አትሮኖስ
281K subscribers
111 photos
3 videos
41 files
481 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ሮሜዎና_ዡልዬት

#ክፍል_ሶስት

#ሜርኮቲዎ
የሆነስ ሆነና ቀጠሮ ግን አለክ?

#ሮሜዎ
የወጣ ፡ ቃል ፡ የለም ፡ አፋችን ፡ ተናግሮ ፡
ዳሩ ፡ ግን ፡ ተያይተን ፡ ባይን ፡ ስንገናኝ ፡
ለኔ ፡ መፈጠሯ ፡ ለልቤ ፡ ተሰማኝ ።
እሷም ፡ እንደዚሁ ፡ በውስጣዊ ፡ ልቧ ፡
አይጠረጠርም ፡ እንደ ፡ እኔ ፡ ማሰቧ ።
እጅግ ፡ የሚያስደንቅ ፡ ለብልኋ፡ አስተዋይ
እነሆ ፡ ይኸ ፡ ነው ፡ የሰው ፡ ፍቅር ፡ ጠባይ
አፍ ፡ ሳይንቀሳቀስ ፡ ታስሮ ፡ በዝምታ ፡
ልብ ፡ ከልብ ፡ ጋራ ፡ ያደርጋል ፡ ጨዋታ ፡
ተወኝ ፡ ልሂድበት ፡ እንግዲህ ፡ ደኅና ፡ እደር ፤
እኔን ፡ አየሁ ፡ ብለህ ፡ ለሰው ፡ አትናገር ።

(ሮሜዎ ፡ ሄደ) ።

#ሮሜዎ ፡ (በዡልዬት ፡ መኝታ ፡ ቤት ፡ አጠገብ • ማታ፡በጨረቃ ከውጭ ፡ ሆኖ)

የሚያፈቅራትን ፡ ልጅ ፡ የሚጠብቅ ፡ ወጣት ፡ ረዝሞ ፡ ይታየዋል ፡ ደቂቃ ፡ እንደ ሰዓት ፤ሰዓቱም ፡ እንደ ፡ ቀን ፥ ቀኑም ፡ እንደ ፡ ዘመን እኔስ ፡ መሞቴ ፡ ነው ፡ በፍቅሯ ፡ ሰመመን ።

(#ዡልዬት ፡ መስኮት ከፍታ'ብቅ'አለች "
አሳቤ ፡ ተነሣ 'ተከፈቱ'ዐይኖቼ፤
ደሜ ፡ ተንቀሳቀስ፡ተፍታቱ ፡ ሥሮቼ ።
ልቤ ፡ ተስፋ፡ ሲቈርጥ ፡ የማትወጣ ፡ መስሎት ፡ ያቻት፡ የኔ ፡ ሥራ ፡ ብቅ አለች ፡ በመስኮት ።
ልቤ ፡ ደስ ፡ ይበልህ ፡ መንፈሴ ተሸበር ፤
የዡልዬትን ፡ ውበት ፡ እንግዴህ 'ልናገር ፤
መስኮቷ ፡ ምሥራቅ ፡ ነው' ፊቷ' የጧት'ጀንበር ብርሃኗ' የለውም ፡ የሚያግደው ' ድንበር ።
ሰላም ፡ ላንቺ ፡ ይሁን ፡ ትልሻለች ፡ ነፍሴ ፤
ጮራሽ፡ ኣለበሰኝ ፡ ከእግር ፡ እስከ ፡ ራሴ ፡
እኔ ፡ እንደምወድሽ ፡ አታውቂውም ፡ ፍቅሬ ፤
አላጫወትኩሽም ፡ ባፌ ፡ ተናግሬ ፡
ካየሁሽ ፡ ይበቃል ፡ ቆሜ' ከሩቅ ፡ ቦታ፤
ያጠግበኛልና 'ያይኖችሽ ፡ ጨዋታ ፡
ዐይንሽ ፡ የሚመስለው ' የርግብ ፡ የሚዳቋ ፣
እኔ ፡ የማልጠግበው 'አለው ፡ ልዩ ፡ ቋንቋ
ዐይኔ ፡ እንደ ፡ ቀለበት ፡ ጣትሽ ፡ ላይ ፡ ተሰካ ፤
እዩት ፡ በቀኝ ፡ እጅዋ 'ጕንጮቿን ' ስትነካ ፡
የእጅ ፡ ሹራብ ፡ ሆኜ፡ ገላሽን ፡ ባለብሰው ፡
ፊትሽን ፡ ጕንጭሽን' ዡልዬት፡ብዳብሰው ፡
ደስታ፡ሕይወቴን'እንደ 'ምን' ባደሰው !

#ዡልዬት
ሮሜዎ፡ሮሜዎ'የልቤ'ወለላ '
እባክህ ፡ ለውጠው ፡ ስምህን ፡ በሌላ ፡
ፍቅራችንን 'ገደል ፡ ሆኖ ፡ የሚያግደው
ቂም ፡ በቀል ፡ ስላለ ፡ ኀጢአት ፡ የወለደው ,
እኔም ፡ ዘሬን ፡ ልካድ፤ አንተም'ዘርህን ፡
የኔ ፡ አባት ፡ ላንተ' አባት ፤ የናንተ ፡ ዘር ፡ ለኛ መሆኑን ' አትርሳ ፡ ባላንጣ 'ደመኛ ።

#ሮሜዎ
ይህን ፡ ኣልዘነጋም ፡ ዡልዬት ፡ ይሰማኛል
ነገር ፡ ግን 'ምን ፡ በቀል'ምንስ'ቂም ፡ ይገኛል ፡
ምንስ ' ጠላትነት ስታስቢው ፡ በሰው ፡
የፍቅር ፡ ማዕበል ፡ የማይደመስሰው ፡
የኔ ፡ አባት ፡ ላንች ፡ አባት' ቢሆንም ፡ ባላንጣ ፡
እኔ ፡ እወድሻለሁ ፡ ነፍሴ ፡ እስክትወጣ ።

#ዡልዬት
ሮሜዎ ፡ እውነት ፡ ነው ፡ ዕድሜ ፡ ለሰው ፡ ክፋት !
በፍቅር ፡ መካከል ፡ አለ ፡ ብዙ፡ ዕንቅፋት ፡
የጌታ ፡ ልጅ'ድኻን 'አይውደድ' ይላሉ ፤
ብዙዎች ፡ ልጃቸውን ' በዚህ ' ይክዳሉ ፡
ዳሩ ፡ ግን ፡ የሰው ፡ ልብ ፡ በሰው ፡ አይመራም
የፍቅራችን ፡ መብራት፡በትእዛዝ አይበራም
ልጅ' ካባት 'አጣልቶ፡ብዙ፡ ሰው ፡ የጐዳ '
ይህን'የመሰለ'አለብን'ብዙ ዕዳ "
ቂም ፡ በቀል ፡ የሚሉት ፡ መከረኛ' ጣጣ'
ካያት ፡ ካባት ' ከናት ' ከዘር ፡ የሚመጣ
እኛ ፡ እንዳንፋቀር ፡ ማንንም ፡ ሳንፈራ ፡
ሆኖብን ፡ ተገኘ ፡ የፍቅር 'ደንቃራ ፤
ዳሩ ፡ ግን ፡ ይህ ፡ እክል ፡ ለሰው ፡ የማይራራ
እጅ ፡ እግር ፡ የሌለው ፡ እኛ፡ የማናውቀው፡
አይችልም ፡ ልብህን ፡ ከልቤ ፡ ሊያርቀው :
ሞንታግስ ምንድነው ፡ ፊደል አይደለም፡ ወይ ?
እኛን ፡ ሊለያየን'አይችልም ፡ ፍቅሬ ፡ ሆይ ፡
ስሟን 'ብንለውጠው ፡ እስቲ ፡ ጽጌ'ረዳ ፡
ይችላል ፡ ወይ ፡ መልኳ፡ ሊለወጥ ' ሊጐዳ
አይችልም ፡ ውሸት ፡ ነው ፡ በማዛ ፡ በውበት ፤
ጽጌ ረዳ'ያው ፡ ነች፡አይነካትም ፡ጕድለት ፡
ሮሜዎም ፡ እንዲሁ ፡ ስሙን ፡ ቢለውጠው ፡
ባሕርዩን 'ኣይችልም ፡ ከቶ ፡ ሊያናውጠው
ተወዳጅነቱ ፡ እስከ ፡ ዘላለሙ ፡
በጠባይ ፡ ነው ፡ እንጂ ፡ አይደለም ፡ በስሙ ።
ያንተ ፡ ስም ፡ ቢለወጥ፡ ዋጋህን ፡ አትርሳ ፡
እኔን ፡ ማግኘትህ ፡ ነው ፡ ያንተ ፡ ትልቅ ፡ ካሳ ።

#ሮሜዎ
በመካከላችን ፡የተገኘው ፡ እክል ፡
ስሜ ፡ ከሆነማ ፡ የኛ ፡ መሰናክል ፡
አጭር ፡ ነው፡ ነገሩ፡ ዡልዬት፡ የኔ፡ ፋና ፡
አንቺን ፡ ደስ ፡ እንዲልሽ ፡ ለፍቅሬ ፡ ዋስትና ፡
ላደርገው ፡ የማልፈቅድ ፡ ነገር ፡ የለምና ፤
ቢያስፈልግ ፡ ልነሣ ፡ ዳግም ፡ ክርስትና ፡
ሲሰማ ፡ እንዳይቀፈው ፡ ስሜን ፡ ያንቺ ፡ ዦሮ ፡
ሮሜዎ ፡ኣይደለሁም ፡ ከዛሬ፡ ጀምሮ ፤
ፍቅርሽና ፡ ፍቅሬ ፡ በዘር ፡ ቂም ፡ ኣይፈርስም ፤
ከዛሬ ጀምሮ' ይለወጥ ፡ የኔ ፡ ስም ።

#ዡልዬት
ማነህ ፡ አንተ ፡ ከዚህ ፡ የቆምከው ፡ ከደጄ ?
ባይኔ ፡ የማላይህ ፡ የማልነካህ ፡ በእጄ ፡
ጨለማ ፡ የለበስክ ፡ የፍቅር ፡ ማዕበል ፡
የልቤ ፡ ነበልባል ፡ ስምህን ፡ ማ ፡ ልበል?

#ሮሜዎ
ባንቺ ፡ ፍቅር ፡ ብቻ፡ የሚኖር ፡ ከርታታ፡
የቀን ፡ ብርሃን ፡ ሸሽቶ ፡ የመጣ ፡ በማታ ፡
አንቺን በመውደዱ ፡ ከራሱ'አብልጦ ፡
ያለ ፡ ስም ፡ የቀረ ፡ ስሙንም ፡ ለውጦ ።

#ዡልዬት
ያጥራችን ፡ ግንቡ ፡ ትልቅ ፡ አይበገር ፤ ..
እንዴት ፡ ነው ፡ የገባህ ፡ አንተም ሳትቸገር ? .
መች ፡አጥር ፡ብቻ ነው ፡ ትልቁን ፡ጉድ ትቼ
ደግሞም ፡ ይገድሉሃል ፡ቢያዩህ ፡ ዘመዶቼ

#ሮሜዎ
ፍቅር ፡ ስለ ፡ ሆነ ፡ ጕልበቴና ፡ ክንፌ ፡
ግንቡ ፡ ሳያግደኝ መጣሁኝ ፡ አልፌ ፡
ጨለማም ፡ አጥርም ፡ ሳያሰናክለኝ ፡
እንዴት ፡ ያለ ፡ ሰው ፡ ነው ፡የሚከለክለኝ ?

#ዡልዬት
ታዲያ ፡ እዚህ ፡ ቢያገኙህ፡ይገድሉህ ፡ የለም ፡ ወይ?

#ሮሜዎ
ለኔ ፡ ምንም ፡ አይዶል ፡ ይህ ፡ ሁሉ ፡ ፍቅሬ ፡ ሆይ ፡
አጥር ፡ እጥሳለሁ ፡ ጦርም ፡ አያግደኝ ፤
ብርሃን ፡ የሞላበት ፡ እኔን ፡ ያሳበደኝ ፡
ጦሩስ ፡ ያንቺ ፡ ዐይን ፡ ነው ፡ የኔን ፡ ልብ ፡ የወጋ
በፍቅር ፡ ኣይተሽኝ ፡ መንፈሴ ፡ ቢረጋ ፤
ምንም ፡ ባላሠጋኝ ፡ የቀረው ፡ አደጋ ።

#ዡልዬት
ሳይህ ፡ በኛ ፡ ግቢ ፡ ይሰማኛል ፡ ሥጋት ፤
በሻምላ ፡ ወይ ፡ በጦር ፡ ልብህን ' ለመውጋት ፡
ስለማይመለስ ፡ ወገኔ ፡ አንተን ፡ አይቶ ፡
ቢያዩህ ፡ አልፈልግም ፡ ምንም ፡ ቢሆን ፡ ከቶ ።

#ሮሜዎ
ዥልዬት ፡ አታስቢ ፡ አትሥጊ ፡ለነፍሴ
ወዳንቺ' ስመጣ፡ ጨለማ ፡ ነው ፡ ልብሴ ፡
ትወጂኝ ፡ አትወጂኝ ፡ ባለመለየቴ ፡
ይህ ፡ ብቻ ፡ ነው ፡ ለኔ ፡ ሕመሜና' ሞቴ ፤
ስለዚህ ፡ ንገሪኝ፡ ምንም ፡ አትደብቂ ፤
ሌላውን'አደጋ ፡ ግድ ፡ የለሽም ፡ ናቂ ።
አትወጂኝ' እንደሆን ፡ ሰፊ ፡ ነው፡ ሐዘኔ ፤
በዚህ ፡ ሕመም ፡ ብቻ ፡ እሞታለሁ ፡ እኔ ።

#ዡልዬት
እፍረት ፡ እንዳይዘኝ ፡ ጨለማ ፡ ለብሼ ፡
እንግዲያው ' ልንገርህ ፡ አሳቤን ፡ ጨርሼ
እፍረት'ደኅናሰንብት መግደርደር ደኅና ሁን
ሮሜዎ 'አንድ ፡ ነገር ፡ ልጠይቅህ ፡ አሁን ፡
ከፊቴ የቆምከው ፡ ወዳጄ ፡ ፍቅሬ 'ሆይ'
ካንጀትህ ' ከልብህ ፡ ትወደኛለህ ' ወይ ?
ማንንም ፡ አልወድም ፡ ብለህ ፡ካንቺ ፡ሌላ
ትናገራለህ ፡ ወይ ፡ አሁን ፡ በመሐላ ?
እኔ ፡ ባንተ ፡ ፍቅር በጣም ፡ ተጨንቄ '
ስለምወድህ ፡ ነው ይህን
#ሮሜዎና_ዡልዬት

#ክፍል_አራት

#ዡልዬት
ይቅርብኝ 'አትማል በውነትም ፡ በውሸት ፡
ደግሞም ፡ ልማል ፡ ብለህ፡አሳብህ ፡ ከጸና
ምን ጊዜም ፡ ጣዖቴ ፡ ፍቅሬ ፡ አንተ ፡ ነህና
በራስህ ፡ ማልልኝ ፡ የኔ ፡ ሁለንተና ።

#ሮሜዎ
እንግዲያውስ ፡ ስሚ ፡ እኔ ፡ አንቺን ፡ መውደዴ ፡

#ዡልዬት
ይቅር ፡ በቃ ፡ አትማል ፤ ተናወጠ ፡ ሆዴ ፡
ፈጥነህ ፡ ብትምልልኝ ፡ አሁን ፡ ዛሬ ፡ ማታ
ምንም ፡ አይሰማኝ ፡ ለልቤ ፡ ደስታ ፡
እንደዚህ ፡ በድንገት ፡ እንዲህ ፡ በችኰላ ፡
እንደዚህ ፡ በቶሎ ፡ የሆነ ፡ መሓላ ፡
መሠረት ፡ የለውም ፡ ይጠፋል ፡ ባንዳፍታ፤
አላፊ ፡ ነፋስ ፡ ነው ፡ የሰማይ ፡ ብልጭታ
የፍቅሩ፡ ቡቃያ ፡ ከዛሬ ፡ ጀምሮ ፡
ለምልሞ ፡ ይጠንክር ፡ በልባችን ፡ አድሮ ፡
እኛም ፡ እዚያ ፡ ድረስ ፡ሆነን ፡ ትዕግሥተኛ
ወደየቤታችን ፡ ገብተን ፡ እንተኛ ።

#ሮሜዎ
ልትሄጂ ፡ ነወይ ፡ ትተሽኝ ፡ በከንቱ ?

#ዥልየት
ይበቃል ፡ ለዛሬ ፡ መሽብን ፡ ሰዓቱ ።

#ሮሜዎ
ስጭኝ ፡ የሚያጠግብ፡አንድ ፡ ቃል ፡ የበቃ

#ዡልዬት
አንተ ፡ ሳትጠይቅ ፡ በፊት፡ዡልዬት ፡ዐውቃ
ሰጥታህ፡ወስደኸዋል፡የፍቅሯን፡ቃል ኪዳን
የተረፈው ፡ ይደር ፡ ለነገ ፡ እንዲረዳን ።

#ሮሜዎ
መልሰሽ ወስደሺው ፡'መልካሙን ፡ ስጦታ

#ዡልዬት
ቃሌን ፡ እሰጣለሁ ፡ ላንተ ፡ በችሮታ
የልቤ ፡ ደግነት ፡ ባሕር ፡ ነው ፡ ስፋቱ ፤
ፍቅሬም ፡ እንደዚሁ፡ ጥልቅ ፡ ነው ፡ ርቀቱ
መልካም ፡ ጠባዮቼ ፡ እነዚህ ፡ ሁለቱ ፡
ሰፊ ፡ ሀብት ፡ናቸው፡ ከሁሉም ፡ የላቁ ፤
ብሰጥህ ፡ ብሰጥህ ፡ ምን ፡ ጊዜም ፡ አያልቁ ።
(#ሞግዚቷ' #ጠራቻት ) ።
ጠሩኝ ፡ ድምፅ ፡ ሰማሁ ፡ በል ፡ ሄድኩኝ፡ደኅኖ፡እደር።
ሞግዚቴ ፡ እሺ ፡ መጣሁ ፤ ሮሜዎ ፡ አንድ ነገር ፡ አለ ፡ የምነግርህ፡አትሂድ፡ጠብቀኝ ፣ (ወደቤት'ግባች) »

#ሮሜዎ : (ብቻውን) "
የዛሬው ፡ ደስታ ፡ ምንኛ ፡ ደነቀኝ ።
ሕልም ፡ ነው ፡ ራእይ፡ ወይስ ' ደግሞ ቅዠት አልችልም ፡ ይህ ፡ ነገር ፡ ከቶ'ልደርስበት ፤
ፀሓዬ ፡ ጠለቀች ፡ ገባች ፡ ወደ ፡ ቤቷ ።
አሁን ፡ ተመልሳ ፡ ዳግም ፡ በመስኮቷ ፡
ብቅ ፡ እስክትል ፡ ድረስ ፡ ሆነብኝ ፡ ጨለማ ፡
ይኸው ፡ ተመለሰ ፡ የብርሃኗ ፡ ግርማ ።

#ዡልዬት ፡(ተመልሳ • መጣች
ሮሜዎ ፡ ልንገርህ ፡ የመጨረሻ ፡ ቃል ፤
እንደምታፈቅረኝ ፡ ዐወቅሁት ፡ ይበቃል ፡
ዳሩ ፡ ግን ፡ ፍቅራችን ፡ መሠረት ፡ አግኝቶ
በተክሊል ፡ ጋብቻ ፡ እንዲፈጸም ፡ ጸንቶ ፡
ትፈቅድ ፡ እንደ ፡ ሆነ ፡ እልካለሁና ፥
ነገ ፡ ሰው ፡ ወዳንተ ፡ ጒዳዩን ፡ ካጠናህ ፡
ካሰበ ፡ በኋላ ፡ መንፈስህ ፡ መርምሮ ፡
የተክሊሉ ፡ ሰዓት ፡ ይሁን ፡ በቀጠር ።
ወስነህ ፡ ላክብኝ ፤ ከዚያ ፡ በኋላ ፡ ግን ፡
ማመንታት ፡ ሳይኖረው ፡ ልቤ ፡ ሳይገነግን
ችግር ፡ ሳያግደኝ ፡ አደጋና ፡ ሞትም ፡
አንተን ፡ ተከትዬ ፡ እሄዳለሁ ፡ የትም ።
ነገር ግን ፡ ያንተ ፡አሳብ ከሌለው ፡ ንጽሕና
የማይሄድ ፡ ከሆነ ፡ እንደኔ ፡ ኅሊና ፡
አትምጣ፡ ወደኔ ፡ አትድከም ፡ በከንቱ
እንግዴህ ፡ ደኅና ፡ ሁን ፡ አለፈ ፡ ሰዓቱ '
ግባ ፡ ወደ ፡ ቤትህ ፡ ፍጠን ፡ አታመንታ ፤
ሊነጋ ፡ ነውና ፡ ይታያል ፡ ወገግታ ፡
ጨለማ ፡ ለቀቀ ፡ ብርሃን ፡ ተከፈተ ፡
ስንት ፡ ሰዓት ፡ ሲሆን ፡ ሰው ፡ ልላክ ፡ ወዳንተ ?

#ሮሜዎ
ሦስት ፡ ሰዓት ሲሆን መልክተኛሽ ፡ ይምጣ

#ዡልዬት
እንግዴህ ፡ ደኅና ፡ ሁን ፡ ፀሓይ ፡ ሳትወጣ
እንግባ ፡ ቤታችን ። (ሄደች)•

#ሮሜዎ
ዡልዬት ፡ ደኅና ፡ ሁኝ፤
ልቤ ፡ ካንቺ ፡ ጋራ ፡ መቅረቱን ፡ እመኝ ። (ሄዴ) •

#ሮሜዎና #ኣባ_ሎራ ፡ (ባባ ' ሎራ' ቤት)

#ሮሜዎ
እንደምን ፡ አድረዋል፡ አባቴ ፡ አባ ፡ ሎራ ?

#አባ_ሎራ
ከምሥራቅ ፡ ሳይታይ ፡ የፀሓይዋ ፡ ሥራ ፡
ማነህ ፡ በማለዳ ፡ የመጣህ ፡ ከቤቴ ?
በጣፋጩ ፡ ድምፅህ ፡ የምትል ፡ አባቴ ።
እረግ ! አንተ ፡ ነህ ፡ ወይ ፡ሮሜዎ ፡ ጐበዙ
ዐይኔ ፡ ደከመና ፡ አላየም ፡ በብዙ ፡
እንደ ፡ ምን ፡ አድረሃል ፡ የምወድህ ፡ ልጄ
ዐይንህ፡በጣም፡ቀልቷል፡ምን ነካህ ወዳጄ ?
አንድ ፡ ሰው ፡ እንደዚህ ፡ በጧት ፡ የሚነሣ
ነገር ፡ ሲያገኘው ፡ ነው ፡ እንቅልፍ ፡ የሚነሳ ፡
አሳብ ፡ የምንለው ፡ የሰላም ፡ መጋኛ ፡
መንፈሱን ፡ ሰፍሮበት ፡ እንቅልፍ ፡ የማይተኛ ፡
ሽማግሌ ፡ ሰው ፡ ነው ፤ ወጣት ፡ ግን ፡ በውኑ ፡
ከእንግዲህ ፡ ያለ ፡ ነገር ፡ ነጻ ፡ በመሆኑ ፡
ተኝቶ ፡ ያነጋል ፡ እንቅልፉን ፡ በሰላም ፤
ስለዚህ ፡ ይህ ፡ ዐይንህ ፡ በደኅናው ፡ አልቀላም ፡
ሮሜዎ ፡ ምን ፡ ሆኖ ፡ ሳይተኛ ፡ ያደረ ?
አለመተኛቱን ፡ ዐይኑ ፡ መሰከረ ።

#ሮሜዎ
እውነት ፡ ነው ፡ ነገር ፡ ግን ፡አርፌያለሁ ፡ በጣም

#አባ_ሎራ
ብታርፍማ ፡ ኖሮ ፡ በሌሊት ፡ አትመጣም ፡
ንገረኝ ፡ አትደብቅ ፡ ወዴት ፡ ነው ፡ ያደርከው ?

#ሮሜዎ
ድል ፡ አድራጊው : ፍቅሯ ፡ መንፈሴን ፡ ማረከው
አባቴ ፡ እጅዎ ፡ ተክሊሌን ፡ ይባርከው ።

#አባ_ሎራ
ያሰብከውን ፡ ነገር ፡ ንገረኝ ፡ አትፍራ ፤
ከመልካሟ ፡ እጮኛህ ፡ ከሮዛሊን ፡ ጋራ ፡
የተክሊል ፡ ቃል ፡ ኪዳን ፡ ዛሬ ፡ ልትሞላ ፡
የመጣህ ፡ መሰለኝ ፡ ሳስበው ፡ በመላ ።

#ሮሜዎ
ሮዛሊን ፡ ቀርታለች ፡ አያንሷት ፡ አባቴ ፡
ትናንትና ፡ ማታ ፡ ተመታ ፡ ደረቴ ፡
ባዲስ ፡ የፍቅር ፡ ጦር ፡ በሰላ ፡ ጐራዴ ፤
ከመውደዷ ፡ ጋራ ፡ ገጠመ ፡ መውደዴ፡
ስሜታችን ፡ እኩል ፡ ፍቅራችን ፡ የጋራ ፡
ሆኖ ፡ ከተገኘ ፡ አባቴ ፡ አባ ፡ ሎራ ፡
ተክሊሉን ፡ ይሙሉልን ፡ በሥልጣንዎ ፡ ባርከው ፡
እኛ ፡ ቂም ፡ የለንም ፤

#አባ_ሎራ
መንፈሴን ፡ ኣወከው
ምን ፡ አመጣህብኝ ፡ የማላውቀው ፡ ምስጢር ፥
መላ ፡ መትቶ ፡ ያውቃል ፡ ብለህ ፡ አትጠርጥር ፤
አልገባኝምና ፡ ያሁኑ ፡ ንግግር ።
ይህን ፡ እንቆቅልሽ ፡ እንደ ፡ ሾላ ፡ ድፍን ፡
ትተህ ፡ ፡ ግለጥልኝ ፡ ነገሩን ፡ ሳትሸፍን ።

#ሮሜዎ
አባቴ ፡ አልደብቅም ፡ ሁሉንም ፡ ገልጬ ፡
ለርስዎ ፡ ልነግር፡ ነው ፡ የመጣ ፡ ሮጬ፡
የነካፑሌን ፡ ልጅ ዡለየትን ፡ ወድጄ ፤
ራሴ ፡ እስቲጠፋ ፡ በፍቅር አብጄ ፡
እሷም ፡ በጣም ወዳኝ፡አድርገን ፡ መሐላ ፡
ተስማምተን ተዋደን ከቈረጥ ኋላ ፡
አሁን 'የሚቀረን'ተክሊል ፡ የሚሞላ ፡
ካህን ፡ ስለ ፡ ሆነ የሚሰጥ፡ ቡራኬ ፡
ከሷ ጋር ፡ መጥቼ ፈትዎ' ተንበርክኬ ፡
ሞልተው 'ያሰናብቱን የተክሊሉን ፡ ሥርዐት
ሰዓቱን 'ይንገሩኝ መቼ እንደምጠራት ።

#አባ_ሎራ
አይጣል፡ነው፡እናንተ፡ የወጣቶች ፡ ወረት፤
ፍቅራቸው ፡ ቃላቸው ፡ የለውም መሠረት፡
የቀድሞ ፡ እጮኛህ ፡ ሮዛሊን 'ተረስታ፡
ሌላ ፡ ልጅ ፡ አግኝተህ አሁን ትናንት ፡ ማታ
እንዴት ተለወጠ፡ ኣሳብህ ፡ ባንድ ፡ አፍታ፡
በሮዛሊን ፡ ፍቅር ፡ ልብህ ፡ እንዲያ፡ግሎ ፡
ዘላለም ፡ የማይበርድ፡እውነተኛ፡መስሎ ፡
ታጫውተኝ ፡ ነበር አሁን ፡ ይኸውና ፡
ያ ፡ ሁሉ ፡ መውደድህ 'ከመቼው 'ቀረና ፡
መጣህ ' ባዲስ ፡ ፍቅር ፡ ልብህ ፡ ተብረክርኮ ፡
ለምታያት፡ሁሉ፡መንፈስህ ፡ ተማርኮ፡

💫ይቀጥላል💫
👍1
#ሮሜዎና_ዡልዬት

#ክፍል_አምስት

ከተሸንፍክማ ' በጕንጮቿ ፡ ቅላት '
በወገቧ ቅጥነት፡ በደረቷ፡ ሙላት'
አበድኩ ፡ ካልክማ፡ ለጥርሶቿ 'ንጣት '
ለባቷ፡ አቀራረጽ ለጠጕርዋ ፡ቀለም ፡
ፍቅርህ ፡ ባይንህ ፡ ላይ ፡ነው፤ በልብህ ፡ አይደለም ይቅር በለኝ፡ልጄ፡ ባሁኑ ፡ ወቀሣ
ለዚች ፡ ከንፈህላት፡ ያችን ' ስትረሳ ፡
አመዛዘንኩና' ሠጋሁ፡ ኣስተውዬ '
ይችንም ፡ እንደዚያች' ትረሳለህ ፡ ብዬ ።

#ሮሜዎ
አባቴ ፡ በፍጹም ፡ ይህን ፡ አይጠርጥሩ፤
የዚችና ፡ የዚያች ፡ ልዩ ፡ ነው ፡ ነገሩ
በምን ፡ ቃል ፡ ልናገር ፡ ይህን ፡ ለማሳመን
በግሪክ ፡ በሮማ ፡ በጥንታዊው ፡ ዘመን ፡
ያነቡ፡ እንደ'ነበር' የእንስሳውን ፡ ሞራ ፡
ይችሉ ፡ እንደ ፡ ሆነ ፡ አባቴ ፡ አባ፡ ሎራ '
እርስዎም ፡ እንደዚሁ፡ የልቤን ፡ ብራና፡
በጥበብ ፡ አውጥተው ፡ገልጠው፡ያንቡና '
የወረት ፡ ምልክት ፡ ቢያገኙ፡ በውስጡ '
ያን ፡ ጊዜ 'ይገባል ፡ ቢንቁኝ ፡ ቢቈጡ ።

#አባ_ሎራ
መልካም ነው አመንኩህ ፡ግን ከዚህ ፡ በኋላ
አንድ ፡ ነገር ፡ አለ ፡ የሚያስቸግር ፡ ሌላ ፤
ካፑሌና ፡ ሞንታግ ፡ የናንተ ፡ አባቶች ፡ .
ወገኖቻቸውን ፡ ጨምረው ፡ ጠላቶች ፡
ባላንጦች ፡ ቂመኞች ፡ ደመኞች ፡ ሲሆኑ ፤
በየመንገዱ ፡ ላይ ፡ እንዳውሬ ፡ እያደኑ ፡
አንዱ ፡ አንዱን ፡ ሲገድለው ፡ ባይኑ ፡ ሲያየው፡ብቻ
እንዴት ፡ ሊፈጸም ፡ ነው ፡ የናንተ ፡ ጋብቻ ? .
ይኖሩ ፡ የለም ፡ ወይ ፡ ዘወትር ፡ በዘመቻ ፡
ዘለዓለም ፡ ለውጊያ ፡ ለጠብ ፡ ተሰልፈው ፡
ለቄስ ፡ ላስታራቂ ፡ ለዳኛ ፡ አሸንፈው ።

#ሮሜዎ
ይኸው፡አባቴ ሆይ ይህ ነው፡ ዋናው ነገር
በዚህ ፡ ላይ ፡ ይገባል ፡ በብዙ ፡ መማከር ፡
እውነት፡ ነው ፡ ቢኖሩ፡ ዘለዓለም ፡እነሱ፡
በጠብ ፡ ባምባጓሮ ፡ ደም ፡ እያፈሰሱ ፡
ለፍርድ ፡ ቢያስቸግሩ የቄስ ፡ ቃል ፡ ባይሰሙ ፡
እኔና ፡ ዡልዬት ፡ ግን ፡ንጹሕ ፡ ነን ፡ ከቂሙ፡
አለ ፡ ወይ ፡ አባቴ ፡ በሃይማኖት ፡ መንገድ
የሚከለክል ፡ ሕግ ፡ እኛ ፡ እንዳንዋደድ ፡
እንግዲህ ፡ አባቴ ፡ ይህንን ፡ ካወቁ ፡
ዘዴውን ፡ ለማግኘት ፡ እርስዎም ፡ ይጨነቁ ፡ቤተ ሰቦቻችን ወሬውን ፡ ሳይሰሙ
ተክሊሉን ፡ በምስጢር ፡ እርስዎ፡ ይፈጽሙ ።

#አባ_ሎራ
ይህንን ፡ ታልህማ ፡ ዘዴ ፡ ጠፍቶ ፡ ለርቁ ፡
ካህንም ፡ አልቀረም ፡ አብሮ ፡ መጨነቁ ፡
ለሁለቱ ፡ ወገን ፡ ሰላምን ፡ መልሶ ፡
ያባቶቻችሁን ፡ ክፉ ፡ ቂም ፡ ደምስሶ ፡
ስለታቸው ፡ ዘወትር ፡ የሰው ፡ ደም ፡ ከማፍሰስ ፡
እንዲቆም ፡ ለማድረግ ፡ ትንሽ ፡ እንዲታገሥ ፡
ለሻምላ ፥ ለጩቤ ፥ ለሰይፍ ፡ ለጐራዴ ፡
ከዚህ ፡ የተሻለ ፡ መች ፡ ይገኛል ፡ ዘዴ ።
የናንተ ፡ ጋብቻ ፡ ይህን ፡ ቂም ፡ አብርዶ ፤
ዕርቅ ፡ ይመሠረታል ፡ ሰላምን ፡ አውርዶ ።

#ሮሜዎ
እንግዴህ፡ አባቴ ፡ እንፍጠን ፡ በቶሎ ፡
ተክሊሉ ፡ ይፈጸም ፡ በዛሬ ፡ቀን ፡ ውሎ ፡
ጊዜና ሰዓቱን ፡ ካልተሻማን ፡ በጣም :
እንዲህ ፡ ያለ ፡ ፍቅር ፡ ዕንቅፋት ፡ አያጣም

#አባ_ሎራ
እንግዲያው ፡ መልካም ፡ ነው ፡ ኑና ፡ ባሥር ፡ ሰዓት፡
ትፈጽማላችሁ ጋብቻችሁን በስራት

#የዡዬየት_ሞግዚትና #ሮሚዎ

#ሞግዚት
መልሱን ፡ ተቀብለሽ ፡ እንድትመጪ ' ብላ
ልካኝ' እመቤቴ ፡ በቶሎ ፡ አስቸኵላ '
ይኸው ፡ መጥቻለሁ፡ መልሱን ፡ ለመቀበል ፤
ቸኩያለሁና ፡ ንገረኝ፡ ቶሎ ፡ በል ።

#ሮሜዎ
ምላሴ 'ያሞግስ ፡ አፌም ፡ ያመስግናት ፤
በውነት' ያንቺ ፡ እመቤት ፡ የተባረከች ፡ ናት
ዐመሏ ' ጠባይዋ ፡ በለጠ ' ከመልኳ፤
ቃሏን ፡ ፈጸመችው ፡ አንቺን ፡ በመላኳ
ዥሮቼ ፡ ተከፍተው 'እሰማለሁና፡
እንግዴህ ፡ ንገሪኝ የዡልዬትን ፡ ዜና ።

#ሞግዚት
ለተነጋገርነው ፡ ትናንትና ፡ ማታ ፡
እንድትልክብኝ' ያሳብህን ፡ ሁኔታ ፡
በመጠበቅ ፡ ላይ ፡ ነኝ ፡ አስታውቀኝ ፡ በቶሎ ፤
በዪና፡ ንገሪው ፤እንደዚህ ፡ ነው፡ ብሎ ፡
አሳቡን ፡ ሲነግርሽ ፡ ተቀብለሽ ፡ አምጪ፡
ብላኝ ' መጥቻለሁ ።

#ሮሜዎ
መልሴን ፡ ስትሰጪ '
እንግዲያው ፡ ንገሪያት ፡ ሮሜዎ ፡ ከልቡ ፡
ይወድሻል ፡ ብለሽ ፡ መንፈሱም ፡ አሳቡ ፡
ወዳንቺ ፡ ነው ፡ በያት ፡ ንገሪያት ፡ አደራ ፤
እስቲ ፡ ልለምንሽ ፡ እባክሽ ፡ ሳልፈራ ፡
እኔ ፡ እንደምወዳት፡ እንደዚሁም ፡ እሷ'
ትወደኝ ፡ እንደሆን ፡ ዡልዬት፡ በመንፈሷ፡
ታውቂዋለሽና ፡ እባክሽ ፡ ንገሪኝ ፡
አሳቧን ፡ ጠባይዋን 'እንዳውቀው ፡
ምከሪኝ ።

#ሞግዚት
ምንም ፡ አልደብቅህ ፡ ልንገርህ ፡ ካንዠቴ
አንተን ፡ ስታፈቅር ፡ ዝልዬት ፡ እመቤቴ'
እመነኝ ፡ ልንገርህ ፡ በውነት ፡ ከልቧ' ነው
የመስፍኑ ዘመድ፡ፓሪስ የሚባለው፡
ሊያገባት፡ ፈልጎ ፡ መሞቱ ፡ ነው ፡ ደክሞ ፡
ጨርሳ ፡ አትወደውም፡ እሷ ፡ ግን ፡ ፈጽሞ
አታንሡ፡ትላለች ፡ የሱን ፡ ስም ፡ ከፊቴ ፤
ትቈጣለችና ፡ ስቈይ ፡ እመቤቴ ፡
ልመለስ ፡ እባክህ ፡ መልሱን ፡ ስጠኝና ፤

#ሮሜዎ
አቀርብልሻለሁ'በሰፊው ፡ ምስጋና ።
እንደዚህ ' በዪና ፡ መልሱንም ፡ ንገሪያት ፤
ከቀትር ፡ በኋላ ፡ ዛሬ ፡ ባሥር ፡ ሰዓት ፡
አባ 'ሎራ፡ ድረስ ፡ አስፈቅዳ ፡ ትምጣ፤
ተናዘን ፡ ተባርከን ፡ የተክሊሉን ፡ጣጣ፡
ደብቀው ፡ በሙሉ ፡ ሊፈጽሙ፡ ቄሱ ፡
ተስማምተናል ፡ በያት ፡ ዛሬ ፡ ሊጨርሱ ።

#አባ_ሎራ #ዡልዬት #ሮሜዎ

#አባ_ሎራ
የናንተ ፡ ጋብቻ ፡ ፍጻሜው ፡ እንዲያምር ፡
ፈጣሪ ፡ ጸጋውን ፡ ምሕረቱን ፡ ይጨምር ።

#ሮሜዎ
አሳቤ ' ሞላልኝ ፡ እንግዲህ ፡ አባቴ ፡
ይህ ፡ ብቻ፡ ነበረ ፡ የቀረኝ ፡ ምኞቴ ።
ከሷ'ጋራ ፡ መጥቼ ፡ ቀርበን ፡ ከመንበሩ፡
ሥራቱን ፡ ከሞላን ፡ አለቀ ፡ ነገሩ ፡
እንግዲህ ፡ ግድ ፡ የለም የመጣ ፡ ቢመጣ

#አባ_ሎራ
ልጄ ፡ ሆይ ፡ ብዙ ነው የዚህ ዓለም ፡ ጣጣ
ለደስታ ፡ ሐዘን ፡ ለማር ፡ አለው ፡ እሬት ፤
ጠፊ ፡ ካጥፊው ፡ ጋራ ፡ ይኖራል ፡ በመሬት
ስለዚህ ፡እግዚአብሔር መጥፎውን ፡ አርቆ
ልጄ ፡ ያኑራችሁ ፡ በሰላም ፡ ጠብቆ ።

(ዡልዩት ፡ መጣች) ።

ፍቅሯንና ፡ ጌጧን ፡ በልቧ ፡ ሸፍና ፡
አልማዟ ፡ ማስተዋል ፡ ወርቋ ፡ ትሕትና ፡
ምስጢሯን ፡ ባሳቧ ፡ በጥበብ ፡ ሰውራ ፡
ይኸው ፡ መጣችልን ፡ መልካሟ ፡ ሙሽራ

#ዡልዬት
ሰላም ፡ ለርስዎ ፡ ይሁን ፡ ኣባቴ ፡ አባ ሎራ

#አባ_ሎራ
ደኅና ፡ ነሽ ወይ? ልጄ። ወጣት ፡ ሴት ፡ ወይዘሮ ፤
መልካም ፡ ጊዜ ፡ መጣሽ ፡ ልክ ፡ በቀጠሮ

#ዡልዬት
አመሰግናለሁ ፡ ለኔም ፡ ለሮሜዎ ፡
አባቴ ፡ ስለ ፡ እኛ ፡ በመቸገርዎ ።

#ሮሜዎ
እንዳንቺ ፡ እንደ ፡ እኔ ፡ በፍቅር ፡ ተሳስረው
ለመጡ ፡ ወጣቶች ፡ ሥራቱን ፡ አክብረው
ፍቅራቸውን ፡ ባርኮ ፡ በእጁ ፡ ሊቀድሰው ፡
ምን ፡ ጊዜም ፡ ሥራው ፡ ነው ፡ ካህን ፡ የሆነ ፡ሰው።

#አባ_ሎራ
እጆቹን ፡ ዘርግቶ ፡ ካህን ፡ ይጠብቃል ፤
እውነት ፡ ነው ፡ ሮሜዎ ፡ የተናገረው ፡ ቃል'
ከቤተ ፡ ክርስቲያን ፡ እንግባና ፡ በሉ ፡
ሳይዘገይ ፡ በቶሎ ፡ ይፈጸም ፡ ተክሊሉ ።

(ቤተ ፡ ክርስቲያን'ገቡ)

(#በቬሮና #ከተማ' #መንገድ) •

#ሜርኩቲዎ #ቤንቮሊዎ ፡ አንድ ፡ የእልፍኝ #አሽከር

#ቤንቮሊዎ
ሜርኩቲዎ ፡ እንሂድ ፡ የካፑሌ ፡ ሰዎች ፡
ይጠፉ ፡ አይመስለኝም በነዚህ መንደሮች
ድንገት ፡ ብንገናኝ ፡ ኋላ ፡ ጠብ ፡ ይነሣል ፤
ደግሞ ፡ ጠብ ሲነሣ ፡ ጸጥታ ፡ ይፈርሳል ፡
ብንሸሽ ፡ ይሻላል ፡ ከዚህ ፡ ሁሉ ፡ ጣጣ ።

#ሜርኩቲዎ
እነሱም ፡ አስበው ፡
👍1
#ሮሜዎና_ዡልዬት


#ክፍል_ሰባት

#ቤንቮሊዎ
ጠቡን ፡ የጀመረው ፡ ክፉ ፡ ቃል ፡ ተናግሮ
ይኸው ፡ ቲባልት ፡ ነው ፡ ሌላ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፤
ከሱ ፡ በቀር ፡ ዛሬ ፡ ጠብ ፡ ያነሣ ፡ የለም ።
እኔና ፡ ሜርኩቲዎን ፡ ሰደበን ፡ ሳንሰድበው
ሮሜዎ ፡ ደረሰ ፡ ድንገት ፡ ሳናስበው ።
እሱም ፡ በደግነት ፡ ቃሉን ፡ አለስልሶ ፡
ልዑል ፡ የሰጡትን ያዋጅ ፡ ቃል ፡ ኣስታውሶ ፡
ቲባልትን ፡ ለመነው ፡ ጠብ ፡ እንዳያነሣ ፤
መቼም ፡ መጥቷልና ፡ እሱ ፡ ግን ፡ ላበሳ ፡
በእልህ ፡ እንቢ ፡ ብሎ ስድቡን ፡ ሲቀጥል
ከሜርኩቲዎ ፡ ጋራ ፡ ተማረሩ ፡ በጥል ፤
ሻምላ ፡ ቢማዘዙ ፡ ቶሎ ፡ መገላገል ፡
አሰብንና ፡ ገባን ፡ ከነሱ ፡ መካከል ።
እኔና ፡ ሮሜዎ ፡ ስንገላግላቸው ፡
ሜርኩቲዎን ለመውጋት ቲባልት ተመቸው
እኛም ፡ አላየንም ሜርኩቲዎን ፡ ሲወጋው
ኋላ ፡ ግን ፡ አየነው ፡ ቁስሉን ፡ ከነ አደጋው
ከሽሸ ፡ በኋላ ፡ ቲባልት ፡ እንደ ፡ ገና ፡
ቢመጣ ፡ ሮሜዎ ፡ ነዶት ፡ ነበርና ፤
ደሙን ፡ ለመበቀል ፡ በንዴት ፡ ተነሥቶ ፡
ከቲባልት ፡ ጋራ ፡ በቅጽበት ፡ ተዋግቶ ፡
ወዲያው በደቂቃ ውጊያው በጣም ሲግል
እኔም ፡ ሳያደርሰኝ ፡ ችዬ ፡ ሳልገላግል ፡
ቲባልት ፡ ቆሰለና ፡ በፍጥነት ፡ ወደቀ ፥
ሮሜዎም ፡ ሸሸና ፡ በዚሁ ፡ አለቀ ፤
ከተናገርኩትም ፡ ከውነቱ ፡ የራቀ ፡
ውሸት ፡ ቢገኝብኝ ፡ ተደርጎ ፡ ምርመራ ፡
ይድረስብኝ ፡ በኔ ፡ የቅጣት ፡ መከራ ።

የካፑሌ ፡ ሚስት (መጣች)

መሠረት ፡ የለውም ፡ ምስክርነቱ ፤
ከእውነተኛው ፡ ነገር ፡ ይበልጣል ፡ ሐሰቱ '
ይህንን ፡ ቢናገር ፡ እያስመሰለ ፡ እሱ ፡
የሞንታግ ወገን ነው ልዑል ሆይ አይርሱ!
በፍርድ ሮሜዎ ፡ ይሙት ፡ ነው ፡ የምለው

#መስፍን
ሮሜዎ ፡ ቲባልትን ፡ ወግቶ ፡ ከገደለው ፡
እናንተ ፡ ስለሱ ፡ ፍርድ ፡ ስጥ ፡ ስትሉ ፡
የሜርኩቲዎን ፡ ደም ፡ ማን ይክፈለኝ ፡ለኔ
ዘመዴ ፡ ነው ፡ እኮ ፥ ሥጋዬ ፡ወገኔ ።

#ሞንታግ
ልዑል ፡ሆይ ሜርኩቲዎን ቲባልት ገደለው
ዐዋጁ 'ቲባልትን ፡ ይሙት' ነው ' የሚለው
ስለዚህ ፡ ቢያስቡት ፡ አሁን ፡ የኔ ፡ ልጅ ፤
ቲባልትን ሲገድለው ፡ዐዋጅ ፈጸመ ፡ እንጅ
ሌላ ፡ ምን ፡ ጨመረ ፡ እስቲ ምን አጠፋ ?

#መስፍን
ሞንታግ ምሕረት አለ ብለህ ፡ እንዳትለፋ፡
ሮሜዎ ፡ በፍጥነት ፡ ዛሬ ፡ ካገር ፡ ይውጣ
ጠባችሁ ፡ በኔ ፡ ላይ ፡ ይኸው ዞሮ ፡ መጣ
በናንተ ፡ ምክንያት ፡ የሞተው ፡ ደጉ ፡ ሰው
ሥጋዬ ፡ ነው ፡ ዛሬ ፡ ደሙ ፡ የፈሰሰው ፡
በሰጠሁት ፡ ዐዋጅ ፡ ራሴ ፡ ወስኜ ፡
እገኛለሁ ፡ እኔ ፡ ጨካኝ ፡ ቀጭ ፡ ሆኜ፡
የፍርዴንም ፡ ሥራ ፡ በቅጣት ፡ ስሠራ ፡
ይቅርታ ፡ የለኝም ፡ ለማንም ፡ አልራራ ።
አማላጅ ፡ ልመና ፡ ጸጸትና ፡ ለቅሶ ፡
ፍርዴን ፡ ሊመልሱት ፡ አይችሉም ፡ ጨርሶ
ስማ ፡ ልጅህ ፡ ዛሬ ፡ የኔን ፡ ትእዛዝ ፡ ሽሮ ፡
የተገኘ ፡ እንደሆን ፡ በከተማው ፡ አድሮ ፡
ዛሬ ፡ ከቬሮና ፡ በፍጥነት ፡ ካልወጣ '
ዕወቀው ' ያለፍርድ' በሞት እንዲቀጣ ።

#ዡልዬትና#ሞግዚቷ ፡ (በቤታቸው) "

#ዡልዬት
እኔና ፡ ሮሜዎ ፡ ዕድላችን ፡ ክፉ ፤
ይደንቃል ፡ ሰርጋችን ፡ እንደዚህ ፡ ማለፉ፡
ሰርጉ አልነበረም ወይ የሰው ፡ልጅ ደስታ
እኛ ፡ ግን ፡ምስኪኖች በዚህ ፡ ሁሉ ፈንታ፡
መሥጋትና ፡ መፍራት ፡ ያባት የናት ፡ ቁጣ
ሆነና ፡ ተገኘ ፡ የተሰጠን ፡ ዕጣ ።
አልገሠግሥ ፡ አለ ፡ ጊዜና ፡ ሰዓቱ ፤
ምነው ፡ የዛሬ ፡ ቀን ፡ ደከመ ፡ ፍጥነቱ ?
ሰዓቱም ፡ ለገመ ፡ ዳተኛ ፡ መሆኑ ፡
ሮሜዎን ፡ ስጠብቅ ፡ አልመሽ ፡አለኝ ፡ ቀኑ
ደግሞ ፡ ሞግዚቴ ፡ ነች ፡ ዋና ፡ ጥፋተኛ ፤
ምነው ፡ ሆነችብኝ ፡ እንደዚህ ፡ ዳተኛ ?
በፊት ፡ ደኅንነቱን ፡ ነግራኝ ፡ ተመልሳ ፡
መሄድ ፡ ትችል ፡ ነበር ዳግም ፡ በግሥገሣ
ሌሊቱ ፡ ሲጨልም ፡ ጨረቃ ፡ ሳትወጣ ፡
ንገሪው ፡ አልኩና ፡ ሮሜዎ ፡ እንዲመጣ '
ብልካት ፡ እንሆ ፡ ቀረች ፡ እዚያው ፡ ቀልጣ
እባክህ ፡ ጨለማ ፡ ፍጠን ፡ በቶሎ ፡ ና ፤
ካልመሸ ፡ ሮሜዎ ፡ ደፍሮ ፡ አይመጣምና
ሌሊቱ' ይተካ ፡ የቀን ፡ ብርሃን ፡ ሄዶ፤
ሮሜዎን ወደ እኔ እንዲያስገባው ፡ ጋርዶ።
ቀኑ ፡ እየደከመ ፡ ብርሃን ፡ እየሸሸ ፡
ፀሓይ ፡ እየጠፋች ፡ ሰዓቱ ፡ እየመሸ ፡
አንተ ፡ ከባድ ፡ ጽልመት፡የሌሊት ፡ ጨለማ
ፈጥነህ ፡ ቶሎ ፡ ድረስ ፡ አትሁን ፡ ደካማ ።
ገሥግሠህ ፡ ሸፍናት ፡ ዓለምን ፡ በጥላ ፤
ጥላህ ፡ ለሮሜዎ ፡ ይሁነው ፡ ከለላ '
ፀሓይም ፡ ጥለቂ ፤ ብርሃንን ፡ አትስጪ ፤
ኮከብ ፡ ተሰወሪ ፡ ጨረቃም ፡ አትውጪ'
ካለም ፡ ገለል ፡ በሉ ፡ ብርሃንና ፡ ፋና ፡
ብርሃን ፡ እሱ፡ ራሱ ፡ ሮሜዎ ፡ ነውና ፡
ያቻት ወዲህ መጣች ብቅ አለች ሞግዚቴ
ደርሳ እስክትነግረኝ ፡ ወሬውን ፡ ከፊቴ ፡
ቸኩያለሁ ፡ በጣም ፡ እንዴት ፡ ያለ ፡ ወሬ ፡
ይዘሽልኝ ፡ መጣሽ ፡ ሞግዚቴ ፡ ሆይ ፡ ዛሬ ?
ምነው ፡ ምን ፡ ሆነሻል ፡ ፊትሽ ፡ ተለወጠ ?

#ሞግዚት
አዬ 'ከንቱ ፡ ነገር ፡ በቃ ፡ ተቈረጠ'
ባጭር ፡ ተቀጠፈ ' ያን ፡ መሳይ ፡ መኰንን
አዬ ፡ጉድ አዬ ፡ ጉድ! ጠላሁ ሰው መሆንን

#ዡልዬት
አሁን ፡ ባሁን 'ሄደሽ ፡ ከኔ ዘንድ ፡ ከወጣሽ'
ምን ፡ዐይነት ፡ኀዘን ነው ይዘሽው የመጣሽ

#ሞግዚት
አወይ 'ሮሜዎ 'ቲባልት ፡ መልካሙ ፡ ሰው፡
እንደ ፡ፋሲካ ፡ በግ ፡ ደሙ ፡ የፈሰሰው ።

#ዡልዬት
ሐዘኑን ' ሰምቼ ፡ ልቤ ፡ ሳይመታ፡
መናገር' አቃተሽ ፡ አፍሽ ፡ አመነታ '
ሮሜዎ ፡ ሞተ፡ ወይ ? ሞቶም ፡እንደ ፡ ሆነ
ንገሪኝ ፡ ምላስሽ ፡ እየሸፋፈነ ፡
ሳይደብቅ ፡ ገልጦልኝ ፡ መርዶውን ፡ ልረዳ
ልቤም ፡ ተሠንጥቆ ፡ በሐዘን ፡ ይፈንዳ ።

#ሞግዚት
ቍስሉንም ፡ አየሁት ፡ በጣም ፡ ያሳዝናል ፤
ሐኪም 'አይጠሩለት ፡ ሞቶ፡ ምን ፡ ይሆናል
ምንም' ትንፋሽ የለው አልፋለች ፡ ሕይወቱ፡
ደሙ ፡ ይመነጫል ፡ ቆስሎ ' ከደረቱ ፤
ከሞተ 'ቁይቷል ደርቋል ፡ ሰውነቱ "
እንዲህ ፡ ያለ ፡ ሥራ መቼም ፡ አልተሠራም
ዥልዬት ፡ የዛሬ ፡ ጉድ ፡ ይቅር ፡ አይወራም
ቲባልት ! ሮሜዎ ! አየሁ ፡ ደሙ ፡ ፈሶ :
ልብሱ ፡ ተበክሎ ፡ መሬቱም ፡ ርሶ ።

#ዡልዬት
ቲባልት ! ሮሜዎ ! ሁለቱንም ፡ ጠርተሽ ፡
ከምታስጨንቂኝ ፡ ንገሪኝ ፡ ለይተሽ '
ሮሜዎ ፡ ባሌ ፡ ነው ፡ ቲባልት ፡ ዘመዴ ፤
የቱ ፡ ነው ፡ የሞተው ፡ ተጨነቀ ፡ ሆዴ
ባለም ፡ ላይ ፡ ከሌሉ ፡ እነዚህ ፡ ሁለቱ ፡
መታከት ፡ ነውና ፡ ሁሉ ፡ ነገር ፡ ከንቱ ፡
የምጽኣት ፡ ቀን ፡ ይሁን ፡ መለከት ፡ ይነፋ ፤
አሁን ፡ ተደምስሶ ፍጥረተ ዓለም ፡ ይጥፋ፡
ባሕር ፡ ጫካ ፥ ገደል ፥ ጅረትም ፡ ተራራ ፡
ፍጡር ፡ እዬዬ ፥ በል ፡ አልቅስ ፡ ከኔ ፡ ጋራ

#ሞግዚት
ሟቹ ፡ ቲባልት ፡ ነው ፡ ካለም ፡ ላይ ፡ የሄደ
ገዳዩ ፡ ሮሜዎ ፡ ካገር ፡ተሰደደ ።

#ዡልዬት
ሮሜዎ ፡ ቲባልትን ፡ ብትዪኝ ፡ ገደለው ፡
አይችልም ፡ መንፈሴ ፡ አምኖ ፡ ሊቀበለው

💫ይቀጥላል💫
#ሮሜዎና_ዡልዬት


#ክፍል_ስምንት


#ሞግዚት
የተሠራውን ፡ ጉድ ፡ እንግዲህ ፡ ዕወቂው
እርገሚው ፡ ሮሜዎን ፡ ከልብሽም ፡ ናቂው
በቀልሽን ፡ ቂምሽን ፡ አድርጊው ፡ የጸና ፤
በውነቱ ፡ ሮሜዎ ፡ ሰው ፡ አይደለምና ።
አብነት ፡ ይሁንሽ ፡ ይህ ፡ መጥፎ ፡ ደመኛ
ሰውን ፡ አትመኝ ፡ እንግዲህ ፡ ዳግመኛ ፡
ፍቅሩም ፡ደግነቱም ፍሬ ቢስ ፡ ነው ፡ ከንቱ
ፈጽሞ ፡ ሰው ፡ የለም መጥፎ ፡ነው ፡ ሰዓቱ
እንዲህ ፡ ያለ ፡ ነገር ፡ ሮሜዎ ፡ ሲሠራ ፡
ማነው ፡ የሚታመን ? ማነው ፡ ባለአደራ ?

#ዡልዬት
ምንም ፡ አልተገኘ ፡ የሚበጀኝ ፡ ለኔ ፤
ሁለት ፡ ስለት ፡ ያለው ፡ ሰይፍ ፡ ነው ፡ ኀዘኔ
ቲባልት ፡ ባይሞት ኖሮ ሮሜዎ ፡ ይሞታል፤
ቲባልት ፡ ባይሸነፍ ፡ ሮሜዎ ፡ ይረታል!
ሮሜዎን ፡ ከልብሽ ፡ ትይኛለሽ ፡ ጥዪው ፤
ምነው ልቤን ገብተሽ መርምረሽ ብታዪው
ለኔም ፡ገዳይ ፡ ቢሆን ፡ ለናቴም ፡ ላባቴ ፡
ሮሜዎን ፡ ለመጥላት አይችልም ፡አንጀቴ
ቲባልትም ፡መጥፎ ነህ ፡ሮሜዎም አትረባ
መሪር ፡ ነው ፡ ከናንተ ፡ የሚተርፈኝ ፡ እንባ
ባሌ ፡ ካገር' ወጣ ፤ቲባልት ፡ ሞተ ፡ በፊት፤
ሐዘኔ ፡ ዐጓጕል ፡ የሌለው ፡ መድኀኒት ፡
እንደ ምን ፡ አድርጌ ደግሞስ ፡ እስከ መቼ
እኖራለሁ ፡ እኔ ፡ እናንተን ፡ አጥቼ ፡
ከቲባልት ፡ መሞት ፡ ሮሜዎ ፡ ስደቱ ፡
ከሮሜዎ ፡ ስደት ፡ ቲባልት ፡ መሞቱ ፡
ቢሆን ፡ ምን ፡ ቸግረው ፡ ሐዘኔ ፡ በተራ ፤
ለማንኛው ፡ ላልቅስ ፡ ወይ ፡ የኔ ፡ መከራ !
ዛሬ ፡ በሠርጌ ፡ ቀን ፡ ደስ ፡ብሎኝ ፡ መዋሌ
ቀረና ፡ ሰው ፡ ገድሎ ፡ እንዲሰደድ ፡ ባሌ '
ቲባልትም ፡ እንዲሞት ፡ አድርጎ ፡ ዕድሌ ፡
ሐዘን ፡ ከሆነ ፡ ለኔ ፡ የደገሰው ፡
ልቤ ፡ ሳያደላ ፡ እንባዬን ፡ ላፍስሰው ።

#ሞግዚት
በእውነት፡ሴት ልጅ ባሏን፡ከወደደች አይቀር
እንዳንች ፡ አድርጎ ፡ ነው ከልቡና ማፍቀር
ከልብ ፡ አዘንኩልሽ ፡ በጣሙን ፡ አድርጌ ፤
አለበት ፡ ገብቼ ፡ ሮሜዎን ፡ ፈልጌ ፡ .
እኔ ፡ አመጣዋለሁ ፡ እንባሽን ፡ አድርቂው
እመኝታ ፡ ቤትሽ ፡ ግቢና ፡ ጠብቂው ።
በስደተኛነት ፡ ሳይሄድ ፡ ነገ ፡ ርቆ ፡
ተሰነባበቱ ፡ ይምጣ ፡ ተደብቆ ።

#ዡልዬት
መልካም ፡ ነው ፡ ሞግዚቴ ፡ሙሽራ ፡ ሲገባ
አጊጦ ፡ ታጅቦ ፡ በዘፈን ፡ ባበባ ፡
በወግ ፡ በማዕርግ ፡ ባለም ፡ በደስታ ፡
በክብር ፡ ነበረ ፡ በብዙ ፡ እልልታ ፤
ሌሊት ፡ ጨለማውን ፡ ከለላው ፡ አድርጎ ፡
የኔ ፡ ሙሽራ ፡ ግን ፡ ይግባ ፡ ተሸሽጎ ።
እንቢ ፡ ብሎ ፡ እንዳይቀር ፡ጠርተሽ ፡ ስታመጪው
እንቺ ፡ ለምልክት ፡ቀለበቴን ፡ ስጪው ፡
(ቀለበቷን ፡ ሰጠቻት)

#አባ_ሎራ (ባባ ሎራ ፡ ቤት)
ሮሜዎ ፡ ብቅ ፡ በል ፡ውጣ ፡ ከጨለማ ፤
የፍርዱን ፡ ቃል ፡ ይዤ ፡ መጣሁ ልጄ ስማ

#ሮሜዎ
ሳልሰማው ፡ ቢዘገይ ፡ ይሻለኝ ፡ ነበረ ፤
ፍርዱ ፡ ምን ፡ ዐይነት ነው ? ልቤ ፡ ተሸበረ

#አባ_ሎራ
መስፍኑ ፡ ፈቀደ ፡ በቀላል ፡ ሊቀጣ ፤
የሞት ፡ ፍርድ ፡ ቀርቶ ፡ካገር ፡ እንድትወጣ

#ሮሜዎ
ጨካኝ ፡ ቅጣት ፡ እንጂ ፡ ከሞትም ፡ የከፋ
ይህ ፍርድ መሪር ነው ያስቈርጣል ፡ ተስፋ
ዥልዬት ፡ ካለችበት ፡ ከተማ ፡ ወጥቼ ፡
ስደተኛ ፡ ሆኜ ፡ አገሬንም ፡ ትቼ ፡
የምኖረው ፡ ኑሮ ፡ እንደ ፡ ምን ፡ ይገፋል ፣
ቀኑና ፡ ሰዓቱ ፡ ደቂቃው ፡ መች ፡ ያልፋል ፡
እንዴት ፡ እችላለሁ ፡ ዡልዬትን ፡ ለመርሳት
ሲኦል ፡ ነው ፡ ኵነኔ ፡ ሞት ፡ገሃነመ ፡ እሳት

#አባ_ሎራ
ደስታህ ፡ ቀረና ፡ በማመስገን ፡ ፈንታ ፡
ለምን ፡ ትረሳለህ ፡ የእግዜርን ፡ ውለታ ፡
ዐዋጁ ፡ የሚያዘው ፡ የሞት፡ ቅጣት ፡ ነበር'
ለምን ፡ አታስብም ፡ ይህን ፡ ትልቅ ፡ ነገር ፡
ሄደህ ፡ ብትቀመጥ ፡ በማንቱ ፡ ከተማ ፡
አገሩ ፡ ጥሩ ፡ ነው ፡ በጣም ፡ የሚስማማ
ልጄ ሆይ ፡ ቅጣቱ ፡ በጣም ፡ የቀለለ ፡
ጥሩ ፡ ነው ፡ ሺ ፡ ጊዜ ፡ ከሞት ፡ የተሻለ ።

#ሮሜዎ
ያስቡት ፡ አባቴ ፡ ነገሩን ፡ ያስተውሉት ፤
ምኑን ፡ ነው እርስዎ ቀላል ነው ፡ የሚሉት

#አባ_ሎራ
ብስጭት ፡ አታብዛ ፡ በጣም ፡ አትናደድ ፤
ከመሞት ፡ ይሻላል ፡ ሺ ፡ ጊዜ ፡ መሰደድ
ልጄ ፡ ዓለም ፡ሰፊ ፡ ነች ወጥተህ ከቬሮና
የትም ፡ ሄደህ ፡ መኖር ፡ ትችላለህና ።

#ሮሜዎ
ወጥቼ ፡ ከሄድኩኝ ፡ እኔ ፡ ከቬሮና ፡
ውሸት ፡ ነው ፡ አባቴ ፡ ምን ፡ዓለም ፡ አለና፡
ሕይወት ፡ ነው ፡ አይበሉት የምኖረው ኑሮ
ዓለም ፡ እዚህ ፡ ቀረ ፡ ከሚስቴ ጋር አብሮ'
ሰው ነህ እንስሳ ዕንጨት አበባና ፡ቅጠል ፡
ፀሐይ ፡ ተከልሎ ፡ አየር ፡ ሳይቀበል ፡
የኖረ ፡ እንደ ፡ ሆነ ፡ ይሞታል ፡ ይደርቃል፤
ለኔም ፡ እንደዚህ ነው ፡ ስደት የሚሉ፡ ቃል
አገሬ ፡ ንብረቴ ፡ አየሬ ፡ ፀሓዬ ፡
ዓለሜ ፡ ትንፋሼ ፡ ሕይወቴ ፡ ሰማዬ ፡
የነበረችውን ፡ ዝልዬትን ፡ አጥቼ ፡
እሷ ፡ ካለችበት ፡ ከተማ ፡ ወጥቼ ፡
መሄዴ ፡ ከሆነ ፡ እሷም ፡ ከኔ ፡ ርቃ ፡
ነጣጥለው ፡ ከለዩን ፡ የኔ ፡ ነገር ፡ በቃ ።
ሕይወቴም ፡ ኑሮዬም ፡ ሞተ ፡ ተበላሸ ፤
ደስታ ፡ ተለየኝ ፡ ከኔ ፡ ርቆ ፡ ሸሸ ፡
እንግዲህ ፡ መቆሜ ፡ ለምንም ፡ አይበጅ ፤
ይህን ፡ኑሮ ፡አይበሉት መናወዝ ነው እንጅ
ፍርድ ፡ ማሻሻያ ፡ የተባለው ፡ ዘዴ ፡
ከመርዝም ፡ ይብሳል ፡ ከጦር ፡ ከጐራዴ '
ስደት ፡ የሚሉ ፡ ቃል ፡ ጨለማ ነው ፡ ገደል
እኔን ፡ አስጨንቆ ፡ መጣ ፡ ለመግደል ።

#አባ_ሎራ
እረ ፡ ስማኝ ፡ ልጄ ፡ ምክሬንም ፡ ተቀበል ፡
ሞትና ፡ መሰደድ ፡ እኩል ፡ ነው ፡ አትበል

#ሮሜዎ
ተመልሰው ፡ ስደት ፡ ወደሚባለው ፡ ቃል ፡
ሊመጡ ፡ ነውና ፡ አባቴ ፡ ይበቃል ፡
ምን ፡ አደከመዎት ፡ በቃ በዚህ ፡ ዓለም ፡
እኔን ፡ የሚያጥናና ፡ ምንም ፡ ነገር ፡ የለም
ከሞት ፡ የባሰ ፡ ነው ፡ የመከራ ፡ ጭቃ ፤
የሮሜዎ ፡ ነገር ፡ ተከተተ ፡ በቃ ።

#አባ_ሎራ
ዐውቃለሁ ፡ እንዲሆን ፡ ስደትህ ፡ መራራ ፤
ግን ፡ መድኀኒት ፡ አለው ለዚህ ፡ ለመከራ'
ዕረፍት ፡ እንድታገኝ ፡ ባሳብ ፡ በኅሊና ፡
የደረሰብህን ፡ ጭንቅህን ፡ እርሳና ፡
ልብህን ፡ መልሰው ፡ ወደ ፡ ፍልስፍና ።

#ሮሜዎ
ዡልዬትን ፡ ፈጥሮልኝ ካልሰጠኝ ፡ አምጥቶ
የመስፍኑን ፡ ብይን ፡ በጥበብ ፡ አጥፍቶ ፡
እኔን ፡ ካላዳነኝ ፡ የርስዎ ፡ ፍልስፍና ፡
ለምንም ፡ አይበጀኝ ፤ የለውም ፡ ርባና ።
(የዡልዬት'ሞግዚት'ከደጅ'ሆና'በር መታች)

#አባ_ሎራ
ተነሣ ፡ ሮሜዎ ፡ ግባ ፡ ወደ ፡ ጓዳ ፤
ስማ ፡ በር ፡ ይመታል ፡ መጣብን ፡ እንግዳ
ተደበቅ ፡ በቶሎ ፡ ጥግ ፡ ይዘህ ወደ ፡ ጐን
ይይዙሃልና ፡ ያገኙህ ፡ እንደሆን ።
(በሩ ይመታል)

#ሮሜዎ
በስደት ፡ ከሆነ ፡ እኔ ፡ የምቀጣ ፡
ምን ፡ ያስጨንቀኛል ፡ የፈቀደው ፡ ይምጣ

#አባ ፡ ሎራ ።
ለምን ፡ ትሆናለህ ፡ አንተ ፡እንደዚህ ፡ ደረቅ
እባክህ ፡ ግባና ፡ በቶሎ ፡ ተደበቅ ፡ (ሮሜዎ ሄደ)
እንዲህ ፡ ባሁን ፡ ሰዓት ፡ የመጣ ፡ በማታ ፡
ማነው ፡ በጨለማ ፡ በሬን ፡ የሚመታ ?

#ሞግዚት
መጥቻለሁና ፡ ልካኝ ፡ እመቤቴ ፤
የዡልዬት ፡ ሞግዚት ፡ ነኝ ያስገቡኝ ፡ አባቴ

#አባ ፡ ሎራ ።
እንኳን ፡ ደኅና መጣሽ ፡ ነይ ግቢ ወዳጄ፤
(ከፍተውላት ገባች)

#ሞግዚት
ሮሜዎን ፡ አጣሁት ፡ ብፈልገው ፡ ሄጄ ።
ይንገሩኝ ፡ አባቴ ፡ ከመሸ ፡ አሁን ፡ ማታ
አይተው ፡ እንደ ፡ ሆነ ፡ ያለበትን ፡ ቦታ ፡

#አባ ፡ ሎራ ።
በሐዘኑ ፡ ሰክሮ ፡ ያለቅሳል
👍1
#ሮሜዎና_ዡልዬት


#ክፍል_ዘጠኝ


#አባ_ሎራ
ለምን ፡ ታስባለህ ፡ እንዲህ ፡ ያለ ፡ ነገር ፤
ብላሽ ፡ ሰው ፡ አትሁን ፡ ሲመክሩህ ፡ ተመከር ,እንደ ፡ ሴት ፡ አታልቅስ ፡ እንዳውሬ ፡ አትቈጣ
እንደ፡እብድ፡አትበሳጭ ፥ ከሰው፡ ግብር፡ አትውጣ
ትመስለኝ ፡ ነበረ ፡ በውነቱ ፡ ጠንካራ ፤
ሰው ፡ ለምን ፡ ይረባል ፡ ካልቻለ ፡ መከራ
መቀጣት ፡ ከወደድህ ፡ በገዛ ፡ እጅህ ፡ ሞተህ ፡
ስለምን ፡ ገደልከው ፡ ቲባልትን ፡ ተዋግተህ ?
በገዛ ፡ እጅህ ፡ ብትሞት ፡ ባለማመዛዘን ፡
መግደልህ ፡ እኮ ፡ ነው ሚስትህን ፡ በሐዘን '
ለዚህ ፡ ነው ፡ ልጄ ፡ ሆይ ፡ ኅሊናና ፡ አእምሮ ፡
ከእግዜር ፡ የተሰጠ ፡ ለሰው ፡ ልጅ ፡ ተፈጥሮ'
ዡልዬት ፡ ጠልታኛለች ፡ ብለህ ፡ ስትሠጋ፡
ሰው ፡ ልካ ፡ ጠራችህ ምሕረትን ፡ አድርጋ
ቲባልት ፡ ሊገድልህ ፡ ቢመጣ ፡ ደንፍቶ ፡
በገዛ ፡ ጥጋቡ ፡ ወደቀ ፡ ተወግቶ "
ባንተም የሞት ቅጣት ሊወድቅ የነበረው
በስደት ፡ ለውጦ ፡ መስፍናችን ፡ ሻረው '
ብትመለከተው : በውነቱ ፡ የት ፡ አለ ፤
እንዳንተ ፡ የቀናው ፡ በጣም ፡ የታደለ ፡
ተጠንቀቅ ፡ በውነቱ ፡ ልጄ ፡ በጣም ፡ ሥጋ
ሳታውቀው ፡ ብትቀር ፡ የደስታን ፡ ዋጋ ፡
ኑሮህ ፡ይበላሻል ፡ አለመጠን ፡ ፍራ ፡
ምን ፡ጊዜም ፡ አይለቅህ ፡ ጭንቅና ፡ መከራ ።
ሚስትህን ምከራት ፡ እንዳትሞት ፡ አልቅሳ
መምሸቱ፡ነውና፡ በል ቶሎ ፡ ተነሣ፡
ነገ ፡ ግን ፡ ለመሄድ ፡ ልብህ ፡ይሰናዳ ፤
ውጣ ፡ ከቬሮና ፡ ሌሊት ፡ በማለዳ
ተዛውረህ ተቀመጥ ፡ ሄደህ ፡ ወደ ፡ ማንቱ
እኛ ፡ ጊዜ ፡ አግኝተን ፡ ሲመቸን ፡ ሰዓቱ ፡
ወገኖቻችሁን ፡ በምክር ፡ አስታርቀን ፡
ጋብቻችሁንም ፡ በገሃድ ፡ ኣስታውቀን ፡ .
ላንተም ፡ ከመስፍኑ ፡ ምሕረትን ፡ ጠይቀን
እንጣጣራለን ፡ ቶሎ ፡ እንድትመለስ
እግዜር ፡ይጠብቅህ በል እስከዚያ ፡ ድረስ
አሁን ፡ ወደ ፡ ዡልዬት ፡ በቶሎ ሂድ ፡ ተነሥ

የካፑሌ ሚስት #ካፑሌ #ፓሪስ

#ፓሪስ
ጉዳዩ ዘገየ ፡ በመዋል' በማደር ፤
ታዲያስ እንዴት ፡ ሆነ ፡የጋብቻው ፡ ነገር ?

#ካፑሌ
ነገሩን ፡ ለዡልዬት ፡ ሳልነግር ፡ መቅረቴ ፡
ወድጄን ፡ አይደለም ፡ እንዲህ ፡ መዘግየቴ
በቲባልት ፡ መሞት ፡ አዝናለች ፡ በብርቱ ፤
ታፈቅረው ፡ ነበረ ፡ ከልቧ ፡ በውነቱ ፡
ስለዚህ ፡ ሐዘኑ ፡ ጥቂት ፡ ሳይረሳ ፡
አልቻልኩም ፡ ጕዳዩን ፡ ለጊዜው ፡ ላነሣ ፡
አድርግልኝና ፡ ከልብህ ፡ ይቅርታ ፤
እኔ ፡ እጨርሳለሁ ፡ ነገሩን ፡ አንድ ፡ አፍታ

#ፓሪስ
እውነት ፡ ነው ሐዘኑ ፈጽሞ ፡ አልተመቸም
ተስማምተንበታል ይህን ጕዳይ ፡ መቼም
እሷም እንቢ እንዳትል ፡ እናንተ ፡ አስቡበት

#የካፑሌሚስት _ ።
ግድ የለም ሠርጋችሁ ይሆናል በፍጥነት

#ካፑሌ
ፓሪስ ሆይ አትሥጋ አይዞህ ይህን ጕዳይ
መሄድ ፡ ትችላለህ ፡ ጥለኸው ፡ በኔ ፡ ላይ
እንዴት ፡ ትወጣለች ፡ ከኔ ፡ ፈቃድ ፡ ልጄ ፤
ያቀረብኩላትን ፡ መርጬ ፡ ወድጄ
ያላንድ ፡ ቅሬታ ፡ አለባት ፡ መቀበል ፤
እንዲያውም ፡ እንፍጠን ፡ ዛሬ ነገ ፡ አንበል
በይ ፡ ፍጠኝ ፡ ሚስቴ ፡ ወደ ፡ ልጅሽ ፡ ሂጂ
በዘዴ ፡ በርጋታ፡ነገሩን አስረጂ ፡
መልካሙ ፡ ልጃችን 'ፓሪስ ፡ አንቺን ፡ ወዶ ፡
እኔም ፡ ደስ ፡ ብሎኝ ፡ አባትሽም ፡ ፈቅዶ ፡
ይኸው ፡ በዚህ መሰሞን ሊያገባሽ ፡ ነውና
ተዘጋጂ፡ በያት ፡ በሙሉ ፡ ልቡና '
በል ፡ አንተም ፡ ንገረኝ ፡ እንደምትፈልገው
ሰርጉ ፡ እንዲፈጸም ለመቼ እናድርገው ?

#ፓሪስ
እንደ ፡ እኔ ፡ ሰርጋችን ፡ የራቀ ፡ ከሚሆን ፡
ቢፈጸም ፡ ይሻላል ፡ አሁን ፡ በዚህ ፡ ሰሞን

#ካፑሌ
እንግዲያው መልካም ነው ባጭር እንደግስ
ተክሊሉም ፡ ይፈጸም ፡ በሚመጣው ፡ ኀሙስ ፡
ጃጃታ ፡ አላበዛም ብዙም ፡ ሰው ፡ አልጠራ ፤
ልጄን ፡ እድራለሁ ፡ ብዬም ፡ አላወራ ፡
ሐዘን ፡ ስለ ፡ ሆነ ፡ቲባልት፡ በመሞቱ ፡
ቅር ፡ ያሰኛልና ፤ ዘመድ ፡ በጥቂቱ ፡
በድብቅ ፡ እንጥራ ፡ ነገር ሳናበዛ ፤
እንደዚህ 'ብናደርግ ፡ ወሬው ፡ ሳይነዛ ፡
ጉዳያችን'ያልቃል፡ያግር፡ ሰው ፡ ሳይሰማ ፤
እንግዲህ ፡ መልካም ፡ ነው ፤ በዚሁ 'እንስማማ ።

#ፓሪስ
እኔም ፡ እስማማለሁ ፡ ይሁን ፡ በዚሁ ፡ ቀን
በሉ ፡ እስከዚያው፡ድረስ፡እግዜር፡ይጠብቀን ። (ሄዳ).

#ካፑሌ ፡ (ለሚስቱ )
እንደዚህ ፡ ያለ ፡ ባል ፡ ትልቅ ፡ ሰው ፡ የበቃ
ቢሄዱ ፡ አይገኝም ፡ እግር ፡ እስቲነቃ ፡
በይ ፡ ቶሎ ፡ ፍጠኚ ፡ ወደ ፡ ልጅሽ ፡ ሂጂ ፤
ነገ ፡ ጧት ፡ አሳቧን ፡ ልቧን ፡ አዘጋጂ ።

#ሮሜዎና #ዡልዬት ፡ (በዥልዬት ' መኝታ ፡ ቤት) ።

#ዡልዬት
አይዞህ፡አትቸኵል ፡ አልነጋም ፡ ሌሊቱ ፤
ቁጭ ፡ በል ፡እናውጋ ፡ ገና ፡ ነው ፡ ሰዓቱ ፡
ተመልከት ጨለማ መሬቱን
ሲሸፍን ፡
የሰማናትም ፡ ወፍ ፡ አሁን ፡ ስትዘፍን ፡
ዞትር ፡ ልማዴ ፡ ነው ፡ ሌሊቱ ፡ ሳይነጋ ፡
መጮህ ፡ ትወዳለች ፡ እመነኝ ፡ አትሥጋ

#ሮሜዎ
ይህች ፡ የንጋት ፡ ወፍ ፡ ነች ፡ አሁን ፡ የጮኸችው ፤
ትክክል ፡ ይታያል ፡ ዡልዬት ፡ ተመልከችው
ሰማይ ወገግ፡ አለ ፡ ያው በምሥራቅ በኩል ፤
ሰዓቱ ፡ ደረሰ ፡ እንግዴህ ፡ ልቸኵል ፡
በቬሮና ፡ አድሬ ፡ ቢያገኙኝ ፡ ሳልወጣ ፡
መስፍኑ ፡ ፈርደዋል ፡ በሞት ፡ እንድቀጣ ፡
ልዳን ፡ ያልኩ ፡ እንደሆን ፡ ሕይወቴን ፡ ወድጄ ፡
መሄድ ፡ ይገባኛል ፡ አሁን ፡ ተሰድጄ ።

#ዡልዬት
እኔ ፡ መች ፡ አጣሁት ፡ ይህ ፡ ያሁኑ ፡ ብርሃን ፡
የሰማይ ፡ ፋና ፡ ነው ፡ የኮከብ ፡ ውጋጋን
ሌሊት ፡ በጨለማ ፡ ሳይነጋ ፡ ሌሊቱ ፡
ለምን ፡ ትሄዳለህ ፡ አሁን ፡ ወደ ፡ ማንቱ ፡
አይዞህ ፡ እንጫወት ሌቱ ፡ አልነጋም ፡ ገና
ጊዜ ፡ አለን ፡ እስኪታይ ፡ የንጋቱ ፡ ፋና ።

#ሮሜዎ
ዘፈኑ ፡ ሲወጣ ፡ አልሰማንም ፡ ካፍ
አልነጋም ፡ ሌሊቱ ፡ አልጮኸችም ፡ ወፍ፡
ይህም ፡ በሰማይ ላይ የሚታይ ፡ ውጋጋን አይደለም ፡ የመጣ ፡ ከፀሓይዋ ፡ ብርሃን ፡
ብለን ፡ እንካደው ፤ አምኜ፡ ልቀበል !
ሳልወጣ ፡ ይያዙኝ ፡ ተይዤም ፡ ልገደል "
ካንቺ ፡ ተለይቼ ፡ የሐዘን ፡ ኵነኔ ፡
ከሚያገኘኝ፡ መሞት ፡ እመርጣለሁ ፡ እኔ ።
አልፈራም ፡ ፈጽሞ ፡ በሞት ልቀጣ
ዡልዬት ፡ ከፈቀደች ፡ የፈለገው ፡ ይምጣ ፡
ወፎች አልተንጫጩም ሌሊቱም ፡ አልነጋ
ዡልዬት ጨዋታ አምጪ እንግዴህ እናውጋ፡

#ዡልዬት
እኔ ፡ ብዬ ፡ ነበር ፡ ገና ፡ ነው ፡ ሌሊቱ፤
አሁን ፡ ገና ፡ታየኝ ፡ ትክክል ፡ መንጋቱ ፡
ንጋት ፡ ነው ፡ የመጣው ፡ ሂድ ፡ ቶሎ ፡ ተነሣ፤
አምልጠህ ፡ ሽሽ ፡ ቶሎ ፡ ብረር ፡ በግሥገሣ ፡
እየው ፡ ተመልከተው ፡ የንጋት ፡ ወገግታ፤
ጨለማውን ቀዶ፡ ሄደ ፡ እየበረታ ፡
አስተውለው ፡ መሬቱ ፡ ሲታየን ፡ ተገልጦ ፤
አሞኘችኝ፡ ወፏ ድምፅዋ ፡ ተለውጦ ፡
ፍጠን ፡ ቶሎ ውጣ እየው፡እንደ፡ ነጋ ፤
ተነሥ ፡ ቶሎ ፡ ጥፋ፤ አይንካህ ፡ አደጋ ።

#ሞግዚት
እናትሽ ፡ ነቅተዋል' እመቤቴ ፡ ዕወቂ፤
መንጋቱ ፡ ነውና ' በጣም' ተጠንቀቂ "
ደኅና ሰንብት ፡ ልበል ፡ እኔው ፡ አስቀድሜ
እንግዴህ ፡ ደኅና'ሁን'ሮሜዎ ፡ ወንድሜ ።

#ሮሜዎ
ዡልዬት ደኅና ሁኝ ፡ ደኅና ሰንብች ፡ ፍቅሬ

#ዡልዬት
አደራ ፡ እንዳገኘው ፡ እኔ ፡ ያንተን ፡ ወሬ ፡
ሁል ፡ ጊዜ ጻፍልኝ ፡ መሆንህን ፡ ጤና ፤
መቼ ፡ እንደማገኝህ ፡ አላውቀውምና ።

#ሮሜዎ
መቼም ፡ ቢሆን ፡ ካንቺ ፡ አይለይም ፡ ልቤ
እጽፍልሻለሁ ፡ ሁል ፡ ጊዜ ፡
ደብዳቤ ።

#ዡልዬት
አንተ ፡ ስታስበው ፡ ወደ ፡ ፊት ፡ ዳግመኛ ፡
እንገናኛለን ፡ ትላለህ ፡ ወይ ፡ እኛ?

#ሮሜዎ
አምናለሁ ፡ ፍቅሬ ፡ ሆይ ፡ አምላክ ፡ እንዲራራ፤
ትምህርት ፡ ይሆነናል 'ያሁኑ ' መከራ ።

#ዡልዬት
የሆንኩትን ፡ እንጂ ፡ እኔ ፡ ግን ፡ ለራሴ ፤
መጥፎ' መጥፎ ነገር ያስባል' መንፈሴ

#ሮሜዎ
ያገኘን ፡ መከራ ፡ ስለ ፡ ሆነ ፡ ብርቱ ፡
ከመንፈሳችን ውስጥ አይጠፋም
ስሜቱ ፤
ዡልዬት ፡ ደኅና ፡ ሁኝ ፡ ረፈደ ፡ ሰዓቱ ፡(ሄዳ).

💫ይቀጥላል💫
#ሮሜዎና_ዡልዬት


#ክፍል_አስር


የካፑሌ ፡ ሚስት (የዡልዬት እናት)
ወዴት ፡ ነው ፡ ያለሽው ፡ ልጄ ፡ ተነሣሽ ፡ ወይ ?

#ዡልዬት
ይኸው ፡ ተነሣሁኝ ፡ ምነው ፡ እናቴ ሆይ ?
(ለብቻዋ ፡ ቀስ ብላ)
ምን ፡ ነካት ፡ እናቴ ፡ እንዲህ ፡ ጧት ፡ ተነሥታ ፈልጋኝ አታውቅም በማለዳ መጥታ ።
(የካፑሌ ሚስት ' ወደልጅዋ፡ወደ፡ዡልዬት መኝታ' ቤት፡ገባች

#የካፑሌ_ሚስት
ዐፈር ፡ አስመሰለሽ ፡ የቲባልት ፡ ሐዘን ፡
ያስፈልጋል ፡ ልጄ ፡ ማሰብ ፡ ማመዛዘን '
እንባ ፡ ቢያፈሱለት ፡ ቢያለቅሱለት በጣም
ሰው ፡ አንዴ ከሞተ ተመልሶ ፡ አይመጣም
ሐዘን ፡ የሚያስረሳ ፡ ደስ ፡ የሚያሰኝ ፡ ወሬ
ይዤ ፡ ወዳንቺ ፡ ዘንድ ፡ መጥቻለሁ' ዛሬ "

#ዡልዬት
እናቴ ፡ ንገሪኝ ፡ እንደ ፡ ምን ፡ ያለ ፡ ነው ?

#የካፑሌ_ሚስት
በቲባልት ፡ መሞት ፡ በብዙ ፡ ያዘነው ፡
ልብሽ ፡ እንዲጽናና ፡ በጣም ፡ በማሰቡ ፡
መልካሙ ፡ አባትሽ ፡ አላረፈም ፡ ልቡ ፤
በዚሁ ፡ ምክንያት ፡ ሳይውልም ፡ ሳያድር ፡
ቈርጧል ለጥሩ ባል ኀሙስ አንቺን ሊድር
ባልሽ ፡ የሚሆነው ቆንዦ ነው ፡ ጌታ ሰው
በዘርም ፡ በገንዘብ ፡ ምንም ፡የማያንሰው !
እንዲያውም ፡ ገልጨ ፡ ልንገርሽ ፡ ካሁኑ ፤
መልካሙ ፡ፓሪስ ፡ ነው ፡ ወጣት ፡ መኰንኑ

#ዡልዬት
እናቴ ፡ ሆይ ፡ምነው ፡ በፊት ፡ ሳንማከር ፡
እንደ ፡ ምን ፡ ይሆናል ፡ እንዲህ ያለ ፡ ነገር
አስቀድመን ፡ እኛ ፡ ተጫጭተን ፡ በደንቡ፡
ሳላውቀው ሳያውቀኝ ፡በፍጥነት ፡ ተጋቡ !
እንዴት ፡ ትላላችሁ ፡ እንዲህ ፡ በችኰላ ?
አሁንም ፡ በቶሎ ፡ ፈልጉለት ፡ መላ'
እኔ ፡ አልችልምና ፡ ለማግባት ፡ በቶሎ ፤
አባቴን 'ንገሪው ፡ እንደ ፡ ምንም ፡ ብሎ
ቃል ቢኖር ምናልባት ለፓሪስ የሰጠው
አንድ' ዘዴ ፡ ፈጥሮ ፡ ቶሎ ፡እንዲለውጠው

#የካፑሌ_ሚስት
አፍሽን ፡ አታጥፊ ፡ ምክንያት ፡ አታምጪ '
ያለቀ ፡ ነገር ፡ ነው ፡ ዐርፈሽ ፡ ተቀመጪ ።

#ዡልዬት
አድምጪኝ ፡ እናቴ ፡ እንግዲያውስ ፡ ስሚ
አባቴም ፡ አይልፋ ፡ አንቺም ፡ ኣትድከሚ'
የመጣ ፡ ቢመጣ ፡ መቼም ፡ቢሆን ደግሞ
እኔ ፡ አላገባም ፡ ፓሪስን ፡ ፈጽሞ ።

#የካፑሌ_ሚስት
አልገባም ፡ ጨርሼ ፡ እኔ ፡ በዚህ ፡ ጣጣ ፤
ንገሪው ፡ ላባትሽ ፡ ይኸው ፡ወዲህ ፡ መጣ

#ካፑሌ ፡ (ገባ)
ምነው ፡ ምን ሆናችሁ ? በይ ልመለስ ሄጄ
ታዲያስ ፡ ነገርሻት ፡ ወይ ነገሩን ፡ ለልጄ ?

#የካፑሌ_ሚስት
እኔ ፡ ከሷ'ጋራ ፡ አልችልም ፡ ክርክር ፤
ትችል ፡ እንደ ፡ ሆነ ፡አስረዳት ፡ በምክር ።

#ካፑሌ
እስቲ ፡ እኮ ፡ ንገሪኝ ፡ ምንድነው ፡ ነገሩ ፡
አሁን ፡ ምን ፡ ይባላል ፡ ደርሶ ፡ ግርግሩ ።

#የካፑሌ_ሚስት
ትችል ፡ ትመስላለህ አንተ ፡ ደግሞ ፡ ደርሶ
የምሥራች ፡ « እንቢ» ፡ ብላለች ፡ ጨርሶ ፡
የመጣ ፡ ቢመጣ ፡ ይልቁንም ፡ ደግሞ ፡
አላገባም ፡ አለች ፡ ፓሪስን ፡ ፈጽሞ ።

#ካፑሌ
እግራችንን ፡ ስማ ፡ እኛን ፡ አመስግና ፡
በትልቅ ፡ ደስታ ፡ መቀበል 'ቀረና ፡
እንቢ ፡ አለች ፡ ብትይኝ ጆሮዬም ፡ አይሰማ
እስቲ ፡ ልስማው ፡ እኔ ፡ ትናገረው ፡ ደግማ

#ዡልዬት
ለክፋት ፡ አይደለም ፡ አትቈጣ ፡ አባቴ ።

#ካፑሌ
እረግ ፡ የኛ ፡ ሕፃን ፡ ትንሿ ፡ ማሚቴ ፡
የማነሽ ፡ ለዛ ፡ ቢስ ፡ የማነሽ ፡ ወልጋዳ ፤
የማነሽ ፡ አመዳም ፡ የማነሽ ፡ ገዳዳ'
ባለወግ ፡ አድርገን እኛ ፡ ነን ያጠፋን ፡
ብታውቂው ፡ ባታውቂው ኧረ ምን ፡ አለፋን
በግድ፡ ነው ፡ እንጂ፡ በኅይል ፡ የምንድር ፡
መች ፡ ያስፈልግና ፡ ይህ ፡ ሁሉ ፡ንግግር
ነገ ፡ በማለዳ ፡ ተዘጋጅተሽ ፡ ውጪ ፣
ከተክሊሉ ፡ ቦታ ፡ ዐውቀሽ ' እንድትመጪ,
ታዛዤ ፡ ነሽና ፡ የወለድኩሽ ፡ ልጄ ፣
እኔ ፡ እድርሻለሁ ፡ በኀይል' አስገድጄ ፤
ለወግ ፡ መጠየቄ ፡ ቅብጠት ፡ነው ፡ አብጄ
እስከዚያ ፡ ድረስ ፡ ግን ፡ በፊቴ ፡ አትለፊ ፤
ዐይንሽን ፡ አልየው ፡ ካጠገቤ ፡ ጥፊ ።

#ዡልዬት
ነገሩን ፡ ላስረዳህ ፡ አባቴ ፡ አድምጠኝ ፤
ጋብቻው ፡ ፈጠነ ፡ ጥቂት ፡ ጊዜ ፡ ስጠኝ

#ካፑሌ
ነገርሽ እሬት ነው ፡ መሪር ነው ፡ ኮምጣጣ
ካፍሽ ፡ ካንደበትሽ ፡ አንድ ፡ቃል፡ አይውጣ'
ሴት ልጅ እንቢ፡ብትል፡አለው አንድ አገባብ
መች ተሠርቶ ያውቃል እንዲህ፡ያለ ጥጋብ
ዘሩ ፡ የታወቀ ነዉ መልኩ ፡ የሚያኰራ ፡
ገንዘብ ፡ የተረፈው ፡ ስሙ ፡ የተጠራ፡
ደኅና ፡ ባል ፡ ፈልጎ ፡ በስንት ፡ መከራ፡
አባቷ ፡ ሲያመጣ ፡ ወዲያ ፡ ወዲህ ፡ ዞሮ '
ከቤት ፡ ተወዝፋ ፡ የኛ ፡ ሴት ፡ ወይዘሮ ፡
እኔ ፡ ባል ፡ አልሻም ፡ ትላለች ፡ ሞጋጌ ፤
መካን ፡ ሰው ፡ ይሻላል ከመውለድ ፡ ባለጌ
ጥኀጋብሽ ፡ ነው ፡ እኮ ደሜን ፡ የሚያፈላው ፤
ምኑ ፡ ነው ፡ እባክሽ ፡ፓሪስ ፡ የሚጠላው ?
ያለባል ፡ ለመኖር ፡ ከሆንሽ ፡
የምትወጂ ፡
ምን ፡ ቸገረኝ፡ እኔ ፡ ወደ ፡ ገዳም ፡ሂጂ ፡
ነገር ፡ ግን ፡ ከሆነ ፡ ማግባትሽ ፡ የማይቀር ፡
የመረጥኩልሽን ፡ ይገባሻል ፡ ማፍቀር ፡
ያላንድ ፡ ክርክር ፡ ያላንድ ፡ ቅሬታ ፡
ፈቃዴን ፡ መቀበል ፡ አለብሽ ፡ ግዴታ ።
የምትይ ፡ ከሆነ ፡ የኔን ፡ ፈቃድ ፡ እንቢ ፡
ከዛሬ ፡ ጀምረሽ ፡ ሂጂ ፡ ገደል ፡ ግቢ ፤
ዐይንሽን ፡ አልየው ፡ በዚህ ፡ በኔ ፡ ግቢ ።
የካፑሌ ፡ ሚስት ።
ቀስ ፡ ብሎ ፡ ነው ፡ እንጂ ፡ አባት ፡ ከመከረ ፡
አንተም ፡ አበዛኸው ፡ ነገርህ ፡ ከረረ ።
ካፑሌ ።
አትግቢ ፡ ፈጽሞ ፡ አንቺ ፡ በኔ ፡ ሥራ ፤
ሂጂ ፡ ወደ ፡ ጓዳ ፡ ከሴቶቹ ፡ ጋራ ፡
ቀኑን ፡ ሙሉ ፡ ባሳብ ፡ ሌሊቱን ፡ በሕልሜ ፡
ባል ፡ ስፈልግላት ፡ በመኖር ፡ ደክሜ ፡
በስንት 'ዐይነት ፡ ዘዴ ፡ እኔ ፡ ተጣጥሬ፡ .
እግዚአብሔር ረድቶኝ ፡ ይኸውና ፡ ዛሬ ፡
የሚሆን ፡ ሰው ፡ ባገኝ ፡ ጨዋ ፡ባለገንዘብ፡
እሜቴ ፡ ፈጠሩ ፡ ሠላሳ ፡ ሺሕ፡ ሰበብ ።
ስሚኝ፡ እኔ ፡ ደግሞ ፡ ልንገርሽ ፡ ካሁኑ፤
እሱን ፡ ካላገባሽ ፡ ታዘቢኝ ፡ በውኑ
የትም ፡ ትሄጃለሽ ፡ አብርሬሽ፡ ከቤቴ፤
እርሜን ፡ አወጣለሁ ፡ ቆርጬሽ ፡ ካንጀቴ
ልጅና ፡ አባት ፡ ሆነን ፡ መኖራችን ፡ ቀርቶ ፡
ክጄሽ ፡ ትሄጃለሽ ፡ አልምርሽም ፡ ከቶ ፡
ስለዚህ ፡ አስቢ፡ ከልብሽ ፡ ምከሪ፤
የሚከተለውን ፡ ተመልክተሽ ፡ ፍሪ'
ካሁኑ ፡ ጀምረሽ ፡ በነገሩ፡ ሥጊ፤
ቃሌ ፡ አይታጠፍም ፡ ኋላ ፡ ልብ ፡ አድርጊ
(ካፑሌ "ከቤት " ወጥቶ ሄደ)

#ዡልዬት
እባክሽ ፡ እናቴ ፡ ለልጅሽ ፡ እዘኚ፤
ባይሆን ፡እንኳን ፡ አንቺ ፡ ከኔ ፡ ወገን ፡ ሁኚ'
ቀኑ ፡ ረዘም ፡ ይበል ጥቂት ፡ ጊዜ ስጡኝ፤
አሳቤን ፡ ሳታውቁ ፡ በከንቱ ፡ አትቁጡኝ ።

ግዴታ፡ ካልሆነ' በጣም ' ካልቸረኝ፡
እንቢ ፡ አልልምና ፡ ምክንያት ፡ ካልኖረኝ ።

#የካፑሌ_ሚስት
ዕዳሽን ፡ በጨርቅሽ ፡ እንደምትፈልጊ '
አንቺ ፡ እንደ ፡ ፈቃድሽ 'እንዳሻሽ አድርጊ ።
(እናቷም' ወጥታ ሄደች)

#ዡልዬት
ርጂኝ ፡ አንቺ ፡ እባክሽ ፡ ምከሪኝ ፡

#ሞግዚቴ
ምስጢር፡ ተካፋዬ፡አንቺ፡ነሽ ፡እናቴ '
የኛን ተክሊል ማንም አይችልም፡ሊያፈርሰው፡
ዳሩ ፡ ግን ፡ድብቅ ፡ ነው አያውቅም፡ማንም፡ሰው፡
እባክሽ ፡ ምከሪኝ ፡ ዘዴ ፡ አታጭምና ፤
ጨነቀኝ ፡ ጠበበኝ'አገኘኝ ፡ ፈተና ።

#ሞግዚት
ቃሌን ፡ ብትሰሚ ፡ ተራዬን ፡ ልናገር ፤
ሮሜዎ ፡ ሰው ፡ ገድሎ ፡ ተሰደደ ፡ ካገር፡
ልትኖሩ ፡ ከሆነ ፡ ለብቻ ፡ ለብቻ ፡
በዚሁ ፡ ይፈርሳል ፡ የናንተ ፡ ጋብቻ ፡
በዚሁ ፡ ላይ ፡ ደግሞ ፡ አባትሽ ፡ ላባቱ
👍1
ቂመኛ ፡ ነውና 'ደመኛ ፡ ጠላቱ ፤
ዕርቅ ፡ይኖራል ፡ ማለት ፡ መጓጓት ፡ ነው ፡ ከንቱ ።
ስለዚህ ፡ ፓሪስን ፡ እሺ ፡ ብለሽ ፡ አግቢ ፤
ሮሜዎን ፡ በልብሽ ፡ በቃሽ ፡ አታስቢ '
ደግሞስ ፡ ምንና፡ ምን ፡ እነዚህ ፡ ሁለቱ ፤
ፓሪስ ፡ የላቀ ፡ ነው ፡ በውበት ፡ በሀብቱ ፡
በዘር፡ በጌትነት'ይበልጣል' በሁሉ ፤
ደግሞስ ፡ ከዚህ ፡ በላይ፡ ሕግስ ፡ ቢሆን ፡
በድብቅ ፡ የሆነው ፡ አይረጋም ፡ተክሊሉ ።

#ዡልየት
እውነት ፡ ካንጀት ነው ወይ ፡ የምትናገሪ ?

#ሞግዚት
ከልቤ ፡ መሆኑን ፡ አትጠራጠሪ ።

#ዡልዬት
መልካም ፡ ነው በይ ሄደሽ ንገሪያት ለናቴ
መሄዴ ፡ ነውና ፡ በፍጥነት ፡ መውጣቴ ፡
ወደ ፡ አባ ፡ ሎራ ፡ ዘንድ በፍጥነት ፡ ደርሼ
እመጣለሁ፡በያት፡አሁን፡ተመልሼ ። (ሞግዚት ' ሄደች) "

(#ዡልዬት ብቻዋን) •
ለማ ፡ ልናገረው ፡ ምስጢሬን ፡ ገልጩ፡
ወደ ፡ አባ ፡ ሎራ ፡ ዘንድ ፡ ልሂድ ፡ እንጂ ፡
ከካህናቶች ፡ ዘንድ ፡ ቢበጅም ፡ ቢከፋ፡
የነፍስ ፡ መድኀኒት፡ ምን ጊዜም ፡ አይጠፋ

💫ይቀጥላል💫
#ሮሜዎና_ዡልዬት


#ክፍል_አስራ_አንድ

#አባ_ሎራና#ዡልየት

#ዡልዬት
ይዘኑልኝ ፡ በጣም ፡ አባቴ ፡ አባ ፡ ሎራ ፤
በኔ ፡ ላይ ፡ ዘንድሮ ፡ የመጣው ፡ መከራ ፡
ፍጻሜ ፡ የለውም ፡ ቈርጫለሁ ፡ ተስፋ፤
ይርዱኝ ፡ እባክዎ ፡ ጨርሼ ፡ ሳልጠፋ ።

#አባ_ሎራ
አዝኛለሁ ፡ ልጄ ፡ ነገሩን ፡ ሰምቼው ፤
አሁን ፡ መጥቶ ፡ ነበር ፡ፓሪስን ፡ አግኝቼው
ተክሊሉን ፡ ለናንተ ፡ ኀሙስ ፡ እንድሞላ ፡
ለምኖኝ ፡ ነበረ ፡ እንዲህ ፡ በችኰላ ፡
እንደ ፡ ምን ፡ ይሆናል ፡ብዬ ፡ መለስኩለት፤
በነገሩ ፡ በጣም ፡ አዝኛለሁ ፡ በውነት ።

#ዡልዬት
እንግዲያው ፡ ከሰሙት ፡ እንሆ ፡ ችግሬ ፤
ሥቃዬ ፡ የጠና ፡ ብርቱ ፡ ነው ፡ አሳሬ
እሄድ ነበር በውነት ሴት፡ ባልሆን' ጠፍቼ
ለፓሪስ ፡ ሊድሩኝ፡ቈርጠው 'ዘመዶቼ
አስጨንቀው ያዙኝ'ይኸው ፡በግዴታ፤
አባትም እናትም የምድር'ሁሉ፡ ጌታ ፡
እግዜር ' የዳረውን ፡ አይችልም ሊያፋታ ።
እኔና 'ሮሜዎን ፡ ሁለቴ ' ሲድረን '
በፊት፡ በጥበቡ' ከልብ' አፋቀረን ፤
ቀጥሎ ፡ በርስዎ ፡ በካህኑ' ሥልጣን ፡
ባርኮ ፡አገናኘን' በተክሊል ፡ ቃል፡ ካዳን ።
አባቴና እናቴ ፡ ይህን ፡ አላወቁ ፤
ለፓሪስ ፡ ሊድሩኝ 'እንሆ 'ታጠቁ '
እንግዴህ ፡ አባቴ ፡ እርስዎ ፡ ከግዜር ፡ ጋራ
በርትተው ፡ ያድኑኝ ፡ ከዚህ ፡ ከመከራ ፡
የማይቻል ፡ ሆኖ ፡ ካልተገኘ ፡ ዘዴ !
ብልሃቱን ፡ መፈለግ ፡ አለብኝ ፡ በግዴ ፡
ይኸው ፡ በዚህ ፡ ጩቤ ፡ ሆዴን ፡ እቀድና ፡
እገላገላለሁ ፡ ከዚህ ፡ ከፈተና

#አባ_ሎራ
ኀጢአቱ ፡ትልቅ ነው ከነፍስ ፡ የሚያስቀጣ
በገዛ ፡ እጅሽ ፡ መሞት ባሳብሽ ፡ አይምጣ
ፓሪስን ለማግባት ልብሽ ፡ ካልፈቀደ
ይህን 'ያኽል፡ በውነት ፡ ሆድሽ ፡ ካልወደደ
ግልጥ ፡ አድርጊና ፡ ንገሪኝ አትፍሪ

#ዡልዬት
እግዚአብሔር ብቻ ነው መንፈስን መርማሪ
ፓሪስን ፡ ከማግባት ፡ በውነቱ ፡ አባቴ ፡
አሁን ባሁን ፡ ፈጥኖ፡ ይምጣ ጊዜ፡ ሞቴ ፡
ልገረፍ ልሰቀል ፥ በሥቃይ ፡ ልገደል ፤
ወስዳችሁ ፡ ወርውሩኝ ጣሉኝ ወደ ፡ ገደል
የትም ፡ ተረስቼ ፡ ልዋረድ ፡ ልጕላላ ፤
ብትፈልጉ ፡ ዳሩኝ ፡ ለዱር ፡ ወሮ ፡ በላ '
ከዥብ ፡ ጋራ ፡ እሰሩኝ ፡ ከነብር ፡ ካንበሳ ፤
ካፅም 'ጋራ ፡ ቅበሩኝ፣ ከትኵስ'ሬሳ፡
እሳት አንድዳችሁ፡ አሁን ፡ ከቶ ፡ ነፍሴ ፡
አቃጥሉኝ ፡ በቁሜ ፡ ከእግር እስከ ፡ ራሴ
ወደ ፡ አራዊት ፡ ጐሬ ጣሉኝ ፡ ወዶ ፡ ዋሻ ፣
ሮሜዎ ከቀረ ምንም ፡ ባል እልሻ

#አባ_ሎራ
እኔም ፡ ባንቺ፡ነገር፡እጅግ፡ተጠብቤ
ልጄ ፡ ሆይ ፡ሐዘንሽ ተሰማኝ፡ ለልቤ ፡
የሚቻልሽ ፡ ቢሆን ፡ ልብሽ ፡ የሚደፍር ፡
አድምጭኝ ልጄ ሆይ ልስጥሽ አንድ ምክር
አሁን ፡ ተመልሰሽ ፡ ስትገቢ ፡ ከቤትሽ ፡
እንደዚህ ፡ በዪና ፡ ንገሪው ፡ ላባትሽ ፡
« ፈቃድህን ፡ ልፈጽም ፡ ፓሪስን ፡ አግብቼ፡
« መጥቻለሁና ፡ ይኸው ፡ ተጸጽቼ ፡
« እንግዴህ ፡ ይደገስ ፡ ሰርጉ ፡ ይሰናዳ »
አባትሽ ፡ ይህነን ፡ ነግረሽው ፡ ሲረዳ '
ይታረቃል ፡ ካንቺ ፡ መንፈሱም ፡ ይረጋል ፤
ከንዴቱ ፡ በርዶ ፡ ይቅርታ ፡ ያደርጋል ።
እኔም ፡ የምሰጥሽ ፡እግዚአብሔር ፡ ቢረዳ
አንድ፡ መድኀኒት ነው ምንም ፡ የማይጎዳ ፡
ልብስሽን ፡ አውልቀሽ ፡ ስትተኝ ፡ ማታ ፡
ደብቀሽ ፡ ሰው ፡ ሳያይ ጠጪው ፡ በቀስታ
ሌሊቱን ፡ ሳትሰሚ ፡ መድኀኒቱ ፡ ሠርቶ ፡
ነገ ፡ ጧት ፡ ከእንቅልፍሽ መነሣትሽ ፡ ቀርቶ
ሞተሽ ፡ ትገኛለሽ ፡ ትንፋሽሽም ፡ ጠፍቶ ፡
ወስደው ፡ ይቀብሩሻል ፡ ሞታለች ፡ ተብሎ
ለቤተ ፡ ሰባችሁ ፡ በሰፊው ፡ ተንጣሎ ፡
አምሮ ፡ በተሠራው ፡በመቃብር ፡ ቤት ፡
ተኝተሽ ፡ ቈይተሽ ፡ ቀንና ፡ ሌሊት ፡
ታዝኖ ፡ ተለቅሶልሽ ፡ ካለቀ ፡ በኋላ ፡
ዐውቀሽ ፡ ትነሻለሽ ፡ አንድ ፡ ቀን ፡ ሲሞላ
እስከዚያ ፡ እሠራለሁ ፡ እኔ ፡ ግን ፡ ተግቼ ፤
ደብዳቤ ፡ እጽፍና ፡ ሮሜዎን ፡ ጠርቼ ፡
እሱም ፡ በቬሮና ፡ ተደብቆ ፡ ገብቶ ፡
ወዳንቺ ፡ መቃብር ፡ ከኔ ፡ ጋራ ፡ መጥቶ ፡
አንቺ ፡ ሳትነሺ 'አጠገብሽ 'ደርሰን ፡
በምስጢር ፡ በፍጥነት ፡ ልብስሽን ፡ አልብሰን አንቺና ፡ ሮሜዎ ከዚህ ፡ ከከተማ
ማንም ሳይጠረጥር ማንም ሰው ሳይሰማ
ወጥታችሁ ፡ሄዳችሁ የትም ፡ በሌላ ፡ አገር
ዕረፍት ፡ አግኝታችሁ ፡ ያለ ፡ ክፉ ፡ ነገር
ኑሩልኝ ፡ በሰላም ፡ በፍጹም ፡ ደስታ ፡
ከናንተ ጋር ይሁን የእግዚአብሔር እርዳታ
ትጠጭው ፡ እንዲሆን ፡ ዡልዬት ፡ ሳትፈሪ'
አስቢና ፡ ቶሎ ፡ ገልጠሽ ፡ ተናገሪ ፡
እኔም ፡ መድኒቱን ልስጥሽ አሁን ፡ ሳልቈይ
ከዚህ በቀር ፡ ዘዴ ፡ የለኝም ፡ ልጄ ፡ ሆይ ።

#ዡልዬት
መልካም ፡ ነው ፡ አባቴ ፡ ያላንድ' ቅሬታ' .
ሳልፈራ፡እጠጣለሁ፡ በትልቅ ፡ ደስታ "
እባ፡ ሎራ ፡ ገብተው ጓዳ መድኀኒቱን በብልቃጥ አመጡ
ዶግሞስ በገዛ እጁ ለመሞት ሲቃጣ ከዚህ የተሻለ ምን ዘዴ ሊመጣ ።
እንግዲያውስ፡እንቺ ፡ ይኸው ፡ መድኀኒቱ :
እግዚአብሔር ልብሽን ፡ ያድርግልሽ ብርቱ

#ዡልዬት
አዝነው ፡ ስለ ፡ ረዱኝ ፡ ልብዎ ፡ ስለ ፡ ራራ
እግዚአብሔር ይስጥልኝ ፡ አባቴ አባ ሎራ

#አባ_ሎራ
ግድ ፡ የለሽም ፡ ልጄ ፡ ሳልዘገይ ፡ ፈጥኜ ፡
እንደ ፡ ምንም ፡ ብዬ ፡ አንድ ፡ ቄስ ፡ ለምኜ
ወደ ፡ ሮሜዎ ፡ ዘንድ ፡ጒዳዩን ፡ ሸሽጌ፥
ደብዳቤውን ፡ ጽፌ ፡ በምስጢር ፡ አድርጌ
እልክለታለሁ ፡ በቶሎ ፡ እንዲመጣ '
ዡልዬት ፡ በኔ ፡ ጣዪው ፤ የቀረውን ፡ ጣጣ

#ካፑሌ#የካፑሌ_ሚስት #ዡልዬት
(ዡልዬት ' ከውጭ መጣች)

#ካፑሌ
በጣም ያሳዝናል ባሕሪሽ ፡ ተበላሸ ፤
ወዴት ሄደሽ ኖሯል ደግሞ ፡ እንዲህ ፡ ከመሽ

💫ይቀጥላል💫
#ሮሜዎና_ዡልዬት


#ክፍል_አስራ_አራት

ለክፋት ፡ ነው ፡እንጂ አልመጣም ፡ በደኅና
እንግዴህ ፡ ልያዘው ፡ ድንገት ፡ ልድረስና ።
(ቀረበ) ።
አንተ ፡ የሞንታግ ፡ ልጅ ፡ዐመፀኛ ፡ መጥፎ
በሰላም ፡ ጸጥታ፡ የተኛውን ፡ ዐርፎ ፡
ምን ፡ ልታደርግ ፡ ነው ፡ ትኵሱን ፡ ሬሳ ፡
ከመቃብሩ ፡ ላይ ፡ በል ፡ እጅህን ፡ አንሣ ፡
ና፡ ወዲህ ፡ ልያዝህ ፡ ከዚህ ፡ ቦታ ፡ ውጣ
ኣሳልፌ ፡ ልስጥህ ፡ በሞት ፡ ለሚቀጣ ።

#ሮሜዎ
አንተ መልካም ወጣት፡ዐርፈህ ሂድ በደኅና
እኔ ፡ ሞገደኛ፡ አጥፊ ፡ ሰው ፡ ነኝና ፡
መዘዜ፡ የበዛ ፡ አሳር ፡ የጐተተኝ፡
ሕይወቴን ፡ የጠላሁ፣ ኑሮ ፡ የታከተኝ፡
ሞትና ፡ መቃብር ፡ ጥፋት ፡ የሸተተኝ ፡
የከፋው ፡ ወንድ ፡ ነኝ ፡ ወደኔ ፡ አትጠጋ ፤ .
ጠብ ፡ አትፈልገኝ' ለሕይወትህ ፡ ሥጋ ።
ቲባልት ፡ እንደዚሁ ፡ ደርሶ : ሳይቸግረው ፡
በመጥፎ፡ ንግግር ፡ ሆዴን ፡ አሳረረው ፡
ሳልፈልግ ፡ ገደልኩት እሱ ባነሣው ፡ ጠብ
አሁን ፡ ደግሞ ፡ አንተ ይብቃህ ፡ አትሳደብ
ነፍሴን ፡ የጠላሁ፡ ሰው ፡ በመሆኔ ፡ ፍራኝ
ሳልወድ ፡ በግዴታ ፡ ዐመፅ ፡ አታሠራኝ ፡
የሚወጣው ፡ ምክር ፡ አሁን ፡ ከመላሴ ፡
አልሠራሁበትም ፡ እኔ ፡ እንኳ ፡ ለራሴ ፡
ስለዚህ ፡ ከራሴ ፡ አብልጬ ፡ ስወድህ ፡
እኔን ፡ አመስግነህ ፡ ይሻላል ፡ መሄድህ ፡
አንድ፡ እብድ ፡ ሰው ዛሬ የሰጠኝን ምክር
ሰምቼ ፡ ድኛለሁ ፡ ብለህ ፡ ይልቅ ፡ ፎክር ።

#ፓሪስ
እኔስ ፡ ኣለቅህም ፡ ከያዝኩህ ፡ በኋላ ፤
መስጠት ፡ ትችላለህ ፡ ምክርህን ፡ ለሌላ

#ሮሜዎ
መሞት ፡ ከፈለገህ ፡ እንቢ ፡ ብለህ ፡ በጄ ፡
እንግዲያው ሞክረኝ መልካም፡ነው ወዳጄ
(ይዋጉና'ፓሪስ ፡ ይወድቃል) ።.
ቲባልትና ፣ፓሪስ ፡ እኔን እያስቆጡ ፣
እኔ ፡ ሳልነካቸው ፡ በግድ ፡ እየመጡ፡
በእጄ ፡ እየተወጉ' ክዚህ ፡ ዓለም ፡ ወጡ ።
እንዲህ ፡ መሞታቸው ፡ ተናግረውኝ ፡ ክፉ
ተፈርዶባቸው ፡ ነው ፡ በኔ' እጅ እንዲጠፉ
እንደዚህ ፡ ከሆነ ፡ ፓሪስ ፡ ያንተም ፡ ዕጣ ፡
ጥፋቱ ፡ ያንተ ፡ ነው ፡ በኔ ፡ እንዳትቈጣ ፡
የዡልዬት ፡ ቁንዥና፡ ደምቆ እንደ ፡ ብርሃን
ጽርሐ አርያም ፡ መስሎ የሰማይ ፡ ውጋጋን
እያንጸባረቀ ፡ ከኮከብ ፡ ሲያበራ ፡
ግርማ፡ተጐናጽፎ፡ በታየበት፡ ስፍራ፡
እንሙት' ወዳጄ ፡ ኣብረን ፡ ከሷ ፡ ጋራ።
(ሮሜዎበዝልዬት፡መቃብር፡ላይየሐዘን ' ንግግር ፡ ያደርጋል)።
ይህችን ፡ ውብ ፡ አበባ ፡ ፍቅር ፡ አሳማሪ ፡
ውሏን ፡ የማትረሳ ፡ ቃል ፡ ኪዳን ፡ አክባሪ ፡
ትወድ ፡ የነበረች ፡ ቁም ፡ ነገር ፡ ጨዋታ፡
እዩልኝ ፡ ከዘመድ ፡ ከሰው ፡ ተለይታ ፡
የኔ ፡ ሆደ፡ ባሻ ፡ ብቻዋን ፡ ተኝታ፡
ተመልከቱት ፡ እጅዋ ፡ ተመልከቱት ፡ ፊቷ ፤
ወዟ ፡ ገና፡ አልጠፋም ። ከሠራ፡ አካላቷ፡
ግንባሯን ፡ ከንፈራን ፡ ተመልከቱ ፡ ጣቷን ፤
ይህን ፡ አበቃቀል ፡ ተክለ ፡ ሰውነቷን ፡
ገላዋ ፡ ያበራል ፡ በደም ፡ ተሸልሞ ፤
ዡልዬት ፡ሞት የነካት፡አትመስልም ፈጽሞ
እባካችሁ ፡ ሰዎች ፡ ሐዘን፡ ተካፈሉኝ፤
ዡልዬት ፡ አልሞተችም ፡ ተኝታለች ፡ በሉኝ
ታውቂ ፡ የነበርሽው ፡ ፍቅራዊ ፡ አቀባበል ፡
ሽቍጥቀጥ ፡እመቤት ባለመልካም ዐመል
ተወዳጁ ፡ ድምፅሽ ፡ ውብ ፡እንደ ፡ ሙዚቃ
በበገናው ፡ ቃሉ ፡ መንፈስ ፡ የሚያነቃ ፡
ዛሬ ፡ ወዴት ፡ ጠፋ? የት ፡ ቦታ ፡ ደረሰ ? .
ደግሞስ ዐይንሽ ፡ ቆቡን ስለ ምን ለበሰ ?
ዡልዩት ፡ ባትሞት ኖሮ፡ በውነት ፡ ባትቀበር
ሮሜዎ ፡ እዚህ ፡ ቆሞ ዝም አትልም ነበር
ባለም ፡ ላይ ፡ ብንሻ ፡ በውነቱ ፡ የት ፡ ኣለ ፡
ጨካኝ አረመኔ ፡ ሞትን ፡ የመሰለ ፡
ጥቂት ፡ አላዘነም ፡ አልሣሣም ፡ ጨርሶ ፡
ይችን ፡ ጽጌ ፡ ረዳ ፡ ሲጥላት ፡ በጥሶ :
ይችን ፡ አሳዛኝ ፡ ልጅ ፡ ትተዋት ፡ ሲሄዱ፡
በሩን ፡ የዘጋ ፡ ሰው ፡ እንዴት ፡ ቻለ ፡ ሆዱ
እይዋት ይችን ቄንጥ እይዋት ይችን ሎጋ
በባዶ፡ አዳራሽ ፡ በመቃብር ፡ ኣልጋ ፡
ወፍ ፡ በማይዞርበት ፡ ጭር ፡ ባለ ፡ ስፍራ ፡
ብቻዋን ፡ ቀርታለች ፡ አዲሷ ፡ ሙሽራ ።
በመከራ ፡ ቅመም ፡ ባሳር ፡ ተለውሶ :
ዡልዬት፡ ሕይወታችን ፡ መሮን ፡ እንደ ፡ኮሶ
ወጣን ፡ ከዚህ ፡ ዓለም ፡ ያላንድ ፡ ደስታ .
እንግዲህ ፡ እንኑር ፡ እዚህ ፡ በጸጥታ ።
ባለም ፡ ቦታ፡ ጠፍቶ ፡ ለመኖር'ተዋደን ፡
እዚህ ፡ ተገናኘን ፡ ካለም ፡ ላይ ፡ ተሰደን
አይቈጨን እንደዚህ ካለም መውጣታችን
በጣም ፡ ደስ ፡ይበለን ፡ በዛሬው ፡ ዕጣችን
ላለሙ ፡ ደስታ ፡ ለረዥሙም ፡ ዕድሜ ፡
ያው ሞት አይደለም ወይ የሁሉ ፍጻሜ ?
ገላዬን ፡ ከገላሽ ፡ ዐፅምሽን ፡ ካዕፅሜ ፡
ሥጋዬን ፡ ከሥጋሽ ፡ ደምሽን ፡ ከደሜ ፡
ቀላቅሎ ፡ የሚያኖር፡ ከተገኘ ፡ ቦታ ፡
ዡልዬት፡ ከዚህ ፡ ወዲያ ፡ ምን አለ ፡ ደስታ
ይቅር ፡ ደኅና ፡ ይሁን ፡ ዓለም ፡ ከነቂሙ ፤
እዚህ ፡ እኔና፡ አንቺ ፡ እስከ ፡ ዘላለሙ ፡
መቃብር፡ ሆኖልን ፡ የጸጥታ ፡ ገዳም ፡
ከዛሬ ፡ ጀምሮ ፡ እንኑር ፡ በሰላም ።
ከሚወዱት፡ጋራ፡ እንዲህ ፡ ጐን ፡ ለጐን ፡
ምንኛ ፡ መልካም ፡ ነው ፡ ዐፈር ፡ ትቢያ ፡ መሆን ።
(ሮሜዎ ፡ መርዝ ፡ ጠጥቶ ፡ ሞተ ።)

#አባ_ሎራ መብራትና፡ጕጠት፡ ይዞ ፡
ወደ፡መቃብሩ፡ ቦታ፡ መጣ ።

#አባ_ሎራ
ስፍራው ፡ አያስኬድም ፡ ሆነና ፡ መቃብር
እያደናቀፈ ፡ ያስቸግራል ፡ ለእግር ፡
አዬ ፡ መከራዬ ፡ በዚሁ ፡ ላይ ፡ ደግሞ ፡
ምንም ፡አይታየኝ ፡ዐይኔ ፡ በጣም ፡ ደክሞ
ማነህ አንተ እዚህ የቆምከው እንደ አጥር ?

#ቤልሻጥር
የሚያውቁኝ ፡ወዳጅዎ ፡እኔ፡ ነኝ ቤልሻጥር ።

#አባ_ሎራ
እግዚአብሔር ይባርክህ በል ልጄ ንገረኝ ፤
በሩቅ ፡ አላይ ፡ ብሎ ፡ ዐይኔ ፡ አስቸገረኝ፡
እዚያ ፡ በካፑሌ ፡ የመቃብር ፡ ስፍራ ፡
መብራት አይደለም፡ ወይ የማየው ፡ ሲበራ?

#ቤልሻጥር
አዎን ፡ ነው ፡ አባቴ ፡ ሄዷል ፡ እዚያ ፡ ቦታ ፡
ወዳጅዎ ፡ ሮሜዎ ፡ የኔ ፡ መልካም ፡ ጌታ

#አባ_ሎራ
ማን ፡ አልከኝ ?

#ቤልሻጥር
ሮሜዎ ።

#አባ_ሎራ
አዬ ፡ የእግዜር ፡ ቀጣ
ምን ፡ ያኽል ፡ ጊዜ ፡ ነው ፡ እሱ ፡ እዚህ ፡ ከመጣ ?

#ቤልሻጥር
ልክ ፡ እኩል ፡ ሰዓት ፡ ነው ።

#አባ_ሎራ
ና፡ እንሂድ፡ ወደ ፡ እሱ

#ቤልሻጥር
አልችልም ፡ አባቴ ፡ አስጠንቅቆ ፡ ራሱ ፡
ወደ ፡ መቃብሩ፡ እሱ ፡ ወዳለበት ፡
ከቶ ፡ እንዳልጠጋ ፡ ሥራውን ፡ ለማየት ፡
ከልክሎኛልና ፡ በሞት ፡ አስፈራርቶ ፤
ትእዛዙን ፡ ለመጣስ ፡ እኔ ፡አልችልም ፡ ከቶ

#አባ_ሎራ
በል ፡ ተወው፡ ልጄ ፡ ሆይ፡ ሠግቷልና፡ ልቤ
እስቲ ፡ ልመልከተው ፡ ብቻዬን፡ቀርቤ።(አባ፡ሎራሄደ)

#ቤልሻጥር ፡ (ብቻውን ) ።
ዛፍ ፡ ተደገፍኩና ፡ እንቅልፍ ወስዶኝ ፡ ኖሮ
በሕልማ፡ ሮሜዎ ፡ አድርጎ ፡ አምባጓሮ ፡
ውጊያ፡ገጠሙና ፡ የኔ ፡ ጌታ ፡ ሲጥል ፡
አየሁ፡ ደግሞ ፡ ዛሬ ፡ ሌላ ፡ ሰው ፡ ሲገድል

#አባ_ሎራ ፡(ብቻውን) ።
ይህ ፡ ደም ፡ ከየት ፡ መጣ ? ይህ ሻምላ ፡ ምንድነው?
እዚህ ፡ የወደቀ ፡ ባለቤት ፡ የሌለው ።
(ዡሊዬት ነቃች ፤ አባ ፡ ሎራ፡ ጥግ ፡ ይዞ ፡ ቆመ) ።

#ዡልዬት
ሮሜዎ ፍቅሬ ሆይ ማን አምጥቶ ጣለህ ?
ይኸ ፡ ደም ምንድነው ? ፓሪስ ፡ ማ፡ገደለህ ?
ጨርሰው ፡ አይሰሙም ፡ ሞተዋል ፡ እነሱ
ትንፋሽም ፡ የላቸው ፡ አይንቀሳቀሱ ፡
የእንቅልፍ ፡ የመኝታ ፡ የዕረፍት ፡ የጸጥታ :
መሆኑ ፡ ቀረና ፡ ሰላማዊ ፡ ቦታ ፤
ከእንቅልፌ ፡ ስነቃ ፡ አወይ ፡ መቃብሬ ፡
የጦር ፡
👍1
ሜዳ ፡ ሆኖ ፡ ጠብቆኛል ፡ ዛሬ ።
ሮሜዮ፡ ምን ፡ ነካው ? ፓሪስን ማ መታው ?
ይህን ፡ እንቆቅልሽ ፡ማነው ፡ የሚፈታው ?

#ኣባ_ሎራ
ይኸውልሽ ፡ ልጄ ፡ እግዜር ፡ አልፈቀደም
እንዳሰብኩት ፡ ሆኖ ፡ ነገሩ ፡ አልሄደም ።
ኣሁንም ፡ ቶሎ ፡ በይ ፡ ውጪ ከዚህ ፡ ቦታ
ሰዎች ፡ መጡ ፡ ከደጅ ይሰማል ፡ ጫጫታ
እንድትገቢ ፡ አድርጌ አንቺን ካንድ ገዳም
እዚያ ፡ ትኖሪያለሽ ፡ ልጄ ፡ ሆይ ፡ በሰላም ፡
እባክሽ ቶሎ በይ፡ ሰዎች ወዲህ መጡ፡

#ዡልዬት
ከዚህ ፡ እኔ ፡ አልሄድም ፡ እርስዎ ፡ ፈጥነው፡ይውጡ።
(ዡልዬት ፡ ብቻዋን ፡ )፣ ( አባ ' ሎራ' ሄደ)
ደግሞ ፡ ይህ ፡ ኩባያ ፡ እዚህ ፡ ምን ፡ አመጣው ?
ምን ፡ ይሆን ሮሜዎ አግኝቶ የጠጣው ?

አሁን ፡ ገና ፡ ገባኝ ፡ ዐይኔ ፡ ተከፈተ ፤
መርዝ ፡ ጠጥቶ ፡ ነው ፡ ሮሜዎ ፡ የሞተ ።
ጥንቱን ፡ ተፈጥሬ ፡ ለዬዬ ፡ ለለቅሶ ፡
እንዴት ፡ ያለው ፡ ሐዘን ፡ ቈየኝ ፡ ተደግሶ :
እኔ ፡ እሱን ፡ ስጠብቅ ፡ እዚህ ፡ ተቀብሬ ፡
በድን ፡ ሆኜ ፡ ሬሳ ፡ቆየሁ ፡ እስከ ፡ ዛሬ ፡
ወይ ፡ አለ ፡ መታደል ፡ መፈጠር፡ ላበሳ ፤
ይኸ ፡ ሁሉ ፡ ድካም ፡ይህ ሁሉ ፡ ግሥገሣ
ለማየት ፡ ኖሯል ፡ ወይ ወድቆ ያንተ ሬሳ፤
ለካ ፡ መልካም ፡ ኖሯል ፡ ብቀር ፡ ሳልነሣ ።
ወደ፡እሱ፡ብመጣ ፡ እኔ አድርጌው ዘመድ፡
እሱስ ቀድሞኝ ሄዷልባላሰብኩት መንገድ
እንዳልቀየመው ፡ የኔ ፡ ከዳተኛ ፡
መጥቶ ፡ ካጠገቤ ፡ እዩት፡እንደ፡ተኛ ።
አወይ ፡ ሮሜዎ ፡ የኔ ፡ ሆደ ፡ ባሻ ፡
አንተ፡ እኔን ፡ ስትፈልግ እኔም አንተን ፡ ስሻ
ብቻህን ፡ ሄደሃል ፡ ሰው ፡ ቀርቶኛል ፡ ሳትል
የጭንቅ ፡ ወዳጅህን ፡ እኔን ፡ ሳታስከትል ፡
አልቀርም ፡ ጠብቀኝ ፡ ባለህበት ፡ ቦታ ፤
ኩባያህ ፡ ባዶ ፡ ነው ፡ የለውም ፡ ጠብታ ፡
አንተ ፡ ቢስ ፡ ሥሥታም ፡ ንፉግ ፡ መኰንኔ
ጨልጠህ ፡ ጠጣኸው ፡ ሳታስተርፍ ፡ ለኔ
ቆየኝ ፡ ደረስኩብህ ፡ በርሬ፡ እንደ ፡ አሞራ፤
ይኸው ፡መምጣቴ ነው ፡ እኔም ካንተ፡ ጋራ
አልሠራህበትም ፡ አንተ ፡ ባለቤቱ ፡
እስቲ ፡ ልታቀፈው ፡ ይግባ ፡ በስለቱ ፡
አንጀቴ ፡ ለጩቤህ ፡ ይሁነው ፡ አፎቱ ።
(በሮሜዎ ፡ ልቤ ፡ ሆዷን ' ወግታ ፡ ሞተች)

#የመጀመሪያ_ዘበኛ
በልምራን ወዴት ነው መንገዱና ስፍራው ?

#የፓሪስ_አሽከር
ይኸው እዚህ ነበር መብራት ፡ የሚበራው

#የመጀመሪያ_ዘበኛ
ምድሩ ፡ ደም ፡ ብቻ፡ነው፡ምድነው፡ ነገሩ?
እስቲ ፡ ቶሎ ፡ ግቡ ፡ ወደ ፡ መቃብሩ፡
ትልቁ ፡ መኰንን ፡ ፓሪስ ፡ ይኸው ፡ ሞቶ ፡
ቀርቷል ፡ በመሬት ፡ ላይ ፡እዚህ ፡ ተዘርግቶ
ከሁለት ፡ ቀን ፡ በፊት ፡ የቀበሯት፡ ሞታ ፡
ዝልዬትም ፡ ወድቃለች በጨቤ ፡ ተወግታ፡
እዩ ፡ ተመልከቱ ፡ በደም ፡ ተለውሳ ፤
አልብሶት ፡ የለም ፡ ወይ ፡ ሜዳውን 'ሬሳ ።
ደግሞስ ፡ ሮሜዎ ፡እዚህ ፡ምን አመጣው፤
እሱም ደግሞ ሞቷል ትንፋሽም አይወጣው ።
ቶሎ ፡ ንገሯቸው ፡ መስፍኑ፡ይጠሩ፤
ደግሞም ፡ ግማሻችሁ ፡ ስፍራውን ፡ መርምሩ ፡
ይጠሩ፡ እነ ፡ ሞንታግ ፡ ይምጡ ፡ እነ ፡ ካፑሌ ፤
ፍተሻ ፡ይደረግ ፡ በዚሁ ፡ ቀበሌ ፡
ምስክር ፡ ተገኝቶ ፡ታሪኩ ፡ እስቲሰማ ፡
የተሰወረ፡ ነው፡ ምስጢሩ ፡ ጨለማ ።

💫ይቀጥላል💫