#ልጩህበት !!
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ታድያ ልጩህ እንጂ ሌላ ምን እላለሁ
የገዛ ጩኸቴ ለኔ እየተሰማ
ንዴቴን
ብሶቴን
ናፍቆቴን ባከስመው
እኔ እየጮህኩኝ እኔ እራሴ ልስማው!!
••••አለ። ጨረስክ አልኩት ።አፍጦ እያየኝ•••
"አዎ ግጥሜን ጨርሻለሁ ግን አንተም ዝም ብለህ አትጩህ እሺ •••
እኔ ከባጃጅህ አልወረድኩ አንተ ግን ከገባሁ ጀምሮ ዝም ብለህ ትጮሀለህ ስማኝ የት እና መቼ እንደምትጮህ ካላወክ ዝም ብትል ይሻላል
ያለበለዚያ ሰሚ ሳይኖር ዝም ብለህ ብትጮህ የራስህ ጩኸት እራስህን ያደነቁርህ እንደሆን እንጂ ምንም አታመጣም !"
ብሎኝ ሲያበቃ ደሞ ወድያው ወደሷ ዞረና
"አንድ ግዜ ብቻ ልጩህ በናትሽ ?"
ሲላት ቀርታኝ የነበረችው እንጥፍጣፊ ትግስት ተሟጠጠች •••
አቦ ባባ ክብር ካልወደደልህ እንዴት እንደምትወርድ ላሳይሀ እንግዲህ ብዬ እጄን ለፀብ እያሰናዳሁ ወርጄ ስጠጋው
"ተው ተው ተው ቦክስ አታባክን ወጣቱ መጀመሪያውኑ እንደዚህ ወንድ ብትሆን ኖሮ አንተ ባጃጅ ውስጥ እስካሁን ማን ይቀመጥ ነበር ፈሪ ፈሪ ነገር ነህ !"
እያለ ከባጃጇ ሲወርድ ልጅቷ በሳቅ ፈነደቀች
ግራ ቀኝ እየተወዛወዘ ትንሽ ከባጃጇ ራቅ እንዳለ ዘወር አለና
"ሞት ይርሳኝ ቻው እሺ የኔ ልጅ ልጅ አልኩ እንዴ አንቺን እንኳን አላደርስም !
ቻው እሺ የኔ ልእልት አንቺን የመሰለች ልጅ ከዚህ አስቀያሚ ሹፌር ጋር በማየቴ ደንግጫለሁ !
ፍችው በናትሽ! " እላት።
"እሺ "አለችው በሳቋ መሀል
"ግን መች ትፈችዋለሽ በናትሽ! እ••• እ ••እ ንገሪኛ?" እያለ ሊመለስ ሲል እኔም እየሳኩ ወደሱ ስጠጋ ፊቱን አዙሮ ከቆምንበት በስተቀኝ መንገድ ዳር ወዳለችው የማትዘጋዋ መጠጥ ቤት አመራ።
ባጃጃን አስነስቼ ከዩንቨርስቲው በቅርብ ርቀት
ጨለማ ውስጥ አቆምኳትና ከመሪው ላይ ተነስቼ እሷ አጠገብ ተቀመጥኩ ። ፊቷ ተቀያየረ።
ካቆምንበት እንቀጥላ አልኳትና
ቅድም የፈለከውን አርገኝ ስትይ ምን ለማለት ፈልገሽ ነበር ?
"በቃ ከፈለክ ልትሰድበኝም ከፈልክ ልታወርደኝም ትችላለህ ሌላ ምንድን ነው?" አለችኝ የጭንቀቷን
ወደ ዩንቨርስቲው ዞሬ ተመለከትኩ አጠገባችን ነው ግቢው ከሩቅ ይታያል ሳቄ መጣ አብራኝ ሳቀች።
ሀይ ስትደርሺ ነው እንዴ ልታወርደኝ ትችላለህ እምትይው? ስላት•••
ጭንቅላቷን ወደ ግራ ሰበቀችና በዝምታ እጇን እያፍተለተለች አይን አይኔን ታየኝ ጀመር
የሆነ ስሜት ተሰማኝ
ታውቂያለሽ ሁለት ወንድሞች አሉኝ ግን እህት የለኝም ቢሆንም እናት አለኝ የማይሆን ቢሆንም እናትም ባይኖረኝ እራሱ አንቺ ላይ የሚጨክን አንጀት የለኝም
ምንም አልደርግሽምም አልሰድብሽምም አላወርድሽምም እሺ መጀመሪያውኑ ብር እንደሌለሽ ብትነግሪኝና በነፃ እንዳደርስሽ ብትጠይቂኝ ለስራ ብወጣም ከሰአቱ አንፃር ላውሬ ጥዬሽ አልሄድም ነበር ።
እያሰብኩ የነበረው ምናልባት መጥፎ ባህሪ ያለው የባጃጅ ሹፌር አጋጥሟት ቢሆን ኖሮስ እያልኩ ነው።
ግን ምን አጋጥሞሽ ነው ማለቴ
በዚህ ሰአት ብቻሽን እዛ ጭፈራ ቤት በር ላይ ለምን ቆምሽ ?ስለራስሽም ብትነግሪኝ ደስ ይለኛል
"አጋጣሚው ከብዙ ነገሮች ጋር የተያያዘ ነው ኬቱ ጋር ልጀምርልህ?
ከፈለግሽው።
"በናትህ አሁን መሽቷል ሞባይሌን ዶርም ጥዬው ወጥቼ ነው ከፈለክ ስልኬን ያዝና ነገ ወይ በሚመችህ ቀን ደውልልኝ አወራሀለሁ!"
እዚሁ ባጃጅ ውስጥ እናድራታለን እንጂ አልፋታሽም አልኳት ኮስተር ብዬ
" እያስገደድከኝ ነው ማለት ነው አለች እሷም በስሱ ከስተር ብላ
ስትስቅም ስትኮሳተርም የሚያምርባት ሴት እሷን አየሁ።
አሁን ከተለያየን ቡሀላ ልታገኝኝ ፍቃደኛ ሁኚ አትሁኝ እርግጠኛ ስላልሆንኩ አሁኑኑ እንድትነግሪኝ እየለመንኩሽ ነው! ከተጫንኩሽ ይቅር ብትነግሪኝ ግን የመጣሽበትን ሂሳብ እንደከፈልሽ እቆጥረዋለሁ አልኳትና አሁንም እኩል ሳቅን።
"ክትክትክትክት ኧረ ባክህ
እሺ ግን ባጭሩ ነው በደንብ እንድትረዳው ገባ ብዬ ብጀምርልህ ይረዝምብኛል?"
አቦ ንገሪኝኛ አታጓጊኝ!።
" እኔ
እኔ
እኔ ማለት እኔ ደሀ ከሚባል ቤተሰብ ነው የተወለድኩት ።
አባቴ አናፂ ነው እናቴ ደግሞ ሽንኩርት ቲማቲም ምናምን ነው ጉሊት ውስጥ የምትቸረችረው
ሁለቱም ፀሀይ ላይ ውለው ፊታቸው ጠቁሮ ከሚያገኙት ገቢ ውስጥ አብዛኛውን እኔን ከሰፈሬ እና ከትምህርት ቤት ጓደኛቼ እኩል ማድረግ ባይችሉ እንኳን ክፍተቱን በመጠኑ አጥብበው ብዙ ሳይሰማኝ እንዳድግ ለማድረግ አውለውታል።
ሳይለብሱ ያለብሱኛል
ለነሱ ርካሽ የተባለውን ጫማ እየተጫሙ ለኔ ውድና ሁለት ሶስት ቅያሪ ጫማ እንዲኖረኝ ለማድረግ ለነሱ የሚያስፈልጉዋቸውን ሁሉ ወደ ጎን ትተዋል !
ሳይደሰቱ እኔን ለማስደሰት የቻሉትን ሁሉ አድርገዋል!
ቢኮራረፉ እኔ ፊት ይስቃሉ!
ቢያዝኑ እኔ ፊት ደስተኛ ለመምሰል ይሞክራሉ!
በአጠቃላይ ለራሳቸው ሳይኖሩ ለኔ ደክመው ለኔ ኖረው ያስተማሩኝን ቤተሰቦቼን ለማስደሰት የምችለው በትምህርቴ ስጎብዝ ነውና ምንም ነገር ሳያታልለኝ በርትቼ በመማር ወደ ዩንቨርስቲ መግቢያ የሚሆን ውጤት አምጥቼ ባስደሰትኳቸው ማግስት ነበር አባዬ እኔ ወደዚህ ለመምጣት የሚያስፈልገኝን ነገር ለሟሟላት ከበፊቱ በተለየ ሁኔታ ያገኘውን ስራ በሙሉ እየሰራ ገንዘቡን እኔው ጋር ማጠራቀም የጀመረው •••"
አለችና ዝም አለች።
ምነው ቀጥይ እንጂ ስላት
"ስላባዬ ሳወራ ጨነቀኝ !
ትንሽ ዝምታ ተፈጠረ በመሀላችን።
ሲጨንቀኝ ደሞ ምን ትዝ እንዳለኝ ታውቃለህ?"
ምን ትዝ አለሽ ?
አንዴ ልጩህ እሚለው የቅድሙ ሰካራም ።
አንዴ ልጩህ እንዴ?"
ስትለኝ ሁለታችንም ባንድ ግዜ ከነበርንበት ሙድ ወጥተን ከባጃጇ ጣራ በላይ ሳቅን።
በናትሽ ቀጥይልኝ ? አልኳት ሳቄን ስጨርስ። ካሳቁ መልስ ደሞ ባንዴ ፊቷን ቅጭም አርጋ ቀጠለች•••
አባዬ ድካሙና እንቅልፉ ተደራርቦበት ነበር ።
ልመጣ ሁለት ሳምንት ሲቀረኝ •••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ታድያ ልጩህ እንጂ ሌላ ምን እላለሁ
የገዛ ጩኸቴ ለኔ እየተሰማ
ንዴቴን
ብሶቴን
ናፍቆቴን ባከስመው
እኔ እየጮህኩኝ እኔ እራሴ ልስማው!!
••••አለ። ጨረስክ አልኩት ።አፍጦ እያየኝ•••
"አዎ ግጥሜን ጨርሻለሁ ግን አንተም ዝም ብለህ አትጩህ እሺ •••
እኔ ከባጃጅህ አልወረድኩ አንተ ግን ከገባሁ ጀምሮ ዝም ብለህ ትጮሀለህ ስማኝ የት እና መቼ እንደምትጮህ ካላወክ ዝም ብትል ይሻላል
ያለበለዚያ ሰሚ ሳይኖር ዝም ብለህ ብትጮህ የራስህ ጩኸት እራስህን ያደነቁርህ እንደሆን እንጂ ምንም አታመጣም !"
ብሎኝ ሲያበቃ ደሞ ወድያው ወደሷ ዞረና
"አንድ ግዜ ብቻ ልጩህ በናትሽ ?"
ሲላት ቀርታኝ የነበረችው እንጥፍጣፊ ትግስት ተሟጠጠች •••
አቦ ባባ ክብር ካልወደደልህ እንዴት እንደምትወርድ ላሳይሀ እንግዲህ ብዬ እጄን ለፀብ እያሰናዳሁ ወርጄ ስጠጋው
"ተው ተው ተው ቦክስ አታባክን ወጣቱ መጀመሪያውኑ እንደዚህ ወንድ ብትሆን ኖሮ አንተ ባጃጅ ውስጥ እስካሁን ማን ይቀመጥ ነበር ፈሪ ፈሪ ነገር ነህ !"
እያለ ከባጃጇ ሲወርድ ልጅቷ በሳቅ ፈነደቀች
ግራ ቀኝ እየተወዛወዘ ትንሽ ከባጃጇ ራቅ እንዳለ ዘወር አለና
"ሞት ይርሳኝ ቻው እሺ የኔ ልጅ ልጅ አልኩ እንዴ አንቺን እንኳን አላደርስም !
ቻው እሺ የኔ ልእልት አንቺን የመሰለች ልጅ ከዚህ አስቀያሚ ሹፌር ጋር በማየቴ ደንግጫለሁ !
ፍችው በናትሽ! " እላት።
"እሺ "አለችው በሳቋ መሀል
"ግን መች ትፈችዋለሽ በናትሽ! እ••• እ ••እ ንገሪኛ?" እያለ ሊመለስ ሲል እኔም እየሳኩ ወደሱ ስጠጋ ፊቱን አዙሮ ከቆምንበት በስተቀኝ መንገድ ዳር ወዳለችው የማትዘጋዋ መጠጥ ቤት አመራ።
ባጃጃን አስነስቼ ከዩንቨርስቲው በቅርብ ርቀት
ጨለማ ውስጥ አቆምኳትና ከመሪው ላይ ተነስቼ እሷ አጠገብ ተቀመጥኩ ። ፊቷ ተቀያየረ።
ካቆምንበት እንቀጥላ አልኳትና
ቅድም የፈለከውን አርገኝ ስትይ ምን ለማለት ፈልገሽ ነበር ?
"በቃ ከፈለክ ልትሰድበኝም ከፈልክ ልታወርደኝም ትችላለህ ሌላ ምንድን ነው?" አለችኝ የጭንቀቷን
ወደ ዩንቨርስቲው ዞሬ ተመለከትኩ አጠገባችን ነው ግቢው ከሩቅ ይታያል ሳቄ መጣ አብራኝ ሳቀች።
ሀይ ስትደርሺ ነው እንዴ ልታወርደኝ ትችላለህ እምትይው? ስላት•••
ጭንቅላቷን ወደ ግራ ሰበቀችና በዝምታ እጇን እያፍተለተለች አይን አይኔን ታየኝ ጀመር
የሆነ ስሜት ተሰማኝ
ታውቂያለሽ ሁለት ወንድሞች አሉኝ ግን እህት የለኝም ቢሆንም እናት አለኝ የማይሆን ቢሆንም እናትም ባይኖረኝ እራሱ አንቺ ላይ የሚጨክን አንጀት የለኝም
ምንም አልደርግሽምም አልሰድብሽምም አላወርድሽምም እሺ መጀመሪያውኑ ብር እንደሌለሽ ብትነግሪኝና በነፃ እንዳደርስሽ ብትጠይቂኝ ለስራ ብወጣም ከሰአቱ አንፃር ላውሬ ጥዬሽ አልሄድም ነበር ።
እያሰብኩ የነበረው ምናልባት መጥፎ ባህሪ ያለው የባጃጅ ሹፌር አጋጥሟት ቢሆን ኖሮስ እያልኩ ነው።
ግን ምን አጋጥሞሽ ነው ማለቴ
በዚህ ሰአት ብቻሽን እዛ ጭፈራ ቤት በር ላይ ለምን ቆምሽ ?ስለራስሽም ብትነግሪኝ ደስ ይለኛል
"አጋጣሚው ከብዙ ነገሮች ጋር የተያያዘ ነው ኬቱ ጋር ልጀምርልህ?
ከፈለግሽው።
"በናትህ አሁን መሽቷል ሞባይሌን ዶርም ጥዬው ወጥቼ ነው ከፈለክ ስልኬን ያዝና ነገ ወይ በሚመችህ ቀን ደውልልኝ አወራሀለሁ!"
እዚሁ ባጃጅ ውስጥ እናድራታለን እንጂ አልፋታሽም አልኳት ኮስተር ብዬ
" እያስገደድከኝ ነው ማለት ነው አለች እሷም በስሱ ከስተር ብላ
ስትስቅም ስትኮሳተርም የሚያምርባት ሴት እሷን አየሁ።
አሁን ከተለያየን ቡሀላ ልታገኝኝ ፍቃደኛ ሁኚ አትሁኝ እርግጠኛ ስላልሆንኩ አሁኑኑ እንድትነግሪኝ እየለመንኩሽ ነው! ከተጫንኩሽ ይቅር ብትነግሪኝ ግን የመጣሽበትን ሂሳብ እንደከፈልሽ እቆጥረዋለሁ አልኳትና አሁንም እኩል ሳቅን።
"ክትክትክትክት ኧረ ባክህ
እሺ ግን ባጭሩ ነው በደንብ እንድትረዳው ገባ ብዬ ብጀምርልህ ይረዝምብኛል?"
አቦ ንገሪኝኛ አታጓጊኝ!።
" እኔ
እኔ
እኔ ማለት እኔ ደሀ ከሚባል ቤተሰብ ነው የተወለድኩት ።
አባቴ አናፂ ነው እናቴ ደግሞ ሽንኩርት ቲማቲም ምናምን ነው ጉሊት ውስጥ የምትቸረችረው
ሁለቱም ፀሀይ ላይ ውለው ፊታቸው ጠቁሮ ከሚያገኙት ገቢ ውስጥ አብዛኛውን እኔን ከሰፈሬ እና ከትምህርት ቤት ጓደኛቼ እኩል ማድረግ ባይችሉ እንኳን ክፍተቱን በመጠኑ አጥብበው ብዙ ሳይሰማኝ እንዳድግ ለማድረግ አውለውታል።
ሳይለብሱ ያለብሱኛል
ለነሱ ርካሽ የተባለውን ጫማ እየተጫሙ ለኔ ውድና ሁለት ሶስት ቅያሪ ጫማ እንዲኖረኝ ለማድረግ ለነሱ የሚያስፈልጉዋቸውን ሁሉ ወደ ጎን ትተዋል !
ሳይደሰቱ እኔን ለማስደሰት የቻሉትን ሁሉ አድርገዋል!
ቢኮራረፉ እኔ ፊት ይስቃሉ!
ቢያዝኑ እኔ ፊት ደስተኛ ለመምሰል ይሞክራሉ!
በአጠቃላይ ለራሳቸው ሳይኖሩ ለኔ ደክመው ለኔ ኖረው ያስተማሩኝን ቤተሰቦቼን ለማስደሰት የምችለው በትምህርቴ ስጎብዝ ነውና ምንም ነገር ሳያታልለኝ በርትቼ በመማር ወደ ዩንቨርስቲ መግቢያ የሚሆን ውጤት አምጥቼ ባስደሰትኳቸው ማግስት ነበር አባዬ እኔ ወደዚህ ለመምጣት የሚያስፈልገኝን ነገር ለሟሟላት ከበፊቱ በተለየ ሁኔታ ያገኘውን ስራ በሙሉ እየሰራ ገንዘቡን እኔው ጋር ማጠራቀም የጀመረው •••"
አለችና ዝም አለች።
ምነው ቀጥይ እንጂ ስላት
"ስላባዬ ሳወራ ጨነቀኝ !
ትንሽ ዝምታ ተፈጠረ በመሀላችን።
ሲጨንቀኝ ደሞ ምን ትዝ እንዳለኝ ታውቃለህ?"
ምን ትዝ አለሽ ?
አንዴ ልጩህ እሚለው የቅድሙ ሰካራም ።
አንዴ ልጩህ እንዴ?"
ስትለኝ ሁለታችንም ባንድ ግዜ ከነበርንበት ሙድ ወጥተን ከባጃጇ ጣራ በላይ ሳቅን።
በናትሽ ቀጥይልኝ ? አልኳት ሳቄን ስጨርስ። ካሳቁ መልስ ደሞ ባንዴ ፊቷን ቅጭም አርጋ ቀጠለች•••
አባዬ ድካሙና እንቅልፉ ተደራርቦበት ነበር ።
ልመጣ ሁለት ሳምንት ሲቀረኝ •••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍2
#ልጩህበት ! !
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
"ስላባዬ ሳወራ ጨነቀኝ !
ትንሽ ዝምታ ተፈጠረ በመሀላችን።
ሲጨንቀኝ ደሞ ምን ትዝ እንዳለኝ ታውቃለህ?"
ምን ትዝ አለሽ ?
አንዴ ልጩህ እሚለው የቅድሙ ሰካራም ።
አንዴ ልጩህ እንዴ?"
ስትለኝ ሁለታችንም ባንድ ግዜ ከነበርንበት ሙድ ወጥተን ከባጃጇ ጣራ በላይ ሳቅን።
በናትሽ ቀጥይልኝ ? አልኳት ሳቄን ስጨርስ። ካሳቁ መልስ ደሞ ባንዴ ፊቷን ቅጭም አርጋ ቀጠለች•••
አባዬ ድካሙና እንቅልፉ ተደራርቦበት ነበር ።
ልመጣ ሁለት ሳምንት ሲቀረኝ •••
••••
ልመጣ ሁለት ሳምንት ሲቀረኝ በሂወቴ እማረሳው መጥፎ አጋጣሚ ተፈጠረ ቀኑ አርብ ነበር አባዬ እንደተለመደው በለሊት ነበር ወደ ስራ የወጣው
ያን ሰሞን የሚሰራበት ቦታ ከኛ ቤት ብዙ ስለማይርቅ እንደነገ ልጀምር ማታ እማዬን በጥዋት እየተነሳሽ ምሳ አትቋጥሪልኝ ቀስ ብለሽ ስሪና አለሜ ታምጣልኝ አላት ስሜ ኤደን ቢሆንም አባ ግን አለሜ የኔአለም እያለ ነው እሚጠራኝ።
ለአራት ቀናት ምሳውን ስራ ቦታ እየወሰድኩለት እስኪበላ እያዋራሁት እምለሳለሁ በአምስተኛው ቀን ጓደኛዬ አርብ እለት ከማዬ ጋር ልብስ ይዥበት የምመጣውን ቦርሳ ለመግዛት አብረን ወጥተን ስለነበር ምሳውን ሳላደርስለት ሰአቱ ሄደብኝ በውስጡ ልጄን ምን አጋጠማት እያለ ሲጨነቅ ነበር ለካ ከቀኑ ሰባት ሰአት ተኩል ላይ ምሳውን ይዤ ከቤት ወጣሁ ከ15 ደቂቃ ቡሀላ ደረስኩ።
ቀና ስል•••
አባዬ በግምት ከመሬት አምስት ሜትር ከፍታ ላይ ተሰቅሎ ስራውን እየሰራ ነው አባ ብዬ ጮክ ብዬ ስጣራ ስቆይበት ጭንቀት ላይ የነበረው አባዬ የኔን የልጁን ድምፅ ድንገት ሲሰማ ደነገጠ መስለኝ ሳይጠነቀቅ እኔን ለማየት የያዘውን ለቆ ዞረ!
ወድያው ከላይ ቁልቁል ሲምዘገዘግ አይኔን ማመን ተሳነኝ በሂወቴ እንደዛን ቀን ደንግጬ አላውቅም ውሃ ሆንኩ ወደ ወደቀው አባቴ መጠጋት ፈርቼ በቆምኩበት ስጮህ ባከባቢው የነበሩ ሰራተኛች ከወደቀበት አንስተው አናቱ ላይ ውሀ ሲያፈሱበት ተመለከትኩ
ተርፏል አባቴ !
ተርፏል አባቴ !
እያልኩ ወደሱ በመሮጥ እያለቀስኩ አንገቱ ላይ ተጠመጠምኩበት።
እግሩና የጎን አጥንቱ ላይ ጉዳት ደረሰበት ያን ቀን አሰሪው ሀኪም ቤት ወስዶ ህክምና ተደረገለት ከዛን ቀን ቡሀላ ግን ዘወር ብሎም አላየውም
ከ አምስት ቀን ቡሀላ እኔ ጋር ያለው ለዩንቨርስቲ ጉዞዬ ብሎ ያጠራቀመው ገንዘብ ለሱ ህክምና እንዳልጠቀምበት ብሎ ሳይሻለው ተሽሎኛል ብሎ ከሀኪም ቤት ወጣና እቤታችን ተኛ
ለሊት ለሊት ሲያቃስት ስለሰማሁት አባ እሺ በለኝ እና በደንብ ታከም እኔ ጋር ባለው ብር ታክመህ ካልዳንክ ወደ ዩንቨርስቲ እንደማልሄድ እወቀው ስለው እሺ አለኝ።
አሳክሜው የተረፈችኝን ይዤ መጣሁ እዚህ ከመጣሁ አራት ወር ሊሞላኝ ነው ግን እስካሁን ስራ አልጀመረም እማዬ በምትሰራው ብቻ ስለሚኖሩ እማን ላለማጨናነቅ ብዬ ምንም ወጪ የለብኝም ብር እንዳትልኪልኝ አልኳት
እዚህ ደግሞ ብዙ ወጭዎች አሉ ኖቶችን(ሀንድ አውቶችን) ኮፒ ከማረግ ጀምሮ ብዙ ነገሮች አሉ በተለይ ሴት ልጅ ከወንድ ልጅ በባሰ ሁኔታ እጇ ላይ ሳንቲም ያስፈልጋታል ሁሉንም ፍላጎቷን ማስቀረት ብትችል የሞድየስን እና የአንዳንድ ነገር ወጪዎቿ ግድ ናቸው።
በዚህ ግቢ ማደሪያ ክፍላችን (ዶርም) ውስጥ በጣም የምቀርባቸው ሁለት ጓደኛች አሉኝ የመጣን ሰሞን ስለሂወታችን ስናወራ የሶስታችንም ቤተሰቦቻች በተቀራራቢ የድህነት ህይወት ውስጥ ያሉ እድሚያችን ፣አለባበሳችን፣ ፍላጎታችን ፣ ችግራችን ባጠቃላይ በተመሳሳይ ህይወት ውስጥ ማለፋችን ነው መሰል ቶሎ ለመቀራረብና እንደህታማቾች ለመተሳሰብ እና ለመተዛዘን ግዜ አልፈጀብንም።
እማንለያይ አንዳችን ላንዳችን የምንጨነቅ ሆንን ከቅባት ጀምሮ የሚያስፈልጉንን አዋጥተን እንገዛለን አንዳችን ያንዳችንን ልብስ ለመልበስ ፍቃድ መጠየቅ አያስፈልገንም የነሱን ባላውቅም እኔ ሁለቱንም በጣም ነው እምወዳቸው ።
ትንሽ እንደቆየን በተለይ አንዲት የሶስተኛ አመት ተማሪ ባጋጣሚ ከአንደኛዋ ጋደኛዬ ጋር ተዋውቋ ዶርማችን መጥታ ከተዋወቀችንና በየቀኑ መምጣት ከጀመረች ቡሀላ ነገሮች በፍጥነት መቀያየር ጀመሩ።
እኔ ልጅቷ የምታወራው ነገር ሁሉ ስለማይጥመኝ ብዙም አልቀርባትም ነበር ።
ከሁለቱ ጋር ግን በጣም ተቀራረበች ጭራሽ ከግቢ ውጪ አምሽተው አንዳንዴም አድረው መምጣት ጀመሩ የት ሄዳችሁ ነው? ስላቸው ከሷ ጋር እንደነበሩ ይነግሩኛል የጓደኝነቴን ትምህርታቸው ላይ እንዱያተኩሩና ከሷ ልጅ ጋር መዞሩን እንዲቀንሱ ብነግራቸውም ጭራሽ ባሰባቸው ። እንደውም እኔም አብሬያቸው ዘና እንድል በተለያየ መንገድ ሊያሳምኑኝ ይሞክሩ ጀመር።
በተዋወቋት ባጭር ግዜ ውስጥ እኔ ለፎቶ ኮፒ ተቸግሬ ፍዳዬን ሳይ እነሱ ልብስና ጫማ በየሳምንቱ መቀያየር ጀመሩ ከኔ ጋር ያላቸው ልዩነት እየሰፋ እየሰፋ መጣ የነበሩት ነገሮች በሙሉ ተለዋወጡ እንኳን ከኔ ጋር ቅባት አዋጥተው ሊገዙ እንኳን ከኔ ጋር ልብስ ሊቀያየሩ የበፊቶቹን ልብሶቻቸውን ከፈለኩ መውሰድ እንደምችል ይነግሩኝ ጀመር።
ቅባት ሻንፖ ሎሽን የመሳሰሉትን ነገሮች ገዝተው ሲሰጡኝና እና ለፎቶ ኮፒ የሚሆነኝን ገንዘብ ስፈልግ እንድጠይቃቸው ሲነግሩኝ ከምልህ በላይ ይሰማኝ ጀመር በቃ በፊት ተሰምቶኝ የማያውቅ የበታችነት ስሜት ተረጋግቼ ማጥናት እስክቸገር ድረስ መጥፎ ሁኔታ ውስጥ ከተተኝ።
በዛ ሁኔታ ውስጥ ሆኜ ደግሞ ያቺ ጓደኛቸው እና እነሱ እነሱን እንድመስል አብሬያቸው እንድውል እና እንዳመሽ ባገኙት አጋጣሚ ይወተውኛል ።
በቅርቡ የመጀመሪያው ሴሚስተር ፈተና ነበርና በየትምህርት አይነቱ ያሉትን ኖቶች ኮፒ ለማድረግ በጣም ሳንቲም ያስፈልገኝ ነበር።
ያቺ ጓደኛቸው ያዘነች መስላ ያንን ወጪ በነሱ በኩል
በመሸፈን በውለታ ከያዘችኝ ቡኋላ
ዶርም መጥታ ፈተና ስንጨርስ አብሬያቸው ወጣ ብዬ ለመዝናናት ፍቃደኛ እንድሆንና ቃል እንድገባላት በነሱ ፊት ጠየቀችኝ ለሶስት ሲያዋክቡኝ ግራ ገባኝ !
ደስ ባይለኝም ያቀደችልኝን ቀድሜ መረዳት አልችልም ነበርና ቃል ገባሁ።
ፈተናው ሊያልቅ አንድ ቀን ሲቀረው ጨነቀኝ
ዛሬ ጥዋት ስድስት ሰአት አከባቢ እነሱ ፈተናው በማለቁ ደስ ሲላቸው እኔን ግን ፍርሀት ፍርሀት አለኝ •••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
"ስላባዬ ሳወራ ጨነቀኝ !
ትንሽ ዝምታ ተፈጠረ በመሀላችን።
ሲጨንቀኝ ደሞ ምን ትዝ እንዳለኝ ታውቃለህ?"
ምን ትዝ አለሽ ?
አንዴ ልጩህ እሚለው የቅድሙ ሰካራም ።
አንዴ ልጩህ እንዴ?"
ስትለኝ ሁለታችንም ባንድ ግዜ ከነበርንበት ሙድ ወጥተን ከባጃጇ ጣራ በላይ ሳቅን።
በናትሽ ቀጥይልኝ ? አልኳት ሳቄን ስጨርስ። ካሳቁ መልስ ደሞ ባንዴ ፊቷን ቅጭም አርጋ ቀጠለች•••
አባዬ ድካሙና እንቅልፉ ተደራርቦበት ነበር ።
ልመጣ ሁለት ሳምንት ሲቀረኝ •••
••••
ልመጣ ሁለት ሳምንት ሲቀረኝ በሂወቴ እማረሳው መጥፎ አጋጣሚ ተፈጠረ ቀኑ አርብ ነበር አባዬ እንደተለመደው በለሊት ነበር ወደ ስራ የወጣው
ያን ሰሞን የሚሰራበት ቦታ ከኛ ቤት ብዙ ስለማይርቅ እንደነገ ልጀምር ማታ እማዬን በጥዋት እየተነሳሽ ምሳ አትቋጥሪልኝ ቀስ ብለሽ ስሪና አለሜ ታምጣልኝ አላት ስሜ ኤደን ቢሆንም አባ ግን አለሜ የኔአለም እያለ ነው እሚጠራኝ።
ለአራት ቀናት ምሳውን ስራ ቦታ እየወሰድኩለት እስኪበላ እያዋራሁት እምለሳለሁ በአምስተኛው ቀን ጓደኛዬ አርብ እለት ከማዬ ጋር ልብስ ይዥበት የምመጣውን ቦርሳ ለመግዛት አብረን ወጥተን ስለነበር ምሳውን ሳላደርስለት ሰአቱ ሄደብኝ በውስጡ ልጄን ምን አጋጠማት እያለ ሲጨነቅ ነበር ለካ ከቀኑ ሰባት ሰአት ተኩል ላይ ምሳውን ይዤ ከቤት ወጣሁ ከ15 ደቂቃ ቡሀላ ደረስኩ።
ቀና ስል•••
አባዬ በግምት ከመሬት አምስት ሜትር ከፍታ ላይ ተሰቅሎ ስራውን እየሰራ ነው አባ ብዬ ጮክ ብዬ ስጣራ ስቆይበት ጭንቀት ላይ የነበረው አባዬ የኔን የልጁን ድምፅ ድንገት ሲሰማ ደነገጠ መስለኝ ሳይጠነቀቅ እኔን ለማየት የያዘውን ለቆ ዞረ!
ወድያው ከላይ ቁልቁል ሲምዘገዘግ አይኔን ማመን ተሳነኝ በሂወቴ እንደዛን ቀን ደንግጬ አላውቅም ውሃ ሆንኩ ወደ ወደቀው አባቴ መጠጋት ፈርቼ በቆምኩበት ስጮህ ባከባቢው የነበሩ ሰራተኛች ከወደቀበት አንስተው አናቱ ላይ ውሀ ሲያፈሱበት ተመለከትኩ
ተርፏል አባቴ !
ተርፏል አባቴ !
እያልኩ ወደሱ በመሮጥ እያለቀስኩ አንገቱ ላይ ተጠመጠምኩበት።
እግሩና የጎን አጥንቱ ላይ ጉዳት ደረሰበት ያን ቀን አሰሪው ሀኪም ቤት ወስዶ ህክምና ተደረገለት ከዛን ቀን ቡሀላ ግን ዘወር ብሎም አላየውም
ከ አምስት ቀን ቡሀላ እኔ ጋር ያለው ለዩንቨርስቲ ጉዞዬ ብሎ ያጠራቀመው ገንዘብ ለሱ ህክምና እንዳልጠቀምበት ብሎ ሳይሻለው ተሽሎኛል ብሎ ከሀኪም ቤት ወጣና እቤታችን ተኛ
ለሊት ለሊት ሲያቃስት ስለሰማሁት አባ እሺ በለኝ እና በደንብ ታከም እኔ ጋር ባለው ብር ታክመህ ካልዳንክ ወደ ዩንቨርስቲ እንደማልሄድ እወቀው ስለው እሺ አለኝ።
አሳክሜው የተረፈችኝን ይዤ መጣሁ እዚህ ከመጣሁ አራት ወር ሊሞላኝ ነው ግን እስካሁን ስራ አልጀመረም እማዬ በምትሰራው ብቻ ስለሚኖሩ እማን ላለማጨናነቅ ብዬ ምንም ወጪ የለብኝም ብር እንዳትልኪልኝ አልኳት
እዚህ ደግሞ ብዙ ወጭዎች አሉ ኖቶችን(ሀንድ አውቶችን) ኮፒ ከማረግ ጀምሮ ብዙ ነገሮች አሉ በተለይ ሴት ልጅ ከወንድ ልጅ በባሰ ሁኔታ እጇ ላይ ሳንቲም ያስፈልጋታል ሁሉንም ፍላጎቷን ማስቀረት ብትችል የሞድየስን እና የአንዳንድ ነገር ወጪዎቿ ግድ ናቸው።
በዚህ ግቢ ማደሪያ ክፍላችን (ዶርም) ውስጥ በጣም የምቀርባቸው ሁለት ጓደኛች አሉኝ የመጣን ሰሞን ስለሂወታችን ስናወራ የሶስታችንም ቤተሰቦቻች በተቀራራቢ የድህነት ህይወት ውስጥ ያሉ እድሚያችን ፣አለባበሳችን፣ ፍላጎታችን ፣ ችግራችን ባጠቃላይ በተመሳሳይ ህይወት ውስጥ ማለፋችን ነው መሰል ቶሎ ለመቀራረብና እንደህታማቾች ለመተሳሰብ እና ለመተዛዘን ግዜ አልፈጀብንም።
እማንለያይ አንዳችን ላንዳችን የምንጨነቅ ሆንን ከቅባት ጀምሮ የሚያስፈልጉንን አዋጥተን እንገዛለን አንዳችን ያንዳችንን ልብስ ለመልበስ ፍቃድ መጠየቅ አያስፈልገንም የነሱን ባላውቅም እኔ ሁለቱንም በጣም ነው እምወዳቸው ።
ትንሽ እንደቆየን በተለይ አንዲት የሶስተኛ አመት ተማሪ ባጋጣሚ ከአንደኛዋ ጋደኛዬ ጋር ተዋውቋ ዶርማችን መጥታ ከተዋወቀችንና በየቀኑ መምጣት ከጀመረች ቡሀላ ነገሮች በፍጥነት መቀያየር ጀመሩ።
እኔ ልጅቷ የምታወራው ነገር ሁሉ ስለማይጥመኝ ብዙም አልቀርባትም ነበር ።
ከሁለቱ ጋር ግን በጣም ተቀራረበች ጭራሽ ከግቢ ውጪ አምሽተው አንዳንዴም አድረው መምጣት ጀመሩ የት ሄዳችሁ ነው? ስላቸው ከሷ ጋር እንደነበሩ ይነግሩኛል የጓደኝነቴን ትምህርታቸው ላይ እንዱያተኩሩና ከሷ ልጅ ጋር መዞሩን እንዲቀንሱ ብነግራቸውም ጭራሽ ባሰባቸው ። እንደውም እኔም አብሬያቸው ዘና እንድል በተለያየ መንገድ ሊያሳምኑኝ ይሞክሩ ጀመር።
በተዋወቋት ባጭር ግዜ ውስጥ እኔ ለፎቶ ኮፒ ተቸግሬ ፍዳዬን ሳይ እነሱ ልብስና ጫማ በየሳምንቱ መቀያየር ጀመሩ ከኔ ጋር ያላቸው ልዩነት እየሰፋ እየሰፋ መጣ የነበሩት ነገሮች በሙሉ ተለዋወጡ እንኳን ከኔ ጋር ቅባት አዋጥተው ሊገዙ እንኳን ከኔ ጋር ልብስ ሊቀያየሩ የበፊቶቹን ልብሶቻቸውን ከፈለኩ መውሰድ እንደምችል ይነግሩኝ ጀመር።
ቅባት ሻንፖ ሎሽን የመሳሰሉትን ነገሮች ገዝተው ሲሰጡኝና እና ለፎቶ ኮፒ የሚሆነኝን ገንዘብ ስፈልግ እንድጠይቃቸው ሲነግሩኝ ከምልህ በላይ ይሰማኝ ጀመር በቃ በፊት ተሰምቶኝ የማያውቅ የበታችነት ስሜት ተረጋግቼ ማጥናት እስክቸገር ድረስ መጥፎ ሁኔታ ውስጥ ከተተኝ።
በዛ ሁኔታ ውስጥ ሆኜ ደግሞ ያቺ ጓደኛቸው እና እነሱ እነሱን እንድመስል አብሬያቸው እንድውል እና እንዳመሽ ባገኙት አጋጣሚ ይወተውኛል ።
በቅርቡ የመጀመሪያው ሴሚስተር ፈተና ነበርና በየትምህርት አይነቱ ያሉትን ኖቶች ኮፒ ለማድረግ በጣም ሳንቲም ያስፈልገኝ ነበር።
ያቺ ጓደኛቸው ያዘነች መስላ ያንን ወጪ በነሱ በኩል
በመሸፈን በውለታ ከያዘችኝ ቡኋላ
ዶርም መጥታ ፈተና ስንጨርስ አብሬያቸው ወጣ ብዬ ለመዝናናት ፍቃደኛ እንድሆንና ቃል እንድገባላት በነሱ ፊት ጠየቀችኝ ለሶስት ሲያዋክቡኝ ግራ ገባኝ !
ደስ ባይለኝም ያቀደችልኝን ቀድሜ መረዳት አልችልም ነበርና ቃል ገባሁ።
ፈተናው ሊያልቅ አንድ ቀን ሲቀረው ጨነቀኝ
ዛሬ ጥዋት ስድስት ሰአት አከባቢ እነሱ ፈተናው በማለቁ ደስ ሲላቸው እኔን ግን ፍርሀት ፍርሀት አለኝ •••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍2
#ልጩህበት !!
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
እያዋከበ ይዞኝ ከወጣ ቡሀላ
" እዛጋ ባጃጅ ታገኛለሽ ቆይ ትንሽ ላስጠጋሽ" እያለ ቁልቁል ወረድን ። እሱ እሄን ሁሉ ሲያወራ ስለደነገጥኩ ነው መሰለኝ ትንፍሽ አላልኩም በቃ ተመለስ ብዬው ቆም እንዳልን ከጀርባው ከሆቴሉ እየተምዘገዘገ የሚመጣውን ሰው ተመለከትኩና
በቆምኩበት በድን ሆንኩ ሁኔታዬ ግራ ገብቶት ሲያፈጥብኝ በጄ ወደሚመጣው ሰው እያመለከትኩ እንደምንም
ወይኔ ተከትለውን መጡ መሰለኝ አልኩት ደንግጦ ዞረ •••
•••
ወድያው መጀመሪያ እየሮጠ የወጣውን የሚያባርሩ ሁለት ወጣቶች ከጀርባው ተከታትለው ወጣ
"እንዴ የሚያባርሩት እኮ ጀለሶቼ ናቸው ምን ተፈጥሮ ነው ? ምን አርጓቸው ነው ?" አለና ድንጋይ አንስቶ ከፊት ጠበቀው።
በናትህ ተው አትጣላ አልኩት በጭንቀት።
ልጁ ግን ገና እኛ ጋር ሳይደርስ ድንገት ወደ ግራ ተኮሩቦ እግሬ አውጪኝ አለ።
ልጁ ድንገት ስልብ ያለባቸው ጓደኛቹ
"ወዴት ሄደ ?
በየቱጋ ነው የሄደው? እያሉ ልጁ በሄደባት ቀጭን እና ጨለማዋ መንገድ ሊገቡ ሲሉ
ቆይ ቆይ ወደጨለማው አትግቡ ! ቆይ ምን አድርጓችሁ ነው ? ምን ተፈጠረ ? ማነው ልጁ? አላቸው ከኔ ጋር የነበረው ልጅ ።
ሁለቱም ቁና ቁና እየተነፈሱ እኩል ማውራት ጀመሩ
••• "ያ ነዋ ጥግ ላይ ብቻውን ደቅ ብሎ ሲቀመቅም የነበረው
እንዴ እኛ የፌኩን ድብድብ ስናጧጥፈው
ማለት ብሩኬ እና እሱ ሲደባደቡ እኔ ደግሞ እማገላግል መስዬ መሀል ላይ ስወክብልሽ ድብድብ ሲያይ ዛሩ ተነስቶበት እንደቀልብ አረገው መሰለኝ ዝም ብሎ ብቻ የሚጠጣውን ቢራ አንስቶ እየተንደረደረ በመምጣት ብሩኬ አናት ላይ አያፈነዳውም ሲል የደነገጥኩት መደንገጥ !
ተጎድቷል እና እሱን እዛ ጥላችሁት መቺውን ለማባረር ሁለታችሁም ትወጣላችሁ መጠጡ ገብቶላችቹሀል ማለት ነው ቻው እሺ እህቴ በቃ ሂጅ አንቺ አለኝና ሶስቱም ተያይዘው ወደ ጭፈራው ቤት እሮጡ
ይህ ሁሉ ነገር በኔ ምክንያት መሆኑን ሳስበው ተሸማቅቄ ጤፍ አከልኩልህ በቆምኩበት እስኪገቡ ድረስ አያየሁዋቸው ጓደኛቸው የከፋ ጉዳት እንዳይደርስበት ተመኘሁ።
አምስት ሳንቲም እጄ ላይ እንደሌለ ትዝ ያለኝ ከሩቁ የምትመጣ ባጃጅ እንዳየሁ ነበር ግራ ገባኝ በግር አልመጣ ነገር ሰአቱም እርቀቱም የማይሆን ሆነብኝ ጨነቀኝ!
ለዛች አውሬ ጥለውኝ የሄዱትን ጓደኛቼን በጣም ብናደድባቸውና እና ብጠላቸውም አማራጭ አልነበረኝምና የመሳፈሪያ ብር ልቀበላቸው ሞባይል እናምጣ ብለው ወደሄዱበት መጀመሪያ ወደነበርንበት ሆቴል ሄድኩ ስደርስ ሆቴሉ ጢም ብሏል መግባት ፈራሁ እዛው ግንብ አጥሩን ተደግፌ እንደቆምኩ ያንተ ባጃጅ መጥታ ቆመች ።
ወድያው ደግሞ አንድ ሰካራም በስልክ እየተጨቃጨቀ ከሆቴሉ ወጣና ከፊት ለፊቴ ቆሞ ያወራ ጀመር አብዛኛው ንግግሩ ስድብ ነበር ቀጥራው የቀረችበትን ሴት መሰለኝ እሚሰድበው።
እንደጨረሰ ወደኔ ዘወር አለልህና
" ውይ ውይ ውይ ውይ ውይ ውይ የኔ ቆንጆ ምነው ብቻሽን እኔንም ወንድ ቀጥሮ አስደግፎኝ ነው እንዳትይኝ ብቻ በእውነት አላምንሽም ነገሩ ተይው ባለጌ ባለጌ ነው !
ሳይደግስ አይጣላም ትል ነበር አያቴ አሁን በስልክ ስሰድባት የነበረችው ልጅ እኮ እኔንም ቀጥራ አስደግፋኝ ነው ኧረ እንኳንም ቀረች የሆነች አስቀያሚ ነገር ነችኮ ሳስበው ሳስበው ግን የኔዋም ያንቺውም እዚሁ ቀጥረውን የቀሩት አብረው ሆነው ሳይሆን አይቀርም ኧረ ነው
እሄው እኔና አንቺን አገናኝቶ የጃቸውን ሰጣቸዎ
"አንተ የሰው ስታጫውት ያንተን እሚያጫውት ይልክልሀል "ትል ነበር አያቴ ኖኖኖ አጎቴ " አለና ጠጋ ብሎ "በይ ነይ እንግባ" አይለኝም አልገባም ስለው እጄን ሊይዘኝ ሲል መንጭቄው ቀጥ ብዬ ወዳንተ ባጃጅ መጣሁ"
ብላ ታሪኩን ስትቋጭልኝ ልጁን ምክንያት አድርጎ ያተረፋትን ፈጣሪን አመሰገንኩ
ልጁ ባያተርፋት ምን ሊፈጠር ይችል እንደነበር ሳስበው ድብልቅልቅ ያለ ስሜት ተሰማኝ ምናልባትም ያ የምትጠጣው ቢራ ውስጥ የከተተችባት ነገር እራሷን እንድትስት የሚያደርግ ነገር ሊሆን ይችላል ከሽንት ቤት እንደተመለሰች ቢራውን ጠጥታ እራሷን ስትስትና "
አይዞሽ ምን ሆነሽ ነው አመመሽ እንዴ እያለች ደግፋ ሰውየው ወደያዘው አልጋ ክፍል አስገብታለት ትሄዳለች አበቃ ።
ወደራሷ ስትመለስ አልያም ጥዋት ስትነሷ የሚሰማትን ስሜት መገመት ይከብዳል ከዛ ቡሀላ ያለውን ሂወቷን ማሰብ ያሳምማል
እሱ ለሳሏት የአንድ ለሊት ደስታ ለሆነችው ትንሽ ስእል የሷን የሂወት ግብ የሆነውን ትልቁን ስእል ሲያጠፋባት ያድራል!
ኤዱዬ ፈጣሪሽን አመስግኝው አየሽ ክፉዎች የሚመጡበት መንገድ የተለያየ ነው አንዳንድ ክፉዎች የክፋት መርዛቸውን በቀጥታ ሊያበሉን ይሞክራሉ በጣም የከፉት ክፉዎች ግን የክፋት መርዛቸውን በስኳር ለውሰው ሊያበሉን የሚሞክሩት ናቸው
አንዱ መንገዳቸው ለኛ ያዘኑ ወይም ጥሩ መስለው በመቅረብ ሲሆን ሌላው መንገዳቸው ደግሞ በደካማ ጎናችን በመግባት በውለታ ጠፍረው በዩልኝታ ተይዘን ወደ ቆፈሩልን ገደል እንድንገባላቸው የሚገፋፉን ናቸው ታድያ ያኔ የፈለገ ውለታ የዋለልን ሰው ቢሆን በማንፈልገው መስመር እንድንጓዝ ሲገፋፋን ያደረገልንን ነገር ሳይሆን ባደረገልን ነገር ምክንያት እየተጫነን መሆኑን አስበን ምንም ሳያደርግልን በዛ ሁኔታ ውስጥ እንድናልፍ ከሚጠይቀን ሰው የበለጠ ሊያናድድን ሲገባ ውለታውን እያሰብን በጭራሽ ገደል መግባት የለብንም ለፎቶ ኮፒ ገንዘብ ስለሰጠችሽ ማድረግም መሆንም ወደማትፈልጊው መንገድ እንድትገቢላት ቃል ስታስገባሽ እሺ ማለት አልነበረብሽም እያልኩሽ ነው
ከቤተሰቦችሽ ጀምሮ ያለውን ሁኔታ በግልፅ ስለነገርሽኝ አመሰግናለሁ
ካሁን ቡሀላ እኔም ተቀጥሬ የምሰራ ካንቺ ቤተሰብ ቡዙ የማይርቅ የኑሮ ሁኔታ ውስጥ ያደኩኝ ቢሆንም በዚህ ሰአት ቢያንስ ካንቺ እሻላለሁና በትምህርት ሂወትሽ የሚያስፈልጉሽን ማለት ከትምህርትሽ ጋር ተያያዥ የሆኑ ወጪዎች እኔ ብሸፍንልሽ ደስ ይለኛል
የሚያስፈልግሽን በግልፅ ልትጠይቂኝ ፍቃደኛ ነሽ ኤዱ ስላት
አይኖቿ እምባ አቀረሩ። መልስ ሳትሰጠኝ አቀረቀረች •••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
እያዋከበ ይዞኝ ከወጣ ቡሀላ
" እዛጋ ባጃጅ ታገኛለሽ ቆይ ትንሽ ላስጠጋሽ" እያለ ቁልቁል ወረድን ። እሱ እሄን ሁሉ ሲያወራ ስለደነገጥኩ ነው መሰለኝ ትንፍሽ አላልኩም በቃ ተመለስ ብዬው ቆም እንዳልን ከጀርባው ከሆቴሉ እየተምዘገዘገ የሚመጣውን ሰው ተመለከትኩና
በቆምኩበት በድን ሆንኩ ሁኔታዬ ግራ ገብቶት ሲያፈጥብኝ በጄ ወደሚመጣው ሰው እያመለከትኩ እንደምንም
ወይኔ ተከትለውን መጡ መሰለኝ አልኩት ደንግጦ ዞረ •••
•••
ወድያው መጀመሪያ እየሮጠ የወጣውን የሚያባርሩ ሁለት ወጣቶች ከጀርባው ተከታትለው ወጣ
"እንዴ የሚያባርሩት እኮ ጀለሶቼ ናቸው ምን ተፈጥሮ ነው ? ምን አርጓቸው ነው ?" አለና ድንጋይ አንስቶ ከፊት ጠበቀው።
በናትህ ተው አትጣላ አልኩት በጭንቀት።
ልጁ ግን ገና እኛ ጋር ሳይደርስ ድንገት ወደ ግራ ተኮሩቦ እግሬ አውጪኝ አለ።
ልጁ ድንገት ስልብ ያለባቸው ጓደኛቹ
"ወዴት ሄደ ?
በየቱጋ ነው የሄደው? እያሉ ልጁ በሄደባት ቀጭን እና ጨለማዋ መንገድ ሊገቡ ሲሉ
ቆይ ቆይ ወደጨለማው አትግቡ ! ቆይ ምን አድርጓችሁ ነው ? ምን ተፈጠረ ? ማነው ልጁ? አላቸው ከኔ ጋር የነበረው ልጅ ።
ሁለቱም ቁና ቁና እየተነፈሱ እኩል ማውራት ጀመሩ
••• "ያ ነዋ ጥግ ላይ ብቻውን ደቅ ብሎ ሲቀመቅም የነበረው
እንዴ እኛ የፌኩን ድብድብ ስናጧጥፈው
ማለት ብሩኬ እና እሱ ሲደባደቡ እኔ ደግሞ እማገላግል መስዬ መሀል ላይ ስወክብልሽ ድብድብ ሲያይ ዛሩ ተነስቶበት እንደቀልብ አረገው መሰለኝ ዝም ብሎ ብቻ የሚጠጣውን ቢራ አንስቶ እየተንደረደረ በመምጣት ብሩኬ አናት ላይ አያፈነዳውም ሲል የደነገጥኩት መደንገጥ !
ተጎድቷል እና እሱን እዛ ጥላችሁት መቺውን ለማባረር ሁለታችሁም ትወጣላችሁ መጠጡ ገብቶላችቹሀል ማለት ነው ቻው እሺ እህቴ በቃ ሂጅ አንቺ አለኝና ሶስቱም ተያይዘው ወደ ጭፈራው ቤት እሮጡ
ይህ ሁሉ ነገር በኔ ምክንያት መሆኑን ሳስበው ተሸማቅቄ ጤፍ አከልኩልህ በቆምኩበት እስኪገቡ ድረስ አያየሁዋቸው ጓደኛቸው የከፋ ጉዳት እንዳይደርስበት ተመኘሁ።
አምስት ሳንቲም እጄ ላይ እንደሌለ ትዝ ያለኝ ከሩቁ የምትመጣ ባጃጅ እንዳየሁ ነበር ግራ ገባኝ በግር አልመጣ ነገር ሰአቱም እርቀቱም የማይሆን ሆነብኝ ጨነቀኝ!
ለዛች አውሬ ጥለውኝ የሄዱትን ጓደኛቼን በጣም ብናደድባቸውና እና ብጠላቸውም አማራጭ አልነበረኝምና የመሳፈሪያ ብር ልቀበላቸው ሞባይል እናምጣ ብለው ወደሄዱበት መጀመሪያ ወደነበርንበት ሆቴል ሄድኩ ስደርስ ሆቴሉ ጢም ብሏል መግባት ፈራሁ እዛው ግንብ አጥሩን ተደግፌ እንደቆምኩ ያንተ ባጃጅ መጥታ ቆመች ።
ወድያው ደግሞ አንድ ሰካራም በስልክ እየተጨቃጨቀ ከሆቴሉ ወጣና ከፊት ለፊቴ ቆሞ ያወራ ጀመር አብዛኛው ንግግሩ ስድብ ነበር ቀጥራው የቀረችበትን ሴት መሰለኝ እሚሰድበው።
እንደጨረሰ ወደኔ ዘወር አለልህና
" ውይ ውይ ውይ ውይ ውይ ውይ የኔ ቆንጆ ምነው ብቻሽን እኔንም ወንድ ቀጥሮ አስደግፎኝ ነው እንዳትይኝ ብቻ በእውነት አላምንሽም ነገሩ ተይው ባለጌ ባለጌ ነው !
ሳይደግስ አይጣላም ትል ነበር አያቴ አሁን በስልክ ስሰድባት የነበረችው ልጅ እኮ እኔንም ቀጥራ አስደግፋኝ ነው ኧረ እንኳንም ቀረች የሆነች አስቀያሚ ነገር ነችኮ ሳስበው ሳስበው ግን የኔዋም ያንቺውም እዚሁ ቀጥረውን የቀሩት አብረው ሆነው ሳይሆን አይቀርም ኧረ ነው
እሄው እኔና አንቺን አገናኝቶ የጃቸውን ሰጣቸዎ
"አንተ የሰው ስታጫውት ያንተን እሚያጫውት ይልክልሀል "ትል ነበር አያቴ ኖኖኖ አጎቴ " አለና ጠጋ ብሎ "በይ ነይ እንግባ" አይለኝም አልገባም ስለው እጄን ሊይዘኝ ሲል መንጭቄው ቀጥ ብዬ ወዳንተ ባጃጅ መጣሁ"
ብላ ታሪኩን ስትቋጭልኝ ልጁን ምክንያት አድርጎ ያተረፋትን ፈጣሪን አመሰገንኩ
ልጁ ባያተርፋት ምን ሊፈጠር ይችል እንደነበር ሳስበው ድብልቅልቅ ያለ ስሜት ተሰማኝ ምናልባትም ያ የምትጠጣው ቢራ ውስጥ የከተተችባት ነገር እራሷን እንድትስት የሚያደርግ ነገር ሊሆን ይችላል ከሽንት ቤት እንደተመለሰች ቢራውን ጠጥታ እራሷን ስትስትና "
አይዞሽ ምን ሆነሽ ነው አመመሽ እንዴ እያለች ደግፋ ሰውየው ወደያዘው አልጋ ክፍል አስገብታለት ትሄዳለች አበቃ ።
ወደራሷ ስትመለስ አልያም ጥዋት ስትነሷ የሚሰማትን ስሜት መገመት ይከብዳል ከዛ ቡሀላ ያለውን ሂወቷን ማሰብ ያሳምማል
እሱ ለሳሏት የአንድ ለሊት ደስታ ለሆነችው ትንሽ ስእል የሷን የሂወት ግብ የሆነውን ትልቁን ስእል ሲያጠፋባት ያድራል!
ኤዱዬ ፈጣሪሽን አመስግኝው አየሽ ክፉዎች የሚመጡበት መንገድ የተለያየ ነው አንዳንድ ክፉዎች የክፋት መርዛቸውን በቀጥታ ሊያበሉን ይሞክራሉ በጣም የከፉት ክፉዎች ግን የክፋት መርዛቸውን በስኳር ለውሰው ሊያበሉን የሚሞክሩት ናቸው
አንዱ መንገዳቸው ለኛ ያዘኑ ወይም ጥሩ መስለው በመቅረብ ሲሆን ሌላው መንገዳቸው ደግሞ በደካማ ጎናችን በመግባት በውለታ ጠፍረው በዩልኝታ ተይዘን ወደ ቆፈሩልን ገደል እንድንገባላቸው የሚገፋፉን ናቸው ታድያ ያኔ የፈለገ ውለታ የዋለልን ሰው ቢሆን በማንፈልገው መስመር እንድንጓዝ ሲገፋፋን ያደረገልንን ነገር ሳይሆን ባደረገልን ነገር ምክንያት እየተጫነን መሆኑን አስበን ምንም ሳያደርግልን በዛ ሁኔታ ውስጥ እንድናልፍ ከሚጠይቀን ሰው የበለጠ ሊያናድድን ሲገባ ውለታውን እያሰብን በጭራሽ ገደል መግባት የለብንም ለፎቶ ኮፒ ገንዘብ ስለሰጠችሽ ማድረግም መሆንም ወደማትፈልጊው መንገድ እንድትገቢላት ቃል ስታስገባሽ እሺ ማለት አልነበረብሽም እያልኩሽ ነው
ከቤተሰቦችሽ ጀምሮ ያለውን ሁኔታ በግልፅ ስለነገርሽኝ አመሰግናለሁ
ካሁን ቡሀላ እኔም ተቀጥሬ የምሰራ ካንቺ ቤተሰብ ቡዙ የማይርቅ የኑሮ ሁኔታ ውስጥ ያደኩኝ ቢሆንም በዚህ ሰአት ቢያንስ ካንቺ እሻላለሁና በትምህርት ሂወትሽ የሚያስፈልጉሽን ማለት ከትምህርትሽ ጋር ተያያዥ የሆኑ ወጪዎች እኔ ብሸፍንልሽ ደስ ይለኛል
የሚያስፈልግሽን በግልፅ ልትጠይቂኝ ፍቃደኛ ነሽ ኤዱ ስላት
አይኖቿ እምባ አቀረሩ። መልስ ሳትሰጠኝ አቀረቀረች •••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍1
#ልጩህበት !!
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ከቤተሰቦችሽ ጀምሮ ያለውን ሁኔታ በግልፅ ስለነገርሽኝ አመሰግናለሁ
ካሁን ቡሀላ እኔም ተቀጥሬ የምሰራ ካንቺ ቤተሰብ ቡዙ የማይርቅ የኑሮ ሁኔታ ውስጥ ያደኩኝ ቢሆንም በዚህ ሰአት ቢያንስ ካንቺ እሻላለሁና በትምህርት ሂወትሽ የሚያስፈልጉሽን ማለት ከትምህርትሽ ጋር ተያያዥ የሆኑ ወጪዎች እኔ ብሸፍንልሽ ደስ ይለኛል
የሚያስፈልግሽን በግልፅ ልትጠይቂኝ ፍቃደኛ ነሽ ኤዱ ስላት
አይኖቿ እምባ አቀረሩ። መልስ ሳትሰጠኝ አቀረቀረች ••
•••
ምነው ?ስላት•••
"አይ ምንም እንዲሁ ገርሞኝ ነው!"
ምኑ?
"እኔና አንተ በብዙ ኪሎ ሜትር ተራርቀን የኖርን ነን አታውቀኝም አላውቅህም አደረከውም አላደረከውም ግን እንዲህ ስትለኝ ከሚያስፈልጋቸው በላይ እያላቸው የጓዳችንን ችግር እያዩ የቅርብ እሩቅ ሆነው ህመማችን የማያማቸው ችግራችን ያራቃቸውን በደና ኑሮ ውስጥ ያሉ የናቴንም ያባቴንም ዘመዶች አስታወስከኝ እማዬ በጣም የዋህ ነች ምንም ባያደርጉላትም ካለቻት ላይ ቀንሳ የሆነ ነገር ገዝታ ሄዳ ትጠይቃቸዋለች እነሱ እሚጠያየቁትም እሚረዳዱትም በንሮ ከሚመስሏቸው ሌሎች ዘመዶቻችን ጋር ነበር።
እያደኩ እና እሄን እያስተዋልኩ ስመጣ እማዬ "ልጠይቃቸው ልሄድ ነው "ስትለኝ በሷ እራሱ መናደድና ባትሄድ ደስ እንደሚለኝ ፊት ለፊት መናገር ጀመርኩ።
እሷ ግን
"ተይ ልጄ ክፉ መስለውሽ እንጂ ክፉ አደሉም ቢሆኑም ደግሞ ሰው ክፉ ሆነ ተብሎ ክፉ አይኮንም ፈጣሪ ሁሉንም እንደየስራው ይስጠው እኔ ግን ሄጄ ሰላም መሆናቸውን አይቼ መምጣት እረፍት ይሰጠኛል እና መጠየቄን አላቋርጥም" ነበር የሁልግዜ መልሷ።
ቢሆንም ግን •••
ከልጅነቴ ጀምሮ አባዬ እና እማዬ ሲከፋቸው በነሱ ሲበሳጩ እኔን በማይገባኝ መንገድ የውስጣቸውን ቁስል እርስ በርስ ለማውራት ሲሞክሩ እኔ በደንብ ይገባኝ ነበር በዛ ምክንያት ዘመዶቻችንን አልወዳቸውም።
እንደውም ስለነሱ ሳስብ ሰው ሁሉ ክፉ ነበር የሚመስለኝ ነገር ግን •••
ለሰው ችግር ደርሰው ሰው በነሱ ደስ ሲለው ሲያዩ በደስታ አለም የምትሞቃቸው ሰው አዝኖ ሲመለከቱ አለም የምትጨልምባቸው ደጋግ ጎሮቤቶቻችን ከክፍ ሰዎች ይልቅ ደግ ሰዎች በቁጥር እንደሚበልጡ አስተማሩኝ ሁሌም በመንገዴ በማላውቃቸው መሀል እንኳን ብገኝ ካሉት ውስጥ እኔን ከሚጎዳኝ ይልቅ እኔን የሚወደኝ እና ከጉዳት የሚታደገኝ ሰው ቁጥሩ የበዛ እንደሆነ እንዳምንና እንዳልፈራ ያደረጉኝ እነዛ ደጋግ የማዬ ጎረቤቶች ናቸው ።
ዛሬ አንተ እንዲህ ስትለኝ እነሱ ትዝ አሉኝና እምባ ተናነቀኝ !!" አለችኝ ።
ቅድም ህይወቷንና ያጋጠማትን ነገር ስትነግረኝ ከተሰማኝ ሀዘን በላይ ይህ ንግግሯ ውስጤን ሲፈነቃቅለው ተሰማኝ ።
ከዛ ሁኔታ ውስጥ ቶሎ መውጣት ፈለኩ••
ሰአቴን አየት አደረኩና ከለሊቱ ሰባት ሰአት ተኩል ሊሆን ነው ኤዱ በቃ በዚህ ሰአት ወደ ግቢ መግባቱ ጥሩ አይመስለኝም
ችግር እንኳን ባያጋጥምሽ የሆነ የሚያውቅሽ ሰው ባጋጣሚ በዚህ ሰአት ስትገቢ ቢያይሽ ስላንቺ ያለው አመለካከት ጥሩ ካለመሆኑም በላይ ነገ ባየሽ ቁጥር አጠገቡ ላሉት እቺ ልጅ እኩለ ለሊት ከደጅ ስትገባ አየሁዋት እያለ ስምሽን ሊያጠፋው ባጠቃላይ በዚህ ሰአት መግባቱ በተለይ ለሴት ሌላ ስም ነው እሚያሰጣት የነበርሽበትን ሁኔታ ማንም አይረዳም ስላት ትከሻዋን ሰበቀችው
"ታድያ ምን ላድርግ " ይመስላል የሰበቃው ትርጉም።
ለምን አልጋ ይዘሽ አታድሪምና ጥዋት አትገቢም?
"አይ ልግባ ባክህ አንተንም ከዚህ በላይ ላስቸግርህ አልፈልግም !"ስትለኝ በግድ አሳመንኳትና አልጋ ፍለጋ ወደ ከተማ ተመለስን
ትንሽ መንገድ በፀጥታ እንደተጓዝን ዝም ስትል እንደፈራች ስለገባኝ እኔ ማውራት ጀመርኩ
ቅድም ስለአንቺ ስለጓደኛችሽ እና ስለዛች ልጅ ስለ መሲ ስታወሪልኝ አንድ ጓደኛዬ ከአመት በፊት ያወርልኝ ነገር ነው ትዝ ያለኝ
"ምን አውርቶልህ ነበር እኔ ካወራሁልህ ጋር የሚመሳሰል ነው?"
ልጁ ቀደም ብሎ ነው በባጃጅ ሹፍርና ስራ የጀመረው አንድ ቀን ካፍቴርያ ቁጭ ብለን ማኪያቶ እየጠጣን •••
የሆነ ሰው እኛ ወዳለንበት ካፌ ገባና ከኛ ራቅ ብሎ ፊት ለፊት ተቀመጠ
"እሄን ሰውዬ ታውቀዋለህ ?አለኝ
ኧረ አላውቀውም ስለው
"እስቲ በደንብ እየው"
በደንብ አየሁት ደነገጥኩ ሰውየውን አፈር አይኳኝ ሲል አውቀዋለሁ
አዎ አንተ አውቀዋለሁ ምን ሆኖ ነው እንደዚህ አይጥ የበላው እስፖንጅ የመሰለው ደሞ በጣም ከስቷል ጆከሩን ስቦ ነው እንዴ ? ስለው
"እኔ በቀላሉ እምታገኘው ብር አንተንም አቅልሎህ እንደሚሄድ ያረጋገጥኩት በዚህ ሰውዬ ነው " ሲለኝ እንዴት? አልኩት
በቃ በቀላሉ ስታገኝ በቀላሉ ታጠፋዋለህ እሱ ደግሞ ብቻውን አይጠፋም አጥፍቶ ጠፉ በለው
ማለት ? አልኩት የተሸፋፈነውን ታሪክ ገላልጦ እንዲነግረኝ •••
"እሄውልህ ሰውየው ደሞዙ ትዝ አይለውም ከደሞዙ ብዙ እጅ በቀላሉ የሚያገኝባቸው ፕሮጀክቶች ነበሩት
ታድያ ብሩም በቀላሉ ይመጣል እሱም በቀላሉ ይረጨዋል ።
ብሩም ብቻውን አልተበተነማ እሱንም በትኖት ሄደ
እኔ በባጃጅ ስራ በደንብ አውቀዋለሁ።
በየቀኑ ጥዋት መጠጣት ይጀምራል ፣ከሰአት በርጫ ይቀመጣል፣ ማታ ጨብሲውን ይቀጥላል ፣
ያለ ስጋ አይበላም ፣አንዴ አብሯት የወጣውን ሴት አይደግምም ፣ በየቀኑ ከተለያዩ ሴቶች ጋር ያድራል እሄን ብር እያሳየ ስንት የግቢ ልጆች እንደቀጠፈ አትጠይቀኝ
እሄው አሁን ብሩ ሳያልቅ እሱን ጨረሰው ያለበትን በሽታ ከምነግርህ የሌለበትን ብጠራ ይቀለኛል
በስኳር ላይ ኮልስትሮል በክልስትሮል ላይ ደምብዛት በደምብዛቱ ላይ ኮብራውንም ሳይስበው አይቀርም
ታድያ ከ ብር በላይ አጥፍቶ ጠፊ የታለ? አታየውም እንዴ ማቆ ብሎኑ እንደላላ አልጋ እየተንቃቃ እኮ ነው እሚሄደው ! አለኝ ሰውየው ከዘራውን እየተደገፈ ተነስቶ ሲወጣ ።
አየሽ ኤዱ ፈጣሪ ሁሉንም ነገር በልኩ
እንድንጠቀም ነው የፈቀደልን በየቤቱ ሰው ኑሮ ከልክ ከልክ በታች እያኖረ ያሸዋል
ሰዎች ግን ሰው ከመርዳት ይልቅ ባገኙት ወይ ባላቸው ብር ከልክ በላይ ለመሆን ይሞክራሉ
ከልክ በላይ የሆነ ነገር ሁሉ ደግሞ ከበሽታ ወይ ከጭንቀት ያለፈ ነገር አያስገኝም እያልኳት እግረ መንገዴን በአይኔ ክፍት የሆነ ሆቴል እየፈለኩ ነበርና የምንሄደው አብዛኛዎቹ ዝግ በመሆናቸው መጀመሪያ ወደተገናኘንበት አከባቢ እየተቃረብን መጣን
"እንዴ ያገኘከኝ ቦታ ልትመልሰኝ ነው እንዴ አንተ ልጅ መሲ ይዘካት ና ብላህ ነው እንዴ?
እያለችኝ እየተሳሳቅን ጠጋ እንዳልን እዛ አከባቢ ካሉት ጭፈራ ቤቶች ከአንደኛው የፀብ የሚመስል ጫጫታ ከሩቅ ተሰማን እና
"ምንድን ነው? ፀብ ነው መሰለኝ እየተባባልን ጠጋ እንዳልን
ቀውጢ ሆኗል መስታወት ሲሰበር ጠርሙዝ ሲፈነዷ ሴቶች ሲጮሁ ይሰማል
እባክህ ብዙ አትጠጋ እያለችኝ ባጃጄን እያቀዘቀዝኩ በቀስታ ስጠጋ ከጭፈራ ቤቱ እየተሯሯጡ መውጣት ጀመሩ ከነዛ መሀል በደም የተጨማለቀችው ቀይ ረጅም ሴት የኤደን ጓደኛ መሆኗን ያወኩት ኤዱ
"ወይይይይይኔ ጉዴ ያቺ እኮ ጋደኛዬ ነች ብላ ስትጮህ ነበር ልብሷም ፊቷም ደም ለብሷል እጇን እያወራጨችና ደሟን ከአይኗ ላይ ለመጥረግ እየሞከረች እየተደነቃቀፈች ወጣችና አቅም አንሷት ወደቀች
የቷ!? አልኳት ደንግጬ ;
ያቺ ያቺ የወደቀችው እኮ ጋደኛዬ ረዱ ነች እያለች ከባጃጄ ላይ ተፈናጥራ በመውረድ ወደ ልጅቷ እያለቀሰች ስትሮጥ
እኔም ተከተልኳት••••••••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ከቤተሰቦችሽ ጀምሮ ያለውን ሁኔታ በግልፅ ስለነገርሽኝ አመሰግናለሁ
ካሁን ቡሀላ እኔም ተቀጥሬ የምሰራ ካንቺ ቤተሰብ ቡዙ የማይርቅ የኑሮ ሁኔታ ውስጥ ያደኩኝ ቢሆንም በዚህ ሰአት ቢያንስ ካንቺ እሻላለሁና በትምህርት ሂወትሽ የሚያስፈልጉሽን ማለት ከትምህርትሽ ጋር ተያያዥ የሆኑ ወጪዎች እኔ ብሸፍንልሽ ደስ ይለኛል
የሚያስፈልግሽን በግልፅ ልትጠይቂኝ ፍቃደኛ ነሽ ኤዱ ስላት
አይኖቿ እምባ አቀረሩ። መልስ ሳትሰጠኝ አቀረቀረች ••
•••
ምነው ?ስላት•••
"አይ ምንም እንዲሁ ገርሞኝ ነው!"
ምኑ?
"እኔና አንተ በብዙ ኪሎ ሜትር ተራርቀን የኖርን ነን አታውቀኝም አላውቅህም አደረከውም አላደረከውም ግን እንዲህ ስትለኝ ከሚያስፈልጋቸው በላይ እያላቸው የጓዳችንን ችግር እያዩ የቅርብ እሩቅ ሆነው ህመማችን የማያማቸው ችግራችን ያራቃቸውን በደና ኑሮ ውስጥ ያሉ የናቴንም ያባቴንም ዘመዶች አስታወስከኝ እማዬ በጣም የዋህ ነች ምንም ባያደርጉላትም ካለቻት ላይ ቀንሳ የሆነ ነገር ገዝታ ሄዳ ትጠይቃቸዋለች እነሱ እሚጠያየቁትም እሚረዳዱትም በንሮ ከሚመስሏቸው ሌሎች ዘመዶቻችን ጋር ነበር።
እያደኩ እና እሄን እያስተዋልኩ ስመጣ እማዬ "ልጠይቃቸው ልሄድ ነው "ስትለኝ በሷ እራሱ መናደድና ባትሄድ ደስ እንደሚለኝ ፊት ለፊት መናገር ጀመርኩ።
እሷ ግን
"ተይ ልጄ ክፉ መስለውሽ እንጂ ክፉ አደሉም ቢሆኑም ደግሞ ሰው ክፉ ሆነ ተብሎ ክፉ አይኮንም ፈጣሪ ሁሉንም እንደየስራው ይስጠው እኔ ግን ሄጄ ሰላም መሆናቸውን አይቼ መምጣት እረፍት ይሰጠኛል እና መጠየቄን አላቋርጥም" ነበር የሁልግዜ መልሷ።
ቢሆንም ግን •••
ከልጅነቴ ጀምሮ አባዬ እና እማዬ ሲከፋቸው በነሱ ሲበሳጩ እኔን በማይገባኝ መንገድ የውስጣቸውን ቁስል እርስ በርስ ለማውራት ሲሞክሩ እኔ በደንብ ይገባኝ ነበር በዛ ምክንያት ዘመዶቻችንን አልወዳቸውም።
እንደውም ስለነሱ ሳስብ ሰው ሁሉ ክፉ ነበር የሚመስለኝ ነገር ግን •••
ለሰው ችግር ደርሰው ሰው በነሱ ደስ ሲለው ሲያዩ በደስታ አለም የምትሞቃቸው ሰው አዝኖ ሲመለከቱ አለም የምትጨልምባቸው ደጋግ ጎሮቤቶቻችን ከክፍ ሰዎች ይልቅ ደግ ሰዎች በቁጥር እንደሚበልጡ አስተማሩኝ ሁሌም በመንገዴ በማላውቃቸው መሀል እንኳን ብገኝ ካሉት ውስጥ እኔን ከሚጎዳኝ ይልቅ እኔን የሚወደኝ እና ከጉዳት የሚታደገኝ ሰው ቁጥሩ የበዛ እንደሆነ እንዳምንና እንዳልፈራ ያደረጉኝ እነዛ ደጋግ የማዬ ጎረቤቶች ናቸው ።
ዛሬ አንተ እንዲህ ስትለኝ እነሱ ትዝ አሉኝና እምባ ተናነቀኝ !!" አለችኝ ።
ቅድም ህይወቷንና ያጋጠማትን ነገር ስትነግረኝ ከተሰማኝ ሀዘን በላይ ይህ ንግግሯ ውስጤን ሲፈነቃቅለው ተሰማኝ ።
ከዛ ሁኔታ ውስጥ ቶሎ መውጣት ፈለኩ••
ሰአቴን አየት አደረኩና ከለሊቱ ሰባት ሰአት ተኩል ሊሆን ነው ኤዱ በቃ በዚህ ሰአት ወደ ግቢ መግባቱ ጥሩ አይመስለኝም
ችግር እንኳን ባያጋጥምሽ የሆነ የሚያውቅሽ ሰው ባጋጣሚ በዚህ ሰአት ስትገቢ ቢያይሽ ስላንቺ ያለው አመለካከት ጥሩ ካለመሆኑም በላይ ነገ ባየሽ ቁጥር አጠገቡ ላሉት እቺ ልጅ እኩለ ለሊት ከደጅ ስትገባ አየሁዋት እያለ ስምሽን ሊያጠፋው ባጠቃላይ በዚህ ሰአት መግባቱ በተለይ ለሴት ሌላ ስም ነው እሚያሰጣት የነበርሽበትን ሁኔታ ማንም አይረዳም ስላት ትከሻዋን ሰበቀችው
"ታድያ ምን ላድርግ " ይመስላል የሰበቃው ትርጉም።
ለምን አልጋ ይዘሽ አታድሪምና ጥዋት አትገቢም?
"አይ ልግባ ባክህ አንተንም ከዚህ በላይ ላስቸግርህ አልፈልግም !"ስትለኝ በግድ አሳመንኳትና አልጋ ፍለጋ ወደ ከተማ ተመለስን
ትንሽ መንገድ በፀጥታ እንደተጓዝን ዝም ስትል እንደፈራች ስለገባኝ እኔ ማውራት ጀመርኩ
ቅድም ስለአንቺ ስለጓደኛችሽ እና ስለዛች ልጅ ስለ መሲ ስታወሪልኝ አንድ ጓደኛዬ ከአመት በፊት ያወርልኝ ነገር ነው ትዝ ያለኝ
"ምን አውርቶልህ ነበር እኔ ካወራሁልህ ጋር የሚመሳሰል ነው?"
ልጁ ቀደም ብሎ ነው በባጃጅ ሹፍርና ስራ የጀመረው አንድ ቀን ካፍቴርያ ቁጭ ብለን ማኪያቶ እየጠጣን •••
የሆነ ሰው እኛ ወዳለንበት ካፌ ገባና ከኛ ራቅ ብሎ ፊት ለፊት ተቀመጠ
"እሄን ሰውዬ ታውቀዋለህ ?አለኝ
ኧረ አላውቀውም ስለው
"እስቲ በደንብ እየው"
በደንብ አየሁት ደነገጥኩ ሰውየውን አፈር አይኳኝ ሲል አውቀዋለሁ
አዎ አንተ አውቀዋለሁ ምን ሆኖ ነው እንደዚህ አይጥ የበላው እስፖንጅ የመሰለው ደሞ በጣም ከስቷል ጆከሩን ስቦ ነው እንዴ ? ስለው
"እኔ በቀላሉ እምታገኘው ብር አንተንም አቅልሎህ እንደሚሄድ ያረጋገጥኩት በዚህ ሰውዬ ነው " ሲለኝ እንዴት? አልኩት
በቃ በቀላሉ ስታገኝ በቀላሉ ታጠፋዋለህ እሱ ደግሞ ብቻውን አይጠፋም አጥፍቶ ጠፉ በለው
ማለት ? አልኩት የተሸፋፈነውን ታሪክ ገላልጦ እንዲነግረኝ •••
"እሄውልህ ሰውየው ደሞዙ ትዝ አይለውም ከደሞዙ ብዙ እጅ በቀላሉ የሚያገኝባቸው ፕሮጀክቶች ነበሩት
ታድያ ብሩም በቀላሉ ይመጣል እሱም በቀላሉ ይረጨዋል ።
ብሩም ብቻውን አልተበተነማ እሱንም በትኖት ሄደ
እኔ በባጃጅ ስራ በደንብ አውቀዋለሁ።
በየቀኑ ጥዋት መጠጣት ይጀምራል ፣ከሰአት በርጫ ይቀመጣል፣ ማታ ጨብሲውን ይቀጥላል ፣
ያለ ስጋ አይበላም ፣አንዴ አብሯት የወጣውን ሴት አይደግምም ፣ በየቀኑ ከተለያዩ ሴቶች ጋር ያድራል እሄን ብር እያሳየ ስንት የግቢ ልጆች እንደቀጠፈ አትጠይቀኝ
እሄው አሁን ብሩ ሳያልቅ እሱን ጨረሰው ያለበትን በሽታ ከምነግርህ የሌለበትን ብጠራ ይቀለኛል
በስኳር ላይ ኮልስትሮል በክልስትሮል ላይ ደምብዛት በደምብዛቱ ላይ ኮብራውንም ሳይስበው አይቀርም
ታድያ ከ ብር በላይ አጥፍቶ ጠፊ የታለ? አታየውም እንዴ ማቆ ብሎኑ እንደላላ አልጋ እየተንቃቃ እኮ ነው እሚሄደው ! አለኝ ሰውየው ከዘራውን እየተደገፈ ተነስቶ ሲወጣ ።
አየሽ ኤዱ ፈጣሪ ሁሉንም ነገር በልኩ
እንድንጠቀም ነው የፈቀደልን በየቤቱ ሰው ኑሮ ከልክ ከልክ በታች እያኖረ ያሸዋል
ሰዎች ግን ሰው ከመርዳት ይልቅ ባገኙት ወይ ባላቸው ብር ከልክ በላይ ለመሆን ይሞክራሉ
ከልክ በላይ የሆነ ነገር ሁሉ ደግሞ ከበሽታ ወይ ከጭንቀት ያለፈ ነገር አያስገኝም እያልኳት እግረ መንገዴን በአይኔ ክፍት የሆነ ሆቴል እየፈለኩ ነበርና የምንሄደው አብዛኛዎቹ ዝግ በመሆናቸው መጀመሪያ ወደተገናኘንበት አከባቢ እየተቃረብን መጣን
"እንዴ ያገኘከኝ ቦታ ልትመልሰኝ ነው እንዴ አንተ ልጅ መሲ ይዘካት ና ብላህ ነው እንዴ?
እያለችኝ እየተሳሳቅን ጠጋ እንዳልን እዛ አከባቢ ካሉት ጭፈራ ቤቶች ከአንደኛው የፀብ የሚመስል ጫጫታ ከሩቅ ተሰማን እና
"ምንድን ነው? ፀብ ነው መሰለኝ እየተባባልን ጠጋ እንዳልን
ቀውጢ ሆኗል መስታወት ሲሰበር ጠርሙዝ ሲፈነዷ ሴቶች ሲጮሁ ይሰማል
እባክህ ብዙ አትጠጋ እያለችኝ ባጃጄን እያቀዘቀዝኩ በቀስታ ስጠጋ ከጭፈራ ቤቱ እየተሯሯጡ መውጣት ጀመሩ ከነዛ መሀል በደም የተጨማለቀችው ቀይ ረጅም ሴት የኤደን ጓደኛ መሆኗን ያወኩት ኤዱ
"ወይይይይይኔ ጉዴ ያቺ እኮ ጋደኛዬ ነች ብላ ስትጮህ ነበር ልብሷም ፊቷም ደም ለብሷል እጇን እያወራጨችና ደሟን ከአይኗ ላይ ለመጥረግ እየሞከረች እየተደነቃቀፈች ወጣችና አቅም አንሷት ወደቀች
የቷ!? አልኳት ደንግጬ ;
ያቺ ያቺ የወደቀችው እኮ ጋደኛዬ ረዱ ነች እያለች ከባጃጄ ላይ ተፈናጥራ በመውረድ ወደ ልጅቷ እያለቀሰች ስትሮጥ
እኔም ተከተልኳት••••••••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍2
#ልጩህበት!!
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
...በቀስታ ስጠጋ ከጭፈራ ቤቱ
እየተሯሯጡ መውጣት ጀመሩ ከነዛ መሀል በደም የተጨማለቀችው ቀይ ረጅም ሴት የኤደን ጓደኛ መሆኗን ያወኩት ኤዱ •••
"ወይይይይይኔ ጉዴ ያቺ እኮ ጋደኛዬ ነች ብላ ስትጮህ ነበር ልብሷም ፊቷም ደም ለብሷል እጇን እያወራጨችና ደሟን ከአይኗ ላይ ለመጥረግ እየሞከረች እየተደነቃቀፈች ወጣችና አቅም አንሷት ወደቀች
የቷ!? አልኳት ደንግጬ ;
ያቺ ያቺ የወደቀችው እኮ ጋደኛዬ ረዱ ነች እያለች ከባጃጄ ላይ ተፈናጥራ በመውረድ ወደ ልጅቷ እያለቀሰች ስትሮጥ
እኔም ተከተልኳት•••••
•••
ተከታትለን ደረስን። መሬት የተዘረረችውን ጓደኛዋን አነሳናትና ወደ ባጃጇ ወሰድናት ። ልጅቷ ኤደንን ስታያት ከዱላው በላይ ቢዥ አለባት ። ግራ ተጋባች።
ግንባሯ አከባቢ ተፈንክታለች ። በቅርብ ርቀት ያለው ሆስፒታል ድል ጮራ ነው ። ወደ ድል ጬራ ድንገተኛ ክፍል ይዣቸው በረርኩ ።
እንደገባን ወድያው እርዳታ ተደረገላት ምናልባት የፈሰሳት ደምና ድንጋጤዉ እንጂ ፍንክቱ ያን ያህል የከፋ አልነበረም።
ከለሊቱ ስምንት ሰአት ተኩል ሆኗል።
" በቃ ደና ነች አይዟችሁ የሰጠሁዋትን አንድ ግልኮስ እንደጨረሰች ትሄዳላችሁ እስከዛው ደጅ ሁኑ አለችን ሌላ የተጎዳ ሰው ወደ ድንገተኛ ክፍሉ ስለመጣ ክፍሉ እንዳይጣበብ።
እኔና ኤደን ወጣንና ግቢ ውስጥ ካለው ቴሌቭዥን ፊት ለፊት ተቀመጥን።
ኤዱ ! አልኳት በዝምታችን መሀል ከድንጋጤዋ እንደተረጋጋች በአተነፋፈሷ እንደተረዳሁ።
ወዬ ዳኒ ! አለችኝ ለኔ የሚጨነቅ የሚመስለውን ገፅታዋን ወደኔ ዞራ እያሳየችኝ።
በጣም ገርመሽኛል ! በእውነት የዋህ ልጅ ነሽ እናትሽ•••
" ሰው ክፉ የሆበበትን ሰው በክፋት ሳይሆን በደግነት የሚረታበት አጋጣሚ ከተፈጠረለት እና ከተጠቀመበት ትክክለኛ አሸናፊው እሱ እንደሆነ እየነገሩም በተግባር እያሳዩም አሳደጉሽ እሄው ዛሬ ፍሬውን እኔ አየሁት!ስላት•••
"እህህህህ በርግጥ ልክ ነህ ክፋትን በክፋት ስንመልስ ያን ሰው ለሌላ ክፋት እናዘጋጀዋለን!
ክፋትን በጥሩ ነገር ስንመልስ እኛም እናሸንፋለን ያን ሰውም ዳግም ሌላው ላይ ክፉ እንዳይሆን አድርገነው ልናልፍ እንችላለን የሚማርና የሚፀፀት ሰው ከሆነ !
እውነቱን ለመናገር እኔ ግን ረዱ እንደዛ ሆና ሳያት እሄን ሁሉ የሀሳብ ስሌት የማሰላበት ግዜ አልነበረኝም በቃ ውስጤ ያዘዘኝን ነው ያደረኩት!"
ተናደድሽባቸው እንጂ አልጠላሻቸውም ማለት ነው?! ስላት
አይ ለዛች እንዲህ እሆናለሁ ብለህ ነው እኔ እንጃ
ምን መሰለህ ይቺ የቲጂ ተከታይ ነች በቃ ቲጂ ወደመራቻት የምትጓዝ ዝም ብላ ወደ ነዷት ሁሉ የምትነዳ የዋህ አይነት ነገር ።
እኔን ወደዚህ አይነት ነገር ውስጥ ለማስገባት ያለፍላጎቴ ሲጫኑኝ ፊቷ ላይ ጭንቀት አነብ ነበር እሷ ግን ነገሮችን የማየትና የመሞከር ጉጉቷ ሀይለኛ ነው ለምን እንደሆነ አላውቅም!
ቢሆንም ከዛች ጭራቅ ጋር ሆነው አንቺን •••
ስላት ሳታስጨርሰኝ •••
"አስበው እስቲ ዳኒዬ ለመሲ እኔም ብሆን እኮ ተታልየላት ነበር ልጁ በአጋጣሚ እዛ ባይኖርና መሲ ያሰበችው ሁሉ ተሳክቶላት ቢሆን
በንጋታው ፊቴ ተቀምጣ
ካሁን ቡሀላ ሁለት አማራጮች አሉሽ አንዱ እኔ ነይ ስልሽ መምጣትና አድርጊ ያልኩሽን ማድረግ ሌላው ከኔ ጋር መጣላትና ለሊቱን ምን ስታደርጊ እንዳደርሽ ሚስጥርሽን በፎቶ አስደግፌ እንድበትንልሽ መፍቀድ ብትለኝ ምን ይውጠኝ ነበር ምንስ አማራጭ አለኝ
ወይ የሷ ለማዳ ውሻ መሆን ያለበለዚያ እራሴን ማጥፋት!"
ስትለኝ ከግር እስከራሴ ውርርር ሲያደርገኝ ታወቀኝ
አቦ የዚች መሲ እምትሏትን ልጅ ፎቶ ስጪኝ በናትሽ ካሁን ቡሀላ ፀቧ ከኔ ጋር ነው
"ኧረ ባባባ ሞት እዚህ ነገር ውስጥ አትግባ በቃ ሁሉም አለፈኮ ካሁን በኋላ የት ታገኘኛለች "
ስትለኝ ዝም ብለሽ ስጭኝ በናትሽ አልኳት
"እኔ ጋር የሷ ፎቶ ምን ያደርጋል ረዱ ሞባይል ግን አለ ግን ምንም አያደርግልህም።"
በዚህ መሀል የረድኤት ቤተሰቦች ብላ ተጣራች ነርሷ። ተነስተን ኤዱ ከፊት እኔ ከኌላ በመሆን ወደ ውስጥ ስንዘልቅ ጭንቅላቷ ዙርያውን በነጭ ፋሻ የታሰረው ረድኤት ተነስታ ቁጭ ብላለች ኤዱን ስታያት አለቀሰች ኤዱም ተንደርድራ አቀፈቻት።
"እሄውልህ እነዚህን መድሀኒቶች ግዙላት እሺ" አለችና የሀኪም ማዘዣ ወረቀቱን ሰጠችኝ ነርሷ።
ካራ ማራ አከባቢ ፔንስዮን (የምኝታ ብቻ) አገልግሎት የሚሰጥ ቤት መኖሩ ትዝ አለኝና ወደዛው ይዣቸው ልሄድ አሰብኩ ገና ከሆስፒታሉ ቅጥር ግቢ ወጣ እንዳልን ኤዱ ረድኤትን በጥያቄ ታጣድፋት ጀመር•••
ምንድን ነው የተፈጠረው?
ማን ነው የመታሽ ?
ቆይ ከማን ጋር ነበርሽ?
ማን እንደመታኝ አላውቅም ከኔ ጋር የነበረው ልጅ ፍቅረኛ ነበረው ለካ!
አብረን እየደነስን ድንገት መጥታ ስታንቀውና ሲወረውራት አብረዋት ይምጡ አይምጡ አላውቅም ወረሩት አብሮኝ ስለነበር ሲወሩት ጮህኩ ብቻ ምናባሽ ትጮሂያለሽ የሚል ወፍራም የሴት ድምፅ ተሰምቶኝ ዘወር ከማለቴ ግንባሬ ላይ የቢራ ጠርሙሱን ስታፈነዳው ትዝ ይለኛል ከዛ በኋላ እንዴት እንደወጣሁ እራሱ አላስታውስም
ማነች እሷ የመታችሽ ፍቅረኛው
ኧረ እሷ እኔን ዞራም አላየችኝ እዛው የምትሰራ ሴተኛ አዳሪ ሳትሆን አትቀርም የመታችኝ ከዚህ በፊት ሳይተዋወቁ አይቀሩም ከገባን ጀምሮ ስትመነቃቀርብኝ ነበር ሳስበው ለፍቅረኛው እሷ ሳትሆን አትቀርም የደወለችላት በመሀል ስልኩን ተውሳው ነበር
ቆይ አንቺ እሱን መች ነው የተዋወቅሽው
ረድኤት "በቀደም መሲ ናት ያስተዋወቀችኝ •• ብላ ገና ወሬዋን ሳትጨርስ•••
አስተዋወቀችኝ አትበይ ረዱ ሸጠችኝ በይ ልጅቷ እኮ ምንም የማያውቁ ፍሬሾችን ከወንዶች ጋር እያገናኘች ቢዝነስ የምትሰራ ጭራቅ ነች እሄን ታውቂያለሽ በናንተ እየተጠቀመች ነው "!
እኔ ነኝ ባለጌዋ ኤዱ እኔ የማረባ ሴት ነኝ ላንቺ ጓደኝነት እንኳን የማልመጥን ተራ ሴት ሆኜ አንቺ ግን ••••
በቃ እራስሽን አትውቀሺ ያቺ ቲጂ ነች አንቺን እዚህ ሁሉ ነገር ውስጥ የከተተችሽ
አይደለም ኤዱ ማንንም ጥፋተኝ ማረግ አልፈልግም ስለኔ የማታውቂው ነገር አለ!
አልጋ አግኝተን ይዣቸው እንደገባሁ
"ምንድን ነው እሱ ስላንቺ የማላውቀው ?" አለቻት ኤዱ ገብተን ቁጭ እንዳልን
••• "ታውቂያለሽ አባቴ በጣም ሀይለኛ ነበር ታላቅ ወንድሜ ደግሞ ቁጭ አባቴን በሱ ነው የወጣው እናቴ ደግሞ በተቃራኒው ልጅን ክፉና ደጉን በመንገር እና በመምከር እንጂ የትወጣሽ የት ገባሽ ከማን ጋር አወራሽ ከማን ጋር ታየሽ ማለታቸውን ሁሌ የምትቃወም እናት ነበረች ግን አይሰሟትም
ወንድም እና አባቴ በኔ ላይ አምባገነን የሚለው ቃል አይገልፃቸውም እንኳን የወንድ የሴት ጓደኛዬ እነሱ ቀልባቸው ካልወደዳት ከኔ ጋር አትቀጥልም ምን ልበላችሁ አባቴ በቤት ታላቅ ወንድሜ በሰፈር እና በትምህርት ቤት መፈናፈኛ አሳጥተው ነው ያሳደጉኝ።
ትምህርት ቤት በጋራ የሚሰሩ የቤት ስራዎች ከወንዶች ጋር ከተደለደልኩ አወቁ አላወቁ ነፍስ ውጪ ነፍስ ግቢ ነው የክፍል ልጆች ግን ስለሚረዱኝ ነይ እንስራ ብለው ብዙም አይጫኑኝም ነበር!
ግን አባቴና ወንድሜ እንዳሰቡት በቁጥጥር ብዛት ስነስርዓት ያላት ሴት ሳይሆን በቁጥጥራቸው ብዛት አጋጣሚውን ስታገኝ ለመፈንዳት ሳይሄን ለመፈነዳዳት የተጠመደች ቦንብ አድርገውኝ አረፉት።
ዩንቨርስቲ ለመመደብ የድልድል ፎርም ስሞላ እንኳን ሆን ብዬ እራቅ እራቅ ያሉ ዩንቨርስቲዎችን ነበር በምርጫዬ ውስጥ የሞላሁት ከነሱ ለመራቅ ስል።
ቁጥጥራቸው ከመብዛቱ የተነሳ ምርር ስላለኝ ለኔ ብለው ነው ብዬ ከማሰብ ፈንታ እነሱን የምጎዳ መስሎኝ እልህ ውስጥ ገባሁ ግን ወድጄ አልነበ
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
...በቀስታ ስጠጋ ከጭፈራ ቤቱ
እየተሯሯጡ መውጣት ጀመሩ ከነዛ መሀል በደም የተጨማለቀችው ቀይ ረጅም ሴት የኤደን ጓደኛ መሆኗን ያወኩት ኤዱ •••
"ወይይይይይኔ ጉዴ ያቺ እኮ ጋደኛዬ ነች ብላ ስትጮህ ነበር ልብሷም ፊቷም ደም ለብሷል እጇን እያወራጨችና ደሟን ከአይኗ ላይ ለመጥረግ እየሞከረች እየተደነቃቀፈች ወጣችና አቅም አንሷት ወደቀች
የቷ!? አልኳት ደንግጬ ;
ያቺ ያቺ የወደቀችው እኮ ጋደኛዬ ረዱ ነች እያለች ከባጃጄ ላይ ተፈናጥራ በመውረድ ወደ ልጅቷ እያለቀሰች ስትሮጥ
እኔም ተከተልኳት•••••
•••
ተከታትለን ደረስን። መሬት የተዘረረችውን ጓደኛዋን አነሳናትና ወደ ባጃጇ ወሰድናት ። ልጅቷ ኤደንን ስታያት ከዱላው በላይ ቢዥ አለባት ። ግራ ተጋባች።
ግንባሯ አከባቢ ተፈንክታለች ። በቅርብ ርቀት ያለው ሆስፒታል ድል ጮራ ነው ። ወደ ድል ጬራ ድንገተኛ ክፍል ይዣቸው በረርኩ ።
እንደገባን ወድያው እርዳታ ተደረገላት ምናልባት የፈሰሳት ደምና ድንጋጤዉ እንጂ ፍንክቱ ያን ያህል የከፋ አልነበረም።
ከለሊቱ ስምንት ሰአት ተኩል ሆኗል።
" በቃ ደና ነች አይዟችሁ የሰጠሁዋትን አንድ ግልኮስ እንደጨረሰች ትሄዳላችሁ እስከዛው ደጅ ሁኑ አለችን ሌላ የተጎዳ ሰው ወደ ድንገተኛ ክፍሉ ስለመጣ ክፍሉ እንዳይጣበብ።
እኔና ኤደን ወጣንና ግቢ ውስጥ ካለው ቴሌቭዥን ፊት ለፊት ተቀመጥን።
ኤዱ ! አልኳት በዝምታችን መሀል ከድንጋጤዋ እንደተረጋጋች በአተነፋፈሷ እንደተረዳሁ።
ወዬ ዳኒ ! አለችኝ ለኔ የሚጨነቅ የሚመስለውን ገፅታዋን ወደኔ ዞራ እያሳየችኝ።
በጣም ገርመሽኛል ! በእውነት የዋህ ልጅ ነሽ እናትሽ•••
" ሰው ክፉ የሆበበትን ሰው በክፋት ሳይሆን በደግነት የሚረታበት አጋጣሚ ከተፈጠረለት እና ከተጠቀመበት ትክክለኛ አሸናፊው እሱ እንደሆነ እየነገሩም በተግባር እያሳዩም አሳደጉሽ እሄው ዛሬ ፍሬውን እኔ አየሁት!ስላት•••
"እህህህህ በርግጥ ልክ ነህ ክፋትን በክፋት ስንመልስ ያን ሰው ለሌላ ክፋት እናዘጋጀዋለን!
ክፋትን በጥሩ ነገር ስንመልስ እኛም እናሸንፋለን ያን ሰውም ዳግም ሌላው ላይ ክፉ እንዳይሆን አድርገነው ልናልፍ እንችላለን የሚማርና የሚፀፀት ሰው ከሆነ !
እውነቱን ለመናገር እኔ ግን ረዱ እንደዛ ሆና ሳያት እሄን ሁሉ የሀሳብ ስሌት የማሰላበት ግዜ አልነበረኝም በቃ ውስጤ ያዘዘኝን ነው ያደረኩት!"
ተናደድሽባቸው እንጂ አልጠላሻቸውም ማለት ነው?! ስላት
አይ ለዛች እንዲህ እሆናለሁ ብለህ ነው እኔ እንጃ
ምን መሰለህ ይቺ የቲጂ ተከታይ ነች በቃ ቲጂ ወደመራቻት የምትጓዝ ዝም ብላ ወደ ነዷት ሁሉ የምትነዳ የዋህ አይነት ነገር ።
እኔን ወደዚህ አይነት ነገር ውስጥ ለማስገባት ያለፍላጎቴ ሲጫኑኝ ፊቷ ላይ ጭንቀት አነብ ነበር እሷ ግን ነገሮችን የማየትና የመሞከር ጉጉቷ ሀይለኛ ነው ለምን እንደሆነ አላውቅም!
ቢሆንም ከዛች ጭራቅ ጋር ሆነው አንቺን •••
ስላት ሳታስጨርሰኝ •••
"አስበው እስቲ ዳኒዬ ለመሲ እኔም ብሆን እኮ ተታልየላት ነበር ልጁ በአጋጣሚ እዛ ባይኖርና መሲ ያሰበችው ሁሉ ተሳክቶላት ቢሆን
በንጋታው ፊቴ ተቀምጣ
ካሁን ቡሀላ ሁለት አማራጮች አሉሽ አንዱ እኔ ነይ ስልሽ መምጣትና አድርጊ ያልኩሽን ማድረግ ሌላው ከኔ ጋር መጣላትና ለሊቱን ምን ስታደርጊ እንዳደርሽ ሚስጥርሽን በፎቶ አስደግፌ እንድበትንልሽ መፍቀድ ብትለኝ ምን ይውጠኝ ነበር ምንስ አማራጭ አለኝ
ወይ የሷ ለማዳ ውሻ መሆን ያለበለዚያ እራሴን ማጥፋት!"
ስትለኝ ከግር እስከራሴ ውርርር ሲያደርገኝ ታወቀኝ
አቦ የዚች መሲ እምትሏትን ልጅ ፎቶ ስጪኝ በናትሽ ካሁን ቡሀላ ፀቧ ከኔ ጋር ነው
"ኧረ ባባባ ሞት እዚህ ነገር ውስጥ አትግባ በቃ ሁሉም አለፈኮ ካሁን በኋላ የት ታገኘኛለች "
ስትለኝ ዝም ብለሽ ስጭኝ በናትሽ አልኳት
"እኔ ጋር የሷ ፎቶ ምን ያደርጋል ረዱ ሞባይል ግን አለ ግን ምንም አያደርግልህም።"
በዚህ መሀል የረድኤት ቤተሰቦች ብላ ተጣራች ነርሷ። ተነስተን ኤዱ ከፊት እኔ ከኌላ በመሆን ወደ ውስጥ ስንዘልቅ ጭንቅላቷ ዙርያውን በነጭ ፋሻ የታሰረው ረድኤት ተነስታ ቁጭ ብላለች ኤዱን ስታያት አለቀሰች ኤዱም ተንደርድራ አቀፈቻት።
"እሄውልህ እነዚህን መድሀኒቶች ግዙላት እሺ" አለችና የሀኪም ማዘዣ ወረቀቱን ሰጠችኝ ነርሷ።
ካራ ማራ አከባቢ ፔንስዮን (የምኝታ ብቻ) አገልግሎት የሚሰጥ ቤት መኖሩ ትዝ አለኝና ወደዛው ይዣቸው ልሄድ አሰብኩ ገና ከሆስፒታሉ ቅጥር ግቢ ወጣ እንዳልን ኤዱ ረድኤትን በጥያቄ ታጣድፋት ጀመር•••
ምንድን ነው የተፈጠረው?
ማን ነው የመታሽ ?
ቆይ ከማን ጋር ነበርሽ?
ማን እንደመታኝ አላውቅም ከኔ ጋር የነበረው ልጅ ፍቅረኛ ነበረው ለካ!
አብረን እየደነስን ድንገት መጥታ ስታንቀውና ሲወረውራት አብረዋት ይምጡ አይምጡ አላውቅም ወረሩት አብሮኝ ስለነበር ሲወሩት ጮህኩ ብቻ ምናባሽ ትጮሂያለሽ የሚል ወፍራም የሴት ድምፅ ተሰምቶኝ ዘወር ከማለቴ ግንባሬ ላይ የቢራ ጠርሙሱን ስታፈነዳው ትዝ ይለኛል ከዛ በኋላ እንዴት እንደወጣሁ እራሱ አላስታውስም
ማነች እሷ የመታችሽ ፍቅረኛው
ኧረ እሷ እኔን ዞራም አላየችኝ እዛው የምትሰራ ሴተኛ አዳሪ ሳትሆን አትቀርም የመታችኝ ከዚህ በፊት ሳይተዋወቁ አይቀሩም ከገባን ጀምሮ ስትመነቃቀርብኝ ነበር ሳስበው ለፍቅረኛው እሷ ሳትሆን አትቀርም የደወለችላት በመሀል ስልኩን ተውሳው ነበር
ቆይ አንቺ እሱን መች ነው የተዋወቅሽው
ረድኤት "በቀደም መሲ ናት ያስተዋወቀችኝ •• ብላ ገና ወሬዋን ሳትጨርስ•••
አስተዋወቀችኝ አትበይ ረዱ ሸጠችኝ በይ ልጅቷ እኮ ምንም የማያውቁ ፍሬሾችን ከወንዶች ጋር እያገናኘች ቢዝነስ የምትሰራ ጭራቅ ነች እሄን ታውቂያለሽ በናንተ እየተጠቀመች ነው "!
እኔ ነኝ ባለጌዋ ኤዱ እኔ የማረባ ሴት ነኝ ላንቺ ጓደኝነት እንኳን የማልመጥን ተራ ሴት ሆኜ አንቺ ግን ••••
በቃ እራስሽን አትውቀሺ ያቺ ቲጂ ነች አንቺን እዚህ ሁሉ ነገር ውስጥ የከተተችሽ
አይደለም ኤዱ ማንንም ጥፋተኝ ማረግ አልፈልግም ስለኔ የማታውቂው ነገር አለ!
አልጋ አግኝተን ይዣቸው እንደገባሁ
"ምንድን ነው እሱ ስላንቺ የማላውቀው ?" አለቻት ኤዱ ገብተን ቁጭ እንዳልን
••• "ታውቂያለሽ አባቴ በጣም ሀይለኛ ነበር ታላቅ ወንድሜ ደግሞ ቁጭ አባቴን በሱ ነው የወጣው እናቴ ደግሞ በተቃራኒው ልጅን ክፉና ደጉን በመንገር እና በመምከር እንጂ የትወጣሽ የት ገባሽ ከማን ጋር አወራሽ ከማን ጋር ታየሽ ማለታቸውን ሁሌ የምትቃወም እናት ነበረች ግን አይሰሟትም
ወንድም እና አባቴ በኔ ላይ አምባገነን የሚለው ቃል አይገልፃቸውም እንኳን የወንድ የሴት ጓደኛዬ እነሱ ቀልባቸው ካልወደዳት ከኔ ጋር አትቀጥልም ምን ልበላችሁ አባቴ በቤት ታላቅ ወንድሜ በሰፈር እና በትምህርት ቤት መፈናፈኛ አሳጥተው ነው ያሳደጉኝ።
ትምህርት ቤት በጋራ የሚሰሩ የቤት ስራዎች ከወንዶች ጋር ከተደለደልኩ አወቁ አላወቁ ነፍስ ውጪ ነፍስ ግቢ ነው የክፍል ልጆች ግን ስለሚረዱኝ ነይ እንስራ ብለው ብዙም አይጫኑኝም ነበር!
ግን አባቴና ወንድሜ እንዳሰቡት በቁጥጥር ብዛት ስነስርዓት ያላት ሴት ሳይሆን በቁጥጥራቸው ብዛት አጋጣሚውን ስታገኝ ለመፈንዳት ሳይሄን ለመፈነዳዳት የተጠመደች ቦንብ አድርገውኝ አረፉት።
ዩንቨርስቲ ለመመደብ የድልድል ፎርም ስሞላ እንኳን ሆን ብዬ እራቅ እራቅ ያሉ ዩንቨርስቲዎችን ነበር በምርጫዬ ውስጥ የሞላሁት ከነሱ ለመራቅ ስል።
ቁጥጥራቸው ከመብዛቱ የተነሳ ምርር ስላለኝ ለኔ ብለው ነው ብዬ ከማሰብ ፈንታ እነሱን የምጎዳ መስሎኝ እልህ ውስጥ ገባሁ ግን ወድጄ አልነበ
👍1
#ልጩህበት !!
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
፡
የሷ ሚስጥር አልገባኝም ነበርና እኔ ከምፈልገው ደስ ካለኝ ወንድ ጋር ለመሆን ስሞክር ታጣጥልብኝ ነበር አንድ ሁለቴ በሀሳቧ ተስማማሁና ተውኩላት በሶስተኛው አንድ ቀን ግቢ ከተወወኩት ልጅ ጋር ኦቨር ማለት አብረን ጭፈራ ወጣን በመሀል ስትደውል አላነሳሁላትም እንዴት እንዳወቀች እንጃ ብቻ ያለንበት ድረስ ቀጥ ብላ መጣችና •••••
ስትጠራኝ ከጀርባዬ ስለነበረች አለየኋትምም አልሰማኋትምም ነበር አብሮኝ ያለው ልጅ •••
"እንዴ ከዚች የሴት ነጋዴ ጋር ደግሞ የት ነው የምትተዋወቁት በይ ሂጂ እየጠራችሽ ነው ! ልታጫርትብሽ ሳይሆን አይቀርም እኔማ በምን አቅሜ እጫረታለሁ"
ሲለኝ አባባሉ ግራ እየገባኝ ዘወር አልኩ ፊቷን ምን አስመስላው እንደቆመች አትጠይቂኝ ።
እንዴት እንደተናደድኩ ከናባዬ ተገላገልኩ ስል እቺን ደሞ ማነው የላከብኝ አልኩ በውስጤ !
አልመጣም ልላት ሁላ ፈልጌ ነበር ።
ልጁን አንዴ አናግሪያት ብመለስ ቅር አይልህም አደል? ስለው•••
"ኧረ በጭራሽ እንደውም ባታናግሪያት ነው እሚሸክከኝ ይልቅ አፍጥኚው ወደዚህ ሳትመጣ!" አለኝ።
ሄድኩ ። ገና አጠገቧ እንደደረስኩ•••
"ስሚ ከኔ እና እኔ እኔ ከማውቃቸው የተከበሩ ሰዎች ጋር አንዴ ከታየሽ ከእንደዚህ አይነቱ መናጢ ተማሪ ጋር መታየት እንዳልነበረብሽ ሳልነግርሽ ማወቅ ነበረብሽ እኮ?!" ስትለኝ የእውነት ደሜ ፈላ
በምናቸው ነው የተከበሩት እሱ ከነሱ በምን ያንሳል?!
"በብራቸው ነዋ በብራቸው ብርርርር ታውቂያለሽ አደል ስንቱን እንደሚያበር ስንቱን እንደሚያስከብር እሄውልሽ እሄ ልጅ ምናልባት መልኩና ወጣትነቱ ያምር ይሆናል ግን ባዶ ነው ባዶ ታውቂያለሽ ለኔ በብዙ ደሀዎች መካከል ያለ አንድ ባለ ብር ለምን ሰላሳ ሁለት ጥርሱ ረግፎ በድዱ አይስቅም ለኔ ቆንጆው እሱ ነው !"
ለኔ ግን አይደለም አንቺም ቆንጆሽ ጋር ሂጂ እኔንም ከቆንጆዬ ጋር ተይኝ ብያት ጥያት ወደ ተማሪው ስመለስ ቤት በኩል እንደወጣ ድራሹ የለም ! አመዴ ቡን አለ!።
ሹክክ ብዬ ስመለስ ሲወጣ ትየው ወይ እንደሚወጣ ቀድማ ትወቅ ብቻ ቀድማ ነበር እየሳቀች የጠበቀችኝ "
አለችና በረጅሙ ተንፍሳ ጭንቅላቷን እየነካካች
"የሷ ጉድ መች ያልቃል እራሴን ሲሻለኝ አወራሻለሁ ። ግን እሄ ልጅ ማነው ኤዱ ?" አለች በአገጯ ወደኔ እያመለከተች። ሁለቱ አልጋ ላይ እኔ ደግሞ ከፊት ለፊታቸው ክፍሉ ውስጥ መስኮት ስር ባለችው አንዲት ወንበር ላይ ተቀምጫለሁ።
"ወንድሜ ነው! ያንቺዋ መሲ ሳታስበው የሰጠችኝ ምርጥ ወንድሜ!"አለቻት ።
ኤደን ስትናገር በጥልቀት እያየችኝ ነበር ንግግሯም ከልቧ ስለመሆኑ ቃናው ያስታውቃል።
"!?" እንዴት አለች ረድኤት ግራ ተጋብታ ።
በዚህ መሀል ጣልቃ ገባሁና እሱን እንቅልፍ እስኪወስዳችሁ ድረስ ታወራላችሁ እኔ ልሂድ አልኳቸው እና የመሲን ፎቶ በግድ ድርቅ ብዬ ከረድኤት ሞባይል ላይ ወደኔ ከላኩ በኋላ ኤዱን ነይ አንዴ ብያት ከክፍሉ ወጣሁ ።
ተከትላኝ እንደወጣች እሄን ለግዜው ያዥው ብዬ የተወሰነ ሳንቲም ሰጥቻት ስልኳን ወስጄ ደና እደሩ ነገ እደውልልሻለሁ ብያት ልሄድ ስል •••
ከአንደበቷ ቃል እንዳይወጣ ሰንጎ ከያዛት ሲቃ ጋር እየታገለች •••
"አመሰግናለሁ እሺ" አለችኝ ።
እንደተለየኋት ሰአቴን ስመለከት ዘጠኝ ተኩል ሆኗል።
ሁልግዜም ቢሆን በማታ ስራ ከዚህ ሰአት በፊት ገብቼ አላውቅም አንዳንዴ እስከ አስር ተኩልም ሰራለሁ። ቀጥታ ወደቤቴ አመራሁ። በንጋታው ከእንቅልፌ ስነቃ ከቀኑ ሰባት ሰአት ተኩልን አለፍ ብሏል። እዛው መኝታዬ ላይ ሆኜ ስልኳ ላይ ደወልኩ። ስልኳ ጥሪ አይቀበልም ግቢ ሄደዉም ተኝተዋል ማለት ነው አልኩና ትንሽ ተገላብጬ ተነሳው ተጣጥቤ ቀማምሼ ወጣ እንዳልኩ ነበር ጆሲ ስልክ ላይ የደወልኩት ዮሴፍ ይባላል በጣም የምወደው ጓደኛዬ ነው ።
ከስራ ወጥቼ እየመጣሁ ነው ስደርስ እደውላለሁ አለኝና ከሰላሳ ደቂቃ በኋላ ደርሶ ደወለልኝ ። እንደተገናኘን ማታ ያጋጠመኝን ነገር ንግግራችንን ሳይቀር አንድ በአንድ ነገርኩት።
በመሲ በጣም ተናዶ ለነኤዱ በጣም አዘነ እና እኔን ግን ከባድ ጥያቄ ጠየቀኝ•••
"ዳኒዬ ለልጅቷ ማለት ለ ኤደን ያልካትና ውስጥህ ያለው ስሜት አይጋጭም አደለ!?" አለኝ።
ምን ለማለት ፈልገህ ነው!? አልኩት ቢገባኝም እንዳልገባኝ ሆኜ ለማሰቢያ የሚሆነኝ አየር ለመያዝ
"ማለት እኔ አሁን በነገርከኝ በነኤደን አጋጣሚ ውስጥ የነበረውን ዳንኤልን አላውቀውም"
የቱን ነበር የምታውቀው? አልኩት አሁንም ባስብም ለአጥጋቢ መልስ ጠብ የሚል ሀሳብ ሲደርቅብኝ ግራ ተጋብቼ!
"ሰዎች ውልታ ውለውልሽ ከመንገድሽ ውጪ እንድትሄጂ ከጠየቁሽ ጥያቸው ብሎ እየመከረ ውለታ ለመዋል ቃል የገባው ጋደኛዬ ዳኒ ኋላ የራሱ ቃል ጠልፎ እንዳይጥለው ፈራሁለት! "አለኝ
አልገባኝም ስለው
" ባክህ ገብቶሀል አታድርቀኝ !" አለኝ
አዎ ገብቶኛል ጆሲዬ ግንኮ አንዳንዴ በንፁህ እህትነት ብቻ የምንቀርባቸው ሴቶች ያስፈልጉናል ቢያንስ አንድ እሷም እንደወንድሟ አንተም እንደህትህ የምታያት ሴት እንድትኖርህ አስበህ አታውቅም ?!ስለው•••
"አላውቅም!" አለኝ ፈርጠም ብሎ
ለምን ?
"የለም ማለቴ አደለም ግን መጨረሻው አያምርም!" አለኝ አሁንም ቁምጭጭ ብሎ
ጆሲዬ መጨረሻውን እያሰብን ነገሮችን የምናጣጥም ከሆነማ መጨረሻችን ሞት መሆኑን እያስታወስን ምንም እንዳይጥመን፣ ምንም እንዳይደንቀን፣ ምንም እንዳይሞቀን ፣ሆነን መኖራችን ነውኮ ስለው
እሱማ መታደል ነዎ የሰው ልእልና ጫፍ ላይ መድረስ ነገ መሞታችንን ሁሌ ካስታወስን ክፋት ይሸሸን ነበርኮ ዳኒዬ
ክርክር ከጀመረ አያቋርጥም ።
አቦ ተወኝ እንግዲህ ይልቅ ባለፈው ያልከውን ሀሳብ ተውከው እንዴ? አልኩት
"የቱን?"
ስራ እንደጀመርኩ አከባቢ ለሁለት አንዲት ክፍል ተከራይተን ለምን ከቤተሰቦቻችን ቤት አንወጣም ያልከኝን ስለው ሳቁን ለቀቀው
ምን ያስቅሀል አልኩት ተናድጄ!
"መከራየቱን አልተስማማህም ነበር እኮ አሁን ምን አዲስ ነገር ተገኘ አየህ ውስጥህ እና ለሷ ያልካት ነገር እንዳይጋጭ ያልኩህ ለዚህ ነው!"ሲለኝ•••
ባክህ ለዛ አደለም ለሊት ለሊት ከስራ ስገባ እየረበሽኳቸው ስለሆነ ነው አልኩት።
"ይሁንልህ" አለኝ አሁንም እየሳቀ።
ማታም ስልኳ ላይ ስሞክር ጥሪ አይቀበልም ዝም ብዬ ወደ ምትማርበት ዩንቨርስቲ ሄድኩና ትናንት አብረን የነበርንበት አከባቢ ጭለማ ውስጥ የባጃጄን መብራት በማጥፋት ስላሳ ደቂቃ ያህል ግቢ ውስጥ ውር ውር ከሚሉት ተማሪዎች በተጨማሪ ከግቢ የሚወጡትን እና የሚገቡትን በአይኔ ስሸኝና ሳስገባ ቆየሁ።
ኤዱን ግን አላየኋትም ። መሄዴን ለጆሲም አልነገርኩትም።
በንጋታው በደላላ አፈላልጌ ከሰፈር ብዙም በማይርቅ በአንድ ትልቅ ግቢ ውስጥ ስፋቷ አራት ባአራት የሆነች ሰርቪስ ቤት አገኘሁ ለጆሲ ደውዬ ማግኘቴን ስነግረው እየሳቀ በል እሺ ኪራዩን ክፈል ከስራ ስወጣ ብር አወጣና ፍራሽ ምናምኑን እንገዛዛለን አለኝ።
ቤታችንን ማብሰያም መቀቀያም የለላት ምርጥ የወንደላጤዎች ቤት አደረግናት በየፍራሻችን ላይ ጋደም እንዳልን ስልኬን አውጥቼ የኤዱ ስልክ ላይ ስሞክር ጠራ ፍንጥር ብዬ ስነሳ •••
"ምን ሆንክ!? " አለኝ ደንግጦ ከፍራሹ ላይ ቀና እያለ!
እየጠራ ነው ስለው
"ማነው እሱ!? አለኝ
የኤዱ ስልክ ነዎ ስለው •••
"ካካካካካካ ••••!" የጆሲ ሳቅ ነበር•••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
፡
የሷ ሚስጥር አልገባኝም ነበርና እኔ ከምፈልገው ደስ ካለኝ ወንድ ጋር ለመሆን ስሞክር ታጣጥልብኝ ነበር አንድ ሁለቴ በሀሳቧ ተስማማሁና ተውኩላት በሶስተኛው አንድ ቀን ግቢ ከተወወኩት ልጅ ጋር ኦቨር ማለት አብረን ጭፈራ ወጣን በመሀል ስትደውል አላነሳሁላትም እንዴት እንዳወቀች እንጃ ብቻ ያለንበት ድረስ ቀጥ ብላ መጣችና •••••
ስትጠራኝ ከጀርባዬ ስለነበረች አለየኋትምም አልሰማኋትምም ነበር አብሮኝ ያለው ልጅ •••
"እንዴ ከዚች የሴት ነጋዴ ጋር ደግሞ የት ነው የምትተዋወቁት በይ ሂጂ እየጠራችሽ ነው ! ልታጫርትብሽ ሳይሆን አይቀርም እኔማ በምን አቅሜ እጫረታለሁ"
ሲለኝ አባባሉ ግራ እየገባኝ ዘወር አልኩ ፊቷን ምን አስመስላው እንደቆመች አትጠይቂኝ ።
እንዴት እንደተናደድኩ ከናባዬ ተገላገልኩ ስል እቺን ደሞ ማነው የላከብኝ አልኩ በውስጤ !
አልመጣም ልላት ሁላ ፈልጌ ነበር ።
ልጁን አንዴ አናግሪያት ብመለስ ቅር አይልህም አደል? ስለው•••
"ኧረ በጭራሽ እንደውም ባታናግሪያት ነው እሚሸክከኝ ይልቅ አፍጥኚው ወደዚህ ሳትመጣ!" አለኝ።
ሄድኩ ። ገና አጠገቧ እንደደረስኩ•••
"ስሚ ከኔ እና እኔ እኔ ከማውቃቸው የተከበሩ ሰዎች ጋር አንዴ ከታየሽ ከእንደዚህ አይነቱ መናጢ ተማሪ ጋር መታየት እንዳልነበረብሽ ሳልነግርሽ ማወቅ ነበረብሽ እኮ?!" ስትለኝ የእውነት ደሜ ፈላ
በምናቸው ነው የተከበሩት እሱ ከነሱ በምን ያንሳል?!
"በብራቸው ነዋ በብራቸው ብርርርር ታውቂያለሽ አደል ስንቱን እንደሚያበር ስንቱን እንደሚያስከብር እሄውልሽ እሄ ልጅ ምናልባት መልኩና ወጣትነቱ ያምር ይሆናል ግን ባዶ ነው ባዶ ታውቂያለሽ ለኔ በብዙ ደሀዎች መካከል ያለ አንድ ባለ ብር ለምን ሰላሳ ሁለት ጥርሱ ረግፎ በድዱ አይስቅም ለኔ ቆንጆው እሱ ነው !"
ለኔ ግን አይደለም አንቺም ቆንጆሽ ጋር ሂጂ እኔንም ከቆንጆዬ ጋር ተይኝ ብያት ጥያት ወደ ተማሪው ስመለስ ቤት በኩል እንደወጣ ድራሹ የለም ! አመዴ ቡን አለ!።
ሹክክ ብዬ ስመለስ ሲወጣ ትየው ወይ እንደሚወጣ ቀድማ ትወቅ ብቻ ቀድማ ነበር እየሳቀች የጠበቀችኝ "
አለችና በረጅሙ ተንፍሳ ጭንቅላቷን እየነካካች
"የሷ ጉድ መች ያልቃል እራሴን ሲሻለኝ አወራሻለሁ ። ግን እሄ ልጅ ማነው ኤዱ ?" አለች በአገጯ ወደኔ እያመለከተች። ሁለቱ አልጋ ላይ እኔ ደግሞ ከፊት ለፊታቸው ክፍሉ ውስጥ መስኮት ስር ባለችው አንዲት ወንበር ላይ ተቀምጫለሁ።
"ወንድሜ ነው! ያንቺዋ መሲ ሳታስበው የሰጠችኝ ምርጥ ወንድሜ!"አለቻት ።
ኤደን ስትናገር በጥልቀት እያየችኝ ነበር ንግግሯም ከልቧ ስለመሆኑ ቃናው ያስታውቃል።
"!?" እንዴት አለች ረድኤት ግራ ተጋብታ ።
በዚህ መሀል ጣልቃ ገባሁና እሱን እንቅልፍ እስኪወስዳችሁ ድረስ ታወራላችሁ እኔ ልሂድ አልኳቸው እና የመሲን ፎቶ በግድ ድርቅ ብዬ ከረድኤት ሞባይል ላይ ወደኔ ከላኩ በኋላ ኤዱን ነይ አንዴ ብያት ከክፍሉ ወጣሁ ።
ተከትላኝ እንደወጣች እሄን ለግዜው ያዥው ብዬ የተወሰነ ሳንቲም ሰጥቻት ስልኳን ወስጄ ደና እደሩ ነገ እደውልልሻለሁ ብያት ልሄድ ስል •••
ከአንደበቷ ቃል እንዳይወጣ ሰንጎ ከያዛት ሲቃ ጋር እየታገለች •••
"አመሰግናለሁ እሺ" አለችኝ ።
እንደተለየኋት ሰአቴን ስመለከት ዘጠኝ ተኩል ሆኗል።
ሁልግዜም ቢሆን በማታ ስራ ከዚህ ሰአት በፊት ገብቼ አላውቅም አንዳንዴ እስከ አስር ተኩልም ሰራለሁ። ቀጥታ ወደቤቴ አመራሁ። በንጋታው ከእንቅልፌ ስነቃ ከቀኑ ሰባት ሰአት ተኩልን አለፍ ብሏል። እዛው መኝታዬ ላይ ሆኜ ስልኳ ላይ ደወልኩ። ስልኳ ጥሪ አይቀበልም ግቢ ሄደዉም ተኝተዋል ማለት ነው አልኩና ትንሽ ተገላብጬ ተነሳው ተጣጥቤ ቀማምሼ ወጣ እንዳልኩ ነበር ጆሲ ስልክ ላይ የደወልኩት ዮሴፍ ይባላል በጣም የምወደው ጓደኛዬ ነው ።
ከስራ ወጥቼ እየመጣሁ ነው ስደርስ እደውላለሁ አለኝና ከሰላሳ ደቂቃ በኋላ ደርሶ ደወለልኝ ። እንደተገናኘን ማታ ያጋጠመኝን ነገር ንግግራችንን ሳይቀር አንድ በአንድ ነገርኩት።
በመሲ በጣም ተናዶ ለነኤዱ በጣም አዘነ እና እኔን ግን ከባድ ጥያቄ ጠየቀኝ•••
"ዳኒዬ ለልጅቷ ማለት ለ ኤደን ያልካትና ውስጥህ ያለው ስሜት አይጋጭም አደለ!?" አለኝ።
ምን ለማለት ፈልገህ ነው!? አልኩት ቢገባኝም እንዳልገባኝ ሆኜ ለማሰቢያ የሚሆነኝ አየር ለመያዝ
"ማለት እኔ አሁን በነገርከኝ በነኤደን አጋጣሚ ውስጥ የነበረውን ዳንኤልን አላውቀውም"
የቱን ነበር የምታውቀው? አልኩት አሁንም ባስብም ለአጥጋቢ መልስ ጠብ የሚል ሀሳብ ሲደርቅብኝ ግራ ተጋብቼ!
"ሰዎች ውልታ ውለውልሽ ከመንገድሽ ውጪ እንድትሄጂ ከጠየቁሽ ጥያቸው ብሎ እየመከረ ውለታ ለመዋል ቃል የገባው ጋደኛዬ ዳኒ ኋላ የራሱ ቃል ጠልፎ እንዳይጥለው ፈራሁለት! "አለኝ
አልገባኝም ስለው
" ባክህ ገብቶሀል አታድርቀኝ !" አለኝ
አዎ ገብቶኛል ጆሲዬ ግንኮ አንዳንዴ በንፁህ እህትነት ብቻ የምንቀርባቸው ሴቶች ያስፈልጉናል ቢያንስ አንድ እሷም እንደወንድሟ አንተም እንደህትህ የምታያት ሴት እንድትኖርህ አስበህ አታውቅም ?!ስለው•••
"አላውቅም!" አለኝ ፈርጠም ብሎ
ለምን ?
"የለም ማለቴ አደለም ግን መጨረሻው አያምርም!" አለኝ አሁንም ቁምጭጭ ብሎ
ጆሲዬ መጨረሻውን እያሰብን ነገሮችን የምናጣጥም ከሆነማ መጨረሻችን ሞት መሆኑን እያስታወስን ምንም እንዳይጥመን፣ ምንም እንዳይደንቀን፣ ምንም እንዳይሞቀን ፣ሆነን መኖራችን ነውኮ ስለው
እሱማ መታደል ነዎ የሰው ልእልና ጫፍ ላይ መድረስ ነገ መሞታችንን ሁሌ ካስታወስን ክፋት ይሸሸን ነበርኮ ዳኒዬ
ክርክር ከጀመረ አያቋርጥም ።
አቦ ተወኝ እንግዲህ ይልቅ ባለፈው ያልከውን ሀሳብ ተውከው እንዴ? አልኩት
"የቱን?"
ስራ እንደጀመርኩ አከባቢ ለሁለት አንዲት ክፍል ተከራይተን ለምን ከቤተሰቦቻችን ቤት አንወጣም ያልከኝን ስለው ሳቁን ለቀቀው
ምን ያስቅሀል አልኩት ተናድጄ!
"መከራየቱን አልተስማማህም ነበር እኮ አሁን ምን አዲስ ነገር ተገኘ አየህ ውስጥህ እና ለሷ ያልካት ነገር እንዳይጋጭ ያልኩህ ለዚህ ነው!"ሲለኝ•••
ባክህ ለዛ አደለም ለሊት ለሊት ከስራ ስገባ እየረበሽኳቸው ስለሆነ ነው አልኩት።
"ይሁንልህ" አለኝ አሁንም እየሳቀ።
ማታም ስልኳ ላይ ስሞክር ጥሪ አይቀበልም ዝም ብዬ ወደ ምትማርበት ዩንቨርስቲ ሄድኩና ትናንት አብረን የነበርንበት አከባቢ ጭለማ ውስጥ የባጃጄን መብራት በማጥፋት ስላሳ ደቂቃ ያህል ግቢ ውስጥ ውር ውር ከሚሉት ተማሪዎች በተጨማሪ ከግቢ የሚወጡትን እና የሚገቡትን በአይኔ ስሸኝና ሳስገባ ቆየሁ።
ኤዱን ግን አላየኋትም ። መሄዴን ለጆሲም አልነገርኩትም።
በንጋታው በደላላ አፈላልጌ ከሰፈር ብዙም በማይርቅ በአንድ ትልቅ ግቢ ውስጥ ስፋቷ አራት ባአራት የሆነች ሰርቪስ ቤት አገኘሁ ለጆሲ ደውዬ ማግኘቴን ስነግረው እየሳቀ በል እሺ ኪራዩን ክፈል ከስራ ስወጣ ብር አወጣና ፍራሽ ምናምኑን እንገዛዛለን አለኝ።
ቤታችንን ማብሰያም መቀቀያም የለላት ምርጥ የወንደላጤዎች ቤት አደረግናት በየፍራሻችን ላይ ጋደም እንዳልን ስልኬን አውጥቼ የኤዱ ስልክ ላይ ስሞክር ጠራ ፍንጥር ብዬ ስነሳ •••
"ምን ሆንክ!? " አለኝ ደንግጦ ከፍራሹ ላይ ቀና እያለ!
እየጠራ ነው ስለው
"ማነው እሱ!? አለኝ
የኤዱ ስልክ ነዎ ስለው •••
"ካካካካካካ ••••!" የጆሲ ሳቅ ነበር•••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
❤1👎1
#ልጩህበት!!
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
የኤዱ ስልክ ላይ ስሞክር ጠራ ፍንጥር ብዬ ስነሳ •••
"ምን ሆንክ!? " አለኝ ደንግጦ ከፍራሹ ላይ ቀና እያለ!
እየጠራ ነው ስለው
"ማነው እሱ!? አለኝ
የኤዱ ስልክ ነዎ ስለው •••
"ካካካካካካ ••••!" የጆሲ ሳቅ ነበር•••
እስቲ ላውራበት የሚል መልክት የያዘ ግልምጫ ገላመጥኩት ኤዱ ስልኩን ያነሳችው መስሎት ሳቁን ባጭሩ ቀጨው።
የኤዱ ስልክ ግን አልተነሳም አሁንም እየጠራ ነው •••" ጢርርርርር•••••ጢርርርርርር••••ጢርርርርርርር•••!"
ጥሪው አለቀና ሴትዮዋ "የደወሉላቸው ደንበኛ ስልክ አይመልስም"! ብላ የማውቀውን እውነት ለመድገም ከመድከሟ በፊት "የ!" እንዳለች አቋረጥኳትና በዝግታ ወደ ፍራሼ ተመለስኩ።
ሽቅብ እያየኝ የነበረው ጆሲ•••
"ምነው? አላነሳችልህም እንዴ?"ሲለኝ •••
አይ "ቤተ መፃህፍት ውስጥ ነኝ ስወጣ እደውልልሀለሁ!" አለችኝ አልኩት።
"ለዚሁ ነው ሳቄን ያቋረጥከኝ ምናለ እስቲ ብስቅበት!"
ካቆምክበት ቀጥላ ! አልኩት በሽቄ።
ዳንዬ የምስቀው አንተን ለማናደድ ቢሆን ኖሮ ካቆምኩበት እቀጥል ነበር እኔ የሳኩት ግን የእውነት ሁኔታህ አስቆኝ ስለሆነ ከቆምኩበት መቀጠል አልችልም"
ባንድ ጉዳይ ላይ ካንድ ግዜ በላይ መሳቅ አይቻልም እያልከኝ ነው?
"አላልኩም እሱ እንደሁኔታው ይወሰናል መቼም ግን ባንድ ጉዳይ የመጀመሪያውን ሳቅ ደግመህ መሳቅም ሆነ ከቆምክበት መቀጠል አትችልም!
ለምሳሌ•••!"
ብሎ ሊቀጥል ሲል
በቃ! በቃ ! ጆሲ በቃህ በናትህ ! ምንድን ነው ነገር እንደዚህ ማስፋት! ያ ፍቅሩ የተባለ ጋደኛህ ግን መጥፎ ልማድ እያለማመደህ ነው!
"ስትል ? እንዴት?" አለኝ ግንባሩን ቋጥሮ
ምን እንዴት አለው ከሱ ጋር ስትገናኙ በቃ የሆነች ርእስ ካገኛችሁ ቀኑን ሙሉ ስትከራከሩባት አደል እንዴ የምትውሉት የሱ ባህሪ ባይጋባብህ ኖሮ ድንገት ተነስተህ
ሳቅ ይደገማል ? አይደገምም ?
በሚል ርእስ ከኔ ጋር ልትከራከር ባልሞከርክ ነበራ?
ቆይ ያ ጓደኛህ ግን እሚያነበው ለመከራከር ነው? ወይስ ለማወቅ? አልኩት•••
"እምትከራከረው እኮ ስታውቅ ነው አለኝ ገልበጥ ብሎ በጀርባው እየተንጋለለ
እማትከራከረው ስለማታውቅ ነው እያልከኝ ነው ? ስለው
"ሰው ያውቃል እሚባለው ምን ያህል ሲያውቅ ነው ? ቆይ የማወቅ መለኪያው ምንድን ነው መቼስ ሰርተፍኬት ነው አትለኝም እንደዛ ቢሆን ሀገራችን ውስጥ •••"
ብሎ ሊቀጥል ሲል ለሁለተኛ ግዜ አቋረጥኩትና•••
ደሞ ጀመርክ እሄን ፖለቲካህን!
ስለፖለቲካ ማውራት አልፈልግም ይልቅ የጠየኩህን መልስልኝ አልኩት•••
"ዳንዬ የሚከራከር ሁሉ ያውቃል ማለት አይደለም እንደውም ሀገራችን ውስጥ የማያውቀው ነው ሁሉንም ነገር ተቆጣጥሮት እሚንጫጫው የሚያውቀው የተሻለው ዝምምምምምምምምምም ብሏል ለምን ይመስልሃል?"
በናትህ እሄን ርእስ ከዛ ከፍቅሩ ጋር ተዳረቅበት ከፈለክ ደውዬ ልጥራልህ እኔን ግን ተወኝ ! አልኩት ኮስተር ብዬ•••
" ወይ ፎንቃ••••• እና እሺ ስለምን እናውራ ቆይ አንተ እምትፈልገው ስለኤደን ብቻ እንድናወራ ነው?"
በናትህ ጆሲ እንዲህ አትበለኝ እኔ እማ ትሙት ኤዱን በጣም እምሳሳላት እህቴ እንደሆነች ነው የሚሰማኝ በሌላ በምንም ነገር አላሰብኳትም! ስለው ፍጥጥ ብሎ ለሰከንዶች አየኝና•••
"በእውነት! አመንኩህ በቃ ካሁን ቡሀላ እንደዚህ አልልህም!" አለኝ ከልቡ ነበር።
በማላውቀው ቁጥር ስልኬ ላይ ተደወለ እንደዋዛ አነሳሁትና •••
ሀሉ ስል•••
" ሄሎ ዳንዬ የኔ ውድ ወንድም እንዴት ነህልኝ ይቅርታ እሺ ረዱን ትንሽ አሟት ስለነበረ እሄን ሁለት ቀን ችግር ላይ ነበርን !"
የሚለውን የኤዱን ድምፅ ሰማሁ!•••
ለምን ደውለሽ አልነገርሽኝም ስላት እየተንተባተበች እኔን ከዛ በላይ ላለማስቸገር አስባ እንጂ ሳላስፈልጋት ቀርቼ እንዳልሆነ ልታስረዳኝ ሞከረች።
በቃ ከዛን ቀን ቡሀላ ቢያንስ በየሁለት ቀኑ በስልክ ቢያንስ በየሁለት ሳምንቱ ደግሞ በአካል እየተገናኘን እናወራለን ሻይ ቡና እንባባላለን ማታ ማታ ከነበረው ስራዬ ቀንም ማታም እስከተወሰነ ሰአት ወደ መስራት ከተሸጋገርኩ ቡኋላ አንዳንዴ ቀን ወደነሱ ግቢ ሰው ይዤ ከሄድኩ ሳላገኛት አልመለስም ።
ብዙ ግዜ እኔ ጋር ስትመጣ ረዱን ይዛት ትመጣለች ትግስት ስለምትባለው ጓደኛቸው ስጠይቃቸው ሁለቱም እየተጋገዙ "እሷ ከመሲ ጋር ተጣብቃ ቀረችኮ!
ዶርምም ለቃለች !
ማንበቡንም ጭራሽ ትታዋለች !
ክላስ እራሱ ብዙ የምትገባ አይመስለኝም!" በማለት ነግረውኛል እነሱ ግን መሲ ባለፈችበት መንገድ እንኳን አንደማያልፉ አውቃለሁ።
በዚህ መልኩ ቅርርባችን ቀጠለ። ከተዋወቅን አራት ወር ከሁለት ሳምንት ሆነን።
ከዛሬ ሶስት ሳምንት በፊት አንድ ጥያቄ ጠይቂያት ነበር መቼ ነው የተከራየኋት ቤት ውስጥ አንቺና ጓደኛሽ ቡና እምታፈሉባት? ብዬ የሁለተኛው መንፈቅ ፈተና መድረሱን ነግራኝ ፈተናውን እንደጨረሱ እንደምትመጣ ቃል ገባችልኝ ። እኔም ፈተናዋን ተፈትና እስክትጨርስ እየደወልኩ እንደማረብሻት ቃል ገባሁላት ። ችግር የለውም ደውል ብትለኝም ደውዬ አላውቅም ዛሬ አርብ ነው በነገረችኝ መሰረት ከሆነ ዛሬ ፈተናው ያልቃል። ስልኳን ስጠባበቅ ነው የዋልኩት እስካሁን ግን አልደወለችም ።
አመሻሹ ላይ ስራ ላይ ሆኜ ስልኬ ጠራ እየነዳሁ ነበርና ባጃጄን ጥግ አስይዤ ስልኬን ከኪሴ አውጥቼ ስመለከተው ኤዱ ነች ሰላምታ ከተለዋወጥን
ቡሀላ የነበረችበት ቦታ የሙዚቃ እና የሰው ጫጫታ ስለነበር የት ነሽ? አልኳት ግቢ ካፌ ውስጥ እንደሆነች ከነገረችኝ
ቡሀላ ነገ ማለት ቅዳሜ ስምንት ሰአት ላይ እንደምትመጣ ነገረችኝ እኔ እራሴ ግቢ ሄጄ እንደምውስዳት ነግሪያት ስራዬን ቀጠልኩ ልክ ከምሽቱ አራት ተኩል ላይ በቃ አቦ ደክሞኛል ልግባ ብዬ እያሰብኩ ስልኬ ጠራ በቋሚነት ስልክ ተቀያይረን ሲፈልጉ እየደወሉ ኮንትራት ከሚይዙኝና ደና ብር ከሚከፍሉኝ ሰዎች መሀከል ቀዳሚው ነበር የደወለው የማይታለፍ ስልክ አልኩ ገና ስልኩን እንዳየሁት።
እሄን ሰውዬ ሳስበው ነገረ ስራው ሁሉ ይገርመኛል የሆነ ድብቅ ማንነት ያለው ሰው ነው ኑሮው ድሬ ዳዋ አይደለም አልፎ አልፎ ነው ከጅግጅጋ ወደ ድሬ የሚመጣው ሁሌም እንደነገ ሊመጣ እንደዛሬ ይደውልልኝና ነገ መጣለሁ የተለመደው ቦታ አልጋ ያዝልኝና ውሃ አስገባልኝ ይለኛል ። ትዛዜን ተቀብዬ ክፍል ይዝለትና እሽግ ውሃውን በብዛት አስገብቼ እጠብቀዋለሁ ። ድሬ ሲቃረብ ይደውላል መግቢያው ላይ ጠብቄ ወደያዝኩለት ክፍል እወስደዋለሁ ።
ጥዋት ቁርስ ምሳ ሰአት ላይ ምሳና ኪሎ ጫቱን እንዲሁም ሌሎች የሚያስፈልጉትን ሁሉ ሴተኛ አዳሪን ጨምሮ አስገባለታለሁ ለሁለት ወይም ለሶስት ሳምንት በዚህ መልኩ ከያዝኩለት ክፍል ሳይወጣ ይቆይና ይሄዳል።
አሁን ከመጣ ስምንት ቀን አልፎታል ።
አንዳንዴ በቆይታው መሀል ቢበዛ አንድ ወይም ሁለት ቀን ወጣ ማለት ካስፈልገው ብቻ በዚህ ሰአት ይደውላል ዛሬም መውጣት ፈልጎ ይሆን እንዴ? እያልኩ ስልኩን አንስቼ ሳናግረው እንደጠረጠርኩት •••
"አቢቲ ዛሬ ወጣ ማለት አስኝቶኛል ትመጣልኝ?" አለኝ ባጃጄን አዙሬ ወዳለበት ከነፍኩ።
ሰው ወደማይበዛበት እና ሁሉም ነገር ወደድ ወዳለበት ጭፈራ ቤት አድርሼው ስመለስ ከኋላዬ የተሳፋሪ መቀመጫው ላይ ስልክ ሲጮህ ስልኩን ጥሎ መውረዱ ገባኝ አንስቼ ሄሎ ስል•••
" አቢቲ ስልኬን ባጃጅህ ውስጥ ጥያት ወረድኩ ታቀብለኝ?" አለኝ።
ጭፈራ ቤቱ ውስጠኛው ክፍል ውስጥ ገብቼ ስልኩን ሰጥቼው ልወጣ ሁለት እርምጃ እንደተራመድኩ ድንገት ወደ ቀኝ ገልመጥ ሳደርግ
ሁለት ሴቶችና አንድ የሰፈራችን ሀብታም ነጋዴ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
የኤዱ ስልክ ላይ ስሞክር ጠራ ፍንጥር ብዬ ስነሳ •••
"ምን ሆንክ!? " አለኝ ደንግጦ ከፍራሹ ላይ ቀና እያለ!
እየጠራ ነው ስለው
"ማነው እሱ!? አለኝ
የኤዱ ስልክ ነዎ ስለው •••
"ካካካካካካ ••••!" የጆሲ ሳቅ ነበር•••
እስቲ ላውራበት የሚል መልክት የያዘ ግልምጫ ገላመጥኩት ኤዱ ስልኩን ያነሳችው መስሎት ሳቁን ባጭሩ ቀጨው።
የኤዱ ስልክ ግን አልተነሳም አሁንም እየጠራ ነው •••" ጢርርርርር•••••ጢርርርርርር••••ጢርርርርርርር•••!"
ጥሪው አለቀና ሴትዮዋ "የደወሉላቸው ደንበኛ ስልክ አይመልስም"! ብላ የማውቀውን እውነት ለመድገም ከመድከሟ በፊት "የ!" እንዳለች አቋረጥኳትና በዝግታ ወደ ፍራሼ ተመለስኩ።
ሽቅብ እያየኝ የነበረው ጆሲ•••
"ምነው? አላነሳችልህም እንዴ?"ሲለኝ •••
አይ "ቤተ መፃህፍት ውስጥ ነኝ ስወጣ እደውልልሀለሁ!" አለችኝ አልኩት።
"ለዚሁ ነው ሳቄን ያቋረጥከኝ ምናለ እስቲ ብስቅበት!"
ካቆምክበት ቀጥላ ! አልኩት በሽቄ።
ዳንዬ የምስቀው አንተን ለማናደድ ቢሆን ኖሮ ካቆምኩበት እቀጥል ነበር እኔ የሳኩት ግን የእውነት ሁኔታህ አስቆኝ ስለሆነ ከቆምኩበት መቀጠል አልችልም"
ባንድ ጉዳይ ላይ ካንድ ግዜ በላይ መሳቅ አይቻልም እያልከኝ ነው?
"አላልኩም እሱ እንደሁኔታው ይወሰናል መቼም ግን ባንድ ጉዳይ የመጀመሪያውን ሳቅ ደግመህ መሳቅም ሆነ ከቆምክበት መቀጠል አትችልም!
ለምሳሌ•••!"
ብሎ ሊቀጥል ሲል
በቃ! በቃ ! ጆሲ በቃህ በናትህ ! ምንድን ነው ነገር እንደዚህ ማስፋት! ያ ፍቅሩ የተባለ ጋደኛህ ግን መጥፎ ልማድ እያለማመደህ ነው!
"ስትል ? እንዴት?" አለኝ ግንባሩን ቋጥሮ
ምን እንዴት አለው ከሱ ጋር ስትገናኙ በቃ የሆነች ርእስ ካገኛችሁ ቀኑን ሙሉ ስትከራከሩባት አደል እንዴ የምትውሉት የሱ ባህሪ ባይጋባብህ ኖሮ ድንገት ተነስተህ
ሳቅ ይደገማል ? አይደገምም ?
በሚል ርእስ ከኔ ጋር ልትከራከር ባልሞከርክ ነበራ?
ቆይ ያ ጓደኛህ ግን እሚያነበው ለመከራከር ነው? ወይስ ለማወቅ? አልኩት•••
"እምትከራከረው እኮ ስታውቅ ነው አለኝ ገልበጥ ብሎ በጀርባው እየተንጋለለ
እማትከራከረው ስለማታውቅ ነው እያልከኝ ነው ? ስለው
"ሰው ያውቃል እሚባለው ምን ያህል ሲያውቅ ነው ? ቆይ የማወቅ መለኪያው ምንድን ነው መቼስ ሰርተፍኬት ነው አትለኝም እንደዛ ቢሆን ሀገራችን ውስጥ •••"
ብሎ ሊቀጥል ሲል ለሁለተኛ ግዜ አቋረጥኩትና•••
ደሞ ጀመርክ እሄን ፖለቲካህን!
ስለፖለቲካ ማውራት አልፈልግም ይልቅ የጠየኩህን መልስልኝ አልኩት•••
"ዳንዬ የሚከራከር ሁሉ ያውቃል ማለት አይደለም እንደውም ሀገራችን ውስጥ የማያውቀው ነው ሁሉንም ነገር ተቆጣጥሮት እሚንጫጫው የሚያውቀው የተሻለው ዝምምምምምምምምምም ብሏል ለምን ይመስልሃል?"
በናትህ እሄን ርእስ ከዛ ከፍቅሩ ጋር ተዳረቅበት ከፈለክ ደውዬ ልጥራልህ እኔን ግን ተወኝ ! አልኩት ኮስተር ብዬ•••
" ወይ ፎንቃ••••• እና እሺ ስለምን እናውራ ቆይ አንተ እምትፈልገው ስለኤደን ብቻ እንድናወራ ነው?"
በናትህ ጆሲ እንዲህ አትበለኝ እኔ እማ ትሙት ኤዱን በጣም እምሳሳላት እህቴ እንደሆነች ነው የሚሰማኝ በሌላ በምንም ነገር አላሰብኳትም! ስለው ፍጥጥ ብሎ ለሰከንዶች አየኝና•••
"በእውነት! አመንኩህ በቃ ካሁን ቡሀላ እንደዚህ አልልህም!" አለኝ ከልቡ ነበር።
በማላውቀው ቁጥር ስልኬ ላይ ተደወለ እንደዋዛ አነሳሁትና •••
ሀሉ ስል•••
" ሄሎ ዳንዬ የኔ ውድ ወንድም እንዴት ነህልኝ ይቅርታ እሺ ረዱን ትንሽ አሟት ስለነበረ እሄን ሁለት ቀን ችግር ላይ ነበርን !"
የሚለውን የኤዱን ድምፅ ሰማሁ!•••
ለምን ደውለሽ አልነገርሽኝም ስላት እየተንተባተበች እኔን ከዛ በላይ ላለማስቸገር አስባ እንጂ ሳላስፈልጋት ቀርቼ እንዳልሆነ ልታስረዳኝ ሞከረች።
በቃ ከዛን ቀን ቡሀላ ቢያንስ በየሁለት ቀኑ በስልክ ቢያንስ በየሁለት ሳምንቱ ደግሞ በአካል እየተገናኘን እናወራለን ሻይ ቡና እንባባላለን ማታ ማታ ከነበረው ስራዬ ቀንም ማታም እስከተወሰነ ሰአት ወደ መስራት ከተሸጋገርኩ ቡኋላ አንዳንዴ ቀን ወደነሱ ግቢ ሰው ይዤ ከሄድኩ ሳላገኛት አልመለስም ።
ብዙ ግዜ እኔ ጋር ስትመጣ ረዱን ይዛት ትመጣለች ትግስት ስለምትባለው ጓደኛቸው ስጠይቃቸው ሁለቱም እየተጋገዙ "እሷ ከመሲ ጋር ተጣብቃ ቀረችኮ!
ዶርምም ለቃለች !
ማንበቡንም ጭራሽ ትታዋለች !
ክላስ እራሱ ብዙ የምትገባ አይመስለኝም!" በማለት ነግረውኛል እነሱ ግን መሲ ባለፈችበት መንገድ እንኳን አንደማያልፉ አውቃለሁ።
በዚህ መልኩ ቅርርባችን ቀጠለ። ከተዋወቅን አራት ወር ከሁለት ሳምንት ሆነን።
ከዛሬ ሶስት ሳምንት በፊት አንድ ጥያቄ ጠይቂያት ነበር መቼ ነው የተከራየኋት ቤት ውስጥ አንቺና ጓደኛሽ ቡና እምታፈሉባት? ብዬ የሁለተኛው መንፈቅ ፈተና መድረሱን ነግራኝ ፈተናውን እንደጨረሱ እንደምትመጣ ቃል ገባችልኝ ። እኔም ፈተናዋን ተፈትና እስክትጨርስ እየደወልኩ እንደማረብሻት ቃል ገባሁላት ። ችግር የለውም ደውል ብትለኝም ደውዬ አላውቅም ዛሬ አርብ ነው በነገረችኝ መሰረት ከሆነ ዛሬ ፈተናው ያልቃል። ስልኳን ስጠባበቅ ነው የዋልኩት እስካሁን ግን አልደወለችም ።
አመሻሹ ላይ ስራ ላይ ሆኜ ስልኬ ጠራ እየነዳሁ ነበርና ባጃጄን ጥግ አስይዤ ስልኬን ከኪሴ አውጥቼ ስመለከተው ኤዱ ነች ሰላምታ ከተለዋወጥን
ቡሀላ የነበረችበት ቦታ የሙዚቃ እና የሰው ጫጫታ ስለነበር የት ነሽ? አልኳት ግቢ ካፌ ውስጥ እንደሆነች ከነገረችኝ
ቡሀላ ነገ ማለት ቅዳሜ ስምንት ሰአት ላይ እንደምትመጣ ነገረችኝ እኔ እራሴ ግቢ ሄጄ እንደምውስዳት ነግሪያት ስራዬን ቀጠልኩ ልክ ከምሽቱ አራት ተኩል ላይ በቃ አቦ ደክሞኛል ልግባ ብዬ እያሰብኩ ስልኬ ጠራ በቋሚነት ስልክ ተቀያይረን ሲፈልጉ እየደወሉ ኮንትራት ከሚይዙኝና ደና ብር ከሚከፍሉኝ ሰዎች መሀከል ቀዳሚው ነበር የደወለው የማይታለፍ ስልክ አልኩ ገና ስልኩን እንዳየሁት።
እሄን ሰውዬ ሳስበው ነገረ ስራው ሁሉ ይገርመኛል የሆነ ድብቅ ማንነት ያለው ሰው ነው ኑሮው ድሬ ዳዋ አይደለም አልፎ አልፎ ነው ከጅግጅጋ ወደ ድሬ የሚመጣው ሁሌም እንደነገ ሊመጣ እንደዛሬ ይደውልልኝና ነገ መጣለሁ የተለመደው ቦታ አልጋ ያዝልኝና ውሃ አስገባልኝ ይለኛል ። ትዛዜን ተቀብዬ ክፍል ይዝለትና እሽግ ውሃውን በብዛት አስገብቼ እጠብቀዋለሁ ። ድሬ ሲቃረብ ይደውላል መግቢያው ላይ ጠብቄ ወደያዝኩለት ክፍል እወስደዋለሁ ።
ጥዋት ቁርስ ምሳ ሰአት ላይ ምሳና ኪሎ ጫቱን እንዲሁም ሌሎች የሚያስፈልጉትን ሁሉ ሴተኛ አዳሪን ጨምሮ አስገባለታለሁ ለሁለት ወይም ለሶስት ሳምንት በዚህ መልኩ ከያዝኩለት ክፍል ሳይወጣ ይቆይና ይሄዳል።
አሁን ከመጣ ስምንት ቀን አልፎታል ።
አንዳንዴ በቆይታው መሀል ቢበዛ አንድ ወይም ሁለት ቀን ወጣ ማለት ካስፈልገው ብቻ በዚህ ሰአት ይደውላል ዛሬም መውጣት ፈልጎ ይሆን እንዴ? እያልኩ ስልኩን አንስቼ ሳናግረው እንደጠረጠርኩት •••
"አቢቲ ዛሬ ወጣ ማለት አስኝቶኛል ትመጣልኝ?" አለኝ ባጃጄን አዙሬ ወዳለበት ከነፍኩ።
ሰው ወደማይበዛበት እና ሁሉም ነገር ወደድ ወዳለበት ጭፈራ ቤት አድርሼው ስመለስ ከኋላዬ የተሳፋሪ መቀመጫው ላይ ስልክ ሲጮህ ስልኩን ጥሎ መውረዱ ገባኝ አንስቼ ሄሎ ስል•••
" አቢቲ ስልኬን ባጃጅህ ውስጥ ጥያት ወረድኩ ታቀብለኝ?" አለኝ።
ጭፈራ ቤቱ ውስጠኛው ክፍል ውስጥ ገብቼ ስልኩን ሰጥቼው ልወጣ ሁለት እርምጃ እንደተራመድኩ ድንገት ወደ ቀኝ ገልመጥ ሳደርግ
ሁለት ሴቶችና አንድ የሰፈራችን ሀብታም ነጋዴ
❤1
#ልጩህበት!
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ጭፈራ ቤቱ ውስጠኛው ክፍል ውስጥ ገብቼ ስልኩን ሰጥቼው ልወጣ ሁለት እርምጃ እንደተራመድኩ ድንገት ወደ ቀኝ ገልመጥ ሳደርግ
ሁለት ሴቶችና አንድ የሰፈራችን ሀብታም ነጋዴ የተቀመጡበት ሶፋ ላይ አይኔ ተተክሎ ቀረ።
ደነገጥኩ!
ሰውየው የኤች አይ ቪ ኤድስ ተሻካሚ የሆነና ሚስቱ በዚሁ በሽታ የሞተችበት ሰው ነው ።
•••ሁለቱ ሴቶች ደግሞ አንዷ ጭራቋ ስትሆን አንዷ ደግሞ ምናልባት የነኤዱ ጓደኛ ሳትሆን አትቀርም ወይኔ ቲጂ እንዲህ አንድፍሬ ልጅ ነሽ ቆይ ኧረ •••
አልኩና እየተጣደፍኩ ከጭፈራ ቤቱ በመውጣት ሞባይሌን ከኪሴ አውጥቼ ፎቶ ማህደሩን ከፈትኩ አልተሳሳትኩም መሲ እራሷ ነች ከንፈሮቼን በሶስት ጣቶቼ ተጭኜ የመሲ ፎቶ ላይ እንዳፈጠጥኩ ወደ ባጃጄ ውስጥ ገብቼ ተቀመጥኩ ።
መደበኛ ስራዎ እሄ መሆኑን አውቃለሁ እኔን ያስደነገጠኝ አገር ምድሩ ሚስቱ በምን እንደሞተችና እሱም ምን እንዳለበት ከሚያውቀው ከዚህ ህሊና ቢስ ቀበጥ ጋር መተዋወቋ ነው።
ምንም የማያውቁ ከየቦታው የሚመጡ ፍሬሽ ተማሪዎችን እያቀረበችለት ሲጫወትባቸው ታየኝ እሷና እሱን ከዚህ ውጪ ምንም ሊያገናኛቸው እንደማይችል ግልፅ ነው ።
ሰውየው እንደሆነ ከመጨረሻዋ ልጅ እኩዮች ጋር ለመጋደም ፈሪሀ ህሊንም ሆነ ፈሪሀ ፈጣሪ ያልፈጠረበት አረመኔ መሆኑን እንኳን እኔ በታክሲ ስራ ምክንያት ከተማ ውስጥ ስቅበዘበዝ የምውል ከቤት የማይወጣ የሰፈራችን ሰው ቢኖር እንኳን ስለዚህ ሰውዬ ለመስማት መጠየቅ አይጠበቅበትም ስለሰፈራችን ሀብታሞች ከተወራ የሚወራ ብዙ ነገር ያለው እሱ ነው።
ባጠቃላይ ሰባት ልጆች አሉት። እናት አባቶቻችን ስለሱ ሲያወሩ•••
" ሀብታም የሆነው አንድ ልጁን ለሰይጣን ገብሮ ነውኮ ልጁ መፍዙዝ ሆኖ ግቢያቸው ውስጥ ካለች አንድ ክፍል ውስጥ ጫቱን ሲደፈልቅ ውሎ ነው እሚያድረው ወደውጪ ሳሰማይወጣ ሰው አያውቀውም!" ሲሉ ሰምቻለሁ
ለሀብት ሲል የገዛ ልጁን እንደዛ ያረገ ሰው ደግሞ ለምድር ቆይታው በቀሩት የተገባደዱ ቀሪ እንጥፍጣፊ አመታት የልጁ ታናሽ እና እኩያ የሚሆኑ ሴት እህቶቻችንን በገንዘብ ሀይል ጨርሶ ለማለቅ ባይሽቀዳደም ነበር እሚገርመኝ!።
ምን እንደማደርግ ግራ ገባኝ ስለዚህ ሰው ማንነት እያወኩ ቢሳካም ባይሳካም ልጅቷን ከሱ ለማስጣል ሳልሞክር ወደቤቴ ብሄድ የሰላም እንቅልፍ እንደማይወሰደኝ ምናልባትም እስክረሳው እና ባስታወስኩት ቁጥር የጥፋተኝነት ስሜት እንደሚለበልበኝ አውቀዋለሁ ።
የሆነ ነገር መሞከር አለብኝ አልኩ ለራሴ ሞክሬ ካቅሜ በላይ ሆኖ ባይሳካ እንኳን ከህሊና ክስ እተርፋለሁ!
አካሄዴን ከማጣራት መጀመር እንዳለብኝ አስብኩ ምክንያቱም መሲ የዚህ አገር ልጅ ስለሆነች ዘመዱ ብትሆንስ አብራቸው ያለችው ልጅ ደግሞ የነ ኤዱ ጓደኛ ትግስት ባትሆንስ?
እዛው ባጃጄ ውስጥ እንዳለሁ ኤዱ ጋር ደወልኩ
አነሳችው። ግዜ ሳላጠፋ ቀጥታ ወደገደለው ገባሁ•••
ኤዱ የጓደኛሽን የትግስትን ፎቶ በቴሌግራም ላኪሊኝ
"ለምን ? ምነው? በሰላም ነው?"
አዎ በሰላም ነው አፍጥኚው!
ላከችልኝ። ትግስት ናት ብላ ኤዱ የላከችው ፎቶና አሁን በዚህ ሰአት ከነመሲ ጋር ያለችው ልጅ ጭራሽ አይገናኝም!
ሌላ ነች ማለት ነው? የግቢ ልጅ ትሆን ? በራሴ ጥያቄዎች ስወዛገብ ኤዱ ደወለች•••
ወዬ ኤዱ
"ምንድን ነው እሱ?" አለችኝ ያየሁትን ነገርኳት
"እስቲ የልጅቷን መልክ ንገረን "አለች።
ከረዱ ጋር አብረው እንደሆኑ ገባኝ ምናልባትም ስልኳን ድምፅ ማጉያ ላይ አድርጋው ለሁለት እየሰሙኝ ነው።
የልጅታን መልክ ማብራራቴን ጀመርኩ•••
ልጅቷማ ደስ የሚል ቅጥነት ያላት! ፀጉሯን ብራውን የተቀባች በጣም ቀይ ! አፍንጫዋ •••
እያልኩ ከአናቷ ጀምሬ ቁልቁል ልወርድላት ስል ካንገቷ ሳልሻገር ልጅቷን አወቋት መሰለኝ ቆይ ቆይ አንዴ ቴሌግራም ላይ ገባና ጠብቀኝ ብላ መልሴን ሳትሰማ ስልኩን ጠረቀመችው።
የላከችው ፎቶ ቴሌግራሜ ላይ እንደገባ በፍጥነት በረገድኩት እሚገርመው ልጅቷ እሄን ፎቶ ከለቀቀች ቡሀላ ፎቶው ላይ ያለውን ልብሷን ሳትቀይር ነው ወደጭፈራ ቤቱ የመጣችው ምናልባትም ወደዚህ አምሮባት ስትመጣ ተነስታ ቴሌግራሟ ላይ ለቃው ይሆናል።
ኤዱ እሄን ፎቶ ኬት ነው ያገኘሽው?
"ዛሬ ቀን ዘጠኝ ሰአት አከባቢ ነው የፌስ ቡክ ፕሮፋይል ፒክቸሯን የቀየረችው ከዛ ላይ እስክሪን ሹት አድርጌ ነው የላኩልህ ምነው ልጅቷ እራሷ ነች እንዴ ዳንዬ!?
አዎ እሷ ናት ስላቸው ሁለቱም ጮሁ!!
ምንድን ነው ምንሆናችሁ ኤዱ?
ቆይ እሷ ትንገርህ እንቺ ብላ ስልኩን ለረድኤት ሰጠቻት •••
" መሲ በመጨረሻም ተሳክቶላት እቺን ልጅ ወጥመዷ ውስጥ ጣለቻት እኔ አላምንም! "
ማለት? አልኳት።
ግራ ገብቶኝ አንቺ ኤዱ እና ትግስትስ በወጥመዷ ውስጥ ገብታችሁ የለ እንዴ
የሚለውን ሀሳብ ለራሴ እያወራሁት ቀጠለች•••
"አንድ ቀን ልጅቷ ባጠገባችን ስታልፍ መሲ ልጅቷን በክፉ አይን ስታያት አየሁና ምነው? ስላት•••
እቺ ልጅ ለጓደኛዋ ድንግል ነኝ የጀመርኩት ነገር የለም ማለቷን ሰምቼ ላጠምዳት ብሞክርም ገገማ አሳ ሆነችብኝ!።
ጋደኛዋ በኔ ቀመር እየተሽቀረቀረች ልታስቀናት ብትሞክርም ልጅቷ አልሞቅ አልደንቅ እንዳላት ነገረችኝ አሁን ሳያት ታስጠላኛለች !
" ብላ ስትነግረኝ •••
ምነው የኔ አይን አርፎባት! ለሆነ ቢዝነስ አቀባብያት ! ሳልተኩሳት የምትክሽፍብኝ ሴት የለችም ስትይ አልነበር እንዴ ታድያ እቺ እንዴት ከሸፈችብሽ ? ስላት
ኮሚሽን ሼር ሳላደርግ ለብቻዬ ማጣጣም ስለፈለኩ እንጂ እኔ መሲ እልህ ውስጥ ከገባሁ የትኛዎም የግቢ ሴት በዘረጋሁላት መረብ ላይ መወዘፏ የማይቀር ነው! "
ኮሚሽን ሼር ላለማረግ ስትል ምን ለማለት ፈልጋ እንደሆነ ጠየኳት እንዲህ አለች•••
እቺ ልጅ ጋደኛዋ ብትሽቀረቀር ብትብለጨለጭ ብልጭ አይልባትም አደል ስለዚህ እቺን በብልጭልጭ ነገር ማጥመድ አይቻልም ለእንደዚህ አይነት ሴቴች ደግሞ እቅድ ሁለት (ፕላን ቢን) እጠቀማለሁ የቱንም ፈተና ብትቋቋም ያንን መቋቋም ይከብዳታል።
እንደዚች አይነቷን በሴት ሳይሆን በወንድ ታጠምጃታለሽ እንኳን የሷን የድንጋይን ልብ የሚያቀልጥ ስንት የድሬ ልጅ ሞልቷል እሄን ያህል እከፍልሀለሁ በግር በጇ ብለህ አጥምዳት ብለው ሁለት ሳምንት ባልሞላ ግዜ ውስጥ አምጣት ያልኩት ቦታ እያክለፈለፈ ያመጣልኛል ግን ከልጅቷ ሽያጭ ግማሹ የሱ ነው ያንን ነው ኮሚሽን ያልኩሽ ብላኝ ነበር ይገርማል በዛ መንገድ ሸውዳ እጇ አስገባቻት ማለት ነው!?"
ስትለኝ እልህ አንቀጠቀጠኝ !
በፍፁም አታስገባትም! ኡልኩና ስልኩን ዘጋሁባት!
ምናልባት ሰውየው በአይን ሊያውቀኝ ስለሚችል ባጃጄ ውስጥ ያለውን ጥቁር ኮፍያ አደረኩና እስከ ግንባሬ ዝቅ አድርጌ አጎበጥኩት !
ሰተት ብዬ ወደ ጭፈራ ቤቱ ገባሁና ከነሱ ትይዩ ኮርነር ላይ ተቀምጬ መጠጥ አዘዝኩ።
መሀላቸው ጎልተው ግራ እንዳጋቧት የሚቅበዘበዘው ፊቷ ይመስክራል ። ምናልባቷ አጥምዶ ያስረከባት ልጅ መጣሁ ብሎ በመውጣት በዛው ቀርቶባት ይሆን አስሬ ዘወር ዘወር እያለች እምታየው? አንጀቴን በላችኝ !!
እየጠጣሁ ሁለቱን አውሬዎች ባየኋቸው ቁጥር ንዴቴ እየጨመረ መጣ!
ሰውየው ያንን በድሜ ብዛት ቶሎ ቶሎ ኩበት እየሆነ የሚያስቸግረውን ከንፈሩን በምራቁ ለማውዛት እየመጠጠ ያቺን አንድ ፍሬ ልጅ ለማሽኮርመም ሲታገል ስመለከተው አለም አስጠላችኝ !
ተነስተህ በባክስ ወደ ጀርባው ዘርረውና ልጅቷን ይዘካት ውጣ ውጣ አለኝ።
መሲ ተነስታ ወደ ሽንት ቤት ስትሄድ ከጀርባ ተከተልኳት ! እሷ ከፊት እኔ ከውኋላ ወደ ሽንት ቤት እምትወስደው ቀጭና መንገድ መሀል ላይ እንደደረስን
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ጭፈራ ቤቱ ውስጠኛው ክፍል ውስጥ ገብቼ ስልኩን ሰጥቼው ልወጣ ሁለት እርምጃ እንደተራመድኩ ድንገት ወደ ቀኝ ገልመጥ ሳደርግ
ሁለት ሴቶችና አንድ የሰፈራችን ሀብታም ነጋዴ የተቀመጡበት ሶፋ ላይ አይኔ ተተክሎ ቀረ።
ደነገጥኩ!
ሰውየው የኤች አይ ቪ ኤድስ ተሻካሚ የሆነና ሚስቱ በዚሁ በሽታ የሞተችበት ሰው ነው ።
•••ሁለቱ ሴቶች ደግሞ አንዷ ጭራቋ ስትሆን አንዷ ደግሞ ምናልባት የነኤዱ ጓደኛ ሳትሆን አትቀርም ወይኔ ቲጂ እንዲህ አንድፍሬ ልጅ ነሽ ቆይ ኧረ •••
አልኩና እየተጣደፍኩ ከጭፈራ ቤቱ በመውጣት ሞባይሌን ከኪሴ አውጥቼ ፎቶ ማህደሩን ከፈትኩ አልተሳሳትኩም መሲ እራሷ ነች ከንፈሮቼን በሶስት ጣቶቼ ተጭኜ የመሲ ፎቶ ላይ እንዳፈጠጥኩ ወደ ባጃጄ ውስጥ ገብቼ ተቀመጥኩ ።
መደበኛ ስራዎ እሄ መሆኑን አውቃለሁ እኔን ያስደነገጠኝ አገር ምድሩ ሚስቱ በምን እንደሞተችና እሱም ምን እንዳለበት ከሚያውቀው ከዚህ ህሊና ቢስ ቀበጥ ጋር መተዋወቋ ነው።
ምንም የማያውቁ ከየቦታው የሚመጡ ፍሬሽ ተማሪዎችን እያቀረበችለት ሲጫወትባቸው ታየኝ እሷና እሱን ከዚህ ውጪ ምንም ሊያገናኛቸው እንደማይችል ግልፅ ነው ።
ሰውየው እንደሆነ ከመጨረሻዋ ልጅ እኩዮች ጋር ለመጋደም ፈሪሀ ህሊንም ሆነ ፈሪሀ ፈጣሪ ያልፈጠረበት አረመኔ መሆኑን እንኳን እኔ በታክሲ ስራ ምክንያት ከተማ ውስጥ ስቅበዘበዝ የምውል ከቤት የማይወጣ የሰፈራችን ሰው ቢኖር እንኳን ስለዚህ ሰውዬ ለመስማት መጠየቅ አይጠበቅበትም ስለሰፈራችን ሀብታሞች ከተወራ የሚወራ ብዙ ነገር ያለው እሱ ነው።
ባጠቃላይ ሰባት ልጆች አሉት። እናት አባቶቻችን ስለሱ ሲያወሩ•••
" ሀብታም የሆነው አንድ ልጁን ለሰይጣን ገብሮ ነውኮ ልጁ መፍዙዝ ሆኖ ግቢያቸው ውስጥ ካለች አንድ ክፍል ውስጥ ጫቱን ሲደፈልቅ ውሎ ነው እሚያድረው ወደውጪ ሳሰማይወጣ ሰው አያውቀውም!" ሲሉ ሰምቻለሁ
ለሀብት ሲል የገዛ ልጁን እንደዛ ያረገ ሰው ደግሞ ለምድር ቆይታው በቀሩት የተገባደዱ ቀሪ እንጥፍጣፊ አመታት የልጁ ታናሽ እና እኩያ የሚሆኑ ሴት እህቶቻችንን በገንዘብ ሀይል ጨርሶ ለማለቅ ባይሽቀዳደም ነበር እሚገርመኝ!።
ምን እንደማደርግ ግራ ገባኝ ስለዚህ ሰው ማንነት እያወኩ ቢሳካም ባይሳካም ልጅቷን ከሱ ለማስጣል ሳልሞክር ወደቤቴ ብሄድ የሰላም እንቅልፍ እንደማይወሰደኝ ምናልባትም እስክረሳው እና ባስታወስኩት ቁጥር የጥፋተኝነት ስሜት እንደሚለበልበኝ አውቀዋለሁ ።
የሆነ ነገር መሞከር አለብኝ አልኩ ለራሴ ሞክሬ ካቅሜ በላይ ሆኖ ባይሳካ እንኳን ከህሊና ክስ እተርፋለሁ!
አካሄዴን ከማጣራት መጀመር እንዳለብኝ አስብኩ ምክንያቱም መሲ የዚህ አገር ልጅ ስለሆነች ዘመዱ ብትሆንስ አብራቸው ያለችው ልጅ ደግሞ የነ ኤዱ ጓደኛ ትግስት ባትሆንስ?
እዛው ባጃጄ ውስጥ እንዳለሁ ኤዱ ጋር ደወልኩ
አነሳችው። ግዜ ሳላጠፋ ቀጥታ ወደገደለው ገባሁ•••
ኤዱ የጓደኛሽን የትግስትን ፎቶ በቴሌግራም ላኪሊኝ
"ለምን ? ምነው? በሰላም ነው?"
አዎ በሰላም ነው አፍጥኚው!
ላከችልኝ። ትግስት ናት ብላ ኤዱ የላከችው ፎቶና አሁን በዚህ ሰአት ከነመሲ ጋር ያለችው ልጅ ጭራሽ አይገናኝም!
ሌላ ነች ማለት ነው? የግቢ ልጅ ትሆን ? በራሴ ጥያቄዎች ስወዛገብ ኤዱ ደወለች•••
ወዬ ኤዱ
"ምንድን ነው እሱ?" አለችኝ ያየሁትን ነገርኳት
"እስቲ የልጅቷን መልክ ንገረን "አለች።
ከረዱ ጋር አብረው እንደሆኑ ገባኝ ምናልባትም ስልኳን ድምፅ ማጉያ ላይ አድርጋው ለሁለት እየሰሙኝ ነው።
የልጅታን መልክ ማብራራቴን ጀመርኩ•••
ልጅቷማ ደስ የሚል ቅጥነት ያላት! ፀጉሯን ብራውን የተቀባች በጣም ቀይ ! አፍንጫዋ •••
እያልኩ ከአናቷ ጀምሬ ቁልቁል ልወርድላት ስል ካንገቷ ሳልሻገር ልጅቷን አወቋት መሰለኝ ቆይ ቆይ አንዴ ቴሌግራም ላይ ገባና ጠብቀኝ ብላ መልሴን ሳትሰማ ስልኩን ጠረቀመችው።
የላከችው ፎቶ ቴሌግራሜ ላይ እንደገባ በፍጥነት በረገድኩት እሚገርመው ልጅቷ እሄን ፎቶ ከለቀቀች ቡሀላ ፎቶው ላይ ያለውን ልብሷን ሳትቀይር ነው ወደጭፈራ ቤቱ የመጣችው ምናልባትም ወደዚህ አምሮባት ስትመጣ ተነስታ ቴሌግራሟ ላይ ለቃው ይሆናል።
ኤዱ እሄን ፎቶ ኬት ነው ያገኘሽው?
"ዛሬ ቀን ዘጠኝ ሰአት አከባቢ ነው የፌስ ቡክ ፕሮፋይል ፒክቸሯን የቀየረችው ከዛ ላይ እስክሪን ሹት አድርጌ ነው የላኩልህ ምነው ልጅቷ እራሷ ነች እንዴ ዳንዬ!?
አዎ እሷ ናት ስላቸው ሁለቱም ጮሁ!!
ምንድን ነው ምንሆናችሁ ኤዱ?
ቆይ እሷ ትንገርህ እንቺ ብላ ስልኩን ለረድኤት ሰጠቻት •••
" መሲ በመጨረሻም ተሳክቶላት እቺን ልጅ ወጥመዷ ውስጥ ጣለቻት እኔ አላምንም! "
ማለት? አልኳት።
ግራ ገብቶኝ አንቺ ኤዱ እና ትግስትስ በወጥመዷ ውስጥ ገብታችሁ የለ እንዴ
የሚለውን ሀሳብ ለራሴ እያወራሁት ቀጠለች•••
"አንድ ቀን ልጅቷ ባጠገባችን ስታልፍ መሲ ልጅቷን በክፉ አይን ስታያት አየሁና ምነው? ስላት•••
እቺ ልጅ ለጓደኛዋ ድንግል ነኝ የጀመርኩት ነገር የለም ማለቷን ሰምቼ ላጠምዳት ብሞክርም ገገማ አሳ ሆነችብኝ!።
ጋደኛዋ በኔ ቀመር እየተሽቀረቀረች ልታስቀናት ብትሞክርም ልጅቷ አልሞቅ አልደንቅ እንዳላት ነገረችኝ አሁን ሳያት ታስጠላኛለች !
" ብላ ስትነግረኝ •••
ምነው የኔ አይን አርፎባት! ለሆነ ቢዝነስ አቀባብያት ! ሳልተኩሳት የምትክሽፍብኝ ሴት የለችም ስትይ አልነበር እንዴ ታድያ እቺ እንዴት ከሸፈችብሽ ? ስላት
ኮሚሽን ሼር ሳላደርግ ለብቻዬ ማጣጣም ስለፈለኩ እንጂ እኔ መሲ እልህ ውስጥ ከገባሁ የትኛዎም የግቢ ሴት በዘረጋሁላት መረብ ላይ መወዘፏ የማይቀር ነው! "
ኮሚሽን ሼር ላለማረግ ስትል ምን ለማለት ፈልጋ እንደሆነ ጠየኳት እንዲህ አለች•••
እቺ ልጅ ጋደኛዋ ብትሽቀረቀር ብትብለጨለጭ ብልጭ አይልባትም አደል ስለዚህ እቺን በብልጭልጭ ነገር ማጥመድ አይቻልም ለእንደዚህ አይነት ሴቴች ደግሞ እቅድ ሁለት (ፕላን ቢን) እጠቀማለሁ የቱንም ፈተና ብትቋቋም ያንን መቋቋም ይከብዳታል።
እንደዚች አይነቷን በሴት ሳይሆን በወንድ ታጠምጃታለሽ እንኳን የሷን የድንጋይን ልብ የሚያቀልጥ ስንት የድሬ ልጅ ሞልቷል እሄን ያህል እከፍልሀለሁ በግር በጇ ብለህ አጥምዳት ብለው ሁለት ሳምንት ባልሞላ ግዜ ውስጥ አምጣት ያልኩት ቦታ እያክለፈለፈ ያመጣልኛል ግን ከልጅቷ ሽያጭ ግማሹ የሱ ነው ያንን ነው ኮሚሽን ያልኩሽ ብላኝ ነበር ይገርማል በዛ መንገድ ሸውዳ እጇ አስገባቻት ማለት ነው!?"
ስትለኝ እልህ አንቀጠቀጠኝ !
በፍፁም አታስገባትም! ኡልኩና ስልኩን ዘጋሁባት!
ምናልባት ሰውየው በአይን ሊያውቀኝ ስለሚችል ባጃጄ ውስጥ ያለውን ጥቁር ኮፍያ አደረኩና እስከ ግንባሬ ዝቅ አድርጌ አጎበጥኩት !
ሰተት ብዬ ወደ ጭፈራ ቤቱ ገባሁና ከነሱ ትይዩ ኮርነር ላይ ተቀምጬ መጠጥ አዘዝኩ።
መሀላቸው ጎልተው ግራ እንዳጋቧት የሚቅበዘበዘው ፊቷ ይመስክራል ። ምናልባቷ አጥምዶ ያስረከባት ልጅ መጣሁ ብሎ በመውጣት በዛው ቀርቶባት ይሆን አስሬ ዘወር ዘወር እያለች እምታየው? አንጀቴን በላችኝ !!
እየጠጣሁ ሁለቱን አውሬዎች ባየኋቸው ቁጥር ንዴቴ እየጨመረ መጣ!
ሰውየው ያንን በድሜ ብዛት ቶሎ ቶሎ ኩበት እየሆነ የሚያስቸግረውን ከንፈሩን በምራቁ ለማውዛት እየመጠጠ ያቺን አንድ ፍሬ ልጅ ለማሽኮርመም ሲታገል ስመለከተው አለም አስጠላችኝ !
ተነስተህ በባክስ ወደ ጀርባው ዘርረውና ልጅቷን ይዘካት ውጣ ውጣ አለኝ።
መሲ ተነስታ ወደ ሽንት ቤት ስትሄድ ከጀርባ ተከተልኳት ! እሷ ከፊት እኔ ከውኋላ ወደ ሽንት ቤት እምትወስደው ቀጭና መንገድ መሀል ላይ እንደደረስን
👍1
#ልጩህበት!!
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ተነስተህ በቦክስ ወደ ጀርባው ዘርረውና ልጅቷን ይዘኃት ውጣ ውጣ አለኝ።
መሲ ተነስታ ወደ ሽንት ቤት ስትሄድ ከጀርባ ተከተልኳት ! እሷ ከፊት እኔ ከኋላ ወደ ሽንት ቤት እምትወስደው ቀጭን መንገድ መሀል ላይ እንደደረስን ከጀርብዬ ኮቴ ሳያሰማ ማጅራቴ አከባቢ •••
ኮሌታዬን ቀብ ሲያደርገኝ በድንጋጤ መንጭቄው በፍጥነት ዞርኩ!
"ክክክ አንተ ምነው ? ሊያጠቃኝ ይችላል ብለህ የምታስበው ጠላት አለህ እንዴ?
ተፈናጠርክ እኮ ካካካ•••!"
ኮንትራት የያዘኝ ሰውዬ ነበር። የሚገርመው እራሴ አምጥቼው ሳበቃ እዛ ጭፈራ ቤት የውስጠኛው ክፍል ውስጥ መኖሩን ጭራሽ ረስቼዋለሁ!
ወደ ወንዶች ሽንት ቤት ጎን ለጎን እየሄድን •••
"ደሞ ደክሞኛል ገብቼ ተኛለሁ ባጃጅ ከፈለክ ብለህ ሌላ ስልክ ሰጥተከኝ አልነበር እንዴ የሄድከው ነው ወይስ ሞባይሉን ሰጠኸኝ ስትወጣ አንዷ ጠልፋህ ነው? መሆን አለበት ! እዚ ቤት ያሉ ሴቶች እኮ ልዩ ናቸው እንኳን
እዚህ ድረስ እራሱ የመጣውን ሰው በአየር ላይ ፖይለቱን አማሎ አውሮፕላን ለመጥለፍ ወደኋላ የማይል ውበት ነው ያላቸው ቆይ የጭፈራ ቤቱ ባለቤት የቁንጅና ውድድር አዘጋጅቶ ከአንድ እስከ አምስት የሚወጡትን ነው እንዴ የሚቀጥረው! ካካካ!"
ኧረ መቆለል አልኩና በሆዴ !
ኧረ አይደለም ባጋጣሚ ነው አልኩት ሸንተን ስንመለስ•••
"ምኑ ነው አጋጣሚ ቆንጆዎች መሆናቸው?"
አይ የኔ እዚህ መከሰት!
"እና ብቻህን ነህ ብቻህን ከሆንክ ለምን ውስጥ እኔጋ አለመጣህም " እያለ አቁሞ ሲነዘንዘኝ መሲ ከሽንት ቤት ወጥታ እየተውረገረገች ባጠገባችን አለፈች። አፈጠጥኩባት ።
እሱም በሚስቁት አይኖቹ እኔ ላይ አፈጠጠብኝ ።
"ተመለስክ?!"
ኬት ?
"ከልጅቷ ላይ ነዋ!"
አዎ አልኩት ፈገግ ብዬ !
በል ና እሄንን እማ እየጠጣን ነው መስማት የምፈልገው ናናናና !" እያለ እጄን እንደያዘ ወደ ውስጥ ገባን።
እዛ የተገኘሁበትን እውነት ልንገረው? አልንገው ? ብነግረውስ ምን ብዬ ልንገረው? ምናልባት ጥሬ እውነቱን እንደወረደ ስነግረው ምናልባት እኔን የተሰማኝ ስሜት ካልተሰማው•••
"ቆይ ከልጅቷ ጋር ዘመድ ናችሁ?"
ኧረ አይደለንም ።
"ትውውቅ አላችሁ ማለት ታውቃታለህ ?"
አይ!
"እሺ ቆይ ልጅቷን ወደሀታል?'
ኧረ በጭራሽ!
"ታድያ ምን አግብቶህ ነው እዚህ ሁሉ ፈተና ውስጥ እራስህን የምትከተው?!" ቢለኝስ!
እኔ የሴቶች እህቶቼ ጉዳትና ጥቃት እንደሚያገባኝ አምናለሁ ይሄ የሚያገባቸው የማይመስላቸው እሄን ምን አገባኝ እያሉ ነገር ግን በማያገባቸው ብዙ ነገሮች ውስጥ እጃቸውን የሚያስገቡ ሰዎች በዙርያችን ብዙ ናቸው።
የሴት ጥቃት አይመለከተኝም እያሉ የአርሰናል መጠቃት የሚያደባድባቸው በሞሉባት ሀገራችን
አላውቃትም!
ዝምድናም የለንም!
አልወደድኳትም!
እያልክ ለሷ መቆም እንቆቅልሽ የሚሆንበትና ምን አገባህ የሚልህ ቢያጋጥምህ ምን ይገርማል?!
ምንም!።
ስለዚህ ምን ልበለው? በቀላሉ የሚፋታኝ አይመስለኝም ።
"ምናገባህ!" እንዳይለኝ ትንሽ ቀየር አድርጌ ልነግረው ወሰንኩና•••
ይሄውልህ ቅድም ሞባይሉን ሰጥቼህ ስወጣ የአንደኛ አመት የዩንቨርስቲ ተማሪ የሆነችውን የአክስቴን ልጅ ከማይሆን ሰው ጋር አየኋት!
ከኔ ጋር ከተጣላን አመት ሆኖናል። ተኮራርፈናል። አንነጋገርም ግን ብንጣላም ስለሰውየው በደንብ ስለማውቅ ጥያት በጭራሽ አልገባም ልጅቷ እንደዚህ አይነት አመል የላትም እርግጠኛ ነኝ ቅድም የገላመጥኳት ልጅ በሆነ መንገድ ሸውዳ አምጥታለት ነው •••
አልኩና ስለመሲና ስለሰውየው በዝርዝር ነገርኩት።
እሄን ግዜ ሰውየው ከኔ በላይ የተቆጣ ነብር ሆኖ ቁጭ አለ። ፊቱ ተለዋወጠ።
"በቃ ይሄን ጉዳይ ለኔ ተወው አንተ ዝምበልና ቁጭ ብለህ ጠጣ!"
ማለት ምን ልታደርግ ነው?!
"ዝም ብለህ ጠጣ! ብዬሀለሁ ዝም ብለህ ጠጣ!" አለኝ ክርድድ ባለ ድምፅ።
ድሮም ነገረ ስራው ግራ ነበር የሚገባኝ አሁን ደግሞ ባንዴ ሲለዋወጥብኝ እኔ እራሴ ፈራሁት ።
ካጠገቤ ሄዶ እነመሲን ከሩቁ አይቷቸው ተመለሰ።
ከደቂቃዎች በኋላ ከነመሲ ጋር ያለው ሰውዬ ቦርጩን እያሻሸ ወደ ሽንት ቤት ሲያልፍ እኩል እየነው! ተያየን••ኀ
"እሄ አሁን ያለፈው ነው አደለ?
"አዎ ግን ምን ልታደርግ ነው?
"አቢቲ አማርኛዬ አልገባ ካለህ የፈለከውን የሚገባህን ቋንቋ ንገረኝና በሱ ላስረዳህ ከዚህ በኋላ ለኔ ተወው የትም እንዳትንቀሳቀስ እዚሁ ቁጭ ብለህ እየጠጣህ ጠብቀኝ !"
ብሎኝ ሰውየውን ተከትሎ ወደ ሽንት ቤት ሄደ።
ብዙም ሳይቆይ ተመልሶ መጣና ምንም ሳይለኝ መጠጣት ጀመረ
ወደሽንት ቤት የሄደውን ሰውዬ ካሁን ካሁን ይመለሳል ብዬ ብጠብቅም አልተመለሰም ጨነቀኝ እንዴ ምን አርጎት መጣ? ግራ ገባኝ
ምን አልከው ሰውየው እኮ ብር ያጠገበው ባለጌ ነው ምን አለህ? ስለው•••
መልስ ሳይሰጠኝ እሄን ውስኪ እንደውሃ እየጠጣ •••
"ጠጣ ጠጣ ያቺን አየሀት ዝም ብላ እያየችህ ነው አብረካት መደነስ ትፈልጋለህ ልጥራት እንዴ?"
አለኝ ጥግ ኮርነር ላይ ካሉት ሴቶች መሀል ወደኛ እያየች ወደምትናጠው ሴት እያመለከተኝ
ወይ መደነስ እኔ ሰውየው እምጥ ይግባ ስምጥ ሄዶ ካናገረው በኋላ ከሽንት ቤት ባለመመለሱ ምን አርጎት ነው የመጣው እያልኩ ግራ ተጋብቻለሁ ጭራሽ ደንስ ይለኛል ምን አይነት ባህሪ ያለው ሰው ነው እሄ ደግሞ ቢያንስ እንኳን የኔ ጭንቀት ለምን አይገባውም እንዴ በራሴ ጉዳይ ዝም በል ጠጣ ደንስ ስላለኝ ዝም የምል ይመስለዋል?!
ወደ ሽንት ቤት ሌላ ሰው በሄደ እና በወጣ ቁጥር እያየሁ በጭንቀት ከመፈንዳቴ በፊት እራሴ ሄጄ ለማረጋገጥ ስለፈለኩ•••
••• እሺ መጣሁ አንዴ ስመለስ አብሪያት እደንሳለሁ አልኩትና ሄድኩ መጀመሪያ ወደነመሲ ገልመጥ ሳደርግ ሁለቱ ብቻ ናቸው እነሱም እንደኔ ሰውየው የት ሄደ ብለው ግራ ተጋብተዋል መሰለኝ ግራና ቀኝ ይገላመጣሉ ።
ወደ ወንዶች ሽንት ቤት በፍጥነት ሄድኩና ከአምስቱ ሽንት ቤቶች መሀከል ክፍት የሆኑትን ሁለቱን አየት አድርጌ በማለፍ ሶስተኛውን ስበረግደው•••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ተነስተህ በቦክስ ወደ ጀርባው ዘርረውና ልጅቷን ይዘኃት ውጣ ውጣ አለኝ።
መሲ ተነስታ ወደ ሽንት ቤት ስትሄድ ከጀርባ ተከተልኳት ! እሷ ከፊት እኔ ከኋላ ወደ ሽንት ቤት እምትወስደው ቀጭን መንገድ መሀል ላይ እንደደረስን ከጀርብዬ ኮቴ ሳያሰማ ማጅራቴ አከባቢ •••
ኮሌታዬን ቀብ ሲያደርገኝ በድንጋጤ መንጭቄው በፍጥነት ዞርኩ!
"ክክክ አንተ ምነው ? ሊያጠቃኝ ይችላል ብለህ የምታስበው ጠላት አለህ እንዴ?
ተፈናጠርክ እኮ ካካካ•••!"
ኮንትራት የያዘኝ ሰውዬ ነበር። የሚገርመው እራሴ አምጥቼው ሳበቃ እዛ ጭፈራ ቤት የውስጠኛው ክፍል ውስጥ መኖሩን ጭራሽ ረስቼዋለሁ!
ወደ ወንዶች ሽንት ቤት ጎን ለጎን እየሄድን •••
"ደሞ ደክሞኛል ገብቼ ተኛለሁ ባጃጅ ከፈለክ ብለህ ሌላ ስልክ ሰጥተከኝ አልነበር እንዴ የሄድከው ነው ወይስ ሞባይሉን ሰጠኸኝ ስትወጣ አንዷ ጠልፋህ ነው? መሆን አለበት ! እዚ ቤት ያሉ ሴቶች እኮ ልዩ ናቸው እንኳን
እዚህ ድረስ እራሱ የመጣውን ሰው በአየር ላይ ፖይለቱን አማሎ አውሮፕላን ለመጥለፍ ወደኋላ የማይል ውበት ነው ያላቸው ቆይ የጭፈራ ቤቱ ባለቤት የቁንጅና ውድድር አዘጋጅቶ ከአንድ እስከ አምስት የሚወጡትን ነው እንዴ የሚቀጥረው! ካካካ!"
ኧረ መቆለል አልኩና በሆዴ !
ኧረ አይደለም ባጋጣሚ ነው አልኩት ሸንተን ስንመለስ•••
"ምኑ ነው አጋጣሚ ቆንጆዎች መሆናቸው?"
አይ የኔ እዚህ መከሰት!
"እና ብቻህን ነህ ብቻህን ከሆንክ ለምን ውስጥ እኔጋ አለመጣህም " እያለ አቁሞ ሲነዘንዘኝ መሲ ከሽንት ቤት ወጥታ እየተውረገረገች ባጠገባችን አለፈች። አፈጠጥኩባት ።
እሱም በሚስቁት አይኖቹ እኔ ላይ አፈጠጠብኝ ።
"ተመለስክ?!"
ኬት ?
"ከልጅቷ ላይ ነዋ!"
አዎ አልኩት ፈገግ ብዬ !
በል ና እሄንን እማ እየጠጣን ነው መስማት የምፈልገው ናናናና !" እያለ እጄን እንደያዘ ወደ ውስጥ ገባን።
እዛ የተገኘሁበትን እውነት ልንገረው? አልንገው ? ብነግረውስ ምን ብዬ ልንገረው? ምናልባት ጥሬ እውነቱን እንደወረደ ስነግረው ምናልባት እኔን የተሰማኝ ስሜት ካልተሰማው•••
"ቆይ ከልጅቷ ጋር ዘመድ ናችሁ?"
ኧረ አይደለንም ።
"ትውውቅ አላችሁ ማለት ታውቃታለህ ?"
አይ!
"እሺ ቆይ ልጅቷን ወደሀታል?'
ኧረ በጭራሽ!
"ታድያ ምን አግብቶህ ነው እዚህ ሁሉ ፈተና ውስጥ እራስህን የምትከተው?!" ቢለኝስ!
እኔ የሴቶች እህቶቼ ጉዳትና ጥቃት እንደሚያገባኝ አምናለሁ ይሄ የሚያገባቸው የማይመስላቸው እሄን ምን አገባኝ እያሉ ነገር ግን በማያገባቸው ብዙ ነገሮች ውስጥ እጃቸውን የሚያስገቡ ሰዎች በዙርያችን ብዙ ናቸው።
የሴት ጥቃት አይመለከተኝም እያሉ የአርሰናል መጠቃት የሚያደባድባቸው በሞሉባት ሀገራችን
አላውቃትም!
ዝምድናም የለንም!
አልወደድኳትም!
እያልክ ለሷ መቆም እንቆቅልሽ የሚሆንበትና ምን አገባህ የሚልህ ቢያጋጥምህ ምን ይገርማል?!
ምንም!።
ስለዚህ ምን ልበለው? በቀላሉ የሚፋታኝ አይመስለኝም ።
"ምናገባህ!" እንዳይለኝ ትንሽ ቀየር አድርጌ ልነግረው ወሰንኩና•••
ይሄውልህ ቅድም ሞባይሉን ሰጥቼህ ስወጣ የአንደኛ አመት የዩንቨርስቲ ተማሪ የሆነችውን የአክስቴን ልጅ ከማይሆን ሰው ጋር አየኋት!
ከኔ ጋር ከተጣላን አመት ሆኖናል። ተኮራርፈናል። አንነጋገርም ግን ብንጣላም ስለሰውየው በደንብ ስለማውቅ ጥያት በጭራሽ አልገባም ልጅቷ እንደዚህ አይነት አመል የላትም እርግጠኛ ነኝ ቅድም የገላመጥኳት ልጅ በሆነ መንገድ ሸውዳ አምጥታለት ነው •••
አልኩና ስለመሲና ስለሰውየው በዝርዝር ነገርኩት።
እሄን ግዜ ሰውየው ከኔ በላይ የተቆጣ ነብር ሆኖ ቁጭ አለ። ፊቱ ተለዋወጠ።
"በቃ ይሄን ጉዳይ ለኔ ተወው አንተ ዝምበልና ቁጭ ብለህ ጠጣ!"
ማለት ምን ልታደርግ ነው?!
"ዝም ብለህ ጠጣ! ብዬሀለሁ ዝም ብለህ ጠጣ!" አለኝ ክርድድ ባለ ድምፅ።
ድሮም ነገረ ስራው ግራ ነበር የሚገባኝ አሁን ደግሞ ባንዴ ሲለዋወጥብኝ እኔ እራሴ ፈራሁት ።
ካጠገቤ ሄዶ እነመሲን ከሩቁ አይቷቸው ተመለሰ።
ከደቂቃዎች በኋላ ከነመሲ ጋር ያለው ሰውዬ ቦርጩን እያሻሸ ወደ ሽንት ቤት ሲያልፍ እኩል እየነው! ተያየን••ኀ
"እሄ አሁን ያለፈው ነው አደለ?
"አዎ ግን ምን ልታደርግ ነው?
"አቢቲ አማርኛዬ አልገባ ካለህ የፈለከውን የሚገባህን ቋንቋ ንገረኝና በሱ ላስረዳህ ከዚህ በኋላ ለኔ ተወው የትም እንዳትንቀሳቀስ እዚሁ ቁጭ ብለህ እየጠጣህ ጠብቀኝ !"
ብሎኝ ሰውየውን ተከትሎ ወደ ሽንት ቤት ሄደ።
ብዙም ሳይቆይ ተመልሶ መጣና ምንም ሳይለኝ መጠጣት ጀመረ
ወደሽንት ቤት የሄደውን ሰውዬ ካሁን ካሁን ይመለሳል ብዬ ብጠብቅም አልተመለሰም ጨነቀኝ እንዴ ምን አርጎት መጣ? ግራ ገባኝ
ምን አልከው ሰውየው እኮ ብር ያጠገበው ባለጌ ነው ምን አለህ? ስለው•••
መልስ ሳይሰጠኝ እሄን ውስኪ እንደውሃ እየጠጣ •••
"ጠጣ ጠጣ ያቺን አየሀት ዝም ብላ እያየችህ ነው አብረካት መደነስ ትፈልጋለህ ልጥራት እንዴ?"
አለኝ ጥግ ኮርነር ላይ ካሉት ሴቶች መሀል ወደኛ እያየች ወደምትናጠው ሴት እያመለከተኝ
ወይ መደነስ እኔ ሰውየው እምጥ ይግባ ስምጥ ሄዶ ካናገረው በኋላ ከሽንት ቤት ባለመመለሱ ምን አርጎት ነው የመጣው እያልኩ ግራ ተጋብቻለሁ ጭራሽ ደንስ ይለኛል ምን አይነት ባህሪ ያለው ሰው ነው እሄ ደግሞ ቢያንስ እንኳን የኔ ጭንቀት ለምን አይገባውም እንዴ በራሴ ጉዳይ ዝም በል ጠጣ ደንስ ስላለኝ ዝም የምል ይመስለዋል?!
ወደ ሽንት ቤት ሌላ ሰው በሄደ እና በወጣ ቁጥር እያየሁ በጭንቀት ከመፈንዳቴ በፊት እራሴ ሄጄ ለማረጋገጥ ስለፈለኩ•••
••• እሺ መጣሁ አንዴ ስመለስ አብሪያት እደንሳለሁ አልኩትና ሄድኩ መጀመሪያ ወደነመሲ ገልመጥ ሳደርግ ሁለቱ ብቻ ናቸው እነሱም እንደኔ ሰውየው የት ሄደ ብለው ግራ ተጋብተዋል መሰለኝ ግራና ቀኝ ይገላመጣሉ ።
ወደ ወንዶች ሽንት ቤት በፍጥነት ሄድኩና ከአምስቱ ሽንት ቤቶች መሀከል ክፍት የሆኑትን ሁለቱን አየት አድርጌ በማለፍ ሶስተኛውን ስበረግደው•••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍1
#ልጩህበት!!
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ወይ መደነስ እኔ ሰውየው እምጥ ይግባ ስምጥ ሄዶ ካናገረው በኋ ላ ከሽንት ቤት ባለመመለሱ ምን አርጎት ነው የመጣው እያልኩ ግራ ተጋብቻለሁ ጭራሽ ደንስ ይለኛል ምን አይነት ባህሪ ያለው ሰው ነው እሄ ደግሞ ቢያንስ እንኳን የኔ ጭንቀት ለምን አይገባውም እንዴ በራሴ ጉዳይ ዝም በል ጠጣ ደንስ ስላለኝ ዝም የምል ይመስለዋል?!
ወደ ሽንት ቤት ሌላ ሰው በሄደ እና በወጣ ቁጥር እያየሁ በጭንቀት ከመፈንዳቴ በፊት እራሴ ሄጄ ለማረጋገጥ ስለፈለኩ•••
••• እሺ መጣሁ አንዴ ስመለስ አብሪያት እደንሳለሁ አልኩትና ሄድኩ መጀመሪያ ወደነመሲ ገልመጥ ሳደርግ ሁለቱ ብቻ ናቸው እነሱም እንደኔ ሰውየው የት ሄደ ብለው ግራ ተጋብተዋል መሰለኝ ግራና ቀኝ ይገላመጣሉ ።
ወደ ወንዶች ሽንት ቤት በፍጥነት ሄድኩና ከአምስቱ ሽንት ቤቶች መሀከል ክፍት የሆኑትን ሁለቱን አየት አድርጌ በማለፍ ሶስተኛውን ስበረግደው•••
----------
"ምን አይነት ሰው ነህ በናትህ! ምሽግ ውስጥ ነው እንዴ ያደከው? አታንኳኳም!" አለኝ በብስጭት አንድ የማላውቀው ሰው።
ይቅርታ ይቅርታ አልኩት ቆሌዬ ተገፎ!።
"ባክህ የምናባህ ይቅርታ ነው ይቅርታ ይላል እንዴ ደሞ የልቡን አድርሶ!" አለኝ።
ንግግሩ ሳቅ ጫረብኝ ።
አይይ ስካር ደጉ ታየኝ እኮ እሱን ሽንት ቤት ተቀምጦ በማየቴ የልቤ ሲደርስ እያልኩ ቀሪ ሁለቱ ክፍሎች ውስጥ ሰውየውን መፈለጌን ቀጠልኩ•••
ሰውየው ድራሹ የለም ። ግራ ተጋብቼ በቆምኩበት ሽንትቤቱን ድንገት ከፍቼበት የተበሳጨው ሰውዬ ቆየት እያለ ሲሳደብ ሰማሁት•••
እንዴ! እሄ ደሞ እያረፈ ነው እንዴ እሚሳደበው!
አልኩና ከውስጥ ዘግተህ አትቀመጥም ነበር ሰካራም! ብየው ወደ ቦታዬ ስመለስ የኮንትራት ደንበኛዬ (ዝም ብለህ ጠጣ ሲለኝ የነበረውን ሰው ) ቦታው ላይ አጣሁት።
የክፍሉን ዙርያ ገባ ቃኘት አደረኩ ። እክፍሉ ውስጥም የለም።
እየተደነባበርኩ እነመሲ ወዳሉበት ክፍል በር ስጠጋ •••
አይኔን ተጠራጠርኩት ! ሽንት ቤት ሰውየውን ፍለጋ ደርሼ እስክመጣ ከምኔው ሄዶ ከምኔው ተዋውቋቸው እና ተግባብቷቸው መሳሳቅ እንደጀመሩ ለማመን በሚከብድ ሁኔታ•••
እሱ ያወራል እነመሲ ይስቃሉ አሁንም ያወራል እነሱ ተያይተው ያሽካካሉ አፌን ከፍቼ ስመለከታቸው ቆየሁና እየሆነ ያለው ነገር ከመጠጡ ጋር ተደምሮ ትርምስምስ እንዳለብኝ ወደ ቦታዬ ተመለስኩ።
ትንሽ ቆየሁና እሱ አልመጣ ሲለኝ መኖር አለመኖራቸውን ላረጋግጥ ድጋሚ ሄድኩ።
ጭራሽ እሱና መሲ ተጣብቀው እየደነሱ ነው። ጀርባዋን ሰጥታው እላዩ ላይ ተጣብቃለች ወገቧን አቅፎ ማጅራቷ አከባቢ እንደመሳም እየቃጣው ለስለስ ባለው ሙዚቃ ይወዛወዛሉ ።
ልጅቷ ቦታዎ ላይ ተቀምጣ ትቁለጨለጫለች ።
ምናልባት አስጠማጇን እራሷን መሲን አጥምዶ ልጅቷን ሊያፋታት አስቦ ይሆን እንዴ?
ብዬ አሰብኩና የሆነ የደስታ ስሜት ውስጤን ሲነዝረው ታውቀኝ።
ሰውየውን ምን አድርጎት ነው? የሚለው ጥያቄ ስላልተመለሰልኝና ዝም ብለህ ጠጣ ከማለት ውጪ ምን እንዳደረገ? እና ምን ሊያደርግ እንዳሰበ በግልፅ ሊነግረኝ ፍቃደኛ ባለመሆኑ ግን ደስታዬ ብርዝ ሆነብኝ!!
በዳንሳችው መሀል ድንገት ተያየን ጠቀሰኝ እኔ ግን ግራ ተጋብቶ ያፈጠጠ እንጂ የሚጨፈን አይን አልነበረኝም እና ምኑም ላልገባኝ ጥቅሻው መልስ ነፈኩት ዝም ብዬው ከራሴ ጋር እያልጎመጎምኩ•••
ግራ አጋባኝ እኮ እሚገርም ሰው ነው እሄ ሰውዬ እያልኩ ወደ ቦታዩ ተመለስኩ ።
በተመለስኩ በደቂቃዎች ውስጥ ወደኔ በመምጣ
"ፈታ በል አቢቲ ዝም ብለህ አትጨናነቅ እኔ አንድ ነገር ላደርግ ካሰብኩ ውጤቱን እንጂ ጅማሬው ማውራት አልወድም! ለምን መሰለህ?••• መጀመራችንን እንጂ መጨረሳችንን የሚያውቀው ፈጣሪ ብቻ ስለሆነ በርግጥ አሁን ያሰብኩትን ነገር ፈጣሪ ሳይሆን ሰይጣን ነው አጨራረሱን የሚያሳምረው አየህ አንዳንዴ ጥሩ ነገር ለመስራት መጥፎ ነገር ውስጥ መግባቱ ግድ ይልሀል የስራህ ውጤት ከፊሉ የፈጣሪ ከፊሉ የሰይጣን ይሆናል ድብልቅ!
ነገር ግን ፈጣሪ ልብን ሰይጣን ስራን ይመረምራል ብዬ ስለማምን እሱ አያሳስበኝም ! ለማንኛውም ስጨርስ ሁሉንም ነገር እነግርሀለሁ አሁን አንተ አታስፈልገኝም ከሀያ ደቂቃ ቡሀላ በር ላይ ሁለት ባጃጅ እፈልጋለሁ ካንተ ጋር ካሁን ቡሀላ ምናልባት ነገ ካልሄድኩ እንገናኝ ይሆናል ብሎኝ ከኔ መልስ ሳይጠብቅ ጥሎኝ ሄደ ።
እንኳን ምን ለማለት እንደፈለገ ሊገባኝ ያለውን መልሼ ማስታወስ አልቻልኩም።
አንዳንድ ሰዎችን ትንሽ ግዜ አብረሀቸው በቆየህ ቁጥር ወይ በደንብ ታውቃቸዋለህ ወይ ጭራሽ እንደማታውቃቸው ይገባሀል የሚለው የጆሲ ጋደኛ ትዝ አለኝ።
ያለኝ አማራጭ መወዛገቤን ትቼ እስከመጨረሻው የሚሆነውን ነገር መመልከት ብቻ ሆነ።
ካስር ደቂቃ ቡሀላ ኮፍያዬን አዘቅዝቄ አንገቴን አቀርቅሬ ከጭፈራ ቤቱ በፍጥነት ወጣሁ ።
ከማውቃቸው በዛ ሰአት ስራ ላይ ይሆናሉ ብዬ ወዳሰበኳቸው ሁለት የባጃጅ ሹፌሮች ደወልኩና በር ላይ እንዲጠብቁአቸው ነግሬ እኔ ራቅ ብዬ ባጃጄ ውስጥ እንዳደፈጥኩ ስጠባበቅ ልክ ባለው ሰአት መሲ እና እሱ ተቃቅፈው ግራና ቀኝ እየትወዛወዙ እና እየተሳሳቁ ልጅቷም በሁኔታቸው አብራ ፈገግ እያለች ወደ ጎን ተደርድረው ከጭፈራ ቤቱ ሲቅወጡ ተመለከትኩ።
ባጃጆቹ ጋር እንደደረሱ ሰውየው ያቀፋትን መሲን ለቅቅ አድርጎ ወደ ልጅታ ተጠጋና አናገራት። ጨብጣው ከፉት ያለው ባጃጅ ውስጥ ጥልቅ አለች እሱና መሲ ሌላኛው ባጃጅ ውስጥ ገቡና ፊትና ኋላ ሆነው ተፈተለኩ እኔም ተከትያቸው ተፈተለኩ ።
በቅርብ እየተከተልኳቸው ልጅቷን ወደ ያዘው የባጃጅ ሹፌር ደወልኩ ። አነሳው።
ምን አለህ? ስለው•••
"ግቢ አድርሳት አለኝ ወደ ግቢ እየወሰድኳት ነው " አለኝ ። በረጅሙ ተነፈስኩ እና ጀግና አቦ አልኩት ግራ ያጋባኝን ሰው።
ወደ ግቢ የሚሄደው ባጃጅና እነመሲን የያዘው ባጃጅ የሚለያዩበት ቦታ ላይ ደረሱ ልጅቷን የያዘው በዲፖ በኩል ሽቅብ ወደ ሰይዶ ሲሸመጥጠው እነመሲን የያዘው ባጃጅ በፀሀይ ሆቴል በኩል ቁልቁል ቆሰቆሰው•••
ወደያዘው ክፍል ይዟት እየሄደ መሆኑን ብረዳም ልጅቷን ትቼ የመሲን መጨረሻ ለማየት ተከተልኳቸው ።
ደረሱ ። ከባጇጃ ወርደው የሰከረችውን መሲን ከመሸከም በማይተናነስ ሀኔታ ደግፎ ወደያዘው ክፍል አስገባት ።
ለሰው ያጠመድሽው እራስሽ ላይ ባርቆ ሊዘርርሽ ነው አይ መሲ !
እያልኩ ወደ ቤቴ ገብቼ ተዘረርኩ ጥዋት ሶስት ሰአት ላይ የቀሰቀሰኝ የስልኬ ጥሪ ነበር ሰውየው ነው በፍጥነት አንስቼው ሀሎ ስል•••
" ደና አደርክ አቢቲ ተመልሼ ወደመጣሁበት እየሄድኩ ነው ምናልባት ከስድስት ወር ቡሀላ እመጣ ይሆናል የማታውን ሙሉ ትያትር ለማየት እና ለመስማት እንደምትፈልግ አውቃለሁ ቴሌግራምህን ክፈት ሶስት መልእክቶች አሉህ በድምፅ! በፅሁፍና; በምስል! ቻው !!"ብቻ ብሎኝ ስልኩን ዘጋው•••
በፍጥነት ቴሌግራም አካውንቴን ስበረግደው ቀድሞ የታየኝ የመሲ ልብስ አልባ ገላ የሚያሳየው ቪድዬ ነበር ከስር የመሲን ስልክ ቁጥር አስቀምጦ
"አቢቲ በዚህ ቁጥሯ የተከፈተ ቴሌግራም አካውንቷ ላይ ቪድዬዋን ልከህ ካሁን ቡሀላ በሴት ተማሪዎች ሂወት መነገዷን እንድታቆም ያለ በለዚያ ግን ቪድዮዋን እንደምትለቀው ነግረህ አስጠንቅቃት!" ይላል በርግጌ ከፍራሼ ላይ ተነሳሁ።
ቪድዮውን ስከፍተው ••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ወይ መደነስ እኔ ሰውየው እምጥ ይግባ ስምጥ ሄዶ ካናገረው በኋ ላ ከሽንት ቤት ባለመመለሱ ምን አርጎት ነው የመጣው እያልኩ ግራ ተጋብቻለሁ ጭራሽ ደንስ ይለኛል ምን አይነት ባህሪ ያለው ሰው ነው እሄ ደግሞ ቢያንስ እንኳን የኔ ጭንቀት ለምን አይገባውም እንዴ በራሴ ጉዳይ ዝም በል ጠጣ ደንስ ስላለኝ ዝም የምል ይመስለዋል?!
ወደ ሽንት ቤት ሌላ ሰው በሄደ እና በወጣ ቁጥር እያየሁ በጭንቀት ከመፈንዳቴ በፊት እራሴ ሄጄ ለማረጋገጥ ስለፈለኩ•••
••• እሺ መጣሁ አንዴ ስመለስ አብሪያት እደንሳለሁ አልኩትና ሄድኩ መጀመሪያ ወደነመሲ ገልመጥ ሳደርግ ሁለቱ ብቻ ናቸው እነሱም እንደኔ ሰውየው የት ሄደ ብለው ግራ ተጋብተዋል መሰለኝ ግራና ቀኝ ይገላመጣሉ ።
ወደ ወንዶች ሽንት ቤት በፍጥነት ሄድኩና ከአምስቱ ሽንት ቤቶች መሀከል ክፍት የሆኑትን ሁለቱን አየት አድርጌ በማለፍ ሶስተኛውን ስበረግደው•••
----------
"ምን አይነት ሰው ነህ በናትህ! ምሽግ ውስጥ ነው እንዴ ያደከው? አታንኳኳም!" አለኝ በብስጭት አንድ የማላውቀው ሰው።
ይቅርታ ይቅርታ አልኩት ቆሌዬ ተገፎ!።
"ባክህ የምናባህ ይቅርታ ነው ይቅርታ ይላል እንዴ ደሞ የልቡን አድርሶ!" አለኝ።
ንግግሩ ሳቅ ጫረብኝ ።
አይይ ስካር ደጉ ታየኝ እኮ እሱን ሽንት ቤት ተቀምጦ በማየቴ የልቤ ሲደርስ እያልኩ ቀሪ ሁለቱ ክፍሎች ውስጥ ሰውየውን መፈለጌን ቀጠልኩ•••
ሰውየው ድራሹ የለም ። ግራ ተጋብቼ በቆምኩበት ሽንትቤቱን ድንገት ከፍቼበት የተበሳጨው ሰውዬ ቆየት እያለ ሲሳደብ ሰማሁት•••
እንዴ! እሄ ደሞ እያረፈ ነው እንዴ እሚሳደበው!
አልኩና ከውስጥ ዘግተህ አትቀመጥም ነበር ሰካራም! ብየው ወደ ቦታዬ ስመለስ የኮንትራት ደንበኛዬ (ዝም ብለህ ጠጣ ሲለኝ የነበረውን ሰው ) ቦታው ላይ አጣሁት።
የክፍሉን ዙርያ ገባ ቃኘት አደረኩ ። እክፍሉ ውስጥም የለም።
እየተደነባበርኩ እነመሲ ወዳሉበት ክፍል በር ስጠጋ •••
አይኔን ተጠራጠርኩት ! ሽንት ቤት ሰውየውን ፍለጋ ደርሼ እስክመጣ ከምኔው ሄዶ ከምኔው ተዋውቋቸው እና ተግባብቷቸው መሳሳቅ እንደጀመሩ ለማመን በሚከብድ ሁኔታ•••
እሱ ያወራል እነመሲ ይስቃሉ አሁንም ያወራል እነሱ ተያይተው ያሽካካሉ አፌን ከፍቼ ስመለከታቸው ቆየሁና እየሆነ ያለው ነገር ከመጠጡ ጋር ተደምሮ ትርምስምስ እንዳለብኝ ወደ ቦታዬ ተመለስኩ።
ትንሽ ቆየሁና እሱ አልመጣ ሲለኝ መኖር አለመኖራቸውን ላረጋግጥ ድጋሚ ሄድኩ።
ጭራሽ እሱና መሲ ተጣብቀው እየደነሱ ነው። ጀርባዋን ሰጥታው እላዩ ላይ ተጣብቃለች ወገቧን አቅፎ ማጅራቷ አከባቢ እንደመሳም እየቃጣው ለስለስ ባለው ሙዚቃ ይወዛወዛሉ ።
ልጅቷ ቦታዎ ላይ ተቀምጣ ትቁለጨለጫለች ።
ምናልባት አስጠማጇን እራሷን መሲን አጥምዶ ልጅቷን ሊያፋታት አስቦ ይሆን እንዴ?
ብዬ አሰብኩና የሆነ የደስታ ስሜት ውስጤን ሲነዝረው ታውቀኝ።
ሰውየውን ምን አድርጎት ነው? የሚለው ጥያቄ ስላልተመለሰልኝና ዝም ብለህ ጠጣ ከማለት ውጪ ምን እንዳደረገ? እና ምን ሊያደርግ እንዳሰበ በግልፅ ሊነግረኝ ፍቃደኛ ባለመሆኑ ግን ደስታዬ ብርዝ ሆነብኝ!!
በዳንሳችው መሀል ድንገት ተያየን ጠቀሰኝ እኔ ግን ግራ ተጋብቶ ያፈጠጠ እንጂ የሚጨፈን አይን አልነበረኝም እና ምኑም ላልገባኝ ጥቅሻው መልስ ነፈኩት ዝም ብዬው ከራሴ ጋር እያልጎመጎምኩ•••
ግራ አጋባኝ እኮ እሚገርም ሰው ነው እሄ ሰውዬ እያልኩ ወደ ቦታዩ ተመለስኩ ።
በተመለስኩ በደቂቃዎች ውስጥ ወደኔ በመምጣ
"ፈታ በል አቢቲ ዝም ብለህ አትጨናነቅ እኔ አንድ ነገር ላደርግ ካሰብኩ ውጤቱን እንጂ ጅማሬው ማውራት አልወድም! ለምን መሰለህ?••• መጀመራችንን እንጂ መጨረሳችንን የሚያውቀው ፈጣሪ ብቻ ስለሆነ በርግጥ አሁን ያሰብኩትን ነገር ፈጣሪ ሳይሆን ሰይጣን ነው አጨራረሱን የሚያሳምረው አየህ አንዳንዴ ጥሩ ነገር ለመስራት መጥፎ ነገር ውስጥ መግባቱ ግድ ይልሀል የስራህ ውጤት ከፊሉ የፈጣሪ ከፊሉ የሰይጣን ይሆናል ድብልቅ!
ነገር ግን ፈጣሪ ልብን ሰይጣን ስራን ይመረምራል ብዬ ስለማምን እሱ አያሳስበኝም ! ለማንኛውም ስጨርስ ሁሉንም ነገር እነግርሀለሁ አሁን አንተ አታስፈልገኝም ከሀያ ደቂቃ ቡሀላ በር ላይ ሁለት ባጃጅ እፈልጋለሁ ካንተ ጋር ካሁን ቡሀላ ምናልባት ነገ ካልሄድኩ እንገናኝ ይሆናል ብሎኝ ከኔ መልስ ሳይጠብቅ ጥሎኝ ሄደ ።
እንኳን ምን ለማለት እንደፈለገ ሊገባኝ ያለውን መልሼ ማስታወስ አልቻልኩም።
አንዳንድ ሰዎችን ትንሽ ግዜ አብረሀቸው በቆየህ ቁጥር ወይ በደንብ ታውቃቸዋለህ ወይ ጭራሽ እንደማታውቃቸው ይገባሀል የሚለው የጆሲ ጋደኛ ትዝ አለኝ።
ያለኝ አማራጭ መወዛገቤን ትቼ እስከመጨረሻው የሚሆነውን ነገር መመልከት ብቻ ሆነ።
ካስር ደቂቃ ቡሀላ ኮፍያዬን አዘቅዝቄ አንገቴን አቀርቅሬ ከጭፈራ ቤቱ በፍጥነት ወጣሁ ።
ከማውቃቸው በዛ ሰአት ስራ ላይ ይሆናሉ ብዬ ወዳሰበኳቸው ሁለት የባጃጅ ሹፌሮች ደወልኩና በር ላይ እንዲጠብቁአቸው ነግሬ እኔ ራቅ ብዬ ባጃጄ ውስጥ እንዳደፈጥኩ ስጠባበቅ ልክ ባለው ሰአት መሲ እና እሱ ተቃቅፈው ግራና ቀኝ እየትወዛወዙ እና እየተሳሳቁ ልጅቷም በሁኔታቸው አብራ ፈገግ እያለች ወደ ጎን ተደርድረው ከጭፈራ ቤቱ ሲቅወጡ ተመለከትኩ።
ባጃጆቹ ጋር እንደደረሱ ሰውየው ያቀፋትን መሲን ለቅቅ አድርጎ ወደ ልጅታ ተጠጋና አናገራት። ጨብጣው ከፉት ያለው ባጃጅ ውስጥ ጥልቅ አለች እሱና መሲ ሌላኛው ባጃጅ ውስጥ ገቡና ፊትና ኋላ ሆነው ተፈተለኩ እኔም ተከትያቸው ተፈተለኩ ።
በቅርብ እየተከተልኳቸው ልጅቷን ወደ ያዘው የባጃጅ ሹፌር ደወልኩ ። አነሳው።
ምን አለህ? ስለው•••
"ግቢ አድርሳት አለኝ ወደ ግቢ እየወሰድኳት ነው " አለኝ ። በረጅሙ ተነፈስኩ እና ጀግና አቦ አልኩት ግራ ያጋባኝን ሰው።
ወደ ግቢ የሚሄደው ባጃጅና እነመሲን የያዘው ባጃጅ የሚለያዩበት ቦታ ላይ ደረሱ ልጅቷን የያዘው በዲፖ በኩል ሽቅብ ወደ ሰይዶ ሲሸመጥጠው እነመሲን የያዘው ባጃጅ በፀሀይ ሆቴል በኩል ቁልቁል ቆሰቆሰው•••
ወደያዘው ክፍል ይዟት እየሄደ መሆኑን ብረዳም ልጅቷን ትቼ የመሲን መጨረሻ ለማየት ተከተልኳቸው ።
ደረሱ ። ከባጇጃ ወርደው የሰከረችውን መሲን ከመሸከም በማይተናነስ ሀኔታ ደግፎ ወደያዘው ክፍል አስገባት ።
ለሰው ያጠመድሽው እራስሽ ላይ ባርቆ ሊዘርርሽ ነው አይ መሲ !
እያልኩ ወደ ቤቴ ገብቼ ተዘረርኩ ጥዋት ሶስት ሰአት ላይ የቀሰቀሰኝ የስልኬ ጥሪ ነበር ሰውየው ነው በፍጥነት አንስቼው ሀሎ ስል•••
" ደና አደርክ አቢቲ ተመልሼ ወደመጣሁበት እየሄድኩ ነው ምናልባት ከስድስት ወር ቡሀላ እመጣ ይሆናል የማታውን ሙሉ ትያትር ለማየት እና ለመስማት እንደምትፈልግ አውቃለሁ ቴሌግራምህን ክፈት ሶስት መልእክቶች አሉህ በድምፅ! በፅሁፍና; በምስል! ቻው !!"ብቻ ብሎኝ ስልኩን ዘጋው•••
በፍጥነት ቴሌግራም አካውንቴን ስበረግደው ቀድሞ የታየኝ የመሲ ልብስ አልባ ገላ የሚያሳየው ቪድዬ ነበር ከስር የመሲን ስልክ ቁጥር አስቀምጦ
"አቢቲ በዚህ ቁጥሯ የተከፈተ ቴሌግራም አካውንቷ ላይ ቪድዬዋን ልከህ ካሁን ቡሀላ በሴት ተማሪዎች ሂወት መነገዷን እንድታቆም ያለ በለዚያ ግን ቪድዮዋን እንደምትለቀው ነግረህ አስጠንቅቃት!" ይላል በርግጌ ከፍራሼ ላይ ተነሳሁ።
ቪድዮውን ስከፍተው ••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍2
#ልጩህበት!!
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ቴሌግራምህን ክፈት ሶስት መልእክቶች አሉህ በድምፅ! በፅሁፍና; በምስል! ቻው !!"ብቻ ብሎኝ ስልኩን ዘጋው•••
በፍጥነት ቴሌግራም አካውንቴን ስበረግደው ቀድሞ የታየኝ የመሲ ልብስ አልባ ገላ የሚያሳየው ቪድዮ ነበር ከስር የመሲን ስልክ ቁጥር አስቀምጦ
"አቢቲ በዚህ ቁጥሯ የተከፈተ ቴሌግራም አካውንቷ ላይ ቪድዮዋን ልከህ ካሁን ቡኋላ በሴት ተማሪዎች ህይወት መነገዷን እንድታቆም ያለ በለዚያ ግን ቪድዮዋን እንደምትለቀው ነግረህ አስጠንቅቃት!" ይላል በርግጌ ከፍራሼ ላይ ተነሳሁ።
ቪድዮውን ስከፍተው •••
የሶስት ደቂቃ እድሜ ሲኖረው በዚች ሶስት ደቂቃ ውስጥ መሲ ያልተቀረፀ የሰውነት እካሏ አልነበረም ስካሯ ከመጠን ያለፈ ነበርና ያላትን በሙሉ እያደረገች ትስቃለች ። የሚገርመው የሰውየው አንዲት ጣት እንኳን በትይንቱ ውስጥ አለመኖሯ ነው።
ተጫወተባት እናቴ ትሙት በደንብ አርጎ ነው የተጫወተባት አልኩኝ ጮክ ብዬ መጮሄ ሳይታወቀኝ።
ለኔ በአለም ደስ የሚሉ ግን ያልተፃፉ ህግ አስከባሪም ፍርድቤትም ዳኛም ሳያስፈልጋቸው ከሚተገበሩ ተፈጥሮአዊ ህጎች አንዱ
"ሁሉም የእጁን ያገኛል "የሚለው የውስጤ እምነት ነው ማንም ቢሆን በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የዘራውን ማጨዱ የማይቀር ነው
ይዘግይም ይፍጠን፡ ይነስም ይብዛ ቅጣቱን መቀበሉ የማይቀር ነው
ስንቶቹን በክፋቷ አሳልፋ እንዳልሰጠቻቸው እሷን ከክፉ የሚጠብቃት ከሷ በብዙ ክንድ ራቀና አጋለጣት በክፋታችን ያራቅነውን የላይኛውን ጠባቂ የትኛውም የምድር ሀይል ሊተካው አይችልምና አብሯት የነበረው የሰፈራችን ሰውዬም አስረክቧት ፈረጠጠ።
ቪድዮውን ዘጋሁትና የድምፅ ቅጂ መልእክትን ከፈትኩት።
የድምፅ ቅጂው በሁለት ሰዎች መካከል የተደረገን ምልልስ ይዟል ።
የት እንደገባ እስካሁን ያልተመለሰልኝን ያንን ሽንት ቤት ድረስ ሄጄ የፈለኩት ሰውዬ ተከትሎት ሄዶ ሲያናግረው ይጀምራል•••
በቅጂው የመጀመሪያ አስር ሰከንዶች የኮቴ እና በጭፈራ ቤቱ በዛች ቅፅበት ሲዘፍን የነበረው የ ቦብ ማርሊ ዘፈን በስሱ ይሰማል ።
ልክ አስራ አንደኛው ሰከንድ ላይ •••
"ጤና ይስጥልኝ ?
ጤና ይስጥልኝ ምን ነበር እንተዋወቃለን ወንድም?
እኔ እንጃ እንተዋወቃለን መሰለኝ እንካ እስቲ እሄን ተመልከት!
ምንድን ነው እሱ ?
አይታይህም እንዴ መታወቂያ ነዋ !
ያ የሰፈራችን ሰው መታወቂያውን ካየ በኋላ መሰለኝ ድምፅ ተቀየረ።
ታድያ ም-ም-ም-ም-ም-ምን ልታዘዝ ጌታዬ? በርግጥ አላወኮትም ወይ ያጠፋሁት ነገር ይኖር ይሆን ?
ያጠፋሁት ነገር ይኖር ይሆን ትላለህ እንዴ ደሞ?
ለነገሩ ላንተም ለብዙዎቹም ለህግም ጥፋት መስሎ የማይታይ ጥፋት ስለሆነ አይታወቅህም
ማለት? እንዴት? መቼ? ምን አድርጌ ? የኔ ጌታ እስቲ ና አረፍ በልና ልጋብዝህ እየጠጣን እናውራ!
ህሊናቸውን በብራቸው ቁልል አፍነው የትውልድን አእምሮ የሚያቀንጭር ስራ ላይ ከተሰማሩ ከብቶች መሀል አንዱ ነህና ሰውን ሁሉ በብር በግብዣ ከመግዛት የሚሻገር አስተሳሰብ የለህም እንኳን እኔን ልትጋብዘኝ ከዚች ሰከንድ ጀምሮ አብረሀት ያለችውን አንድ ፍሬ ልጅ ደግመህ ሳታያት እዚሁ ቆሜ እያየሁህ በጓሮ በር ሹልክ ብለህ ጥፋ! ያለበለዚያ •••
ኧረ እሺ እሺ ጌታዬ እሄዳለሁ ግን የጓሮ በር ያለው አይመስለኝም ቤቱ!
በዛጋ ወደ ሽንት ቤቱ መጊቢያ በስተቀኝ በኩል ባለችው ቀጭን መንገድ ወደ ውስጥ ትንሽ ሄደህ ደረጃውን ቁልቁል ስትወርድ በር ታገኛለህ
እሺ ጌታዬ እሄው ያለብኝ ሂሳብ ነው!
ፍጠን!
እሺ እሄው ሄድኩኮ!"
ሰውየውን በዚህ መልኩ ቆሌውን ገፎ ማባረሩን ሳዳምጥ ከተሰማኝን ደስታ ጋር ግን እሄ ሰውዬ ማን ነው? ለምንድን ነው መታወቂያውን ሲያሳየው እንደዛ ምላሱን የዋጣት ይመስል ንግግሩ ሁሉ የተቆላለፈበት ?የሚለው ጥያቄ ገዝፎ አንቃጨለብኝ!።
ሰውየውን ለግዜው እንቆቅልሽ እንደሆነብኝ ተውኩትና ጆሲን ቀስቅሼ ከማታ ጀምሮ የተፈጠረውን ነገር ነገርኩት።
"ለማንኛውም ቪድዮውን ለመሲ ከመላክህ በፊት አስብበት ማለቴ አረጋጋው !" አለኝ።
ቅዳሜን በጣም እወዳታለሁ በዛ ላይ ዛሬ ከኤዱ ጋር ቀጠሮ አለን።
ከቀኑ ልክ 7:30 ላይ ኤዱ ደወለችና ሰፈር መድረሷንና ያለችበትን ቦታ ነገረችኝ ።
ስትነሺ ደውይልኝ መጥቼ እወስድሻለሁ ብያት ስለነበር ለምን ቀድማ እንዳልደወለችልኝ እየጠየኳት ከቤት ወጣሁና ብር ላይ, ያቆምኳትን ባጃጄን! አስነስቼ ከነፍኩ ።
እነሱ ሳያዩኝ ገና ከሩቁ እንዳየሁዋቸው ደነገጥኩ ግን ምን አስደነገጠኝ ? እኔ እንጃ!
ኤዱ ብቻዋን አልነበረም የመጣችው ሶስት ናቸው ከረድኤት አንድ ባለባበሱ ፍንድትድት ያለ ወጣት ወንድ አብሮአቸው አለ።
ማንም አብሮአቸው ቢኖር ግን ምን አገባኝ ?
ግን ለምን ሶስት ሆነው እንደሚመጡ ቀድማ አልነገረችኝም ?
ግን ማን ነው? እያልኩ መልስ በለላቸው ጥያቄዎቼ እራሴንም ባጃጇንም እያጣደፍኩ አጠገባቸው ደረስኩ።
ከሷ እና ከረድኤት ጋር በመተቃቀፍ ሞቅ ያለ የቅርብ ሰው ሰላምታ ከተለዋወጥን ብሀላ ፈንጠር ብሎ ሞባይሉን የሚነካካውን ልጅ እያመለከተችኝ ዳንዬ ተዋወቀው ባለፈው ከመሲ አስመለጠኝ ያልኩህ የክፍሌ ልጅ ፣ ጓደኛዬ እሱ ነው አለችና ደሞ እሱን
ቴዲዬ ተዋወቁ ምርጥ ወንድሜን " አለችው
ልጥጥ እንዳለ እጁን ዘርፕጋልኝ ጨበጥኩትና ግቡ እንሂድ አልኳቸው።
ባጃጅ ውስጥ ገብተው ወደቤት እየሄድን በመካከላችን ወሬ ጠፋ!።
በኔ በኩል የልጁ ሁኔታ ይሁን ሌላ ባይገባኝም የሆነ ደስ የማይል አዲስ ስሜት ውስጤ ሲላወስ እያዳመጥኩት ነበርና ዝም ማለቴንም አላስተዋልኩትም ነበር ።
እቤት እንደደረስን የውስጤ ስሜት ፊቴ ላይ እንዳይታይ እየታገልኩ ላጫውታቸው ብሞክርም ልጁ እኔ ከረድኤትም ይሁን ከኤዱ አልያም ከሁለቱን ጋር ወሬ ስጀምር እየጠበቀ በማክሸፍ ነበርና የራሱን የሚተኩሰው ሊያስወራኝ አልቻለም።
መናደድ ጀመርኩ። ልጁ እኔ ብቻ ላውራ አድምጡኝ በማለት የሚከተለውን ሙድና የኔን ንዴት በመጠኑም ቡሆን የተረዳችው ኤዱ ጀርባዋን ለሱ ሰጥታ እኔን ለማዋራት ሞከረች።
ከቆይታ በኋላ ካርድ ልግዛ በሚል ሰበብ ወጣ ብሎ ሲመለስ በፊት የነበረበትን ቦታ ትቶ እኔና ኤዱ መሀል ገብቶ ሲቀመጥ ንዴቴን መመጠንም መቆጣጠርም አቅቶኝ ጠፍቶ ድንገት ሀይል ጨምሮ እንደመጣ መብራት ሁለመናዬ ቦግ •••••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ቴሌግራምህን ክፈት ሶስት መልእክቶች አሉህ በድምፅ! በፅሁፍና; በምስል! ቻው !!"ብቻ ብሎኝ ስልኩን ዘጋው•••
በፍጥነት ቴሌግራም አካውንቴን ስበረግደው ቀድሞ የታየኝ የመሲ ልብስ አልባ ገላ የሚያሳየው ቪድዮ ነበር ከስር የመሲን ስልክ ቁጥር አስቀምጦ
"አቢቲ በዚህ ቁጥሯ የተከፈተ ቴሌግራም አካውንቷ ላይ ቪድዮዋን ልከህ ካሁን ቡኋላ በሴት ተማሪዎች ህይወት መነገዷን እንድታቆም ያለ በለዚያ ግን ቪድዮዋን እንደምትለቀው ነግረህ አስጠንቅቃት!" ይላል በርግጌ ከፍራሼ ላይ ተነሳሁ።
ቪድዮውን ስከፍተው •••
የሶስት ደቂቃ እድሜ ሲኖረው በዚች ሶስት ደቂቃ ውስጥ መሲ ያልተቀረፀ የሰውነት እካሏ አልነበረም ስካሯ ከመጠን ያለፈ ነበርና ያላትን በሙሉ እያደረገች ትስቃለች ። የሚገርመው የሰውየው አንዲት ጣት እንኳን በትይንቱ ውስጥ አለመኖሯ ነው።
ተጫወተባት እናቴ ትሙት በደንብ አርጎ ነው የተጫወተባት አልኩኝ ጮክ ብዬ መጮሄ ሳይታወቀኝ።
ለኔ በአለም ደስ የሚሉ ግን ያልተፃፉ ህግ አስከባሪም ፍርድቤትም ዳኛም ሳያስፈልጋቸው ከሚተገበሩ ተፈጥሮአዊ ህጎች አንዱ
"ሁሉም የእጁን ያገኛል "የሚለው የውስጤ እምነት ነው ማንም ቢሆን በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የዘራውን ማጨዱ የማይቀር ነው
ይዘግይም ይፍጠን፡ ይነስም ይብዛ ቅጣቱን መቀበሉ የማይቀር ነው
ስንቶቹን በክፋቷ አሳልፋ እንዳልሰጠቻቸው እሷን ከክፉ የሚጠብቃት ከሷ በብዙ ክንድ ራቀና አጋለጣት በክፋታችን ያራቅነውን የላይኛውን ጠባቂ የትኛውም የምድር ሀይል ሊተካው አይችልምና አብሯት የነበረው የሰፈራችን ሰውዬም አስረክቧት ፈረጠጠ።
ቪድዮውን ዘጋሁትና የድምፅ ቅጂ መልእክትን ከፈትኩት።
የድምፅ ቅጂው በሁለት ሰዎች መካከል የተደረገን ምልልስ ይዟል ።
የት እንደገባ እስካሁን ያልተመለሰልኝን ያንን ሽንት ቤት ድረስ ሄጄ የፈለኩት ሰውዬ ተከትሎት ሄዶ ሲያናግረው ይጀምራል•••
በቅጂው የመጀመሪያ አስር ሰከንዶች የኮቴ እና በጭፈራ ቤቱ በዛች ቅፅበት ሲዘፍን የነበረው የ ቦብ ማርሊ ዘፈን በስሱ ይሰማል ።
ልክ አስራ አንደኛው ሰከንድ ላይ •••
"ጤና ይስጥልኝ ?
ጤና ይስጥልኝ ምን ነበር እንተዋወቃለን ወንድም?
እኔ እንጃ እንተዋወቃለን መሰለኝ እንካ እስቲ እሄን ተመልከት!
ምንድን ነው እሱ ?
አይታይህም እንዴ መታወቂያ ነዋ !
ያ የሰፈራችን ሰው መታወቂያውን ካየ በኋላ መሰለኝ ድምፅ ተቀየረ።
ታድያ ም-ም-ም-ም-ም-ምን ልታዘዝ ጌታዬ? በርግጥ አላወኮትም ወይ ያጠፋሁት ነገር ይኖር ይሆን ?
ያጠፋሁት ነገር ይኖር ይሆን ትላለህ እንዴ ደሞ?
ለነገሩ ላንተም ለብዙዎቹም ለህግም ጥፋት መስሎ የማይታይ ጥፋት ስለሆነ አይታወቅህም
ማለት? እንዴት? መቼ? ምን አድርጌ ? የኔ ጌታ እስቲ ና አረፍ በልና ልጋብዝህ እየጠጣን እናውራ!
ህሊናቸውን በብራቸው ቁልል አፍነው የትውልድን አእምሮ የሚያቀንጭር ስራ ላይ ከተሰማሩ ከብቶች መሀል አንዱ ነህና ሰውን ሁሉ በብር በግብዣ ከመግዛት የሚሻገር አስተሳሰብ የለህም እንኳን እኔን ልትጋብዘኝ ከዚች ሰከንድ ጀምሮ አብረሀት ያለችውን አንድ ፍሬ ልጅ ደግመህ ሳታያት እዚሁ ቆሜ እያየሁህ በጓሮ በር ሹልክ ብለህ ጥፋ! ያለበለዚያ •••
ኧረ እሺ እሺ ጌታዬ እሄዳለሁ ግን የጓሮ በር ያለው አይመስለኝም ቤቱ!
በዛጋ ወደ ሽንት ቤቱ መጊቢያ በስተቀኝ በኩል ባለችው ቀጭን መንገድ ወደ ውስጥ ትንሽ ሄደህ ደረጃውን ቁልቁል ስትወርድ በር ታገኛለህ
እሺ ጌታዬ እሄው ያለብኝ ሂሳብ ነው!
ፍጠን!
እሺ እሄው ሄድኩኮ!"
ሰውየውን በዚህ መልኩ ቆሌውን ገፎ ማባረሩን ሳዳምጥ ከተሰማኝን ደስታ ጋር ግን እሄ ሰውዬ ማን ነው? ለምንድን ነው መታወቂያውን ሲያሳየው እንደዛ ምላሱን የዋጣት ይመስል ንግግሩ ሁሉ የተቆላለፈበት ?የሚለው ጥያቄ ገዝፎ አንቃጨለብኝ!።
ሰውየውን ለግዜው እንቆቅልሽ እንደሆነብኝ ተውኩትና ጆሲን ቀስቅሼ ከማታ ጀምሮ የተፈጠረውን ነገር ነገርኩት።
"ለማንኛውም ቪድዮውን ለመሲ ከመላክህ በፊት አስብበት ማለቴ አረጋጋው !" አለኝ።
ቅዳሜን በጣም እወዳታለሁ በዛ ላይ ዛሬ ከኤዱ ጋር ቀጠሮ አለን።
ከቀኑ ልክ 7:30 ላይ ኤዱ ደወለችና ሰፈር መድረሷንና ያለችበትን ቦታ ነገረችኝ ።
ስትነሺ ደውይልኝ መጥቼ እወስድሻለሁ ብያት ስለነበር ለምን ቀድማ እንዳልደወለችልኝ እየጠየኳት ከቤት ወጣሁና ብር ላይ, ያቆምኳትን ባጃጄን! አስነስቼ ከነፍኩ ።
እነሱ ሳያዩኝ ገና ከሩቁ እንዳየሁዋቸው ደነገጥኩ ግን ምን አስደነገጠኝ ? እኔ እንጃ!
ኤዱ ብቻዋን አልነበረም የመጣችው ሶስት ናቸው ከረድኤት አንድ ባለባበሱ ፍንድትድት ያለ ወጣት ወንድ አብሮአቸው አለ።
ማንም አብሮአቸው ቢኖር ግን ምን አገባኝ ?
ግን ለምን ሶስት ሆነው እንደሚመጡ ቀድማ አልነገረችኝም ?
ግን ማን ነው? እያልኩ መልስ በለላቸው ጥያቄዎቼ እራሴንም ባጃጇንም እያጣደፍኩ አጠገባቸው ደረስኩ።
ከሷ እና ከረድኤት ጋር በመተቃቀፍ ሞቅ ያለ የቅርብ ሰው ሰላምታ ከተለዋወጥን ብሀላ ፈንጠር ብሎ ሞባይሉን የሚነካካውን ልጅ እያመለከተችኝ ዳንዬ ተዋወቀው ባለፈው ከመሲ አስመለጠኝ ያልኩህ የክፍሌ ልጅ ፣ ጓደኛዬ እሱ ነው አለችና ደሞ እሱን
ቴዲዬ ተዋወቁ ምርጥ ወንድሜን " አለችው
ልጥጥ እንዳለ እጁን ዘርፕጋልኝ ጨበጥኩትና ግቡ እንሂድ አልኳቸው።
ባጃጅ ውስጥ ገብተው ወደቤት እየሄድን በመካከላችን ወሬ ጠፋ!።
በኔ በኩል የልጁ ሁኔታ ይሁን ሌላ ባይገባኝም የሆነ ደስ የማይል አዲስ ስሜት ውስጤ ሲላወስ እያዳመጥኩት ነበርና ዝም ማለቴንም አላስተዋልኩትም ነበር ።
እቤት እንደደረስን የውስጤ ስሜት ፊቴ ላይ እንዳይታይ እየታገልኩ ላጫውታቸው ብሞክርም ልጁ እኔ ከረድኤትም ይሁን ከኤዱ አልያም ከሁለቱን ጋር ወሬ ስጀምር እየጠበቀ በማክሸፍ ነበርና የራሱን የሚተኩሰው ሊያስወራኝ አልቻለም።
መናደድ ጀመርኩ። ልጁ እኔ ብቻ ላውራ አድምጡኝ በማለት የሚከተለውን ሙድና የኔን ንዴት በመጠኑም ቡሆን የተረዳችው ኤዱ ጀርባዋን ለሱ ሰጥታ እኔን ለማዋራት ሞከረች።
ከቆይታ በኋላ ካርድ ልግዛ በሚል ሰበብ ወጣ ብሎ ሲመለስ በፊት የነበረበትን ቦታ ትቶ እኔና ኤዱ መሀል ገብቶ ሲቀመጥ ንዴቴን መመጠንም መቆጣጠርም አቅቶኝ ጠፍቶ ድንገት ሀይል ጨምሮ እንደመጣ መብራት ሁለመናዬ ቦግ •••••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍1
#ልጩህበት!!
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
፡
፡
መናደድ ጀመርኩ። ልጁ እኔ ብቻ ላውራ አድምጡኝ በማለት የሚከተለውን ሙድና የኔን ንዴት በመጠኑም ቢሆን የተረዳችው ኤዱ ጀርባዋን ለሱ ሰጥታ እኔን ለማዋራት ሞከረች።
ከቆይታ በኋላ ካርድ ልግዛ በሚል ሰበብ ወጣ ብሎ ሲመለስ በፊት የነበረበትን ቦታ ትቶ እኔና ኤዱ መሀል ገብቶ ሲቀመጥ ንዴቴን መመጠንም መቆጣጠርም አቅቶኝ ጠፍቶ ድንገት ሀይል ጨምሮ እንደመጣ መብራት ሁለመናዬ ቦግ
••••
ቦግ አለ። ነደድኩ!፤ ፊቴ ተቀያየረ!፤ ደምስሬ ተወጣጠረ!
ልጁ ግን አየት አደረገኝና ከቁብም ሳይቆጥረኝ •••
"ኤድሻ ፌስ ቡክ ላይ የሆነ ፈን ነገር አይቼ እኮ ነው ቆይ ላሳይሽ እይውሟ እሄንን፤ እሄን አየሽው"እያለ ከሞባይሉ ላይ አይኗ እንዳይነቀል ስላደረጋት እሷም ሳታየኝ ተንጨርጭሬ እንደቀዘቀዝኩ ሆን ብሎ እኔን ለማናደድ እንደዛ እንደሚያደርግ በደንብ ያስታውቃል ብድግ አልኩና•••
እቤቴ ባትመጣ በዚህ አመት ከተጣላኋቸው ሰዎች አንዱ ትሆን ነበር ግን ምን ያረጋል
እቤቱ የመጣን ሰው ካልነከስኩ የሚለው ውሻ ብቻ ነው ውሻ ነገር ነህ አቦ! ገገማ! እያልኩ በውስጤ እየተሳደብኩ ተነስቼ ወጣሁና ግቢ ውስጥ ፊቴን መታጠብ ጀመርኩ።
ተመልሼ ስገባ እራሱ እያወራ እነሱ ሳይስቁ እራሱ ይስቃል ። የነበረን ቆይታ በልጁ ምክንያት ምኑም ሳይጥመኝ በሱ ውትወታ " በቃ እንሂድ" ብለው ተነሱ አላግደረደርካቸውም።
ከቤት እንደወጣን ግቢ ላድርሰችሁ ? አልኳቸው።
ከልቤ ነበር ከኛ ሰፈር ግቢ ድረስ ኮንትራት ካልያዙ በስተቀር ቀጥታ የሚወስዳቸው ታክሲ የለምና እንዳይቸገሩ ብዬ በማሰብ
"ስራ ትወጣለህ እንዴ ከዚህ ቡሀላ? አለችኝ ኤዱ
ስራ እንደማልወጣና እነሱን ብቻ አድርሻቸው ወደ ቤት እንደምመለስ ስነግራት•••
" አይሆንም በቃ ለኛ ብለህማ እዛ ድረስ መድከም የለብህም በትራንስፖርት እንሄዳለን!" ብላ ድርቅ አለች!
ተሰነባብተን ወደ ቤት ተመለስኩ።
አመሻሹ ላይ ጆሲ ድንገት በሩን ብርግድ አድርጎ ሲገባ ደንብሬ ተነሳሁ•••
"በለው በለው በቅዳሜ ቀን መጋደም ! ምን ሆነሀል አንተ ? እኔኮ የዳኒ እንግዳ ሄደች እንዴ ብዬ ሚሚ ባለሱቋን ስጠይቃት " ቆዩኮ ከወጡ!" ስትለኝ ገርሞኛል ቆይ ቆይ•••
በማህበር ተደራጅተው ነው እንዴ የመጡት?
እኔ እሷን ብቻ የቀጠርካት መስሎኝ አደል እንዴ የተቀየስኩት እዚሁ ደቅ ብዬ የቅዳሜ በርጫየን እንዳላጣጥም መሄድ እማልፈልግበት ቦታ ሄጄ ተጦልቤ ነው የመጣሁት ሰራህልኝ አቦ ቀጥሪያታለሁ ትመጣለች ከምትለኝ ይመጣሉ አትለኝም ወይ ምናለ ከመጡ ቡሀላስ ብትደውል መጥቼ ጀማውን እቀላቀል አልነበር እንዴ ! ግን እንዴት ነበር ውሎ?"
ኧረ ብትኖርልኝ ይሻለኝ ነበር ጆስዬ እኔም የመጨረሻ ተደውኬ ነው የዋልኩት !።
"እንዴ ለምን?" አለኝ ከበር ላይ ወደ ውስጥ ገብቶ አጠገቤ እየተቀመጠ
አላ! አብሯት የመጣው ልጅ ደዋኪ ነገር ነው ባክህ
"ማነው ልጁ ዝም ብሎ ጀለሳቸው ነው ወይስ•••?
አቦ ! ያ ነዎ! ባለፈው መሲ ልታስበላት ስትል ከጀለሶቹ ጋር ቀመር ቀምረው አስመለጣት ብዬ የነገርኩሁ የክፍሏ ልጅ
የፈራሁት ደረሰ ወይኔ ወንድሜን አንተ በህትነት ምናምን ነው እምንከባከባት እያልክ እራስህንም እኔንም ስትሸውድ በፍቅር የሚንከባከባትን አምጥታ አስተዋወቀችህ? ፍቅረኛዬ ነው ተዋወቀው ብላህ እጅ አፈችው አደል ?"
ውይይይይ ጆሲ ደግሞ እስቲ አሁን ማን እንደዛ አለ ? እንደዛ አለችኝ አልኩህ? ወጣኝ!?
"ታድያ እንደዛ ካልሆነ ምን አናደደህ? ብዬ ነዋ!"
አሃ! እኔ እምናደደው እሱ ስለጠበሳት ብቻ ነው ማለት ነው?
"ታድያ ፍላጎቱ እንደዛ መሆኑን ወይ አብሯት መሆኑን ብታውቅ እንጂ በምን ትናደዳለህ በዚ የማትናደድ ከሆነማ በምንም ልትናደድ አትችልም!"
ማለት?
"በዚህ ካልተናደድክ ሌላው ምክንያት እንዳለ ከዚህ በታች ነው ብዬ ነዋ!"
ይሆናል ብሎ ከመደምደም በምን ተናደድክ ብሎ መጠየቅ አይሻልም?
"እሺ በምን ተናደድክ?"
በቃ ልጁ እኔን ብቻ አድምጡኝ ከኔጋ ብቻ አውሩ ሙድ የሚያራምድ ነገር ነው ማለት•••አልኩና ከመጡ ጀምሮ የነበረውን ሁኔታ ነግሬው ሳበቃ••••
"ካካካካካ•••!" ሳቁን ለቀቀው!።
ምን ያስቅሀል?! አልኩት ተናድጄ!
" አይ ዳንዬ በዚህ ያልተሳቀ በምን ይሳቃል የፍቅርን አመል ስለማውቀው ነው አንድ ፈላስፋ ምን እንደሚል ታውቃለህ••••"
አላውቅምም ደሞም እንዳታወራልኝ ! ኤጭ አሁንስ አንተና ያ ጓደኛህ ወሬያችሁ ጅማሮውን በሙሉ
" አንድ ፈላስፋ ምን እንዳለ ታውቃለህ?
"እገሌ የተባለው መፅሀፍ ላይ ምን እንደሚል ታውቃለህ?
አንድ ምሁር ሰው ምን እንዳለ ልንገርህ?
በሚል እያሟሻችሁ የራሳችሁን ሀሳብ በቀላሉ ሰው እንዲቀበለው ለማድረግ የምትሄዱበት መንገድና
አለም ላይ ምን ተፈጠረ ብዬ ዜና ለማዳመጥ በተቀመጥኩ ቁጥር የሀገራችን የቲቪና ራድዬ ሚድያዎች
"ምሁራን ተናገሩ!
የህግ ባለሞያዎች ገለፁ!።
ነዎሪዎች እንዲህ አሉ !/
እገሌ እንዲህ አለ
እገሊት እንዲህ አለች" እያሉ የግልን አስተያየት ምልከታ አንድ ሰአት በሙሉ ዜና ብለው የሚያደርቁን ነገር እንዴት እንደሰለቸኝ •••
"በናትህ ይጠቅምሀል እቺን ብቻ አድምጠኝ ፈላስፋው እውቅ የግሪክ ፈላስፋ ነው ምን አለ መሰለህ ••••" ብሎ ሊቀጥል ሲል•••
በናትህ ተወኝ አልኩትና በንዴት ተነስቼ ክፍሉን ለቅቄለት ወጣሁ ። ስራ አልወጣም ያልኩት ሰውዬ ባጃጄን አስነስቼ ወደ ከተማ ከነፍኩ።
ንዴቴን በስራ ለመርሳት ተፍ ተፍ ስል አምሽቼ ልክ ከምሽቱ አራት ሰአት አከባቢ ከገንደቆሬ ወደ ሼል እየመጣሁ ብሎሰም ሆቴል ኩርባው ጋር እንደደረስኩ አንድ እድሜው በአርባዎቹ መጀመሪያ ላይ የሚሆነው ፈርጠም ያለ ጎልማሳ ሰው ሁለት እጁን በየተራ እያርገበገበ•••
"ባጃጅ ኮንትራት ኮንትራት " አለኝ ። አቆምኩና
የት? አልኩት ፊቱ ላይ እንደእሳት የሚንቀለቀለውን ንዴቱን እያስተዋልኩ
"የት እንደሆነች አላውቅም !
የገባችበት ጉድጓድ ውስጥ ገብቼ እስካገኛት ከኔ ጋር ነህ!
ያልከኝን እከፍላለሁ !"
አለኝና መጀመሪያ የምንሄድበትን ሆቴል ነገረኝ።
እየሄዱን በየመሀሉ •••
" እኔ ላይ! ለኔ እሄ ይገባኛል!" እያለ የአንዱ እጁን መዳፍ በሌላኛው እጁ ቡጢ ያጎነዋል።
ተናድጄ ብወጣ ከኔ የባሰ በንዴት የተከነ ሰው አጋጠመኝና የራሴን ንዴት ረሳሁት። ምን ሆኖ ይሆን እንዲህ ግብግብ ያለው? አልኩ ለራሴ።
ምን ሆነህ ነው ዘመዴ? አልኩት ፈራ ተባ እያልኩ•••
"ወይይይ ሴት ! አይይይ ሴት ገና ለገና ለሳምንት ያህል ለስልጠና ሀረር ሄጃለሁ ስላልኳት በከተማው የለም ብላ እግሬ ከመውጣቱ ቱ የማትረባ !
እሄማ መጀመሪያ የተቀባበለ እንጂ ሄጄ ገና ሶስት ቀን እንኳን ሳይሞላኝ ኬት ይመጣል እስካሁንም እየተጫወትሽብኝ ነበር ማለት ነው እኔ አንቺ ለማግባት ስሰናዳ በግዜ ጉድሽን ያሰማኝ!
ዛሬ ምን እንደሚውጥሽ አያለሁ "! አለ ።
ከንግግሩ ለኔ ጥያቄ መልስ እየሰጠኝ ይሁን ብሶቱን እየተነፈሰ መረዳት ተሳነኝና ግራ ተገብቼ ዝምታን መረጥኩ ። ትንሽ ቆየና •••
"የገዛ ጓደኛዬ አይቷት አይቷት እኮ ነው የደወለልኝ በአይነ ብረቱ ነው ያያት ወይኔ ደጉ ደግነቴን የዋህነቴን አይታ ነው የተጫወተችብኝ እነሱ እኮ ደግ ወንድ አይወዱም ዛሬ እጅ ከፍንጅ ስይዛት ምን እንደሚውጣት አያለሁ አጠገባ ያለውን ሰውዬ ትውጠው እንደሆነ እንተያያለን !"አለ።
ሁሉም ነገር ገባኝ። ፍቅረኛውን ከሰው ጋር ያያት ጓደኛው ደውሎለት እንደመጣ ተረዳሁ። በዚህ ሁኔታው ቢያገኛት ምን ሊፈጠር እንደሚችል ሳስበው ጨነቀኝ ።
ከሰው ጋር ታየች የተባለበት ሆቴል በር ላይ እንደደረስን በፍጥነት
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
፡
፡
መናደድ ጀመርኩ። ልጁ እኔ ብቻ ላውራ አድምጡኝ በማለት የሚከተለውን ሙድና የኔን ንዴት በመጠኑም ቢሆን የተረዳችው ኤዱ ጀርባዋን ለሱ ሰጥታ እኔን ለማዋራት ሞከረች።
ከቆይታ በኋላ ካርድ ልግዛ በሚል ሰበብ ወጣ ብሎ ሲመለስ በፊት የነበረበትን ቦታ ትቶ እኔና ኤዱ መሀል ገብቶ ሲቀመጥ ንዴቴን መመጠንም መቆጣጠርም አቅቶኝ ጠፍቶ ድንገት ሀይል ጨምሮ እንደመጣ መብራት ሁለመናዬ ቦግ
••••
ቦግ አለ። ነደድኩ!፤ ፊቴ ተቀያየረ!፤ ደምስሬ ተወጣጠረ!
ልጁ ግን አየት አደረገኝና ከቁብም ሳይቆጥረኝ •••
"ኤድሻ ፌስ ቡክ ላይ የሆነ ፈን ነገር አይቼ እኮ ነው ቆይ ላሳይሽ እይውሟ እሄንን፤ እሄን አየሽው"እያለ ከሞባይሉ ላይ አይኗ እንዳይነቀል ስላደረጋት እሷም ሳታየኝ ተንጨርጭሬ እንደቀዘቀዝኩ ሆን ብሎ እኔን ለማናደድ እንደዛ እንደሚያደርግ በደንብ ያስታውቃል ብድግ አልኩና•••
እቤቴ ባትመጣ በዚህ አመት ከተጣላኋቸው ሰዎች አንዱ ትሆን ነበር ግን ምን ያረጋል
እቤቱ የመጣን ሰው ካልነከስኩ የሚለው ውሻ ብቻ ነው ውሻ ነገር ነህ አቦ! ገገማ! እያልኩ በውስጤ እየተሳደብኩ ተነስቼ ወጣሁና ግቢ ውስጥ ፊቴን መታጠብ ጀመርኩ።
ተመልሼ ስገባ እራሱ እያወራ እነሱ ሳይስቁ እራሱ ይስቃል ። የነበረን ቆይታ በልጁ ምክንያት ምኑም ሳይጥመኝ በሱ ውትወታ " በቃ እንሂድ" ብለው ተነሱ አላግደረደርካቸውም።
ከቤት እንደወጣን ግቢ ላድርሰችሁ ? አልኳቸው።
ከልቤ ነበር ከኛ ሰፈር ግቢ ድረስ ኮንትራት ካልያዙ በስተቀር ቀጥታ የሚወስዳቸው ታክሲ የለምና እንዳይቸገሩ ብዬ በማሰብ
"ስራ ትወጣለህ እንዴ ከዚህ ቡሀላ? አለችኝ ኤዱ
ስራ እንደማልወጣና እነሱን ብቻ አድርሻቸው ወደ ቤት እንደምመለስ ስነግራት•••
" አይሆንም በቃ ለኛ ብለህማ እዛ ድረስ መድከም የለብህም በትራንስፖርት እንሄዳለን!" ብላ ድርቅ አለች!
ተሰነባብተን ወደ ቤት ተመለስኩ።
አመሻሹ ላይ ጆሲ ድንገት በሩን ብርግድ አድርጎ ሲገባ ደንብሬ ተነሳሁ•••
"በለው በለው በቅዳሜ ቀን መጋደም ! ምን ሆነሀል አንተ ? እኔኮ የዳኒ እንግዳ ሄደች እንዴ ብዬ ሚሚ ባለሱቋን ስጠይቃት " ቆዩኮ ከወጡ!" ስትለኝ ገርሞኛል ቆይ ቆይ•••
በማህበር ተደራጅተው ነው እንዴ የመጡት?
እኔ እሷን ብቻ የቀጠርካት መስሎኝ አደል እንዴ የተቀየስኩት እዚሁ ደቅ ብዬ የቅዳሜ በርጫየን እንዳላጣጥም መሄድ እማልፈልግበት ቦታ ሄጄ ተጦልቤ ነው የመጣሁት ሰራህልኝ አቦ ቀጥሪያታለሁ ትመጣለች ከምትለኝ ይመጣሉ አትለኝም ወይ ምናለ ከመጡ ቡሀላስ ብትደውል መጥቼ ጀማውን እቀላቀል አልነበር እንዴ ! ግን እንዴት ነበር ውሎ?"
ኧረ ብትኖርልኝ ይሻለኝ ነበር ጆስዬ እኔም የመጨረሻ ተደውኬ ነው የዋልኩት !።
"እንዴ ለምን?" አለኝ ከበር ላይ ወደ ውስጥ ገብቶ አጠገቤ እየተቀመጠ
አላ! አብሯት የመጣው ልጅ ደዋኪ ነገር ነው ባክህ
"ማነው ልጁ ዝም ብሎ ጀለሳቸው ነው ወይስ•••?
አቦ ! ያ ነዎ! ባለፈው መሲ ልታስበላት ስትል ከጀለሶቹ ጋር ቀመር ቀምረው አስመለጣት ብዬ የነገርኩሁ የክፍሏ ልጅ
የፈራሁት ደረሰ ወይኔ ወንድሜን አንተ በህትነት ምናምን ነው እምንከባከባት እያልክ እራስህንም እኔንም ስትሸውድ በፍቅር የሚንከባከባትን አምጥታ አስተዋወቀችህ? ፍቅረኛዬ ነው ተዋወቀው ብላህ እጅ አፈችው አደል ?"
ውይይይይ ጆሲ ደግሞ እስቲ አሁን ማን እንደዛ አለ ? እንደዛ አለችኝ አልኩህ? ወጣኝ!?
"ታድያ እንደዛ ካልሆነ ምን አናደደህ? ብዬ ነዋ!"
አሃ! እኔ እምናደደው እሱ ስለጠበሳት ብቻ ነው ማለት ነው?
"ታድያ ፍላጎቱ እንደዛ መሆኑን ወይ አብሯት መሆኑን ብታውቅ እንጂ በምን ትናደዳለህ በዚ የማትናደድ ከሆነማ በምንም ልትናደድ አትችልም!"
ማለት?
"በዚህ ካልተናደድክ ሌላው ምክንያት እንዳለ ከዚህ በታች ነው ብዬ ነዋ!"
ይሆናል ብሎ ከመደምደም በምን ተናደድክ ብሎ መጠየቅ አይሻልም?
"እሺ በምን ተናደድክ?"
በቃ ልጁ እኔን ብቻ አድምጡኝ ከኔጋ ብቻ አውሩ ሙድ የሚያራምድ ነገር ነው ማለት•••አልኩና ከመጡ ጀምሮ የነበረውን ሁኔታ ነግሬው ሳበቃ••••
"ካካካካካ•••!" ሳቁን ለቀቀው!።
ምን ያስቅሀል?! አልኩት ተናድጄ!
" አይ ዳንዬ በዚህ ያልተሳቀ በምን ይሳቃል የፍቅርን አመል ስለማውቀው ነው አንድ ፈላስፋ ምን እንደሚል ታውቃለህ••••"
አላውቅምም ደሞም እንዳታወራልኝ ! ኤጭ አሁንስ አንተና ያ ጓደኛህ ወሬያችሁ ጅማሮውን በሙሉ
" አንድ ፈላስፋ ምን እንዳለ ታውቃለህ?
"እገሌ የተባለው መፅሀፍ ላይ ምን እንደሚል ታውቃለህ?
አንድ ምሁር ሰው ምን እንዳለ ልንገርህ?
በሚል እያሟሻችሁ የራሳችሁን ሀሳብ በቀላሉ ሰው እንዲቀበለው ለማድረግ የምትሄዱበት መንገድና
አለም ላይ ምን ተፈጠረ ብዬ ዜና ለማዳመጥ በተቀመጥኩ ቁጥር የሀገራችን የቲቪና ራድዬ ሚድያዎች
"ምሁራን ተናገሩ!
የህግ ባለሞያዎች ገለፁ!።
ነዎሪዎች እንዲህ አሉ !/
እገሌ እንዲህ አለ
እገሊት እንዲህ አለች" እያሉ የግልን አስተያየት ምልከታ አንድ ሰአት በሙሉ ዜና ብለው የሚያደርቁን ነገር እንዴት እንደሰለቸኝ •••
"በናትህ ይጠቅምሀል እቺን ብቻ አድምጠኝ ፈላስፋው እውቅ የግሪክ ፈላስፋ ነው ምን አለ መሰለህ ••••" ብሎ ሊቀጥል ሲል•••
በናትህ ተወኝ አልኩትና በንዴት ተነስቼ ክፍሉን ለቅቄለት ወጣሁ ። ስራ አልወጣም ያልኩት ሰውዬ ባጃጄን አስነስቼ ወደ ከተማ ከነፍኩ።
ንዴቴን በስራ ለመርሳት ተፍ ተፍ ስል አምሽቼ ልክ ከምሽቱ አራት ሰአት አከባቢ ከገንደቆሬ ወደ ሼል እየመጣሁ ብሎሰም ሆቴል ኩርባው ጋር እንደደረስኩ አንድ እድሜው በአርባዎቹ መጀመሪያ ላይ የሚሆነው ፈርጠም ያለ ጎልማሳ ሰው ሁለት እጁን በየተራ እያርገበገበ•••
"ባጃጅ ኮንትራት ኮንትራት " አለኝ ። አቆምኩና
የት? አልኩት ፊቱ ላይ እንደእሳት የሚንቀለቀለውን ንዴቱን እያስተዋልኩ
"የት እንደሆነች አላውቅም !
የገባችበት ጉድጓድ ውስጥ ገብቼ እስካገኛት ከኔ ጋር ነህ!
ያልከኝን እከፍላለሁ !"
አለኝና መጀመሪያ የምንሄድበትን ሆቴል ነገረኝ።
እየሄዱን በየመሀሉ •••
" እኔ ላይ! ለኔ እሄ ይገባኛል!" እያለ የአንዱ እጁን መዳፍ በሌላኛው እጁ ቡጢ ያጎነዋል።
ተናድጄ ብወጣ ከኔ የባሰ በንዴት የተከነ ሰው አጋጠመኝና የራሴን ንዴት ረሳሁት። ምን ሆኖ ይሆን እንዲህ ግብግብ ያለው? አልኩ ለራሴ።
ምን ሆነህ ነው ዘመዴ? አልኩት ፈራ ተባ እያልኩ•••
"ወይይይ ሴት ! አይይይ ሴት ገና ለገና ለሳምንት ያህል ለስልጠና ሀረር ሄጃለሁ ስላልኳት በከተማው የለም ብላ እግሬ ከመውጣቱ ቱ የማትረባ !
እሄማ መጀመሪያ የተቀባበለ እንጂ ሄጄ ገና ሶስት ቀን እንኳን ሳይሞላኝ ኬት ይመጣል እስካሁንም እየተጫወትሽብኝ ነበር ማለት ነው እኔ አንቺ ለማግባት ስሰናዳ በግዜ ጉድሽን ያሰማኝ!
ዛሬ ምን እንደሚውጥሽ አያለሁ "! አለ ።
ከንግግሩ ለኔ ጥያቄ መልስ እየሰጠኝ ይሁን ብሶቱን እየተነፈሰ መረዳት ተሳነኝና ግራ ተገብቼ ዝምታን መረጥኩ ። ትንሽ ቆየና •••
"የገዛ ጓደኛዬ አይቷት አይቷት እኮ ነው የደወለልኝ በአይነ ብረቱ ነው ያያት ወይኔ ደጉ ደግነቴን የዋህነቴን አይታ ነው የተጫወተችብኝ እነሱ እኮ ደግ ወንድ አይወዱም ዛሬ እጅ ከፍንጅ ስይዛት ምን እንደሚውጣት አያለሁ አጠገባ ያለውን ሰውዬ ትውጠው እንደሆነ እንተያያለን !"አለ።
ሁሉም ነገር ገባኝ። ፍቅረኛውን ከሰው ጋር ያያት ጓደኛው ደውሎለት እንደመጣ ተረዳሁ። በዚህ ሁኔታው ቢያገኛት ምን ሊፈጠር እንደሚችል ሳስበው ጨነቀኝ ።
ከሰው ጋር ታየች የተባለበት ሆቴል በር ላይ እንደደረስን በፍጥነት
👍1
#ልጩህበት!!
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ምን ሊፈጠር እንደሚችል ሳስበው ጨነቀኝ ።
ከሰው ጋር ታየች የተባለበት ሆቴል በር ላይ እንደደረስን በፍጥነት በመውረድ እጁን እያወናጨፈ ወደ ሆቴሉ ቅጥር ግቢ ሲግሰግስ ወርጄ ተከተልኩት•••
ወደ ውስጥ ስንዘልቅ ያን ያህልም ሰው ስላልነበረ አየት አየት አድርጎ እየወጣን•••
"የለችም ባክህ••• እዚህ መጥታ ጭር ሲል ደብሯት ቦታ እንቀይር ብላው ይሆናል አውቃታለሁ እኮ ልትዝናና ስትወጣ ግርግር ትወዳለች ሰው ከማን ጋር እንደሆነች እንዳያስተውላት ነው መሰለኝ ከኔም ጋር ስትዝናና ቦታው በሰዎች ጢም ካላለ አይመቻትም!
ወይኔ ደጉ ያኔ መች ገባኝ !
አሁን አሁን እኮ ነው ቀስ እያለ ነገረ ስራዋ በሙሉ የሚገለጥልኝ
የባጥ የቋጡን እየለፈለፈ ተመልሰን ባጃጇ ውስጥ እንደገባን
"ንዳው! ንዳው! አለኝ።
ወዴት ልንዳው? ስለው•••
"ከሶስቱ ውጪ አትሆንም!" አለና
ትኖራለች ብሎ የሚጠረጥርባቸውን ሶስት ጭፈራ እና ሆቴል ቤቶች ነግሮኝ
"ከሚቀርብህ ጀምር" አለኝ።
በቅርብ ወዳለው አዙሬ መንዳት እንደጀመርኩ ፍቅረኛውን ከሌላ ሰው ጋር ስትቀብጥ ያያት ጓደኛው ሲደውልለት ከምሽቱ ሁለት ሰአት ተኩል አልፎ እንደነበርና በብስጭት ከሀረር ብቻውን አንድ ሚኒባስ በመያዝ የሙሉ ሰው ከፍሎ እንደመጣ ነገረኝ።
አሳዘነኝ።
ምናልባት የእውነት ሆኖ ከሆነ የሆነው ሆነ የኔ ስጋት ግን በሷ መከዳቱ ሳያንስ በብስጭት ያልሆነ ፀብ ውስጥ ገብቶ መታሰር የሚሉት ሌላ ጣጣ ውስጥ እንዳይገባ ነው።
ቢረጋጋ ጥሩ ነበር ምን ብዬ ላረጋጋው ? ትንሽ አሰብ አደረኩና
ቆይ ብታገኛት••• ማለቴ እንደተባለው ከሰው ጋር ሆና ብታገኛት ምን ልታደርግ ነው?
"እኔ እንጃ ብቻ ላግኛት ያኔ የሚሆነው ይሆናል በናትህ ራቅ ስለሚል ፍጠን!
በበኩሌ ከወንድ ልጅ ጋር ተዝናናች ማለት ወሰለተች ማለት ነው ብዬ አላምንም!
ተዝናንታ ክብሯን ጠብቃ ወደ ቤቷ ልትመለስ አስባ ሊሆን እንደሚችልም ማሰቡ ጥሩ ነው ያንን ካሰብክ ቡሀላ የሚፀፅትህን ነገር ከማድረግ ትቆጠብና ቅድሚያ ቢያንስ እርግጠኛ ለመሆን ትሞክራለህ አይመስልህም ስለው
አይመስለኝም በጭራሽ አይመስለኝም እኔ የፍቅር ሂወቴን በመሰለኝ ሳይሆን ልቤ በሚለኝ በራሴ እምነት ነው የምመራው
በኔ እምነት ሴት ልጅ አንሶላ የተጋፈፈች ቀን ሳይሆን ወንዶችን ቀለል ብላ የመቅረብ ባህሪ ያላት መሆኑን ያወኩ ቀን ነው እምነቷንና እምነቴን የምታጎድለው!"
ማለት?
ቀለል ብላ የመቅረብ ስትል ጭራሽ የወንድ ዘር መቅረብ የለባትም እያልከኝ እንዳይሆን?! ስለው
"አንድ ነገር ልጠይቅህ ?" አለ ።
ጠይቀኝ
"ለግዜው የማይፈልገው ገንዘብ እንዳለው ማበደር እንደሚችል እያወክ 300 ብር አበድረኝ ስትለው የለኝም ብሎ የከለከለህን ሰው በሌላ ግዜ አንድ ሺ ብር አበድረኝ ብለህ ትጠይቀዋለህ?
ካላበድኩ በስተቀር እንኳን ሺ አንድ ብርም አልጠይቀውም ግን እሄ ከፍቅር ወይም ካነሳነው ጉዳይ ጋር ምን አገናኘው?
"ሌላ ጥያቄ ልድገምህ ያኔ በምን መልኩ እንደሚገናኝ ሳልነግርህ እራስህ ትረዳዋለህ"
እሺ ቀጥል
"ታክሲ ውስጥ ባጋጣሚ አጠገብህ የተቀመጠችውን ሴት ልታዋራት ልታጫውታት ስትሞክር ፊቷን እንዳኮማተረች ወደ አንተ አንድም ግዜ እንኳን ዞራ ሳታይ ልክ እንደሹፌሩ ፊት ለፊቷን ብቻ እየተመለከተች ጫወታህን ባጭር ባጭሩ ዝግት የሚያደርግ መልስ እየመለሰች ብታከሽፍብህ ከመለያየታችሁ በፊት ስልክ ቁጥሯን ለመጠየቅ ትደፍራለህ?"
ሰውየው ነገሮችን ቤት በኩል እያገናኛቸው እንደሆነ እያሰላሰልኩ መልስ ሳልሰጠው ስለ ዘገየሁ
"መልስልኛ! ትጠይቃታለህ?!
እንዴ ፊቷን አጨማዳው እንዴት ልጠይቃት እችላለሁ አልጠይቃትም መጀመሪያ ልግባባት ስሞክር ፊት ከነሳችኝ ከታክሲው እስክወርድ ዞሬም ሳላያት እንደምሄድ እርግጠኛ ነኝ።
" አየህ መጀመሪያ ቀለል ብላ አንተ የባጥ የቆጡን ስትቀባጥር ከገለፈጠችልህ ግን ስልክ ለመጠየቅ ቀለለህ ማለት ነው!
ስልክ ስጠይቅ በቀላሉ ከተሰጠህ ደግሞ ደውሎ እንገናኝ ልጋብዝሽ ለማለት ቀለለህ
ግብዣህን በቀላሉ ከተቀበለች ወደ ቀጣዩ ጉዳይህ ለመግባት አልጋ ባልጋ ሆነልህ ማለት ነው ስለዚህ እቺ ሴት የኔዋ ብትሆን እምነቷን የሸረሸረችው መቼ ነው? ብዬ እራሴን ብጠይቅ
በኔ እምነት አልጋ ውስጥ ሳይሆን ታክሲ ውስጥ የተገናኛችሁ ቀን ነው ያን ቀን እኔ ባጋጣሚ እሷ ሳታየኝ ከጀርባችሁ ቁጭ ብዬ ቢሆን መጨረሻችሁን አልጠብቅም እንደከዳችኝ የምቆጥረው ያኔውኑ ነው!"
ሲለኝ የእውነት ነበርና አመለካከቱ ያስደነገጠኝ
በዚህ ሀሳብህ በፍፁም አልስማማም እስቲ አንተንም አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ አንዳንድ ሴቶች
ፍቅረኛም ባልም ሳይኖራቸው ፣ ያሉበት ሁኔታ ፍቅር ለመጀመር ፈቅዶላቸው፣ ውስጣቸውም ፍቅር ለመጀመር ፍላጎት እያለው
በዛ ላይ ሽቅርቅር ብለው እየወጡ በተለያየ አጋጣሚ ከወንዶች ጋር በተገናኙ ቁጥር ወንዶቹ ሊቀርቧቸው ሲሞክሩ ኮሶ የጋቷቸው ይመስል
ፊታቸውን ከስክሰው የወንዶችን ቆሌ የሚገፉት በምን ምክንያት ነው?ስለው•••
"አይነጥላ ነው አዎ አይነ ጥላ ያለባት ሴት ካልሆነች በስተቀር በዚህ ሁኔታ ላይ ሆና በጤናዋ እንደዚህ የምትሆን ሴት ብዙ የምትኖር አይመስለኝም! ብሎኝ አረፈው። ሳይታወቀኝ እየጮህኩ
አትሳሳት ይልቅ
የተግባባች ፣ የሳቀች፣ ወንዶችን በቀላሉ የቀረበች ሴት ሁሉ ሌላ ፍላጎት አላት የተኮሳተረች ሴት ሁሉ ደግሞ ፍላጎት ስለለላት ነው ብለህ መደምደም ትልቅ ስተት መሆኑንን ብታምን የተሻለ ይመስለኛል!
አንተ ምናልባት ከፍቅረኛህ ውጪ ልክ እንደወንዶች ጓደኛችህ በጓደኝነት የምትቀርባቸው ሴቶች ከሌሉ አላቅም!
እኔም ወንድሜቼም ጋደኞቼም በዚህ መልኩ የምንቀርባቸው ሴቶች አሉ አንዳንድ ሴቶች እንደውም ሁሉም ወይም አብዛኛቹ የቅርብ ጋደኛቻቸው ወንዶች እንዲሆኑ እንደሚፈልጉና እንደሆኑም የሚናገሩ አሉ ።
በጋደኝነት ህይወታቸው ወጣ ብሎ ከመዝናናት አንስቶ ብዙ ነገሪችን በጋራ ያሳልፋሉ ያ ማለት በተገኘው አጋጣሚ በሙሉ ሌላ ጉዳይ ውስጥ ይገባሉ ማለት አይደለም!።
"እሱማ ፍቅረኛ ወይም ባል ሳይኖራቸው ሊሆን ይችላል"
ኧረ እያላችው ! እሄውልህ ማናችንም ብንሆን የምንፈልገውን ነገር ለማድረግ የሚከለክለን የፍቅር ጓደኛ መኖር ወይም አለመኖሩ ሳይሆን የውስጣችን ስብእናና የልባችን ትርታ ብቻ ነው
ምንም ነገር ለማድረግ መቀራረብ ሳይሆን መተዋወቅ በማያስፈልግበት በዚህ ዘመን ፍቅረኛህን ታሟኝ የምታደርገው ወንድ አትቅረቢ እያልክ በመጮህ ሳይሆን እራስህን ልቧ ውስጥ ማስቀመጥ ከቻልክ ብቻ ነው ያለበለዚያ ፍቅረኛ ሳይሆን እረኛ ሆነህ ትቀራለህ"! አንተን ለማለት ፈልጌ አይደለም ይቅርታ አመለካከቴን ነው ያወራሁት አልኩትና በዛው ቀጠል አድርጌ•••
ወደ ሆቴሉ እየደረስን ነው ይልቅ አሁን ወደ ጉዳያችን እንመለስና እንደታናሽ ወንድም እምመክርህ ምናልባት ከሰው ጋር ሆና ብታገኛት በኔ በኩል ኩሩና በሳል ወንድ ሆነህ ብታሳያት ደስ ይለኛል!
"ማለት?!"
የተባለው እውነት ሆኖ ከተገኘ በቃ አለ አይደል ምንም ሳትናደድ
ለሁሉም ነገር አመሰግናለሁ እንኳንም በግዜ አወኩሽ መልካሙን ሁሉ እመኝልሻለህ!" ብለህ ብቻ ብትለያት
"ምንምንምምን !? "ያልተነካ ግልግል ያውቃል" አሉ ደሞ መች በግዜ አወኳት ከዛ በፊት ያንከራተተችኝን ተወው እሺ ብላኝ አብረን ከሆንን እንኳን አንድ አመት ከስድስ ወር ሆኖናል እኮ!"
ቢሆንም ገና አልተጋባችሁም ብዬ ነዋ!
"እና ባንጋባስ?!"
ማለቴ እንደምታገባት እርግጠኛ ካልሆነች•••
አልኩና መናደዱን ከድምፁ በመረዳቴ ያሰብኩትን ሳልጨርሰው ዝም አልኩ•••
"ካልሁነች ምን?! ጨርሰዋ !
ኧረ በናትህ ተወኝና
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ምን ሊፈጠር እንደሚችል ሳስበው ጨነቀኝ ።
ከሰው ጋር ታየች የተባለበት ሆቴል በር ላይ እንደደረስን በፍጥነት በመውረድ እጁን እያወናጨፈ ወደ ሆቴሉ ቅጥር ግቢ ሲግሰግስ ወርጄ ተከተልኩት•••
ወደ ውስጥ ስንዘልቅ ያን ያህልም ሰው ስላልነበረ አየት አየት አድርጎ እየወጣን•••
"የለችም ባክህ••• እዚህ መጥታ ጭር ሲል ደብሯት ቦታ እንቀይር ብላው ይሆናል አውቃታለሁ እኮ ልትዝናና ስትወጣ ግርግር ትወዳለች ሰው ከማን ጋር እንደሆነች እንዳያስተውላት ነው መሰለኝ ከኔም ጋር ስትዝናና ቦታው በሰዎች ጢም ካላለ አይመቻትም!
ወይኔ ደጉ ያኔ መች ገባኝ !
አሁን አሁን እኮ ነው ቀስ እያለ ነገረ ስራዋ በሙሉ የሚገለጥልኝ
የባጥ የቋጡን እየለፈለፈ ተመልሰን ባጃጇ ውስጥ እንደገባን
"ንዳው! ንዳው! አለኝ።
ወዴት ልንዳው? ስለው•••
"ከሶስቱ ውጪ አትሆንም!" አለና
ትኖራለች ብሎ የሚጠረጥርባቸውን ሶስት ጭፈራ እና ሆቴል ቤቶች ነግሮኝ
"ከሚቀርብህ ጀምር" አለኝ።
በቅርብ ወዳለው አዙሬ መንዳት እንደጀመርኩ ፍቅረኛውን ከሌላ ሰው ጋር ስትቀብጥ ያያት ጓደኛው ሲደውልለት ከምሽቱ ሁለት ሰአት ተኩል አልፎ እንደነበርና በብስጭት ከሀረር ብቻውን አንድ ሚኒባስ በመያዝ የሙሉ ሰው ከፍሎ እንደመጣ ነገረኝ።
አሳዘነኝ።
ምናልባት የእውነት ሆኖ ከሆነ የሆነው ሆነ የኔ ስጋት ግን በሷ መከዳቱ ሳያንስ በብስጭት ያልሆነ ፀብ ውስጥ ገብቶ መታሰር የሚሉት ሌላ ጣጣ ውስጥ እንዳይገባ ነው።
ቢረጋጋ ጥሩ ነበር ምን ብዬ ላረጋጋው ? ትንሽ አሰብ አደረኩና
ቆይ ብታገኛት••• ማለቴ እንደተባለው ከሰው ጋር ሆና ብታገኛት ምን ልታደርግ ነው?
"እኔ እንጃ ብቻ ላግኛት ያኔ የሚሆነው ይሆናል በናትህ ራቅ ስለሚል ፍጠን!
በበኩሌ ከወንድ ልጅ ጋር ተዝናናች ማለት ወሰለተች ማለት ነው ብዬ አላምንም!
ተዝናንታ ክብሯን ጠብቃ ወደ ቤቷ ልትመለስ አስባ ሊሆን እንደሚችልም ማሰቡ ጥሩ ነው ያንን ካሰብክ ቡሀላ የሚፀፅትህን ነገር ከማድረግ ትቆጠብና ቅድሚያ ቢያንስ እርግጠኛ ለመሆን ትሞክራለህ አይመስልህም ስለው
አይመስለኝም በጭራሽ አይመስለኝም እኔ የፍቅር ሂወቴን በመሰለኝ ሳይሆን ልቤ በሚለኝ በራሴ እምነት ነው የምመራው
በኔ እምነት ሴት ልጅ አንሶላ የተጋፈፈች ቀን ሳይሆን ወንዶችን ቀለል ብላ የመቅረብ ባህሪ ያላት መሆኑን ያወኩ ቀን ነው እምነቷንና እምነቴን የምታጎድለው!"
ማለት?
ቀለል ብላ የመቅረብ ስትል ጭራሽ የወንድ ዘር መቅረብ የለባትም እያልከኝ እንዳይሆን?! ስለው
"አንድ ነገር ልጠይቅህ ?" አለ ።
ጠይቀኝ
"ለግዜው የማይፈልገው ገንዘብ እንዳለው ማበደር እንደሚችል እያወክ 300 ብር አበድረኝ ስትለው የለኝም ብሎ የከለከለህን ሰው በሌላ ግዜ አንድ ሺ ብር አበድረኝ ብለህ ትጠይቀዋለህ?
ካላበድኩ በስተቀር እንኳን ሺ አንድ ብርም አልጠይቀውም ግን እሄ ከፍቅር ወይም ካነሳነው ጉዳይ ጋር ምን አገናኘው?
"ሌላ ጥያቄ ልድገምህ ያኔ በምን መልኩ እንደሚገናኝ ሳልነግርህ እራስህ ትረዳዋለህ"
እሺ ቀጥል
"ታክሲ ውስጥ ባጋጣሚ አጠገብህ የተቀመጠችውን ሴት ልታዋራት ልታጫውታት ስትሞክር ፊቷን እንዳኮማተረች ወደ አንተ አንድም ግዜ እንኳን ዞራ ሳታይ ልክ እንደሹፌሩ ፊት ለፊቷን ብቻ እየተመለከተች ጫወታህን ባጭር ባጭሩ ዝግት የሚያደርግ መልስ እየመለሰች ብታከሽፍብህ ከመለያየታችሁ በፊት ስልክ ቁጥሯን ለመጠየቅ ትደፍራለህ?"
ሰውየው ነገሮችን ቤት በኩል እያገናኛቸው እንደሆነ እያሰላሰልኩ መልስ ሳልሰጠው ስለ ዘገየሁ
"መልስልኛ! ትጠይቃታለህ?!
እንዴ ፊቷን አጨማዳው እንዴት ልጠይቃት እችላለሁ አልጠይቃትም መጀመሪያ ልግባባት ስሞክር ፊት ከነሳችኝ ከታክሲው እስክወርድ ዞሬም ሳላያት እንደምሄድ እርግጠኛ ነኝ።
" አየህ መጀመሪያ ቀለል ብላ አንተ የባጥ የቆጡን ስትቀባጥር ከገለፈጠችልህ ግን ስልክ ለመጠየቅ ቀለለህ ማለት ነው!
ስልክ ስጠይቅ በቀላሉ ከተሰጠህ ደግሞ ደውሎ እንገናኝ ልጋብዝሽ ለማለት ቀለለህ
ግብዣህን በቀላሉ ከተቀበለች ወደ ቀጣዩ ጉዳይህ ለመግባት አልጋ ባልጋ ሆነልህ ማለት ነው ስለዚህ እቺ ሴት የኔዋ ብትሆን እምነቷን የሸረሸረችው መቼ ነው? ብዬ እራሴን ብጠይቅ
በኔ እምነት አልጋ ውስጥ ሳይሆን ታክሲ ውስጥ የተገናኛችሁ ቀን ነው ያን ቀን እኔ ባጋጣሚ እሷ ሳታየኝ ከጀርባችሁ ቁጭ ብዬ ቢሆን መጨረሻችሁን አልጠብቅም እንደከዳችኝ የምቆጥረው ያኔውኑ ነው!"
ሲለኝ የእውነት ነበርና አመለካከቱ ያስደነገጠኝ
በዚህ ሀሳብህ በፍፁም አልስማማም እስቲ አንተንም አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ አንዳንድ ሴቶች
ፍቅረኛም ባልም ሳይኖራቸው ፣ ያሉበት ሁኔታ ፍቅር ለመጀመር ፈቅዶላቸው፣ ውስጣቸውም ፍቅር ለመጀመር ፍላጎት እያለው
በዛ ላይ ሽቅርቅር ብለው እየወጡ በተለያየ አጋጣሚ ከወንዶች ጋር በተገናኙ ቁጥር ወንዶቹ ሊቀርቧቸው ሲሞክሩ ኮሶ የጋቷቸው ይመስል
ፊታቸውን ከስክሰው የወንዶችን ቆሌ የሚገፉት በምን ምክንያት ነው?ስለው•••
"አይነጥላ ነው አዎ አይነ ጥላ ያለባት ሴት ካልሆነች በስተቀር በዚህ ሁኔታ ላይ ሆና በጤናዋ እንደዚህ የምትሆን ሴት ብዙ የምትኖር አይመስለኝም! ብሎኝ አረፈው። ሳይታወቀኝ እየጮህኩ
አትሳሳት ይልቅ
የተግባባች ፣ የሳቀች፣ ወንዶችን በቀላሉ የቀረበች ሴት ሁሉ ሌላ ፍላጎት አላት የተኮሳተረች ሴት ሁሉ ደግሞ ፍላጎት ስለለላት ነው ብለህ መደምደም ትልቅ ስተት መሆኑንን ብታምን የተሻለ ይመስለኛል!
አንተ ምናልባት ከፍቅረኛህ ውጪ ልክ እንደወንዶች ጓደኛችህ በጓደኝነት የምትቀርባቸው ሴቶች ከሌሉ አላቅም!
እኔም ወንድሜቼም ጋደኞቼም በዚህ መልኩ የምንቀርባቸው ሴቶች አሉ አንዳንድ ሴቶች እንደውም ሁሉም ወይም አብዛኛቹ የቅርብ ጋደኛቻቸው ወንዶች እንዲሆኑ እንደሚፈልጉና እንደሆኑም የሚናገሩ አሉ ።
በጋደኝነት ህይወታቸው ወጣ ብሎ ከመዝናናት አንስቶ ብዙ ነገሪችን በጋራ ያሳልፋሉ ያ ማለት በተገኘው አጋጣሚ በሙሉ ሌላ ጉዳይ ውስጥ ይገባሉ ማለት አይደለም!።
"እሱማ ፍቅረኛ ወይም ባል ሳይኖራቸው ሊሆን ይችላል"
ኧረ እያላችው ! እሄውልህ ማናችንም ብንሆን የምንፈልገውን ነገር ለማድረግ የሚከለክለን የፍቅር ጓደኛ መኖር ወይም አለመኖሩ ሳይሆን የውስጣችን ስብእናና የልባችን ትርታ ብቻ ነው
ምንም ነገር ለማድረግ መቀራረብ ሳይሆን መተዋወቅ በማያስፈልግበት በዚህ ዘመን ፍቅረኛህን ታሟኝ የምታደርገው ወንድ አትቅረቢ እያልክ በመጮህ ሳይሆን እራስህን ልቧ ውስጥ ማስቀመጥ ከቻልክ ብቻ ነው ያለበለዚያ ፍቅረኛ ሳይሆን እረኛ ሆነህ ትቀራለህ"! አንተን ለማለት ፈልጌ አይደለም ይቅርታ አመለካከቴን ነው ያወራሁት አልኩትና በዛው ቀጠል አድርጌ•••
ወደ ሆቴሉ እየደረስን ነው ይልቅ አሁን ወደ ጉዳያችን እንመለስና እንደታናሽ ወንድም እምመክርህ ምናልባት ከሰው ጋር ሆና ብታገኛት በኔ በኩል ኩሩና በሳል ወንድ ሆነህ ብታሳያት ደስ ይለኛል!
"ማለት?!"
የተባለው እውነት ሆኖ ከተገኘ በቃ አለ አይደል ምንም ሳትናደድ
ለሁሉም ነገር አመሰግናለሁ እንኳንም በግዜ አወኩሽ መልካሙን ሁሉ እመኝልሻለህ!" ብለህ ብቻ ብትለያት
"ምንምንምምን !? "ያልተነካ ግልግል ያውቃል" አሉ ደሞ መች በግዜ አወኳት ከዛ በፊት ያንከራተተችኝን ተወው እሺ ብላኝ አብረን ከሆንን እንኳን አንድ አመት ከስድስ ወር ሆኖናል እኮ!"
ቢሆንም ገና አልተጋባችሁም ብዬ ነዋ!
"እና ባንጋባስ?!"
ማለቴ እንደምታገባት እርግጠኛ ካልሆነች•••
አልኩና መናደዱን ከድምፁ በመረዳቴ ያሰብኩትን ሳልጨርሰው ዝም አልኩ•••
"ካልሁነች ምን?! ጨርሰዋ !
ኧረ በናትህ ተወኝና
👍2
#ልጩህበት!!
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ኧረ በናትህ ተወኝና ዝም ብለህ ንዳ አንተ ደሞ
ነው ወይስ አብሯት ያለው ሰውዬ አጎትህ ነው ብዙ ተከራከርክላት እኮ !"
ሲለኝ እውነትም ዝም ብዬ ብነዳስ አልኩና ዝም አልኩ ።
እንደደረስን ምንም ሳይለኝ ወርዶ ወደ ሆቴሉ ሲገባ ተከትየው ገባሁ።
በር ላይ ቆም ሲል ቆምኩ።
ወደውስጥ ገልመጥ ገልመጥ አደረገና ካጠገቤ ድንገት ተፈናጥሮ በመሄድ ቀዝቀዝ ባለው ዘፈን ጥንድ ጥንድ ሆነው ተጣብቀው ከሚወዘወዙት መሀል•••
በስተግራዋ እስከ ባቷ መገባደጃ የተቀደደ ትከሻውን በዞሩ ሁለት ቀጫጭን ገመዶች ተንጠልጥሎ ከደረቷ ጀምሮ ቁልቁል ገላዋ ላይ ቀዳዋ እስኪመስል የተጣበቀ እሮዝ ቀለም ያለው የራት ልብስ ለብሷ አብሯት እሚደንሰው ሰው አንገት ውስጥ በፍቅር መርከብ እየተንሳፈፈች የምትደንሰውን ሴት ክንዷን ይዞ በመጎተት ከሰውየው እቅፍ ውስጥ መንጭቆ አወጣት!
እሷ ምን መጣ ብላ በድንጋጤ ስትዞር፤ እሱ ፊቷን አይቶ የሱ ፍቅር አለመሆኗን ሲረዳና አብሯት ያለው ሰው ይቅርታ የምትለውን ቃል ከፉ አውጥቶ እስኪጨርሳት እንኳን ግዜ ሳይሰጠው ተደፈርኩ በሚል ስሜት እንደነብር ተወርውሮ አንገቱን ሲያንቀው ዘልዬ መሀላቸው ገባሁ!
ይቅርታ አርግለት ባባ በስተት ነው በስተት ነው ስለው መጀመሪያውኑ ፊቷን እንዳየ ሲደነግጥ አስተውሎት ነበር መሰለኝ ከማነቅ ውጪ ቦክስ እንኳን ሳይሰነዝር•••
"እብድህን ወደዛ ይዘህልን ውጣ ባክህ ! ብሎ እሱን ገፈተረውና ሽምቅቅ ብላ ወደቆመችው ፍቅሩ ዞሮ •••
" አስደነገጠሽ አይደል የኔ ማር?!" አላት። እኛም በፍጥነት ተያይዘን ውልቅ አልን።
ባጃጅ ውስጥ ገብተን ወደሶስተኛው ቤት ጉዞ እንደጀመርን ድንጋጤው ለቀቀው መሰለኝ•••
"አይገርምም የሰይጣን ስራ ቁመቷ፣ ከለሯ፣ ፀጉራ ከነ አያያዟ እራሷን ቁጭ እኮ ነች በዛላይ የለበሰችው ልብስ ተውሳት ነው እንዴ እውነቴን ነው ሀሉንም ነገር ከፍቅረኛዬ የተዋሰችው እኮ ነው እምትመስለው ቢያንስ እንኳን በውፍረት መለያየት የለባቸውም ደባዋ እራሱ ቁጭ የኔዋን!" ሲል
ሳቄን በጭራሽ መቆጣጠር አልቻልኩም ኪኪኪኪኪ•••
"ሳቅ አንተ ምን አለብህ!"
እና በዛች ሰከንድ ውስጥ እሄን ሁሉ ደባዋን (ቂጧን ) ሳይቀር ማየትህ ቢያስቀኝ በኔ ይፈረዳል?
"ኧረ አይፈረድም"
እሄኔ ልጅቷ ከፍቅረኛህ ጋር በብዙ ነገሯ ትለያይ ይሆናል አንዳንዴ ውስጣችን የሚፈልገውን ነው አይናችን የሚያየው ለዛ ይሆናል።
አልኩትና በሆዴ ዛሬማ የከተሟዋ ሴቶች ሁሉ እሷን መስለው ነው እሚታዩህ ብዬ አከልኩበት።
ሶስተኛው ቤት ገባን እዛም አልነበረችም።
አሁን የቀረን አንድ ቦታ ብቻ ነው ወደዛው መብረር ጀመርን።
ልንደርስ ትንሽ ሲቀረን መንገድ ላይ ወዳለ ወደ አንድ ከፍንዳታዎችና ከዩንቨርስቲ ተማሪዎች ውጪ ሌላ ሰው ወደማይገባበት ቀውጢ ጭፈራ ቤት እየተገላመጥኩ መቸስ እዚህ አትኖርም አደል ስለው•••
ድንገት በሩ ላይ ኤዱን አየኋት ሊያውም ከዛ ልጅ ጋር!
በፍጥነት እየነዳ ድንገት ሰው እንደገባበት ሹፌር ልቤ ስንጥቅ ሲል ፍሬኑን ጭምቅ አደረኩት ባጃጇ ሲጢጢጢጢጢጢ ብላ ቀጥ ስትል ሰውየው ተፈናጥሮ ወደ ትከሻዬ መጣና ሳይመለስ •••
"ምነው! ሰው ገባብህ? ውሻ ገባብህ?" እያለ ወደ ፊት በማንጋጠጥ ምን እንደገባብኝ ለማየት ሲሞክር •••
ሰው አይቼ ነው።አልኩት።
"ማንን? አየሀት? እሷን ነው? የቱጋ? የታለች?" ሲል •••
ማነች እሷ አልኩት ግራ ተጋብቼ
" የኔዋ ነቻ! የኔዋ ጉድ ሌላ ማንን ታያለህ!"
ወይ ጉድ••••
"የጨነቀው እርጉዝ ያገባል ብለው ከሚተርቱ የጨነቀው የሚናገረውን አያውቀው ቢሉ ኖሮ ሳይሻል አይቀርም እስቲ አሁን የሱን ፍቅረኛ የት አውቂያት ነው የማያት ?
እንኳን ለኔ ለራሱም ሳትጠፋበት አትቀርም እያልኩ ውስጥ ጫጫታው ስላልተመቻቸው ሳይሆን አይቀርም ስልክ ለማናገር ወጥተው አንድ ስልክ እየተቀባበሉ በጋራ ከሚያውቁት ከሌላ ሰው ጋር እያወሩና እርስ በርስ እየተያዩ ወደ ሚሳሳቁት ወደ እነ ኤደን ከርቀት እንዳፈጠጥኩ •••
ወርደህ ቀጥ ብለህ ሂድላት ከዛ ኤዱ ቅድም ከቤት ስትወጡ ወደ ግቢ ነው እምንሄደው ብለሽ መዋሸቱ ለምን አስፈለገ እኔን ዋሽኝ ችግር የለውም ግን በዚህ ሰአት ሊያውም እዚህ በየቀኑ ፀብ በማያጣው ጭፈራ ቤት ውስጥ ምን ትሰሪያለሽ በላት በላት የሚል ስሜት ተሰማኝ።
ዘወር ብዬ ሰውየውን ሳየው እሱም ግራ ተጋብቶ እኔን ተከትሎ እነ ኤዱ ላይ አፍጥጧል።
መለስ አለና " ማነች? ታውቃታለህ? " አለኝ
ማነች ልበለው? አዎ ያክስቴ ልጅ ነች፤ የዩንቨርስቲ ተማሪ ነች በዚህ ሰአት ከወንድ ጋር ጭፈራ ቤት••••
አላስጨረሰኝም •••
"ታድያ ምን ችግር አለው አለው አብረው ተዝናንተው የሚለያዩ ንፁህ ጋደኛሞች ሊሆኑ ይችላሉ ። አለኝ በስላቅ ።
በንዴት •••
አዎ ችግር የለውም ይዝናኑ እኛም እንሂድ አልኩና ባጃጇን አስነስቼ ወደ መጨረሻው ቤት ጋለብኳት።
ደርሰን እሱ ከፊት እኔ ከጀርባው ተከታትለን እንደገባን
"ያቿትና"
አለኝ ፊት ለፊት ካንድ ሰው ጋር የተቀመጠች ቆንጂዬ ሴት ተመለከትኩ ።
ወደሱ ስዞር አራት ጣቶቹን ከንፈሩ ላይ ጭኖ እንዳፈጠጠባቸው ትንሽ ቆየና
"ውይ ውርዴት !
አቤት ቅሌት !
እሄ እኮ ውጪ ሀገር የነበረ ያክስቷ ልጅ ነው የሰርጋችሁን ግማሽ ወጪ እኔ እችላችሃምሀለሁ ብሎ ቃል ገብቶልናል! በቅርብ ነው የመጣው።
ጓደኛዬም ያላወቀው ለዛ ነው!
እነደመጣ አዲስ አበባ ነበር ያረፈው ሰሞኑን ወደ ድሬ ይመጣል ስትለኝ ነበር እንደዛ ሲፎክር የነበረው ሰው ጭራሽ "ደብቀኝ እንዳታየኝ ! "
እያለ እኔን ጎትቶ ከጀርባዬ ተደበቀና
"ዝም ብለህ ወደ ኋላ ና እንውጣ!" አለኝ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ኧረ በናትህ ተወኝና ዝም ብለህ ንዳ አንተ ደሞ
ነው ወይስ አብሯት ያለው ሰውዬ አጎትህ ነው ብዙ ተከራከርክላት እኮ !"
ሲለኝ እውነትም ዝም ብዬ ብነዳስ አልኩና ዝም አልኩ ።
እንደደረስን ምንም ሳይለኝ ወርዶ ወደ ሆቴሉ ሲገባ ተከትየው ገባሁ።
በር ላይ ቆም ሲል ቆምኩ።
ወደውስጥ ገልመጥ ገልመጥ አደረገና ካጠገቤ ድንገት ተፈናጥሮ በመሄድ ቀዝቀዝ ባለው ዘፈን ጥንድ ጥንድ ሆነው ተጣብቀው ከሚወዘወዙት መሀል•••
በስተግራዋ እስከ ባቷ መገባደጃ የተቀደደ ትከሻውን በዞሩ ሁለት ቀጫጭን ገመዶች ተንጠልጥሎ ከደረቷ ጀምሮ ቁልቁል ገላዋ ላይ ቀዳዋ እስኪመስል የተጣበቀ እሮዝ ቀለም ያለው የራት ልብስ ለብሷ አብሯት እሚደንሰው ሰው አንገት ውስጥ በፍቅር መርከብ እየተንሳፈፈች የምትደንሰውን ሴት ክንዷን ይዞ በመጎተት ከሰውየው እቅፍ ውስጥ መንጭቆ አወጣት!
እሷ ምን መጣ ብላ በድንጋጤ ስትዞር፤ እሱ ፊቷን አይቶ የሱ ፍቅር አለመሆኗን ሲረዳና አብሯት ያለው ሰው ይቅርታ የምትለውን ቃል ከፉ አውጥቶ እስኪጨርሳት እንኳን ግዜ ሳይሰጠው ተደፈርኩ በሚል ስሜት እንደነብር ተወርውሮ አንገቱን ሲያንቀው ዘልዬ መሀላቸው ገባሁ!
ይቅርታ አርግለት ባባ በስተት ነው በስተት ነው ስለው መጀመሪያውኑ ፊቷን እንዳየ ሲደነግጥ አስተውሎት ነበር መሰለኝ ከማነቅ ውጪ ቦክስ እንኳን ሳይሰነዝር•••
"እብድህን ወደዛ ይዘህልን ውጣ ባክህ ! ብሎ እሱን ገፈተረውና ሽምቅቅ ብላ ወደቆመችው ፍቅሩ ዞሮ •••
" አስደነገጠሽ አይደል የኔ ማር?!" አላት። እኛም በፍጥነት ተያይዘን ውልቅ አልን።
ባጃጅ ውስጥ ገብተን ወደሶስተኛው ቤት ጉዞ እንደጀመርን ድንጋጤው ለቀቀው መሰለኝ•••
"አይገርምም የሰይጣን ስራ ቁመቷ፣ ከለሯ፣ ፀጉራ ከነ አያያዟ እራሷን ቁጭ እኮ ነች በዛላይ የለበሰችው ልብስ ተውሳት ነው እንዴ እውነቴን ነው ሀሉንም ነገር ከፍቅረኛዬ የተዋሰችው እኮ ነው እምትመስለው ቢያንስ እንኳን በውፍረት መለያየት የለባቸውም ደባዋ እራሱ ቁጭ የኔዋን!" ሲል
ሳቄን በጭራሽ መቆጣጠር አልቻልኩም ኪኪኪኪኪ•••
"ሳቅ አንተ ምን አለብህ!"
እና በዛች ሰከንድ ውስጥ እሄን ሁሉ ደባዋን (ቂጧን ) ሳይቀር ማየትህ ቢያስቀኝ በኔ ይፈረዳል?
"ኧረ አይፈረድም"
እሄኔ ልጅቷ ከፍቅረኛህ ጋር በብዙ ነገሯ ትለያይ ይሆናል አንዳንዴ ውስጣችን የሚፈልገውን ነው አይናችን የሚያየው ለዛ ይሆናል።
አልኩትና በሆዴ ዛሬማ የከተሟዋ ሴቶች ሁሉ እሷን መስለው ነው እሚታዩህ ብዬ አከልኩበት።
ሶስተኛው ቤት ገባን እዛም አልነበረችም።
አሁን የቀረን አንድ ቦታ ብቻ ነው ወደዛው መብረር ጀመርን።
ልንደርስ ትንሽ ሲቀረን መንገድ ላይ ወዳለ ወደ አንድ ከፍንዳታዎችና ከዩንቨርስቲ ተማሪዎች ውጪ ሌላ ሰው ወደማይገባበት ቀውጢ ጭፈራ ቤት እየተገላመጥኩ መቸስ እዚህ አትኖርም አደል ስለው•••
ድንገት በሩ ላይ ኤዱን አየኋት ሊያውም ከዛ ልጅ ጋር!
በፍጥነት እየነዳ ድንገት ሰው እንደገባበት ሹፌር ልቤ ስንጥቅ ሲል ፍሬኑን ጭምቅ አደረኩት ባጃጇ ሲጢጢጢጢጢጢ ብላ ቀጥ ስትል ሰውየው ተፈናጥሮ ወደ ትከሻዬ መጣና ሳይመለስ •••
"ምነው! ሰው ገባብህ? ውሻ ገባብህ?" እያለ ወደ ፊት በማንጋጠጥ ምን እንደገባብኝ ለማየት ሲሞክር •••
ሰው አይቼ ነው።አልኩት።
"ማንን? አየሀት? እሷን ነው? የቱጋ? የታለች?" ሲል •••
ማነች እሷ አልኩት ግራ ተጋብቼ
" የኔዋ ነቻ! የኔዋ ጉድ ሌላ ማንን ታያለህ!"
ወይ ጉድ••••
"የጨነቀው እርጉዝ ያገባል ብለው ከሚተርቱ የጨነቀው የሚናገረውን አያውቀው ቢሉ ኖሮ ሳይሻል አይቀርም እስቲ አሁን የሱን ፍቅረኛ የት አውቂያት ነው የማያት ?
እንኳን ለኔ ለራሱም ሳትጠፋበት አትቀርም እያልኩ ውስጥ ጫጫታው ስላልተመቻቸው ሳይሆን አይቀርም ስልክ ለማናገር ወጥተው አንድ ስልክ እየተቀባበሉ በጋራ ከሚያውቁት ከሌላ ሰው ጋር እያወሩና እርስ በርስ እየተያዩ ወደ ሚሳሳቁት ወደ እነ ኤደን ከርቀት እንዳፈጠጥኩ •••
ወርደህ ቀጥ ብለህ ሂድላት ከዛ ኤዱ ቅድም ከቤት ስትወጡ ወደ ግቢ ነው እምንሄደው ብለሽ መዋሸቱ ለምን አስፈለገ እኔን ዋሽኝ ችግር የለውም ግን በዚህ ሰአት ሊያውም እዚህ በየቀኑ ፀብ በማያጣው ጭፈራ ቤት ውስጥ ምን ትሰሪያለሽ በላት በላት የሚል ስሜት ተሰማኝ።
ዘወር ብዬ ሰውየውን ሳየው እሱም ግራ ተጋብቶ እኔን ተከትሎ እነ ኤዱ ላይ አፍጥጧል።
መለስ አለና " ማነች? ታውቃታለህ? " አለኝ
ማነች ልበለው? አዎ ያክስቴ ልጅ ነች፤ የዩንቨርስቲ ተማሪ ነች በዚህ ሰአት ከወንድ ጋር ጭፈራ ቤት••••
አላስጨረሰኝም •••
"ታድያ ምን ችግር አለው አለው አብረው ተዝናንተው የሚለያዩ ንፁህ ጋደኛሞች ሊሆኑ ይችላሉ ። አለኝ በስላቅ ።
በንዴት •••
አዎ ችግር የለውም ይዝናኑ እኛም እንሂድ አልኩና ባጃጇን አስነስቼ ወደ መጨረሻው ቤት ጋለብኳት።
ደርሰን እሱ ከፊት እኔ ከጀርባው ተከታትለን እንደገባን
"ያቿትና"
አለኝ ፊት ለፊት ካንድ ሰው ጋር የተቀመጠች ቆንጂዬ ሴት ተመለከትኩ ።
ወደሱ ስዞር አራት ጣቶቹን ከንፈሩ ላይ ጭኖ እንዳፈጠጠባቸው ትንሽ ቆየና
"ውይ ውርዴት !
አቤት ቅሌት !
እሄ እኮ ውጪ ሀገር የነበረ ያክስቷ ልጅ ነው የሰርጋችሁን ግማሽ ወጪ እኔ እችላችሃምሀለሁ ብሎ ቃል ገብቶልናል! በቅርብ ነው የመጣው።
ጓደኛዬም ያላወቀው ለዛ ነው!
እነደመጣ አዲስ አበባ ነበር ያረፈው ሰሞኑን ወደ ድሬ ይመጣል ስትለኝ ነበር እንደዛ ሲፎክር የነበረው ሰው ጭራሽ "ደብቀኝ እንዳታየኝ ! "
እያለ እኔን ጎትቶ ከጀርባዬ ተደበቀና
"ዝም ብለህ ወደ ኋላ ና እንውጣ!" አለኝ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#ልጩህበት!!
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ደርሰን እሱ ከፊት እኔ ከጀርባው ተከታትለን እንደገባን
"ያቿትና"
አለኝ ፊት ለፊት ካንድ ሰው ጋር የተቀመጠች ቆንጂዬ ሴት ተመለከትኩ ።
ወደሱ ስዞር አራት ጣቶቹን ከንፈሩ ላይ ጭኖ እንዳፈጠጠባቸው ትንሽ ቆየና
"ውይ ውርዴት !
አቤት ቅሌት !
እሄ እኮ ውጪ ሀገር የነበረ ያክስቷ ልጅ ነው የሰርጋችሁን ግማሽ ወጪ እኔ እችላችሃምሀለሁ ብሎ ቃል ገብቴልናል! በቅርብ ነው የመጣው።
ጓደኛዬም ያላወቀው ለዛ ነው!
እነደመጣ አዲስ አበባ ነበር ያረፈው ሰሞኑን ወደ ድሬ ይመጣል ስትለኝ ነበር እንደዛ ሲፎክር የነበረው ሰው ጭራሽ "ደብቀኝ እንዳታየኝ ! "
እያለ እኔን ጎትቶ ከጀርባዬ ተደበቀና
"ዝም ብለህ ወደ ኋላ ና እንውጣ!" አለኝ።
እየተጓተትን ወጣን።
እሺ አሁን ወዴት እንሂድ? ስለው•••
"ዛሬ በቃ ካንተ ጋር የመረጥከው ቦታ ስጠጣ አድሬ ጥዋት በዛው ወደሀረር መመለስ ነው
እምፈልገው ግን ፍቃደኛ ከሆንክ ነው ?"
አለኝ እኔም በኤዱ ተከፍቼ ስለነበር መጠጣት ፈለኩ በሀሳቡ ተስማማሁና ተያይዘን ሄድን እየጠጣን ስለራሱ ብዙ እያወራልኝ ቆየና ድንገት በመሀል •••
"ቅድም ከልጁ ጋር ያየሀት ልጅ ግን እውነት ያክስትህ ልጅ ነች እንዳትዎሸኝ በናትህ እ ያክስትህ ልጅ ነች?"
ለምን ጠየከኝ ? አልኩት
"እኔ እንጃ የሆነ የፍቅር ስሜት አይንህ ውስጥ ያነበብኩ መስሎኝ ነው እ ተሳሳትኩ?!"
ኧረ በጭራሽ የፍቅር ስሜት እኔ ላይ ልታነብማ አትችልም ግን ያክስቴ ልጅ አይደለችም ብዬ ስለኤዱ በስሱ ነገርኩት ጎህ ሲቀድ ትዝ ይለኛል ግን ብዙ ከመጠጣቴ የተነሳ መች? እና እንዴት? እሱ ወደ ሀረር እኔም ወደ ቤት እንደገባሁ ትዝ አይለኝም።
በነጋታው ስድስት ሰአት አከባቢ ተነሳሁና ገላዬን ተጣጥቤ ወደ ስራ ወጣሁ።
በአከባቢያችን ባለ አንድ ምግብ ቤት ገብቼ ምሳ አዘዝኩና ከመምጣቱ በፊት ኤደንጋ ደወልኩ።
አነሳችው ድምፁዋ ስትጨፍር ማደሯን ይመሰክራል ሰላምታ ከተለዋወጥን ቡሀላ•••
የት ነሽ?
"ዶርም ነኝ ጋደም ብዬ !
ትናንት ታክሲ አገኛችሁ?
አዎ ዳንዬ ካንተ ጋር እንደወጣን ወድያው ነው ያገኘነው;"
በግዜ ገባችሁ?
አዎ ምነው?
አይ ምንም ከአንደበትሽ ልስማው ብዬ ነው!
ምኑን ዳኒ?
በቃ ተይው!
ምን ሆነሀል ዳኒ!?
ምን ሆንኩ?!
"አይ ምን እንደጠየከኝ እንኳን ሳይገባኝ በቃ ተይው ስትለኝ ግራ ገብቶኝ ነው"
በቃ እንደውም እንኳን ያልገባሽ ወሬ እንቀይር••
እሺ ካልክ!
እሺ!
"እሺ ምን!"
እሺ ምንም!
እንዴ ዳኒ ግራ አጋባከኝ እኮ ወሬ እንቀይር አላልክም እሺ ስለ ምን እናውራ?"
ምን አዲስ ነገር አለ?
"ምንም ዳኒዬ ምን አዲስ ነገር ይኖራል ብለህ ነው"
በቃ እሺ
በቃ እሺ ምን?
በቃ እሺ ቻዋ አዲስ ነገር ከሌለ!
"እሺ ቻው ግን•••" እያለች ስልኩን ዘጋሁት።
ስራው አስጠላኝ ባጃጄን ላጣቢ ሰጥቼ ገብቼ ተኛሁ።
ከትንሽ ቆይታ ቡሀላ ጆሲ እና ያ ጅምር እብድ ጓደኛው በርጫቸውን ይዘው እየተሳሳቁ ሲገቡ በሆዴ ተደፍቼ በመተኛት የተኛ ሰው መሰልኩ።
ጆሲ••••" እንዴ ዳኒ ስራ ወጥተህ አልነበር እንዴ በል ተነስ አትደብረን •••" ምናምን እያለ ሊቀሰቅሰኝ ቢሞክርም አውቆ የተኛን እንዲሉ ዝም አልኩ።
ከቆይታ ቡሀላ ከነመኖሬም ረስተውኝ ጆሲ እና ጓደኛው በራሳቸው አለም ውስጥ ገብተው የባጥ የቋጡን መዘባረቅ ጀመሩ።
የተኛሁ መስዬ ብተኛም ወሬያቸው እረፍት ነሳኝ ከአንዱ ርእስ ወደ ሌላ ለመሄድ ምንም አይነት ቅድመ ሁኔታ አይጠብቁም ወሬያቸውን ይጀምሩታል እንጂ አያልቅም።
ብስጭትጭት ብዬ በመነሳት ቤቱን ጥየላቸው ስወጣ ጆሲ•••
"ና እንጂ ዳንዬ! ወዴት ልትሄድ ነው? ረበሽንህ እንዴ! ማታ ሰክረህ ምን ስትል እንደነበር ልንገርህ ክክክክ !"
መልስ ሳልሰጠው ወጥቼ ሄድኩ።
ከዛን ቀን ቡሀላ ህይወቴ እራሱ የሰከረ ሆኖ ታየኝ ከኤዱ ጋር እንኳን ልንገናኝ ስልክ ተደዋውለን ሰላም ሰላም ከመባባል ውጪ የረባ ነገር ሳናወራ ወራቶች ተቆጠሩ የሷን ባላውቅም እኔ ግን ከራሴ ጋር ስለሷ ሳላወራ አድሬ አላውቅም ።
ጥፋተኛዋ እሷ ሆና ሳለ ስለመገናኘት አንስታብኝ ስለማታውቅ እልህ ያዘኝ ።አንድም ቀን ላግኝሽ ሳልላት አልፎ አልፎ በስልክ ድምጿን ብቻ እየሰማሁ ብቆይም ጤነኛ አለነበርኩም።
ለካ ከፍቅር ጋር እንደመጣላት ከባድ በሽታ የለም ቆይ በአለም ላይ ከፍቅር ጋር ተጣልቶ ያሸነፈ ጀግና አለመኖሩን እያወቁ ፀብ መግጠም ምን ይሉታል እኔ ማነኝ እናነው እንኳን ተራው እኔ ክርስቶስም የተረታው ለፍቅር አይደል እንዴ?! ምን እሚሉት ነው እሄ ትንቅንቅ ! እውነታውን ብረዳም ብቻየን መታመም ብቻ ሆነ ስራዬ ያለሁበትን ሁኔታ እንኳን ለሷ ለጓደኛዬ ለጆሲም አልነገርኩትም ።
ሁኔታዬን ተረድቶ ሲጠይቀኝም መልሴ ቀና አልነበረም በብስጭት እጬህበታለሁ።
"ማፍቀር እኮ መታደል ነው ዳንዬ አፍቅረሀታል በቃ ለምን አታምንም?!" ሲለኝ
ቁስሉን እንደነኩበት አንበሳ ቁጣዬ ገንፍሎ እጮሀለሁ እሱም ድርቅ ያለ ደረቅ አደል ይስቅና •••
"ጩኸትህ መሸነፍህን በደንብ በፍቅሯ መንበርከክህን ያረጋግጥልኛል እንጂ ሀሳቤን አያስቀይረኝም ይልቅ ብናወራ ይሻላል በጩኸት ዝም ልታስብለኝ አትሞክር!
ጓደኛዬ አንተኮ መፍታት ያቃተህ እራስህ ያሰርከውን ገመድ ነው አውቃለሁ እራስህ ያሰርከውን ገመድ መፍታት አለመቻል እጅግ ያበሳጫል ነገር ግን እየተበሳጨህ አልፈታ ያለህን ቋጠሮ ጎትተህ ልትበጥሰው በሞከርክ ቁጥር ጭራሽ እያጠበከው እንደምትሄድ እወቀው!!
በቃ ልትበጥሰው ልታስቀረው አለመቻልህን እመን ያኔ ቢያንስ ላትበጥሰው እየጎተትክ ከማጥበቅ ትቆጠብ ይሆናል!
ለማንም ሳትናገር ብቻህን በተብሰከሰክ ቁጥር መጨረሻህ ማበድ ይሆናል እሺ እሄን እወቀው ብሎኝ ካጠገቤ ይሄዳል!
ቤቱን ብቻውን አገኘዋለሀ!
ያኔ "" ኤዱን በናትሽ አንዴ ብቻ ልጩህ!?" ያላት ሰካራም ፊቴ ድቅን ይላል በሩን እዘጋና ልክ እንደሱ እጬሀለሁ !
በዚህ ሁኔታ ብዙ ታገልኩ ዛሬ ግን አልቻልኩም!
ለሊቱን ሙሉ በህልሜ ሳያት ስላደርኩ ነው መሰለኝ ናፍቆቴ ልኩን አለፈ ባላገኛት እንኳን ወደዛ አጥር ወደለለው ዩንቨርስቲያቸው ሄጄ ከሩቁ አይቻት ልመለስ ሄድኩ።
ደርሼ አምስት ደቂቃ ያክል እንኳን ሳልቆም ከሩቅ ኤዱን አየኋት !
ግን ብቻዋን አልነበረችም ከልጁ ጋር ነች ውስጤ ሲፈነቃቀል ታወቀኝ እዛው በቆምኩበት
ጩህ ጩህ ስሟን ከፍ አድርገህ ጥራት ጥራት አለኝ••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ደርሰን እሱ ከፊት እኔ ከጀርባው ተከታትለን እንደገባን
"ያቿትና"
አለኝ ፊት ለፊት ካንድ ሰው ጋር የተቀመጠች ቆንጂዬ ሴት ተመለከትኩ ።
ወደሱ ስዞር አራት ጣቶቹን ከንፈሩ ላይ ጭኖ እንዳፈጠጠባቸው ትንሽ ቆየና
"ውይ ውርዴት !
አቤት ቅሌት !
እሄ እኮ ውጪ ሀገር የነበረ ያክስቷ ልጅ ነው የሰርጋችሁን ግማሽ ወጪ እኔ እችላችሃምሀለሁ ብሎ ቃል ገብቴልናል! በቅርብ ነው የመጣው።
ጓደኛዬም ያላወቀው ለዛ ነው!
እነደመጣ አዲስ አበባ ነበር ያረፈው ሰሞኑን ወደ ድሬ ይመጣል ስትለኝ ነበር እንደዛ ሲፎክር የነበረው ሰው ጭራሽ "ደብቀኝ እንዳታየኝ ! "
እያለ እኔን ጎትቶ ከጀርባዬ ተደበቀና
"ዝም ብለህ ወደ ኋላ ና እንውጣ!" አለኝ።
እየተጓተትን ወጣን።
እሺ አሁን ወዴት እንሂድ? ስለው•••
"ዛሬ በቃ ካንተ ጋር የመረጥከው ቦታ ስጠጣ አድሬ ጥዋት በዛው ወደሀረር መመለስ ነው
እምፈልገው ግን ፍቃደኛ ከሆንክ ነው ?"
አለኝ እኔም በኤዱ ተከፍቼ ስለነበር መጠጣት ፈለኩ በሀሳቡ ተስማማሁና ተያይዘን ሄድን እየጠጣን ስለራሱ ብዙ እያወራልኝ ቆየና ድንገት በመሀል •••
"ቅድም ከልጁ ጋር ያየሀት ልጅ ግን እውነት ያክስትህ ልጅ ነች እንዳትዎሸኝ በናትህ እ ያክስትህ ልጅ ነች?"
ለምን ጠየከኝ ? አልኩት
"እኔ እንጃ የሆነ የፍቅር ስሜት አይንህ ውስጥ ያነበብኩ መስሎኝ ነው እ ተሳሳትኩ?!"
ኧረ በጭራሽ የፍቅር ስሜት እኔ ላይ ልታነብማ አትችልም ግን ያክስቴ ልጅ አይደለችም ብዬ ስለኤዱ በስሱ ነገርኩት ጎህ ሲቀድ ትዝ ይለኛል ግን ብዙ ከመጠጣቴ የተነሳ መች? እና እንዴት? እሱ ወደ ሀረር እኔም ወደ ቤት እንደገባሁ ትዝ አይለኝም።
በነጋታው ስድስት ሰአት አከባቢ ተነሳሁና ገላዬን ተጣጥቤ ወደ ስራ ወጣሁ።
በአከባቢያችን ባለ አንድ ምግብ ቤት ገብቼ ምሳ አዘዝኩና ከመምጣቱ በፊት ኤደንጋ ደወልኩ።
አነሳችው ድምፁዋ ስትጨፍር ማደሯን ይመሰክራል ሰላምታ ከተለዋወጥን ቡሀላ•••
የት ነሽ?
"ዶርም ነኝ ጋደም ብዬ !
ትናንት ታክሲ አገኛችሁ?
አዎ ዳንዬ ካንተ ጋር እንደወጣን ወድያው ነው ያገኘነው;"
በግዜ ገባችሁ?
አዎ ምነው?
አይ ምንም ከአንደበትሽ ልስማው ብዬ ነው!
ምኑን ዳኒ?
በቃ ተይው!
ምን ሆነሀል ዳኒ!?
ምን ሆንኩ?!
"አይ ምን እንደጠየከኝ እንኳን ሳይገባኝ በቃ ተይው ስትለኝ ግራ ገብቶኝ ነው"
በቃ እንደውም እንኳን ያልገባሽ ወሬ እንቀይር••
እሺ ካልክ!
እሺ!
"እሺ ምን!"
እሺ ምንም!
እንዴ ዳኒ ግራ አጋባከኝ እኮ ወሬ እንቀይር አላልክም እሺ ስለ ምን እናውራ?"
ምን አዲስ ነገር አለ?
"ምንም ዳኒዬ ምን አዲስ ነገር ይኖራል ብለህ ነው"
በቃ እሺ
በቃ እሺ ምን?
በቃ እሺ ቻዋ አዲስ ነገር ከሌለ!
"እሺ ቻው ግን•••" እያለች ስልኩን ዘጋሁት።
ስራው አስጠላኝ ባጃጄን ላጣቢ ሰጥቼ ገብቼ ተኛሁ።
ከትንሽ ቆይታ ቡሀላ ጆሲ እና ያ ጅምር እብድ ጓደኛው በርጫቸውን ይዘው እየተሳሳቁ ሲገቡ በሆዴ ተደፍቼ በመተኛት የተኛ ሰው መሰልኩ።
ጆሲ••••" እንዴ ዳኒ ስራ ወጥተህ አልነበር እንዴ በል ተነስ አትደብረን •••" ምናምን እያለ ሊቀሰቅሰኝ ቢሞክርም አውቆ የተኛን እንዲሉ ዝም አልኩ።
ከቆይታ ቡሀላ ከነመኖሬም ረስተውኝ ጆሲ እና ጓደኛው በራሳቸው አለም ውስጥ ገብተው የባጥ የቋጡን መዘባረቅ ጀመሩ።
የተኛሁ መስዬ ብተኛም ወሬያቸው እረፍት ነሳኝ ከአንዱ ርእስ ወደ ሌላ ለመሄድ ምንም አይነት ቅድመ ሁኔታ አይጠብቁም ወሬያቸውን ይጀምሩታል እንጂ አያልቅም።
ብስጭትጭት ብዬ በመነሳት ቤቱን ጥየላቸው ስወጣ ጆሲ•••
"ና እንጂ ዳንዬ! ወዴት ልትሄድ ነው? ረበሽንህ እንዴ! ማታ ሰክረህ ምን ስትል እንደነበር ልንገርህ ክክክክ !"
መልስ ሳልሰጠው ወጥቼ ሄድኩ።
ከዛን ቀን ቡሀላ ህይወቴ እራሱ የሰከረ ሆኖ ታየኝ ከኤዱ ጋር እንኳን ልንገናኝ ስልክ ተደዋውለን ሰላም ሰላም ከመባባል ውጪ የረባ ነገር ሳናወራ ወራቶች ተቆጠሩ የሷን ባላውቅም እኔ ግን ከራሴ ጋር ስለሷ ሳላወራ አድሬ አላውቅም ።
ጥፋተኛዋ እሷ ሆና ሳለ ስለመገናኘት አንስታብኝ ስለማታውቅ እልህ ያዘኝ ።አንድም ቀን ላግኝሽ ሳልላት አልፎ አልፎ በስልክ ድምጿን ብቻ እየሰማሁ ብቆይም ጤነኛ አለነበርኩም።
ለካ ከፍቅር ጋር እንደመጣላት ከባድ በሽታ የለም ቆይ በአለም ላይ ከፍቅር ጋር ተጣልቶ ያሸነፈ ጀግና አለመኖሩን እያወቁ ፀብ መግጠም ምን ይሉታል እኔ ማነኝ እናነው እንኳን ተራው እኔ ክርስቶስም የተረታው ለፍቅር አይደል እንዴ?! ምን እሚሉት ነው እሄ ትንቅንቅ ! እውነታውን ብረዳም ብቻየን መታመም ብቻ ሆነ ስራዬ ያለሁበትን ሁኔታ እንኳን ለሷ ለጓደኛዬ ለጆሲም አልነገርኩትም ።
ሁኔታዬን ተረድቶ ሲጠይቀኝም መልሴ ቀና አልነበረም በብስጭት እጬህበታለሁ።
"ማፍቀር እኮ መታደል ነው ዳንዬ አፍቅረሀታል በቃ ለምን አታምንም?!" ሲለኝ
ቁስሉን እንደነኩበት አንበሳ ቁጣዬ ገንፍሎ እጮሀለሁ እሱም ድርቅ ያለ ደረቅ አደል ይስቅና •••
"ጩኸትህ መሸነፍህን በደንብ በፍቅሯ መንበርከክህን ያረጋግጥልኛል እንጂ ሀሳቤን አያስቀይረኝም ይልቅ ብናወራ ይሻላል በጩኸት ዝም ልታስብለኝ አትሞክር!
ጓደኛዬ አንተኮ መፍታት ያቃተህ እራስህ ያሰርከውን ገመድ ነው አውቃለሁ እራስህ ያሰርከውን ገመድ መፍታት አለመቻል እጅግ ያበሳጫል ነገር ግን እየተበሳጨህ አልፈታ ያለህን ቋጠሮ ጎትተህ ልትበጥሰው በሞከርክ ቁጥር ጭራሽ እያጠበከው እንደምትሄድ እወቀው!!
በቃ ልትበጥሰው ልታስቀረው አለመቻልህን እመን ያኔ ቢያንስ ላትበጥሰው እየጎተትክ ከማጥበቅ ትቆጠብ ይሆናል!
ለማንም ሳትናገር ብቻህን በተብሰከሰክ ቁጥር መጨረሻህ ማበድ ይሆናል እሺ እሄን እወቀው ብሎኝ ካጠገቤ ይሄዳል!
ቤቱን ብቻውን አገኘዋለሀ!
ያኔ "" ኤዱን በናትሽ አንዴ ብቻ ልጩህ!?" ያላት ሰካራም ፊቴ ድቅን ይላል በሩን እዘጋና ልክ እንደሱ እጬሀለሁ !
በዚህ ሁኔታ ብዙ ታገልኩ ዛሬ ግን አልቻልኩም!
ለሊቱን ሙሉ በህልሜ ሳያት ስላደርኩ ነው መሰለኝ ናፍቆቴ ልኩን አለፈ ባላገኛት እንኳን ወደዛ አጥር ወደለለው ዩንቨርስቲያቸው ሄጄ ከሩቁ አይቻት ልመለስ ሄድኩ።
ደርሼ አምስት ደቂቃ ያክል እንኳን ሳልቆም ከሩቅ ኤዱን አየኋት !
ግን ብቻዋን አልነበረችም ከልጁ ጋር ነች ውስጤ ሲፈነቃቀል ታወቀኝ እዛው በቆምኩበት
ጩህ ጩህ ስሟን ከፍ አድርገህ ጥራት ጥራት አለኝ••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍1
#ልጩህበት!!
:
:
#ክፍል_ሀያ
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
በዚህ ሁኔታ ብዙ ታገልኩ ዛሬ ግን አልቻልኩም!
ለሊቱን ሙሉ በህልሜ ሳያት ስላደርኩ ነው መሰለኝ ናፍቆቴ ልኩን አለፈ ባላገኛት እንኳን ወደዛ አጥር ወደሌለው ዩንቨርስቲያቸው ሄጄ ከሩቁ አይቻት ልመለስ ሄድኩ።
ደርሼ አምስት ደቂቃ ያክል እንኳን ሳልቆም ከሩቅ ኤዱን አየኋት !
ግን ብቻዋን አልነበረችም ከልጁ ጋር ነች ውስጤ ሲፈነቃቀል ታወቀኝ እዛው በቆምኩበት
ጩህ ጩህ ስሟን ከፍ አድርገህ ጥራት ጥራት አለኝ••
ግን አልጮሆኩም ዝም ብዬ ፈዝዤ ስመለከታቸው ሁለት የማላውቃቸው ሴቶች መጥተው ተቀላቀሏቸው ወድያው ልጁ ሁለቱን እጃቸውን ጨብጦ ትከሻቸውን በመግጨት ኤዱን ግን ጉንጯን በመሳም ተሰናበታቸውና በርምጃ ከግቢው መውጣት ጀመረ ውስጤ በልጁ እና በኤዱ መካከል የሆነ ነገር እንዳለ እርግጠኛ ሆነ መሰለኝ ፍርሀት ፍርሀት ሲለው ታወቀኝ።
የቆመ ባጃጅ ውስጥ ገብቶ ሲሄድ ተከተልኩት።
ከዚራ አከባቢ ሲደርስ ወርዶ የሆነ ካፍቴርያ ውስጥ ገባ ።
ትንሽ ቆየት አልኩና እዛ ካፍቴሪያ ውስጥ ድንገት እንደተከሰተ ሰው መስዬ ገባሁ ።
ልጁና አንዲት የምታምር ሴት ጎን ለጎን ተቀምጠው ጭማቂ በስትሮ እየማጉ ያወራሉ።
ክው አልኩ እሄ ልጅ ኤዱን እያጃጃላት ባልሆነ እቺ ደሞ ማነች እያልኩ በውስጤ ፈንጠር አልኩና ጀርባዬን ሰጥቻቸው ተቀመጥኩ። ስልኬን አውጥቼ ለኤዱ ደወልኩላት•••
"ወዬ የዘጋከኝ ወንድሜ!" አለች እየሳቀኝ እቺ ልጅ ደግሞ እሄ ወንድሜ እምትለውን ነገር አፏ ላይ ነው እንዴ ያተሙባት እያልኩ ለራሴ የት እንደሆነች ጠየኳት ግቢ ከጓደኛቿ ጋር መሆኗን እንደነገረችኝ
ጓደኛሽ ደና ነው? ስላት ደህና መሆኑን ነግሯት ዛሬ እሚገርም ኳስ አለ ብሏት እኛ ሰፈር ወዳለው ድሬ ዳዋ እስታዲየም ኳስ ሊመለከት መሄዱን አከለችበት"
ተሰናብቻት ስልኩን ዘጋሁትና ። ኳስ ሜዳው ካፌ ኳሷ ደሞ ልጅቷ እንዳትሆን ብቻ አልኩና ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ወደ ልጅ በመሄድ ድንገት እንዳየሁት ሆኜ ሰላምታ ተለዋውጠን ፍቃደኛ ከሆነ አንድ ግዜ ለ አምስት ደቂቃ ላናግረው እንደምፈልግ ስነግረው ፍቃደኛ ቢሆንም ከኤዱ ጋር ምን አይነት ግኑኝነት እንዳላቸው ስጠይቀው
በጣም በሚያስጠላ ሁኔታ ምን አገባህ የሚል ስሜት ባዘለ መልኩ መልስ ሊሰጠኝ ሲሞክር አቋርጬው ቤተሰቦቿ እንዴት ሆነው እንዳስተማሯት ስለነገረችኝ እንዳትሰናከል በማሰብ እንጂ እሱ እንዳለው እንደማያገባኝና ያንንም ጠንቅቄ እንደማውቅ ነግሬው መልስ ሳይሰጠኝ በቆመበት ጥዬው ሄድኩ።
እንዲሁ እንደተወዛገብኩ ቀን ቀኖችን ቀኖች ሳምንትን ሳምንት ወርን ወሮች አመትን እያስከተሉ ነጎዱ እነኤዱም ሁለት አመት ተምረው የመጨረሻውን አንድ አመት መማር ከጀመሩ አንድ ወር ሆናቸው።
ያሁኖቹን ባላውቃቸውም መጀመርያ ላይ ጓደኛቿ ከነበሩት ትግስት ከመሲ ጋር አብሯ ስታብድ ትምህርቷን በአግባቡ ስላልተከታተለች እስከመጨረሻው ላትመለስ ከትምህርት ቤቱ ተባራ እዚሁ ድሬ ዳዋ ልዩ ስሙ ነምበር ዋን በመባል ወደ ሚታወቀው አከባቢ አንድ ሆቴል ውስጥ በአስተናጋጅነት ስትቀጠር ረድኤት ደሞ ለአንድ አመት ተቀጥታ ወደ ቤተሰቦቿ መሄዷን ነግራኛለች ።
ኤዱ ግን ልትመረቅ ወራቶች ብቻ ቀርተዋታል ልትመረቅ መሆኑን ባሰብኩ ቁጥር ጭንቀቴ ይጨምራል ስጨነቅ እንቅልፍ አጣለሁ ከጭንቀቴ ለመደበቅ እንቅልፍ ለመተኛት ስል ማታ ማታ ቋሚ ጠጪ ከሆንኩ ቆየሁ።
ሁሌም የምጠጣው ለመጀመሪያ ግዜ ኤዱን በሩ ላይ ቆማ ያየኋት ጭፈራ ቤት ውስጥ ነው ።
ወደ ውስጥ ከመግባቴ በፊት የቆመችባትን ቦታ ቆም ብዬ አያለሁ ኤዱ ግን የለችም ጠጥቼ ስወጣ ግን ወደዛ ከተመለከትኩ ቆማ ትታየኛለች እራሴንም እሷንም እየተሳደብኩ ወደ ቤት እንደምገባ ብዙ ግዜ ዳኒ ነግሮኛል ዛሬም እዛው እየጠጣሁ ነው።
በግዜ ስለገባሁ ሙዚቃው በስሱ ነው የተከፈተው ነገር ግን ከኔ በሁለት እርምጃ ርቀት እንደኔው ብቻውን የሚጠጣው ሰው ሰላሜን አሳጣኝ በሱ ምክንያት እራሴን ማዳመጥ አልቻልኩም ሰውየው አስተናጋጇን ያለ ምንም ምክንያት ይሰድባታል።
እሱ በሰደባት ቁጥር እኔ እናደዳለሁ።
የማይሆን ጥያቄ ይጠይቃትና መልስ አልሰጥ ስትለው ይሰድባታል •••
"ቆይ እሄ ቂጥሽ ሀይ ኮፒ ነው ኦርጅናል? ንገሪኝ ሀይ ኮፒ ነው ? ሳላረጋግጥ እማ ወይ ፍንክች "
ይላል እሚፈነክት ይፈንክተውና ምን ማረጋገጥ እንደፈለገ ሳስበው ደሞ ሳቄ ይመጣል ።
ትንሽ ቆይቶ ያጨበጭብና ሌላ ይዛለት እንድትመጣ ያዛል። ልክ እንዳመጣችለት ሊነካት እየሞከረ•••
" እንዴ ንገሪኛ እኛ ሀይኮፒም ዩዝድም ባንድ ላይ ጉዳት ነው ንገሪኛ በናትሽ !"
ሲል ልጅቷ ተበሳጭታ መልስ ስለሰጠችው ብድግ አለ ሊመታት ያኔ የኔም ንዴት ገነፈለና ተንደርድሬ በጥፊ ከመሬቱ ጋር አላትሜ አርፎ እንዲጠጣ አስጠነቅቄው ወደ ቦታዬ ተመለስኩ ።
ሰውየው መለፍለፉን አላቆመም ወይ እሱ ወይ እኔ ከዛ ቤት ካልወጣን ዝም እንደማይል ስለገባኝ ተነስቼ ወጣሁና ግማሽ ኪሎ ሜትር አከባቢ በግሬ ተጉዤ " ጨለማው ቤት" በመባል ወደ ሚታወቀው ሆቴል ገባሁ።
ብዙ ግዜ ጥንዶች የሚዝናኑበት ሆቴል ቢሆንም እኔ ብቻዬን ቁጭ ብዬ ስጠጣ ሁለት ቢራ ጨርሼ ሶስተኛውን እንዳገባደድኩ ከፊት ለፊቴ በቅርብ ርቀት ከተቀመጡት ሶስት ሰዎች መካከል ድንገት ቦግ ብሎ በበራው የሞባይል መብራት የመሀለኛዋን እየኋት•••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
:
:
#ክፍል_ሀያ
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
በዚህ ሁኔታ ብዙ ታገልኩ ዛሬ ግን አልቻልኩም!
ለሊቱን ሙሉ በህልሜ ሳያት ስላደርኩ ነው መሰለኝ ናፍቆቴ ልኩን አለፈ ባላገኛት እንኳን ወደዛ አጥር ወደሌለው ዩንቨርስቲያቸው ሄጄ ከሩቁ አይቻት ልመለስ ሄድኩ።
ደርሼ አምስት ደቂቃ ያክል እንኳን ሳልቆም ከሩቅ ኤዱን አየኋት !
ግን ብቻዋን አልነበረችም ከልጁ ጋር ነች ውስጤ ሲፈነቃቀል ታወቀኝ እዛው በቆምኩበት
ጩህ ጩህ ስሟን ከፍ አድርገህ ጥራት ጥራት አለኝ••
ግን አልጮሆኩም ዝም ብዬ ፈዝዤ ስመለከታቸው ሁለት የማላውቃቸው ሴቶች መጥተው ተቀላቀሏቸው ወድያው ልጁ ሁለቱን እጃቸውን ጨብጦ ትከሻቸውን በመግጨት ኤዱን ግን ጉንጯን በመሳም ተሰናበታቸውና በርምጃ ከግቢው መውጣት ጀመረ ውስጤ በልጁ እና በኤዱ መካከል የሆነ ነገር እንዳለ እርግጠኛ ሆነ መሰለኝ ፍርሀት ፍርሀት ሲለው ታወቀኝ።
የቆመ ባጃጅ ውስጥ ገብቶ ሲሄድ ተከተልኩት።
ከዚራ አከባቢ ሲደርስ ወርዶ የሆነ ካፍቴርያ ውስጥ ገባ ።
ትንሽ ቆየት አልኩና እዛ ካፍቴሪያ ውስጥ ድንገት እንደተከሰተ ሰው መስዬ ገባሁ ።
ልጁና አንዲት የምታምር ሴት ጎን ለጎን ተቀምጠው ጭማቂ በስትሮ እየማጉ ያወራሉ።
ክው አልኩ እሄ ልጅ ኤዱን እያጃጃላት ባልሆነ እቺ ደሞ ማነች እያልኩ በውስጤ ፈንጠር አልኩና ጀርባዬን ሰጥቻቸው ተቀመጥኩ። ስልኬን አውጥቼ ለኤዱ ደወልኩላት•••
"ወዬ የዘጋከኝ ወንድሜ!" አለች እየሳቀኝ እቺ ልጅ ደግሞ እሄ ወንድሜ እምትለውን ነገር አፏ ላይ ነው እንዴ ያተሙባት እያልኩ ለራሴ የት እንደሆነች ጠየኳት ግቢ ከጓደኛቿ ጋር መሆኗን እንደነገረችኝ
ጓደኛሽ ደና ነው? ስላት ደህና መሆኑን ነግሯት ዛሬ እሚገርም ኳስ አለ ብሏት እኛ ሰፈር ወዳለው ድሬ ዳዋ እስታዲየም ኳስ ሊመለከት መሄዱን አከለችበት"
ተሰናብቻት ስልኩን ዘጋሁትና ። ኳስ ሜዳው ካፌ ኳሷ ደሞ ልጅቷ እንዳትሆን ብቻ አልኩና ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ወደ ልጅ በመሄድ ድንገት እንዳየሁት ሆኜ ሰላምታ ተለዋውጠን ፍቃደኛ ከሆነ አንድ ግዜ ለ አምስት ደቂቃ ላናግረው እንደምፈልግ ስነግረው ፍቃደኛ ቢሆንም ከኤዱ ጋር ምን አይነት ግኑኝነት እንዳላቸው ስጠይቀው
በጣም በሚያስጠላ ሁኔታ ምን አገባህ የሚል ስሜት ባዘለ መልኩ መልስ ሊሰጠኝ ሲሞክር አቋርጬው ቤተሰቦቿ እንዴት ሆነው እንዳስተማሯት ስለነገረችኝ እንዳትሰናከል በማሰብ እንጂ እሱ እንዳለው እንደማያገባኝና ያንንም ጠንቅቄ እንደማውቅ ነግሬው መልስ ሳይሰጠኝ በቆመበት ጥዬው ሄድኩ።
እንዲሁ እንደተወዛገብኩ ቀን ቀኖችን ቀኖች ሳምንትን ሳምንት ወርን ወሮች አመትን እያስከተሉ ነጎዱ እነኤዱም ሁለት አመት ተምረው የመጨረሻውን አንድ አመት መማር ከጀመሩ አንድ ወር ሆናቸው።
ያሁኖቹን ባላውቃቸውም መጀመርያ ላይ ጓደኛቿ ከነበሩት ትግስት ከመሲ ጋር አብሯ ስታብድ ትምህርቷን በአግባቡ ስላልተከታተለች እስከመጨረሻው ላትመለስ ከትምህርት ቤቱ ተባራ እዚሁ ድሬ ዳዋ ልዩ ስሙ ነምበር ዋን በመባል ወደ ሚታወቀው አከባቢ አንድ ሆቴል ውስጥ በአስተናጋጅነት ስትቀጠር ረድኤት ደሞ ለአንድ አመት ተቀጥታ ወደ ቤተሰቦቿ መሄዷን ነግራኛለች ።
ኤዱ ግን ልትመረቅ ወራቶች ብቻ ቀርተዋታል ልትመረቅ መሆኑን ባሰብኩ ቁጥር ጭንቀቴ ይጨምራል ስጨነቅ እንቅልፍ አጣለሁ ከጭንቀቴ ለመደበቅ እንቅልፍ ለመተኛት ስል ማታ ማታ ቋሚ ጠጪ ከሆንኩ ቆየሁ።
ሁሌም የምጠጣው ለመጀመሪያ ግዜ ኤዱን በሩ ላይ ቆማ ያየኋት ጭፈራ ቤት ውስጥ ነው ።
ወደ ውስጥ ከመግባቴ በፊት የቆመችባትን ቦታ ቆም ብዬ አያለሁ ኤዱ ግን የለችም ጠጥቼ ስወጣ ግን ወደዛ ከተመለከትኩ ቆማ ትታየኛለች እራሴንም እሷንም እየተሳደብኩ ወደ ቤት እንደምገባ ብዙ ግዜ ዳኒ ነግሮኛል ዛሬም እዛው እየጠጣሁ ነው።
በግዜ ስለገባሁ ሙዚቃው በስሱ ነው የተከፈተው ነገር ግን ከኔ በሁለት እርምጃ ርቀት እንደኔው ብቻውን የሚጠጣው ሰው ሰላሜን አሳጣኝ በሱ ምክንያት እራሴን ማዳመጥ አልቻልኩም ሰውየው አስተናጋጇን ያለ ምንም ምክንያት ይሰድባታል።
እሱ በሰደባት ቁጥር እኔ እናደዳለሁ።
የማይሆን ጥያቄ ይጠይቃትና መልስ አልሰጥ ስትለው ይሰድባታል •••
"ቆይ እሄ ቂጥሽ ሀይ ኮፒ ነው ኦርጅናል? ንገሪኝ ሀይ ኮፒ ነው ? ሳላረጋግጥ እማ ወይ ፍንክች "
ይላል እሚፈነክት ይፈንክተውና ምን ማረጋገጥ እንደፈለገ ሳስበው ደሞ ሳቄ ይመጣል ።
ትንሽ ቆይቶ ያጨበጭብና ሌላ ይዛለት እንድትመጣ ያዛል። ልክ እንዳመጣችለት ሊነካት እየሞከረ•••
" እንዴ ንገሪኛ እኛ ሀይኮፒም ዩዝድም ባንድ ላይ ጉዳት ነው ንገሪኛ በናትሽ !"
ሲል ልጅቷ ተበሳጭታ መልስ ስለሰጠችው ብድግ አለ ሊመታት ያኔ የኔም ንዴት ገነፈለና ተንደርድሬ በጥፊ ከመሬቱ ጋር አላትሜ አርፎ እንዲጠጣ አስጠነቅቄው ወደ ቦታዬ ተመለስኩ ።
ሰውየው መለፍለፉን አላቆመም ወይ እሱ ወይ እኔ ከዛ ቤት ካልወጣን ዝም እንደማይል ስለገባኝ ተነስቼ ወጣሁና ግማሽ ኪሎ ሜትር አከባቢ በግሬ ተጉዤ " ጨለማው ቤት" በመባል ወደ ሚታወቀው ሆቴል ገባሁ።
ብዙ ግዜ ጥንዶች የሚዝናኑበት ሆቴል ቢሆንም እኔ ብቻዬን ቁጭ ብዬ ስጠጣ ሁለት ቢራ ጨርሼ ሶስተኛውን እንዳገባደድኩ ከፊት ለፊቴ በቅርብ ርቀት ከተቀመጡት ሶስት ሰዎች መካከል ድንገት ቦግ ብሎ በበራው የሞባይል መብራት የመሀለኛዋን እየኋት•••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍2
#ልጩህበት!!
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ሰውየው መለፍለፉን አላቆመም ወይ እሱ ወይ እኔ ከዛ ቤት ካልወጣን ዝም እንደማይል ስለገባኝ ተነስቼ ወጣሁና ግማሽ ኪሎ ሜትር አከባቢ በግሬ ተጉዤ " ጨለማው ቤት" በመባል ወደ ሚታወቀው ሆቴል ገባሁ።
ብዙ ግዜ ጥንዶች የሚዝናኑበት ሆቴል ቢሆንም እኔ ብቻዬን ቁጭ ብዬ ስጠጣ ሁለት ቢራ ጨርሼ ሶስተኛውን እንዳገባደድኩ ከፊት ለፊቴ በቅርብ ርቀት ከተቀመጡት ሶስት ሰዎች መካከል ድንገት ቦግ ብሎ በበራው የሞባይል መብራት የመሀለኛዋን እየኋት•••
ያቺን እርኩስ አየኋት እስከዛሬ ሳያት ከሚሰማኝ የንዴት ስሜት በተለየ ሁኔታ ጠላቴ መስላ ታየችኝ የግቢ ሴቶች ላይ ብቻ ሳይሆን እኔ ሂወት ላይም የተጫወተች መስሎ ተሰማኝ።
አዎ እሷ ነች ለኔ እና ለኤዱ መተዋወቅ ምክንያት ሆና እዚህ የማልወጣው የፍቅር ገደል ውስጥ ወድቄ የመንፈስ ስብራት እንዲያጋጥመኝ የሞራል የደስታ ባጠቃላይ የኑሮ ጣእምና ለዛዋ ሁሉ እንዲጠፋብኝ ቀንደኛዋ ተዋናይ እሷ ነች ብዬ አሰብኩኝ ።
አዋ! እሷ ነች ያን ቀን ኤዱን አታላ ለዛ ፀያፍ ስራዋ አመቻችታ ይዛት ባትወጣ ኖሮ እኔና ኤዱ ባልተዋወቅን ባላየኋት ባላየችኝ እህቴ ብዬ ስቀርባት ዉንድሟ አርጋኝ ባላረፈችው ነበር
እሷ እስከዛሬም እንደወንድሟ እያየችኝ የኔ ግን ምን እንደገለበጠው ባይገባኝም ወደማላውቀውና ለኔ አዲስ ወደሆነ ከባድ የፍቅር ስሜት ተገልብጦ እንዲህ ቀንና ለሊቱ ባልተገለባበጠብኝ ነበር።
አንዳንዴ ኧረ የምን አንዳንዴ ሁሌም ቢሆን በተለይ ከራሴ ጋር የሚያላትመኝ ፍቅር ከያዘኝ ወዲህ ምነው ባላወኳት እላለሁ ።
ደሞ መልሼ በተለይ ከተዋወቅን ጀምሮ በቃሌ መሰረት እንዳትሳቀቅ በማሰብ ያሰፈልገኛል ብላ ጠየቀችኝም አልጠየቀችኝም በየወሩ አቅሜ የፈቀደውን ያህል በባንክ አካውንቷ ሳስገባላት ወድያው ትደውልና•••
"በመጀመሪያ አንተን ሳይሆን ከናት እና አባቴ ባትወለድም አንተን የመሰለ ወንድም በስጦታ የሰጠኝ ፈጣዬን ሁሌም አመሰግናለሁ በመቀጠል ደሞ አንተንም እመሰግናለሁ እሺ ወንድሜ "
የምትለኝ ሁሌም የማይቀየር ንግግሯ
ሀሳቤን ያስቀይረኝና መተዋወቃችንን ሳይሆን ማፍቀሬን በመኮነን ከራሴ ጋር እጣላለሁ
ሆነም ቀረ ከብዙ ግዜ ቡሀላ ያጋጠመችኝን አሁን ከፊቴ ሶስት ደረጃ ከፍ ብላ ከአንድ ክልስ ከሚመስል ሰውና ከሌላ አዲስ እንቡጥ ሴት ጋር ተቀምጣ የምታስካካውን መሲን በጭራሽ እንደማላልፋት ወሰንኩ!
ሞባይሌን አወጣሁ!
በሁለተኛው ሲም ካርድ ስም ቀይሬ በከፈትኩት ቴሌግራም•••
ካሁን ቡሀላ የግቢ ሴቶችን እያወጣሽ እንደእቃ ስትቸረችሪ ቢያጋጥመኝ ወይ ብሰማ እሄን ጉድሽን በሁሉም ማህበራዊ ሚድያ ለቅቄ መደበቂያ እንደማሳጣሽ እወቂ!
አሁንም አብራሽ ያለችውን ልጅ ቶሎ ወደ ግቢ መልሻት ከሚል አጭር ትእዛዝ ጋር ያ ሰውዬ የላከልኝን የራሷን ቪድዮ ወደ ቴሌግራም አካውንቷ ላኩላትና ወድያው ሞባይሌን ኪሴ ከትቼ እምትሆነውን መጠባበቅ ጀመርኩ።
የቴሌግራም ማሳወቂያውን (notification) አጥፍታዋለች መሰለኝ አዲስ መልክት እንዳላት ስላልነገራት ጭራሽ ሞባይሏን ከፍታ ሳታየው ቆየች።
ስልኳ ላይ መልክት መላክ ግድ ሆነብኝ ቴሌግራም አካውንትሽ ላይ መልክት አለሽ ገብተሽ ተመልከችው ብዬ ላኩ።
ወድያው ሞባይሏ ብልጭ ብሎ ድርግም ሲል አየሁት።
ከፍታ እየተመለከተችው ነው
ቪድዮውን አይታው ነው መሰለኝ በርግጋ ከመቀመጫዋ ተነሳች ፀጉሯን እንደመንጨት እያደረጋት ቪድዮውን የላከልሽ ሰው ውጪ በር ላይ ነው ያሏት ይመስል ያደረገችው ተረከዘ ረጅም ጫማ መሆኑን ረስታ እየተውረገረገች በፍጥነት ደረጃውን ለመውረድ ስትሞክር ባየር ላይ ተበረጋግዳ መሬት ተሰጣች ።
ፈገግ አልኩ አናቴ ላይ ያለውን ኮፍያ ዝቅ እያደረኩ።
ሁሉም ተደነጋግጦ ወደሷ ሲሮጥ ለቅሶ በተናነቀው ድምፅ
"ምንም አልሆንኩም እንዳትጠጉኝ!" ብላ በእልህ ተነሳችና የተጎዳ እግሯን እየጎተተች እና እስከባቷ የተሰነጠቀውን ሮዝ የራት ልብሷን ለማራገፍ እየሞከረች በደመነፍስ የሆቴሉ የውጪ በር ላይ ደረሳ ወደላይና ወደ ታች እየተገላመጠች የጠረጠረችውን ሰው መፈለግ ጀመረች።
ምንም ማየት ባለመቻሏ ተስፋ ቆረጠች ያኔ ስትወድቅ የተመታችበት ቦታ ህመመ ተሰማት ጎኗ አከባቢ ይዛ እያቃሰተች መቆም ስላቃታት ቁጭ ብላ ማልቀስ ጀመረች።
ሰውየውና አብራት የነበረችው ልጅ አጠገቧ እንደደረሱ ልጅቷ በጣም ተጨንቃ ዝቅ ብላ ልታናግራት ልታባብላት በምትሞክርበት ሰአት መሲ ተቀየረችባት•••
"ዞወር በይልኝ ወደዛ ያንቺ ገዳፋ ነው እሄ ሁሉ መጀመሪያም ምንሽም አልጣመኝም ነበር ካሁን ቡሀላ ላይሽ አልፈልግም አሁኑኑ ባጃጅ ያዢና ቀጥ ብለሽ ወደ ግቢ ሂጂ !" በማለት ስታምባርቅባት ልጅቷ ሽምቅቅ ብላ ዘወር አለች ሄደች ወደግቢ ።
"ጎበዝ መሲ ትዛዝ ታከብሪያለሽ ማለት ነው!" ብዬ መልክት ላኩላትና ስልኬን አጥፍቼ ኪሴ ውስጥ ከተትኩ እሄን ግዜ እንደ እብድ አደረጋት መልክቱ እየደረሳት ያለው እዛው ሆቴል ውስጥ እየተዝናና ካለ በቅርብ ርቀት ከሚያያት ሰው መሆኑን እርግጠኛ ሆነች ።
እንደምንም ተነስታ ስልክ መደወል ጀመረች ወደኔ እምትሞክር መስሎኝ ነበር ጎረምሶቿን እየጠራች እንደሆነ የገባኝ ሶስት
ክብደት ገፊ ፣ደረተ ሰፋፊ ፣ ባስተሳሰብ ደሞ ቀፋፊ የሆኑ በጭንቅላታቸው ሳይሆን በተከመረው ጡንቻቸው የሚያስቡ ወጣቶች ከመቅስፈት ደርሰው መሲን በመክበብ ምን እንደፈጠረ ሲጠይቋት እንደተመለከትኩ ነው ።
በመሲ ጥሪ በዛ ፍጥነት ሰው ሊደበድቡ መምጣታቸውን ሳስበው ለህሊናቸው ሳይሆን ለሆዳቸው የሚኖሩ አሳሞች መስለው ታዩኝ
መሲ ማነች ? ምንድን ነች? ስራዋ ምንድን ነው ማንን ነው የምታስደበድበን ? ለምን?
አያገባቸውም ብቻ ትክፈላቸው እንጂ እንደ እንስሳ ወደፈለገችበት ትነዳቸዋለች ። ገልቱዎች ።
ዘበኛውን ሰው እንዳይወጣ አስጠነቀቁትና
መሀላቸው አድርገዋት ግቢ ውስጥ መዟዟር ጀመሩ ብዙ ሰው የለም ያሉትም ጥንድ ጥንድ ሆነው ነው የተቀመጡት ብቻዬን ቁጭ ያልኩት እኔ ብቻ ነኝ ።
ደረታቸውን ገልብጠው እየተሽከረከሩ የሚዝናኑትን ሰዎች ምን እንደሚሏቸው ባላውቅም አንዳንዶቹን ጠጋ ብለው እያናገሩ ያንዳንዶቹን ሞባይላቸውን ተቀብለው እየመለሱላቸው እኔ ወዳለሁበት ቦታ መጠጋት ጀመሩ።
ሂሳብ ዘጋሁ።
እነዚህን ዱባ ጭንቅላቶች ፈርቼ ሳይሆን የሰው ሆቴል ውስጥ ብጥብጥ ተፈጥሮ ላለመታሰር ስል ተነስቼ ወደ መውጫው በር ስጠጋ•••
" እንዳታስወጣው! ጥበቃ እንዳታስወጣው !"
የሚለው የመሲ ጩኸት ጆሮዬ ላይ አንቃጨለብኝ ዘወር ስል እሷ ከጀርባቸው ቆማ ሶስቱም ወደኔ ሲመጡ እየኋቸው•••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ሰውየው መለፍለፉን አላቆመም ወይ እሱ ወይ እኔ ከዛ ቤት ካልወጣን ዝም እንደማይል ስለገባኝ ተነስቼ ወጣሁና ግማሽ ኪሎ ሜትር አከባቢ በግሬ ተጉዤ " ጨለማው ቤት" በመባል ወደ ሚታወቀው ሆቴል ገባሁ።
ብዙ ግዜ ጥንዶች የሚዝናኑበት ሆቴል ቢሆንም እኔ ብቻዬን ቁጭ ብዬ ስጠጣ ሁለት ቢራ ጨርሼ ሶስተኛውን እንዳገባደድኩ ከፊት ለፊቴ በቅርብ ርቀት ከተቀመጡት ሶስት ሰዎች መካከል ድንገት ቦግ ብሎ በበራው የሞባይል መብራት የመሀለኛዋን እየኋት•••
ያቺን እርኩስ አየኋት እስከዛሬ ሳያት ከሚሰማኝ የንዴት ስሜት በተለየ ሁኔታ ጠላቴ መስላ ታየችኝ የግቢ ሴቶች ላይ ብቻ ሳይሆን እኔ ሂወት ላይም የተጫወተች መስሎ ተሰማኝ።
አዎ እሷ ነች ለኔ እና ለኤዱ መተዋወቅ ምክንያት ሆና እዚህ የማልወጣው የፍቅር ገደል ውስጥ ወድቄ የመንፈስ ስብራት እንዲያጋጥመኝ የሞራል የደስታ ባጠቃላይ የኑሮ ጣእምና ለዛዋ ሁሉ እንዲጠፋብኝ ቀንደኛዋ ተዋናይ እሷ ነች ብዬ አሰብኩኝ ።
አዋ! እሷ ነች ያን ቀን ኤዱን አታላ ለዛ ፀያፍ ስራዋ አመቻችታ ይዛት ባትወጣ ኖሮ እኔና ኤዱ ባልተዋወቅን ባላየኋት ባላየችኝ እህቴ ብዬ ስቀርባት ዉንድሟ አርጋኝ ባላረፈችው ነበር
እሷ እስከዛሬም እንደወንድሟ እያየችኝ የኔ ግን ምን እንደገለበጠው ባይገባኝም ወደማላውቀውና ለኔ አዲስ ወደሆነ ከባድ የፍቅር ስሜት ተገልብጦ እንዲህ ቀንና ለሊቱ ባልተገለባበጠብኝ ነበር።
አንዳንዴ ኧረ የምን አንዳንዴ ሁሌም ቢሆን በተለይ ከራሴ ጋር የሚያላትመኝ ፍቅር ከያዘኝ ወዲህ ምነው ባላወኳት እላለሁ ።
ደሞ መልሼ በተለይ ከተዋወቅን ጀምሮ በቃሌ መሰረት እንዳትሳቀቅ በማሰብ ያሰፈልገኛል ብላ ጠየቀችኝም አልጠየቀችኝም በየወሩ አቅሜ የፈቀደውን ያህል በባንክ አካውንቷ ሳስገባላት ወድያው ትደውልና•••
"በመጀመሪያ አንተን ሳይሆን ከናት እና አባቴ ባትወለድም አንተን የመሰለ ወንድም በስጦታ የሰጠኝ ፈጣዬን ሁሌም አመሰግናለሁ በመቀጠል ደሞ አንተንም እመሰግናለሁ እሺ ወንድሜ "
የምትለኝ ሁሌም የማይቀየር ንግግሯ
ሀሳቤን ያስቀይረኝና መተዋወቃችንን ሳይሆን ማፍቀሬን በመኮነን ከራሴ ጋር እጣላለሁ
ሆነም ቀረ ከብዙ ግዜ ቡሀላ ያጋጠመችኝን አሁን ከፊቴ ሶስት ደረጃ ከፍ ብላ ከአንድ ክልስ ከሚመስል ሰውና ከሌላ አዲስ እንቡጥ ሴት ጋር ተቀምጣ የምታስካካውን መሲን በጭራሽ እንደማላልፋት ወሰንኩ!
ሞባይሌን አወጣሁ!
በሁለተኛው ሲም ካርድ ስም ቀይሬ በከፈትኩት ቴሌግራም•••
ካሁን ቡሀላ የግቢ ሴቶችን እያወጣሽ እንደእቃ ስትቸረችሪ ቢያጋጥመኝ ወይ ብሰማ እሄን ጉድሽን በሁሉም ማህበራዊ ሚድያ ለቅቄ መደበቂያ እንደማሳጣሽ እወቂ!
አሁንም አብራሽ ያለችውን ልጅ ቶሎ ወደ ግቢ መልሻት ከሚል አጭር ትእዛዝ ጋር ያ ሰውዬ የላከልኝን የራሷን ቪድዮ ወደ ቴሌግራም አካውንቷ ላኩላትና ወድያው ሞባይሌን ኪሴ ከትቼ እምትሆነውን መጠባበቅ ጀመርኩ።
የቴሌግራም ማሳወቂያውን (notification) አጥፍታዋለች መሰለኝ አዲስ መልክት እንዳላት ስላልነገራት ጭራሽ ሞባይሏን ከፍታ ሳታየው ቆየች።
ስልኳ ላይ መልክት መላክ ግድ ሆነብኝ ቴሌግራም አካውንትሽ ላይ መልክት አለሽ ገብተሽ ተመልከችው ብዬ ላኩ።
ወድያው ሞባይሏ ብልጭ ብሎ ድርግም ሲል አየሁት።
ከፍታ እየተመለከተችው ነው
ቪድዮውን አይታው ነው መሰለኝ በርግጋ ከመቀመጫዋ ተነሳች ፀጉሯን እንደመንጨት እያደረጋት ቪድዮውን የላከልሽ ሰው ውጪ በር ላይ ነው ያሏት ይመስል ያደረገችው ተረከዘ ረጅም ጫማ መሆኑን ረስታ እየተውረገረገች በፍጥነት ደረጃውን ለመውረድ ስትሞክር ባየር ላይ ተበረጋግዳ መሬት ተሰጣች ።
ፈገግ አልኩ አናቴ ላይ ያለውን ኮፍያ ዝቅ እያደረኩ።
ሁሉም ተደነጋግጦ ወደሷ ሲሮጥ ለቅሶ በተናነቀው ድምፅ
"ምንም አልሆንኩም እንዳትጠጉኝ!" ብላ በእልህ ተነሳችና የተጎዳ እግሯን እየጎተተች እና እስከባቷ የተሰነጠቀውን ሮዝ የራት ልብሷን ለማራገፍ እየሞከረች በደመነፍስ የሆቴሉ የውጪ በር ላይ ደረሳ ወደላይና ወደ ታች እየተገላመጠች የጠረጠረችውን ሰው መፈለግ ጀመረች።
ምንም ማየት ባለመቻሏ ተስፋ ቆረጠች ያኔ ስትወድቅ የተመታችበት ቦታ ህመመ ተሰማት ጎኗ አከባቢ ይዛ እያቃሰተች መቆም ስላቃታት ቁጭ ብላ ማልቀስ ጀመረች።
ሰውየውና አብራት የነበረችው ልጅ አጠገቧ እንደደረሱ ልጅቷ በጣም ተጨንቃ ዝቅ ብላ ልታናግራት ልታባብላት በምትሞክርበት ሰአት መሲ ተቀየረችባት•••
"ዞወር በይልኝ ወደዛ ያንቺ ገዳፋ ነው እሄ ሁሉ መጀመሪያም ምንሽም አልጣመኝም ነበር ካሁን ቡሀላ ላይሽ አልፈልግም አሁኑኑ ባጃጅ ያዢና ቀጥ ብለሽ ወደ ግቢ ሂጂ !" በማለት ስታምባርቅባት ልጅቷ ሽምቅቅ ብላ ዘወር አለች ሄደች ወደግቢ ።
"ጎበዝ መሲ ትዛዝ ታከብሪያለሽ ማለት ነው!" ብዬ መልክት ላኩላትና ስልኬን አጥፍቼ ኪሴ ውስጥ ከተትኩ እሄን ግዜ እንደ እብድ አደረጋት መልክቱ እየደረሳት ያለው እዛው ሆቴል ውስጥ እየተዝናና ካለ በቅርብ ርቀት ከሚያያት ሰው መሆኑን እርግጠኛ ሆነች ።
እንደምንም ተነስታ ስልክ መደወል ጀመረች ወደኔ እምትሞክር መስሎኝ ነበር ጎረምሶቿን እየጠራች እንደሆነ የገባኝ ሶስት
ክብደት ገፊ ፣ደረተ ሰፋፊ ፣ ባስተሳሰብ ደሞ ቀፋፊ የሆኑ በጭንቅላታቸው ሳይሆን በተከመረው ጡንቻቸው የሚያስቡ ወጣቶች ከመቅስፈት ደርሰው መሲን በመክበብ ምን እንደፈጠረ ሲጠይቋት እንደተመለከትኩ ነው ።
በመሲ ጥሪ በዛ ፍጥነት ሰው ሊደበድቡ መምጣታቸውን ሳስበው ለህሊናቸው ሳይሆን ለሆዳቸው የሚኖሩ አሳሞች መስለው ታዩኝ
መሲ ማነች ? ምንድን ነች? ስራዋ ምንድን ነው ማንን ነው የምታስደበድበን ? ለምን?
አያገባቸውም ብቻ ትክፈላቸው እንጂ እንደ እንስሳ ወደፈለገችበት ትነዳቸዋለች ። ገልቱዎች ።
ዘበኛውን ሰው እንዳይወጣ አስጠነቀቁትና
መሀላቸው አድርገዋት ግቢ ውስጥ መዟዟር ጀመሩ ብዙ ሰው የለም ያሉትም ጥንድ ጥንድ ሆነው ነው የተቀመጡት ብቻዬን ቁጭ ያልኩት እኔ ብቻ ነኝ ።
ደረታቸውን ገልብጠው እየተሽከረከሩ የሚዝናኑትን ሰዎች ምን እንደሚሏቸው ባላውቅም አንዳንዶቹን ጠጋ ብለው እያናገሩ ያንዳንዶቹን ሞባይላቸውን ተቀብለው እየመለሱላቸው እኔ ወዳለሁበት ቦታ መጠጋት ጀመሩ።
ሂሳብ ዘጋሁ።
እነዚህን ዱባ ጭንቅላቶች ፈርቼ ሳይሆን የሰው ሆቴል ውስጥ ብጥብጥ ተፈጥሮ ላለመታሰር ስል ተነስቼ ወደ መውጫው በር ስጠጋ•••
" እንዳታስወጣው! ጥበቃ እንዳታስወጣው !"
የሚለው የመሲ ጩኸት ጆሮዬ ላይ አንቃጨለብኝ ዘወር ስል እሷ ከጀርባቸው ቆማ ሶስቱም ወደኔ ሲመጡ እየኋቸው•••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍1
#ልጩህበት!!
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
በመሲ ጥሪ በዛ ፍጥነት ሰው ሊደበድቡ መምጣታቸውን ሳስበው ለህሊናቸው ሳይሆን ለሆዳቸው የሚኖሩ አሳሞች መስለው ታዩኝ መሲ ማነች ? ምንድን ነች? አያገባቸውም ብቻ ትክፈላቸው እንጂ እንደ እንስሳ ወደፈለገችበት ትነዳቸዋለች ። ገልቱዎች ።
ጥበቃውን ሰው እንዳይወጣ አስጠነቀቁትና
መሀላቸው አድርገዋት ግቢ ውስጥ መዟዟር ጀመሩ ብዙ ሰው የለም ያሉትም ጥንድ ጥንድ ሆነው ነው የተቀመጡት ብቻዬን ቁጭ ያልኩት እኔ ብቻ ነኝ ።
ደረታቸውን ገልብጠው እየተሽከረከሩ የሚዝናኑትን ሰዎች ምን እንደሚሏቸው ባላውቅም አንዳንዶቹን ጠጋ ብለው እያናገሩ ያንዳንዶቹን ሞባይላቸውን ተቀብለው እየመለሱላቸው እኔ ወዳለሁበት ቦታ መጠጋት ጀመሩ።
ሂሳብ ዘጋሁ።
እነዚህን ዱባ ጭንቅላቶች ፈርቼ ሳይሆን የሰው ሆቴል ውስጥ ብጥብጥ ተፈጥሮ ላለመታሰር ስል ተነስቼ ወደ መውጫው በር ስጠጋ•••
" እንዳታስወጣው! ጥበቃ እንዳታስወጣው !"
የሚለው የመሲ ጩኸት ጆሮዬ ላይ አንቃጨለብኝ ዘወር ስል እሷ ከጀርባቸው ቆማ ሶስቱም ወደኔ ሲመጡ እየኋቸው•••
ጥበቃው ወደኔ ተጠግቶ አየት አደረገኝና ጠቀስ አርጎኝ ሳቁ ልገንፍልብህ እንዳለው ሰው በእጁ አፉን ይዞ ወደነሱ ዞረና
" ማንን ዳኒን?" አላቸው በአመልካች ጣቱ ወደኔ እያመላከታቸው •••
" እሱን ነው እንዳይወጣ ያልሽው አንቺ ልጅ? "የቀበጡ ለት•••"
አለ የሀገር ሰው ትሰሚያለሽ እሱን እንኳን እኔ ታንክ አያቆመውም ቅድም ስትፎክሪ የነበረው እሱን ለማስመታት ነው እንዴ ?
ቆይ ዛሬ ነው ድሬ የገባችሁት? እንግዶች ናችሁ እንዴ?
ዳኒኮ በካራቴ ትምህርት ጥቁሩን ቀበቶ እንደ አባቶቹ ዝናር ደጋግሞ ወገቡ ላይ የጠመጠመ የድሬ ዥግና ነው !
ቆይ ቆይ ቆይ በወፈረ መስሎሽ ነው እነኝህን ይዘሽ የመጣሽው ምነው "ለሀምሳ ጋን አንድ አሎሎ ይበቃል " ብለው ቲተርቱ ውልእንኳ ብሎብሽ አያውቅም?
ታይነኩት አይነካም ምላሳችሁንም እግራችሁንም ሰብስባችሁ ሂዱ ዳንዬ በል አንተም ሂድ ምን ይደረግ
አንዳንዱ ተማን ጋር እንደተጣላ የሚገባው ተተወቀጠ ቡሀላ ነው !
ቢያውቁህማ እንኳንስ ለጠብ አስቁመው ሊሉኝ ሰአት ጠይቀው ለማለትም ባልደፈሩ ነበር በል ሂድ መሽቷል!"
ሲለኝ ገለማምጫቸው ሁለት እጄን ኪሴ ውስጥ ከትቼ ብወጣም ከወጣሁ ቡሀላ ካልወጣሁ እያለ ከሚታገልኝ ሳቅ ጋር መታገል ፈተና እንደሆነብኝ ጉንጬን ነፍቼ ትንሽ ራቅ እንዳልኩ ሳቄን ለቀኩት!
ወይ ጥቁር ቀበቶ! ኬት አምጥቶት ነው?
የባጃጇ ነው እንዳልል ባጃጄ ቀበቶ የላትም ።
ከጥበቃው ጋር የምንተዋወቀው በስራ ነው
አልፎ አልፎ ቀን ቀን በብዛት ደሞ ማታ ማታ ሆቴሉ ውስጥ የሚዝናኑ ብሎም እዛው አልጋ ይዘው ድሬ ሰንበትበት ብለው የሚሄዱ ደንበኞቻቸው ታክሲ እንዲጠራላቸው ሲነግሩት ደውሎ ይጠራኛል የተወሰነ ኮምሽን አስብለታለሁ እሄን እማደርገው ከብዙ ሆቴል ጥበቃዎች ጋር ነው አንድ ሁለቴ እዛ ስጠቀም ጋብዤዋለሁ አለቀ ከዚህ ያለፈ ቅርርብ አልነበረንም ።
ባንድ ግዜ የከተማው አክተር አድርጎኝ ቁጭ ሲል እንኳን እነመሲ እኔ እራሴ እራሴን ሳልፈራው አልቀረሁም ወይ የሰው ነገር እራሴን ታዘብኩት እሱ በካበኝ ቁጥር ፍታቸው ሁለት እግሬን ከፈት አድርጌ ፊቴን አጨፍግጌ በመቆም በለለኝ ደረት ስወጣጠር ፈንድቼ ነበርኮ እያልኩ በራሴው ንግግር እኔው እየሳኩ ወደቤት ስገባ ደንግጦ ከንቅልፉ የባነነው ጆሲ ቀና ብሎ አየኝና •••
"ወይኔ ወንድሜን ለየልህ በቃ!?"አለኝ።
ስማ ጆስዬ በዚህ ሰአት ቢለይልኝማ በምን እድሌ እየውልህ ጆስዬ ሁሉንም ነገር ስንፈልግ የምንሆነው ሳንፈልግ የማንሆነው ቢሆን ኤዱን እስክረሳት ብቻ ባብድ ደስ ይለኝ ነበር!
"ከዚህ በላይ! በል ተኛ አሁን ጥዋት እናወራለን" ሲለኝ ተኛሁ።
ረፋድ አራት ሰአት አከባቢ ከንቅልፌ ነቃሁ።
ማታ የዘጋሁትን ስልኬን ስክፍተው መሲ ሶስት መልክቶችን በተከታታይ ስልኬ ላይ ልካልኛለች ።
ከፍቼ ማንበብ ጀመርኩ•••
የመጀመሪያው መልከት እባክህ ወንድሜ እንደዛ እንዳታረግ ትንሽ አላሳዝንህም ? ቆይ እህት የለህም ?" ይላል
ሁለተኛው መልክቷ" ያንን ቪድዬ እንዳልከው እምትለቀው ከሆነ እራሴን እንደማጠፋ እወቅ! ይፀፅትሀል!" ይላል
ሶስተኛው መልክቷ" ጨነቀኝ ኧረ በናትህ መልስ እንኳን ስጠኝ!" ይላል ።
አሳዘነችኝ ልበል ኧረ አልልም !።
መልስ መፃፍ ጀመርኩ•••
አንቺ ክፉ ልታደርጊባቸው ስለቻልሽ ሌሎች ላይ ክፉ ስታደርጊ አንቺ ላይ ክፉ የማረግ አቅም ያለው ሌላ ሰው እንዳለ አትርሺ ቢሆንም ከስተትሽ ተምረሽ ክፋትሽን ካቆምሽ አንቺን በመጉዳቴ ሳይሆን በማስተማሬ ብዙ አተርፋለሁና በጭራሽ አልጎዳሽም!
መልክቱን ልክ እንደላኩት ስራ ሄዷኩ ያለው ጆሲ ተመልሶ መጣ ።
ምነው ጆሲ ስራ የለም እንዴ ለምን መጣህ?
"አንተን ላናግር መነጋገር አለብን ዳኒ!"
ስለምን?
"ስላንተ ነዋ!"
ስለኔ ምን ?
"ቆይ ዳኒ ለምን እኔንስ ታስጨንቀኛለህ እንደወንድሜ እማይህ ጓደኛዬ ነህ ያንተ እንዲህ መሆን የሚያስደስተኝ ይመስልሀል እንዴ?
ምን ሆንኩ?
ምን ያልሆንከው አለ! ስራህን በአግባቡ እየሰራህ
አይደለም ፣ ማታ ማታ አዘውትረህ ትጠጣለህ ከኔ ጋር እንኳን ማውራት አስጠልቶካል የኔስ ችግር የለውም ቤተሰብጋም እኮ ሄደህ አታውቅም እናትህ ሳያዩህ ሲያድሩ ምን ያህል እንደሚጨነቁ ታውቃለህ አንተን ፍለጋ እዚህ ድረስ መምጣት አለባቸው ዳኒ! ቆይ እስከመቼ እውነቱን ልንገርህ እኔ ወስኛለሁ ይቺ ኤደን የምትላትን ልጅ ሄጄ አናግራታለሁ!"
ብሎኝ ከቤት ሲወጣ ተከትዬው ወጥቼ አንገቱን አነኩትና
አታደርገውም ዳኒ አልኩት
"ቆይ ለምን" አለኝ እጄን እያስለቀቀ
ለምን እንደሆነ እነግርሀለሁ።
እሺ ወይ ያቺ የምትወድህን የኔን ሲስተር ጓደኛ ጀምራትና ይቺን ኤደን ተብዬዋን እርሳታ በቃ ዳኒ !"
ካካካካካ ኤዱን ነው በሷ እምረሳት አልኩት ከልቤ ነበር የሳኩበት!
አትሳቅ ዳኒ እንድትስቅብኝ አደለም ስራ አስፈቅጄ የመጣሁት ሁለት አማራጭ አለህ አንዱን ካልመረጥክ ከኔጋም ትጣላለህ!
ምኑን ከምኑ ነው እምመርጠው?
"ወይ ኤደንን እኔ ሄጄ እንዳናግራት መፍቀድ ካልሆነ ከልጅቷ ጋር ፍቅር ጀምረህ ኤደንን መርሳት!"
ጆሲ አምርሯል ግራ ገባኝ ። ኤዱን እንዲያናግራት በጭራሽ እንደማልፈልግ አውቃለሁ ሁለተኛው ምርጫ ደግሞ ጡጫ ሆነብኝ ቢሆንም•••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
በመሲ ጥሪ በዛ ፍጥነት ሰው ሊደበድቡ መምጣታቸውን ሳስበው ለህሊናቸው ሳይሆን ለሆዳቸው የሚኖሩ አሳሞች መስለው ታዩኝ መሲ ማነች ? ምንድን ነች? አያገባቸውም ብቻ ትክፈላቸው እንጂ እንደ እንስሳ ወደፈለገችበት ትነዳቸዋለች ። ገልቱዎች ።
ጥበቃውን ሰው እንዳይወጣ አስጠነቀቁትና
መሀላቸው አድርገዋት ግቢ ውስጥ መዟዟር ጀመሩ ብዙ ሰው የለም ያሉትም ጥንድ ጥንድ ሆነው ነው የተቀመጡት ብቻዬን ቁጭ ያልኩት እኔ ብቻ ነኝ ።
ደረታቸውን ገልብጠው እየተሽከረከሩ የሚዝናኑትን ሰዎች ምን እንደሚሏቸው ባላውቅም አንዳንዶቹን ጠጋ ብለው እያናገሩ ያንዳንዶቹን ሞባይላቸውን ተቀብለው እየመለሱላቸው እኔ ወዳለሁበት ቦታ መጠጋት ጀመሩ።
ሂሳብ ዘጋሁ።
እነዚህን ዱባ ጭንቅላቶች ፈርቼ ሳይሆን የሰው ሆቴል ውስጥ ብጥብጥ ተፈጥሮ ላለመታሰር ስል ተነስቼ ወደ መውጫው በር ስጠጋ•••
" እንዳታስወጣው! ጥበቃ እንዳታስወጣው !"
የሚለው የመሲ ጩኸት ጆሮዬ ላይ አንቃጨለብኝ ዘወር ስል እሷ ከጀርባቸው ቆማ ሶስቱም ወደኔ ሲመጡ እየኋቸው•••
ጥበቃው ወደኔ ተጠግቶ አየት አደረገኝና ጠቀስ አርጎኝ ሳቁ ልገንፍልብህ እንዳለው ሰው በእጁ አፉን ይዞ ወደነሱ ዞረና
" ማንን ዳኒን?" አላቸው በአመልካች ጣቱ ወደኔ እያመላከታቸው •••
" እሱን ነው እንዳይወጣ ያልሽው አንቺ ልጅ? "የቀበጡ ለት•••"
አለ የሀገር ሰው ትሰሚያለሽ እሱን እንኳን እኔ ታንክ አያቆመውም ቅድም ስትፎክሪ የነበረው እሱን ለማስመታት ነው እንዴ ?
ቆይ ዛሬ ነው ድሬ የገባችሁት? እንግዶች ናችሁ እንዴ?
ዳኒኮ በካራቴ ትምህርት ጥቁሩን ቀበቶ እንደ አባቶቹ ዝናር ደጋግሞ ወገቡ ላይ የጠመጠመ የድሬ ዥግና ነው !
ቆይ ቆይ ቆይ በወፈረ መስሎሽ ነው እነኝህን ይዘሽ የመጣሽው ምነው "ለሀምሳ ጋን አንድ አሎሎ ይበቃል " ብለው ቲተርቱ ውልእንኳ ብሎብሽ አያውቅም?
ታይነኩት አይነካም ምላሳችሁንም እግራችሁንም ሰብስባችሁ ሂዱ ዳንዬ በል አንተም ሂድ ምን ይደረግ
አንዳንዱ ተማን ጋር እንደተጣላ የሚገባው ተተወቀጠ ቡሀላ ነው !
ቢያውቁህማ እንኳንስ ለጠብ አስቁመው ሊሉኝ ሰአት ጠይቀው ለማለትም ባልደፈሩ ነበር በል ሂድ መሽቷል!"
ሲለኝ ገለማምጫቸው ሁለት እጄን ኪሴ ውስጥ ከትቼ ብወጣም ከወጣሁ ቡሀላ ካልወጣሁ እያለ ከሚታገልኝ ሳቅ ጋር መታገል ፈተና እንደሆነብኝ ጉንጬን ነፍቼ ትንሽ ራቅ እንዳልኩ ሳቄን ለቀኩት!
ወይ ጥቁር ቀበቶ! ኬት አምጥቶት ነው?
የባጃጇ ነው እንዳልል ባጃጄ ቀበቶ የላትም ።
ከጥበቃው ጋር የምንተዋወቀው በስራ ነው
አልፎ አልፎ ቀን ቀን በብዛት ደሞ ማታ ማታ ሆቴሉ ውስጥ የሚዝናኑ ብሎም እዛው አልጋ ይዘው ድሬ ሰንበትበት ብለው የሚሄዱ ደንበኞቻቸው ታክሲ እንዲጠራላቸው ሲነግሩት ደውሎ ይጠራኛል የተወሰነ ኮምሽን አስብለታለሁ እሄን እማደርገው ከብዙ ሆቴል ጥበቃዎች ጋር ነው አንድ ሁለቴ እዛ ስጠቀም ጋብዤዋለሁ አለቀ ከዚህ ያለፈ ቅርርብ አልነበረንም ።
ባንድ ግዜ የከተማው አክተር አድርጎኝ ቁጭ ሲል እንኳን እነመሲ እኔ እራሴ እራሴን ሳልፈራው አልቀረሁም ወይ የሰው ነገር እራሴን ታዘብኩት እሱ በካበኝ ቁጥር ፍታቸው ሁለት እግሬን ከፈት አድርጌ ፊቴን አጨፍግጌ በመቆም በለለኝ ደረት ስወጣጠር ፈንድቼ ነበርኮ እያልኩ በራሴው ንግግር እኔው እየሳኩ ወደቤት ስገባ ደንግጦ ከንቅልፉ የባነነው ጆሲ ቀና ብሎ አየኝና •••
"ወይኔ ወንድሜን ለየልህ በቃ!?"አለኝ።
ስማ ጆስዬ በዚህ ሰአት ቢለይልኝማ በምን እድሌ እየውልህ ጆስዬ ሁሉንም ነገር ስንፈልግ የምንሆነው ሳንፈልግ የማንሆነው ቢሆን ኤዱን እስክረሳት ብቻ ባብድ ደስ ይለኝ ነበር!
"ከዚህ በላይ! በል ተኛ አሁን ጥዋት እናወራለን" ሲለኝ ተኛሁ።
ረፋድ አራት ሰአት አከባቢ ከንቅልፌ ነቃሁ።
ማታ የዘጋሁትን ስልኬን ስክፍተው መሲ ሶስት መልክቶችን በተከታታይ ስልኬ ላይ ልካልኛለች ።
ከፍቼ ማንበብ ጀመርኩ•••
የመጀመሪያው መልከት እባክህ ወንድሜ እንደዛ እንዳታረግ ትንሽ አላሳዝንህም ? ቆይ እህት የለህም ?" ይላል
ሁለተኛው መልክቷ" ያንን ቪድዬ እንዳልከው እምትለቀው ከሆነ እራሴን እንደማጠፋ እወቅ! ይፀፅትሀል!" ይላል
ሶስተኛው መልክቷ" ጨነቀኝ ኧረ በናትህ መልስ እንኳን ስጠኝ!" ይላል ።
አሳዘነችኝ ልበል ኧረ አልልም !።
መልስ መፃፍ ጀመርኩ•••
አንቺ ክፉ ልታደርጊባቸው ስለቻልሽ ሌሎች ላይ ክፉ ስታደርጊ አንቺ ላይ ክፉ የማረግ አቅም ያለው ሌላ ሰው እንዳለ አትርሺ ቢሆንም ከስተትሽ ተምረሽ ክፋትሽን ካቆምሽ አንቺን በመጉዳቴ ሳይሆን በማስተማሬ ብዙ አተርፋለሁና በጭራሽ አልጎዳሽም!
መልክቱን ልክ እንደላኩት ስራ ሄዷኩ ያለው ጆሲ ተመልሶ መጣ ።
ምነው ጆሲ ስራ የለም እንዴ ለምን መጣህ?
"አንተን ላናግር መነጋገር አለብን ዳኒ!"
ስለምን?
"ስላንተ ነዋ!"
ስለኔ ምን ?
"ቆይ ዳኒ ለምን እኔንስ ታስጨንቀኛለህ እንደወንድሜ እማይህ ጓደኛዬ ነህ ያንተ እንዲህ መሆን የሚያስደስተኝ ይመስልሀል እንዴ?
ምን ሆንኩ?
ምን ያልሆንከው አለ! ስራህን በአግባቡ እየሰራህ
አይደለም ፣ ማታ ማታ አዘውትረህ ትጠጣለህ ከኔ ጋር እንኳን ማውራት አስጠልቶካል የኔስ ችግር የለውም ቤተሰብጋም እኮ ሄደህ አታውቅም እናትህ ሳያዩህ ሲያድሩ ምን ያህል እንደሚጨነቁ ታውቃለህ አንተን ፍለጋ እዚህ ድረስ መምጣት አለባቸው ዳኒ! ቆይ እስከመቼ እውነቱን ልንገርህ እኔ ወስኛለሁ ይቺ ኤደን የምትላትን ልጅ ሄጄ አናግራታለሁ!"
ብሎኝ ከቤት ሲወጣ ተከትዬው ወጥቼ አንገቱን አነኩትና
አታደርገውም ዳኒ አልኩት
"ቆይ ለምን" አለኝ እጄን እያስለቀቀ
ለምን እንደሆነ እነግርሀለሁ።
እሺ ወይ ያቺ የምትወድህን የኔን ሲስተር ጓደኛ ጀምራትና ይቺን ኤደን ተብዬዋን እርሳታ በቃ ዳኒ !"
ካካካካካ ኤዱን ነው በሷ እምረሳት አልኩት ከልቤ ነበር የሳኩበት!
አትሳቅ ዳኒ እንድትስቅብኝ አደለም ስራ አስፈቅጄ የመጣሁት ሁለት አማራጭ አለህ አንዱን ካልመረጥክ ከኔጋም ትጣላለህ!
ምኑን ከምኑ ነው እምመርጠው?
"ወይ ኤደንን እኔ ሄጄ እንዳናግራት መፍቀድ ካልሆነ ከልጅቷ ጋር ፍቅር ጀምረህ ኤደንን መርሳት!"
ጆሲ አምርሯል ግራ ገባኝ ። ኤዱን እንዲያናግራት በጭራሽ እንደማልፈልግ አውቃለሁ ሁለተኛው ምርጫ ደግሞ ጡጫ ሆነብኝ ቢሆንም•••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍1
#ልጩህበት!!
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ምኑን ከምኑ ነው እምመርጠው?
"ወይ ኤደንን እኔ ሄጄ እንዳናግራት መፍቀድ ካልሆነ ከልጅቷ ጋር ፍቅር ጀምረህ ኤደንን መርሳት!"
ጆሲ አምርሯል ግራ ገባኝ ። ኤዱን እንዲያናግራት በጭራሽ እንደማልፈልግ አውቃለሁ ሁለተኛው ምርጫ ደግሞ ጡጫ ሆነብኝ ቢሆንም•••
ውስጤ እንደማይሆን እያወቀው ከዳኒ ጭቅጭቅ ለመገላገል ስል •እሺ አልኩት
በቃ እሺ!
"በቃ እሺ ምን በየትኛው ሀሳብ?"
"በቃ ካልካት ልጅ ጋር እንቀራረባለና!"
አዋ ዳንዬ አንዳንዴ እንኳን እንደዚህ እሺ በለኝ እስቲ ዳንዬ ዋናው መቀራረባችሁ ነው ከዛ ቡሀላ ሌላው ይከተላል ኤዱንስ ቢሆን ሳትቀርባት አላፈቀርካት!"
እሺ አልኩህ እኮ በቃ አልኩት። ከዛች ሰአት ጀምሮ ጆሲ ስራውን ጀመረ ።
ልጅቷን እቤት ያመጣትና መጣሁ ብሎ በመውጣት ጥሎን ይጠፋል።
መቀራረብ ብንጀምርም እውነቱን ለመናገር እሷን ለብቻዋ ከማገኛት ይልቅ ኤዱን ከልጁ ጋር ሆና ባገኛት እመርጥ ነበር።
ለሶስት ወር ልጅቷ እና ጆሲ ስራ አደረጉኝ የተቀየረ ስሜት አልነበረም በመሀል ድንገት ለተከታታይ ቀናት ጥፍት አለች።
ለስድስት ቀን ያህል ድምጿንም ስልኳንም አጥፍታ ከተሰወረች ቡሀላ በሰባተኛው ቀን እኔና ጆሲ ሰፈር ውስጥ ቁጭ ባልንበት እራሷ ጆሲ ስልክ ላይ ደወለች።
ስልኩን ለሁለታችንም እንዲሰማ አደረገና •••
" ምን ሆነሽ ነው የጠፋሽው?" የጆሲ ጥያቄ ነበር
" ምን ላድርግ ጓደኛህ ኤደን የምትባል ሰይጣን አጠናፍራዋለች መሰለኝ በተገናኘን ቁጥር ወሬው ሁሉ ከሷ አያልፍም እንዴ እኔ ልጅቷን ሳላውቃት ሁላ እንድጠላት ነው ያደርገኝ በጣም ነው የተጎዳሁት ጆሲ ከቻልክ ጓደኛህን ወይ አሳክመው ወይ ፀበል ውሰደው " ብላው እርፍ አለች ።
ጆሲ ዘወር ብሎ ሲያፈጥምኝ ተነስቼ ካጠገቡ ሄድኩ።
ከዛን ቀን ቡሀላ ከጆሲ ጋር ስለምንም ነገር ሳናወራ የኤዱ ምርቃት ሰባት ቀን( ሳምንት) ቀረው ።
ስድስት ቀን ሲቀረው ደውላ ቤተሰቦቿ ለምርቃቷ ከሁለት ቀን ቡሀላ እንደሚመጡ እና ከምርቃቷ ቡሀላ አብራቸው ወደ አዲስ አበባ እንደምትሄድ ነገረችኝ ።
ይህ ንግግሯ መብረቅ በሉት ለኔ ።ጨነቀኝ ።
ያን ቀን ጠጥቼ ብገባም እንቅልፍ እንቢ አለኝ እኩለ ለሊት ላይ አንድ ሀሰብ መጣልኝ።
ተነስቼ ለኤዱ ደብዳቤ መፃፍ ጀመርኩ•••
••••• ለኤደን
ኤዱዬ ህይወትን መራራም ጣፋጭም እንድትሆን ካደረጓት ምክንያቶች አንዱ ምን እንደሆነ ታውቂያለሽ?
እኛ ሰዎች ስላለፈው እና ስለ አሁኑ እንጂ ነገ ምን እንደሚፈጠር እለማወቃችን ነው ።
ነገን አለማወቅ የራሱ የሆነ ብዙ ጥሩም መጥፎም ገፅታዎች አሉት።
ነገ የሚከሰተውን መጥፎ ነገር ቀድመን ስናውቅ እና ነገ የሚከሰተውን ጥሩ ነገር ቀድመን ስናውቅ የሚሰሙን ሁለት ተቃራኒ ስሜቶች ናቸው።
እንዲህ ያልኩሽ አሁን የሆንኩትን ነገር ያኔ በዛ በብርድ እዛ ሆቴል በር ላይ ቆመሽ ባየሁሽ ሰአት ቀድሜ ባውቀው ምን እወስን ነበር ብዬ ሁሌም እራሴን ስለምጠይቀው ነው
"አሁን ምን ሆንክ? ትይ ይሆኖል። ምንም አታውቂምና ጥያቄሽ ልክ ነው የኔ ስስት ያኔ ካሁን ቡሀላ ወንድምሽ ነኝ ስልሽ አንቺም ተቀብለሽ የእውነት ወንድም አድርገሽኛልና ምን ሆንክ ብትይኝ ባንቺ አይፈረድም እኔ ግን ብዙ ሆኛለሁ አንቺን በማፍቀሬ እንኳን አንቺ እኔ እንኳን የማላውቀው ሌላ ዳኒ እንደሆኑኩ አውቃለሁ።
ኤዱዬ አፈቅርሻለሁ!
ይህን ስታነቢ ምን ትይኝ ይሆን?
በቃሌ የማልገኝ እራስ ወዳድ ነኝ አደል ኤዱዬ?
በጣም ይቅርታ።
ከግዜ ቡሀላ ለኔም ባልገባኝ መንገድ ውስጤ ተቀያይሮ ካቅሜ በላይ ሆኖብኝ እንጂ ያኔ ወንድም እሆንሻለሁ ከጎንሽ ነኝ እንደወንድምሽ እይኝ ያልኩሽ ግን ከልቤ ነበር!።
ሁሌም ቃሌን ያጠፍኩ መስሎ ይሰማኛል ላንቺ ስላልነገርኩሽ ምንም ባትይኝም ብታውቅ ምን ትለኛለች እያልኩ ከመሸማቀቅ አልዳንኩም።
ፍቅር የሻቱትን ማግኘት ብቻ አይደለምና የኔ እንደማትሆኚ እያሰብኩም አፈቅርሻለሁ።
ከምንም ነገር በላይ አንቺን በእውኔም በህልሜም ማየት፣ ስላንቺ ማሰብ ፣ ስላንቺ ማውራት ያስደስተኛል ። ካንቺ ውጪ ሁሉ ነገር አልጥምህ ካለኝ ወራቶች ተቆጥረዋል።
"ታድያ በነበረን ግዜ በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ውስጥ ከነበርክ እንዴት አልነገርከኝም?
ወይም እንዴት ከፊትህ መረዳት አልቻልኩም? " ትይኝ ይሆናል
በፍቅር ንዳድ ከመለብለብ በላይ በልብ ውስጥ ያለውን የፍቅር እሳት አውጥቶ ላፈቀሩት ሰው ንዳዱን ማሳየት ለብዙ አፍቃሪዎች ከባድ ነው።
እኔን ግን አውጥቶ ከመናገሩም በላይ ከባድ የሆነብኝ ብነግርሽ የሚሰማሽን ስሜት ማሰብ ነው።
ፍቅረኛሽ ሆኜ ቢሆን አሁን ወንድምሽ በመሆኔ የተደሰትሽውን ያክል እምትደሰቺ መስሎ አይታየኝም ።
ካፌ ሻይ ቡና እያልን ፊት ለፊቴ ቁጭ ብለሽ ከናት ካባቴ ባትወለድም አንተን የመሰለ ወንድም በስጦታ ስለሰጠኝ እያልሽ ፈጣሪን ስታመሰግኚ ስሰማ እንኳን ልነግርሽ ማፍቀሬን የምታውቂብኝ እየመሰለኝ ምክንያት ፈጥሬ ካጠገብሽ እሽሻለሁ ።
ጆሲ ጓደኛዬ ምን እንደሚለኝ ታውቂያለሽ ኤዱዬ?
••••" አንተኮ መፍታት ያቃተህ መጀመሪያ ላይ እራስህ አጥብቀህ ያሰርከውን ቋጠሮ ነው አልፈታ ባለህ ቁጥር ደግሞ በንዴት ለመበጠስ እየሞከርክ የበለጠ ታጠብቀዋለህ!" ይለኛል
እውነቱን ነው ትዝ ይልሻል እዱዬ?
ስለመሲ ስናወራ አንድ ሰው ውለታ ውሎልሽ ውለታውን በመንተራስ ከፍላጎትሽ ውጪ የሚጫንሽ ከሆነ ውለታ ሳያስቀድም ተመሳሳይ ጥያቄ ከሚጠይቅሽ ሰው በላይ እርኩስ ነው ብዬሽ ነበር ።
እኔም የፍቅር ጥያቄዬ ካደረኩልሽ ትንሽ ውለታ ጋር እንዳይያያዝብኝ ፈራሁ።
አንቺንም እኔን ወንድም እንጂ ፍቅረኛ የማድረግ ፍላጎት ውስጥሽ ሳይኖር የምጫንሽ ጥያቄዬን ባለመቀበልና እኔን ባለማስከፋት መሀል ሆነሽ የምትጨነቂ መስሎ ታየኝ ።
በዚህ መሀል እናንተ ባታዩኝም ከልጁ ጋር ሆኖችሁ ብዙ ቦታዎች ታጋጥሙኝ ጀመር።
ያኔ በሱም ባንቺም ሳይሆን በራሴ ይበልጥ መናደድ ጀመርኩ ።
ህመምህ መድሀኒት የለውም አትድንም እንደተባለ በሽተኛ የፍቅር ህመሜ ፈውስ የሆንሽውን አንቺን የኔ እንደማላደርግሽ ተረዳሁ ።
ኤዱዬ በመመረቅሽ እንኳን ደስ አለሽ!
በመመረቅሽ የተሰማሽን ደስታ ትንሽ ሳታጣጥሚውና ከድሬ ሳትወጪ አንብበሽው ሌላ ስሜት ውስጥ እንድትገቢ ስላልፈለኩ ነው ይህን ደብዳቤ በእጅሽ ሳልሰጥሽ ከምርቃቷ ቡሀላ ወደ አዲስ አባባ ስሸኛት ሳታየኝ የልብስ ሻንጣዋ ውስጥ አስቀምጥላታለሁ ባየችው ግዜ ትየው ብዬ የወሰንኩት።
በነበረን ስሜት ወንድምሽ ሆኜ ልሸኝሽ ቀናቶች ቀርተዋል ለዛም ተዘጋጅቻለሁ ።
የኔ ኤደን ዛሬም ቢሆን ስላወኩሽ ደስተኛ ነኝ።
የማንም ሁኚ እኔ ግን አፈቅርሻለሁ። መቼም ቢሆን አረሳሽም። ዝምምምም ብዬ ሳፈቅርሽ እኖራለሁ።
ሰላም ሁኚ!
ዳኒ ነኝ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ምኑን ከምኑ ነው እምመርጠው?
"ወይ ኤደንን እኔ ሄጄ እንዳናግራት መፍቀድ ካልሆነ ከልጅቷ ጋር ፍቅር ጀምረህ ኤደንን መርሳት!"
ጆሲ አምርሯል ግራ ገባኝ ። ኤዱን እንዲያናግራት በጭራሽ እንደማልፈልግ አውቃለሁ ሁለተኛው ምርጫ ደግሞ ጡጫ ሆነብኝ ቢሆንም•••
ውስጤ እንደማይሆን እያወቀው ከዳኒ ጭቅጭቅ ለመገላገል ስል •እሺ አልኩት
በቃ እሺ!
"በቃ እሺ ምን በየትኛው ሀሳብ?"
"በቃ ካልካት ልጅ ጋር እንቀራረባለና!"
አዋ ዳንዬ አንዳንዴ እንኳን እንደዚህ እሺ በለኝ እስቲ ዳንዬ ዋናው መቀራረባችሁ ነው ከዛ ቡሀላ ሌላው ይከተላል ኤዱንስ ቢሆን ሳትቀርባት አላፈቀርካት!"
እሺ አልኩህ እኮ በቃ አልኩት። ከዛች ሰአት ጀምሮ ጆሲ ስራውን ጀመረ ።
ልጅቷን እቤት ያመጣትና መጣሁ ብሎ በመውጣት ጥሎን ይጠፋል።
መቀራረብ ብንጀምርም እውነቱን ለመናገር እሷን ለብቻዋ ከማገኛት ይልቅ ኤዱን ከልጁ ጋር ሆና ባገኛት እመርጥ ነበር።
ለሶስት ወር ልጅቷ እና ጆሲ ስራ አደረጉኝ የተቀየረ ስሜት አልነበረም በመሀል ድንገት ለተከታታይ ቀናት ጥፍት አለች።
ለስድስት ቀን ያህል ድምጿንም ስልኳንም አጥፍታ ከተሰወረች ቡሀላ በሰባተኛው ቀን እኔና ጆሲ ሰፈር ውስጥ ቁጭ ባልንበት እራሷ ጆሲ ስልክ ላይ ደወለች።
ስልኩን ለሁለታችንም እንዲሰማ አደረገና •••
" ምን ሆነሽ ነው የጠፋሽው?" የጆሲ ጥያቄ ነበር
" ምን ላድርግ ጓደኛህ ኤደን የምትባል ሰይጣን አጠናፍራዋለች መሰለኝ በተገናኘን ቁጥር ወሬው ሁሉ ከሷ አያልፍም እንዴ እኔ ልጅቷን ሳላውቃት ሁላ እንድጠላት ነው ያደርገኝ በጣም ነው የተጎዳሁት ጆሲ ከቻልክ ጓደኛህን ወይ አሳክመው ወይ ፀበል ውሰደው " ብላው እርፍ አለች ።
ጆሲ ዘወር ብሎ ሲያፈጥምኝ ተነስቼ ካጠገቡ ሄድኩ።
ከዛን ቀን ቡሀላ ከጆሲ ጋር ስለምንም ነገር ሳናወራ የኤዱ ምርቃት ሰባት ቀን( ሳምንት) ቀረው ።
ስድስት ቀን ሲቀረው ደውላ ቤተሰቦቿ ለምርቃቷ ከሁለት ቀን ቡሀላ እንደሚመጡ እና ከምርቃቷ ቡሀላ አብራቸው ወደ አዲስ አበባ እንደምትሄድ ነገረችኝ ።
ይህ ንግግሯ መብረቅ በሉት ለኔ ።ጨነቀኝ ።
ያን ቀን ጠጥቼ ብገባም እንቅልፍ እንቢ አለኝ እኩለ ለሊት ላይ አንድ ሀሰብ መጣልኝ።
ተነስቼ ለኤዱ ደብዳቤ መፃፍ ጀመርኩ•••
••••• ለኤደን
ኤዱዬ ህይወትን መራራም ጣፋጭም እንድትሆን ካደረጓት ምክንያቶች አንዱ ምን እንደሆነ ታውቂያለሽ?
እኛ ሰዎች ስላለፈው እና ስለ አሁኑ እንጂ ነገ ምን እንደሚፈጠር እለማወቃችን ነው ።
ነገን አለማወቅ የራሱ የሆነ ብዙ ጥሩም መጥፎም ገፅታዎች አሉት።
ነገ የሚከሰተውን መጥፎ ነገር ቀድመን ስናውቅ እና ነገ የሚከሰተውን ጥሩ ነገር ቀድመን ስናውቅ የሚሰሙን ሁለት ተቃራኒ ስሜቶች ናቸው።
እንዲህ ያልኩሽ አሁን የሆንኩትን ነገር ያኔ በዛ በብርድ እዛ ሆቴል በር ላይ ቆመሽ ባየሁሽ ሰአት ቀድሜ ባውቀው ምን እወስን ነበር ብዬ ሁሌም እራሴን ስለምጠይቀው ነው
"አሁን ምን ሆንክ? ትይ ይሆኖል። ምንም አታውቂምና ጥያቄሽ ልክ ነው የኔ ስስት ያኔ ካሁን ቡሀላ ወንድምሽ ነኝ ስልሽ አንቺም ተቀብለሽ የእውነት ወንድም አድርገሽኛልና ምን ሆንክ ብትይኝ ባንቺ አይፈረድም እኔ ግን ብዙ ሆኛለሁ አንቺን በማፍቀሬ እንኳን አንቺ እኔ እንኳን የማላውቀው ሌላ ዳኒ እንደሆኑኩ አውቃለሁ።
ኤዱዬ አፈቅርሻለሁ!
ይህን ስታነቢ ምን ትይኝ ይሆን?
በቃሌ የማልገኝ እራስ ወዳድ ነኝ አደል ኤዱዬ?
በጣም ይቅርታ።
ከግዜ ቡሀላ ለኔም ባልገባኝ መንገድ ውስጤ ተቀያይሮ ካቅሜ በላይ ሆኖብኝ እንጂ ያኔ ወንድም እሆንሻለሁ ከጎንሽ ነኝ እንደወንድምሽ እይኝ ያልኩሽ ግን ከልቤ ነበር!።
ሁሌም ቃሌን ያጠፍኩ መስሎ ይሰማኛል ላንቺ ስላልነገርኩሽ ምንም ባትይኝም ብታውቅ ምን ትለኛለች እያልኩ ከመሸማቀቅ አልዳንኩም።
ፍቅር የሻቱትን ማግኘት ብቻ አይደለምና የኔ እንደማትሆኚ እያሰብኩም አፈቅርሻለሁ።
ከምንም ነገር በላይ አንቺን በእውኔም በህልሜም ማየት፣ ስላንቺ ማሰብ ፣ ስላንቺ ማውራት ያስደስተኛል ። ካንቺ ውጪ ሁሉ ነገር አልጥምህ ካለኝ ወራቶች ተቆጥረዋል።
"ታድያ በነበረን ግዜ በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ውስጥ ከነበርክ እንዴት አልነገርከኝም?
ወይም እንዴት ከፊትህ መረዳት አልቻልኩም? " ትይኝ ይሆናል
በፍቅር ንዳድ ከመለብለብ በላይ በልብ ውስጥ ያለውን የፍቅር እሳት አውጥቶ ላፈቀሩት ሰው ንዳዱን ማሳየት ለብዙ አፍቃሪዎች ከባድ ነው።
እኔን ግን አውጥቶ ከመናገሩም በላይ ከባድ የሆነብኝ ብነግርሽ የሚሰማሽን ስሜት ማሰብ ነው።
ፍቅረኛሽ ሆኜ ቢሆን አሁን ወንድምሽ በመሆኔ የተደሰትሽውን ያክል እምትደሰቺ መስሎ አይታየኝም ።
ካፌ ሻይ ቡና እያልን ፊት ለፊቴ ቁጭ ብለሽ ከናት ካባቴ ባትወለድም አንተን የመሰለ ወንድም በስጦታ ስለሰጠኝ እያልሽ ፈጣሪን ስታመሰግኚ ስሰማ እንኳን ልነግርሽ ማፍቀሬን የምታውቂብኝ እየመሰለኝ ምክንያት ፈጥሬ ካጠገብሽ እሽሻለሁ ።
ጆሲ ጓደኛዬ ምን እንደሚለኝ ታውቂያለሽ ኤዱዬ?
••••" አንተኮ መፍታት ያቃተህ መጀመሪያ ላይ እራስህ አጥብቀህ ያሰርከውን ቋጠሮ ነው አልፈታ ባለህ ቁጥር ደግሞ በንዴት ለመበጠስ እየሞከርክ የበለጠ ታጠብቀዋለህ!" ይለኛል
እውነቱን ነው ትዝ ይልሻል እዱዬ?
ስለመሲ ስናወራ አንድ ሰው ውለታ ውሎልሽ ውለታውን በመንተራስ ከፍላጎትሽ ውጪ የሚጫንሽ ከሆነ ውለታ ሳያስቀድም ተመሳሳይ ጥያቄ ከሚጠይቅሽ ሰው በላይ እርኩስ ነው ብዬሽ ነበር ።
እኔም የፍቅር ጥያቄዬ ካደረኩልሽ ትንሽ ውለታ ጋር እንዳይያያዝብኝ ፈራሁ።
አንቺንም እኔን ወንድም እንጂ ፍቅረኛ የማድረግ ፍላጎት ውስጥሽ ሳይኖር የምጫንሽ ጥያቄዬን ባለመቀበልና እኔን ባለማስከፋት መሀል ሆነሽ የምትጨነቂ መስሎ ታየኝ ።
በዚህ መሀል እናንተ ባታዩኝም ከልጁ ጋር ሆኖችሁ ብዙ ቦታዎች ታጋጥሙኝ ጀመር።
ያኔ በሱም ባንቺም ሳይሆን በራሴ ይበልጥ መናደድ ጀመርኩ ።
ህመምህ መድሀኒት የለውም አትድንም እንደተባለ በሽተኛ የፍቅር ህመሜ ፈውስ የሆንሽውን አንቺን የኔ እንደማላደርግሽ ተረዳሁ ።
ኤዱዬ በመመረቅሽ እንኳን ደስ አለሽ!
በመመረቅሽ የተሰማሽን ደስታ ትንሽ ሳታጣጥሚውና ከድሬ ሳትወጪ አንብበሽው ሌላ ስሜት ውስጥ እንድትገቢ ስላልፈለኩ ነው ይህን ደብዳቤ በእጅሽ ሳልሰጥሽ ከምርቃቷ ቡሀላ ወደ አዲስ አባባ ስሸኛት ሳታየኝ የልብስ ሻንጣዋ ውስጥ አስቀምጥላታለሁ ባየችው ግዜ ትየው ብዬ የወሰንኩት።
በነበረን ስሜት ወንድምሽ ሆኜ ልሸኝሽ ቀናቶች ቀርተዋል ለዛም ተዘጋጅቻለሁ ።
የኔ ኤደን ዛሬም ቢሆን ስላወኩሽ ደስተኛ ነኝ።
የማንም ሁኚ እኔ ግን አፈቅርሻለሁ። መቼም ቢሆን አረሳሽም። ዝምምምም ብዬ ሳፈቅርሽ እኖራለሁ።
ሰላም ሁኚ!
ዳኒ ነኝ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍3
#ልጩህበት!!
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አራት(የመጨረሻው ክፍል)
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ሌላ ስሜት ውስጥ እንድትገቢ ስላልፈለኩ ነው ይህን ደብዳቤ በእጅሽ ሳልሰጥሽ ከምርቃቷ ቡሀላ ወደ አዲስ አባባ ስሸኛት ሳታየኝ የልብስ ሻንጣዋ ውስጥ አስቀምጥላታለሁ ባየችው ግዜ ትየው ብዬ የወሰንኩት።
በነበረን ስሜት ወንድምሽ ሆኜ ልሸኝሽ ቀናቶች ቀርተዋል ለዛም ተዘጋጅቻለሁ ።
የኔ ኤደን ዛሬም ቢሆን ስላወኩሽ ደስተኛ ነኝ።
የማንም ሁኚ እኔ ግን አፈቅርሻለሁ። መቼም ቢሆን አረሳሽም። ዝምምምም ብዬ ሳፈቅርሽ እኖራለሁ።
ሰላም ሁኚ!
ዳኒ ነኝ።
ደብዳቤውን ፅፌ እንደጨረስኩ ለመውረድ ተጨማሪ ሀይል እየጠበቀ ያቀረረውን እንባዬን ከአይኖቼ ላይ ጠራረኩና ተጠቅልዬ ተኛሁ።
የውስጤን በትንሹም ቢሆን አውጥቼ ስልፃፍኩት ነው መሰለኝ ቅልል ያለኝ መስሎ ተሰማኝ ። እንቃልፍ ይዞኝ ከመሄዱ በፊት ፈጣሪዬ አንተ ያልከው ብቻ ይሁን! አልኩ ። እንቅልፍ ወሰደኝ።
ጥዋት ከንቅልፌ ስነቃ ጆሲ እክፍላችን ውስጥ መሀል ግድግዳ ላይ በሰቀላት ክብ መስታወት እየተመለከተ እርጥብ ፀጉሩን ያደራርቃል ።
በኔ ተናዶ ስለምንም ጉዳይ ከኔ ጋር ማውራት ካቆመ ቢቆይም ላወራው ፈለኩ•••
ጆሲ ለኤደን እኮ ደብዳቤ ፃፍኩላት !
"ተው ባክህ! ምነው ቁልቁል?"
ምንድነው ቁልቁል?
"በቴክኖሎጂ ተሽቀንጥሮ የተጣለውን የፍቅር ደብዳቤ መፃፃፍ ኬት ፈልገህ አገኘከው ብዬ ነዋ!"
የመረጥኩት መንገድ እሱን ስለሆነ ከወደቀበት አነሳሁት!
"ምርጫህ ከሆነ ይሁን ግን ምነው ፈጠንክ ገና ከመተዋወቃችሁ!"
እያላገጥክ ነው ጂሲ?
"እያላገጥክ ያለኸው እማ አንተ ነህ ዳንዬ እሄን ሁሉ ግዜ በፍቅሯ ፍዳህን ስታይ ቆይተህ
አንተስ ወደህ ነው ባንተ እንደዛ መሆን እኔንም ቤተሰቦችህንም በጭንቀት ስትንጠን ከርመክ አሁን ልጅቷ ትምህርቷን ጨርሳ አንተንም ሀገሩንም ጥላ ልትሄድ ቀናቶች ሲቀሯት ምን ብለህ ልትፅፍላት ነው ?
እባክሽ ጥለሽኝ አትሂጂ ወይ ተያይዘን እንሂድ ልትላት ነው?
ቆይ በዚህ ሰአት ምን ልትላት ነው!?
አፈቅርሻለሁ ነው አፈቅርሽ ነበር ?"
ጆሲ በቃህ እንግዲህ አታናደኝ !
ከተረዳኸኝ እኔ ለሷ ያለኝ ፍቅር እሷን በማግኘትና በማጣት የሚወሰን አይደለም !
የትም ትሁን የማንም ትሁን አፈቅራታለሁ!
ደሞም ደብዳቤውን የፃፍኩት አሁን ልሰጣት አይደለም!
"ምን ማለት ነው ? ከሄደች ቡሀላ በፖስታ ቤት ልትልክላት ባልሆነ!"
ለምን አይሆንም ?ቢሆንስ?
" እንዴ ታድያ ለምን መፃፉ አስፈለገህ ዝም ብልህ እንዲሁ ፍቅር ዲዳ ያረገህ ይመስል ትንፍሽ ሳትል እንደተለጎምክ ለምን አትሸኛትም?
አዋ እንደተለጎምኩ እሸኛታለሁ ከልጁ ጋር ፍቅር እንደጀመሩ እርግጠኛ ነኝ የኔ ላትሆን ላስጨንቃት አልፈልግም !
"ታድያ እንደዛ ካሰብክ ተዋታ ! እርሳታ በቃ ደብዳቤውን እዛ ደርሳስ ቢሆን ስትልክላት ማንበባቧ ይቀራል እንዴ ያኔስ አትጨነቅም ነው የድሬዳዋ እና ያዲስ አበባ ጭንቀት ይለያያል!"
ጭንቀቱ ላይለያይ ይችላል ያንን የማደርገው በሁለት ምክንያት ነው
አንድ አሁን በመመረቋ የተሰማትን ደስታ ላለመረበሽ
ሁለተኛው እና ዋናው ምክንያቴ ደግሞ ተመርቃ ከሄደች ከኔ ምንም ነገር በማትፈልግበት ሁኔታ ውስጥ ስትሆን ለመወሰን ነፃ ትሆናለች
"አየህ አሁንም ዙረህ ዙረህ ቋጠሮው ጋር ሄድክ ዳንዬ እሄን ቋጠሮ መፍታት ወይ መተው ካልቻልክ በሷ ጉዳይ ከኔ ጋር መቼም አንግባባም "
ብሎኝ ጥሎኝ ወጣ። እሱ ባይሰማኝም
እንኳን ካንተ ጋር ከራሴም መግባባት አልቻልኩም ጓደኛዬ ይቅርታ ስላስጨነኩህ አልኩ ለራሴ።
የኤዱ ቤተሰቦች ድሬ ዳዋ ከመድረሳቸው ከሰአታት በፊት ያ ከመደብደብ ያተረፈኝ ጥበቃ ወደ ሚሰራበት ሆቴል ሄድኩና አልጋ ያዝኩላቸው ስገባ አለነበረም ስወጣ ገና ከሩቅ ሲያየኝ መሳቅ ጀመረ አጠገቡ ስደርስም•••
" ካካካካ ስማ እኔ እኮ እነዛን ልጆች አውቃቸዋለሁ ያን ቀን የባጥ የቋጡን ቀባጥሬ ባላስመልጥህ ለቀብር እሚሆንም እንኳን አያስቀሩልህም ነበር
የት እንደማውቃቸው ታውቃለህ•••"
ብሎ ሊቀጥል ሲል እኔም ፈገግ እያልኩ አቦ ሌላ ግዜ በሰፊው እናወራለን እሺ ከአዲስ አበባ የሚመጣ እንግዳ ልቀበል ነው ደርሰዋል ብየው የሻሂ ሰጠሁትና ሄድኩ።
ከኤዱ ጋር ሆነን ቤተሰቦቿን እየጠበቅን ያ ልጅ በየደቂቃው ይደውል ነበር ስታናግረውም ከኔ ፈንጠር እያለች ነበር ቤተሰቦቿ ደርሰው በኔው ባጃጅ ወደ ያዝኩላቸው ማረፊያ ሄድን ።
እንደደረስን •••
"እማ ዳኒ ማለት እኮ እሱ ነው " አለች እናትና አባቷን በየተራ ልብ በሚሰውረው ፈገግታዋ እያቻቸው።
አቤት ምርቃት እናትና አቧቷ እየተቀባበሉ የመረቁኝ ምርቃት ሰምቸው ሁላ አላውቅም ካሁን ቡሀላ በሂወት ዘመኔ ማንም እኔ ነኝ ያለ ተራጋሚ የፈለገውን አይነት እርግማን ቢረግመኝ እራሱ እሄን ምርቃት አሸንፎት እንደማይደርስብኝ እርግጠኛ ነኝ።
ኤዱ በተመረቀችበት እለት መሄዷን እያሰብኩ ውስጤ ሀዘን ቢሰማውም መመረቋ በሷና በቤተሰቦቿ ፊት ላይ የማየው የደስታ ጥግ ግን ሀዘኔን ለግዜውም ቢሆን አክሽፎት ደስታቸውን ለመጋራት ተገደድኩ።
እንዳትደርስ የፈራኋት የመጨረሻዋ ሰአት ደረሰች።
እኔና ኤዱ በኔ ባጃጅ ወደ ግቢ ሄድንና ከግቢ ያመጣቻቸውን ሻንጣዋን ጨምሮ ሌሎች የግል እቃዎቿን ባጃጇ ውስጥ አስገብታ•••
"ዳኒዬ መጣሁ እሺ ጓደኛቼን ልሰናበታቸው" ብላኝ ሄደች።
ደብዳቤውን ከውሃላ ኪሴ አወጣሁና የልብስ ሻንጣዋን ከፍቼ ልብሶቿ መሀል አርቄ ቀበርኩት።
ሀሙስ ከለሊቱ 10:30 ድሬ ዳዋ የድሮ ባቡር ጣብያ ፊት ለፊት ባጃጄን ተደግፌ ቆሚያለሁ
ከኔ ፊት ለፊት እነ ኤዱን ይዞ ወደ አዲስ አበቧ የሚነጉደው ዘመናዊ አውቶብስ የተሳፋሪዎቹን እቃ ከታች ሆዱ ውስጥ ተሳፋሪዎቹን ደግሞ ከላይ ጭኖ ለመምዘግዘግ መዘጋጀቱን በሚያጓራው ድምፁ ያውጃል።
ኤዱ አንዴ ከኛ ራቅ ብለው የያዙትን እቃ ወደሚያስመዝኑት ቤተሰቦቿ አንዴ ውስጤ ትርምስምስ እንዳለ ባጃጄን ተደግፌ ወደ ቆምኩት ወደኔ ሄድ መለስ ትላለች ።
ግራ ግብት! ጭንቅ !እንዳላት ታስታውቃለች ።
ያን ስሜት የፈጠረባት የኔ ሁኔታ ሳይሆን አይቀርም ።
ምንም ማውራት ሳንችል በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች ካቅማችን በላይ ሆነና መላቀስ ጀመርን በቃ ተላቀስን እሷን እያባበልኩ እኔ አለቀስኩ።
እኔን እያባብለች እሷም አለቀሰች ።
ተለያየን ሄዱ ።
በሄደች በአራተኛው ቀን ስልኬ ላይ በማላውቀው ቁጥር ተደወለ አነሳሁት ••• ኤዱ ነች•••
"ዳንዬ ቆይ ለምን ለምን ለምን " ብቻ ብላ ማልቀስ ጀመረች ደብዳቤውን አግኝታ አንብባው እንደሆነ ገባኝ ።
በስልክም ከመላቀስ ውጩ ብዙ ማውራት አልቻልንም ነገር ግን በሷ ምክንያት በመጎዳቴ እጅግ ማዘኗንና ከልጁ ጋር በፍቅር አብራ መሆኗን ነገረችኝ ለኔ አዲስ አልነበረም በነበርኩበት ከባድ የድብርት ሂወት ቀጠልኩ።
ይህ ከሆነ አንድ አመት ከሁለት ወር እንደሆነው
እንደሁልግዜው ማታ በስካር ጥንብዝ ብዬ ገብቼ ተኝቻለሁ እዛው እንደተኛሁ ከቀኑ አምስት ሰአት አከባቢ ከተኛሁበት በሀይል ተቀሰቀስኩ ብንን ስል ጆሲ ጓደኛዬ እና የኔዋ ኤደን አጠገብ ላጠገብ ቆመዋል።
ወይ መቃዥት አልኩና አይኔን እየጠራረኩ ከተኛሁበት ብድግ ብዬ ቆምኩ አሁንም ፊት ለፊቴ ጎን ለጎን ቆመዋል።ግን ዝም ብለው ያዩኛል እንጂ ትንፍሽ አይሉም።
ያበድኩ የለየልኝ መሰለኝ።ወደ ጆሲ ተጠጋሁና ነካ አደረኩት ።ያኔ ባሰብኝ።ለራሴ አዘንኩ እንባዬ በሁለቱም አይኖቼ ግጥም አለ። የጆሲንም እንባ ያየሁት መሰለኝ።
ጆስዬ በናትህ ተንፍስ!?
ጆሲ እባክህ እውነት ነው እየቃዥህ አይደለም በለኝ ።
ህልም ነው እንዳትለኝ እሺ ጆሲ?
አጠገቤ የቆመችው ያንተዋ ኤደን ነች በለኝ
ተወርውራ አንገቴ ላይ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አራት(የመጨረሻው ክፍል)
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ሌላ ስሜት ውስጥ እንድትገቢ ስላልፈለኩ ነው ይህን ደብዳቤ በእጅሽ ሳልሰጥሽ ከምርቃቷ ቡሀላ ወደ አዲስ አባባ ስሸኛት ሳታየኝ የልብስ ሻንጣዋ ውስጥ አስቀምጥላታለሁ ባየችው ግዜ ትየው ብዬ የወሰንኩት።
በነበረን ስሜት ወንድምሽ ሆኜ ልሸኝሽ ቀናቶች ቀርተዋል ለዛም ተዘጋጅቻለሁ ።
የኔ ኤደን ዛሬም ቢሆን ስላወኩሽ ደስተኛ ነኝ።
የማንም ሁኚ እኔ ግን አፈቅርሻለሁ። መቼም ቢሆን አረሳሽም። ዝምምምም ብዬ ሳፈቅርሽ እኖራለሁ።
ሰላም ሁኚ!
ዳኒ ነኝ።
ደብዳቤውን ፅፌ እንደጨረስኩ ለመውረድ ተጨማሪ ሀይል እየጠበቀ ያቀረረውን እንባዬን ከአይኖቼ ላይ ጠራረኩና ተጠቅልዬ ተኛሁ።
የውስጤን በትንሹም ቢሆን አውጥቼ ስልፃፍኩት ነው መሰለኝ ቅልል ያለኝ መስሎ ተሰማኝ ። እንቃልፍ ይዞኝ ከመሄዱ በፊት ፈጣሪዬ አንተ ያልከው ብቻ ይሁን! አልኩ ። እንቅልፍ ወሰደኝ።
ጥዋት ከንቅልፌ ስነቃ ጆሲ እክፍላችን ውስጥ መሀል ግድግዳ ላይ በሰቀላት ክብ መስታወት እየተመለከተ እርጥብ ፀጉሩን ያደራርቃል ።
በኔ ተናዶ ስለምንም ጉዳይ ከኔ ጋር ማውራት ካቆመ ቢቆይም ላወራው ፈለኩ•••
ጆሲ ለኤደን እኮ ደብዳቤ ፃፍኩላት !
"ተው ባክህ! ምነው ቁልቁል?"
ምንድነው ቁልቁል?
"በቴክኖሎጂ ተሽቀንጥሮ የተጣለውን የፍቅር ደብዳቤ መፃፃፍ ኬት ፈልገህ አገኘከው ብዬ ነዋ!"
የመረጥኩት መንገድ እሱን ስለሆነ ከወደቀበት አነሳሁት!
"ምርጫህ ከሆነ ይሁን ግን ምነው ፈጠንክ ገና ከመተዋወቃችሁ!"
እያላገጥክ ነው ጂሲ?
"እያላገጥክ ያለኸው እማ አንተ ነህ ዳንዬ እሄን ሁሉ ግዜ በፍቅሯ ፍዳህን ስታይ ቆይተህ
አንተስ ወደህ ነው ባንተ እንደዛ መሆን እኔንም ቤተሰቦችህንም በጭንቀት ስትንጠን ከርመክ አሁን ልጅቷ ትምህርቷን ጨርሳ አንተንም ሀገሩንም ጥላ ልትሄድ ቀናቶች ሲቀሯት ምን ብለህ ልትፅፍላት ነው ?
እባክሽ ጥለሽኝ አትሂጂ ወይ ተያይዘን እንሂድ ልትላት ነው?
ቆይ በዚህ ሰአት ምን ልትላት ነው!?
አፈቅርሻለሁ ነው አፈቅርሽ ነበር ?"
ጆሲ በቃህ እንግዲህ አታናደኝ !
ከተረዳኸኝ እኔ ለሷ ያለኝ ፍቅር እሷን በማግኘትና በማጣት የሚወሰን አይደለም !
የትም ትሁን የማንም ትሁን አፈቅራታለሁ!
ደሞም ደብዳቤውን የፃፍኩት አሁን ልሰጣት አይደለም!
"ምን ማለት ነው ? ከሄደች ቡሀላ በፖስታ ቤት ልትልክላት ባልሆነ!"
ለምን አይሆንም ?ቢሆንስ?
" እንዴ ታድያ ለምን መፃፉ አስፈለገህ ዝም ብልህ እንዲሁ ፍቅር ዲዳ ያረገህ ይመስል ትንፍሽ ሳትል እንደተለጎምክ ለምን አትሸኛትም?
አዋ እንደተለጎምኩ እሸኛታለሁ ከልጁ ጋር ፍቅር እንደጀመሩ እርግጠኛ ነኝ የኔ ላትሆን ላስጨንቃት አልፈልግም !
"ታድያ እንደዛ ካሰብክ ተዋታ ! እርሳታ በቃ ደብዳቤውን እዛ ደርሳስ ቢሆን ስትልክላት ማንበባቧ ይቀራል እንዴ ያኔስ አትጨነቅም ነው የድሬዳዋ እና ያዲስ አበባ ጭንቀት ይለያያል!"
ጭንቀቱ ላይለያይ ይችላል ያንን የማደርገው በሁለት ምክንያት ነው
አንድ አሁን በመመረቋ የተሰማትን ደስታ ላለመረበሽ
ሁለተኛው እና ዋናው ምክንያቴ ደግሞ ተመርቃ ከሄደች ከኔ ምንም ነገር በማትፈልግበት ሁኔታ ውስጥ ስትሆን ለመወሰን ነፃ ትሆናለች
"አየህ አሁንም ዙረህ ዙረህ ቋጠሮው ጋር ሄድክ ዳንዬ እሄን ቋጠሮ መፍታት ወይ መተው ካልቻልክ በሷ ጉዳይ ከኔ ጋር መቼም አንግባባም "
ብሎኝ ጥሎኝ ወጣ። እሱ ባይሰማኝም
እንኳን ካንተ ጋር ከራሴም መግባባት አልቻልኩም ጓደኛዬ ይቅርታ ስላስጨነኩህ አልኩ ለራሴ።
የኤዱ ቤተሰቦች ድሬ ዳዋ ከመድረሳቸው ከሰአታት በፊት ያ ከመደብደብ ያተረፈኝ ጥበቃ ወደ ሚሰራበት ሆቴል ሄድኩና አልጋ ያዝኩላቸው ስገባ አለነበረም ስወጣ ገና ከሩቅ ሲያየኝ መሳቅ ጀመረ አጠገቡ ስደርስም•••
" ካካካካ ስማ እኔ እኮ እነዛን ልጆች አውቃቸዋለሁ ያን ቀን የባጥ የቋጡን ቀባጥሬ ባላስመልጥህ ለቀብር እሚሆንም እንኳን አያስቀሩልህም ነበር
የት እንደማውቃቸው ታውቃለህ•••"
ብሎ ሊቀጥል ሲል እኔም ፈገግ እያልኩ አቦ ሌላ ግዜ በሰፊው እናወራለን እሺ ከአዲስ አበባ የሚመጣ እንግዳ ልቀበል ነው ደርሰዋል ብየው የሻሂ ሰጠሁትና ሄድኩ።
ከኤዱ ጋር ሆነን ቤተሰቦቿን እየጠበቅን ያ ልጅ በየደቂቃው ይደውል ነበር ስታናግረውም ከኔ ፈንጠር እያለች ነበር ቤተሰቦቿ ደርሰው በኔው ባጃጅ ወደ ያዝኩላቸው ማረፊያ ሄድን ።
እንደደረስን •••
"እማ ዳኒ ማለት እኮ እሱ ነው " አለች እናትና አባቷን በየተራ ልብ በሚሰውረው ፈገግታዋ እያቻቸው።
አቤት ምርቃት እናትና አቧቷ እየተቀባበሉ የመረቁኝ ምርቃት ሰምቸው ሁላ አላውቅም ካሁን ቡሀላ በሂወት ዘመኔ ማንም እኔ ነኝ ያለ ተራጋሚ የፈለገውን አይነት እርግማን ቢረግመኝ እራሱ እሄን ምርቃት አሸንፎት እንደማይደርስብኝ እርግጠኛ ነኝ።
ኤዱ በተመረቀችበት እለት መሄዷን እያሰብኩ ውስጤ ሀዘን ቢሰማውም መመረቋ በሷና በቤተሰቦቿ ፊት ላይ የማየው የደስታ ጥግ ግን ሀዘኔን ለግዜውም ቢሆን አክሽፎት ደስታቸውን ለመጋራት ተገደድኩ።
እንዳትደርስ የፈራኋት የመጨረሻዋ ሰአት ደረሰች።
እኔና ኤዱ በኔ ባጃጅ ወደ ግቢ ሄድንና ከግቢ ያመጣቻቸውን ሻንጣዋን ጨምሮ ሌሎች የግል እቃዎቿን ባጃጇ ውስጥ አስገብታ•••
"ዳኒዬ መጣሁ እሺ ጓደኛቼን ልሰናበታቸው" ብላኝ ሄደች።
ደብዳቤውን ከውሃላ ኪሴ አወጣሁና የልብስ ሻንጣዋን ከፍቼ ልብሶቿ መሀል አርቄ ቀበርኩት።
ሀሙስ ከለሊቱ 10:30 ድሬ ዳዋ የድሮ ባቡር ጣብያ ፊት ለፊት ባጃጄን ተደግፌ ቆሚያለሁ
ከኔ ፊት ለፊት እነ ኤዱን ይዞ ወደ አዲስ አበቧ የሚነጉደው ዘመናዊ አውቶብስ የተሳፋሪዎቹን እቃ ከታች ሆዱ ውስጥ ተሳፋሪዎቹን ደግሞ ከላይ ጭኖ ለመምዘግዘግ መዘጋጀቱን በሚያጓራው ድምፁ ያውጃል።
ኤዱ አንዴ ከኛ ራቅ ብለው የያዙትን እቃ ወደሚያስመዝኑት ቤተሰቦቿ አንዴ ውስጤ ትርምስምስ እንዳለ ባጃጄን ተደግፌ ወደ ቆምኩት ወደኔ ሄድ መለስ ትላለች ።
ግራ ግብት! ጭንቅ !እንዳላት ታስታውቃለች ።
ያን ስሜት የፈጠረባት የኔ ሁኔታ ሳይሆን አይቀርም ።
ምንም ማውራት ሳንችል በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች ካቅማችን በላይ ሆነና መላቀስ ጀመርን በቃ ተላቀስን እሷን እያባበልኩ እኔ አለቀስኩ።
እኔን እያባብለች እሷም አለቀሰች ።
ተለያየን ሄዱ ።
በሄደች በአራተኛው ቀን ስልኬ ላይ በማላውቀው ቁጥር ተደወለ አነሳሁት ••• ኤዱ ነች•••
"ዳንዬ ቆይ ለምን ለምን ለምን " ብቻ ብላ ማልቀስ ጀመረች ደብዳቤውን አግኝታ አንብባው እንደሆነ ገባኝ ።
በስልክም ከመላቀስ ውጩ ብዙ ማውራት አልቻልንም ነገር ግን በሷ ምክንያት በመጎዳቴ እጅግ ማዘኗንና ከልጁ ጋር በፍቅር አብራ መሆኗን ነገረችኝ ለኔ አዲስ አልነበረም በነበርኩበት ከባድ የድብርት ሂወት ቀጠልኩ።
ይህ ከሆነ አንድ አመት ከሁለት ወር እንደሆነው
እንደሁልግዜው ማታ በስካር ጥንብዝ ብዬ ገብቼ ተኝቻለሁ እዛው እንደተኛሁ ከቀኑ አምስት ሰአት አከባቢ ከተኛሁበት በሀይል ተቀሰቀስኩ ብንን ስል ጆሲ ጓደኛዬ እና የኔዋ ኤደን አጠገብ ላጠገብ ቆመዋል።
ወይ መቃዥት አልኩና አይኔን እየጠራረኩ ከተኛሁበት ብድግ ብዬ ቆምኩ አሁንም ፊት ለፊቴ ጎን ለጎን ቆመዋል።ግን ዝም ብለው ያዩኛል እንጂ ትንፍሽ አይሉም።
ያበድኩ የለየልኝ መሰለኝ።ወደ ጆሲ ተጠጋሁና ነካ አደረኩት ።ያኔ ባሰብኝ።ለራሴ አዘንኩ እንባዬ በሁለቱም አይኖቼ ግጥም አለ። የጆሲንም እንባ ያየሁት መሰለኝ።
ጆስዬ በናትህ ተንፍስ!?
ጆሲ እባክህ እውነት ነው እየቃዥህ አይደለም በለኝ ።
ህልም ነው እንዳትለኝ እሺ ጆሲ?
አጠገቤ የቆመችው ያንተዋ ኤደን ነች በለኝ
ተወርውራ አንገቴ ላይ
👍2