆናል?››ሲል ድርቅ ያለ መልስ መለሰለት፡፡
‹‹አሁን እንዴት እንደሆኑ ደውለህ ጠየቅክ?››
‹‹ለምን ብዬ ጠይቃለሁ?››
‹‹በትክክል መጠየቅ ይገባሀል…›››
‹‹የትናንቱንም እንዴት እንዳደረኩት ግራ እየገባኝ ነው››
‹‹እንደውም ተነስ እንሂድና አይተናቸው እንምጣ፡፡››
አላዛር ግራ በመጋባት አፍጥጦ ሲያየው ከቆየ በኃላ፡፡‹‹ሰላም ነህ ግን?››ሲል ጠየቀው፡፡
‹‹ምነው…ምኔ ነው ሰላም አልመስል ያለህ ?››ሲል መልሶ ጠየቀው፡፡
‹‹ የምናገረው አይገባህም እንዴ? ትናንት በዛ ለሊት ለእሱ ስል ራሴም ተንከራትቼ እናንተንም ሳንከራተት ማደሬ እራሱ እየቆጨኝ ነው ..ጭራሽ ዛሬም ደግሜ ቤት ሄጄ እንድጠይቀው ትፈልጋለህ?፡፡››
‹‹ተወው በኃላ እንዳትፀፀት …ላንተው ብዬ ነው፡፡እኔ አባቴ ጠጪም ሌባም ፤ቁማርተኛም ..ምንም ሆኖ ምንም በህይወት ቢኖርልኝ እንዴት እንደምደሰት ልትገምት አትችልም፡፡በዚህ አለም ላይ እንደቤተሰብ ወሳኝ ነገር የለም፡፡ከፋም ለማም በጨለማ ቀናቶችህ አብረውህ የሚንከራተቱት እነሱ ናቸው፡፡..ቤተሰብ በህይወት መንገድ ወሳኙ አጋር እንደሆነ አውቃለው፡፡የገንዘብ ችግር ቢኖርብህ ቤተሰብ ካለህ ታልፈዋለ…ክፉኛ ብትታመም ቤተሰብ ካለህ ህመምህን ቻል አድርገህ በቀላሉ ማገገም ትችላለህ …ሀገርህ ፈርሳ ስደት ላይ ብትሆን እራሱ ቤተሰብህ ከጎንህ ካለ እንደምንም እየተደጋገፍክ ያንን ክፉ ቀን ታልፈዋለህ፡፡››
‹‹ገባኝ…የእኔ ቤተሰብ እናቴና እህቶቼ ናቸው፡፡በተጨማሪ ደግሞ እናንተ ወንድሞቼ አላችሁልኝ…እርግጥ እናቴ የለችም….ሁለት እህቶቼ ግን አሁንም አሉልኝ..እነሱ በቂዬ ናቸው፡፡ለእኔ አባቴ ከእናቴ ቀድሞ ነው የሞተው…አሁን እሱን ሳይ በድን አካሉ ብቻ ነው ሲንቀሳቀስ የማየው..ነፍሱ ውስጡ የለችም፡፡››
አለማየሁ ሊያሳምነው ስላልቻለ ተበሳጨ‹‹በቃ ቸው..ድሮም አንተ ከጠመምክ መመለሻ የለህም››አለውና ፊቱን አዙሮ መራመድ ጀመረ፡፡
‹‹ቆይ አትሂድ..ና እንካ››አለና እጁን ወደባንኮኒው በመስደድ ብር በእጁ አስጨበጠው፡፡
‹‹ምንድነው?››
‹‹ማኪያቶ ልጋብዝህ ነበር …መውጣት አልቻልኩም..ስለዚህ ብቻህን ጠጣ››አለው፡፡
አለማየሁም‹‹አመሰግናለሁ፡፡››ብሎት የሰጠውን ብር በእጁ እያሻሸ አካባቢውን ለቆ ሄደ ..የእሱ ሀሳብ አላዛርን አሳምኖ አባቱ ቤት አብሮት መሄድ ነበር፡፡፡ያንን የፈለገው ያችን ውብ የጓደኛውን አባት ሚስት ዳግመኛ ለማየት ነው፡፡ከትናንትናው ምሽት ጀምሮ ፈፅሞ ከምናቡ ሊያሸሻት አልተቻለውም፡፡የአላዛር መገገም ግን እቅዱን ሁሉ ገደል ከተተበት፡፡
ከአላዛር ሱቅ ከራቀ በኃላ መዳፉን ፈልቅቆ ሲያየው ድፍን መቶ ብር ነው፡፡ስልኩን አወጣ ..ሰሎሜ ጋር ለመደወል ነው የፈለገው፡፡መቶ ብር ካለው ወይ ይዟት ሲኒማ ቤት ይገባል ወይ ደግሞ አንድ ካፌ ቁጭ ብለው ማኪያቶ እየተጎነጩ ዘና ይላሉ፡፡እቅዱ እንደዛ ነው፡፡
‹‹ሄሎ ››
‹‹ምነው? አሁን ተለይተሀኝ ሄደህ አሁን ናፈቅኩህ እንዴ?››
‹‹ውይ ሰው ጠፍቶ አንቺ ትናፍቂኛለሽ…..?ጉረኛ ነሽ››
‹‹እመን …..››
‹‹ለምን ብዬ ነው የማምነው?››
‹‹እሺ ለምን ፈለከኝ?››
‹‹ምን እየሰራሽ ነው…?አመድ በኪሴ ስላለ ዘና ላድርግሽ ብዬ ነው…››
‹‹አንድ ጥብስ የማይገዛ ብር ይዘህ..ዘና ላድርግሽ ብዬ ነው ስትል ትንሽ አይሸምምህም?››
‹‹አንቺ ምስጋና ቢስ…ይሄኔ በኪስሽ አምስት ብር የለም…አሁን ትወጪያለሽ ወይስ አትወጪም?››
‹‹አዝናለሁ እቴቴ...ዘመዶቾ ጋር እንሂድ ብላኝ ለመሄድ እየተዘጋጀን ነው፡፡››
‹‹የት ?ሰንዳፋ?››
‹‹አዎ…ምነው መሄድ ትፈልጋለህ እንዴ?››
‹‹አይ ይለፈኝ…ግን ታድራላችሁ እንዴ?››
‹‹አዎ… ነገ ነው ምንመጣው፡፡››
‹‹እሺ መልካም መንገድ፡፡››
‹‹አንተ ደግሞ በጊዜ ወደቤት ግባ …እቴቴ እንዳታዘርፈኝ እያለች ነው ፡፡››
‹‹እሺ …አታስቢ በያት፡፡››ብሎ ስልኩን ዘጋውና ተቀያሪ ሀሳብ ማብላላት ጀመረ…ወዲያው ነው መሳጭ የሆነ ሀሳብ ብልጭ ያለለት‹‹ መንገድ ተሻገረና ወደአትክልት መሸጫ ሱቅ ሄደ ..አንድ ኪሎ ሙዝ ገዛ፡፡ ታክሲ ውስጥ ገባ ፡፡ቀጥታ ወደአላዛር አባት ሰፈር ነው የሄደው፡፡ደረሰና የውጪውን በራፍ አንኳኳ…፡፡
ከተወሰነ ጥበቃ በኃላ ተከፈተለት…
ይህቺን ሴት ለሁለተኛ ጊዜ ሲያያት ይበልጥ አምራና ውብ ሆና ነው የታየችው፡፡አስካለ ፈፅሞ አየዋለሁ ብላ ያልጠበቀችው ስለሆነ በጣም ነው የደነገጠችው፡፡
በዝምታ አፍጥጣ ስታየው ግራ ተጋባና ‹‹ምነው አላወቅሺኝም እንዴ?››ሲል ጠየቃት፡፡
በራፉን ጋርዳ እንደቆመች‹‹ይቅርታ እንዲህ በቅርቡ ደግሜ አይሀለው ብዬ ስላልገመትኩ ነው…እንጂማ አንተን እንዴት እረሳሀለው፡››አለችው ፡፡
በጥቁር ፔስታል የያዘውን ሙዝ እንድታይ እያወዛወዘ፡፡‹‹ጋሼን ለመጠየቅ ነው የመጣሁት››አላት፡፡
‹‹ግባ…ና ግባ››አለችና በራፉን ለቀቀችለትና ቀድማው ወደውስጥ መራመድ ጀመረች ፡፡ከኃላዋ ተከተላት፡፡ገቡ፡፡
‹‹ቁጭ በል፡፡››ሙዙን አቀበላትና ፈራ ተባ እያለ ቁጭ አለ፡፡
‹‹አሁን የእውነት ሰውዬው እሷቸውን ልጠይቅ እንደመጣው ያምኑኛል?››ሲል ከዚህ በፊት ያላሰበውን ነገር አሰበ‹‹አይ አላዛር ነው የላከኝ ..ስራ ላይ ስለሆንኩ ሰላም መሆኑን እይልኝ ሳለለኝ ነው የመጣሁት፡፡››እለዋለው ሲል ወሰና ተረጋጋ፡፡ሙዙን ተቀበለችውና ጠረጴዛ ላይ አስቀምጣ..ከፊት ለፊቱ ሄዳ ተቀመጠች፡፡
‹‹ጋሼ ተኝተዋል እንዴ?››ፈራ ተባ እያለ ጠየቃት፡፡
‹‹‹የሉም ስራ ገብተዋል››
በረጅሙ ተነፈሰ‹‹እንደዛ ነው…በደንብ ተሻሏቸዋል ማለት ነው?››
‹‹አዎ በደንብ ተሽሏቸዋል፡፡አተነፋፈስህ ግን ባለመኖራቸው ደስ ያለህ ይመስላል››አለችው፡፡ የውስጡን ስላነበበችበት አፈረ፡፡
‹‹አይ..ያው አለ አይደለ..ከድሮም ጀምሮ እፈራቸዋለው…ለዛ ነው፡፡››
‹‹ታዲያ ይሄን ያህል የሚያጨናንቅህ ከሆነ ለምን መጣህ?››ብላ ሲፈራው የቆየውን ከባድ ጥያቄ ጠየቀችው፡፡
‹‹ያው አላዛር ስራ ላይ ስለሆነ መጥቶ ሊጠይቃቸው አልቻለም…እይልኝ ብሎ ስላስቸገረኝ ነው››ከደቂቃ በፊት ያቀናበረውን ምክንያት ነገራት፡፡
ፈገግ አለች….
‹‹ምነው?››
‹‹አይ …እኔ ደግሞ እኔን ለማየት የመጣህ መስሎኝ ደስ ብሎኝ ነበር?››ስትል ያልጠበቀውን አማላይ አይነት መልስ ሰጠችው፡፡
‹‹እሱማ ..ያው እግረመንገዴን አንቺንም ማየትና እንዴት እንደሆንሽ ማወቅ ስለፈለኩ ነው የመጣሁት፡፡››ሲል በከፊል አመነላት፡፡
‹‹ስለመጣህ ደስ ብሎኛል…መጣው ተጫወት›› ብላ ወደውስጥ ገባችና ..ሻይ ጥዳ….ተመለሰች፡፡
ሞባይሉን አወጣና ሰዓቱን ተመለከተ..5፡20 ይላል፡፡‹‹ምሳ ሰዓት እየቀረበ ነው….››አላት፡፡
‹‹አዎ ..ምነው እርቦሀል ላቅርብ እንዴ?››
‹‹አይ!! ማለቴ ጋሼ አሁን ለምሳ ይመጣሉ ለማለት ነው፡፡››
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
////
ዘሚካኤል ተገትሮ በቆመበት የክፍሉ መሀከላዊ ስፍራ እንደደነዘዘ ነው፡፡ልጅቱ አስር ለማይሞሉ ደቂቃዎች ብቻ አብራው ብታሳልፍም….ግን ደግሞ ለቀናት ያህል ያቀፋትና ለሳዕታት ሲስማት የቆየ አይነት ስሜት ነው እየተሰማው ያለው…‹‹.ለምን ጉዳይ መጣች ምን ሰርታ ሄደች?››ብሎ ሲያስብ ሳይወድ ፈገግ አለ…ከቆመበት ተንቀሳቀሰና እጁ ላይ ያለውን የሰርግ የጥሪ ካርድ የያዘውን ፖስታ በራፉ አጠገብ በሚገኘው ቆሻሻ ማጠረቀሚያ ቅርጫት ውስጥ ጨምድዶ ወረወረው፡፡
ለዛች ስሟን እንኳን ላልነገረችው ሴት ልጅ እንደነገራት በዚህ አለም ምንም አይነት ወንድም ሆነ ቤተሰብ አያስፈልገውም እና ወደ የትኛውም ሰርግ የመሄድ ፍላጎት የለውም። እንደውም ከተቻለው ስለቤተሰብ በውስጡ የቀረውን እንጥፍጣፊ ትዝታ ከልቡ አሟጦ መሰረዝ ነው ፍላጎቱ፡፡
ከወገብ በላይ ራቁቱን መሆኑን ትዝ ሲለው ወደጠረጴዛው ሄደና ያወለቀውን ልብስ መልሶ ለበሰው..መጀመሪያ እቅዱ ቀጣይ የሙዚቃ ማቅረቢያ ሰዓቱ እስኪደርስ ድረስ ሻወር ገብቶ ከተለቃለቀ በኃላ 30 ወይም 40 ደቂቃ መተኛትና እረፍት መውሰድ ነበር፡፡አሁን ግን ሻወር የመውሰድም ሆነ የመተኛት ፍላጎቱ ከውስጡ በኖ ጠፍቷል…ቀጥታ ሶፋው ላይ ሄደና ተቀመጠ፡፡ፊትለፊት ካለው ጠረጴዛ ላይ ያለውን የውስኪ ጠርሙስ አነሳና ከፍቶ በብርጭቆ ቀድቶ እየተጎነጨ ማሰላሰል ጀመረ….
‹‹ይህቺ ልጅ ምኑን ነክታ እንዴት ስሜቱን ድፍርስርስ አድርጋ እንደሄደች አያውቅም…ወንድሙ ላይ የያዘበት ቂምና የተበሳጨበት ብስጭት አሁንም ትኩስ ነው፡፡
‹‹ግን የዛን ጊዜ ፈቅዶልኝ አባቴን በዛ ቢላዋ ጨቅጭቄ ብገድለው ኖሮስ…?››ሁል ጊዜ እራሱን የሚጠይቀው ጥያቄ ነው፡፡
አዎ ወንድሙ በድብድብ እና በትግል ባያስቆመው ኖሮ እሱም ይሄን ጊዜ የእድሜ ልክ ፍርድ ተፈርዶበት በአባቱ ምትክ እስር ቤት ውስጥ ተቆልፎበት ተስፋ የሌለው ህይወት ይኖር እንደነበረ…እርግጠኛ ነው፡፡
‹‹ታዲያ እኮ ሚካኤል ወንድምህ የእድሜ ልክ ባለውለታህ እንጂ ጠላትህ አይደለም?››አለው አእምሮው፡፡
‹‹ለምን..ያማ እውነት አይደለም….እሱ እኮ እንደዛ ያደረገው እኔን ከመከራ ለማትረፍ አስቦ ሳይሆን ለዛ ጨካኝ እና ገዳይ አባቱ ለማገዝ ፈልጎ ነው››
‹‹አይ እሱ የአንተ አእምሮ አንሻፎ የተረጎመው ትርጉም ነው…እንደዛም ቢሆን እንኳን በዛ ታሪክ ውስጥ ዋናው ተጠቃሚ አንተ ነህ፡፡በወቅቱ ዝም ብሎህ ያሰብከውን እንድታደርግ ቢፈቅድልህ ኖሮ ዛሬ በዚህ ጊዜ ዝነኛው ድምፃዊና ተዋናዩ ዘሚካኤል የለም ነበር…ሀመር መኪና የሚነዳው…የተንጣለለ ውድና ውብ ቪላ ቤት ውስጥ የሚኖረው…ከአደባባይ እስከቤተመንግስት የሚታወቀውና የሚጋበዘው የመገናኛ ብዙሀኖች የዜና ማጣፈጫ የሆነው ዘሚካኤል አይኖርም ነበር፡፡››ሲል እራሱን በራሱ በዝርዝር አስረዳ፡፡
የአእምሮው የእርስ በርስ ጭቅጭቅ ከዚህ በላይ ማስቀጠል አልቻለም..ምክንያቱም በንዴትና በቁጭት አእምሮው ብቻ ሳይሆን መላ ሰውነቱ እየጋለበት ነው፡፡ጠረጴዛው ላይ ያለውን ብርጭቆ አነሳና ጠቀም አድርጎ ተጎነጨለት እና መልሶ አስቀመጠው፡፡
ከዛ ስለሌላ ነገር ለማሰብ ሞከረ ..ግን አሁንም አእምሮውን የሞላችው ያቺ ከደቂቃዎች በፊት ከሰውነቱ ለጥፎ ያቀፋትና ለሁለት ሰከንድ ሲስማት የነበረችው ሴት ነች፡፡‹‹ቆይ ይህቺ ልጅ ምን የተለየ ነገር ቢኖራት ነው ከአእምሮዬ ልትወጣ ያልቻለችው ?››እራሱን ጠየቀ…‹‹ከንፈሯ ላይ አስማት አለ መሰለኝ…››አለና ፈገግ አለ….‹‹ምን አለ ስሟን እና የሞባይል ቁጥሯን ብጠይቃት ኖሮ…?››በጣም ተቆጨ፡፡
ደግሞ እሷም እሱን በምንም አይነት ሁኔታ ደግማ የማግኘት ፍላጎት እንደሌላት በሚያሳይ ሁኔታ ነው የመጣችበትን ጉዳይ ተናግራ የጥሪ ካርድን እጁ ላይ አስቀምጣ ነው ውልቅ ብላ የሄደችው፡፡
‹‹ባለትዳር ትሆን እንዴ?››የሚል ሀሳብ በአእምሮ ብልጭ አለበት፡፡
ሀሳብን መቋጫ ሳያበጅለት በራፉ በስሱ ተቆረቆረ…ብርጭቆ ውስጥ የቀረችውን ውስኪ ጨለጠና ሶፋውን ለቆ ወደበራፉ ሄደ ..ቀጣይ ዝግጅቱን የሚያቀርብበት ጊዜ መድረሱን ለማሳወቅ በራፉን እንደቆረቆሩ ያውቀል..በራፉን ከፍቶ ሲወጣ ንቁ ሆነው የሚጠብቁት ሁለት ወጠምሻ ጋርዶች ከግራና ከቀኝ ከበቡት፡፡ ሁለት እርምጃ ከተራመደ በኃላ የሆነ ነገር ወደኃላ ሳበው…መልሶ ፊቱን ዞረና ወደክፍሉ ተመለሰ….ከውስጥ በኩል ከበራፉ በስተቀኝ ወዳለው የቆሻሻ ማጠራቀሚያ ባስኬት አጎነበሰና አጣጥፎ የጣለውን የሰርግ ጥሪ ወረቀት አነሳ ፡፡የሱሪ ኋላ ኪስ ውስጥ ጨመረውና መልሶ ወጣ..ለምን እንዲህ እንዳደረገ ቢጠየቅ ምንም አይነት መልስ የለውም …እንዲሁ በደመነፍስ ያደረገው ነገር ነው፡፡
////
አሁን የዘሚካኤል ምስል ከሙሉ አቋሙ ጋር በአእምሯዋ እየተራወጠ ነው፡፡ሁለቱ ወንድማማቾች ከቁመትና ከፀባይ ውጭ በሌላው ነገር በሚያስደንቅ ሁኔታ ይመሳሰላሉ። የሚካኤል ባህሪያት ከዘሚካኤል ትንሽ ደብዘዝ ያሉ ነበሩ እና የዓይኑ ቀለም ንፁህ ፣ ጠንከር ያለ ሰማያዊ ነበረ ፣ ግን ሁለቱም ሰዎች ተመሳሳይ ውብ ፈገግታ፣ ክብ የፊት ቅርፅ እና ሰልካካ አፍንጫ.. ወተት ከመሰሉ ነጫጭ ድርድር ጥርሶች ጋር አላቸው፤››
እየሾፈረች ያለችውን ቪታራ መኪና ኤክስፐረስ መንገድ ውስጥ አስገብታ ወደ አዳማ እያሽከረከረች ሲሆን አሁንም ስለዛ ዘ-ሚካኤል ስለሚባለው ድምጻዊ ነው የምታሰላስለው፡፡ለሊት 8 ሰዓት ላይ ከእሱ ተለይታ እዛው በአቅራቢያው ወደተከራየችው ፕንሲዬን ሄዳ ለመተኛት ብትሞክርም ምንም እንቅልፍ በአይኗ ሳይዞር እንዲሁ ስትበሳጭና ስትገላበጥ ነው ያደረችው፡፡
ስለእሱ ማሰብ የጀመረችው ቀደም ብላ ታሪኩን ከየጋዜጦችና ከዪቲዩብ ቻናሎች እየሰበሰበች በምታዳምጥበት ጊዜ ነው፡፡እርግጥ ታውቀለች በዩቲዩቭ የቀረበ ዜና ሁሉ በተለይ ስለፍቅርና ፃታዊ ግንኙነት የሚነዙት አብዛኞቹ ተመልካች ለማግኘት የታስቡ…በውሸት የሚፈበረኩ እንደሚሆን ታምናለች..ግን ቢሆንም‹‹ እሳት በሌለበት ጭስ አይጨስም….››በማለት ለሰው ስሜት የማይጨነቅ ጋጠወጥ ወሲባም አድርጋ ስላው ነበር፡፡እና ደግሞ ለሊት እንዳየችው አልተሳሳተችም…በዛ ለሊት እዛ ክፍል ውስጥ ሲያገኛት መጀመሪያ ያደረገው ወደራሱ ስቦ ከንፈሯ ላይ መጣበቅ ነው…..ስለዛች ቅፅበት ስታስብ ከንፈሯ ተንቀጠቀጠባት….የሚያበሳጨው ደግሞ ለማንም ሴት ግርማ ሞገሱንና ውበቱን ለመቋቋም አስቸጋሪ የሆነ ሰው መሆኑን በራሷ ማረጋገጧ ነው…ባለፉት ስድስት አመታት በጣም ብዙ ከሆኑ ወንዶች በብዙ የተለያዩ አጋጣሚዎች ሊፈታተኗት ሞክረው ሾልካና አሳስቃ ..አንዳንዱንም ተኮሳትራና አስፈራርታ እራሷን ማትረፍ ችላለች..ከእሱ ጋር ግን በአንድ እይታ ነው ተዝለፍልፋ እቅፉ ውስጥ የወደቀችው፡፡
እንደምንም ከእቅፉ ወጥታ ለማምለጥ ወደበራፉ በምትራመድበት ጊዜ እንኳን ተንደርድሮ መጥቶ እጇን ይዞ ጎትቶ እንዲያስቀራት እና ተሸክሞ ሶፋው ላይ እንዲጥላት በውስጧ እየተመኘች ነበር፡፡ግን በተመሳሳይ ጊዜ እንደዛ በመመኘቷ እራሷን ስትወቅስና ስትራገም ነበር፡፡
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
////
ዘሚካኤል ተገትሮ በቆመበት የክፍሉ መሀከላዊ ስፍራ እንደደነዘዘ ነው፡፡ልጅቱ አስር ለማይሞሉ ደቂቃዎች ብቻ አብራው ብታሳልፍም….ግን ደግሞ ለቀናት ያህል ያቀፋትና ለሳዕታት ሲስማት የቆየ አይነት ስሜት ነው እየተሰማው ያለው…‹‹.ለምን ጉዳይ መጣች ምን ሰርታ ሄደች?››ብሎ ሲያስብ ሳይወድ ፈገግ አለ…ከቆመበት ተንቀሳቀሰና እጁ ላይ ያለውን የሰርግ የጥሪ ካርድ የያዘውን ፖስታ በራፉ አጠገብ በሚገኘው ቆሻሻ ማጠረቀሚያ ቅርጫት ውስጥ ጨምድዶ ወረወረው፡፡
ለዛች ስሟን እንኳን ላልነገረችው ሴት ልጅ እንደነገራት በዚህ አለም ምንም አይነት ወንድም ሆነ ቤተሰብ አያስፈልገውም እና ወደ የትኛውም ሰርግ የመሄድ ፍላጎት የለውም። እንደውም ከተቻለው ስለቤተሰብ በውስጡ የቀረውን እንጥፍጣፊ ትዝታ ከልቡ አሟጦ መሰረዝ ነው ፍላጎቱ፡፡
ከወገብ በላይ ራቁቱን መሆኑን ትዝ ሲለው ወደጠረጴዛው ሄደና ያወለቀውን ልብስ መልሶ ለበሰው..መጀመሪያ እቅዱ ቀጣይ የሙዚቃ ማቅረቢያ ሰዓቱ እስኪደርስ ድረስ ሻወር ገብቶ ከተለቃለቀ በኃላ 30 ወይም 40 ደቂቃ መተኛትና እረፍት መውሰድ ነበር፡፡አሁን ግን ሻወር የመውሰድም ሆነ የመተኛት ፍላጎቱ ከውስጡ በኖ ጠፍቷል…ቀጥታ ሶፋው ላይ ሄደና ተቀመጠ፡፡ፊትለፊት ካለው ጠረጴዛ ላይ ያለውን የውስኪ ጠርሙስ አነሳና ከፍቶ በብርጭቆ ቀድቶ እየተጎነጨ ማሰላሰል ጀመረ….
‹‹ይህቺ ልጅ ምኑን ነክታ እንዴት ስሜቱን ድፍርስርስ አድርጋ እንደሄደች አያውቅም…ወንድሙ ላይ የያዘበት ቂምና የተበሳጨበት ብስጭት አሁንም ትኩስ ነው፡፡
‹‹ግን የዛን ጊዜ ፈቅዶልኝ አባቴን በዛ ቢላዋ ጨቅጭቄ ብገድለው ኖሮስ…?››ሁል ጊዜ እራሱን የሚጠይቀው ጥያቄ ነው፡፡
አዎ ወንድሙ በድብድብ እና በትግል ባያስቆመው ኖሮ እሱም ይሄን ጊዜ የእድሜ ልክ ፍርድ ተፈርዶበት በአባቱ ምትክ እስር ቤት ውስጥ ተቆልፎበት ተስፋ የሌለው ህይወት ይኖር እንደነበረ…እርግጠኛ ነው፡፡
‹‹ታዲያ እኮ ሚካኤል ወንድምህ የእድሜ ልክ ባለውለታህ እንጂ ጠላትህ አይደለም?››አለው አእምሮው፡፡
‹‹ለምን..ያማ እውነት አይደለም….እሱ እኮ እንደዛ ያደረገው እኔን ከመከራ ለማትረፍ አስቦ ሳይሆን ለዛ ጨካኝ እና ገዳይ አባቱ ለማገዝ ፈልጎ ነው››
‹‹አይ እሱ የአንተ አእምሮ አንሻፎ የተረጎመው ትርጉም ነው…እንደዛም ቢሆን እንኳን በዛ ታሪክ ውስጥ ዋናው ተጠቃሚ አንተ ነህ፡፡በወቅቱ ዝም ብሎህ ያሰብከውን እንድታደርግ ቢፈቅድልህ ኖሮ ዛሬ በዚህ ጊዜ ዝነኛው ድምፃዊና ተዋናዩ ዘሚካኤል የለም ነበር…ሀመር መኪና የሚነዳው…የተንጣለለ ውድና ውብ ቪላ ቤት ውስጥ የሚኖረው…ከአደባባይ እስከቤተመንግስት የሚታወቀውና የሚጋበዘው የመገናኛ ብዙሀኖች የዜና ማጣፈጫ የሆነው ዘሚካኤል አይኖርም ነበር፡፡››ሲል እራሱን በራሱ በዝርዝር አስረዳ፡፡
የአእምሮው የእርስ በርስ ጭቅጭቅ ከዚህ በላይ ማስቀጠል አልቻለም..ምክንያቱም በንዴትና በቁጭት አእምሮው ብቻ ሳይሆን መላ ሰውነቱ እየጋለበት ነው፡፡ጠረጴዛው ላይ ያለውን ብርጭቆ አነሳና ጠቀም አድርጎ ተጎነጨለት እና መልሶ አስቀመጠው፡፡
ከዛ ስለሌላ ነገር ለማሰብ ሞከረ ..ግን አሁንም አእምሮውን የሞላችው ያቺ ከደቂቃዎች በፊት ከሰውነቱ ለጥፎ ያቀፋትና ለሁለት ሰከንድ ሲስማት የነበረችው ሴት ነች፡፡‹‹ቆይ ይህቺ ልጅ ምን የተለየ ነገር ቢኖራት ነው ከአእምሮዬ ልትወጣ ያልቻለችው ?››እራሱን ጠየቀ…‹‹ከንፈሯ ላይ አስማት አለ መሰለኝ…››አለና ፈገግ አለ….‹‹ምን አለ ስሟን እና የሞባይል ቁጥሯን ብጠይቃት ኖሮ…?››በጣም ተቆጨ፡፡
ደግሞ እሷም እሱን በምንም አይነት ሁኔታ ደግማ የማግኘት ፍላጎት እንደሌላት በሚያሳይ ሁኔታ ነው የመጣችበትን ጉዳይ ተናግራ የጥሪ ካርድን እጁ ላይ አስቀምጣ ነው ውልቅ ብላ የሄደችው፡፡
‹‹ባለትዳር ትሆን እንዴ?››የሚል ሀሳብ በአእምሮ ብልጭ አለበት፡፡
ሀሳብን መቋጫ ሳያበጅለት በራፉ በስሱ ተቆረቆረ…ብርጭቆ ውስጥ የቀረችውን ውስኪ ጨለጠና ሶፋውን ለቆ ወደበራፉ ሄደ ..ቀጣይ ዝግጅቱን የሚያቀርብበት ጊዜ መድረሱን ለማሳወቅ በራፉን እንደቆረቆሩ ያውቀል..በራፉን ከፍቶ ሲወጣ ንቁ ሆነው የሚጠብቁት ሁለት ወጠምሻ ጋርዶች ከግራና ከቀኝ ከበቡት፡፡ ሁለት እርምጃ ከተራመደ በኃላ የሆነ ነገር ወደኃላ ሳበው…መልሶ ፊቱን ዞረና ወደክፍሉ ተመለሰ….ከውስጥ በኩል ከበራፉ በስተቀኝ ወዳለው የቆሻሻ ማጠራቀሚያ ባስኬት አጎነበሰና አጣጥፎ የጣለውን የሰርግ ጥሪ ወረቀት አነሳ ፡፡የሱሪ ኋላ ኪስ ውስጥ ጨመረውና መልሶ ወጣ..ለምን እንዲህ እንዳደረገ ቢጠየቅ ምንም አይነት መልስ የለውም …እንዲሁ በደመነፍስ ያደረገው ነገር ነው፡፡
////
አሁን የዘሚካኤል ምስል ከሙሉ አቋሙ ጋር በአእምሯዋ እየተራወጠ ነው፡፡ሁለቱ ወንድማማቾች ከቁመትና ከፀባይ ውጭ በሌላው ነገር በሚያስደንቅ ሁኔታ ይመሳሰላሉ። የሚካኤል ባህሪያት ከዘሚካኤል ትንሽ ደብዘዝ ያሉ ነበሩ እና የዓይኑ ቀለም ንፁህ ፣ ጠንከር ያለ ሰማያዊ ነበረ ፣ ግን ሁለቱም ሰዎች ተመሳሳይ ውብ ፈገግታ፣ ክብ የፊት ቅርፅ እና ሰልካካ አፍንጫ.. ወተት ከመሰሉ ነጫጭ ድርድር ጥርሶች ጋር አላቸው፤››
እየሾፈረች ያለችውን ቪታራ መኪና ኤክስፐረስ መንገድ ውስጥ አስገብታ ወደ አዳማ እያሽከረከረች ሲሆን አሁንም ስለዛ ዘ-ሚካኤል ስለሚባለው ድምጻዊ ነው የምታሰላስለው፡፡ለሊት 8 ሰዓት ላይ ከእሱ ተለይታ እዛው በአቅራቢያው ወደተከራየችው ፕንሲዬን ሄዳ ለመተኛት ብትሞክርም ምንም እንቅልፍ በአይኗ ሳይዞር እንዲሁ ስትበሳጭና ስትገላበጥ ነው ያደረችው፡፡
ስለእሱ ማሰብ የጀመረችው ቀደም ብላ ታሪኩን ከየጋዜጦችና ከዪቲዩብ ቻናሎች እየሰበሰበች በምታዳምጥበት ጊዜ ነው፡፡እርግጥ ታውቀለች በዩቲዩቭ የቀረበ ዜና ሁሉ በተለይ ስለፍቅርና ፃታዊ ግንኙነት የሚነዙት አብዛኞቹ ተመልካች ለማግኘት የታስቡ…በውሸት የሚፈበረኩ እንደሚሆን ታምናለች..ግን ቢሆንም‹‹ እሳት በሌለበት ጭስ አይጨስም….››በማለት ለሰው ስሜት የማይጨነቅ ጋጠወጥ ወሲባም አድርጋ ስላው ነበር፡፡እና ደግሞ ለሊት እንዳየችው አልተሳሳተችም…በዛ ለሊት እዛ ክፍል ውስጥ ሲያገኛት መጀመሪያ ያደረገው ወደራሱ ስቦ ከንፈሯ ላይ መጣበቅ ነው…..ስለዛች ቅፅበት ስታስብ ከንፈሯ ተንቀጠቀጠባት….የሚያበሳጨው ደግሞ ለማንም ሴት ግርማ ሞገሱንና ውበቱን ለመቋቋም አስቸጋሪ የሆነ ሰው መሆኑን በራሷ ማረጋገጧ ነው…ባለፉት ስድስት አመታት በጣም ብዙ ከሆኑ ወንዶች በብዙ የተለያዩ አጋጣሚዎች ሊፈታተኗት ሞክረው ሾልካና አሳስቃ ..አንዳንዱንም ተኮሳትራና አስፈራርታ እራሷን ማትረፍ ችላለች..ከእሱ ጋር ግን በአንድ እይታ ነው ተዝለፍልፋ እቅፉ ውስጥ የወደቀችው፡፡
እንደምንም ከእቅፉ ወጥታ ለማምለጥ ወደበራፉ በምትራመድበት ጊዜ እንኳን ተንደርድሮ መጥቶ እጇን ይዞ ጎትቶ እንዲያስቀራት እና ተሸክሞ ሶፋው ላይ እንዲጥላት በውስጧ እየተመኘች ነበር፡፡ግን በተመሳሳይ ጊዜ እንደዛ በመመኘቷ እራሷን ስትወቅስና ስትራገም ነበር፡፡