ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.82K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
393 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
#ተአምረ ማርያም የተባለው ጉደኛ መጽሐፍ የምንወዳትን ድንግል ማርያምን ያከበረ የሚመስል ነገር ግን #ስድብ እና #ክህደት የሞላበት ስለመሆኑ እርግጥ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ከተጻፈ #ከ1400 ዓመት በኋላ በኢትዮጵያ ንጉሥ በዘርዓ ያዕቆብ የተደረሰ ሲሆን በወቅቱ የነበሩ የቤተ ክርስቲያናችን ሊቃውንት እና ምእመናን ይህ ልዩ ወንጌል ከሐዋርያት ትምህርት የወጣ ስለሆነ #አንቀበለውም በማለታቸው፣ እስከ…


ታሪኩ ሲጀምር

መጽሐፉ “ #ቅምር” በሚባል አገር አንድ ሰው ነበር
#ወኢየበልዕ እክለ ወኢ ሥጋ ላሕም ወኢ ካልአ እንሥሣ አላ ይበልዕ ሥጋ ሰብእ”
ትርጉም:- እህል፥ የላም፥ ሥጋ የሌሎችንም እንሥሳ ሥጋ አይበላም ነበር የሰው ሥጋ ይበላ ነበር እንጂ” #ቁ 68።)

« #ወዘበልዖሙሰ ሰብእ የአክሉ ፸ወ፰ተ ነፍሳተ ወኀልቁ ወተወድኡ ዓርካኒሁ ወፍቁራኒሁ ወአዝማዲሁ ወመገብቱ»
ትርጉም:- «የበላቸውም ሰዎች #78 ነፍሳት ያህላሉ ባልንጀሮቹ ወዳጆቹም ዘመዶቹም ቤተ ሰቦቹም አለቁ ተጨረሱ» #ቁ 69)
ሰውየው ልጆቹን #ከበላ በኋላ ከቤት ወጥቶ ሄደ በማለት ታሪኩ ይቀጥላል። ሲዞርም ሁለንተናው #በደዌ #ሥጋ #የታመመ ሰው አገኘ።( #ቁ 92) #ሊበላው #አስቦ ነበር ነገር ግን #በደዌው ምክንያት ሰለጠላው #ሊበላው #አልወደደም። በደዌ የተያዘው ሰው ግን ፈጽሞ #የተጠማ ስለነበረ " #በላዔ ሰብን "
ስለ
#እ #ግ #ዚ #አ #ብ #ሄ #ር
ብለህ #ውሃ #አጠጣኝ አለው " በላዔ ሰብ ግን
#ተ
#ቆ
#ጣ
#ለሁለተኛ ጊዜ ስለ #ጻድቃን እና ስለ #ሰማዕታት #አጠጣኝ አለው፤ አሁንም #በላዔ ሰብእ ፈጽሞ #ተቆጣው #ሊያጠጣው #አልፈለገም#የተጠማው #ሰው #ሦስተኛ
#ፈጣሪን #ስለወለደች
ስለ #ማ #ር #ያ #ም #አጠጣኝ አለው። በዚህ ጊዜ #በላዔ ሰብእ እስኪ #ቃልህን #ድገመው አለ፤ #አምላክን #ስለወለደች #ስለማርያም ብለህ #አጠጣኝ #አለው በዚህ ጊዜ #በላዔ ሰብእ « #ስለዚህች ስም ከሲኦል #እንደምታድን ሰምቻለሁ» አለ አሁንም እኔ በሷ #ተማጽኛለሁ #በማርያም #ስም #እንካ #ጠጣ #አለው#ውሃው ትንሽ ስለነበር እጁ ላይ ፈሶ ቀረ ጉሮሮውንም አንጣጣው እንጂ ጥሙን አልቆረጠለትም በማለት ያጭውተናል።

እስቲ እንደው ይሄን ምን #ትሉታላቹ
ለነገሩ ይሄን ያነበበ ትክክለኛ ክርስቲያን ምን እንደሚል መገመት አይከብደውም።

#ነገርዬውን ስናስተውለው #በላዔ #ሰብእ #ስለ #እግዚአብሔር ተብሎ #በእግዚአብሔር #ስም #ሲለመን#እግዚአብሔርን #አላውቅም ብሏል። ይህ ሰው #እምነት #የለሽ ከመሆኑም በላይ እንዲያውም ውሃ በመስጠት ፈንታ ስሙ ሲጠራ ተቆጥቷል። #በማርያም ተብሎ ሲለመን ግን #ውሃውን #ሰጠ። የእግዚአብሔርን ይቅርታ ተጠራጥሮ በማርያም ስም #በሰጠው ውሃ #እንደሚድን ነው #ያመነው#የክህደቱ ምሥጢር፣ ምንፍቅናው፣ ኑፋቄው እዚህ ላይ ነው። ይህ ትምህርት ህዝባችንን
በሚቀቀለው #ንፍሮ
በሚጠመቀው #ጠላ
በሚዘከረው #ዝክር #እድናለሁ የሚል አጉል #ተስፋ እንዲይዝ አድርጎታል።
#ዝክርሽን የዘከረ፣ #ስምሽን #የጠራ #ይድናል #የሚለው ባዕድ ወንጌል ተቀባይነት እንዲያገኝ #የበላዔ ሰብን #ልብ ወለድ ታሪክ #እንደማስረጃ አድርጎ #ለማሳመን #ለሕዝብ #የቀረበ ነው።

ታሪኩ ይቀጥልና የምድሩን ጨርሶ በላይ በሰማይ በእግዚአብሐር የፍርድ ዙፋን የተከናወነውን በታዛቢነት ተቀምጦ ያየ ይመስል ሊነግረን ይሞክራል። #በላዔ ሰብ #አንድ #ዋሻ ውስጥ #ገብቶ #ሞተ
« #ወመጽኡ መላእክተ ጽልመት በአፍርሆ ወበ አደንግጾ ወከበብዎ ወአውጽኡ ነፍሶ በጕጸት ወበግዱድ»
ትርጉም:- « #በማስፈራትና በማስደንገጥ የጨለማ አበጋዞች አጋንንት መጥተው ከበቡት በመቀማትና በግድ ነፍሱን ከሥጋው ለዩ»
ይላል #ደራሲው ይህ ሁሉ ሲሆን ቁጭ ብሎ የሚመለከት #ይመስላል። ይህ በእንዲህ እንዳለ መላእክት ይህን ጉዳይ #ለማርያም ነገራት #ድንግል ማርያም #ግን #በስሟ #ያጠጣውን #ቀዝቃዛ #ጽዋ #ውሃ #በጎኑ #ተሸክሞ #ስላየችው ደስ አላት
« #ወርእየት እግዝእትነ ቅድስት ድንግል ወላዲተ አምላክ በገቦሁ ማየ ምልአ ሕፍን ዘአስተየ ለነዳይ ምጽዋተ ቤእንተ ስማ ወተፈስሐት ሶቤሃ»
ትርጉም:- « #እመቤታችን ስለ ስሟ ለድሀ ምጽዋት አድርጎ ያጠጣውን ጥርኝ ውሃ በጎኑ አይታ ያን ጊዜ ደስ አላት» ማለት ነው።
#ነፍሳት በምድር ላይ እንደፈለጋቸው ሲቀላውጡ ኖረው አንድ ቀን የሰጡትን #ውሃ ወደ ሰማይ ሲሄዱ ተሸክመው እንደሚገኙ የሚያስተምር #የክርስትና #ትምህርት የለም። የዚህ ነፍሰ ገዳይ ነፍስ ግን በጎኗ ጥርኝ ውሃ ተሸክማ ስትሄድ ማርያም አየችና ደስ አላት ይለናል። ነፍሳት ወደ #ማርያም ሳይደርሱ ወደ #እግዚአብሔር #እንደማይቀርቡ ( #ቁ 111) ላይ ይናገራል #ድንግል ማርያም #የበላዔ #ሰብን #ነፍስ #ውሃ ተሸክማ #ያየቻት በዚህ ምክንያት ነው።

በመጨረሻ #መላእክት #የበላዔ ሰብን #ነፍስ ወደ #እግዚአብሔር ፊት #አደረሷትና #ልቅሶና #ጥርስ ማፋጨት #ወዳለበት #ጣሏት የሚል ትእዛዝ #ከዙፋኑ ወጣ ይላል። በዚህ ጊዜ #ድንግል ማርያም #ማርልኝ #እያለች ለመነች #በስሜ #ቀዝቃዛ #ጽዋ #ውሃ ያጠጣውን #ልትምርልኝአሳየ ቃል #ገብተህልኝ #አልነበረምን? አለች። እግዚአብሔርም ፍርዱን ገልብጦ ሚካኤልን #ጥርኝ ውሃንና #78ቱን #ነፍሳት መዝንልኝ አለው። #ሚካኤልም #ውሃንና #78ቱን #ነፍሳት ሲመዝን #ውሃ ቀለለ #ነፍሳት ግን #ክብደት #አሳዩ ይላል።
#ድንግል ማርያም ግን #ፈጠን
ብላ #በውሃው ላይ #ጥላዋን #ጣለችበት #በዚህ ጊዜ #ውሃው #ከበደ #ነፍሳት #ግን #ቀለሉ
#በላዔ ሰብም በማርያም #ጥላ
ምክንያት #ለትንሽ
#ከሲኦል #አመለጠ #በማለት #አስቂኝ #ልቦለድ #ያስነብበናል#ይህም ታሪክ #እውነት ነው ተብሎ #አመታዊ በአል ሆኖ #እንዲከበር#ዜማ ተዘጋጅቶለት #መልክ #ተድርሶለት #እንዲነገር #ተብሎ #በየካቲት 16 ቀን #ታስቦ ይውላል። የየካቲት አስራ ስድስት #የኪዳነ ምሕረት በዓል ይህን ቃል ኪዳን የተመለከተ ነው።

@gedlatnadersanat
👇👇👇


ሮሜ 8÷34

" #የሞተው÷ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው÷ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው÷ ደግሞ ስለ እኛ #የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፡፡"

#ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ መልእክቱ ማስተላልፍ የፈለገው ‹‹ #እንግዲህ #በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን #ኵነኔ የለባቸውም›› የሚለውን ነው (ቊጥር 1)፡፡ ሐዋርያው በመቀጠል ‹‹ #በክርስቶስ ኢየሱስ ያለው #የሕይወት መንፈስ ሕግ #ከኀጢአትና #ከሞት ሕግ ዐርነት›› ያወጣን መሆኑን ያበሥርና (ቊጥር 2) እንደ #ሥጋ ፈቃድ ሳይሆን እንደ #መንፈስ ፈቃድ መመላለስ እንደሚገባን ይመክራል፡፡ ምክንያቱንም ደግሞ ‹‹ስለ #ሥጋ ማሰብ #ሞት ነውና÷ ስለ #መንፈስ ማሰብ ግን #ሕይወትና #ሰላም ነው›› በሚል ያስቀምጣል (ቊጥር 6)፡፡ ስለዚህ እንደ #ሥጋ ፈቃድ ሳይሆን እንደ #መንፈስ ፈቃድ መመላለስ እንደሚገባ ካሰፈረ በኋላ ‹‹ #አባ #አባት ብለን የምንጮኽበትን #የልጅነት #መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ እንደገና #ለፍርሀት #የባርነትን #መንፈስ አልተቀበላችሁምና›› ይላል (ቊጥር 15)፡፡ በመቀጠል ልጆች ከሆንን ደግሞ ወራሾች ነን ይልና ‹‹ #ዐብረንም ደግሞ እንድንከበር ዐብረን #መከራ ብንቀበል #ከክርስቶስ ጋር አብረን #ወራሾች ነን›› የሚል ሐሳብ ያቀርባል፡፡ ነገር ግን #መከራው #ልንወርሰው ካለው ክብር ጋር ሲመዛዘን ‹‹ምንም እንዳይደለ አስባለሁ››፡፡ ይህ ግን ለእኛ ብቻ ሳይሆን ለፍጥረት በሙሉ በመሆኑ ‹‹ #የፍጥረት ናፍቆት የእግዚአብሔርን ልጆች #መገለጥ›› በመቃተት በተስፋ እየተጠባበቀ መሆኑን ይገልጻል፡፡ በመቃተት ላይ ያለው ግን #ፍጥረት ብቻ ሳይሆን እኛም ጭምር መሆናችንን ያስቀምጥና ‹‹ #እንዲሁም ደግሞ #መንፈስ #ድካማችንን ያግዛል፤ እንዴት #እንድንጸልይ እንደሚገባን አናውቅምና÷ ነገር ግን #መንፈስ ራሱ በማይነገር መቃተት #ይማልድልናል›› ይላል፡፡ ምክንያቱንም ‹‹ #ልብንም የሚመረምረው #የመንፈስ ዐሳብ ምን እንደ ሆነ ያውቃል÷ እንደ #እግዚአብሔር ፈቃድ ስለ #ቅዱሳን #ይማልዳልና›› በማለት ያስቀምጣል፡፡ ከዚህ ቡኋላ ቀደም ሲል ያቀረበውን በዚህ ምድር የሚያገኘንን #መከራ መነሻ በማድረግ ‹‹ #እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ #አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ #ለበጎ #እንዲደረግ እናውቃለን›› በማለት ይጀምርና #እግዚአብሔር #አስቀድሞ እንደ #ወሰነን፣ እንደ #ጠራን#እንዳጸደቀን እና #እንዳከበረን አስፍሮ ‹‹ #እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ ማን #ይቃወመናል?›› የሚል ጥያቄ ያነሣል፡፡ እንግዲህ ከዚህ ሁሉ በኋላ ነው ‹‹ #እግዚአብሔር የመረጣቸውን ማን #ይከሳቸዋል? #የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው÷ #የሚኰንንስ ማን ነው?›› የሚለውን ጥያቄ በማንሣት #የኰናኙን ማንነት ለማሳየት ጥረት የሚያደርገው፡፡ ለዚህ ጥያቄ መልስ ለመስጠት #ኰናኙ
▶️ "የሞተ"
(ሞቱ አንድ ጊዜ ብቻ የሆነ ወደፊት የማይደገም በመሆኑ በኃላፊ ጊዜ ነው የተቀመጠው)፣

▶️ "ከሙታንም የተነሣ"
(ትንሣኤውም ቢሆን ሞትን ድል አድርጎ በተነሣበት ጊዜ ብቻ የሆነ አንድ ክንውን ነውና የተነሣ አለው)፣

▶️ "በእግዚአብሔር ቀኝ ያለ"
(በእግዚአብሔር ቀኝ መሆኑ ስለ ሰው ልጆች ሊታይ ነው(ዕብ 9፥24)፡፡ ይሄውም የምልጃ ሥራው አካል ነውና አሁንም ስለ እኛ በእግዚአብሔር ቀኝ አለ፡፡ ስለዚህ ነው ሐዋርያው በእግዚአብሔር ቀኝ ነበረ ሳይሆን አለ ያለው)፣

▶️ "ስለ እኛ የሚማልድ" (የክርስቶስ ምልጃ ምንም እንኳ አንድ ጊዜ በመስቀል ላይ በተሠራው ሥራ የተፈጸመ ስለ ሆነ የማይደጋገም ቢሆንም፣ ቀደም ሲል እንደ ተባለው አሁንም ስለ እኛ በመታየት ይቅርታን እንድናገኝ ያደርጋልና ሐዋርያው ስለ እኛ የሚማልድ በማለት አሁንም አማላጃችን መሆኑን ተናገረ።) በማለት ስለ እኛ #የሚማልድ መሆኑን በማሳየት በዚህ ምድር ላይ ያለውን #መከራ #ማሸነፍ የሚቻልበትን #ማበረታቻ ይሰጣል፡፡ ይህ ምንባብ #እግዚአብሔር #የመረጣቸውን #የሚከሳቸው #ማን ነው? ለሚለው #ጥያቄ #ማንም የሚል ምላሽ የሚሰጥ ሲሆን ማንም #ሊከሳቸው የማይችልበት #ምክንያት ደግሞ ስለ #እነርሱ #ሞቶ የነበረ #ሞትን #ድል አድርጎ #የተነሣው እና #በአብ ቀኝ ሆኖ #የሚያማልድላቸው #ስላለ ነው በሚል ነው የሚያስቀምጠው፡፡ #ሐዋርያው ቀደም ሲል #በክርስቶስ #ኢየሱስ ላሉት #አሁን #ኵነኔ የለባቸውም ማለቱን ማስታወሱም #ጠቃሚ ነው (ቊጥር 1)።
@ ( #ጳውሎስ "ስለ እኛ የሚማልደው" በማለት እርሱም #በክርስቶስ ኢየሱስ #የምልጃ ስራ ተጠቃሚ መሆኑን ይናገራል። አንዳንዶች #ሐዋሪያው #ጳውሎስን ጨምሮ በርካታ ሰዎችን #በምልጃ ስራ ውስጥ አሰልፈው #የክርስቶስን የምልጃ ስራ ፊት ለፊት በመቃወም ላይ ናቸው። #ሐዋሪያው በዚህ ክፍል ላይ እርሱ #አማላጅ ስለመሆኑ ሳይሆን #ስለ ኢየሱስ #አማላጅነት እና እርሱም #በኢየሱስ #ምልጃ ተጠቃሚ ስለ መሆኑ ነው የሚያስተምረው። #መጽሀፉ እንደሚለው ደግሞ #ኢየሱስ የእኛ ብቻ ሳይሆን #የቅዱስ ጳውሎስም #አማላጅ ነው። ስለ ሌሎች #ያማልዳል የሚባለው #ጳውሎስ #በክርስቶስ ምልጃ ተጠቃሚ እንደሆነ የገለጸውን መመልከት ሁላችንም #አማላጅ #እርሱ ብቻ ወደ ሆነው ወደ #ክርስቶስ እንድንጠጋ ያበረታታል።)

#በመቀጠልም ስለ እኛ #ከሞተው#ሞትን ድል አድርጎ #ከተነሣው#በእግዚአብሔር ቀኝ ካለው እና #ስለ እኛ #ከሚያማልደው ‹‹ #ከክርስቶስ #ፍቅር ማን ይለየናል? #መከራ÷ ወይስ #ጭንቀት÷ ወይስ #ስደት÷ ወይስ #ራብ÷ ወይስ #ራቁትነት÷ ወይስ #ፍርሀት÷ ወይስ #ሰይፍ ነውን?›› ሲል ይጠይቃል፡፡ በእርግጥም ከዚህ #ጌታ ምንም የሚለየን የለም፡፡ ‹‹ #ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ #እንገደላለን÷ #እንደሚታረዱ #በጎች ተቈጠርን ተብሎ›› ተጽፏልና፡፡ ‹‹በዚህ ሁሉ ግን #በወደደን [በአማላጃችን] #በእርሱ #ከአሸናፊዎች እንበልጣለን፡፡ #ሞት ቢሆን÷ #ሕይወትም ቢሆን÷ #መላእክትም ቢሆኑ÷ #ግዛትም ቢሆን÷ #ያለውም ቢሆን÷ #የሚመጣውም ቢሆን÷ #ኀይላትም ቢሆኑ÷ #ከፍታም ቢሆን÷ #ዝቅታም ቢሆን÷ #ልዩ ፍጥረትም ቢሆን #በክርስቶስ ኢየሱስ #በጌታችን ካለ #ከእግዚአብሔር #ፍቅር ሊለየን #እንዳይችል ተረድቼአለሁ›› በማለት #ምዕራፉ ያበቃል፡፡ #በዚህ ምዕራፍ ውስጥ #አሁን #ኵነኔ #የለብንም በማለት የጀመረው #ሐዋርያው #ክርስቲያኖች ስለሚያጋጥማቸው ነገር #እየመከረና #እያበረታታ ሁሉን #በጽናት #ማሸነፍ እንዳለባቸው ሲናገር፣ ‹‹ #እግዚአብሔር #የመረጣቸውን ማን #ይከሳቸዋል? #የሚያጸድቅ #እግዚአብሔር ነው÷ #የሚኰንንስ ማን ነው?›› ለሚሉት #ጥያቄዎች መልስ ለመስጠት ‹‹ #ስለ እኛ የሚማልደው #ክርስቶስ #ኢየሱስ›› መሆኑን ነገረን፡፡ ለዚህስ ሳይሆን ይቀራል #በአንድምታው ላይ ‹‹ #እሱ #ቢያጸድቅ ማን #ይኰንነናል፡፡ #ኢየሱስ ክርስቶስ #ሞተ #ከሙታንም #ተለይቶ #ተነሣ፡፡ #በአብ #ዕሪና(እኩል፣ መተካከል) #ይኖራል ስለ እኛ #ይከራከራል፡፡ #መከራከርስ የለም #ስለ እኛ #በዕለተ #ዐርብ #ባደረገው #ተልእኮ ፍጹም #ዋጋችንን #የምናገኝ ስለ ሆነ›› እንደ ሆነ የሰፈረው????
📖/፤ ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፣ የቅዱስ ጳውሎስ መጽሀፍ ንባቡና ትርጓሜው (አ.አ፣ ግንቦት 1988) ገጽ 70።
📖/፤ መሐሪ ትርፌ (ሊቀ ሊቃውንት)፣ የቅዱስ ጳውሎስ መጽሀፍ ንባቡ ከነትርጓሜው (አ.አ፤ ጥቅምት 23 1948) ገጽ 100።

#እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል/ዩሀ 8፥32/

ይቀጥላል..(ሮሜ 8፥34)
@gedlatnadersanat @teeod
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
ሮሜ 8÷34 " #የሞተው÷ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው÷ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው÷ ደግሞ ስለ እኛ #የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፡፡" #ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ መልእክቱ ማስተላልፍ የፈለገው ‹‹ #እንግዲህ #በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን #ኵነኔ የለባቸውም›› የሚለውን ነው (ቊጥር 1)፡፡ ሐዋርያው በመቀጠል ‹‹ #በክርስቶስ ኢየሱስ ያለው #የሕይወት መንፈስ ሕግ #ከኀጢአትና…


ስለዚህም ክፍሉን ስናየው እግዚአብሔር #የመረጣቸውን ማን #ይከሳቸዋል? ብሎ ጠየቀ ።ምን ብሎ
መለሰ? << #የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው>>ብሎ ነው የመለሰው ።ይህ ማለት
ከሳሹ ማነው? #እግዚአብሔር ነው ማለት አይደለም ።ምክንያቱም #እግዚአብሔር #የመረጣቸውን ራሱ #አይከሳቸውምና በተመሳሳይም
<< #የሚኮንንስ ማነው?
>ብሎ ጠየቀ ምን ብሎ መለሰ? የሞተው ይልቁንም #ከሙታን የተነሣው #በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው ደግሞ #ስለ እኛ #የሚማልደው #ክርስቶስ #ኢየሱስ ነው
ብሎ ነው የመለሰው ።
<< #የሚኮንንስ ማነው?>>
የምትለዋን ጥያቄ ስንመለከት #የሚኮንን ከምትለው ቀጥሎ <#ስ> ፊደል
መግባቷ አንድን ነገር በተመለከተ #በዚያው ጉዳይ ላይ #በድጋሜ የተጠየቀ መሆኑን ያመለክታል። #የእግዚአብሔርን #ምርጦች በተመለከተ " #ማን #ይከሳቸዋል?"ብሎ ጠይቆ ነበርና "" #የሚኮንንስ #ማነው"" ብሎ #በድጋሜ ይጠይቃል ።ይህ ማለት #እግዚአብሔር #የመረጣቸውን #ማን #ይከሳቸዋል?
#እግዚአብሔር #የመረጣቸውን #ማን #ይኮንናቸዋል?ማለት ነው ወይም ደግሞ
<< #እግዚአብሔር የመረጣቸውን ማን #ይከሳቸዋል ? #የሚኮንናቸውስ ማነው?
>>ማለት ነው።
ወይም
<< #የእግዚአብሔርን ምርጦች ማን #ይከሳቸዋል?
ማንስ #ይኮንናቸዋል? >>ማለት ነው ።
ለምሳሌ ፦
<< #የአስቴር እኅት #ስሟ #ማነው? #የእናቷስ?>>
ብየ ብጠይቅ ምን እያልኩ ነው? < #የአስቴር እኅት ስሟ ማነው? #የእስቴር እናት ስሟ #ማነው?> ማለት ነው ።
< #ስ> ፊደል አስቴርን በተመለከተ #በድጋሜ #የተጠየቀ መሆኑን ያመለክታል ።

ስለዚህ #እግዚአብሔር #የመረጣቸውን ማን #ይከሳቸዋል ብሎ ጠይቆ #የሚኮንንስ
#ማነው? ማለቱ የእግዚአብሔርን ምርጦች #የሚኮንናቸው ማነው? ማለቱ ነው።
ደግሜ ልበለው
"< #እግዚአብሔር #የመረጣቸውን ማን #ይከሳቸዋል? ማንስ
#ይኮንናቸዋል?> ማለት ነው ።


እስኪ #በ1938 ዕትም የተጻፈውን ቃል ተመልከቱ ፦
<<እግዚአብሔር የመረጣቸውን ሰዎች የሚነቅላቸው ማነው #እሱ #ካጸደቀ ማነው #የሚኮንን? >>
ይላል ።እንግዲህ ተመልከቱ ፦ ።<<እሱ #ካጸደቀ ማነው #የሚኮንን?>>የሚለውን
በደንብ አስምሩበት ።
አንድምታ ተርጓሚዎችም ፦
<< #ለእመ ለሊሁ #ያጸድቅ #መኑ #ዘይኮንን ፤ " #እሱ #ቢያጸድቅ #ማን #ይኮንናል?>> ብለውታል።
#እግዚአብሔር #ያጸደቀውን ማን #ይኮንናል? ማለት እንደሆነ
ልትረዱ ይገባል። #የሚኮንንስ ማነው የሚለው #ጥያቄ #እግዚአብሔር #መርጦ
#ያጸደቃቸውን ማን #ይኮንናቸዋል ማለት ነው ።ይህን አስቡበት!!

" #ቅዱስ #ዮሐንስ #አፈወርቅም" ሲተረጉም እንዲህ ብሏል ፦
<< #እግዚአብሔር #ዘውዱን #አቀዳጅቶናል #የሚኮንነን #ማነው? #ክርስቶስ
#ሞቶልናልና #መሞት ብቻ አይደለም #ከዚህም በኋላ #ስለ #እኛ #ስለሚማልድ #ማን #ይኮንነናል>
በማለት ተርጉሞታል።
📖/፤ ሐመር መጽሔት ሐምሌ 2007፥ ገጽ10።

#እንግዲህ #ቃሉን እንዴት እንደተገነዘቡት አስተውሉ!! ክርስቶስ
#ሞቶልናልና ማነው #የሚኮንነን? ክርስቶስ #ይማልድልናልና ማነው #የሚኮንነን?
በማለት ነው ያብራራው።
በእርግጥም #መሠረታዊ #ሐሳቡ ይህ ነበር ።
-----
@gedlatnadersanat
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
ስለዚህም ክፍሉን ስናየው እግዚአብሔር #የመረጣቸውን ማን #ይከሳቸዋል? ብሎ ጠየቀ ።ምን ብሎ መለሰ? << #የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው>>ብሎ ነው የመለሰው ።ይህ ማለት ከሳሹ ማነው? #እግዚአብሔር ነው ማለት አይደለም ።ምክንያቱም #እግዚአብሔር #የመረጣቸውን ራሱ #አይከሳቸውምና በተመሳሳይም << #የሚኮንንስ ማነው? >ብሎ ጠየቀ ምን ብሎ መለሰ? የሞተው ይልቁንም #ከሙታን የተነሣው #በእግዚአብሔር…
<< #እግዚአብሔር የመረጣቸውን #የሚከሳቸው ማነው? #የሚያጸድቅ #እግዚአብሔር
ነው>> ሮሜ8:33 አለ።

< #የሚያጸድቅ #እግዚአብሔር ነው>> አለ። #እግዚአብሔር #የሚያጸድቀው #እነማንን
ነው? አግዚአብሔር #የሚያጸድቀው እሱ #የመረጣቸውን ነው።
እሱ < #የጠራቸውን እነዚህን #አጸደቃቸው> ሮሜ8:30 እግዚአብሔር #የመረጣቸውን እሱ ራሱ #የሚያጸድቃቸው ከሆነ እንግዲህ በእነዚህ ምርጦች ላይ ክስ ማንሳት የሚችል
ማነው? #ማንም ሊኖር አይችልም
#እግዚአብሔር የመረጣቸውን ማንም #ሊከሳቸው አይችልም ለምን? ምክንያቱም #እግዚአብሔር #አምላካችን
#የመረጣቸውን #ምርጦቹን #የሚያጸድቅ አምላክ ነውና።
#እርሱ የመረጣቸውን
#ያጸድቃል ።እርሱ መርጦ #ያጸደቃቸውን ማን #ይከሳቸዋል?
<የጠራቸውን እነዚህን አጸደቃቸው> ተብሎ ተጽፏል። እርሱ እንዲህ አድርጎ ያጸደቀውን ማን
#ሊከስ ይችላል? ማንም #ሊከሳቸው አይችልም ።
---
<< #የሚኮንንስ ማነው? #የሞተው ይልቁን ከሙታን የተነሣው #በእግዚአብሔር ቀኝ
ያለው ደግሞም ስለ እኛ #የሚማልደው #ክርስቶስ #ኢየሱስ ነው >>
ከላይ እንዳየነው #ዮሐንስ አፈወርቅ እንደገለጸው
<< #እግዚአብሔር ዘውዱን
አቀዳጅቶናል ማን #ይኮንነናል? #ክርስቶስ ስለሞተልን ደግሞም ከዚህ በኋላ
#ስለሚማልድልን ማን #ይኮንነናል>> ባለበት አገላለጽ ስንመለከተው
#እግዚአብሔር #የመረጣቸውን #ያጸድቃቸዋል ፣ታዲያ እርሱ መርጦ #ያጸደቃቸውን
#የሚከሳቸው ማነው? #የሚኮንናቸውስ ማነው? ማንም #ሊኮንናቸው አይችልም።
እግዚአብሔር #የመረጣቸውን #የሚኮንናቸውስ ማነው? ማንም።
እግዚአብሔር #ምርጦቹን #የመረጣቸው በክርስቶስ ነው ።
<< #ቅዱስና #ነውር የሌለን #በፍቅር እንሆን ዘንድ #በክርስቶስ ኢየሱስ
#መረጠን>>ኤፌ1:4
-
ይላል።
ታዲያ እነዚህ የእግዚአብሔር ምርጦች #በክርስቶስ ናቸው።
#በክርስቶስ #ኢየሱስ ላሉት ደግሞ #ኩነኔ የለባቸዎም << #በክርስቶስ #ኢየሱስ #ላሉት አሁን #ኩነኔ የለባቸውም >>ሮሜ8:1
#በክርስቶስ #ኢየሱስ የሆኑት እነዚህ የእግዚአብሔር ምርጦች አሁን #ኩነኔ #የለባቸውም#ኩነኔ #የሌለባቸውን እነዚህን ምርጦች ማን #ይኮንናቸዋል? ማንም
#ሊኮንናቸው አይችልም።
ለምን? ምክንያቱም ለእነርሱ ሲል #የሞተ አለ ፣ለእነርሱ
ሲል #ከሞት የተነሳ አለ ፣ለእነርሱ ሲል #በእግዚአብሔር ቀኝ #የተቀመጠ አለ
፣ ለእነርሱ ሲል #የሚማልድ #ሊቀ #ካህናት አለ እርሱም #ክርስቶስ #ኢየሱስ ነው።
የእግዚአብሔር ምርጦች #ከኩነኔ #ነጻ የመሆናቸው #ማረጋገጫ በክርስቶስ ሞት
#ትንሣኤ#እርገት እና #ምልጃ ነው ።
#እግዚአብሔር #የመረጣቸውን ማን #ይኮንናቸዋል? ማንም #አይኮንናቸውም
ምክንያቱም ለእነርሱ ሲል #የሞተ አለ እርሱም #ክርስቶስ ነው።
#ክርስቶስ #ለምርጦቹ ሲል በደላቸውን ተሸክሞ በእንጨት ላይ #ሞቷል#በበደላቸው
የሚመጣባቸው #ፍርድ እሱ #ተሸክሟል #ፍርዱም #በሞቱ ተፈጽሟል ፣ታዲያ
#ክርስቶስ #ኢየሱስ የሞተላቸውን እነዚህን ምርጦች ማነው #የሚኮንን?
ከእግዚአብሔር ጋር በክርስቶስ #ሞት #ታርቀዋል /ሮሜ5:8/
ታዲያ ማነው #የሚኮንናቸው? ስለእነርሱ #መሞት ብቻ አይደለም ይልቁንም ስለ እነርሱ #ከሞት #ተነሥቷል ፣ለምን #ከሞት ተነሣ? ።
< #እኛን #ስለማጽደቅ #ከሙታን #ተነሣ> /ሮሜ4:24/
ተብሏል።
#ከሞቱ በበለጠ #ትንሣኤው #ከኩነኔ #ለመዳናቸው ትልቅ ዋስትናቸው ነው። እነርሱን #ለማጽደቅ ከሞት #ተነስቷል #በትንሣኤውም #ጸድቀዋል ፣በክርስቶስ
#ትንሣኤ #የጸደቁትን እነዚህን የእግዚአብሔር ምርጦች #ማን #ይኮንናቸዋል?
እነዚህ ምርጦች #ከእግዚአብሔር ጋር #በልጁ #በክርስቶስ #ሞት #ታርቀዋል
ይልቁንም #ከሞት #ተነስቶ ሕያው ሆኖ በመኖሩ በህይወቱ ደግሞ ይድናሉ ፦
< #ከእግዚአብሔር ጋር #በልጁ ሞት #ከታረቅን #ይልቁንም ከታረቅን በኋላ #በሕይወቱ #እንድናለን> /ሮሜ5:11/
#ክርስቶስ ባይነሳ ኖሮ #ጽድቃቸው አይረጋገጥም
ነበረ ኃጢአተኛ ሆነው ይቀሩ ነበር << #ክርስቶስ #ካልተነሣ እምነታችሁ ከንቱ ናት
እስከ አሁን ድረሰ #በኃጢአታችሁ #አላችሁ>> /1ኛቆሮ15:17/ #በክርስቶስ ትንሣኤ
ዘለለማዊ #ጽድቅ አግኝተዋል።
#እግዚአብሔር #በልጁ #ትንሣኤ #ያጸደቃቸውን
ምርጦቹን ማን #ይኮንናቸዋል? ማንም። ስለዚህ #የክርስቶስ #ትንሣኤ #ከኩነኔ #የሚድኑበት ማረጋገጫቸው ሆኗልና የእግዚአብሔርን ምርጦች ማንም
#አይኮንናቸውም
#ይህም ብቻ አይደለም #ክርስቶስ ወደ #ሰማይ አርጎ
#በእግዚአብሔር ቀኝ መቀመጡም ታላቅ የደኅንነት #ማረጋገጫቸው ነው።
#ክርስቶስ ወደ ሰማይ የወጣው #የሰዎችን ሥጋ #እንደያዘ ነው።
<< #ወደላይ
#በወጣህ ጊዜ ምርኮን ማረክህ>> /ኤፌ4:7/ እንደተባለ ክርስቶስ #በኃጢአት #በሕግ
#በሞት #በሰይጣን እንዲሁም ከማንኛውም ጠላት ሥር የነበረውን #የሰውን ሥጋ
ከጠላት ማርኮ በድል አድራጊነት ይዞት #በሰማያዊ ሥፍራ #በቀኙ ሥጋችንን #ሲያስቀምጠው በእርሱ #በኩል ከሞት በላይ መሆናችን ማንም ዝቅ ሊያደርገው
#በማይችል ከፍታ ላይ #መሆናችን ሲታወቅ በእርግጥም በእንዲህ አይነት ከፍታ
#ከፍ ያደረጋቸውን የእግዚአብሔር ምርጦች ማንም #ሊኮንናቸው አይችልም።
<< #ከክርስቶስ ጋር አስነሳን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ #ስፍራ ከእርሱ ጋር
#አስቀመጠን >> /ኤፌ2:7/ለው
ያለውም ይህን ነው ።
#ስለ እነርሱም በእግዚአብሔር ፊት #ይታይላቸው ዘንድ
ወደ ሰማይ #ገብቷልና #ማንም #ይኮንናቸው ዘንድ አይችልም
/ዕብ9:24/

እግዚአብሔር መርጦ #ያጸደቀንን ማን #ይከሰናል? #ክርስቶስ #ለኃጢአታችን
#የሞተልንን ማን #ይኮንነናል? #ክርስቶስ እኛን #ለማጽደቅ ከሞት ተነስቷል ታዲያ
ማን #ይኮንነናል? ስለ እኛ በእግዚአብሔር ፊት #ይታይ ዘንድ ወደ ሰማይ
ገብቷልና ማን #ይኮንነናል? ክርስቶስ #ስለ እኛ #ይማልዳልና ማን ይኮንነናል?

አሜን ሃሌ ሉያ። ማንም

የክፍሉ ዓብይ ሀሳብ ይህ ነው። ይህንን ከተረዳን። ነገ ደግሞ ስለዚህ ጥቅስ የተነሱትንና የተባሉትን የተለያዩ ኑፋቄዎች እንመለከታለን።

#እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል/ዩሀ 8፥32/

ይቀጥላል..(ሮሜ 8፥34)
@gedlatnadersanat @teeod
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
<< #እግዚአብሔር የመረጣቸውን #የሚከሳቸው ማነው? #የሚያጸድቅ #እግዚአብሔር ነው>> ሮሜ8:33 አለ። < #የሚያጸድቅ #እግዚአብሔር ነው>> አለ። #እግዚአብሔር #የሚያጸድቀው #እነማንን ነው? አግዚአብሔር #የሚያጸድቀው እሱ #የመረጣቸውን ነው። እሱ < #የጠራቸውን እነዚህን #አጸደቃቸው> ሮሜ8:30 እግዚአብሔር #የመረጣቸውን እሱ ራሱ #የሚያጸድቃቸው ከሆነ እንግዲህ በእነዚህ ምርጦች ላይ ክስ ማንሳት…
🔽▶️

*⃣ #ሮሜ 8፥34 እና #የመናፍቃኑ እርስ በእርስ አለመግባባት፦

‹‹ #የሞተው፥ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው፥ #በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፥ ደግሞ ስለ እኛ #የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው›› (ሮሜ 8፡34)፡፡

#በልማድ ለያዙት #የተሳሳተ ትምህርት አልመች ያለውና #በምንፍቅና #ጎዳና ላይ ሆነው #የአዳኛችንን #የኢየሱስ ክርስቶስ #የማዳን ግብር የሆነው #የምልጃ ሥራውን ሽምጥጥ አድርገው #በመካድ ላሉት #ሰዎች ይህ #ጥቅስ #ራስ ምታት ሆኖባቸው ይታያል፡፡ ከዚህም የተነሳ #ቤተክርስቲያኗ ይህን ጥቅስ " #የሚፈርድ ማን ነው? የሞተው፥ ይልቁንም #ከሙታን ተለይቶ የተነሳው፥ በእግዚአብሄር ቀኝ የተቀመጠው፥ ደግሞም " #ስለእኛ #የሚፈርደው" ኢየሱስ ክርስቶስ ነው" በሚል አስቀምጣዋለች።
📖 2000 እትም 80 አሀዱ መጽሀፍ ቅዱስ
ለዚህም ደግሞ እንደ #ምክንያት የቀረበው " #የሚማልደው የሚለው ከጊዜ ቡሀላ #መናፍቃን #የጨመሩት ነው እንጂ ቀደም ሲል የነበረው #የግእዙ ትርጉም #የሚፈርደው ነው የሚለው" የሚል ነው።" ይህንንም ተከትሎ ብዙዎች የተለያዩ #ምክንያቶችንና ማስተባበያዎችን ለማቅረብ ሞክረዋል። እስኪ #ከብዙዎች አንዳንዶቹን እንያቸው፤

〽️1፦ ‹‹የጠራው #የግእዙ #የመጽሐፍ ቅዱስ #ኀይለ ቃል ተለውጦና #በዘመናት ሁሉ ለዚህች #ቤተ ክርስቲያን መቼም ቢሆን #መልካም ዐስበው በማያውቁ ይልቁንም #ፈራርሳ #ቢያይዋት ደስ በሚሰኙ #የክርስቶስን #ፈራጅነት በካዱ #በባሕር ማዶ #ቀሣጪዎች ብዙ ጊዜ #ተሰርዞ #ተቀይሮ ይገኛል›› የሚል #አስተያየት ይሰጣሉ። ለዚህም #በ1938 በፊላደልፊያ የታተመው #መጽሀፍ ቅዱስ፣ #በ1975 #በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ጊዜ " #ከግእዝ ወደ ዐማርኛ" የተመለሰው ዐዲስ ኪዳን(በግዕዝና በአማርኛ የታተመውን)፣ #በ1953 #በአሥመራ የታተመው ዐዲስ ኪዳን እና #በ1938 የታተመው #የዐማርኛ #ዐዲስ ኪዳን #መጻህፍትን ይጠቅሳሉ።
📖/፤ ሮዳስ ታደሰ (መጋቤ ዐዲስ)፣ ነገረ ክርስቶስ - ክፍል አንድ (የካቲት 2008)፤ ገጽ 479
📖/፤በርሀ ተስፋ መስቀል (መምህር)፣ "አንባቢው ያስተውል" (መቕለ፣2005) ገጽ 33 የግርጌ ማስተወሻ።
📖/፤ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምዕመናን የቅዱስ እስጢፋኖስ ጉባኤ፤ ፍኖተ ብርሃን(ጥቅምት 1990) ገጽ 51።
( #ደስታ ተክለ ወልድ፤ ዐዲስ ያማርኛ መዝገበ ቃላት
"ቀሠጠ"፦ #በስውር ከፍሎ ሰረቀ፣ #ወሰደ#ዐበለ
"ቀሣጢ"፦ #የቀሠጠ#የሚቀሥጥ ዐባይ #ሌባ፤ ብሎ ያስቀምጠዋል(ገጽ 1093)። በዚህ ትርጉም መሰረት ጸሀፊው " #ቀሣጢዎች" ሲሉ " #የሰውን ነገር #የሚወስድ#የሚሰርቅ#ሌባ ለማለት መሆኑን ልብ ይሏል።)

▶️ #በዚህ ጽሑፍ መሠረት " #ይማልዳል የሚለው #መናፍቃን #የጨመሩት እንጂ ትክክለኛ #ትርጉም አይደለም፡፡" ነገር ግን ጸሐፊው ማስተዋል የተሣናቸው #ሐዋርያው #ግእዝ #የጽሑፍ ቋንቋ ባልነበረበት ዘመን ይህን #መልእክት #ለሮሜ ሰዎች #የላከ መሆኑን ነው፡፡ ሐሳቡን #ግልጽ ለማድረግ ይህ #መልእክት #ወደ ሮሜ ሰዎች ሲላክ #ግእዝ ለጽሑፍ #የማይመችና #አናባቢ የሌለው #ቋንቋ ነበር፡፡ በዚህም #ምክንያት #ግእዝ #የሮሜን #መልእክት ለማስተናገድ #አቅም #አልነበረውምና #በግእዝ የተጻፈውን #ምንጭ ማድረግ #የተበከለ #ምንጭ እንደ #መጠጣት ይሆናል፡፡ ስለዚህ ማንም ብልህ አንባቢ #ቀዳሚውን #ምንጭ መፈለግ ግድ ይለዋል።
ግሪኩ እንዲህ ይላል..

τίς ὁ κατακρινῶν ? Χριστὸς Ἰησοῦς ὁ ἀποθανών , μᾶλλον δὲ ἐγερθείς (ἐκ νεκρῶν) ὅς ‹καί› ἐστιν ἐν δεξι το Θεο ὃς καὶ #ἐντυγχάνει(ኢንቲጋኬኖ) ὑπὲρ ἡμῶν /ሮሜ 8፥34/

*⃣" #entugchanó"፦
to chance upon, by impl. confer with, by ext. entreat
Original Word፦
#ἐντυγχάνω
Part of Speech፦
#Verb
Transliteration: #entugchanó
Phonetic Spelling፦
( #en-toong-khan'-o)
Short Definition፦
I meet, encounter, call upon, to chance upon, confer with, to #entract(in favor or against), deal with, make a #petition, make #intercession
📖/፤ STRONGS GREEK DICTIONARY OF THE NEW TESTAMENT፤ pg 29. No.1793)

👉 http://biblehub.com/greek/5241.htm

👉 https://www.biblestudytools.com/lexicons/greek/nas/entugchano.html

ከተለያዩ የግሪክ ቅጂዎችም ስናይ፦ 👇
http://biblehub.com/texts/romans/8-34.htm

Nestle Greek New Testament 1904

τίς ὁ κατακρινῶν; Χριστὸς Ἰησοῦς ὁ ἀποθανών, μᾶλλον δὲ ἐγερθείς, ὅς ἐστιν ἐν δεξιᾷ τοῦ Θεοῦ, ὃς καὶ #ἐντυγχάνει ὑπὲρ ἡμῶν.

Westcott and Hort 1881

τίς ὁ κατακρινῶν; Χριστὸς Ἰησοῦς ὁ ἀποθανών, μᾶλλον δὲ ἐγερθεὶς ἐκ νεκρῶν, ὅς ἐστιν ἐν δεξιᾷ τοῦ θεοῦ, ὃς καὶ #ἐντυγχάνει ὑπὲρ ἡμῶν·

Westcott and Hort / [NA27 variants]

τίς ὁ κατακρινῶν; Χριστὸς Ἰησοῦς ὁ ἀποθανών, μᾶλλον δὲ ἐγερθεὶς (ἐκ νεκρῶν), ὅς [καί] ἐστιν ἐν δεξιᾷ τοῦ θεοῦ, ὃς καὶ #ἐντυγχάνει ὑπὲρ ἡμῶν·

RP Byzantine Majority Text 2005

τίς ὁ κατακρίνων; Χριστὸς ὁ ἀποθανών, μᾶλλον δὲ καὶ ἐγερθείς, ὃς καὶ ἔστιν ἐν δεξιᾷ τοῦ θεοῦ, ὃς καὶ #ἐντυγχάνει ὑπὲρ ἡμῶν.

Greek Orthodox Church 1904

τίς ὁ κατακρινῶν; Χριστὸς ὁ ἀποθανών, μᾶλλον δὲ καὶ ἐγερθείς, ὃς καὶ ἔστιν ἐν δεξιᾷ τοῦ Θεοῦ, ὃς καὶ #ἐντυγχάνει ὑπὲρ ἡμῶν.

Tischendorf 8th Edition

τίς ὁ κατακρινῶν; Χριστὸς Ἰησοῦς ὁ ἀποθανών, μᾶλλον δὲ ἐγερθείς, ὃς ἐστιν ἐν δεξιᾷ τοῦ θεοῦ, ὃς καὶ #ἐντυγχάνει ὑπὲρ ἡμῶν.

Scrivener's Textus Receptus 1894

τίς ὁ κατακρίνων; Χριστὸς ὁ ἀποθανών, μᾶλλον δὲ καὶ ἐγερθείς, ὃς καὶ ἔστιν ἐν δεξιᾷ τοῦ Θεοῦ, ὃς καὶ #ἐντυγχάνει ὑπὲρ ἡμῶν.

Stephanus Textus Receptus 1550

τίς ὁ κατακρινῶν Χριστὸς ὁ ἀποθανών μᾶλλον δὲ καί ἐγερθείς ὃς καὶ ἐστιν ἐν δεξιᾷ τοῦ θεοῦ ὃς καὶ #ἐντυγχάνει ὑπὲρ ἡμῶν.

@gedlatnadersanat
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
ዕብራውያን 7፤ 20-28 << እነርሱም ያለ #መሐላ #ካህናት ሆነዋልና፤ #እርሱ ግን። ጌታ። አንተ #እንደ #መልከ ጼዴቅ ሹመት #ለዘላለም #ካህን ነህ ብሎ #ማለ #አይጸጸትም ብሎ በተናገረለት #ከመሐላ ጋር #ካህን ሆኖአልና ያለ #መሐላ #ካህን እንዳልሆነ መጠን፥ እንዲሁ #ኢየሱስ #ለሚሻል #ኪዳን #ዋስ ሆኖአል። #እነርሱም እንዳይኖሩ #ሞት ስለ ከለከላቸው #ካህናት የሆኑት ብዙ ናቸው፤ #እርሱ…


ዕብራውያን 9፥15 እና 24

<<ስለዚህም የፊተኛው ኪዳን ሲጸና ሕግን የተላለፉትን የሚቤዥ ሞት ስለ ሆነ፥ የተጠሩት #የዘላለምን #ርስት #የተስፋ #ቃል እንዲቀበሉ እርሱ ፨የአዲስ ኪዳን #መካከለኛ፨ ነው። . . . ክርስቶስ በእጅ ወደ ተሰራች፥ የእውነተኛይቱ ምሳሌ ወደ ምትሆን #ቅድስት አልገባምና፥ ነገር ግን #በእግዚአብሔር #ፊት #ስለ #እኛ #አሁን #ይታይ ዘንድ ወደ እርስዋ ወደ #ሰማይ ገባ።>>


#ክርስቶስ ለምንድን ነው •የዐዲስ ኪዳን መካከለኛ• የሆነው? ለሚለው ጥያቄ መልስ የሚሰጠው ይሄኛው ክፍል <<የተጠሩት #የዘላለም #ርስት የተስፋ ቃል እንዲቀበሉ>> መሆኑን ያስረዳል። <በአሮንና በልጆቹ>፣ <በአብርሃምና በሙሴ>፣ <በዳዊትና በነቢያት> የተሠሩ #የመካከለኛነት #ሥራዎች ሁሉ #የዘላለምን #ርስት #ለማውረስ የሚሆን ምንም ዐይነት #ተስፋ የሌላቸው መሆኑ፣ #የክርስቶን #የመካከለኝነት ሥራ እንዴት #የላቀ እንደ ሆነ ያሳያል። እንዲህ ያለውን #የመካከለኛነት #ሥራ ከእርሱ #በፊት የሠራው የለም ከእርሱም #ቡኋላ ሊሠራው የሚችል #አይኖርም። በመሆኑም #ሰዎች ሁሉ #ተስፋቸው #ክርስቶስ ብቻ በመሆኑ የእርሱን #የመካከለኛነት #ሥራ በሙሉ #ደስታ #መቀበል ይገባቸዋል። #ኢየሱስ #በሰው እጅ ወዳልተሰራችው #እውነተኛይቱ #ቤተ #መቅደስ የገባው መጽሐፍ እንደሚለው <<ስለ እኛ #አሁን ይታይ ዘንድ>> ማለትም #የምልጃን #ሥራ ይሰራ ዘንድ ነው።

#ሐዋርያው የዐዲስ ኪዳን #መካከለኛ በሚል ክርስቶስን ሲጠራው #በሰው እና #በእግዚአብሄር #መካከል በመግባት ስለ ሠራው #የማዳን (የዕርቅ) #ሥራ ሆኖ ሳለ ይህን #እውነት #መዋጥ የተሳናቸው ሰዎች፦
ስለ <ሊቀ ካህናችን ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ከባሕርይ አባቱ ከአብ፣ ከራሱና ማኅየዊ (አዳኝ) ከሚሆን ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ያስታርቀን ዘንድ የባሪያውን መልክ ይዞ (የእኛን ባሕርይ ነሥቶ) #ትምክህታችን ከምትሆን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ ሰው ሆነ፤ አምላክ የሆነ ሰው ሰውም የሆነ አምላክ (መካከለኛ) ሆነ፤ በተዋሕዶ አንድ ባሕርይ የሆነ ሥግው ቃል (Incarnated word)፣ አምላክ ወሰብእ (አምላክም ሰውም) (መካከለኛ) ሆነ>

በሚል መካከለኛ ሲል አምላክነቱን እና ሰውነቱን ለማመልከት ነው የሚል መልእክት ያስተላልፋሉ[1]።

#ክርስቶስ ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ መሆኑ እውነት ነው። ይህም በነገረ ድነታችን ላይ ወሳኝ ቦታ አለው። ነገር ግን ይህ ምንባብ ክርስቶስ ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ ስለ መሆኑ የሚናገር ባለ መሆኑ ይህን ምንባብ መሠረት አድርጎ ሊቀርብ የሞከረው ማብራርያ የኢየሱስን መካከለኛነት ለመሸፈን ሆን ተብሎ የቀረበ መሆኑ ግልጽ ነው። ሐዋርያው፤ ፦

<<ይህም ለአሁኑ ጊዜ ምሳሌ ነው፥ እንደዚህም መባና መስዋዕት ይቀርባሉ፤ እነዚህም እስከ መታደስ ዘመን ድረስ የተደረጉ፥ ስለ ምግብና ስለ መጠጥም ስለ ልዩ ልዩ መታጠብም የሚሆኑ #የሥጋ #ሥርዓቶች #ብቻ #ናቸውና የሚያመልከውን #በህሊና #ፍጹም #ሊያደርጉት አይችሉም። ነገር ግን #ክርስቶስ ይመጣ ዘንድ ላለው መልካም ነገር #ሊቀ #ካህናት #ሆኖ፥ በምትበልጠውና በምትሻለው በእጆችም ባልተሠራች ማለት ለዚህ ፍጥረት ባልሆነች ድንኳን፥ #የዘላለምን #ቤዛነት አግኝቶ #አንድ #ጊዜ #ፈጽሞ ወደ #ቅድስት #በገዛ #ደሙ #ገባ እንጂ #በፍየሎችና #በጥጆች #ደም አይደለም። የኮርማዎችና የፍየሎች ደም በረከሱትም ላይ የተረጨ የጊደር አመድ ሥጋን ለማንጻት የሚቀድሱ ከሆኑ፥ ነውር የሌለው ሆኖ በዘላለም መንፈስ #ራሱን #ለእግዚአብሔር #ያቀረበ #የክርስቶስ #ደም እንዴት #ይልቅ ሕያውን እግዚአብሔርን ልታመልኩ ከሞተ ሥራ #ሕሊናችሁን #ያነጻ ይሆን?>> (ቁ. 9-14)

የሚለውን ካሰፈረ ቡኋላ < #ስለዚህም> በማለት 15ኛውን ቁጥር ይቀጥላል። ይህ ክፍል የሚያመለክተው ክርስቶስ በገዛ ደሙ እንጂ በፍየሎችና በበጎች ደም ዕርቅን ያመጣልን አለመሆኑን ነው። እነዚህ ስርአቶች የሥጋ ስርአቶች ብቻ ነበሩ ማለትም ኃጢአትን መሸፈን ነው እንጂ ማስወገድ አይችሉም። የሚያመልከውን በኅሊና ፍጹም ሊያደርጉት አይችሉም። ለዚህም ነው <ራሱን ለእግዚአብሄር ያቀረበ የክርስቶስ ደም እንዴት ከሞተ ሥራ ኅሊናችሁን ያነጻ ይሆን?> በማለት የሰፈረው። ይህም ክርስቶስ የዐዲስ ኪዳን መካከለኛ እንዲባል ምክንያት ሆኗል። ወደ ቅድስት በእግዚአብሄር ፊት ስለእኛ አሁን ይታይ ዘንድ በገዛ ደሙ ነውና የገባው።

የዕብራውያን መልእክት አንድምታም፦

< . . . . በተጨማሪም በየዓመቱ አንድ ጊዜ ከሚገቡት ከአሮናውያን ካህናት በተለየ ሁኔታ ክርስቶስ አንድ ጊዜ ፈጽሞ ወደ ሰማይ ገብቷል። ወደ ሰማይ የገባውም ቀድሞ የዘላለም ቤዛነትን ያስገኘላቸውን #በክህነት #አገልግሎቱ #ሊረዳቸው ነው[2]።>

#እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል/ዩሀ 8፥32/

ይቀጥላል..
@gedlatnadersanat @teeod

"ማጣቀሻ"
____________
[1] ሮዳስ ታደሰ (መጋቤ ዐዲስ)፣ <ነገረ ክርስቶስ> _ ክፍል 1 (የካቲት 2008) ገጽ 495።

[2] GBV፣ የዕብራውያን መልእክት አንድምታ (ትርጓሜው ከነንባቡ)፣ 1998 ገጽ 74
<<እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ...>> የሚለውን የተቀነባበረ <የጸሎት> ክፍል #በኢየሱስ ክርስቶስ #አስተምህሮ #ወቅት ብቻ ሳይሆን ከእሱ ቡሀላም ለብዙ #ዘመናት አልነበረም። ምናልባትም ሌሎች እንደሚሉት #ማርያም ገና #ክርስቶስን ሳትወልድ የነበረ #የገብርኤል #ሰላምታ ነው ተብሎ እንዳይወሰድ እንኳን #መልአኩ መጥቶ ያደረገው #ውይይት እንጂ #ጸሎት አይደለም። #ክርስቶስም #ለደቀመዛሙርቱ #ጸሎት ባስተማረበት #ወቅት #የገብርኤልንም #ሰላምታ ጨምሩበት በማለት ባስተላለፈ ነበር፤ ያንን ደግሞ አላደረገውም [ማቴ 6፤ 1-13፣ ሉቃ 11፤ 1-4]። << #በሰማያት የምትኖር #አባታችን ሆይ....>> የሚለው #የጸሎት #አስተምህሮቱን #ድንግል ማርያምን በትክክል በሚያውቋት #በደቀመዛሙርቱ ፊት ምናልባትም #በአስተምሮው #ወቅት ብዙ ጊዜ በምትገኝዋም #በድንግል #ማርያምም በራሷ ፊትም ተናግሯል።

▶️ ስለሆነም የተቀነባበረው <<የማርያም የጸሎት>> ምዕራፍ #በክርስቶስ #ወቅት ያልነበረ ከዚያም ቡኋላ #ሐዋሪያቱ #በአገልግሎታቸውና #በጸሎታቸውም ወቅት የማያውቁትና #የጥንት #ቤተ ክርስቲያን #አባቶችም በልዩ ልዩ ምክንያት #ጉባኤ ሲያደርጉ ለምሳሌ፦ #በኒቂያ ጉባኤ #በ325 ዓ.ም 318 የሃይማኖት አባቶች በእነ #እስክንድሮስ አፈጉባዔነት በንጉስ #ቆስጠንጢኖስ ዘመን ተሰብስበው #አርዮስን <<ወልድ #ፍጡር ነው>> ያለበትን #የክህደት ትምህርት #ሲያወግዙና #የሃይማኖት መግለጫ ሲያወጡ #ኢየሱስን ከመውለዷ ውጭ #ስለማርያም ፈጽሞ #መሠረታዊ #ትምህርት እንኳ በወቅቱ እንዳልነበረ መረዳት ይችላል። እንዲሁም #በቁስጥንጥንያ #በ375 ዓ.ም 150 #የሃይማኖት #አባቶች #በጢሞቴዎስ ዘአልቦጥሪት በንጉሥ ዘየዓቢ #ቴዎደስዩስ ወቅት #መቅደንዩስ << #መንፈስ ቅዱስ #ሕጹጽ ወይም #ሀይል ብቻ>> ብሎ በተነሳ ጊዜ ተሰብስበው #አውግዘው ትምህርቱንና እርሱን ሲለዩ #የቤተክርስቲያንን አጠቃላይ #የአስተምህሮ #መግለጫ ሲያወጡ ያኔም ቢሆን #ኢየሱስን #ከመውለዷ ውጪ #ስለማርያም ያስተላለፉት ምንም #አዲስ #ትምህርት የለም። #በኤፌሶን ሀገርም #በ435 ዓ.ም 200 #የሃይማኖት #አባቶች #በቄርሎስ አፈጉባዔነት በቴዎደስዩስ ዘይንእስ ንጉሥነት ጊዜ ንስጥሮስ << #ክርስቶስ #ሁለት #አካል #ሁለት #ባህሪይ ነው>> ብሎ ሲነሳ #እርሱንም #ትምህርቱንም #አውግዘው #የቤተክርስቲያንን አጠቃላይ #አስተምህሮ በመግለጫ መልክ ሲያስቀምጡ ድንግል #ማርያም #ክርስቶስን እንደወለደች ብቻ እንጂ << #እመቤታችን>> ብለውም ሆነ << #ለምኝልን>> የሚል አስተምህሮ አያውቁም። #ጤናማ #አስተምህሮ አይደለምና።

▶️ ዛሬ ሁሉም #አብያተክርስቲያናት የሚቀበሉት #ሙሉ #የሃይማኖት #መግለጫቸው

<<ሁሉን በያዘ ሰማይና ምድርን የሚታይና የማይታየውን በፈጠረ በአንድ አምላክ በእግዚአብሔር አብ እናምናለን። ዓለም ሳይፈጠር ከእርሱ ጋር በነበረ የአብ አንድ ልጁ በሚሆን በአንድ ጌታ በኢየሱስ ክርስቶስም እናምናለን። ከብርሃን የተገኘ ብርሃን የተፈጠረ ሳይሆን የተወለደ በመለኮቱ ከአብ ጋር የሚተካከል ሁሉ በእርሱ የሆነ ያለ እርሱ ግን ምን ምንም የሆነ የለም በሰማይም ያለ በምድርም ያለ ስለእኛ ስለ ሰዎች ስለመዳናችን ከሰማይ ወረደ ከቅድስት ድንግል ማርያም በመንፈስ ቅዱስ ግብር ፈጽሞ ሰው ሆኖ በጴንጤናዊ በጲላጦስ ዘመን ስለ እኛ ተሰቀለ ታመመ ሞተ ተቀበረም በሶስተኛውም ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሳ። በክብር ወደ ሰማይ ዐረገ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ ዳግመኛም በሕያዋንና ሙታንንም ይፈርድ ዘንድ በጌትነት ይመጣል ለመንግስቱም ፍጻሜ የለውም ጌታ ማህየዊ በሚሆን ከአብ በሰረጸ በመንፈስ ቅዱስም እናምናለን እንሰግድለት እናመሰግነውም ዘንድ ከአብና ከወልድ ጋር በነብያት የተነገረ ከሁሉ በላይ በምትሆን ሐዋሪያት በሰበሰባት በአንዲት ቤተክርስቲያን እናምናለን። ኃጢአትን ለማስተሰረይ በአንዲት ጥምቀት እናምናለን። የሙታንንም መነሳት ተስፋ እናደርጋለን የሚመጣውንም ሕይወት ለዘላለሙ አሜን።>> የሚል ነው።

ይህንንም መግለጫ #በ1530 ዓ.ም #ሉተራውያን << #የአውግስበርግ #መግለጫ>> በሚል አጸደቁ። እንዲሁም #በ1546 ዓ.ም #ካቶሊክ በድጋሜ << #የትሬንት #መግለጫ>> በማለት አጸደቀችው። #በ1571 ዓ.ም ደግሞ #የአንግሊካን #ቸርች መግለጫውን ተቀብላ አጸደቀችው። #በ1646 ዓ.ም #ፕሪስቢቴሪያን << #የዌስት #ሚኒስቴር #መግለጫ>> በሚል አጸደቀችው[1]።

▶️ ኦርቶዶክስ #ቤተክርስቲያን መግለጫውን በድጋሜ << #ጸሎተ #ሃይማኖት>> በማለት #በ1426-1460 ዓ.ም በኢትዮጵያ የነገሰው #አጼ #ዘርዓ ያዕቆብ ሙሉውን ተቀበሉና ሌላ #በመጨመር << #ለማርያምና #ለእፀ መስቀሉ (ለመስቀሉ እንጨት) #ስግደት ይገባቸዋል>> በማለት እንዲሁም <<እመቤታችን ...ሆይ>> የሚለውን <<ከአባታችን ሆይ>> #ቀጥሎ እንዲባል ብሎ #አዋጅ አወጣ። ከዚህም የተነሳ በርካታ #ካህናት << #አባቶቻችን ካስቀመጡት #ከሃይማኖት #መግለጫው ውጪ ተጨማሪውን #አንቀበልም>> በማለታቸው #በሰይፍ እንደቆራረጣቸውና እንዳሳደዳቸው #ገድለ #እስጢፋኖስ#ገድለ #አበው ወአኀው፣ #ገድለ #አባ አበከረዙል፣ #ገድለ #አባ ዕዝራ፣ #ገድለ #ደቂቀ እስጢፋኖስን ማንበብ #በቂ ነው።

▶️ ነገር ግን #በዘር #ቅብብሎሽ አማካኝነት የነበረው #የንግስና #ሥርአት ለዚህ <<አዳራሻውን ወደ ሳተው ጸሎት>> ሰፊ እድል አግኝቶ #ሰይፍ ያስፈራቸውና በክርስትናው #ትምህርት ብዙም #መሰረታዊ #እውቀት ያልነበራቸው #ህዝብና #ካህናት #የጸሎት #ምዕራፋቸው አድርገው ለቀጣዩ #ትውልድ በማስተላለፋቸው ይሀው አሁን የምናየውን #ከእግዚአብሄር #ቃል ውጪ የሆነ #ትውልድ ፈጥረውልናል። ዛሬ ዛሬ #በየጸሎቱ #መዛግብት ውስጥ እየተጨመረ ተጽፎ #ምዕመናን ሁሉ #በቀን ቢያንስ #አንድ ጊዜ እንዲደግመው በመደረጉ እንግዳው <<ጸሎት>> #የተለመደ ሆኖ ቀረ። እንዲያውም በዚህ #ዘመን አስቀድመን እንዳልነው <<እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ...>> የሚለውን #መጽሀፍ ቅዱሳዊ ለማስመሰል #ጥቅሶችን ያለቦታቸው እንደ #ስጋ #ዘንጥለውና #በጣጥሰው #መጽሀፍ ቅዱሳዊ ለማስመሰል የሚታገሉ ተነስተዋል። እኛ ግን <<የእግዚአብሔርን ቃል #ቀላቅለው #እንደሚሸቃቅጡት እንደ #ብዙዎቹ አይደለንምና፤ #በቅንነት ግን ከእግዚአብሔር እንደ #ተላክን #በእግዚአብሔር ፊት #በክርስቶስ ሆነን እንናገራለን።>> [2ቆሮ 2፥17]

✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆

"ማጣቀሻዎች - References"
_________
[1] 📚፤ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት መካነ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን፤ አውግስበርግ ሃይማኖታዊ መግለጫ፤ በአማርኛ የተተረጎመ፤ አ.አ፥ 1993 ዓ.ም።
▶️ በ1962 -1965 እ.ኤ.አ የ2ኛው #የካቶሊክ #የቫቲካን ጉባዔ <<ስለማርያም የሚሰጠው ትምህርት እውቅና እንዲያገኝና የማርያም ምስል ከፍ ተደርጎ እንዲያዝና እንዲሰገድለት ቅዱስ ተብሎም እንዲጠራ የአምልኮም መገልገያ እንዲሆን ወስነናል፤ ይህ የሲኖዶስ ውሳኔ ለቅድስት ማርያም ያለንን አክብሮት ለማሳየት ነው>> አለ[1]።

▶️ ይህን #የቫቲካን #ሲኖዶስን ጨምሮ ብዙ #ሰዎች #ምስልን ለመቀበል የወሰኑት <<ምስልን ማክበር ባለቤቱን ማክበር ነው>> በሚል #የተሳሳተ ሃሳብ ነው። አንዳንድ ጊዜም #ጣዖት ብለው የሚያስቡት #በእግዚአብሔርና #በማርያም አልያም #በመላዕክት #ተመስሎ የተሳለውን ወይም የተቀረጸውን ሳይሆን #በእንስሳት፣ በተለያዩ #ቁሳቁሶች መልክ የተዘጋጀውን #ቅርጽ ብቻ ይመስላቸዋል። በእርግጥ እነርሱም ቢሆኑ #አምልኮና #ስግደት ከቀረበባቸው #ጣኦታት ናቸው። ነገር ግን እንኳንስ #በማርያም #በእግዚአብሔር በራሱ #መልክን ሰርቶ ማስቀመጥ ብሎም ወደ #ምስሉ መስገድ #እግዚአብሔር ከመቃወምም ባለፈ #ይጸየፋል#ሙሴ ለእስራኤል ህዝብ #ሲያስጠነቅቅ

<<እግዚአብሔርም በእሳት ውስጥ ሆኖ ተናገራችሁ፤ የቃልን ድምፅ ሰማችሁ፥ መልክ ግን አላያችሁም፤ ድምፅን ብቻ ሰማችሁ።. . . እግዚአብሔር በኮሬብ በእሳት ውስጥ ሆኖ በተናገራችሁ ጊዜ መልክ ከቶ አላያችሁምና እጅግ ተጠንቀቁ፤ እንዳትረክሱ፥ የተቀረጸውን ምስል የማናቸውንም ነገር ምሳሌ፥ በወንድ ወይም በሴት መልክ የተሠራውን፥. . . ሰግደህላቸው አምልከሃቸውም እንዳትስት ተጠንቀቅ።>> [ዘዳ 4፤ 12፣ 15-19]።

▶️ ከዚህ #ከበድ ካለ #ማስጠንቀቂያ እንደምንረዳው #በኮሬብ ለእስራኤል #እግዚአብሔር ራሱን ሲገልጥ #ያለመልክ በመሆኑ ይህን ይመስላል ብሎ #መሳልም #መቅረጽም ብሎም #መስገድ መሳት እንደሆነ እንረዳለን። #እግዚአብሔር እንኳንስ #ለማርያም ለራሱም ቢሆን #በተቀረጸ #ምስል #አምልኮ እንዲቀርብለት ፈጽሞ አይፈልግም።

▶️ በ15ኛው #ክፍለ ዘመን የነበሩት #እስጢፋኖሳውያን የአፄ ዘርዓያዕቆብ #አፍቅሮተ #ጣኦታት የተጠናወታቸው ሰዎች <<ምስለ ፍቁር ወልዳ>> ለሚባለው #ስዕል እንዲሰግዱ ቢያሳዩአቸው #ሥዕሉን አድንቀው <<ለሰው ስራ አትስገዱ>> የሚለውን #አምላካዊ #ትዕዛዝ በማስታወስ <<የሰው ስራ ነውና አንሰግድም>> እንዳሉ ገድላቸው ይተርካል[2]።

▶️ ሌሎችም ለምሳሌ #ዘሚካኤልና #ገማርያ የሚባሉ 2 ሊቃውንት <<አልቦቱ መልክዓ ለእግዚአብሔር ከመ መልክዓ ሰብዕ - እግዚአብሔር የሰው መልክ የሚመስል መልክ የለውም>> በማለታቸው አጼ #ዘርዓ ያዕቆብ #ተቆጥቶና #ተከራክሮ አስቀጥቷቸዋል[3]።

▶️ ደቂቀ እስጢፋኖስ ይወቁት አይወቁት አይታወቅም እንጂ #ለስዕል #አይሰገድም የሚለው እውነት #በኢትዮጵያ ታሪክ አዲስ ሃሳብ አይደለም። እነርሱ ከመነሳታቸው #ከ150 አመት በፊትም እዚያው ትግራይ <<ለስዕል አይሰገድም ጣኦት ነው፣ ሰሌዳ ነው>> ያሉ ታላላቅ #የሃይማኖት #አባቶች ነበሩ። ነገር ግን #አጼ #ያግብአ #ጽዮን[4] [1278-1286] <<በዚህ ጥያቄ እያመነታሁ ሳለው ቀይ ሴት (እመቤታችን) ተገልፃልኝ <<ለሥዕሌ መስገድ ይገባል ብላኛለችና ያልታዘዘ ገመድ ለአንገቱ ያከማቸው ንብረቱ ለሰራዊቴ ቤቱ ከጠመንጃዬ አፎት ለምታወጣ እሳት ይደረጋል>> ሲሉ #ነጋሪት #ጎስመው ስላወጁ ያገሩ ሰዎች ሁሉ #የስዕለ #ማርያም #አምልኮ ትምህርት ተደናግጠው ለጊዜውም ቢሆን ከንጉሱ #ጥይት ለመትረፍ <<ንጉሱ ያዘዘንን ሁሉ እናደርጋለን ለስዕልም እንሰግዳለን>> እንዳሉና በዚህም #እንቅስቃሴው ቀዝቀዝ እንዳለ የታሪክ ጸሀፊዎች ዘግበውታል[5]። <<እንግዲህ እግዚአብሔርን በማን ትመስሉታላቹ ወይስ በምን ምሳሌ ታስተያዩታላችሁ>> {ኢሳ 40፥18}።

<<እንግዲህ የእግዚአብሔር ዘመዶች ከሆንን፥ አምላክ በሰው ብልሃትና አሳብ የተቀረጸውን ወርቅ ወይም ብር ወይም ድንጋይ እንዲመስል እናስብ ዘንድ አይገባንም።>> [ሐዋ 17፥29]።

<<እኔ እግዚአብሔር ነኝ፤ ስሜ ይህ ነው፤ ክብሬን ለሌላ፥ ምስጋናዬንም ለተቀረጹ ምስሎች አልሰጥም።>> [ኢሳ 42፥8]።

<<እግዚአብሔር መንፈስ ነው የሚመለከውም በእውነትና በመንፈስ ነው>> [ዩሐ 4፥24]።

▶️ በመሆኑም #ምስሎች ወደ #ቤተክርስቲያን በገቡበት #ትርጉማቸው #ለማስተማሪያነት ካልሆነ በቀር #ለስርዓተ #አምልኮ መጠቀሚያ ሊውሉ አይገባም። <<ፀልዩ ቅድመ ስዕላ ለቅድስት ድንግል-በቅድስት ድንግል ማርያም ስዕል ፊት ፀልዩ>> ብሎ #ዘርዓያዕቆብ ያወጀው #አዋጅ #የኃጢአት አዋጅ ነውና ዲያቆኑ ቢተወው #ከእግዚአብሔር ጋር #መስማማት ነው።

<<የተቀረጸውንም የአምላኮቻቸውን ምስል በእሳት ታቃጥላለህ፤ የተሠራባቸውን ብርና ወርቅ አትመኝ፤ በአምላክህም በእግዚአብሔር ዘንድ ርኩስ ነውና እንዳትጠመድበት ከእርሱ ምንም አትውሰድ። እንደ እርሱም ርጉም እንዳትሆን ርኩስን ነገር ወደ ቤትህ አታግባ፤ ርጉም ነውና ተጸየፈው፥ ጥላውም።>> ይላል እግዚአብሔር [ዘዳ 7፤ 25-26]።

✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆

"ማጣቀሻዎች - References"
_________
[1] 📚፤ "The Docmates of Vatican vol. 2 pp 94,95, Londen 1973.

[2] 📚፤ ገድለ አባ ዕዝራ ገጽ 38።

[3] 📚፤ ጌታቸው ሀይሌ፤ "ደቂቀ እስጢፋኖስ በህገ አምላክ" ገጽ 28፣ የህዳግ ማብራሪያ፤ 1996 ዓ.ም።

[4] 〽️ https://en.m.wikipedia.org/wiki/Yagbe'u_Seyon

[5] 📚፤ K.contirossini, the act፥ vol 16 (1965)፤ pp. 12-14።

📚፤ ጌታቸው ሀይሌ፤ "ደቂቀ እስጢፋኖስ በህገ አምላክ" ገጽ 24፣ 1996 ዓ.ም።

@gedlatnadersanat
(9.5▶️) ይቀጥላል...
@gedlatnadersanat