#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...ወደ ሆስፒታል ገሰገሰች
ፍፁም የህክምና ሰወች ተረባርበዉ ትንሽ ነብሱ መለስ አለች
ህመሙን የሚቀንስ መድሀኒት ተሰጥቶት ከዋጠ በኋላ
ከትራሱ ጋር ድጋሜ ጭንቅላቱን አገናኘዉ
እንደ ህመም ከባድ ወቅት የለም በጤነኝነት ስንኖር ዋጋ ሰጥተን
ባናስበዉም ስንታመም እና ስቃይ ዉስጥ ስንሆን ግን ሁሉ ነገራችን ተወስዶ ጤናችን ቢመለስ እንለምናለን
አብዛኞቻችን ለጤናችን አስበን አናዉቅም ጥንቃቄም የለንም
ምኞታችን ብር ላይ ያተኮረ ይሆናል ይለፋል ይለፋል በስተመጨረሻ ጤና ጠፍቶ ስንሰቃይ በህመም እጅ ዉስጥ
ስንወድቅ ብራችንን በሙሉ ለጤናችን መልሰን እናዉላለን
እንደ ፍፁም በአደጋ ህመም ላይ ሲወደቅ ግን ምን ይደረጋል
ሳያስበዉ እና ሳይጠብቀዉ ለዚህ በቃ የዚህ ሁሉ ጦስ ደግሞ
የፍቃዱ ተንኮል በተጨማሪም የቤዛዊት ማገናዘብ አለመቻል ናቸዉ።
እንቅልፍ መተኛት ባይፈልግም አልጋዉ ላይ ጋደም ብሎ
አይኖቹን ያንከራትታል
"እግሬ ለወደፊቱም መራመድ ባይችልስ?"
በድን እግሮቹን ለማንቀሳቀስ እየሞከረ
በፊት ልጅ እያለ ከጉዋደኞቹ ጋር እሩጫ ሲወዳደሩ አንደኛ እንደሚወጣ አስታዉሶ ፈገግ አለ ወደ አሁኑ ያለበት ህይወት ሲያስብ ግን እንባ እና ተስፋ መቁረጥ
ስለሚከቡት ላለማሰብ በብርድ ልብሱ ተጠቅልሎ ተኛ።
ቤዛዊት ብቻዋን እንድትሄድ ቤተሰቦቿ አልፈቀዱላትም ነበር
እህቷ አብራት ነበረች የተኛበትን አልጋም ስለምታዉቀዉ ልታሳያት ተከተለቻት።
ከቦታዉ ደርሰዉ አልጋዉ አጠገብ ቆሙ ተጠቅልሎ የተኛ አካል
በብርድ ልብሱ ቅርፅ ሰርቶ ይታያል ፍፁምን ለማየት የጓጓችዉ
ቤዛዊት እንዲነሳ እግሩን በእጆቿ ነካ ነካ ነረገችዉ አልሰማ አላት
"ፍ ፁ ም ..."
እህቷ የፍፁም እግሮች እንደማይሰሩ እንደማይሰሙ
ብታዉቅም ለመንገር ግን
ከብዷት እህቷ የምታረገዉን በሀዘኔታ ታያለች።
"ፍ ፁ ም ፍፁም..."
የሚሉ ቃላቶች የእዉነት እየሆኑ በቅዠት መልክ ስለተሰሙት
አቤት ለማለት አይኖቹን ከፍቶ ከብርድ ልብሱ ተገለጠ
ፊት ለፊቱ ቤዛዊት ቆማለች የጠቆረች የከሳች የተጎዳች መሰለዉ
ለማማተብ የዘረጋዉን እጁን አይኑን ባለማመን ጠራረገበት
እሷ ፊት ላይ ለስለስ ያለ ፈገግታ እየታየ ቀረበችዉ
ወደ ጉንጮቹ ከመጠጋቷ በፊት እህቷን አየት አርጋት ሳመችዉ
እህቷም ስለገባት እንዲያወሩ ጥላቸዉ ወደ ዉጪ ወጣች
የደረቀ እና የተጣበቀ ከንፈሩን እያለያየ
"እንዴት ነሽ ቤዚ..."
"ደህና ነኝ አንተስ አልተጎዳክም አደል ..."
በእጆቿ እየደባበሰችዉ
"ምንም አልተጎዳሁም..."
ህመሙን ዋጥ እያረገ እሷ ስለመጣች ደስ እያለዉ
ፊቷን አተኩሮ እያየ ፈግታዋ እንደድሮዋ አልደምቅልህ አለዉ
ደህንነቷ አሰጋዉ ጠፍታ ነበር የተባለዉን አስታዉሶ ልጠይቃት
አልጠይቃት እያለ በዉስጡ ማሰብ ጀመረ።
በእስዋ በኩልም ፍፁምን ታሞ አልጋ ላይ ስታየዉ ዉስጧ እርብሽ ብሏል ከትምህርት ቤት እንደተባረረ ወሬ
ስለሰማች በእሷ ምክንያት መሆኑን ገምታለች
የተገጨዉም ይሄኔ እኔን ለማዋራት ትምህርት ቤት ሲመጣ
ነዉ እያለች ሁለቱም በራሳቸዉ ሀሳብ ሰምጠዉ ቆይተዉ
"ቀሚስሽ ደሞ እንዴት ያምራል .."
ጨዋታ ለመጀመር አስቦ ለየት ስላለበት አለባበሷ
"የእማማ ስንቄ ነዉ እንዴት ጥሩ ሰዉ መሰሉክ የሆነ ቀን አብረን ሄደን አስተዋዉቅሀለዉ..."
መራመድ እንደማይችል ትዝ ስላለዉ ማዉራት እየከበደዉ
በመስማማት አንገቱን ነቀነቀ
"ምግብ በልተሀል ለምን ከአልጋ ወርደህ አትቀመጥም "
ፈጠን ያለ ጥያቄ ጠየቀችዉ
"በልቻለሁ.."
ተስፋ በቆረጠ አነጋገር
ቤዛዊት መቀመጥ ብቻ ሳይሆን ተነስቶ ተቃቅፈዉ
የሆድ የሆዳቸዉን እያወሩ ከሚጨንቀዉ ሆስፒታል
ፍፁምን ይዛዉ ብትወጣ ደስታዋ ነዉ
ነገር ግን ፍፁም መንቀሳቀስ የፈለገ አልመሰላትም
"ተቀይመሀኛል እንዴ መጥቼ ስላልጠየኩህ"
ከንፈሯን እያጣመመች
"አረ አልተቀየምኩሽም"
እጆቹን ሰዶ እጆን ያዛት
"እሺ ተነስ..."
አይኖቹን እስዋ ላይ ተክሎ እግሮቹን ለማንቀሳቀስ መታገል ጀመረ
"እ ህ ..........አ"
እየከበደዉ እልህ እየተናነቀዉ በእጆቹ ታግዞ
አልጋዉ ጠርዝ ላይ በመከራ ተቀመጠ
ቤዛዊት ግራ ተጋብታ እያየችዉ ነዉ ልታግዘዉ እየሞከረች
እንዳትረዳዉ በእጆቹ ምልክት ስላሳያት ፈዛ በሀዘኔታ ታየዋለች
በደንብ አልተሻለዉም በማለት እንባዋን ለመቆጣጠር እየታገለች
ከጀርባዋ ያለዉን ዊልቸር እየጠቆማት
"እሱን ጠጋ አርጊልኝ"
አዘዛት
ላለ ማልቀስ እየታገለች አስጠጋችለት ከአልጋዉ ወርዶ
ዊልቸሩ ላይ ሊቀመጥ ሲል ግን
የዊልቸሩ ጎማወች ስለሚንቀሳቀሱ ለመቀመጥ ሲታገል
ሚዛኑን ሳቶ ከመዉደቅ ቤዛዊት በእጆቿ ደግፋ አተረፈችዉ
ተደናግጠዉ ተያዩ ወድያዉ እንዲቀመጥ ካገዘችዉ በኋላ መሳቅ ጀመሩ።
የቤዛዊት እህት ተመልሳ ወደ ፍፁም እና ቤዛዊት ተጠጋች
ልብ አላሏትም ሁለቱም የሞቀ ጨዋታ ላይ ናቸዉ
እስከ አሁን ይነግራታል ብላ በማሰብ
"እግርህ አሁን ለዉጥ አለዉ..."
ወሬያቸዉን አቋርጠዉ ተመለከቷት
"ጥሩ ነዉ ለዉጥ አለዉ "
አላት እና ፈገግ አለ ቤዛዊት ባትኖር መዉደቁ እንደ ነበር
እያስታወሰ የቤዛዊት እህትም ፊቱ ላይ ፈገግታ ስታይ ሳቀች
ፈገግታዋ ከቤዛዊት ጋር ይመሳሰላል ፍፁም ተገርሞ አያት በልቡ
"ቁጭ ቤዛዊትን" እያለ
ቤዛዊት የእህቷን አሳሳቅ አልወደደችዉም ደስ አላላትም
ዉስጧ ንዴት እየተቀጣጠለ ነዉ ህመሟ መንስኤ ነዉ የሚፈልገዉ
በተለይ የፍፁምንም እህቷን እያየ መሳቁን ስታይ
"እገላታለሁ"
ስትል በታመዉ ህሊናዋ እህቷ ላይ ዛተች።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...ወደ ሆስፒታል ገሰገሰች
ፍፁም የህክምና ሰወች ተረባርበዉ ትንሽ ነብሱ መለስ አለች
ህመሙን የሚቀንስ መድሀኒት ተሰጥቶት ከዋጠ በኋላ
ከትራሱ ጋር ድጋሜ ጭንቅላቱን አገናኘዉ
እንደ ህመም ከባድ ወቅት የለም በጤነኝነት ስንኖር ዋጋ ሰጥተን
ባናስበዉም ስንታመም እና ስቃይ ዉስጥ ስንሆን ግን ሁሉ ነገራችን ተወስዶ ጤናችን ቢመለስ እንለምናለን
አብዛኞቻችን ለጤናችን አስበን አናዉቅም ጥንቃቄም የለንም
ምኞታችን ብር ላይ ያተኮረ ይሆናል ይለፋል ይለፋል በስተመጨረሻ ጤና ጠፍቶ ስንሰቃይ በህመም እጅ ዉስጥ
ስንወድቅ ብራችንን በሙሉ ለጤናችን መልሰን እናዉላለን
እንደ ፍፁም በአደጋ ህመም ላይ ሲወደቅ ግን ምን ይደረጋል
ሳያስበዉ እና ሳይጠብቀዉ ለዚህ በቃ የዚህ ሁሉ ጦስ ደግሞ
የፍቃዱ ተንኮል በተጨማሪም የቤዛዊት ማገናዘብ አለመቻል ናቸዉ።
እንቅልፍ መተኛት ባይፈልግም አልጋዉ ላይ ጋደም ብሎ
አይኖቹን ያንከራትታል
"እግሬ ለወደፊቱም መራመድ ባይችልስ?"
በድን እግሮቹን ለማንቀሳቀስ እየሞከረ
በፊት ልጅ እያለ ከጉዋደኞቹ ጋር እሩጫ ሲወዳደሩ አንደኛ እንደሚወጣ አስታዉሶ ፈገግ አለ ወደ አሁኑ ያለበት ህይወት ሲያስብ ግን እንባ እና ተስፋ መቁረጥ
ስለሚከቡት ላለማሰብ በብርድ ልብሱ ተጠቅልሎ ተኛ።
ቤዛዊት ብቻዋን እንድትሄድ ቤተሰቦቿ አልፈቀዱላትም ነበር
እህቷ አብራት ነበረች የተኛበትን አልጋም ስለምታዉቀዉ ልታሳያት ተከተለቻት።
ከቦታዉ ደርሰዉ አልጋዉ አጠገብ ቆሙ ተጠቅልሎ የተኛ አካል
በብርድ ልብሱ ቅርፅ ሰርቶ ይታያል ፍፁምን ለማየት የጓጓችዉ
ቤዛዊት እንዲነሳ እግሩን በእጆቿ ነካ ነካ ነረገችዉ አልሰማ አላት
"ፍ ፁ ም ..."
እህቷ የፍፁም እግሮች እንደማይሰሩ እንደማይሰሙ
ብታዉቅም ለመንገር ግን
ከብዷት እህቷ የምታረገዉን በሀዘኔታ ታያለች።
"ፍ ፁ ም ፍፁም..."
የሚሉ ቃላቶች የእዉነት እየሆኑ በቅዠት መልክ ስለተሰሙት
አቤት ለማለት አይኖቹን ከፍቶ ከብርድ ልብሱ ተገለጠ
ፊት ለፊቱ ቤዛዊት ቆማለች የጠቆረች የከሳች የተጎዳች መሰለዉ
ለማማተብ የዘረጋዉን እጁን አይኑን ባለማመን ጠራረገበት
እሷ ፊት ላይ ለስለስ ያለ ፈገግታ እየታየ ቀረበችዉ
ወደ ጉንጮቹ ከመጠጋቷ በፊት እህቷን አየት አርጋት ሳመችዉ
እህቷም ስለገባት እንዲያወሩ ጥላቸዉ ወደ ዉጪ ወጣች
የደረቀ እና የተጣበቀ ከንፈሩን እያለያየ
"እንዴት ነሽ ቤዚ..."
"ደህና ነኝ አንተስ አልተጎዳክም አደል ..."
በእጆቿ እየደባበሰችዉ
"ምንም አልተጎዳሁም..."
ህመሙን ዋጥ እያረገ እሷ ስለመጣች ደስ እያለዉ
ፊቷን አተኩሮ እያየ ፈግታዋ እንደድሮዋ አልደምቅልህ አለዉ
ደህንነቷ አሰጋዉ ጠፍታ ነበር የተባለዉን አስታዉሶ ልጠይቃት
አልጠይቃት እያለ በዉስጡ ማሰብ ጀመረ።
በእስዋ በኩልም ፍፁምን ታሞ አልጋ ላይ ስታየዉ ዉስጧ እርብሽ ብሏል ከትምህርት ቤት እንደተባረረ ወሬ
ስለሰማች በእሷ ምክንያት መሆኑን ገምታለች
የተገጨዉም ይሄኔ እኔን ለማዋራት ትምህርት ቤት ሲመጣ
ነዉ እያለች ሁለቱም በራሳቸዉ ሀሳብ ሰምጠዉ ቆይተዉ
"ቀሚስሽ ደሞ እንዴት ያምራል .."
ጨዋታ ለመጀመር አስቦ ለየት ስላለበት አለባበሷ
"የእማማ ስንቄ ነዉ እንዴት ጥሩ ሰዉ መሰሉክ የሆነ ቀን አብረን ሄደን አስተዋዉቅሀለዉ..."
መራመድ እንደማይችል ትዝ ስላለዉ ማዉራት እየከበደዉ
በመስማማት አንገቱን ነቀነቀ
"ምግብ በልተሀል ለምን ከአልጋ ወርደህ አትቀመጥም "
ፈጠን ያለ ጥያቄ ጠየቀችዉ
"በልቻለሁ.."
ተስፋ በቆረጠ አነጋገር
ቤዛዊት መቀመጥ ብቻ ሳይሆን ተነስቶ ተቃቅፈዉ
የሆድ የሆዳቸዉን እያወሩ ከሚጨንቀዉ ሆስፒታል
ፍፁምን ይዛዉ ብትወጣ ደስታዋ ነዉ
ነገር ግን ፍፁም መንቀሳቀስ የፈለገ አልመሰላትም
"ተቀይመሀኛል እንዴ መጥቼ ስላልጠየኩህ"
ከንፈሯን እያጣመመች
"አረ አልተቀየምኩሽም"
እጆቹን ሰዶ እጆን ያዛት
"እሺ ተነስ..."
አይኖቹን እስዋ ላይ ተክሎ እግሮቹን ለማንቀሳቀስ መታገል ጀመረ
"እ ህ ..........አ"
እየከበደዉ እልህ እየተናነቀዉ በእጆቹ ታግዞ
አልጋዉ ጠርዝ ላይ በመከራ ተቀመጠ
ቤዛዊት ግራ ተጋብታ እያየችዉ ነዉ ልታግዘዉ እየሞከረች
እንዳትረዳዉ በእጆቹ ምልክት ስላሳያት ፈዛ በሀዘኔታ ታየዋለች
በደንብ አልተሻለዉም በማለት እንባዋን ለመቆጣጠር እየታገለች
ከጀርባዋ ያለዉን ዊልቸር እየጠቆማት
"እሱን ጠጋ አርጊልኝ"
አዘዛት
ላለ ማልቀስ እየታገለች አስጠጋችለት ከአልጋዉ ወርዶ
ዊልቸሩ ላይ ሊቀመጥ ሲል ግን
የዊልቸሩ ጎማወች ስለሚንቀሳቀሱ ለመቀመጥ ሲታገል
ሚዛኑን ሳቶ ከመዉደቅ ቤዛዊት በእጆቿ ደግፋ አተረፈችዉ
ተደናግጠዉ ተያዩ ወድያዉ እንዲቀመጥ ካገዘችዉ በኋላ መሳቅ ጀመሩ።
የቤዛዊት እህት ተመልሳ ወደ ፍፁም እና ቤዛዊት ተጠጋች
ልብ አላሏትም ሁለቱም የሞቀ ጨዋታ ላይ ናቸዉ
እስከ አሁን ይነግራታል ብላ በማሰብ
"እግርህ አሁን ለዉጥ አለዉ..."
ወሬያቸዉን አቋርጠዉ ተመለከቷት
"ጥሩ ነዉ ለዉጥ አለዉ "
አላት እና ፈገግ አለ ቤዛዊት ባትኖር መዉደቁ እንደ ነበር
እያስታወሰ የቤዛዊት እህትም ፊቱ ላይ ፈገግታ ስታይ ሳቀች
ፈገግታዋ ከቤዛዊት ጋር ይመሳሰላል ፍፁም ተገርሞ አያት በልቡ
"ቁጭ ቤዛዊትን" እያለ
ቤዛዊት የእህቷን አሳሳቅ አልወደደችዉም ደስ አላላትም
ዉስጧ ንዴት እየተቀጣጠለ ነዉ ህመሟ መንስኤ ነዉ የሚፈልገዉ
በተለይ የፍፁምንም እህቷን እያየ መሳቁን ስታይ
"እገላታለሁ"
ስትል በታመዉ ህሊናዋ እህቷ ላይ ዛተች።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
#ልጩህበት!!
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ምኑን ከምኑ ነው እምመርጠው?
"ወይ ኤደንን እኔ ሄጄ እንዳናግራት መፍቀድ ካልሆነ ከልጅቷ ጋር ፍቅር ጀምረህ ኤደንን መርሳት!"
ጆሲ አምርሯል ግራ ገባኝ ። ኤዱን እንዲያናግራት በጭራሽ እንደማልፈልግ አውቃለሁ ሁለተኛው ምርጫ ደግሞ ጡጫ ሆነብኝ ቢሆንም•••
ውስጤ እንደማይሆን እያወቀው ከዳኒ ጭቅጭቅ ለመገላገል ስል •እሺ አልኩት
በቃ እሺ!
"በቃ እሺ ምን በየትኛው ሀሳብ?"
"በቃ ካልካት ልጅ ጋር እንቀራረባለና!"
አዋ ዳንዬ አንዳንዴ እንኳን እንደዚህ እሺ በለኝ እስቲ ዳንዬ ዋናው መቀራረባችሁ ነው ከዛ ቡሀላ ሌላው ይከተላል ኤዱንስ ቢሆን ሳትቀርባት አላፈቀርካት!"
እሺ አልኩህ እኮ በቃ አልኩት። ከዛች ሰአት ጀምሮ ጆሲ ስራውን ጀመረ ።
ልጅቷን እቤት ያመጣትና መጣሁ ብሎ በመውጣት ጥሎን ይጠፋል።
መቀራረብ ብንጀምርም እውነቱን ለመናገር እሷን ለብቻዋ ከማገኛት ይልቅ ኤዱን ከልጁ ጋር ሆና ባገኛት እመርጥ ነበር።
ለሶስት ወር ልጅቷ እና ጆሲ ስራ አደረጉኝ የተቀየረ ስሜት አልነበረም በመሀል ድንገት ለተከታታይ ቀናት ጥፍት አለች።
ለስድስት ቀን ያህል ድምጿንም ስልኳንም አጥፍታ ከተሰወረች ቡሀላ በሰባተኛው ቀን እኔና ጆሲ ሰፈር ውስጥ ቁጭ ባልንበት እራሷ ጆሲ ስልክ ላይ ደወለች።
ስልኩን ለሁለታችንም እንዲሰማ አደረገና •••
" ምን ሆነሽ ነው የጠፋሽው?" የጆሲ ጥያቄ ነበር
" ምን ላድርግ ጓደኛህ ኤደን የምትባል ሰይጣን አጠናፍራዋለች መሰለኝ በተገናኘን ቁጥር ወሬው ሁሉ ከሷ አያልፍም እንዴ እኔ ልጅቷን ሳላውቃት ሁላ እንድጠላት ነው ያደርገኝ በጣም ነው የተጎዳሁት ጆሲ ከቻልክ ጓደኛህን ወይ አሳክመው ወይ ፀበል ውሰደው " ብላው እርፍ አለች ።
ጆሲ ዘወር ብሎ ሲያፈጥምኝ ተነስቼ ካጠገቡ ሄድኩ።
ከዛን ቀን ቡሀላ ከጆሲ ጋር ስለምንም ነገር ሳናወራ የኤዱ ምርቃት ሰባት ቀን( ሳምንት) ቀረው ።
ስድስት ቀን ሲቀረው ደውላ ቤተሰቦቿ ለምርቃቷ ከሁለት ቀን ቡሀላ እንደሚመጡ እና ከምርቃቷ ቡሀላ አብራቸው ወደ አዲስ አበባ እንደምትሄድ ነገረችኝ ።
ይህ ንግግሯ መብረቅ በሉት ለኔ ።ጨነቀኝ ።
ያን ቀን ጠጥቼ ብገባም እንቅልፍ እንቢ አለኝ እኩለ ለሊት ላይ አንድ ሀሰብ መጣልኝ።
ተነስቼ ለኤዱ ደብዳቤ መፃፍ ጀመርኩ•••
••••• ለኤደን
ኤዱዬ ህይወትን መራራም ጣፋጭም እንድትሆን ካደረጓት ምክንያቶች አንዱ ምን እንደሆነ ታውቂያለሽ?
እኛ ሰዎች ስላለፈው እና ስለ አሁኑ እንጂ ነገ ምን እንደሚፈጠር እለማወቃችን ነው ።
ነገን አለማወቅ የራሱ የሆነ ብዙ ጥሩም መጥፎም ገፅታዎች አሉት።
ነገ የሚከሰተውን መጥፎ ነገር ቀድመን ስናውቅ እና ነገ የሚከሰተውን ጥሩ ነገር ቀድመን ስናውቅ የሚሰሙን ሁለት ተቃራኒ ስሜቶች ናቸው።
እንዲህ ያልኩሽ አሁን የሆንኩትን ነገር ያኔ በዛ በብርድ እዛ ሆቴል በር ላይ ቆመሽ ባየሁሽ ሰአት ቀድሜ ባውቀው ምን እወስን ነበር ብዬ ሁሌም እራሴን ስለምጠይቀው ነው
"አሁን ምን ሆንክ? ትይ ይሆኖል። ምንም አታውቂምና ጥያቄሽ ልክ ነው የኔ ስስት ያኔ ካሁን ቡሀላ ወንድምሽ ነኝ ስልሽ አንቺም ተቀብለሽ የእውነት ወንድም አድርገሽኛልና ምን ሆንክ ብትይኝ ባንቺ አይፈረድም እኔ ግን ብዙ ሆኛለሁ አንቺን በማፍቀሬ እንኳን አንቺ እኔ እንኳን የማላውቀው ሌላ ዳኒ እንደሆኑኩ አውቃለሁ።
ኤዱዬ አፈቅርሻለሁ!
ይህን ስታነቢ ምን ትይኝ ይሆን?
በቃሌ የማልገኝ እራስ ወዳድ ነኝ አደል ኤዱዬ?
በጣም ይቅርታ።
ከግዜ ቡሀላ ለኔም ባልገባኝ መንገድ ውስጤ ተቀያይሮ ካቅሜ በላይ ሆኖብኝ እንጂ ያኔ ወንድም እሆንሻለሁ ከጎንሽ ነኝ እንደወንድምሽ እይኝ ያልኩሽ ግን ከልቤ ነበር!።
ሁሌም ቃሌን ያጠፍኩ መስሎ ይሰማኛል ላንቺ ስላልነገርኩሽ ምንም ባትይኝም ብታውቅ ምን ትለኛለች እያልኩ ከመሸማቀቅ አልዳንኩም።
ፍቅር የሻቱትን ማግኘት ብቻ አይደለምና የኔ እንደማትሆኚ እያሰብኩም አፈቅርሻለሁ።
ከምንም ነገር በላይ አንቺን በእውኔም በህልሜም ማየት፣ ስላንቺ ማሰብ ፣ ስላንቺ ማውራት ያስደስተኛል ። ካንቺ ውጪ ሁሉ ነገር አልጥምህ ካለኝ ወራቶች ተቆጥረዋል።
"ታድያ በነበረን ግዜ በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ውስጥ ከነበርክ እንዴት አልነገርከኝም?
ወይም እንዴት ከፊትህ መረዳት አልቻልኩም? " ትይኝ ይሆናል
በፍቅር ንዳድ ከመለብለብ በላይ በልብ ውስጥ ያለውን የፍቅር እሳት አውጥቶ ላፈቀሩት ሰው ንዳዱን ማሳየት ለብዙ አፍቃሪዎች ከባድ ነው።
እኔን ግን አውጥቶ ከመናገሩም በላይ ከባድ የሆነብኝ ብነግርሽ የሚሰማሽን ስሜት ማሰብ ነው።
ፍቅረኛሽ ሆኜ ቢሆን አሁን ወንድምሽ በመሆኔ የተደሰትሽውን ያክል እምትደሰቺ መስሎ አይታየኝም ።
ካፌ ሻይ ቡና እያልን ፊት ለፊቴ ቁጭ ብለሽ ከናት ካባቴ ባትወለድም አንተን የመሰለ ወንድም በስጦታ ስለሰጠኝ እያልሽ ፈጣሪን ስታመሰግኚ ስሰማ እንኳን ልነግርሽ ማፍቀሬን የምታውቂብኝ እየመሰለኝ ምክንያት ፈጥሬ ካጠገብሽ እሽሻለሁ ።
ጆሲ ጓደኛዬ ምን እንደሚለኝ ታውቂያለሽ ኤዱዬ?
••••" አንተኮ መፍታት ያቃተህ መጀመሪያ ላይ እራስህ አጥብቀህ ያሰርከውን ቋጠሮ ነው አልፈታ ባለህ ቁጥር ደግሞ በንዴት ለመበጠስ እየሞከርክ የበለጠ ታጠብቀዋለህ!" ይለኛል
እውነቱን ነው ትዝ ይልሻል እዱዬ?
ስለመሲ ስናወራ አንድ ሰው ውለታ ውሎልሽ ውለታውን በመንተራስ ከፍላጎትሽ ውጪ የሚጫንሽ ከሆነ ውለታ ሳያስቀድም ተመሳሳይ ጥያቄ ከሚጠይቅሽ ሰው በላይ እርኩስ ነው ብዬሽ ነበር ።
እኔም የፍቅር ጥያቄዬ ካደረኩልሽ ትንሽ ውለታ ጋር እንዳይያያዝብኝ ፈራሁ።
አንቺንም እኔን ወንድም እንጂ ፍቅረኛ የማድረግ ፍላጎት ውስጥሽ ሳይኖር የምጫንሽ ጥያቄዬን ባለመቀበልና እኔን ባለማስከፋት መሀል ሆነሽ የምትጨነቂ መስሎ ታየኝ ።
በዚህ መሀል እናንተ ባታዩኝም ከልጁ ጋር ሆኖችሁ ብዙ ቦታዎች ታጋጥሙኝ ጀመር።
ያኔ በሱም ባንቺም ሳይሆን በራሴ ይበልጥ መናደድ ጀመርኩ ።
ህመምህ መድሀኒት የለውም አትድንም እንደተባለ በሽተኛ የፍቅር ህመሜ ፈውስ የሆንሽውን አንቺን የኔ እንደማላደርግሽ ተረዳሁ ።
ኤዱዬ በመመረቅሽ እንኳን ደስ አለሽ!
በመመረቅሽ የተሰማሽን ደስታ ትንሽ ሳታጣጥሚውና ከድሬ ሳትወጪ አንብበሽው ሌላ ስሜት ውስጥ እንድትገቢ ስላልፈለኩ ነው ይህን ደብዳቤ በእጅሽ ሳልሰጥሽ ከምርቃቷ ቡሀላ ወደ አዲስ አባባ ስሸኛት ሳታየኝ የልብስ ሻንጣዋ ውስጥ አስቀምጥላታለሁ ባየችው ግዜ ትየው ብዬ የወሰንኩት።
በነበረን ስሜት ወንድምሽ ሆኜ ልሸኝሽ ቀናቶች ቀርተዋል ለዛም ተዘጋጅቻለሁ ።
የኔ ኤደን ዛሬም ቢሆን ስላወኩሽ ደስተኛ ነኝ።
የማንም ሁኚ እኔ ግን አፈቅርሻለሁ። መቼም ቢሆን አረሳሽም። ዝምምምም ብዬ ሳፈቅርሽ እኖራለሁ።
ሰላም ሁኚ!
ዳኒ ነኝ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ምኑን ከምኑ ነው እምመርጠው?
"ወይ ኤደንን እኔ ሄጄ እንዳናግራት መፍቀድ ካልሆነ ከልጅቷ ጋር ፍቅር ጀምረህ ኤደንን መርሳት!"
ጆሲ አምርሯል ግራ ገባኝ ። ኤዱን እንዲያናግራት በጭራሽ እንደማልፈልግ አውቃለሁ ሁለተኛው ምርጫ ደግሞ ጡጫ ሆነብኝ ቢሆንም•••
ውስጤ እንደማይሆን እያወቀው ከዳኒ ጭቅጭቅ ለመገላገል ስል •እሺ አልኩት
በቃ እሺ!
"በቃ እሺ ምን በየትኛው ሀሳብ?"
"በቃ ካልካት ልጅ ጋር እንቀራረባለና!"
አዋ ዳንዬ አንዳንዴ እንኳን እንደዚህ እሺ በለኝ እስቲ ዳንዬ ዋናው መቀራረባችሁ ነው ከዛ ቡሀላ ሌላው ይከተላል ኤዱንስ ቢሆን ሳትቀርባት አላፈቀርካት!"
እሺ አልኩህ እኮ በቃ አልኩት። ከዛች ሰአት ጀምሮ ጆሲ ስራውን ጀመረ ።
ልጅቷን እቤት ያመጣትና መጣሁ ብሎ በመውጣት ጥሎን ይጠፋል።
መቀራረብ ብንጀምርም እውነቱን ለመናገር እሷን ለብቻዋ ከማገኛት ይልቅ ኤዱን ከልጁ ጋር ሆና ባገኛት እመርጥ ነበር።
ለሶስት ወር ልጅቷ እና ጆሲ ስራ አደረጉኝ የተቀየረ ስሜት አልነበረም በመሀል ድንገት ለተከታታይ ቀናት ጥፍት አለች።
ለስድስት ቀን ያህል ድምጿንም ስልኳንም አጥፍታ ከተሰወረች ቡሀላ በሰባተኛው ቀን እኔና ጆሲ ሰፈር ውስጥ ቁጭ ባልንበት እራሷ ጆሲ ስልክ ላይ ደወለች።
ስልኩን ለሁለታችንም እንዲሰማ አደረገና •••
" ምን ሆነሽ ነው የጠፋሽው?" የጆሲ ጥያቄ ነበር
" ምን ላድርግ ጓደኛህ ኤደን የምትባል ሰይጣን አጠናፍራዋለች መሰለኝ በተገናኘን ቁጥር ወሬው ሁሉ ከሷ አያልፍም እንዴ እኔ ልጅቷን ሳላውቃት ሁላ እንድጠላት ነው ያደርገኝ በጣም ነው የተጎዳሁት ጆሲ ከቻልክ ጓደኛህን ወይ አሳክመው ወይ ፀበል ውሰደው " ብላው እርፍ አለች ።
ጆሲ ዘወር ብሎ ሲያፈጥምኝ ተነስቼ ካጠገቡ ሄድኩ።
ከዛን ቀን ቡሀላ ከጆሲ ጋር ስለምንም ነገር ሳናወራ የኤዱ ምርቃት ሰባት ቀን( ሳምንት) ቀረው ።
ስድስት ቀን ሲቀረው ደውላ ቤተሰቦቿ ለምርቃቷ ከሁለት ቀን ቡሀላ እንደሚመጡ እና ከምርቃቷ ቡሀላ አብራቸው ወደ አዲስ አበባ እንደምትሄድ ነገረችኝ ።
ይህ ንግግሯ መብረቅ በሉት ለኔ ።ጨነቀኝ ።
ያን ቀን ጠጥቼ ብገባም እንቅልፍ እንቢ አለኝ እኩለ ለሊት ላይ አንድ ሀሰብ መጣልኝ።
ተነስቼ ለኤዱ ደብዳቤ መፃፍ ጀመርኩ•••
••••• ለኤደን
ኤዱዬ ህይወትን መራራም ጣፋጭም እንድትሆን ካደረጓት ምክንያቶች አንዱ ምን እንደሆነ ታውቂያለሽ?
እኛ ሰዎች ስላለፈው እና ስለ አሁኑ እንጂ ነገ ምን እንደሚፈጠር እለማወቃችን ነው ።
ነገን አለማወቅ የራሱ የሆነ ብዙ ጥሩም መጥፎም ገፅታዎች አሉት።
ነገ የሚከሰተውን መጥፎ ነገር ቀድመን ስናውቅ እና ነገ የሚከሰተውን ጥሩ ነገር ቀድመን ስናውቅ የሚሰሙን ሁለት ተቃራኒ ስሜቶች ናቸው።
እንዲህ ያልኩሽ አሁን የሆንኩትን ነገር ያኔ በዛ በብርድ እዛ ሆቴል በር ላይ ቆመሽ ባየሁሽ ሰአት ቀድሜ ባውቀው ምን እወስን ነበር ብዬ ሁሌም እራሴን ስለምጠይቀው ነው
"አሁን ምን ሆንክ? ትይ ይሆኖል። ምንም አታውቂምና ጥያቄሽ ልክ ነው የኔ ስስት ያኔ ካሁን ቡሀላ ወንድምሽ ነኝ ስልሽ አንቺም ተቀብለሽ የእውነት ወንድም አድርገሽኛልና ምን ሆንክ ብትይኝ ባንቺ አይፈረድም እኔ ግን ብዙ ሆኛለሁ አንቺን በማፍቀሬ እንኳን አንቺ እኔ እንኳን የማላውቀው ሌላ ዳኒ እንደሆኑኩ አውቃለሁ።
ኤዱዬ አፈቅርሻለሁ!
ይህን ስታነቢ ምን ትይኝ ይሆን?
በቃሌ የማልገኝ እራስ ወዳድ ነኝ አደል ኤዱዬ?
በጣም ይቅርታ።
ከግዜ ቡሀላ ለኔም ባልገባኝ መንገድ ውስጤ ተቀያይሮ ካቅሜ በላይ ሆኖብኝ እንጂ ያኔ ወንድም እሆንሻለሁ ከጎንሽ ነኝ እንደወንድምሽ እይኝ ያልኩሽ ግን ከልቤ ነበር!።
ሁሌም ቃሌን ያጠፍኩ መስሎ ይሰማኛል ላንቺ ስላልነገርኩሽ ምንም ባትይኝም ብታውቅ ምን ትለኛለች እያልኩ ከመሸማቀቅ አልዳንኩም።
ፍቅር የሻቱትን ማግኘት ብቻ አይደለምና የኔ እንደማትሆኚ እያሰብኩም አፈቅርሻለሁ።
ከምንም ነገር በላይ አንቺን በእውኔም በህልሜም ማየት፣ ስላንቺ ማሰብ ፣ ስላንቺ ማውራት ያስደስተኛል ። ካንቺ ውጪ ሁሉ ነገር አልጥምህ ካለኝ ወራቶች ተቆጥረዋል።
"ታድያ በነበረን ግዜ በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ውስጥ ከነበርክ እንዴት አልነገርከኝም?
ወይም እንዴት ከፊትህ መረዳት አልቻልኩም? " ትይኝ ይሆናል
በፍቅር ንዳድ ከመለብለብ በላይ በልብ ውስጥ ያለውን የፍቅር እሳት አውጥቶ ላፈቀሩት ሰው ንዳዱን ማሳየት ለብዙ አፍቃሪዎች ከባድ ነው።
እኔን ግን አውጥቶ ከመናገሩም በላይ ከባድ የሆነብኝ ብነግርሽ የሚሰማሽን ስሜት ማሰብ ነው።
ፍቅረኛሽ ሆኜ ቢሆን አሁን ወንድምሽ በመሆኔ የተደሰትሽውን ያክል እምትደሰቺ መስሎ አይታየኝም ።
ካፌ ሻይ ቡና እያልን ፊት ለፊቴ ቁጭ ብለሽ ከናት ካባቴ ባትወለድም አንተን የመሰለ ወንድም በስጦታ ስለሰጠኝ እያልሽ ፈጣሪን ስታመሰግኚ ስሰማ እንኳን ልነግርሽ ማፍቀሬን የምታውቂብኝ እየመሰለኝ ምክንያት ፈጥሬ ካጠገብሽ እሽሻለሁ ።
ጆሲ ጓደኛዬ ምን እንደሚለኝ ታውቂያለሽ ኤዱዬ?
••••" አንተኮ መፍታት ያቃተህ መጀመሪያ ላይ እራስህ አጥብቀህ ያሰርከውን ቋጠሮ ነው አልፈታ ባለህ ቁጥር ደግሞ በንዴት ለመበጠስ እየሞከርክ የበለጠ ታጠብቀዋለህ!" ይለኛል
እውነቱን ነው ትዝ ይልሻል እዱዬ?
ስለመሲ ስናወራ አንድ ሰው ውለታ ውሎልሽ ውለታውን በመንተራስ ከፍላጎትሽ ውጪ የሚጫንሽ ከሆነ ውለታ ሳያስቀድም ተመሳሳይ ጥያቄ ከሚጠይቅሽ ሰው በላይ እርኩስ ነው ብዬሽ ነበር ።
እኔም የፍቅር ጥያቄዬ ካደረኩልሽ ትንሽ ውለታ ጋር እንዳይያያዝብኝ ፈራሁ።
አንቺንም እኔን ወንድም እንጂ ፍቅረኛ የማድረግ ፍላጎት ውስጥሽ ሳይኖር የምጫንሽ ጥያቄዬን ባለመቀበልና እኔን ባለማስከፋት መሀል ሆነሽ የምትጨነቂ መስሎ ታየኝ ።
በዚህ መሀል እናንተ ባታዩኝም ከልጁ ጋር ሆኖችሁ ብዙ ቦታዎች ታጋጥሙኝ ጀመር።
ያኔ በሱም ባንቺም ሳይሆን በራሴ ይበልጥ መናደድ ጀመርኩ ።
ህመምህ መድሀኒት የለውም አትድንም እንደተባለ በሽተኛ የፍቅር ህመሜ ፈውስ የሆንሽውን አንቺን የኔ እንደማላደርግሽ ተረዳሁ ።
ኤዱዬ በመመረቅሽ እንኳን ደስ አለሽ!
በመመረቅሽ የተሰማሽን ደስታ ትንሽ ሳታጣጥሚውና ከድሬ ሳትወጪ አንብበሽው ሌላ ስሜት ውስጥ እንድትገቢ ስላልፈለኩ ነው ይህን ደብዳቤ በእጅሽ ሳልሰጥሽ ከምርቃቷ ቡሀላ ወደ አዲስ አባባ ስሸኛት ሳታየኝ የልብስ ሻንጣዋ ውስጥ አስቀምጥላታለሁ ባየችው ግዜ ትየው ብዬ የወሰንኩት።
በነበረን ስሜት ወንድምሽ ሆኜ ልሸኝሽ ቀናቶች ቀርተዋል ለዛም ተዘጋጅቻለሁ ።
የኔ ኤደን ዛሬም ቢሆን ስላወኩሽ ደስተኛ ነኝ።
የማንም ሁኚ እኔ ግን አፈቅርሻለሁ። መቼም ቢሆን አረሳሽም። ዝምምምም ብዬ ሳፈቅርሽ እኖራለሁ።
ሰላም ሁኚ!
ዳኒ ነኝ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#ለኀጥአን_የመጣ
#ክፍል_ሀያ_ሶስት(የመጨረሻ ክፍል)
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
አስር ስዓት ሲሆን አውቶብሱ ካምቢያ ከምትባል ከተማ አደረሰን። የመጨረሻ ፌርማታው ነበር። ፍሪ ታውንን ለቀን
ከመጣን ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳፋሪዎቹ ፊት ተፈታ። ግን ብዙም አልቆየም! ድንበር ለማለፍ ክፍያ ስንጠየቅ የሁሉም ፊት መልሶ ተኮማተረ አጉረመረምን፡፡ ሁሉም ሰው ከካልሲው
ውስጥ፣ ከውስጥ ሱሪ እና ከረባት ሳይቀር የተረፈ ገንዘብ ካለ ፈለገ። ሶስት መቶ ሊዮንስ (የሴራሊዮን ገንዘብ) ነበር
የተጠየቅነው:: አንድ ሰው ከገዛ ሃገር ለቆ ለመውጣት ለምንድን ነው ሚከፍለው? አሰብኩ ግን መከራከር አልችልም:: ከፈልኩ:: የይለፍ ወረቀቱ ላይ ማህተም እንደተደረገልኝ ወዲያው ወደ ጊኒ
ደንበር ተሻገርኩ። ዋና ከተማዋ ኮናክሪ ለመድረስ ደግሞ ገና ብዙ መንገድ ይቀረኛል። ወደ ከተማው የሚወስድ አውቶብስ ለማግኘት ቶሎ ቶሎ መራመድ ጀመርኩ። ጊኒ ውስጥ የሚነገር
የትኛውንም ቋንቋ መናገር አልችልም ምን ማድረግ እንዳለብኝም አላሰብኩበትም ነበር። ትንሽ አስጨነቀኝ ግን ከሃገሬ በህይወት መውጣቴ ትልቅ ነገር ነው::
ኮናክሪ የሚሄድ አውቶብሶች የጊኒ ወታደሮች ባቆሟቸው ኬላዎች በኩል ነበር የሚቆሙት፡፡ በኬላዎቹ ተጠግተው
በፈለጉት መጠን የጊኒን ገንዘብ የሚመነዝሩ ሰዎች ነበሩ።
ወታደሮቹ ይሄን ጥቁር ገበያ የሚከላከሉ መስሎኝ ነበር ግን ግድ አይሰጣቸውም:: ገንዘቤን ቀይሬ ወደ ኬላው ተጠጋሁ። ደንበሩ ላይ ያሉ ወታደሮች ወይ እንግሊዝኛ መናገር አይችሉም ወይ
ደግሞ እንደሚችሉ ማሳወቅ አይፈልጉም:: መሳሪያቸውን ብቻ
በተጠንቀቅ ይዘዋል፡፡ ቀና ብየ ማየት አልፈለኩም። ከዚህ በፊት ወታደር እንደነበርኩ እና አሁን ግን ትቼው እሸሸሁ መሆኑን ማሳበቅ አልፈለኩም::
አውቶብሱን ለማግኘት ጥቁር ቡናማ የሆኑ የጣውላ ቤቶችን ማለፍ ነበረብኝ። ውስጥ ወታደሮች የሰዎችን ሻንጣ ይበረብራሉ።ሰዎች ደግሞ መረጃዎቻቸውን ለሃላፊዎች ያሳያሉ። የእኔ ተራ ሲደርስ ወታደሮቹ ሻንጣየን ከፍተው በውስ ጡ ያለውን ሁሉ መሬት ላይ ዘረገፉት። ብዙ እቃ ስላልነበረኝ ለመሰብሰብ እና መልሶ ለመክተት ብዙም አያስቸግርም፡፡ ሁለት ቲ ሸርት፣ ሁለት
ዉስጥ ሱሪ እና ሶስት ጥንድ ሱሪዎች ብቻ ነበሩ::
ከጣውላ ቤቱ ስወጣ መረጃዎቼን ማሳየት ነበረብኝ፡፡ ብዙ ጠረጴዛዎቹ እና ወታደሮች ደግሞ የማንጎ ዛፍ ስር ነበሩ።
መሳሪዎቻቸው ወንበራቸው ላይ ወይም የአንዳንዶቹ ጠረጴዛዎቹ ላይ ተቀምጦ ነበር፡፡ ለማን ማሳየት እንዳለብኝ
አላውቅም::
አንድ ወታደር ወደ እሱ እንደሄድ ምልክት አሳየኝ። እጁን ዘረጋ እና የይለፍ ወረቀቴን ተቀበለኝ። ወታደሩ በማይገባኝ አንድ
ቋንቋ ተናገረ።የይለፍ ወረቀቴን የደረት ኪሱ ውስጥ አስገባው እና እጁን ጠረጴዛ አድርጎ አትኩሮ ተመለከተኝ። አቀረቀርኩ
ወታደሩ አገጩን ቀና አደረገኝ፡፡ የይለፍ ወረቀቴን ከኪሱ አውጥቶ መረመረ። አይኑ ቀላ ፊቱ ላይ ፈገግታ ይታይ ነበር።
እጁን አጥፎ ተደላድሎ ተቀመጠ። ፈገግ አልኩ እሱም ሳቀ።በቋንቋው የሆነ ነገር አለና እጁን እንደገና ጠረጴዛው ላይ አደረገ።ፈገግታው እየጠፋ ሄደ፡፡ የተወሰነ ገንዘብ እጁ ላይ አስቀመጥኩ።
የይለፍ ወረቀቴን ከኪሱ አውጥቶ ሰጠኝ እና በሩ እንዳልፍ ጠቆመኝ፡፡
ብዙ አውቶብሶች ስለነበሩ ወደ ኮናክሪ ለመሄድ አውቶብስ መያዝ እንዳለብኝ አላውቅም ግራ ገባኝ፡፡ ሰዎችን ለመጠየቅ ብሞክርም ማንም ሊረዳኝ አልቻለም:: የማውቀው ፈረንሳይኛ
ቃል bonjour ቦንጁር ብቻ ነበር፡፡
ግራ ገብቶኝ ቁሜያለሁ አንድ አልፎ ሂያጅ በኪሮ ቋንቋ ሲያጉረመርም ሰማሁትና “ ጤና ይስጥልኝ” ብየ ወደ ኮናክሪ
የሚወስደው አውቶብስ የትኛው እንደሆነ ጠየቅኩት። እሱም ወደ ዛው እንደሚጓዝ ነገረኝ እና ወደ ከአፍ እስከ ገደፉ ጢም
ብሎ የሞላ አውቶብስ ውስጥ ገባን፡፡ በየ ሃምሳ ሜትሩ ወደ አስራ አምስት የሚጠጉ ኬላዎች ላይ ወታደሮች ነበሩ እና ወታደሮቹ ምህረት የለሽ ነበሩ። ወታደሮቹ መክፈል የማችሉትን እየደበደቡ
ከአውቶብሱ ያወርዷቸዋል። እኔ ግን እድለኛ ነበርኩ። ከአጠገቤ የነበረው ሰውየ ልጅ ስለመሰልኳቸው ብዙ ኬላዎችን በነፃ አልፌያለሁ። የእሱን መረጃ ያያሉ እና የሁለታችንንም እሱን
ያስከፍላሉ፡፡ ሰውየው የገባው አይመስለኝም:: ገንዘብ ጉዳዩ አይደለም ኮናክሪ መግባት ብቻ ነበር የሚፈልገው:: የመግቢያ ክፍያው ሶስት መቶ ሊዮንስ እንደሆነ ሰዎች ሲያወሩ ሰማሁ።
መቶ ሊዮንስ ብቻ ነበር የቀረኝ፡፡ ምንድን ነው ማደርገው? ብየ ማሰብ ጀመርኩ። ይሄ ሁሉ መንገድ የመጣሁት ለከንቱ ነው? ወደ ፍሪ ታውን መመለስ እንኳ ብፈልግ የምመለስበት ገንዘብ የለኝም:: አይኖቼ እንባ አቀረሩ። ተረበሽኩ ከዚህ መውጫ መንገዱ አልታይህ አለኝ፡፡ አንድ የይለፍ ወረቀቱ የተመታለት ሰው ከኬላ ወደ አውቶብስ ሲመለስ ሻንጣውን ጥሎ አየሁ። የተወሰነ ካመነታሁ በኋላ እድሉን ልጠቀምበት ወሰንኩ። ሰልፉን ትቼ ሻንጣውን ይዤ ተከልኩት:: አውቶብስ ውስጥ ገብቼ መጨረሻ ወንበር ላይ ተደብቄ ተቀመጥኩ። አውቶብሱ ቀስ ብሎ ከወጣ በኋላ ፍጥነቱን ጨመረ። በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሃገሪቱ
ገባሁ በኋላ ግን ችግር ይሆናል፡፡
አውቶብሱ ወደ ኮናክሪ ሲደርስ መጨነቅ ጀመርኩ። ከደረስኩ በኋላ ምን እንደማደርግ አላውቅም:: የሴራሊዮን አምባሳደር ስደተኞች በጊዜዊነት ግቢው ውስጥ እንደሚያሳድር ሰምቻለሁ
ግን ኢምባሲው የት እንደሆነ እንኳ አላውቅም:: ጃሎህ ከሚባል
ፉላኒ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ አርብቶ አደር ጎሳ) ጋር ነበር የተቀመጥኩት። ጃሎህ ፍሪ ታውን እንደኖረ ነገረኝ፡፡ ስለ ጦርነቱ እና በሃገሪቱ ላይ ስላስከተለው ጉዳት አወራን። በኋላ ስልክ ቁጥሩን ሰጠኝ እና ከተማዋን ስንቀሳቀስ እርዳታ ካስፈለገኝ እንድደውልለት ነገረኝ። ማደሪያ እንደሌለኝ ልነግረው ፈለኩ ግን
ቀድሞኝ ወረደ። አብሮኝ የመጣውን ሴራ ሊዮናዊ ፈለኩ ግን ላገኘው አልቻልኩም። ከደቂቃዎች በኋላ አውቶብሱ ግዙፍ
መናሃሪያ ውስጥ ገባ። ወጥቼ ሁሉም ሲሄድ ተመለከትኩ። ተነፈስኩ እና እጆቼ ራሴ ላይ ጭኜ ወደ አግድም ወንበር ሂጄ
ተቀመጥኩ። ፊቴን በእጆቼ ሸፍኜ “ለሊቱን ሙሉ ከዚህ መቀመጥ አልችልም” ብየ ለራሴ አጉረመረምኩ።
ብዙ ታክሲዎች ነበሩ እና አውቶብሱ መናሃሪያ የደረሱ ሰዎች ሁሉ ይዟቸዎል። እኔም ብቸኛ ሚሄድበት የጠፋው እንግዳ
መስየ መታየት ስላልፈለኩ አንዱ
ታክሲ ውስጥ ገባሁ። ሹፌሩ በፈረንሳይኛ ሲናገር ወዴት እንደምሄድ እየጠቀኝ እንደሆነ ገመትኩ። ሴራ ሊዮን ቆንስላ አ ኢምባሲ” ብየ ነገርኩት።በመስኮት ስመለከት የመብራት ምሶሶዎች ላይ የመንገድ መብራቶቹ ተንበርግገው
ተንጠልጥለዋል። ብርሃናቸው ከጨረቃ ብርሃን ሳይበልጥ አይቀርም። ታክሲው ኢምባሲው ፊት ለፊት ቆመ እና የምፈልገው ቦታ ይዞኝ እንደመጣ
ለማረጋገጥ ወደ አረንጓዴ፣ ነጭ እና ሰማያዊ ባንዴራ ጠቆመኝ፡፡ራሴን በማወዛወዝ ትክክል እንደሆነ ከገለፅኩለት በኋላ ከታክሲው ወረድኩ
በኤንባሲው በር ላይ ጠባቂዎቹ በኪሪዎ የይለፍ ወረቀቴን እንዳሳይ ጠየቁኝ፡፡ አሳየኋቸው እና ወደ ግቢው እንድገባ ፈቀዱልኝ::
በግቢው ውስጥ ከሃምሳ በላይ ሰዎች ሲኖሩ እንደእኔ መጠጊያ ያጡ ሳይሆኑ አይቀሩም፡፡ አብዛኖቹ ትራስ ብቻ አድርገው ተጋድመዋል። ጓዛቸውን ወይም ሻንጣቸውን ከጎናቸው አስቀምጠዋል። ሰዎቹ ማታ ማታ ከዚህ የሚያድሩ ሲሆን ቀን ቀን ወደ ውጭ ይወጣሉ። ጥግ ላይ ቦታ አገኘሁ እና መሬት ተቀምጨ ጀርባየን ወደ ግድግዳው አስጠጋሁ። ስዎቹን ሳይ
ከጦርነቱ ለማምለጥ ያለፍኩባቸው ሰፈሮች ትዝ አሉኝ።
#ክፍል_ሀያ_ሶስት(የመጨረሻ ክፍል)
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
አስር ስዓት ሲሆን አውቶብሱ ካምቢያ ከምትባል ከተማ አደረሰን። የመጨረሻ ፌርማታው ነበር። ፍሪ ታውንን ለቀን
ከመጣን ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳፋሪዎቹ ፊት ተፈታ። ግን ብዙም አልቆየም! ድንበር ለማለፍ ክፍያ ስንጠየቅ የሁሉም ፊት መልሶ ተኮማተረ አጉረመረምን፡፡ ሁሉም ሰው ከካልሲው
ውስጥ፣ ከውስጥ ሱሪ እና ከረባት ሳይቀር የተረፈ ገንዘብ ካለ ፈለገ። ሶስት መቶ ሊዮንስ (የሴራሊዮን ገንዘብ) ነበር
የተጠየቅነው:: አንድ ሰው ከገዛ ሃገር ለቆ ለመውጣት ለምንድን ነው ሚከፍለው? አሰብኩ ግን መከራከር አልችልም:: ከፈልኩ:: የይለፍ ወረቀቱ ላይ ማህተም እንደተደረገልኝ ወዲያው ወደ ጊኒ
ደንበር ተሻገርኩ። ዋና ከተማዋ ኮናክሪ ለመድረስ ደግሞ ገና ብዙ መንገድ ይቀረኛል። ወደ ከተማው የሚወስድ አውቶብስ ለማግኘት ቶሎ ቶሎ መራመድ ጀመርኩ። ጊኒ ውስጥ የሚነገር
የትኛውንም ቋንቋ መናገር አልችልም ምን ማድረግ እንዳለብኝም አላሰብኩበትም ነበር። ትንሽ አስጨነቀኝ ግን ከሃገሬ በህይወት መውጣቴ ትልቅ ነገር ነው::
ኮናክሪ የሚሄድ አውቶብሶች የጊኒ ወታደሮች ባቆሟቸው ኬላዎች በኩል ነበር የሚቆሙት፡፡ በኬላዎቹ ተጠግተው
በፈለጉት መጠን የጊኒን ገንዘብ የሚመነዝሩ ሰዎች ነበሩ።
ወታደሮቹ ይሄን ጥቁር ገበያ የሚከላከሉ መስሎኝ ነበር ግን ግድ አይሰጣቸውም:: ገንዘቤን ቀይሬ ወደ ኬላው ተጠጋሁ። ደንበሩ ላይ ያሉ ወታደሮች ወይ እንግሊዝኛ መናገር አይችሉም ወይ
ደግሞ እንደሚችሉ ማሳወቅ አይፈልጉም:: መሳሪያቸውን ብቻ
በተጠንቀቅ ይዘዋል፡፡ ቀና ብየ ማየት አልፈለኩም። ከዚህ በፊት ወታደር እንደነበርኩ እና አሁን ግን ትቼው እሸሸሁ መሆኑን ማሳበቅ አልፈለኩም::
አውቶብሱን ለማግኘት ጥቁር ቡናማ የሆኑ የጣውላ ቤቶችን ማለፍ ነበረብኝ። ውስጥ ወታደሮች የሰዎችን ሻንጣ ይበረብራሉ።ሰዎች ደግሞ መረጃዎቻቸውን ለሃላፊዎች ያሳያሉ። የእኔ ተራ ሲደርስ ወታደሮቹ ሻንጣየን ከፍተው በውስ ጡ ያለውን ሁሉ መሬት ላይ ዘረገፉት። ብዙ እቃ ስላልነበረኝ ለመሰብሰብ እና መልሶ ለመክተት ብዙም አያስቸግርም፡፡ ሁለት ቲ ሸርት፣ ሁለት
ዉስጥ ሱሪ እና ሶስት ጥንድ ሱሪዎች ብቻ ነበሩ::
ከጣውላ ቤቱ ስወጣ መረጃዎቼን ማሳየት ነበረብኝ፡፡ ብዙ ጠረጴዛዎቹ እና ወታደሮች ደግሞ የማንጎ ዛፍ ስር ነበሩ።
መሳሪዎቻቸው ወንበራቸው ላይ ወይም የአንዳንዶቹ ጠረጴዛዎቹ ላይ ተቀምጦ ነበር፡፡ ለማን ማሳየት እንዳለብኝ
አላውቅም::
አንድ ወታደር ወደ እሱ እንደሄድ ምልክት አሳየኝ። እጁን ዘረጋ እና የይለፍ ወረቀቴን ተቀበለኝ። ወታደሩ በማይገባኝ አንድ
ቋንቋ ተናገረ።የይለፍ ወረቀቴን የደረት ኪሱ ውስጥ አስገባው እና እጁን ጠረጴዛ አድርጎ አትኩሮ ተመለከተኝ። አቀረቀርኩ
ወታደሩ አገጩን ቀና አደረገኝ፡፡ የይለፍ ወረቀቴን ከኪሱ አውጥቶ መረመረ። አይኑ ቀላ ፊቱ ላይ ፈገግታ ይታይ ነበር።
እጁን አጥፎ ተደላድሎ ተቀመጠ። ፈገግ አልኩ እሱም ሳቀ።በቋንቋው የሆነ ነገር አለና እጁን እንደገና ጠረጴዛው ላይ አደረገ።ፈገግታው እየጠፋ ሄደ፡፡ የተወሰነ ገንዘብ እጁ ላይ አስቀመጥኩ።
የይለፍ ወረቀቴን ከኪሱ አውጥቶ ሰጠኝ እና በሩ እንዳልፍ ጠቆመኝ፡፡
ብዙ አውቶብሶች ስለነበሩ ወደ ኮናክሪ ለመሄድ አውቶብስ መያዝ እንዳለብኝ አላውቅም ግራ ገባኝ፡፡ ሰዎችን ለመጠየቅ ብሞክርም ማንም ሊረዳኝ አልቻለም:: የማውቀው ፈረንሳይኛ
ቃል bonjour ቦንጁር ብቻ ነበር፡፡
ግራ ገብቶኝ ቁሜያለሁ አንድ አልፎ ሂያጅ በኪሮ ቋንቋ ሲያጉረመርም ሰማሁትና “ ጤና ይስጥልኝ” ብየ ወደ ኮናክሪ
የሚወስደው አውቶብስ የትኛው እንደሆነ ጠየቅኩት። እሱም ወደ ዛው እንደሚጓዝ ነገረኝ እና ወደ ከአፍ እስከ ገደፉ ጢም
ብሎ የሞላ አውቶብስ ውስጥ ገባን፡፡ በየ ሃምሳ ሜትሩ ወደ አስራ አምስት የሚጠጉ ኬላዎች ላይ ወታደሮች ነበሩ እና ወታደሮቹ ምህረት የለሽ ነበሩ። ወታደሮቹ መክፈል የማችሉትን እየደበደቡ
ከአውቶብሱ ያወርዷቸዋል። እኔ ግን እድለኛ ነበርኩ። ከአጠገቤ የነበረው ሰውየ ልጅ ስለመሰልኳቸው ብዙ ኬላዎችን በነፃ አልፌያለሁ። የእሱን መረጃ ያያሉ እና የሁለታችንንም እሱን
ያስከፍላሉ፡፡ ሰውየው የገባው አይመስለኝም:: ገንዘብ ጉዳዩ አይደለም ኮናክሪ መግባት ብቻ ነበር የሚፈልገው:: የመግቢያ ክፍያው ሶስት መቶ ሊዮንስ እንደሆነ ሰዎች ሲያወሩ ሰማሁ።
መቶ ሊዮንስ ብቻ ነበር የቀረኝ፡፡ ምንድን ነው ማደርገው? ብየ ማሰብ ጀመርኩ። ይሄ ሁሉ መንገድ የመጣሁት ለከንቱ ነው? ወደ ፍሪ ታውን መመለስ እንኳ ብፈልግ የምመለስበት ገንዘብ የለኝም:: አይኖቼ እንባ አቀረሩ። ተረበሽኩ ከዚህ መውጫ መንገዱ አልታይህ አለኝ፡፡ አንድ የይለፍ ወረቀቱ የተመታለት ሰው ከኬላ ወደ አውቶብስ ሲመለስ ሻንጣውን ጥሎ አየሁ። የተወሰነ ካመነታሁ በኋላ እድሉን ልጠቀምበት ወሰንኩ። ሰልፉን ትቼ ሻንጣውን ይዤ ተከልኩት:: አውቶብስ ውስጥ ገብቼ መጨረሻ ወንበር ላይ ተደብቄ ተቀመጥኩ። አውቶብሱ ቀስ ብሎ ከወጣ በኋላ ፍጥነቱን ጨመረ። በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሃገሪቱ
ገባሁ በኋላ ግን ችግር ይሆናል፡፡
አውቶብሱ ወደ ኮናክሪ ሲደርስ መጨነቅ ጀመርኩ። ከደረስኩ በኋላ ምን እንደማደርግ አላውቅም:: የሴራሊዮን አምባሳደር ስደተኞች በጊዜዊነት ግቢው ውስጥ እንደሚያሳድር ሰምቻለሁ
ግን ኢምባሲው የት እንደሆነ እንኳ አላውቅም:: ጃሎህ ከሚባል
ፉላኒ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ አርብቶ አደር ጎሳ) ጋር ነበር የተቀመጥኩት። ጃሎህ ፍሪ ታውን እንደኖረ ነገረኝ፡፡ ስለ ጦርነቱ እና በሃገሪቱ ላይ ስላስከተለው ጉዳት አወራን። በኋላ ስልክ ቁጥሩን ሰጠኝ እና ከተማዋን ስንቀሳቀስ እርዳታ ካስፈለገኝ እንድደውልለት ነገረኝ። ማደሪያ እንደሌለኝ ልነግረው ፈለኩ ግን
ቀድሞኝ ወረደ። አብሮኝ የመጣውን ሴራ ሊዮናዊ ፈለኩ ግን ላገኘው አልቻልኩም። ከደቂቃዎች በኋላ አውቶብሱ ግዙፍ
መናሃሪያ ውስጥ ገባ። ወጥቼ ሁሉም ሲሄድ ተመለከትኩ። ተነፈስኩ እና እጆቼ ራሴ ላይ ጭኜ ወደ አግድም ወንበር ሂጄ
ተቀመጥኩ። ፊቴን በእጆቼ ሸፍኜ “ለሊቱን ሙሉ ከዚህ መቀመጥ አልችልም” ብየ ለራሴ አጉረመረምኩ።
ብዙ ታክሲዎች ነበሩ እና አውቶብሱ መናሃሪያ የደረሱ ሰዎች ሁሉ ይዟቸዎል። እኔም ብቸኛ ሚሄድበት የጠፋው እንግዳ
መስየ መታየት ስላልፈለኩ አንዱ
ታክሲ ውስጥ ገባሁ። ሹፌሩ በፈረንሳይኛ ሲናገር ወዴት እንደምሄድ እየጠቀኝ እንደሆነ ገመትኩ። ሴራ ሊዮን ቆንስላ አ ኢምባሲ” ብየ ነገርኩት።በመስኮት ስመለከት የመብራት ምሶሶዎች ላይ የመንገድ መብራቶቹ ተንበርግገው
ተንጠልጥለዋል። ብርሃናቸው ከጨረቃ ብርሃን ሳይበልጥ አይቀርም። ታክሲው ኢምባሲው ፊት ለፊት ቆመ እና የምፈልገው ቦታ ይዞኝ እንደመጣ
ለማረጋገጥ ወደ አረንጓዴ፣ ነጭ እና ሰማያዊ ባንዴራ ጠቆመኝ፡፡ራሴን በማወዛወዝ ትክክል እንደሆነ ከገለፅኩለት በኋላ ከታክሲው ወረድኩ
በኤንባሲው በር ላይ ጠባቂዎቹ በኪሪዎ የይለፍ ወረቀቴን እንዳሳይ ጠየቁኝ፡፡ አሳየኋቸው እና ወደ ግቢው እንድገባ ፈቀዱልኝ::
በግቢው ውስጥ ከሃምሳ በላይ ሰዎች ሲኖሩ እንደእኔ መጠጊያ ያጡ ሳይሆኑ አይቀሩም፡፡ አብዛኖቹ ትራስ ብቻ አድርገው ተጋድመዋል። ጓዛቸውን ወይም ሻንጣቸውን ከጎናቸው አስቀምጠዋል። ሰዎቹ ማታ ማታ ከዚህ የሚያድሩ ሲሆን ቀን ቀን ወደ ውጭ ይወጣሉ። ጥግ ላይ ቦታ አገኘሁ እና መሬት ተቀምጨ ጀርባየን ወደ ግድግዳው አስጠጋሁ። ስዎቹን ሳይ
ከጦርነቱ ለማምለጥ ያለፍኩባቸው ሰፈሮች ትዝ አሉኝ።
#የታካሚው_ማስታወሻ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)
“ወደ ዚህ ስትመጣ የመጀመሪያህ ነው?”
“አዎ።”
“ትቆያለህ?”
ሳምንት አካባቢ።”
“እዚያ ማዶ ሚታየው አፄ ዮሐንስ አንገታቸው የተቀላበት ቦታ ነው።” እጁን ከመንገዱ በላይ እየጠቆመ::
“መተማ ዮሐንስ ደረስን ማለት ነው?”
“አዎ፡፡ አሁን ገብተናል፡፡” ልቤ ድንግጥ ድንግጥ አለብኝ፡፡ ሚኒባሱ እየቆመ፣ ሰዎችን ያወርዳል። እስከዛሬ ያልተሰማኝ ፍርሀት እየተሰማኝ ነው፡፡ ዝም አልኩ፡፡ ወደ ስንብት እየተጠጋሁ ነው፡፡
የማውራትም የማወቅም ፍላጎት የለኝም፡፡ ዝም ብዬ በዐይኔ ከተማውን መፈለግ ጀምረኩ፡፡ በግራና በቀኝ የተደረደሩ የጭቃ ቤቶች፣ ጭር ያለ ከተማ ነው፡፡ እንደጠበኩት ግርግር የበዛበት ከተማ አይደለም፡፡ ሰዐቴን አየሁ፤ አስር ተኩል፡፡ አብዛኛው ሰው ወርዶ አልቋል፡፡
“መናኸሪያ ትገባለህ?” ወያላው ፊቱን አዙሮ ጠየቀኝ፡፡
“አይ አልገባም፡፡”
“ካልገባህ መጨረሻው እዚህ ነው።”
“እሺ አውርደኝ!”
በጭራሽ እንደገመትኩት አይደለም፡፡ ለማደሪያ ሚሆን አልጋ ቤት እንኳን እስካሁን አላየሁም፡፡ ከተማዋ ትሞቃለች። አስራ አንድ ሰዓት እየሆነ ቢሆንም፣ በጣም ይወብቃል፡፡ ፍርሀት ነው መሰል፣ በጣም እያላበኝ ነው። ዝም ብዬ ዋና መንገዱን ይዤ፣ አልጋ ቤት ፍለጋ
ተጓዝኩኝ፡፡ ነጋዴ የሚርመሰመስበት፣ አዲስ ሰው፣ ፀጉረ ልውጥ ሰው
ከዐይን የማይገባበት ብዬ የገመትኩት ከተማ፣ ትንሽዬ መንደር ሆና አገኘኋት፡፡ መንገድ ዳር በብሎኬት የታጠረ ሰፊ ግቢ ያለው ሆቴል አየሁ፡፡ ሰላም ሆቴል ይላል፡፡ አላንገራገርኩም፡፡ ዘው ብዬ ገባሁ፡፡ ብቻ
አልጋ በኖረ፡፡
“አልጋ አለ?”
“አለ፡፡”
“እስቲ አሳዩኝ?”
“ባለሻወር ነው፣ ያለሻወር?”
“ባለሻወር፡፡” ቁልፍ አመጣችና አሳየችኝ፡፡
“ስንት ነው?”
“አንድ መቶ ሃምሳ ብር፡፡” ብሩን ሰጠኋትና ቦርሳዬን አስቀመጥኩ።
ሻወር ቤት ገብቼ ሻወር ቼክ ሳደርግ ውሀ የለችም፡፡ ዞር ስል፣ውሀ በባልዲ ተቀምጧል፡፡ በጣም አልቦኛል፣ ተለቃለኩኝ፡፡ እራት በልቼ ቢራ መጠጣት ጀመርኩ፡፡ ሙቀት ስለሆነ ተጠጣልኝ፡፡ ማታ ጥሩ እንቅልፍ ተኝቼ አደርኩ፡፡ ቀን ወጥቼ ከተማውን ዙሪያውን ሳይ ዋልኩ፡፡
በፍፁም እኔ እንዳሰብኩት አይደለም፡፡ የከተማው ዙሪያ ለጥ ያለ ለእርሻ የሚውል ሜዳ ሲሆን፣ ዛፎች በእርቀት ነው የሚገኙት፡፡ ስዞር ውዬ አመሻሹ ላይ፣ ቢራዬን እየጠጣሁ ምን እንደሚችል ሳስብ፣ አርሴማ ገዳም የሚል ሀሳብ መጣብኝ፡፡
#ኑሮ_በገዳም
ሽቅብ ዝግዛግ ሆኖ በተሰራውን የጥረጊያ መንገድረገ፣ በግራና በቀኝ በዛፎች ተከቧል፡፡ ከፊት ለፊቴ፣ አጠር ያለ ወጣት፣ የክርስቲያኖ ሮናልዶ ስዕል ያለበት ጥቁር የጨርቅ ሻንጣ በጀርባው ተሸክሞ በዝግታ ያዘግማል። እየተከታተልን ወደ ገዳሙ ዘልቀን ገባን። ከገዳሙ መግቢያ
በር ትንሽ ፈቅ ብላ ያለች የጭቃ ቤት ጋር ስንደርስ፤
“እንኳን ደህና መጣችሁ። ምዝገባ ቢጤ አለች።” አለን ፊቱ መጠጥ ያለ ጠይም ወጣት፡፡
“እሺ!” ብዬ ቆምኩኝ፡፡ ልጁን መዝግቦ ከጨርሰ በኋላ፣ ትንሽ ቆየኝ ብሎት እኔን መመዝግብ ጀመረ፡፡ ስም፣ እድሜ፣ የመጡበት አድራሻ፣ የአደጋ ግዜ ተጠሪ...፣ ሁሉንም ቀይሬ ነገርኩት፡፡
“ለስንት ግዜ ነው ሚቆዩት?”
“ለሦስት ሳምንት፡፡”
“መታወቂያ ይዘዋል?”
“አልያዝኩም፡፡” አልተጫነኝም፡፡
“እሺ፣ እንግዶቻችን፣ እኔ መልካሙ እባላለሁ፡፡ በገዳሙ አስተባባሪ ነኝ፡፡ አሁን ማደሪያ ቦታ እሰጣችኋለው፡፡ ገዳሙን
አስጎበኛችኋለው፤ ስለ ገዳሙ ታሪክ፣ መተዳደሪያ ደንብና ሌሎች መረጃዎችን እነግራችኋለው፡፡ እዚህ ገዳም፣ ማንኛውም አዲስ ሱባኤተኛ ሲገባ እናንተ እንዳደረጋችሁት ተመዝግቦ ነው፡፡ ገዳሙ የአርምሞ ገዳም ነው:: ማውራት ክልክል ነው፡፡ አስገዳጅ ነገር ካላጋጠማችሁ በስተቀር፣ ማውራት አይቻልም፡፡ የግድ ማውራት ካስፈለገ እንኳ፣ ዝግ ባለ ድምፅ፣ በለሆሳስ ነው ማውራት ሚቻለው፡፡ እዚህ መዳን የሚገኘው በአርምሞ ውስጥ ነው፡፡”
ከኛ ውጪ ለሌላ ሰው እንዳይሰማ፣ በሆዱ እንደሚያወራ፣ በጣም ዝግ ባለ ድምፅ ያወራናል፡፡ በአርምሞና በለሆሳስ ማለት እንዲህ ነው' ብዬ አሰብኩ፡፡ የሚያወራው እንዲሰማን፣ አንገታችንን ወደሱ አሰገግን፡፡ እያወራን ወደ ማደሪያችን ወሰደን፡፡ እያንዳንዱ ከሁለት መቶ ምዕመን በላይ የሚይዝ፣ አራት የማደሪያ አዳራሾች አሉ፡፡ ሁለቱ የወንድ፣ ሁለቱ የሴት እንደሆነ ነገረን፡፡ ቦታ ሊሰጠን ወደ አንደኛው አዳራሽ ይዞን ገባ፡፡ በውስጡ ከመቶ ሚበልጡ ምዕመናን አሉ፡፡አሰላሁት። በግምት በገዳሙ አንድ ሺህ የሚጠጉ ሱባኤያተኛ ምዕመናን
እንዳሉ ገመትኩኝ፡፡ ገዳሙ ግን ሰው ያለው አይመስልም፡፡ ዝም፣ ጭጭ፣ ያለ ነው፡፡ ሁሉም በለሆሳስ ፀሎት ላይ ነው፡፡ ሰላምታ እንኳ፣ ጎንበስ ቀና በመባባል ብቻ ነው፡፡ ምንም አይነት የሰው ድምፅ አይሰማም፡፡የወፎች ጭጭታና የዛፎች ሽው ሽውታ ብቻ ነው፡፡ በጣም ደስ ይላል፡፡መንፈስን ያድሳል፡፡ አዕምሮን ያረጋጋል፡፡ ፈውስ በመንፈስ ቅዱስ
ባይላክም እንኳ፣ የቦታው ድባብ ፈውስን ይሰጣል።
“እና ሌላው...” አለ መልካሙ ቦታችንን ሰጥቶን ከአዳራሹ ይዞን እየወጣ፣ “ማንኛውም ምእመን ወደ ገዳሙ ለሱባኤ ሲገባ፤ ፀጉሩን መላጨት፣ ንስሀ መግባትና ስግደት መውሰድ አለበት፡፡” አለን እኔን እኔን እየተመለከተ፡፡
“እሺ፡፡ ማን ነው ሚላጨን?”
“እርስ በእረስ ነው ምትለጫጩት፡፡ ፈራህ እንዴ..? አንተን እኔ ቆንጆ አድርጌ እላጭሃለው፡፡” የከተማ ልጅ መሆኔን አውቆ ነው መሰል፣ ከገባን ጀምሮ እኔን እኔን እየተመለከተ ነው ሲያወራ የነበረው፡፡
“እሺ” አልኩት፡፡ አሁን ስለራሴ ብዙም ግድ የለኝም፡፡ ምላጭ ግቢ ካለው ሱቅ ተገዝቶ ሁለታችንንም ላጨን፡፡ ነብስ ካወኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ፀጉሬን ተላጨሁ፡፡ እየላጨንም ስለ ገዳሙ መተዳደሪያ ደንብ ይነግረናል።
“በገዳሙ፣ በቀን ሁለት ጊዜ ብቻ ነው የሚበላው፡፡ ጥዋት ቅዳሴ እንዳለቀና ማታ አስራ ሁለት ሰዐት። አስራ ሁለት ሰዐት ካለፈ መመገብ አይቻልም፡፡ ገዳሙ መብራት ስለሌለው፣ ማታ ማታ ሻማ ነው
ምትጠቀሙት። ሻማ ከዚህ ሱቅ መግዛት ትችላላችሁ፡፡ የማታ ሦስት ሰዓት ፀሎት ካበቃ ቦሃላ ሻማ ማብራት አይቻልም፡፡ የእንቅልፍ ሰዓት ነው፡፡ እንዳያችሁት፣ የቦታ ጥበት ስላለ አንድ ሰው፣ በአንድ መዳበሪያ በታ ላይ ነው መተኛት ያለበት፡፡ የለሊቱ ዘጠኝ ሰአት ፀሎት ላይ ሁሉም
ምዕመን መገኘት ግዴታ ነው፡፡” ሁለታችንንም ላጭቶ ሲጨርስ አስራ
አንድ ሰዐት ሆኖ የሰርክ ፕሮግራም ተጀመረ።
“በሉ ተነሱ እንሂድ፣ የሚቸግራችሁ ነገር ካለ እዚሁ ስላለን በፈለጋችሁት ሰዓት ጠይቁኝ ፤ ” ብሎ ፕሮግራሙ ወደ ሚካሄድበት ስፍራ ወሰደን፡፡
የገዳም ኑሮዬ ተጀመረ፡፡ ለሊት ዘጠኝ ሰዓት መነሳት በጣም ከባድ ነው፡፡ ግን፣ አማራጭ የለም፡፡ አስተባባሪዎች እየዞሩ ይቀሰቅሳሉ።ያልተነሳ ሰው ላይ ቀዝቃዛ ውሃ ይረጫሉ፡፡ የመጀመሪያ ቀናቶች ላይ
በጣም ከበደኝ፡፡ ከእንቅልፍ ሳልነቃ ውሃ ሲረጩኝ እንደ ኤሌክትሪክ ይነዝረኛል፡፡ ሁለት ሦስት ቀን ሲደጋግሙኝ፣ ገና ድምፃቸውን ስሰማ መነሳት ጀመርኩ፡፡ ፀሎትና ምህላው እስከ ጥዋቱ አስራ ሁለት ሰዓት ይደረጋል፤ ከዛ ወደ ፀበል።
ገዳሙን ቅጥር ግቢ በደንብ ለማማወቅ እየተዟዟርኩ ማየት ጀመርኩ፡፡ የአርሴማ ገዳም በሃገራችን እንዳሉት አብዛኞቹ ገዳማት፣በተራራማ ቦታ ላይ ከየተመሰረተ ነው፡፡ የገዳሙ መስራችና አስተዳዳሪ
የሆኑት መነኩሴ፣ እድሜያቸው ሃምሳ ዓመት ቢሆን ነው፡፡ ገዳሙ በእውቀት እንዲለማ በደንብ አስበውበት እንደመሰረቱት ገዳሙ አፍ አውጥቶ ይናገራል፡፡ ከመሰረቱት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)
“ወደ ዚህ ስትመጣ የመጀመሪያህ ነው?”
“አዎ።”
“ትቆያለህ?”
ሳምንት አካባቢ።”
“እዚያ ማዶ ሚታየው አፄ ዮሐንስ አንገታቸው የተቀላበት ቦታ ነው።” እጁን ከመንገዱ በላይ እየጠቆመ::
“መተማ ዮሐንስ ደረስን ማለት ነው?”
“አዎ፡፡ አሁን ገብተናል፡፡” ልቤ ድንግጥ ድንግጥ አለብኝ፡፡ ሚኒባሱ እየቆመ፣ ሰዎችን ያወርዳል። እስከዛሬ ያልተሰማኝ ፍርሀት እየተሰማኝ ነው፡፡ ዝም አልኩ፡፡ ወደ ስንብት እየተጠጋሁ ነው፡፡
የማውራትም የማወቅም ፍላጎት የለኝም፡፡ ዝም ብዬ በዐይኔ ከተማውን መፈለግ ጀምረኩ፡፡ በግራና በቀኝ የተደረደሩ የጭቃ ቤቶች፣ ጭር ያለ ከተማ ነው፡፡ እንደጠበኩት ግርግር የበዛበት ከተማ አይደለም፡፡ ሰዐቴን አየሁ፤ አስር ተኩል፡፡ አብዛኛው ሰው ወርዶ አልቋል፡፡
“መናኸሪያ ትገባለህ?” ወያላው ፊቱን አዙሮ ጠየቀኝ፡፡
“አይ አልገባም፡፡”
“ካልገባህ መጨረሻው እዚህ ነው።”
“እሺ አውርደኝ!”
በጭራሽ እንደገመትኩት አይደለም፡፡ ለማደሪያ ሚሆን አልጋ ቤት እንኳን እስካሁን አላየሁም፡፡ ከተማዋ ትሞቃለች። አስራ አንድ ሰዓት እየሆነ ቢሆንም፣ በጣም ይወብቃል፡፡ ፍርሀት ነው መሰል፣ በጣም እያላበኝ ነው። ዝም ብዬ ዋና መንገዱን ይዤ፣ አልጋ ቤት ፍለጋ
ተጓዝኩኝ፡፡ ነጋዴ የሚርመሰመስበት፣ አዲስ ሰው፣ ፀጉረ ልውጥ ሰው
ከዐይን የማይገባበት ብዬ የገመትኩት ከተማ፣ ትንሽዬ መንደር ሆና አገኘኋት፡፡ መንገድ ዳር በብሎኬት የታጠረ ሰፊ ግቢ ያለው ሆቴል አየሁ፡፡ ሰላም ሆቴል ይላል፡፡ አላንገራገርኩም፡፡ ዘው ብዬ ገባሁ፡፡ ብቻ
አልጋ በኖረ፡፡
“አልጋ አለ?”
“አለ፡፡”
“እስቲ አሳዩኝ?”
“ባለሻወር ነው፣ ያለሻወር?”
“ባለሻወር፡፡” ቁልፍ አመጣችና አሳየችኝ፡፡
“ስንት ነው?”
“አንድ መቶ ሃምሳ ብር፡፡” ብሩን ሰጠኋትና ቦርሳዬን አስቀመጥኩ።
ሻወር ቤት ገብቼ ሻወር ቼክ ሳደርግ ውሀ የለችም፡፡ ዞር ስል፣ውሀ በባልዲ ተቀምጧል፡፡ በጣም አልቦኛል፣ ተለቃለኩኝ፡፡ እራት በልቼ ቢራ መጠጣት ጀመርኩ፡፡ ሙቀት ስለሆነ ተጠጣልኝ፡፡ ማታ ጥሩ እንቅልፍ ተኝቼ አደርኩ፡፡ ቀን ወጥቼ ከተማውን ዙሪያውን ሳይ ዋልኩ፡፡
በፍፁም እኔ እንዳሰብኩት አይደለም፡፡ የከተማው ዙሪያ ለጥ ያለ ለእርሻ የሚውል ሜዳ ሲሆን፣ ዛፎች በእርቀት ነው የሚገኙት፡፡ ስዞር ውዬ አመሻሹ ላይ፣ ቢራዬን እየጠጣሁ ምን እንደሚችል ሳስብ፣ አርሴማ ገዳም የሚል ሀሳብ መጣብኝ፡፡
#ኑሮ_በገዳም
ሽቅብ ዝግዛግ ሆኖ በተሰራውን የጥረጊያ መንገድረገ፣ በግራና በቀኝ በዛፎች ተከቧል፡፡ ከፊት ለፊቴ፣ አጠር ያለ ወጣት፣ የክርስቲያኖ ሮናልዶ ስዕል ያለበት ጥቁር የጨርቅ ሻንጣ በጀርባው ተሸክሞ በዝግታ ያዘግማል። እየተከታተልን ወደ ገዳሙ ዘልቀን ገባን። ከገዳሙ መግቢያ
በር ትንሽ ፈቅ ብላ ያለች የጭቃ ቤት ጋር ስንደርስ፤
“እንኳን ደህና መጣችሁ። ምዝገባ ቢጤ አለች።” አለን ፊቱ መጠጥ ያለ ጠይም ወጣት፡፡
“እሺ!” ብዬ ቆምኩኝ፡፡ ልጁን መዝግቦ ከጨርሰ በኋላ፣ ትንሽ ቆየኝ ብሎት እኔን መመዝግብ ጀመረ፡፡ ስም፣ እድሜ፣ የመጡበት አድራሻ፣ የአደጋ ግዜ ተጠሪ...፣ ሁሉንም ቀይሬ ነገርኩት፡፡
“ለስንት ግዜ ነው ሚቆዩት?”
“ለሦስት ሳምንት፡፡”
“መታወቂያ ይዘዋል?”
“አልያዝኩም፡፡” አልተጫነኝም፡፡
“እሺ፣ እንግዶቻችን፣ እኔ መልካሙ እባላለሁ፡፡ በገዳሙ አስተባባሪ ነኝ፡፡ አሁን ማደሪያ ቦታ እሰጣችኋለው፡፡ ገዳሙን
አስጎበኛችኋለው፤ ስለ ገዳሙ ታሪክ፣ መተዳደሪያ ደንብና ሌሎች መረጃዎችን እነግራችኋለው፡፡ እዚህ ገዳም፣ ማንኛውም አዲስ ሱባኤተኛ ሲገባ እናንተ እንዳደረጋችሁት ተመዝግቦ ነው፡፡ ገዳሙ የአርምሞ ገዳም ነው:: ማውራት ክልክል ነው፡፡ አስገዳጅ ነገር ካላጋጠማችሁ በስተቀር፣ ማውራት አይቻልም፡፡ የግድ ማውራት ካስፈለገ እንኳ፣ ዝግ ባለ ድምፅ፣ በለሆሳስ ነው ማውራት ሚቻለው፡፡ እዚህ መዳን የሚገኘው በአርምሞ ውስጥ ነው፡፡”
ከኛ ውጪ ለሌላ ሰው እንዳይሰማ፣ በሆዱ እንደሚያወራ፣ በጣም ዝግ ባለ ድምፅ ያወራናል፡፡ በአርምሞና በለሆሳስ ማለት እንዲህ ነው' ብዬ አሰብኩ፡፡ የሚያወራው እንዲሰማን፣ አንገታችንን ወደሱ አሰገግን፡፡ እያወራን ወደ ማደሪያችን ወሰደን፡፡ እያንዳንዱ ከሁለት መቶ ምዕመን በላይ የሚይዝ፣ አራት የማደሪያ አዳራሾች አሉ፡፡ ሁለቱ የወንድ፣ ሁለቱ የሴት እንደሆነ ነገረን፡፡ ቦታ ሊሰጠን ወደ አንደኛው አዳራሽ ይዞን ገባ፡፡ በውስጡ ከመቶ ሚበልጡ ምዕመናን አሉ፡፡አሰላሁት። በግምት በገዳሙ አንድ ሺህ የሚጠጉ ሱባኤያተኛ ምዕመናን
እንዳሉ ገመትኩኝ፡፡ ገዳሙ ግን ሰው ያለው አይመስልም፡፡ ዝም፣ ጭጭ፣ ያለ ነው፡፡ ሁሉም በለሆሳስ ፀሎት ላይ ነው፡፡ ሰላምታ እንኳ፣ ጎንበስ ቀና በመባባል ብቻ ነው፡፡ ምንም አይነት የሰው ድምፅ አይሰማም፡፡የወፎች ጭጭታና የዛፎች ሽው ሽውታ ብቻ ነው፡፡ በጣም ደስ ይላል፡፡መንፈስን ያድሳል፡፡ አዕምሮን ያረጋጋል፡፡ ፈውስ በመንፈስ ቅዱስ
ባይላክም እንኳ፣ የቦታው ድባብ ፈውስን ይሰጣል።
“እና ሌላው...” አለ መልካሙ ቦታችንን ሰጥቶን ከአዳራሹ ይዞን እየወጣ፣ “ማንኛውም ምእመን ወደ ገዳሙ ለሱባኤ ሲገባ፤ ፀጉሩን መላጨት፣ ንስሀ መግባትና ስግደት መውሰድ አለበት፡፡” አለን እኔን እኔን እየተመለከተ፡፡
“እሺ፡፡ ማን ነው ሚላጨን?”
“እርስ በእረስ ነው ምትለጫጩት፡፡ ፈራህ እንዴ..? አንተን እኔ ቆንጆ አድርጌ እላጭሃለው፡፡” የከተማ ልጅ መሆኔን አውቆ ነው መሰል፣ ከገባን ጀምሮ እኔን እኔን እየተመለከተ ነው ሲያወራ የነበረው፡፡
“እሺ” አልኩት፡፡ አሁን ስለራሴ ብዙም ግድ የለኝም፡፡ ምላጭ ግቢ ካለው ሱቅ ተገዝቶ ሁለታችንንም ላጨን፡፡ ነብስ ካወኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ፀጉሬን ተላጨሁ፡፡ እየላጨንም ስለ ገዳሙ መተዳደሪያ ደንብ ይነግረናል።
“በገዳሙ፣ በቀን ሁለት ጊዜ ብቻ ነው የሚበላው፡፡ ጥዋት ቅዳሴ እንዳለቀና ማታ አስራ ሁለት ሰዐት። አስራ ሁለት ሰዐት ካለፈ መመገብ አይቻልም፡፡ ገዳሙ መብራት ስለሌለው፣ ማታ ማታ ሻማ ነው
ምትጠቀሙት። ሻማ ከዚህ ሱቅ መግዛት ትችላላችሁ፡፡ የማታ ሦስት ሰዓት ፀሎት ካበቃ ቦሃላ ሻማ ማብራት አይቻልም፡፡ የእንቅልፍ ሰዓት ነው፡፡ እንዳያችሁት፣ የቦታ ጥበት ስላለ አንድ ሰው፣ በአንድ መዳበሪያ በታ ላይ ነው መተኛት ያለበት፡፡ የለሊቱ ዘጠኝ ሰአት ፀሎት ላይ ሁሉም
ምዕመን መገኘት ግዴታ ነው፡፡” ሁለታችንንም ላጭቶ ሲጨርስ አስራ
አንድ ሰዐት ሆኖ የሰርክ ፕሮግራም ተጀመረ።
“በሉ ተነሱ እንሂድ፣ የሚቸግራችሁ ነገር ካለ እዚሁ ስላለን በፈለጋችሁት ሰዓት ጠይቁኝ ፤ ” ብሎ ፕሮግራሙ ወደ ሚካሄድበት ስፍራ ወሰደን፡፡
የገዳም ኑሮዬ ተጀመረ፡፡ ለሊት ዘጠኝ ሰዓት መነሳት በጣም ከባድ ነው፡፡ ግን፣ አማራጭ የለም፡፡ አስተባባሪዎች እየዞሩ ይቀሰቅሳሉ።ያልተነሳ ሰው ላይ ቀዝቃዛ ውሃ ይረጫሉ፡፡ የመጀመሪያ ቀናቶች ላይ
በጣም ከበደኝ፡፡ ከእንቅልፍ ሳልነቃ ውሃ ሲረጩኝ እንደ ኤሌክትሪክ ይነዝረኛል፡፡ ሁለት ሦስት ቀን ሲደጋግሙኝ፣ ገና ድምፃቸውን ስሰማ መነሳት ጀመርኩ፡፡ ፀሎትና ምህላው እስከ ጥዋቱ አስራ ሁለት ሰዓት ይደረጋል፤ ከዛ ወደ ፀበል።
ገዳሙን ቅጥር ግቢ በደንብ ለማማወቅ እየተዟዟርኩ ማየት ጀመርኩ፡፡ የአርሴማ ገዳም በሃገራችን እንዳሉት አብዛኞቹ ገዳማት፣በተራራማ ቦታ ላይ ከየተመሰረተ ነው፡፡ የገዳሙ መስራችና አስተዳዳሪ
የሆኑት መነኩሴ፣ እድሜያቸው ሃምሳ ዓመት ቢሆን ነው፡፡ ገዳሙ በእውቀት እንዲለማ በደንብ አስበውበት እንደመሰረቱት ገዳሙ አፍ አውጥቶ ይናገራል፡፡ ከመሰረቱት
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
ሻምበል ብሩክና ትህትና ድንበሩ ከተዋወቁ ዛሬ ልክ አንድ ወራቸው፡፡ የፍቅራቸው ወርሃዊ ልደት ውል የሚበጅበት ቀን በመሣሣም ደረጃ የቆየው ፍቅር ዛሬ ወደ አካላዊ ውህደት ሊሸጋገር እቅድ ተይዞለታል። ሻምበል ብሩክም ሆነ ትህትና የዛሬውን ቀን በልዩ ጉጉት ነው የጠበቁት።
እሁድ ዕለት አሥመራ መንገድ በሚገኘው በሻምበል ብሩክ ቤት ለማደር የወሰነችበት ቀን ነበር፡፡ ወደ ዶክተር ባይከዳኝ ቀጠሮ ስትሄድ የሚሰማት ስሜት ከቀጠሮው በስተጀርባ ባለው ምክንያት አስገዳጅነት እንጂ በፍቅር አስገዳጅነት አልነበረም፡፡
ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር የምትፈጽማቸው ግንኙነቶች እውነተኛ ስሜቷን የምትገልጽባቸው ሳይሆኑ፤ በተላበሰችው ጭምብል እውነተኛ ማንነቷን ደብቃ፤ በመድረክ ላይ ትያትር የምትሰራ ተዋናይ ሆና ነው የምትውለው፡፡ በሻምበል ብሩክ ፍቅር ግን ሰውነቷ እንደሻማ እየቀለጠ፣
ልቧ በዕልልታ እየጨፈረች፤ ሁለንተናዋን አሳልፋ የምትሰጠው በደስታ ስሜት ሰክራ ነው፡፡ በተለይ የመጀመሪያዋ በሆነው የወንድ ልጅ ፍቅር የተረታችለት ሰው፤ እንደዘመኑ ወጣቶች በአንድ ነገር ላይ ብቻ ትኩረት የሚሰጥ ሳይሆን በሷ ቦታ ሆኖ ሁሉን ነገር የሚያስብላትና፤
የሚያጽናናት፤ ሆኖ በመገኘቱ ፈጣሪዋን ታመሰግናለች፡፡
ብቻ አንዳንድ ጊዜ የሰው ልጅ ሥጋ ለባሽ ፍጡር ነውና፣ ሰው ተላላና ደካማ ፍጡር ነውና፤ ሰው ሰው ነውና፤ ይህ ሁሉ ፍቅር ድንገት ብን ብሎ ጠፍቶ፣ ሻምበል ብሩክም ተለውጦ፣ እንዳይከዳት ልቧ
መጠርጠሩ አልቀረም፡፡
እንደዚያ ታስብና ደግሞ አስተሳሰቧ ትክክል ባለመሆኑ እራሷን ወቅሳ “ብሩኬ አይለወጥም”
በማለት መልሳ መጽናናትን ታሳድራለች፡፡ በዛሬው ዕለት ሻምበል ብሩክ ቤት ለማደር ቀጠሮውን በልቧ የወሰደችው በከፍተኛ ደስታ ነው። ምናልባት የዛሬው አዳር ደግሞ ያንን ተንከባክባ ያቆየችውን የልጃገረድነት ወግ፣ ብር አምባሯን የምትፈተሽበት ወቅት ሊሆን ይችላል፡፡ ከዚያ በኋላ “ዞር በይ” ቢላትስ? ልቧ
በመጠራጠርና፤ ባለመጠራጠር፤ስሜት መሀል ገብቶ ሲዋዥቅ ከዋለ በኋላ
አንድ ነገር አሰበች።
ለሻምበል ብሩክ ልጃገረድ መሆኗን ገልጻለት፤ እንደ ወጉ፤ እንደ ሥርዐቱ፤ በጫጉላ ቤት ብር አምባሯን ልትሰጠው ያላትን ምኞች የሱን ስሜትና ፍላጐት ከተረዳች በኋላ ካሳወቀችውና በአጠቃላይ ስለማንኛውም ነገር አብረው በጋራ መወሰን እንደሚችሉ ገምታ፤ በዚሁ ሃሳብ ፀናች።
“እማይዬ ዛሬ አዜቢና ጋ ነው የማድረው ፓርቲ አዘጋጅታለች' በማለት እናቷን ዋሸቻት።
“ባርቲ ደግሞ ምንድነው ትሁቴ?” እናት በመጠራጠር ስሜት፡፡
“ያው ነዋ! ጓደኞቿ ተሰባስበን ስንጫወት ማደር ማለት ነዋ!” እየሳቀች፡፡
አደራሽን የኔ እራስሽን ጠብቂ!!” እናቷ ዐይን ዐይኖቿን እያየቻት።የውጭ አዳር የተሰማው ገና ዛሬ ነው፡፡
“ምንም ችግር የለም:: ማሚ ሙች!” ጉንጫን ሳመቻት፡፡ እናቷ በልቧ
ዝግጅቷን አሰበችው፡፡ በጠዋት ተነስቶ መተጣጠቡ፣ ቀኑን ሙሉ ሲመረጥ የተዋለው ልብስ፣ ሦስት ጊዜ አውልቃ ቀይራለች። መስተዋቱ ሥራ አልፈታም፡፡ መኳኳሉ ሁሉ ያልተለመደ ነበር።
በልቧ ወደ ሻምበል ብሩክ እንደምትሄድ ብታውቀውም የሰጠቻትን ምክንያት ይሁን ብላ ተቀበለቻት፡፡
ዛሬ ሻምበል ብሩክ ጋ የምታድር መሆኗን ለአንዱአለም ስለነገረችው በጊዜ ወደቤት እንዲገባ ተስማምተዋል። በዚህ ላይ የቤት ሰራተኛዋ እታፈራሁ ታክላበት እናቷን በመንከባከብ በኩል ኃላፊነቱን
ስለሚወስዱ የሚያስጨንቃት ነገር አልነበረም፡፡ ሁሉንም አጥብቃ አደራ
ብላ፤ ከቤት የወጣችው ከቀኑ አሥራ ሁለት ሰዓት ላይ ነበር።
ሻምበል ብሩክ ዛሬ ሽር ጉድ ሲል አርፍዷል። አልጋው ቦታ ሲመረጥለት፤ ሲንከራተት፤ የቤቱ ቁሳቁሶች በሙሉ በአዲስ መልክ አንዴ በጭንቅላታቸው፧ አንዴ በእግራቸው፤ ሲቆሙ፤ ቦታ ሲመረጥላቸው ነው የተዋለው፡፡
በዛሬው የቤት ዝግጅት ላይ ሠራተኛዋ ብቻ ሳትሆን ሁለቱም ታናናሽ ወንድሞቹ አብረውት ቤቱን ሲያተራምሱት ነው የዋሉት፡፡
በመጨረሻ ላይ ግን ከዚያ በፊት ያልታየበት ዓይነት ሥርዓትና መልክ ይዞ ሲያይ ሻምበል ብሩክ ተደነቀ፡፡
በእርግጥም ይህ ሁሉ የሆነው በትህትና ምክንያት መሆኑን ሲያስብ፤ የትዳር ውጥኑ አግባብ መሆኑን አመነ። በዚያ በቤቱ ሥርዓት ተማርኮ ወደሌላ ሃሳብ ውስጥ ገባ፡፡
ባለፋቸው መጥፎ ጊዜያቶች ውስጥ የተጐዳ ልቡ፣ በትህትና የወደፊት የትዳር እመቤቱ አማካይነት ሊታደስና፤ ሲታነጽ፤ ታየው።
እናም የትዳር መዓዛ በርቀት ሸተተው፡፡ ይህ በርቀት የሚሸተው የትዳር መዓዛ ቀርቦ እንዲያውደው ተመኘ፡፡
ትህትና እስከምትመጣለት የቀጠሮው ሰዓት እስከሚደርስ ድረስ ተንቆራጠጠ።
ዛሬ የሚነግራት ትልቅ ጉዳይ አለው። እሷም እንደሱ በጉዳዩ
ላይ ፈቃደኛ ከሆነች ጉዳዩ የምሥራች ይሆናል። እሷን የፈለጋት ጊዜያዊ
ፍቅረኛ እንድትሆነው ሳይሆን፤ ዘላቂ የትዳር ጓደኛው እንድትሆን ነው::
ይህ እሱ የጓጓለትን በፀጋ ከተቀበለችለት ደስታው እጥፍ ድርብ ይሆናል፡፡
“ትሁት.. ትሁት.. ትሁት.. ስሟን ደጋገመው። በልቡ፡፡
ልክ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ላይ ታላቋ እንግዳ የዱር ጽጌረዳ መስላ አምራና፤ ደምቃ ከች! አለች፡፡ ቤቱን ከዚህ ቀደም አንድ ሁለት ጊዜ አይታዋለች፡፡ የዛሬውን ልዩ የሚያደርገው ለማደር ወስና የመጣችበት ዕለት በመሆኑ ነው፡፡
ሻምበል ብሩክ ከደጅ ወጥቶ እየተጠባበቃት ነበር። በሁለመናው
አቅፎ ተቀበላት፡፡
ከዚያም አጥሩን ዘልቀው እየተሳሳቁ፣ እጅ ለእኛ ተያይዘው ወደ ቤት ገቡ፡፡
የሻምበል ብሩክ ሁለት ታናናሽ ወንድሞቹ ሰላምታ አቅርበውላት ትንሽ ከተጫወቱ በኋላ የግል ነፃነት ሊሰጧቸው ወጡ።
ዛሬ የሻምበል ብሩክ ቤት ልዩ ሆናለች:: ትህትናም ከዚያ በፊት ያየቸው ቤት መሆኑ እስከሚያጠራጠራት ድረስ የቤት ዕቃዎቹ አቀማመጥ አስደንቋታል፡፡
ሻምበል ብሩክ የትዳር ምኞቱን ሊገልጽላት ሲያሰላስል፤ እሷ ደግሞ ሌላ የምትገልጽለት እጹብ ድንቅ የሆነ የምስራች ነበራት። ሻምበል ብሩክ በፍቅር ቢወድቅላትም፤ ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ ያልገመተውን ገፀ በረከት ልታቀርብለት ማሰቧን ቢያውቅ ኖሮ ምንኛ ደስተኛ ይሆን ነበር?፣
ቀለል ያለ እራት ከበሉ በኋላ ይሄንን የቀዘቀዘ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራቸውን
መኮምኮም ቀጠሉ። ዛሬ ቢራው አልመረራትም። የፍቅር ስኳር
ተጨምሮበት ነው መሰል፤ ከምትወደው ሰው ጋር በፍቅር እየቀለጡ፤ ሲኮመኩሙት ማር ሆነና ቁጭ አለ፡፡ ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር ሆና ስትጠጣው የግራዋ ጭማቂ ያህል ነበር የሚመራት። አሁን ግን ጣፈጣት፡፡
አንዱን ቢራ ጨረስችና በህይወቷ ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለተኛውን የቢራ ጠርሙስ ጨበጠች፡፡ ሻምበል ብሩክ የወደፊት የትዳር ጓደኛው ከምትሆን ቆንጆ ጋር እያሳለፈ ባለው ጊዜ እጅግ ከመደሰቱም በላይ ከረጅም ዓመታት በፊት እጮኛው ከነበረችው በድሏ ጋር ያሳልፉ የነበረውን ዓይነት ልዩ ስሜት አጫረበትና፤ ጨዋታውን በሰፊው ቀጠለ። እየተቃቀፉ መላላሱ ፤ መሳሳሙ፤ ሁሉ ለጉድ ነበር፡፡
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ሲሆን ወደ መኝታ ክፍላቸው መሄድ ፈለጉ።
የመኝታ ክፍሏ በንጽህና የተጠበቀች ናት። እንደገቡ በነጭ ስስ የመጋረጃ ጨርቅ የተሸፈነውን ባለመስታወት መስኮት ሲገልጡት ፍንትው ብላ ደምቃ የወጣችው ጨረቃ ብርሃኗን ወደመኝታ ክፍላቸው ውስጥ አዘለቀችላቸው...
ያንን የጨረቃ ውበት ሲያስተውሉ፤ መብራቱን አጠፉት በዚያች ክፍል
ውስጥ ጨረቃና ፍቅር ነገሱ ከዚያም ልብሳቸውን እንደለበሱ አልጋቸው ላይ ጋደም ብለው መላፋታቸውን ቀጠሉ....
የትህትና ሁኔታ የተለየ ነበር ከዚያ በፊት ለወንድ ልጅ የነበራት ስሜት ምን እንደ ነበረና አሁን ምን እየሆነች እንዳለች
ስታስበው
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
ሻምበል ብሩክና ትህትና ድንበሩ ከተዋወቁ ዛሬ ልክ አንድ ወራቸው፡፡ የፍቅራቸው ወርሃዊ ልደት ውል የሚበጅበት ቀን በመሣሣም ደረጃ የቆየው ፍቅር ዛሬ ወደ አካላዊ ውህደት ሊሸጋገር እቅድ ተይዞለታል። ሻምበል ብሩክም ሆነ ትህትና የዛሬውን ቀን በልዩ ጉጉት ነው የጠበቁት።
እሁድ ዕለት አሥመራ መንገድ በሚገኘው በሻምበል ብሩክ ቤት ለማደር የወሰነችበት ቀን ነበር፡፡ ወደ ዶክተር ባይከዳኝ ቀጠሮ ስትሄድ የሚሰማት ስሜት ከቀጠሮው በስተጀርባ ባለው ምክንያት አስገዳጅነት እንጂ በፍቅር አስገዳጅነት አልነበረም፡፡
ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር የምትፈጽማቸው ግንኙነቶች እውነተኛ ስሜቷን የምትገልጽባቸው ሳይሆኑ፤ በተላበሰችው ጭምብል እውነተኛ ማንነቷን ደብቃ፤ በመድረክ ላይ ትያትር የምትሰራ ተዋናይ ሆና ነው የምትውለው፡፡ በሻምበል ብሩክ ፍቅር ግን ሰውነቷ እንደሻማ እየቀለጠ፣
ልቧ በዕልልታ እየጨፈረች፤ ሁለንተናዋን አሳልፋ የምትሰጠው በደስታ ስሜት ሰክራ ነው፡፡ በተለይ የመጀመሪያዋ በሆነው የወንድ ልጅ ፍቅር የተረታችለት ሰው፤ እንደዘመኑ ወጣቶች በአንድ ነገር ላይ ብቻ ትኩረት የሚሰጥ ሳይሆን በሷ ቦታ ሆኖ ሁሉን ነገር የሚያስብላትና፤
የሚያጽናናት፤ ሆኖ በመገኘቱ ፈጣሪዋን ታመሰግናለች፡፡
ብቻ አንዳንድ ጊዜ የሰው ልጅ ሥጋ ለባሽ ፍጡር ነውና፣ ሰው ተላላና ደካማ ፍጡር ነውና፤ ሰው ሰው ነውና፤ ይህ ሁሉ ፍቅር ድንገት ብን ብሎ ጠፍቶ፣ ሻምበል ብሩክም ተለውጦ፣ እንዳይከዳት ልቧ
መጠርጠሩ አልቀረም፡፡
እንደዚያ ታስብና ደግሞ አስተሳሰቧ ትክክል ባለመሆኑ እራሷን ወቅሳ “ብሩኬ አይለወጥም”
በማለት መልሳ መጽናናትን ታሳድራለች፡፡ በዛሬው ዕለት ሻምበል ብሩክ ቤት ለማደር ቀጠሮውን በልቧ የወሰደችው በከፍተኛ ደስታ ነው። ምናልባት የዛሬው አዳር ደግሞ ያንን ተንከባክባ ያቆየችውን የልጃገረድነት ወግ፣ ብር አምባሯን የምትፈተሽበት ወቅት ሊሆን ይችላል፡፡ ከዚያ በኋላ “ዞር በይ” ቢላትስ? ልቧ
በመጠራጠርና፤ ባለመጠራጠር፤ስሜት መሀል ገብቶ ሲዋዥቅ ከዋለ በኋላ
አንድ ነገር አሰበች።
ለሻምበል ብሩክ ልጃገረድ መሆኗን ገልጻለት፤ እንደ ወጉ፤ እንደ ሥርዐቱ፤ በጫጉላ ቤት ብር አምባሯን ልትሰጠው ያላትን ምኞች የሱን ስሜትና ፍላጐት ከተረዳች በኋላ ካሳወቀችውና በአጠቃላይ ስለማንኛውም ነገር አብረው በጋራ መወሰን እንደሚችሉ ገምታ፤ በዚሁ ሃሳብ ፀናች።
“እማይዬ ዛሬ አዜቢና ጋ ነው የማድረው ፓርቲ አዘጋጅታለች' በማለት እናቷን ዋሸቻት።
“ባርቲ ደግሞ ምንድነው ትሁቴ?” እናት በመጠራጠር ስሜት፡፡
“ያው ነዋ! ጓደኞቿ ተሰባስበን ስንጫወት ማደር ማለት ነዋ!” እየሳቀች፡፡
አደራሽን የኔ እራስሽን ጠብቂ!!” እናቷ ዐይን ዐይኖቿን እያየቻት።የውጭ አዳር የተሰማው ገና ዛሬ ነው፡፡
“ምንም ችግር የለም:: ማሚ ሙች!” ጉንጫን ሳመቻት፡፡ እናቷ በልቧ
ዝግጅቷን አሰበችው፡፡ በጠዋት ተነስቶ መተጣጠቡ፣ ቀኑን ሙሉ ሲመረጥ የተዋለው ልብስ፣ ሦስት ጊዜ አውልቃ ቀይራለች። መስተዋቱ ሥራ አልፈታም፡፡ መኳኳሉ ሁሉ ያልተለመደ ነበር።
በልቧ ወደ ሻምበል ብሩክ እንደምትሄድ ብታውቀውም የሰጠቻትን ምክንያት ይሁን ብላ ተቀበለቻት፡፡
ዛሬ ሻምበል ብሩክ ጋ የምታድር መሆኗን ለአንዱአለም ስለነገረችው በጊዜ ወደቤት እንዲገባ ተስማምተዋል። በዚህ ላይ የቤት ሰራተኛዋ እታፈራሁ ታክላበት እናቷን በመንከባከብ በኩል ኃላፊነቱን
ስለሚወስዱ የሚያስጨንቃት ነገር አልነበረም፡፡ ሁሉንም አጥብቃ አደራ
ብላ፤ ከቤት የወጣችው ከቀኑ አሥራ ሁለት ሰዓት ላይ ነበር።
ሻምበል ብሩክ ዛሬ ሽር ጉድ ሲል አርፍዷል። አልጋው ቦታ ሲመረጥለት፤ ሲንከራተት፤ የቤቱ ቁሳቁሶች በሙሉ በአዲስ መልክ አንዴ በጭንቅላታቸው፧ አንዴ በእግራቸው፤ ሲቆሙ፤ ቦታ ሲመረጥላቸው ነው የተዋለው፡፡
በዛሬው የቤት ዝግጅት ላይ ሠራተኛዋ ብቻ ሳትሆን ሁለቱም ታናናሽ ወንድሞቹ አብረውት ቤቱን ሲያተራምሱት ነው የዋሉት፡፡
በመጨረሻ ላይ ግን ከዚያ በፊት ያልታየበት ዓይነት ሥርዓትና መልክ ይዞ ሲያይ ሻምበል ብሩክ ተደነቀ፡፡
በእርግጥም ይህ ሁሉ የሆነው በትህትና ምክንያት መሆኑን ሲያስብ፤ የትዳር ውጥኑ አግባብ መሆኑን አመነ። በዚያ በቤቱ ሥርዓት ተማርኮ ወደሌላ ሃሳብ ውስጥ ገባ፡፡
ባለፋቸው መጥፎ ጊዜያቶች ውስጥ የተጐዳ ልቡ፣ በትህትና የወደፊት የትዳር እመቤቱ አማካይነት ሊታደስና፤ ሲታነጽ፤ ታየው።
እናም የትዳር መዓዛ በርቀት ሸተተው፡፡ ይህ በርቀት የሚሸተው የትዳር መዓዛ ቀርቦ እንዲያውደው ተመኘ፡፡
ትህትና እስከምትመጣለት የቀጠሮው ሰዓት እስከሚደርስ ድረስ ተንቆራጠጠ።
ዛሬ የሚነግራት ትልቅ ጉዳይ አለው። እሷም እንደሱ በጉዳዩ
ላይ ፈቃደኛ ከሆነች ጉዳዩ የምሥራች ይሆናል። እሷን የፈለጋት ጊዜያዊ
ፍቅረኛ እንድትሆነው ሳይሆን፤ ዘላቂ የትዳር ጓደኛው እንድትሆን ነው::
ይህ እሱ የጓጓለትን በፀጋ ከተቀበለችለት ደስታው እጥፍ ድርብ ይሆናል፡፡
“ትሁት.. ትሁት.. ትሁት.. ስሟን ደጋገመው። በልቡ፡፡
ልክ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ላይ ታላቋ እንግዳ የዱር ጽጌረዳ መስላ አምራና፤ ደምቃ ከች! አለች፡፡ ቤቱን ከዚህ ቀደም አንድ ሁለት ጊዜ አይታዋለች፡፡ የዛሬውን ልዩ የሚያደርገው ለማደር ወስና የመጣችበት ዕለት በመሆኑ ነው፡፡
ሻምበል ብሩክ ከደጅ ወጥቶ እየተጠባበቃት ነበር። በሁለመናው
አቅፎ ተቀበላት፡፡
ከዚያም አጥሩን ዘልቀው እየተሳሳቁ፣ እጅ ለእኛ ተያይዘው ወደ ቤት ገቡ፡፡
የሻምበል ብሩክ ሁለት ታናናሽ ወንድሞቹ ሰላምታ አቅርበውላት ትንሽ ከተጫወቱ በኋላ የግል ነፃነት ሊሰጧቸው ወጡ።
ዛሬ የሻምበል ብሩክ ቤት ልዩ ሆናለች:: ትህትናም ከዚያ በፊት ያየቸው ቤት መሆኑ እስከሚያጠራጠራት ድረስ የቤት ዕቃዎቹ አቀማመጥ አስደንቋታል፡፡
ሻምበል ብሩክ የትዳር ምኞቱን ሊገልጽላት ሲያሰላስል፤ እሷ ደግሞ ሌላ የምትገልጽለት እጹብ ድንቅ የሆነ የምስራች ነበራት። ሻምበል ብሩክ በፍቅር ቢወድቅላትም፤ ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ ያልገመተውን ገፀ በረከት ልታቀርብለት ማሰቧን ቢያውቅ ኖሮ ምንኛ ደስተኛ ይሆን ነበር?፣
ቀለል ያለ እራት ከበሉ በኋላ ይሄንን የቀዘቀዘ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራቸውን
መኮምኮም ቀጠሉ። ዛሬ ቢራው አልመረራትም። የፍቅር ስኳር
ተጨምሮበት ነው መሰል፤ ከምትወደው ሰው ጋር በፍቅር እየቀለጡ፤ ሲኮመኩሙት ማር ሆነና ቁጭ አለ፡፡ ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር ሆና ስትጠጣው የግራዋ ጭማቂ ያህል ነበር የሚመራት። አሁን ግን ጣፈጣት፡፡
አንዱን ቢራ ጨረስችና በህይወቷ ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለተኛውን የቢራ ጠርሙስ ጨበጠች፡፡ ሻምበል ብሩክ የወደፊት የትዳር ጓደኛው ከምትሆን ቆንጆ ጋር እያሳለፈ ባለው ጊዜ እጅግ ከመደሰቱም በላይ ከረጅም ዓመታት በፊት እጮኛው ከነበረችው በድሏ ጋር ያሳልፉ የነበረውን ዓይነት ልዩ ስሜት አጫረበትና፤ ጨዋታውን በሰፊው ቀጠለ። እየተቃቀፉ መላላሱ ፤ መሳሳሙ፤ ሁሉ ለጉድ ነበር፡፡
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ሲሆን ወደ መኝታ ክፍላቸው መሄድ ፈለጉ።
የመኝታ ክፍሏ በንጽህና የተጠበቀች ናት። እንደገቡ በነጭ ስስ የመጋረጃ ጨርቅ የተሸፈነውን ባለመስታወት መስኮት ሲገልጡት ፍንትው ብላ ደምቃ የወጣችው ጨረቃ ብርሃኗን ወደመኝታ ክፍላቸው ውስጥ አዘለቀችላቸው...
ያንን የጨረቃ ውበት ሲያስተውሉ፤ መብራቱን አጠፉት በዚያች ክፍል
ውስጥ ጨረቃና ፍቅር ነገሱ ከዚያም ልብሳቸውን እንደለበሱ አልጋቸው ላይ ጋደም ብለው መላፋታቸውን ቀጠሉ....
የትህትና ሁኔታ የተለየ ነበር ከዚያ በፊት ለወንድ ልጅ የነበራት ስሜት ምን እንደ ነበረና አሁን ምን እየሆነች እንዳለች
ስታስበው
#የፍቅር_ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
....ዋናው አዛዥ ብሩዲም ወደ ጉድማን ዞሮ “አንተም ማስታወሻዎቹን
አንብበህ ጨርሰሃል አይደል? እሺ በጆንሰን ሀሳብ ትስማማለህ?”
ጉድማንም የእግሮቹን ንብብሮሽ ስላልተመቸው ቀያየራቸው እና ዶክተር
ሮበርትስ ስለ በሽተኞቿ በማስታወሻዎቿ ላይ የፃፈቻቸውን ነገሮች በውስጡ
መከለስ ጀመረ።
ዶክተር ሮበርትስ ማስታወሻዎቹን ሌላ ሰው ያነባቸዋል ስላልገመተች ስለ በሽተኞቿ የተሰማትን ነገሮች ሁሉ ነው ማስታወሻዋ ላይ ያሰፈረችው። ይህንን ደግሞ ያደረገችው ምናልባት በሚቀጥለው የህክምና ጊዜያቸው ላይ በሽተኞቿን ስታገኛቸው ከግለሰባዊ ባህርያቸው በመነሳት ልትረዳቸው በማሰብ እንደሆነም ያምናል። ግን እዚህ ላይ ጆንሰን ለዶክተሯ ያለው ጥላቻ ወደዚህ አይነት ማጠቃለያ ላይ እንዲደርስ ሊያደርገው እንደሚችል እንዴት አላሰበውም? ይህንን በውስጡ ሲያውጠነጥን ቆየ እና
“መልካም ማስታወሻዎቹ ላይ ስለ ታካሚዎቿ ስነ ባህሪ ግምገማን (ፍርድን)
አካሂዳለች ብዬ አምናለሁ” ብሎ መለሰ፡፡
ይሄኔም ጆንሰን የሹፈት ሳቅ ሳቀበት እና ግምገማ አልክ? ሮበርትስ እኮ ይህቺ ሊዛ ፍላንገን የተባለችን ሴት ትጠላታለች። በማስታወሻዋ ላይ ሊዛ ፍላንገን የምትገልፃት ለድርጊቷ መጠየቅ እንዳለባት ማለትም በሌሎች ሴቶች (ሚስቶች) ላይ ለፈጠረችው ስቃይ መጠየቅ እንዳለባት ነው የማስታወሻዋ ዋነኛ ሀሳብ” አለ፡፡
“ዋነኛው ሀሳብ ደግሞ ምንድነው?” ብሎ አዛዡ ግራ ተጋብቶ ጠየቀው።
ሚኪ ሮበርትስ ውሽማ በሚሆኑ ሴቶች ላይ ሁሉ ቂም አላት” አለ ጆንስን፡፡
“እንዴ ይሄ እኮ ሃጢአቱን እሷ ላይ ማብዛት ነው።” ብሎ ጉድማን
ጣልቃ ገባ ።
“ይመስልሀል? እኔ ግን አይመስለኝም፡፡ ለማንኛውም ማስታወሻዋን
ካነበብኩኝ በኋላ ለምንድነው በሊዛ ፍላንገን ላይ ይህን ይህል ቅሬታ
ያደረባት? ብዬ ራሴን ጠየቅኩኝ” ብሎ ጆንሰን ማብራሪያውን በመቀጠልም
“በመጨረሻም ነገሩ ከሟች ባሏ ጋር በተገናኘ እንደሆነ ለማወቅ በቃሁ”
“ባሏ ሞቶ አይደል እንዴ?” ብሎ አዛዥ ብሩዲ ጉንጩን እያሸ ጠየቀ::
“ልክ ነው ባሏ ሞቷል። ዶክተር ዳግላስ ሮበርትስ ባለፈው ዓመት በ 405 ኛው ጎዳና ላይ የአደጋው ምክንያት ባልታወቀ የመኪና አደጋ ህይወቱን አጥቷል። ግን በወቅቱ መኪናው ውስጥ ከእሱ ጎን ማን እንደነበር እስቲ ገምቱ” አላቸው፡፡ ሁለቱም አዛዥ ብሩዲ እና ጉድማን ግምታቸውን ለማስቀመጥ በጥሩ ስሜት ውስጥ ስላልሆኑ ምላሹን እንዲሰጣቸው
እያፈጠጡበት ዝም አሉ።
“ውሽማው አብራው ነበረች!” ብሎ ጉድማን በመቀጠልም “የሆነች
ሩሲያዊ ሴትን ከጎኑ አስቀምጦ መኪናውን ሲያሽከረክር ነበር አደጋው የደረሰው። በአደጋው ሁለቱም ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡ ያን ዕለት ነበር ዶክተር ኒኪ ሮበርትስ ባሏ ከትዳር ውጪ ያለውን ግንኙነት ለመጀመሪያ ጊዜ ያወቀችው እንግዲህ”
የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች በአደጋው ከነደደ መኪና ውስጥ የሁለት ሰዎችን ሬሳ ሲያወጡ እሷ ምን ሊሰማት እንደሚችል አስቡት እስቲ! የውስጥ ህመሙን? ውርደቱን? ሁሉም ሰው እና እናንተም ጭምር ሁለቱ ምን ያህል የሚቀናበት ትዳር እንዳላቸው ታምኑ አልነበር?” ብሎ ጆንሰን ጉድማንን አገኘሁህ በሚል ስሜት ተመለከተው፡፡
ኒኪም ማታ ላይ ስለ ባሏ በግልፅ ነግራዋለች፡፡ ስለ ባሏ የተናገረችበት
መንገድ ግን ሀዘን እና ንዴት የተቀላቀለበት እንደሆነም በወቅቱ ተረድቶ
ነበር። ያም ቢሆን ግን ስለ ባሏ ውሽማ ምንም አይነት ነገር እንዳልነገረችው
አስታወሰ። በተጨማሪ ደግሞ ኒኪን ያገባ ወንድ ምንጎድሎበት ነው ሌላ ውሽማ የሚይዘው? ዊሊ ባደን ቫለንቲና ስላረጀችበት ሊሆን ይችላል ሌላ
ወጣት ሴት የወሸመው፡፡ ስለዚህም ጆንሰን ሆን ብሎ ነገሩን እንደፈጠረ
ገመተ፡፡
“ይህንን አንተ እንዴት አወቅክ?” ብሎ በቁጣ ድምፅ ጠየቀው፡፡
“በኢንተርኔት ላይ ተገልፆ ነበር፡፡” ብሎ ጆንሰን መለስ እና በመቀጠልም
“ወዲያው አደጋው እንደደረሰ ሳይሆን ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ነው። ታዲያ ዜናው ላይ የተገለፀው:: ከዶክተር ዳግላስ አጠገብ አንዲት ሴት ብቻ
ነበረች ብሎ ነው የዘገበው፡፡ እኔ ግን የዶውግን እና የኒኪን የቅርብ ጓደኞቻቸውን አግኝቼ በመጠየቅ እውነቱን ለማረጋገጥ በቃሁ። ይሄንን አስቀያሚ ሚስጥሯንም ደብቃናለች። ይህ ሚስጥሯም ነው እንግዲህ ከፍተኛ
ንዴት ውስጥ የሚከታት...”
“እሺ ባሏ እንደፈለገ እየማገጠ ነበር እንበል። ታዲያ ይህ ነገር ከሁለቱ
ግድያዎች ጋር ምን ያገናኘዋል?” ብሎ ብሩዲ ጆንሰንን ጠየቀው፡፡
“ጌታዬ እኔ በዚህ ዙሪያ ስላሉ ነገሮች በትንሹም ቢሆን ምርመራዎቼን
ለማድረግ ሞክሬ ነበር። ከሁለት ቀናት በፊት ስለ አደጋው የተደረገውን
ሪፖርትንም ለማየት ሞክሬ ነበር። በዚህም ስለ ዶክተር ዳግላስ እና ስለ
ሩስያዊት ውሽማው ለማወቅ የበኩሌን ጥረት ሳደርግ ነበር።”
ይሄኔም ጉድማን ከተቀመጠበት ፍንጥር ብሎ ተነሳ እና “ይሄን ነገር እኮ
አልነገርከኝም!” ብሎ በመጮጮህ ተቃውሞውን አሰማ፡፡
እንዴ አንተ ሥራ በዝቶብህ ነበር እኮ ታስታውሳለህ?” ብሎ ጆንሰን መለሰለት እና “በዚያ ላይ ደግሞ አንተው ራስህ እንዳወራህልኝ ግልፅ አልነበርክም። ለማንኛውም አታስብ ስለ አደጋው የቀረበ ሪፖርት አንድም የተመዘገበ ነገር አላገኘሁም”
“ምን ማለትህ ነው?” ብሎ ነገሩ እንቆቅልሽ የሆነበት አዛዥ ብሩዲ
ጥያቄውን አቀረበ፡፡
“አዎን ሲስተሙ ላይ አደጋው የተመዘገበ አንድም ሪፖርት የለም ወይንም አደጋው ጨርሶ አልተመዘገበም ወይንም ደግሞ የተመዘገበውን የሆነ ሰው ሰርዞታል” ብሎ ሲናገር አዛዥ ብሩዲ በስልቸታ ፊት ሲያየው ጊዜ ጆንስን ማብራሪያውን ቀጠለ። “ወደ ነጥቤ እየመጣሁ ነው አንዴ ታገሱኝ።ይሄ ደግሞ ነገሩን ይበልጥ እንድመረምረው ምክንያት ሆነኝ። አደጋው እንደደረሰ እንኳን እኔ ማንም ሰው ያውቀዋል። አደጋው በየጋዜጦቹ ላይ
በጊዜው ሲፃፍ ነበር፡፡ በተለይ ደግሞ ኤል.ኤ.ታይምስ ዶክተር ዳግላስ ምን
ያህል ትሁት እና ጨዋ ሰው እንደሆነ፣ ባሏ የሞተባትንም ዶክተር ኒኪንም
ምን ያህል የተጎዳች ቆንጆ መልከ መልካም አድርጎ ነበር ሲፅፍላቸው
ማንኛውም ጋዜጣ ወይንም መፅሄት ግን አብራው ስለሞተችው ሩስያዊት
አልገለፁም፡፡ የሩስያዊቷ ጉዳይ የወጣው ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ነበር።
ለማንኛውም ዶክተር ግላስ ቴስላ መኪናዋን የገዛበትን የመኪና መሸጫ
ቦታን ፈልጌ አገኘሁት:: እዚያም ደርሼ ከአደጋው በኋላ የመኪናውን
የኮምፒውተር ሲስተም የመረመረውን ኢንጅነር አግኝቼው ነበር። እሱ
እንደነገረኝም ከአደጋው በፊት የመኪናው የኮምፒውተር ሲስተም ተበላሽቶ
ነበር።
“ተበላሽቶ ነበር ማለት?”
“በሪሞት ኮንትሮል ሀክ ተደርጎ ነበር” አለ እና ጆንሰን ማብራሪያውን በመቀጠልም “በነገሩ በጣም እርግጠኛ ባይሆንም የመኪናው የኮምፒውተር ሲስተም ኮድ ተዛብቶ ስለነበረ ይሄ የኮድ መዛባት ደግሞ መኪናው የሆነ ፍጥነት ካለፈ በኋላ የፍጥነትና እና የፍሬን ሲስተሙ ተናብበው እንዳይሰሩ እንደሚያደርጋቸው ገምቶ ነበር፡፡ ይህንን ነገርም በወቅቱ ለአለቃው አመልክቶ ነበር። አለቃውም ነገሩን ለፖሊስ ሪፖርት እንዲያደርግም
አሳስቦት ነበር”
“እናስ ጉዳዩን ለፖሊስ አመለከተ አለቃው?” ብሩዲ ጠየቀ፡፡
“ቅድም እንደነገርኳችሁ ስለ አደጋው ሪፖርት የተመዘገበ ነገር የለም::
ስለዚህ የኢንጅነሩ አለቃ ጉዳዩን ለፖሊስ ያመልክት አያመልክት ለማወቅ አልቻልኩም፡፡ የኢንጅነር ዴመን አለቃም ባለፈው ፋሲካ በልብ በሽታ ህይወቱ አልፏል” አላቸው
ጆንስን ይህንን ከተናገረ በኋላ ጉድማን እና የፖሊስ አዛዥ ብሩዲ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
....ዋናው አዛዥ ብሩዲም ወደ ጉድማን ዞሮ “አንተም ማስታወሻዎቹን
አንብበህ ጨርሰሃል አይደል? እሺ በጆንሰን ሀሳብ ትስማማለህ?”
ጉድማንም የእግሮቹን ንብብሮሽ ስላልተመቸው ቀያየራቸው እና ዶክተር
ሮበርትስ ስለ በሽተኞቿ በማስታወሻዎቿ ላይ የፃፈቻቸውን ነገሮች በውስጡ
መከለስ ጀመረ።
ዶክተር ሮበርትስ ማስታወሻዎቹን ሌላ ሰው ያነባቸዋል ስላልገመተች ስለ በሽተኞቿ የተሰማትን ነገሮች ሁሉ ነው ማስታወሻዋ ላይ ያሰፈረችው። ይህንን ደግሞ ያደረገችው ምናልባት በሚቀጥለው የህክምና ጊዜያቸው ላይ በሽተኞቿን ስታገኛቸው ከግለሰባዊ ባህርያቸው በመነሳት ልትረዳቸው በማሰብ እንደሆነም ያምናል። ግን እዚህ ላይ ጆንሰን ለዶክተሯ ያለው ጥላቻ ወደዚህ አይነት ማጠቃለያ ላይ እንዲደርስ ሊያደርገው እንደሚችል እንዴት አላሰበውም? ይህንን በውስጡ ሲያውጠነጥን ቆየ እና
“መልካም ማስታወሻዎቹ ላይ ስለ ታካሚዎቿ ስነ ባህሪ ግምገማን (ፍርድን)
አካሂዳለች ብዬ አምናለሁ” ብሎ መለሰ፡፡
ይሄኔም ጆንሰን የሹፈት ሳቅ ሳቀበት እና ግምገማ አልክ? ሮበርትስ እኮ ይህቺ ሊዛ ፍላንገን የተባለችን ሴት ትጠላታለች። በማስታወሻዋ ላይ ሊዛ ፍላንገን የምትገልፃት ለድርጊቷ መጠየቅ እንዳለባት ማለትም በሌሎች ሴቶች (ሚስቶች) ላይ ለፈጠረችው ስቃይ መጠየቅ እንዳለባት ነው የማስታወሻዋ ዋነኛ ሀሳብ” አለ፡፡
“ዋነኛው ሀሳብ ደግሞ ምንድነው?” ብሎ አዛዡ ግራ ተጋብቶ ጠየቀው።
ሚኪ ሮበርትስ ውሽማ በሚሆኑ ሴቶች ላይ ሁሉ ቂም አላት” አለ ጆንስን፡፡
“እንዴ ይሄ እኮ ሃጢአቱን እሷ ላይ ማብዛት ነው።” ብሎ ጉድማን
ጣልቃ ገባ ።
“ይመስልሀል? እኔ ግን አይመስለኝም፡፡ ለማንኛውም ማስታወሻዋን
ካነበብኩኝ በኋላ ለምንድነው በሊዛ ፍላንገን ላይ ይህን ይህል ቅሬታ
ያደረባት? ብዬ ራሴን ጠየቅኩኝ” ብሎ ጆንሰን ማብራሪያውን በመቀጠልም
“በመጨረሻም ነገሩ ከሟች ባሏ ጋር በተገናኘ እንደሆነ ለማወቅ በቃሁ”
“ባሏ ሞቶ አይደል እንዴ?” ብሎ አዛዥ ብሩዲ ጉንጩን እያሸ ጠየቀ::
“ልክ ነው ባሏ ሞቷል። ዶክተር ዳግላስ ሮበርትስ ባለፈው ዓመት በ 405 ኛው ጎዳና ላይ የአደጋው ምክንያት ባልታወቀ የመኪና አደጋ ህይወቱን አጥቷል። ግን በወቅቱ መኪናው ውስጥ ከእሱ ጎን ማን እንደነበር እስቲ ገምቱ” አላቸው፡፡ ሁለቱም አዛዥ ብሩዲ እና ጉድማን ግምታቸውን ለማስቀመጥ በጥሩ ስሜት ውስጥ ስላልሆኑ ምላሹን እንዲሰጣቸው
እያፈጠጡበት ዝም አሉ።
“ውሽማው አብራው ነበረች!” ብሎ ጉድማን በመቀጠልም “የሆነች
ሩሲያዊ ሴትን ከጎኑ አስቀምጦ መኪናውን ሲያሽከረክር ነበር አደጋው የደረሰው። በአደጋው ሁለቱም ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡ ያን ዕለት ነበር ዶክተር ኒኪ ሮበርትስ ባሏ ከትዳር ውጪ ያለውን ግንኙነት ለመጀመሪያ ጊዜ ያወቀችው እንግዲህ”
የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች በአደጋው ከነደደ መኪና ውስጥ የሁለት ሰዎችን ሬሳ ሲያወጡ እሷ ምን ሊሰማት እንደሚችል አስቡት እስቲ! የውስጥ ህመሙን? ውርደቱን? ሁሉም ሰው እና እናንተም ጭምር ሁለቱ ምን ያህል የሚቀናበት ትዳር እንዳላቸው ታምኑ አልነበር?” ብሎ ጆንሰን ጉድማንን አገኘሁህ በሚል ስሜት ተመለከተው፡፡
ኒኪም ማታ ላይ ስለ ባሏ በግልፅ ነግራዋለች፡፡ ስለ ባሏ የተናገረችበት
መንገድ ግን ሀዘን እና ንዴት የተቀላቀለበት እንደሆነም በወቅቱ ተረድቶ
ነበር። ያም ቢሆን ግን ስለ ባሏ ውሽማ ምንም አይነት ነገር እንዳልነገረችው
አስታወሰ። በተጨማሪ ደግሞ ኒኪን ያገባ ወንድ ምንጎድሎበት ነው ሌላ ውሽማ የሚይዘው? ዊሊ ባደን ቫለንቲና ስላረጀችበት ሊሆን ይችላል ሌላ
ወጣት ሴት የወሸመው፡፡ ስለዚህም ጆንሰን ሆን ብሎ ነገሩን እንደፈጠረ
ገመተ፡፡
“ይህንን አንተ እንዴት አወቅክ?” ብሎ በቁጣ ድምፅ ጠየቀው፡፡
“በኢንተርኔት ላይ ተገልፆ ነበር፡፡” ብሎ ጆንሰን መለስ እና በመቀጠልም
“ወዲያው አደጋው እንደደረሰ ሳይሆን ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ነው። ታዲያ ዜናው ላይ የተገለፀው:: ከዶክተር ዳግላስ አጠገብ አንዲት ሴት ብቻ
ነበረች ብሎ ነው የዘገበው፡፡ እኔ ግን የዶውግን እና የኒኪን የቅርብ ጓደኞቻቸውን አግኝቼ በመጠየቅ እውነቱን ለማረጋገጥ በቃሁ። ይሄንን አስቀያሚ ሚስጥሯንም ደብቃናለች። ይህ ሚስጥሯም ነው እንግዲህ ከፍተኛ
ንዴት ውስጥ የሚከታት...”
“እሺ ባሏ እንደፈለገ እየማገጠ ነበር እንበል። ታዲያ ይህ ነገር ከሁለቱ
ግድያዎች ጋር ምን ያገናኘዋል?” ብሎ ብሩዲ ጆንሰንን ጠየቀው፡፡
“ጌታዬ እኔ በዚህ ዙሪያ ስላሉ ነገሮች በትንሹም ቢሆን ምርመራዎቼን
ለማድረግ ሞክሬ ነበር። ከሁለት ቀናት በፊት ስለ አደጋው የተደረገውን
ሪፖርትንም ለማየት ሞክሬ ነበር። በዚህም ስለ ዶክተር ዳግላስ እና ስለ
ሩስያዊት ውሽማው ለማወቅ የበኩሌን ጥረት ሳደርግ ነበር።”
ይሄኔም ጉድማን ከተቀመጠበት ፍንጥር ብሎ ተነሳ እና “ይሄን ነገር እኮ
አልነገርከኝም!” ብሎ በመጮጮህ ተቃውሞውን አሰማ፡፡
እንዴ አንተ ሥራ በዝቶብህ ነበር እኮ ታስታውሳለህ?” ብሎ ጆንሰን መለሰለት እና “በዚያ ላይ ደግሞ አንተው ራስህ እንዳወራህልኝ ግልፅ አልነበርክም። ለማንኛውም አታስብ ስለ አደጋው የቀረበ ሪፖርት አንድም የተመዘገበ ነገር አላገኘሁም”
“ምን ማለትህ ነው?” ብሎ ነገሩ እንቆቅልሽ የሆነበት አዛዥ ብሩዲ
ጥያቄውን አቀረበ፡፡
“አዎን ሲስተሙ ላይ አደጋው የተመዘገበ አንድም ሪፖርት የለም ወይንም አደጋው ጨርሶ አልተመዘገበም ወይንም ደግሞ የተመዘገበውን የሆነ ሰው ሰርዞታል” ብሎ ሲናገር አዛዥ ብሩዲ በስልቸታ ፊት ሲያየው ጊዜ ጆንስን ማብራሪያውን ቀጠለ። “ወደ ነጥቤ እየመጣሁ ነው አንዴ ታገሱኝ።ይሄ ደግሞ ነገሩን ይበልጥ እንድመረምረው ምክንያት ሆነኝ። አደጋው እንደደረሰ እንኳን እኔ ማንም ሰው ያውቀዋል። አደጋው በየጋዜጦቹ ላይ
በጊዜው ሲፃፍ ነበር፡፡ በተለይ ደግሞ ኤል.ኤ.ታይምስ ዶክተር ዳግላስ ምን
ያህል ትሁት እና ጨዋ ሰው እንደሆነ፣ ባሏ የሞተባትንም ዶክተር ኒኪንም
ምን ያህል የተጎዳች ቆንጆ መልከ መልካም አድርጎ ነበር ሲፅፍላቸው
ማንኛውም ጋዜጣ ወይንም መፅሄት ግን አብራው ስለሞተችው ሩስያዊት
አልገለፁም፡፡ የሩስያዊቷ ጉዳይ የወጣው ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ነበር።
ለማንኛውም ዶክተር ግላስ ቴስላ መኪናዋን የገዛበትን የመኪና መሸጫ
ቦታን ፈልጌ አገኘሁት:: እዚያም ደርሼ ከአደጋው በኋላ የመኪናውን
የኮምፒውተር ሲስተም የመረመረውን ኢንጅነር አግኝቼው ነበር። እሱ
እንደነገረኝም ከአደጋው በፊት የመኪናው የኮምፒውተር ሲስተም ተበላሽቶ
ነበር።
“ተበላሽቶ ነበር ማለት?”
“በሪሞት ኮንትሮል ሀክ ተደርጎ ነበር” አለ እና ጆንሰን ማብራሪያውን በመቀጠልም “በነገሩ በጣም እርግጠኛ ባይሆንም የመኪናው የኮምፒውተር ሲስተም ኮድ ተዛብቶ ስለነበረ ይሄ የኮድ መዛባት ደግሞ መኪናው የሆነ ፍጥነት ካለፈ በኋላ የፍጥነትና እና የፍሬን ሲስተሙ ተናብበው እንዳይሰሩ እንደሚያደርጋቸው ገምቶ ነበር፡፡ ይህንን ነገርም በወቅቱ ለአለቃው አመልክቶ ነበር። አለቃውም ነገሩን ለፖሊስ ሪፖርት እንዲያደርግም
አሳስቦት ነበር”
“እናስ ጉዳዩን ለፖሊስ አመለከተ አለቃው?” ብሩዲ ጠየቀ፡፡
“ቅድም እንደነገርኳችሁ ስለ አደጋው ሪፖርት የተመዘገበ ነገር የለም::
ስለዚህ የኢንጅነሩ አለቃ ጉዳዩን ለፖሊስ ያመልክት አያመልክት ለማወቅ አልቻልኩም፡፡ የኢንጅነር ዴመን አለቃም ባለፈው ፋሲካ በልብ በሽታ ህይወቱ አልፏል” አላቸው
ጆንስን ይህንን ከተናገረ በኋላ ጉድማን እና የፖሊስ አዛዥ ብሩዲ
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....ቱሉ ሀጤ የተከናነበችውን የጨለማ ካባ አውልቃ ወደዚያ ለመጣል
በመሽኮርመም ላይ ትገኛለች። ጨለማው ብርታቱን ለማሳየት በሚያቅራራበት፣ ንጋትም ብርሃንን ካልፈነጠቅሁ እያለ በሚንጠራራበት በዚያ ውድቅት ለሊት እንቅልፍ በአይኑ አልዞርልህ ያለው ሰው አንዴ በቀኝ ጎኑ አንዴ ደግሞ በግራ ጎኑ እየተገላበጠ ምሽትና ንጋት የበላይነታት
ውን ለማረጋገጥ በገጠሙት የጦርነት አውድማ ላይ ትጥቅ ይዞ ሳይዋጋ
ጉዳት የደረስበት ቁስለኛ ሆኖ ያለዕረፍት ያቃስታል። ድቅድቁ ጨለማ ከዋጣት መንደር የበለጠ የጨለመበት ሙሉ ዳፍንት ሌሊት ሆኖበት ያደረውና ከሚስቱ ፀባይ መለዋወጥ ጋር ሰሞኑን ከህሊናው ጋር ጦርነት ገጥሞ የሰነበተው ገበየው ቱሉ ሃጤ ለበለችውጨለማ በከፋ ሁኔታ
ጨልሞበት ዙሪያው ገደል ሆኖበት በሃሳብና በጭንቀት መወራጨቱን ቀጥሏል...
ባክዎ እማማ ዓለም ፀባይዋን ለምን እንደለወጠችብኝ ይጠይቁልኝ፡፡ ሳላውቀው አስቀይሜአት ከሆነ ይቅርታ ታድርግልኝ፡፡ በድያት ከሆነ እክሳለሁ እንጂ የድሮዋ ዓለሚቱ አልሆነችልኝም” ብሎ ለአማቹ ስሞታ ነግሮ ነበር።
የዓለሚቱ እናት ልጃቸውን በጣም ስለሚወዷትና ስለሚፈሯትም ጭምር
ጣጣውን በልባቸው እያወቁት “እስቲ ቀስ ብለን እንጠይቃታለን ካጠፋች
እናስመክራታለን ጥፋቱ ያንተ ከሆነ ደግሞ ጥፋትህን እንድታርም ሽማግሌ
ፊት እናወቃቅሳችኋለን እስከዚያው ድረስ ታገሳት” ሲሉ ተስፋ ስጥተውት ነበረ፡፡ እሱም ያንን የተስፋ ቃል ስንቆ ሽማግሌ ተሰብስቦ አንተ አጥፍተሀል አንቺ አጥፍተሻል እየተባባሉ የሚወቃቀሱበትን ቀን በናፍቆት እየተጠባበቀ ነው። ዓለሚቱ ግን እየባሰባት እንጂ እየበረደች ልትሄድ
አልቻለችም፡፡ በተለይ የዛሬው ሁኔታዋ ከወትሮው በተለዬ ሁኔታ እጅግ
አስፈሪ ሆነበት።ያ የሚለሰልሰው ገላዋ እንደ አባጨጓሬ ኮሰኮሰው። ጀርባዋን አዞረችበት። ሊዳብሳት ሲፈልጋት ሽሽችው። እጁን ሲዘረጋ አመናጨቀችው። ኤጭ!.. በልቡ ብዙ ነገር ተመኘ፡፡ “ምን አባቱ ለየትኛው ኑሮ ነው? ብርር ብዬ ብጠፋስ? ዐይኔን ማየት ካስጠላት እስከ መጨረሻው ከዐይኗ ብርቅላትስ?” ዝም ብሎ ወደማያውቀው አገር ቢሄድ ዓለሚቱን ሸሽቶ ከአድማስ እስከ አድማስ ቢጓዝ ከዚያም ናፍቆቱ አንገብግቧት
ጥፋተኛነቷ ተሰምቷት እንደ ድሮው “ገበየሁዬ” እያለች እሱን ለማግኘት
እግሯ እስከሚነቃ ድረስ ፍለጋ ብትጓዝ ተመኘ፡፡ አገሩን ጥሉ መንኖ ገዳም ቢገባ፣ የቤተክርስቲያን አገልጋይ ባህታዊ ሆኖ ጢሙን አሳድጎ ስለ ነፍሱ እንጂ ስለ ስጋው የማይጨነቅ መነኩሴ ሆኖ መኖርን ተመኘ፡፡
በዚች በማትጠገብና ነገር ግን በማትጣፍጥ ዓለም ውስጥ ምሬቷን እየተጎነጨ ከመኖር ይልቅ ምናኔን መረጠ፡፡ ግማሽ አካሉ፣ የመኖሩ አለኝታ
ጣፋጫ ዓለሚቱ ጀርባዋን ከሰጠችው ገሀዷ ዓለምም አልፈለገችውምና
ገሀዷ አለም ጠላት፡፡ በእርሻ ሲተዳደር ድካሙ ልፋቱ ሁሉ በዓለሚቱ
ፍቅር ይካካስለት ነበር፡፡ አሁን ግን እሷም ይኸውና ጀርባዋን ሰጥታዋለች፡፡ ለወትሮው ዓለምዬ እባክሽ ትንሽ ይንጋ አትነሺ ትንሽ እንቆይ?"እያላ ከእቅፉ ውስጥ እንዳትወጣ ጭምቅ አድርጎ ሲይዛት እሷም ከጉያው ውስጥ ላለመውጣት በልቧ እየተመኘች የውሽቷን ስትታገለው ለሊቱ ይነጋና ምቀኛው ዶሮ ኩኩሉ!” ኸረ እባካችሁ ነግቷል!” ሲል ያሳብቃል። ከዚያም እሷ ቀድማ ትነሳና ቤቱን ታጫጭስበታለች። ከብቶቹን ለግጦሽ ከማሰማራቱ በፊት ሻይ ታፈላለትና “እስኪ ሞቅ ያድርግህ ገበየሁዬ?” ትለዋለች። ይቺ ለሱ ማር የነበረች ዓለሚቱ፣የሱ አሳቢ ተንከባካቢ የነበረች ዓለሚቱ ፊቷ እንደ ሀምሌ ክረምት መክበድ፣ ሙቅ ሰውነቷ
እንደ በረዶ መቀዝቀዘ ከጀመረና ንግግሯ እንደ ሬት እየመረረ መምጣት ከጀመረ ውሎ አደረ። ሁሉንም መታገሴ ጥፋተኛነቴን ያመንኩ ያስመስልብኛል በማለት ትንሽ ለመቆጣት የሞከረ ቀን ፀቡ ይበልጥ እየተካረረ ይሄዳል። ከዚያም ይደነግጥና ተመልሶ ልምምጡን ይቀጥላል። አንዳንድ ጊዜ ንዴቱ ከኣቅሙ በላይ ይሆንበትና ብድግ ብሎ ቤቱን ጥሎላት ሊጠፋ ይከጅለዋል፡፡ በዚህ ጊዜ ደግሞ እነኝያ በግራና በቀኝ ከበውት ለሀጫቸውን የሚያዝረከርኩበት፣እነኝያ ልቡ ሊጋልብ ሲነሳ ልጓም የሚሆኑበት፣ እነኝያ ልቡ ሲቃጠል ውሃ የሚያፈሱበት ህፃናት ልጆቹ ትውስ ይሉትና ጥሏቸው ለመጥፋት በማሰቡ ራሱን ይወቅሳል።
የዛሬን አያድርገውና ያኔ እንደዚህ እንደ አሁኑ ከሁለትነት ወደ አራትነት ከመሸጋገራቸው በፊት“ዓለምዬ ፍቅራችን እጥፍ ድርብ የሚሆንበት ጊዜ መቼ
ነው?” ብሎ ሲጠይቃት ከፍተኛ የልጅ ጉጉትና ምኞት እንዳለው የምታውቀው ዓለሚቱ በስርጉድ ጉንጮቿ ሳቅ ትልለትና ያበጠ ሆዷን በጣቷ እየጠቆመችው “የማሙሽዬ ወይንም የማሚቱ እናት ስሆን።አንተም የአባትነት ወግ ማዕረግ ሲደርስህ አይደል ገበየሁ?” ትልና ጉንጩን ከንፈሩን ሳም ስታደርገው ደስታ ልቡን ይሞላውና ደግሞ እንደገና አንጠጋ
ገብ ብለው ተቃቅፈው ሲተሻሹ ሲላላሱ በልቧ ማህደር ውስጥ የተደበቀውን የፍቅር ሚስጢር ከዐይኖቿ ውስጥ እንደሚያነብባት ሁሉ ዐይን ዐይኖቿን በፍቅር ትኩር ብሎ ሲመለከታት እንደማፈር ትልና አንገቱ ስር ሽጉጥ ስትልበት ከዚያም ስሜታቸው በእጥፍ ይንርና እንደ ስስት እንጀራ እርስ በርስ መሻማት ሲጀምሩ ይሄ ሁሉ በወረት እንደ ባህር ዛፍ ቅጠል ቦግ ብሎ ወዲያውኑ ድርግም ብሎ የጠፋ ሳይሆን ሰባት ዓመት ሙሉ አብሮአቸው የዘለቀ ነበር፡፡ አሁን ግን ይሄ ሁሉ እንዳልነበረ ሆኖ ከጥቂት ወራት ወዲህ የዓለሚቱ ሙሉ ለሙሉ መለወጥ አእምሮውን ሲበጠብጠው ከረመ፡፡ አለሚቱ ግን ይሄ ሁሉ ገበየሁ የሚታወሰው ትዝታ አንድ
እንኳ ለምልክት ሳይተርፍ ከአእምሮዋ ሙሉ በሙሉ ጠፍቶ የሠራ አካላቷን እንደ ሻማ ለሚያቀልጣት፣ በፍቅር ለተረታችለት፣ ቁመናው ቀጥ ያለ ሽመል ለሚመስለውና በአለንጋ መሳይ ጣቶቹ ሁለመናዋን እያሻሽ ነፍሷን ለሚያስደስትላት ለጎንቻ ፍቅር ስትል የገበየሁ ህይወት ኢምንት ሆኖ ታያት። በተለይ ደግሞ ከጥቂት ጊዜ በኋላ አጠገቧ የተኛው ሰው ቀዝቃዛ በድን እንደሚሆን እየታወቃት እየፈራችው ሰውነቷን ሲነካት እየተሸማቀቀች ከምንጊዜውም በከፋ ሁኔታ ተጠየፈችው። ሸሸችው።ገበየሁ የሆዱን በሆዱ ችሎ የለሊት አዳሩ እየደነቀው ጋቢውን ከላይ ደረበና ቀስ ብሎ ተነሳ፡፡ ዓለሚቱን የያዛት እንቅልፍ የውሽት መሆኑን ሳያውቅ እንዳይቀሰቅሳት ተጠንቅቆ ከአልጋው ላይ ወረደና እንደወትሮው ከብቶቹ ከመታለባቸው በፊት ትንሽ ሳር እንዲግጡ በለሊቱ በረቱን ከፍቶ ይዟቸው ወጣ....
ሰው ከእናቱ ማህፀን ሲወለድ ተረግዞ፣
በሞት ጎዳና ላይ ይጀምራል ጉዞ፡፡
ፊት ለፊት እያየው ትልቁን አደጋ፣
ልቡ ሲያፈገፍግ ዕድሜው ግን ሲጠጋ፣
ሲያውቀው በመሞቱ በጣም ይጨነቃል፣
መሸሻ በማጣት ቆሞ ይጠብቃል፣
የእግዚአብሔርን ፀጋ!
በዕድሜ ባለፀጋነት በማይቀረው የሞት ጎዳና ላይ መጓዝ የተፈጥሮ ህግ ነው። ነገር ግን ወደ ህይወት ጎዳና ለመጓዝ የህይወትን ውጣ ውረድ ፈተና ለማለፍ በሚደረግ ትንቅንቅ ውስጥ ባልተጠበቀ ጊዜ በተለይም እንደ ገበየሁ ላለ ልጆቹን ስሞ ላልጠገበ ሰው ሞት እጅግ አስደንጋጭ ነው። ገበየሁ ከዛሬ ነገ የሚስቱ ፀባይ ተሻሽሉ የሻከረው ልቧ ለስልሶ እርቀ ሰላም በመካከላቸው ወርዶ ትዳሩ ሰምሮ ልጆቻቸውን በፍቅር
የሚያሳድጉበትን ቀን ሲናፍቅ በዚያኛው ወገን ደግሞ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ይቺን ዓለም እንዲስናበታት የማድረግ እቅድ ወጥቶ ዝግጅቱ ተጠናቆ ወደተግባር የሚሽጋገርበት የሞት ድግስ ተደግሶለታል። እሱ በተበደለ እሱ ከነልጆቹ በተሰቃየ እሱ ፍቅሩን በተነጠቀ ጎንቻና አለሚቱ የሞት ፍርድ ከፈረዱበት ስንብተዋል። በዚሁ መሰረት ጎንቻ ሲዘጋጅ
ሾተሉን ሲሞርድ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....ቱሉ ሀጤ የተከናነበችውን የጨለማ ካባ አውልቃ ወደዚያ ለመጣል
በመሽኮርመም ላይ ትገኛለች። ጨለማው ብርታቱን ለማሳየት በሚያቅራራበት፣ ንጋትም ብርሃንን ካልፈነጠቅሁ እያለ በሚንጠራራበት በዚያ ውድቅት ለሊት እንቅልፍ በአይኑ አልዞርልህ ያለው ሰው አንዴ በቀኝ ጎኑ አንዴ ደግሞ በግራ ጎኑ እየተገላበጠ ምሽትና ንጋት የበላይነታት
ውን ለማረጋገጥ በገጠሙት የጦርነት አውድማ ላይ ትጥቅ ይዞ ሳይዋጋ
ጉዳት የደረስበት ቁስለኛ ሆኖ ያለዕረፍት ያቃስታል። ድቅድቁ ጨለማ ከዋጣት መንደር የበለጠ የጨለመበት ሙሉ ዳፍንት ሌሊት ሆኖበት ያደረውና ከሚስቱ ፀባይ መለዋወጥ ጋር ሰሞኑን ከህሊናው ጋር ጦርነት ገጥሞ የሰነበተው ገበየው ቱሉ ሃጤ ለበለችውጨለማ በከፋ ሁኔታ
ጨልሞበት ዙሪያው ገደል ሆኖበት በሃሳብና በጭንቀት መወራጨቱን ቀጥሏል...
ባክዎ እማማ ዓለም ፀባይዋን ለምን እንደለወጠችብኝ ይጠይቁልኝ፡፡ ሳላውቀው አስቀይሜአት ከሆነ ይቅርታ ታድርግልኝ፡፡ በድያት ከሆነ እክሳለሁ እንጂ የድሮዋ ዓለሚቱ አልሆነችልኝም” ብሎ ለአማቹ ስሞታ ነግሮ ነበር።
የዓለሚቱ እናት ልጃቸውን በጣም ስለሚወዷትና ስለሚፈሯትም ጭምር
ጣጣውን በልባቸው እያወቁት “እስቲ ቀስ ብለን እንጠይቃታለን ካጠፋች
እናስመክራታለን ጥፋቱ ያንተ ከሆነ ደግሞ ጥፋትህን እንድታርም ሽማግሌ
ፊት እናወቃቅሳችኋለን እስከዚያው ድረስ ታገሳት” ሲሉ ተስፋ ስጥተውት ነበረ፡፡ እሱም ያንን የተስፋ ቃል ስንቆ ሽማግሌ ተሰብስቦ አንተ አጥፍተሀል አንቺ አጥፍተሻል እየተባባሉ የሚወቃቀሱበትን ቀን በናፍቆት እየተጠባበቀ ነው። ዓለሚቱ ግን እየባሰባት እንጂ እየበረደች ልትሄድ
አልቻለችም፡፡ በተለይ የዛሬው ሁኔታዋ ከወትሮው በተለዬ ሁኔታ እጅግ
አስፈሪ ሆነበት።ያ የሚለሰልሰው ገላዋ እንደ አባጨጓሬ ኮሰኮሰው። ጀርባዋን አዞረችበት። ሊዳብሳት ሲፈልጋት ሽሽችው። እጁን ሲዘረጋ አመናጨቀችው። ኤጭ!.. በልቡ ብዙ ነገር ተመኘ፡፡ “ምን አባቱ ለየትኛው ኑሮ ነው? ብርር ብዬ ብጠፋስ? ዐይኔን ማየት ካስጠላት እስከ መጨረሻው ከዐይኗ ብርቅላትስ?” ዝም ብሎ ወደማያውቀው አገር ቢሄድ ዓለሚቱን ሸሽቶ ከአድማስ እስከ አድማስ ቢጓዝ ከዚያም ናፍቆቱ አንገብግቧት
ጥፋተኛነቷ ተሰምቷት እንደ ድሮው “ገበየሁዬ” እያለች እሱን ለማግኘት
እግሯ እስከሚነቃ ድረስ ፍለጋ ብትጓዝ ተመኘ፡፡ አገሩን ጥሉ መንኖ ገዳም ቢገባ፣ የቤተክርስቲያን አገልጋይ ባህታዊ ሆኖ ጢሙን አሳድጎ ስለ ነፍሱ እንጂ ስለ ስጋው የማይጨነቅ መነኩሴ ሆኖ መኖርን ተመኘ፡፡
በዚች በማትጠገብና ነገር ግን በማትጣፍጥ ዓለም ውስጥ ምሬቷን እየተጎነጨ ከመኖር ይልቅ ምናኔን መረጠ፡፡ ግማሽ አካሉ፣ የመኖሩ አለኝታ
ጣፋጫ ዓለሚቱ ጀርባዋን ከሰጠችው ገሀዷ ዓለምም አልፈለገችውምና
ገሀዷ አለም ጠላት፡፡ በእርሻ ሲተዳደር ድካሙ ልፋቱ ሁሉ በዓለሚቱ
ፍቅር ይካካስለት ነበር፡፡ አሁን ግን እሷም ይኸውና ጀርባዋን ሰጥታዋለች፡፡ ለወትሮው ዓለምዬ እባክሽ ትንሽ ይንጋ አትነሺ ትንሽ እንቆይ?"እያላ ከእቅፉ ውስጥ እንዳትወጣ ጭምቅ አድርጎ ሲይዛት እሷም ከጉያው ውስጥ ላለመውጣት በልቧ እየተመኘች የውሽቷን ስትታገለው ለሊቱ ይነጋና ምቀኛው ዶሮ ኩኩሉ!” ኸረ እባካችሁ ነግቷል!” ሲል ያሳብቃል። ከዚያም እሷ ቀድማ ትነሳና ቤቱን ታጫጭስበታለች። ከብቶቹን ለግጦሽ ከማሰማራቱ በፊት ሻይ ታፈላለትና “እስኪ ሞቅ ያድርግህ ገበየሁዬ?” ትለዋለች። ይቺ ለሱ ማር የነበረች ዓለሚቱ፣የሱ አሳቢ ተንከባካቢ የነበረች ዓለሚቱ ፊቷ እንደ ሀምሌ ክረምት መክበድ፣ ሙቅ ሰውነቷ
እንደ በረዶ መቀዝቀዘ ከጀመረና ንግግሯ እንደ ሬት እየመረረ መምጣት ከጀመረ ውሎ አደረ። ሁሉንም መታገሴ ጥፋተኛነቴን ያመንኩ ያስመስልብኛል በማለት ትንሽ ለመቆጣት የሞከረ ቀን ፀቡ ይበልጥ እየተካረረ ይሄዳል። ከዚያም ይደነግጥና ተመልሶ ልምምጡን ይቀጥላል። አንዳንድ ጊዜ ንዴቱ ከኣቅሙ በላይ ይሆንበትና ብድግ ብሎ ቤቱን ጥሎላት ሊጠፋ ይከጅለዋል፡፡ በዚህ ጊዜ ደግሞ እነኝያ በግራና በቀኝ ከበውት ለሀጫቸውን የሚያዝረከርኩበት፣እነኝያ ልቡ ሊጋልብ ሲነሳ ልጓም የሚሆኑበት፣ እነኝያ ልቡ ሲቃጠል ውሃ የሚያፈሱበት ህፃናት ልጆቹ ትውስ ይሉትና ጥሏቸው ለመጥፋት በማሰቡ ራሱን ይወቅሳል።
የዛሬን አያድርገውና ያኔ እንደዚህ እንደ አሁኑ ከሁለትነት ወደ አራትነት ከመሸጋገራቸው በፊት“ዓለምዬ ፍቅራችን እጥፍ ድርብ የሚሆንበት ጊዜ መቼ
ነው?” ብሎ ሲጠይቃት ከፍተኛ የልጅ ጉጉትና ምኞት እንዳለው የምታውቀው ዓለሚቱ በስርጉድ ጉንጮቿ ሳቅ ትልለትና ያበጠ ሆዷን በጣቷ እየጠቆመችው “የማሙሽዬ ወይንም የማሚቱ እናት ስሆን።አንተም የአባትነት ወግ ማዕረግ ሲደርስህ አይደል ገበየሁ?” ትልና ጉንጩን ከንፈሩን ሳም ስታደርገው ደስታ ልቡን ይሞላውና ደግሞ እንደገና አንጠጋ
ገብ ብለው ተቃቅፈው ሲተሻሹ ሲላላሱ በልቧ ማህደር ውስጥ የተደበቀውን የፍቅር ሚስጢር ከዐይኖቿ ውስጥ እንደሚያነብባት ሁሉ ዐይን ዐይኖቿን በፍቅር ትኩር ብሎ ሲመለከታት እንደማፈር ትልና አንገቱ ስር ሽጉጥ ስትልበት ከዚያም ስሜታቸው በእጥፍ ይንርና እንደ ስስት እንጀራ እርስ በርስ መሻማት ሲጀምሩ ይሄ ሁሉ በወረት እንደ ባህር ዛፍ ቅጠል ቦግ ብሎ ወዲያውኑ ድርግም ብሎ የጠፋ ሳይሆን ሰባት ዓመት ሙሉ አብሮአቸው የዘለቀ ነበር፡፡ አሁን ግን ይሄ ሁሉ እንዳልነበረ ሆኖ ከጥቂት ወራት ወዲህ የዓለሚቱ ሙሉ ለሙሉ መለወጥ አእምሮውን ሲበጠብጠው ከረመ፡፡ አለሚቱ ግን ይሄ ሁሉ ገበየሁ የሚታወሰው ትዝታ አንድ
እንኳ ለምልክት ሳይተርፍ ከአእምሮዋ ሙሉ በሙሉ ጠፍቶ የሠራ አካላቷን እንደ ሻማ ለሚያቀልጣት፣ በፍቅር ለተረታችለት፣ ቁመናው ቀጥ ያለ ሽመል ለሚመስለውና በአለንጋ መሳይ ጣቶቹ ሁለመናዋን እያሻሽ ነፍሷን ለሚያስደስትላት ለጎንቻ ፍቅር ስትል የገበየሁ ህይወት ኢምንት ሆኖ ታያት። በተለይ ደግሞ ከጥቂት ጊዜ በኋላ አጠገቧ የተኛው ሰው ቀዝቃዛ በድን እንደሚሆን እየታወቃት እየፈራችው ሰውነቷን ሲነካት እየተሸማቀቀች ከምንጊዜውም በከፋ ሁኔታ ተጠየፈችው። ሸሸችው።ገበየሁ የሆዱን በሆዱ ችሎ የለሊት አዳሩ እየደነቀው ጋቢውን ከላይ ደረበና ቀስ ብሎ ተነሳ፡፡ ዓለሚቱን የያዛት እንቅልፍ የውሽት መሆኑን ሳያውቅ እንዳይቀሰቅሳት ተጠንቅቆ ከአልጋው ላይ ወረደና እንደወትሮው ከብቶቹ ከመታለባቸው በፊት ትንሽ ሳር እንዲግጡ በለሊቱ በረቱን ከፍቶ ይዟቸው ወጣ....
ሰው ከእናቱ ማህፀን ሲወለድ ተረግዞ፣
በሞት ጎዳና ላይ ይጀምራል ጉዞ፡፡
ፊት ለፊት እያየው ትልቁን አደጋ፣
ልቡ ሲያፈገፍግ ዕድሜው ግን ሲጠጋ፣
ሲያውቀው በመሞቱ በጣም ይጨነቃል፣
መሸሻ በማጣት ቆሞ ይጠብቃል፣
የእግዚአብሔርን ፀጋ!
በዕድሜ ባለፀጋነት በማይቀረው የሞት ጎዳና ላይ መጓዝ የተፈጥሮ ህግ ነው። ነገር ግን ወደ ህይወት ጎዳና ለመጓዝ የህይወትን ውጣ ውረድ ፈተና ለማለፍ በሚደረግ ትንቅንቅ ውስጥ ባልተጠበቀ ጊዜ በተለይም እንደ ገበየሁ ላለ ልጆቹን ስሞ ላልጠገበ ሰው ሞት እጅግ አስደንጋጭ ነው። ገበየሁ ከዛሬ ነገ የሚስቱ ፀባይ ተሻሽሉ የሻከረው ልቧ ለስልሶ እርቀ ሰላም በመካከላቸው ወርዶ ትዳሩ ሰምሮ ልጆቻቸውን በፍቅር
የሚያሳድጉበትን ቀን ሲናፍቅ በዚያኛው ወገን ደግሞ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ይቺን ዓለም እንዲስናበታት የማድረግ እቅድ ወጥቶ ዝግጅቱ ተጠናቆ ወደተግባር የሚሽጋገርበት የሞት ድግስ ተደግሶለታል። እሱ በተበደለ እሱ ከነልጆቹ በተሰቃየ እሱ ፍቅሩን በተነጠቀ ጎንቻና አለሚቱ የሞት ፍርድ ከፈረዱበት ስንብተዋል። በዚሁ መሰረት ጎንቻ ሲዘጋጅ
ሾተሉን ሲሞርድ
#ያልታበሱ_እንባዎች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...«ምነው ሔዩ በር ላይ ቆምሽ?» ሲል ጠየቃት።
«ብዙ ስለቆየሁ ወደ ቤቴ ልሄድ ተነስቼ ነው፡፡ አለችው በእጆቿ ደረቱን እየደባበሰችና ቀና ብላ ዓይኖቹን በዓይኖቿ እየተመለከተች፡፡
«ለሔዩ ምን አደረግሽላት ትርፌ?» አለ እስቻለው ወደ ትርፌ ዞር ብሎ፡፡
«ምንም ጋሼ አስቻለው፤ ወሬ ብቻ»
«ምሳ በልተሽ ሂጂያ ሔዩ!!»
«በፍጹም አስቹ! እት አበባ ስራ መምጫዋ ስለሆነ ብሄድ ይሻላል»
«ስሞት»
«አይሆንም አስቹ በአጋጣሚ መገኛኘታችን በራሱ በቂ ነው፡፡»
አስቻለው አሁንም ከንፈሮቿን ሳም ካደረገ በኃላ «በይ እሺ ከቸኮልሽ»
ሂጂ አለና እስከ ውጭ በር ሸኝቶ ተሰናብቷት ወደ ቤቱ ተመልሶ ገባ፡፡
አልጋው ላይ ቁጭ አለና ያነ በእጁ ይዞት የነበረውን ካኪ ፖስታ በጥድፊያ ይከፍት ጀመር፡፡ ከአሜሪካ ካሊፎርኒያ ግዛት ከዶክተር ደጀኔ አድማሱ የተላክለት ደብዳቤ ነው። አስቻለው ጫማውን አውልቆ አልጋው ላይ ወጣና ትራሶቹን አነባብሮ ከአንገቱ ቀና ብሎ በጀርባው ጋለል በማለት ደብዳቤውን ማንበብ ጀመረ።
«የምወድህና የማከብርህ እንዲሁም የምናፍቅህ ውድ ወንድሜ ነርስ አስቻለው ፍስሃ፥ ከቶ ለጤናህ እንደምን አለህ? ፈጣሪ አምላክ ይመስገን እኔ በጣም ደህና ነኝ።
«የምወድህ አስቻለው፡ የመኪና አደጋ ደርሶብህ እንደነበር አውቃለሁ፡፡ አደጋው ቀደረሰ
በሶስተኛ ቀን በተኛህበት ሆስፒታል ተገኝቼ ልጠይቅህም ሞክሪ ነበር። በወቅቱ ራስህን አታውቅም ነበርና፡ እኔ ደግሞ የበረራ ፕርግራሜ በማግስቱ
ስለነበር ሆዴ እያዘነ ትቼህ ሄጃለሁ። ይሁንና የኢትዮጵያ አየር ክልል ወጥቼ፣ በሱዳንና በግብጽ እንዲሁም በሜድትራኒያን ባህር፡ ከዚያም በአውሮጳ ሰማይ ላይ
ተንሳፍፌ በበረራ ላይ በነበርኩበት ጊዜ ሁሉ ስለ አንተ እያለቀስኩ ነበር፡፡ አሜሪካም ከገባሁ በኋላ የአንተ ነገር ከእዕምርዩ አልወጣ ብሎኝ ለቀናት ያህል ተሰቃይቻለሁ። የኋላ ኋላ ግን ከአደጋው ሙሉ በሙሉ አገግመህ ወደ ስራህ የመመለስህን ዜና
ስስማ አምላኬን ከልብ አመስግኛለሁ። ወደፊትም ፈጣሪህ ከሁሉም ነገር
እንዲጠብቅህ እፀልያለሁ።
«ውድ ወንድሜ አስቻለሁ። መቸም ደብዳቤዬ እንደ ደረሰህ መጀመሪያ የሚታሰብህ ምን ዓይነት ኑሮ እየኖርኩ ስለመሆኔ የምገልጽልህ ነገር ይመስለኛል።
መሰደዴ የመከፋት ውጤት ነውና አሜሪካ ውስጥ ምን ያሆሎ እንደደላኝ ወይም እንዳልደላኝ ለማውቅ ትጓጓ ይሆናል። በኔ በኩል 'ደላኝ' ወይም 'ከፋኝ'ብዬ
ልነግርህ አልፈልግም፡፡ አኗኗሬን ልግለጽልህና ምደባውን ራስህ ፈርጀው፡፡
«የአሜሪካ ውስጥ በእየዕለቱ ያገኘሁትን ሁሉ ስሰራ እውላለሁ። ስራዬን ሳጠናቅቅ ለስራው የተመደበው ገንዘብ በሙሉ ይከፈለኛል። ዛሬ አንዱ ጋር ስስራ
ውዩ ነገ ወደ ሌላው ብሄድ መልቂያ አልጠየቅም፡፡ በስራ ዘመቻ ሰበብ የጉልበቴን
ዋጋ ማንም አይነጥቀኝም፡፡ በስላም ስሰራ ውዬ የሰላም እንቅልፍ እተኛለሁ። «እገሌ
ስለኔ ምን ይላል? ነገ ምን ያደርገኝ ወይም ያስደርገኝ ይሆን? ብዬ አልጨነቅም፡፡
በሰራሁት መጠን ትክክለኛ ክፍያ ስለምቀበል የገንዘብ ችግር አይገባኝም። የልደታ ዕለት ደሞዝ ወስጄ እስከ ቀጣዩ ልደታ ቀቃኝ አልበቃኝ ብዬ ስጨነቅ አልሰነብትም፡፡
እለታዊ አዋዋሌና የሆዴ ነገር ይህን ይመስላል፡፡ የመንፈስህስ ነገር ካልከኝ ግን ጣጣው ብዙ ነው። በመሰረቱ ማንም ሰው በሀገሩ ውስጥ ተከፍቶ በተሰደደበት አገር ደስ ይለዋል ማለት ዘበት ነው ምናልባት 'ከመሞት መሰንበት' ለሚለው
የሃገራችን ብሂል ምላሽ ይሆን እንደሆን እንጂ። ስደት ደግሞ
የመንፈስ ርሃብ ውጤት ነው።
መንፈሱ የተራበ ሰው የቱንም ያህል የጣፈጠና የበዛ ምግበ ቢበላ ሁልጌዜም ውስጡ ባዶ ነው እኔም እንዲሁ ባዶዬን እኖራለሁ።
«አሜሪካ ደግሞ የጭፍን ፖለቲካል ሰለባ ሆነውለተሰደዱባት ሁሉ የባሰ የመንፈስ ረሃብ የምትለቅ ሃገር ነች፡፡ የዚች ደብዳቢየም ዋንኛ ይዘት በዚሁ ዙሪያ የሚያጠነጥን ነውና በፅሞና አንብብልኝ። በዚያው ውስጤንም ትረዳዋለህ።
«አየህ አስቻለው አሜሪካኖች ወደ ስልጣን ሲወጡ መንገዳቸው በህዝብ መሀል ነው። ለስልጣን የሚደረግ ትልቅ ጦርነት አለ። መሳሪያው ግን መድፍና
መትረየስ አይደለም የጠራና የነጠረ ሀሳብ' በሩቅ የሚታይ ራዕይ ከራእዕዩ ጫፍ
የሚደርስ የፖለቲካ አመለካከትና አሰራር ቅደም ተከተል ወይም ፕሮግራዎ" እንጂ።ባሩዳቸው የሰላ ምላስና ርቱዕ አንደበት ነው የጦርነቱ ቦታ ክብ ጠረጴዛ ነው።
የውጊያ ወረዳዎች እልፍ አእላፍን የሚይዙ ሰፋፊ አዳራሾች ናቸው
በዚህ የትግል ሜዳ አሸንፎ ስልጣን ላይ የወጣ ሁሉ ስራውን የሚያከናውነው በሕዝብ
ይሁንታ በፀደቀ ህገ መንግስት መሰረት ነው። ማንም የስልጣን ክልሉን አልፎ ሲገኝ ያለቀጠሮ በሕዝብ ጩህት ስልጣን ይለቃል
ስለሆነም አሜሪካ ባለስልጣን
ሕዝብን ፈርቶ የሚኖርባት እንጂ ሕዝብ ባለ ስልጣንን እየፈራ የሚኖርባት ሀገር አይደለችም።
እንዴት ደ.....ስ የምትል አገር መሰለችህ!!
«የምወድህ አስቻለው፡- እዚህ አሜሪካ ውስጥ ባገኘሁት ብርሃን የሀገሪን ጨለማ አሻግሬ ሳየው አቤት ማስፈራራቱ! አቤት ማስጠላቱ! አቤት ማስጨነቁ!
የመንፈስ ርሀብ የሚለቅብኝም ይህ ሁኔታ ነው። በእውነት ያንቀጠቅጣል! በእውነት ይዘገንናል! በእውነት ያንገፈግፋል! የዚህ ሁሉ ድምር ውጤት እንቅልፍ እያሳጣ እኔንም ሁል ጊዜ ያስለቅሰኛል።
የሀገራችን አምባገነኖች ከየትም ይነሱ፤ በየትም ይምጡ፣ መቸም
ይድረሱ፥ ነገር ግን አንድ የጋራ መለያ ባህሪ አላቸው፤ ይህም በፊትለፊት በህዝባቸው ስም እየማሉ በስውር ግን የገዛ ሕዝባቸውን በጠላትነት የመፈረጅ
መስሪነታቸው ነው። መሠረታዊ ምክንያቱ ደግሞ ስልጣን ላይ የሚወጡት በሀይል እንጂ የህዝብ ይሁንታ አግኝተው ስላልሆነ ነው፡፡ ግን ደግሞ ስልጣኑን ይፈልጉታል። በድሀ ሀገር ስልጣን የሀብት ምንጭ ነውና ከያዙትም በኋላ ሙጭኝ ይሉበታል። ይቆዩበት ዘንድ ጠላታችን የሚሉትን ሕዝብ ያተረማምሱታል።ቢያንስ በሁለት እንዳንዴም ከዚያ በላይ በሆነ አመዳደብ ይከፋፍሉታል። አንዱን
ወገን ወዳጅ አድርገው ሌላውን በጠላትነት ይፈርጁታል። የጠሉትን ወገን የተለያየ
ስም እየለጠፉ ይበልጥ እንዲጠላ አውርተው ያስወሩበታል። በዚህም የጠላታቸውን እርስ በእርስ ጠላትነት ይፈጥራሉ፡፡ ሕዝብና ሕገብ የጎሪጥ እንዲተያይ ያደርጉና
ጥላቻና ጥርጣሬን ያነግሱበታል። በዚህ ጊዜ የራሳቸውን የስልጣን ኮርቻ ያደላድላሉ፣ የችሎታ ሳይሆን የብልጠት አካሄድ
በመነዘረቱ የግጭቶች ሁሉ! የጦርነቶች ሁሉ፣የቅራኔዎች ሁሉ
መሠረታዊ ምክንያት ኢኮኖሚ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ጥቅም!! ፖለቲካ የሚባላው ነገር የዚሁ ፍላጎት ልጣጭ ነው። በተላይ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ድሀ አገሮች አምባገነኖች ከስልጣን ላይ የሚወጡት ይህንኑ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለመቆጣጠር ነው።ሁሉን ነገር በመዳፋቸው ውስጥ ማስገባት የአምባገነኖች ልዩ ባህሪ ነውና፡፡
በዚህ አያበቁም፡ የስልጣን ጊዜያቸው እስከ መቼ ድረስ መሆኑን በውል ስለማያቁት 'ክፉ ቀን' ቢመጣ እያሉ በተለያየ መንገድ መዘጋጀት ይጀምራሉ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...«ምነው ሔዩ በር ላይ ቆምሽ?» ሲል ጠየቃት።
«ብዙ ስለቆየሁ ወደ ቤቴ ልሄድ ተነስቼ ነው፡፡ አለችው በእጆቿ ደረቱን እየደባበሰችና ቀና ብላ ዓይኖቹን በዓይኖቿ እየተመለከተች፡፡
«ለሔዩ ምን አደረግሽላት ትርፌ?» አለ እስቻለው ወደ ትርፌ ዞር ብሎ፡፡
«ምንም ጋሼ አስቻለው፤ ወሬ ብቻ»
«ምሳ በልተሽ ሂጂያ ሔዩ!!»
«በፍጹም አስቹ! እት አበባ ስራ መምጫዋ ስለሆነ ብሄድ ይሻላል»
«ስሞት»
«አይሆንም አስቹ በአጋጣሚ መገኛኘታችን በራሱ በቂ ነው፡፡»
አስቻለው አሁንም ከንፈሮቿን ሳም ካደረገ በኃላ «በይ እሺ ከቸኮልሽ»
ሂጂ አለና እስከ ውጭ በር ሸኝቶ ተሰናብቷት ወደ ቤቱ ተመልሶ ገባ፡፡
አልጋው ላይ ቁጭ አለና ያነ በእጁ ይዞት የነበረውን ካኪ ፖስታ በጥድፊያ ይከፍት ጀመር፡፡ ከአሜሪካ ካሊፎርኒያ ግዛት ከዶክተር ደጀኔ አድማሱ የተላክለት ደብዳቤ ነው። አስቻለው ጫማውን አውልቆ አልጋው ላይ ወጣና ትራሶቹን አነባብሮ ከአንገቱ ቀና ብሎ በጀርባው ጋለል በማለት ደብዳቤውን ማንበብ ጀመረ።
«የምወድህና የማከብርህ እንዲሁም የምናፍቅህ ውድ ወንድሜ ነርስ አስቻለው ፍስሃ፥ ከቶ ለጤናህ እንደምን አለህ? ፈጣሪ አምላክ ይመስገን እኔ በጣም ደህና ነኝ።
«የምወድህ አስቻለው፡ የመኪና አደጋ ደርሶብህ እንደነበር አውቃለሁ፡፡ አደጋው ቀደረሰ
በሶስተኛ ቀን በተኛህበት ሆስፒታል ተገኝቼ ልጠይቅህም ሞክሪ ነበር። በወቅቱ ራስህን አታውቅም ነበርና፡ እኔ ደግሞ የበረራ ፕርግራሜ በማግስቱ
ስለነበር ሆዴ እያዘነ ትቼህ ሄጃለሁ። ይሁንና የኢትዮጵያ አየር ክልል ወጥቼ፣ በሱዳንና በግብጽ እንዲሁም በሜድትራኒያን ባህር፡ ከዚያም በአውሮጳ ሰማይ ላይ
ተንሳፍፌ በበረራ ላይ በነበርኩበት ጊዜ ሁሉ ስለ አንተ እያለቀስኩ ነበር፡፡ አሜሪካም ከገባሁ በኋላ የአንተ ነገር ከእዕምርዩ አልወጣ ብሎኝ ለቀናት ያህል ተሰቃይቻለሁ። የኋላ ኋላ ግን ከአደጋው ሙሉ በሙሉ አገግመህ ወደ ስራህ የመመለስህን ዜና
ስስማ አምላኬን ከልብ አመስግኛለሁ። ወደፊትም ፈጣሪህ ከሁሉም ነገር
እንዲጠብቅህ እፀልያለሁ።
«ውድ ወንድሜ አስቻለሁ። መቸም ደብዳቤዬ እንደ ደረሰህ መጀመሪያ የሚታሰብህ ምን ዓይነት ኑሮ እየኖርኩ ስለመሆኔ የምገልጽልህ ነገር ይመስለኛል።
መሰደዴ የመከፋት ውጤት ነውና አሜሪካ ውስጥ ምን ያሆሎ እንደደላኝ ወይም እንዳልደላኝ ለማውቅ ትጓጓ ይሆናል። በኔ በኩል 'ደላኝ' ወይም 'ከፋኝ'ብዬ
ልነግርህ አልፈልግም፡፡ አኗኗሬን ልግለጽልህና ምደባውን ራስህ ፈርጀው፡፡
«የአሜሪካ ውስጥ በእየዕለቱ ያገኘሁትን ሁሉ ስሰራ እውላለሁ። ስራዬን ሳጠናቅቅ ለስራው የተመደበው ገንዘብ በሙሉ ይከፈለኛል። ዛሬ አንዱ ጋር ስስራ
ውዩ ነገ ወደ ሌላው ብሄድ መልቂያ አልጠየቅም፡፡ በስራ ዘመቻ ሰበብ የጉልበቴን
ዋጋ ማንም አይነጥቀኝም፡፡ በስላም ስሰራ ውዬ የሰላም እንቅልፍ እተኛለሁ። «እገሌ
ስለኔ ምን ይላል? ነገ ምን ያደርገኝ ወይም ያስደርገኝ ይሆን? ብዬ አልጨነቅም፡፡
በሰራሁት መጠን ትክክለኛ ክፍያ ስለምቀበል የገንዘብ ችግር አይገባኝም። የልደታ ዕለት ደሞዝ ወስጄ እስከ ቀጣዩ ልደታ ቀቃኝ አልበቃኝ ብዬ ስጨነቅ አልሰነብትም፡፡
እለታዊ አዋዋሌና የሆዴ ነገር ይህን ይመስላል፡፡ የመንፈስህስ ነገር ካልከኝ ግን ጣጣው ብዙ ነው። በመሰረቱ ማንም ሰው በሀገሩ ውስጥ ተከፍቶ በተሰደደበት አገር ደስ ይለዋል ማለት ዘበት ነው ምናልባት 'ከመሞት መሰንበት' ለሚለው
የሃገራችን ብሂል ምላሽ ይሆን እንደሆን እንጂ። ስደት ደግሞ
የመንፈስ ርሃብ ውጤት ነው።
መንፈሱ የተራበ ሰው የቱንም ያህል የጣፈጠና የበዛ ምግበ ቢበላ ሁልጌዜም ውስጡ ባዶ ነው እኔም እንዲሁ ባዶዬን እኖራለሁ።
«አሜሪካ ደግሞ የጭፍን ፖለቲካል ሰለባ ሆነውለተሰደዱባት ሁሉ የባሰ የመንፈስ ረሃብ የምትለቅ ሃገር ነች፡፡ የዚች ደብዳቢየም ዋንኛ ይዘት በዚሁ ዙሪያ የሚያጠነጥን ነውና በፅሞና አንብብልኝ። በዚያው ውስጤንም ትረዳዋለህ።
«አየህ አስቻለው አሜሪካኖች ወደ ስልጣን ሲወጡ መንገዳቸው በህዝብ መሀል ነው። ለስልጣን የሚደረግ ትልቅ ጦርነት አለ። መሳሪያው ግን መድፍና
መትረየስ አይደለም የጠራና የነጠረ ሀሳብ' በሩቅ የሚታይ ራዕይ ከራእዕዩ ጫፍ
የሚደርስ የፖለቲካ አመለካከትና አሰራር ቅደም ተከተል ወይም ፕሮግራዎ" እንጂ።ባሩዳቸው የሰላ ምላስና ርቱዕ አንደበት ነው የጦርነቱ ቦታ ክብ ጠረጴዛ ነው።
የውጊያ ወረዳዎች እልፍ አእላፍን የሚይዙ ሰፋፊ አዳራሾች ናቸው
በዚህ የትግል ሜዳ አሸንፎ ስልጣን ላይ የወጣ ሁሉ ስራውን የሚያከናውነው በሕዝብ
ይሁንታ በፀደቀ ህገ መንግስት መሰረት ነው። ማንም የስልጣን ክልሉን አልፎ ሲገኝ ያለቀጠሮ በሕዝብ ጩህት ስልጣን ይለቃል
ስለሆነም አሜሪካ ባለስልጣን
ሕዝብን ፈርቶ የሚኖርባት እንጂ ሕዝብ ባለ ስልጣንን እየፈራ የሚኖርባት ሀገር አይደለችም።
እንዴት ደ.....ስ የምትል አገር መሰለችህ!!
«የምወድህ አስቻለው፡- እዚህ አሜሪካ ውስጥ ባገኘሁት ብርሃን የሀገሪን ጨለማ አሻግሬ ሳየው አቤት ማስፈራራቱ! አቤት ማስጠላቱ! አቤት ማስጨነቁ!
የመንፈስ ርሀብ የሚለቅብኝም ይህ ሁኔታ ነው። በእውነት ያንቀጠቅጣል! በእውነት ይዘገንናል! በእውነት ያንገፈግፋል! የዚህ ሁሉ ድምር ውጤት እንቅልፍ እያሳጣ እኔንም ሁል ጊዜ ያስለቅሰኛል።
የሀገራችን አምባገነኖች ከየትም ይነሱ፤ በየትም ይምጡ፣ መቸም
ይድረሱ፥ ነገር ግን አንድ የጋራ መለያ ባህሪ አላቸው፤ ይህም በፊትለፊት በህዝባቸው ስም እየማሉ በስውር ግን የገዛ ሕዝባቸውን በጠላትነት የመፈረጅ
መስሪነታቸው ነው። መሠረታዊ ምክንያቱ ደግሞ ስልጣን ላይ የሚወጡት በሀይል እንጂ የህዝብ ይሁንታ አግኝተው ስላልሆነ ነው፡፡ ግን ደግሞ ስልጣኑን ይፈልጉታል። በድሀ ሀገር ስልጣን የሀብት ምንጭ ነውና ከያዙትም በኋላ ሙጭኝ ይሉበታል። ይቆዩበት ዘንድ ጠላታችን የሚሉትን ሕዝብ ያተረማምሱታል።ቢያንስ በሁለት እንዳንዴም ከዚያ በላይ በሆነ አመዳደብ ይከፋፍሉታል። አንዱን
ወገን ወዳጅ አድርገው ሌላውን በጠላትነት ይፈርጁታል። የጠሉትን ወገን የተለያየ
ስም እየለጠፉ ይበልጥ እንዲጠላ አውርተው ያስወሩበታል። በዚህም የጠላታቸውን እርስ በእርስ ጠላትነት ይፈጥራሉ፡፡ ሕዝብና ሕገብ የጎሪጥ እንዲተያይ ያደርጉና
ጥላቻና ጥርጣሬን ያነግሱበታል። በዚህ ጊዜ የራሳቸውን የስልጣን ኮርቻ ያደላድላሉ፣ የችሎታ ሳይሆን የብልጠት አካሄድ
በመነዘረቱ የግጭቶች ሁሉ! የጦርነቶች ሁሉ፣የቅራኔዎች ሁሉ
መሠረታዊ ምክንያት ኢኮኖሚ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ጥቅም!! ፖለቲካ የሚባላው ነገር የዚሁ ፍላጎት ልጣጭ ነው። በተላይ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ድሀ አገሮች አምባገነኖች ከስልጣን ላይ የሚወጡት ይህንኑ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለመቆጣጠር ነው።ሁሉን ነገር በመዳፋቸው ውስጥ ማስገባት የአምባገነኖች ልዩ ባህሪ ነውና፡፡
በዚህ አያበቁም፡ የስልጣን ጊዜያቸው እስከ መቼ ድረስ መሆኑን በውል ስለማያቁት 'ክፉ ቀን' ቢመጣ እያሉ በተለያየ መንገድ መዘጋጀት ይጀምራሉ
#ትኩሳት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
የሞት ጥሪ
አማንዳ
ወደ ኤክስ ልንመለስ ሶስት ቀን ሲቀረን ሲልቪ ቤቶቿን ለመሰናበት ሄደች። ጊዜው ንፁህ ብርህንና ለስላሳ ሙቀት በዝግተኛው ነፋስ የሚንሳፈፉበት ውብ የፀደይ ቀን ነበር። የፓሪስ ሴቶች ወደ ሰፊው ስመ ጥሩ ጎዳና ወደ ሻንዜሊዜ እንደሚጎርፉ ታወቀኝ፡፡ በሜትሮ ወደዚያው ሄድኩ ሱቆቹ የፀደይ ሞድ ልብሶቻቸውን መስኮቶቻቸው ላይ ዘርግተዋል፤ ካፌዎቹ ጠረጴዛ ወምበሮቻቸውን ወደ መንገዱ
አውጥተው ከአብዛኛዎቹ ጠረጴዛዎች በላይ በልዩ ልዩ ቀለማት ያጌጡ ሰፋፊ ጃንጥላዎችን ዘርግተዋል። ሰዉ ይንጋጋል፤ ትራፊኩ ይፈሳል። አንዱ ካፈ ውጪ ሰዉ የሚተላለፍበት ቦታ አንዲት ትንሽ ጠረጴዛ አጠገብ ተቀመጥኩ
በፀደይ ቀን ሻንዚሊዜ ጎዳናው ዳር ቁጭ ብሎ ቢራ እየጠጡ
አላፊ አግዳሚዋን ፈረንሳዊት እና የስንትና ስንት ሌላ አገር ሴት
መቃኘት። ከዚህ የበለጠ ምን ደስታ ይገኛል? ሴቶቹ የፀደዩን
ብርሀንና ነፋስ ለመቀበል የፈነዱ አበባዎች ይመስላሉ፡፡ የወፍ ቋንቋ
መሳይ ፈረንሳይኛቸውን በልዝብ ድምፃቸው እንደዘፈን እየተቀባበሉ፣የተነጠፈውን ድንጋይ በረዥም ተረከዛቸው ኳ! ኳ! እያረጉ፤ ውብ ዳሌያቸውን እያወዛወዙ ወደላይና ወደታች ይተላለፋሉ፡፡ አይኔ
አብሯቸው ይመላለሳል
ቀስ እያለ አይኔ ሰከረ፡፡ ውበት በዛበት። የአንዷን ኩሩ አረማመድ ሳደንቅ ትንሽ እንደ ተራመደችልኝ፡ ህዝቡ መሀል ገብታ ትጠፋለች፡፡ የሌላዋ ግሩም ቅርፅ አይኔን ይስባል፡ ከዳሌዋና ከባት ከተረከዟ የቱን እንደምመርጥ ገና ሳልወስን ህዝቡ ይውጣታል። ደሞ
የአንዷ ፀጉርና አንገት ልቤን ይወስደዋል። የምትቀጥለዋ ወጣት ነጭ ጥብቅ ያለ ሱሪ ለብሳ ስታልፍ አይኔ በዳሌዋ እንቅስቃሴ ላይ ይተከላል። እሷንም ሚንጋጋው ህዝብ ይውጣታል። ሌላ ወበት ሌላ ሴት ላይ ተጭኖ ሲሄድ አይኔን ይስባል። እንደዚህ ሰል አይኔ ሰከረ
የቢራዩን ሂሳብ ከፍዬ ወደ ፕላስ ደ ሌትዋል በኩል ስራመድ
የአንዷ ፀጉር አይኔን ማረካው:: ሴትዮዋ ከኋላ ሲያዩዋት ምንም
አትል አረ ሻንለዚ ስላየሁዋት ነው እንጂ ሌላ ቦታ ባያት በጣም ደስ ትላለች። አጠር ያለች ወጣት ናት። ቀይ ቦርሳ አንጠልጥላለች። ገላዋን እቀፍ አርጎ የሚሸፍን፣ ነጭ ባለ ሽንሽን የፀደይ
ቀሚስ ለብሳለች። ወገቧን ሰፊ ቀይ ቀበቶ አቅፎታል። ቀይ
ባለረዥም ተረከዝ ጫማ የረገጡት እግሮቿ ወፈር ብለው፣ ቀለማቸው ወደ ቡናማ የሚያደላ ነው። ወፍራም ዳሌዋ ከነጭ ልብሷ
ስር ሲመዛዝ ያስታውቃል፣ ምኞት ይቀሰቅሳል። ግን ዋናው ውበቷ
ፀጉሯ ነው:: ይሄ ንፁህ ነጭ ፀጉሯ ወደኋላዋ ትከሻዋ ድረስ ተለቆ፣
ፀሀዩ ውስጥ ይብለጨለጫል። የረጋ የጨረቃ ብርህን የሚመስል
ንፁህ ፀጉር ከዚህ በፊት የት ነው ያየሁት? የት? መቼ? የት?
ሴትዮዋ ወደ ቀኝ በኩል ተጠምዛ ከሻንዜሊዜ ወጥታ፣ አንድ
ሌላ መንገድ ይዛ ወደሳይ በኩል መራመድ ጀመረች። ለምን
ተከተልኳት? አላውቅም
መንገዱ ዳር ብዙ መኪናዎች ቆመው ነበር፡ እሷ አንድ ጥቁር
ጃጉዋር ስፖርት መኪና ውስጥ ገባች። አልፌያት ወደ ላይ በኩል
መንገዴን ስቀጥል፣
“Hi there!” አለችኝ። ባለሁበት ቆምኩ፡፡ የአማንዳ፥ ድምፅ!
ጆሮዬን ማመን አልቻልኩም፡፡ ግን ፀጉሩ የሷ ነው። አሁንም
አስታወስኩ። ወደሷ ዞርኩ፡፡ ከመኪናዋ ወጥታ እየሮጠች መጣችና ተጠመጠመችብኝ። ሽቶዋ በጣም ደስ ይላል።
“አማንዳ ነሽ እውነት?
«እዎን»
«ታድያ ያ ሁሉ ጮማ የት ሄደ?»
«ሸጥኩት» አለችና ትንሽ ከኔ ራቅ ብላ አንድ ሁለት ጊዜ
እየተሽከረከረች ምን ይመስልሀል?» አለችኝ
«ተአምር ነው፡፡ በአይኔ ባላይሽ ኖሮ አላምንም ነበር»
"Thank you"
«እውነቴን ነው:: አሁንኮ ማን እንደሆንሽ ሳላውቅ ከኋላሽ
በኩል ሳይሽ የማናት ቆንጆ ፈረንሳይ? እያልኩ ስከተልሽ ነበር»
«አንዲት ሴት ምን መስማት እንደምትወድ ብጥር አርገህ
ታውቃለህ መቸስ፡»
«እውነቴን ነው ኧረ!»
«ደስ ካልኩህ አብረኸኝ ምሳ ብላ እስቲ»
«ጥሩ»
ወደ ቆንጆ ጥቁር መኪናዋ ገባን፡፡ አማንዳ ድሮ ቁምቡርስ
ነበረች፣ አሁን ግን ቢራቢሮ ሆናለች። ትርፍ እገጯ ጠፍቷል፣
አንገቷ ዙርያ ተጠፍጥፎ የነበረው ጯማ ረግፏል። ፊቷ ሙሉ ነው፡
ግን ደስ ይላል፡፡ ከንፈሮቿ ሮዝ ብጤ ቀለም ተቀብተው፣ ሰማያዊ
አይኖቿ በጥንቃቄ ተኩለው፣ ቀይ ጉትቻዋ ከነጭ ፀጉሯ አጠገብ
ሲታይ በረዶ አጠገብ የተንጠለጠለ እንጆሪ ይመስላል።
ከአስቀያሚዎቹ ሴቶች ማህበር ወጥታ፣ ቆንጆዎቹ ማህበር
ገብታለች፡፡ ድምፅዋ ሳይቀር ተለውጧል። ድሮ አልቃሻ ብጤ ነበር፤አሁን ግን ልስልስ ያለ ቆንጆ ድምፅ ነው
«ንገሪኝ እስቲ፡ ምን እንደዚህ ለወጠሽ?» አልኳት
«አንድ ሰካራም አለችኝ
«ምን?»
«ሉን ተሰናብቼ ወደ አገሬ ስሄድ፡ ኤሮፕላኑ ውስጥ አንድ
ሰውዬ አጠገብ ተቀመጥኩ፡፡ ሰውየው ሰክሮ ነበር። ሉ ትዝ እያለኝ ለብቻዬ ሳለቅስ
« ምን ያስለቅስሻል? የወደድሽው ሰውዬ እምቢ አለሽ? ደግ አረገ! በዚህ እድሜሽ ምን እንዲህ አወፈረሽ? አለኝና ያኔውኑ
ረሳኝ፣ እንቅልፍ ወሰደው
«እኔ ግን ቃላቱን እስከ መቼም አልረሳቸውም። ለመጀመርያ
ጊዜ አንድ እውነት ተገለፀልኝ። ይኸውም፣ ጅል ሆኜ ነው እንጂ፣
ውፍረቴን እንደ ጭነት ተሸክሜ መዞር የለብኝም፡፡ ጭነቱን አውርጄ ልጥለው እችላለሁ። ልጥለው ቆረጥኩ። ሳን ፍራንሲስኮ ሄጄ ሙያቸው ክብደት መቀነስ ከሆነ ሰዎች ጋር አራት ወር ሙሉ ሰራሁ። ውጤቱን አንተም አመሰገንክልኝ አለች። ሳቋ ውስጥ ወጣትነትና የህይወት ድል አድራጊነት ይጨፍራል!
ባለ አራት ኮከብ (ማለት ከሁሉ ይበልጥ ምቾት ያለበት) ሆቴሏ
ወሰደችኝ። ክፍሏ ሆነን በቴሌፎን ሁለት ምሳ አዘዘች። አሁንም
አስደነቀችኝ። ኤክስ ሳውቃት ፈረንሳይኛውን በአስቀያሚ የአሜሪካን ቅላፄ ነበር የምታዜመው፣ አሁን ግን የፓሪስ ፈረንሳይኛ ሊሆን ምንም አልቀረው:: እያየችኝ ስትስቅ
“እንደዚህ የሚያስደስት ለውጥ አይቼ አላውቅም።
"Thank you, you re really sweet" አለችኝ
ከምሳ በኋላ «ፓሪስ ምን ትሰራለህ?» አለችኝ፡፡ ነገርኳት፡፡
«አንቺስ?» አልኳት።
«ከኒው ዮርክ የዛሬ ሳምንት መጣሁ፡፡ ይሄ ጃጉዋር ከኢንግላንድ እስኪመጣልኝ ነበር " ምጠብቀው። ነገ ወይም ተነገ ወድያ ወደ ኤክስ መሄዴ ነው:: . . ሉን ማግኘት አለብኝ፡፡ ደህና ነው? አሁንስ የሚፈልገኝ ይመስልሀል? ለጊዜው ሴት አልያዘ እንደሆነ ጥርጥር የለውም። ይዞ እንደሆነ፣ ነጥቄ መውሰድ ይኖርብኛል።»
«ምን?»
«ነጥቄ እወስደዋለሁ። ምነው ገረመህ? የድሮዋ አማንዳ
መስዬህለሁ እንዴ? ተለውጫለሁኮ:: ተዘጋጅቼ ነው የመጣሁት፡፡ ቢያንስ አርባ የሳይኮሎጂ መፅሀፍ አንብቤያለሁ። ደሞ ሉን
አውቀዋለሁ፡፡ ግብረ ስጋ በጣም ይወዳል። ለሱም ተዘጋጅቻለሁ፡፡»
«እንዴት?»
«ለሌላ ሰው ቢሆን ይህን አልነግረውም። አንተ ግን
ትወደኛለህ። ወፍራም ሳለሁም ትወደኝ ነበር፡፡ ለኔ ግድ ነበረህ፡፡
የተሻልኩ ሰው ሆኜ ስላየኸኝ ደሞ በጣም ደስ ብሎሀል። ይሄ ለኔ
ትልቅ ስጦታ ነው። በጣም ተወዳጅ ነህ፡፡ እና ለምን እንደሆነ
ሳላውቅ በጣም አምንሀለሁ፡፡ ለምንድነው እማምንህ?»
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
የሞት ጥሪ
አማንዳ
ወደ ኤክስ ልንመለስ ሶስት ቀን ሲቀረን ሲልቪ ቤቶቿን ለመሰናበት ሄደች። ጊዜው ንፁህ ብርህንና ለስላሳ ሙቀት በዝግተኛው ነፋስ የሚንሳፈፉበት ውብ የፀደይ ቀን ነበር። የፓሪስ ሴቶች ወደ ሰፊው ስመ ጥሩ ጎዳና ወደ ሻንዜሊዜ እንደሚጎርፉ ታወቀኝ፡፡ በሜትሮ ወደዚያው ሄድኩ ሱቆቹ የፀደይ ሞድ ልብሶቻቸውን መስኮቶቻቸው ላይ ዘርግተዋል፤ ካፌዎቹ ጠረጴዛ ወምበሮቻቸውን ወደ መንገዱ
አውጥተው ከአብዛኛዎቹ ጠረጴዛዎች በላይ በልዩ ልዩ ቀለማት ያጌጡ ሰፋፊ ጃንጥላዎችን ዘርግተዋል። ሰዉ ይንጋጋል፤ ትራፊኩ ይፈሳል። አንዱ ካፈ ውጪ ሰዉ የሚተላለፍበት ቦታ አንዲት ትንሽ ጠረጴዛ አጠገብ ተቀመጥኩ
በፀደይ ቀን ሻንዚሊዜ ጎዳናው ዳር ቁጭ ብሎ ቢራ እየጠጡ
አላፊ አግዳሚዋን ፈረንሳዊት እና የስንትና ስንት ሌላ አገር ሴት
መቃኘት። ከዚህ የበለጠ ምን ደስታ ይገኛል? ሴቶቹ የፀደዩን
ብርሀንና ነፋስ ለመቀበል የፈነዱ አበባዎች ይመስላሉ፡፡ የወፍ ቋንቋ
መሳይ ፈረንሳይኛቸውን በልዝብ ድምፃቸው እንደዘፈን እየተቀባበሉ፣የተነጠፈውን ድንጋይ በረዥም ተረከዛቸው ኳ! ኳ! እያረጉ፤ ውብ ዳሌያቸውን እያወዛወዙ ወደላይና ወደታች ይተላለፋሉ፡፡ አይኔ
አብሯቸው ይመላለሳል
ቀስ እያለ አይኔ ሰከረ፡፡ ውበት በዛበት። የአንዷን ኩሩ አረማመድ ሳደንቅ ትንሽ እንደ ተራመደችልኝ፡ ህዝቡ መሀል ገብታ ትጠፋለች፡፡ የሌላዋ ግሩም ቅርፅ አይኔን ይስባል፡ ከዳሌዋና ከባት ከተረከዟ የቱን እንደምመርጥ ገና ሳልወስን ህዝቡ ይውጣታል። ደሞ
የአንዷ ፀጉርና አንገት ልቤን ይወስደዋል። የምትቀጥለዋ ወጣት ነጭ ጥብቅ ያለ ሱሪ ለብሳ ስታልፍ አይኔ በዳሌዋ እንቅስቃሴ ላይ ይተከላል። እሷንም ሚንጋጋው ህዝብ ይውጣታል። ሌላ ወበት ሌላ ሴት ላይ ተጭኖ ሲሄድ አይኔን ይስባል። እንደዚህ ሰል አይኔ ሰከረ
የቢራዩን ሂሳብ ከፍዬ ወደ ፕላስ ደ ሌትዋል በኩል ስራመድ
የአንዷ ፀጉር አይኔን ማረካው:: ሴትዮዋ ከኋላ ሲያዩዋት ምንም
አትል አረ ሻንለዚ ስላየሁዋት ነው እንጂ ሌላ ቦታ ባያት በጣም ደስ ትላለች። አጠር ያለች ወጣት ናት። ቀይ ቦርሳ አንጠልጥላለች። ገላዋን እቀፍ አርጎ የሚሸፍን፣ ነጭ ባለ ሽንሽን የፀደይ
ቀሚስ ለብሳለች። ወገቧን ሰፊ ቀይ ቀበቶ አቅፎታል። ቀይ
ባለረዥም ተረከዝ ጫማ የረገጡት እግሮቿ ወፈር ብለው፣ ቀለማቸው ወደ ቡናማ የሚያደላ ነው። ወፍራም ዳሌዋ ከነጭ ልብሷ
ስር ሲመዛዝ ያስታውቃል፣ ምኞት ይቀሰቅሳል። ግን ዋናው ውበቷ
ፀጉሯ ነው:: ይሄ ንፁህ ነጭ ፀጉሯ ወደኋላዋ ትከሻዋ ድረስ ተለቆ፣
ፀሀዩ ውስጥ ይብለጨለጫል። የረጋ የጨረቃ ብርህን የሚመስል
ንፁህ ፀጉር ከዚህ በፊት የት ነው ያየሁት? የት? መቼ? የት?
ሴትዮዋ ወደ ቀኝ በኩል ተጠምዛ ከሻንዜሊዜ ወጥታ፣ አንድ
ሌላ መንገድ ይዛ ወደሳይ በኩል መራመድ ጀመረች። ለምን
ተከተልኳት? አላውቅም
መንገዱ ዳር ብዙ መኪናዎች ቆመው ነበር፡ እሷ አንድ ጥቁር
ጃጉዋር ስፖርት መኪና ውስጥ ገባች። አልፌያት ወደ ላይ በኩል
መንገዴን ስቀጥል፣
“Hi there!” አለችኝ። ባለሁበት ቆምኩ፡፡ የአማንዳ፥ ድምፅ!
ጆሮዬን ማመን አልቻልኩም፡፡ ግን ፀጉሩ የሷ ነው። አሁንም
አስታወስኩ። ወደሷ ዞርኩ፡፡ ከመኪናዋ ወጥታ እየሮጠች መጣችና ተጠመጠመችብኝ። ሽቶዋ በጣም ደስ ይላል።
“አማንዳ ነሽ እውነት?
«እዎን»
«ታድያ ያ ሁሉ ጮማ የት ሄደ?»
«ሸጥኩት» አለችና ትንሽ ከኔ ራቅ ብላ አንድ ሁለት ጊዜ
እየተሽከረከረች ምን ይመስልሀል?» አለችኝ
«ተአምር ነው፡፡ በአይኔ ባላይሽ ኖሮ አላምንም ነበር»
"Thank you"
«እውነቴን ነው:: አሁንኮ ማን እንደሆንሽ ሳላውቅ ከኋላሽ
በኩል ሳይሽ የማናት ቆንጆ ፈረንሳይ? እያልኩ ስከተልሽ ነበር»
«አንዲት ሴት ምን መስማት እንደምትወድ ብጥር አርገህ
ታውቃለህ መቸስ፡»
«እውነቴን ነው ኧረ!»
«ደስ ካልኩህ አብረኸኝ ምሳ ብላ እስቲ»
«ጥሩ»
ወደ ቆንጆ ጥቁር መኪናዋ ገባን፡፡ አማንዳ ድሮ ቁምቡርስ
ነበረች፣ አሁን ግን ቢራቢሮ ሆናለች። ትርፍ እገጯ ጠፍቷል፣
አንገቷ ዙርያ ተጠፍጥፎ የነበረው ጯማ ረግፏል። ፊቷ ሙሉ ነው፡
ግን ደስ ይላል፡፡ ከንፈሮቿ ሮዝ ብጤ ቀለም ተቀብተው፣ ሰማያዊ
አይኖቿ በጥንቃቄ ተኩለው፣ ቀይ ጉትቻዋ ከነጭ ፀጉሯ አጠገብ
ሲታይ በረዶ አጠገብ የተንጠለጠለ እንጆሪ ይመስላል።
ከአስቀያሚዎቹ ሴቶች ማህበር ወጥታ፣ ቆንጆዎቹ ማህበር
ገብታለች፡፡ ድምፅዋ ሳይቀር ተለውጧል። ድሮ አልቃሻ ብጤ ነበር፤አሁን ግን ልስልስ ያለ ቆንጆ ድምፅ ነው
«ንገሪኝ እስቲ፡ ምን እንደዚህ ለወጠሽ?» አልኳት
«አንድ ሰካራም አለችኝ
«ምን?»
«ሉን ተሰናብቼ ወደ አገሬ ስሄድ፡ ኤሮፕላኑ ውስጥ አንድ
ሰውዬ አጠገብ ተቀመጥኩ፡፡ ሰውየው ሰክሮ ነበር። ሉ ትዝ እያለኝ ለብቻዬ ሳለቅስ
« ምን ያስለቅስሻል? የወደድሽው ሰውዬ እምቢ አለሽ? ደግ አረገ! በዚህ እድሜሽ ምን እንዲህ አወፈረሽ? አለኝና ያኔውኑ
ረሳኝ፣ እንቅልፍ ወሰደው
«እኔ ግን ቃላቱን እስከ መቼም አልረሳቸውም። ለመጀመርያ
ጊዜ አንድ እውነት ተገለፀልኝ። ይኸውም፣ ጅል ሆኜ ነው እንጂ፣
ውፍረቴን እንደ ጭነት ተሸክሜ መዞር የለብኝም፡፡ ጭነቱን አውርጄ ልጥለው እችላለሁ። ልጥለው ቆረጥኩ። ሳን ፍራንሲስኮ ሄጄ ሙያቸው ክብደት መቀነስ ከሆነ ሰዎች ጋር አራት ወር ሙሉ ሰራሁ። ውጤቱን አንተም አመሰገንክልኝ አለች። ሳቋ ውስጥ ወጣትነትና የህይወት ድል አድራጊነት ይጨፍራል!
ባለ አራት ኮከብ (ማለት ከሁሉ ይበልጥ ምቾት ያለበት) ሆቴሏ
ወሰደችኝ። ክፍሏ ሆነን በቴሌፎን ሁለት ምሳ አዘዘች። አሁንም
አስደነቀችኝ። ኤክስ ሳውቃት ፈረንሳይኛውን በአስቀያሚ የአሜሪካን ቅላፄ ነበር የምታዜመው፣ አሁን ግን የፓሪስ ፈረንሳይኛ ሊሆን ምንም አልቀረው:: እያየችኝ ስትስቅ
“እንደዚህ የሚያስደስት ለውጥ አይቼ አላውቅም።
"Thank you, you re really sweet" አለችኝ
ከምሳ በኋላ «ፓሪስ ምን ትሰራለህ?» አለችኝ፡፡ ነገርኳት፡፡
«አንቺስ?» አልኳት።
«ከኒው ዮርክ የዛሬ ሳምንት መጣሁ፡፡ ይሄ ጃጉዋር ከኢንግላንድ እስኪመጣልኝ ነበር " ምጠብቀው። ነገ ወይም ተነገ ወድያ ወደ ኤክስ መሄዴ ነው:: . . ሉን ማግኘት አለብኝ፡፡ ደህና ነው? አሁንስ የሚፈልገኝ ይመስልሀል? ለጊዜው ሴት አልያዘ እንደሆነ ጥርጥር የለውም። ይዞ እንደሆነ፣ ነጥቄ መውሰድ ይኖርብኛል።»
«ምን?»
«ነጥቄ እወስደዋለሁ። ምነው ገረመህ? የድሮዋ አማንዳ
መስዬህለሁ እንዴ? ተለውጫለሁኮ:: ተዘጋጅቼ ነው የመጣሁት፡፡ ቢያንስ አርባ የሳይኮሎጂ መፅሀፍ አንብቤያለሁ። ደሞ ሉን
አውቀዋለሁ፡፡ ግብረ ስጋ በጣም ይወዳል። ለሱም ተዘጋጅቻለሁ፡፡»
«እንዴት?»
«ለሌላ ሰው ቢሆን ይህን አልነግረውም። አንተ ግን
ትወደኛለህ። ወፍራም ሳለሁም ትወደኝ ነበር፡፡ ለኔ ግድ ነበረህ፡፡
የተሻልኩ ሰው ሆኜ ስላየኸኝ ደሞ በጣም ደስ ብሎሀል። ይሄ ለኔ
ትልቅ ስጦታ ነው። በጣም ተወዳጅ ነህ፡፡ እና ለምን እንደሆነ
ሳላውቅ በጣም አምንሀለሁ፡፡ ለምንድነው እማምንህ?»
#ሳቤላ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
ለሚስተርና ለሚስዝ ካርላይል ጋብቻ ደስታቸውን ለመግለጽ የአካባቢው ታላላቅ ሰዎች እንደየአቅማቸውና እንደ ደረጃቸው በተለያዩ ሠረገዎች እየሆኑ በልዩ
ልዩ የክብር ልብሶች አጊጠው ጌጠኛ ልብስ በለበሱ አሽከሮች እየታጀቡ ኢስትሊን መግባት ጀመሩ ።
ሚስተር ካርይል መኖሪያውን ኢስት ሊን ቢያደርግም እመቤት ሳቤላ ቬንን ባያገባ ኖሮ እነዚያ ሁሉ መኳንንትና ወይዛዝርት ይኸን ያሀል ክብር ሰጥተው እሱን ጥየቃ ብለው እንደዚህ በብዛት አይንጋጉለትም ነበር "
ደስታቸውን ለመግለጽ ከመጡት ታላላቅ ሰዎች መካከል ጀስቲስ” ሔር'ሚስቱና ልጁ ባርባራ ሔር ነበሩ " በነዚያ ጭራቸው መሬት በሚነካ ኣካላተ ሙሉና ጸጉረ ለስላሳ ፈረሶች ይሳብ የነበረው ጥንታዊ ሠረገላ የሚንቀሳቀሰው እንደ ዛሬው በመሳሰሉ አጋጣሚዎችና ከፍተኛ የበዓል ቀኖች ብቻ ነበር "
እንግዶቹ ኢስት ሊን በደረሱበት ሰዓት ሳቤላ ከመልበሻ ክፍሏ ሆና ጆይስ ከሷ ጋር ስለምትጠቃለልበት መንግድ ትነጋገር ነበር » ጆይስም የደንገጡርነቱን ሥራ ደኅና እየተለማመደችው ስለ ነበርና ሚስ ካርላይልም ያለምምንም ቅሬታ እንደ ምትፈቅድላት ስለምታውቅ ወይዘሮ ሳቤላ ከፈቀደች ደስ እያላት ከሷ ጋር ለመሆን እንደምትፈልግ ስትነግራት ነበር " በዚህ መኻል በር ተንኳኳ " ጆይስ በሩን ስትከፍተው አንዲት የዌስት ሊን ተወላጅ የሆነች አዲስ የተቀጠረች ሠራተኛ ሆና አገኘቻት " ሳቤላ ሁለቱ ሴቶች የሚባባሉትን ትስማ ነበር ።
« እሜቴ አሉ ? »
« አሉ »
« እንግዶች መጥተዋል " ፒተር ንገሪ ብሎ ልኮኝ ነው ። እነማን መሰሉሽ ? ሚስተር “ጀስቲስ” ሔር ከነቤተሰባቸው እሷም አብራ አለች " መቸም ያለባበስ ነገር አታንሺው የራስ መሸፈኛዋ በውስጡ ሰማያዊ ጥሩንባ ቅርጽ አበቦች አሉት " በስተውጪ መጥረጊያ የሚያክል ነጭ ላባ ሰክታበታለች ከሠረገላ ስትወርድ ልብ ብዬ አየኋት " »
« ማናት እሷ ? » አለች ጆይስ ፊቷን ኮስተር አድርጋ
« ሚስ ባርባራ ናታ እስኪ ተመልከች አሁን እሷም ልጠይቅ ብላ መምጣቷ ምን ይባላል ? ይልቅ እሜቴን መርዝ እንዳታጠጣቸው ቢጠነቀቁ ይሻላል »
ጆይስ ሠራተኛይቱን በዛው ሸኝታ ' በሩን ዘጋችና ወደ እመቤቷ ተመለሰች "በሹክሹክታ የተመላለሱትን ነገር ሳቤላ መስማቷን አላወቀችም "
« ሱዛን ናት " እንግዶች መምጣታቸውን ልትነግር ነው የመጣችው • ሚስተር ጀስቲስ ሔር ' ሚስዝ ሔርና ሚስ ባርባራ ከሳሎን ገብተው ተቀምጠዋል ትላለች »
ሳቤላ ሱዛን ስለ ተናረችው ምስጢራዊ ነገር ኢያሰበች እንግዶች ወዶ ዐረፉበት ክፍል ወረደች "
ዳኛው አዲስ ሰው ሠራሽ ጸጉር ያጠለቀ ጉረኛና የተናገረውን ቃል ማያጥፍ ችክ ያለ ሰው ይመስላል ሚስዝ ሔር ልስልስ ግርጥት ያለች ወይዘሮ ስትሆን ባርባራ ደግሞ የምታምር ቆንጆ ናት " ሳቤላ ስትገባ እንዳየቻቸው ያሳደሩባት ስሜት ይህን ይመስል ነበር "
ብዙ ሲጫወቱ ቆዩ " ሳቤላ ያቺን መከረኛና ረቂቅ ወይዘሮ ሚስዝ ሔርን ስታያት በጣም ወደደቻት ሚስ ካርይል ስትግባ እንግዶቹ ለመሔድ ተነሱ" ሚስ ካርላይል ግን ለባርባራ የምታሳያት ነገር ስለ ነበራት እንዲቆዩ ብትሞክርም
በዐሥራ አንድ ሰዓት ከቤቱ እንግዳ ስለጠራና አሁን ግማሽ ሰዓት ብቻ ስለ ቀረው ባርባራ ብትፈልግ ልትቆይ መቻሏን ነግሮ ከሚስቱ ጋር ተያይዘው ሔዱ "
ባርባራ ፊቷ ደም መሰለ ሆኖም ሚስ ኮርኒሊያ ካርላይል ያቀረበችላት የራት ሰዓት ደረሰ ሳቤላ የራት ልብስ ለመልበስ ከፎቅ ወደሚገኘው ክፍል
ወጣች " ጆይስ እዛው ስትጠብቃት አገኘቻት " ወዲያው ከሷ ጋር ስለምትሆንባት
ጉዳይ መነጋግር ጀመሩ
« እሜቴ » አለች ጆይስ « ሚስ ካርላይልን አነጋግሬአቸዋለሁ " ወደ እርስዎ ብዛወር ፈቃደኛ ናቸው " ነገር ግን በታሪኬ አንድ ደስ የማይል ነገር ስለ አለበት
አስቀድሜ መግለጽ እንዳለብኝ ነግረውኛል እኔም ራሴ አስቤበት ነበር " ሚስ ካርላይል ጠባያቸው ደስ አይልም ግን እውነተኛና ቀጥተኛ ሰው ናቸው "
« ምንድን ነው ደስ የማይለው ታሪክሽ ? »
« አባቴ የሚስተር ካርላይል አባት ጸሐፊ ነበር " እናቴ በስምንት ዓመቴ ሞተችና አባቴ የሚስተር ኬን ዋርሳ የምትሆን ሴት አግብቶ አፌ የምትባለዋን እኅቴን ወለዶችለት እሷም አፊ ገና ያመት ልጅ ሳለች ሞተች " ሕፃኗም የናቷ
አክስት ልታሳድጋት ወሰደቻት እኔ ግን ከአባቴ ጋር ሁኘ በልጅነቴ ትምሀርት ቤት እመላለስ ነበር ካደግሁ በኋላ ባርኔጣ ሥራና ልብስ ሰፌት ተማርኩ አባቴ የራሱ
የሆነ ቤት ከጫካው ዳር ነበረው " የቤት ሥራ የምትረዳ የቀን ሠራተኛ ነበረች እሷም በየቀኑ ከኛ ጋር የምትቆየው ለጥቂት ሰአት ብቻ ነበር አባቴን እንዳይከፋው እየተንከባከብኩ ጊዜ ሲኖረኝ ብቻ ከአንዳንድ ወይዛዝርት ቤት እየሔድኩ እሠራ ነበር "
« በዚህ ዐይነት ብዙ ዓመት ከኖርን በኋላ አፊ ተመልሳ መጣችና ከኛ ጋር ተቀመጠች አክስቲቱም ሞተች " ገንዘቧም አብሮ ሞተና ምንም እንኳን አፊን በደንብ ብታሳድጋትም ስትሞት አንድም ነገር ልትተውላት አልቻለችም " እኛም አፊ ፈራናት " አለባበሷና ልዩ ፍሳጐቷ ሰማይ ነበር ደስተኛ መልከኛና የተቅበጠበጠች ነበረች" ከዌስት ሊን የሕዝብ ንባብ ቤት እየተዋሰች የምታመጣቸውን መጻሕፍት ከማንበብ በቀር አንድም ነገር አትሠራም ነበር አባቴ ደግሞ ይኸን ጠባይዋን
አልወደደውም እኛ ለራሳችን ለፍቶ አዳሪዎች ስንሆን እሷ ደግሞ አክስቷ ቤት እንደ ለመደችው ትዘባነንብን ጀመች እንዲህ ስትል ስትል ከሪቻርድ ሔር ተዋወቀች "
ወይዘሮ ሳቤላ ' ቶሎ ቀና ብላ አየቻት
« የሚስተር ጀስቲስ ሔር ብቸኛ ወንድ ልጅና ! የሚስ ባርባራ ወንድም ነው አፊ ፊት ስትሰጠው ጊዜ ፍቅር ያዘው ከዚያም ቀስ በቀስ ሌሎችንም መሳብ ጀመረች አባታችን በሥራ ምክንያት ከቤት በማይኖርበት ጊዜ አጫፋሪዎቿ
የፈለገችውን እየያዘች ከቤት ታመሻለች።
« ከብዙ ወዳጆቿ አንዱና ዋናው ሪቻርድ ሔር ነበር ሌላ ደግሞ ራቅ ካለ ቦታ በፈረስ እየመጣ የሚጠይቃት ወዳጅ ነበራት " እሱ ግን አስከዚህም የነበረ አይመስለኝም " ከሚስተር ሪቻርድ ሔር ጋር የነበራት ግንኙነት ግን አባቴን እስከ ገደለበት ድረስ ቀጠለ "
« ማን ? » አለች ሳቤላ ድንግጥ ብላ ።
« ሪቻርድ ሔር ነዋ . . .እሜቴ » አባቴ እነዚህ የትልቅ ሰዎች ልጆች ድሆች ሴቶች ልጆችን የሚከታተሏቸው ለጋብቻ እያሰቧቸው እንዳልነበር ያውቅ ነበር በርግጥ በሚስተር ሪቻርድ ቀና አመለካከት ባይኖረውና በአፊጉዳት ያደርሳል ብሎ
ቢጠረጥረው ኖሮ ጠበቅ ያለ ገደብ ይፈጥር ነበር " አንድ ቀን ዌስት ሊን ላይ ስዎች የሷን ስም ከሪቻርድ ጋር አዳብለው በክፉ ሰያነሡት ሰማ ማታ ሲጠጣ እኔ ባለሁበት ከሪቻርድ ጋር ያላት ግንኙነት እንዳይቀጥል እሷም ፊት እንዳትሰጠ ለአፊ ነገራት " ይገርምዎታል በበነጋው ማታ ሪቻርድ ሔር አባቴን በጥይት ገደለው » አለቻት።
« አቤት እንዴት ያሳዝናል ልጀ ! »
« ታዲያ ይህ ነገር ሆነ ተብሎ የተፈጸመ ይሁን ወይም ካለመጠንቀቅ ጠበንጃው ጋር ሲታገል ይባርቅበት አልታወቀም ሕዝቡ በማን አለብኝነት የተፈጸመ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
ለሚስተርና ለሚስዝ ካርላይል ጋብቻ ደስታቸውን ለመግለጽ የአካባቢው ታላላቅ ሰዎች እንደየአቅማቸውና እንደ ደረጃቸው በተለያዩ ሠረገዎች እየሆኑ በልዩ
ልዩ የክብር ልብሶች አጊጠው ጌጠኛ ልብስ በለበሱ አሽከሮች እየታጀቡ ኢስትሊን መግባት ጀመሩ ።
ሚስተር ካርይል መኖሪያውን ኢስት ሊን ቢያደርግም እመቤት ሳቤላ ቬንን ባያገባ ኖሮ እነዚያ ሁሉ መኳንንትና ወይዛዝርት ይኸን ያሀል ክብር ሰጥተው እሱን ጥየቃ ብለው እንደዚህ በብዛት አይንጋጉለትም ነበር "
ደስታቸውን ለመግለጽ ከመጡት ታላላቅ ሰዎች መካከል ጀስቲስ” ሔር'ሚስቱና ልጁ ባርባራ ሔር ነበሩ " በነዚያ ጭራቸው መሬት በሚነካ ኣካላተ ሙሉና ጸጉረ ለስላሳ ፈረሶች ይሳብ የነበረው ጥንታዊ ሠረገላ የሚንቀሳቀሰው እንደ ዛሬው በመሳሰሉ አጋጣሚዎችና ከፍተኛ የበዓል ቀኖች ብቻ ነበር "
እንግዶቹ ኢስት ሊን በደረሱበት ሰዓት ሳቤላ ከመልበሻ ክፍሏ ሆና ጆይስ ከሷ ጋር ስለምትጠቃለልበት መንግድ ትነጋገር ነበር » ጆይስም የደንገጡርነቱን ሥራ ደኅና እየተለማመደችው ስለ ነበርና ሚስ ካርላይልም ያለምምንም ቅሬታ እንደ ምትፈቅድላት ስለምታውቅ ወይዘሮ ሳቤላ ከፈቀደች ደስ እያላት ከሷ ጋር ለመሆን እንደምትፈልግ ስትነግራት ነበር " በዚህ መኻል በር ተንኳኳ " ጆይስ በሩን ስትከፍተው አንዲት የዌስት ሊን ተወላጅ የሆነች አዲስ የተቀጠረች ሠራተኛ ሆና አገኘቻት " ሳቤላ ሁለቱ ሴቶች የሚባባሉትን ትስማ ነበር ።
« እሜቴ አሉ ? »
« አሉ »
« እንግዶች መጥተዋል " ፒተር ንገሪ ብሎ ልኮኝ ነው ። እነማን መሰሉሽ ? ሚስተር “ጀስቲስ” ሔር ከነቤተሰባቸው እሷም አብራ አለች " መቸም ያለባበስ ነገር አታንሺው የራስ መሸፈኛዋ በውስጡ ሰማያዊ ጥሩንባ ቅርጽ አበቦች አሉት " በስተውጪ መጥረጊያ የሚያክል ነጭ ላባ ሰክታበታለች ከሠረገላ ስትወርድ ልብ ብዬ አየኋት " »
« ማናት እሷ ? » አለች ጆይስ ፊቷን ኮስተር አድርጋ
« ሚስ ባርባራ ናታ እስኪ ተመልከች አሁን እሷም ልጠይቅ ብላ መምጣቷ ምን ይባላል ? ይልቅ እሜቴን መርዝ እንዳታጠጣቸው ቢጠነቀቁ ይሻላል »
ጆይስ ሠራተኛይቱን በዛው ሸኝታ ' በሩን ዘጋችና ወደ እመቤቷ ተመለሰች "በሹክሹክታ የተመላለሱትን ነገር ሳቤላ መስማቷን አላወቀችም "
« ሱዛን ናት " እንግዶች መምጣታቸውን ልትነግር ነው የመጣችው • ሚስተር ጀስቲስ ሔር ' ሚስዝ ሔርና ሚስ ባርባራ ከሳሎን ገብተው ተቀምጠዋል ትላለች »
ሳቤላ ሱዛን ስለ ተናረችው ምስጢራዊ ነገር ኢያሰበች እንግዶች ወዶ ዐረፉበት ክፍል ወረደች "
ዳኛው አዲስ ሰው ሠራሽ ጸጉር ያጠለቀ ጉረኛና የተናገረውን ቃል ማያጥፍ ችክ ያለ ሰው ይመስላል ሚስዝ ሔር ልስልስ ግርጥት ያለች ወይዘሮ ስትሆን ባርባራ ደግሞ የምታምር ቆንጆ ናት " ሳቤላ ስትገባ እንዳየቻቸው ያሳደሩባት ስሜት ይህን ይመስል ነበር "
ብዙ ሲጫወቱ ቆዩ " ሳቤላ ያቺን መከረኛና ረቂቅ ወይዘሮ ሚስዝ ሔርን ስታያት በጣም ወደደቻት ሚስ ካርይል ስትግባ እንግዶቹ ለመሔድ ተነሱ" ሚስ ካርላይል ግን ለባርባራ የምታሳያት ነገር ስለ ነበራት እንዲቆዩ ብትሞክርም
በዐሥራ አንድ ሰዓት ከቤቱ እንግዳ ስለጠራና አሁን ግማሽ ሰዓት ብቻ ስለ ቀረው ባርባራ ብትፈልግ ልትቆይ መቻሏን ነግሮ ከሚስቱ ጋር ተያይዘው ሔዱ "
ባርባራ ፊቷ ደም መሰለ ሆኖም ሚስ ኮርኒሊያ ካርላይል ያቀረበችላት የራት ሰዓት ደረሰ ሳቤላ የራት ልብስ ለመልበስ ከፎቅ ወደሚገኘው ክፍል
ወጣች " ጆይስ እዛው ስትጠብቃት አገኘቻት " ወዲያው ከሷ ጋር ስለምትሆንባት
ጉዳይ መነጋግር ጀመሩ
« እሜቴ » አለች ጆይስ « ሚስ ካርላይልን አነጋግሬአቸዋለሁ " ወደ እርስዎ ብዛወር ፈቃደኛ ናቸው " ነገር ግን በታሪኬ አንድ ደስ የማይል ነገር ስለ አለበት
አስቀድሜ መግለጽ እንዳለብኝ ነግረውኛል እኔም ራሴ አስቤበት ነበር " ሚስ ካርላይል ጠባያቸው ደስ አይልም ግን እውነተኛና ቀጥተኛ ሰው ናቸው "
« ምንድን ነው ደስ የማይለው ታሪክሽ ? »
« አባቴ የሚስተር ካርላይል አባት ጸሐፊ ነበር " እናቴ በስምንት ዓመቴ ሞተችና አባቴ የሚስተር ኬን ዋርሳ የምትሆን ሴት አግብቶ አፌ የምትባለዋን እኅቴን ወለዶችለት እሷም አፊ ገና ያመት ልጅ ሳለች ሞተች " ሕፃኗም የናቷ
አክስት ልታሳድጋት ወሰደቻት እኔ ግን ከአባቴ ጋር ሁኘ በልጅነቴ ትምሀርት ቤት እመላለስ ነበር ካደግሁ በኋላ ባርኔጣ ሥራና ልብስ ሰፌት ተማርኩ አባቴ የራሱ
የሆነ ቤት ከጫካው ዳር ነበረው " የቤት ሥራ የምትረዳ የቀን ሠራተኛ ነበረች እሷም በየቀኑ ከኛ ጋር የምትቆየው ለጥቂት ሰአት ብቻ ነበር አባቴን እንዳይከፋው እየተንከባከብኩ ጊዜ ሲኖረኝ ብቻ ከአንዳንድ ወይዛዝርት ቤት እየሔድኩ እሠራ ነበር "
« በዚህ ዐይነት ብዙ ዓመት ከኖርን በኋላ አፊ ተመልሳ መጣችና ከኛ ጋር ተቀመጠች አክስቲቱም ሞተች " ገንዘቧም አብሮ ሞተና ምንም እንኳን አፊን በደንብ ብታሳድጋትም ስትሞት አንድም ነገር ልትተውላት አልቻለችም " እኛም አፊ ፈራናት " አለባበሷና ልዩ ፍሳጐቷ ሰማይ ነበር ደስተኛ መልከኛና የተቅበጠበጠች ነበረች" ከዌስት ሊን የሕዝብ ንባብ ቤት እየተዋሰች የምታመጣቸውን መጻሕፍት ከማንበብ በቀር አንድም ነገር አትሠራም ነበር አባቴ ደግሞ ይኸን ጠባይዋን
አልወደደውም እኛ ለራሳችን ለፍቶ አዳሪዎች ስንሆን እሷ ደግሞ አክስቷ ቤት እንደ ለመደችው ትዘባነንብን ጀመች እንዲህ ስትል ስትል ከሪቻርድ ሔር ተዋወቀች "
ወይዘሮ ሳቤላ ' ቶሎ ቀና ብላ አየቻት
« የሚስተር ጀስቲስ ሔር ብቸኛ ወንድ ልጅና ! የሚስ ባርባራ ወንድም ነው አፊ ፊት ስትሰጠው ጊዜ ፍቅር ያዘው ከዚያም ቀስ በቀስ ሌሎችንም መሳብ ጀመረች አባታችን በሥራ ምክንያት ከቤት በማይኖርበት ጊዜ አጫፋሪዎቿ
የፈለገችውን እየያዘች ከቤት ታመሻለች።
« ከብዙ ወዳጆቿ አንዱና ዋናው ሪቻርድ ሔር ነበር ሌላ ደግሞ ራቅ ካለ ቦታ በፈረስ እየመጣ የሚጠይቃት ወዳጅ ነበራት " እሱ ግን አስከዚህም የነበረ አይመስለኝም " ከሚስተር ሪቻርድ ሔር ጋር የነበራት ግንኙነት ግን አባቴን እስከ ገደለበት ድረስ ቀጠለ "
« ማን ? » አለች ሳቤላ ድንግጥ ብላ ።
« ሪቻርድ ሔር ነዋ . . .እሜቴ » አባቴ እነዚህ የትልቅ ሰዎች ልጆች ድሆች ሴቶች ልጆችን የሚከታተሏቸው ለጋብቻ እያሰቧቸው እንዳልነበር ያውቅ ነበር በርግጥ በሚስተር ሪቻርድ ቀና አመለካከት ባይኖረውና በአፊጉዳት ያደርሳል ብሎ
ቢጠረጥረው ኖሮ ጠበቅ ያለ ገደብ ይፈጥር ነበር " አንድ ቀን ዌስት ሊን ላይ ስዎች የሷን ስም ከሪቻርድ ጋር አዳብለው በክፉ ሰያነሡት ሰማ ማታ ሲጠጣ እኔ ባለሁበት ከሪቻርድ ጋር ያላት ግንኙነት እንዳይቀጥል እሷም ፊት እንዳትሰጠ ለአፊ ነገራት " ይገርምዎታል በበነጋው ማታ ሪቻርድ ሔር አባቴን በጥይት ገደለው » አለቻት።
« አቤት እንዴት ያሳዝናል ልጀ ! »
« ታዲያ ይህ ነገር ሆነ ተብሎ የተፈጸመ ይሁን ወይም ካለመጠንቀቅ ጠበንጃው ጋር ሲታገል ይባርቅበት አልታወቀም ሕዝቡ በማን አለብኝነት የተፈጸመ
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
ማደግ፣ ብልህ መሆን
ልክ እንደ መጀመሪያው አመት ሁሉ ሌላኛውም አመት አለፈ እናታችን ልትጎበኘን የምትመጣበት ቀን እየቀነሰ መጣ ከስንት አንድ ጊዜ ስትመጣም
ሁሌም ከዚህ ለመውጣት ጥቂት ሳምንታት ብቻ እንደቀሩን እንድናምንና ተስፋ እንድናደርግ የሚያደርገን ቃል ትገባልናለች። በእያንዳንዱ ምሽት መጨረሻ ላይ የምናደርገው ነገር ቢኖር የቀን መቁጠሪያው ላይ በትልቁ
የኤክስ ምልክት ማድረግ ነው።
አሁን ትላልቅ ቀይ የኤክስ ምልክቶች ያሉባቸው ሶስት የቀን መቁጠሪያዎች አሉን፡ የመጀመሪያው በግማሽ ብቻ ቀይ የኤክስ ምልክት የተደረገበት ነው።
ሁለተኛው ሙሉ በሙሉ ምልክት ተደርጎበታል፡ ሶስተኛው ደግሞ ግማሹ በኤክስ ምልክት ተሞልቷል፡ እየሞተ ያለው አያታችን አሁን ስልሳ ስምንት
አመት ሆኖታል። ሁልጊዜም የመጨረሻ ትንፋሹ ነው እየተባለ እኛ በተረሳ ቦታ እየተጠባበቅን እሱ ግን አሁንም መኖሩን ቀጥሏል ስልሳ ዘጠኝ አመት
እንዲሆነው እየኖረ ይመስላል።
ሀሙስ ሀሙስ በፎክስወርዝ ቤት ውስጥ ያሉ ሠራተኞች ወደ ከተማ
የሚሄዱበት ቀን ነው፡ እኔና ክሪስቶፈር ጥቁሩ ጣራ ላይ ወጥተን ጋደም በማለት የፀሀይ ብርሃን የምናገኘውና ከጨረቃና ከኮከቦች ስር ሆነን አየር
የምንቀበለው እነሱ በሚወጡ ጊዜ ነው በጣም ከፍ ያለና አደገኛ ቢሆንም ንፁህ አየር የተጠማው ቆዳችንን ማስታገስ የምንችልበት ብቸኛ ቦታ ቢኖር ጣሪያው ብቻ ነው።
እግራችንን በጭስ ማውጫው በኩል የሁለቱ ቤቶች ጣራዎች የሚገናኙበት ጥግ ላይ ስናደርግ ደህንነት ተሰማን የተደበቅንበት ቦታ መሬት ላይ ካለው ሰው ሁሉ ይከልለናል: የአያትየው ቁጣ ገና መተግበር ስላልጀመረ እኔና
ክሪስ ግዴለሾች ሆነን ነበር መታጠቢያ ቤት የምንጠቀመው ሁሌ ተጠንቅቀን አይደለም። አንዳንዴ ልብሶቻችንን ሙሉ በሙሉ ላንለብስ እንችላለን አንድ
ክፍል ቤት ውስጥ ውለን እያደርን ሁልጊዜ ውስጣዊ የአካል ክፍሎቻችንን ከተቃራኒ ፆታ ሚስጥር ማድረግ ከባድ ነበር።
እውነቱን ለመናገር ማንኛችንም ማን ምን እንዳየ ግድ አልነበረንም።
ግድ ሊኖረን ግን ይገባ ነበር
መጠንቀቅ ነበረብን መቼም ቢሆን የእናታችንን በአለንጋ የተተለተለ ጀርባ መርሳት አልነበረብንም።
እናታችን የተገረፈችበት ጊዜ እጅግ ሩቅ፣ የዘለአለም ያህል የራቀ ሆኖ
ተሰምቶን ነበር።
አሁን እስካለሁበት አስራዎቹ የእድሜ ክልል ድረስ አንድም ቀን የራሴን እርቃን ሙሉ በሙሉ አይቼው አላውቅም: እርቃኗን የሆነች ሴት በስዕልም
እንኳን አይቼ አላውቅም ከእምነበረድ የተሰሩ እርቃን ሀውልቶች አይቼ የማውቅ ቢሆንም እነሱ ግን ሁሉንም አያሳዩም።
ስለዚህ እርቃኔን ለማየት መስታወት ፈለግኩ። የመድኃኒት ማስቀመጫው ቁምሳጥን ላይ ያለው መስተዋት ከፍ ብሎ የተሰቀለ ስለሆነ በደንብ አያሳይም፡ ስለዚህ ሙሉ በሙሉ እርቃን ሆኜ ራሴን ለማየት ክፍሉ ውስጥ ብቻዬን እስክሆን መጠበቅ አለብኝ ከዚያ ከመልበሻው መስታወት ፊት እርቃኔን ቆሜ እንደፈለግኩ አተኩሬ እመለከታለሁ። በራሴ ሰውነት እደሰታለሁ፣ አደንቃለሁ።
ተሳካልቶልኝ መኝታ ክፍላችን ውስጥ ያለው መስተዋት ፊት ለፊት እርቃኔን ቆምኩ የሆርሞኖች መለወጥ ያመጣው ነገር የሚገርም ነው! በእርግጠኝነት
እዚህ ስመጣ ከነበርኩት በላይ በጣም ቆንጆ ሆኛለሁ። ፊቴን፣ ፀጉሬን፣ እግሮቼን፣ እንዲሁም ደረቴን እያየሁ ነው: ከአንድ ጎን ወደ ሌላ ጎን እየተሽከረከርኩ መስታወቱ ላይ ያለውን ምስሌን እያደነቅኩ ነው። በራሴ
ተመስጫለሁ።
የሆነ ሰው ከጀርባ እየተመለከተኝ እንደሆነ ስለተሰማኝ ድንገት ስዞር ክሪስ ቁም ሳጥኑ የፈጠረው ጥላ ውስጥ ቆሞ ሲያየኝ ያዝኩት: ጣሪያው ስር ካለው
ክፍል እየመጣ ነበር እዚያ ቆሞ የነበረው ለምን ያህል ጊዜ ይሆን? ሳደርግ የነበረውን እርቃንን የማየት ብልግና አይቶ ይሆን? አምላኬ እንዳላየ ተስፋ
አለኝ:
ክሪስ በቆመበት ደንዝዟል፡ ልክ ከዚህ በፊት አይቶኝ እንደማያውቅ ሁሉ ሰማያዊ አይኖቹ ላይ የተለየ ብርሀን ይታይ ነበር፡ ምናልባት እርቃናችንን ሆነን ፀሀይ ስንሞቅ መንትዮቹም አብረውን ስለሚሆኑ ሀሳቡን ወንድማዊና ንፁህ ያደርግ ስለነበረ አፍጥጦ አያየኝም ነበር ማለት ነው።
አይኖቹ በእፍረት ቀልተው፣ ከፊቴ ወደታች ወደ ጡቶቼ ከዚያ ወደ ታች...ወደ ታች ሄደው እግሮቼ ጋ ደረሱና እንደገና በዝግታ ወደ ላይ ተመለሱ።
በፈለገ ጊዜ እንዴት ማሾፊያ እንደሚያደርገኝ ጠንቅቆ በሚያውቀው ወንድሜ
አይን አጉል ስርአት አጥባቂ ሆኜ ላለመታየት ምን ማድረግ እንዳለብኝ እርግጠኛ ባለመሆን እየተንቀጠቀጥኩ ቆምኩ፡ ከዚህ በፊት አይቼው የማላውቀው አይነት እንግዳና ትልቅ ሰው መሰለኝ፡ በሌላ በኩል ደግሞ
ሰውነቴን ለመሸፈን ብንቀሳቀስ ለማየት የተራበውን ነገር የምነጥቀው ይመስል
የደከመው፣ የፈዘዘና ግራ የተጋባ ይመስል ነበር።
እዚያው እንደተገተረ ሰአቱም የቆመ ይመስል ነበር። እኔም አይኖቹ ከኋላ መስታወት ውስጥ የሚያንፀባርቀውን ምስል በውስጣቸው ለማስቀረት ሲሞክሩ
ስመለከት እያመነታሁ “ክሪስ እባክህ ሂድ” አልኩት።
የሰማኝ አይመስልም ዝም ብሎ አፍጥጠጧል በጣም አፈርኩ ብብቴ ስር እርጥበት ተሰማኝ፡፡ ልቤም እንግዳ በሆነ ሁኔታ
መምታት ጀመረ፡ እጁን ስኳር የሚቀመጥበት ዕቃ ውስጥ ሲከት እንደተያዘ ህፃን ልጅ የሆንኩ መሰለኝ፡ ይሁንና አስተያየቱና አይኖቹ ወደ ህይወት
መለሱኝና ልቤ በሚያስፈራ ሁኔታ በከባዱ መምታት ጀመረ፡ በፍርሀት
ተሞላሁ: ለምንድነው የፈራሁት? ክሪስ እኮ ነው ለመጀመሪያ ጊዜ የምር የሆነ እፍረት ተሰማኝ፡ ከዚያ ፈጠን ብዬ ያወለቅኩትን
ቀሚሴን ብድግ አደረግኩ: በዚህ ራሴን መከለልና እንዲሄድ መንገር እችላለሁ።
“ተይ” አለኝ፡ ቀሚሱን በእጄ እንደያዝኩ
“አንተኮ…” ተንተባተብኩ የበለጠ ተንቀጠቀጥኩ፡
“አውቃለሁ ማየት እንደሌለብኝ፡ ግን ደግሞ በጣም ቆንጆ ነሽ፡ ከዚህ በፊት አይቼሽ የማውቅ ሁሉ አልመሰለኝም: አብሬሽ ውዬ እያደርኩ እንዴት እንደዚህ ቆንጆ ሆነሽ ስታድጊ አላስተዋልኩም?"
እሱን ከመመልከትና በአይኖቼ ከመለመን በቀር እንደዚህ አይነት ጥያቄ እንዴት ይመለሳል? ይሄኔ ከኋላዬ በበሩ የቁልፍ ማስገቢያ መክፈቻ ቁልፉ ሲገባ ሰማሁ። አያትየው! ከመግባቷ በፊት በፍጥነት ቀሚሴን በጭንቅላቴ
አጥልቄ ወደታች ጎተትኩት። አምላኬ! እጅጌውን ማግኘት አልቻልኩም ጭንቅላቴ በቀሚሱ ተሸፍኖ ሌላው ሰውነቴ ግን እርቃን ሆኖ ነበር። እናም አያትየው አጠገቤ ነች! ላያት ባልችልም ግን ተሰምቶኛል!
በመጨረሻ እንደምንም እጅጌውን አስገባሁና ቀሚሴን ወደታች ሳብኩት። ነገር ግን እነዚያ ግራጫ ድንጋይ አይኖቿ ውስጥ እርቃኔን በደንብ እንደተመለከተችኝ
አይቻለሁ አይኖቿን ከእኔ ላይ አንስታ ክሪስን ዘልቆ የሚወጋ በሚመስል አይነት አፈጠጠችበት፡ እንደፈዘዘ ነው። “በመጨረሻ ያዝኳችሁ! ፈጠነም ዘገየም እንደምይዛችሁ አውቅ ነበር!” አለች:
ይህ ልክ ከቅዠቶቼ እንደ አንዱ ነው... ልብስ ሳልለብስ በአያትየውና በእግዚአብሔር ፊት
ክሪስ ከቆመበት ጥግ ወጣና መልስ ለመስጠት ወደፊት ተራመደ። “ያዝሽን?
ምንድነው የያዝሽው? ምንም:”
ምንም...
ምንም...
ምንም...
የሚያስተጋባ ድምፅ፡፡ በእሷ አይን ግን ሁሉንም ነገር ስናደርግ ይዛናለች።
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
ማደግ፣ ብልህ መሆን
ልክ እንደ መጀመሪያው አመት ሁሉ ሌላኛውም አመት አለፈ እናታችን ልትጎበኘን የምትመጣበት ቀን እየቀነሰ መጣ ከስንት አንድ ጊዜ ስትመጣም
ሁሌም ከዚህ ለመውጣት ጥቂት ሳምንታት ብቻ እንደቀሩን እንድናምንና ተስፋ እንድናደርግ የሚያደርገን ቃል ትገባልናለች። በእያንዳንዱ ምሽት መጨረሻ ላይ የምናደርገው ነገር ቢኖር የቀን መቁጠሪያው ላይ በትልቁ
የኤክስ ምልክት ማድረግ ነው።
አሁን ትላልቅ ቀይ የኤክስ ምልክቶች ያሉባቸው ሶስት የቀን መቁጠሪያዎች አሉን፡ የመጀመሪያው በግማሽ ብቻ ቀይ የኤክስ ምልክት የተደረገበት ነው።
ሁለተኛው ሙሉ በሙሉ ምልክት ተደርጎበታል፡ ሶስተኛው ደግሞ ግማሹ በኤክስ ምልክት ተሞልቷል፡ እየሞተ ያለው አያታችን አሁን ስልሳ ስምንት
አመት ሆኖታል። ሁልጊዜም የመጨረሻ ትንፋሹ ነው እየተባለ እኛ በተረሳ ቦታ እየተጠባበቅን እሱ ግን አሁንም መኖሩን ቀጥሏል ስልሳ ዘጠኝ አመት
እንዲሆነው እየኖረ ይመስላል።
ሀሙስ ሀሙስ በፎክስወርዝ ቤት ውስጥ ያሉ ሠራተኞች ወደ ከተማ
የሚሄዱበት ቀን ነው፡ እኔና ክሪስቶፈር ጥቁሩ ጣራ ላይ ወጥተን ጋደም በማለት የፀሀይ ብርሃን የምናገኘውና ከጨረቃና ከኮከቦች ስር ሆነን አየር
የምንቀበለው እነሱ በሚወጡ ጊዜ ነው በጣም ከፍ ያለና አደገኛ ቢሆንም ንፁህ አየር የተጠማው ቆዳችንን ማስታገስ የምንችልበት ብቸኛ ቦታ ቢኖር ጣሪያው ብቻ ነው።
እግራችንን በጭስ ማውጫው በኩል የሁለቱ ቤቶች ጣራዎች የሚገናኙበት ጥግ ላይ ስናደርግ ደህንነት ተሰማን የተደበቅንበት ቦታ መሬት ላይ ካለው ሰው ሁሉ ይከልለናል: የአያትየው ቁጣ ገና መተግበር ስላልጀመረ እኔና
ክሪስ ግዴለሾች ሆነን ነበር መታጠቢያ ቤት የምንጠቀመው ሁሌ ተጠንቅቀን አይደለም። አንዳንዴ ልብሶቻችንን ሙሉ በሙሉ ላንለብስ እንችላለን አንድ
ክፍል ቤት ውስጥ ውለን እያደርን ሁልጊዜ ውስጣዊ የአካል ክፍሎቻችንን ከተቃራኒ ፆታ ሚስጥር ማድረግ ከባድ ነበር።
እውነቱን ለመናገር ማንኛችንም ማን ምን እንዳየ ግድ አልነበረንም።
ግድ ሊኖረን ግን ይገባ ነበር
መጠንቀቅ ነበረብን መቼም ቢሆን የእናታችንን በአለንጋ የተተለተለ ጀርባ መርሳት አልነበረብንም።
እናታችን የተገረፈችበት ጊዜ እጅግ ሩቅ፣ የዘለአለም ያህል የራቀ ሆኖ
ተሰምቶን ነበር።
አሁን እስካለሁበት አስራዎቹ የእድሜ ክልል ድረስ አንድም ቀን የራሴን እርቃን ሙሉ በሙሉ አይቼው አላውቅም: እርቃኗን የሆነች ሴት በስዕልም
እንኳን አይቼ አላውቅም ከእምነበረድ የተሰሩ እርቃን ሀውልቶች አይቼ የማውቅ ቢሆንም እነሱ ግን ሁሉንም አያሳዩም።
ስለዚህ እርቃኔን ለማየት መስታወት ፈለግኩ። የመድኃኒት ማስቀመጫው ቁምሳጥን ላይ ያለው መስተዋት ከፍ ብሎ የተሰቀለ ስለሆነ በደንብ አያሳይም፡ ስለዚህ ሙሉ በሙሉ እርቃን ሆኜ ራሴን ለማየት ክፍሉ ውስጥ ብቻዬን እስክሆን መጠበቅ አለብኝ ከዚያ ከመልበሻው መስታወት ፊት እርቃኔን ቆሜ እንደፈለግኩ አተኩሬ እመለከታለሁ። በራሴ ሰውነት እደሰታለሁ፣ አደንቃለሁ።
ተሳካልቶልኝ መኝታ ክፍላችን ውስጥ ያለው መስተዋት ፊት ለፊት እርቃኔን ቆምኩ የሆርሞኖች መለወጥ ያመጣው ነገር የሚገርም ነው! በእርግጠኝነት
እዚህ ስመጣ ከነበርኩት በላይ በጣም ቆንጆ ሆኛለሁ። ፊቴን፣ ፀጉሬን፣ እግሮቼን፣ እንዲሁም ደረቴን እያየሁ ነው: ከአንድ ጎን ወደ ሌላ ጎን እየተሽከረከርኩ መስታወቱ ላይ ያለውን ምስሌን እያደነቅኩ ነው። በራሴ
ተመስጫለሁ።
የሆነ ሰው ከጀርባ እየተመለከተኝ እንደሆነ ስለተሰማኝ ድንገት ስዞር ክሪስ ቁም ሳጥኑ የፈጠረው ጥላ ውስጥ ቆሞ ሲያየኝ ያዝኩት: ጣሪያው ስር ካለው
ክፍል እየመጣ ነበር እዚያ ቆሞ የነበረው ለምን ያህል ጊዜ ይሆን? ሳደርግ የነበረውን እርቃንን የማየት ብልግና አይቶ ይሆን? አምላኬ እንዳላየ ተስፋ
አለኝ:
ክሪስ በቆመበት ደንዝዟል፡ ልክ ከዚህ በፊት አይቶኝ እንደማያውቅ ሁሉ ሰማያዊ አይኖቹ ላይ የተለየ ብርሀን ይታይ ነበር፡ ምናልባት እርቃናችንን ሆነን ፀሀይ ስንሞቅ መንትዮቹም አብረውን ስለሚሆኑ ሀሳቡን ወንድማዊና ንፁህ ያደርግ ስለነበረ አፍጥጦ አያየኝም ነበር ማለት ነው።
አይኖቹ በእፍረት ቀልተው፣ ከፊቴ ወደታች ወደ ጡቶቼ ከዚያ ወደ ታች...ወደ ታች ሄደው እግሮቼ ጋ ደረሱና እንደገና በዝግታ ወደ ላይ ተመለሱ።
በፈለገ ጊዜ እንዴት ማሾፊያ እንደሚያደርገኝ ጠንቅቆ በሚያውቀው ወንድሜ
አይን አጉል ስርአት አጥባቂ ሆኜ ላለመታየት ምን ማድረግ እንዳለብኝ እርግጠኛ ባለመሆን እየተንቀጠቀጥኩ ቆምኩ፡ ከዚህ በፊት አይቼው የማላውቀው አይነት እንግዳና ትልቅ ሰው መሰለኝ፡ በሌላ በኩል ደግሞ
ሰውነቴን ለመሸፈን ብንቀሳቀስ ለማየት የተራበውን ነገር የምነጥቀው ይመስል
የደከመው፣ የፈዘዘና ግራ የተጋባ ይመስል ነበር።
እዚያው እንደተገተረ ሰአቱም የቆመ ይመስል ነበር። እኔም አይኖቹ ከኋላ መስታወት ውስጥ የሚያንፀባርቀውን ምስል በውስጣቸው ለማስቀረት ሲሞክሩ
ስመለከት እያመነታሁ “ክሪስ እባክህ ሂድ” አልኩት።
የሰማኝ አይመስልም ዝም ብሎ አፍጥጠጧል በጣም አፈርኩ ብብቴ ስር እርጥበት ተሰማኝ፡፡ ልቤም እንግዳ በሆነ ሁኔታ
መምታት ጀመረ፡ እጁን ስኳር የሚቀመጥበት ዕቃ ውስጥ ሲከት እንደተያዘ ህፃን ልጅ የሆንኩ መሰለኝ፡ ይሁንና አስተያየቱና አይኖቹ ወደ ህይወት
መለሱኝና ልቤ በሚያስፈራ ሁኔታ በከባዱ መምታት ጀመረ፡ በፍርሀት
ተሞላሁ: ለምንድነው የፈራሁት? ክሪስ እኮ ነው ለመጀመሪያ ጊዜ የምር የሆነ እፍረት ተሰማኝ፡ ከዚያ ፈጠን ብዬ ያወለቅኩትን
ቀሚሴን ብድግ አደረግኩ: በዚህ ራሴን መከለልና እንዲሄድ መንገር እችላለሁ።
“ተይ” አለኝ፡ ቀሚሱን በእጄ እንደያዝኩ
“አንተኮ…” ተንተባተብኩ የበለጠ ተንቀጠቀጥኩ፡
“አውቃለሁ ማየት እንደሌለብኝ፡ ግን ደግሞ በጣም ቆንጆ ነሽ፡ ከዚህ በፊት አይቼሽ የማውቅ ሁሉ አልመሰለኝም: አብሬሽ ውዬ እያደርኩ እንዴት እንደዚህ ቆንጆ ሆነሽ ስታድጊ አላስተዋልኩም?"
እሱን ከመመልከትና በአይኖቼ ከመለመን በቀር እንደዚህ አይነት ጥያቄ እንዴት ይመለሳል? ይሄኔ ከኋላዬ በበሩ የቁልፍ ማስገቢያ መክፈቻ ቁልፉ ሲገባ ሰማሁ። አያትየው! ከመግባቷ በፊት በፍጥነት ቀሚሴን በጭንቅላቴ
አጥልቄ ወደታች ጎተትኩት። አምላኬ! እጅጌውን ማግኘት አልቻልኩም ጭንቅላቴ በቀሚሱ ተሸፍኖ ሌላው ሰውነቴ ግን እርቃን ሆኖ ነበር። እናም አያትየው አጠገቤ ነች! ላያት ባልችልም ግን ተሰምቶኛል!
በመጨረሻ እንደምንም እጅጌውን አስገባሁና ቀሚሴን ወደታች ሳብኩት። ነገር ግን እነዚያ ግራጫ ድንጋይ አይኖቿ ውስጥ እርቃኔን በደንብ እንደተመለከተችኝ
አይቻለሁ አይኖቿን ከእኔ ላይ አንስታ ክሪስን ዘልቆ የሚወጋ በሚመስል አይነት አፈጠጠችበት፡ እንደፈዘዘ ነው። “በመጨረሻ ያዝኳችሁ! ፈጠነም ዘገየም እንደምይዛችሁ አውቅ ነበር!” አለች:
ይህ ልክ ከቅዠቶቼ እንደ አንዱ ነው... ልብስ ሳልለብስ በአያትየውና በእግዚአብሔር ፊት
ክሪስ ከቆመበት ጥግ ወጣና መልስ ለመስጠት ወደፊት ተራመደ። “ያዝሽን?
ምንድነው የያዝሽው? ምንም:”
ምንም...
ምንም...
ምንም...
የሚያስተጋባ ድምፅ፡፡ በእሷ አይን ግን ሁሉንም ነገር ስናደርግ ይዛናለች።
#ጠላፊዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_በወንዳየሁ_ንጉሴ
በተቃራኒው ጦርነት
ወደ ተዘፈቀች አገር መመለሱ ራሱ አንድ ያልተፈታ እንቆቅልሽ ነው፡.... እዚህ ነገር ውስጥ በመጀመሪያ ደረጃ ለምን ገባሁ? አለች ልቧ
እየተሰበረ ሁን ለመጸጸት ጊዜ የለም፡ አንዴ ስለወሰንኩ ወደ ኋላ
የምልበት ነገር የለም፡፡ የተተፋ ምራቅ ተመልሶ አይዋጥም አለች መልሳ
በሆዷ ሀሳቧ አንድ ቦታ አልረጋ ብሏት፡
ማርክ እጇን ለቀም አድርጎ ሲይዝ እንዳይለቃት ፈራች፡፡ ‹አንድ ጊዜ ሃሳብሽን ለውጠሻል። አሁንም ደግመሽ መለወጥ ትችያለሽ›› አለ ለማሳመን፡፡
ከኔ ጋር አሜሪካ እንሂድና ላግባሽ፡፡ ልጆቻችንን ይዘን ባህር ዳር እንጫወታለን የምንወልዳቸው ልጆች ቴኒስ እየተጫወቱ፣ እየዋኙ ብስክሌት እየነዱ ያድጋሉ፡ ስንት ልጅ ነው መውለድ የምትፈልጊው?››
አሁን መወላወሉን አቁማለች፡፡ ‹‹ማርክ እያደረኩት ያለሁት ነገር ጥሩ አይደለም፡፡ ተመልሼ ወዳገሬ እሄዳለሁ›› አለች፡፡
ያለችውን የተቀበለ መሆኑን ተረዳች፡፡ ሁለቱም ሀዘን ገብቷቸውና የሚሰሩትን አጥተው ዓይን ላይን ይተያያሉ፡፡ የሚናገሩት ጠፍቷቸው ዝም
ዝም ብለዋል፡
ከዚያም መርቪን ቡና ቤት ውስጥ ዘው ብሎ ገባ፡፡
ዳያና ባሏ ፊቷ መጥቶ ድቅን ሲልባት ዓይኗን ማመን አቃታት፡ ልክ
አንድ የሆነ መንፈስ ፊት የቆመ ይመስል አፈጠጠችበት፡ እንዴት እዚህ ሊመጣ ቻለ? ሊሆን አይችልም
‹‹እዚህ ተገኘሽ አይደል!›› አለ መርቪን በተለመደው አስገምጋሚ ድምጹ
ዳያና ግራ ተጋባች፡፡ መርቪን እዚህ መገኘቱ አስደንቋታል፣ አስፈርቷታል፣ እፎይታ ሆኗታል፣ ቅሌት ውስጥም ከቷታል፡፡ ከሌላ ወንድ ጋር እጅ ለእጅ ተያይዛ ባሏ ሲደርስባት በደመነፍስ እጇን ከማርክ እጅ መንጭቃ አላቀቀች
ማርክም ‹‹ምንድነው እሱ?›› ሲል ጠየቃት ነገሩ ስላልገባው፡
መርቪን ሁለት እጁን ወገቡ ላይ አድርጎ ፊታቸው ተገትሯል፡
‹‹ማነው ይሄ ፊታችን የተገተረው?›› ሲል ጠየቀ ማርክ፡፡
‹‹ባሌ መርቪን ነው›› አለች በደከመ ድምጽ፡
‹‹ወይ አምላኬ!›› አለ ማርክ፡
‹‹እንዴት እዚህ ልትመጣ ቻልክ መርቪን?›› ስትል ጠየቀች ዳያና የምንተ እፍረቷን፡፡
‹‹ብራሴ አይሮፕላን በርሬ መጣሁ›› አለ ቁርጥ ባለ የአነጋገር ባህሪው:
ቆዳ ጃኬት የለበሰ ሲሆን በእጁ የሞተር ሳይክል ነጂ ቆብ አንጠልጥሏል፡፡
‹‹ኧረ ለመሆኑ እዚህ መሆናችንን እንዴት አወቅህ?›› ስትል ጥያቄዋን
ደገመች፡፡
‹በጻፍሽልኝ ደብዳቤ አሜሪካ እንደምትሄጂ ገልጸሻል፡ ወደ አሜሪካ
የሚኬደው ደግሞ በሰማይ በራሪ ጀልባ ብቻ መሆኑ ይታወቃል›› አለ በድል
አድራጊነት፡፡
የሷን ዱካ ተከታትሎ የምትሄድበትን መንገድ ገምቶ እሷ ጋ በመድረሱ ደስ እንዳለው ከገጽታው ይነበባል፡ በራሱ አይሮፕላን በርሮ ሊደርስባቸው
እንደሚችል ፈጽሞ አልጠረጠረችም፡፡ በዚህ መንገድ ተከታትሎ ስለደረሰባት ደካማ ነኝ ስትል አሰበች፡፡
ከእነሱ ትይዩ ባለው
ወንበር ላይ ተቀመጠና
‹‹እስቲ ዊስኪ አምጪልኝ›› ሲል አዘዘ አስተናጋጇን፡፡
ማርክ ብርጭቆውን አንስቶ ባንዴ ሲጨልጥ ዳያና ታየዋለች::በመጀመሪያ መርቪንን ሲያየው ተርበትብቶ ነበር፡፡ በኋላ ግን መርቪን አምባጓሮ እንደማያነሳ ሲገነዘብ ተረጋጋ ሆኖም ወምበሩን ገፋ አደረገና ከዳያና ፈንጠር ብሎ ተቀመጠ፡፡ የሰው ሚስት እጅ እንደያዝ ባሏ ከተፍ ሲልበት ሳያፍር አልቀረም፡
ዳያና ድፍረት እንዲሰጣት ብላ ከአልኮሉ ተጎነጨች፡ መርቪን በጭንቀት ያያታል። ግራ መጋባቱንና መጎዳቱን ከፊቱ ስታይ ደረቱ ውስጥ
ተወሸቂ! ተወሸቂ! አላት፡፡ ከፊቱ ምን እንደሚጠብቀው ሳያውቅ እሷን ፍለጋ
አገር አቋርጦ መጥቷል፡፡ እጇን ሰዳ በማጽናናት ሁኔታ ክንዱን ያዝ አደረገችው፡፡
ሚስቱ በውሽማዋ ፊት ያዝ ስታደርገው መርቪን ማርክን በእፍረት አየት አደረገው፡፡ ዊስኪው ሲመጣለት አንስቶ በአንድ ትንፋሽ ጨለጠው::
ማርክ በበኩሉ ዳያናን የሚያጣ መስሎት ወምበሩን ወደ እሷ አስጠጋ
ዳያና በሁኔታው ግራ ተጋባች፡፡ እንደዚህ አይነት ነገር ከዚህ በፊት
ገጥሟት አያውቅም:: ሁለቱም ሰዎች ይወዱዋታል ከሁለቱም ጋር ተኝታለች፡ ሁለቱም ይህን ያውቃሉ፡፡ በጣም አሳፋሪ፡፡ ሁለቱንም ማጽናናት ፈለገች፧ ሆኖም ፈራች፡፡ አሁን ወደ መከላከሉ አዘምብላለች። ከሁለቱም ራቅ ብላ ተቀመጠችና ‹‹መርቪን አንተን ልጎዳ ብዬ አይደለም እዚህ መዘዝ ውስጥ የገባሁት›› አለች
መርቪን ፊቱን ቅጭም አድርጎ ‹‹አምንሻለሁ›› አለ
‹‹ታምነኛለህ? የሆነውን ሁሉ ትቀበለዋለህ?›› አለች ዳያና፡፡
መርቪን ማርክ ላይ አፍጥጦ ነገር ለመፈለግ በሚመስል ሁኔታ
ተጠጋውና ውሽማሽ አሜሪካዊ ይመስላል፤ከአፍ የወደቀ ጥሬ!
የተመኘሺውን አግኘተሻል›› አለ፡፡
ማርክ አፈገፈገ፤ ምንም ቃል ሳይተነፍስ መርቪንን አፍጥጦ ያየዋል ማርክ ጠብ ፈላጊ አይነት ሰው አይደለም፡፡ ሁኔታው ግራ አጋብቶታል፡ ከዚህ በፊት ተገናኝተው ባያውቁም መርቪን ዋና ባላንጣው ነው፡፡ ማታ ማታ ዳያና አቅፋው የምትተኛው ሰው ማን ይሆን?› ሲል ራሱን ሲጠይቅ ከርሟል፡፡ አሁን ማን እንደሆነ አውቆታል። ከማርክ ጋር ሲተያይ መርቪን ስለማርክ ምንም የተጨነቀ አይመስልም፡፡
ዳያና ሁለቱን ባላንጣዎች ተመለከተቻቸው፡ ምንም የሚያመሳስላቸው ነገር የለም መርቪን ዘንካታ፣ ጠብ ያለሽ በዳቦ የሚል፣ ኮስታራና ነርቨስ ነው ማርክ
ደግሞ አጭር፣ ሽክ ያለ፣ ነቃ ያለና ስው ሲናገር ጆሮ የሚሰጥ ሰው ነው ማርክ
አንድ ቀን ይህን ታሪክ በኮመዲ ስራው ውስጥ አካቶ ሳያቀርበው አይቀርም ስትል ዳያና አሰበች፡
አይኖቿ እምባ አንቆርዝዘዋል፡ መሃረብ አውጥታ ንፍጧን ተናፈጠች
«ልክስክስ መሆኔን አውቄዋለሁ›› አለች፡
‹‹ልክስክስ!›› ሲል አሾፈ መርቪን ቃሉ አንሶበት፡፡ ‹‹በጣም የጅል ስራ
ዳያና ባሏ በተናገረው ተሸማቀቀች፡ ብዙ ጊዜ ስድቡ አፏን እንዳዘጋት
ነው፡፡ ዛሬ ግን ከስድብም በላይ ይገባታል፡፡
አስተናጋጇና ጥግ ተቀምጠው መጠጣቸውን የሚኮመኩሙት ሁለት
ሰዎች ሁሉን ነገር ጣጥለው ትእይንቱን በጉጉት ይመለከታሉ፤ ‹‹ምን ይከተል ይሆን?› እያሉ።
መርቪን አስተናጋጇን ጠራና ‹የኔ ቆንጆ ሳንድዊች ብታመጪልኝ›› ሲል አዘዛት እሷም ‹‹እሺ የኔ ጌታ›› አለችው በፍጹም ትህትና፡፡
አስተናጋጆች መርቪንን ይወዱታል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ኑሮ እያስጠላኝ መጥቷል ትንሽ ደስታ አገኝ ብዬ ነው አሜሪካ ለመሄድ የወሰንኩት›› አለች ዳያና፡፡
"ትንሽ ደስታ አገኝ ብዬ ነው ያልሽው! አሜሪካ ጓደኛ የለሽ፣ ዘመድ የለሽ፣ ቤት የለሽ. . .አዕምሮሽ ማሰብ አቆመ እንዴ!›› አለ መርቪን፡፡
ዳያና መርቪን ስለደረሰላት አምላኳን ብታመሰግንም እንዳይጨክንባት
ፈርታለች ማርክ በእጁ ትከሻዋን ነካ አደረገና ‹‹ለምንድነው አሜሪካ ደስታ
የማታገኚው፧ እዚያ ለመሄድ ማሰብሽ ስህተት አይደለም›› አላት ድምጹን
ዝቅ አድርጎ፡፡
መርቪንን ከዚህ በላይ ማናደዱ አስፈርቷታል፡፡ ምናልባትም ትቷት
ተመልሶ ይሄድ ይሆናል፡ በማርክና በሉሉ ቤል ፊት ‹‹አልፈልግሽም›› ብሎ
ቢላት እንዴት እንደሚያበሳጫት መገመት አስቸጋሪ ነው፡፡ አያደርግም
አይባልም፡፡ መርቪን ተከትሏት ባይመጣ ጥሩ ነበር፡፡ ይህ ማለት ደግሞ
እዚሁ አንድ ውሳኔ ላይ መድረስ ይኖርበታል፡፡ ከዚያም ብርጭቆዋን አነሳችና ከንፈሯን አስነክታ ‹‹ይህን መጠጥ አልፈልግም›› ብላ መልሳ አስቀመጠችው
በዚህ ጊዜ ማርክ ‹‹ሻይ ላምጣልሽ?›› አላት፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_በወንዳየሁ_ንጉሴ
በተቃራኒው ጦርነት
ወደ ተዘፈቀች አገር መመለሱ ራሱ አንድ ያልተፈታ እንቆቅልሽ ነው፡.... እዚህ ነገር ውስጥ በመጀመሪያ ደረጃ ለምን ገባሁ? አለች ልቧ
እየተሰበረ ሁን ለመጸጸት ጊዜ የለም፡ አንዴ ስለወሰንኩ ወደ ኋላ
የምልበት ነገር የለም፡፡ የተተፋ ምራቅ ተመልሶ አይዋጥም አለች መልሳ
በሆዷ ሀሳቧ አንድ ቦታ አልረጋ ብሏት፡
ማርክ እጇን ለቀም አድርጎ ሲይዝ እንዳይለቃት ፈራች፡፡ ‹አንድ ጊዜ ሃሳብሽን ለውጠሻል። አሁንም ደግመሽ መለወጥ ትችያለሽ›› አለ ለማሳመን፡፡
ከኔ ጋር አሜሪካ እንሂድና ላግባሽ፡፡ ልጆቻችንን ይዘን ባህር ዳር እንጫወታለን የምንወልዳቸው ልጆች ቴኒስ እየተጫወቱ፣ እየዋኙ ብስክሌት እየነዱ ያድጋሉ፡ ስንት ልጅ ነው መውለድ የምትፈልጊው?››
አሁን መወላወሉን አቁማለች፡፡ ‹‹ማርክ እያደረኩት ያለሁት ነገር ጥሩ አይደለም፡፡ ተመልሼ ወዳገሬ እሄዳለሁ›› አለች፡፡
ያለችውን የተቀበለ መሆኑን ተረዳች፡፡ ሁለቱም ሀዘን ገብቷቸውና የሚሰሩትን አጥተው ዓይን ላይን ይተያያሉ፡፡ የሚናገሩት ጠፍቷቸው ዝም
ዝም ብለዋል፡
ከዚያም መርቪን ቡና ቤት ውስጥ ዘው ብሎ ገባ፡፡
ዳያና ባሏ ፊቷ መጥቶ ድቅን ሲልባት ዓይኗን ማመን አቃታት፡ ልክ
አንድ የሆነ መንፈስ ፊት የቆመ ይመስል አፈጠጠችበት፡ እንዴት እዚህ ሊመጣ ቻለ? ሊሆን አይችልም
‹‹እዚህ ተገኘሽ አይደል!›› አለ መርቪን በተለመደው አስገምጋሚ ድምጹ
ዳያና ግራ ተጋባች፡፡ መርቪን እዚህ መገኘቱ አስደንቋታል፣ አስፈርቷታል፣ እፎይታ ሆኗታል፣ ቅሌት ውስጥም ከቷታል፡፡ ከሌላ ወንድ ጋር እጅ ለእጅ ተያይዛ ባሏ ሲደርስባት በደመነፍስ እጇን ከማርክ እጅ መንጭቃ አላቀቀች
ማርክም ‹‹ምንድነው እሱ?›› ሲል ጠየቃት ነገሩ ስላልገባው፡
መርቪን ሁለት እጁን ወገቡ ላይ አድርጎ ፊታቸው ተገትሯል፡
‹‹ማነው ይሄ ፊታችን የተገተረው?›› ሲል ጠየቀ ማርክ፡፡
‹‹ባሌ መርቪን ነው›› አለች በደከመ ድምጽ፡
‹‹ወይ አምላኬ!›› አለ ማርክ፡
‹‹እንዴት እዚህ ልትመጣ ቻልክ መርቪን?›› ስትል ጠየቀች ዳያና የምንተ እፍረቷን፡፡
‹‹ብራሴ አይሮፕላን በርሬ መጣሁ›› አለ ቁርጥ ባለ የአነጋገር ባህሪው:
ቆዳ ጃኬት የለበሰ ሲሆን በእጁ የሞተር ሳይክል ነጂ ቆብ አንጠልጥሏል፡፡
‹‹ኧረ ለመሆኑ እዚህ መሆናችንን እንዴት አወቅህ?›› ስትል ጥያቄዋን
ደገመች፡፡
‹በጻፍሽልኝ ደብዳቤ አሜሪካ እንደምትሄጂ ገልጸሻል፡ ወደ አሜሪካ
የሚኬደው ደግሞ በሰማይ በራሪ ጀልባ ብቻ መሆኑ ይታወቃል›› አለ በድል
አድራጊነት፡፡
የሷን ዱካ ተከታትሎ የምትሄድበትን መንገድ ገምቶ እሷ ጋ በመድረሱ ደስ እንዳለው ከገጽታው ይነበባል፡ በራሱ አይሮፕላን በርሮ ሊደርስባቸው
እንደሚችል ፈጽሞ አልጠረጠረችም፡፡ በዚህ መንገድ ተከታትሎ ስለደረሰባት ደካማ ነኝ ስትል አሰበች፡፡
ከእነሱ ትይዩ ባለው
ወንበር ላይ ተቀመጠና
‹‹እስቲ ዊስኪ አምጪልኝ›› ሲል አዘዘ አስተናጋጇን፡፡
ማርክ ብርጭቆውን አንስቶ ባንዴ ሲጨልጥ ዳያና ታየዋለች::በመጀመሪያ መርቪንን ሲያየው ተርበትብቶ ነበር፡፡ በኋላ ግን መርቪን አምባጓሮ እንደማያነሳ ሲገነዘብ ተረጋጋ ሆኖም ወምበሩን ገፋ አደረገና ከዳያና ፈንጠር ብሎ ተቀመጠ፡፡ የሰው ሚስት እጅ እንደያዝ ባሏ ከተፍ ሲልበት ሳያፍር አልቀረም፡
ዳያና ድፍረት እንዲሰጣት ብላ ከአልኮሉ ተጎነጨች፡ መርቪን በጭንቀት ያያታል። ግራ መጋባቱንና መጎዳቱን ከፊቱ ስታይ ደረቱ ውስጥ
ተወሸቂ! ተወሸቂ! አላት፡፡ ከፊቱ ምን እንደሚጠብቀው ሳያውቅ እሷን ፍለጋ
አገር አቋርጦ መጥቷል፡፡ እጇን ሰዳ በማጽናናት ሁኔታ ክንዱን ያዝ አደረገችው፡፡
ሚስቱ በውሽማዋ ፊት ያዝ ስታደርገው መርቪን ማርክን በእፍረት አየት አደረገው፡፡ ዊስኪው ሲመጣለት አንስቶ በአንድ ትንፋሽ ጨለጠው::
ማርክ በበኩሉ ዳያናን የሚያጣ መስሎት ወምበሩን ወደ እሷ አስጠጋ
ዳያና በሁኔታው ግራ ተጋባች፡፡ እንደዚህ አይነት ነገር ከዚህ በፊት
ገጥሟት አያውቅም:: ሁለቱም ሰዎች ይወዱዋታል ከሁለቱም ጋር ተኝታለች፡ ሁለቱም ይህን ያውቃሉ፡፡ በጣም አሳፋሪ፡፡ ሁለቱንም ማጽናናት ፈለገች፧ ሆኖም ፈራች፡፡ አሁን ወደ መከላከሉ አዘምብላለች። ከሁለቱም ራቅ ብላ ተቀመጠችና ‹‹መርቪን አንተን ልጎዳ ብዬ አይደለም እዚህ መዘዝ ውስጥ የገባሁት›› አለች
መርቪን ፊቱን ቅጭም አድርጎ ‹‹አምንሻለሁ›› አለ
‹‹ታምነኛለህ? የሆነውን ሁሉ ትቀበለዋለህ?›› አለች ዳያና፡፡
መርቪን ማርክ ላይ አፍጥጦ ነገር ለመፈለግ በሚመስል ሁኔታ
ተጠጋውና ውሽማሽ አሜሪካዊ ይመስላል፤ከአፍ የወደቀ ጥሬ!
የተመኘሺውን አግኘተሻል›› አለ፡፡
ማርክ አፈገፈገ፤ ምንም ቃል ሳይተነፍስ መርቪንን አፍጥጦ ያየዋል ማርክ ጠብ ፈላጊ አይነት ሰው አይደለም፡፡ ሁኔታው ግራ አጋብቶታል፡ ከዚህ በፊት ተገናኝተው ባያውቁም መርቪን ዋና ባላንጣው ነው፡፡ ማታ ማታ ዳያና አቅፋው የምትተኛው ሰው ማን ይሆን?› ሲል ራሱን ሲጠይቅ ከርሟል፡፡ አሁን ማን እንደሆነ አውቆታል። ከማርክ ጋር ሲተያይ መርቪን ስለማርክ ምንም የተጨነቀ አይመስልም፡፡
ዳያና ሁለቱን ባላንጣዎች ተመለከተቻቸው፡ ምንም የሚያመሳስላቸው ነገር የለም መርቪን ዘንካታ፣ ጠብ ያለሽ በዳቦ የሚል፣ ኮስታራና ነርቨስ ነው ማርክ
ደግሞ አጭር፣ ሽክ ያለ፣ ነቃ ያለና ስው ሲናገር ጆሮ የሚሰጥ ሰው ነው ማርክ
አንድ ቀን ይህን ታሪክ በኮመዲ ስራው ውስጥ አካቶ ሳያቀርበው አይቀርም ስትል ዳያና አሰበች፡
አይኖቿ እምባ አንቆርዝዘዋል፡ መሃረብ አውጥታ ንፍጧን ተናፈጠች
«ልክስክስ መሆኔን አውቄዋለሁ›› አለች፡
‹‹ልክስክስ!›› ሲል አሾፈ መርቪን ቃሉ አንሶበት፡፡ ‹‹በጣም የጅል ስራ
ዳያና ባሏ በተናገረው ተሸማቀቀች፡ ብዙ ጊዜ ስድቡ አፏን እንዳዘጋት
ነው፡፡ ዛሬ ግን ከስድብም በላይ ይገባታል፡፡
አስተናጋጇና ጥግ ተቀምጠው መጠጣቸውን የሚኮመኩሙት ሁለት
ሰዎች ሁሉን ነገር ጣጥለው ትእይንቱን በጉጉት ይመለከታሉ፤ ‹‹ምን ይከተል ይሆን?› እያሉ።
መርቪን አስተናጋጇን ጠራና ‹የኔ ቆንጆ ሳንድዊች ብታመጪልኝ›› ሲል አዘዛት እሷም ‹‹እሺ የኔ ጌታ›› አለችው በፍጹም ትህትና፡፡
አስተናጋጆች መርቪንን ይወዱታል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ኑሮ እያስጠላኝ መጥቷል ትንሽ ደስታ አገኝ ብዬ ነው አሜሪካ ለመሄድ የወሰንኩት›› አለች ዳያና፡፡
"ትንሽ ደስታ አገኝ ብዬ ነው ያልሽው! አሜሪካ ጓደኛ የለሽ፣ ዘመድ የለሽ፣ ቤት የለሽ. . .አዕምሮሽ ማሰብ አቆመ እንዴ!›› አለ መርቪን፡፡
ዳያና መርቪን ስለደረሰላት አምላኳን ብታመሰግንም እንዳይጨክንባት
ፈርታለች ማርክ በእጁ ትከሻዋን ነካ አደረገና ‹‹ለምንድነው አሜሪካ ደስታ
የማታገኚው፧ እዚያ ለመሄድ ማሰብሽ ስህተት አይደለም›› አላት ድምጹን
ዝቅ አድርጎ፡፡
መርቪንን ከዚህ በላይ ማናደዱ አስፈርቷታል፡፡ ምናልባትም ትቷት
ተመልሶ ይሄድ ይሆናል፡ በማርክና በሉሉ ቤል ፊት ‹‹አልፈልግሽም›› ብሎ
ቢላት እንዴት እንደሚያበሳጫት መገመት አስቸጋሪ ነው፡፡ አያደርግም
አይባልም፡፡ መርቪን ተከትሏት ባይመጣ ጥሩ ነበር፡፡ ይህ ማለት ደግሞ
እዚሁ አንድ ውሳኔ ላይ መድረስ ይኖርበታል፡፡ ከዚያም ብርጭቆዋን አነሳችና ከንፈሯን አስነክታ ‹‹ይህን መጠጥ አልፈልግም›› ብላ መልሳ አስቀመጠችው
በዚህ ጊዜ ማርክ ‹‹ሻይ ላምጣልሽ?›› አላት፡፡
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////
መቼስ የሀገራችን የሚካሄድ ትንሽም ሆነ ትላልቅ ዝግጅቶች ተሳስተው እንኳን ከመዝረክረክ አያመልጡም።እና ይጀመራል ከተባለበት ሰዓት 40 ደቂቃ አርፈደው ጀመሩ...ዝግጅቱ ከተጀመረ ከአንድ ሰአት በኃላ የሽልማቱ ፕሮግራም ተጀመረ ። እንደአጋጣሚ ሽልማቱ ከታችኛው ክፍል ነው የተጀመረው...
‹‹ አማካይ ውጤት 97.5 በማምጣት ከሁለተኛ-ለ ክፍል እንዲሁም ከአጠቃላዩ ሶስቱም የሁለተኛ ክፍል ተማሪዎች አንደኛ በመውጣት ልዩ ተሸላሚያችን ተአምር እዬብ ..››አካባቢው በጭብጨባ ተነጋ.. ቤተሰቦቼ ሁሉም ከተቀመጡበት ተነስተው አካባቢውን ቀወጡት..፡፡በስሜት ካሜራዬን ደቅኜ ወደፊት ተጠጋሁ .በተቻለኝ መጠን ልጄን በካሜራዬ ለማደን ሙከራዬን ቀጠልኩ...፡፡የእኔ ልዕልት እየተንሳፈፈች ወደመድረክ
እየቀረበች ነው...፡፡
እናትዬውና አክስቶቾ ሰፌድ የሚያካክል አይፓዳቸውን ቀስረው ከኃላ ተከተሏት...፡፡መድረክ ላይ ወጥታ ከክብር እንግዳው ሽልማቷን ስትቀበል ስመለከት እንባዬን ከመርገፍ ላግደው አልቻልኩም...የራስ ልጅ እንዲህ በክብር አደባባይ ላይ ብዙዎችን በአድናቆት ሲያስጨበጭብ ማየት ለአንድ ወላጅ ምን አይነት ልብን በደስታ የሚያጥለቀልቅ መባረክ እንደሆነ እድሉ የገጠመው ወላጅ ብቻ ነው የሚያውቀው።
እኔም በጊዜው እዚህ መድረክ ላይ እስኪሰለቸኝ ድረስ በተደጋጋሚ በመውጣት ተሸልሜበታለሁ...በዛን ወቅት ግን እቤተሠቧቼ አሁን እኔ የተሠማኝን አይነት ልዩ ስሜት እንደሚሰማቸው ገምቼ አላውቅም ነበር...፡፡ልጄ ሽልማቷን በአየር ላይ እያወዛወዘች ህዝብን አስጨበጨበች።ከዛ በእኔ አቅጣጫ ስትደርስ ሽልማቱን ባለበት አቆመችና ትኩር ብላ ወደእኔ ተመለከተች፤ እኔም በደስታ እጄን እስኪያመኝ በአየር ላይ አወናጨፍኩት..ከዛ ለሌላ ተሸላሚ መድረኩን ለቃ ስትወርድ እኔም ፈጠን ብዬ በፊት ወደነበኩበት ቦታ ተመለስኩ…፡፡
ዘመዶቾ ከበዋት ያውካካሉ እያንዳንዱ በየተራ አብረዋት ፎቶ ይነሳሉ…፡፡ቀናሁ… በጣም ቀናሁ…..እኔም ከመሀከላቸው መገኘት ነበረብኝ፡፡.ቁጭ አልኩና በሀሳብ ሰመጥኩ፡፡.አይኖቼ እንባ አግተዋል….፡፡ትንሽ ፊት ሚያሳየኝ ወይ ሚነካካኝ ነገር ባገኝ እዘረግፈዋለሁ….፡፡
አንድ ነገር ተከሻዬን ከኃላዬ ነካኝ…..ከሀሳብ ባነንኩና ዞር ስል ልጄ ነች…፡፡
‹‹አባዬ ተከተለኝ›› ብላ ብን ብላ ወደኃላ ሄደችና ከእኔ ጀርባ ባለ የመማሪያ ክፍል ግድግዳ ኮርነር ተጠመዘዘች፡፡ፊቴን ወደ ፊትለፊት ላኩ ፡፡ወደዘመዶቼ፡፡ በራሳቸው ነገር ተጠምደው ያውካካሉ.፡፡ፈጠን አልኩና ተንቀሳቀስኩ፡፡ ልጄ ወደሄደችበት በፍጥት ሄድኩ ፡፡እንደተጠመዝኩ አገኘኋት፡፡ እጄን ያዘችና በፈጣን እርምጃ ወደፊት መጓዝ ጀመረች.፡፡ዝምብዬ ተጎተትኩላት…፡፡ምን ልታደርግ እንደሆነ አልገባኝም…፡፡ክፍሉን አለፈችና ሌላ ጠባብ መንገድ ውስጥ ይዛኝ ገባች፡፡ጥቂት ተራመድንና በፅድና በአትክልት የደመቀ የት/ቤቱ መናፈሻ ውስጥ ገባን፡፡ ምትፈልግበት ቦታ ከደረሰች በኃላ አዲስ እንዳገኘችኝ ነገር ተጠመጠመችብኝ፡፡
‹‹እንዳያዩን ብዬ እኮ ነው እዚህ ይዤህ የመጣሁት››
‹‹አይፈልጉሽም?››
‹‹ቶሎ እመለሳለሁ… ሽንት ቤት ብያቸው ነው የመጣሁት››
‹‹የእኔ ብልጥ በጣም ነው የኮራሁብሽ….፡፡.በጣም ነው ያስደሰሽኝ ….፡፡እንቺ ይህቺ ያዘጋጀውልሽ ትንሽ ስጦታ ነች›አልኩና በሚያብረቀርቅ የስጦታ ወረቀት አምሮ የተጠቀለ እና በፔስታል ያለ ስጦታዬን ሰጣኋት..
‹‹አባዬ ምንድነው? ልክፈተው?››
‹አይ እቤት ብቻሽን ስትሆኚ ተከፍቺዋለሽ›
‹‹እሺ አበባዬ አመሰግናለሁ…በጣም አስደስተህኛል›ብላ ወደታች አስጎንብሳ ጉንጬን ሳመቺኝና
‹አባዬ ፎቶ እንነሳና ልሂዳ..›
‹‹እሺ …እሺ›› አልኩና የያዝኩትን ካሜራ በራሱ እንዲያነሳ አጀስት በማድረግ አንድ አምስት የሚሆኑ ፎቶዎች ተነሳን፡፡
‹‹አሁን ልሂድ አባዬ››
‹የእኔ ማር ሂጀ …አሁን እኔም ወደአዲስአባ ልመለስ…ማታ ብቻሽን ስትሆኚ ደውይልኝ››
‹‹እሺ አባዬ…ሌላ ጊዜም መጥተህ ታየኛለህ አይደል.?››
‹‹የእኔ ማር ከአሁን ወዲህ አንቺን ሳላይ ብዙ ጊዜ መቆየት ስለማልችል .አዎ መጥቼ አይሻለሁ›
አገላብጬ ሳምኳት.እሷም ሳመችኝና እንዳመጣጧ እየተሹለከለክች ብን ብላ ሄደች.፡፡እኔ እዛ መናፈሻ ውስጥ ለታሪክ ድምቀት የታነፀ በድን ሀውልት መስዬ ለረጅም ደቂቃዎች ቆምኩ፡፡ አሁን እንደቅድሙ የተንጠለጠለውን እንባዬን ገድቤ ማቆየት አልቻልኩም….ዝርግፍ ብሎ ሲንጠባጠብ እኔም ልክ እንደሌላ ሰው በትዝብት እያየሁት ነው፡፡ከዛ በኃላማ ወደዝግጅቱም አልተመለስኩም፡፡ ምን ላደርግ…?ሹልክ ብዬ ግቢውን ለቅቄ ወጣሁና ወደመናኸሪያ ነው ያመራሁት.፡፡ከዛ ቀጥታ ወደ አዲስአባዬ ፡፡
✨ይቀጥላል✨
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////
መቼስ የሀገራችን የሚካሄድ ትንሽም ሆነ ትላልቅ ዝግጅቶች ተሳስተው እንኳን ከመዝረክረክ አያመልጡም።እና ይጀመራል ከተባለበት ሰዓት 40 ደቂቃ አርፈደው ጀመሩ...ዝግጅቱ ከተጀመረ ከአንድ ሰአት በኃላ የሽልማቱ ፕሮግራም ተጀመረ ። እንደአጋጣሚ ሽልማቱ ከታችኛው ክፍል ነው የተጀመረው...
‹‹ አማካይ ውጤት 97.5 በማምጣት ከሁለተኛ-ለ ክፍል እንዲሁም ከአጠቃላዩ ሶስቱም የሁለተኛ ክፍል ተማሪዎች አንደኛ በመውጣት ልዩ ተሸላሚያችን ተአምር እዬብ ..››አካባቢው በጭብጨባ ተነጋ.. ቤተሰቦቼ ሁሉም ከተቀመጡበት ተነስተው አካባቢውን ቀወጡት..፡፡በስሜት ካሜራዬን ደቅኜ ወደፊት ተጠጋሁ .በተቻለኝ መጠን ልጄን በካሜራዬ ለማደን ሙከራዬን ቀጠልኩ...፡፡የእኔ ልዕልት እየተንሳፈፈች ወደመድረክ
እየቀረበች ነው...፡፡
እናትዬውና አክስቶቾ ሰፌድ የሚያካክል አይፓዳቸውን ቀስረው ከኃላ ተከተሏት...፡፡መድረክ ላይ ወጥታ ከክብር እንግዳው ሽልማቷን ስትቀበል ስመለከት እንባዬን ከመርገፍ ላግደው አልቻልኩም...የራስ ልጅ እንዲህ በክብር አደባባይ ላይ ብዙዎችን በአድናቆት ሲያስጨበጭብ ማየት ለአንድ ወላጅ ምን አይነት ልብን በደስታ የሚያጥለቀልቅ መባረክ እንደሆነ እድሉ የገጠመው ወላጅ ብቻ ነው የሚያውቀው።
እኔም በጊዜው እዚህ መድረክ ላይ እስኪሰለቸኝ ድረስ በተደጋጋሚ በመውጣት ተሸልሜበታለሁ...በዛን ወቅት ግን እቤተሠቧቼ አሁን እኔ የተሠማኝን አይነት ልዩ ስሜት እንደሚሰማቸው ገምቼ አላውቅም ነበር...፡፡ልጄ ሽልማቷን በአየር ላይ እያወዛወዘች ህዝብን አስጨበጨበች።ከዛ በእኔ አቅጣጫ ስትደርስ ሽልማቱን ባለበት አቆመችና ትኩር ብላ ወደእኔ ተመለከተች፤ እኔም በደስታ እጄን እስኪያመኝ በአየር ላይ አወናጨፍኩት..ከዛ ለሌላ ተሸላሚ መድረኩን ለቃ ስትወርድ እኔም ፈጠን ብዬ በፊት ወደነበኩበት ቦታ ተመለስኩ…፡፡
ዘመዶቾ ከበዋት ያውካካሉ እያንዳንዱ በየተራ አብረዋት ፎቶ ይነሳሉ…፡፡ቀናሁ… በጣም ቀናሁ…..እኔም ከመሀከላቸው መገኘት ነበረብኝ፡፡.ቁጭ አልኩና በሀሳብ ሰመጥኩ፡፡.አይኖቼ እንባ አግተዋል….፡፡ትንሽ ፊት ሚያሳየኝ ወይ ሚነካካኝ ነገር ባገኝ እዘረግፈዋለሁ….፡፡
አንድ ነገር ተከሻዬን ከኃላዬ ነካኝ…..ከሀሳብ ባነንኩና ዞር ስል ልጄ ነች…፡፡
‹‹አባዬ ተከተለኝ›› ብላ ብን ብላ ወደኃላ ሄደችና ከእኔ ጀርባ ባለ የመማሪያ ክፍል ግድግዳ ኮርነር ተጠመዘዘች፡፡ፊቴን ወደ ፊትለፊት ላኩ ፡፡ወደዘመዶቼ፡፡ በራሳቸው ነገር ተጠምደው ያውካካሉ.፡፡ፈጠን አልኩና ተንቀሳቀስኩ፡፡ ልጄ ወደሄደችበት በፍጥት ሄድኩ ፡፡እንደተጠመዝኩ አገኘኋት፡፡ እጄን ያዘችና በፈጣን እርምጃ ወደፊት መጓዝ ጀመረች.፡፡ዝምብዬ ተጎተትኩላት…፡፡ምን ልታደርግ እንደሆነ አልገባኝም…፡፡ክፍሉን አለፈችና ሌላ ጠባብ መንገድ ውስጥ ይዛኝ ገባች፡፡ጥቂት ተራመድንና በፅድና በአትክልት የደመቀ የት/ቤቱ መናፈሻ ውስጥ ገባን፡፡ ምትፈልግበት ቦታ ከደረሰች በኃላ አዲስ እንዳገኘችኝ ነገር ተጠመጠመችብኝ፡፡
‹‹እንዳያዩን ብዬ እኮ ነው እዚህ ይዤህ የመጣሁት››
‹‹አይፈልጉሽም?››
‹‹ቶሎ እመለሳለሁ… ሽንት ቤት ብያቸው ነው የመጣሁት››
‹‹የእኔ ብልጥ በጣም ነው የኮራሁብሽ….፡፡.በጣም ነው ያስደሰሽኝ ….፡፡እንቺ ይህቺ ያዘጋጀውልሽ ትንሽ ስጦታ ነች›አልኩና በሚያብረቀርቅ የስጦታ ወረቀት አምሮ የተጠቀለ እና በፔስታል ያለ ስጦታዬን ሰጣኋት..
‹‹አባዬ ምንድነው? ልክፈተው?››
‹አይ እቤት ብቻሽን ስትሆኚ ተከፍቺዋለሽ›
‹‹እሺ አበባዬ አመሰግናለሁ…በጣም አስደስተህኛል›ብላ ወደታች አስጎንብሳ ጉንጬን ሳመቺኝና
‹አባዬ ፎቶ እንነሳና ልሂዳ..›
‹‹እሺ …እሺ›› አልኩና የያዝኩትን ካሜራ በራሱ እንዲያነሳ አጀስት በማድረግ አንድ አምስት የሚሆኑ ፎቶዎች ተነሳን፡፡
‹‹አሁን ልሂድ አባዬ››
‹የእኔ ማር ሂጀ …አሁን እኔም ወደአዲስአባ ልመለስ…ማታ ብቻሽን ስትሆኚ ደውይልኝ››
‹‹እሺ አባዬ…ሌላ ጊዜም መጥተህ ታየኛለህ አይደል.?››
‹‹የእኔ ማር ከአሁን ወዲህ አንቺን ሳላይ ብዙ ጊዜ መቆየት ስለማልችል .አዎ መጥቼ አይሻለሁ›
አገላብጬ ሳምኳት.እሷም ሳመችኝና እንዳመጣጧ እየተሹለከለክች ብን ብላ ሄደች.፡፡እኔ እዛ መናፈሻ ውስጥ ለታሪክ ድምቀት የታነፀ በድን ሀውልት መስዬ ለረጅም ደቂቃዎች ቆምኩ፡፡ አሁን እንደቅድሙ የተንጠለጠለውን እንባዬን ገድቤ ማቆየት አልቻልኩም….ዝርግፍ ብሎ ሲንጠባጠብ እኔም ልክ እንደሌላ ሰው በትዝብት እያየሁት ነው፡፡ከዛ በኃላማ ወደዝግጅቱም አልተመለስኩም፡፡ ምን ላደርግ…?ሹልክ ብዬ ግቢውን ለቅቄ ወጣሁና ወደመናኸሪያ ነው ያመራሁት.፡፡ከዛ ቀጥታ ወደ አዲስአባዬ ፡፡
✨ይቀጥላል✨
#ባል_አስይዞ_ቁማር
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
በእቅዷ መሰረት ኩሪፍቱ ይገኛሉ….ትናንትና ከመሸ ነው የገቡት፡፡ከጥዋቱ ሁለተ ሰዓት አካባቢ ሆኗል..መኝታውን ለቆ ተነስቶ ክፍል ውስጥ ሲንጎራደድ ከጀመረ 30 ደቂቃ ያህል አልፎታል አንዴ መታጠቢያ ቤት ይገባል…አንዴ ወደበረንዳ ይወጣል…እኔ እየሰማው ቢሆንም አንቅልፍ ውስጥ እንዳለ ሰው አድፍጣ ዝም….መታጠቢያ ቤት ሲገባ ፈጠን ብላ ተነሳችና ከቦርሳዋ ውስጥ መከታተያ ካሜራዋን በማውጣት ወንበር ላይ የተንጠለጠለው ጃኬቱ ላይ አንዳይታይ አድርጋ ኮሌታው አካባቢ አጣበቀችውና ቶሎ ብላ ወደመኝታዋ ተመለሰች …በስተመጨረሻ ትግስት አጥቶ ,..ፈራ ተባ እያለው ወደአልጋው ቀረበና ትከሻዋን ይዞ እየነቀቃት…..
‹‹ፍቅር ተኝተሸ ቀረሸ እኮ …በጣም እርቦኛል..ተነሽ ቁርስ እንብላ››አላት
‹‹ተወኝ በናትህ እንቅልፌን አልጠገብኩም…ጊፍቲን ቀስቅሳትና አብራችሁ ብሉ››
‹‹ተይ እንጂ ፍቅር..››
‹‹እየረበሽከኝ አኮ ነው..በፈጣሪ ተወኝ››ተነጫነጨችበት፡፡
‹‹እሺ.ስትነሺ ተቀላቀይን›› ብሎ ዘረጥ ዘረጥ እያለ ክፍሉን ለቆ ለመውጣት ወደበሩ መራመድ ጀመረ…ፍፁም ንቁ ሁና ከአንገቷ ቀና አለችና..
‹‹እንዴ?››አለችው፡፡
በሁኔታዋ ግራ በመጋባት‹‹ምነው ልጠብቅሽ ?ትመጪያለሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አይ አልመጣም ግን የውጩን ቅዝቃዜ አታየውም እንዴ…?››
‹‹እና ምን ?
ተኝተን እንዋል?››
ምን ለማለት እንደፈለገች አልተገለፀለትም፡፡
‹‹አላልኩም..በኃላ ኩሪፍቱ ወስደሽ ብርድ አስመታሺኝ እያልክ ስትወቅሰኝ እንዳትከርም….ጃኬትህን ለብሰህ ውጣ››
‹‹አረ ተይ… እንዲህ ተመችቶኛል››
‹‹አይሆን …ነገርኩህ እኮ….››
‹‹አንቺ ደግሞ በሚሆነውማ በማይሆነውም መጨነቅ ታበዢዋለሽ…እኔ እኮ እስፖርተኛ ነኝ የምን በርድ ነው››እያለ በማጉረምረም ወደኃላ ተመልሶ ጃኬቱን ከተንጠለጠለበት ወንበር በማንሳት እየለበሰ ወጥቶ ሄደ…ፈገግ አለች…‹‹አይ ወንዶች ነገረ ሰራቸው እኮ የህፃን ነው..በቀላሉ የሚታለሉ ገራገር ፍጥሮች… ሲመጣባቸውም እንደዛው ደንባራ አውሬዎች ናቸው…›አለችና …ከተኛችበት ተስፈንጥራ በመነሳት ክፍሉን ከውስጥ ቆለፈችው…ከዛ ላፕቶፖን አወጣችና ከፈተችው.. በገዛ እጮኛዋ ደረት ላይ የሰካችውን ካሜራ ጋር የሚየገናኝውን አፕ ቁልፍ አበራችው…በዛን ሰከንድ አዲስአባ ቤቱ አልጋ ላይ ተኝቶ የሚገኘው የቃል ስልክ ድምፅ አሰማ …ፈጥኖ ተነሳና ልክ ልዩ እንዳደረገችው ላፕቶፑን አነሳና አበራ…ከፈተውና ልዩ የምታየውን ማየት ጀመረ….
አዎ መድህኒ እየሄደ ነው..ጊፍቲ የተኛችበት መኝታ ክፍል በረንዳ ላይ እየወጣ ነው..አንኳኳ፡፡በራፍ ተከፈተና ጊፍቲ ከውስጥ ወጣች…ለባብሳና ሜካፖን ተቀባብታ ዝንጥ ብላለች…
‹‹እንዲህ ነው ንቁ ሴት..››አለ መድህኔ
እንደመሽኮርም አለችና‹ያው ለስራ ለሊት አይደለ ተነስቼ ምዘጋጀው ልምድ ሆኖብኝ ነው››
‹‹አይ በጣም ጥሩ ነው…በይ ወደ ቁርስ እንሂድ››
‹‹ልዩስ?››
‹‹እሷ እንቅልፍ ይበልጥብኛል ብላ እምቢ አለች›
በራፉን እየቆለፈች‹‹ምነው ማታ አምሽታችሁ ነበር እንዴ?››አለችው
‹‹ማለት? ጎድተሀታል ወይ እያልሺኝ ነው?›ሲል ጥያቄዋን በሌላ ጥያቄ መለሰላት፡፡
ፊቷ ቀላ..‹እረ እኔ…ማለቴ..›ተንተባተበች፡፡
‹‹ግድ የለም ስቀልድ ነው ..እውነታው ግን ልዩ እንዲህ ነች…አንዳንዴ ቅምጥል የሀብታም ልጅ መሆን አጎጉል ያደርግሻል…›ወደቁርስ እየሄዱ ነው ልዩን የሚያሟት፡፡
ጥያቄ አስመስላ በውስጡ ግን አድናቆት እና ልብ ሚያሞቅ ቃል ጨምራበት፡፡‹‹አንተም እኮ የሀብታም ልጅ መሰልከኝ…ግን ይሄው በጥዋት ንቁ ሆነህ ተነስተሀል›› አለችው….
‹‹አይ…የእኔ ስሙ ብቻ ነው…አባቴ እንዲህ የዋዛ ሰው መስሎሻል…እቤት ውስጥ ከ12 ሰዓት በኃላ የአንድ አመት ህፃን እራሱ አይተኛም…እያንዳንዱ የቤቱ ልጅ የየራሱ የስራ ድርሻ አለው….አልጋችንን እናነጥፋለን….አትክልት ዉሀ እናጠጣለን…ግቢ እንጠርጋለን…ከዛ በኃላ ነው ልብሳችንን ቀይረን ቁርሳችንን በልተን ወደ ትምህርት ቤት የምንሄደው….ከዛም ስንመለሰ ተመሳሳይ የተግተለተለ ስራ ይጠብቀናል…. የሚገርመው ደግሞ ይሄን ሁሉ ስራ የምንሰራው እኮ መአት ሰራተኞችና የደረሱ የዘመድ ልጆች ጭምር እቤት ውስጥ እያሉ ነው››
‹‹እና አሁን አንደዛ በመሆኑ እያማረርክ እንዳይሆን?››
‹‹አይ ሙሉ በሙሉ እያማራርኩ አይደለም...የእሱ አስተዳደግ አሁን ስራ ወዳድና ውጤታማ እንድሆነ አደርጎኛል….ግን ደግሞ ልጅነቴን ልክ እንደልጅ ሆኜ አጣጥሜ ተጫውቼ ስላላደኩ አሁንም የሆነ ከፍት ይሰማኛል…መኪና እየነዳሁ በሆነ መንደር ውስጥ በማልፍበት ወቅት ልጆች መንገድ ዳር ተሰብስበው ብይ ሲጫወቱ ካየሁ ወርደህ አብርህችው ተጫወት የሚል ስሜት ይቀስፈኛል..ሌላው ይቀር ጭቃ እያቦኩ ግድብ የሚገድቡ ህፃናት ሳይ ውሰጤ ይቀናል እና አሁንም ያላደገ ህፃን በውስጤ ያለ ይመስለኛል፡፡››
‹‹እና አንተ ከልዩ ምትወልዳቸውን ልጆች እንዴት ለማሳደግ አሰብክ?››ብላ ጠየቀችው፡
በዚህ ጥያቄ ልዩን በጣም ነው ያስገረማት‹‹እኔ እንኳን አስቤ የማላውቀውን ገራሚ ጥያቄ ነው›በማት መልሱን ልትሰማ ቋመጠች…ይህ መገረም አዲስአባ ያለው ቃልም ተጋብቶበታል፡፡
ጊፍቲና መድሀኔ ይሄን በሚያወሩበት ጊዜ ፊት ለፊት ተቀምጠው የሚፈለጉትን ቁርስ ከተደረደረው ቢፌ ላይ ወስደው ቁርስ እየተመገብ ነው፡፡
‹‹ልጅቷ ግን ፀሀፊ ሳትሆን ጋዤጠኛ ነው የምትመስለው፡፡ምን ብሎ ይመስልስላት ይሆን›አለች ልዩ…መድህኔ የጎረሰውን አላምጦ ማውራት እስኪጀምር በጉጉት ትጠብቅ ነበር..
‹‹እንደእኔም ወግ አጥባቂ አስተዳደግ ሳይሆን እንደልዩም መረን የለቀቀ ስንፍና የተጫጫነው ሳይሆን በመካከል ባላ ዘመናዊ አስተዳደግ እንዲያድጉልኝ ነው ምፈልገው››ሲል መለሰላት፡፡
ከትከት ብላ ሳቀች‹‹መረን የለቀቀ›› ስላለኝ የተደሰተች ይመስላል፡፡
‹‹ግን ስንት ልጅ ምትውልደ ይምስልሀል?›
‹‹እኔማ ስድስት ልጆች ብንወልድ ደስ ይለኛል…ግን ከማን?››
በዚህ መልሱ ፊት ለፊት ተቀምጣ ምታዳምጠው ጊፍቲ ብቻም ሳትሆን ከጀርባ ሆነው በሚስጠጥር የሚከታተሎቸው ልዩና ቃልም ጭምር ናቸው የደነገጡት
‹‹እንዴት ከማ…?ከሚስትህ ነዋ..›ጊፍቲ በገረሜታ ተሞልታ ጠየቀችው፡
‹‹ከሚስትህ ማለት ከልዩ?››
‹‹እንዴ ግራ አጋባሀኝ እኮ…ሌላ ሚስት አለህ እንዴ?››
እሱማ የለኝም...ልዩን ሳስባት ግን አንድ ልጅ እንኳን በስርአቱ አምጣ መውለድ የምትችል አይመስለኝም…ምግቧን እንኳን በእጆቾ ጠቅልላ መብላት የሚከብዳት እና በአጉራሽ የምትመገብ ቅንጡ .ልጅ ነች፡፡ታዲያ ልጅን የሚያህል ነገር አርግዛ…. ለዛውም ዘጠኝ ወር….ለዛውም ደጋግማ… ምን አልባት የመጀመሪያውን እንደወረት ልታደርገው ትችላለች.. ከዛ በኋላ ላሉት ግን እርግጠኛ ነኝ መሀፀን ተከራይልኝ ነው የምትለው››
ጊፍቲ ከት ብላ ሳቀች…‹‹ጓደኛዬንማ እንዲህ አትላትም…ይሄን ያህል ምነው?››መቆርቆሮ ሳይሆን የሆነ የሽሙጥና እሷ የተሻለች እንደሆነች በሚያረጋግጥ ስሜት ነው፡፡
እሱ ግን ቀጠለበት‹ባክሽ በጥልቀት ስለማታውቂያት ነው….የእሷ ጉዳይ ከምልሽም በላይ ነው….እኔ ከልጅነቴ ጀምሮ ነው ያማውቃት….ቤተሰብ ነን….አሁንም የማስተዳድረው ካማፓኒ የሁለታችን ቤተሰቦች በጋራ የመሰረቱት ነው››
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
በእቅዷ መሰረት ኩሪፍቱ ይገኛሉ….ትናንትና ከመሸ ነው የገቡት፡፡ከጥዋቱ ሁለተ ሰዓት አካባቢ ሆኗል..መኝታውን ለቆ ተነስቶ ክፍል ውስጥ ሲንጎራደድ ከጀመረ 30 ደቂቃ ያህል አልፎታል አንዴ መታጠቢያ ቤት ይገባል…አንዴ ወደበረንዳ ይወጣል…እኔ እየሰማው ቢሆንም አንቅልፍ ውስጥ እንዳለ ሰው አድፍጣ ዝም….መታጠቢያ ቤት ሲገባ ፈጠን ብላ ተነሳችና ከቦርሳዋ ውስጥ መከታተያ ካሜራዋን በማውጣት ወንበር ላይ የተንጠለጠለው ጃኬቱ ላይ አንዳይታይ አድርጋ ኮሌታው አካባቢ አጣበቀችውና ቶሎ ብላ ወደመኝታዋ ተመለሰች …በስተመጨረሻ ትግስት አጥቶ ,..ፈራ ተባ እያለው ወደአልጋው ቀረበና ትከሻዋን ይዞ እየነቀቃት…..
‹‹ፍቅር ተኝተሸ ቀረሸ እኮ …በጣም እርቦኛል..ተነሽ ቁርስ እንብላ››አላት
‹‹ተወኝ በናትህ እንቅልፌን አልጠገብኩም…ጊፍቲን ቀስቅሳትና አብራችሁ ብሉ››
‹‹ተይ እንጂ ፍቅር..››
‹‹እየረበሽከኝ አኮ ነው..በፈጣሪ ተወኝ››ተነጫነጨችበት፡፡
‹‹እሺ.ስትነሺ ተቀላቀይን›› ብሎ ዘረጥ ዘረጥ እያለ ክፍሉን ለቆ ለመውጣት ወደበሩ መራመድ ጀመረ…ፍፁም ንቁ ሁና ከአንገቷ ቀና አለችና..
‹‹እንዴ?››አለችው፡፡
በሁኔታዋ ግራ በመጋባት‹‹ምነው ልጠብቅሽ ?ትመጪያለሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አይ አልመጣም ግን የውጩን ቅዝቃዜ አታየውም እንዴ…?››
‹‹እና ምን ?
ተኝተን እንዋል?››
ምን ለማለት እንደፈለገች አልተገለፀለትም፡፡
‹‹አላልኩም..በኃላ ኩሪፍቱ ወስደሽ ብርድ አስመታሺኝ እያልክ ስትወቅሰኝ እንዳትከርም….ጃኬትህን ለብሰህ ውጣ››
‹‹አረ ተይ… እንዲህ ተመችቶኛል››
‹‹አይሆን …ነገርኩህ እኮ….››
‹‹አንቺ ደግሞ በሚሆነውማ በማይሆነውም መጨነቅ ታበዢዋለሽ…እኔ እኮ እስፖርተኛ ነኝ የምን በርድ ነው››እያለ በማጉረምረም ወደኃላ ተመልሶ ጃኬቱን ከተንጠለጠለበት ወንበር በማንሳት እየለበሰ ወጥቶ ሄደ…ፈገግ አለች…‹‹አይ ወንዶች ነገረ ሰራቸው እኮ የህፃን ነው..በቀላሉ የሚታለሉ ገራገር ፍጥሮች… ሲመጣባቸውም እንደዛው ደንባራ አውሬዎች ናቸው…›አለችና …ከተኛችበት ተስፈንጥራ በመነሳት ክፍሉን ከውስጥ ቆለፈችው…ከዛ ላፕቶፖን አወጣችና ከፈተችው.. በገዛ እጮኛዋ ደረት ላይ የሰካችውን ካሜራ ጋር የሚየገናኝውን አፕ ቁልፍ አበራችው…በዛን ሰከንድ አዲስአባ ቤቱ አልጋ ላይ ተኝቶ የሚገኘው የቃል ስልክ ድምፅ አሰማ …ፈጥኖ ተነሳና ልክ ልዩ እንዳደረገችው ላፕቶፑን አነሳና አበራ…ከፈተውና ልዩ የምታየውን ማየት ጀመረ….
አዎ መድህኒ እየሄደ ነው..ጊፍቲ የተኛችበት መኝታ ክፍል በረንዳ ላይ እየወጣ ነው..አንኳኳ፡፡በራፍ ተከፈተና ጊፍቲ ከውስጥ ወጣች…ለባብሳና ሜካፖን ተቀባብታ ዝንጥ ብላለች…
‹‹እንዲህ ነው ንቁ ሴት..››አለ መድህኔ
እንደመሽኮርም አለችና‹ያው ለስራ ለሊት አይደለ ተነስቼ ምዘጋጀው ልምድ ሆኖብኝ ነው››
‹‹አይ በጣም ጥሩ ነው…በይ ወደ ቁርስ እንሂድ››
‹‹ልዩስ?››
‹‹እሷ እንቅልፍ ይበልጥብኛል ብላ እምቢ አለች›
በራፉን እየቆለፈች‹‹ምነው ማታ አምሽታችሁ ነበር እንዴ?››አለችው
‹‹ማለት? ጎድተሀታል ወይ እያልሺኝ ነው?›ሲል ጥያቄዋን በሌላ ጥያቄ መለሰላት፡፡
ፊቷ ቀላ..‹እረ እኔ…ማለቴ..›ተንተባተበች፡፡
‹‹ግድ የለም ስቀልድ ነው ..እውነታው ግን ልዩ እንዲህ ነች…አንዳንዴ ቅምጥል የሀብታም ልጅ መሆን አጎጉል ያደርግሻል…›ወደቁርስ እየሄዱ ነው ልዩን የሚያሟት፡፡
ጥያቄ አስመስላ በውስጡ ግን አድናቆት እና ልብ ሚያሞቅ ቃል ጨምራበት፡፡‹‹አንተም እኮ የሀብታም ልጅ መሰልከኝ…ግን ይሄው በጥዋት ንቁ ሆነህ ተነስተሀል›› አለችው….
‹‹አይ…የእኔ ስሙ ብቻ ነው…አባቴ እንዲህ የዋዛ ሰው መስሎሻል…እቤት ውስጥ ከ12 ሰዓት በኃላ የአንድ አመት ህፃን እራሱ አይተኛም…እያንዳንዱ የቤቱ ልጅ የየራሱ የስራ ድርሻ አለው….አልጋችንን እናነጥፋለን….አትክልት ዉሀ እናጠጣለን…ግቢ እንጠርጋለን…ከዛ በኃላ ነው ልብሳችንን ቀይረን ቁርሳችንን በልተን ወደ ትምህርት ቤት የምንሄደው….ከዛም ስንመለሰ ተመሳሳይ የተግተለተለ ስራ ይጠብቀናል…. የሚገርመው ደግሞ ይሄን ሁሉ ስራ የምንሰራው እኮ መአት ሰራተኞችና የደረሱ የዘመድ ልጆች ጭምር እቤት ውስጥ እያሉ ነው››
‹‹እና አሁን አንደዛ በመሆኑ እያማረርክ እንዳይሆን?››
‹‹አይ ሙሉ በሙሉ እያማራርኩ አይደለም...የእሱ አስተዳደግ አሁን ስራ ወዳድና ውጤታማ እንድሆነ አደርጎኛል….ግን ደግሞ ልጅነቴን ልክ እንደልጅ ሆኜ አጣጥሜ ተጫውቼ ስላላደኩ አሁንም የሆነ ከፍት ይሰማኛል…መኪና እየነዳሁ በሆነ መንደር ውስጥ በማልፍበት ወቅት ልጆች መንገድ ዳር ተሰብስበው ብይ ሲጫወቱ ካየሁ ወርደህ አብርህችው ተጫወት የሚል ስሜት ይቀስፈኛል..ሌላው ይቀር ጭቃ እያቦኩ ግድብ የሚገድቡ ህፃናት ሳይ ውሰጤ ይቀናል እና አሁንም ያላደገ ህፃን በውስጤ ያለ ይመስለኛል፡፡››
‹‹እና አንተ ከልዩ ምትወልዳቸውን ልጆች እንዴት ለማሳደግ አሰብክ?››ብላ ጠየቀችው፡
በዚህ ጥያቄ ልዩን በጣም ነው ያስገረማት‹‹እኔ እንኳን አስቤ የማላውቀውን ገራሚ ጥያቄ ነው›በማት መልሱን ልትሰማ ቋመጠች…ይህ መገረም አዲስአባ ያለው ቃልም ተጋብቶበታል፡፡
ጊፍቲና መድሀኔ ይሄን በሚያወሩበት ጊዜ ፊት ለፊት ተቀምጠው የሚፈለጉትን ቁርስ ከተደረደረው ቢፌ ላይ ወስደው ቁርስ እየተመገብ ነው፡፡
‹‹ልጅቷ ግን ፀሀፊ ሳትሆን ጋዤጠኛ ነው የምትመስለው፡፡ምን ብሎ ይመስልስላት ይሆን›አለች ልዩ…መድህኔ የጎረሰውን አላምጦ ማውራት እስኪጀምር በጉጉት ትጠብቅ ነበር..
‹‹እንደእኔም ወግ አጥባቂ አስተዳደግ ሳይሆን እንደልዩም መረን የለቀቀ ስንፍና የተጫጫነው ሳይሆን በመካከል ባላ ዘመናዊ አስተዳደግ እንዲያድጉልኝ ነው ምፈልገው››ሲል መለሰላት፡፡
ከትከት ብላ ሳቀች‹‹መረን የለቀቀ›› ስላለኝ የተደሰተች ይመስላል፡፡
‹‹ግን ስንት ልጅ ምትውልደ ይምስልሀል?›
‹‹እኔማ ስድስት ልጆች ብንወልድ ደስ ይለኛል…ግን ከማን?››
በዚህ መልሱ ፊት ለፊት ተቀምጣ ምታዳምጠው ጊፍቲ ብቻም ሳትሆን ከጀርባ ሆነው በሚስጠጥር የሚከታተሎቸው ልዩና ቃልም ጭምር ናቸው የደነገጡት
‹‹እንዴት ከማ…?ከሚስትህ ነዋ..›ጊፍቲ በገረሜታ ተሞልታ ጠየቀችው፡
‹‹ከሚስትህ ማለት ከልዩ?››
‹‹እንዴ ግራ አጋባሀኝ እኮ…ሌላ ሚስት አለህ እንዴ?››
እሱማ የለኝም...ልዩን ሳስባት ግን አንድ ልጅ እንኳን በስርአቱ አምጣ መውለድ የምትችል አይመስለኝም…ምግቧን እንኳን በእጆቾ ጠቅልላ መብላት የሚከብዳት እና በአጉራሽ የምትመገብ ቅንጡ .ልጅ ነች፡፡ታዲያ ልጅን የሚያህል ነገር አርግዛ…. ለዛውም ዘጠኝ ወር….ለዛውም ደጋግማ… ምን አልባት የመጀመሪያውን እንደወረት ልታደርገው ትችላለች.. ከዛ በኋላ ላሉት ግን እርግጠኛ ነኝ መሀፀን ተከራይልኝ ነው የምትለው››
ጊፍቲ ከት ብላ ሳቀች…‹‹ጓደኛዬንማ እንዲህ አትላትም…ይሄን ያህል ምነው?››መቆርቆሮ ሳይሆን የሆነ የሽሙጥና እሷ የተሻለች እንደሆነች በሚያረጋግጥ ስሜት ነው፡፡
እሱ ግን ቀጠለበት‹ባክሽ በጥልቀት ስለማታውቂያት ነው….የእሷ ጉዳይ ከምልሽም በላይ ነው….እኔ ከልጅነቴ ጀምሮ ነው ያማውቃት….ቤተሰብ ነን….አሁንም የማስተዳድረው ካማፓኒ የሁለታችን ቤተሰቦች በጋራ የመሰረቱት ነው››
#ታምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
/
እዚህ አብሬያቸው ከምኖረው የሰው ልጆች የበለጠ እውቀትና የረቀቀ ጥበብ የሰጣችሁ እሱ መሆኑን ታማናለችሁ ወይ? .በመካከላችሁ ያለው ግንኙነትስ እንዴት ነው ?ማለቴ በእናንተ እና በእግዚያብሄር መካከል…አንድ ጊዜ ስለአንተ ከእማዬ የሰማሁትን ለአንድ ቄስ ብነግራቸው….እነሱ ከእግዚያብሄር ተጣልተው ወደምድር ተወርውረው የነበሩ የመላእክት ዘሮች ናቸው ብለው አስረዱኝ...ወደምድር መጥተው ከሰው ልጆች ጋር ተስማምተው እንዲኖሩ ቢፈቅድላቸውም.እነሱ ግን መላውን የሰው ልጅ በከሉት ..ሰላማዊውን ፍጡር ጦር መሳሪያ አሰራርና ጎራዴ አሞረረድ ከዛም አልፎ የጦርነት ጥበብ እና የዘረፋና ግድያ ስልቶችን በማስተማር እርስ በርስ አጫረሱት ..በስርዓትና ይኖር የነበረውን ግብረሰዶምና ሊዚቢያ አደረጉት..እግዚያብሄር በጥበብና በፍቅር በመፍጠር በምድር የበተናቸውን እንስሳትን አንዱን ከሌላው እያዳቀሉ አስፈሪና አጥፊ ፍጥረታትና መፍጠር ጀመሩ..የጥንቆላና የሞርት ጥበብን ለሰው ልጅ በማስተማር አእምሮውን በከሉት ከዛ አምላክ ተቆጣና የጥፋት ውሀ ላከ ..ምድርንም በውስጦ ያሉትን ከእነሱ ጋር የተባበሩትን ትምህርታቸውንና በጥባቸው የተደሙትን ሁሉ አጠፋ…የሰው ለጅና እንስሳቱ ለዘር እንዲሆን ጥንድ እየሆነ በኖህ መርከብ ተጠልሎ እንደተረፈ ሁሉ.አነሱም የተወሰኑት የረቀቀ ጥበባቸው በመጠቀም ምድርን ለቀው በመሰደድ በጥፋት ውሀው ሙሉ በሙሉ ከመጥፋት እራሳቸውን ያተረፉ ይመስለኛል ….
እንደምገምተው ከሆነ አሁን አባቴ የምትይውና በሌላ አለም እንደሚኖር ለእናትሽ የነገራት ፍጥረት ከእነሱ አንዱ ነው አሉኝ…..፡፡ከእግዚያብሄር ጋረ የሚያቀያይምሽና ሀይማኖትሽ የሚያስክድሽ ከይሲ ፍጥረት ስለሆነ ቢመጣ እንኳን እንዳትቀርቢው.በስመአብ፤ወልድ ወመንፈስ ቅዱስ በማለት ደጋግመሽ በማማተብ ከስርሽ አባሪው ብለው መከሩኝ ..አልተከራከርኮቸውም ምን አልባት ያሉት እውነት ሊሆን ይችላል ብዬ አሰብኩ፡፡እንኳን ሙለ በመሉ የእናንተ ዘር መሆነን ተችሎ ይቅርና እኔ እራሱ ያንተ ደም በውስጤ ስላለ በውስጤ የሚንቀለቀለው የክፋት ኃይልና የወሲብ ጥማት እኔ ነኝ የማውቀው፡፡ከቄሱ ጋር ያልተስማማሁበት አንድ ነገር ቢኖር ቢመጣ እንዳትቀርቢው ብለው ያሉኝን ነው..ወይ ብትመጣ እንዴት እንደምጠመጠምብህ ሳስበው እራሱ ውስጤ በደስታ ይነዝራል፡፡
ይቀልዳሉ እንዴ? ሴይጣንም ሆንክ እግዚያሄር አባቴ ነህ…መርጬ አይደለም ካንተ የተፈጠርኩት..
እና ለማለት የፈለኩት እውነትም ቄሱ ያሉኝ ነገር የእውነት ከሆነ በመጀመሪያ በእናንተና በእግዚያሄር መካከል የነበረውንም አለመጋባባት ምክንያትም የሚያስረዳኝ አካል አላገኘሁም…ስለዚህ ማን ጥፋተኛ ማን ትክክል እንደሆነ መወሰን አልችልም…ደግሞ እግዚያብሄር ይሳሳታል እንዴ?አቦ እኔ እንጃ …ለማኛውም እስከአሁን የዘበዘብኩትን ሁሉ እርሳውና ለእናቴ እባክህ ምትችለውን አድርግ…›ሀሳቧን ሳትቋጭ ዝናቡ ዣ ብሎ መርገፈ ጀመረ….በትላልቅ ዕድሜ ጠገብ ዛፎችና በርካታ ቁጥቆጦችና ሰርጎ የሚረግፍ በመሆኑ ዝናቡ ከላይ በሚረግፈው ልክ ሳይሆን በየቅርንጫፎቹ እየተሹለኮለከ በቅጠሎች ላይ የተንኳለለ ነበር እሷ ጋር ሚደርሰው፡፡ እሷ ግን ግድም አልነበራትም…..ቦታም ቀይራ ለመጠለል አልሞከረችም…. ልክ እዛ ደን ውስጥ ዛፎቹ ስር ተተክላ እንደበቀለች ታዳጊ ችግኝ.. በደስታ ቅርንጫፎቾንና መላ አካሏን ወዲህ ወዲያ እያዋወዘች የሚዘንበውን ዝናብ በፍቅር እንደምትመጥ አይነት እሷም ተመሳሳዩን ነበር ያደረገችው..
ከ20 ደቂቃ በኃላ ዝናቡ ቢያባራም እየተንኳለለ ከቅርንጫፎቹ ቅጠሎች የሚንጠባጠበው ውሀ ግን አልተቋረጠም ነበር….ንስሯ እንደአካሄዷ አካባቢውን እየደረማመሰ መጥቶ ከፊት ለፊቷ አረፈ፤በቅርንጫፎቹ ውስጥ እየሾለከ ሲመጣ አካሉ ላይ ካረፉበት የውሀ እንክበብሎች በስተቀር ሲሄድ እንደነበረው ፍፅም ደረቅ አካል ነው ያለው፡፡ያው ይሄ የእሱ ብቻ ሳይሆን የሁሉም ንስሮች ፀጋ ነው፡ዝናብ ሲዘንብ ደመናውን ሰንጥቀው አልፈው ከበላዩ ይሆኑን ወደታች አዘቅዝቀው በትዝብት ያዩታል..ምድርና በውስጧ ያሉት ሌሎች ፍጥረቶች ሁሉ ግን በሰማይ የሚበሩትን ሌሎች እዋፍቶችም ሳይቀሩ ወደዱም አልወዱም ወይ መሸሸጊያ ዋሻ ይፈልጋሉ ወይ ደግሞ በዝናቡ ይቀጠቀጣሉ፡፡
‹‹እሺ የት ሄደህ መጣህ?››
እምሮውን ከፈተላት.የሄደበትን ቦታ ሳይሆን እናቷ የምትድንበትን ዘዴ ነው የነገራት፡፡መጀመሪያው መድሀኒት ጨካኝ ነፍስ ያላቸው…ከ7 ሰዎች በላይ የገደሉ የሶስት ሰዎችን አንገት ቆርጦ እናትትሽ ቤት ውስጥ መቅበር ነው›የሚል መልዕክት በእምሮዋ ፃፈላት፡
‹‹ምን እያልከኝ ነው….እኔ ሰው ልገድል ነው…?ለዛውም አስፈሪና ጭራቅ የሆኑ ሰዎችን?››
‹‹ለዚህ እኮ ነው….የእናትሽን ሞት በፀጋ ተቀበይ የምልሽ››ሲል በእምሮ መለሰላት፡፡
‹‹አንተ ከእናቴ ነጥለህ ብቻዬን ምን ልታደርገኝ አስበሀል….?ሀዘኔ ያስደስትሀል ማለት ነው..?››
እዕምሮውን በነጭ ቀለም ሞላው …እንዲህ የሚያደርገው ሲያዝንና በንግግሯ ወይም በድርጊቷ ሲበሳጭ እንደሆነ ታውቃለች፡››
‹‹ይቅርታ ላስከፋህ ፈልጌ አይደለም….በቃ አደርገዋለሁ…ሶስት ሰው ጭንቅላት አይደል፡፡ለዛውም የሶስት ጨካኝና ገዳይ የሆኑ ሰዎች ጭንቅላት… .አረ አደርገዋለሁ ደግሞ ለእናቴ››ስትል ፎከረች፡፡
‹‹እንደዛ ከሆነ በ15 ቀን ውስጥ ጭንቅላቱ ተገኝቶ መቀበር አለበት….ይሄ ጉዳይ በትክክል ከተፈፀመ እናትሽን ለአንድ አመት በህይወት ያቆያታል፡፡
‹‹ፈክቶና በተስፋ ተሞልቶ የነበረው ፊቷ በአንዴ ጨለመ››
‹‹ምን ማለት ነው…?እኔ ለእናቴ እኮ መቶ አመት ነው የምመኝላት….ከተቻለም ዘላለም እንድትኖር፡››
‹‹መጀመሪያ ይሄንን ማድረግ ነው የምትችይው ..ከዛ ደግሞ ሌላውን ዕድሜ እናትሽ እንድታገኝ ምን ማድረግ እንዳለብሽ እናወራለን›››
‹‹ለምን ያኔ ?አሁን አትነግረኝም…ምን ያሰደብቅሀል ?››
‹‹የመጀመሪያው ካልተሳካ ሁለተኛውን ማወቅሽ ምንም እርባን የለውም …..››ብሎ ፍቃዷን ሳይጠብቅ ከአካባቢው ለቆ በረረ…ሆዱ ባዶ ስለሆነ የሚበላ ነገር ለማደን ነው ወደ ደኑ በጥልቀት የገባው….እሷም እንዴት አድርጋ ጨካኝና ወንጀለኛ ሰዎችን ጭንቅላት በ3 ቀን ውስጥ ማግኘት እደምተችል እያሰላሰለች ወደቤቷ ጉዞዋን ቀጠለች፡፡
ንስሯ ግን ተከትሏት አልሄደም..በተቃራኒው ሰማዩን ሰንጥቆ በረረ…
✨ይቀጥላል✨
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
/
እዚህ አብሬያቸው ከምኖረው የሰው ልጆች የበለጠ እውቀትና የረቀቀ ጥበብ የሰጣችሁ እሱ መሆኑን ታማናለችሁ ወይ? .በመካከላችሁ ያለው ግንኙነትስ እንዴት ነው ?ማለቴ በእናንተ እና በእግዚያብሄር መካከል…አንድ ጊዜ ስለአንተ ከእማዬ የሰማሁትን ለአንድ ቄስ ብነግራቸው….እነሱ ከእግዚያብሄር ተጣልተው ወደምድር ተወርውረው የነበሩ የመላእክት ዘሮች ናቸው ብለው አስረዱኝ...ወደምድር መጥተው ከሰው ልጆች ጋር ተስማምተው እንዲኖሩ ቢፈቅድላቸውም.እነሱ ግን መላውን የሰው ልጅ በከሉት ..ሰላማዊውን ፍጡር ጦር መሳሪያ አሰራርና ጎራዴ አሞረረድ ከዛም አልፎ የጦርነት ጥበብ እና የዘረፋና ግድያ ስልቶችን በማስተማር እርስ በርስ አጫረሱት ..በስርዓትና ይኖር የነበረውን ግብረሰዶምና ሊዚቢያ አደረጉት..እግዚያብሄር በጥበብና በፍቅር በመፍጠር በምድር የበተናቸውን እንስሳትን አንዱን ከሌላው እያዳቀሉ አስፈሪና አጥፊ ፍጥረታትና መፍጠር ጀመሩ..የጥንቆላና የሞርት ጥበብን ለሰው ልጅ በማስተማር አእምሮውን በከሉት ከዛ አምላክ ተቆጣና የጥፋት ውሀ ላከ ..ምድርንም በውስጦ ያሉትን ከእነሱ ጋር የተባበሩትን ትምህርታቸውንና በጥባቸው የተደሙትን ሁሉ አጠፋ…የሰው ለጅና እንስሳቱ ለዘር እንዲሆን ጥንድ እየሆነ በኖህ መርከብ ተጠልሎ እንደተረፈ ሁሉ.አነሱም የተወሰኑት የረቀቀ ጥበባቸው በመጠቀም ምድርን ለቀው በመሰደድ በጥፋት ውሀው ሙሉ በሙሉ ከመጥፋት እራሳቸውን ያተረፉ ይመስለኛል ….
እንደምገምተው ከሆነ አሁን አባቴ የምትይውና በሌላ አለም እንደሚኖር ለእናትሽ የነገራት ፍጥረት ከእነሱ አንዱ ነው አሉኝ…..፡፡ከእግዚያብሄር ጋረ የሚያቀያይምሽና ሀይማኖትሽ የሚያስክድሽ ከይሲ ፍጥረት ስለሆነ ቢመጣ እንኳን እንዳትቀርቢው.በስመአብ፤ወልድ ወመንፈስ ቅዱስ በማለት ደጋግመሽ በማማተብ ከስርሽ አባሪው ብለው መከሩኝ ..አልተከራከርኮቸውም ምን አልባት ያሉት እውነት ሊሆን ይችላል ብዬ አሰብኩ፡፡እንኳን ሙለ በመሉ የእናንተ ዘር መሆነን ተችሎ ይቅርና እኔ እራሱ ያንተ ደም በውስጤ ስላለ በውስጤ የሚንቀለቀለው የክፋት ኃይልና የወሲብ ጥማት እኔ ነኝ የማውቀው፡፡ከቄሱ ጋር ያልተስማማሁበት አንድ ነገር ቢኖር ቢመጣ እንዳትቀርቢው ብለው ያሉኝን ነው..ወይ ብትመጣ እንዴት እንደምጠመጠምብህ ሳስበው እራሱ ውስጤ በደስታ ይነዝራል፡፡
ይቀልዳሉ እንዴ? ሴይጣንም ሆንክ እግዚያሄር አባቴ ነህ…መርጬ አይደለም ካንተ የተፈጠርኩት..
እና ለማለት የፈለኩት እውነትም ቄሱ ያሉኝ ነገር የእውነት ከሆነ በመጀመሪያ በእናንተና በእግዚያሄር መካከል የነበረውንም አለመጋባባት ምክንያትም የሚያስረዳኝ አካል አላገኘሁም…ስለዚህ ማን ጥፋተኛ ማን ትክክል እንደሆነ መወሰን አልችልም…ደግሞ እግዚያብሄር ይሳሳታል እንዴ?አቦ እኔ እንጃ …ለማኛውም እስከአሁን የዘበዘብኩትን ሁሉ እርሳውና ለእናቴ እባክህ ምትችለውን አድርግ…›ሀሳቧን ሳትቋጭ ዝናቡ ዣ ብሎ መርገፈ ጀመረ….በትላልቅ ዕድሜ ጠገብ ዛፎችና በርካታ ቁጥቆጦችና ሰርጎ የሚረግፍ በመሆኑ ዝናቡ ከላይ በሚረግፈው ልክ ሳይሆን በየቅርንጫፎቹ እየተሹለኮለከ በቅጠሎች ላይ የተንኳለለ ነበር እሷ ጋር ሚደርሰው፡፡ እሷ ግን ግድም አልነበራትም…..ቦታም ቀይራ ለመጠለል አልሞከረችም…. ልክ እዛ ደን ውስጥ ዛፎቹ ስር ተተክላ እንደበቀለች ታዳጊ ችግኝ.. በደስታ ቅርንጫፎቾንና መላ አካሏን ወዲህ ወዲያ እያዋወዘች የሚዘንበውን ዝናብ በፍቅር እንደምትመጥ አይነት እሷም ተመሳሳዩን ነበር ያደረገችው..
ከ20 ደቂቃ በኃላ ዝናቡ ቢያባራም እየተንኳለለ ከቅርንጫፎቹ ቅጠሎች የሚንጠባጠበው ውሀ ግን አልተቋረጠም ነበር….ንስሯ እንደአካሄዷ አካባቢውን እየደረማመሰ መጥቶ ከፊት ለፊቷ አረፈ፤በቅርንጫፎቹ ውስጥ እየሾለከ ሲመጣ አካሉ ላይ ካረፉበት የውሀ እንክበብሎች በስተቀር ሲሄድ እንደነበረው ፍፅም ደረቅ አካል ነው ያለው፡፡ያው ይሄ የእሱ ብቻ ሳይሆን የሁሉም ንስሮች ፀጋ ነው፡ዝናብ ሲዘንብ ደመናውን ሰንጥቀው አልፈው ከበላዩ ይሆኑን ወደታች አዘቅዝቀው በትዝብት ያዩታል..ምድርና በውስጧ ያሉት ሌሎች ፍጥረቶች ሁሉ ግን በሰማይ የሚበሩትን ሌሎች እዋፍቶችም ሳይቀሩ ወደዱም አልወዱም ወይ መሸሸጊያ ዋሻ ይፈልጋሉ ወይ ደግሞ በዝናቡ ይቀጠቀጣሉ፡፡
‹‹እሺ የት ሄደህ መጣህ?››
እምሮውን ከፈተላት.የሄደበትን ቦታ ሳይሆን እናቷ የምትድንበትን ዘዴ ነው የነገራት፡፡መጀመሪያው መድሀኒት ጨካኝ ነፍስ ያላቸው…ከ7 ሰዎች በላይ የገደሉ የሶስት ሰዎችን አንገት ቆርጦ እናትትሽ ቤት ውስጥ መቅበር ነው›የሚል መልዕክት በእምሮዋ ፃፈላት፡
‹‹ምን እያልከኝ ነው….እኔ ሰው ልገድል ነው…?ለዛውም አስፈሪና ጭራቅ የሆኑ ሰዎችን?››
‹‹ለዚህ እኮ ነው….የእናትሽን ሞት በፀጋ ተቀበይ የምልሽ››ሲል በእምሮ መለሰላት፡፡
‹‹አንተ ከእናቴ ነጥለህ ብቻዬን ምን ልታደርገኝ አስበሀል….?ሀዘኔ ያስደስትሀል ማለት ነው..?››
እዕምሮውን በነጭ ቀለም ሞላው …እንዲህ የሚያደርገው ሲያዝንና በንግግሯ ወይም በድርጊቷ ሲበሳጭ እንደሆነ ታውቃለች፡››
‹‹ይቅርታ ላስከፋህ ፈልጌ አይደለም….በቃ አደርገዋለሁ…ሶስት ሰው ጭንቅላት አይደል፡፡ለዛውም የሶስት ጨካኝና ገዳይ የሆኑ ሰዎች ጭንቅላት… .አረ አደርገዋለሁ ደግሞ ለእናቴ››ስትል ፎከረች፡፡
‹‹እንደዛ ከሆነ በ15 ቀን ውስጥ ጭንቅላቱ ተገኝቶ መቀበር አለበት….ይሄ ጉዳይ በትክክል ከተፈፀመ እናትሽን ለአንድ አመት በህይወት ያቆያታል፡፡
‹‹ፈክቶና በተስፋ ተሞልቶ የነበረው ፊቷ በአንዴ ጨለመ››
‹‹ምን ማለት ነው…?እኔ ለእናቴ እኮ መቶ አመት ነው የምመኝላት….ከተቻለም ዘላለም እንድትኖር፡››
‹‹መጀመሪያ ይሄንን ማድረግ ነው የምትችይው ..ከዛ ደግሞ ሌላውን ዕድሜ እናትሽ እንድታገኝ ምን ማድረግ እንዳለብሽ እናወራለን›››
‹‹ለምን ያኔ ?አሁን አትነግረኝም…ምን ያሰደብቅሀል ?››
‹‹የመጀመሪያው ካልተሳካ ሁለተኛውን ማወቅሽ ምንም እርባን የለውም …..››ብሎ ፍቃዷን ሳይጠብቅ ከአካባቢው ለቆ በረረ…ሆዱ ባዶ ስለሆነ የሚበላ ነገር ለማደን ነው ወደ ደኑ በጥልቀት የገባው….እሷም እንዴት አድርጋ ጨካኝና ወንጀለኛ ሰዎችን ጭንቅላት በ3 ቀን ውስጥ ማግኘት እደምተችል እያሰላሰለች ወደቤቷ ጉዞዋን ቀጠለች፡፡
ንስሯ ግን ተከትሏት አልሄደም..በተቃራኒው ሰማዩን ሰንጥቆ በረረ…
✨ይቀጥላል✨
#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹዋቤ
ሁሴን ትንግርትን እንደያዘ ቤቱ ሲገባ የገጠመው ከገመተው በላይ የሆነ ዝግጅት ነው፡፡ ለወር ያህል የታሠበበት ይመስል ሁሉ
ነገር ደምቋል፡፡ ሳሎኑ በዲኮሬሽን አሸብርቋል፡፡
ቤቱ ውስጥ ያሉ ሠዎች የጎደሉ ነገሮችን ለሟሟላት ከወዲህ ወዲያ ውር ውር ይላሉ፡፡
የሳሎኑን በር ዘልቀው ወደ ውስጥ ከገቡ በኋላ ግን የቤቱ ድባብ ሙሉ በሙሉ ነበር የተቀየረው፡፡ ሁሉም በያለበት ደንዝዘው ቆሙ፡፡ ፎዚያ፣ ኤደን፣ ሠሎሞን፣ የሠለሞን ሁለት መንታ ልጆች፣ አንድ የጎረቤት አሮጊት፣ እቤቱ ውስጥ የጠበቁት ሠዎች ናቸው፡፡ ሁሉም ፈዞ እንደቆመ ሁሴን የትንግርትን እጆቿን ይዞ
እየጎተተ ወደ ሶፋው ወስዶ አስቀመጣትና ወደ መኝታ ክፍሉ አመራ፡፡
‹‹አልተሳካም ማለት ነው?›› ሠሎሞን ነበር ከደብረ ዘይት ጀምሮ አንደበቷን ተቆልፎ የደነዘዘችውን ትንግርትን የጠየቃት፡፡ሌሎችም መልሱን ለመስማት ወደ እሷ ተጠግተው ቆመዋል፡፡
‹‹ምን ነካችሁ? ምን ተፈጠረ?›› መልስ ስታጣ ዳግመኛ የጠየቀችው ፎዚያ ነች፡፡ከድንዛዜዋ ሳትወጣ ‹‹ባካችሁ ተውኝ እሱኑ ጠይቁት፤ እኔ ምንም አላውቅም፡፡››ብላ መለሰችላቸው፡፡
‹‹አብረሽው አልነበርሽ እንዴ?›› ኤደን ነች ጣልቃ የገባችው፡፡ ትንግርት ቀና ብላ አየቻት፡፡ እስከአሁን መኖሯን አላወቀችም ነበር፡፡
‹‹ነበርኩ.. ግን ለምን እራሱን አትጠይቁትም›› ተበሳጨች፡፡
‹‹ተዋት በቃ.... ለማንኛውም ተረጋጉ መጣሁ፡፡›› በማለት ወደ መኝታ ክፍል ፈራ ተባ እያለ አመራ፤ሰሎሞን፡፡ ዘልቆ ሲገባ ያልጠበቀው ነገር ነው ያየው፡፡ሁሴን በፈገግታ ተጥለቅልቆ.. ለብሶ የመጣውን ልብስ አውልቆ
ቡኒ ከለር ያለውን የጣሊያን ሱፉን እየለበሠ ነበር::
‹‹ምን እየተከናወነ ነው?›› ሠሎሞን በገረሜታ ጠየቀው፡፡
‹‹ሙሽራ አይደለሁ… እየተዘጋጀሁ ነዋ!!››
‹‹አግኝተሀታል ማለት ነው?››
<አግኝቻታለሁ ግን ይዣት አልመጣሁም .. አላናገርኳትም፤ እዛው ጥያት ነው የመጣሁት፡፡
‹‹አንተ ሠውዬ ጭራሽ ለይቶልሀል ማለት ነው?›› ይሄን ሁሉ ጊዜ ቁም ስቅላችንን ስታሳየን ከርመህ አንተም ይሄን ያህል ተሠቃይተህ ካገኘሀት በኋላ ጥያት መጣሁ ስትል ምን ለማለት ፈልገህ ነው?››
‹‹ባክህ አትነጫነጭ .. ድግሳችሁ አይከስርም አንድ እቅድ አለኝ ሂድና ንገራቸው.. ሁሉም ለእራት ዝግጁ ይሁኑ፤ አስር ደቂቃ አይፈጅብኝም መጣሁ፡፡››
‹‹ለነገሩ እውነትህን ነው... የለፋንበትን እራትማ መሬት ላይ ደፍተን አንሄድም፡፡ ሁለተኛ ግን ካንተ ጋር አብሮ የሚያብድ ሠው የምታገኝ አይምሰልህ፡፡ደግሞ ልጆቼን አንከርፍፌ መምጣቴ፡፡›› በማለት እየተበሳጨ ወደ ሳሎን ተመለሠ፡፡
ሁሉም መቀመጫቸውን ይዘው የእራት ድግሱን ለመቋደስ ሲዘጋጁ ሠዓቱ ሁለት ተኩል ሆኖ ነበር፡፡ እንዳንዱ ቤት ውስጥ ካሉት መጠጦች የሚስማማውን እየመረጠ ይዟል፡፡ የሁሴን ፊት በፈገግታ መጥለቅለቅ የቤቱን የቀድሞ ድባብ በተወሠነ ደረጃም ቢሆን አሻሽሎታል፡፡ ትንግርት ግን አሁንም እንደደነዘዘች ነው፡፡
ከጎኑ ብትቀመጥም ሩቅ ኪሎ ሜትሮች በሀሳብ ርቃ ሄዳለች፡፡ ፎዚያ ወደ እራት ዝግጅቱ ለማምራት ፈራ ተባ በምትልበት ቅጽበት ሁሴን እጁን በማጨብጨብ መናገር የሚፈልገው ነገር እንዳለ ሲናገር ሁሉም
በታላቅ ፀጥታ ውስጥ ገባ፡፡ ፎዚያም ክፍት ወንበር ፈልጋ ተቀመጠች፡፡ ሁሉም በአዕምሮአቸው የሚያጉላሉትን ጥያቄዎች መልስ ከንግግሩ ለማግኘት ጓጉቷል፡፡
‹‹ወደ እራት ፕሮግራሙ እንደዚህ በተጨናነቀና በታፈነ ድባብ እንድንገባ አልፈለኩም፡፡ በመጀመሪያ ኤደን ምን አልባት ጥሪዬን አትቀበይም ብዬ አስቤ ነበር ስለተገኘሽ በጣም ደስ ብሎኛል፡፡ መንታዎቹ ዕፀ - ህይወት እና ዕፀ - ፍቅርም ስለተገኛችሁ በጣም አስደስታችሁኛል፡፡ እናታችሁ ብትመጣም ደስ ይለኝ ነበር ግን ምንም አይደል…›› ንግግሩን ገታ አደረገና እጁን ወደ ኪሱ ከቶ አበባ እና ቀለበት ይዞ መጥቶ ጠረጴዛ ላይ አስቀመጠው፡፡
‹‹እንግዲህ የሦስት ቀን ተልዕኮዬን አጠናቅቄ መጥቻለሁ፤ እናንተም ይሄንን በማስመልከት በሞቀ ዝግጅት ተቀብላችሁኛል፡፡ ይሁን እንጂ አንድ የጠበቃችሁት ነገር ማለት የፈለጋችሁት ሠው ለማየት አልቻላችሁም፡፡ የዚህንም
ምክንያት እንዳብራራላችሁ የምትፈልጉ ይመስለኛል፡፡መቶ ፐርሰንት እርግጠኛ ባልሆንም ለሁለት ዓመታት በማይጨበጥ ፍቅር ያሠቃየችኝን ደራሲ ዛሬ ያገኘኋት መስሎኛል ፤ነገር ግን ላናግራት ወይንም በተስማማነው መሠረት ይሄንን እንቡጥ አበባ ላበረክትላት፤ ይሄንን ቀለበትም ላጠልቅላት አልቻልኩም፡፡ እንዲህ ስላችሁ የማትሆን ሴት ሆና ስላገኘኋት እንዳይመስላችሁ ፤እንዳውም ከጠበኳት በላይ ቆንጆ፤ ከአሠብኳት በላይ ውብ ነች፡፡ ጠይም የሆነ ኢትዮጵያዊ የቆዳ ቀለም፤ሞዴሊስት ለመሆን የሚያስችላት የሠውነት ቅርጽ፤ገና ያልተነካ እንቡጥ ወጣትነት፤በቃ አሟልቶ የፈጠራት የምትባል ዓይነት ነበረች፡፡››
‹‹እና መጨረሻው ምን ሆነ?›› ትዕግስት አጥታ ጣልቃ የገባችው ኤደን ነበረች፡፡ ከስምንት ወር በኋላ በአንድ ቤት ውስጥ ከእሱ ጋር ስትቀመጥ ዛሬ የመጀመሪያዋ ነው፡፡አሁንም ታፈቅረዋለች፤ግን በበፊቱ መልክ አይደለም፡፡ ከእሱ ጋር የነበራትን አብሮነት ሙሉ በሙሉ በጥሳዋለች፡፡ሌላ ሕይወት ሌላ የፍቅር መንገድ ውስጥ ገብታለች፡፡ እንዲያም ሆና ታፈቅረዋለች፡፡ስለምታፈቅረውም… ያፈቀራትን፤ለረጅም ጊዜ የተጎዳባትን፤ከእሷ ጋርም የተለያየባትን ልጅ አግኝቶ ጥሩ የፍቅር ስኬት ቢያጋጥመው በዚህን ወቅት ደስተኛ ትሆን ነበር፡፡ አሁን ግን ምኞቷ ሁሉ በመክሸፉ ግራ መጋባት ውስጥ ገብታለች፡፡
ሁሴን ንግግሩን ቀጠለ <<....መጨረሻም ሀሳቤን ቀየርኩ፡፡ ሳስበውና ውስጤን በጥልቀት ሳዳምጠው፤ ከእሷ በላይ ማጣት ማልፈልጋት፤ ከእሷ በላይ የማፈቅራት ልጅ ልቤ ውስጥ አገኘሁ፡፡››
‹‹ማነች?›› ከሦስት ሠው አፍ ነበር የወጣው፡፡
ሠሎሞን፣ ፎዚያ እና ኤደን፤ እንደተማከረ ሠው
በአንዴ አፋቸውን ከፈቱ፡፡ ትንግርት በመጠኑ
እንደመነቃቃት ብላ አይኖቿን አፍጣ
ታስተውለው ጀመር፡፡
ምን እየተካሄደ እንደሆነ ብዙም ያልገባቸው ከጎረቤት የተገኙት አሮጊትና መንታዎቹ የሠሎሞን ልጆች በዝምታ ይቁለጨለጫሉ፡፡
‹‹ማንነቷን ልነግራችሁ አይደል…፡፡›› አበባውን አነሳ ፊቱን ከጎኑ ወደ ተቀመጠችው ትንግርት አዞረ ...‹‹እነሆ ይሄ የሦስተኛና የመጨረሻ ዕድሌን የምሞክርበት የፍቅር መግለጫ አበባ ነው፡፡ ትንግርት አንቺን ከምስጢር በላይ እንደማፈቅርሽ ዛሬ በደንብ ነው የገባኝ፡፡ ዛሬውኑ ላገባሽ እፈልጋለሁ፤ እባክሽ አታሳፍሪኝ፡፡››
የቤቱ ሠው ሁሉ የሚካሄደውን ትዕይንት ማመን አልቻለም፡፡ አንደ ትንግርት ግን ሁሉም ነገር ቅዠት የሆነበት የለም፡፡ ሁሴን አበባውን እንድትቀበለው እጆቹን ለልመና እንደዘረጋ ነው፡፡ እሷ ግን መንቀሳቀስ አልቻለችም፤ ወንበሩን ወደ ኋላ አንፏቆ ክፍት ቦታ ካገኘ በኋላ በጉልበቱ ተንበረከከና አንገቱን በትህትና ወደ መሬት ደፍቶ ‹‹እባክሽ ተቀበይኝ፡፡›› አላት፡፡
‹‹ተቀበይው›› ሠሎሞን ነበር፡፡
<ተቀበይው ተቀበይው ሁሉም...» በመቀባበል ጮኹባት፡፡በደመነፍስ እጇን ዘርግታ ተቀበለችው፡፡ እቤቱ በጭብጨባ ደመቀ፡፡ በማስከተልም ጠረጴዛ ላይ ያለውን ቀለበት አንስቶ ጣቷ ላይ አጠለቀላት፡፡ዳግመኛ ደማቅ ጭብጨባ በቤቱ ተስተጋባ፡፡ የትንግር፦ ጉንጮች በእንባ ራሱ…፡፡ ቀስ ብላ አጠገቧ ያለውን ቦርሳዋን አነሳችና የጎን ኪሱን ከፈተችው፡፡ እጇን ሠደደችና የልብ ቅርፅ ኖሮት መሀከሉ የእሱ ስም የመጀመሪያ ፊደል ያለበት ሀብል መዛ አወጣችና አንገቱ ላይ አጠለቀችለት፡፡ አሁን ደግሞ ግራ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹዋቤ
ሁሴን ትንግርትን እንደያዘ ቤቱ ሲገባ የገጠመው ከገመተው በላይ የሆነ ዝግጅት ነው፡፡ ለወር ያህል የታሠበበት ይመስል ሁሉ
ነገር ደምቋል፡፡ ሳሎኑ በዲኮሬሽን አሸብርቋል፡፡
ቤቱ ውስጥ ያሉ ሠዎች የጎደሉ ነገሮችን ለሟሟላት ከወዲህ ወዲያ ውር ውር ይላሉ፡፡
የሳሎኑን በር ዘልቀው ወደ ውስጥ ከገቡ በኋላ ግን የቤቱ ድባብ ሙሉ በሙሉ ነበር የተቀየረው፡፡ ሁሉም በያለበት ደንዝዘው ቆሙ፡፡ ፎዚያ፣ ኤደን፣ ሠሎሞን፣ የሠለሞን ሁለት መንታ ልጆች፣ አንድ የጎረቤት አሮጊት፣ እቤቱ ውስጥ የጠበቁት ሠዎች ናቸው፡፡ ሁሉም ፈዞ እንደቆመ ሁሴን የትንግርትን እጆቿን ይዞ
እየጎተተ ወደ ሶፋው ወስዶ አስቀመጣትና ወደ መኝታ ክፍሉ አመራ፡፡
‹‹አልተሳካም ማለት ነው?›› ሠሎሞን ነበር ከደብረ ዘይት ጀምሮ አንደበቷን ተቆልፎ የደነዘዘችውን ትንግርትን የጠየቃት፡፡ሌሎችም መልሱን ለመስማት ወደ እሷ ተጠግተው ቆመዋል፡፡
‹‹ምን ነካችሁ? ምን ተፈጠረ?›› መልስ ስታጣ ዳግመኛ የጠየቀችው ፎዚያ ነች፡፡ከድንዛዜዋ ሳትወጣ ‹‹ባካችሁ ተውኝ እሱኑ ጠይቁት፤ እኔ ምንም አላውቅም፡፡››ብላ መለሰችላቸው፡፡
‹‹አብረሽው አልነበርሽ እንዴ?›› ኤደን ነች ጣልቃ የገባችው፡፡ ትንግርት ቀና ብላ አየቻት፡፡ እስከአሁን መኖሯን አላወቀችም ነበር፡፡
‹‹ነበርኩ.. ግን ለምን እራሱን አትጠይቁትም›› ተበሳጨች፡፡
‹‹ተዋት በቃ.... ለማንኛውም ተረጋጉ መጣሁ፡፡›› በማለት ወደ መኝታ ክፍል ፈራ ተባ እያለ አመራ፤ሰሎሞን፡፡ ዘልቆ ሲገባ ያልጠበቀው ነገር ነው ያየው፡፡ሁሴን በፈገግታ ተጥለቅልቆ.. ለብሶ የመጣውን ልብስ አውልቆ
ቡኒ ከለር ያለውን የጣሊያን ሱፉን እየለበሠ ነበር::
‹‹ምን እየተከናወነ ነው?›› ሠሎሞን በገረሜታ ጠየቀው፡፡
‹‹ሙሽራ አይደለሁ… እየተዘጋጀሁ ነዋ!!››
‹‹አግኝተሀታል ማለት ነው?››
<አግኝቻታለሁ ግን ይዣት አልመጣሁም .. አላናገርኳትም፤ እዛው ጥያት ነው የመጣሁት፡፡
‹‹አንተ ሠውዬ ጭራሽ ለይቶልሀል ማለት ነው?›› ይሄን ሁሉ ጊዜ ቁም ስቅላችንን ስታሳየን ከርመህ አንተም ይሄን ያህል ተሠቃይተህ ካገኘሀት በኋላ ጥያት መጣሁ ስትል ምን ለማለት ፈልገህ ነው?››
‹‹ባክህ አትነጫነጭ .. ድግሳችሁ አይከስርም አንድ እቅድ አለኝ ሂድና ንገራቸው.. ሁሉም ለእራት ዝግጁ ይሁኑ፤ አስር ደቂቃ አይፈጅብኝም መጣሁ፡፡››
‹‹ለነገሩ እውነትህን ነው... የለፋንበትን እራትማ መሬት ላይ ደፍተን አንሄድም፡፡ ሁለተኛ ግን ካንተ ጋር አብሮ የሚያብድ ሠው የምታገኝ አይምሰልህ፡፡ደግሞ ልጆቼን አንከርፍፌ መምጣቴ፡፡›› በማለት እየተበሳጨ ወደ ሳሎን ተመለሠ፡፡
ሁሉም መቀመጫቸውን ይዘው የእራት ድግሱን ለመቋደስ ሲዘጋጁ ሠዓቱ ሁለት ተኩል ሆኖ ነበር፡፡ እንዳንዱ ቤት ውስጥ ካሉት መጠጦች የሚስማማውን እየመረጠ ይዟል፡፡ የሁሴን ፊት በፈገግታ መጥለቅለቅ የቤቱን የቀድሞ ድባብ በተወሠነ ደረጃም ቢሆን አሻሽሎታል፡፡ ትንግርት ግን አሁንም እንደደነዘዘች ነው፡፡
ከጎኑ ብትቀመጥም ሩቅ ኪሎ ሜትሮች በሀሳብ ርቃ ሄዳለች፡፡ ፎዚያ ወደ እራት ዝግጅቱ ለማምራት ፈራ ተባ በምትልበት ቅጽበት ሁሴን እጁን በማጨብጨብ መናገር የሚፈልገው ነገር እንዳለ ሲናገር ሁሉም
በታላቅ ፀጥታ ውስጥ ገባ፡፡ ፎዚያም ክፍት ወንበር ፈልጋ ተቀመጠች፡፡ ሁሉም በአዕምሮአቸው የሚያጉላሉትን ጥያቄዎች መልስ ከንግግሩ ለማግኘት ጓጉቷል፡፡
‹‹ወደ እራት ፕሮግራሙ እንደዚህ በተጨናነቀና በታፈነ ድባብ እንድንገባ አልፈለኩም፡፡ በመጀመሪያ ኤደን ምን አልባት ጥሪዬን አትቀበይም ብዬ አስቤ ነበር ስለተገኘሽ በጣም ደስ ብሎኛል፡፡ መንታዎቹ ዕፀ - ህይወት እና ዕፀ - ፍቅርም ስለተገኛችሁ በጣም አስደስታችሁኛል፡፡ እናታችሁ ብትመጣም ደስ ይለኝ ነበር ግን ምንም አይደል…›› ንግግሩን ገታ አደረገና እጁን ወደ ኪሱ ከቶ አበባ እና ቀለበት ይዞ መጥቶ ጠረጴዛ ላይ አስቀመጠው፡፡
‹‹እንግዲህ የሦስት ቀን ተልዕኮዬን አጠናቅቄ መጥቻለሁ፤ እናንተም ይሄንን በማስመልከት በሞቀ ዝግጅት ተቀብላችሁኛል፡፡ ይሁን እንጂ አንድ የጠበቃችሁት ነገር ማለት የፈለጋችሁት ሠው ለማየት አልቻላችሁም፡፡ የዚህንም
ምክንያት እንዳብራራላችሁ የምትፈልጉ ይመስለኛል፡፡መቶ ፐርሰንት እርግጠኛ ባልሆንም ለሁለት ዓመታት በማይጨበጥ ፍቅር ያሠቃየችኝን ደራሲ ዛሬ ያገኘኋት መስሎኛል ፤ነገር ግን ላናግራት ወይንም በተስማማነው መሠረት ይሄንን እንቡጥ አበባ ላበረክትላት፤ ይሄንን ቀለበትም ላጠልቅላት አልቻልኩም፡፡ እንዲህ ስላችሁ የማትሆን ሴት ሆና ስላገኘኋት እንዳይመስላችሁ ፤እንዳውም ከጠበኳት በላይ ቆንጆ፤ ከአሠብኳት በላይ ውብ ነች፡፡ ጠይም የሆነ ኢትዮጵያዊ የቆዳ ቀለም፤ሞዴሊስት ለመሆን የሚያስችላት የሠውነት ቅርጽ፤ገና ያልተነካ እንቡጥ ወጣትነት፤በቃ አሟልቶ የፈጠራት የምትባል ዓይነት ነበረች፡፡››
‹‹እና መጨረሻው ምን ሆነ?›› ትዕግስት አጥታ ጣልቃ የገባችው ኤደን ነበረች፡፡ ከስምንት ወር በኋላ በአንድ ቤት ውስጥ ከእሱ ጋር ስትቀመጥ ዛሬ የመጀመሪያዋ ነው፡፡አሁንም ታፈቅረዋለች፤ግን በበፊቱ መልክ አይደለም፡፡ ከእሱ ጋር የነበራትን አብሮነት ሙሉ በሙሉ በጥሳዋለች፡፡ሌላ ሕይወት ሌላ የፍቅር መንገድ ውስጥ ገብታለች፡፡ እንዲያም ሆና ታፈቅረዋለች፡፡ስለምታፈቅረውም… ያፈቀራትን፤ለረጅም ጊዜ የተጎዳባትን፤ከእሷ ጋርም የተለያየባትን ልጅ አግኝቶ ጥሩ የፍቅር ስኬት ቢያጋጥመው በዚህን ወቅት ደስተኛ ትሆን ነበር፡፡ አሁን ግን ምኞቷ ሁሉ በመክሸፉ ግራ መጋባት ውስጥ ገብታለች፡፡
ሁሴን ንግግሩን ቀጠለ <<....መጨረሻም ሀሳቤን ቀየርኩ፡፡ ሳስበውና ውስጤን በጥልቀት ሳዳምጠው፤ ከእሷ በላይ ማጣት ማልፈልጋት፤ ከእሷ በላይ የማፈቅራት ልጅ ልቤ ውስጥ አገኘሁ፡፡››
‹‹ማነች?›› ከሦስት ሠው አፍ ነበር የወጣው፡፡
ሠሎሞን፣ ፎዚያ እና ኤደን፤ እንደተማከረ ሠው
በአንዴ አፋቸውን ከፈቱ፡፡ ትንግርት በመጠኑ
እንደመነቃቃት ብላ አይኖቿን አፍጣ
ታስተውለው ጀመር፡፡
ምን እየተካሄደ እንደሆነ ብዙም ያልገባቸው ከጎረቤት የተገኙት አሮጊትና መንታዎቹ የሠሎሞን ልጆች በዝምታ ይቁለጨለጫሉ፡፡
‹‹ማንነቷን ልነግራችሁ አይደል…፡፡›› አበባውን አነሳ ፊቱን ከጎኑ ወደ ተቀመጠችው ትንግርት አዞረ ...‹‹እነሆ ይሄ የሦስተኛና የመጨረሻ ዕድሌን የምሞክርበት የፍቅር መግለጫ አበባ ነው፡፡ ትንግርት አንቺን ከምስጢር በላይ እንደማፈቅርሽ ዛሬ በደንብ ነው የገባኝ፡፡ ዛሬውኑ ላገባሽ እፈልጋለሁ፤ እባክሽ አታሳፍሪኝ፡፡››
የቤቱ ሠው ሁሉ የሚካሄደውን ትዕይንት ማመን አልቻለም፡፡ አንደ ትንግርት ግን ሁሉም ነገር ቅዠት የሆነበት የለም፡፡ ሁሴን አበባውን እንድትቀበለው እጆቹን ለልመና እንደዘረጋ ነው፡፡ እሷ ግን መንቀሳቀስ አልቻለችም፤ ወንበሩን ወደ ኋላ አንፏቆ ክፍት ቦታ ካገኘ በኋላ በጉልበቱ ተንበረከከና አንገቱን በትህትና ወደ መሬት ደፍቶ ‹‹እባክሽ ተቀበይኝ፡፡›› አላት፡፡
‹‹ተቀበይው›› ሠሎሞን ነበር፡፡
<ተቀበይው ተቀበይው ሁሉም...» በመቀባበል ጮኹባት፡፡በደመነፍስ እጇን ዘርግታ ተቀበለችው፡፡ እቤቱ በጭብጨባ ደመቀ፡፡ በማስከተልም ጠረጴዛ ላይ ያለውን ቀለበት አንስቶ ጣቷ ላይ አጠለቀላት፡፡ዳግመኛ ደማቅ ጭብጨባ በቤቱ ተስተጋባ፡፡ የትንግር፦ ጉንጮች በእንባ ራሱ…፡፡ ቀስ ብላ አጠገቧ ያለውን ቦርሳዋን አነሳችና የጎን ኪሱን ከፈተችው፡፡ እጇን ሠደደችና የልብ ቅርፅ ኖሮት መሀከሉ የእሱ ስም የመጀመሪያ ፊደል ያለበት ሀብል መዛ አወጣችና አንገቱ ላይ አጠለቀችለት፡፡ አሁን ደግሞ ግራ
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ዛሬ ላይ…አሁን
ሳባ ከሰመጠችበት የአመታት ትዝታ ወጥታ…ወዳለችበት ስትመለስ ከታላቅ መገረም ጋር ነው፡፡በዛን ወቅት በዛን ለሊት በወሲብ የረካችውን እርካታ በህይወቷ ሙሉ ድጋሚ አግኝታው አታውቅም..እናም ደግሞ ፈፅሞ አትዘነጋውም..እርግጥ ሴት ሆና የመጀመሪያ ቀን የወሲብ ገጠመኟን በመጥፎም ሆነ በክፉ የማታስታውስ የለችም…የእሷ ግን ከነጣዕምና ከነቃናው ዕድሜ ልኳን ይሄው እንዲህ ስብርብር ብላ አቅሏን አጥታ ደንዝዛ እንኳን ምንም የደበዘዘ ነገር የለም፡፡ እንደምንም ከተቀመጠችበት ተነስታ ለመቆም ስትሞክር እግሯ የእሷ መሆኑ እስኪጠፋት ድረስ ደንዝዞ ከቁጥጥሯ ውጭ ሆኗል ..እንደምንም ፈጠን አለችና የበረንዳውን ብረት በመያዝ ቆመች….ከድንዛዜዋ እስክትወጣ ከ5 ደቂቃ በላይ ወስደባት…
ትዝ ይላታል እዚህ ቦታ ስትቀመጥ ከለሊቱ 8 ሰዓት አካባቢ ነበር..አሁን ግን ነግቶ..ወፎች ግቢ ውስጥ ያሉ ሁለት ዛፎች ላይ ሰፍረው ጭጭጭ እያሉ መንፈስ የሚያንሰፈስፍ ሚስጥራዊ መዝሙር አየዘመሩ ነው…ግቢ ውስጥ ከወዲህ ወዲያ ስትንጎራድድ ዘበኛዋ ለኦሎምፒክ እንደሚዘጋጅ አትሌት በዛ ለሊት የስፖርት ቱታ ለብሶ ግቢው ውስጥ ባለ ከፍት ቦታ ስፖርት እየሰራ ነው….በርከት ላሉ ደቂቃዎች ቆማ ተመለከተችው…አንዴ ፑሻፕ ይሰራል፤ደግሞ ክብደት ያነሳል፤ደግሞ ቁጭ ብድግ ይላል፡፡
‹ታድለህ..››አለችና ወደውስጥ ገባች፡፡
…ቀጥታ ወደሻወር ቤት ነው ያመራችው…ሰውነቷን ታጠበች..ለመታጠብ ረጅም ሰዓት ነው የፈጀባት.. ምን አልባትም ከአንድ ሰዓት በላይ....ከዛ ልብሷን ቀየረች..የተወሰነ ሜካፕ በመጠቀም ራሷን አሰማመረችና መድሀኒቷን ወደቦርሳዋ በማስገባት መኝታ ቤቷን ለቃ ለመውጣት ዝግጁ ስትሆን ሁለት ሰዓት ከሩብ ሆኖ ነበር….ቀጥታ ወደሆስፒታል ነው የምትሄደው…እርግጥ ለቀጠሮዋ ሶስት ቀን ይቀረዋል..ግን ደግሞ ላለፉት ሶስት ቀን መድሀኒቷን አልተጠቀመችም..ያንን ለሀኪሟ ተናግራ መፍትሄ የሚለውን እንዲነግራት ትፈልጋለች….እርግጥ ልታገኘው የፈለገችው ለዚህ ብቻ አይደለም…ከእሱ ጋር መነጋገር ሰላም እንዲሰማት ስለሚያደርጋት ነው፡፡ ፎቅ ላይ ካለው መኝታ ቤቷ ወደሳሎን ስትወርድ ፊት ለፊቷ ባለው የምግብ ጠረጴዛ በምግብ ተሞልቶ አየች…ግራ ገባት…ሞባይሏን አወጣችና ሰዓቷን መልሳ አየችው 2.20 ነው፡፡ተመላላሽ ሰራተኛዋ ከ3 ሰዓት በፊት ስትገባ አይታት አታውቅም …እንደዛ አይነት ንግግርም የላቸውም
‹‹…ታዲያ አንዴት ዛሬ ልታደርገው ቻለች?››በማለት ቦርሳዋን ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠችና ወደኪችን ስትሄድ፤ባዶ ነው፡፡ ኪችኑ ሁሉ ነገር ፅድት ብሎ እቃዎች ሁሉ በየቦታቸው ስለተቀመጡ ከነጋ ሰው የገባበትም አይመስልም፡፡ ቀጥታ ወደምግቡ ተመለሰችና እየጣፈጣት የምትፈልገውን ያህል ከተመገበች በኃላ እጇን ተጣጥባ ቦርሳዋን ይዛ ወጣችና ቀጥታ ወደ መኪናዋ ስትሄድ ትናንት ከአሰላ ስትመጣ አልብሷት የነበረውን አቧራና ጭቃ ከላዩ ላይ ተወግዶ ፏ ብላ ፀድታለች፡፡ደስ አላት፡፡ገባችና ቁልፏን አሽከርክራ ሞተሩን ማሞቅ ጀመረች በዚህን ጊዜ የመኪናውን ድምፅ ሰምቶ ከዘበኛ ቤት ወጣና በራፉን ከፈተላት..መኪናዋን አንቀሳቀሰችና .ስሩ.ስትደርስ.አቆመች አንገቷን በመስኮት አወጣችና..‹‹መኪናዬን ንፁህ ስላደረክልኝ አመሰግናለሁ››አለችው
‹‹አረ ችግር የለውም…ቁጭ ከምል ብዬ ነው››
‹‹ሳሎን ቁርስ አለልህ.. ግባና ብላ ››
‹‹እሺ እበላለሁ››
‹‹እሺ ቻው›ብላ መኪናዋን አንቀሳቀሰችና ወዲያው መልሳ አቆመችው፡፡
‹‹ይቅርታ ስምህ አይያዝልኝም››
‹‹ቀናው››
‹‹ያልተለመደ ስም ነው…ቆይ አለም መጥታ ነበረ አይደል.?ታዲያ.የት ሄደች?››
‹‹መቼ? ዛሬ ከሆነ አልመጣችም፡፡››
‹‹ታዲያ ቁርሱን ማን ነው የሰራው?››አቀረቀረ…
‹‹ምነው መልስ የለህም?››ኮስተርተር ብላ ጠየቀችው፡፡
‹‹ምነው የማይሆን ነገር ሰራሁ እንዴ?››
የምትመልሰው ግራ ገባት ‹‹እኔ እንጃ.. ለማንኛውም በጣም ይጣፍጣል›› አለችውና ከመገረም ውስጥ ሳትወጣ መኪናውን አስነስታ ተፈተለከች፡፡
ከዶክተሩ ጋር ተገናኝታ ፊት ለፊት ተቀምጣለች…የሆነውን ነገር ሁሉ ነግራው ምክር እየሰጣት ነው፡፡
ይሄውልሽ ሳባ .ይሄንን ነገር ሲሪዬስ አድርገሽ እንድትወስጂው እፈልጋለሁ››
‹‹እሺ ዶ/ር ሁለተኛ አይለመደኝም፡፡››
‹‹ቤተሰቦችሽም ሊረዱሽ ይገባል፡፡››
‹‹ቤተሰቦቼ አሰላ ነው ያሉት‹‹ያንን ማድረግ አይችሉም፡፡››
‹‹ሳባ ከእኔ በተጨማሪ በቅርብሽ ሆኖ ሁሉን ነገር እየተከታተለ ሊረዳሽ የሚችል ሰው ማግኘት አለብሽ.››.
‹‹አይ ዶ/ር እንዲሁ እድሜ ለመግፋት ካልሆነ በስተቀር የእኔ ነገር ተስፋ.ያለው........ .አይመስለኝም…በአጠቃላይ.መኖርደክሞኛል..መጨረሻ.መዳረሻዬ.
መቃብር ቤት፤
ከዛ ካመለጥኩ በሰንሰለት ታስሬ አማኑኤል…በጣም እድለኛ ከሆንኩ ደግሞ እስር ቤት የሚሆን ይመስለኛል››
‹‹ከእንደዚህ አይነት አሉታዊ አስተሳሰቦች ራስሽን ማራቅ አለብሽ..አሉታዊ ሀሳብ ቀስ በቀስ በመጀመሪያ በአዕምሯችን ስሩን እየሰደደ ይሄዳል.. ከዛ የምናስብበትን መንገድ ይቀይራል፡፡ እኛ ደግሞ የሀሳባችን ውጤት ስለሆንን በሂደት በአላስፈላጊ መንገድ እንድንጓዝ እየቀየረን ይሄዳል፡፡ ቀድሞ የማናውቀው አይነት ሰው ከውስጣችን ይበቅላል››
‹‹.ይበቅላል አልክ…በቅሎ አድጓል እኮ…ብቻ ዶ/ር ሁሉ ነገር ይጨንቃል››
እኮ የምልሽ እሱን ነው.መድሀኒቱ ብቻውን ብዙም ውጤታማ አይሆንም፤ አንቺም በተስፋ መታገል አለብሽ፡፡ ከዚህ ውጥረት በአፋጣኝ እራስሽን ማላቀቅ አለብሽ ምን መሰለሽ ውጥረት ከቁጥጥራችን ውጭ ከወጣ ወደ ስራ ህይወታችን ይሄድና ስህተት የሆነ ውሳኔ እንድንወስን ያደርገናል፡፡ ከዛም አልፎ የቤተሰብ ህይወታችን ላይ ጫና ያሳድራል፡፡ውጥረት ያመጣብንን ችግር በወቅቱና በሰዓቱ ካልተቆጣጠርነው እዕምሯችንና አካላችንን ይቆጣጠርና የጤና ችግር ከማስከተሉም በላይ አካላዊ በሽታና አእምሮአዊ በሽታ ያስከትልብናል..በሂደትም ለባህሪ ለውጥ ይዳርገናል፡፡ የባህሪ ለውጥ ማለት ደግሞ የምናስብበት መንገድ ነገሮችን የምናይበትና የምንመዝንበት ሚዛን እየተቀየረና እየተዛባ ይሄዳል ማለት ነው፡፡ ያ ደግሞ በውሳኔያችን ላይ ለውጥ ያመጣል፡፡ በስተመጨረሻም የሕይወታችንን መስመር ሙሉ ለሙሉ የመቀየር አቅም ይኖረዋል፡፡ስለዚህ በአእምሮችን ላይ የሚከሰት ማንኛውንም ውጥረት በጊዜና በሰአቱ ማከም ይጠበቅብናል፡፡ ለዛ ነው የምጨቀጭቅሽ››
‹‹እሺ ዶ/ር እሞክራለሁ..ማለቴ ለጤናዬ እፋለማለሁ››
አዎ እንደዛ ማድረግ አለብሽ…አየሽ ራሳችን ከውስጣችን ጋር ስናጣምር ህይወት ምን ያህል ንፁህ በደስታ የተሞላችና ህመም አልባ እንደሆነች እንረዳለን፡፡ለአዕምሯችን ማንኛውንም አይነት ጥያቄ ብናቀርብለት ያለማቅማማት መልስ ይሰጠናል፡፡ ጥያቄው ብዛትም ሆነ ክብደት ችግር የለውም ብቻ ሁሌ መልስ አያጣም፡፡ ችግሩ መልሱ ትክክል ሊሆንም ላይሆንም ይችላል..ስለዚህ እኛም ራሳችንን የምንጠይቅበት ሆነ ሌሎች የሚጠይቁንን ጥያቄዎች መጠንቀቅ አለብን፡፡ ምክንያቱም አዕምሯችን የሚሰጠን መልስ በምናቀርብለት የጥያቄ ይዘት ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ ለምሳሌ ይህች ሀገር ወዴት እየሄደች ነው? የሚል ጥያቄ ለአዕምሯችን ቢቀርብለት ቀድሞ የሚመጣለት መልስ ስለጦርነት፤ስለኑሮ ውድነትና፤መሰል ነገሮች ነው...መልሱም በዛ ዙሪያ የሚሽከረከር ነው የሚሆነው፡፡ በተለየ መንገድ ደግሞ ኢትዬጵያ ላንቺ ምንሽ ነች? ቢሆን ጥያቄው...ስለውበቷ፤ ስለ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ዛሬ ላይ…አሁን
ሳባ ከሰመጠችበት የአመታት ትዝታ ወጥታ…ወዳለችበት ስትመለስ ከታላቅ መገረም ጋር ነው፡፡በዛን ወቅት በዛን ለሊት በወሲብ የረካችውን እርካታ በህይወቷ ሙሉ ድጋሚ አግኝታው አታውቅም..እናም ደግሞ ፈፅሞ አትዘነጋውም..እርግጥ ሴት ሆና የመጀመሪያ ቀን የወሲብ ገጠመኟን በመጥፎም ሆነ በክፉ የማታስታውስ የለችም…የእሷ ግን ከነጣዕምና ከነቃናው ዕድሜ ልኳን ይሄው እንዲህ ስብርብር ብላ አቅሏን አጥታ ደንዝዛ እንኳን ምንም የደበዘዘ ነገር የለም፡፡ እንደምንም ከተቀመጠችበት ተነስታ ለመቆም ስትሞክር እግሯ የእሷ መሆኑ እስኪጠፋት ድረስ ደንዝዞ ከቁጥጥሯ ውጭ ሆኗል ..እንደምንም ፈጠን አለችና የበረንዳውን ብረት በመያዝ ቆመች….ከድንዛዜዋ እስክትወጣ ከ5 ደቂቃ በላይ ወስደባት…
ትዝ ይላታል እዚህ ቦታ ስትቀመጥ ከለሊቱ 8 ሰዓት አካባቢ ነበር..አሁን ግን ነግቶ..ወፎች ግቢ ውስጥ ያሉ ሁለት ዛፎች ላይ ሰፍረው ጭጭጭ እያሉ መንፈስ የሚያንሰፈስፍ ሚስጥራዊ መዝሙር አየዘመሩ ነው…ግቢ ውስጥ ከወዲህ ወዲያ ስትንጎራድድ ዘበኛዋ ለኦሎምፒክ እንደሚዘጋጅ አትሌት በዛ ለሊት የስፖርት ቱታ ለብሶ ግቢው ውስጥ ባለ ከፍት ቦታ ስፖርት እየሰራ ነው….በርከት ላሉ ደቂቃዎች ቆማ ተመለከተችው…አንዴ ፑሻፕ ይሰራል፤ደግሞ ክብደት ያነሳል፤ደግሞ ቁጭ ብድግ ይላል፡፡
‹ታድለህ..››አለችና ወደውስጥ ገባች፡፡
…ቀጥታ ወደሻወር ቤት ነው ያመራችው…ሰውነቷን ታጠበች..ለመታጠብ ረጅም ሰዓት ነው የፈጀባት.. ምን አልባትም ከአንድ ሰዓት በላይ....ከዛ ልብሷን ቀየረች..የተወሰነ ሜካፕ በመጠቀም ራሷን አሰማመረችና መድሀኒቷን ወደቦርሳዋ በማስገባት መኝታ ቤቷን ለቃ ለመውጣት ዝግጁ ስትሆን ሁለት ሰዓት ከሩብ ሆኖ ነበር….ቀጥታ ወደሆስፒታል ነው የምትሄደው…እርግጥ ለቀጠሮዋ ሶስት ቀን ይቀረዋል..ግን ደግሞ ላለፉት ሶስት ቀን መድሀኒቷን አልተጠቀመችም..ያንን ለሀኪሟ ተናግራ መፍትሄ የሚለውን እንዲነግራት ትፈልጋለች….እርግጥ ልታገኘው የፈለገችው ለዚህ ብቻ አይደለም…ከእሱ ጋር መነጋገር ሰላም እንዲሰማት ስለሚያደርጋት ነው፡፡ ፎቅ ላይ ካለው መኝታ ቤቷ ወደሳሎን ስትወርድ ፊት ለፊቷ ባለው የምግብ ጠረጴዛ በምግብ ተሞልቶ አየች…ግራ ገባት…ሞባይሏን አወጣችና ሰዓቷን መልሳ አየችው 2.20 ነው፡፡ተመላላሽ ሰራተኛዋ ከ3 ሰዓት በፊት ስትገባ አይታት አታውቅም …እንደዛ አይነት ንግግርም የላቸውም
‹‹…ታዲያ አንዴት ዛሬ ልታደርገው ቻለች?››በማለት ቦርሳዋን ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠችና ወደኪችን ስትሄድ፤ባዶ ነው፡፡ ኪችኑ ሁሉ ነገር ፅድት ብሎ እቃዎች ሁሉ በየቦታቸው ስለተቀመጡ ከነጋ ሰው የገባበትም አይመስልም፡፡ ቀጥታ ወደምግቡ ተመለሰችና እየጣፈጣት የምትፈልገውን ያህል ከተመገበች በኃላ እጇን ተጣጥባ ቦርሳዋን ይዛ ወጣችና ቀጥታ ወደ መኪናዋ ስትሄድ ትናንት ከአሰላ ስትመጣ አልብሷት የነበረውን አቧራና ጭቃ ከላዩ ላይ ተወግዶ ፏ ብላ ፀድታለች፡፡ደስ አላት፡፡ገባችና ቁልፏን አሽከርክራ ሞተሩን ማሞቅ ጀመረች በዚህን ጊዜ የመኪናውን ድምፅ ሰምቶ ከዘበኛ ቤት ወጣና በራፉን ከፈተላት..መኪናዋን አንቀሳቀሰችና .ስሩ.ስትደርስ.አቆመች አንገቷን በመስኮት አወጣችና..‹‹መኪናዬን ንፁህ ስላደረክልኝ አመሰግናለሁ››አለችው
‹‹አረ ችግር የለውም…ቁጭ ከምል ብዬ ነው››
‹‹ሳሎን ቁርስ አለልህ.. ግባና ብላ ››
‹‹እሺ እበላለሁ››
‹‹እሺ ቻው›ብላ መኪናዋን አንቀሳቀሰችና ወዲያው መልሳ አቆመችው፡፡
‹‹ይቅርታ ስምህ አይያዝልኝም››
‹‹ቀናው››
‹‹ያልተለመደ ስም ነው…ቆይ አለም መጥታ ነበረ አይደል.?ታዲያ.የት ሄደች?››
‹‹መቼ? ዛሬ ከሆነ አልመጣችም፡፡››
‹‹ታዲያ ቁርሱን ማን ነው የሰራው?››አቀረቀረ…
‹‹ምነው መልስ የለህም?››ኮስተርተር ብላ ጠየቀችው፡፡
‹‹ምነው የማይሆን ነገር ሰራሁ እንዴ?››
የምትመልሰው ግራ ገባት ‹‹እኔ እንጃ.. ለማንኛውም በጣም ይጣፍጣል›› አለችውና ከመገረም ውስጥ ሳትወጣ መኪናውን አስነስታ ተፈተለከች፡፡
ከዶክተሩ ጋር ተገናኝታ ፊት ለፊት ተቀምጣለች…የሆነውን ነገር ሁሉ ነግራው ምክር እየሰጣት ነው፡፡
ይሄውልሽ ሳባ .ይሄንን ነገር ሲሪዬስ አድርገሽ እንድትወስጂው እፈልጋለሁ››
‹‹እሺ ዶ/ር ሁለተኛ አይለመደኝም፡፡››
‹‹ቤተሰቦችሽም ሊረዱሽ ይገባል፡፡››
‹‹ቤተሰቦቼ አሰላ ነው ያሉት‹‹ያንን ማድረግ አይችሉም፡፡››
‹‹ሳባ ከእኔ በተጨማሪ በቅርብሽ ሆኖ ሁሉን ነገር እየተከታተለ ሊረዳሽ የሚችል ሰው ማግኘት አለብሽ.››.
‹‹አይ ዶ/ር እንዲሁ እድሜ ለመግፋት ካልሆነ በስተቀር የእኔ ነገር ተስፋ.ያለው........ .አይመስለኝም…በአጠቃላይ.መኖርደክሞኛል..መጨረሻ.መዳረሻዬ.
መቃብር ቤት፤
ከዛ ካመለጥኩ በሰንሰለት ታስሬ አማኑኤል…በጣም እድለኛ ከሆንኩ ደግሞ እስር ቤት የሚሆን ይመስለኛል››
‹‹ከእንደዚህ አይነት አሉታዊ አስተሳሰቦች ራስሽን ማራቅ አለብሽ..አሉታዊ ሀሳብ ቀስ በቀስ በመጀመሪያ በአዕምሯችን ስሩን እየሰደደ ይሄዳል.. ከዛ የምናስብበትን መንገድ ይቀይራል፡፡ እኛ ደግሞ የሀሳባችን ውጤት ስለሆንን በሂደት በአላስፈላጊ መንገድ እንድንጓዝ እየቀየረን ይሄዳል፡፡ ቀድሞ የማናውቀው አይነት ሰው ከውስጣችን ይበቅላል››
‹‹.ይበቅላል አልክ…በቅሎ አድጓል እኮ…ብቻ ዶ/ር ሁሉ ነገር ይጨንቃል››
እኮ የምልሽ እሱን ነው.መድሀኒቱ ብቻውን ብዙም ውጤታማ አይሆንም፤ አንቺም በተስፋ መታገል አለብሽ፡፡ ከዚህ ውጥረት በአፋጣኝ እራስሽን ማላቀቅ አለብሽ ምን መሰለሽ ውጥረት ከቁጥጥራችን ውጭ ከወጣ ወደ ስራ ህይወታችን ይሄድና ስህተት የሆነ ውሳኔ እንድንወስን ያደርገናል፡፡ ከዛም አልፎ የቤተሰብ ህይወታችን ላይ ጫና ያሳድራል፡፡ውጥረት ያመጣብንን ችግር በወቅቱና በሰዓቱ ካልተቆጣጠርነው እዕምሯችንና አካላችንን ይቆጣጠርና የጤና ችግር ከማስከተሉም በላይ አካላዊ በሽታና አእምሮአዊ በሽታ ያስከትልብናል..በሂደትም ለባህሪ ለውጥ ይዳርገናል፡፡ የባህሪ ለውጥ ማለት ደግሞ የምናስብበት መንገድ ነገሮችን የምናይበትና የምንመዝንበት ሚዛን እየተቀየረና እየተዛባ ይሄዳል ማለት ነው፡፡ ያ ደግሞ በውሳኔያችን ላይ ለውጥ ያመጣል፡፡ በስተመጨረሻም የሕይወታችንን መስመር ሙሉ ለሙሉ የመቀየር አቅም ይኖረዋል፡፡ስለዚህ በአእምሮችን ላይ የሚከሰት ማንኛውንም ውጥረት በጊዜና በሰአቱ ማከም ይጠበቅብናል፡፡ ለዛ ነው የምጨቀጭቅሽ››
‹‹እሺ ዶ/ር እሞክራለሁ..ማለቴ ለጤናዬ እፋለማለሁ››
አዎ እንደዛ ማድረግ አለብሽ…አየሽ ራሳችን ከውስጣችን ጋር ስናጣምር ህይወት ምን ያህል ንፁህ በደስታ የተሞላችና ህመም አልባ እንደሆነች እንረዳለን፡፡ለአዕምሯችን ማንኛውንም አይነት ጥያቄ ብናቀርብለት ያለማቅማማት መልስ ይሰጠናል፡፡ ጥያቄው ብዛትም ሆነ ክብደት ችግር የለውም ብቻ ሁሌ መልስ አያጣም፡፡ ችግሩ መልሱ ትክክል ሊሆንም ላይሆንም ይችላል..ስለዚህ እኛም ራሳችንን የምንጠይቅበት ሆነ ሌሎች የሚጠይቁንን ጥያቄዎች መጠንቀቅ አለብን፡፡ ምክንያቱም አዕምሯችን የሚሰጠን መልስ በምናቀርብለት የጥያቄ ይዘት ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ ለምሳሌ ይህች ሀገር ወዴት እየሄደች ነው? የሚል ጥያቄ ለአዕምሯችን ቢቀርብለት ቀድሞ የሚመጣለት መልስ ስለጦርነት፤ስለኑሮ ውድነትና፤መሰል ነገሮች ነው...መልሱም በዛ ዙሪያ የሚሽከረከር ነው የሚሆነው፡፡ በተለየ መንገድ ደግሞ ኢትዬጵያ ላንቺ ምንሽ ነች? ቢሆን ጥያቄው...ስለውበቷ፤ ስለ
#ኢትዬጵያዊቷ_ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ሁለቱም እርቃናቸውን ተኝተው ፊት ለፊት እየተያዩ ማውራት ቀጠሉ?
"የሆነ ነገር ትጠይቀኛለህ ብዬ ስጠብቅ ነበር ግን ማድረግ አልቻልክም"አለችው
እንደመደንገጥ ብሎ ፀጉሯን በእጆቹ እየላገ"ምንድነው የእኔ ፍቅር?ምን ልጠይቅሽ?"
"ከዚህ በፊት የዛሬ ሳምንት አካባቢ ከዚህ ደን በሰላም ከወጣን ደግመህ ጠይቀኝ ብዬህ ነበር...አሁን ሳስበው ግን ጥያቄውን ሙሉ በሙሉ ረስተኸዋል…በፊትም ከልብህ አልነበረም የጠየቅከኝ ማለት ነው "አለች እንደማኩረፍ ብላ።
"አንቺ በጣም ተሳስተሻል...ያንን ጥያቄ ለደቂቃም ረስቼው አላውቅም..አሁን ደግሜ ብጠይቃትና እምቢ ብትለኝ እንዴት ነው የምቋቋመው?"ብዬ ሰግቼ ነበር ...
"እና "
"እናማ...አንቺ ቆንጆ ጠይም ወጣት ወደሀገርሽ ይዘሽኝ ብትበሪ ምን ይመስልሻል?"
"ይዞ መሄድን ይዤህ ሄዳለው።ግን ልመለስ ብትል ማንም አይሰማህም"
"ይሁን ተስማምቼያለው...አልፎ..አልፎ ሀገሬ ሲናፍቀኝ ይዘሽኝ መጥተሽ እንደምታሳይኝ እተማመናለው።››
"እሱን ፀባይህ እየታየ የሚወሰን ነው።"ብላ ከመኝታዋ ተነሳችና እርቃን ገላዋን ለእሱ እይታ አጋልጣ ወረደች..ቀጥታ ወደሰካችው ስልኳ ሄደችና ነቀለችው።ተመልሳ መጣችና አልጋው ጠርዝ ላይ ቁጭ ብላ ወደሀገር ቤት ወንድሟ ጋር ደወለች.፡፡ከሰከንዶች በኃላ የወንሟን ተወዳጅ ድምፅ በጆሮዋ ሲንቆረቆር ልትሰማ እንደሆነ ስታስብ ሰውነቷን ሌላ ዙር ሙቀት ወረራት...ግን እንዳሰበችው የወንድሟ ሞባይል ሊጠራ አልቻለም...ደግማ ሞከረች።በሁለተኛ ቁጥሩም ሞከረች ተመሳሳይ ነው።
"ብሽቅ...በዚህ ቀን ሞባይሉን ያጠፍል"ተበሳጨች።ሌላ ተለዋጭ ሀሳብ መጣላት።የምስራቅ ቁጥርን ከሞባይሏ ፈለገችና ደወለች።ልክ እንደወንድሟ ስልክ የእሷም አይሰራም።
‹‹የሰዎቹ ስልክ ሁሉ አይሰራም"በተኛበት አይኖቹን እያቁለጨለጨ እየተመለከታት ለነበረው ካርሎስ ነገረችው። ከተኛበት ተነሳና ከአልጋው ወርዶ አልጋ ልብሱን ከአልጋው ላይ ገፎ እርቃን ሰውነቷን በማልበስ"አይዞሽ ተረጋጊ...አህጉር አቋራጭ ጥሪ እኮ ነው እያደረግሽ ያለሽው፡፡ ኔትወርኩ ችግር ሊኖርበት ይችላል...አሁን ባይሆን ጥዋት ሲነጋ ሊሰራ ይችላል...ካልሆነም ሌላ ዘዴ እንፈልጋለን።››ሲል ሊያፅናናት ሞከረ፡፡
ሌላ ዘዴ ሲላት በአእምሮዋ ተለዋጭ ዘዴ ብልጭ አለባት፡፡ ለወንድሞ...ነፃ እንደወጣችና ከቀናት በኃላ ወደሀገሯ እንደምትመለስ ልትፅፍለት ወሰነችና ኢሜሏን ከፈተች። ከአለም እይታ በተሰወረችባቸው 20 በሚሆኑ ቀናቶች በርካታ ኢሜሎች ተልከውላታል።አብዛኛዎቹ ከወንድሟ.. ከዛም ከመስሪያ ቤቷ ሲሆን ለመጨረሻ ጊዜ ግን የተላከላት ከማትጠብቀው ሰው ነበር… በድንጋጤ ከተቀመጠችበት ተነስታ ስትቆም ካርሎስ አልብሷት የነበረው አልጋ ልብስ ከላዩ ላይ ወደቀና እርቃኗን ቀረች...
‹‹ምንድነው ፍቅር...?››
‹‹ሰውዬው ተደጋጋሚ መልዕክት ልኮልኛል?››
ግራ ገባው"የትኛው ሰውዬ?"
"ሀለቃህ...ዳግላስ?"
ከመደንገጡ የተነሳ ተንደርድሮ ወደእሷ ቀረበና ሞባይሉን ከእጇ ተቀበላትና ኢሜሉን ተራ በተራ እየከፈተ አየ...ከዛ በድንጋጤ እግሮቹ ዝሎ ወለሉ ላይ ተዘረፈጠ..ኑሀሚም ድንጋጤው ክፍኛ አዝሏት ስሩ ተንበረከከች፡፡
ስልኩን ተቀብላው ኢሜሉን በማንበብ የሆነውን ለመረዳት የሚያስችል ጥንካሬ ከውስጧ ማግኘት አልቻለችም።ሽው እያለ መጥቶ እርቃን ሰውነቷን የሚገርፋት እርጥብ አየር ነፍሷን ጭምር እያቀዘቀዘው ነው።
"ምንድነው የሆነው?"ጥንካሬዋን አሰባስባ የሆነውን ሁሉ ከእሱ አንደበት ለመስማት ጠየቀችው።ስልኩን መልሶ ከፈተና በኢሜሏ የተላከለትን ፎቶዎች አወጣና"ወንድምሽ...እዚህ መጥቷል"አላት
"ወንድሜ ?እዚህ እንዴት?››ካርሎስ የሚያወራው ነገር ምንም እየገባት አይደለም፡፡
"አላውቅም ግን..እይ ተመልከቺ ዳግላስ እጅ ነው ያለው...ፎቶውን ወደእሷ አቅርቦ እያሳያት"ይሄውልሽ...ይሄንን ቦታ በደንብ አውቀዋለው፡፡ ማንም ሊደርሶበት የማይችለው የዳግላስ ምሽግ የሆነው ሳንቹዋሪ ነው።››
ፎቶውን ተቀበለችና በፍዘት ትመለከተው ጀመር...ዥውውውው አለባትና ቀድሞ ስልኩ ከእጇ ላይ ተንሸራቶ ወደቀባት...ፈጠን ብሎ ሊደግፍት ሲንቀሳቀስ ቀድማ ወደኃላዋ እራሷን ስታ ተዘረረች...በፋጥነት ተነሳና አፋፍሶ አቅፎ አልጋ ላይ አስተኛት።ልብስ ደራርቦ አለበሳትና ከድንጋጤ እስክትወጣ መጠበቅ ጀመረ።
###
ኮሎምቢያ/አማዞ ደን ማህፀን ውስጥ
ካርሎስ በተሰበረ ልብ ምርጫ አልባ ሆኖ በህይወቱ የመጨረሻውን ፍቅር ያፈቀራትን ይቺን ጠይም ኢትዬጵያዊ ሴት ሳይወድ በግድ ከማናአስ ወደ ቲጎና በፕሌን… ከዛ ደግሞ በጀልበ ከብራዚል ድንበር ወደኮሎምቢያ አሻግሯትና ላቲሲያ ከተማ ጫፍ ድረስ ሸኛት፡ከዛ እሱ ከዳግላስ የንፍስ ጠላቶች ጋር ለመደራደር ደቡብ ምእራብ ኮሎምቢያ ድንበር ተጠግታ ወደምትገኘው የቪንዚዎላዋ ሳና-ካርሎስ ከተማ ጉዞ ጀመረ …፡፡
ይህቺን ያፈቀራትን አፍሪካዊ ሴት ማዳን ማለት እራሱን ማዳን ማለት ነው፡፡ሰው እራሱን ለማዳን ደግሞ ምንም ያደርጋል፡፡ዳግላስን ያገኙትን ማንኛውንም አጋጣሚ ተጠቅመው ሊያጠፉት የሚፈልጉ የቢዝነስ ተፎካካሪዎች እንዳሉት ያውቃል..እሱ ደግሞ ስለ ዳግላስ የቢዝነስ ሚስጥሮች ፤ መግቢያ መውጫውን ፤ድክመትና ጥንካሬውን በደንብ ያውቃል…አሁን የሚያገኛቸው ሰዎቹ ደግሞ ሃይልና ብር አላቸው….እነሱ እሱን አምነውት ከተቀበሉትና አብረውት ለመስራት ከወሰኑ ዳግላስን እስከወዲያኛው አስወግዶ ኑሀሚንና ወንድሟን ነፃ ለማውጣት የሰለለችው ቢሆን ተስፋ አለው፡፡ያ ተስፋ ካልተሳካ ነፍሱን እንደሚያስከፍለው ያውቃል…ቢሆንም ግድ የለውም…ያቺ የሰለለች ተስፋ ከመቶ አንድ ፐርሰንት ብትሆንም እንኳን ከመሞከር ወደኃላ አይልም..ለዛ ነው እሷን ወደዳግላስ ልኮ እሱ የዳግላስን ጠላቶች አግኝቶ ለመደራደር ጊዜ ሳያባክን ጉዞ የጀመረው፡፡
ኑሀሚ ካርሎስ እንደነገራት ላቲሲያ ከተማ በተቀመጠችበት ሆቴል ነው አንድ ሰዓት እንኳን ሰትቆይ የዳግላስ ሰዎች በቁጥጥር ስር ያዋሏት፡፡በመጀመሪያ እዛ ላቴሲያ ከከተማው ወጣ ብሎ አማዞን ወንዝ ደር ካለ ወደ አንድ ሰዋራ ቤት ነበር የወሰዷት፡፡ለአራት ቃናት ያህል እዛው አስቀመጧት፡፡በየቀኑ የሚያስፈልጋትን ያህል ምግብ ፤ልብስ እና መጠጥ ያቀርቡላታል፡፡ግን ማንም ሊናግራት የሚደፍር ፤ብታናገራቸውም የሚመልስላት አልነበረም፡፡በየቀኑ ምግብ እና መጠጥ እንዲሁም የሚያስፈልጋትን ነገር የሚያመጡ ሁለት ሰዎች አሉ….መጥተው እቤቱ ጠረጴዛ ላይ አስቀምጠውላት ይሄዳሉ….ብታናግራቸው አይመልስላትም፡፡ጠባቂዎቾ እርስ በርስም ቁጥብ ቃላትን ሲለዋወጡ ብትሰማ እንኳን በማይገባት ቋንቋ ስለሆነ ምንም መረዳት የምትችለው ነገር አልነበረም ፡፡ይበልጥ ልትቆጣጠረው የሚከብዳት ጥልቅ ድባቴ ውስጥ እየገባች መጣች፡፡እሷ ካለችበት ቤት አስር ሜትር እርቃ ባለች ጎጆ አንድ ዘመናዊ መሳሪያ የታጠቀ ጎረምሳ ሁሌ ንቁ ሆኖ ሲጠብቃት ታየዋለች…ወደእሷ መጥቶ ለማውራት አይሞክርም…እሷም ወደእሱ ለመቀረብ ምንም ጥረት ኣላደረገችም፡፡ይህን ጠበቂ ወይ ጥላው ወይ ገድላው በቀላሉ ማምለጥ እንደምትች ታውቃለች…..ግን ያ አይደለም እቅዷ፡፡ አሁን ሂጂ አምልጪ የሚላት አዛኝ ሰው ቢኖር እራሱ እሺ ምትልበት ሁኔታ ላይ አይደለም ያለችው፡፡አሁን የእሷ ጥረት ወደፊት ስምጥ ወደሆነው የአማዞን ደን ማህፀን ውስጥ ገብቶ ወንድሟን ማግኘት ነው…ምንም ያህል ዋጋ ቢያስከፍላት ግድ የላትም፡፡እንደው ወንድሟንና ምስራቅን የማትረፍ እድሉ ባይኖራት እንኳን የዩትን መከራ አብራ አይታ የሚጎነጩትን
( በአመዞን ደን ውስጥ)፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ሁለቱም እርቃናቸውን ተኝተው ፊት ለፊት እየተያዩ ማውራት ቀጠሉ?
"የሆነ ነገር ትጠይቀኛለህ ብዬ ስጠብቅ ነበር ግን ማድረግ አልቻልክም"አለችው
እንደመደንገጥ ብሎ ፀጉሯን በእጆቹ እየላገ"ምንድነው የእኔ ፍቅር?ምን ልጠይቅሽ?"
"ከዚህ በፊት የዛሬ ሳምንት አካባቢ ከዚህ ደን በሰላም ከወጣን ደግመህ ጠይቀኝ ብዬህ ነበር...አሁን ሳስበው ግን ጥያቄውን ሙሉ በሙሉ ረስተኸዋል…በፊትም ከልብህ አልነበረም የጠየቅከኝ ማለት ነው "አለች እንደማኩረፍ ብላ።
"አንቺ በጣም ተሳስተሻል...ያንን ጥያቄ ለደቂቃም ረስቼው አላውቅም..አሁን ደግሜ ብጠይቃትና እምቢ ብትለኝ እንዴት ነው የምቋቋመው?"ብዬ ሰግቼ ነበር ...
"እና "
"እናማ...አንቺ ቆንጆ ጠይም ወጣት ወደሀገርሽ ይዘሽኝ ብትበሪ ምን ይመስልሻል?"
"ይዞ መሄድን ይዤህ ሄዳለው።ግን ልመለስ ብትል ማንም አይሰማህም"
"ይሁን ተስማምቼያለው...አልፎ..አልፎ ሀገሬ ሲናፍቀኝ ይዘሽኝ መጥተሽ እንደምታሳይኝ እተማመናለው።››
"እሱን ፀባይህ እየታየ የሚወሰን ነው።"ብላ ከመኝታዋ ተነሳችና እርቃን ገላዋን ለእሱ እይታ አጋልጣ ወረደች..ቀጥታ ወደሰካችው ስልኳ ሄደችና ነቀለችው።ተመልሳ መጣችና አልጋው ጠርዝ ላይ ቁጭ ብላ ወደሀገር ቤት ወንድሟ ጋር ደወለች.፡፡ከሰከንዶች በኃላ የወንሟን ተወዳጅ ድምፅ በጆሮዋ ሲንቆረቆር ልትሰማ እንደሆነ ስታስብ ሰውነቷን ሌላ ዙር ሙቀት ወረራት...ግን እንዳሰበችው የወንድሟ ሞባይል ሊጠራ አልቻለም...ደግማ ሞከረች።በሁለተኛ ቁጥሩም ሞከረች ተመሳሳይ ነው።
"ብሽቅ...በዚህ ቀን ሞባይሉን ያጠፍል"ተበሳጨች።ሌላ ተለዋጭ ሀሳብ መጣላት።የምስራቅ ቁጥርን ከሞባይሏ ፈለገችና ደወለች።ልክ እንደወንድሟ ስልክ የእሷም አይሰራም።
‹‹የሰዎቹ ስልክ ሁሉ አይሰራም"በተኛበት አይኖቹን እያቁለጨለጨ እየተመለከታት ለነበረው ካርሎስ ነገረችው። ከተኛበት ተነሳና ከአልጋው ወርዶ አልጋ ልብሱን ከአልጋው ላይ ገፎ እርቃን ሰውነቷን በማልበስ"አይዞሽ ተረጋጊ...አህጉር አቋራጭ ጥሪ እኮ ነው እያደረግሽ ያለሽው፡፡ ኔትወርኩ ችግር ሊኖርበት ይችላል...አሁን ባይሆን ጥዋት ሲነጋ ሊሰራ ይችላል...ካልሆነም ሌላ ዘዴ እንፈልጋለን።››ሲል ሊያፅናናት ሞከረ፡፡
ሌላ ዘዴ ሲላት በአእምሮዋ ተለዋጭ ዘዴ ብልጭ አለባት፡፡ ለወንድሞ...ነፃ እንደወጣችና ከቀናት በኃላ ወደሀገሯ እንደምትመለስ ልትፅፍለት ወሰነችና ኢሜሏን ከፈተች። ከአለም እይታ በተሰወረችባቸው 20 በሚሆኑ ቀናቶች በርካታ ኢሜሎች ተልከውላታል።አብዛኛዎቹ ከወንድሟ.. ከዛም ከመስሪያ ቤቷ ሲሆን ለመጨረሻ ጊዜ ግን የተላከላት ከማትጠብቀው ሰው ነበር… በድንጋጤ ከተቀመጠችበት ተነስታ ስትቆም ካርሎስ አልብሷት የነበረው አልጋ ልብስ ከላዩ ላይ ወደቀና እርቃኗን ቀረች...
‹‹ምንድነው ፍቅር...?››
‹‹ሰውዬው ተደጋጋሚ መልዕክት ልኮልኛል?››
ግራ ገባው"የትኛው ሰውዬ?"
"ሀለቃህ...ዳግላስ?"
ከመደንገጡ የተነሳ ተንደርድሮ ወደእሷ ቀረበና ሞባይሉን ከእጇ ተቀበላትና ኢሜሉን ተራ በተራ እየከፈተ አየ...ከዛ በድንጋጤ እግሮቹ ዝሎ ወለሉ ላይ ተዘረፈጠ..ኑሀሚም ድንጋጤው ክፍኛ አዝሏት ስሩ ተንበረከከች፡፡
ስልኩን ተቀብላው ኢሜሉን በማንበብ የሆነውን ለመረዳት የሚያስችል ጥንካሬ ከውስጧ ማግኘት አልቻለችም።ሽው እያለ መጥቶ እርቃን ሰውነቷን የሚገርፋት እርጥብ አየር ነፍሷን ጭምር እያቀዘቀዘው ነው።
"ምንድነው የሆነው?"ጥንካሬዋን አሰባስባ የሆነውን ሁሉ ከእሱ አንደበት ለመስማት ጠየቀችው።ስልኩን መልሶ ከፈተና በኢሜሏ የተላከለትን ፎቶዎች አወጣና"ወንድምሽ...እዚህ መጥቷል"አላት
"ወንድሜ ?እዚህ እንዴት?››ካርሎስ የሚያወራው ነገር ምንም እየገባት አይደለም፡፡
"አላውቅም ግን..እይ ተመልከቺ ዳግላስ እጅ ነው ያለው...ፎቶውን ወደእሷ አቅርቦ እያሳያት"ይሄውልሽ...ይሄንን ቦታ በደንብ አውቀዋለው፡፡ ማንም ሊደርሶበት የማይችለው የዳግላስ ምሽግ የሆነው ሳንቹዋሪ ነው።››
ፎቶውን ተቀበለችና በፍዘት ትመለከተው ጀመር...ዥውውውው አለባትና ቀድሞ ስልኩ ከእጇ ላይ ተንሸራቶ ወደቀባት...ፈጠን ብሎ ሊደግፍት ሲንቀሳቀስ ቀድማ ወደኃላዋ እራሷን ስታ ተዘረረች...በፋጥነት ተነሳና አፋፍሶ አቅፎ አልጋ ላይ አስተኛት።ልብስ ደራርቦ አለበሳትና ከድንጋጤ እስክትወጣ መጠበቅ ጀመረ።
###
ኮሎምቢያ/አማዞ ደን ማህፀን ውስጥ
ካርሎስ በተሰበረ ልብ ምርጫ አልባ ሆኖ በህይወቱ የመጨረሻውን ፍቅር ያፈቀራትን ይቺን ጠይም ኢትዬጵያዊ ሴት ሳይወድ በግድ ከማናአስ ወደ ቲጎና በፕሌን… ከዛ ደግሞ በጀልበ ከብራዚል ድንበር ወደኮሎምቢያ አሻግሯትና ላቲሲያ ከተማ ጫፍ ድረስ ሸኛት፡ከዛ እሱ ከዳግላስ የንፍስ ጠላቶች ጋር ለመደራደር ደቡብ ምእራብ ኮሎምቢያ ድንበር ተጠግታ ወደምትገኘው የቪንዚዎላዋ ሳና-ካርሎስ ከተማ ጉዞ ጀመረ …፡፡
ይህቺን ያፈቀራትን አፍሪካዊ ሴት ማዳን ማለት እራሱን ማዳን ማለት ነው፡፡ሰው እራሱን ለማዳን ደግሞ ምንም ያደርጋል፡፡ዳግላስን ያገኙትን ማንኛውንም አጋጣሚ ተጠቅመው ሊያጠፉት የሚፈልጉ የቢዝነስ ተፎካካሪዎች እንዳሉት ያውቃል..እሱ ደግሞ ስለ ዳግላስ የቢዝነስ ሚስጥሮች ፤ መግቢያ መውጫውን ፤ድክመትና ጥንካሬውን በደንብ ያውቃል…አሁን የሚያገኛቸው ሰዎቹ ደግሞ ሃይልና ብር አላቸው….እነሱ እሱን አምነውት ከተቀበሉትና አብረውት ለመስራት ከወሰኑ ዳግላስን እስከወዲያኛው አስወግዶ ኑሀሚንና ወንድሟን ነፃ ለማውጣት የሰለለችው ቢሆን ተስፋ አለው፡፡ያ ተስፋ ካልተሳካ ነፍሱን እንደሚያስከፍለው ያውቃል…ቢሆንም ግድ የለውም…ያቺ የሰለለች ተስፋ ከመቶ አንድ ፐርሰንት ብትሆንም እንኳን ከመሞከር ወደኃላ አይልም..ለዛ ነው እሷን ወደዳግላስ ልኮ እሱ የዳግላስን ጠላቶች አግኝቶ ለመደራደር ጊዜ ሳያባክን ጉዞ የጀመረው፡፡
ኑሀሚ ካርሎስ እንደነገራት ላቲሲያ ከተማ በተቀመጠችበት ሆቴል ነው አንድ ሰዓት እንኳን ሰትቆይ የዳግላስ ሰዎች በቁጥጥር ስር ያዋሏት፡፡በመጀመሪያ እዛ ላቴሲያ ከከተማው ወጣ ብሎ አማዞን ወንዝ ደር ካለ ወደ አንድ ሰዋራ ቤት ነበር የወሰዷት፡፡ለአራት ቃናት ያህል እዛው አስቀመጧት፡፡በየቀኑ የሚያስፈልጋትን ያህል ምግብ ፤ልብስ እና መጠጥ ያቀርቡላታል፡፡ግን ማንም ሊናግራት የሚደፍር ፤ብታናገራቸውም የሚመልስላት አልነበረም፡፡በየቀኑ ምግብ እና መጠጥ እንዲሁም የሚያስፈልጋትን ነገር የሚያመጡ ሁለት ሰዎች አሉ….መጥተው እቤቱ ጠረጴዛ ላይ አስቀምጠውላት ይሄዳሉ….ብታናግራቸው አይመልስላትም፡፡ጠባቂዎቾ እርስ በርስም ቁጥብ ቃላትን ሲለዋወጡ ብትሰማ እንኳን በማይገባት ቋንቋ ስለሆነ ምንም መረዳት የምትችለው ነገር አልነበረም ፡፡ይበልጥ ልትቆጣጠረው የሚከብዳት ጥልቅ ድባቴ ውስጥ እየገባች መጣች፡፡እሷ ካለችበት ቤት አስር ሜትር እርቃ ባለች ጎጆ አንድ ዘመናዊ መሳሪያ የታጠቀ ጎረምሳ ሁሌ ንቁ ሆኖ ሲጠብቃት ታየዋለች…ወደእሷ መጥቶ ለማውራት አይሞክርም…እሷም ወደእሱ ለመቀረብ ምንም ጥረት ኣላደረገችም፡፡ይህን ጠበቂ ወይ ጥላው ወይ ገድላው በቀላሉ ማምለጥ እንደምትች ታውቃለች…..ግን ያ አይደለም እቅዷ፡፡ አሁን ሂጂ አምልጪ የሚላት አዛኝ ሰው ቢኖር እራሱ እሺ ምትልበት ሁኔታ ላይ አይደለም ያለችው፡፡አሁን የእሷ ጥረት ወደፊት ስምጥ ወደሆነው የአማዞን ደን ማህፀን ውስጥ ገብቶ ወንድሟን ማግኘት ነው…ምንም ያህል ዋጋ ቢያስከፍላት ግድ የላትም፡፡እንደው ወንድሟንና ምስራቅን የማትረፍ እድሉ ባይኖራት እንኳን የዩትን መከራ አብራ አይታ የሚጎነጩትን
#ጉዞ_በፀሎት
(አቃቂ እና ቦሌ)
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
በማግስቱ የናፈቀው ቢሮ የገባው አራት ሰዓት አካባቢ ነበር….የማታው ስካር አንጎበሩ ሙሉ በሙሉ አለቀቀውም…አሁንም ጭንቅላቱን እየወቀረው ነው፡፡ለፀሀፊው መምጣቱን
ስላልነገራት አልገባችም…ከፍቶ ገባና ቁጭ አለ ..የሚሰራው ስራ ስላልነበረ የሚያደርገው ነገር ግራ ገባው..ስልክ አውጥቶ ደወለ፡፡
‹‹እንዴት ነሽ…ለሊሴ?››
‹‹ደህና ነኝ ሰለሞን…እንዴት ነው ስራ?››
‹‹አሪፍ ነው..አሁን ተመልሼለሁ…ቢሮ ነው ያለሁት››
‹‹ውይ ለምን ሳትነግረኝ..ቀድሜ ገብቼ አፀዳድቼ ጠብቅህ ነበረ እኮ››
‹‹አይ ችግር የለውም..ቢሮው አሁንም ንፅና የተስተካከለ ነው››
‹‹አዎ እሱማ በሶስት ቀን አንዴ ከፍቼ አናፍሰዋለው….እና ስራህን ጨረስክ ማለት ነው?››
‹‹አይ አልጨረስኩም…በመሀል የሶስት ቀን እረፍት ስላለኝ ነው የመጣሁት…ለመሆኑ ያንቺ ነገር እንዴት ሆነ?››
‹‹የቱ?››
‹‹የሁለቱ ፍቅረኞችሽ ነገር?››
ለሊሴ ሰለሞን ባቀረበላት ሀሳብ መሰረት ከሁለት ፍቅረኞቾ መካከል አንዱን ለባልነት ለመምረጥ ምታደርገውን ጥረት ወዲያው ነበር የጀመረችው ….መጀመሪያ ነጋዴውን ለአንድ ወር ላታገኘው እንደማትችል ነግራ ከመንግስት ሰራተኛው ጋር ነበር የቀጠለችው..ሲደውልላት ትሄዳለች..ዝም ሲላት ትደውልለታልች….ከስራ መልስ ሳታገኘው ወደቤት አትገባም…እሁድ ቢያንስ ግማሹን ሰዓት ከእሱ ጋር ነች፡፡ይበልጥ ትኩረቷን ሰብስባ ከእሱ ጋር ባሳለፈች መጠን በፊት ከምታውቀው በላይ እያወቀችው …በፊት ከምታዳምጠው በላይ እያዳመጠችው መጣች፡፡አሁን ያለበትን የኑሮ ደረጃ ብቻ ሳይሆን ..
የወደፊት እቅዶቹንና እነዛን እቅዶች ለማሳካት እያደረገ ያለውን ተጋድሎም እየተረዳችና እየተገነዘበች መጣች…..እሱ ላይ ያላት ቅሬታ ባገባው እኔን አኑሮ ቤተሰቦቼንም እንድረዳ የሚያበቃኝ ህይወት ሊሰጠኝ አይችልም የሚል ነበር…አሁን ስታስበው ግን ያንን ከእሱ ብቻ መጠበቅ እንደሌለባት ነው የገባት…እሱ ባለው ቁርጠኝነት ላይ እሷ ተጨምራበት ካገዘችውና ከጎኑ ሆና አብራው ከታገለች ጎዶሎው ሊሞላ የሚችል አይነት እንደሆነ ተረድታለች…ግን ውሳኔ ላይ ከመድረሷ በፊት ለእሱ የመደበችለት ወር ተገባደደ እና ለዛኛው የሰጠችውን ተመሳሳይ ምክንያት ሰጥታ ..ለአንድ ወር ያህል ልትደውልለትም ሆነ ልታገኘው እንደማትችል ነገራ ወደነጋዴው ሄደች፡፡
በእውነት ነገዴው ጋር ልክ እንደወትሮ ሁሉ ነገር ተሰርቶ ያለቀ ሆኖ ነው የጠበቃት…ቤቱ የተዘጋጀ..እቃዎቹ የተደራጁ ናቸው…አዎ እያንዳንዱን ሀብቱንና አኗኗሩን ተራ በተራ አሳያት፣ቀጥታ እንዳገባችው ሕይወቷን ወደመስራት ሳይሆን የተሰራ ህይወት ውስጥ ገብቶ ለመኖር መሞከር ብቻ እንደሚጠበቅባት ተረዳች ፣ግን ለምን ልቧ ወደኃላ እንደሚጎትታት ግልፅ ሊሆንላት አልቻለም‹‹…ታግዬ ያላሸነፉኩት በሌላ እጅ የተሰራ ህይወት ምን ትርጉም ይኖረዋል?››እራሷን ጠየቀች… መልሱ ቀላል አልነበረም….፡፡
ሁሉንም ሂደት አንድ በአንድ ዘርዝራ አስረዳችው፡፡ ሰለሞንም‹‹እና ምን ተሰማሽ?››ሲል ጠየቃት
‹‹አሁንም እንደተወዛገብኩ ነው…ግን በአእምሮዬ ውስጥ የሚመላለሱ ጥያቄዎች በፊት ከሚመላለሱት የተለዩ ናቸው…እንግዲህ እኔ በህይወቴ ጠንከር ያሉ ውሳኔዎችን የማስተላለፍ ከፍተኛ ድክመት እንደለብኝ ነው የተረዳሁት፡፡››
‹‹አይ እንደዛ አይመስለኝም …አንቺ ቀሪ ህይወትሽን አብሮሽ በደስታ የሚዘልቅና ከቤተሰቦችሽም ጋ ተሰስማምቶ የሚያኮራሽ ለፍፅምነት የተጠጋ ባል እየፈለግሽ ነው….በዚህ ምድር ላይ ደግሞ ለፍጽምና የተጠጋ ነገር መምረጥ ቀላል ነገር አይደለም፡፡አንድ ታሪክ ልንገርሽ..
‹‹ደስ ይለኛል››
ደቀ መዝሙሩ መምህሩን ‹‹ፍፁምና በህይወታችን እንዴት አድርገን ነው ፍፅማዊ የሆነ ነገር መጎናፀፍ የምንችለው? ሲል ጠየቀው ፡፡ መምህሩም አሰብ አደረገና ‹‹የዚህን መልስ
እንድነግርህ ከፈለክ በፊት ለፊት በር ወደ ግቢው የአትክልት ስፍራ ቀጥ ብለህ ግባ ።በመንገድህ ከምታገኛቸው አበቦች መካከል በጣም የሚያምረውንና ደስ ያሰኘህን ቀንጥስና በጎሮ በር ውጣ …አንዴ ያለፍከውን አበባ ከእንደገና ወደኃላ ተመልሰህ መቅጠፍ አትችልም አሉት።›› አለው ።እሱም ትዕዛዙን አክብሮ እንዳተባለው ወደ አትክልቱ ስፍራ ገባና እስከመጨረሻው ጥግ ከተጓዘ በኃላ ባዶ እጅን በጓሮ በር ወጣ።
መምህሩ ‹‹ለምንድነው አንድ ቀንበጥ አበባ እንኳን ይዘህ መውጣት ያልቻልከው?››ሲሉ ጠየቁት፡፡
‹‹ምርጥ የተባለውን አበባ ወዲያው እንደገባሁ ነበረ ያገኘሁት... ግን የተሻለ አገኛለሁ ብዬ በማሰብ ሳልቀነጥስ ወደፊት ቀጠልኩ .. መጨረሻው ላይም ደረስኩ.. ወደኃላ የመመለስ እድል ስለሌለኝ ባዶዬን ለመውጣት ተገደድኩ›› ሲል መለሰ።
መምህሩ መልሱን ሲሰሙ ፈገግ አሉና ‹‹አዎ! ትክክል ነህ ፤ህይወት እንደዛ ነው ።ፍፁምናን ለማግኘት ይበልጥ በዳከርን ቁጥር ብኩን እየሆንክ ትሄዳለህ።እውነተኛ ፍፁምናን መቼም የትም አታገኝም።››ሲሉ መለሱለት። ‹‹ገባሽ አይደል?››
‹‹አዎ ገብቶኛል››
‹‹እንግዲያው ፍፅም በምናብ አለም ካስቀመጥሽው ወንድ ጋር የሚስማማ ባል እንደማታገኚ አውቀሽ ለሚማጡት 10 ቀናት ሁለቱንም ሳታገኚ አስቢበት..ከዛ ማንኛቸው ናቸው የበለጠ የሚናፍቁሽ..የትኛው ቢያቅፍሽ ትፈልጊያለሽ ….?ማንኛቸው የልጆችሽ አባት ቢሆኑ ይሻላል..?በህልምሽ እየደጋገመ የሚመጣው የትኛው ነው?፡፡ለ10 ቀን አስቢበት፡፡››
‹‹እሺ እንደዛ አደርገላው..ግን አሁን አሁን እየገባኝ ያለው እኔ ከባሌ ምን እጠብቃለው ብቻ ሳይሆን ለባሌስ ምን ይዤለት ሄዳለው…?የሚለውን በጥልቀት ማሰብና መዘጋጀት እንዳለብኝ ነው፡፡ ››
‹‹ጎበዝ ነሽ…ይሄ ትልቅ መረዳት ነው..በይ ደህና እደሪ››
‹‹ውይ …ከመዝጋትህ በፊት…ድፍረት አይሁንብኝና ዛሬ ቤት ለምን አትመጣም››
‹‹ለምን?››
‹‹እማዬ የማሪያም ድግስ አለባት….ማህበርተኞቹ እስከ10 ሰዓት ነው የሚቆዩት 11 ሰዓት ብትመጣ በጣም ደስ ይለኝ ነበር…››
‹‹አረ ተይ››
‹‹ምን አለበት…ቤተሰቦቼ በጣም ነው ደስ የሚላቸው››
‹‹11 ሰዓት ነው ያልሽኝ?፡፡››
‹‹አዎ 11 ሰዓት››
ብቻውን ሆኖ ስለአስቴር እያሰበ ከሚሰቃይ ከሰው ጋር ተቀላቅሎ የባጥ የቆጡን እያወራ ሊረሳት ቢሞክር እንደሚሻለው አሰበእና ‹‹በቃ እሺ መጣለሁ››አላት፡፡
‹‹በቃ አቃቂ ፖሊስ ጣቢያው ጋር ስትደርስ ደውልልኝ..ወጥቼ እቀበልሀለው››
‹‹እሺ ደውላለው››
ስልኩን ዘጋው፡፡ እሺ ማለቱን ፍጽም አላመነም….ጠበል ለመቅመስ ከሜክሲኮ
አቃቂ….ለመሆኑ በህይወቱ ጠበል የተጠራውና ጥሪውን አክብሮ የሄደው መቼ ነው..?ፍጽም አያስታውስም….
እንዳለችው …..እንደደወለላት ደቂቃ ሳታባክን ነው ወጥታ የተቀበለችው….መኪናውን
እዛው አስፓልት ዳር ፓርክ አደረገና ተከትሏት ይዛው ሄደችው.. ግን ወደሚያስደነግጥ ቦታ ነው ይዛው የሄደችው…ይሄንን ግቢ ትናንትና በዚህን ሰዓት መኪና ውስጥ ሆኖ ከአሰሪዎቹ ጋር በመሆን ሲሰልለው ነበር …‹‹ምን አይነት መገጣጠም ነው?››ለለሊሴ ምንም አይነት የመደነቅና የመገረም ስሜት ሳያሳያት ተከተላት፡፡አሁን ነገሮችን ገጣጥሞ ሲያስብ በፀሎት እሱን እንዴት እንዳገኘችውና ስልኩን ከማን እንደወሰደች ተገለፀለት፡፡
(አቃቂ እና ቦሌ)
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
በማግስቱ የናፈቀው ቢሮ የገባው አራት ሰዓት አካባቢ ነበር….የማታው ስካር አንጎበሩ ሙሉ በሙሉ አለቀቀውም…አሁንም ጭንቅላቱን እየወቀረው ነው፡፡ለፀሀፊው መምጣቱን
ስላልነገራት አልገባችም…ከፍቶ ገባና ቁጭ አለ ..የሚሰራው ስራ ስላልነበረ የሚያደርገው ነገር ግራ ገባው..ስልክ አውጥቶ ደወለ፡፡
‹‹እንዴት ነሽ…ለሊሴ?››
‹‹ደህና ነኝ ሰለሞን…እንዴት ነው ስራ?››
‹‹አሪፍ ነው..አሁን ተመልሼለሁ…ቢሮ ነው ያለሁት››
‹‹ውይ ለምን ሳትነግረኝ..ቀድሜ ገብቼ አፀዳድቼ ጠብቅህ ነበረ እኮ››
‹‹አይ ችግር የለውም..ቢሮው አሁንም ንፅና የተስተካከለ ነው››
‹‹አዎ እሱማ በሶስት ቀን አንዴ ከፍቼ አናፍሰዋለው….እና ስራህን ጨረስክ ማለት ነው?››
‹‹አይ አልጨረስኩም…በመሀል የሶስት ቀን እረፍት ስላለኝ ነው የመጣሁት…ለመሆኑ ያንቺ ነገር እንዴት ሆነ?››
‹‹የቱ?››
‹‹የሁለቱ ፍቅረኞችሽ ነገር?››
ለሊሴ ሰለሞን ባቀረበላት ሀሳብ መሰረት ከሁለት ፍቅረኞቾ መካከል አንዱን ለባልነት ለመምረጥ ምታደርገውን ጥረት ወዲያው ነበር የጀመረችው ….መጀመሪያ ነጋዴውን ለአንድ ወር ላታገኘው እንደማትችል ነግራ ከመንግስት ሰራተኛው ጋር ነበር የቀጠለችው..ሲደውልላት ትሄዳለች..ዝም ሲላት ትደውልለታልች….ከስራ መልስ ሳታገኘው ወደቤት አትገባም…እሁድ ቢያንስ ግማሹን ሰዓት ከእሱ ጋር ነች፡፡ይበልጥ ትኩረቷን ሰብስባ ከእሱ ጋር ባሳለፈች መጠን በፊት ከምታውቀው በላይ እያወቀችው …በፊት ከምታዳምጠው በላይ እያዳመጠችው መጣች፡፡አሁን ያለበትን የኑሮ ደረጃ ብቻ ሳይሆን ..
የወደፊት እቅዶቹንና እነዛን እቅዶች ለማሳካት እያደረገ ያለውን ተጋድሎም እየተረዳችና እየተገነዘበች መጣች…..እሱ ላይ ያላት ቅሬታ ባገባው እኔን አኑሮ ቤተሰቦቼንም እንድረዳ የሚያበቃኝ ህይወት ሊሰጠኝ አይችልም የሚል ነበር…አሁን ስታስበው ግን ያንን ከእሱ ብቻ መጠበቅ እንደሌለባት ነው የገባት…እሱ ባለው ቁርጠኝነት ላይ እሷ ተጨምራበት ካገዘችውና ከጎኑ ሆና አብራው ከታገለች ጎዶሎው ሊሞላ የሚችል አይነት እንደሆነ ተረድታለች…ግን ውሳኔ ላይ ከመድረሷ በፊት ለእሱ የመደበችለት ወር ተገባደደ እና ለዛኛው የሰጠችውን ተመሳሳይ ምክንያት ሰጥታ ..ለአንድ ወር ያህል ልትደውልለትም ሆነ ልታገኘው እንደማትችል ነገራ ወደነጋዴው ሄደች፡፡
በእውነት ነገዴው ጋር ልክ እንደወትሮ ሁሉ ነገር ተሰርቶ ያለቀ ሆኖ ነው የጠበቃት…ቤቱ የተዘጋጀ..እቃዎቹ የተደራጁ ናቸው…አዎ እያንዳንዱን ሀብቱንና አኗኗሩን ተራ በተራ አሳያት፣ቀጥታ እንዳገባችው ሕይወቷን ወደመስራት ሳይሆን የተሰራ ህይወት ውስጥ ገብቶ ለመኖር መሞከር ብቻ እንደሚጠበቅባት ተረዳች ፣ግን ለምን ልቧ ወደኃላ እንደሚጎትታት ግልፅ ሊሆንላት አልቻለም‹‹…ታግዬ ያላሸነፉኩት በሌላ እጅ የተሰራ ህይወት ምን ትርጉም ይኖረዋል?››እራሷን ጠየቀች… መልሱ ቀላል አልነበረም….፡፡
ሁሉንም ሂደት አንድ በአንድ ዘርዝራ አስረዳችው፡፡ ሰለሞንም‹‹እና ምን ተሰማሽ?››ሲል ጠየቃት
‹‹አሁንም እንደተወዛገብኩ ነው…ግን በአእምሮዬ ውስጥ የሚመላለሱ ጥያቄዎች በፊት ከሚመላለሱት የተለዩ ናቸው…እንግዲህ እኔ በህይወቴ ጠንከር ያሉ ውሳኔዎችን የማስተላለፍ ከፍተኛ ድክመት እንደለብኝ ነው የተረዳሁት፡፡››
‹‹አይ እንደዛ አይመስለኝም …አንቺ ቀሪ ህይወትሽን አብሮሽ በደስታ የሚዘልቅና ከቤተሰቦችሽም ጋ ተሰስማምቶ የሚያኮራሽ ለፍፅምነት የተጠጋ ባል እየፈለግሽ ነው….በዚህ ምድር ላይ ደግሞ ለፍጽምና የተጠጋ ነገር መምረጥ ቀላል ነገር አይደለም፡፡አንድ ታሪክ ልንገርሽ..
‹‹ደስ ይለኛል››
ደቀ መዝሙሩ መምህሩን ‹‹ፍፁምና በህይወታችን እንዴት አድርገን ነው ፍፅማዊ የሆነ ነገር መጎናፀፍ የምንችለው? ሲል ጠየቀው ፡፡ መምህሩም አሰብ አደረገና ‹‹የዚህን መልስ
እንድነግርህ ከፈለክ በፊት ለፊት በር ወደ ግቢው የአትክልት ስፍራ ቀጥ ብለህ ግባ ።በመንገድህ ከምታገኛቸው አበቦች መካከል በጣም የሚያምረውንና ደስ ያሰኘህን ቀንጥስና በጎሮ በር ውጣ …አንዴ ያለፍከውን አበባ ከእንደገና ወደኃላ ተመልሰህ መቅጠፍ አትችልም አሉት።›› አለው ።እሱም ትዕዛዙን አክብሮ እንዳተባለው ወደ አትክልቱ ስፍራ ገባና እስከመጨረሻው ጥግ ከተጓዘ በኃላ ባዶ እጅን በጓሮ በር ወጣ።
መምህሩ ‹‹ለምንድነው አንድ ቀንበጥ አበባ እንኳን ይዘህ መውጣት ያልቻልከው?››ሲሉ ጠየቁት፡፡
‹‹ምርጥ የተባለውን አበባ ወዲያው እንደገባሁ ነበረ ያገኘሁት... ግን የተሻለ አገኛለሁ ብዬ በማሰብ ሳልቀነጥስ ወደፊት ቀጠልኩ .. መጨረሻው ላይም ደረስኩ.. ወደኃላ የመመለስ እድል ስለሌለኝ ባዶዬን ለመውጣት ተገደድኩ›› ሲል መለሰ።
መምህሩ መልሱን ሲሰሙ ፈገግ አሉና ‹‹አዎ! ትክክል ነህ ፤ህይወት እንደዛ ነው ።ፍፁምናን ለማግኘት ይበልጥ በዳከርን ቁጥር ብኩን እየሆንክ ትሄዳለህ።እውነተኛ ፍፁምናን መቼም የትም አታገኝም።››ሲሉ መለሱለት። ‹‹ገባሽ አይደል?››
‹‹አዎ ገብቶኛል››
‹‹እንግዲያው ፍፅም በምናብ አለም ካስቀመጥሽው ወንድ ጋር የሚስማማ ባል እንደማታገኚ አውቀሽ ለሚማጡት 10 ቀናት ሁለቱንም ሳታገኚ አስቢበት..ከዛ ማንኛቸው ናቸው የበለጠ የሚናፍቁሽ..የትኛው ቢያቅፍሽ ትፈልጊያለሽ ….?ማንኛቸው የልጆችሽ አባት ቢሆኑ ይሻላል..?በህልምሽ እየደጋገመ የሚመጣው የትኛው ነው?፡፡ለ10 ቀን አስቢበት፡፡››
‹‹እሺ እንደዛ አደርገላው..ግን አሁን አሁን እየገባኝ ያለው እኔ ከባሌ ምን እጠብቃለው ብቻ ሳይሆን ለባሌስ ምን ይዤለት ሄዳለው…?የሚለውን በጥልቀት ማሰብና መዘጋጀት እንዳለብኝ ነው፡፡ ››
‹‹ጎበዝ ነሽ…ይሄ ትልቅ መረዳት ነው..በይ ደህና እደሪ››
‹‹ውይ …ከመዝጋትህ በፊት…ድፍረት አይሁንብኝና ዛሬ ቤት ለምን አትመጣም››
‹‹ለምን?››
‹‹እማዬ የማሪያም ድግስ አለባት….ማህበርተኞቹ እስከ10 ሰዓት ነው የሚቆዩት 11 ሰዓት ብትመጣ በጣም ደስ ይለኝ ነበር…››
‹‹አረ ተይ››
‹‹ምን አለበት…ቤተሰቦቼ በጣም ነው ደስ የሚላቸው››
‹‹11 ሰዓት ነው ያልሽኝ?፡፡››
‹‹አዎ 11 ሰዓት››
ብቻውን ሆኖ ስለአስቴር እያሰበ ከሚሰቃይ ከሰው ጋር ተቀላቅሎ የባጥ የቆጡን እያወራ ሊረሳት ቢሞክር እንደሚሻለው አሰበእና ‹‹በቃ እሺ መጣለሁ››አላት፡፡
‹‹በቃ አቃቂ ፖሊስ ጣቢያው ጋር ስትደርስ ደውልልኝ..ወጥቼ እቀበልሀለው››
‹‹እሺ ደውላለው››
ስልኩን ዘጋው፡፡ እሺ ማለቱን ፍጽም አላመነም….ጠበል ለመቅመስ ከሜክሲኮ
አቃቂ….ለመሆኑ በህይወቱ ጠበል የተጠራውና ጥሪውን አክብሮ የሄደው መቼ ነው..?ፍጽም አያስታውስም….
እንዳለችው …..እንደደወለላት ደቂቃ ሳታባክን ነው ወጥታ የተቀበለችው….መኪናውን
እዛው አስፓልት ዳር ፓርክ አደረገና ተከትሏት ይዛው ሄደችው.. ግን ወደሚያስደነግጥ ቦታ ነው ይዛው የሄደችው…ይሄንን ግቢ ትናንትና በዚህን ሰዓት መኪና ውስጥ ሆኖ ከአሰሪዎቹ ጋር በመሆን ሲሰልለው ነበር …‹‹ምን አይነት መገጣጠም ነው?››ለለሊሴ ምንም አይነት የመደነቅና የመገረም ስሜት ሳያሳያት ተከተላት፡፡አሁን ነገሮችን ገጣጥሞ ሲያስብ በፀሎት እሱን እንዴት እንዳገኘችውና ስልኩን ከማን እንደወሰደች ተገለፀለት፡፡
#የድንግሊቷ_አፍቃሪዎች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
=====================
‹‹እናንተ ደግሞ ጅል አትሁኑ…ሰሎሜ ሰው ነች…ሰው ስለሆነች ታማለች…የተመመ ሰው ደግሞ በትክክለኛው ጊዜ ትክክለኛውን ህክምና ካላገኘ ይሞታል….ይሄ ሀቅ ለሌላ ሰው ከሰራ ለሰሎሜም ይሰራል፡፡››ሁሴን ነበር የተናገረው፡፡
‹‹አንተ ደግሞ ሁሉን ነገር አውቃለሁ የምትለው ነገር አለ››አለማየሁ በብስጭት መለሰለት፡፡
‹‹ትክክል ነኛ..ከእናንተ በተሻለ ብዙ ነገር አውቃለሁ…ይልቅስ ሰሎሜ ቀዶ-ጥገናዋን እንድታደርግ እኛ ምን ማድረግ አለብን ?የሚለውን መነጋገር ነው የሚጠቅመን፡፡››
‹‹ትክክል ነህ..የመጣልህ ሀሳብ አለ?››አለማየሁ ነው በጉጉት የጠየቀው፡፡
የቀዶ ጥገና እንዲደረግላት የተወሰነበትንና እና የገንዘቡን መጠን የሚገልፅ ደብዳቤ ማግኘት አለብን›› ሁሴን ሀሳብ አቀረበ፡፡
‹‹አግኝተንስ ምን እናደርገዋለን?››አላዛር ጠየቀ፡፡
‹‹በሰፈር ጠቅላላ ዞረን እንለምናለን…በትምህርት ቤታችንም እንለምናለን፡፡››
‹‹ጥሩ ሀሳብ ነው..ግን ያንን ሁሉ ብር የምናገኝ ይመስልሀል?››በጥርጣሬ ጠየቁት፡፡
‹‹እስከቻልነው እንሞክራለን…ካልሞላልን ደግሞ ሌላ ዘዴ እንፈልጋለን..አሁን ደብዳቤውን እንዴት እንደምናገኝ ማሰብ አለብን››
‹‹ለምን ሀኪም ቤት ሄደን ሰሎሜን የሚያክማትን ሀኪም አንጠይቀውም…››አላዛር ነው ሀሳቡን ያቀረበው፡፡
‹‹አይ አንተ ጅል የሆንክ ልጅ..አሁን ሄደን ብንጠይቀው ለ13 አመት ልጇች እንዲህ አይነት መረጃ ሚሰጠን ይመስልሀል?››
‹‹እኔ እንጃ ግራ ስለገባኝ እኮ ነው፡፡››
‹‹ለምን እቴቴን አንጠይቃትም..እሷ ደብዳቤውን ልታስወጣልን ትችላለች››
‹‹አሌክስ ትክክል ነው..ጊዜ ሳናባክን አቴቴን እናናግራት››ሁሴን በአለማየሁ ሀሳብ ወዲያው ተስማማ፡፡
‹‹ግን እኮ እሷ ሆስፒታል ነው ያለችው››
‹‹እኮ እንሂዳ››
ተስማሙና ቀጥታ ሰሎሜ ወደተኛችበት ሆስፒታል ነበር የሄዱት፡፡ሰሎሜ የተኛችበት ክፍል ገብተው ያለችበትን ሁኔታ ካዩ በኃላ‹‹እቴቴ አንዴ ውጭ ልናናግርሽ ፈልገን ነበር፡፡››ሲሉ ጠየቋት፡፡
‹‹ምነው በሰላም?››
‹‹በሰላም ነው..ሰሎሜ ስለተኛች እዚህ ስናወራ እንዳንቀሰቅሳት ነው››አለ ሁሴን፡፡
‹‹እሺ እንዳላችሁ ››በማለት ተስማምታ ተከትላቸው ወጣች፡፡እዛው ሆስፒታሉ በረንዳ ላይ ካለ አግዳሚ ወንበር ላይ በመደዳ ተቀመጡ፡፡
ለነገሩ ብዙም ትኩረት ባለመስጠት‹‹እሺ ልጆች ..ለምንድነበር የፈለጋችሁኝ?››ስትል ጠየቀቻቸው፡፡
‹‹ሰሎሜ እንዴት ነች?››
ቀዝቀዝ ባለ ስሜት ‹‹ደህና ነች..ምንም አትል››ስትል መለሰችላቸው፡፡
‹‹ማለት ስለቀዶ ጥገናው ነው የምናወራሽ…?እንዴት ነው የሚሆነው…?ያን ያህል ብር ከየት ታመጪያለሽ?››
‹‹ልጇች አትጨነቁ..ከየትም ብዬ ከየትም ይሄንን ብር አግኝቼ ብቸኛ ልጄን ማሳከም አለብኝ….አታስቡ ጓደኛችሁን እንድትድን የተቻለኝን አደርጋለሁ፡፡››ስትል እንባ እየተናነቃት መለሰችላቸው፡፡በእውነት ብሩን ከየት እንደምታመጣው…የትኞቹን ዘመዶቾን እንደምታስቸግር…የትኛውን ንብረቷን ብትሸጥ የተጠየቀችውን ብር ማግኘት እንደምትችል ምንም አይነት ሀሳብም ሆነ ተስፋ አልነበራት፡፡ግን ለልጆቹ ይሄንን ምን ብላ በምን አይነት ቋንቋ ልታስረዳቸው ትችላለች፡፡ለዛ ነው በደፈናው ልታፅናናቸው የወሰነችው፡፡
‹‹እቴቴ…ሰሎሜን ለማዳን የተቻለንን ብቻ ሳይሆን ከምንችለው በላይ ነው ማድረግ ያለብን…ሶስታችንም ልክ እንደአንቺ እሷን ለማጣት ዝግጁ አይደለንም…እና የሆነ ነገር ለማድረግ አስበናል፡››ሁሴን ነበር ተናጋሪው፡፡
አቴቴ ግራ በመጋባት‹‹ምን ማለት ነው …?እናንተ ደግሞ ምን ማድረግ ትችላላችሁ?››
‹‹ከሀኪም ቤቱ ቀዶ ጥገና ማድረግ እንዳለባት መወሰኑን እና ለዛም የሚያስፈልገውን ብር የሚገልጽ ደብዳቤ እንዲሰጡሽ ጠይቂያቸው››
‹‹ማለት ..ደብዳቤው ምን ያደርግልኛል?››
‹‹አይ ላንቺ አይደለም..ለእኛ ያስፈልገናል››
‹‹ለምን .?.ምን ልታደርጉበት?››
ትምህርት ቤታቸውን ሆነ በሰፈራችን እርዳታ እየዞርን እንጠይቃለን..ከየአንዳንዱ ሰው አንድ ብርም ሆነ አስር ብር እየዞርን እንሰበስባለን…ለዛ ግን ሰው እንዲያምነን እና ስራችን ቀላል እንዲሆንልን መረጃው ያስፈልገናል፡፡››
በወቅቱ የሰሎሜ እናት ስሜቷን መቆጣጠር አልቻለችም ነበር…ሁሉንም አንድ ላይ አቅፋ ጉያዋ ውስጥ በመወሸቅ ስቅስቅ ብላ ነበር ማልቀስ የጀመረች፡፡
አለማየሁ ጉንጮ ላይ ያለውን እንባ በመዳፎቹ እየጠረገላት ‹‹እቴቴ አይዞሽ.. አታልቅሺ …ሰሎሜን እናድናታለን…እሷ የእኛ ንግስት ነች..ንግስታችንን ማጣት አንፈልግም፡፡››ሲል አፅናናት ፡፡
‹‹ያስለቀሰኝ ሀዘን አይደለም ደስታ ነው፡፡ልጄን ወንድም ወይም እህት ሳልወልድላት ብቸኛ አደረኳት ብዬ ብዙ ጊዜ አዝኜና አልቅሼ ነበር፡፡አሁን ግን እንደተሳሳትኩ በደንብ ነው የገባኝ፡፡ወንድሞች ቢኖሯትም እናንተ ከምትወዷትና ከምትንከባከቧት በላይ ሊንከባከቧት አይችሉም ነበር፡፡
በጣም ነው የማመሰግናችሁ፡፡ እናንተ ስላላችኋት ልጄ በጣም እድለኛ ነች››
‹‹አይ እቴቴ….እሷ ስላለችን እኛ ነን እድለኞች…አሁን መላቀሱ አይጠቅመንም…ሂጂና ዶክተሮቹን ጠይቀሽ ደብዳቤውን አግኚልን፡፡››
‹‹እሺ በቃ ውስጥ ገብታችሁ ጠብቁኝ …መጣሁ››ብላ በነጠላዋ ጫፍ በጉንጮቾ የረገፈ እንባዋን እየጠረገች ወደአስተዳደር ቢሮ ሄደች፡፡
ደብዳቤውን በእጃቸው ካስገቡ በኋላ ሰፈራቸው ወደሚገኝ ባነር መታሚያ ቤት ነበር የሄድት፡፡ ደብዳቤውን አሳይተውና ሁኔታውን አስረድተው…የሰሎሜ አሳዛኝ ፎቶ የሚታይበትንና ያለችበትን ሁኔታ እጥር ምጥን ባለ ግልፅ ዓረፍተ ነገር አፅፈው ሁለት ሜትር በአንድ ሜትር በሆነ ባነር አሳተሙ፡፡ ..በማግስቱ ወደትምህርት ቤት ይዘው ሄዱ፡፡ቀጥታ ወደ ዳሪክተሩ ቢሮ ሄዱና ሁኔታውን አስረዱት….፡፡.ተማሪዎች በተሰለፉበት ባነሩ ለሁሉም እንዲታይ ተዘርግቶ ሰሎሜ ያለችበትን ሁኔታና የሚያስፈልጋትን ነገር ለሁለቱም ፈረቃ ተማሪዎች ተነገረ…፡፡በእለቱ በኪሳቸው ያላቸው ተማሪዎች ወዲያውኑ ማዋጣት ጀመሩ…ሁለት ሺ ሶስት መቶ ብር አካባቢ ተሰበሰበ፡፡በማግስቱ ሁሉም ተማሪ ለወላጆቹ በማስረዳት የቻለውን ይዞ እንዲመጣና በስም ጠሪዎች አማካይነት በየክፍሉ እንዲሰበስብ ተደረገ፡፡
በአጠቃላይ በሶስት ቀን ውስጥ ከመላው ተማሪና አስተማሪዎች 23 ሺ ብር ተሰበሰበ፡፡ትምህርት ቤቱ የሰሎሜን እናት ጠርቶ ቀጥታ ብሩን አስረከባት፡፡ የትምህርት ቤቱን ቅፅር ግቢ በእልልታ አናጋችው….ሶስቱን የልጇን ጓደኞች እያገላላበጠች ሳመቻቸው፡፡ከልቧ መረቀቻቸው፡፡ከነፍሷ ወደደቻቸው፡፡
እነአለማየሁ ግን እንደእሷ ባገኙት ነገር ፍፅም ደስታ አልተሰማቸውም ነበር፡፡የእነሱ ግምት ቢያንስ 40 እና 50 ሺ ብር እናገኛለን የሚል ነበር፡፡ወዲያው ጊዜ ሳያባክኑ ባነሩን ለሁለት ጉን ለጉን ይዘው አንደኛው በአጀንዳ ላይ እያንዳዱ ሰው የሚሰጠውን ስምና ብር እየመዘገበ በሰፈር ውስጥ እያንዳንዱን ቤት እያንኳኩ እና የድርጅቶችንም ቢሮ ዘልቀው እየገቡ ጭምር መጠየቅ ጀመሩ፡፡
በአራት ቀን ውስጥ ሌላ 20 ሺ ብር አገኙና ለእናትዬው አስረከቧት..፡፡እሷ በፊት ደብተሯ ላይ የነበራትናን ከቢሮዋ ሰራተኞች ተዋጥቶ የተሰጣት አንድ ላይ ሆኖ እነሱ ከሰበሰቡት ጋር 50 ሺ ብር አካባቢ በእጇ ያዘች፡፡
ሶስቱም በአንድ ላይ ተሰብስበው ሄደው ‹‹እቴቴ..አሁን ስንት ብር ሆነልሽ?››ብለው ጠየቋት፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
=====================
‹‹እናንተ ደግሞ ጅል አትሁኑ…ሰሎሜ ሰው ነች…ሰው ስለሆነች ታማለች…የተመመ ሰው ደግሞ በትክክለኛው ጊዜ ትክክለኛውን ህክምና ካላገኘ ይሞታል….ይሄ ሀቅ ለሌላ ሰው ከሰራ ለሰሎሜም ይሰራል፡፡››ሁሴን ነበር የተናገረው፡፡
‹‹አንተ ደግሞ ሁሉን ነገር አውቃለሁ የምትለው ነገር አለ››አለማየሁ በብስጭት መለሰለት፡፡
‹‹ትክክል ነኛ..ከእናንተ በተሻለ ብዙ ነገር አውቃለሁ…ይልቅስ ሰሎሜ ቀዶ-ጥገናዋን እንድታደርግ እኛ ምን ማድረግ አለብን ?የሚለውን መነጋገር ነው የሚጠቅመን፡፡››
‹‹ትክክል ነህ..የመጣልህ ሀሳብ አለ?››አለማየሁ ነው በጉጉት የጠየቀው፡፡
የቀዶ ጥገና እንዲደረግላት የተወሰነበትንና እና የገንዘቡን መጠን የሚገልፅ ደብዳቤ ማግኘት አለብን›› ሁሴን ሀሳብ አቀረበ፡፡
‹‹አግኝተንስ ምን እናደርገዋለን?››አላዛር ጠየቀ፡፡
‹‹በሰፈር ጠቅላላ ዞረን እንለምናለን…በትምህርት ቤታችንም እንለምናለን፡፡››
‹‹ጥሩ ሀሳብ ነው..ግን ያንን ሁሉ ብር የምናገኝ ይመስልሀል?››በጥርጣሬ ጠየቁት፡፡
‹‹እስከቻልነው እንሞክራለን…ካልሞላልን ደግሞ ሌላ ዘዴ እንፈልጋለን..አሁን ደብዳቤውን እንዴት እንደምናገኝ ማሰብ አለብን››
‹‹ለምን ሀኪም ቤት ሄደን ሰሎሜን የሚያክማትን ሀኪም አንጠይቀውም…››አላዛር ነው ሀሳቡን ያቀረበው፡፡
‹‹አይ አንተ ጅል የሆንክ ልጅ..አሁን ሄደን ብንጠይቀው ለ13 አመት ልጇች እንዲህ አይነት መረጃ ሚሰጠን ይመስልሀል?››
‹‹እኔ እንጃ ግራ ስለገባኝ እኮ ነው፡፡››
‹‹ለምን እቴቴን አንጠይቃትም..እሷ ደብዳቤውን ልታስወጣልን ትችላለች››
‹‹አሌክስ ትክክል ነው..ጊዜ ሳናባክን አቴቴን እናናግራት››ሁሴን በአለማየሁ ሀሳብ ወዲያው ተስማማ፡፡
‹‹ግን እኮ እሷ ሆስፒታል ነው ያለችው››
‹‹እኮ እንሂዳ››
ተስማሙና ቀጥታ ሰሎሜ ወደተኛችበት ሆስፒታል ነበር የሄዱት፡፡ሰሎሜ የተኛችበት ክፍል ገብተው ያለችበትን ሁኔታ ካዩ በኃላ‹‹እቴቴ አንዴ ውጭ ልናናግርሽ ፈልገን ነበር፡፡››ሲሉ ጠየቋት፡፡
‹‹ምነው በሰላም?››
‹‹በሰላም ነው..ሰሎሜ ስለተኛች እዚህ ስናወራ እንዳንቀሰቅሳት ነው››አለ ሁሴን፡፡
‹‹እሺ እንዳላችሁ ››በማለት ተስማምታ ተከትላቸው ወጣች፡፡እዛው ሆስፒታሉ በረንዳ ላይ ካለ አግዳሚ ወንበር ላይ በመደዳ ተቀመጡ፡፡
ለነገሩ ብዙም ትኩረት ባለመስጠት‹‹እሺ ልጆች ..ለምንድነበር የፈለጋችሁኝ?››ስትል ጠየቀቻቸው፡፡
‹‹ሰሎሜ እንዴት ነች?››
ቀዝቀዝ ባለ ስሜት ‹‹ደህና ነች..ምንም አትል››ስትል መለሰችላቸው፡፡
‹‹ማለት ስለቀዶ ጥገናው ነው የምናወራሽ…?እንዴት ነው የሚሆነው…?ያን ያህል ብር ከየት ታመጪያለሽ?››
‹‹ልጇች አትጨነቁ..ከየትም ብዬ ከየትም ይሄንን ብር አግኝቼ ብቸኛ ልጄን ማሳከም አለብኝ….አታስቡ ጓደኛችሁን እንድትድን የተቻለኝን አደርጋለሁ፡፡››ስትል እንባ እየተናነቃት መለሰችላቸው፡፡በእውነት ብሩን ከየት እንደምታመጣው…የትኞቹን ዘመዶቾን እንደምታስቸግር…የትኛውን ንብረቷን ብትሸጥ የተጠየቀችውን ብር ማግኘት እንደምትችል ምንም አይነት ሀሳብም ሆነ ተስፋ አልነበራት፡፡ግን ለልጆቹ ይሄንን ምን ብላ በምን አይነት ቋንቋ ልታስረዳቸው ትችላለች፡፡ለዛ ነው በደፈናው ልታፅናናቸው የወሰነችው፡፡
‹‹እቴቴ…ሰሎሜን ለማዳን የተቻለንን ብቻ ሳይሆን ከምንችለው በላይ ነው ማድረግ ያለብን…ሶስታችንም ልክ እንደአንቺ እሷን ለማጣት ዝግጁ አይደለንም…እና የሆነ ነገር ለማድረግ አስበናል፡››ሁሴን ነበር ተናጋሪው፡፡
አቴቴ ግራ በመጋባት‹‹ምን ማለት ነው …?እናንተ ደግሞ ምን ማድረግ ትችላላችሁ?››
‹‹ከሀኪም ቤቱ ቀዶ ጥገና ማድረግ እንዳለባት መወሰኑን እና ለዛም የሚያስፈልገውን ብር የሚገልጽ ደብዳቤ እንዲሰጡሽ ጠይቂያቸው››
‹‹ማለት ..ደብዳቤው ምን ያደርግልኛል?››
‹‹አይ ላንቺ አይደለም..ለእኛ ያስፈልገናል››
‹‹ለምን .?.ምን ልታደርጉበት?››
ትምህርት ቤታቸውን ሆነ በሰፈራችን እርዳታ እየዞርን እንጠይቃለን..ከየአንዳንዱ ሰው አንድ ብርም ሆነ አስር ብር እየዞርን እንሰበስባለን…ለዛ ግን ሰው እንዲያምነን እና ስራችን ቀላል እንዲሆንልን መረጃው ያስፈልገናል፡፡››
በወቅቱ የሰሎሜ እናት ስሜቷን መቆጣጠር አልቻለችም ነበር…ሁሉንም አንድ ላይ አቅፋ ጉያዋ ውስጥ በመወሸቅ ስቅስቅ ብላ ነበር ማልቀስ የጀመረች፡፡
አለማየሁ ጉንጮ ላይ ያለውን እንባ በመዳፎቹ እየጠረገላት ‹‹እቴቴ አይዞሽ.. አታልቅሺ …ሰሎሜን እናድናታለን…እሷ የእኛ ንግስት ነች..ንግስታችንን ማጣት አንፈልግም፡፡››ሲል አፅናናት ፡፡
‹‹ያስለቀሰኝ ሀዘን አይደለም ደስታ ነው፡፡ልጄን ወንድም ወይም እህት ሳልወልድላት ብቸኛ አደረኳት ብዬ ብዙ ጊዜ አዝኜና አልቅሼ ነበር፡፡አሁን ግን እንደተሳሳትኩ በደንብ ነው የገባኝ፡፡ወንድሞች ቢኖሯትም እናንተ ከምትወዷትና ከምትንከባከቧት በላይ ሊንከባከቧት አይችሉም ነበር፡፡
በጣም ነው የማመሰግናችሁ፡፡ እናንተ ስላላችኋት ልጄ በጣም እድለኛ ነች››
‹‹አይ እቴቴ….እሷ ስላለችን እኛ ነን እድለኞች…አሁን መላቀሱ አይጠቅመንም…ሂጂና ዶክተሮቹን ጠይቀሽ ደብዳቤውን አግኚልን፡፡››
‹‹እሺ በቃ ውስጥ ገብታችሁ ጠብቁኝ …መጣሁ››ብላ በነጠላዋ ጫፍ በጉንጮቾ የረገፈ እንባዋን እየጠረገች ወደአስተዳደር ቢሮ ሄደች፡፡
ደብዳቤውን በእጃቸው ካስገቡ በኋላ ሰፈራቸው ወደሚገኝ ባነር መታሚያ ቤት ነበር የሄድት፡፡ ደብዳቤውን አሳይተውና ሁኔታውን አስረድተው…የሰሎሜ አሳዛኝ ፎቶ የሚታይበትንና ያለችበትን ሁኔታ እጥር ምጥን ባለ ግልፅ ዓረፍተ ነገር አፅፈው ሁለት ሜትር በአንድ ሜትር በሆነ ባነር አሳተሙ፡፡ ..በማግስቱ ወደትምህርት ቤት ይዘው ሄዱ፡፡ቀጥታ ወደ ዳሪክተሩ ቢሮ ሄዱና ሁኔታውን አስረዱት….፡፡.ተማሪዎች በተሰለፉበት ባነሩ ለሁሉም እንዲታይ ተዘርግቶ ሰሎሜ ያለችበትን ሁኔታና የሚያስፈልጋትን ነገር ለሁለቱም ፈረቃ ተማሪዎች ተነገረ…፡፡በእለቱ በኪሳቸው ያላቸው ተማሪዎች ወዲያውኑ ማዋጣት ጀመሩ…ሁለት ሺ ሶስት መቶ ብር አካባቢ ተሰበሰበ፡፡በማግስቱ ሁሉም ተማሪ ለወላጆቹ በማስረዳት የቻለውን ይዞ እንዲመጣና በስም ጠሪዎች አማካይነት በየክፍሉ እንዲሰበስብ ተደረገ፡፡
በአጠቃላይ በሶስት ቀን ውስጥ ከመላው ተማሪና አስተማሪዎች 23 ሺ ብር ተሰበሰበ፡፡ትምህርት ቤቱ የሰሎሜን እናት ጠርቶ ቀጥታ ብሩን አስረከባት፡፡ የትምህርት ቤቱን ቅፅር ግቢ በእልልታ አናጋችው….ሶስቱን የልጇን ጓደኞች እያገላላበጠች ሳመቻቸው፡፡ከልቧ መረቀቻቸው፡፡ከነፍሷ ወደደቻቸው፡፡
እነአለማየሁ ግን እንደእሷ ባገኙት ነገር ፍፅም ደስታ አልተሰማቸውም ነበር፡፡የእነሱ ግምት ቢያንስ 40 እና 50 ሺ ብር እናገኛለን የሚል ነበር፡፡ወዲያው ጊዜ ሳያባክኑ ባነሩን ለሁለት ጉን ለጉን ይዘው አንደኛው በአጀንዳ ላይ እያንዳዱ ሰው የሚሰጠውን ስምና ብር እየመዘገበ በሰፈር ውስጥ እያንዳንዱን ቤት እያንኳኩ እና የድርጅቶችንም ቢሮ ዘልቀው እየገቡ ጭምር መጠየቅ ጀመሩ፡፡
በአራት ቀን ውስጥ ሌላ 20 ሺ ብር አገኙና ለእናትዬው አስረከቧት..፡፡እሷ በፊት ደብተሯ ላይ የነበራትናን ከቢሮዋ ሰራተኞች ተዋጥቶ የተሰጣት አንድ ላይ ሆኖ እነሱ ከሰበሰቡት ጋር 50 ሺ ብር አካባቢ በእጇ ያዘች፡፡
ሶስቱም በአንድ ላይ ተሰብስበው ሄደው ‹‹እቴቴ..አሁን ስንት ብር ሆነልሽ?››ብለው ጠየቋት፡፡