አትሮኖስ
281K subscribers
111 photos
3 videos
41 files
481 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
ሜዳ ፡ ሆኖ ፡ ጠብቆኛል ፡ ዛሬ ።
ሮሜዮ፡ ምን ፡ ነካው ? ፓሪስን ማ መታው ?
ይህን ፡ እንቆቅልሽ ፡ማነው ፡ የሚፈታው ?

#ኣባ_ሎራ
ይኸውልሽ ፡ ልጄ ፡ እግዜር ፡ አልፈቀደም
እንዳሰብኩት ፡ ሆኖ ፡ ነገሩ ፡ አልሄደም ።
ኣሁንም ፡ ቶሎ ፡ በይ ፡ ውጪ ከዚህ ፡ ቦታ
ሰዎች ፡ መጡ ፡ ከደጅ ይሰማል ፡ ጫጫታ
እንድትገቢ ፡ አድርጌ አንቺን ካንድ ገዳም
እዚያ ፡ ትኖሪያለሽ ፡ ልጄ ፡ ሆይ ፡ በሰላም ፡
እባክሽ ቶሎ በይ፡ ሰዎች ወዲህ መጡ፡

#ዡልዬት
ከዚህ ፡ እኔ ፡ አልሄድም ፡ እርስዎ ፡ ፈጥነው፡ይውጡ።
(ዡልዬት ፡ ብቻዋን ፡ )፣ ( አባ ' ሎራ' ሄደ)
ደግሞ ፡ ይህ ፡ ኩባያ ፡ እዚህ ፡ ምን ፡ አመጣው ?
ምን ፡ ይሆን ሮሜዎ አግኝቶ የጠጣው ?

አሁን ፡ ገና ፡ ገባኝ ፡ ዐይኔ ፡ ተከፈተ ፤
መርዝ ፡ ጠጥቶ ፡ ነው ፡ ሮሜዎ ፡ የሞተ ።
ጥንቱን ፡ ተፈጥሬ ፡ ለዬዬ ፡ ለለቅሶ ፡
እንዴት ፡ ያለው ፡ ሐዘን ፡ ቈየኝ ፡ ተደግሶ :
እኔ ፡ እሱን ፡ ስጠብቅ ፡ እዚህ ፡ ተቀብሬ ፡
በድን ፡ ሆኜ ፡ ሬሳ ፡ቆየሁ ፡ እስከ ፡ ዛሬ ፡
ወይ ፡ አለ ፡ መታደል ፡ መፈጠር፡ ላበሳ ፤
ይኸ ፡ ሁሉ ፡ ድካም ፡ይህ ሁሉ ፡ ግሥገሣ
ለማየት ፡ ኖሯል ፡ ወይ ወድቆ ያንተ ሬሳ፤
ለካ ፡ መልካም ፡ ኖሯል ፡ ብቀር ፡ ሳልነሣ ።
ወደ፡እሱ፡ብመጣ ፡ እኔ አድርጌው ዘመድ፡
እሱስ ቀድሞኝ ሄዷልባላሰብኩት መንገድ
እንዳልቀየመው ፡ የኔ ፡ ከዳተኛ ፡
መጥቶ ፡ ካጠገቤ ፡ እዩት፡እንደ፡ተኛ ።
አወይ ፡ ሮሜዎ ፡ የኔ ፡ ሆደ ፡ ባሻ ፡
አንተ፡ እኔን ፡ ስትፈልግ እኔም አንተን ፡ ስሻ
ብቻህን ፡ ሄደሃል ፡ ሰው ፡ ቀርቶኛል ፡ ሳትል
የጭንቅ ፡ ወዳጅህን ፡ እኔን ፡ ሳታስከትል ፡
አልቀርም ፡ ጠብቀኝ ፡ ባለህበት ፡ ቦታ ፤
ኩባያህ ፡ ባዶ ፡ ነው ፡ የለውም ፡ ጠብታ ፡
አንተ ፡ ቢስ ፡ ሥሥታም ፡ ንፉግ ፡ መኰንኔ
ጨልጠህ ፡ ጠጣኸው ፡ ሳታስተርፍ ፡ ለኔ
ቆየኝ ፡ ደረስኩብህ ፡ በርሬ፡ እንደ ፡ አሞራ፤
ይኸው ፡መምጣቴ ነው ፡ እኔም ካንተ፡ ጋራ
አልሠራህበትም ፡ አንተ ፡ ባለቤቱ ፡
እስቲ ፡ ልታቀፈው ፡ ይግባ ፡ በስለቱ ፡
አንጀቴ ፡ ለጩቤህ ፡ ይሁነው ፡ አፎቱ ።
(በሮሜዎ ፡ ልቤ ፡ ሆዷን ' ወግታ ፡ ሞተች)

#የመጀመሪያ_ዘበኛ
በልምራን ወዴት ነው መንገዱና ስፍራው ?

#የፓሪስ_አሽከር
ይኸው እዚህ ነበር መብራት ፡ የሚበራው

#የመጀመሪያ_ዘበኛ
ምድሩ ፡ ደም ፡ ብቻ፡ነው፡ምድነው፡ ነገሩ?
እስቲ ፡ ቶሎ ፡ ግቡ ፡ ወደ ፡ መቃብሩ፡
ትልቁ ፡ መኰንን ፡ ፓሪስ ፡ ይኸው ፡ ሞቶ ፡
ቀርቷል ፡ በመሬት ፡ ላይ ፡እዚህ ፡ ተዘርግቶ
ከሁለት ፡ ቀን ፡ በፊት ፡ የቀበሯት፡ ሞታ ፡
ዝልዬትም ፡ ወድቃለች በጨቤ ፡ ተወግታ፡
እዩ ፡ ተመልከቱ ፡ በደም ፡ ተለውሳ ፤
አልብሶት ፡ የለም ፡ ወይ ፡ ሜዳውን 'ሬሳ ።
ደግሞስ ፡ ሮሜዎ ፡እዚህ ፡ምን አመጣው፤
እሱም ደግሞ ሞቷል ትንፋሽም አይወጣው ።
ቶሎ ፡ ንገሯቸው ፡ መስፍኑ፡ይጠሩ፤
ደግሞም ፡ ግማሻችሁ ፡ ስፍራውን ፡ መርምሩ ፡
ይጠሩ፡ እነ ፡ ሞንታግ ፡ ይምጡ ፡ እነ ፡ ካፑሌ ፤
ፍተሻ ፡ይደረግ ፡ በዚሁ ፡ ቀበሌ ፡
ምስክር ፡ ተገኝቶ ፡ታሪኩ ፡ እስቲሰማ ፡
የተሰወረ፡ ነው፡ ምስጢሩ ፡ ጨለማ ።

💫ይቀጥላል💫
#ሮሜዎና_ዡልዬት


#ክፍል_አስራ_አምስት(የመጨረሻ
ክፍል)

#ሁለተኛ_ዘበኛ
ይኸው ፡ አገኘነው ፡ የሮሜዎን ፡ አሽከር

#የመጀመሪያ_ዘበኛ
መስፍኑ ፡ እስቲመጡ፡ እንዳይመረመር ።
(ሦስተኛ ፡ ዘበኛ ፡ ከአባ ' ሎራ፡ጋራ፡ መጣ)

#ሦስተኛ_ዘበኛ
እያንቀጠቀጠው ፡ ጥግ ፡ ይዞ ፡ ሲያለቅስ
ይኸውና ፡ ደግሞ ፡ አገኘሁ ፡ አንድ ፡ ቄስ ፡
ለምን ፡ እንደ ፡ ያዘው ፡ አልታወቀም፡ ከቶ ፡
ጕጠቱን ፡ ቀማነው ፡ በእጁ ፡ ላይ ፡ተገኝቶ

#የመጀመሪያ_ዘበኛ
መስፍኑ ፡ እስቲመጡ ፡ እሱን ፡ አትልቀቁ ፤
የሚጠረጠር ፡ ነው ፡ ይዛችሁ ፡ ጠብቁ ።
(መስፍኑ ፡ ታጅቦ ፡ መጣ) ።

#መስፍን
እኔን ፡ የሚያስጠራ ፡ ሳይነጋ ፡ ሌሊቱ ፤
ምንድነው ፡ንገሩኝ ፡ እስቲ ፡ ምክንያቱ ? ..
(ካፑሌ ' ፤ ሚስቱና ሌሎች ሰዎች መጡ)

#ካፑሌ
ምስጢሩ ፡ ምንድነው ፡ የሰዉ ጫጫታ ?

#የካፑሌ_ሚስት
እረ ፡ እንዲህ ፡ አይደለም ፡ የሕዝቡ ጋጋታ ፡
ግማሹ ፡ ሮሜዎ ፡ ግማሹ ፡ ዡልዬት ፡
ግማሾቹም ፡ ፓሪስ ፡ እያሉ ፡ በጩኸት ፡
ወደ ፡ እኛ ፡ መቃብር ፡ ገቡ ፡ እየተጋፉ ።

#መስፍን
ነገሩን ፡ ንገሩኝ፡ ደግም ፡ ሆነ፡ ክፉ ።

#የመጀመሪያ_ዘበኛ
ልዑል ፡ ሆይ ፡ ያስተውሉ'ፓሪስን ፡ተገድሎ
እዩት ፡ ሮሜዎ ፡ መሬት ፡ ላይ ፡ ተንጋሎ ፡
ቀድሞ ፡ የሞተችው ፡ ዡልዬት ፡ ተመልሳ፣
እይዋት ፡ እሷ ፡ ደግሞ ፡ በደም ተለውሳ ።

#መስፍን
ይህ ፡ ዐመፅ ፡ እንደ፡ምን ፡ ሆኖ ፡ እንደ ፡ ተሠራ ፍጠኑ ፡ በቶሎ ፡ይደረግ ፡ ምርመራ

#የመጀመሪያ_ዘበኛ
የሮሜዎ ፡ ሎሌ ፥ ካንድ ፡ ካህን ፡ ጋራ ፡
እነሆ ፡ ተገኝቷል ፡ አሁን ፡ በዚህ ፡ ስፍራ ።

#ካፑሌ
ሚስቴ ፡ ተመልከቺ ፡ ልጃችን ፡ ተኝታ ፥
እዪው ፡ ደሟ ፡ ሲፈስ ሆዷ ላይ ፡ ተወግታ
አስተውዪው ይህ ጩቤ ከመጣበት ፡ ቦታ
ከሞንታግ ልጅ ላይ ነው ተመልከች አፎቱ
ባዶውን ፡ ይታያል ፡ ይግባሽ ፡ ምክንያቱ ።

#የካፑሌ_ሚስት
እባክህን ፡ ተወኝ ፡ እኔ ፡ አልችልም ፡ ማየት
ወይ፡ልጄ ፡ ወይ ልጄ ፡ ወይ፡ ልጄ ፡ ዝልዬት
ሐዘን ፡ ጨፈለቀኝ ፡ ውሃ ፡ ሆንኩኝ ፡ እኔ ፤
ይህንን ፡ ትልቅ ፡ ጕድ ፡ ይህንን ፡ ጭካኔ፡
ኣይችልም ፡ አይችልም። ሊመለከት ዐይኔ
(ሞንታግና ፡ ሌሎች ፡ ሰዎች ፡ መጡ) "

#መስፍን
ሞንታግ ፡ ወዲህ ፡ ቅረብ ፡ ተመልከተው ፡ አንተ ፡ልጅህን ፡ አስተውለው ፥ እየው ፡ እንደ ፡ ሞተ ።

#ሞንታግ
የልጅዋ ፡ መሰደድ ፡ ሆኖባት ፡ በሽታ ፡
ሚስቴ ፡ ሌሊት ፡ ሞተች በሐዘን ተጐድታ
ያሁን ፡ ሐዘኔ ፡ ግን በጣም ፡ ትልቅ መዓት
የባሰ ፡ ጐዳት፡ ነው ፡ የመጣ ፡ ለቅጣት ።

#መስፍን
እንባህን ፡ አግደው ፡ አትቸኵል ፡ ለማልቀስ
በፊት ፡ ምርመራውን ፡ ይገባል ፡ መጨረስ
ያመፁን ፡ ምክንያት፡ ምንጩን ፡ እንወቀው
ምርመራው ይጀመር አብረን ፡ እንዝለቀው
የተያዙት ፡ ሰዎች ፡ በፍጥነት ፡ ይቅረቡ ።

#አባ_ሎራ
እዚህ ፡ ያላችሁት ፡ አሁን ፡ ስታስቡ ፡
እኔ ፡ መገኘቴ ፡ በዚህ ፡ ዐመፅ ፡ ቦታ ፡
ያስጠረጥረኛል ፡ ገፍቶ ፡ በግዴታ ፡
ዳሩ ፡ ግን ፡ ነገሩን ፡ ልናገረውና ፡
ተረዱት ፡ ዕወቁት ፡ የኔን ፡ ንጽሕና ።

#መስፍን
ታሪኩን ፡ እንስማ ፡ በሉ ፡ ይናገሩ ።

#አባ_ሎራ
ሐተታ ፡ አላበዛም ፡ ልናገር ፡ ባጭሩ ፤
ረዥም ፡ አይደለም ፡ቀላል፡ ነው ምስጢሩ
መልካሙ ፡ ሮሜዎ ፡ ይህ አሁን ፡ የሞተው ለዡልዬት ፡ባሏ ነው በተክሊል ተጋብተው
ቃል ኪዳን ሞልተዋል ቈርበው እንደ ሕጉ
በሃይማኖት ሥራት ቃል፡ ኪዳን ሲያደርጉ
የተክሊሉን ፡ ሥራት ፡ ባርኮ ፡ የቀደሰው ፡
እኔው ፡ ራሴ ፡ ነኝ፤ አይደለም ፡ ሌላ ፡ ሰው
በዚያው ቀን ቲባልትን ቢገድለው ፡ ተፈርዶ
ከዚህ ፡ አገር ፡ ወጣ ፡ ሮሜዎ ፡ ተሰዶ፡
ዡልዬት ፡ ዘመዶቿ ፡ ይህንን ፡ ሳያውቁ ፡
ለፓሪስ ፡ ሊድሯት ፡ እሷን ፡ ቢያስጨንቁ ፡
በሐዘን ፡ አልቅሳ ፡ ነገረችኝ ፡ መጥታ ፤
ዘዴ ፡ ካልተገኘ ፡ በገዛ ፡ እጅዋ ፡ ሞታ ፡
ልትድን ፡ አሰበች ፡ ካገኛት ፡ ፈተና ፤
እኔም ፡ በዚህ ፡ ነገር ፡ በጣም ፡ አዘንኩና ፡
መድኀኒት ፡ ሰጠኋት ሕይወት ፡ አጠውልጎ
እንቅልፍ ፡ የሚያስተኛ እንደ ሞት ፡ አድርጎ
ከዚያም ፡ ለሮሜዎ ፡ ወረቀት ፡ ጽፌለት ፡
እንዲመጣ ፡አዘዝኩት ገሥግሦ በፍጥነት
ከእንቅልፋ፡ ስትነቃ የመርዙ ኃይል ፡ አልቆ
እንዲወስዳት ፡ ነበረ ውጭ ፡ አገር ፡ ደብቆ
የኔንም ፡ ወረቀት ፡ የወሰደልኝ ፡ ሰው ፡
የኛ ፡ ካህን ፡ ነበር ፤ እሱም ፡ ሳያደርሰው ፡
እክል፡ ስላገኘው ፡ በሄደበት ፡ ቦታ ፡
መልሶ ፡ አመጣልኝ ፡ ትናንትና ፡ ማታ ።
የዡልየት ፡ መነሻ ፡ ሌሊት ፡ ስለ ፡ ነበር ፡
እኔም ፡ በጨለማ ፡ መጣሁ ፡ ስደናበር ፡
አሳቤ ፡ ነበረ ፡ ሮሜዎ ፡እስቲመጣ ፡
ደብቄ ፡ ላቆያት ፡ ከቤት ፡ ሳላስወጣ ፡
ዳሩ፡ግን ፡ ገሥግሼ ፡ እኔ ፡ ከዚህ ፡ ስደርስ
ወድቀው ፡ አየኋቸው ፡ ሮሜዎና፡ ፓሪስ ።
እሷም ፡ ነቃችና ፡ ወዲያው ፡ ስትነሣ ፡
እግዜር ፡ ያመጣውን ፡ ብትቀበል ፡ ታግሣ
የሚሻል ፡ መሆኑን ፡ ላስረዳት ፡ ሞክሬ ፡
ከደጅ ፡ ድምፅ ሰማሁ ሳጥናናት በምክሬ
ለመንኳት ፡ እንድትሄድ ፡ እኔን ፡ ተከትላ ፥
ምክሬን ፡ አልሰማችም ቀረች እንቢ ፡ ብላ
እኔም ፡ የመጣውን ፡ ለማየት ፡ በኋላ ፤
ወጥቼ ፡ መጣሁኝ ፡ ይኸው ፡ እዚህ ፡ ቦታ
ያስረዳ፡ ነበረ ፡ የዡልዬት ፡ ሁኔታ ፡
ሐዘኗ ፡ መሆኑን ፡ በጣም ፡ የበረታ ።
ከዚያ በኋላ ፡ ግን ፡ የሆነውን ፡ ነገር ፡
አላየሁምና ፡ አልችልም ፡ መናገር ፡
ዡልዬት ፡ ሮሜዎን በተክሊል ፡ ማግባቷን
ታውቀዋለችና ፡ ጠይቁ ፡ ሞግዚቷን ፡
እንግዴህ ፡ ልቀጣ ፡ ቃሌ ፡ ቢገኝበት ፡
በውስጡ ፡ የገባ ፡ ሐሰትና፡ ውሸት

#መስፍን
ጻድቅ ፡ሰው ኣድርገን ፡እርስዎን ከማክበር
አቋርጠን ፡ አናውቅም የሮሜዎን ፡ አሽከር
በፍጥነት ፡ አቅርቡት ፡ ያየውን ፡ ይናገር ።

#ቤልሻጥር
የዡልዬትን ፡ መሞት ፡ ጌታዬ ፡ ብነግረው ፡
መርዶውን ፡ ሲሰማ ፡ ሐዘን ፡ አሰከረው ፡
ወዲያው ፡ ተነሣና ፡ እየገሠገሠ ፡
ሌሊት ፡ እዚህ ፡ ቦታ ፡ ከኔ ፡ ጋር ፡ ደረሰ ።
ይህንን ፡ ደብዳቤ ፡ ላባቴ ፡ ስጥ ፡ ብሎ ፡
እኔን ፡ እንዳልገባ ፡ በብርቱ ፡ ከልክሎ ፡
ትእዛዙን ፡ ባልፈጽም ፡ በሞት ፡ አስፈራርቶ
አየሁት ፡ ሲገባ ፡ እኔን ፡ እዚህ ፡ ትቶ ።

#መስፍን
ደብዳቤውን ፡ ስጠኝ እስቲ ፡ ልመልከተው
የፓሪስም ፡ አሽከር ፡ ይጠራ ወዴት ፡ ነው ?
(የፓሪስአሽከር ፡ ቀረበ) ።
ሌሊት ፡ በጨለማ ፡ ደግሞ ፡ ያንተ ፡ ጌታ ፡
እዚህ ፡ ለምን ፡ መጣ ፡ እመቃብር ፡ ቦታ ?

#የፓሪስ_አሽከር
አበባ ፡ ሊያስቀምጥ ፡ እመቃብሯ ፡ ላይ ፡
መጣና ፡ እኔንም ፡ እዚሁ ፡ ሁኜ ፡ እንዳይ ፡
አዞኝ ፡ እንድጠብቅ ፡ እዚህ ፡ እንድቀመጥ
ሰው ፡የመጣ እንደሆን ምልክት እንድሰጥ
ስጠብቅ አንድ፡ ሰው፡ መብራት ይዞ መጣ
አፍጨሁ ፡ ጌታዬም ፡ ከመቃብር ፡ ወጣ ።
ሁለቱ ፡ ሲዋጉ ፡ ይኸው ፡ እዚህ ፡ ስፍራ ፡
ቶሎ ፡ ሮጬ ፡ ወጣሁ ፡ ዘበኛ ፡ ልጠራ ።

#መስፍን
አምነን ፡ ለመቀበል ፡ እኛ ፡ የቄሱን ፡ ቃል ፡
ተመልክቼዋለሁ ፥ ደብዳቤው ፡ ይበቃል ።
የፍቅራቸው ፡ ነገር ፡ የዡልዬትም ፡ መሞት
ይኸው ፡ ይነበባል ፡ በደብዳቤው ፡ ጽፎት
ሁሉንም ፡ ገልጦታል ፤ ከዡልዬትም ፡ ጋራ
ለመሞት መምጣቱን ይኸው እዚህ ስፍራ
መድኀኒት የሚሸጥ ድኻ ሰው ፡ አግኝቶ
መርዝ
👎1