#ሮሜዎና_ዡልዬት
#ክፍል_አራት
#ዡልዬት ።
ይቅርብኝ 'አትማል በውነትም ፡ በውሸት ፡
ደግሞም ፡ ልማል ፡ ብለህ፡አሳብህ ፡ ከጸና
ምን ጊዜም ፡ ጣዖቴ ፡ ፍቅሬ ፡ አንተ ፡ ነህና
በራስህ ፡ ማልልኝ ፡ የኔ ፡ ሁለንተና ።
#ሮሜዎ ።
እንግዲያውስ ፡ ስሚ ፡ እኔ ፡ አንቺን ፡ መውደዴ ፡
#ዡልዬት
ይቅር ፡ በቃ ፡ አትማል ፤ ተናወጠ ፡ ሆዴ ፡
ፈጥነህ ፡ ብትምልልኝ ፡ አሁን ፡ ዛሬ ፡ ማታ
ምንም ፡ አይሰማኝ ፡ ለልቤ ፡ ደስታ ፡
እንደዚህ ፡ በድንገት ፡ እንዲህ ፡ በችኰላ ፡
እንደዚህ ፡ በቶሎ ፡ የሆነ ፡ መሓላ ፡
መሠረት ፡ የለውም ፡ ይጠፋል ፡ ባንዳፍታ፤
አላፊ ፡ ነፋስ ፡ ነው ፡ የሰማይ ፡ ብልጭታ
የፍቅሩ፡ ቡቃያ ፡ ከዛሬ ፡ ጀምሮ ፡
ለምልሞ ፡ ይጠንክር ፡ በልባችን ፡ አድሮ ፡
እኛም ፡ እዚያ ፡ ድረስ ፡ሆነን ፡ ትዕግሥተኛ
ወደየቤታችን ፡ ገብተን ፡ እንተኛ ።
#ሮሜዎ ።
ልትሄጂ ፡ ነወይ ፡ ትተሽኝ ፡ በከንቱ ?
#ዥልየት ።
ይበቃል ፡ ለዛሬ ፡ መሽብን ፡ ሰዓቱ ።
#ሮሜዎ ።
ስጭኝ ፡ የሚያጠግብ፡አንድ ፡ ቃል ፡ የበቃ
#ዡልዬት ።
አንተ ፡ ሳትጠይቅ ፡ በፊት፡ዡልዬት ፡ዐውቃ
ሰጥታህ፡ወስደኸዋል፡የፍቅሯን፡ቃል ኪዳን
የተረፈው ፡ ይደር ፡ ለነገ ፡ እንዲረዳን ።
#ሮሜዎ ።
መልሰሽ ወስደሺው ፡'መልካሙን ፡ ስጦታ
#ዡልዬት ።
ቃሌን ፡ እሰጣለሁ ፡ ላንተ ፡ በችሮታ
የልቤ ፡ ደግነት ፡ ባሕር ፡ ነው ፡ ስፋቱ ፤
ፍቅሬም ፡ እንደዚሁ፡ ጥልቅ ፡ ነው ፡ ርቀቱ
መልካም ፡ ጠባዮቼ ፡ እነዚህ ፡ ሁለቱ ፡
ሰፊ ፡ ሀብት ፡ናቸው፡ ከሁሉም ፡ የላቁ ፤
ብሰጥህ ፡ ብሰጥህ ፡ ምን ፡ ጊዜም ፡ አያልቁ ።
(#ሞግዚቷ' #ጠራቻት ) ።
ጠሩኝ ፡ ድምፅ ፡ ሰማሁ ፡ በል ፡ ሄድኩኝ፡ደኅኖ፡እደር።
ሞግዚቴ ፡ እሺ ፡ መጣሁ ፤ ሮሜዎ ፡ አንድ ነገር ፡ አለ ፡ የምነግርህ፡አትሂድ፡ጠብቀኝ ፣ (ወደቤት'ግባች) »
#ሮሜዎ : (ብቻውን) "
የዛሬው ፡ ደስታ ፡ ምንኛ ፡ ደነቀኝ ።
ሕልም ፡ ነው ፡ ራእይ፡ ወይስ ' ደግሞ ቅዠት አልችልም ፡ ይህ ፡ ነገር ፡ ከቶ'ልደርስበት ፤
ፀሓዬ ፡ ጠለቀች ፡ ገባች ፡ ወደ ፡ ቤቷ ።
አሁን ፡ ተመልሳ ፡ ዳግም ፡ በመስኮቷ ፡
ብቅ ፡ እስክትል ፡ ድረስ ፡ ሆነብኝ ፡ ጨለማ ፡
ይኸው ፡ ተመለሰ ፡ የብርሃኗ ፡ ግርማ ።
#ዡልዬት ፡(ተመልሳ • መጣች
ሮሜዎ ፡ ልንገርህ ፡ የመጨረሻ ፡ ቃል ፤
እንደምታፈቅረኝ ፡ ዐወቅሁት ፡ ይበቃል ፡
ዳሩ ፡ ግን ፡ ፍቅራችን ፡ መሠረት ፡ አግኝቶ
በተክሊል ፡ ጋብቻ ፡ እንዲፈጸም ፡ ጸንቶ ፡
ትፈቅድ ፡ እንደ ፡ ሆነ ፡ እልካለሁና ፥
ነገ ፡ ሰው ፡ ወዳንተ ፡ ጒዳዩን ፡ ካጠናህ ፡
ካሰበ ፡ በኋላ ፡ መንፈስህ ፡ መርምሮ ፡
የተክሊሉ ፡ ሰዓት ፡ ይሁን ፡ በቀጠር ።
ወስነህ ፡ ላክብኝ ፤ ከዚያ ፡ በኋላ ፡ ግን ፡
ማመንታት ፡ ሳይኖረው ፡ ልቤ ፡ ሳይገነግን
ችግር ፡ ሳያግደኝ ፡ አደጋና ፡ ሞትም ፡
አንተን ፡ ተከትዬ ፡ እሄዳለሁ ፡ የትም ።
ነገር ግን ፡ ያንተ ፡አሳብ ከሌለው ፡ ንጽሕና
የማይሄድ ፡ ከሆነ ፡ እንደኔ ፡ ኅሊና ፡
አትምጣ፡ ወደኔ ፡ አትድከም ፡ በከንቱ
እንግዴህ ፡ ደኅና ፡ ሁን ፡ አለፈ ፡ ሰዓቱ '
ግባ ፡ ወደ ፡ ቤትህ ፡ ፍጠን ፡ አታመንታ ፤
ሊነጋ ፡ ነውና ፡ ይታያል ፡ ወገግታ ፡
ጨለማ ፡ ለቀቀ ፡ ብርሃን ፡ ተከፈተ ፡
ስንት ፡ ሰዓት ፡ ሲሆን ፡ ሰው ፡ ልላክ ፡ ወዳንተ ?
#ሮሜዎ
ሦስት ፡ ሰዓት ሲሆን መልክተኛሽ ፡ ይምጣ
#ዡልዬት ።
እንግዴህ ፡ ደኅና ፡ ሁን ፡ ፀሓይ ፡ ሳትወጣ
እንግባ ፡ ቤታችን ። (ሄደች)•
#ሮሜዎ ።
ዡልዬት ፡ ደኅና ፡ ሁኝ፤
ልቤ ፡ ካንቺ ፡ ጋራ ፡ መቅረቱን ፡ እመኝ ። (ሄዴ) •
#ሮሜዎና #ኣባ_ሎራ ፡ (ባባ ' ሎራ' ቤት)
#ሮሜዎ ።
እንደምን ፡ አድረዋል፡ አባቴ ፡ አባ ፡ ሎራ ?
#አባ_ሎራ
ከምሥራቅ ፡ ሳይታይ ፡ የፀሓይዋ ፡ ሥራ ፡
ማነህ ፡ በማለዳ ፡ የመጣህ ፡ ከቤቴ ?
በጣፋጩ ፡ ድምፅህ ፡ የምትል ፡ አባቴ ።
እረግ ! አንተ ፡ ነህ ፡ ወይ ፡ሮሜዎ ፡ ጐበዙ
ዐይኔ ፡ ደከመና ፡ አላየም ፡ በብዙ ፡
እንደ ፡ ምን ፡ አድረሃል ፡ የምወድህ ፡ ልጄ
ዐይንህ፡በጣም፡ቀልቷል፡ምን ነካህ ወዳጄ ?
አንድ ፡ ሰው ፡ እንደዚህ ፡ በጧት ፡ የሚነሣ
ነገር ፡ ሲያገኘው ፡ ነው ፡ እንቅልፍ ፡ የሚነሳ ፡
አሳብ ፡ የምንለው ፡ የሰላም ፡ መጋኛ ፡
መንፈሱን ፡ ሰፍሮበት ፡ እንቅልፍ ፡ የማይተኛ ፡
ሽማግሌ ፡ ሰው ፡ ነው ፤ ወጣት ፡ ግን ፡ በውኑ ፡
ከእንግዲህ ፡ ያለ ፡ ነገር ፡ ነጻ ፡ በመሆኑ ፡
ተኝቶ ፡ ያነጋል ፡ እንቅልፉን ፡ በሰላም ፤
ስለዚህ ፡ ይህ ፡ ዐይንህ ፡ በደኅናው ፡ አልቀላም ፡
ሮሜዎ ፡ ምን ፡ ሆኖ ፡ ሳይተኛ ፡ ያደረ ?
አለመተኛቱን ፡ ዐይኑ ፡ መሰከረ ።
#ሮሜዎ ።
እውነት ፡ ነው ፡ ነገር ፡ ግን ፡አርፌያለሁ ፡ በጣም
#አባ_ሎራ ።
ብታርፍማ ፡ ኖሮ ፡ በሌሊት ፡ አትመጣም ፡
ንገረኝ ፡ አትደብቅ ፡ ወዴት ፡ ነው ፡ ያደርከው ?
#ሮሜዎ ።
ድል ፡ አድራጊው : ፍቅሯ ፡ መንፈሴን ፡ ማረከው
አባቴ ፡ እጅዎ ፡ ተክሊሌን ፡ ይባርከው ።
#አባ_ሎራ ።
ያሰብከውን ፡ ነገር ፡ ንገረኝ ፡ አትፍራ ፤
ከመልካሟ ፡ እጮኛህ ፡ ከሮዛሊን ፡ ጋራ ፡
የተክሊል ፡ ቃል ፡ ኪዳን ፡ ዛሬ ፡ ልትሞላ ፡
የመጣህ ፡ መሰለኝ ፡ ሳስበው ፡ በመላ ።
#ሮሜዎ ።
ሮዛሊን ፡ ቀርታለች ፡ አያንሷት ፡ አባቴ ፡
ትናንትና ፡ ማታ ፡ ተመታ ፡ ደረቴ ፡
ባዲስ ፡ የፍቅር ፡ ጦር ፡ በሰላ ፡ ጐራዴ ፤
ከመውደዷ ፡ ጋራ ፡ ገጠመ ፡ መውደዴ፡
ስሜታችን ፡ እኩል ፡ ፍቅራችን ፡ የጋራ ፡
ሆኖ ፡ ከተገኘ ፡ አባቴ ፡ አባ ፡ ሎራ ፡
ተክሊሉን ፡ ይሙሉልን ፡ በሥልጣንዎ ፡ ባርከው ፡
እኛ ፡ ቂም ፡ የለንም ፤
#አባ_ሎራ ።
መንፈሴን ፡ ኣወከው
ምን ፡ አመጣህብኝ ፡ የማላውቀው ፡ ምስጢር ፥
መላ ፡ መትቶ ፡ ያውቃል ፡ ብለህ ፡ አትጠርጥር ፤
አልገባኝምና ፡ ያሁኑ ፡ ንግግር ።
ይህን ፡ እንቆቅልሽ ፡ እንደ ፡ ሾላ ፡ ድፍን ፡
ትተህ ፡ ፡ ግለጥልኝ ፡ ነገሩን ፡ ሳትሸፍን ።
#ሮሜዎ ።
አባቴ ፡ አልደብቅም ፡ ሁሉንም ፡ ገልጬ ፡
ለርስዎ ፡ ልነግር፡ ነው ፡ የመጣ ፡ ሮጬ፡
የነካፑሌን ፡ ልጅ ዡለየትን ፡ ወድጄ ፤
ራሴ ፡ እስቲጠፋ ፡ በፍቅር አብጄ ፡
እሷም ፡ በጣም ወዳኝ፡አድርገን ፡ መሐላ ፡
ተስማምተን ተዋደን ከቈረጥ ኋላ ፡
አሁን 'የሚቀረን'ተክሊል ፡ የሚሞላ ፡
ካህን ፡ ስለ ፡ ሆነ የሚሰጥ፡ ቡራኬ ፡
ከሷ ጋር ፡ መጥቼ ፈትዎ' ተንበርክኬ ፡
ሞልተው 'ያሰናብቱን የተክሊሉን ፡ ሥርዐት
ሰዓቱን 'ይንገሩኝ መቼ እንደምጠራት ።
#አባ_ሎራ
አይጣል፡ነው፡እናንተ፡ የወጣቶች ፡ ወረት፤
ፍቅራቸው ፡ ቃላቸው ፡ የለውም መሠረት፡
የቀድሞ ፡ እጮኛህ ፡ ሮዛሊን 'ተረስታ፡
ሌላ ፡ ልጅ ፡ አግኝተህ አሁን ትናንት ፡ ማታ
እንዴት ተለወጠ፡ ኣሳብህ ፡ ባንድ ፡ አፍታ፡
በሮዛሊን ፡ ፍቅር ፡ ልብህ ፡ እንዲያ፡ግሎ ፡
ዘላለም ፡ የማይበርድ፡እውነተኛ፡መስሎ ፡
ታጫውተኝ ፡ ነበር አሁን ፡ ይኸውና ፡
ያ ፡ ሁሉ ፡ መውደድህ 'ከመቼው 'ቀረና ፡
መጣህ ' ባዲስ ፡ ፍቅር ፡ ልብህ ፡ ተብረክርኮ ፡
ለምታያት፡ሁሉ፡መንፈስህ ፡ ተማርኮ፡
💫ይቀጥላል💫
#ክፍል_አራት
#ዡልዬት ።
ይቅርብኝ 'አትማል በውነትም ፡ በውሸት ፡
ደግሞም ፡ ልማል ፡ ብለህ፡አሳብህ ፡ ከጸና
ምን ጊዜም ፡ ጣዖቴ ፡ ፍቅሬ ፡ አንተ ፡ ነህና
በራስህ ፡ ማልልኝ ፡ የኔ ፡ ሁለንተና ።
#ሮሜዎ ።
እንግዲያውስ ፡ ስሚ ፡ እኔ ፡ አንቺን ፡ መውደዴ ፡
#ዡልዬት
ይቅር ፡ በቃ ፡ አትማል ፤ ተናወጠ ፡ ሆዴ ፡
ፈጥነህ ፡ ብትምልልኝ ፡ አሁን ፡ ዛሬ ፡ ማታ
ምንም ፡ አይሰማኝ ፡ ለልቤ ፡ ደስታ ፡
እንደዚህ ፡ በድንገት ፡ እንዲህ ፡ በችኰላ ፡
እንደዚህ ፡ በቶሎ ፡ የሆነ ፡ መሓላ ፡
መሠረት ፡ የለውም ፡ ይጠፋል ፡ ባንዳፍታ፤
አላፊ ፡ ነፋስ ፡ ነው ፡ የሰማይ ፡ ብልጭታ
የፍቅሩ፡ ቡቃያ ፡ ከዛሬ ፡ ጀምሮ ፡
ለምልሞ ፡ ይጠንክር ፡ በልባችን ፡ አድሮ ፡
እኛም ፡ እዚያ ፡ ድረስ ፡ሆነን ፡ ትዕግሥተኛ
ወደየቤታችን ፡ ገብተን ፡ እንተኛ ።
#ሮሜዎ ።
ልትሄጂ ፡ ነወይ ፡ ትተሽኝ ፡ በከንቱ ?
#ዥልየት ።
ይበቃል ፡ ለዛሬ ፡ መሽብን ፡ ሰዓቱ ።
#ሮሜዎ ።
ስጭኝ ፡ የሚያጠግብ፡አንድ ፡ ቃል ፡ የበቃ
#ዡልዬት ።
አንተ ፡ ሳትጠይቅ ፡ በፊት፡ዡልዬት ፡ዐውቃ
ሰጥታህ፡ወስደኸዋል፡የፍቅሯን፡ቃል ኪዳን
የተረፈው ፡ ይደር ፡ ለነገ ፡ እንዲረዳን ።
#ሮሜዎ ።
መልሰሽ ወስደሺው ፡'መልካሙን ፡ ስጦታ
#ዡልዬት ።
ቃሌን ፡ እሰጣለሁ ፡ ላንተ ፡ በችሮታ
የልቤ ፡ ደግነት ፡ ባሕር ፡ ነው ፡ ስፋቱ ፤
ፍቅሬም ፡ እንደዚሁ፡ ጥልቅ ፡ ነው ፡ ርቀቱ
መልካም ፡ ጠባዮቼ ፡ እነዚህ ፡ ሁለቱ ፡
ሰፊ ፡ ሀብት ፡ናቸው፡ ከሁሉም ፡ የላቁ ፤
ብሰጥህ ፡ ብሰጥህ ፡ ምን ፡ ጊዜም ፡ አያልቁ ።
(#ሞግዚቷ' #ጠራቻት ) ።
ጠሩኝ ፡ ድምፅ ፡ ሰማሁ ፡ በል ፡ ሄድኩኝ፡ደኅኖ፡እደር።
ሞግዚቴ ፡ እሺ ፡ መጣሁ ፤ ሮሜዎ ፡ አንድ ነገር ፡ አለ ፡ የምነግርህ፡አትሂድ፡ጠብቀኝ ፣ (ወደቤት'ግባች) »
#ሮሜዎ : (ብቻውን) "
የዛሬው ፡ ደስታ ፡ ምንኛ ፡ ደነቀኝ ።
ሕልም ፡ ነው ፡ ራእይ፡ ወይስ ' ደግሞ ቅዠት አልችልም ፡ ይህ ፡ ነገር ፡ ከቶ'ልደርስበት ፤
ፀሓዬ ፡ ጠለቀች ፡ ገባች ፡ ወደ ፡ ቤቷ ።
አሁን ፡ ተመልሳ ፡ ዳግም ፡ በመስኮቷ ፡
ብቅ ፡ እስክትል ፡ ድረስ ፡ ሆነብኝ ፡ ጨለማ ፡
ይኸው ፡ ተመለሰ ፡ የብርሃኗ ፡ ግርማ ።
#ዡልዬት ፡(ተመልሳ • መጣች
ሮሜዎ ፡ ልንገርህ ፡ የመጨረሻ ፡ ቃል ፤
እንደምታፈቅረኝ ፡ ዐወቅሁት ፡ ይበቃል ፡
ዳሩ ፡ ግን ፡ ፍቅራችን ፡ መሠረት ፡ አግኝቶ
በተክሊል ፡ ጋብቻ ፡ እንዲፈጸም ፡ ጸንቶ ፡
ትፈቅድ ፡ እንደ ፡ ሆነ ፡ እልካለሁና ፥
ነገ ፡ ሰው ፡ ወዳንተ ፡ ጒዳዩን ፡ ካጠናህ ፡
ካሰበ ፡ በኋላ ፡ መንፈስህ ፡ መርምሮ ፡
የተክሊሉ ፡ ሰዓት ፡ ይሁን ፡ በቀጠር ።
ወስነህ ፡ ላክብኝ ፤ ከዚያ ፡ በኋላ ፡ ግን ፡
ማመንታት ፡ ሳይኖረው ፡ ልቤ ፡ ሳይገነግን
ችግር ፡ ሳያግደኝ ፡ አደጋና ፡ ሞትም ፡
አንተን ፡ ተከትዬ ፡ እሄዳለሁ ፡ የትም ።
ነገር ግን ፡ ያንተ ፡አሳብ ከሌለው ፡ ንጽሕና
የማይሄድ ፡ ከሆነ ፡ እንደኔ ፡ ኅሊና ፡
አትምጣ፡ ወደኔ ፡ አትድከም ፡ በከንቱ
እንግዴህ ፡ ደኅና ፡ ሁን ፡ አለፈ ፡ ሰዓቱ '
ግባ ፡ ወደ ፡ ቤትህ ፡ ፍጠን ፡ አታመንታ ፤
ሊነጋ ፡ ነውና ፡ ይታያል ፡ ወገግታ ፡
ጨለማ ፡ ለቀቀ ፡ ብርሃን ፡ ተከፈተ ፡
ስንት ፡ ሰዓት ፡ ሲሆን ፡ ሰው ፡ ልላክ ፡ ወዳንተ ?
#ሮሜዎ
ሦስት ፡ ሰዓት ሲሆን መልክተኛሽ ፡ ይምጣ
#ዡልዬት ።
እንግዴህ ፡ ደኅና ፡ ሁን ፡ ፀሓይ ፡ ሳትወጣ
እንግባ ፡ ቤታችን ። (ሄደች)•
#ሮሜዎ ።
ዡልዬት ፡ ደኅና ፡ ሁኝ፤
ልቤ ፡ ካንቺ ፡ ጋራ ፡ መቅረቱን ፡ እመኝ ። (ሄዴ) •
#ሮሜዎና #ኣባ_ሎራ ፡ (ባባ ' ሎራ' ቤት)
#ሮሜዎ ።
እንደምን ፡ አድረዋል፡ አባቴ ፡ አባ ፡ ሎራ ?
#አባ_ሎራ
ከምሥራቅ ፡ ሳይታይ ፡ የፀሓይዋ ፡ ሥራ ፡
ማነህ ፡ በማለዳ ፡ የመጣህ ፡ ከቤቴ ?
በጣፋጩ ፡ ድምፅህ ፡ የምትል ፡ አባቴ ።
እረግ ! አንተ ፡ ነህ ፡ ወይ ፡ሮሜዎ ፡ ጐበዙ
ዐይኔ ፡ ደከመና ፡ አላየም ፡ በብዙ ፡
እንደ ፡ ምን ፡ አድረሃል ፡ የምወድህ ፡ ልጄ
ዐይንህ፡በጣም፡ቀልቷል፡ምን ነካህ ወዳጄ ?
አንድ ፡ ሰው ፡ እንደዚህ ፡ በጧት ፡ የሚነሣ
ነገር ፡ ሲያገኘው ፡ ነው ፡ እንቅልፍ ፡ የሚነሳ ፡
አሳብ ፡ የምንለው ፡ የሰላም ፡ መጋኛ ፡
መንፈሱን ፡ ሰፍሮበት ፡ እንቅልፍ ፡ የማይተኛ ፡
ሽማግሌ ፡ ሰው ፡ ነው ፤ ወጣት ፡ ግን ፡ በውኑ ፡
ከእንግዲህ ፡ ያለ ፡ ነገር ፡ ነጻ ፡ በመሆኑ ፡
ተኝቶ ፡ ያነጋል ፡ እንቅልፉን ፡ በሰላም ፤
ስለዚህ ፡ ይህ ፡ ዐይንህ ፡ በደኅናው ፡ አልቀላም ፡
ሮሜዎ ፡ ምን ፡ ሆኖ ፡ ሳይተኛ ፡ ያደረ ?
አለመተኛቱን ፡ ዐይኑ ፡ መሰከረ ።
#ሮሜዎ ።
እውነት ፡ ነው ፡ ነገር ፡ ግን ፡አርፌያለሁ ፡ በጣም
#አባ_ሎራ ።
ብታርፍማ ፡ ኖሮ ፡ በሌሊት ፡ አትመጣም ፡
ንገረኝ ፡ አትደብቅ ፡ ወዴት ፡ ነው ፡ ያደርከው ?
#ሮሜዎ ።
ድል ፡ አድራጊው : ፍቅሯ ፡ መንፈሴን ፡ ማረከው
አባቴ ፡ እጅዎ ፡ ተክሊሌን ፡ ይባርከው ።
#አባ_ሎራ ።
ያሰብከውን ፡ ነገር ፡ ንገረኝ ፡ አትፍራ ፤
ከመልካሟ ፡ እጮኛህ ፡ ከሮዛሊን ፡ ጋራ ፡
የተክሊል ፡ ቃል ፡ ኪዳን ፡ ዛሬ ፡ ልትሞላ ፡
የመጣህ ፡ መሰለኝ ፡ ሳስበው ፡ በመላ ።
#ሮሜዎ ።
ሮዛሊን ፡ ቀርታለች ፡ አያንሷት ፡ አባቴ ፡
ትናንትና ፡ ማታ ፡ ተመታ ፡ ደረቴ ፡
ባዲስ ፡ የፍቅር ፡ ጦር ፡ በሰላ ፡ ጐራዴ ፤
ከመውደዷ ፡ ጋራ ፡ ገጠመ ፡ መውደዴ፡
ስሜታችን ፡ እኩል ፡ ፍቅራችን ፡ የጋራ ፡
ሆኖ ፡ ከተገኘ ፡ አባቴ ፡ አባ ፡ ሎራ ፡
ተክሊሉን ፡ ይሙሉልን ፡ በሥልጣንዎ ፡ ባርከው ፡
እኛ ፡ ቂም ፡ የለንም ፤
#አባ_ሎራ ።
መንፈሴን ፡ ኣወከው
ምን ፡ አመጣህብኝ ፡ የማላውቀው ፡ ምስጢር ፥
መላ ፡ መትቶ ፡ ያውቃል ፡ ብለህ ፡ አትጠርጥር ፤
አልገባኝምና ፡ ያሁኑ ፡ ንግግር ።
ይህን ፡ እንቆቅልሽ ፡ እንደ ፡ ሾላ ፡ ድፍን ፡
ትተህ ፡ ፡ ግለጥልኝ ፡ ነገሩን ፡ ሳትሸፍን ።
#ሮሜዎ ።
አባቴ ፡ አልደብቅም ፡ ሁሉንም ፡ ገልጬ ፡
ለርስዎ ፡ ልነግር፡ ነው ፡ የመጣ ፡ ሮጬ፡
የነካፑሌን ፡ ልጅ ዡለየትን ፡ ወድጄ ፤
ራሴ ፡ እስቲጠፋ ፡ በፍቅር አብጄ ፡
እሷም ፡ በጣም ወዳኝ፡አድርገን ፡ መሐላ ፡
ተስማምተን ተዋደን ከቈረጥ ኋላ ፡
አሁን 'የሚቀረን'ተክሊል ፡ የሚሞላ ፡
ካህን ፡ ስለ ፡ ሆነ የሚሰጥ፡ ቡራኬ ፡
ከሷ ጋር ፡ መጥቼ ፈትዎ' ተንበርክኬ ፡
ሞልተው 'ያሰናብቱን የተክሊሉን ፡ ሥርዐት
ሰዓቱን 'ይንገሩኝ መቼ እንደምጠራት ።
#አባ_ሎራ
አይጣል፡ነው፡እናንተ፡ የወጣቶች ፡ ወረት፤
ፍቅራቸው ፡ ቃላቸው ፡ የለውም መሠረት፡
የቀድሞ ፡ እጮኛህ ፡ ሮዛሊን 'ተረስታ፡
ሌላ ፡ ልጅ ፡ አግኝተህ አሁን ትናንት ፡ ማታ
እንዴት ተለወጠ፡ ኣሳብህ ፡ ባንድ ፡ አፍታ፡
በሮዛሊን ፡ ፍቅር ፡ ልብህ ፡ እንዲያ፡ግሎ ፡
ዘላለም ፡ የማይበርድ፡እውነተኛ፡መስሎ ፡
ታጫውተኝ ፡ ነበር አሁን ፡ ይኸውና ፡
ያ ፡ ሁሉ ፡ መውደድህ 'ከመቼው 'ቀረና ፡
መጣህ ' ባዲስ ፡ ፍቅር ፡ ልብህ ፡ ተብረክርኮ ፡
ለምታያት፡ሁሉ፡መንፈስህ ፡ ተማርኮ፡
💫ይቀጥላል💫
👍1