#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
.....ሻምበል ብሩክ ይመስላታል፡፡
የሆነ ደስ የሚል መናፈሻ ውስጥ እጅ ለእጅ ተያይዘው፣ ሲንሸራሸሩ ከቆዩ በኋላ፤ ወደ ኣንድ ጥላው ቀዝቀዝ ያለ፣ ንፁህ አየር ወደሚነፍስበት የወይን ዛፍ ሥር
ይመጡና ከሥሩ ካለው ለምለም ሣር ላይ ጋደም ይላሉ::
በዚህ ጊዜ እሷ እሱን ትራስ አድርጋ፣ ፀጥ ያለውን ኣካባቢ እየቃኙ የተፈጥሮ ውበትን ሲያደንቁ፤ የሁለቱም ዐይኖች ከፊት
ለፊታቸው በሚያዩዋት የጽጌዳ ቅርንጫፍ ላይ ባለችው እንቡጥ ጽጌረዳ አበባ ተማርኮ፤ ጽጌረዳዋን ሲመለከቱ ከቆዩ በኋላ፤ ስለዚያች ጽጌረዳ ለመናገር በአንድ ጊዜ “ እንዴ ” ብለው ይጀምራሉ፡፡
"ምን ልትል ነበር?” ትለዋለች እየሣቀች::
“አንቺስ ምን ልትይ ነበር?” ይላታል እሱም እየሳቀ::
“እንዴት ታምራለች ልል ነበር” ስትለው..
“እኔም እንደሱ ልል ነበር:: ከማማሯም በላይ ደግሞ ልክ የሁለታችንን ፍቅር ትመስላለች ልልሽ ነበር” ይልና ቁልቁል ወርዶ ከንፈሯን ይስማታል፡፡
“ማማሯስ እሺ የሁለታችንን ፍቅር እንዴት ነው የምትመስለው?” ትለዋለች:: ስለፍቅራቸው የበለጠ እንዲያወራላት
ጓጉታ::
“ያልፈነዳ እንቡጥ ጽጌረዳ በአበባነት ደረጃ ላይ ካለው ፍቅራችን ጋር ይመሳሰላል” ይላታል፡፡
“አበባው ፍሬ የሚሆነው መቼ ነው ብሩኬ?” አይን፤ ዐይኑን ሽቅብ እያየች ትጠይቀዋለች::
ወፎች የሚዘምሩ ይመስላታል፡፡ ንፋሱ ሽውው ይላል፡፡ዛፎች ይደንሣሉ፡፡ሰማዩ የጠራ ነው፡፡ሌላ ዓለም፡: ልዩ ዓለም.....
“የሠርጋችን ዕለት በዚያ በጫጉላ ቤት ውስጥ አሀዱ ብለን ትዳርን ስንቀድሰው፡፡ አይመስልሽም ትሁቲና? ቆይ እንዲያውም ይህችን ጽጌረዳ ስለፍቅራችን ገፀበረከት ላቅርብልሽ” ይልና ብድግ ብሎ ያቺን የምታምር እንቡጥ ጽጌረዳ አበባ ቀጥፎ ያመጣና
ይሰጣታል::
“በሠርጋችን ዕለት? .... በጫጉላ ቤት? .... አሀዱ ብለን?... ስንቀድሰው?
ምን ዐይነት ጣጣ ነው? የሆነውን ሁሉ
ብነግረውስ? የጫጉላ ቤቱ ዕቅዳችን መፍረሱን፣ እንደሻው አስገድዶ ክብረ ንፅህናዬን መድፈሩን፤ ብገልጽለትስ?
አያምነኝ ይሆን?
በቃሽኝ አታላይ ነሽ ይለኝ ይሆን? ልንገረው? እያለቀስኩ ልግለጽለት
ወይንስ ልተወው? ወይኔ አምላኬ ምን ጣጣ ውስጥ ከተትከኝ? ወይኔ
ብሩኬ በዚህ ምክንያት እንለያይ ይሆን?...” በስጋት ተዋጠች፡፡
ይህንን ፍርሃቷን በልቧ አምቃ በጭንቀት እንደተዋጠች፤
ሻምበል ብሩክ ቀጥፎ የሰጣትን ጽጌረዳ እንባ በጋረዳቸው ዐይኖቿ ትኩር ብላ መመልከቷን ቀጠለች::
ያቺ የምታምር ጽጌረዳ፣ ያንን የመሰለ ማራኪ ውበት የተላበሰች ለምለም እንቡጥ አባባ፣ ቀስ በቀስ እየጠወለገች፣
እየጠወለገች፣እየደረቀች ሄደችና፣ በእጇ ላይ እንዳለች እርር ብላ ተንኮሻኩሻ ደቀቀች::
በዚህ ጊዜ ትህትና በድንጋጤ ተወራጭታ ከገባችበት አስደንጋጭ የህልም ዓለም ስትወጣ፤ ሰውነቷ ሁሉ በላብ ተዘፍቆ
መንቀጥቀጥ ጀመረች::
ቀስ ብላ ያየችውን ህልም ስትመረምር ፍርሃት ነገሰባትና፤ ሆድ ብሷት “በቃ ልክ ነው:: ህልሜ ትክክል ነው:: ብሩኬን አጣሁት ማለት ነው፡፡ ወይኔ ወይኔ” እያለች ስቅስቅ ብላ ዐይኖቿ
እስከሚያብጡ ድረስ አለቀሰች፡፡
ሻምበል ብሩክ ልጃገረድ ያለመህኗን ሲያውቅ፤ ውሸታም ባለጌ አድርጐ እንደሚገምታት፤ በቃሽኝ እንደሚላት፤ ጠርጥራ ልቧ በሀዘን ተሰበረ::
በዚህ መጥፎ ስሜት ውስጥ ገብታ በሃሣብ ስትዋዥቅ ከቆየች በኋላ፤ ሻምበል ብሩክን የራሷ አድርጋ ለማስቀረት የሚያስችላትን ዘዴ ማውጠንጠን ጀመረች፡፡ በመጨረሻም የሆነ ሃሣብ መጣላት::
“ማን ያውቃል? ዛሬም እንደበፊቱ ሁሉ ልጃገረድ የመሆኔ ምልክቱ ሙሉ ለሙሉ ላይጠፋ ይችላልና የማያስታውቅ ከሆነ ለምን አንድ ሙከራ አላደርግም?” ስትል አሰበች። በመጨረሻም ከሻምበል
ብሩክ ጋር ከመገናኘቷ በፊት ራሷን በዶክተር ልትፈትሽ ወሰነች::
አንዴ ላይታፈስ የፈሰሰ ውሃ፤ በድጋሚ የሚገኝ መስሏት ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር ቀጠሮ ያዘች::
ከመቸኮሏ የተነሳ አርብ ዕለት ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር በያዘችው ቀጠሮ መሠረት
ወደ ቤት እንደደረሱ ተያይዘው ወደ ቤት እንደደረሱ ሠራተኛዋን አገላብጣ ሣመቻት::
ምነው ፍቅርሽ በዛ?” አለቻት ሠራተኛዋ በልቧ፡፡ ትህትና ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር ካሳለፈችው ጊዜ ሁሉ ለየት ያለው የዛሬው ነው:: ለዛሬው ግንኙነታቸው የራሷ ምክንያት ስለአላት፤ የሚሆነውን ቶሎ ለማወቅ፤ ቶሎ ወደ አልጋ ለመሄድ
ቸኮለች፡፡
ቢሆንም ግን ይህንን መቸኮሏን
ዶክተር እንዲያውቅባት አላደረገችም::
እንደተለመደው ሁሉ ዶክተር እራሱን ሊፈትሽ፤ እሷም የልጃገረድነት ሚስጥሯን ልትፈትሽ፤ ተፈላልገውና፤ ተግባብተው፤
ተያይዘው፤ ወደ መኝታ ክፍል ገቡ::
ዶክተር በዚያ ረገድ በራሱ ላይ እምነት እያጣ ስለሄደ በውስጡ የነበረው ጉጉት ቀዝቅዟል፡፡ ሆኖም እንደተለመደው የማይጠገብ ውብ የልጅነት ገላዋ የሚያመነጨውን ሙቀት ለመቋደስ ያህል ብቻ መፍጨርጨሩን ቀጠለ፡፡
......
እሷ ደግሞ በሥጋት እንደተዋጠች ከአሁን አሁን
“ምን ዐይነት ሁኔታ ይፈጠር ይሆን? ልጃገረድ በመሆንና ባለመሆን መካከል ያለው ልዩነት ምን ይመስል ይሆን? በማለት ቁርጧን ለማወቅ ልቧ ትር፤
ትር፤ እያለች የሚያደርገውን
እያንዳንዷን እንቅስቃሴ በንቃት ትከታተላለች፡፡
ቀስ በቀስ አካሉ ከአካሏ ጋር እየተሟሟቀ ፤እየተዋሀደ፣ እየተግባባ፤ መጣና የሷ ገላ እሾህ አመኬላውን አስወግዶ ሊያስተናግደው ዝግጁ መሆኑን ሳያውቅ፣ በሀይል ሲታገላት፤ባልጠበቀው መንገድ ተቀብሎ ያስተናግደው ጀመር፡፡
ትህትና ያንን ሁኔታ ስትመለከት ቅስሟ ስብር ብሎ፤ በሃሣብ ጭልጥ ብላ ሄዳ ሌላ ዓለም ውስጥ ገባች፡፡ ዶክተር ባይከዳኝ ደግሞ በዚያ ባጋጠመው አዲስ ሁኔታ ተደንቆ ጉድ ነው!” አለና ለጊዜው ከገባበት ስሜታዊ ረመጥ ወጥቶ እፎይታ ለማግኘት ያህል ጉልበቱን
እንደድሮው እንደአፍላ የጉርምስና ዘመኑ አድርጐ መጫወቱን ቀጠለ፡፡
በቀላሉ ሊበርድ አልቻለም፡፡ ሰፋ ያለ ጊዜ ወስዶ ተጫወተ፡፡
ይህቺ ሰው ጨው አላት መሰለኝ” እያለ በሚያደርገው ነገር ሁሉ እየተደነቀ ነበር፡፡
ነበር፡፡
እሱ እንደዚያ በደስታ ሲቃ ተውጦ ሲቦርቅ ፣እሷ ግን በድን አካሏን ከሥሩ አጋድማ ዐይኖቿ በከፈቱት ቧንቧዎች እየታጠበች
ዶክተር የልቡ ሲደርስ ቀስ በቀስ ከዚያ ከሚናጥበት የስሜት ማዕበል ወጥቶ የሆነውን ነገር እንደ አዲስ ያስበው ጀመር፡፡
በዚህ ጊዜ የሆነ የቅናት ስሜት ተለኮሰበትና ገላው በንዴት እየተቃጠለ ይጨስ ጀመር፡፡በወሲብ በኩል እርካታን ቢያገኝም፣ ልቡ በዚያው ልክ የምሬት
ደም ሲረጭ ተሰማው::
የልቡ ከደረሰ በኋላ ንጽህናዋን የወሰደው እሱ ባለመሆኑ፤የሆነ የቅናትና የዝቅተኝነት ስሜት አእምሮውን ሰርስሮት ገባ፡፡
መጀመሪያ ካገኛት ቀን ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ ያደረገው ድካሙ ሁሉ ከንቱ መቅረቱን ሲያስታውሰው፤ ያንን ውብ ገላዋን ለሌላ ሰው አሳልፋ መስጠቷን ሲያሰላስለው፣ በንዴት እያረረ፣ ጨጓራው ተቀቅሎ እንደገነተረ ሥጋ ሲገነትር ተሰማው:: የተናቀ የተተፋ መሰለው፡፡
የዚያን ጊዜ የልቡን በልቡ አድርጐ.....
“ትህትና እንደዚህ የማደርገው እኮ ስለምጠብቅሽ ነው” ያላት ቀን
“ይገባኛል ዶክተር” ነበር ያለችው:: ግን ዋሸችው:: እሱ ሲጠብቃት እሷ ከዳችው።
እሱ ተንከባክቦ ያቆየውን ውድ ነገር ለሌላ አስረክባቸው መጣች:: ዶክተር ሁሉም ነገር እንደሰንሰለት ተያይዞ በሃሣቡ
መጣበት:: ደካማነቱ የራሱ ሆኖ ሳለ ራሷን አሳልፋ የሰጠችውን ልጅ ሞራሏን
ሊነካው ፈለገ፡፡የሱ ሞራል ተነክቷል፤ ቅስሙ ተሰብሯልና፤ አጥንት በሌለው ምላሱ አጥንት የሚሰብር ንግግር ሊናገራት ፈልጎ ... ጠጋ አላትና
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
.....ሻምበል ብሩክ ይመስላታል፡፡
የሆነ ደስ የሚል መናፈሻ ውስጥ እጅ ለእጅ ተያይዘው፣ ሲንሸራሸሩ ከቆዩ በኋላ፤ ወደ ኣንድ ጥላው ቀዝቀዝ ያለ፣ ንፁህ አየር ወደሚነፍስበት የወይን ዛፍ ሥር
ይመጡና ከሥሩ ካለው ለምለም ሣር ላይ ጋደም ይላሉ::
በዚህ ጊዜ እሷ እሱን ትራስ አድርጋ፣ ፀጥ ያለውን ኣካባቢ እየቃኙ የተፈጥሮ ውበትን ሲያደንቁ፤ የሁለቱም ዐይኖች ከፊት
ለፊታቸው በሚያዩዋት የጽጌዳ ቅርንጫፍ ላይ ባለችው እንቡጥ ጽጌረዳ አበባ ተማርኮ፤ ጽጌረዳዋን ሲመለከቱ ከቆዩ በኋላ፤ ስለዚያች ጽጌረዳ ለመናገር በአንድ ጊዜ “ እንዴ ” ብለው ይጀምራሉ፡፡
"ምን ልትል ነበር?” ትለዋለች እየሣቀች::
“አንቺስ ምን ልትይ ነበር?” ይላታል እሱም እየሳቀ::
“እንዴት ታምራለች ልል ነበር” ስትለው..
“እኔም እንደሱ ልል ነበር:: ከማማሯም በላይ ደግሞ ልክ የሁለታችንን ፍቅር ትመስላለች ልልሽ ነበር” ይልና ቁልቁል ወርዶ ከንፈሯን ይስማታል፡፡
“ማማሯስ እሺ የሁለታችንን ፍቅር እንዴት ነው የምትመስለው?” ትለዋለች:: ስለፍቅራቸው የበለጠ እንዲያወራላት
ጓጉታ::
“ያልፈነዳ እንቡጥ ጽጌረዳ በአበባነት ደረጃ ላይ ካለው ፍቅራችን ጋር ይመሳሰላል” ይላታል፡፡
“አበባው ፍሬ የሚሆነው መቼ ነው ብሩኬ?” አይን፤ ዐይኑን ሽቅብ እያየች ትጠይቀዋለች::
ወፎች የሚዘምሩ ይመስላታል፡፡ ንፋሱ ሽውው ይላል፡፡ዛፎች ይደንሣሉ፡፡ሰማዩ የጠራ ነው፡፡ሌላ ዓለም፡: ልዩ ዓለም.....
“የሠርጋችን ዕለት በዚያ በጫጉላ ቤት ውስጥ አሀዱ ብለን ትዳርን ስንቀድሰው፡፡ አይመስልሽም ትሁቲና? ቆይ እንዲያውም ይህችን ጽጌረዳ ስለፍቅራችን ገፀበረከት ላቅርብልሽ” ይልና ብድግ ብሎ ያቺን የምታምር እንቡጥ ጽጌረዳ አበባ ቀጥፎ ያመጣና
ይሰጣታል::
“በሠርጋችን ዕለት? .... በጫጉላ ቤት? .... አሀዱ ብለን?... ስንቀድሰው?
ምን ዐይነት ጣጣ ነው? የሆነውን ሁሉ
ብነግረውስ? የጫጉላ ቤቱ ዕቅዳችን መፍረሱን፣ እንደሻው አስገድዶ ክብረ ንፅህናዬን መድፈሩን፤ ብገልጽለትስ?
አያምነኝ ይሆን?
በቃሽኝ አታላይ ነሽ ይለኝ ይሆን? ልንገረው? እያለቀስኩ ልግለጽለት
ወይንስ ልተወው? ወይኔ አምላኬ ምን ጣጣ ውስጥ ከተትከኝ? ወይኔ
ብሩኬ በዚህ ምክንያት እንለያይ ይሆን?...” በስጋት ተዋጠች፡፡
ይህንን ፍርሃቷን በልቧ አምቃ በጭንቀት እንደተዋጠች፤
ሻምበል ብሩክ ቀጥፎ የሰጣትን ጽጌረዳ እንባ በጋረዳቸው ዐይኖቿ ትኩር ብላ መመልከቷን ቀጠለች::
ያቺ የምታምር ጽጌረዳ፣ ያንን የመሰለ ማራኪ ውበት የተላበሰች ለምለም እንቡጥ አባባ፣ ቀስ በቀስ እየጠወለገች፣
እየጠወለገች፣እየደረቀች ሄደችና፣ በእጇ ላይ እንዳለች እርር ብላ ተንኮሻኩሻ ደቀቀች::
በዚህ ጊዜ ትህትና በድንጋጤ ተወራጭታ ከገባችበት አስደንጋጭ የህልም ዓለም ስትወጣ፤ ሰውነቷ ሁሉ በላብ ተዘፍቆ
መንቀጥቀጥ ጀመረች::
ቀስ ብላ ያየችውን ህልም ስትመረምር ፍርሃት ነገሰባትና፤ ሆድ ብሷት “በቃ ልክ ነው:: ህልሜ ትክክል ነው:: ብሩኬን አጣሁት ማለት ነው፡፡ ወይኔ ወይኔ” እያለች ስቅስቅ ብላ ዐይኖቿ
እስከሚያብጡ ድረስ አለቀሰች፡፡
ሻምበል ብሩክ ልጃገረድ ያለመህኗን ሲያውቅ፤ ውሸታም ባለጌ አድርጐ እንደሚገምታት፤ በቃሽኝ እንደሚላት፤ ጠርጥራ ልቧ በሀዘን ተሰበረ::
በዚህ መጥፎ ስሜት ውስጥ ገብታ በሃሣብ ስትዋዥቅ ከቆየች በኋላ፤ ሻምበል ብሩክን የራሷ አድርጋ ለማስቀረት የሚያስችላትን ዘዴ ማውጠንጠን ጀመረች፡፡ በመጨረሻም የሆነ ሃሣብ መጣላት::
“ማን ያውቃል? ዛሬም እንደበፊቱ ሁሉ ልጃገረድ የመሆኔ ምልክቱ ሙሉ ለሙሉ ላይጠፋ ይችላልና የማያስታውቅ ከሆነ ለምን አንድ ሙከራ አላደርግም?” ስትል አሰበች። በመጨረሻም ከሻምበል
ብሩክ ጋር ከመገናኘቷ በፊት ራሷን በዶክተር ልትፈትሽ ወሰነች::
አንዴ ላይታፈስ የፈሰሰ ውሃ፤ በድጋሚ የሚገኝ መስሏት ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር ቀጠሮ ያዘች::
ከመቸኮሏ የተነሳ አርብ ዕለት ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር በያዘችው ቀጠሮ መሠረት
ወደ ቤት እንደደረሱ ተያይዘው ወደ ቤት እንደደረሱ ሠራተኛዋን አገላብጣ ሣመቻት::
ምነው ፍቅርሽ በዛ?” አለቻት ሠራተኛዋ በልቧ፡፡ ትህትና ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር ካሳለፈችው ጊዜ ሁሉ ለየት ያለው የዛሬው ነው:: ለዛሬው ግንኙነታቸው የራሷ ምክንያት ስለአላት፤ የሚሆነውን ቶሎ ለማወቅ፤ ቶሎ ወደ አልጋ ለመሄድ
ቸኮለች፡፡
ቢሆንም ግን ይህንን መቸኮሏን
ዶክተር እንዲያውቅባት አላደረገችም::
እንደተለመደው ሁሉ ዶክተር እራሱን ሊፈትሽ፤ እሷም የልጃገረድነት ሚስጥሯን ልትፈትሽ፤ ተፈላልገውና፤ ተግባብተው፤
ተያይዘው፤ ወደ መኝታ ክፍል ገቡ::
ዶክተር በዚያ ረገድ በራሱ ላይ እምነት እያጣ ስለሄደ በውስጡ የነበረው ጉጉት ቀዝቅዟል፡፡ ሆኖም እንደተለመደው የማይጠገብ ውብ የልጅነት ገላዋ የሚያመነጨውን ሙቀት ለመቋደስ ያህል ብቻ መፍጨርጨሩን ቀጠለ፡፡
......
እሷ ደግሞ በሥጋት እንደተዋጠች ከአሁን አሁን
“ምን ዐይነት ሁኔታ ይፈጠር ይሆን? ልጃገረድ በመሆንና ባለመሆን መካከል ያለው ልዩነት ምን ይመስል ይሆን? በማለት ቁርጧን ለማወቅ ልቧ ትር፤
ትር፤ እያለች የሚያደርገውን
እያንዳንዷን እንቅስቃሴ በንቃት ትከታተላለች፡፡
ቀስ በቀስ አካሉ ከአካሏ ጋር እየተሟሟቀ ፤እየተዋሀደ፣ እየተግባባ፤ መጣና የሷ ገላ እሾህ አመኬላውን አስወግዶ ሊያስተናግደው ዝግጁ መሆኑን ሳያውቅ፣ በሀይል ሲታገላት፤ባልጠበቀው መንገድ ተቀብሎ ያስተናግደው ጀመር፡፡
ትህትና ያንን ሁኔታ ስትመለከት ቅስሟ ስብር ብሎ፤ በሃሣብ ጭልጥ ብላ ሄዳ ሌላ ዓለም ውስጥ ገባች፡፡ ዶክተር ባይከዳኝ ደግሞ በዚያ ባጋጠመው አዲስ ሁኔታ ተደንቆ ጉድ ነው!” አለና ለጊዜው ከገባበት ስሜታዊ ረመጥ ወጥቶ እፎይታ ለማግኘት ያህል ጉልበቱን
እንደድሮው እንደአፍላ የጉርምስና ዘመኑ አድርጐ መጫወቱን ቀጠለ፡፡
በቀላሉ ሊበርድ አልቻለም፡፡ ሰፋ ያለ ጊዜ ወስዶ ተጫወተ፡፡
ይህቺ ሰው ጨው አላት መሰለኝ” እያለ በሚያደርገው ነገር ሁሉ እየተደነቀ ነበር፡፡
ነበር፡፡
እሱ እንደዚያ በደስታ ሲቃ ተውጦ ሲቦርቅ ፣እሷ ግን በድን አካሏን ከሥሩ አጋድማ ዐይኖቿ በከፈቱት ቧንቧዎች እየታጠበች
ዶክተር የልቡ ሲደርስ ቀስ በቀስ ከዚያ ከሚናጥበት የስሜት ማዕበል ወጥቶ የሆነውን ነገር እንደ አዲስ ያስበው ጀመር፡፡
በዚህ ጊዜ የሆነ የቅናት ስሜት ተለኮሰበትና ገላው በንዴት እየተቃጠለ ይጨስ ጀመር፡፡በወሲብ በኩል እርካታን ቢያገኝም፣ ልቡ በዚያው ልክ የምሬት
ደም ሲረጭ ተሰማው::
የልቡ ከደረሰ በኋላ ንጽህናዋን የወሰደው እሱ ባለመሆኑ፤የሆነ የቅናትና የዝቅተኝነት ስሜት አእምሮውን ሰርስሮት ገባ፡፡
መጀመሪያ ካገኛት ቀን ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ ያደረገው ድካሙ ሁሉ ከንቱ መቅረቱን ሲያስታውሰው፤ ያንን ውብ ገላዋን ለሌላ ሰው አሳልፋ መስጠቷን ሲያሰላስለው፣ በንዴት እያረረ፣ ጨጓራው ተቀቅሎ እንደገነተረ ሥጋ ሲገነትር ተሰማው:: የተናቀ የተተፋ መሰለው፡፡
የዚያን ጊዜ የልቡን በልቡ አድርጐ.....
“ትህትና እንደዚህ የማደርገው እኮ ስለምጠብቅሽ ነው” ያላት ቀን
“ይገባኛል ዶክተር” ነበር ያለችው:: ግን ዋሸችው:: እሱ ሲጠብቃት እሷ ከዳችው።
እሱ ተንከባክቦ ያቆየውን ውድ ነገር ለሌላ አስረክባቸው መጣች:: ዶክተር ሁሉም ነገር እንደሰንሰለት ተያይዞ በሃሣቡ
መጣበት:: ደካማነቱ የራሱ ሆኖ ሳለ ራሷን አሳልፋ የሰጠችውን ልጅ ሞራሏን
ሊነካው ፈለገ፡፡የሱ ሞራል ተነክቷል፤ ቅስሙ ተሰብሯልና፤ አጥንት በሌለው ምላሱ አጥንት የሚሰብር ንግግር ሊናገራት ፈልጎ ... ጠጋ አላትና
#ቆንጆዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
......ብዙም ሳይቆይ አንድ ቀጭን አጭር ሰው መንገዱን ተሻግሮ ወደ ቢጫዋ ቁርስ ቤት ሲጣደፍ ተመለከተ፡፡ኮቱን ትከሻው ላይ እንጠልጥሎታል፡፡ ከአፍሪካ አንድነት ድርጅት ጽህፈት ቤት ፊት ለፊት ካለው የላይቤርያ ኤምባሲ እስከ ቁርስ ቤቷ ለመድረስ ብዙ ባያስኬድም ወደፊት ደፋ
ደፋ የሚለው ሰው ረዥም መንገድ የተጓዘ ይመስላል፡፡ ሰውየው ከቁርስ ቤቷ እንደደረስ ወደውስጥ ከመግባቱ በፊት ቆም ብሎ ዙሪያውን ተገላምጦ
ተመለከተ፡፡ ወዲያው ዘው ብሎ ወደ ውስጥ ገባ፡፡
ሰውየው ወደ ውስጥ ሲገባ ናትናኤል ፈጠን ብሎ ከጥግ ወዳለ
የህዝብ ስልክ አመራና አንብቦ በጭንቅላቱ የያዘውን የቢጫዋን ቁርስ ቤት ቁጥር ደወለ፡፡
“አ.ቤት::” አለ የሴት ወይዘሮ ድምፅ፡፡
ያ ክምር ጡታቸው መጥቶ ፊቱ ላይ ድቅን አለበት ናትናኤል፡፡
“እንደምን ዋሉ...ደህና ኖት?” ሴትየዋ መልስ ከመስጠታቸው በፊት አጣደፋቸው “ገብረየሱስ ነኝ..እንደምን ኖት?!” አለ እንደሚያውቃቸው ተዝናንቶ፡፡ “እባኮት ስዩም ጋር ቀጠሮ ነበረን እርሶ ቤት
ያገናኙኝ…ስዩም ይበሉልኝ…እቤትዎ ውስጥ ነው ያለው…ደህና ኖት ግን
እርስዎ..በሉ ስዩምን ያገናኙኝ..” በላይ ቀላይ አጣደፋቸው፡፡
“የማን ስዩምን? አሉ ሴትየዋ ፋታ ሲያገኙ፡፡
“እንዴ!.. ረሱን እንዴ? እቤትዎ በልተን ጠጥተን? አይ የርሶ ነገር! ይብሉ ስዩም ይበሉልኝ፡፡ አይ የርሶ ነገር! ደንበኞቾንም ይረሱ ጀመር?” አጣደፋቸው፡፡
“ኧረ ንሽቴ! የምን መርሳት አመጣህብኝ::!” አሉ ሴትየዋ ድፍረት
አሰባስበው:: “ደሞ እናንተን ደንበኞቼን ልርሳ? ሄ! ሄ! ሄ! ገና ሳላረጅ ምነው
ባክህ! ደህና ነህ ግን አንተ ጠፋህሳ?”
ሴትየዋ ሲጣሩ “ስዩም የሚባል! ስልክ?” ሲሉ በስልኩ ውስጥ ተሰማው፡፡ ነፍሱ መለስ አለችለት:: ስልኩን ጆሮው ላይ እንዳይጠራቅምበት ሰግቶ ነበር፡፡
“ሀሎ… ” አለው ያው ነፍናፋ ድምፅ፡፡
“ስዩም? ” ናትናኤል ቆፍጠን ባለ ድምፅ ጠየቀ፡፡
“ነኝ.የት…?”
“ዝም ብለህ አዳምጠኝ::ቁርስ ቤቷ ውስጥ ይጠብቀኛል ብለህ አስበህ
ከሆነ ሞኝ ነህ፡፡ መልዕክቱን ብቻ እሰጥሀለሁ፡፡ ትስማማለህ?” አለ ናትናኤል ጥድፊያ በተቀላቀለው ድምፅ፡፡
“አዎ አዎ፡: ቀጥል፡፡”
“ጥሩ…. እንዳልኩህ ካልቨርት ለአንተ የማደርስለትን መልዕክትና፡ በርከት ያለ ገንዘብ ሰጥቶኛል፡፡ መልእክቱን ከመስጠቴ በፊት ግን አንተነትህን ማረጋገጥ አለብኝ፡፡”
“ነኝ..ነኝ ግድ የለም:: ስዩም ነኝ፡፡”
“ዝም ብለህ አዳምጠኝ! ለምጠይቅህ ጥያቄ ብቻ ኣጫጭር መልስ ነው የምፈልገው፡፡” አለ ናትናኤል ሰውየውን ይበልጥ ለማደናገር ቱግ ብሎ:: “ካልቨርት በየትኛው ጣቱ ላይ ነው ቀለበት የሚያደርገው?” ያዘጋጃትን ማስመሰያ ጥያቄ አስቀደሙ:: በአውራጣቱ፡ ላያ ቢለውም ግድ አልነበ
ረውም፡፡ ነገር ግን ወደ ዋናዎቹ ጥያቄዎች ከመግባቱ በፊት የሰውየውን
ጭንቅላት ማሟሸት አለበት፡፡
“ቀለበት አያደርግም ካልቨርት::” አለ ሰውየው በሚያስደንቅ ፍጥነት::
“ጥሩ፡፡ አሁንም ፈጣን መልስ እፈልጋለሁ:: ተጠንቀቅ ብትሳሳት
ወይ ብትጠራጠር፡፡ ብትዘገይ ስልኩን ዘግቼ ነው የምሄደው:: የምፈልገው
ትክክለኛውን ስዩም ነው:: የያዝኩትን በርካታ ገንዘብ ላልሆነ ሰው ማስታቀፍ፣
አልፈልግም:: አድምጥ:: የካዛንቺሷ ሴት ስም ማነው?” ናትናኤል በጭንቀት
ትንፋሹን ያዘ፡፡
“የምሥራች ይልማ!” አለ ሰውየው ሌላ ሰው እንዳይቀድመው የፈራ ይመስል በጥድፊያ፡፡
“የስልክ ቁጥሯስ?” አከታትሉ ጠየቀው፡፡
“ትዝ አይለኝም::?”
“እንግዳው ስዩም አያደለህም፡፡ደህና ዋል።”
“ቆይ! ቆይ አለ ነፍናፋው ድምፅ በጭንቀት ተወጥሮ፡፡ቆይ
ስልኩን እንዳትዘጋው። ”
ማስታወሻዬን ልይ… ቆይ አንዴ. እ…ኤ… አዎ ...ይኸው..”
ናትናኤል ስልኩን በጆርውና በትከሻው መሃል ይዞ ሰውየው የነገረውን የስልክ ቁጥር በወረቀት ላይ ይጽፍ ጀመር፡፡ ድንገት ላይ ከሜክሲኮ አደባባይ አቅጣጫ ኣንድ ነጭ ፎርድ መኪና በከፍተኛ ፍጥነት መጥታ ከቢጫዋ ቁርስ ቤት በር ላይ ቆመች:: ወዲያው ከውስጥ የነበሩ ሁለት ሰዎች በሮቻቸውን እየከፈቱ፡ ወረዱ። ሁለቱም የመኪናዋን በሮች
ለመቆለፍ አንኳን ሳይሞክሩ. እየተጣደፉ ወደ ቁርስ ቤቷ አመሩ። ጥቋቁር ኮትና ሱሪ ለብስው የኮታቸውን ቁልፎች ቆልፈዋቸዋል። ናትናኤል ፈሊጡ ገባው:: ቶሎ ዘዴ መቀየስ እንዳለበት ተረዳ፡፡
“ጥሩ፡፡” አለ ድምፁን ሳይቀይር ረጋ ባለ መንፈስ፡፡ “ስዩም ያለሁት ናዝሬት ነው:: ነገ ከጠዋቱ ልክ በአራት ሰዓት ናዝሬት ከቴሌመኒኬሽን ሕንፃ ፊት ለፊት 'ግሪር ሆቴል' የሚል ቤት አለ እዛ እጠብቅሃለሁ:: ነጭ ኮትና ጥቁር መነጸር አደርጋለሁ፡፡ ፒፓ አጨሳለሁ፡፡ ኣደራ ያወራነውን በምሥጢር ያዘው ናትናኤል ስልኩን ዘግቶ እራቅ ብሎ ይጠባበቅ ጀመር፡፡
ወንዲያው ከቢጫዋ ቁርስ ቤት የላይቤርያው ኤምባሲ ሾፌር ሁለቱን
ስዎች አስከትሎ ብቅ አለ፡፡ ሦስቱ" ተከታትለው ወደ መኪናዋ ገቡ፡፡
መኪናዋ ግን አልተንቀሳቀሰችም፡፡ ከኋላ የተቀመጠው የላይቤርያው ኤምባሲ
ሾፌር እጆቹን እያወናጨፈ ሲያወራ ሁለቱ ሰዎች ፊታቸውን ወደኋላ መልሰው ሲያዳምጡት ቆዩ፡፡
ከጥቂት ደቂቃዎች ሰኋላ ስዩም ከመኪናዋ ዕርዶ ለብቻው መንገዱን ተሻግሮ ወደ መሥሪያ ቤቱ አቅጣጫ ሲያመራ ነጯ ፎርድ ተጠምዝዛ ሽቅብ በሜክስኮ አደባባይ አቅጣጫ ተፈተለከች፡፡
ፈገግ አለ ናትናኤል፡፡ “ነገ ናዝሬት እንገናኝ” አለ ከራሱ ጋር፡፡ ወዲያው ኪሱ ከቷት የነበረችውን ወረቀት አወጥቶ አነበባት፡፡ ካዛንቺስ የምሥራች ይልማ
የፈለገውን ይኸን ነበር፡፡ስሟንና የስልክ ቁጥሯን፡፡የፈለገውን ሁሉ አግኝቷል።
የላይቤርያው ሾፌር ያለጥርጥር ለበላይ አለቆቹ አስታውቋል፤ ለአብርሃም አለቆች:: ቢሆንም ለጊዜው አትኩሮታቸው ናዝሬት ከተማ ውስጥ ስለሚሆን እዛው ነው የሚሄዱት፡፡ የአውሬውም ጆሮ በአካባቢው ካለ የእውሬውም አይን ናዝሬት ላይ ነው የሚያፈጥ:: ሁሉም ናዝሬት ነው የሚንጋጉት፡፡ አሁን ነው ጊዜው:: አሁን ነው መነቃነቅ ያለባት፡፡
ሃሎ። “ የህዝብ ስልኩ ውስጥ ሳንቲም ጨምሮ ደወለ፡፡
ሃ..ሎው” ሙልቅቅ ያለ የሴት ድምፅ ጆሮው ውስጥ ዥረር አለበት፡፡
“እ... የምሥራች ይልማ ሆቴል ነው. እባኮት…”
“አዎ ነው፡፡ ማንን ላቅርብሎት?” ሙልቅቅቅ አለችበት፡፡
“እንደምንዋልሽ የኔ እመቤት፡፡ እ...ከባህር ዳር ነበር የመጣሁት፡፡
ባልንጀራዬ መስተንግዷችሁን አድንቆ እናንተጋ እንዳርፍ የስልክ ቁጥራችሁን
ሰጥቶኝ ነበር፡፡ እ... ለባለቤቲቱም ደብዳቤ ይዤ ነበር፡፡ ግን ቤታችሁን
ላገኘው አልቻልኩም፡፡ ባክሽ..
“እይውሎት…. " አቋረጠችው:: “ሞቢል ነዳጅ ማደያው አለ አይደል ካዛንቺስ?” የልጅቷ ድምፅ ሲወርድ እንደ ተልባ ነው፡፡
“ያውቁታል...? በቃ በሱጋ ቀጥታ ሲሄዱ እንደዚህ በስተቀኝ ወደ ላይ ወደግራ የሚታጠፍ መንገድ አለ.. አ..ዎ! እሱን ትተው በስተቀኝ ትንሽ እንደሄዱ በትልቁ
'የምሥራች ሆቴል' የሚል ማስታወቂያ አለ፡፡ አጥሩ ሮዝ ቀለም የተቀባ..”
እቅጣጫውን ከነምልክቱ ጥርት አድርጋ ነገረችው::
ናትናኤል ወዲያውነ ታክሲ ተሳፍሮ ወደ ካዛንቺስ በረረ፡፡ እዚያ ሲደርስ ምን እንደሚያደርግ ግን ለራሱም ግልፅ አልሆነለትም:: በሁለት ታክሲ አሳብሮ የምሥራች ሆቴልን ደጃፍ አለፍ እንዳለ የታክሲውን ሂሣብ ከፍሎ ወረደና ጋቢውን ትከሻው ላይ ቆልሎ ዘውዲቱ የገባችለትን አዲሱን ምርኩዙን እያስቀደመ እሱ እየተክተለ መንገድ ባሻገር ያለውን ሆቴል
እያጠና አለፈ፡፡ እራቅ ብሎ ከሄደ በኋላ ከአንድ የአውቶቡስ ፌርማታ ከለላ
አድርጎ ተቀምጦ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
......ብዙም ሳይቆይ አንድ ቀጭን አጭር ሰው መንገዱን ተሻግሮ ወደ ቢጫዋ ቁርስ ቤት ሲጣደፍ ተመለከተ፡፡ኮቱን ትከሻው ላይ እንጠልጥሎታል፡፡ ከአፍሪካ አንድነት ድርጅት ጽህፈት ቤት ፊት ለፊት ካለው የላይቤርያ ኤምባሲ እስከ ቁርስ ቤቷ ለመድረስ ብዙ ባያስኬድም ወደፊት ደፋ
ደፋ የሚለው ሰው ረዥም መንገድ የተጓዘ ይመስላል፡፡ ሰውየው ከቁርስ ቤቷ እንደደረስ ወደውስጥ ከመግባቱ በፊት ቆም ብሎ ዙሪያውን ተገላምጦ
ተመለከተ፡፡ ወዲያው ዘው ብሎ ወደ ውስጥ ገባ፡፡
ሰውየው ወደ ውስጥ ሲገባ ናትናኤል ፈጠን ብሎ ከጥግ ወዳለ
የህዝብ ስልክ አመራና አንብቦ በጭንቅላቱ የያዘውን የቢጫዋን ቁርስ ቤት ቁጥር ደወለ፡፡
“አ.ቤት::” አለ የሴት ወይዘሮ ድምፅ፡፡
ያ ክምር ጡታቸው መጥቶ ፊቱ ላይ ድቅን አለበት ናትናኤል፡፡
“እንደምን ዋሉ...ደህና ኖት?” ሴትየዋ መልስ ከመስጠታቸው በፊት አጣደፋቸው “ገብረየሱስ ነኝ..እንደምን ኖት?!” አለ እንደሚያውቃቸው ተዝናንቶ፡፡ “እባኮት ስዩም ጋር ቀጠሮ ነበረን እርሶ ቤት
ያገናኙኝ…ስዩም ይበሉልኝ…እቤትዎ ውስጥ ነው ያለው…ደህና ኖት ግን
እርስዎ..በሉ ስዩምን ያገናኙኝ..” በላይ ቀላይ አጣደፋቸው፡፡
“የማን ስዩምን? አሉ ሴትየዋ ፋታ ሲያገኙ፡፡
“እንዴ!.. ረሱን እንዴ? እቤትዎ በልተን ጠጥተን? አይ የርሶ ነገር! ይብሉ ስዩም ይበሉልኝ፡፡ አይ የርሶ ነገር! ደንበኞቾንም ይረሱ ጀመር?” አጣደፋቸው፡፡
“ኧረ ንሽቴ! የምን መርሳት አመጣህብኝ::!” አሉ ሴትየዋ ድፍረት
አሰባስበው:: “ደሞ እናንተን ደንበኞቼን ልርሳ? ሄ! ሄ! ሄ! ገና ሳላረጅ ምነው
ባክህ! ደህና ነህ ግን አንተ ጠፋህሳ?”
ሴትየዋ ሲጣሩ “ስዩም የሚባል! ስልክ?” ሲሉ በስልኩ ውስጥ ተሰማው፡፡ ነፍሱ መለስ አለችለት:: ስልኩን ጆሮው ላይ እንዳይጠራቅምበት ሰግቶ ነበር፡፡
“ሀሎ… ” አለው ያው ነፍናፋ ድምፅ፡፡
“ስዩም? ” ናትናኤል ቆፍጠን ባለ ድምፅ ጠየቀ፡፡
“ነኝ.የት…?”
“ዝም ብለህ አዳምጠኝ::ቁርስ ቤቷ ውስጥ ይጠብቀኛል ብለህ አስበህ
ከሆነ ሞኝ ነህ፡፡ መልዕክቱን ብቻ እሰጥሀለሁ፡፡ ትስማማለህ?” አለ ናትናኤል ጥድፊያ በተቀላቀለው ድምፅ፡፡
“አዎ አዎ፡: ቀጥል፡፡”
“ጥሩ…. እንዳልኩህ ካልቨርት ለአንተ የማደርስለትን መልዕክትና፡ በርከት ያለ ገንዘብ ሰጥቶኛል፡፡ መልእክቱን ከመስጠቴ በፊት ግን አንተነትህን ማረጋገጥ አለብኝ፡፡”
“ነኝ..ነኝ ግድ የለም:: ስዩም ነኝ፡፡”
“ዝም ብለህ አዳምጠኝ! ለምጠይቅህ ጥያቄ ብቻ ኣጫጭር መልስ ነው የምፈልገው፡፡” አለ ናትናኤል ሰውየውን ይበልጥ ለማደናገር ቱግ ብሎ:: “ካልቨርት በየትኛው ጣቱ ላይ ነው ቀለበት የሚያደርገው?” ያዘጋጃትን ማስመሰያ ጥያቄ አስቀደሙ:: በአውራጣቱ፡ ላያ ቢለውም ግድ አልነበ
ረውም፡፡ ነገር ግን ወደ ዋናዎቹ ጥያቄዎች ከመግባቱ በፊት የሰውየውን
ጭንቅላት ማሟሸት አለበት፡፡
“ቀለበት አያደርግም ካልቨርት::” አለ ሰውየው በሚያስደንቅ ፍጥነት::
“ጥሩ፡፡ አሁንም ፈጣን መልስ እፈልጋለሁ:: ተጠንቀቅ ብትሳሳት
ወይ ብትጠራጠር፡፡ ብትዘገይ ስልኩን ዘግቼ ነው የምሄደው:: የምፈልገው
ትክክለኛውን ስዩም ነው:: የያዝኩትን በርካታ ገንዘብ ላልሆነ ሰው ማስታቀፍ፣
አልፈልግም:: አድምጥ:: የካዛንቺሷ ሴት ስም ማነው?” ናትናኤል በጭንቀት
ትንፋሹን ያዘ፡፡
“የምሥራች ይልማ!” አለ ሰውየው ሌላ ሰው እንዳይቀድመው የፈራ ይመስል በጥድፊያ፡፡
“የስልክ ቁጥሯስ?” አከታትሉ ጠየቀው፡፡
“ትዝ አይለኝም::?”
“እንግዳው ስዩም አያደለህም፡፡ደህና ዋል።”
“ቆይ! ቆይ አለ ነፍናፋው ድምፅ በጭንቀት ተወጥሮ፡፡ቆይ
ስልኩን እንዳትዘጋው። ”
ማስታወሻዬን ልይ… ቆይ አንዴ. እ…ኤ… አዎ ...ይኸው..”
ናትናኤል ስልኩን በጆርውና በትከሻው መሃል ይዞ ሰውየው የነገረውን የስልክ ቁጥር በወረቀት ላይ ይጽፍ ጀመር፡፡ ድንገት ላይ ከሜክሲኮ አደባባይ አቅጣጫ ኣንድ ነጭ ፎርድ መኪና በከፍተኛ ፍጥነት መጥታ ከቢጫዋ ቁርስ ቤት በር ላይ ቆመች:: ወዲያው ከውስጥ የነበሩ ሁለት ሰዎች በሮቻቸውን እየከፈቱ፡ ወረዱ። ሁለቱም የመኪናዋን በሮች
ለመቆለፍ አንኳን ሳይሞክሩ. እየተጣደፉ ወደ ቁርስ ቤቷ አመሩ። ጥቋቁር ኮትና ሱሪ ለብስው የኮታቸውን ቁልፎች ቆልፈዋቸዋል። ናትናኤል ፈሊጡ ገባው:: ቶሎ ዘዴ መቀየስ እንዳለበት ተረዳ፡፡
“ጥሩ፡፡” አለ ድምፁን ሳይቀይር ረጋ ባለ መንፈስ፡፡ “ስዩም ያለሁት ናዝሬት ነው:: ነገ ከጠዋቱ ልክ በአራት ሰዓት ናዝሬት ከቴሌመኒኬሽን ሕንፃ ፊት ለፊት 'ግሪር ሆቴል' የሚል ቤት አለ እዛ እጠብቅሃለሁ:: ነጭ ኮትና ጥቁር መነጸር አደርጋለሁ፡፡ ፒፓ አጨሳለሁ፡፡ ኣደራ ያወራነውን በምሥጢር ያዘው ናትናኤል ስልኩን ዘግቶ እራቅ ብሎ ይጠባበቅ ጀመር፡፡
ወንዲያው ከቢጫዋ ቁርስ ቤት የላይቤርያው ኤምባሲ ሾፌር ሁለቱን
ስዎች አስከትሎ ብቅ አለ፡፡ ሦስቱ" ተከታትለው ወደ መኪናዋ ገቡ፡፡
መኪናዋ ግን አልተንቀሳቀሰችም፡፡ ከኋላ የተቀመጠው የላይቤርያው ኤምባሲ
ሾፌር እጆቹን እያወናጨፈ ሲያወራ ሁለቱ ሰዎች ፊታቸውን ወደኋላ መልሰው ሲያዳምጡት ቆዩ፡፡
ከጥቂት ደቂቃዎች ሰኋላ ስዩም ከመኪናዋ ዕርዶ ለብቻው መንገዱን ተሻግሮ ወደ መሥሪያ ቤቱ አቅጣጫ ሲያመራ ነጯ ፎርድ ተጠምዝዛ ሽቅብ በሜክስኮ አደባባይ አቅጣጫ ተፈተለከች፡፡
ፈገግ አለ ናትናኤል፡፡ “ነገ ናዝሬት እንገናኝ” አለ ከራሱ ጋር፡፡ ወዲያው ኪሱ ከቷት የነበረችውን ወረቀት አወጥቶ አነበባት፡፡ ካዛንቺስ የምሥራች ይልማ
የፈለገውን ይኸን ነበር፡፡ስሟንና የስልክ ቁጥሯን፡፡የፈለገውን ሁሉ አግኝቷል።
የላይቤርያው ሾፌር ያለጥርጥር ለበላይ አለቆቹ አስታውቋል፤ ለአብርሃም አለቆች:: ቢሆንም ለጊዜው አትኩሮታቸው ናዝሬት ከተማ ውስጥ ስለሚሆን እዛው ነው የሚሄዱት፡፡ የአውሬውም ጆሮ በአካባቢው ካለ የእውሬውም አይን ናዝሬት ላይ ነው የሚያፈጥ:: ሁሉም ናዝሬት ነው የሚንጋጉት፡፡ አሁን ነው ጊዜው:: አሁን ነው መነቃነቅ ያለባት፡፡
ሃሎ። “ የህዝብ ስልኩ ውስጥ ሳንቲም ጨምሮ ደወለ፡፡
ሃ..ሎው” ሙልቅቅ ያለ የሴት ድምፅ ጆሮው ውስጥ ዥረር አለበት፡፡
“እ... የምሥራች ይልማ ሆቴል ነው. እባኮት…”
“አዎ ነው፡፡ ማንን ላቅርብሎት?” ሙልቅቅቅ አለችበት፡፡
“እንደምንዋልሽ የኔ እመቤት፡፡ እ...ከባህር ዳር ነበር የመጣሁት፡፡
ባልንጀራዬ መስተንግዷችሁን አድንቆ እናንተጋ እንዳርፍ የስልክ ቁጥራችሁን
ሰጥቶኝ ነበር፡፡ እ... ለባለቤቲቱም ደብዳቤ ይዤ ነበር፡፡ ግን ቤታችሁን
ላገኘው አልቻልኩም፡፡ ባክሽ..
“እይውሎት…. " አቋረጠችው:: “ሞቢል ነዳጅ ማደያው አለ አይደል ካዛንቺስ?” የልጅቷ ድምፅ ሲወርድ እንደ ተልባ ነው፡፡
“ያውቁታል...? በቃ በሱጋ ቀጥታ ሲሄዱ እንደዚህ በስተቀኝ ወደ ላይ ወደግራ የሚታጠፍ መንገድ አለ.. አ..ዎ! እሱን ትተው በስተቀኝ ትንሽ እንደሄዱ በትልቁ
'የምሥራች ሆቴል' የሚል ማስታወቂያ አለ፡፡ አጥሩ ሮዝ ቀለም የተቀባ..”
እቅጣጫውን ከነምልክቱ ጥርት አድርጋ ነገረችው::
ናትናኤል ወዲያውነ ታክሲ ተሳፍሮ ወደ ካዛንቺስ በረረ፡፡ እዚያ ሲደርስ ምን እንደሚያደርግ ግን ለራሱም ግልፅ አልሆነለትም:: በሁለት ታክሲ አሳብሮ የምሥራች ሆቴልን ደጃፍ አለፍ እንዳለ የታክሲውን ሂሣብ ከፍሎ ወረደና ጋቢውን ትከሻው ላይ ቆልሎ ዘውዲቱ የገባችለትን አዲሱን ምርኩዙን እያስቀደመ እሱ እየተክተለ መንገድ ባሻገር ያለውን ሆቴል
እያጠና አለፈ፡፡ እራቅ ብሎ ከሄደ በኋላ ከአንድ የአውቶቡስ ፌርማታ ከለላ
አድርጎ ተቀምጦ
#የፍቅር_ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
....ከዘጠኝ ዓመታት በፊት
ዴሪክ ዊልያምስ ሙሉ መስታወት በሆነው የቢሮ በር አሻግሮ ከእንግዳ
ማረፊያ ክፍል ውስጥ የተቀመጡትን ባል እና ሚስቶችን እየተመለከታቸው
ነው፡፡
ቢሮው ትልቅ እና ውድ በሆኑ እቃዎች የተሞላ ነው፡፡ የእንግዳ ማረፊያ ክፍሉም ቢሆን ኮርኒሱ ከፍ ብሎ የተሰራ ከመሆኑም በላይ በጥሩ የዲዛይን ባለሙያ እና በደንብ ባጌጡ ሶፋዎች የተሞላ ነው፡፡
ጠረጴዛዎቹ ላይም ላይፍ ስታይል መፅሄቶች ሞልተውታል፡፡ ይህ እንዲሆን ያደረገችው ደግሞ የዴሪክ ዊልያምስ አዲሱ ሚስቱ ሎርያን ነች፡፡
“ማሬ ገንዘብ ለማግኘት እኮ ገንዘብ ማውጣት ይኖርብናል” የሚለው
ምክርዋ ዋነኛው ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ “ሰዎችን መጀመሪያ ባገኘሃቸው
ጊዜ ነው ልታስደስታቸው የምትችለው ሌላ እድል የለህም” የሚለው ነው።
ዴሪክ የሎርያንን ምክር ተግባራዊ ያደርግ የነበረው ስለምወዳት ነው ብሎ
ያስባል ወይንም ደግሞ ምርጥ ጡቶችና ያበደ መቀመጫ ስላላት እና ሌሎች
ሰዎችን ትታ እሱን በመምረጥዋ ሊሆን ይችላል ብሎ አንዳንዴ ይፈላሰፋል።
ለማንኛውም ይሄ “ገንዘብ ለማግኘት እኮ ገንዘብ ማውጣት ይኖርብናል የሚለው ፍልስፍና ሲሰራ ተመልክቷል። ምክንያቱም አዲሱ ቢሮው ከተሰራ
በኋላ የእሱ ተፈላጊነት በስልሳ ፐርሰንት ጨምሯል። ገቢውም ቢሆን በሶስት
እጥፍ ለማደግ ችሏል፡፡ ምናልባትም ይሄ
ሊሆን የቻለው ሰዎች ለሚያገኙት
አገልግሎት ብዙ ገንዘብ ሲያወጡ ነገሩ እንደሚከናወንላቸው ስለሚያምኑ ሊሆን ይችላል፡፡ ማንም ሰው ደግሞ እርካሽ የሆነ አገልግሎት አይፈልግም ብላ ሚስቱ የምትነግረው ነገር ትክክል ስለሆነም ሊሆን ይችላል፡፡
የዛሬዎቹ ጥንዶች ግን ለዴሪክ አገልግሎት የከፈሉት ክፍያ ትንሽ
ከመሆኑም በላይ ከዚህ በፊትም ለሰራላቸው የተለያዩ ምርመራዎች
ያልከፈሉት ብዙ ዕዳዎች አለባቸው፡፡ ለምን እንደሆነ አያውቀውም ብቻ
ለእነርሱ ከልብ የመነጨ የሃዘኔታ ስሜት ይሰማዋል። ለምንስ ዛሬ ሊያገኙት
እንደመጡ ሲያስብ ደግሞ ልቡን ፍርሃት ፍርሃት ብሎታል። እነሱ ግን እጅ
ለእጅ ተያይዘው እና ጣቶቻቸውን አቆላልፈው ጎን ለጎን ተቀምጠዋል።
ሰውዬው ተከር ክላንሲ ይባላል፡፡ ጥቅጥቅ ያለ በደንብ የተገነባ ሰውነት
አለው፡፡ ደንዳና አንገቱን ጥብቅ አድርጎ በሸሚዙ ስለቆለፈው የታነቀ ይመስላል፡፡ ካኪ ሱሪ እና ጂንስ ሱሪ ለብሷል፡፡ ወግ አጥባቂ ነገርም ስለሆነ ምናልባት ልብሱን ሲያወልቅ ሰውነቱ ላይ የሪፐብሊካን ፓርቲ ምልክት የሆነውን ዝሆን ተነቅሶት ሊሆን ይችላል፡፡ ሁሉ ነገሩን በጥንቃቄ እና
በስርአቱ የሚከውን ሰው መሆኑን ፊቱን በማየት ብቻ ማወቅ ይቻላል። ያም
ቢሆን ግን የደረሰበት ከፍተኛ ሀዘን እና ውስጣዊ ሀዘኑን ከፊቱ ላይ ማንበብ
ይቻላል። ዕድሜው በአርባዎቹ አጋማሽ ላይ ቢገኝም ሲታይ ግን የስልሳ
አመት ሽማግሌ ነበር የሚመስለው፡፡ አንድ ልጅን በሞት ማጣትን የሚመስል
ከባድ ሀዘን አይገኝም፡፡ ነገር ግን ይህቺን አንድ ልጅህን ጠፍታ ሳትገኝ መቅረትዋ በወላጅ የዋህ ልብም የጠፋችው ልጅ የሆነ ቀን ላይ ተገኝታ ወደ ቤትዋ በመመለስ የወላጆችዋን ስቃይ እንዲያበቃ ታደርጋለች ብሎ መጠበቅን
የመሰለ እጅግ በጣም ስሜትን የሚጎዳ ነገር እንደሌለ ዴሪክ ዊልያምስ በደንብ
ይገባዋል፡፡
ባለቤቱ ሜሪ ግን በጥሩ ሁኔታ ላይ የምትገኝ ትመስላለች። እርግጥ ነው
እሷም ብትሆን ይደክማታል፤ ያም ሆኖ ግን የልጅዋን ዕጣ ፈንታ ከባሏ በታቃራኒ መልኩ ተቀብላ ነገረ አለሙን ሁሉ ረስታ የተቀመጠች ሴት ሆናለች፡፡ ለዚህም ሊሆን ይችላል በውስጧ የሚገኘውን ስቃይዋን ፊቷ ላይ ማንበብ የማይቻለው፡፡ ይሄ ጥሩ ነው፤ ቢያንስ ከሁለቱ አንዱ እውነታውን ተቀብለውታል ብሎ ዊልያምስ አሰበ፡፡
ለሶስት ሳምንት ያህል ሜክሲኮ ሲቲ ውስጥ ዊሊያምስ የክላንሲን ልጅ
ቻርሎቴን ለመፈለግ ሲኳትን ነበር፡፡
ከመጥፋትዋ በፊት ያሉትን የቻርሎቴ
ውሎዎችን አና ያገኘቻቸውን ሰዎች በማግኘትም ዱካዋን ለመፈለግ ጥረት
ሲያደርግ ቆየ፡፡ ቆንጅየዋ ቻርሎቴ ክላንሲ ረጅም ናት፤ በተለይ ደግሞ ከሃገሬው የሜክሲኮ ሴቶች አንጻር በቀላሉ በምትኖርበት አካባቢ የምትለይ
ቢሆንም ከጠፋችበት ምሽት በኋላ ማንም ሰው አይቷት እንደማያውቅ ነበር
የነገሩት፡፡
በመጀመሪያ ጊዜ ባል እና ሚስቱ የቻርሎቴ ወላጆች ስለ ቻርሎቴ የፍለጋ
ሁኔታ በደንብ አልነገሩትም ነበር፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት አባቷ ተከር አላንሲ የውጭ ሀገር ፖሊሶች በተለይ ደግሞ የሜክሲኮ ፖሊሶች በሙሉ የማይረቡ ናቸው ብሎ ስለሚያምን ነበር፡፡ ስለዚህም በፍለጋው ላይ ምናልባትም ኤፍ.ቢ.አይ እና በሜክሲኮ የአሜሪካ ቆንስላ በጉዳዩ ላይ ቢገቡበት ልጁ የምትገኝ መስሎት ነበር፡፡ ነገር ግን በሚገርም ሁኔታ ከሜክሲኮ ፖሊሶች በባሰ መልኩ የልጁን ጉዳይ ችላ ስላሉት ንዴቱን በዚህ
መልኩ ነበር የገለጸለት፡፡
“ስለ ቻርሊ እኮ ምንም ደንታ የላቸውም” ብሎ በመጮህ ነበር ተከር ክላንሲ በሁሉም ነገር ተስፋ ቆርጦ እሱን ለመቅጠር በመጣ ጊዜ የተናገረው
እሷ የአሜሪካ ዜግነት ያላት ሴት አይደለችም እንዴ? ታዲያ ለምንድነው
በየጥሻው ውስጥ የማይፈልጓት?”
ዊልያምስ የተከር ክላንሲ ንዴት ይገባዋል ግን ደግሞ በኤፍ.ቢ.አይ እና በቆንጽላው ጽ/ቤት አልተገረመም፡፡ “አሳዛኙ ነገር ግን ምን መሰላችሁ ቻርሎቴን በደንብ ሊፈልጓት የሚችሉት እሷ የሀብታም ልጅ ወይንም የባለስልጣን ልጅ ብትሆን ነበር፡፡ ስለሆነም የኤፍ ቢ አይ ሰዎች እሷን ለመፈለግ ጊዜያቸውን እና ሀብታቸውን ማውጣት አይፈልጉም፡፡ እሷ
ለመጨረሻ ጊዜ ወደ እናንተ ስትደውልላችሁ እድሜዋ ከ18 አመት በላይ ነበር፡፡ ብዙ ልጆች ደግሞ በዚህ እድሜያቸው ላይ ለወላጆቻቸው ሳይናገሩ
ከሆነ ሰው ጋር ሊጠፉ ይችላሉ፡፡”
ቻርሊ በፍፁም እንደዚህ ያለ ነገር አታደርግም” አለ ተከር ክላንሲ፡፡በዚያ ላይ ደግሞ ለአመታት ያህል በእኛ ላይ ጨክና ሳታናግረን አትተወንም፡፡” ሲል ሚስቱም ቀጠል አድርጋ “ሚስተር ዊልያምስ የሆነ ነገር ልጃችን ላይ እንደደረሰባት ይታወቀናል” ብላ እምባዋን ታግላ አስቀረችው እና ወይዘሮ ባደን እንደነገረችንኸውን ሜክሲኮ ውስጥ በየአመቱ ቱሪስቶች እና ሌሎች ሰዎች እንደሚታገቱ ነው፡፡”
“ምን አልሽኝ?” ብሎ ዊልያምስ ጠየቀ፡፡
“ቫለንቲና ባደን ናት፡፡ የዊሊ ባደን ሚስት ናት፡፡ የጠፉ ሰዎችን የሚያፈላልጉ የበጎ አድራጎት ድርጅት የከፈተች ናት።ከማንም በላይ ቻርሎቴን ለመፈለግ እገዛ አድርጋልናለች አለው ተከር ክላንሲ፡፡”
ይህንን ሲሰማ በድንገት አንድ ነገር ትዝ አለው ተከር፡፡ የሆነ ማታ ላይ ሁለት ታላላቅ ክለቦች እየተጫወቱ በነበሩበት የእራት ሰዓት ላይ ልጆቻቸውን እንዲያፈላልጉላቸው ሲማጸኑ እንደነበር አስታወሰ፡፡ ያኔ በዚህ የእረፍት ሰዓት ላይ ለሚተላለፉ ማንኛውም ነገሮች በጣም ውድ የሆነ ዋጋ ለቲቪ ጣቢያዎች ተከፍሎ ነው፡፡ ስለዚህም ይህንን የማስታውቂያ ክፍያ የከፈለችው
የዊሊ ባደን ሚስት ቫለንቲና ባደን መሆንዋን ተረዳ፡፡
“በፍፁም ወደዚያ እንድትሄድ ልፈቅድላት አይገባኝም ነበር፡፡” አለ ተከር ክላንሲ በቁጭት፡፡
“ምን መሰለህ ሚስ ባደን በእገታ የተወሰዱ ሰዎችን በማፈላለግና
ለአጋቾቹ የማስለቀቂያ ክፍያ እየከፈለች ታጋቾችን ከቤተሰቦቻቸው ጋር
እንደምታገኛኝ ነው የምናውቀው፡፡ ይሄው እንግዲህ ስለልጃችን ግን አንድም
ሰው እስካሁን ድረስ የደወለልን የለም፡፡ ይሄ ነገር ጥሩ ይሁን መጥፎ ሊገባን
አልቻለም” አለችው ሜሪ ክላንሲ፡፡
መጥፎ ነው እንጂ ብሎ አሰበ ዊልያምስ ደግሞም ይህቺ ቫለንቲና
ባደን ለቻርሎቴ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
....ከዘጠኝ ዓመታት በፊት
ዴሪክ ዊልያምስ ሙሉ መስታወት በሆነው የቢሮ በር አሻግሮ ከእንግዳ
ማረፊያ ክፍል ውስጥ የተቀመጡትን ባል እና ሚስቶችን እየተመለከታቸው
ነው፡፡
ቢሮው ትልቅ እና ውድ በሆኑ እቃዎች የተሞላ ነው፡፡ የእንግዳ ማረፊያ ክፍሉም ቢሆን ኮርኒሱ ከፍ ብሎ የተሰራ ከመሆኑም በላይ በጥሩ የዲዛይን ባለሙያ እና በደንብ ባጌጡ ሶፋዎች የተሞላ ነው፡፡
ጠረጴዛዎቹ ላይም ላይፍ ስታይል መፅሄቶች ሞልተውታል፡፡ ይህ እንዲሆን ያደረገችው ደግሞ የዴሪክ ዊልያምስ አዲሱ ሚስቱ ሎርያን ነች፡፡
“ማሬ ገንዘብ ለማግኘት እኮ ገንዘብ ማውጣት ይኖርብናል” የሚለው
ምክርዋ ዋነኛው ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ “ሰዎችን መጀመሪያ ባገኘሃቸው
ጊዜ ነው ልታስደስታቸው የምትችለው ሌላ እድል የለህም” የሚለው ነው።
ዴሪክ የሎርያንን ምክር ተግባራዊ ያደርግ የነበረው ስለምወዳት ነው ብሎ
ያስባል ወይንም ደግሞ ምርጥ ጡቶችና ያበደ መቀመጫ ስላላት እና ሌሎች
ሰዎችን ትታ እሱን በመምረጥዋ ሊሆን ይችላል ብሎ አንዳንዴ ይፈላሰፋል።
ለማንኛውም ይሄ “ገንዘብ ለማግኘት እኮ ገንዘብ ማውጣት ይኖርብናል የሚለው ፍልስፍና ሲሰራ ተመልክቷል። ምክንያቱም አዲሱ ቢሮው ከተሰራ
በኋላ የእሱ ተፈላጊነት በስልሳ ፐርሰንት ጨምሯል። ገቢውም ቢሆን በሶስት
እጥፍ ለማደግ ችሏል፡፡ ምናልባትም ይሄ
ሊሆን የቻለው ሰዎች ለሚያገኙት
አገልግሎት ብዙ ገንዘብ ሲያወጡ ነገሩ እንደሚከናወንላቸው ስለሚያምኑ ሊሆን ይችላል፡፡ ማንም ሰው ደግሞ እርካሽ የሆነ አገልግሎት አይፈልግም ብላ ሚስቱ የምትነግረው ነገር ትክክል ስለሆነም ሊሆን ይችላል፡፡
የዛሬዎቹ ጥንዶች ግን ለዴሪክ አገልግሎት የከፈሉት ክፍያ ትንሽ
ከመሆኑም በላይ ከዚህ በፊትም ለሰራላቸው የተለያዩ ምርመራዎች
ያልከፈሉት ብዙ ዕዳዎች አለባቸው፡፡ ለምን እንደሆነ አያውቀውም ብቻ
ለእነርሱ ከልብ የመነጨ የሃዘኔታ ስሜት ይሰማዋል። ለምንስ ዛሬ ሊያገኙት
እንደመጡ ሲያስብ ደግሞ ልቡን ፍርሃት ፍርሃት ብሎታል። እነሱ ግን እጅ
ለእጅ ተያይዘው እና ጣቶቻቸውን አቆላልፈው ጎን ለጎን ተቀምጠዋል።
ሰውዬው ተከር ክላንሲ ይባላል፡፡ ጥቅጥቅ ያለ በደንብ የተገነባ ሰውነት
አለው፡፡ ደንዳና አንገቱን ጥብቅ አድርጎ በሸሚዙ ስለቆለፈው የታነቀ ይመስላል፡፡ ካኪ ሱሪ እና ጂንስ ሱሪ ለብሷል፡፡ ወግ አጥባቂ ነገርም ስለሆነ ምናልባት ልብሱን ሲያወልቅ ሰውነቱ ላይ የሪፐብሊካን ፓርቲ ምልክት የሆነውን ዝሆን ተነቅሶት ሊሆን ይችላል፡፡ ሁሉ ነገሩን በጥንቃቄ እና
በስርአቱ የሚከውን ሰው መሆኑን ፊቱን በማየት ብቻ ማወቅ ይቻላል። ያም
ቢሆን ግን የደረሰበት ከፍተኛ ሀዘን እና ውስጣዊ ሀዘኑን ከፊቱ ላይ ማንበብ
ይቻላል። ዕድሜው በአርባዎቹ አጋማሽ ላይ ቢገኝም ሲታይ ግን የስልሳ
አመት ሽማግሌ ነበር የሚመስለው፡፡ አንድ ልጅን በሞት ማጣትን የሚመስል
ከባድ ሀዘን አይገኝም፡፡ ነገር ግን ይህቺን አንድ ልጅህን ጠፍታ ሳትገኝ መቅረትዋ በወላጅ የዋህ ልብም የጠፋችው ልጅ የሆነ ቀን ላይ ተገኝታ ወደ ቤትዋ በመመለስ የወላጆችዋን ስቃይ እንዲያበቃ ታደርጋለች ብሎ መጠበቅን
የመሰለ እጅግ በጣም ስሜትን የሚጎዳ ነገር እንደሌለ ዴሪክ ዊልያምስ በደንብ
ይገባዋል፡፡
ባለቤቱ ሜሪ ግን በጥሩ ሁኔታ ላይ የምትገኝ ትመስላለች። እርግጥ ነው
እሷም ብትሆን ይደክማታል፤ ያም ሆኖ ግን የልጅዋን ዕጣ ፈንታ ከባሏ በታቃራኒ መልኩ ተቀብላ ነገረ አለሙን ሁሉ ረስታ የተቀመጠች ሴት ሆናለች፡፡ ለዚህም ሊሆን ይችላል በውስጧ የሚገኘውን ስቃይዋን ፊቷ ላይ ማንበብ የማይቻለው፡፡ ይሄ ጥሩ ነው፤ ቢያንስ ከሁለቱ አንዱ እውነታውን ተቀብለውታል ብሎ ዊልያምስ አሰበ፡፡
ለሶስት ሳምንት ያህል ሜክሲኮ ሲቲ ውስጥ ዊሊያምስ የክላንሲን ልጅ
ቻርሎቴን ለመፈለግ ሲኳትን ነበር፡፡
ከመጥፋትዋ በፊት ያሉትን የቻርሎቴ
ውሎዎችን አና ያገኘቻቸውን ሰዎች በማግኘትም ዱካዋን ለመፈለግ ጥረት
ሲያደርግ ቆየ፡፡ ቆንጅየዋ ቻርሎቴ ክላንሲ ረጅም ናት፤ በተለይ ደግሞ ከሃገሬው የሜክሲኮ ሴቶች አንጻር በቀላሉ በምትኖርበት አካባቢ የምትለይ
ቢሆንም ከጠፋችበት ምሽት በኋላ ማንም ሰው አይቷት እንደማያውቅ ነበር
የነገሩት፡፡
በመጀመሪያ ጊዜ ባል እና ሚስቱ የቻርሎቴ ወላጆች ስለ ቻርሎቴ የፍለጋ
ሁኔታ በደንብ አልነገሩትም ነበር፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት አባቷ ተከር አላንሲ የውጭ ሀገር ፖሊሶች በተለይ ደግሞ የሜክሲኮ ፖሊሶች በሙሉ የማይረቡ ናቸው ብሎ ስለሚያምን ነበር፡፡ ስለዚህም በፍለጋው ላይ ምናልባትም ኤፍ.ቢ.አይ እና በሜክሲኮ የአሜሪካ ቆንስላ በጉዳዩ ላይ ቢገቡበት ልጁ የምትገኝ መስሎት ነበር፡፡ ነገር ግን በሚገርም ሁኔታ ከሜክሲኮ ፖሊሶች በባሰ መልኩ የልጁን ጉዳይ ችላ ስላሉት ንዴቱን በዚህ
መልኩ ነበር የገለጸለት፡፡
“ስለ ቻርሊ እኮ ምንም ደንታ የላቸውም” ብሎ በመጮህ ነበር ተከር ክላንሲ በሁሉም ነገር ተስፋ ቆርጦ እሱን ለመቅጠር በመጣ ጊዜ የተናገረው
እሷ የአሜሪካ ዜግነት ያላት ሴት አይደለችም እንዴ? ታዲያ ለምንድነው
በየጥሻው ውስጥ የማይፈልጓት?”
ዊልያምስ የተከር ክላንሲ ንዴት ይገባዋል ግን ደግሞ በኤፍ.ቢ.አይ እና በቆንጽላው ጽ/ቤት አልተገረመም፡፡ “አሳዛኙ ነገር ግን ምን መሰላችሁ ቻርሎቴን በደንብ ሊፈልጓት የሚችሉት እሷ የሀብታም ልጅ ወይንም የባለስልጣን ልጅ ብትሆን ነበር፡፡ ስለሆነም የኤፍ ቢ አይ ሰዎች እሷን ለመፈለግ ጊዜያቸውን እና ሀብታቸውን ማውጣት አይፈልጉም፡፡ እሷ
ለመጨረሻ ጊዜ ወደ እናንተ ስትደውልላችሁ እድሜዋ ከ18 አመት በላይ ነበር፡፡ ብዙ ልጆች ደግሞ በዚህ እድሜያቸው ላይ ለወላጆቻቸው ሳይናገሩ
ከሆነ ሰው ጋር ሊጠፉ ይችላሉ፡፡”
ቻርሊ በፍፁም እንደዚህ ያለ ነገር አታደርግም” አለ ተከር ክላንሲ፡፡በዚያ ላይ ደግሞ ለአመታት ያህል በእኛ ላይ ጨክና ሳታናግረን አትተወንም፡፡” ሲል ሚስቱም ቀጠል አድርጋ “ሚስተር ዊልያምስ የሆነ ነገር ልጃችን ላይ እንደደረሰባት ይታወቀናል” ብላ እምባዋን ታግላ አስቀረችው እና ወይዘሮ ባደን እንደነገረችንኸውን ሜክሲኮ ውስጥ በየአመቱ ቱሪስቶች እና ሌሎች ሰዎች እንደሚታገቱ ነው፡፡”
“ምን አልሽኝ?” ብሎ ዊልያምስ ጠየቀ፡፡
“ቫለንቲና ባደን ናት፡፡ የዊሊ ባደን ሚስት ናት፡፡ የጠፉ ሰዎችን የሚያፈላልጉ የበጎ አድራጎት ድርጅት የከፈተች ናት።ከማንም በላይ ቻርሎቴን ለመፈለግ እገዛ አድርጋልናለች አለው ተከር ክላንሲ፡፡”
ይህንን ሲሰማ በድንገት አንድ ነገር ትዝ አለው ተከር፡፡ የሆነ ማታ ላይ ሁለት ታላላቅ ክለቦች እየተጫወቱ በነበሩበት የእራት ሰዓት ላይ ልጆቻቸውን እንዲያፈላልጉላቸው ሲማጸኑ እንደነበር አስታወሰ፡፡ ያኔ በዚህ የእረፍት ሰዓት ላይ ለሚተላለፉ ማንኛውም ነገሮች በጣም ውድ የሆነ ዋጋ ለቲቪ ጣቢያዎች ተከፍሎ ነው፡፡ ስለዚህም ይህንን የማስታውቂያ ክፍያ የከፈለችው
የዊሊ ባደን ሚስት ቫለንቲና ባደን መሆንዋን ተረዳ፡፡
“በፍፁም ወደዚያ እንድትሄድ ልፈቅድላት አይገባኝም ነበር፡፡” አለ ተከር ክላንሲ በቁጭት፡፡
“ምን መሰለህ ሚስ ባደን በእገታ የተወሰዱ ሰዎችን በማፈላለግና
ለአጋቾቹ የማስለቀቂያ ክፍያ እየከፈለች ታጋቾችን ከቤተሰቦቻቸው ጋር
እንደምታገኛኝ ነው የምናውቀው፡፡ ይሄው እንግዲህ ስለልጃችን ግን አንድም
ሰው እስካሁን ድረስ የደወለልን የለም፡፡ ይሄ ነገር ጥሩ ይሁን መጥፎ ሊገባን
አልቻለም” አለችው ሜሪ ክላንሲ፡፡
መጥፎ ነው እንጂ ብሎ አሰበ ዊልያምስ ደግሞም ይህቺ ቫለንቲና
ባደን ለቻርሎቴ
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
እናቴም የአባቴን አኳኋንና ለዘብተኛ አነጋገር በመከተል እንደ ወትሮዋ አልተቆጣችኝም
ከየውብነሽ ጋር መገናኘቴን ቀጠልኩ። አባቴ ስለ እኔ ያለውን አስተያየት እምብዛም እንዳልለወጠው አጣራሁ፡፡ እናቴም የእኔን ደጅ ደጅ ማየት ችላ እንዳለችውና እንኳን ከዚያች ከመናጢ ገረድ ጋር አብሮ ያልታየና ስማችንን ያላስጠፋው እንጂ የኋላ ኋላ መመለሱና ልብ መግዛቱ አይቀርም፡፡ እኔም ለጊዜው ንድድ ያለኝ ከገረድ ጋር መዋልና መልከስከሱ ነበር፣ ሌላ ሌላውስ ግድ የለም” ማለቷን የዋህ ተመስዩ ከየውብነሽ ሰማሁ፡፡
ያም ሆነ ይህ አንድ ቀን የእኔንና የየወዲያነሽን ጉዳይ ይፋ ለማውጣት ቆርጬ በምነሣበት ጊዜ ንትርክና ከባድ የቤተሰብ ውዝግብ እንደሚያጋጥመኝ በእርግጠኝነት ወለል ብሎ ታየኝ፡፡ ካለፈ አገደም ከሥራ መልስ በምሳ ሰዓት ወደ ወላጆቼ ቤት እየሄድኩ የሻከረ ሆዳቸውንና
አስተያየታቸውን ደረጃ በደረጃ ለመለወጥ ጥሩ ጥረት አደረግሁ፡፡ ተደጋጋሚ
ሙከራዩ ትንሽ የለውጥ ፍሬ አሳየ፡፡ በተለይም ከእናቴ ጋር የማደርገው ወሬና
ጨዋታ ሁሉ አስደሳች ቅርርብ ፈጠረ፡፡ ትንሽም ፊቷ በኀዘን የሚጠወልግና
የጠራራ ቅጠል የምትመስለው ደህና እደሪ ብዬ ለመሄድ በምነሣበት ጊዜ
ነበር።
አንድ ቀን ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ ከየውብነሽ ጋር መኝታ ቤቷ ውስጥ
ተቀምጠን ሞቅ ደመቅ ያለ መሬ ስናወራ «አንተ ጌታነህ» አለችኝ፡፡ ዐይኖቿ
የትዝታዋን ክብደት ለማስረዳት እየቦዙ ያነዩ ዱሮ ከዚያች ከገረዳችን ጋር
እንዲያ ስትሆን አባባ ያየኛል፣ ይሰማብኛል ብለሀ አልፈራህም?» ብላ
ታላቅነቴን በማክበር የኃፍረት ሣቅ ሣቀች። ምናልባት አንዳንድ ያልሰማሁትን
ነገር ታሰማኝ ይሆናል በማለት ልበ ግልጽ
ተመስዩ «እንዳልታይና እንዳይሰማብኝ ያልሠራሁትና ያልፈጸምኩት ዘድ አልነበረም። አንቺንም በጣም እፈራሽና እጠራጠርሽ ነበር» አልኩና አልጋዋ ላይ ጣል ያደረገችውን የሰነበተ ጋዜጣ ማገላበጥ ጀመርኩ። አንገቷን ወደ ቀኝ ሰበር አድርጋ የማገላብጠውን
ጋዜጣ እየተመለከተች ግን እኮ እያደር እንዳፈቀርካትና ከወዲያ ወዲህ
እየተመላለሰች በምትሠራበት ጊዜ ዐይኖችህ አብረዋት እንደሚዋትቱ ኣሳምሬ ዐውቅ ነበር፡፡ ከእንጀራ አቅም እንኳ ሌላ ሰው ሲያቀርብልህ ደስ አይልህም ነበር። እሷም የዋዛ ሾላካ አልነበረችም ! ኋላማ ልናባርራት አቅራቢያ
አረማመዷና አነጋገሯ፣ ጸጉር አሠራሯና አለባበሷ ሁሉ በጣም ተሻሽሉ ነበር፡፡
እኔ ከሁሉም ከሁሉም የማይረሳኝ ጠባይዋና ሲያዝዋት እሺ ባይነቷ ነው፡፡ ምን ይሆናል፣ ያ መሳይ መልክ ያለ ቦታው ቀረ፡፡ እሷ የተማረች ሆና ውጪ
ውጪውን ብናገኛት ኖሮ... እኔ ግን እስከ ዛሬ ድረስ ስለ እሷ አንዳችም ወሬ
ሰምቼ አላውቅም» ብላ አጠናቀቀች። የወሬ ከረጢቷን መፍታቷ ስለ ታወቀኝ
ለጊዜው ውስጣዊ ብስጭቴን ኣፍኜ ባናነሣው ይሻላል ያለፈው አልፏል እንጂ
ብሳሳትም ባልሳሳትም ከዚህ ቤት ስታባርሯት እርጉዝ ነበረች። ቀስ ብላችሁ
ሹክ ብትሉኝ ኖሮ እንደምንም አንዱ ጋ አስጠጋትና ትወልድ ነበር፡፡
ይኸንዬ እኔን አባብዬ” ሲል አንቺን ደግሞ ”እቴቴ' እቴ ሸንኮሬ 'እት -አይገኝ” ይልሽ ነበር» አልኳት፡፡ የአሁኑን የ'ወዲያነሽን ሕይወትና ኑሮ የማታውቀዋ እኅቴ ከሁሉም ከሁሉም በጣም የሚያሳዝነኝ» ብላ ቀጠለች፣
«ያነዪ አንተ ወደ ሥራ ወጣ ከማለትu እማዬ በአባባ ከዘራ ታፋ ታፋዋን'
ጀርባ ጀርባዋን ስትደበድባት ኩርምት ብላ ስትደበደብ የወረደባት የዱላ መዓት ነው፡፡ በመጨረሻ የተሰነዘረው ዱላ መኻል እናቷ ላይ በማረፉ ደሟ በጸጉሯ ውስጥ እየተንጀረጀረ ትከሻዋ ላይ ተንጠፈጠፈ፡፡ ነፍስ ይዟትም ይሁን ያሰበችውን እንጃ ከዘራውን ይዛ እለቅም በማለቷ እኔም እናቴን የተዳፈረችብኝና ግብግብ የምትገጥማት ስለመሰለኝ ሁለት ጊዜ በጥፊ አላስኳት።
«እሷ ግን ቀና ብላ አይታ፣ አንቺም? አንቺም? ጨክነሽ ትመቺኝ የውብነሽ? ኣይ ድኃ መሆን!” ያለችኝ ዛሬም አንጀት አንጀቴን ይበላኛል፡፡»
«እሷ ግን በጣም የተንገበገበችውና ያለቀሰችው ከቤት በመባረሯና
በመደብደቧ ሳይሆን እንተን ሳትሰናበትሀና ሳታይህ በመሔዷ ነበር። ከሥራ ስትመለስ መንገድ ላይ ጠብቃ እንዳታግባባሀና በሴት እንባዋ እንዳታታልልህ ከዚህ አካባቢ ያባረርናት በዘበኛ ነበር» ብላ ያን ዚያ ቀደም አሳርሮ
ያከሰለኝን መራራ ነገር እንደገና ጋተችኝ፡፡ የየወዲያነሽ መከራና እንግልት
ሁሉ ከተቀበረበት የትዝብት መቃብር ወጥቶ ነጭ ዓፅሙ ፊት ለፊቴ ተገተረ፡፡ ሌላ ተጨማሪ ነገር በመስማት አንጎሌን ማጥመልመል ስላልፈለግሁ
«ነገ አራት ሰዓት ላይ ዕጓለ ማውታ ስለምሔድ አብረን እንሂድ። ከዚያ በኋላ
ደግሞ ሌላ የማማክርሽ ጉዳይ ስላለ ቀደም ብለሽ ቀበና ድልድይ አጠገብ
ጠብቂኝ ብያት ወጣሁ፡፡
በማግሥቱ እሑድ እኅቴና ባለቤቴ ዕጓለ ማውታ እንዳይገናኙብኝ፡ የወዲያነሽን «እንግዳ ይዤ እመጣለሁና ተዘጋጅተሽ እንድትጠብቂኝ፡ ከዚያ በኋላ እንሔዳለን» ብያት ከቤት ወጣሁ፡፡ መኪና መግዛቴን መላ ቤተሰቦቼ ስላልሰሙ የውብነሽ የምትጠብቀኝ በእግር እንጂ በመኪና ይመጣል ብላ አልነበረም፡፡ ጥቂት ደቂቃዎች ዘግየት ብዬ ቀጠሮእችን ቦታ ስደርስ የውብነሽ ተረከዘ ሹል ጫማ አድርጋ ከጉልበቷ ትንሽ ከፍ ያለ ቀለመ ብዙ የፈረንጅ ቅድ ቀሚስና ነጭ ሸሚዝ ለብሳ ቡናማ ኮረጆዋን አንግታ ድልድዩ አካባቢ ስትጠብቀኝ አገኘኋት። መኪና አጠገቧ ደርሳ በመቆሟ ባለ መኪናውም እኔ መሆኔን ባለማወቋ ፊቷን በቁጣ ከሰከሰች፡፡ እንዳንድ የጎዳና ሴቶች
ለመግደርደር ሲሉ የሚያሳዩት አኳኋን ትዝ አለኝና የየውብነሽ አድራጎት አሣቀኝ፡፡ ወዲያው ወጣ ብዬ ወደ እርሷ ተራመድኩ። ከመኪና ወጥቶ ወደ
እርሷ የሚራመደው ሰው ታላቅ ወንድሟ መሆኑን ስታውቅ የአድናቆት ሣቅ
ሣቀች፡፡
«መኪና ገዛሁ እንዳትለኝ አለችኝ፡፡ «አዎ ገዛሁ እኔም ወጉ ይድረሰኝ ብዬ ገና ሁለተኛ ወሯን መያዟ ነው» አልኩና እየተሣሣቅን ተጨባበጥን፡፡
«የውቤ፣ ይቺንም ታድያ ቤተሰብ እንዳይሰማ፣ እንድ ቀን ሁሉንም ነገር
አጠራቅሜ አቀርበዋለሁ፡፡» «ሌላ ደግሞ ምን የሚነገር አለህ?» ብላ አየችኝ፡፡
«እኔ ገና ብዙ የሚነገር ነገር አለኝ» ብያት መኪና ውስጥ ገብተን መንገድ
ቀጠልን፡፡ በአሥራ አምስት ደቂቃ ውስጥ አግድመት ቁልቁለቱን ጨርሰን
ሕፃናት ማሳደጊያ ድርጅት ደረስን፡፡ ለምለሙ መስክ ላይ ትላልቅና ትናንሽ
ልጆች እንደ ጥሬ ፈስሰው ልዩ ልዩ ጨዋታዎች ይጫወታሉ። ከትንንሾቹ
ልጆች መኻል አንድ የግራ ዐይኑ የጠፋችና በዐይን አር የተጨማለቀች
ሰማያዊ ቁምጣና ትከሻው ላይ የተጣፈች እሷኑ መሰል ኮት የለበሰ ልጅ
በሩጫ መጥቶ ጨበጠኝ፡፡ የጋሻዬነህ ጓደኛ ነው:: ከኪሴ ከረሜላ ኣውጥቼ ሰጠሁት። የውብነሽ በድንጋጤ አፏን ከፍታ «ምነው ምን ሆነ? ዐይኑን ምን ነካው? ደኅና አልነበረም እንዴ !?» አለችኝ፡፡
«ይህ እኮ ያ ከዚህ ቀደም ያየሽው የጓደኛዬ ልጅ አይደለም፣ ይኸ ጓደኛዉ ነው:: አሁን ሮጦ ይጠራልናል» አልኩና የደነገጠውን ስሜቷን በደስታ
አደስኩት:: ከረሜላውን ልጦ ጎረሰና ተለይቶን ሔደ። እምብዛም ሳይቆይ
ጋሻነህን ይዞት መጣ፡፡ አንዲት በጣም የጠወለገች ነጭ አበባ ይዞ ነበረ።
እጆቼን ከብብቱ ሥር አስገብቼ በማንሣት ጉንጮቹን ስስም ሁሉም ነገር
ጥሉኝ ጠፋ፡፡ የውብነሽ ቀበል ብላ አገላብጣ ሳመችው:: ቀድሞውንም የሙት ልጅ ነው ብዬ ነግሬያት ስለ ነበር በርኅራኄ ተመለከተችው:: አላስችል ስላላት ዕንባ ተናነቃት። መሐረቧን አውጥቃ ዐይኖቿን አበሰች። «ለመሆኑ ያባቱ ዘመዶች እየመጡ ይጠይቁታል እንዴ?» አለችኝ፡፡ ልጅ ያለው መሆኑን የሰማ አንድም
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
እናቴም የአባቴን አኳኋንና ለዘብተኛ አነጋገር በመከተል እንደ ወትሮዋ አልተቆጣችኝም
ከየውብነሽ ጋር መገናኘቴን ቀጠልኩ። አባቴ ስለ እኔ ያለውን አስተያየት እምብዛም እንዳልለወጠው አጣራሁ፡፡ እናቴም የእኔን ደጅ ደጅ ማየት ችላ እንዳለችውና እንኳን ከዚያች ከመናጢ ገረድ ጋር አብሮ ያልታየና ስማችንን ያላስጠፋው እንጂ የኋላ ኋላ መመለሱና ልብ መግዛቱ አይቀርም፡፡ እኔም ለጊዜው ንድድ ያለኝ ከገረድ ጋር መዋልና መልከስከሱ ነበር፣ ሌላ ሌላውስ ግድ የለም” ማለቷን የዋህ ተመስዩ ከየውብነሽ ሰማሁ፡፡
ያም ሆነ ይህ አንድ ቀን የእኔንና የየወዲያነሽን ጉዳይ ይፋ ለማውጣት ቆርጬ በምነሣበት ጊዜ ንትርክና ከባድ የቤተሰብ ውዝግብ እንደሚያጋጥመኝ በእርግጠኝነት ወለል ብሎ ታየኝ፡፡ ካለፈ አገደም ከሥራ መልስ በምሳ ሰዓት ወደ ወላጆቼ ቤት እየሄድኩ የሻከረ ሆዳቸውንና
አስተያየታቸውን ደረጃ በደረጃ ለመለወጥ ጥሩ ጥረት አደረግሁ፡፡ ተደጋጋሚ
ሙከራዩ ትንሽ የለውጥ ፍሬ አሳየ፡፡ በተለይም ከእናቴ ጋር የማደርገው ወሬና
ጨዋታ ሁሉ አስደሳች ቅርርብ ፈጠረ፡፡ ትንሽም ፊቷ በኀዘን የሚጠወልግና
የጠራራ ቅጠል የምትመስለው ደህና እደሪ ብዬ ለመሄድ በምነሣበት ጊዜ
ነበር።
አንድ ቀን ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ ከየውብነሽ ጋር መኝታ ቤቷ ውስጥ
ተቀምጠን ሞቅ ደመቅ ያለ መሬ ስናወራ «አንተ ጌታነህ» አለችኝ፡፡ ዐይኖቿ
የትዝታዋን ክብደት ለማስረዳት እየቦዙ ያነዩ ዱሮ ከዚያች ከገረዳችን ጋር
እንዲያ ስትሆን አባባ ያየኛል፣ ይሰማብኛል ብለሀ አልፈራህም?» ብላ
ታላቅነቴን በማክበር የኃፍረት ሣቅ ሣቀች። ምናልባት አንዳንድ ያልሰማሁትን
ነገር ታሰማኝ ይሆናል በማለት ልበ ግልጽ
ተመስዩ «እንዳልታይና እንዳይሰማብኝ ያልሠራሁትና ያልፈጸምኩት ዘድ አልነበረም። አንቺንም በጣም እፈራሽና እጠራጠርሽ ነበር» አልኩና አልጋዋ ላይ ጣል ያደረገችውን የሰነበተ ጋዜጣ ማገላበጥ ጀመርኩ። አንገቷን ወደ ቀኝ ሰበር አድርጋ የማገላብጠውን
ጋዜጣ እየተመለከተች ግን እኮ እያደር እንዳፈቀርካትና ከወዲያ ወዲህ
እየተመላለሰች በምትሠራበት ጊዜ ዐይኖችህ አብረዋት እንደሚዋትቱ ኣሳምሬ ዐውቅ ነበር፡፡ ከእንጀራ አቅም እንኳ ሌላ ሰው ሲያቀርብልህ ደስ አይልህም ነበር። እሷም የዋዛ ሾላካ አልነበረችም ! ኋላማ ልናባርራት አቅራቢያ
አረማመዷና አነጋገሯ፣ ጸጉር አሠራሯና አለባበሷ ሁሉ በጣም ተሻሽሉ ነበር፡፡
እኔ ከሁሉም ከሁሉም የማይረሳኝ ጠባይዋና ሲያዝዋት እሺ ባይነቷ ነው፡፡ ምን ይሆናል፣ ያ መሳይ መልክ ያለ ቦታው ቀረ፡፡ እሷ የተማረች ሆና ውጪ
ውጪውን ብናገኛት ኖሮ... እኔ ግን እስከ ዛሬ ድረስ ስለ እሷ አንዳችም ወሬ
ሰምቼ አላውቅም» ብላ አጠናቀቀች። የወሬ ከረጢቷን መፍታቷ ስለ ታወቀኝ
ለጊዜው ውስጣዊ ብስጭቴን ኣፍኜ ባናነሣው ይሻላል ያለፈው አልፏል እንጂ
ብሳሳትም ባልሳሳትም ከዚህ ቤት ስታባርሯት እርጉዝ ነበረች። ቀስ ብላችሁ
ሹክ ብትሉኝ ኖሮ እንደምንም አንዱ ጋ አስጠጋትና ትወልድ ነበር፡፡
ይኸንዬ እኔን አባብዬ” ሲል አንቺን ደግሞ ”እቴቴ' እቴ ሸንኮሬ 'እት -አይገኝ” ይልሽ ነበር» አልኳት፡፡ የአሁኑን የ'ወዲያነሽን ሕይወትና ኑሮ የማታውቀዋ እኅቴ ከሁሉም ከሁሉም በጣም የሚያሳዝነኝ» ብላ ቀጠለች፣
«ያነዪ አንተ ወደ ሥራ ወጣ ከማለትu እማዬ በአባባ ከዘራ ታፋ ታፋዋን'
ጀርባ ጀርባዋን ስትደበድባት ኩርምት ብላ ስትደበደብ የወረደባት የዱላ መዓት ነው፡፡ በመጨረሻ የተሰነዘረው ዱላ መኻል እናቷ ላይ በማረፉ ደሟ በጸጉሯ ውስጥ እየተንጀረጀረ ትከሻዋ ላይ ተንጠፈጠፈ፡፡ ነፍስ ይዟትም ይሁን ያሰበችውን እንጃ ከዘራውን ይዛ እለቅም በማለቷ እኔም እናቴን የተዳፈረችብኝና ግብግብ የምትገጥማት ስለመሰለኝ ሁለት ጊዜ በጥፊ አላስኳት።
«እሷ ግን ቀና ብላ አይታ፣ አንቺም? አንቺም? ጨክነሽ ትመቺኝ የውብነሽ? ኣይ ድኃ መሆን!” ያለችኝ ዛሬም አንጀት አንጀቴን ይበላኛል፡፡»
«እሷ ግን በጣም የተንገበገበችውና ያለቀሰችው ከቤት በመባረሯና
በመደብደቧ ሳይሆን እንተን ሳትሰናበትሀና ሳታይህ በመሔዷ ነበር። ከሥራ ስትመለስ መንገድ ላይ ጠብቃ እንዳታግባባሀና በሴት እንባዋ እንዳታታልልህ ከዚህ አካባቢ ያባረርናት በዘበኛ ነበር» ብላ ያን ዚያ ቀደም አሳርሮ
ያከሰለኝን መራራ ነገር እንደገና ጋተችኝ፡፡ የየወዲያነሽ መከራና እንግልት
ሁሉ ከተቀበረበት የትዝብት መቃብር ወጥቶ ነጭ ዓፅሙ ፊት ለፊቴ ተገተረ፡፡ ሌላ ተጨማሪ ነገር በመስማት አንጎሌን ማጥመልመል ስላልፈለግሁ
«ነገ አራት ሰዓት ላይ ዕጓለ ማውታ ስለምሔድ አብረን እንሂድ። ከዚያ በኋላ
ደግሞ ሌላ የማማክርሽ ጉዳይ ስላለ ቀደም ብለሽ ቀበና ድልድይ አጠገብ
ጠብቂኝ ብያት ወጣሁ፡፡
በማግሥቱ እሑድ እኅቴና ባለቤቴ ዕጓለ ማውታ እንዳይገናኙብኝ፡ የወዲያነሽን «እንግዳ ይዤ እመጣለሁና ተዘጋጅተሽ እንድትጠብቂኝ፡ ከዚያ በኋላ እንሔዳለን» ብያት ከቤት ወጣሁ፡፡ መኪና መግዛቴን መላ ቤተሰቦቼ ስላልሰሙ የውብነሽ የምትጠብቀኝ በእግር እንጂ በመኪና ይመጣል ብላ አልነበረም፡፡ ጥቂት ደቂቃዎች ዘግየት ብዬ ቀጠሮእችን ቦታ ስደርስ የውብነሽ ተረከዘ ሹል ጫማ አድርጋ ከጉልበቷ ትንሽ ከፍ ያለ ቀለመ ብዙ የፈረንጅ ቅድ ቀሚስና ነጭ ሸሚዝ ለብሳ ቡናማ ኮረጆዋን አንግታ ድልድዩ አካባቢ ስትጠብቀኝ አገኘኋት። መኪና አጠገቧ ደርሳ በመቆሟ ባለ መኪናውም እኔ መሆኔን ባለማወቋ ፊቷን በቁጣ ከሰከሰች፡፡ እንዳንድ የጎዳና ሴቶች
ለመግደርደር ሲሉ የሚያሳዩት አኳኋን ትዝ አለኝና የየውብነሽ አድራጎት አሣቀኝ፡፡ ወዲያው ወጣ ብዬ ወደ እርሷ ተራመድኩ። ከመኪና ወጥቶ ወደ
እርሷ የሚራመደው ሰው ታላቅ ወንድሟ መሆኑን ስታውቅ የአድናቆት ሣቅ
ሣቀች፡፡
«መኪና ገዛሁ እንዳትለኝ አለችኝ፡፡ «አዎ ገዛሁ እኔም ወጉ ይድረሰኝ ብዬ ገና ሁለተኛ ወሯን መያዟ ነው» አልኩና እየተሣሣቅን ተጨባበጥን፡፡
«የውቤ፣ ይቺንም ታድያ ቤተሰብ እንዳይሰማ፣ እንድ ቀን ሁሉንም ነገር
አጠራቅሜ አቀርበዋለሁ፡፡» «ሌላ ደግሞ ምን የሚነገር አለህ?» ብላ አየችኝ፡፡
«እኔ ገና ብዙ የሚነገር ነገር አለኝ» ብያት መኪና ውስጥ ገብተን መንገድ
ቀጠልን፡፡ በአሥራ አምስት ደቂቃ ውስጥ አግድመት ቁልቁለቱን ጨርሰን
ሕፃናት ማሳደጊያ ድርጅት ደረስን፡፡ ለምለሙ መስክ ላይ ትላልቅና ትናንሽ
ልጆች እንደ ጥሬ ፈስሰው ልዩ ልዩ ጨዋታዎች ይጫወታሉ። ከትንንሾቹ
ልጆች መኻል አንድ የግራ ዐይኑ የጠፋችና በዐይን አር የተጨማለቀች
ሰማያዊ ቁምጣና ትከሻው ላይ የተጣፈች እሷኑ መሰል ኮት የለበሰ ልጅ
በሩጫ መጥቶ ጨበጠኝ፡፡ የጋሻዬነህ ጓደኛ ነው:: ከኪሴ ከረሜላ ኣውጥቼ ሰጠሁት። የውብነሽ በድንጋጤ አፏን ከፍታ «ምነው ምን ሆነ? ዐይኑን ምን ነካው? ደኅና አልነበረም እንዴ !?» አለችኝ፡፡
«ይህ እኮ ያ ከዚህ ቀደም ያየሽው የጓደኛዬ ልጅ አይደለም፣ ይኸ ጓደኛዉ ነው:: አሁን ሮጦ ይጠራልናል» አልኩና የደነገጠውን ስሜቷን በደስታ
አደስኩት:: ከረሜላውን ልጦ ጎረሰና ተለይቶን ሔደ። እምብዛም ሳይቆይ
ጋሻነህን ይዞት መጣ፡፡ አንዲት በጣም የጠወለገች ነጭ አበባ ይዞ ነበረ።
እጆቼን ከብብቱ ሥር አስገብቼ በማንሣት ጉንጮቹን ስስም ሁሉም ነገር
ጥሉኝ ጠፋ፡፡ የውብነሽ ቀበል ብላ አገላብጣ ሳመችው:: ቀድሞውንም የሙት ልጅ ነው ብዬ ነግሬያት ስለ ነበር በርኅራኄ ተመለከተችው:: አላስችል ስላላት ዕንባ ተናነቃት። መሐረቧን አውጥቃ ዐይኖቿን አበሰች። «ለመሆኑ ያባቱ ዘመዶች እየመጡ ይጠይቁታል እንዴ?» አለችኝ፡፡ ልጅ ያለው መሆኑን የሰማ አንድም
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....“አንተን ለማግኘት ስል ያልገባሁበት ዋሻ፣ያልፈነቀልኩት ድንጋይ አልነበረም፡፡ ዳሩ ምን ያደርጋል?እንደ ሌሎቹ በቀላሉ የምትገኝ ሰው አልሆንክም፡፡ የተፈፀመብኝ ጥቃት ከባድና ጊዜ የማይሰጥ በመሆኑ ልቤ እያወቀው፣ ልቤ እየጠረጠረ ከማይረቡ ምናምንቴዎች ጋር ውለታ ውስጥ ገባሁ። እንዳንተ ስማቸው ያልገነነ፣ ቱስ ቱስ ማለት የጀመሩ ሾላኮች በመሆናቸው ብዙ ገንዘብ ካስወጡኝ በኋላ አንዳች ቁም ነገር ሳይፈፅሙ ሸሽተውኛል ተደብቀውኛል። በዚህ ምክንያት ተበሳጭቼ ቀን ከለሊት አፈላልጌ መልዕክተኛ ልኬብህ በብዙ ድካም ሳገኝህ የተሰማኝ ደስታ
ወደር አልነበረውም፡፡ እንደዚህ በግንባር ልታነጋግረኝ መወሰንህን ስሰማ ደግሞ ደስታዬ እጅግ ከፍተኛ ሆኖ ነበር፡፡ጎንቻ የልቤን የሚፈፅምልኝ ካንተ ወዲያ ሊኖር እንደማይችል ቀድሞውኑ የታወቀ ነው” በማለት አንጀቱን ከበላው በኋላ ዝርዝሩን ይተርክለት ጀመር፡፡
“የሹመት ጓደኛዬ ነው። ባላባት ጃኖ ይባላል። በባህላችን በወልገራ የጋብቻ ደንብ እህቴን ስድርለት እሱ ደግሞ በለውጡ እህቱን ድሮልኝ ነበር፡፡ እኔ የሱን እህት በወግ በማዕረግ አክብሬ ነበር የያዝኳት። እሱ ግን እህቴን
እንደ ባሪያ እየረገጠ በደል ሲያበዛባት፣ ሲያሰቃያት ተማረረች። በመጨረሻም የሱ ሚስት የኔ እህት በደሉ አንገሽገሻትና በድንገት ጥላው ጠፋች። ከዚያ በኋላ ሰላም ይነሳኝ፣ ይበጠብጠኝ ጀመር፡፡ እኔ ጥለሽው ጥፊ፣ እኔ ትዳርሽን አፍርሺ ብዬ እንደመከርኳት ሁሉ ሚስቴን መልስልኝ ያለበለዚያ ዝምድናችን ይበላሻል እያለ ያስፈራራኝ ጀመር።መልዕክተኛ በተደጋጋሚ ላከብኝ፡፡ በግንባር ተገናኝተን ተነጋገርን፡፡ ጭቅጭቁ ሲብስብኝ መቆሚያ መቀመጫ ሲያሳጣኝ እህቴን ካለችበት ቦታ አስጠርቼ ላግባባት ሞከርኩ፡፡ ወደ ትዳሯ እንድትመለስ እግሯ ላይ ወድቄ ለመንኳት ወደዚያ የስቃይ ኑሮ ተመለሺ የምትለኝ ከሆነ ህይወቴን አጠፋለሁ ካንተ
ምንም የምፈልገው ነገር የለም በነፃነቴ ውስጥ ግን አትግባ ብላ እያለቀሰች በምሬት መለሰችልኝ፡፡ በጣም አስፈራራችኝ፡፡ ከፍላጎቷ ውጭ እንድትመለስ ባስገድዳት ህይወቷን ታጠፋለች የሚል ፍርሃት አደረብኝ፡፡ያደረኩትን ጥረትና የሰጠችኝን መልስ በዝርዝር አጫወትኩት፡፡ በወዳጅነታችን ውስጥ በፍፁም ቅያሜ እንዳይኖር ለመንኩት። እህቴ ብትሆንም በሱ ሚስት ህይወት ላይ ማዘዝ እንደማልችል አስረዳሁት፡፡ ምን ዋጋ አለው? ድንጋይ ራስ ነው! በፍፁም ማመዛዘን የማይችል ድንጋይ ራስ!! ችግሬን ሊረዳ አልቻለም፡፡ ያንን ሁሉ ልፋቴንና ጥረቴን ዋጋ አሳጥቶት ቂም ቋጠረብኝ፡፡ የኔን ትዳር ለመበጥበጥ፣የኔን ትዳር ለማፍረስ እንቅልፍ አጣ። ለእህቱ በተደጋጋሚ መልዕክተኛ ላከባት፡፡ የሱ እህት ብቸኛ አድርጋኝ ጥላኝ ስትጠፋ፣ ትዳሬን አፍርሳ ስትሄድ አንቺ ግን የሱን ጎጆ ታሞቂያለሽ፡፡ የወንድምሽ በደል የማይሰማሽ ለወንድምሽ የማትቆረቆሪ አህያ
ነሽ።እህቱ ጥላኝ እንደጠፋች ጥለሽው ካልጠፋሽ ዳግመኛ እህት አለችኝ ብዬ አላወራም እያለ ነዘነዛትና ፍቅራችን እንዲደፈርስ ትዳራችን እንዲ ፈራርስ አደረገ፡፡ ከዚያም የምወዳት ሚስቴ ሳልበድላት ምንም ሳላስቀይማት በድንገት.. በድንገት ጥላኝ ጠፋች”
የስድስት ሚስቶች ባል የሆነው ባላባት ቱሬ የሚያወራው ተረት አፉን እንኳን ወለም አላደረገውም ነበር፡፡ የደረሰበት በደል ከፍተኛ መሆኑን ጎንቻ እንዲረዳለትና ቁጭት እንዲያድርበት ለማድረግ ሰሞኑን ሲያጠና የከረመውን ልብ ወለድ እንደ እውነተኛ ታሪክ ሲያወራለት እዚያ የነበሩት በሙሉ አፋቸውን ከፍተው እንደ አዲስ ያዳምጡት ነበር፡፡ በተገላቢጦሽ በጃኖ ላይ የደረሰውን በደል በራሱ ላይ እንደደረስ አድርጎ ጃኖን በዳይ ራሱን ተበዳይ አድርጎ ፊቱን በእንባ ቀረሽ ንዴት ቁጥር ፈታ እያ
ደረገ ማስረዳቱን ቀጠለ።
“ስው ቢበድለኝም ጓደኛዬ ቢከዳኝም እግዚአብሔር አልከዳኝምና በደሌን አይቶ ካለኝ፡፡ ሀዘኔን አይቶ ፈጣሪ አስደሰተኝ፡ እምባዬን አበሰልኝ፡፡ አለላ የመሰለች ልጁን በቦሩ ጃዊ ባላባትነት ውስጥ ጭቃሹም የሆነው አቶ ገመቹ ዳረልኝ፡፡ በዚህ ጊዜ የበለጠ ቅናት አቃጠለው:: እህቱ ጥላኝ እንድትጠፋ፣ ረግጣኝ እንድትሄድ ካደረገ በኋላ ለእህቱ ተቆርቋሪ መስሎ እህቴ የደከመችበትን ንብረት፣ እህቴ ጎንበስ ቀና ብላ ያቆመችውን ጎጆ
ማንም መንገደኛ ገብቶ አይንደላቀቅበትም ሲል ዛተብኝ፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ የሱ እህት ይዛልኝ የመጣችው ሰባራ ሳንቲም አልነበረም፡፡ በሞላ በተትረፈረፈ ቤት ገብታ መሞላቀቁ አጥግቧት ጠፋች እንጂ እሷ ያመጣችው አንድም ነገር አልነበረም፡፡ ከኔ ምን ጎድሎ? ምን ጠፍቶ? እሱ ግን ለእህቱ የተቆረቆረ በማስመሰል ለካንስ ሊያጠቃኝ አስቦ ኖሯል፡፡ የሱ እህት ለዚችኛዋ ሚስቴ ገረዷ የእግሯ እጣቢ እንኳ አትሆንም ነበር፡፡ ያጠቃኛል የዚያን አይነት አስከፊ በደል ያደርስብኛል ብዬ በፍፁም ባልጠበኩት ሰዓት ባላባት ጃኖ አጠቃኝ፡፡ ተዘጋጅቶ ዘመድ አዝማዱን አሰባስቦ
ጦሩን ጭኖ በሌሊት ከበበኝ፡ ሚስቴን…. ሚስቴን... በሃይል... ሳልዘጋጅበት.ሳላስበው ...ነጥቆኝ ሄደ” እንባ እየተናነቀው አስረዳ፡፡
እውነተኛው ታሪክ ግን ባላባት ቱሬ እንደሚያወራው ሳይሆን የምስኪኑ
ገበሬ የጃኖን እዚህ ቀረሽ የማትባል እጮኛውን ባላባት ቱሬ በሀብትና በሥልጣኑ ተመክቶ፣ ወላጆቿን በከብትና በገንዘብ ገበራ ዐይናቸውን አሳውሮ የአሥራ ስምንት ዓመቷን ልጃገረድ ሌቱናን ጠልፎ ከወሰዳት በኋላ በባላባትነት ግዛቱ ውስጥ ድል ባለ ሠርግ ያገባት መሆኑ ነው ሀቁ። ገንዘብና ሀብት ባይኖረውም ዛሬ በቱሬ አንደበት የባላባትነት ማዕረግ የተሰጠው ጃኖ የጉልበትና የወኔ ደሃ አልነበረም። እንደ ነፍሱ የሚወዳት እጮኛውን ጉብሏን ሌቱናን ቱሬ በገንዘብ ኃይል አፍኗት ሲሄድ፣ የድንግልነት ክብሯን ሲወስድ እየታየው ገላው እስከሚቃጠል ድረስ በንዴት
ቢጋይም፣ እልህ ቢተናነቀውም አንድ ቀን የሱ አንጡራ ሀብት መሆኗን እንደሚያረጋግጥና እጮኛውን በነጠቅው በቱሬ ላይ አደጋ ጥሎ እንደሚወስዳት ጥርጥር አልነበረውም፡፡ ቱሬ የጓጓው ያንን የቀዘቀዘ ገላውን የም
ታሞቅለትን፣ ብዙ ንብረት ያወጣባትን ቆንጆዋን ሌቱናን ጎንቻ እንዲያስመልስለት ነው። ጎንቻ ተራ ውንብድና አይፈፅምም የሚለውን ዜና በመስማቱ የሌላ ታሪክ እየፈጠረ ገበሬውን ባላባት አድርጎ በመሾም ለመተረክ የተገደደውም ከዚህ እውነታ በመነሳት ነው፡፡
በእርግጥም ጎንቻ ትንሽ ስራ፣ ትልቅ ስራ በሚል የወንጀል አይነትን የሚያማርጥ ቢሆንም ጥሩ ገንዘብ እስካስታቀፉት ድረስ የህፃን ጉሮሮ ከመቀንጠስ ወደ ኋላ የማይል ጨካኝ መሆኑን ቢያውቀው ኖሮ ይሄንን ያክል
መጨነቅ ባላስፈለገው ነበር፡፡
“የፈለከውን ያክል ብር ብትስጠኝ አንድ ተራ ገበሬ ለመግደል አገር
አቋርጬ አልሄድም” ይለኛል ብሎ ስለፈራ እንባውን እየጠራረገ እጅግ ከፍተኛ የሆነ በደል የተፈፀመበት ሰው መስሎ እየተንቀጠቀጠ ኑዛዜውን ቀጠለ፡፡
“ምንም እንኳ እድሜዬ ቢገፋ፣ አቅሜ ቢዳከም አባቴ የወለደኝ ወንድ ጀግና ነበርኩ፡፡ ጃኖ ግን ወንድነቴን ጀግንነቴን ሰልቦታል። ልቤን በሀዘን አኮስምኖታል። ዝናዬን አጉድፎታል። ተኝቶ ሚስቱን ያስነጠቀ ባላባት አሰኝቶ በባላባትነት ግዛቴ ውስጥ አዋርዶኛል። ህዝቡ እንዲንቀኝ፣ እንዳይታዘዘኝ አድርጓል፡፡ ጉልበት በነበረኝ ጊዜ አባርሬ ይዣለሁ። ገድዬ ፎክሬአለሁ።ጃኖ ግን አቅሜ ቢደክም፣ዕድሜ ቢጫጫነኝ ንቆኝ የለበስኩትን ሱሪ አስወልቆ ቀሚስ አልብሶኛል። ጉልበት የእግዚአብሔር መሆኑን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....“አንተን ለማግኘት ስል ያልገባሁበት ዋሻ፣ያልፈነቀልኩት ድንጋይ አልነበረም፡፡ ዳሩ ምን ያደርጋል?እንደ ሌሎቹ በቀላሉ የምትገኝ ሰው አልሆንክም፡፡ የተፈፀመብኝ ጥቃት ከባድና ጊዜ የማይሰጥ በመሆኑ ልቤ እያወቀው፣ ልቤ እየጠረጠረ ከማይረቡ ምናምንቴዎች ጋር ውለታ ውስጥ ገባሁ። እንዳንተ ስማቸው ያልገነነ፣ ቱስ ቱስ ማለት የጀመሩ ሾላኮች በመሆናቸው ብዙ ገንዘብ ካስወጡኝ በኋላ አንዳች ቁም ነገር ሳይፈፅሙ ሸሽተውኛል ተደብቀውኛል። በዚህ ምክንያት ተበሳጭቼ ቀን ከለሊት አፈላልጌ መልዕክተኛ ልኬብህ በብዙ ድካም ሳገኝህ የተሰማኝ ደስታ
ወደር አልነበረውም፡፡ እንደዚህ በግንባር ልታነጋግረኝ መወሰንህን ስሰማ ደግሞ ደስታዬ እጅግ ከፍተኛ ሆኖ ነበር፡፡ጎንቻ የልቤን የሚፈፅምልኝ ካንተ ወዲያ ሊኖር እንደማይችል ቀድሞውኑ የታወቀ ነው” በማለት አንጀቱን ከበላው በኋላ ዝርዝሩን ይተርክለት ጀመር፡፡
“የሹመት ጓደኛዬ ነው። ባላባት ጃኖ ይባላል። በባህላችን በወልገራ የጋብቻ ደንብ እህቴን ስድርለት እሱ ደግሞ በለውጡ እህቱን ድሮልኝ ነበር፡፡ እኔ የሱን እህት በወግ በማዕረግ አክብሬ ነበር የያዝኳት። እሱ ግን እህቴን
እንደ ባሪያ እየረገጠ በደል ሲያበዛባት፣ ሲያሰቃያት ተማረረች። በመጨረሻም የሱ ሚስት የኔ እህት በደሉ አንገሽገሻትና በድንገት ጥላው ጠፋች። ከዚያ በኋላ ሰላም ይነሳኝ፣ ይበጠብጠኝ ጀመር፡፡ እኔ ጥለሽው ጥፊ፣ እኔ ትዳርሽን አፍርሺ ብዬ እንደመከርኳት ሁሉ ሚስቴን መልስልኝ ያለበለዚያ ዝምድናችን ይበላሻል እያለ ያስፈራራኝ ጀመር።መልዕክተኛ በተደጋጋሚ ላከብኝ፡፡ በግንባር ተገናኝተን ተነጋገርን፡፡ ጭቅጭቁ ሲብስብኝ መቆሚያ መቀመጫ ሲያሳጣኝ እህቴን ካለችበት ቦታ አስጠርቼ ላግባባት ሞከርኩ፡፡ ወደ ትዳሯ እንድትመለስ እግሯ ላይ ወድቄ ለመንኳት ወደዚያ የስቃይ ኑሮ ተመለሺ የምትለኝ ከሆነ ህይወቴን አጠፋለሁ ካንተ
ምንም የምፈልገው ነገር የለም በነፃነቴ ውስጥ ግን አትግባ ብላ እያለቀሰች በምሬት መለሰችልኝ፡፡ በጣም አስፈራራችኝ፡፡ ከፍላጎቷ ውጭ እንድትመለስ ባስገድዳት ህይወቷን ታጠፋለች የሚል ፍርሃት አደረብኝ፡፡ያደረኩትን ጥረትና የሰጠችኝን መልስ በዝርዝር አጫወትኩት፡፡ በወዳጅነታችን ውስጥ በፍፁም ቅያሜ እንዳይኖር ለመንኩት። እህቴ ብትሆንም በሱ ሚስት ህይወት ላይ ማዘዝ እንደማልችል አስረዳሁት፡፡ ምን ዋጋ አለው? ድንጋይ ራስ ነው! በፍፁም ማመዛዘን የማይችል ድንጋይ ራስ!! ችግሬን ሊረዳ አልቻለም፡፡ ያንን ሁሉ ልፋቴንና ጥረቴን ዋጋ አሳጥቶት ቂም ቋጠረብኝ፡፡ የኔን ትዳር ለመበጥበጥ፣የኔን ትዳር ለማፍረስ እንቅልፍ አጣ። ለእህቱ በተደጋጋሚ መልዕክተኛ ላከባት፡፡ የሱ እህት ብቸኛ አድርጋኝ ጥላኝ ስትጠፋ፣ ትዳሬን አፍርሳ ስትሄድ አንቺ ግን የሱን ጎጆ ታሞቂያለሽ፡፡ የወንድምሽ በደል የማይሰማሽ ለወንድምሽ የማትቆረቆሪ አህያ
ነሽ።እህቱ ጥላኝ እንደጠፋች ጥለሽው ካልጠፋሽ ዳግመኛ እህት አለችኝ ብዬ አላወራም እያለ ነዘነዛትና ፍቅራችን እንዲደፈርስ ትዳራችን እንዲ ፈራርስ አደረገ፡፡ ከዚያም የምወዳት ሚስቴ ሳልበድላት ምንም ሳላስቀይማት በድንገት.. በድንገት ጥላኝ ጠፋች”
የስድስት ሚስቶች ባል የሆነው ባላባት ቱሬ የሚያወራው ተረት አፉን እንኳን ወለም አላደረገውም ነበር፡፡ የደረሰበት በደል ከፍተኛ መሆኑን ጎንቻ እንዲረዳለትና ቁጭት እንዲያድርበት ለማድረግ ሰሞኑን ሲያጠና የከረመውን ልብ ወለድ እንደ እውነተኛ ታሪክ ሲያወራለት እዚያ የነበሩት በሙሉ አፋቸውን ከፍተው እንደ አዲስ ያዳምጡት ነበር፡፡ በተገላቢጦሽ በጃኖ ላይ የደረሰውን በደል በራሱ ላይ እንደደረስ አድርጎ ጃኖን በዳይ ራሱን ተበዳይ አድርጎ ፊቱን በእንባ ቀረሽ ንዴት ቁጥር ፈታ እያ
ደረገ ማስረዳቱን ቀጠለ።
“ስው ቢበድለኝም ጓደኛዬ ቢከዳኝም እግዚአብሔር አልከዳኝምና በደሌን አይቶ ካለኝ፡፡ ሀዘኔን አይቶ ፈጣሪ አስደሰተኝ፡ እምባዬን አበሰልኝ፡፡ አለላ የመሰለች ልጁን በቦሩ ጃዊ ባላባትነት ውስጥ ጭቃሹም የሆነው አቶ ገመቹ ዳረልኝ፡፡ በዚህ ጊዜ የበለጠ ቅናት አቃጠለው:: እህቱ ጥላኝ እንድትጠፋ፣ ረግጣኝ እንድትሄድ ካደረገ በኋላ ለእህቱ ተቆርቋሪ መስሎ እህቴ የደከመችበትን ንብረት፣ እህቴ ጎንበስ ቀና ብላ ያቆመችውን ጎጆ
ማንም መንገደኛ ገብቶ አይንደላቀቅበትም ሲል ዛተብኝ፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ የሱ እህት ይዛልኝ የመጣችው ሰባራ ሳንቲም አልነበረም፡፡ በሞላ በተትረፈረፈ ቤት ገብታ መሞላቀቁ አጥግቧት ጠፋች እንጂ እሷ ያመጣችው አንድም ነገር አልነበረም፡፡ ከኔ ምን ጎድሎ? ምን ጠፍቶ? እሱ ግን ለእህቱ የተቆረቆረ በማስመሰል ለካንስ ሊያጠቃኝ አስቦ ኖሯል፡፡ የሱ እህት ለዚችኛዋ ሚስቴ ገረዷ የእግሯ እጣቢ እንኳ አትሆንም ነበር፡፡ ያጠቃኛል የዚያን አይነት አስከፊ በደል ያደርስብኛል ብዬ በፍፁም ባልጠበኩት ሰዓት ባላባት ጃኖ አጠቃኝ፡፡ ተዘጋጅቶ ዘመድ አዝማዱን አሰባስቦ
ጦሩን ጭኖ በሌሊት ከበበኝ፡ ሚስቴን…. ሚስቴን... በሃይል... ሳልዘጋጅበት.ሳላስበው ...ነጥቆኝ ሄደ” እንባ እየተናነቀው አስረዳ፡፡
እውነተኛው ታሪክ ግን ባላባት ቱሬ እንደሚያወራው ሳይሆን የምስኪኑ
ገበሬ የጃኖን እዚህ ቀረሽ የማትባል እጮኛውን ባላባት ቱሬ በሀብትና በሥልጣኑ ተመክቶ፣ ወላጆቿን በከብትና በገንዘብ ገበራ ዐይናቸውን አሳውሮ የአሥራ ስምንት ዓመቷን ልጃገረድ ሌቱናን ጠልፎ ከወሰዳት በኋላ በባላባትነት ግዛቱ ውስጥ ድል ባለ ሠርግ ያገባት መሆኑ ነው ሀቁ። ገንዘብና ሀብት ባይኖረውም ዛሬ በቱሬ አንደበት የባላባትነት ማዕረግ የተሰጠው ጃኖ የጉልበትና የወኔ ደሃ አልነበረም። እንደ ነፍሱ የሚወዳት እጮኛውን ጉብሏን ሌቱናን ቱሬ በገንዘብ ኃይል አፍኗት ሲሄድ፣ የድንግልነት ክብሯን ሲወስድ እየታየው ገላው እስከሚቃጠል ድረስ በንዴት
ቢጋይም፣ እልህ ቢተናነቀውም አንድ ቀን የሱ አንጡራ ሀብት መሆኗን እንደሚያረጋግጥና እጮኛውን በነጠቅው በቱሬ ላይ አደጋ ጥሎ እንደሚወስዳት ጥርጥር አልነበረውም፡፡ ቱሬ የጓጓው ያንን የቀዘቀዘ ገላውን የም
ታሞቅለትን፣ ብዙ ንብረት ያወጣባትን ቆንጆዋን ሌቱናን ጎንቻ እንዲያስመልስለት ነው። ጎንቻ ተራ ውንብድና አይፈፅምም የሚለውን ዜና በመስማቱ የሌላ ታሪክ እየፈጠረ ገበሬውን ባላባት አድርጎ በመሾም ለመተረክ የተገደደውም ከዚህ እውነታ በመነሳት ነው፡፡
በእርግጥም ጎንቻ ትንሽ ስራ፣ ትልቅ ስራ በሚል የወንጀል አይነትን የሚያማርጥ ቢሆንም ጥሩ ገንዘብ እስካስታቀፉት ድረስ የህፃን ጉሮሮ ከመቀንጠስ ወደ ኋላ የማይል ጨካኝ መሆኑን ቢያውቀው ኖሮ ይሄንን ያክል
መጨነቅ ባላስፈለገው ነበር፡፡
“የፈለከውን ያክል ብር ብትስጠኝ አንድ ተራ ገበሬ ለመግደል አገር
አቋርጬ አልሄድም” ይለኛል ብሎ ስለፈራ እንባውን እየጠራረገ እጅግ ከፍተኛ የሆነ በደል የተፈፀመበት ሰው መስሎ እየተንቀጠቀጠ ኑዛዜውን ቀጠለ፡፡
“ምንም እንኳ እድሜዬ ቢገፋ፣ አቅሜ ቢዳከም አባቴ የወለደኝ ወንድ ጀግና ነበርኩ፡፡ ጃኖ ግን ወንድነቴን ጀግንነቴን ሰልቦታል። ልቤን በሀዘን አኮስምኖታል። ዝናዬን አጉድፎታል። ተኝቶ ሚስቱን ያስነጠቀ ባላባት አሰኝቶ በባላባትነት ግዛቴ ውስጥ አዋርዶኛል። ህዝቡ እንዲንቀኝ፣ እንዳይታዘዘኝ አድርጓል፡፡ ጉልበት በነበረኝ ጊዜ አባርሬ ይዣለሁ። ገድዬ ፎክሬአለሁ።ጃኖ ግን አቅሜ ቢደክም፣ዕድሜ ቢጫጫነኝ ንቆኝ የለበስኩትን ሱሪ አስወልቆ ቀሚስ አልብሶኛል። ጉልበት የእግዚአብሔር መሆኑን
#ያልታበሱ_እንባዎች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
....ስድስት ወር ተብሎ የሄደው አስቻለው እንኳን መመለስ ድምፁ እንኳ ሳይሰማ ድፍን ሰባቶ ወረሰ አልፈዋል። ይህ ሁኔታ በዲላ የፍቅር ቤተሰቦቹ ላይ ስጋትና
ጭንቀት ፈጥሮ ያተረማምሳቸው ይዟል ከሁሉም በላይ ደግሞ ሔዋንን።
አስቻለው ወደ አስመራ ሲሄድ ለዲላ የፍቅር ቤተሰቦቹ የገባው ቃል ነበር ቶሎ ቶሎ ደብዳቤ ሊፅፍ ሁኔታዎች በፈቀዱለት መጠን ስልክም ሊደውል ለነገሩ አንዲት ደብዳቤ ፅፏል።ያቺም ብትሆን ገና አስመራ በገባ ሦስተኛ ቀን ላይ ድንገት ወደ አዲስ አበባ የሚመለስ ሰው አግኝቶ ኖሮ ደህና መድረሱን የገለፀበት እንጂ
ዝርዝር የናፍቆት ሀሳብና የተሟላ አድራሻውን የያዘች አልነበረችም። በዚያች ደብዳቤ ላይ የጠለፀው ነገር ቢኖር ወደፊት ቋሚ አድራሻውን ሲያውቅ ሌላ ደብዳቤ እንደሚፅፍና ምናልባት ከአዲስ አበባ ወደ አስመራ በአውሮፕላን ላይ በነበረበት ወቅት ከሔዋን በመለየቱ ምክንያት ሆዱ ባብቶ በናፍቆት ስሜት ውስጥ ሆኖ የቋጠራቸው እንደሆኑ የሚገመቱ ጥቂት የግጥም ስንኞችን ብቻ ነበር።ያቺ ደብዳቤ ዲላ የደረሰችውም ስትጣጣል ሰንብታ ከተጻፈች ከአንድ ወር በኋላ ነበር፡፡
በቃ ሌላ የለም።
ሔዋን በልቧ ከአንድ ድምዳሜ ላይ ደርሳለች፤ እስቻለው ደህና ባይሆን ነው። ከሚል። የአስቻለውን ደህና አለመሆን ባሰበች ቁጥር ሁለት ነገሮች በሁለት ቦይ እየፈሰሱ በሀሳብ ይወስዷታል። በአንድ በኩል የአስቻለው ደህና አለመሆን
ፍቅሯን ሊያሳጣት ነው የዕድሜ ልክ የመንፈስ ስብራት፡፡ በሌላ በኩል ስለ እሷ "ብልግና" ሸዋዬ ለቤተሰቦቿ የጻፈችባትን ደብዳቤ ታስታውሳለች። ያ ደግሞ የቤተሰቦቿን በተለይም የእናቷን ሆድ እንዳሻከረባት ትገምታለች፡፡ ይህን ሁኔታ ማስቀየር ያስችላል ብላ የምትገምተው የአስቻለውን መልካም ሰውነት ነበር፡፡
እናትና አባቷ አንድ ቀን አስቻለውን ሲያውቁትና መልካም ሰውነቱን ሲረዱት ምርጫዋ ትክክል እንደሆነ በመረዳት የሻከረ ሆዳቸው ይሽርልኛል ብላ ትጓጓ ነበር፡፡አስቻለው ደህና ካልሆነና ምናልባትም ያልተመለሰ እንደሆነ ግን ከሁለት ዛፍ የወደቀች ልትሆን ነው። ጭንቅና ፍርሀቷም ከዚሁ ስጋት ይመነጫል።
ታፈሡ፣ በልሁና መርዕድ የሔዋንን ጭንቀት በብዙ መንገድ ይጋሩታል።
የአስቻለው ደብዳቤ አለመጻፍ፣ ስልክ አለመደወልና የመምጫው ጊዜም በአንድ ወር የዘመኑን እውነታዎች በራሳቸው መንገድ እየተረጎሙ ራሳቸውንም ሆነ ሔዋንን ማፅናናት አልቦዘኑም፡፡ ወትሮም እንደሚያደርጉት ሁሉ ጫት በመቃም ሰበብ ቀደም ሲል በልሁ፤ አሁን ደግሞ ሔዋንና ትርፌ በሚኖሩበት ቤት እየተሰበሰቡ መዋልና ማምሸታቸውን ቀጥለዋል፡፡ በዚያው ሂደት በበርካታ ጉዳዮች ላይ ደጋግመው ይነጋገራሉ፡፡ የአስቻለውን ደብዳቤ አለመጻፍ ጉዳይ ያነሱና ከወቅቱ ሁኔታ ጋር ለማገናዘብ ይሞክራሉ። በዚያን ወቅት መንግስት በፖስታ ቅብብሎሽ ላይ ከፍተኛ ቁጥጥር ያደርግ ነበር። ተቃዋሚዎች ከደጋፊዎቻቸው ጋር ምስጢር
ይለዋወጣሉ በሚል ስጋት በተለይ የተጠርጣሪ ሰዎችን ፖስታ እየቀደዱ መንገድ ላይ ያስቀሩ እንደነበር በሰፊው ይታወቃል። በተለይ ከኤርትራ ወደ ሌሎች
የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚላኩ ደብዳቤዎች ለተላከሳቸው ሰዎች የመድረሳቸው ዕድል
አስተማማኝ አልነበረም፡፡ ምናልባት አስቻለውም የሚጽፈው ደብዳቤ መንገድ ላይ ተቀዶ እየቀረ ይሆናል። እሱ ደግሞ የተከፋ ብሶተኛ ነውና ይህንኑ ስሜት በደብዳቤው ላይ አስፍሮ ከተገኘ የባሰ ይጠረጠርና ሁለተኛውም ሦስተኛም ደብዳቤዎቹ የዚሁ ሰለባ እየሆኑ ቀርተው ሊሆን ይችላል በማለት
ግምትና ጥርጣሪዎቹን ይገልፃሉ። ስልክ ያለመደወሉንም ጉዳይ ከዚሁ ከወቅቱ እውነታ ለይተው
አያዩትም።በወቅቱ ከአዲስ አበባም ሆነ ከሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች አስመራን በሽቦ የሚያገናኝ ስልክ አልነበረም፣ በዓመታት ጦርነት ተበጣጥሰው
አልቀዋልና። አማራጭ የመገናኛ መንገዶች ራዲዮና ቴሌ ግራም አሊያም ገመድ አልባ ማይክሮ ዌቭ ስልክ ናቸው። ራዲዮና ቴሌ ግራም ደግሞ ለአብዛኛው ሰው እንደ ልብ አይገኙም፡፡ የማይክሮ ዌብ ስልክም ገና በጅምር የቴክኖሎጂ ደረጃ ላይ ነው
ከሚሰራበት ጊዜ የማይሰራበት ጊዜ ይበልጣል። በሚሰራበትም ወቅት ወረፋው አስልቺ ነው፡፡ የእነታፈሡ ግምት ታዲያ አስቻለው በዚህም ቢል በዚያ አልሆንለት እያለ ተቸግሮ ነው›› በሚል ሀሳብ ይደመድማል። የአስቻለው የመመለሻ ጊዜ ማለፉንም ካነሱ ምናልባት የአይሮፕላን ጉዞ ወረፋ አልደርስ ብሎት ይሆናል ከሚል ግምት አያልፍም፡፡
ይህ ሁሉ ምክንያታዊ ትንተና ግን ለሔዋን አይገባትም ትሰማቸዋለች እንጂ አታዳምጣቸውም፡፡ ለእሷ አንድ ነገር ብቻ ግልፅ ነው፤ በቃ አስቻለው አልመጣም ድምፁም አልተሰማም ምክንያቱ ደግሞ ደህና አለመሆኑ ነው። የሚያስጨንቃት የእሱ ደህና አለመሆንና ምናልባትም ያልመጣ እንደሆነ የሚፈጠርባት የመንፈስ ቁስል ነው። የዚህ ሁሉ አጠቃላይ ውጤት ታዲያ ራሷ ተጨንቃ እነታፈሡንም ማስጨነቋ ነው።
ሁኔታዋ ሁሉ ያሳዝናቸው ይዟል።
በልሁ ታዲያ ይህንን ችግር አንድ ቀንም ቢሆን የቀረፈ መስሎት ነው በሙዚቃ ዘና ትልለት ዘንድ የመግቢያ ትኬት መግዛቱ።
በልሁ ትኬቶቹን ይዞ በቀጥታ ያመራው ቀድሞ የእሱ፣ ዛሬ ደግሞ የሔዋንና የትርፌ መኖሪያ ወደ ሆነው ቤት አቅጣጫ ነበር። ነገር ግን ከአንደኛ መንገድ ብዙም ሳይርቅ መርዕድ ከታች በኩል አስፋልቱን ይዞ ወደ ላይ ለመጣው አገኘውና «ትኬት ገዝተሃል?» ሲል በቅድሚያ ጠየቀው፡፡ የምን ትኬት?» አለ መርዕድ በርገግ ብሎ።
«ዛሬ እኮ የፖሊስ ኦርኬስትራ መጥቷል»
ባክህ ተው ለአንድ ቀን ምሽት እሥር ብር ከማወጣ በቋሚነት የምስማው አንድ ካሴት ብገዛ አይሻልም?» አለው።
«እስቲ በልጅ እግርህ ወደነ ሔዋን ልላክህ!»
«ለምን?»
በልሁ ቲኬቶቹን ከኪሱ አውጥቶ እያሳየው «ሔዋንና ትርፌ ዛሬ እንኳ ይዝናኑ ብዬ ትኬት ገዝቼላቸዋለሁ:: ስጣቸውና ስዓቱ ሲደርስ አዳራሹ ድረስ
እንዲመጡ ንገራቸው:: እነሱን አስገብተን እኛ ወደየጉዳያችን እንሄዳለን» አለው።መርዕድ አላቅማማም፣ ቲኬቶቹን ተቀበለውና ሲመለስ የት እንደሚገናኙ ቀጠሮ ይዘው ወደ ሔዋንና ትርፌ ቤት ገሰገሰ፡፡
የሙዚቃ ድግሱ ማስታወቂያ በድምጽ ማጉያ ይነገር በነበረበት ወቅት ብዙዎች ያለ መታደም
አዝማሚያ የሚያመለክት አስተያየት ይሰጡ የነበረ ቢሆንም
በወቅቱ እስከ ሰላሳ ሺህ ህዝብ የሚኖርባት ዲላ ከተማ ውስጥ ከእንድ ሺ በላይ የማይዘውን የህዝብ መሰብሰቢያ አዳራሽ የሚሞላ የሙዚቃ አፍቃሪ አልጠፋም፡፡ሰዓቱ ደርሶ ሔዋንን እና ትርፌን በቀጠሩበት ቦታ አግኝተዋቸው ወደ አዳራሹ ይዘዋቸው በመግባት ቦታ ሊያሲዟቸው ቢሞክሩም እነሱ
ቲኬት ስላልያዙ ወደ አዳራሹ ለመግባት ተከለከሉ።በዚያ ምትክ ትዕይንቱ፡ እንዳይርቃቸው ወደፊት ሄደው መቀመጥ እንዳለባቸው
መከሯቸውና እነሱ ወደ ውጭ ተመለሱ።
ሔዋን እና ትርፌ ግን አገባቡ ጭንቅ አላቸው፡፡ በዚህ ዓይነት ዝግጅትና አዳራሽ ውስጥ ታዳሚ ሁነው አያውቁም፡፡ የዝግጅቱ ተካፋይ ለመሆን የጓጉ ቢሆንም
ሌላ ሰው እንደሚያደርገው ቦታ መርጠው ለመቀመጥ ድፍረቱን አጡ። እንዲያውም
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
....ስድስት ወር ተብሎ የሄደው አስቻለው እንኳን መመለስ ድምፁ እንኳ ሳይሰማ ድፍን ሰባቶ ወረሰ አልፈዋል። ይህ ሁኔታ በዲላ የፍቅር ቤተሰቦቹ ላይ ስጋትና
ጭንቀት ፈጥሮ ያተረማምሳቸው ይዟል ከሁሉም በላይ ደግሞ ሔዋንን።
አስቻለው ወደ አስመራ ሲሄድ ለዲላ የፍቅር ቤተሰቦቹ የገባው ቃል ነበር ቶሎ ቶሎ ደብዳቤ ሊፅፍ ሁኔታዎች በፈቀዱለት መጠን ስልክም ሊደውል ለነገሩ አንዲት ደብዳቤ ፅፏል።ያቺም ብትሆን ገና አስመራ በገባ ሦስተኛ ቀን ላይ ድንገት ወደ አዲስ አበባ የሚመለስ ሰው አግኝቶ ኖሮ ደህና መድረሱን የገለፀበት እንጂ
ዝርዝር የናፍቆት ሀሳብና የተሟላ አድራሻውን የያዘች አልነበረችም። በዚያች ደብዳቤ ላይ የጠለፀው ነገር ቢኖር ወደፊት ቋሚ አድራሻውን ሲያውቅ ሌላ ደብዳቤ እንደሚፅፍና ምናልባት ከአዲስ አበባ ወደ አስመራ በአውሮፕላን ላይ በነበረበት ወቅት ከሔዋን በመለየቱ ምክንያት ሆዱ ባብቶ በናፍቆት ስሜት ውስጥ ሆኖ የቋጠራቸው እንደሆኑ የሚገመቱ ጥቂት የግጥም ስንኞችን ብቻ ነበር።ያቺ ደብዳቤ ዲላ የደረሰችውም ስትጣጣል ሰንብታ ከተጻፈች ከአንድ ወር በኋላ ነበር፡፡
በቃ ሌላ የለም።
ሔዋን በልቧ ከአንድ ድምዳሜ ላይ ደርሳለች፤ እስቻለው ደህና ባይሆን ነው። ከሚል። የአስቻለውን ደህና አለመሆን ባሰበች ቁጥር ሁለት ነገሮች በሁለት ቦይ እየፈሰሱ በሀሳብ ይወስዷታል። በአንድ በኩል የአስቻለው ደህና አለመሆን
ፍቅሯን ሊያሳጣት ነው የዕድሜ ልክ የመንፈስ ስብራት፡፡ በሌላ በኩል ስለ እሷ "ብልግና" ሸዋዬ ለቤተሰቦቿ የጻፈችባትን ደብዳቤ ታስታውሳለች። ያ ደግሞ የቤተሰቦቿን በተለይም የእናቷን ሆድ እንዳሻከረባት ትገምታለች፡፡ ይህን ሁኔታ ማስቀየር ያስችላል ብላ የምትገምተው የአስቻለውን መልካም ሰውነት ነበር፡፡
እናትና አባቷ አንድ ቀን አስቻለውን ሲያውቁትና መልካም ሰውነቱን ሲረዱት ምርጫዋ ትክክል እንደሆነ በመረዳት የሻከረ ሆዳቸው ይሽርልኛል ብላ ትጓጓ ነበር፡፡አስቻለው ደህና ካልሆነና ምናልባትም ያልተመለሰ እንደሆነ ግን ከሁለት ዛፍ የወደቀች ልትሆን ነው። ጭንቅና ፍርሀቷም ከዚሁ ስጋት ይመነጫል።
ታፈሡ፣ በልሁና መርዕድ የሔዋንን ጭንቀት በብዙ መንገድ ይጋሩታል።
የአስቻለው ደብዳቤ አለመጻፍ፣ ስልክ አለመደወልና የመምጫው ጊዜም በአንድ ወር የዘመኑን እውነታዎች በራሳቸው መንገድ እየተረጎሙ ራሳቸውንም ሆነ ሔዋንን ማፅናናት አልቦዘኑም፡፡ ወትሮም እንደሚያደርጉት ሁሉ ጫት በመቃም ሰበብ ቀደም ሲል በልሁ፤ አሁን ደግሞ ሔዋንና ትርፌ በሚኖሩበት ቤት እየተሰበሰቡ መዋልና ማምሸታቸውን ቀጥለዋል፡፡ በዚያው ሂደት በበርካታ ጉዳዮች ላይ ደጋግመው ይነጋገራሉ፡፡ የአስቻለውን ደብዳቤ አለመጻፍ ጉዳይ ያነሱና ከወቅቱ ሁኔታ ጋር ለማገናዘብ ይሞክራሉ። በዚያን ወቅት መንግስት በፖስታ ቅብብሎሽ ላይ ከፍተኛ ቁጥጥር ያደርግ ነበር። ተቃዋሚዎች ከደጋፊዎቻቸው ጋር ምስጢር
ይለዋወጣሉ በሚል ስጋት በተለይ የተጠርጣሪ ሰዎችን ፖስታ እየቀደዱ መንገድ ላይ ያስቀሩ እንደነበር በሰፊው ይታወቃል። በተለይ ከኤርትራ ወደ ሌሎች
የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚላኩ ደብዳቤዎች ለተላከሳቸው ሰዎች የመድረሳቸው ዕድል
አስተማማኝ አልነበረም፡፡ ምናልባት አስቻለውም የሚጽፈው ደብዳቤ መንገድ ላይ ተቀዶ እየቀረ ይሆናል። እሱ ደግሞ የተከፋ ብሶተኛ ነውና ይህንኑ ስሜት በደብዳቤው ላይ አስፍሮ ከተገኘ የባሰ ይጠረጠርና ሁለተኛውም ሦስተኛም ደብዳቤዎቹ የዚሁ ሰለባ እየሆኑ ቀርተው ሊሆን ይችላል በማለት
ግምትና ጥርጣሪዎቹን ይገልፃሉ። ስልክ ያለመደወሉንም ጉዳይ ከዚሁ ከወቅቱ እውነታ ለይተው
አያዩትም።በወቅቱ ከአዲስ አበባም ሆነ ከሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች አስመራን በሽቦ የሚያገናኝ ስልክ አልነበረም፣ በዓመታት ጦርነት ተበጣጥሰው
አልቀዋልና። አማራጭ የመገናኛ መንገዶች ራዲዮና ቴሌ ግራም አሊያም ገመድ አልባ ማይክሮ ዌቭ ስልክ ናቸው። ራዲዮና ቴሌ ግራም ደግሞ ለአብዛኛው ሰው እንደ ልብ አይገኙም፡፡ የማይክሮ ዌብ ስልክም ገና በጅምር የቴክኖሎጂ ደረጃ ላይ ነው
ከሚሰራበት ጊዜ የማይሰራበት ጊዜ ይበልጣል። በሚሰራበትም ወቅት ወረፋው አስልቺ ነው፡፡ የእነታፈሡ ግምት ታዲያ አስቻለው በዚህም ቢል በዚያ አልሆንለት እያለ ተቸግሮ ነው›› በሚል ሀሳብ ይደመድማል። የአስቻለው የመመለሻ ጊዜ ማለፉንም ካነሱ ምናልባት የአይሮፕላን ጉዞ ወረፋ አልደርስ ብሎት ይሆናል ከሚል ግምት አያልፍም፡፡
ይህ ሁሉ ምክንያታዊ ትንተና ግን ለሔዋን አይገባትም ትሰማቸዋለች እንጂ አታዳምጣቸውም፡፡ ለእሷ አንድ ነገር ብቻ ግልፅ ነው፤ በቃ አስቻለው አልመጣም ድምፁም አልተሰማም ምክንያቱ ደግሞ ደህና አለመሆኑ ነው። የሚያስጨንቃት የእሱ ደህና አለመሆንና ምናልባትም ያልመጣ እንደሆነ የሚፈጠርባት የመንፈስ ቁስል ነው። የዚህ ሁሉ አጠቃላይ ውጤት ታዲያ ራሷ ተጨንቃ እነታፈሡንም ማስጨነቋ ነው።
ሁኔታዋ ሁሉ ያሳዝናቸው ይዟል።
በልሁ ታዲያ ይህንን ችግር አንድ ቀንም ቢሆን የቀረፈ መስሎት ነው በሙዚቃ ዘና ትልለት ዘንድ የመግቢያ ትኬት መግዛቱ።
በልሁ ትኬቶቹን ይዞ በቀጥታ ያመራው ቀድሞ የእሱ፣ ዛሬ ደግሞ የሔዋንና የትርፌ መኖሪያ ወደ ሆነው ቤት አቅጣጫ ነበር። ነገር ግን ከአንደኛ መንገድ ብዙም ሳይርቅ መርዕድ ከታች በኩል አስፋልቱን ይዞ ወደ ላይ ለመጣው አገኘውና «ትኬት ገዝተሃል?» ሲል በቅድሚያ ጠየቀው፡፡ የምን ትኬት?» አለ መርዕድ በርገግ ብሎ።
«ዛሬ እኮ የፖሊስ ኦርኬስትራ መጥቷል»
ባክህ ተው ለአንድ ቀን ምሽት እሥር ብር ከማወጣ በቋሚነት የምስማው አንድ ካሴት ብገዛ አይሻልም?» አለው።
«እስቲ በልጅ እግርህ ወደነ ሔዋን ልላክህ!»
«ለምን?»
በልሁ ቲኬቶቹን ከኪሱ አውጥቶ እያሳየው «ሔዋንና ትርፌ ዛሬ እንኳ ይዝናኑ ብዬ ትኬት ገዝቼላቸዋለሁ:: ስጣቸውና ስዓቱ ሲደርስ አዳራሹ ድረስ
እንዲመጡ ንገራቸው:: እነሱን አስገብተን እኛ ወደየጉዳያችን እንሄዳለን» አለው።መርዕድ አላቅማማም፣ ቲኬቶቹን ተቀበለውና ሲመለስ የት እንደሚገናኙ ቀጠሮ ይዘው ወደ ሔዋንና ትርፌ ቤት ገሰገሰ፡፡
የሙዚቃ ድግሱ ማስታወቂያ በድምጽ ማጉያ ይነገር በነበረበት ወቅት ብዙዎች ያለ መታደም
አዝማሚያ የሚያመለክት አስተያየት ይሰጡ የነበረ ቢሆንም
በወቅቱ እስከ ሰላሳ ሺህ ህዝብ የሚኖርባት ዲላ ከተማ ውስጥ ከእንድ ሺ በላይ የማይዘውን የህዝብ መሰብሰቢያ አዳራሽ የሚሞላ የሙዚቃ አፍቃሪ አልጠፋም፡፡ሰዓቱ ደርሶ ሔዋንን እና ትርፌን በቀጠሩበት ቦታ አግኝተዋቸው ወደ አዳራሹ ይዘዋቸው በመግባት ቦታ ሊያሲዟቸው ቢሞክሩም እነሱ
ቲኬት ስላልያዙ ወደ አዳራሹ ለመግባት ተከለከሉ።በዚያ ምትክ ትዕይንቱ፡ እንዳይርቃቸው ወደፊት ሄደው መቀመጥ እንዳለባቸው
መከሯቸውና እነሱ ወደ ውጭ ተመለሱ።
ሔዋን እና ትርፌ ግን አገባቡ ጭንቅ አላቸው፡፡ በዚህ ዓይነት ዝግጅትና አዳራሽ ውስጥ ታዳሚ ሁነው አያውቁም፡፡ የዝግጅቱ ተካፋይ ለመሆን የጓጉ ቢሆንም
ሌላ ሰው እንደሚያደርገው ቦታ መርጠው ለመቀመጥ ድፍረቱን አጡ። እንዲያውም
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
“መንግሥታችሁን ታጥናላችሁ፤ አልጋችሁን ትጠብቅላችሁ” እያሉ
መረቋቸው።
ሕዝቡ ከሚፈልጋቸው ነገሮች አንዱ አብያተ ክርስቲያናት
እንዲሠሩለት በመሆኑ ምንትዋብ ስለጉዳዩ ከልጇ ከብርሃን ሰገድ
ኢያሱ ጋር መከረች። ኢያሱ አስራ አንድ ዓመት አልፎታል። ንጉሠ
ነገሥቱ እሱ በመሆኑ፣ሳታማክረው የምታደርገው ነገር የለም።
አንድ ከሰዐት በኋላ፣ ቤተመንግሥት እንግዳ መቀበያው ክፍል ተቀምጠዋል። ሁለቱም ያንን መጠነኛ ስፋት ያለውን ክፍል ይወዱታል።ቅልብጭ ያለ በመሆኑ፣ የልባቸውን ለመጫወትና ስለመንግሥት ሆነ
ስለራሳቸው ጉዳይ ለማውራት ይመቻቸዋል።
ቀይ ከፋይ ጨርቅ የለበሱ ወንበሮች ዙርያውን ተደርድረዋል።
ምንትዋብ ከመግቢያው በስተቀኝ በኩል ከቀንድ የተሠራው የካባና
የባርኔጣ ማሳረፊያ ላይ ጎን ለጎን የተሰቀሉትን የእሷንና የእሱን ካባዎች ትመለከታለች። የቀረበላትን ጠጅ ቀመሰችና ቀና ብላ አየችው።
ኢያሱ ደረስህልኝ። እንዲህ አድገህ በማየቴ ታላቅ ደስታ
ይሰማኛል። ደጅ ኻልወጣሁ እያልክ ምታስቸግርበት ግዝየ ስንኳ ሩቅ አልነበረም። ያነዜ ዛዲያ አንዱ ይገድልብኛል እያልሁ እጨነቅ ነበር።አሁን እያደግህ ስትመጣ ሁሉ ነገር እየገባህ መጣ። እዝጊሃር ይመስገን” አለችው።
“አንቺ እኮ ለኔ በጣም ስለምትጨነቂ ነው እንጂ ምወጣውና ምገባው ኸሰው ጋር ነው። ምኑ ነው ሲጨንቅሽ የነበረው?”
“አየ ኢያሱ የእናት ሆድ ምን ያለ እንደሆነ አለማወቅህ ነው
እንዲህ ሚያስብልህ። አሁን እንደምታየው አገራችን ሰላም ሁኗል እኔም እንግዲህ ፊት አንስቸልህ እንደነበረው ልቤ ያለው ቤተክሲያን ማሠራት ላይ ነው። ድኻው ቤተክሲያን እንድናሠራለት ይፈልጋል ። እኔም ብሆን ነፍስ ካወቅሁ ዠምሮ ክፍሌ ለሆነችው ለቁስቋም ማርያም ቤተክሲያን ማሳነጽ ፈልጋለሁ። ጃንሆይም እኮ በነገሡ ባመታቸው ነው
ኸዝኸ ኸጐንደር ቅዱስ ሩፋኤልን የተከሉት። ደፈጫ ኪዳነ ምረትንም
እሳቸው ናቸው የደበሩ። አያትህ ታላቁ ኢያሱም ቢሆኑ ደብረብርሃን
ሥላሴንና አደባባይ ተክለሃይማኖትን የመሳሰሉ ቤተክሲያኖች ተክለዋል። ታቦት ተሸክመው እደብረብርሃን ሥላሤ ከመንበሩ ሲያገቡ ማዶል እንዴ፡-
ወዴት ሂዶ ኑራል ሰሞነኛ ቄሱ፣
ታቦት ተሸከመ ዘውዱን ትቶ ኢያሱ።
የተሸሽገውን ያባቱን ቅስና፤
ገለጠው ኢያሱ ታቦት አነሳና።
አየነው ኢያሱ ደብረብርሃን ቁሞ፣
ሰውነቱን ትቶ መላክ ሆነ ደሞ።
ሥላሴን ቢሸከም ኢያሱ ገነነ፤
ላራቱ ኪሩቤል አምስተኛ ሆነ።
ተብሎ የተገጠመላቸው?” አለችው።
ፈገግ አለ።
ጐንደር የገባች ቀን ያየቻቸውን፣ ከዚያ በኋላ የተሳለመቻቸውን፣
የደጎመቻቸውንና ሳትሰስት ጉልት እና መሬት የሰጠቻቸውን አብያት
ክርስቲያናት ሁሉ ባየችና ባሰበች ቁጥር፣ ጐንደር የቤተክርስቲያን
ባለፀጋ እንደሆነች ብታውቅም፣ የኔ የምትላትን እንደምታሠራ ስትዝት ቆየታ ጊዜው አሁን ነው pብላለች። ከባሏ ሞት በኋላ፣ “ሁሉን በግዝየው ማረግ” የሚለው ሐሳብ አእምሮዋን በመግዛቱ ጊዜ ሳታባክን ማድረግ
ያለባትን ማድረግ እንዳለባት ራሷን ስታስታውስ ቆይታለች።
እናም እንዳልሁህ ለቁስቋም ቤተክሲያን ላቆምላት ተነስቻለሁ።"
“አንቺ እናቴ እንዳልሽው ይሁን” አላት።
“ያባቶችህ በረከት አይለይህ። እኔ መቸም አሳቤ ብዙ ነው።
ቤተክሲያን ብቻ ሳይሆን ለኔም ቤተመንግሥትና ሌላም ሌላም ማሠራት ፈልጋለሁ። አንተም የራስህ መኖሪያ ያስፈልግሀል። ይኸ ላንተ ሊሆንህ ይችላል” አለችው።
አሁን የሚኖሩበት አፄ ፋሲለደስ ቅጥር ግቢ ውስጥ ስላሠራችው
ቤተመንግሥት እያወራች። ቀጥላም፣ “ሙያ ያላቸው ጠርአና ሶሪያዎቹ ኸኛ ሰዎች ጋር ሁነው ቢሠሩ ብዬ አስቤያለሁ። እንዳው እንደ ገብረሥላሤ ያለ ግንበኛ ባገኝማ! እንዳው እንዴት ያለ ግንበኛ ነበር ይላሉ። በአያትህ ግዝየ ዠምሮ ነበረ። ኸኛ ሰዎችም አላፊ ሁነው ሚሠሩም መድባለሁ።”
ባለችው ተስማማ።
ሳይውል ሳያድር ግንበኞችና ባለሙያዎች ተቀጥረው ከፋሲለደስ ቤተመንግሥት እምብዛም ሳይርቅ፣ ጉብታ ላይ የደብረ ፀሐይ ቁስቋም ግንባታ ተጀመረ። ባጭር ጊዜ መቃረቢያው ተሠርቶ አልቆ ቅዳሜ
ቀን ታቦተ ሕጉ ከአቡነ ክርስቶዶሉ ቤት ተነስቶ ወደ ቁስቋም ሲወሰድ፣የፊት ዐጀብ ከፊት እየመራ፣ የጎንና የኋላ ዐጀብ ተከትሎ፣ አስቴር ብላ የሰየመቻትን ሕፃን ከግራዝማች ኢያሱ በቅርቡ የወለደችው አራሷ ምንትዋብ በበቅሎ፣ ዳግማዊ ኢያሱ በፈረስ ሆነው፣ የወርቅ በትረ መንግሥታቸውን ጨብጠውና ግርማ ሞገስ ተጎናጽፈው፣ ለሽኝት
ወጡ።
ዐቃቤ ሰዐቱና ዕጨጌው እነሱን ሲከተሉ፣ ካህናቱ ቀይና አረንጓዴ
ለብሰው ሰንደቅ እያውለበለቡ፣ የወርቅና የብር መስቀልና የወርቅ
ፀናፅል ይዘው፣ እየዘመሩና እያሸበሸቡ፣ ነጋሪት እየተጎሰመ፣ መኳንንቱ፣ሊቃውንቱ፣ ወይዛዝርቱና ባለሟሉ ደግሞ እንደየደረጃቸው ተሰልፈው
ተከተሉ።
ሕዝቡ መንገድ ዳር ቆሞ መሬት እየሳመ በዕልልታና በሆታ
ተቀበላቸው። ታቦተ ሕጉ በአቡኑ ተባርኮ ቤተመቅደስ ገባ።
ምንትዋብም ዋናውን የቁስቋም ማርያም ሆነ የሌሎች ግንባታዎችን እንዲከታተሉ አዛዥ ተክለሃይማኖትን፣ አዛዥ ሕርያቆስን፣ አዛዥ ናቡቴን፣ አዛዥ ማሞንና በጅሮንድ ኢሳያስን የበላይ ተቆጣጣሪ አድርጋ
ሾመች። ግሪክና ሶርያውያን ሕንጻ ሥራ አዋቂዎችም ተፈልገው
መጥተው ከሃገሬው ሰው ጋር ሆነው እንዲሠሩ ተደረገ።
ምንትዋብና ኢያሱ ከሥራው አልተለዩም። ምንትዋብ ዘወትር
ጠዋት የቤተመንግሥት ጉዳይ ከፈጸመችና ካስፈጸመች በኋላ፣ እሷ በቅሎ ላይ፣ ኢያሱ ፈረስ ላይ ሆነው በባልደራስ በር ወጥተው ቁስቋም ግንባታ ስፍራ ይሄዳሉ።
ኢያሱ ከቀቢዎች ጎን ሆኖ እየቀባ፣ እሷ እየተቸች፣ ያልወደደችውን
እያስፈረሰች፣ ራሷ በምትፈልገው መሠረት እያሰራች፣ ዕንጨት
ከአርማጨሆና ከወልቃይት እያስመጣች፣ በድንጋይ ባለ ሰባት በሯ ቁስቋም ማርያም ተሠራች። ውስጥ መግቢያ ደረጃዎቿ ከሕንድ በመጣ ሸክላ ተሰሩላት። ግቢዋ ዝግባ፣ ጥድና ወይራ ተተከለበት፣ አፈር ደብረ
ቍስቋም ከምትገኝበት ሃገር ከግብፅ መጥቶ ተበተነበት። ቁስቋም ከውስጥና ከውጭ በወርቅ አሸበረቀች።
ምንትዋብ በሥዕል ልታስጌጣት ብላ ያንን የልጅነት ምስሏን የላከውን ሠዓሊ ማስመጣት ፈለገች። ትዝ ሲላት የሰውየውን ሆነ የመነኩሴውን ስም አታውቅም። መነኩሴውን ራሳቸውን ማን ብላ እንምታስፈልጋቸው ግራ ገባት፤ ተበሳጨች።
በመጨረሻም ቁስቋም ጐንደር ባሉ ሠዓሊዎች ሥራዎች አጌጠች።ምንትዋብ ከውስጥ የማርያምን ሥዕል አሥላ፣ ከፋይ ካባዋን በትንንሹ አስቀድዳ ዙርያውን አስለጠፈችበት::
ግንባታ መጠናቀቂያው ላይ ማስጌጫ ገንዘብ ሲያጥር፣ ሥራው እንዳይቋረጥ ምንትዋብ ከራሷ ወርቅ፣ ቀለበቷ ሳይቀር፣ ሰጠች።አንድ ሰሞን ጐንደር “ጉድ” አለ፤ “እቴጌ የጣታቸው ቀለበት ሳይቀር ለቤተክሲያን ማሠሪያ ሰጡ” እያለ አደነቀ።
የቁስቋም ማርያም ግንባታ በሦስት ዓመት ውስጥ ተጠናቀቀ።
ታቦቷ በታላቅ በዓል ቋሚ ማደሪያዋ ስትገባ ሕዝቡ፣ “እሰይ! እሰይ!” አለ፣ አመሰገነ። ካህናቱ ምንትዋብንና ኢያሱን፣ “
ለማርያም ቁስቋምን
እንዳቆማችሁላት፣ ቤተመቅደሷንም ዐይናችሁ እንቅልፍ ሳያይ ደፋ ቀና
ብላችሁ እንደሠራችሁላት፣ ለናንተም ትቁምላችሁ። መንግሥታችሁን ታጥናላችሁ፤ አልጋችሁን ትጠብቅላችሁ” እያሉ መረቋቸው።
ምንትዋብ ከልጇ ጋር ቁስቋም ማርያምን ማደራጀት ላይ አተኮረች። አንድ ቀን፣ የየደብሩን ካህናትና ሊቃውንት ወርቅ ሰቀላ ሰበሰበቻቸው።
“እቴጌ ምን ሊሉን ነው?” እያሉ እርስ በእርስ ተጠያየቁ።
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
“መንግሥታችሁን ታጥናላችሁ፤ አልጋችሁን ትጠብቅላችሁ” እያሉ
መረቋቸው።
ሕዝቡ ከሚፈልጋቸው ነገሮች አንዱ አብያተ ክርስቲያናት
እንዲሠሩለት በመሆኑ ምንትዋብ ስለጉዳዩ ከልጇ ከብርሃን ሰገድ
ኢያሱ ጋር መከረች። ኢያሱ አስራ አንድ ዓመት አልፎታል። ንጉሠ
ነገሥቱ እሱ በመሆኑ፣ሳታማክረው የምታደርገው ነገር የለም።
አንድ ከሰዐት በኋላ፣ ቤተመንግሥት እንግዳ መቀበያው ክፍል ተቀምጠዋል። ሁለቱም ያንን መጠነኛ ስፋት ያለውን ክፍል ይወዱታል።ቅልብጭ ያለ በመሆኑ፣ የልባቸውን ለመጫወትና ስለመንግሥት ሆነ
ስለራሳቸው ጉዳይ ለማውራት ይመቻቸዋል።
ቀይ ከፋይ ጨርቅ የለበሱ ወንበሮች ዙርያውን ተደርድረዋል።
ምንትዋብ ከመግቢያው በስተቀኝ በኩል ከቀንድ የተሠራው የካባና
የባርኔጣ ማሳረፊያ ላይ ጎን ለጎን የተሰቀሉትን የእሷንና የእሱን ካባዎች ትመለከታለች። የቀረበላትን ጠጅ ቀመሰችና ቀና ብላ አየችው።
ኢያሱ ደረስህልኝ። እንዲህ አድገህ በማየቴ ታላቅ ደስታ
ይሰማኛል። ደጅ ኻልወጣሁ እያልክ ምታስቸግርበት ግዝየ ስንኳ ሩቅ አልነበረም። ያነዜ ዛዲያ አንዱ ይገድልብኛል እያልሁ እጨነቅ ነበር።አሁን እያደግህ ስትመጣ ሁሉ ነገር እየገባህ መጣ። እዝጊሃር ይመስገን” አለችው።
“አንቺ እኮ ለኔ በጣም ስለምትጨነቂ ነው እንጂ ምወጣውና ምገባው ኸሰው ጋር ነው። ምኑ ነው ሲጨንቅሽ የነበረው?”
“አየ ኢያሱ የእናት ሆድ ምን ያለ እንደሆነ አለማወቅህ ነው
እንዲህ ሚያስብልህ። አሁን እንደምታየው አገራችን ሰላም ሁኗል እኔም እንግዲህ ፊት አንስቸልህ እንደነበረው ልቤ ያለው ቤተክሲያን ማሠራት ላይ ነው። ድኻው ቤተክሲያን እንድናሠራለት ይፈልጋል ። እኔም ብሆን ነፍስ ካወቅሁ ዠምሮ ክፍሌ ለሆነችው ለቁስቋም ማርያም ቤተክሲያን ማሳነጽ ፈልጋለሁ። ጃንሆይም እኮ በነገሡ ባመታቸው ነው
ኸዝኸ ኸጐንደር ቅዱስ ሩፋኤልን የተከሉት። ደፈጫ ኪዳነ ምረትንም
እሳቸው ናቸው የደበሩ። አያትህ ታላቁ ኢያሱም ቢሆኑ ደብረብርሃን
ሥላሴንና አደባባይ ተክለሃይማኖትን የመሳሰሉ ቤተክሲያኖች ተክለዋል። ታቦት ተሸክመው እደብረብርሃን ሥላሤ ከመንበሩ ሲያገቡ ማዶል እንዴ፡-
ወዴት ሂዶ ኑራል ሰሞነኛ ቄሱ፣
ታቦት ተሸከመ ዘውዱን ትቶ ኢያሱ።
የተሸሽገውን ያባቱን ቅስና፤
ገለጠው ኢያሱ ታቦት አነሳና።
አየነው ኢያሱ ደብረብርሃን ቁሞ፣
ሰውነቱን ትቶ መላክ ሆነ ደሞ።
ሥላሴን ቢሸከም ኢያሱ ገነነ፤
ላራቱ ኪሩቤል አምስተኛ ሆነ።
ተብሎ የተገጠመላቸው?” አለችው።
ፈገግ አለ።
ጐንደር የገባች ቀን ያየቻቸውን፣ ከዚያ በኋላ የተሳለመቻቸውን፣
የደጎመቻቸውንና ሳትሰስት ጉልት እና መሬት የሰጠቻቸውን አብያት
ክርስቲያናት ሁሉ ባየችና ባሰበች ቁጥር፣ ጐንደር የቤተክርስቲያን
ባለፀጋ እንደሆነች ብታውቅም፣ የኔ የምትላትን እንደምታሠራ ስትዝት ቆየታ ጊዜው አሁን ነው pብላለች። ከባሏ ሞት በኋላ፣ “ሁሉን በግዝየው ማረግ” የሚለው ሐሳብ አእምሮዋን በመግዛቱ ጊዜ ሳታባክን ማድረግ
ያለባትን ማድረግ እንዳለባት ራሷን ስታስታውስ ቆይታለች።
እናም እንዳልሁህ ለቁስቋም ቤተክሲያን ላቆምላት ተነስቻለሁ።"
“አንቺ እናቴ እንዳልሽው ይሁን” አላት።
“ያባቶችህ በረከት አይለይህ። እኔ መቸም አሳቤ ብዙ ነው።
ቤተክሲያን ብቻ ሳይሆን ለኔም ቤተመንግሥትና ሌላም ሌላም ማሠራት ፈልጋለሁ። አንተም የራስህ መኖሪያ ያስፈልግሀል። ይኸ ላንተ ሊሆንህ ይችላል” አለችው።
አሁን የሚኖሩበት አፄ ፋሲለደስ ቅጥር ግቢ ውስጥ ስላሠራችው
ቤተመንግሥት እያወራች። ቀጥላም፣ “ሙያ ያላቸው ጠርአና ሶሪያዎቹ ኸኛ ሰዎች ጋር ሁነው ቢሠሩ ብዬ አስቤያለሁ። እንዳው እንደ ገብረሥላሤ ያለ ግንበኛ ባገኝማ! እንዳው እንዴት ያለ ግንበኛ ነበር ይላሉ። በአያትህ ግዝየ ዠምሮ ነበረ። ኸኛ ሰዎችም አላፊ ሁነው ሚሠሩም መድባለሁ።”
ባለችው ተስማማ።
ሳይውል ሳያድር ግንበኞችና ባለሙያዎች ተቀጥረው ከፋሲለደስ ቤተመንግሥት እምብዛም ሳይርቅ፣ ጉብታ ላይ የደብረ ፀሐይ ቁስቋም ግንባታ ተጀመረ። ባጭር ጊዜ መቃረቢያው ተሠርቶ አልቆ ቅዳሜ
ቀን ታቦተ ሕጉ ከአቡነ ክርስቶዶሉ ቤት ተነስቶ ወደ ቁስቋም ሲወሰድ፣የፊት ዐጀብ ከፊት እየመራ፣ የጎንና የኋላ ዐጀብ ተከትሎ፣ አስቴር ብላ የሰየመቻትን ሕፃን ከግራዝማች ኢያሱ በቅርቡ የወለደችው አራሷ ምንትዋብ በበቅሎ፣ ዳግማዊ ኢያሱ በፈረስ ሆነው፣ የወርቅ በትረ መንግሥታቸውን ጨብጠውና ግርማ ሞገስ ተጎናጽፈው፣ ለሽኝት
ወጡ።
ዐቃቤ ሰዐቱና ዕጨጌው እነሱን ሲከተሉ፣ ካህናቱ ቀይና አረንጓዴ
ለብሰው ሰንደቅ እያውለበለቡ፣ የወርቅና የብር መስቀልና የወርቅ
ፀናፅል ይዘው፣ እየዘመሩና እያሸበሸቡ፣ ነጋሪት እየተጎሰመ፣ መኳንንቱ፣ሊቃውንቱ፣ ወይዛዝርቱና ባለሟሉ ደግሞ እንደየደረጃቸው ተሰልፈው
ተከተሉ።
ሕዝቡ መንገድ ዳር ቆሞ መሬት እየሳመ በዕልልታና በሆታ
ተቀበላቸው። ታቦተ ሕጉ በአቡኑ ተባርኮ ቤተመቅደስ ገባ።
ምንትዋብም ዋናውን የቁስቋም ማርያም ሆነ የሌሎች ግንባታዎችን እንዲከታተሉ አዛዥ ተክለሃይማኖትን፣ አዛዥ ሕርያቆስን፣ አዛዥ ናቡቴን፣ አዛዥ ማሞንና በጅሮንድ ኢሳያስን የበላይ ተቆጣጣሪ አድርጋ
ሾመች። ግሪክና ሶርያውያን ሕንጻ ሥራ አዋቂዎችም ተፈልገው
መጥተው ከሃገሬው ሰው ጋር ሆነው እንዲሠሩ ተደረገ።
ምንትዋብና ኢያሱ ከሥራው አልተለዩም። ምንትዋብ ዘወትር
ጠዋት የቤተመንግሥት ጉዳይ ከፈጸመችና ካስፈጸመች በኋላ፣ እሷ በቅሎ ላይ፣ ኢያሱ ፈረስ ላይ ሆነው በባልደራስ በር ወጥተው ቁስቋም ግንባታ ስፍራ ይሄዳሉ።
ኢያሱ ከቀቢዎች ጎን ሆኖ እየቀባ፣ እሷ እየተቸች፣ ያልወደደችውን
እያስፈረሰች፣ ራሷ በምትፈልገው መሠረት እያሰራች፣ ዕንጨት
ከአርማጨሆና ከወልቃይት እያስመጣች፣ በድንጋይ ባለ ሰባት በሯ ቁስቋም ማርያም ተሠራች። ውስጥ መግቢያ ደረጃዎቿ ከሕንድ በመጣ ሸክላ ተሰሩላት። ግቢዋ ዝግባ፣ ጥድና ወይራ ተተከለበት፣ አፈር ደብረ
ቍስቋም ከምትገኝበት ሃገር ከግብፅ መጥቶ ተበተነበት። ቁስቋም ከውስጥና ከውጭ በወርቅ አሸበረቀች።
ምንትዋብ በሥዕል ልታስጌጣት ብላ ያንን የልጅነት ምስሏን የላከውን ሠዓሊ ማስመጣት ፈለገች። ትዝ ሲላት የሰውየውን ሆነ የመነኩሴውን ስም አታውቅም። መነኩሴውን ራሳቸውን ማን ብላ እንምታስፈልጋቸው ግራ ገባት፤ ተበሳጨች።
በመጨረሻም ቁስቋም ጐንደር ባሉ ሠዓሊዎች ሥራዎች አጌጠች።ምንትዋብ ከውስጥ የማርያምን ሥዕል አሥላ፣ ከፋይ ካባዋን በትንንሹ አስቀድዳ ዙርያውን አስለጠፈችበት::
ግንባታ መጠናቀቂያው ላይ ማስጌጫ ገንዘብ ሲያጥር፣ ሥራው እንዳይቋረጥ ምንትዋብ ከራሷ ወርቅ፣ ቀለበቷ ሳይቀር፣ ሰጠች።አንድ ሰሞን ጐንደር “ጉድ” አለ፤ “እቴጌ የጣታቸው ቀለበት ሳይቀር ለቤተክሲያን ማሠሪያ ሰጡ” እያለ አደነቀ።
የቁስቋም ማርያም ግንባታ በሦስት ዓመት ውስጥ ተጠናቀቀ።
ታቦቷ በታላቅ በዓል ቋሚ ማደሪያዋ ስትገባ ሕዝቡ፣ “እሰይ! እሰይ!” አለ፣ አመሰገነ። ካህናቱ ምንትዋብንና ኢያሱን፣ “
ለማርያም ቁስቋምን
እንዳቆማችሁላት፣ ቤተመቅደሷንም ዐይናችሁ እንቅልፍ ሳያይ ደፋ ቀና
ብላችሁ እንደሠራችሁላት፣ ለናንተም ትቁምላችሁ። መንግሥታችሁን ታጥናላችሁ፤ አልጋችሁን ትጠብቅላችሁ” እያሉ መረቋቸው።
ምንትዋብ ከልጇ ጋር ቁስቋም ማርያምን ማደራጀት ላይ አተኮረች። አንድ ቀን፣ የየደብሩን ካህናትና ሊቃውንት ወርቅ ሰቀላ ሰበሰበቻቸው።
“እቴጌ ምን ሊሉን ነው?” እያሉ እርስ በእርስ ተጠያየቁ።
#ትኩሳት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
....ጧት ተነስቼ ቁርስ ከበላሁ በኋላ ከሲልቪ ቤት ወጥቼ ወደ
ሲቴ አመራሁ፡፡ ትላንት “ማታ ባህራም ኪሴ ውስጥ ያስቀመጠውን ወረቀት መንገድ ላይ አነበብኩት፡፡ ኒኮል የፃፈችለት ደብዳቤ ነው
«ውድ ባህራም
«እንዴት ልጀምር? አስቸጋሪ ነው። እወድሀለሁ፣ ከልቤ እወድሀለሁ። አሁን የምነግርህ ነገር የማልወድህ ሊያስመስለኝ
ይችላል። ግን እወድሀለሁ፤ ከልቤ አፈቅርሀለሁ
«ያለሬቮሉሽን መኖር አትችልም። ከኔ ጋር መኖር አትችልም። ስለዚህ እኔን ትተኸኝ መሄድ አለብህ
«እኔ ስለሪቮሉሽን በጭራሽ ሊገባኝ የማይችል ብዙ ብዙ ነገር
አለ። ለምሳሌ ደም ማፍሰስ። ብዙ ተከራክረንበታል፣ ታስታውሳለሁ::
ደጋግመህ አይገባሽም! ስለሪቮሉሽን በጭራሽ አይገቤሽም ብለኸኛል። እውነትክን ነው:: አይገባኝም። ግን በደምብ የገባኝ አንድ ነገር አለ። አንተ ያለ ሬቮሉሽንህ መኖር አትችልም። ስለዚህ መለያየት አለብን።
“ከዚህ ቀጥሎ የምነግርሀ ሊገባህ አይችልም። ስለዚህ እንዲገባህ ለማድረግ አትሞክር። ዝም ብለህ እመነው። ይኸው የማፈቅረው አንተን ነው። የተረገዘው ልጅ ግን ያንተ አይደለም። የሉልሰገድ ነው። ልነግርህ ሞክሬ ነበር። ብዙ ጊዜ ሞከርኩ፣ አቃተኝ፡፡ አሁንም
ቢሆን መነፅራሙ ጓደኛህ ባያግዘኝ ኖሮ አልችልም ነበር
አዝናለሁ:: ስላደረስኩብህ ሁሉ ችግር በጣም አዝናለሁ።
ብትችል በልብህ ይቅር በለኝ። ባትችል ጥላኝ፡፡ ብቻ ሂድና
ሬቮሉሽንህ ውስጥ ኑር። ደስታ ሊስጥህ የሚችል እሱ ብቻ ነው።
በሄድክበት ይቅናህ፡፡ ደህና ሁን።
ያንተ ኒኮል።
P S ልታገኘኝ አትሞክር። አታገኘኝም። ልሰናበትህ ባለመቻሌ አዝናለሁ። ግን ፊትህ ላይ ቂም ማየት እፈራለሁ። ደህና ሁን። ይህን ደብዳቢ ሶስት ጊዜ ደጋግሜ አነበብኩት፡፡ ኒኮል ለምን
ፃፈችው ይህን? ቀዳደድኩት። ቁርጥራጮቹን በተንኳቸው:: ሲቲ ሄጄ ገላዬን ታጥቤ፣ ልብሴን ቀይሬ ወደ ኒኮል ቤት ሄድኩ አልጋዋ ላይ ተጋድማ ሲጋራ እያጨሰች ሙዚቃ ትሰማለች ታቹን ነጭ ክሮሽ እንደ ሸማኔ ጥለት የከበበው ቡና አይነት ቀሚስ ለብሳለች። ስገባ ፈገግ እያለች
«እንኳን መጣህ! ጭር ብሎኝ ነበር» አለችኝ
ደህና ነሽ?
«ደህና ነኝ፡፡ በጣም ደህና ነኝ። ግን ሌላ ሰው ማየት
አልፈልግም። እባክህን በሩን ቆልፈው።
ቆልፌው ስመጣ፣ የተጋደመችበት አልጋ ላይ እንድቀሙጥ በእጇ አመለከተችኝ። ጥፍሮቿ ሀምራዊ ተቀብተው ያብለጨልጫሉ።
ተቀመጥኩ፣ አየሁዋት። በጣም የተለወጠች መሰለኝ፡፡ ከንፈሮቿ እንደ ጥፍርቿ ሀምራዊ መሳይ ቀለም ተቀብተዋል፡ ቅንድቦቿን ወደ ሰማያዊ የሚወስድ ጥቁር ቀለም አድምቋቸዋል፣ ከግምባሯ ንጣት ጋር ሲታዩ በጣም ያምራሉ። የአይኖቿ ቆዳ ልክ የአይኖቿን
የሚመስል ውሀ እረንጓዴ ኩል ተቀብቶ፣ አይኖቿ ውስጥ ተነክሮ
የወጣ ይመስላል። ከመጠን በላይ አምሮባታል። ከጥንታዊት
ግብፃዊት ጋር ያለሁ መሰለኝ። ፀጉሯ እንደ ድሮው አመዳም
አይደለም፡ ንፁህ ቡናማ ቀለም ተነክሯል
«ምን ነካሽ?» አልኳት
«ምነው?»
«እንደዚህ የምታምሪ አይመስለኝም ነበር»
"Merci
«እውነት ግን ምንድነው?» አልኳት
«እንደዚህ ነኝ፡፡ ሳዝን ሰው እንዲያውቅብኝ አልፈልግም። አሁን
ያዘንኩ እመስላለሁ?»
በጭራሽ
«ለዚህ ነው አይኔንም የተኳልኩት፣ ፀጉሬንም የተነከርኩት»
«አዝነሻል?»
«እንደ ዛሬም አዝኜ አላውቅ፡፡ ሲሄድ ደህና ዋል አለህ?»
«አዎን»
የፃፍኩለትን አሳየህ?»
«አዎን፡፡ ለምን ፃፍሽው?»
«እንዴት እንደፃፍኩት ልንገርህ?»
«ንገሪኝ»
«ከትላንት ወድያ ማታ፣ እንደዚህ ተጋድሜ ሙዚቃ ስሰማ፣
አንድ ሰው መጣ፡ መልኩ ሰው ይመስላል እንጂ እንደኔና እንዳንተ
ህዋሳቱ ውስጥ ደም እንደሚፈስ ልምልልህ አልችልም። ምናልባት
ከነሀስ የተሰራ ሰው ሊሆንም ይችላል። ረዥም ቀጭን ነው፡ መነፅር ያረጋል። ግምባር የለውም፡ ከአይኑ ቀጥሎ አናቱ ይመጣል፡፡ ድምፁ ወፍራም ከመሆኑ የተነሳ ከሆዱ እንጂ ከጉሮሮው የሚወጣ
አይመስልም»
«ጠልተሽዋል እ?»
«መጥላት አይደለም፡፡ ፈራሁት። ቀፈፈኝ፡፡ አየህ፣ ገባና
በወፍራም ድምፁ
ኮል ማለት እርስዎ ነዎት?» አለኝ
ነኝ» አልኩት
“ጥሩ። እኔ ከኢራን ኮሙኒስት ፓርቲ ተልኬ የመጣሁ ነኝ
«ታድያ እኔ ከኢራን ኮሙኒስት ፓርቲ ምን አለኝ?
«እርስዎ አይናገሩ፡፡ ጊዜ የለኝም» አለኝ፡፡ ድምፁ በጭራሽ
አይለዋወጥም፡፡ ምንም ነገር ሲናገር በዚያው በወፍራም ድምፅ ነው
“የኢራን ኮሙኒስት ፓርቲ ባህራምን ይፈልገዋል፡፡ በጣም
ይፈልገዋል። እኔን ፓርቲው ልኮኛል። ከትእዛዝ ጋር፡፡ ወያም
ባህራምን ይዘኸው ና፣ ወይም ገድለኸው ተመለስ ተብያለህ
ግደለው? ለምን?» አልኩት
ቀላል ምክንያት፡፡ የኛን ምስጢር ያውቃል፡፡ ምስጢራችንን
በሙሉ ያውቃል፡፡ ስለዚህ፣ ወይም ከኔ ጋር ይምጣል፡ ወይም
ይሞታል። ሌላ ምርጫ የለም፡፡ ግን አንድ ነገር አለ» አለኝ
ምን?»
ባህራም አልመጣም የሚለው በእርስዎ ምክንያት ነው:: እርስዎ
ባይኖሩ ይመጣል፡፡ ስለዚህ እርስዎ እንዳይኖሩ ማድረግ፡፡»
ሆዱ እየፈራ፤ «እንዴት?» አልኩት
«መግደል» አለኝና፣ ከኪሱ አንድ የታጠፈ ጩቤ አወጣ፡፡ ጫን
ሲለው ጩቤው እንደ ብልጭታ ክፍት አለ ሻህን ልግደለው!' አለኝና፤ ያንን የኢራን
ስእል አመለከተኝ፡፡ ባህራም ነው እዚያ የለጠፈው፡፡ ልተኛ ስልና ልነሳ ስል፣ ሻህ እንዲታየኝ እፈልጋለሁ ብሎ ሰቀለው::»
ግድግዳው ላይ የኢራን ሻህ የጦር ጠቅላይ አዛዥ የማእረግ
ልብሱን ለብሶ ቆሞ በከለር የተነሳው ትልቅ ፎቶ አለ
"ለምሳሌ ሻህ እርስዎ ነዎት። ጉሮሮውን ይመልከተቱ" አለና
ጩቤዋን ወረወራት። የሻህ ጉሮሮ ላይ ስክት አለች። ሰውየው ወደ
ስእሉ ሄዶ ጩቤውን ነቀለና አጥፎ ኪሱ ከተተ መንገድ ላይ እርስዎ ሲራመዱ ወይም ሲሮጡ እኔ በፈጣን መኪና እየሄድኩ ጩቤ ብወረውር፣ ጉሮሮዎትን እልስተውም፡፡ ገባዎት?» አለኝ። በድምፁ ሊያስፈራራኝ በጭራሽ አልሞከረም፡ ልክ የጂኦሜትሪ ፕሮብሌም እንደሚያስረዳኝ ያህል ነበር ገባኝ» አልኩት። እንደዚያን ጊዜ ፈርቼ አላውቅም
«ለባህራም ይንገሩት»
«ምን ብዩ?»
«ያረገዝኩት ካንተ አይደለም፣ ይበሉት
«ታድያ ከማን ነው ልበለው?»
« እንደፈለጉ። ለምሳሌ እጀምሺድ ወይም ከሉልሰገድ ነው
ሊሉት ይችላሉ፡፡ እነሱን ሊጠይቃቸው አይችልም»
«እሺ» አልኩና ደብዳቤውን ፃፈኩ። አጣጥፎ ኪሱ ሲከተው
«ባሀራም ይህንን ካነበበ በኋላም ከርስዎ ጋር መሄድ ባይፈቅድስ?»
አልኩት
«እምቢ አይልም»
«ቢልስ?»
«እገድለዋለሁ። ደህና እደሩ» አለኝና ወጣ። እንደሱ ያለ
ከሰውነት የራቀ ሰው አጋጥሞኝ አያውቅም
ኒኮል ዝም አለች፡፡ ዝም ብዬ እየኋት። በጣም ታምራለች።
ውሀ እረንጓዴ ኩሏና ሀምራዊ የከንፈር ቀለሟ የፈርኦን ዘመን
ግብፃዊት አስመስሏታል። ሳቅ አለች
«ምነው ትኩር ብለህ ታየኛለህ?»
«አማርሽኝ» አልኳት። ውስጡን ደነገጥኩ። እንደዚህ ለማለት
አላሰብኩም ነበር። ውሀ አረንጓዴ ቆዳ ሽፍን ግልጥ በሚያደርጋቸው
ውህ እረንጓዴ እይኖቿ አየችኝ፡፡ ሀምራዊ ከናፍሯ በፈገግታ
ተላቀቁ። እጄን ጉልበቷ ላይ አሳረፍኩ፣ አልከለከለችኝም
«ጫማዬን ላወልቅ ነው» አልኳት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
....ጧት ተነስቼ ቁርስ ከበላሁ በኋላ ከሲልቪ ቤት ወጥቼ ወደ
ሲቴ አመራሁ፡፡ ትላንት “ማታ ባህራም ኪሴ ውስጥ ያስቀመጠውን ወረቀት መንገድ ላይ አነበብኩት፡፡ ኒኮል የፃፈችለት ደብዳቤ ነው
«ውድ ባህራም
«እንዴት ልጀምር? አስቸጋሪ ነው። እወድሀለሁ፣ ከልቤ እወድሀለሁ። አሁን የምነግርህ ነገር የማልወድህ ሊያስመስለኝ
ይችላል። ግን እወድሀለሁ፤ ከልቤ አፈቅርሀለሁ
«ያለሬቮሉሽን መኖር አትችልም። ከኔ ጋር መኖር አትችልም። ስለዚህ እኔን ትተኸኝ መሄድ አለብህ
«እኔ ስለሪቮሉሽን በጭራሽ ሊገባኝ የማይችል ብዙ ብዙ ነገር
አለ። ለምሳሌ ደም ማፍሰስ። ብዙ ተከራክረንበታል፣ ታስታውሳለሁ::
ደጋግመህ አይገባሽም! ስለሪቮሉሽን በጭራሽ አይገቤሽም ብለኸኛል። እውነትክን ነው:: አይገባኝም። ግን በደምብ የገባኝ አንድ ነገር አለ። አንተ ያለ ሬቮሉሽንህ መኖር አትችልም። ስለዚህ መለያየት አለብን።
“ከዚህ ቀጥሎ የምነግርሀ ሊገባህ አይችልም። ስለዚህ እንዲገባህ ለማድረግ አትሞክር። ዝም ብለህ እመነው። ይኸው የማፈቅረው አንተን ነው። የተረገዘው ልጅ ግን ያንተ አይደለም። የሉልሰገድ ነው። ልነግርህ ሞክሬ ነበር። ብዙ ጊዜ ሞከርኩ፣ አቃተኝ፡፡ አሁንም
ቢሆን መነፅራሙ ጓደኛህ ባያግዘኝ ኖሮ አልችልም ነበር
አዝናለሁ:: ስላደረስኩብህ ሁሉ ችግር በጣም አዝናለሁ።
ብትችል በልብህ ይቅር በለኝ። ባትችል ጥላኝ፡፡ ብቻ ሂድና
ሬቮሉሽንህ ውስጥ ኑር። ደስታ ሊስጥህ የሚችል እሱ ብቻ ነው።
በሄድክበት ይቅናህ፡፡ ደህና ሁን።
ያንተ ኒኮል።
P S ልታገኘኝ አትሞክር። አታገኘኝም። ልሰናበትህ ባለመቻሌ አዝናለሁ። ግን ፊትህ ላይ ቂም ማየት እፈራለሁ። ደህና ሁን። ይህን ደብዳቢ ሶስት ጊዜ ደጋግሜ አነበብኩት፡፡ ኒኮል ለምን
ፃፈችው ይህን? ቀዳደድኩት። ቁርጥራጮቹን በተንኳቸው:: ሲቲ ሄጄ ገላዬን ታጥቤ፣ ልብሴን ቀይሬ ወደ ኒኮል ቤት ሄድኩ አልጋዋ ላይ ተጋድማ ሲጋራ እያጨሰች ሙዚቃ ትሰማለች ታቹን ነጭ ክሮሽ እንደ ሸማኔ ጥለት የከበበው ቡና አይነት ቀሚስ ለብሳለች። ስገባ ፈገግ እያለች
«እንኳን መጣህ! ጭር ብሎኝ ነበር» አለችኝ
ደህና ነሽ?
«ደህና ነኝ፡፡ በጣም ደህና ነኝ። ግን ሌላ ሰው ማየት
አልፈልግም። እባክህን በሩን ቆልፈው።
ቆልፌው ስመጣ፣ የተጋደመችበት አልጋ ላይ እንድቀሙጥ በእጇ አመለከተችኝ። ጥፍሮቿ ሀምራዊ ተቀብተው ያብለጨልጫሉ።
ተቀመጥኩ፣ አየሁዋት። በጣም የተለወጠች መሰለኝ፡፡ ከንፈሮቿ እንደ ጥፍርቿ ሀምራዊ መሳይ ቀለም ተቀብተዋል፡ ቅንድቦቿን ወደ ሰማያዊ የሚወስድ ጥቁር ቀለም አድምቋቸዋል፣ ከግምባሯ ንጣት ጋር ሲታዩ በጣም ያምራሉ። የአይኖቿ ቆዳ ልክ የአይኖቿን
የሚመስል ውሀ እረንጓዴ ኩል ተቀብቶ፣ አይኖቿ ውስጥ ተነክሮ
የወጣ ይመስላል። ከመጠን በላይ አምሮባታል። ከጥንታዊት
ግብፃዊት ጋር ያለሁ መሰለኝ። ፀጉሯ እንደ ድሮው አመዳም
አይደለም፡ ንፁህ ቡናማ ቀለም ተነክሯል
«ምን ነካሽ?» አልኳት
«ምነው?»
«እንደዚህ የምታምሪ አይመስለኝም ነበር»
"Merci
«እውነት ግን ምንድነው?» አልኳት
«እንደዚህ ነኝ፡፡ ሳዝን ሰው እንዲያውቅብኝ አልፈልግም። አሁን
ያዘንኩ እመስላለሁ?»
በጭራሽ
«ለዚህ ነው አይኔንም የተኳልኩት፣ ፀጉሬንም የተነከርኩት»
«አዝነሻል?»
«እንደ ዛሬም አዝኜ አላውቅ፡፡ ሲሄድ ደህና ዋል አለህ?»
«አዎን»
የፃፍኩለትን አሳየህ?»
«አዎን፡፡ ለምን ፃፍሽው?»
«እንዴት እንደፃፍኩት ልንገርህ?»
«ንገሪኝ»
«ከትላንት ወድያ ማታ፣ እንደዚህ ተጋድሜ ሙዚቃ ስሰማ፣
አንድ ሰው መጣ፡ መልኩ ሰው ይመስላል እንጂ እንደኔና እንዳንተ
ህዋሳቱ ውስጥ ደም እንደሚፈስ ልምልልህ አልችልም። ምናልባት
ከነሀስ የተሰራ ሰው ሊሆንም ይችላል። ረዥም ቀጭን ነው፡ መነፅር ያረጋል። ግምባር የለውም፡ ከአይኑ ቀጥሎ አናቱ ይመጣል፡፡ ድምፁ ወፍራም ከመሆኑ የተነሳ ከሆዱ እንጂ ከጉሮሮው የሚወጣ
አይመስልም»
«ጠልተሽዋል እ?»
«መጥላት አይደለም፡፡ ፈራሁት። ቀፈፈኝ፡፡ አየህ፣ ገባና
በወፍራም ድምፁ
ኮል ማለት እርስዎ ነዎት?» አለኝ
ነኝ» አልኩት
“ጥሩ። እኔ ከኢራን ኮሙኒስት ፓርቲ ተልኬ የመጣሁ ነኝ
«ታድያ እኔ ከኢራን ኮሙኒስት ፓርቲ ምን አለኝ?
«እርስዎ አይናገሩ፡፡ ጊዜ የለኝም» አለኝ፡፡ ድምፁ በጭራሽ
አይለዋወጥም፡፡ ምንም ነገር ሲናገር በዚያው በወፍራም ድምፅ ነው
“የኢራን ኮሙኒስት ፓርቲ ባህራምን ይፈልገዋል፡፡ በጣም
ይፈልገዋል። እኔን ፓርቲው ልኮኛል። ከትእዛዝ ጋር፡፡ ወያም
ባህራምን ይዘኸው ና፣ ወይም ገድለኸው ተመለስ ተብያለህ
ግደለው? ለምን?» አልኩት
ቀላል ምክንያት፡፡ የኛን ምስጢር ያውቃል፡፡ ምስጢራችንን
በሙሉ ያውቃል፡፡ ስለዚህ፣ ወይም ከኔ ጋር ይምጣል፡ ወይም
ይሞታል። ሌላ ምርጫ የለም፡፡ ግን አንድ ነገር አለ» አለኝ
ምን?»
ባህራም አልመጣም የሚለው በእርስዎ ምክንያት ነው:: እርስዎ
ባይኖሩ ይመጣል፡፡ ስለዚህ እርስዎ እንዳይኖሩ ማድረግ፡፡»
ሆዱ እየፈራ፤ «እንዴት?» አልኩት
«መግደል» አለኝና፣ ከኪሱ አንድ የታጠፈ ጩቤ አወጣ፡፡ ጫን
ሲለው ጩቤው እንደ ብልጭታ ክፍት አለ ሻህን ልግደለው!' አለኝና፤ ያንን የኢራን
ስእል አመለከተኝ፡፡ ባህራም ነው እዚያ የለጠፈው፡፡ ልተኛ ስልና ልነሳ ስል፣ ሻህ እንዲታየኝ እፈልጋለሁ ብሎ ሰቀለው::»
ግድግዳው ላይ የኢራን ሻህ የጦር ጠቅላይ አዛዥ የማእረግ
ልብሱን ለብሶ ቆሞ በከለር የተነሳው ትልቅ ፎቶ አለ
"ለምሳሌ ሻህ እርስዎ ነዎት። ጉሮሮውን ይመልከተቱ" አለና
ጩቤዋን ወረወራት። የሻህ ጉሮሮ ላይ ስክት አለች። ሰውየው ወደ
ስእሉ ሄዶ ጩቤውን ነቀለና አጥፎ ኪሱ ከተተ መንገድ ላይ እርስዎ ሲራመዱ ወይም ሲሮጡ እኔ በፈጣን መኪና እየሄድኩ ጩቤ ብወረውር፣ ጉሮሮዎትን እልስተውም፡፡ ገባዎት?» አለኝ። በድምፁ ሊያስፈራራኝ በጭራሽ አልሞከረም፡ ልክ የጂኦሜትሪ ፕሮብሌም እንደሚያስረዳኝ ያህል ነበር ገባኝ» አልኩት። እንደዚያን ጊዜ ፈርቼ አላውቅም
«ለባህራም ይንገሩት»
«ምን ብዩ?»
«ያረገዝኩት ካንተ አይደለም፣ ይበሉት
«ታድያ ከማን ነው ልበለው?»
« እንደፈለጉ። ለምሳሌ እጀምሺድ ወይም ከሉልሰገድ ነው
ሊሉት ይችላሉ፡፡ እነሱን ሊጠይቃቸው አይችልም»
«እሺ» አልኩና ደብዳቤውን ፃፈኩ። አጣጥፎ ኪሱ ሲከተው
«ባሀራም ይህንን ካነበበ በኋላም ከርስዎ ጋር መሄድ ባይፈቅድስ?»
አልኩት
«እምቢ አይልም»
«ቢልስ?»
«እገድለዋለሁ። ደህና እደሩ» አለኝና ወጣ። እንደሱ ያለ
ከሰውነት የራቀ ሰው አጋጥሞኝ አያውቅም
ኒኮል ዝም አለች፡፡ ዝም ብዬ እየኋት። በጣም ታምራለች።
ውሀ እረንጓዴ ኩሏና ሀምራዊ የከንፈር ቀለሟ የፈርኦን ዘመን
ግብፃዊት አስመስሏታል። ሳቅ አለች
«ምነው ትኩር ብለህ ታየኛለህ?»
«አማርሽኝ» አልኳት። ውስጡን ደነገጥኩ። እንደዚህ ለማለት
አላሰብኩም ነበር። ውሀ አረንጓዴ ቆዳ ሽፍን ግልጥ በሚያደርጋቸው
ውህ እረንጓዴ እይኖቿ አየችኝ፡፡ ሀምራዊ ከናፍሯ በፈገግታ
ተላቀቁ። እጄን ጉልበቷ ላይ አሳረፍኩ፣ አልከለከለችኝም
«ጫማዬን ላወልቅ ነው» አልኳት
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...ማሪየስ በመጨረሻ ስለናፖሊዮን ጦር ሠራዊት ነበር ከሚያነብበው::መፅሀፍ አልፎ አልፎ የአባቱ ስም ያያል የንጉሱ ስም ግን በየምራፍ ይጠቀሳል
አገሪትዋ በሙሉ ለንጉሱ እንደተሰራች ተደርጎ ነበር ፅሁፉ የቀረቡት እንደ መአበል ከውስጥ አካሉ አንድ ነገር ሲያብጥ ተሰማው:: አባቱ በአጠገቡ አልፎ በሹክሹክታ ያነጋገረው መሰለው::
ተደርጎ ነበር ጸሐፉ የቀረበው:: እንደ ማዕበል ከውስጥ አካለ አንድ ነገር ሲያብጥ ተሰማው
አባቱ በአጠገቡ አልፎ በሽኩክታ ያነጋገረው መሰለው የከበሮ፤ የመድፍ፤ የመለከት፤ በሩቁ የሚሰማ የሠራዊትና የፈረስ ኮቴ
ከፊቱ ድቅን አለ፡፡ ማንበቡን ትቶ በመስኮት ወደ ሰማይ ተመለከተ::
የሚያብለጨልጭ ነገር ከሰማይ ተወርውሮ የሚያነብበው መጽሐፍ ውስጥ የወደቀ መሰለው፡፡ ፍርሃት፣ ፍርሃት አለው፡፡ የሚተነፍሰው በግድ ሆነ::
ሰውነቱ ራደ:: ማን እንዳዘዘውና ምን እንዳስገደደው ሳይታወቀው
ከተቀመጠበት ብድግ አለ፡፡ ወደ መስኮቱ ሄዶ እጆቹን ወደ ውጭ ዘረጋ::
በጨለማ ሰማዩንና ምድሩን በዓይኑ ማተረ፡፡ ዓለም ጸጥ ረጭ ብላለች::በድንገት «እድሜ ለንገሠ ነገሥቱ» ሲል ጮኸ፤ በማፌዝ፡፡
ከዚያን እለት ጀምሮ ማሪየስ ጨርሶ ተለወጠ፡፡ ለአባቱ ንጉሠ ነገሥቱ እንደ ተወዳጅ ካፕቴን እንደነበሩ ተገነዘበ፡፡ ተወዳጁን ካፕቴን ያደንቅና ለእርሱም ሕይወቱን አሳልፎ እንደሰጠ ታወቀው:: ለማሪየስ ናፖሊዮን ማለት ግን ከዚህ የበለጠ ነበር፡፡ የወደፊት ተስፋ ፧ የድምበር
መከታና የፈረንሳይ አለኝታ ከናፖሊዮን ቦናፓርቴ ላይ አየ:: ናፖሊዮን ጨካኝ ሊሆን ይችላል፡፡ ግን እርሱ መታየት ያለበት ከሪፑብሊክ ምስረታ፧
ከለውጥ፤ ከአብዮት ጋር ነው:: ናፖሊዮን የሕዝብ ሰው እንደሆነ አመነ፡፡አባቱ ጦር ሜዳ የተዋጋውና ሕይወቱን አሳልፎ የሰጠው ለሰዎች እኩልነትና "
ለሪፑብሊኩ ምሥረታ እንደሆነ በፍጹም ልቡ ተቀበለ፡፡ የዚህ ተቃዋሚ የሆነውን የቡርዣን አገዛዝ ጠላ፡፡
አያቱ መሴይ ጊልኖርማንድ የሚደግፉት እርሱ የጠላውን ነበር፡፡ በዚህ የተነሣ በአያትና በልጅ ልጅ መካከል አለመግባባት ተፈጠረ:: ከነአካቴው አያቱ ከአባቱ ጋር ያለያዩት በዚህ መሠረታዊ የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት እንደሆነ በተገነዘበ ጊዜ አያቱን በጣም ጠላቸው:: በዚህ በግል ጥቅም በታወሩ ሰው ምክንያት ርህራሄ በተለየው ጭካኔ ልጅ ሊያፈቅረው ከሚችል አባቱ፧ አባት ከሚወደው ልጁ መለያየታቸው እጅግ በጣም አሳዘነው። ማሪየስ ከአባቱ ጋር የተለያየው በዚህ ምክንያት መሆኑን ባወቀ ጊዜ ለአባቱ
ያለው ፍቅር ሲገነፍል ለአያቱ የነበረው ጥላቻ ግን ከደሙ ጋር ተዋሃደ። አባቱ ማለት ለሰዎች ደኅንነት፤ ለሰዎች እኩልነትና ለትክክለኛ ፍርድ የቆመ ታላቅ ሰው ማለት ሲሆን፧ መሴይ ጊልኖርማንድ ማለት ደግሞ
በግል ጥቅም የታወሩ፤ ለጥቂት ሰዎች ደኅንነት ጥብቅና የቆመና እንደ መዥገር በሰዎች ደም የሰቡ ሰው ናቸው።ስለዚህ ቅራኔያቸው የሚታረቅ አልሆነም፡፡ ይህም የአያቱን ዓይን ላለማየት አስወሰነው:: ሰበብ አስባብ
እየፈጠረ ከቤት ይጠፋ ጀመር፡፡ አክስቱ ድንገት አግኝተው የት እንደነበር ሲጠይቁት «ጥናት በዝቶብኝ ከጓደኞቼ ጋር ሳጠና፧ ፈተና ስለነበረብን ከአንድ ጓደኛዬ ቤት ውስጥ ተዘግተን ስናጠና፧ ፍርድ ቤት ሄደን ስለፍርድ
አሰጣጥ ትምህርት ስንቀስም፤ አሁን ትምህርቴን ወደማጠናቀቁ ስለሆነ የመመረቂያ ጽሑፍ መጻፍ ስለጀመርሁ ቤተ መጻሕፍት ውስጥ ስለምውል»እያለ ሌላም፤ ሌላም መልስ ይሰጣቸዋል::
አያቱ ግን «ማሪየስ ፍቅር ይዞት ፍቅረኛው እያንከራተተችው ነው»
በሚል መደምደሚያ ላይ ስለደረሰና እርሳቸውም በዚህ ዓይነት ገጠመኝ ያለፉ ስለሆነ ብዙም አልተጨነቁበትም:: ሆኖም ማሪየስ እንኳን ቀን ሊገባ አድሮም የሚመጣበት ጊዜ በረከተ።
አንድ ቀን ‹‹የት ሊሄድ ይችላል?» ሲሉ አክስቱ ጠየቁ::
ማሪየስ አባቱ በጻፈለት ማስታወሻ መሠረት ተናድዬን ለመጠየቅ
ሞንትፌርሜ ሄዶአል፡፡ ከዚያም የቀድሞውን የዋተርሉ ሃምሣ አለቃ ፧የዛሬው የሆቴል ቤት ጌታ ሚስተር ቴናድዬ ከስሮ ሆቴል ቤቱ ስለተዘጋ ፍለጋው አራት ቀን ወሰደበት።
በእርግጥ ፈሩን እየለቀቀ ነው» አሉ አያቱ እንደዚያ ሲቆይ፡፡
በጥቁር ጨርቅ የተንጠለጠለ አንድ ነገር ከሸሚዞ ስር ከአንገቱ ላይ ማሰሩን አባትና ልጅ ቀደም ሲል ማየታቸውን አንስተው ተወያዩ::
ማሪየስ ለመጀመሪያ ጊዜ ከፓሪስ ከተማ ሲጠፋ የሄደው ወደ ቬርኖን ነበር። ቬርኖን ከተማ ሄዶ በጠፋ ቁጥር አያቱ «ተኝቶ ነው» ይላሉ፡፡
አንድ ቀን ጠዋት ማሪየስ ከቬርኖን ተመልሶ ከቤት ሲገባ አያቱ
ይሰሙታል፡፡ ከሁለት ቀን የአሳብ ጭንቀትና መንገድ በኋላ ስለነበረ
የተመለሰው በጣም ደክሞታል:: ብዙ እንቅልፍ ስላላገኘ ቶሎ ብሎ ለአንድ ሰአት እንኳን ቢሆን ለመተኛት ይፈልጋል፡፡ ኮቱንና አንገቱ ላይ ያጠለቀውን
አውልቆ አልጋው ላይ ወረወረ፡፡ እንዳይረበሽ ከመዋኛ ሥፍራ አጠገብ በሚገኝ ክፍል ውስጥ ለመተኛት ፈልጎ ወደዚያው ሄደ:: ጤነኛ የሆነ ሽማግሌዎች በጠዋት መንቃታቸው የተለመደ ስለሆነ መሴይ ጊልኖርማንድ በዚያን እለት በጠዋት በመንቃታቸው ማርየስ ከውጭ ሲገባ ሰሙት ካልጋቸው ተነስተው በሽማግሌ እግር ቶሉ ቶሉ በመራመድ የማሪየስ የመኝታ ቤት ወደነበረበት ክፍል ወደ ፎቅ ወጡ:: የወጡት ሊያቅፉና
ሊስሙት፧ በዚያውም ከየት እንደሚመጣ ሊጠይቁት ነበር፡፡ ግን ከክፍሉ ሲደርሱ ማሪየስ አልነበረም:: አልጋው እንደተነጠፈ ነው:: ኮቱና አንገቱ ላይ የሚያንጠለጥለው በጥቁር ሪሪበ የታሠረው ነገር ከአልጋው ላይ
ተቀምጠዋል፡፡
«ይህቺ ጥሩ ናት» አሉ መሴይ ጊልኖርማንድ::
ልጃቸው ወደ ነበሩበት ወደ ምድር ቤት ሳሉን ወረዱ:: እህትየው
ተነስተው ኖሮ ከሳሉን ቤት ቁጭ ብለው ጥልፍ ይጠልፋሉ፡፡ መሴይ
ጊልኖርማንድ በአንድ እጃቸው የማሪየስን ኮት በሌላ እጃቸው አንገቱ ላይ የሚያንጠለጥለውን ነገር ይዘዋል::
«ድል ይሉሻል ይኼ ነው ፤ ምስጢሩን ሳንደርስበት አንቀርም::
መጨረሻውን እንደርስበታለን፤ ይኸውልሽ ጉዳ» ሲሉ ጮሁ ፤ ልጃቸው ከነበሩበት ክፍል እንደገቡ፡፡
በሪበን የተንጠለጠለው ነገር የሳጥን ቅርጽ ያለውና የሚከፈት ነው ሽማግሌው ሳይከፍቱት አተኩረው ተመለከቱት::
‹‹አባባ ፧ ክፈተውና እንየው» አለች ልጃቸው::
ሳጥኑን ጫን ሲሉት ይከፈታል፡፡ በውስጠ ያገኙት ከብጣሽ ወረቀት
በስተቀር ሌላ ነገር አልነበረም::
«ከአንድዋ ፍቅረኛው ወደ ሌላዋ» አለ መሴይ ጊልኖርማንድ በኃይል
እየሳቀ:: «ምን እንደሆነ አውቀዋለሁ ፤ የፍቅር ደብዳቤ!››
‹‹ይሆናል፧ ይነበባ!» አለች የማሪየስ አክስት::
መነጽርዋን አደረገች፡፡ ወረቀቱን ዘረጋጋችና አነበበችው::
«ለምወድህ ልጄ ፣ ዋተርሉ ጦር ሜዳ ላይ በተደረገው ጦርነት
ስለፈጸምኩት ጀብዱ የባሮንነት ማዕረግ ተሰጥቶኝ ነበር፡፡ ማዕረጉን በደሜ የዋጀሁት ስለሆነ ለልጄ ማውረስ እችላለሁ:: እኔ አሁን ማዕረጉ ይገባዋል ወይም አይገባውም ብዬ መናገር የለብኝም:: ››
የአባትና የልጅ ፊት እንዴት እንደተለዋወጠና ስሜታቸው ምን እንደነበር መግለጽ ያዳግታል:: የሞት ጥላ እንደተጋረደበት ሰው በብሽቀት ደነዘዙ፤ እብድ ሆኑ:: በንዴት ሰከኑ:: ዝም ዝም ተባባሉ፡፡ በመጨረሻ መሴይ ጊልኖርማንድ እርስ በራሱ እንደሚናገር ሰው እጅግ ዝቅ ባለ ድምፅ ተናገሩ::
‹‹የዚያ ጦረኛ የእጅ ጽሑፍ ነው::»
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...ማሪየስ በመጨረሻ ስለናፖሊዮን ጦር ሠራዊት ነበር ከሚያነብበው::መፅሀፍ አልፎ አልፎ የአባቱ ስም ያያል የንጉሱ ስም ግን በየምራፍ ይጠቀሳል
አገሪትዋ በሙሉ ለንጉሱ እንደተሰራች ተደርጎ ነበር ፅሁፉ የቀረቡት እንደ መአበል ከውስጥ አካሉ አንድ ነገር ሲያብጥ ተሰማው:: አባቱ በአጠገቡ አልፎ በሹክሹክታ ያነጋገረው መሰለው::
ተደርጎ ነበር ጸሐፉ የቀረበው:: እንደ ማዕበል ከውስጥ አካለ አንድ ነገር ሲያብጥ ተሰማው
አባቱ በአጠገቡ አልፎ በሽኩክታ ያነጋገረው መሰለው የከበሮ፤ የመድፍ፤ የመለከት፤ በሩቁ የሚሰማ የሠራዊትና የፈረስ ኮቴ
ከፊቱ ድቅን አለ፡፡ ማንበቡን ትቶ በመስኮት ወደ ሰማይ ተመለከተ::
የሚያብለጨልጭ ነገር ከሰማይ ተወርውሮ የሚያነብበው መጽሐፍ ውስጥ የወደቀ መሰለው፡፡ ፍርሃት፣ ፍርሃት አለው፡፡ የሚተነፍሰው በግድ ሆነ::
ሰውነቱ ራደ:: ማን እንዳዘዘውና ምን እንዳስገደደው ሳይታወቀው
ከተቀመጠበት ብድግ አለ፡፡ ወደ መስኮቱ ሄዶ እጆቹን ወደ ውጭ ዘረጋ::
በጨለማ ሰማዩንና ምድሩን በዓይኑ ማተረ፡፡ ዓለም ጸጥ ረጭ ብላለች::በድንገት «እድሜ ለንገሠ ነገሥቱ» ሲል ጮኸ፤ በማፌዝ፡፡
ከዚያን እለት ጀምሮ ማሪየስ ጨርሶ ተለወጠ፡፡ ለአባቱ ንጉሠ ነገሥቱ እንደ ተወዳጅ ካፕቴን እንደነበሩ ተገነዘበ፡፡ ተወዳጁን ካፕቴን ያደንቅና ለእርሱም ሕይወቱን አሳልፎ እንደሰጠ ታወቀው:: ለማሪየስ ናፖሊዮን ማለት ግን ከዚህ የበለጠ ነበር፡፡ የወደፊት ተስፋ ፧ የድምበር
መከታና የፈረንሳይ አለኝታ ከናፖሊዮን ቦናፓርቴ ላይ አየ:: ናፖሊዮን ጨካኝ ሊሆን ይችላል፡፡ ግን እርሱ መታየት ያለበት ከሪፑብሊክ ምስረታ፧
ከለውጥ፤ ከአብዮት ጋር ነው:: ናፖሊዮን የሕዝብ ሰው እንደሆነ አመነ፡፡አባቱ ጦር ሜዳ የተዋጋውና ሕይወቱን አሳልፎ የሰጠው ለሰዎች እኩልነትና "
ለሪፑብሊኩ ምሥረታ እንደሆነ በፍጹም ልቡ ተቀበለ፡፡ የዚህ ተቃዋሚ የሆነውን የቡርዣን አገዛዝ ጠላ፡፡
አያቱ መሴይ ጊልኖርማንድ የሚደግፉት እርሱ የጠላውን ነበር፡፡ በዚህ የተነሣ በአያትና በልጅ ልጅ መካከል አለመግባባት ተፈጠረ:: ከነአካቴው አያቱ ከአባቱ ጋር ያለያዩት በዚህ መሠረታዊ የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት እንደሆነ በተገነዘበ ጊዜ አያቱን በጣም ጠላቸው:: በዚህ በግል ጥቅም በታወሩ ሰው ምክንያት ርህራሄ በተለየው ጭካኔ ልጅ ሊያፈቅረው ከሚችል አባቱ፧ አባት ከሚወደው ልጁ መለያየታቸው እጅግ በጣም አሳዘነው። ማሪየስ ከአባቱ ጋር የተለያየው በዚህ ምክንያት መሆኑን ባወቀ ጊዜ ለአባቱ
ያለው ፍቅር ሲገነፍል ለአያቱ የነበረው ጥላቻ ግን ከደሙ ጋር ተዋሃደ። አባቱ ማለት ለሰዎች ደኅንነት፤ ለሰዎች እኩልነትና ለትክክለኛ ፍርድ የቆመ ታላቅ ሰው ማለት ሲሆን፧ መሴይ ጊልኖርማንድ ማለት ደግሞ
በግል ጥቅም የታወሩ፤ ለጥቂት ሰዎች ደኅንነት ጥብቅና የቆመና እንደ መዥገር በሰዎች ደም የሰቡ ሰው ናቸው።ስለዚህ ቅራኔያቸው የሚታረቅ አልሆነም፡፡ ይህም የአያቱን ዓይን ላለማየት አስወሰነው:: ሰበብ አስባብ
እየፈጠረ ከቤት ይጠፋ ጀመር፡፡ አክስቱ ድንገት አግኝተው የት እንደነበር ሲጠይቁት «ጥናት በዝቶብኝ ከጓደኞቼ ጋር ሳጠና፧ ፈተና ስለነበረብን ከአንድ ጓደኛዬ ቤት ውስጥ ተዘግተን ስናጠና፧ ፍርድ ቤት ሄደን ስለፍርድ
አሰጣጥ ትምህርት ስንቀስም፤ አሁን ትምህርቴን ወደማጠናቀቁ ስለሆነ የመመረቂያ ጽሑፍ መጻፍ ስለጀመርሁ ቤተ መጻሕፍት ውስጥ ስለምውል»እያለ ሌላም፤ ሌላም መልስ ይሰጣቸዋል::
አያቱ ግን «ማሪየስ ፍቅር ይዞት ፍቅረኛው እያንከራተተችው ነው»
በሚል መደምደሚያ ላይ ስለደረሰና እርሳቸውም በዚህ ዓይነት ገጠመኝ ያለፉ ስለሆነ ብዙም አልተጨነቁበትም:: ሆኖም ማሪየስ እንኳን ቀን ሊገባ አድሮም የሚመጣበት ጊዜ በረከተ።
አንድ ቀን ‹‹የት ሊሄድ ይችላል?» ሲሉ አክስቱ ጠየቁ::
ማሪየስ አባቱ በጻፈለት ማስታወሻ መሠረት ተናድዬን ለመጠየቅ
ሞንትፌርሜ ሄዶአል፡፡ ከዚያም የቀድሞውን የዋተርሉ ሃምሣ አለቃ ፧የዛሬው የሆቴል ቤት ጌታ ሚስተር ቴናድዬ ከስሮ ሆቴል ቤቱ ስለተዘጋ ፍለጋው አራት ቀን ወሰደበት።
በእርግጥ ፈሩን እየለቀቀ ነው» አሉ አያቱ እንደዚያ ሲቆይ፡፡
በጥቁር ጨርቅ የተንጠለጠለ አንድ ነገር ከሸሚዞ ስር ከአንገቱ ላይ ማሰሩን አባትና ልጅ ቀደም ሲል ማየታቸውን አንስተው ተወያዩ::
ማሪየስ ለመጀመሪያ ጊዜ ከፓሪስ ከተማ ሲጠፋ የሄደው ወደ ቬርኖን ነበር። ቬርኖን ከተማ ሄዶ በጠፋ ቁጥር አያቱ «ተኝቶ ነው» ይላሉ፡፡
አንድ ቀን ጠዋት ማሪየስ ከቬርኖን ተመልሶ ከቤት ሲገባ አያቱ
ይሰሙታል፡፡ ከሁለት ቀን የአሳብ ጭንቀትና መንገድ በኋላ ስለነበረ
የተመለሰው በጣም ደክሞታል:: ብዙ እንቅልፍ ስላላገኘ ቶሎ ብሎ ለአንድ ሰአት እንኳን ቢሆን ለመተኛት ይፈልጋል፡፡ ኮቱንና አንገቱ ላይ ያጠለቀውን
አውልቆ አልጋው ላይ ወረወረ፡፡ እንዳይረበሽ ከመዋኛ ሥፍራ አጠገብ በሚገኝ ክፍል ውስጥ ለመተኛት ፈልጎ ወደዚያው ሄደ:: ጤነኛ የሆነ ሽማግሌዎች በጠዋት መንቃታቸው የተለመደ ስለሆነ መሴይ ጊልኖርማንድ በዚያን እለት በጠዋት በመንቃታቸው ማርየስ ከውጭ ሲገባ ሰሙት ካልጋቸው ተነስተው በሽማግሌ እግር ቶሉ ቶሉ በመራመድ የማሪየስ የመኝታ ቤት ወደነበረበት ክፍል ወደ ፎቅ ወጡ:: የወጡት ሊያቅፉና
ሊስሙት፧ በዚያውም ከየት እንደሚመጣ ሊጠይቁት ነበር፡፡ ግን ከክፍሉ ሲደርሱ ማሪየስ አልነበረም:: አልጋው እንደተነጠፈ ነው:: ኮቱና አንገቱ ላይ የሚያንጠለጥለው በጥቁር ሪሪበ የታሠረው ነገር ከአልጋው ላይ
ተቀምጠዋል፡፡
«ይህቺ ጥሩ ናት» አሉ መሴይ ጊልኖርማንድ::
ልጃቸው ወደ ነበሩበት ወደ ምድር ቤት ሳሉን ወረዱ:: እህትየው
ተነስተው ኖሮ ከሳሉን ቤት ቁጭ ብለው ጥልፍ ይጠልፋሉ፡፡ መሴይ
ጊልኖርማንድ በአንድ እጃቸው የማሪየስን ኮት በሌላ እጃቸው አንገቱ ላይ የሚያንጠለጥለውን ነገር ይዘዋል::
«ድል ይሉሻል ይኼ ነው ፤ ምስጢሩን ሳንደርስበት አንቀርም::
መጨረሻውን እንደርስበታለን፤ ይኸውልሽ ጉዳ» ሲሉ ጮሁ ፤ ልጃቸው ከነበሩበት ክፍል እንደገቡ፡፡
በሪበን የተንጠለጠለው ነገር የሳጥን ቅርጽ ያለውና የሚከፈት ነው ሽማግሌው ሳይከፍቱት አተኩረው ተመለከቱት::
‹‹አባባ ፧ ክፈተውና እንየው» አለች ልጃቸው::
ሳጥኑን ጫን ሲሉት ይከፈታል፡፡ በውስጠ ያገኙት ከብጣሽ ወረቀት
በስተቀር ሌላ ነገር አልነበረም::
«ከአንድዋ ፍቅረኛው ወደ ሌላዋ» አለ መሴይ ጊልኖርማንድ በኃይል
እየሳቀ:: «ምን እንደሆነ አውቀዋለሁ ፤ የፍቅር ደብዳቤ!››
‹‹ይሆናል፧ ይነበባ!» አለች የማሪየስ አክስት::
መነጽርዋን አደረገች፡፡ ወረቀቱን ዘረጋጋችና አነበበችው::
«ለምወድህ ልጄ ፣ ዋተርሉ ጦር ሜዳ ላይ በተደረገው ጦርነት
ስለፈጸምኩት ጀብዱ የባሮንነት ማዕረግ ተሰጥቶኝ ነበር፡፡ ማዕረጉን በደሜ የዋጀሁት ስለሆነ ለልጄ ማውረስ እችላለሁ:: እኔ አሁን ማዕረጉ ይገባዋል ወይም አይገባውም ብዬ መናገር የለብኝም:: ››
የአባትና የልጅ ፊት እንዴት እንደተለዋወጠና ስሜታቸው ምን እንደነበር መግለጽ ያዳግታል:: የሞት ጥላ እንደተጋረደበት ሰው በብሽቀት ደነዘዙ፤ እብድ ሆኑ:: በንዴት ሰከኑ:: ዝም ዝም ተባባሉ፡፡ በመጨረሻ መሴይ ጊልኖርማንድ እርስ በራሱ እንደሚናገር ሰው እጅግ ዝቅ ባለ ድምፅ ተናገሩ::
‹‹የዚያ ጦረኛ የእጅ ጽሑፍ ነው::»
#ሳቤላ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
...“ ኧረ እኔ እንጃ ጌታዬ እኔ ካፒቴን ቶርንን አንድ ጊዜ ብቻ ስለ ነበር ያየሁት አሁን ዐውቀዋለሁ ለማለት አልደፍርም " ይኸን ሰውዬ ላየውም ስለዚያኛው ሰውዬ የመጣልኝ ትዝታ የለም " ሰዉዬውን ሳየው ምንም አይቸው የማውቅም አልመሰለኝም "
ስለዚህ ሚስተር ካርላይል ከጆይስ ምንም ጠቃሚ ፍንጭ አላግኘም በበነጋው ኦትዌይ ቤተልን ፈልጎ አግኘው "
"ያ ከሔርበርት ቤተሰብ ጋር ያለፈው ካፒቴን ቶርን የሚባለውን ስው ደኅና አድርገህ ታውቀዋለህ ? አለው
“ አዎን! ሁለት ሰዓት ያህል ከሱ ጋር መቆየት በደንብ ለመተዋወቅ የሚበቃ ከሆነ በቀደም ሔርበርት ዘንድ ሔጄ ሳለ ሰውየው መጣ እዚያ ስናወጋ ብዙ ቆየን ግን ለምን ጠየቅኽኝ ?”
“ ያ አፊ ሆሊጆንን ያሳድድ የነበረው ቶርን የሚባለው እሱ ነው ከፈለግህ እውነቱን ልትነግረኝ ትችላለህ " "
ቤተል ድርቅ ብሎ ቀረ “ እንዴት ያለ እግር ያወጣ ውሸት ነው ! አለ
ቆይቶ ቆይቶ “ ይኸ ያ አይደለም አይደለም እንዴ የማን ቶርን ነው እሱ ?”
“ ዐውቀህ እያምታታህ ነው ቤተል " ከሆሊጆን ግድያ ጋር የተያያዘው ቶርን የሚባለው ሰው ይኸው አይደለም ?
ምን ሆንክብኝ ... ሚስተር ካርላይል እኔ ከአፊ ጋር የሚተዋወቅ ቶርን
የሚባል ሰው መኖሩን እንደማላውቅ ነግሬህ ነበር " ለምንድነው ቃሌ የማይታመነው? እኔ ቶርንን ከበቀደም በቀር አይቸው አላውቅም ካስፈለገ እምላለሁ” ብሎት ጥሎት ሔዶ
ቤተል የቶርንና የአፊ ስም ሲነሣበት ከዚህ በፊት እንዳዶፈደረግው ሁሎ አሁንም
መልኩ ተለዋወጠ አንድ ዐይነት ጭንቀት ሲፈጠርበት ታየ " ከዚህ ስምና ግድያ ጋር የተሳሰረ ምስጢር መኖሩን ለሚስተር ካርላይል ተሰማው " በግምት ምንም ማድረግ አልቻለም " የቤተል መልስም ፍንጭ አልሰጠውም » ከዚያ እሱም ወደ
ቢሮው ሲሔድ ቶም ሔርበትን አገኘውና ቶርን ከነሱ ጋር ብዙ ይሰነብት እንደሆነ ቢጠይቀው : ወዴፊት ካልመጣ በቀር ለአሁኑ ግን መሔዱን ነገረው "
ሚስተር ካርላይል ለራት ወደ ቤቱ ሲሔድ ሚስዝ ሔርን ለመጠየቅ አስመስሎ ወደ ዐፀዱ ጐራ አለ » ባርባራ የሚስተር ካርላይልን መልስ ለመስማት ልቧ ተንጠለጠለ ። ሚስዝ ሔርን አነጋግሮ ሲወጣ ተከትላው ወጣች ።
“ ምን ፍንጭ አገኘህ ?
“ ምንም የሚረባ ነገር አልተገኘም ሰውየውም ሒዷል ”
“ ሔደ! "
ባለፈው ምሽት ባርባራ ወደ ቤቷ እንደ ተመለሰች ሰውየውን ከቶም ሔርበት ጋር እንዴት ወደ ቤቱ እንደ ወሰዳቸው ኋላም ቶም ሔርበትን አግኝቶት ምን እንዳለውና ከቤተል ጋርም መነጋገሩን ሁሉ አጫወታት
“ምናልባት የነገሩን አዝማሚያ በመገመት ፈርቶ ይሆን የሔደው? አለችው "
አይመስለኝም መጀመሪያውንስ ለምን ይመጣ ኖሯል ?
ግን የተጠረጠረ መሆኑን የሚጠቁም ቃል አለመናገርህን እርግጠኛ ነህ ?
ምንም አልተናገርኩም ፡
ሰውየው ግን ምንድነው ?
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ጥቂት ዓታት ዐለፉ
ሰማህ ሚስተር ካርላይል እስኪ ቦታ ትለውጥ ለምላሌ ወደ ቤልጅግ ወይም ወደ ፈረንሳይ
ሊረዳት ይችላል ባሕር ጠረፎች ብትወስዳት ፡ በባሕሩ ውሃ ስትታጠብ በጣም ሊረዳት ይችላል።
“ ከቤት ርቃ መሔዱ ለሷ ደኅና ይመስልሃል ? ”
“ አዎን ይመስለኛል " አየህ ይህ ነው የምትለው የአካል ቀውስ ካለ 'በሕክምና መከታተል ስለሚገባ ቦታ መለወጡ ፡ አየር መቀየሩ ሁሉ አይታየኝም"ክስዊስ ተራሮች ቢወጡ ወይም ከዴንቨር ሸለቆ ቢወርዱ ዋጋ የለውም » እንደሷ ያለ የድካም ሰመመን ላለበት ግን አየርና ቦታ ለወጥ በጣም ይጠቅማል " ብርታቷን
በእንደዚህ ዐይነት ጥረቶች እያባበልክ ለመመለስ ከመሞክር በቀር ሌላ ምንም ማድረግ አይቻልም ”
“ እስኪ ከሷ ጋር ልምከርበት ”
“ እኔም ነግሬያት ነበር” አለ ዶክተር ማርቲን ፡ የሐሳቧ አቅራቢ : አልተቀበለችኝም በሽተኞቹ ሁልጊዜም ከቤታቸው መራቅ ደስ አይላቸውም መሔዷ ግን አስፈላጊ ነው።
ንግግሩ ስለ እመቤት ሳቤላ ነበር በአሁኑ ጊዜ በኢስት ሊን ሳቤላ ዊልያምና አርኪባልድ የሚባሉ ፡ የመጨረሻዉ የዐሥራ ሁለት ወር ልጅ የሆነ : ሦስት ልጆች
ደርሰዋል ሁለት ወር ያሀል ቀደም ብሎ ሳቤላ ክፉኛ ታማ ዳነች ግን ድቅቅ አድርጎ ስለ ለቀቃት ሰውነቷ አልጠነክር አለ ሚስተር ዌይንራይት ያላደረገው ጥረት
አልነበረም ግን ከመባስ በቀር ምንም አልተሻላትም በመጨረሻ ዶክተር ማርቲን ከሊንበራ ተጠርቶ መጣ እሱም ሁኔታውን አይቶ ያየርና የቦታ ለውጥ አዘዘ
ሳቤላ የሐኪሙን ትእዛዝ ለመቀበል በተለይ እስከ ፈረንሳይ ጠረፍ ለመሔድ አልፈቀደችም
በሚስተር ኬን ትርዒት ጊዜ ያየናት ሚስዝ ዱሲ ፓሪስ ላይ ዐሥራ ስምንት ወር ስትቀመጥ ለሳቤላ ሁለት ጊዜ ጽፋላት ነበር አሁን ደግሞ ወደ ቡሎኝሱር ሜር ሔዳ አንድ ሁለት ወር እንደምትቆይ ጻፈችላት » የሳቤላ እመቢታ የብቸኝነት ፍራቻ እንደሚሆን በመገመት አሁን ግን ዱሲ ካለችላት እሺ ማለት እንዳለባት
ሐኪሞቹ አመኑ ዶክተር ማርቲንና ሚስተር ዌይንራይት ሊያግባቧት ሞከሩ
“ ደሞ ለዚያውም ቡሎኝሱርሜር ! እሱማ ደኅናውና ባለጌው ሁሉ የሚጠራቀምበት ነው ይባል የለ ? አለች ሳቤላ ነገሩን በመቃወም
ሚስተር ካርላይልም አብሯት ለመሔድና ለመቆየት ስለማይመቸው ሚስቱን
ወደዚያ ለመላክ ደስ አላለውም " እንዲያውም ትሩቪል ወደሚባለው አርፍለር አጠገብ ወደሚገኘው የባሕር ዳርቻ መናፈሻ ብትሔድለት መረጠ " ሐኪሞቹ ግን ብቸኝነት አንድ በሽታ በመሆኑ የፈለገው ሕዝብ ቢጠራቀምበትም መዝናናት ስለምትችል ቡሎኝ ሔዳ ከሚስዝ ዱሲ ጋር እንድትገናኝ መከሩ ።
ሚስተር ካርላይልም ተሸነፈና አመነበት « እሷም እነዚያን ሁሉ መቃወም ስለተሳናት ተቀበለች "
በርግጥ ሰውነቷ ያለመጠን ተጐሳቁሉ ነበር " ፊቷ እልቅ ብሎ ወቷል ደስ የሚሉት አሳዛኝ ዐይኖቿ ጥቁርቁር ብለው ገውለል ገውለል ይላሉ እጆቿ ጅማታቸው ወጥቶ በትኰሳት ይፋጃሉ ጊዜው ሙቀት ቢሆንም የሚሞቅ ልብስ ደራርባ ሳትንቀሳቀስ እንደ ተቀመጠች ትውላለች ልጆቿ ሲጫወቱ ትመለከታለች" ያካባቢ ገመግሞችንና ሜዳዎችን ተራሮችን ትመለከታለች " አንዳንድ ጊዜ በዝግ ሰረገላ ተንቀሳቅሳ ትመለሳለች።
እንደዚያ እንደ ሆነች የባሏና የባርባራ ግንኙነት ነገር እንደገና ተመለሰባት ለጥቂት ዓመታት ደህና ረስታው ነበር " አዲስም ሆነ አሮጌ ቅሬታ ሲሰማት ድካሟ
ይጠናባታል የሆነ ያልሆነ ሐሳብ ይመጣባታል ሚስተር ካርላይል በርግጥ የሚወዳት መሆኑንም ትጠራጠራለች ምናልባት ልቡ ባርባራን እየወደደ እሷን ለዝና
ሲል በጌታ ልጅነቷና በውበቷ ብቻ የመረጣት መስሎ ይታያታል " በተጋቡ በመጀመሪያ ዓመት ያሳያት የነበረው እንክብካቤ ቀስ በቀስ ወደ ስክነት ተለውጧል መቼም ይህ ዐይነት ጠባይ ያልተከሠተበት ጋብቻ አይገኝም " ምክንያቱም ፍቅር ስለሚቀነስ ሳይሆን የጊዜና የተለምዶ አሠራር ነው ማንኛውም እየቆየ የተለመደ ነገር ሁሉ እንደ አዲስ አያስደንቅም ፣ አያስጨንቅም በጋብቻ ዓለምም እጮኛና አዲስ ባል አፍለኛ ፍቅሩን ለመግለጽ ብዙ ነገር ቢቀባጥር ሴቶች ሊያምኑት ይችላሉ " እየቆየ መጨነቅ መጠበቡን እየቀነሰ ቢመጣ ግን ሊቀየሙት አይገባም " ለምሳሌ ሕፃናትን እንመልከት " አዲስ ታምቡር የተገዛለት ወንድ ልጅና የልጅ ምስል አሻንጉሊት የተገዛላት ሴት ልጅ አዲሶቹን መጫወቻዎች ይስሟቸዋል ያቅፏቸዋል እንቅ አድርገው ይዘው ከመሬት እንኳን አያስቀምጧቸውም ሌላውን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
...“ ኧረ እኔ እንጃ ጌታዬ እኔ ካፒቴን ቶርንን አንድ ጊዜ ብቻ ስለ ነበር ያየሁት አሁን ዐውቀዋለሁ ለማለት አልደፍርም " ይኸን ሰውዬ ላየውም ስለዚያኛው ሰውዬ የመጣልኝ ትዝታ የለም " ሰዉዬውን ሳየው ምንም አይቸው የማውቅም አልመሰለኝም "
ስለዚህ ሚስተር ካርላይል ከጆይስ ምንም ጠቃሚ ፍንጭ አላግኘም በበነጋው ኦትዌይ ቤተልን ፈልጎ አግኘው "
"ያ ከሔርበርት ቤተሰብ ጋር ያለፈው ካፒቴን ቶርን የሚባለውን ስው ደኅና አድርገህ ታውቀዋለህ ? አለው
“ አዎን! ሁለት ሰዓት ያህል ከሱ ጋር መቆየት በደንብ ለመተዋወቅ የሚበቃ ከሆነ በቀደም ሔርበርት ዘንድ ሔጄ ሳለ ሰውየው መጣ እዚያ ስናወጋ ብዙ ቆየን ግን ለምን ጠየቅኽኝ ?”
“ ያ አፊ ሆሊጆንን ያሳድድ የነበረው ቶርን የሚባለው እሱ ነው ከፈለግህ እውነቱን ልትነግረኝ ትችላለህ " "
ቤተል ድርቅ ብሎ ቀረ “ እንዴት ያለ እግር ያወጣ ውሸት ነው ! አለ
ቆይቶ ቆይቶ “ ይኸ ያ አይደለም አይደለም እንዴ የማን ቶርን ነው እሱ ?”
“ ዐውቀህ እያምታታህ ነው ቤተል " ከሆሊጆን ግድያ ጋር የተያያዘው ቶርን የሚባለው ሰው ይኸው አይደለም ?
ምን ሆንክብኝ ... ሚስተር ካርላይል እኔ ከአፊ ጋር የሚተዋወቅ ቶርን
የሚባል ሰው መኖሩን እንደማላውቅ ነግሬህ ነበር " ለምንድነው ቃሌ የማይታመነው? እኔ ቶርንን ከበቀደም በቀር አይቸው አላውቅም ካስፈለገ እምላለሁ” ብሎት ጥሎት ሔዶ
ቤተል የቶርንና የአፊ ስም ሲነሣበት ከዚህ በፊት እንዳዶፈደረግው ሁሎ አሁንም
መልኩ ተለዋወጠ አንድ ዐይነት ጭንቀት ሲፈጠርበት ታየ " ከዚህ ስምና ግድያ ጋር የተሳሰረ ምስጢር መኖሩን ለሚስተር ካርላይል ተሰማው " በግምት ምንም ማድረግ አልቻለም " የቤተል መልስም ፍንጭ አልሰጠውም » ከዚያ እሱም ወደ
ቢሮው ሲሔድ ቶም ሔርበትን አገኘውና ቶርን ከነሱ ጋር ብዙ ይሰነብት እንደሆነ ቢጠይቀው : ወዴፊት ካልመጣ በቀር ለአሁኑ ግን መሔዱን ነገረው "
ሚስተር ካርላይል ለራት ወደ ቤቱ ሲሔድ ሚስዝ ሔርን ለመጠየቅ አስመስሎ ወደ ዐፀዱ ጐራ አለ » ባርባራ የሚስተር ካርላይልን መልስ ለመስማት ልቧ ተንጠለጠለ ። ሚስዝ ሔርን አነጋግሮ ሲወጣ ተከትላው ወጣች ።
“ ምን ፍንጭ አገኘህ ?
“ ምንም የሚረባ ነገር አልተገኘም ሰውየውም ሒዷል ”
“ ሔደ! "
ባለፈው ምሽት ባርባራ ወደ ቤቷ እንደ ተመለሰች ሰውየውን ከቶም ሔርበት ጋር እንዴት ወደ ቤቱ እንደ ወሰዳቸው ኋላም ቶም ሔርበትን አግኝቶት ምን እንዳለውና ከቤተል ጋርም መነጋገሩን ሁሉ አጫወታት
“ምናልባት የነገሩን አዝማሚያ በመገመት ፈርቶ ይሆን የሔደው? አለችው "
አይመስለኝም መጀመሪያውንስ ለምን ይመጣ ኖሯል ?
ግን የተጠረጠረ መሆኑን የሚጠቁም ቃል አለመናገርህን እርግጠኛ ነህ ?
ምንም አልተናገርኩም ፡
ሰውየው ግን ምንድነው ?
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ጥቂት ዓታት ዐለፉ
ሰማህ ሚስተር ካርላይል እስኪ ቦታ ትለውጥ ለምላሌ ወደ ቤልጅግ ወይም ወደ ፈረንሳይ
ሊረዳት ይችላል ባሕር ጠረፎች ብትወስዳት ፡ በባሕሩ ውሃ ስትታጠብ በጣም ሊረዳት ይችላል።
“ ከቤት ርቃ መሔዱ ለሷ ደኅና ይመስልሃል ? ”
“ አዎን ይመስለኛል " አየህ ይህ ነው የምትለው የአካል ቀውስ ካለ 'በሕክምና መከታተል ስለሚገባ ቦታ መለወጡ ፡ አየር መቀየሩ ሁሉ አይታየኝም"ክስዊስ ተራሮች ቢወጡ ወይም ከዴንቨር ሸለቆ ቢወርዱ ዋጋ የለውም » እንደሷ ያለ የድካም ሰመመን ላለበት ግን አየርና ቦታ ለወጥ በጣም ይጠቅማል " ብርታቷን
በእንደዚህ ዐይነት ጥረቶች እያባበልክ ለመመለስ ከመሞክር በቀር ሌላ ምንም ማድረግ አይቻልም ”
“ እስኪ ከሷ ጋር ልምከርበት ”
“ እኔም ነግሬያት ነበር” አለ ዶክተር ማርቲን ፡ የሐሳቧ አቅራቢ : አልተቀበለችኝም በሽተኞቹ ሁልጊዜም ከቤታቸው መራቅ ደስ አይላቸውም መሔዷ ግን አስፈላጊ ነው።
ንግግሩ ስለ እመቤት ሳቤላ ነበር በአሁኑ ጊዜ በኢስት ሊን ሳቤላ ዊልያምና አርኪባልድ የሚባሉ ፡ የመጨረሻዉ የዐሥራ ሁለት ወር ልጅ የሆነ : ሦስት ልጆች
ደርሰዋል ሁለት ወር ያሀል ቀደም ብሎ ሳቤላ ክፉኛ ታማ ዳነች ግን ድቅቅ አድርጎ ስለ ለቀቃት ሰውነቷ አልጠነክር አለ ሚስተር ዌይንራይት ያላደረገው ጥረት
አልነበረም ግን ከመባስ በቀር ምንም አልተሻላትም በመጨረሻ ዶክተር ማርቲን ከሊንበራ ተጠርቶ መጣ እሱም ሁኔታውን አይቶ ያየርና የቦታ ለውጥ አዘዘ
ሳቤላ የሐኪሙን ትእዛዝ ለመቀበል በተለይ እስከ ፈረንሳይ ጠረፍ ለመሔድ አልፈቀደችም
በሚስተር ኬን ትርዒት ጊዜ ያየናት ሚስዝ ዱሲ ፓሪስ ላይ ዐሥራ ስምንት ወር ስትቀመጥ ለሳቤላ ሁለት ጊዜ ጽፋላት ነበር አሁን ደግሞ ወደ ቡሎኝሱር ሜር ሔዳ አንድ ሁለት ወር እንደምትቆይ ጻፈችላት » የሳቤላ እመቢታ የብቸኝነት ፍራቻ እንደሚሆን በመገመት አሁን ግን ዱሲ ካለችላት እሺ ማለት እንዳለባት
ሐኪሞቹ አመኑ ዶክተር ማርቲንና ሚስተር ዌይንራይት ሊያግባቧት ሞከሩ
“ ደሞ ለዚያውም ቡሎኝሱርሜር ! እሱማ ደኅናውና ባለጌው ሁሉ የሚጠራቀምበት ነው ይባል የለ ? አለች ሳቤላ ነገሩን በመቃወም
ሚስተር ካርላይልም አብሯት ለመሔድና ለመቆየት ስለማይመቸው ሚስቱን
ወደዚያ ለመላክ ደስ አላለውም " እንዲያውም ትሩቪል ወደሚባለው አርፍለር አጠገብ ወደሚገኘው የባሕር ዳርቻ መናፈሻ ብትሔድለት መረጠ " ሐኪሞቹ ግን ብቸኝነት አንድ በሽታ በመሆኑ የፈለገው ሕዝብ ቢጠራቀምበትም መዝናናት ስለምትችል ቡሎኝ ሔዳ ከሚስዝ ዱሲ ጋር እንድትገናኝ መከሩ ።
ሚስተር ካርላይልም ተሸነፈና አመነበት « እሷም እነዚያን ሁሉ መቃወም ስለተሳናት ተቀበለች "
በርግጥ ሰውነቷ ያለመጠን ተጐሳቁሉ ነበር " ፊቷ እልቅ ብሎ ወቷል ደስ የሚሉት አሳዛኝ ዐይኖቿ ጥቁርቁር ብለው ገውለል ገውለል ይላሉ እጆቿ ጅማታቸው ወጥቶ በትኰሳት ይፋጃሉ ጊዜው ሙቀት ቢሆንም የሚሞቅ ልብስ ደራርባ ሳትንቀሳቀስ እንደ ተቀመጠች ትውላለች ልጆቿ ሲጫወቱ ትመለከታለች" ያካባቢ ገመግሞችንና ሜዳዎችን ተራሮችን ትመለከታለች " አንዳንድ ጊዜ በዝግ ሰረገላ ተንቀሳቅሳ ትመለሳለች።
እንደዚያ እንደ ሆነች የባሏና የባርባራ ግንኙነት ነገር እንደገና ተመለሰባት ለጥቂት ዓመታት ደህና ረስታው ነበር " አዲስም ሆነ አሮጌ ቅሬታ ሲሰማት ድካሟ
ይጠናባታል የሆነ ያልሆነ ሐሳብ ይመጣባታል ሚስተር ካርላይል በርግጥ የሚወዳት መሆኑንም ትጠራጠራለች ምናልባት ልቡ ባርባራን እየወደደ እሷን ለዝና
ሲል በጌታ ልጅነቷና በውበቷ ብቻ የመረጣት መስሎ ይታያታል " በተጋቡ በመጀመሪያ ዓመት ያሳያት የነበረው እንክብካቤ ቀስ በቀስ ወደ ስክነት ተለውጧል መቼም ይህ ዐይነት ጠባይ ያልተከሠተበት ጋብቻ አይገኝም " ምክንያቱም ፍቅር ስለሚቀነስ ሳይሆን የጊዜና የተለምዶ አሠራር ነው ማንኛውም እየቆየ የተለመደ ነገር ሁሉ እንደ አዲስ አያስደንቅም ፣ አያስጨንቅም በጋብቻ ዓለምም እጮኛና አዲስ ባል አፍለኛ ፍቅሩን ለመግለጽ ብዙ ነገር ቢቀባጥር ሴቶች ሊያምኑት ይችላሉ " እየቆየ መጨነቅ መጠበቡን እየቀነሰ ቢመጣ ግን ሊቀየሙት አይገባም " ለምሳሌ ሕፃናትን እንመልከት " አዲስ ታምቡር የተገዛለት ወንድ ልጅና የልጅ ምስል አሻንጉሊት የተገዛላት ሴት ልጅ አዲሶቹን መጫወቻዎች ይስሟቸዋል ያቅፏቸዋል እንቅ አድርገው ይዘው ከመሬት እንኳን አያስቀምጧቸውም ሌላውን
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
በመጨሻ እኖታችን
እኔና ክሪስ በግርፋቱ ቀን በመሀከላችን ስለተፈጠረው ነገር በፍፁም አላወራንም
በአብዛኛው አተኩሮ ሲመለከተኝ እይዘዋለሁ፧ ግን አይኖቼ አይኖቹን ሲመለከቱ አይኖቹን ያሸሻል እኔም ሳየው ከያዘኝ አይኖቼን ወዲያው እመልሳለሁ።
እኔም እሱም በየቀ እያደግን ነው፡ ጡቶቼ ሙሉ ሆነዋል። ዳሌዬ ሰፋ ብሎ ወገቤ ቀጠን ብሏል ግንባሬ አካባቢ የተቆረጠው ፀጉሬ አድጎ ደስ በሚል አይነት ተጠቅልሏል። ክሪስ ደግሞ ትከሻው ሰፍቷል። ደረቱና ክንዶቹ የበለጠ ወንዳወንድ ሆነዋል አንድ ጊዜ ጣሪያው ስር ያለው ክፍል ውስጥ
ሆኖ የተገረመ በሚመስል አይነት ወንድነቱን ወደታች ሲመለከትና ሲለካው
ይዤዋለሁ። ርዝመቱ ምን ጥቅም እንዳለው ለማወቅ ስለጓጓሁ “ለምን?” ብዬ
ስጠይቀው አንድ ጊዜ አባታችንን እርቃኑን ሆኖ እንዳየውና አሁን ያየው
ነገር መጠኑ በቂ እንደማይመስል ነገረኝና ፊቱን አዞረ። ልክ እኔ እናታችን የምትለብሰው የጡት መያዣ መጠን ስንት እንደሆነ ማወቅ እንደምፈልገው ማለት ነበር። “እንደገና እንደዚያ እንዳታደርግ።" አልኩት። ኮሪ ያለው የወንድ አካል ትንሽ ስለሆነ ክሪስን ተመልክቶ ልክ እንደ ክሪስ መጠኑ ትንሽ ነው
የሚል ስሜት ቢሰማውስ?
ድንገት የመማሪያ ክፍሉን ወንበሮች ማፅዳቴን አቁሜ ወደ ኬሪና ኮሪ ተመለከትኩ፡ አምላኬ! በጣም መቀራረብ እንዴት እይታን እንደሚያደበዝዝ!
ሁለት አመት ከአራት ወር የተቆለፈብን ቢሆንም መንትዮቹ እዚህ የመጣን
ጊዜ ከነበሩት አልተለወጡም ጭንቅላታቸው ተለቅ ብሎ ስለሚታይ የአይኖቻቸው መጠን ያነሰ ይመስላል፡ ሰውነታቸው ጭንቅላታቸውን መሸከም
የሚችል አይመስልም ፍዝዝ ብለው ወደ መስኮቱ ያስጠጋነው አሮጌ ፍራሽ
ላይ ተቀምጠዋል እስኪተኙ ጠበቅኩና ቀስ ብዬ ለክሪስ “ተመልከታቸው ምንም አላደጉም: ጭንቅላታቸው ብቻ ነው ትልቅ የሆነው:” አልኩት።
በከባዱ ተነፈሰ፤ ከዚያ አይኖቹን አጥብቦ ወደ መንትዮቹ ቀረበና የገረጣውን ቆዳቸውን ለመንካት ዝቅ አለ፡ “ውጪ ጣሪያው ላይ ከእኛ ጋር ወጥተው ፀሀይና ንፁህ አየር ቢነካቸው ጥሩ ይሆን ነበር ካቲ፤ ምንም ያህል ቢጮሁና ቢንፈራገጡ ወደ ውጪ እንዲወጡ ማስገደድ አለብን” አለኝ።
እንቅልፍ ላይ እንዳሉ ተሸክመን ወደ ጣሪያው ብንወስዳቸውና ፀሀይ ላይ ሆነው እኛ እንዳቀፍናቸው ቢነቁ ደህንነት ይሰማቸዋል ብለን አሰብንና ክሪ ኮሪን በጥንቃቄ ሲያነሳ፣ እኔም ኬሪን ብድግ አደረግኳት ወደ ተከፈተው የጣሪያው ስር ክፍል መስኮት ቀረብን፡ የጣሪያውን የኋላ ክፍል መጠቀም የተሻለ ነው: ቀኑ ሀሙስ ስለሆነና ሰራተኞቹ ቀኑን ሙሉ ከተማ ስለሚውሉ ጣሪያው ላይ ወጥተን የምንዝናናበት ብቸኛው ቀን ነው።
ክሪስ ቀስ ብሎ ኮሪን እንደያዘ መስኮቱን አልፎ ሲወጣ የበጋ ፀሀይ ኮሪን
ከእንቅልፉ አነቃው ዙሪያውን ሲመለከት እኔም ኬሪን ተሸክሜ ጣሪያው ላይ
ልወጣ መሆኑን ሲመለከት ጮኸ! ኬሪ ከእንቅልፏ ባነነች። ክሪስ ኮሪን ይዞ
ጣሪያው ጫፍ ላይ ሆኖ እኔ ደግሞ የት እየወሰድኳት እንደሆነ ስትመለከት
ጩኸቷን አቀለጠችው።
ክሪስ ጣሪያው ጫፍ ላይ እንዳለ “አምጫት! ለራሳቸው ነው ይህንን ማድረግ አለብን:” አለኝ፡ መጮህ ብቻ አይደለም እየተራገጡና እየመቱን ነበር።ኬሪ ክንዴ ላይ ስትነክሰኝ እኔም ጮህኩ። በጣም ትንንሾች ቢሆኑም አደጋ ላይ እንደሆኑ በማሰባቸው በጣም በጥንካሬ እየታገሉን ነበር። ፊቴን አዙሬ ወደ መማሪያ ክፍሉ መስኮት አቀናሁና እየተንቀጠቀጥኩ ኬሪን በእግሮቿ አቆምኳት እኔም አየር አጥሮኝ እያለከለክኩ ወንበሩን ተደግፌ በሰላም ወደ ውስጥ እንድመልሳት ስላደረገኝ እግዚአብሔርን አመሰገንኩ። ክሪስም ኮሪን
እህቱ አጠገብ መለሰው፡ ሙከራችን ጥቅም አልነበረውም እነሱን ጣሪያው ላይ እንዲወጡ ማስገደድ የአራታችንንም ህይወት አደጋ ላይ መጣል ነው።
በጣም ስለተናደዱብን በመጀመሪያ ቀን ወደዚህ ክፍል ስንመጣ ቁመታቸውን
ወደ ለካንበት ግድግዳ ምልክት ስንወስዳቸው ሁሉ እየታገሉን ነበር ክሪስ
ሁለቱንም ቦታው ላይ አድርጎ ሲይዝልኝ እኔ ምን ያህል እንዳደጉ ለማንበብ
ሞከርኩ፡
ሊሆን መቻሉን ባለማመን በድንጋጤ አፈጠጥኩ: በዚህ ሁሉ ጊዜ የጨመሩት
ሁለት ኢንች ብቻ ነው? ሁለት ኢንች! እኔና ክሪስ ከአምስት እስከ ሰባት
አመት እድሜያችን መሀከል ብዙ በጣም ብዙ ነበር ያደግነው ሲወለዱም
ክብደታቸው ትንሽ የነበረ ቢሆንም የተሻለ ማደግ ነበረባቸው።
የደነገጠና የፈራ ገፅታዬን ማየት እንዳይችሉ በእጆቼ ፊቴን መሸፈን ነበረብኝ፡፡
ከዚያ ሳግ ጉሮሮዬን ሲይዘኝ ጀርባዬን ሰጥቻቸው ፊቴን አዞርኩ።
“አሁን እንዲሄዱ መልቀቅ ትችላለህ” አልኩት ዞር ብዬ ሳያቸው ልክ እንደ ሁለት አይጦች በደረጃው እየተንደረደሩ ወደ ተወዳጁ ቴሌቪዥን ሮጡ።
ክሪስ hጀርባዬ ቆሞ እየጠበቀ ነው: “ምን ያህል ቁመት ጨምረዋል?” አለኝ:
ፈጠን ብዬ እምባዬን በእጄ ጠራርጌ ወደ እሱ ዞርኩ ከዚያ አይኖቹን እየተመለከትኩ ሁለት ኢንች እንደሆነ ነገርኩት᎓ አይኖቼ ውስጥ ህመም ነበር።
እሱም ያየው ያንን ነበር:
ጠደ እኔ ተጠግቶ አቀፈኝና ጭንቅላቴን ወደ ደረቱ አስጠጋኝ፡ አለቀስኩ በጣም
አለቀስኩ ይህንን በማድረጓ እናታችንን ጠላኋት የእውነት ጠላኋት! ልጆች እንደ አትክልት እንደሆኑና ለማደግ የፀሀይ ብርሃን እንደሚያስፈልጋቸው
ታውቃለች በወንድሜ እቅፍ ውስጥ እንዳለሁ ተንቀጠቀጥኩ። ነፃ ስንሆን
እንደገና ቆንጆ እንደሚሆኑ ራሴን ለማሳመን እየሞከርኩ ነበር። ቆንጆ ይሆናሉ፤ ያጡትን አመታት ያካክሳሉ፡ ልክ የፀሀይ ብርሃን ማግኘት ሲጀምሩ እንደ አትክልት ያድጋሉ። አዎ ያድጋሉ፤ ጎንጮቻቸው በጣም የጎደጎዱት፣አይኖቻቸው ወደ ውስጥ የገቡት ረጅም ጊዜ ቤት ውስጥ ስለሚቀመጡ ነው እና ያ ሁሉ ሊስተካከል ይችላል፤ አይችልም?
ከዚያ በሻካራ ድምፅ “ገንዘብ ነው አለምን የሚያሽከረክራት ወይስ ፍቅር? ለመንትዮቹ በቂ ፍቅር ሰጥተናቸዋል እናም ስድስት፣ ሰባት፣ ምናልባትም ስምንት ኢንች ቁመት መጨመር ነበረባቸው: ሁለት ብቻ አልነበረም" አልኩ፡
እኔና ክሪስ ወደዛ ወደ ደብዛዛው እስር ቤታችን ተመለስንና እንደ ሁልጊዜው
እጆቻቸውን እንዲታጠቡ ላክናቸው የምግብ ጠረጴዛችን ጋ በፀጥታ ተቀምጠን ሳንድዊቻችንን እየበላንና ወተት እየጠጣን ቲቪ ስንመለከት የክፍላችን በር ተከፈተ: መዞር አልፈለኩም ነበር። ግን ዞርኩ:
እናታችን እየሳቀች ወደ ክፍሉ ገባች የሚያምር ልብስ ለብሳለች የለበሰችው
ጃኬት አንገቱና እጆቹ ላይ ፀጉር አለው: “ውዶቼ!” አለች በመጓጓት አይነት
ሰላምታ: ከዚያ አንዳችንም ሰላም ልንላት ባለመነሳታችን እያመነታችና እርግጠኛ ባልሆነ ስሜት “መጥቻለሁ! ስታዩኝ ደስ አላላችሁም? ስላየኋችሁ እንዴት ደስ እንዳለኝ አታውቁም በጣም ስናፍቃችሁ፣ ስለናንተ ሳስብና ሳልም ነበር፡ እና በጣም በጥንቃቄ የመረጥኳቸው የሚያምሩ ስጦታዎች አምጥቼላችኋለሁ: እስክታዩዋቸው ጠብቁ፡፡ ረጅም ጊዜ የጠፋሁበትን ማካካስ እፈልጋለሁ፡ ለምን እንደምሄድ ልነግራችሁ ፈልጌ ነበር፣ እውነቴን ነው፣
ግን በጣም የተወሳሰበ ነው: ለምን ያህል ጊዜ እንደምቆይ አላወቅኩም
ነበር። ናፍቃችሁኛል! በደንብ ተይዛችኋል አይደል? አልተሰቃያችሁም
ተሰቃይታችኋል እንዴ?”
ተሰቃይታችኋል? ናፍቃችሁኛል? እሷ ማናት? አፍጥጬ እያየኋትና አራት
የተደበቁ ልጆች የሌሎችን ህይወት እንዴት አስቸጋሪ እንደሚያደርጉ እየሰማሁ
መጥፎ ሀሳቦች መጡብኝ፡ ሁለተኛ በጭራሽ እንዳትጠጋኝ ላደርጋት ፈለግኩ።ከዚያ አቅማማሁ በተስፋ ተሞልቼ እንደገና ልወዳትና ላምናትም ፈለግኩ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
በመጨሻ እኖታችን
እኔና ክሪስ በግርፋቱ ቀን በመሀከላችን ስለተፈጠረው ነገር በፍፁም አላወራንም
በአብዛኛው አተኩሮ ሲመለከተኝ እይዘዋለሁ፧ ግን አይኖቼ አይኖቹን ሲመለከቱ አይኖቹን ያሸሻል እኔም ሳየው ከያዘኝ አይኖቼን ወዲያው እመልሳለሁ።
እኔም እሱም በየቀ እያደግን ነው፡ ጡቶቼ ሙሉ ሆነዋል። ዳሌዬ ሰፋ ብሎ ወገቤ ቀጠን ብሏል ግንባሬ አካባቢ የተቆረጠው ፀጉሬ አድጎ ደስ በሚል አይነት ተጠቅልሏል። ክሪስ ደግሞ ትከሻው ሰፍቷል። ደረቱና ክንዶቹ የበለጠ ወንዳወንድ ሆነዋል አንድ ጊዜ ጣሪያው ስር ያለው ክፍል ውስጥ
ሆኖ የተገረመ በሚመስል አይነት ወንድነቱን ወደታች ሲመለከትና ሲለካው
ይዤዋለሁ። ርዝመቱ ምን ጥቅም እንዳለው ለማወቅ ስለጓጓሁ “ለምን?” ብዬ
ስጠይቀው አንድ ጊዜ አባታችንን እርቃኑን ሆኖ እንዳየውና አሁን ያየው
ነገር መጠኑ በቂ እንደማይመስል ነገረኝና ፊቱን አዞረ። ልክ እኔ እናታችን የምትለብሰው የጡት መያዣ መጠን ስንት እንደሆነ ማወቅ እንደምፈልገው ማለት ነበር። “እንደገና እንደዚያ እንዳታደርግ።" አልኩት። ኮሪ ያለው የወንድ አካል ትንሽ ስለሆነ ክሪስን ተመልክቶ ልክ እንደ ክሪስ መጠኑ ትንሽ ነው
የሚል ስሜት ቢሰማውስ?
ድንገት የመማሪያ ክፍሉን ወንበሮች ማፅዳቴን አቁሜ ወደ ኬሪና ኮሪ ተመለከትኩ፡ አምላኬ! በጣም መቀራረብ እንዴት እይታን እንደሚያደበዝዝ!
ሁለት አመት ከአራት ወር የተቆለፈብን ቢሆንም መንትዮቹ እዚህ የመጣን
ጊዜ ከነበሩት አልተለወጡም ጭንቅላታቸው ተለቅ ብሎ ስለሚታይ የአይኖቻቸው መጠን ያነሰ ይመስላል፡ ሰውነታቸው ጭንቅላታቸውን መሸከም
የሚችል አይመስልም ፍዝዝ ብለው ወደ መስኮቱ ያስጠጋነው አሮጌ ፍራሽ
ላይ ተቀምጠዋል እስኪተኙ ጠበቅኩና ቀስ ብዬ ለክሪስ “ተመልከታቸው ምንም አላደጉም: ጭንቅላታቸው ብቻ ነው ትልቅ የሆነው:” አልኩት።
በከባዱ ተነፈሰ፤ ከዚያ አይኖቹን አጥብቦ ወደ መንትዮቹ ቀረበና የገረጣውን ቆዳቸውን ለመንካት ዝቅ አለ፡ “ውጪ ጣሪያው ላይ ከእኛ ጋር ወጥተው ፀሀይና ንፁህ አየር ቢነካቸው ጥሩ ይሆን ነበር ካቲ፤ ምንም ያህል ቢጮሁና ቢንፈራገጡ ወደ ውጪ እንዲወጡ ማስገደድ አለብን” አለኝ።
እንቅልፍ ላይ እንዳሉ ተሸክመን ወደ ጣሪያው ብንወስዳቸውና ፀሀይ ላይ ሆነው እኛ እንዳቀፍናቸው ቢነቁ ደህንነት ይሰማቸዋል ብለን አሰብንና ክሪ ኮሪን በጥንቃቄ ሲያነሳ፣ እኔም ኬሪን ብድግ አደረግኳት ወደ ተከፈተው የጣሪያው ስር ክፍል መስኮት ቀረብን፡ የጣሪያውን የኋላ ክፍል መጠቀም የተሻለ ነው: ቀኑ ሀሙስ ስለሆነና ሰራተኞቹ ቀኑን ሙሉ ከተማ ስለሚውሉ ጣሪያው ላይ ወጥተን የምንዝናናበት ብቸኛው ቀን ነው።
ክሪስ ቀስ ብሎ ኮሪን እንደያዘ መስኮቱን አልፎ ሲወጣ የበጋ ፀሀይ ኮሪን
ከእንቅልፉ አነቃው ዙሪያውን ሲመለከት እኔም ኬሪን ተሸክሜ ጣሪያው ላይ
ልወጣ መሆኑን ሲመለከት ጮኸ! ኬሪ ከእንቅልፏ ባነነች። ክሪስ ኮሪን ይዞ
ጣሪያው ጫፍ ላይ ሆኖ እኔ ደግሞ የት እየወሰድኳት እንደሆነ ስትመለከት
ጩኸቷን አቀለጠችው።
ክሪስ ጣሪያው ጫፍ ላይ እንዳለ “አምጫት! ለራሳቸው ነው ይህንን ማድረግ አለብን:” አለኝ፡ መጮህ ብቻ አይደለም እየተራገጡና እየመቱን ነበር።ኬሪ ክንዴ ላይ ስትነክሰኝ እኔም ጮህኩ። በጣም ትንንሾች ቢሆኑም አደጋ ላይ እንደሆኑ በማሰባቸው በጣም በጥንካሬ እየታገሉን ነበር። ፊቴን አዙሬ ወደ መማሪያ ክፍሉ መስኮት አቀናሁና እየተንቀጠቀጥኩ ኬሪን በእግሮቿ አቆምኳት እኔም አየር አጥሮኝ እያለከለክኩ ወንበሩን ተደግፌ በሰላም ወደ ውስጥ እንድመልሳት ስላደረገኝ እግዚአብሔርን አመሰገንኩ። ክሪስም ኮሪን
እህቱ አጠገብ መለሰው፡ ሙከራችን ጥቅም አልነበረውም እነሱን ጣሪያው ላይ እንዲወጡ ማስገደድ የአራታችንንም ህይወት አደጋ ላይ መጣል ነው።
በጣም ስለተናደዱብን በመጀመሪያ ቀን ወደዚህ ክፍል ስንመጣ ቁመታቸውን
ወደ ለካንበት ግድግዳ ምልክት ስንወስዳቸው ሁሉ እየታገሉን ነበር ክሪስ
ሁለቱንም ቦታው ላይ አድርጎ ሲይዝልኝ እኔ ምን ያህል እንዳደጉ ለማንበብ
ሞከርኩ፡
ሊሆን መቻሉን ባለማመን በድንጋጤ አፈጠጥኩ: በዚህ ሁሉ ጊዜ የጨመሩት
ሁለት ኢንች ብቻ ነው? ሁለት ኢንች! እኔና ክሪስ ከአምስት እስከ ሰባት
አመት እድሜያችን መሀከል ብዙ በጣም ብዙ ነበር ያደግነው ሲወለዱም
ክብደታቸው ትንሽ የነበረ ቢሆንም የተሻለ ማደግ ነበረባቸው።
የደነገጠና የፈራ ገፅታዬን ማየት እንዳይችሉ በእጆቼ ፊቴን መሸፈን ነበረብኝ፡፡
ከዚያ ሳግ ጉሮሮዬን ሲይዘኝ ጀርባዬን ሰጥቻቸው ፊቴን አዞርኩ።
“አሁን እንዲሄዱ መልቀቅ ትችላለህ” አልኩት ዞር ብዬ ሳያቸው ልክ እንደ ሁለት አይጦች በደረጃው እየተንደረደሩ ወደ ተወዳጁ ቴሌቪዥን ሮጡ።
ክሪስ hጀርባዬ ቆሞ እየጠበቀ ነው: “ምን ያህል ቁመት ጨምረዋል?” አለኝ:
ፈጠን ብዬ እምባዬን በእጄ ጠራርጌ ወደ እሱ ዞርኩ ከዚያ አይኖቹን እየተመለከትኩ ሁለት ኢንች እንደሆነ ነገርኩት᎓ አይኖቼ ውስጥ ህመም ነበር።
እሱም ያየው ያንን ነበር:
ጠደ እኔ ተጠግቶ አቀፈኝና ጭንቅላቴን ወደ ደረቱ አስጠጋኝ፡ አለቀስኩ በጣም
አለቀስኩ ይህንን በማድረጓ እናታችንን ጠላኋት የእውነት ጠላኋት! ልጆች እንደ አትክልት እንደሆኑና ለማደግ የፀሀይ ብርሃን እንደሚያስፈልጋቸው
ታውቃለች በወንድሜ እቅፍ ውስጥ እንዳለሁ ተንቀጠቀጥኩ። ነፃ ስንሆን
እንደገና ቆንጆ እንደሚሆኑ ራሴን ለማሳመን እየሞከርኩ ነበር። ቆንጆ ይሆናሉ፤ ያጡትን አመታት ያካክሳሉ፡ ልክ የፀሀይ ብርሃን ማግኘት ሲጀምሩ እንደ አትክልት ያድጋሉ። አዎ ያድጋሉ፤ ጎንጮቻቸው በጣም የጎደጎዱት፣አይኖቻቸው ወደ ውስጥ የገቡት ረጅም ጊዜ ቤት ውስጥ ስለሚቀመጡ ነው እና ያ ሁሉ ሊስተካከል ይችላል፤ አይችልም?
ከዚያ በሻካራ ድምፅ “ገንዘብ ነው አለምን የሚያሽከረክራት ወይስ ፍቅር? ለመንትዮቹ በቂ ፍቅር ሰጥተናቸዋል እናም ስድስት፣ ሰባት፣ ምናልባትም ስምንት ኢንች ቁመት መጨመር ነበረባቸው: ሁለት ብቻ አልነበረም" አልኩ፡
እኔና ክሪስ ወደዛ ወደ ደብዛዛው እስር ቤታችን ተመለስንና እንደ ሁልጊዜው
እጆቻቸውን እንዲታጠቡ ላክናቸው የምግብ ጠረጴዛችን ጋ በፀጥታ ተቀምጠን ሳንድዊቻችንን እየበላንና ወተት እየጠጣን ቲቪ ስንመለከት የክፍላችን በር ተከፈተ: መዞር አልፈለኩም ነበር። ግን ዞርኩ:
እናታችን እየሳቀች ወደ ክፍሉ ገባች የሚያምር ልብስ ለብሳለች የለበሰችው
ጃኬት አንገቱና እጆቹ ላይ ፀጉር አለው: “ውዶቼ!” አለች በመጓጓት አይነት
ሰላምታ: ከዚያ አንዳችንም ሰላም ልንላት ባለመነሳታችን እያመነታችና እርግጠኛ ባልሆነ ስሜት “መጥቻለሁ! ስታዩኝ ደስ አላላችሁም? ስላየኋችሁ እንዴት ደስ እንዳለኝ አታውቁም በጣም ስናፍቃችሁ፣ ስለናንተ ሳስብና ሳልም ነበር፡ እና በጣም በጥንቃቄ የመረጥኳቸው የሚያምሩ ስጦታዎች አምጥቼላችኋለሁ: እስክታዩዋቸው ጠብቁ፡፡ ረጅም ጊዜ የጠፋሁበትን ማካካስ እፈልጋለሁ፡ ለምን እንደምሄድ ልነግራችሁ ፈልጌ ነበር፣ እውነቴን ነው፣
ግን በጣም የተወሳሰበ ነው: ለምን ያህል ጊዜ እንደምቆይ አላወቅኩም
ነበር። ናፍቃችሁኛል! በደንብ ተይዛችኋል አይደል? አልተሰቃያችሁም
ተሰቃይታችኋል እንዴ?”
ተሰቃይታችኋል? ናፍቃችሁኛል? እሷ ማናት? አፍጥጬ እያየኋትና አራት
የተደበቁ ልጆች የሌሎችን ህይወት እንዴት አስቸጋሪ እንደሚያደርጉ እየሰማሁ
መጥፎ ሀሳቦች መጡብኝ፡ ሁለተኛ በጭራሽ እንዳትጠጋኝ ላደርጋት ፈለግኩ።ከዚያ አቅማማሁ በተስፋ ተሞልቼ እንደገና ልወዳትና ላምናትም ፈለግኩ
#ጠላፊዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_በወንዳየሁ_ንጉሴ
ማርጋሬት ደስ ደስ ብሏታል፡ ከእውነተኛ ሌባ ጋር መወዳጀቷን ማመን
እያቃታት ነው፡ አንድ ሰው ‹‹እኔ ሌባ ነኝ›› ቢላት አታምነውም፡ ነገር ግን
ሄሪ አንድ ጊዜ ፖሊስ ጣቢያ ተከሶ ስላየችው ‹‹እኔ ሌባ ነኝ›› ቢላት እውነቱን መሆኑን አወቀች።
ከስርዓት ውጭ የሚኖሩ ሰዎች ማለትም ወንጀለኞች ለህግና ለመንግስት የማይገዙ ሰዎች፣ ሴተኛ አዳሪዎችና በረንዳ አዳሪዎች ሁልጊዜ
ያስደንቋታል፡ እነሱ ነጻ ሰዎች ናቸው፡፡ በእርግጥ በህብረተሰቡ የተተፋ ሰው
ጥሩ ነው የሚል አመለካከት የላትም፡፡ ነገር ግን እንደ ሄሪ ያሉ ሰዎች አድርጉ የተባሉትን ሁሉ ለማድረግ አይፈቅዱም፡ይህ ነጻነታቸው ነው ማርጋሬትን የሚያስቀናት፡፡ አንዳንዴ የወታደር ልብስ ለብሶ ጠመንጃውን ታጥቆ በየመንደሩ እየዞረ ህዝብ የሚዘርፍ ሽፍታ መሆን ያምራታል እንደዚህ አይነት ሰዎች ገጥመዋት አያውቁም: አንድ ጊዜ በለንደን ጎዳናዎች
ላይ ሴተኛ አዳሪ መስላቸው ሊደፍሯት የመጡትን ሰዎች ባታይ የምታውቅበት ሁኔታ አልነበረም፡፡
ሄሪ እሷ የምትመኘውን ነገር ሁሉ ያሟላ ሆኖ ነው ያገኘችው የፈለገውን ማድረግ የሚችል ሰው! ዛሬ ጧት አሜሪካ ለመሄድ ወሰነና ዛሬ ከሰዓት በኋላ አይሮፕላኑ ላይ ተገኘ፡፡ ሌሊቱን በሙሉ መደነስና ቀኑን በሙሉ መጋደም ከፈለገ ያደርገዋል፡ ከልካይ የለበትም፡፡ መብላት የፈለገውን ይበላል፧ መጠጣት የፈለገውን ይጠጣል፡ ገንዘብ ከፈለገ ገንዘባቸውን መጣያ
ካጡ ባለጸጎች ይሰርቃል፡ እሱ ነጻ የሆነ ሰው ነው፡
ስለሄሪ በይበልጥ ማወቅ ፈለገች፡ ከእሱ ጋር ራት ሳትበላ ያሳለፈቻቸው
ቀናት ቁጭት ውስጥ ጣሏት፡፡
ባሮን ጋቦንና ካርል ሃርትማን ከኦክሰንፎርድ ቤተሰብ ቀጥሎ ተቀምጠዋል እነዚህ ሰዎች ይሁዲ ስለሆኑ ነው ገና ወደ መብል ክፍሉ እንደገቡ ሎርድ ኦክሰንፎርድ ክፉኛ የገላመጧቸው፡አብረዋቸው
የተቀመጡት ኦሊስ ፊልድና ፍራንክ ጎርደን ናቸው፡፡ ፍራንክ ጎርደን በዕድሜ
hሄሪ ብዙም የማይበልጥ መልከ መልካም ወጣት ነው፡፡ ኦሊስ ፊልድ ደግሞ
ኑሮ የጠመመበት የመሰለ በዕድሜ ገፋ ያለ ራሰ በራ ሰው ነው፡፡
ፎየንስ ላይ አይሮፕላኑ ሲያርፍ ሁሉም ሰው ከአይሮፕላኑ ወጥቶ
በየፊናው ሲበታተን እነዚህ ሁለት ሰዎች አይሮፕላኑ ውስጥ በመቅረታቸው
የለው ሁሉ መነጋገሪያ ሆነው ነበር፡፡
ሶስተኛው የመመገቢያ ጠረጴዛ ላይ ሉሉ ቤልና ሾርባው ጨው የበዛበት ነው እያሉ ሲያማርሩ የዋሉት ልዕልት ላቪኒያ ተቀምጠዋል ከነሱ ጋር ፎየንስ ላይ የተሳፈሩት ሚስተር ላቭሴይና ሚስስ ሌኔሃን ተቀምጠዋል። ወሬ መለቃቀም የሚወደው ፔርሲ እነዚህ ሰዎች ባልና ሚስት ባይሆኑም የሙሽሮቹን ክፍል እንደሚጋሩ ወሬ ለጠማቸው አውርቷል
ባልና ሚስት ያልሆኑ ሰዎች ይህን ክፍል እንዲይዙ ፓን አሜሪካን አየር
መንገድ እንዴት እንደፈቀደላቸው ማርጋሬት ገርሟታል። አየር መንገዱ ብዙ ሰዎች ወደ አሜሪካ መሄድ ስለፈለጉ ህጉን መጋፋት የግድ ሆኖበታል፡
ፔርሲ ጥቁር የይሁዲዎች ኮፊያ አናቱ ላይ ደፍቷል፡ ማርጋሬት ይህን ስታይ በሳቅ ተንፈቀፈቀች፡፡ ከየት ነው ያመጣው! አባቱ ግን ‹‹ጅል!›› ብለው ተሳድበው ኮፍያውን መንጭቀው ወረወሩት፡፡
ሌዲ ኦክሰንፎርድ ኤልሳቤት ተለይታቸው ከሄደች ወዲህ ለመጀመሪያ
ጊዜ ፊታቸው በመጠኑ ፈካ ብሏል፡፡
ሌዲ ኦክሰንፎርድ ‹‹የራት ሰዓታችን ገና ነው›› አሉ፡፡
ሎርድ ኦክሰንፎርድ ደግሞ ‹‹አንድ ሰዓት ተኩል ሆኗል እኮ›› አሉ፡፡
‹‹ለምንድነው ታዲያ ያልጨለመው?››
‹‹እንግሊዝ አገር አሁን ጨለማ ነው፡ አሁን ግን ከአየርላንድ ባህር
ጠረፍ ሶስት መቶ ማይል ርቀት ላይ ነው የምንገኘው ጸሃይዋን እያሳደድን
ነው›› አለ ፔርሲ፡፡
‹‹መቼም መጨለሙ አይቀርም››
‹‹ምናልባት ሶስት ሰዓት ላይ የሚጨልም ይመስለኛል›› አለ ፔርሲ
‹‹ጥሩ›› አሉ እናት፡፡
እንደማይጨልም
‹‹ጸሃይዋን ተከትለን በፍጥነት ብንጓዝ
እንደማይጨልም ታውቃላችሁ? አለ ፔርሲ፡፡
‹‹እንደዚህ አይነት ፍጥነት ያለው አይሮፕላን የሰው ልጅ ይሰራል ብዬ አልገምትም›› አሉ አባት ከኔ በላይ አዋቂ የለም በሚል ግብዝነት፡
ቦትውድ ካናዳ ለመድረስ አስራ ስድስት ሰዓት ተኩል ይፈጃል›› አለ ፔርሲ ‹‹እዚያ በግሪንዊች ሰዓት አቆጣጠር ከጧቱ ሶስት ሰአት እንደርሳለን››
‹‹ካናዳ ስንት ሰዓት ይሆናል ማለት ነው?,,
‹‹የኒውፋንድላንድ ካናዳ የሰዓት አቆጣጠር ከግሪንዊች የሰዓት አቆጣጠር ሶስት ሰዓት ወደ ኋላ ነው›› አለ ፔርሲ፡፡
እናት የፔርሲን ችሎታ አጤኑና ‹‹ወንዶች የቴክኒክ እውቀት ላይ ጎበዞች ናቸው›› አሉ፡፡
ማርጋሬት በእናቷ አነጋገር ተናደደች፡፡ እናት የቴክኒክ ነገሮች ሴቶች አይገባቸውም ብለው ያምናሉ፡፡ ‹‹ወንዶች ሴቶች ጎበዝ ሲሆኑ አይወዱም››
ብለዋታል ብዙ ጊዜ፡ በዚህ ጉዳይ ማርጋሬት ከእናቷ ጋር እሰጥ አገባ ውስጥ መግባት ባትፈልግም እሷ ግን አታምንበትም፡ ይህን የሚቀበሉ ወንዶች ደደቦች ናቸው ብላ ነው የምትገምተው ጎበዝ ወንድ ጎበዝ ሴት ይወዳል፡
አጠገባቸው ካለው ጠረጴዛ ዙሪያ የተቀመጡት ባሮን ጋቦንና ካርል ሃርትማን ክርክር ገጥመዋል አጠገባቸው ያሉት የጠረጴዛ ተጋሪዎች
ባይገባቸውም በጸጥታ ያዳምጣሉ: ሁለቱ ሰዎች አይሮፕላኑ ላይ ከወጡ
ጀምሮ ጥልቅ ውይይት ሲያደርጉ ይታያሉ፡፡ በዓለም ከታወቀ ሳይንቲስት
ጋር እንደዚህ ያለውን ውይይት የምታደርጉ ከሆነ ውይይቱ ጥብቅ መሆኑ
አያስደንቅም፡፡ በክርክራቸው ውስጥ ፍልስጤምንና እስራኤልን በተደጋጋሚ ያነሳሉ፡ ማርጋሬት የውይይት ርዕሳቸውን ስትሰማ
‹‹አባባ ምን ይል
ይሆን?›› እያለች አስሬ ታያቸዋለች፡፡ እሳቸውም የሁለቱ ሰዎች ውይይት
አልጥም ብሏቸው አኩርፈዋል፡፡ አባቷ ነገር እንዳይጭሩ ርዕስ ለማስለወጥ
‹‹አይሮፕላኑ የሚጓዘው ኃይለኛ ነፋስ በቀላቀለ ዝናብ ውስጥ ነው›› አለች
‹‹እንዴት አወቅሽ?›› አለ ፔርሲ አነጋገሩ ቅናት ያለበት መሆኑ ይታወቃል፡፡ በበረራ መረጃ ከማርጋሬት ይልቅ እሱ ነው ኤክስፐርቱ።
‹‹ሄሪ ነገረኝ››
‹‹እሱ እንዴት ያውቃል?››
‹‹እሱ ዛሬ ራት የበላው ከበረራ መሃንዲሱና ከናቪጌተሩ ጋር ነው፡››
ማርጋሬት ዝናቡ ችግር ይፈጥራል ብላ አልገመተችም፡፡ በእርግጥ
በዝናብ ውስጥ መጓዝ ምቾት ቢነሳም ለክፉ አይሰጥም፡፡
ሎርድ ኦክሰንፎርድ ብርጭቋቸው ውስጥ የቀረውን ቪኖ አጋቡና ሌላ
እንዲጨመርላቸው ቆጣ ብለው ጠየቁ፡፡ ዝናቡ ችግር ያመጣል ብለው ፈሩ
እንዴ? ከተለመደው በላይ እየጠጡ መሆናቸውን ማርጋሬት ተገንዝባለች።
ፊታቸው ከመጠጥ ብዛት ፍም መስሏል: ዓይናቸው ፈጧል፡ ምናልባትም
ነርቭ ሆነዋል፡፡በኤልሳቤት መኮብለል ክፉኛ ተበሳጭተዋል
እናትም ማርጋሬትን ‹‹ሚስተር መምበሪን አጫውቺው›› አሏት፡
ማርጋሬት የእናቷ አባባል ገርሟት ‹‹ለምን?›› ስትል ጠየቀች፡ ሲያዩት
ሰው እንዲያናግረው የሚፈልግ አይመስልም፡
‹‹ምናልባትም አይናፋር ሳይሆን አይቀርም›› አሉ እናት፡፡
እማማ ከመቼ ወዲህ ነው ለአይናፋሮች መቆርቆር የጀመረችው?የሚሆን ነገር አይደለም፡፡ ‹‹ግን ምን ማለትሽ ነው?›› ስትል ጠየቀች ማርጋሬት።
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_በወንዳየሁ_ንጉሴ
ማርጋሬት ደስ ደስ ብሏታል፡ ከእውነተኛ ሌባ ጋር መወዳጀቷን ማመን
እያቃታት ነው፡ አንድ ሰው ‹‹እኔ ሌባ ነኝ›› ቢላት አታምነውም፡ ነገር ግን
ሄሪ አንድ ጊዜ ፖሊስ ጣቢያ ተከሶ ስላየችው ‹‹እኔ ሌባ ነኝ›› ቢላት እውነቱን መሆኑን አወቀች።
ከስርዓት ውጭ የሚኖሩ ሰዎች ማለትም ወንጀለኞች ለህግና ለመንግስት የማይገዙ ሰዎች፣ ሴተኛ አዳሪዎችና በረንዳ አዳሪዎች ሁልጊዜ
ያስደንቋታል፡ እነሱ ነጻ ሰዎች ናቸው፡፡ በእርግጥ በህብረተሰቡ የተተፋ ሰው
ጥሩ ነው የሚል አመለካከት የላትም፡፡ ነገር ግን እንደ ሄሪ ያሉ ሰዎች አድርጉ የተባሉትን ሁሉ ለማድረግ አይፈቅዱም፡ይህ ነጻነታቸው ነው ማርጋሬትን የሚያስቀናት፡፡ አንዳንዴ የወታደር ልብስ ለብሶ ጠመንጃውን ታጥቆ በየመንደሩ እየዞረ ህዝብ የሚዘርፍ ሽፍታ መሆን ያምራታል እንደዚህ አይነት ሰዎች ገጥመዋት አያውቁም: አንድ ጊዜ በለንደን ጎዳናዎች
ላይ ሴተኛ አዳሪ መስላቸው ሊደፍሯት የመጡትን ሰዎች ባታይ የምታውቅበት ሁኔታ አልነበረም፡፡
ሄሪ እሷ የምትመኘውን ነገር ሁሉ ያሟላ ሆኖ ነው ያገኘችው የፈለገውን ማድረግ የሚችል ሰው! ዛሬ ጧት አሜሪካ ለመሄድ ወሰነና ዛሬ ከሰዓት በኋላ አይሮፕላኑ ላይ ተገኘ፡፡ ሌሊቱን በሙሉ መደነስና ቀኑን በሙሉ መጋደም ከፈለገ ያደርገዋል፡ ከልካይ የለበትም፡፡ መብላት የፈለገውን ይበላል፧ መጠጣት የፈለገውን ይጠጣል፡ ገንዘብ ከፈለገ ገንዘባቸውን መጣያ
ካጡ ባለጸጎች ይሰርቃል፡ እሱ ነጻ የሆነ ሰው ነው፡
ስለሄሪ በይበልጥ ማወቅ ፈለገች፡ ከእሱ ጋር ራት ሳትበላ ያሳለፈቻቸው
ቀናት ቁጭት ውስጥ ጣሏት፡፡
ባሮን ጋቦንና ካርል ሃርትማን ከኦክሰንፎርድ ቤተሰብ ቀጥሎ ተቀምጠዋል እነዚህ ሰዎች ይሁዲ ስለሆኑ ነው ገና ወደ መብል ክፍሉ እንደገቡ ሎርድ ኦክሰንፎርድ ክፉኛ የገላመጧቸው፡አብረዋቸው
የተቀመጡት ኦሊስ ፊልድና ፍራንክ ጎርደን ናቸው፡፡ ፍራንክ ጎርደን በዕድሜ
hሄሪ ብዙም የማይበልጥ መልከ መልካም ወጣት ነው፡፡ ኦሊስ ፊልድ ደግሞ
ኑሮ የጠመመበት የመሰለ በዕድሜ ገፋ ያለ ራሰ በራ ሰው ነው፡፡
ፎየንስ ላይ አይሮፕላኑ ሲያርፍ ሁሉም ሰው ከአይሮፕላኑ ወጥቶ
በየፊናው ሲበታተን እነዚህ ሁለት ሰዎች አይሮፕላኑ ውስጥ በመቅረታቸው
የለው ሁሉ መነጋገሪያ ሆነው ነበር፡፡
ሶስተኛው የመመገቢያ ጠረጴዛ ላይ ሉሉ ቤልና ሾርባው ጨው የበዛበት ነው እያሉ ሲያማርሩ የዋሉት ልዕልት ላቪኒያ ተቀምጠዋል ከነሱ ጋር ፎየንስ ላይ የተሳፈሩት ሚስተር ላቭሴይና ሚስስ ሌኔሃን ተቀምጠዋል። ወሬ መለቃቀም የሚወደው ፔርሲ እነዚህ ሰዎች ባልና ሚስት ባይሆኑም የሙሽሮቹን ክፍል እንደሚጋሩ ወሬ ለጠማቸው አውርቷል
ባልና ሚስት ያልሆኑ ሰዎች ይህን ክፍል እንዲይዙ ፓን አሜሪካን አየር
መንገድ እንዴት እንደፈቀደላቸው ማርጋሬት ገርሟታል። አየር መንገዱ ብዙ ሰዎች ወደ አሜሪካ መሄድ ስለፈለጉ ህጉን መጋፋት የግድ ሆኖበታል፡
ፔርሲ ጥቁር የይሁዲዎች ኮፊያ አናቱ ላይ ደፍቷል፡ ማርጋሬት ይህን ስታይ በሳቅ ተንፈቀፈቀች፡፡ ከየት ነው ያመጣው! አባቱ ግን ‹‹ጅል!›› ብለው ተሳድበው ኮፍያውን መንጭቀው ወረወሩት፡፡
ሌዲ ኦክሰንፎርድ ኤልሳቤት ተለይታቸው ከሄደች ወዲህ ለመጀመሪያ
ጊዜ ፊታቸው በመጠኑ ፈካ ብሏል፡፡
ሌዲ ኦክሰንፎርድ ‹‹የራት ሰዓታችን ገና ነው›› አሉ፡፡
ሎርድ ኦክሰንፎርድ ደግሞ ‹‹አንድ ሰዓት ተኩል ሆኗል እኮ›› አሉ፡፡
‹‹ለምንድነው ታዲያ ያልጨለመው?››
‹‹እንግሊዝ አገር አሁን ጨለማ ነው፡ አሁን ግን ከአየርላንድ ባህር
ጠረፍ ሶስት መቶ ማይል ርቀት ላይ ነው የምንገኘው ጸሃይዋን እያሳደድን
ነው›› አለ ፔርሲ፡፡
‹‹መቼም መጨለሙ አይቀርም››
‹‹ምናልባት ሶስት ሰዓት ላይ የሚጨልም ይመስለኛል›› አለ ፔርሲ
‹‹ጥሩ›› አሉ እናት፡፡
እንደማይጨልም
‹‹ጸሃይዋን ተከትለን በፍጥነት ብንጓዝ
እንደማይጨልም ታውቃላችሁ? አለ ፔርሲ፡፡
‹‹እንደዚህ አይነት ፍጥነት ያለው አይሮፕላን የሰው ልጅ ይሰራል ብዬ አልገምትም›› አሉ አባት ከኔ በላይ አዋቂ የለም በሚል ግብዝነት፡
ቦትውድ ካናዳ ለመድረስ አስራ ስድስት ሰዓት ተኩል ይፈጃል›› አለ ፔርሲ ‹‹እዚያ በግሪንዊች ሰዓት አቆጣጠር ከጧቱ ሶስት ሰአት እንደርሳለን››
‹‹ካናዳ ስንት ሰዓት ይሆናል ማለት ነው?,,
‹‹የኒውፋንድላንድ ካናዳ የሰዓት አቆጣጠር ከግሪንዊች የሰዓት አቆጣጠር ሶስት ሰዓት ወደ ኋላ ነው›› አለ ፔርሲ፡፡
እናት የፔርሲን ችሎታ አጤኑና ‹‹ወንዶች የቴክኒክ እውቀት ላይ ጎበዞች ናቸው›› አሉ፡፡
ማርጋሬት በእናቷ አነጋገር ተናደደች፡፡ እናት የቴክኒክ ነገሮች ሴቶች አይገባቸውም ብለው ያምናሉ፡፡ ‹‹ወንዶች ሴቶች ጎበዝ ሲሆኑ አይወዱም››
ብለዋታል ብዙ ጊዜ፡ በዚህ ጉዳይ ማርጋሬት ከእናቷ ጋር እሰጥ አገባ ውስጥ መግባት ባትፈልግም እሷ ግን አታምንበትም፡ ይህን የሚቀበሉ ወንዶች ደደቦች ናቸው ብላ ነው የምትገምተው ጎበዝ ወንድ ጎበዝ ሴት ይወዳል፡
አጠገባቸው ካለው ጠረጴዛ ዙሪያ የተቀመጡት ባሮን ጋቦንና ካርል ሃርትማን ክርክር ገጥመዋል አጠገባቸው ያሉት የጠረጴዛ ተጋሪዎች
ባይገባቸውም በጸጥታ ያዳምጣሉ: ሁለቱ ሰዎች አይሮፕላኑ ላይ ከወጡ
ጀምሮ ጥልቅ ውይይት ሲያደርጉ ይታያሉ፡፡ በዓለም ከታወቀ ሳይንቲስት
ጋር እንደዚህ ያለውን ውይይት የምታደርጉ ከሆነ ውይይቱ ጥብቅ መሆኑ
አያስደንቅም፡፡ በክርክራቸው ውስጥ ፍልስጤምንና እስራኤልን በተደጋጋሚ ያነሳሉ፡ ማርጋሬት የውይይት ርዕሳቸውን ስትሰማ
‹‹አባባ ምን ይል
ይሆን?›› እያለች አስሬ ታያቸዋለች፡፡ እሳቸውም የሁለቱ ሰዎች ውይይት
አልጥም ብሏቸው አኩርፈዋል፡፡ አባቷ ነገር እንዳይጭሩ ርዕስ ለማስለወጥ
‹‹አይሮፕላኑ የሚጓዘው ኃይለኛ ነፋስ በቀላቀለ ዝናብ ውስጥ ነው›› አለች
‹‹እንዴት አወቅሽ?›› አለ ፔርሲ አነጋገሩ ቅናት ያለበት መሆኑ ይታወቃል፡፡ በበረራ መረጃ ከማርጋሬት ይልቅ እሱ ነው ኤክስፐርቱ።
‹‹ሄሪ ነገረኝ››
‹‹እሱ እንዴት ያውቃል?››
‹‹እሱ ዛሬ ራት የበላው ከበረራ መሃንዲሱና ከናቪጌተሩ ጋር ነው፡››
ማርጋሬት ዝናቡ ችግር ይፈጥራል ብላ አልገመተችም፡፡ በእርግጥ
በዝናብ ውስጥ መጓዝ ምቾት ቢነሳም ለክፉ አይሰጥም፡፡
ሎርድ ኦክሰንፎርድ ብርጭቋቸው ውስጥ የቀረውን ቪኖ አጋቡና ሌላ
እንዲጨመርላቸው ቆጣ ብለው ጠየቁ፡፡ ዝናቡ ችግር ያመጣል ብለው ፈሩ
እንዴ? ከተለመደው በላይ እየጠጡ መሆናቸውን ማርጋሬት ተገንዝባለች።
ፊታቸው ከመጠጥ ብዛት ፍም መስሏል: ዓይናቸው ፈጧል፡ ምናልባትም
ነርቭ ሆነዋል፡፡በኤልሳቤት መኮብለል ክፉኛ ተበሳጭተዋል
እናትም ማርጋሬትን ‹‹ሚስተር መምበሪን አጫውቺው›› አሏት፡
ማርጋሬት የእናቷ አባባል ገርሟት ‹‹ለምን?›› ስትል ጠየቀች፡ ሲያዩት
ሰው እንዲያናግረው የሚፈልግ አይመስልም፡
‹‹ምናልባትም አይናፋር ሳይሆን አይቀርም›› አሉ እናት፡፡
እማማ ከመቼ ወዲህ ነው ለአይናፋሮች መቆርቆር የጀመረችው?የሚሆን ነገር አይደለም፡፡ ‹‹ግን ምን ማለትሽ ነው?›› ስትል ጠየቀች ማርጋሬት።
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ኮንችትና ሶራ የሶስተኛ ቀን የኦሞ ወንዝ ላይ ጉዟቸውን
ሲጀምሩ አየሩ ጨፍገግ ያለና ሰማዩ በጥቁር ዳመናዎች የተሸፈነ
ነበር፡፡
“ብንቆይ አይሻልም ኮንችት"
“አይ! አስቸጋሪውን ጉዞ ብንጋፈጠው ይሻላል፡፡ ምናልባት እየተጓዝን ዝናቡን ልናመልጠው እንችል ይሆናል፡፡ስለዚህ ቶሉ
መንቀሳቀሳችን ይሻላል፡"
“ወንዙ ላይ ዝናቡ ከያዘንስ?''
“ያኔ ከወንዙ ወጥተን ድንኳን ወጥረን እንጠለላለን፤ እዚህ
ሆኖ ሳይሞክሩ ተሸናፊ መሆን ግን አልፈልግም" አለችው፡
“እሽ በኔ በኩል ለጉዞ ዝግጁ ነኝ፡፡"
“ቆየኝ አንዴ” ብላው ለመፀዳዳት ወደ ጫካው ገባች፡፡ ሶራ የወንዝ ላይ ጉዞ አስደሳችም አስፈሪም እንደሆነ እየተረዳ መጥቷል፡፡
በተለይ ከመጀመሪው ቀን ቀጥሎ በነበረው ውድቅት ሌሊት አንበሶች የድሪያ ወቅታቸ በመሆኑ ከድንኳናቸው ብዙም ሳይርቅ እያገሱ ሲታገሉ
ኮንችትና ሶራ ከአሁ አሁን ላያችን ላይ ወጡ ገነጣጥለው ሊቀራመቱን ነው ሲሉ እንቅልፍ በዓይናቸው ሳይዞር ነው ያደሩት።
በሁሉተኛው ቀን ደግሞ ድንገት የጣለው ከባድ ዝናብ ድንኳናቸውን በጎርፍ ውጦ ልብሳቸው በሙሉ ረጥቦ በዚያ ጥርስ
በሚፋጨው ብርድ እንደከበት ዛፍ ስር ጎን ለጎን ኵርም† ብለው
አንዱ በሌላው ትንፋሽ ሙቀት እየተጋሩ ነበር የመከራ ሌሊቱን ያሳለፉት።
ስለዚህ በነጋታው እስከ አጥንታችው ድረስ ዘልቆ የገባው ቆፈን እስኪወጣላቸው ፀይይ ላይ ተሰጥተው አረፈዱ ሰውነታቸውን ማዘዝና ማንቀሳቀስ ሲችሉ በጎርፍ የተዋጠውን ድንኳን ነቅለው
እቃውን አውጥተው… ፀሐይ ላይ አሰጡት ከዚያ ረጅም ሰዓት ቆይተው ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ ተነስተው ሰላሳ ኪሎ ሜትር ተጉዘው እንቅልፍና ድካም ተጫጭኖአችው ስለነበር ደረቅ ዳቦና ብስኩት ብቻ ተመግበው ተኙ ልክ እንደሞተ ሰው ተኝተው
አድረው ሲነቁ ስማዩ የታቀፈውን ጥላሽት የመሰለ ዳመና እላያችው
ላይ ሊዘረግፈው ተዘጋጅቷል።
የሶራ ምርጫ ዝናቡን ማሳለፍ ይሻላል ነበር ኮንችት ግን ሃሳቡን ልተቀበለችውም።
አሁን መሄድ እንችላለን የህይወት ማዳኛ ጃኬቱን ልበስ ሱሪውን አውልቀውና የዋና ፓንትህን ታጠቅ አለችው ሶራ የተባለውን እየፈፀመ አያት የለበሰችው የዋና ፓንቷን ነው
ጭኖችዋ ከምን ጊዜውም በላይ አምረዋል: ከላይ ቀይ የህይወት ማዳኛ ጃኬቷን ቀይ ሄልሜቷን ደፍታ ዮጉዞ ቦርሳን ከጀርባሞ አዝላለች ሶራም እንደ እሷ ትጥቁን እያስመረ ስማዩን ቀና ብሎ
አየው ጠቁሯል
ጀልባዋን ውሃው ላይ ካሳረፉ በኋላ ድንኳናቸው
ምግባቸውን የማብሰያ እቃቸውን… ከጀልባው መሀል አስቀምጠው
በጣም አስፈላጊ የሆነውን ቁሳቁስ በጀርባ ቦርሳቸው አዘሉት፡፡ ከዚያ “አድሪፍት" የምትለው ጀልባ ላይ ያለውን ረጅም ገመድ ወገባቸው ላይ ካለው ሰፊ ቀበቶ ጋር አያያዙት፡፡
ጀልባዋ ላይ ወጥተው ሚዛናቸውን ለመጠበቅ ከኋላ በኩል ግራና ቀኙ ተቀመጡና መቅዘፊያቸውን አንስተው አውራ ጣታቸውን
በማንሳት ዝግጁ ተባባሉና ወደ ኦሞ ወንዝ መሃል ሄደው ቁልቁል ቀዘፉ
ሰማዩ እንደ ተቆጣ ነብር ማጉረምረም ጀመረ። ድንገት ሰማዩ በቀጫጭን የብርሃን ዝግዛግ እየተሰነጣጠቀ ብልጭታው
ይታይና ብራቁ ድብልቅልቅ ብሎ መጮሁ እየጨመረ ሄደ፡፡
“ኮንችት!” ብሎ ጠርቶ አያት፡፡ ቶሎ ቶሎ ትቀዝፋለች ለማምለጥ፡፡ ድክም ያላት መሆኑ በዚያ ቆፈን የሚወርደው ላቧ ያስታውቃል፡፡ ሶራ አዘነላት፡፡ ምን ሊያደርግላት እንደሚችል አሰበ፡፡
መላው አጥጋቢ አልመሰለውም፡፡ ይሻል ይሆናል ብሎ ገመተና ጮክ
በማለት ደግሞ ጠራት፡-
“ኮንችት…….” ሲል ሰማዩ ብልጭልጭ አለና የጆሮ
ታንቡራቸው የተነደለ እስኪመስል ብራቁ ጮኸ፡፡ሁለቱም በደመነፍስ ዝቅ አሉ በድንጋጤ፡፡
ኮንቺት አያቷ ትዝ አላት አደራው ተጭኗት ኖሯል፡፡
ማንኛውንም መስዋዕትነት ከፍላ አደራውን መፈፀም መቻል አለበት፡፡ህሊናዋ ከዚህ ግዴታዋ ውልፍት እንድትል አይፈቅድላትም፡፡ የዚያ ምስኪን ኢትዮጵያዊ አያቷን ዘመዶች ከመፈለግ ከአቅሟ በላይ በሆነ
ችግር ሞት ጥፍሩን አሽሎ መጣሁ' እያለ ቢያስፈራራትም እንኳ
ላለመሽሽ ለራሷ ቃል ገብታለች፡፡ ብዙ ጊዜ በዚህ ጉዳይ ላይ አስባ
ከማያዳግም ውሳኔ ላይ ደርሳለች፡፡
ብራቁ ካለፈ በኋላ ማጉረምረሙ እየበዛ የመጣውን ሰማይ ቀና ብሎ አየና ሶራ ኮንችትን አያት፡፡ ከዝያቡ ሊያድናት ፈለገ
ስለዚህ ጮክ ብሎ ጠራት
ኮንችት ለምን ጉዞውን አቁመን እንጠለልም፡፡ ከዚያ…" ብሎ ሃሣቡን ሳይጨርስ ገሃነም ግባ እሽ ቦቅቧቃ ፈሪ ነህ! ወደፈለግበት መሄድ
ትችላለህ! እኔን ግን አትጥራኝ ደደብ!" አለችው፡ ሶራ መብረቁ ጭንቅላቱ ላይ እንደወደቀ ሁሉ ክው አለ። ስላዘነላት ነበር የጠየቃት እሷ ግን አውሬ ሆነችበት ።
ሶራ እንደተወጋ አውሬ ሸቅሽቆት ውስጡ የገባው አነጋገሯ አደነዘዘው አበሸቀው።
ዝናቡ ህፃናት የሚጫወቱበትን ብይ እያካከለ ዥጉድጉድ
ብሎ መውረድ ጀመረ፡፡ ኮንችትና ሶራ ማየት እንኳ ተሳናቸው፡፡የመዋኛ መነፅራቸውን አደረጉ: ጉሙ እየሸፈነ ይበልጥ ማየት
ተሳናቸው፡ ቀስ እያለ ደግሞ አዙሪቱ ሰማያዊ ጀልባዋን ወደ ታች ሳይሆን እንባለሌ ያዞራት ጀመር፡፡
ሁለቱም ባለ ሃይላቸው ቀዘፉ አዙሪቱ ደግሞ እነሱን
ይበልጥ እያሽከረከረ ቀዘፋቸው፡፡ ቁልቁልና ሽቅቡ ዳሩና መሃሉ እስኪጠፋቸው ድረስ ከላይ ዝናቡ ከታች ዙሪቱ ልባቸውን
አጠፈው፡
ድንገት ደግሞ ዥው ብለው በአየር ላይ ሲንሳፈፉ እነሱ
ከሥር ጀልባዋና ውሃው ከላይ ሆኑ፡፡ ከሁሉም የከፋው አዲስ መከራ
ተጀመረ፡፡ ኮንችትና ሶራ ውሃው ያላጋቸዋል ያሰጥማቸዋል። ዝናቡ
ከላይ ዶፉን ያወርደዋል፡፡ ወገባቸው ላይ ገመዷን ያሰሯት ጀልባም
ወዲህ ወዲያ ትመነጭቃቸዋለች በጀልባዋ ወለል የነበረውን
ጓዛቸውንም ኦሞ ሰለቀጠው፡፡
ሰማዩ አልበቃውም ያጉረመርማል ይጮሃል፤
ይወርዳል. ኦሞ ወንዝም እርጋታው ጠፍቶ ይደነፋል ይሽከረከራል እላይ ደርሶ ይፈርጣል አሶች አዞዎችና ጉማሬዎች የሚሉትና
የሆኑት አይታወቅም፡፡ ኮንችትና ሶራ ግን አበሳቸውን ያያሉ። በኒያ
ወጣቶች መሃል ውሃ ገባ በቅጽበት እንደ ተራራ የገዘፈ ችግርና መከራ ላያቸው ላይ ተከመረ ይባስ ብሎ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ አካባቢውን ፅልመት አለበሰው፡፡ ኮንችት መከራው ሲበዛባት ያመለጠች መስሏት የጀልባዋን ገመድ ከጎኗ ፈታችው፡፡ ከዚያ ከሶራና ከጀልባዋ ተጠፋፋች… እሪ ይላል ሰማዩ፡- አካባቢው
በእሮሮ በእግዚኦታ ተዋጠ፡፡
ሶራ ጀልባዋ እየጎተተችው ብዙ ከተጓዘ በኋላ በጭንቅ ወደ ዳር ወጣ፡፡ የይወት ማዳኛ ጃኬቱና ሄልሜቱ ነፍሱን አተረፋት፡ ዝናቡ ቆሟል ቀና ብሉ ሰማዩን አየ፡፡ ሰማዩ ጠርቷልı ጨረቃ ወጥታለች ከዋክብት ብልጭ ድርግም ይላሉ፡፡ ሶራ የሆነውን ሁሉ
ለማሰብ ሞከረ፡፡
ጀልባዋ ከሱ ጋር ነች፡፡ ኮንችት ግን አብራው የለችም፡ ያች መለሎዋ ያች ኢትዮጵያዊት ደፋርና የፍቅር ልዕልቱ አጠገቡ
የለችም፡፡ ከጀልባዋ ጋር ያያዘችው ገመድ ተበጥሷል፡፡
ሶራ ኦሞን ዞር ብሉ አየው፡፡
“ኦሞ አላማ ያለውን ሰው እውን ትበላለህ?” ብሎት ማልቀስ ጀመረ ሶራ። ጮኸ “ፍቅሬን ምሳሌዬን… ተነጠቅሁ” ብሎ ቀና
ብሎ ሰማዩን እያዬ ተማፀነ፡፡
እኔንም መብላት አለብህ ኦሞ፡፡ልትነጣጥለን አይገባም ሲሆን እኔን ማስቀደም ነበረብህ…” እየተንቀጠቀጠ አለቀሰ፡፡
“ምነው እግዚአብሔር... ምነው! የኦሞ ወንዝ ዳርን ጭቃ እያፈሰ ፊቱን እየቀባ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ ለአምላኩ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ኮንችትና ሶራ የሶስተኛ ቀን የኦሞ ወንዝ ላይ ጉዟቸውን
ሲጀምሩ አየሩ ጨፍገግ ያለና ሰማዩ በጥቁር ዳመናዎች የተሸፈነ
ነበር፡፡
“ብንቆይ አይሻልም ኮንችት"
“አይ! አስቸጋሪውን ጉዞ ብንጋፈጠው ይሻላል፡፡ ምናልባት እየተጓዝን ዝናቡን ልናመልጠው እንችል ይሆናል፡፡ስለዚህ ቶሉ
መንቀሳቀሳችን ይሻላል፡"
“ወንዙ ላይ ዝናቡ ከያዘንስ?''
“ያኔ ከወንዙ ወጥተን ድንኳን ወጥረን እንጠለላለን፤ እዚህ
ሆኖ ሳይሞክሩ ተሸናፊ መሆን ግን አልፈልግም" አለችው፡
“እሽ በኔ በኩል ለጉዞ ዝግጁ ነኝ፡፡"
“ቆየኝ አንዴ” ብላው ለመፀዳዳት ወደ ጫካው ገባች፡፡ ሶራ የወንዝ ላይ ጉዞ አስደሳችም አስፈሪም እንደሆነ እየተረዳ መጥቷል፡፡
በተለይ ከመጀመሪው ቀን ቀጥሎ በነበረው ውድቅት ሌሊት አንበሶች የድሪያ ወቅታቸ በመሆኑ ከድንኳናቸው ብዙም ሳይርቅ እያገሱ ሲታገሉ
ኮንችትና ሶራ ከአሁ አሁን ላያችን ላይ ወጡ ገነጣጥለው ሊቀራመቱን ነው ሲሉ እንቅልፍ በዓይናቸው ሳይዞር ነው ያደሩት።
በሁሉተኛው ቀን ደግሞ ድንገት የጣለው ከባድ ዝናብ ድንኳናቸውን በጎርፍ ውጦ ልብሳቸው በሙሉ ረጥቦ በዚያ ጥርስ
በሚፋጨው ብርድ እንደከበት ዛፍ ስር ጎን ለጎን ኵርም† ብለው
አንዱ በሌላው ትንፋሽ ሙቀት እየተጋሩ ነበር የመከራ ሌሊቱን ያሳለፉት።
ስለዚህ በነጋታው እስከ አጥንታችው ድረስ ዘልቆ የገባው ቆፈን እስኪወጣላቸው ፀይይ ላይ ተሰጥተው አረፈዱ ሰውነታቸውን ማዘዝና ማንቀሳቀስ ሲችሉ በጎርፍ የተዋጠውን ድንኳን ነቅለው
እቃውን አውጥተው… ፀሐይ ላይ አሰጡት ከዚያ ረጅም ሰዓት ቆይተው ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ ተነስተው ሰላሳ ኪሎ ሜትር ተጉዘው እንቅልፍና ድካም ተጫጭኖአችው ስለነበር ደረቅ ዳቦና ብስኩት ብቻ ተመግበው ተኙ ልክ እንደሞተ ሰው ተኝተው
አድረው ሲነቁ ስማዩ የታቀፈውን ጥላሽት የመሰለ ዳመና እላያችው
ላይ ሊዘረግፈው ተዘጋጅቷል።
የሶራ ምርጫ ዝናቡን ማሳለፍ ይሻላል ነበር ኮንችት ግን ሃሳቡን ልተቀበለችውም።
አሁን መሄድ እንችላለን የህይወት ማዳኛ ጃኬቱን ልበስ ሱሪውን አውልቀውና የዋና ፓንትህን ታጠቅ አለችው ሶራ የተባለውን እየፈፀመ አያት የለበሰችው የዋና ፓንቷን ነው
ጭኖችዋ ከምን ጊዜውም በላይ አምረዋል: ከላይ ቀይ የህይወት ማዳኛ ጃኬቷን ቀይ ሄልሜቷን ደፍታ ዮጉዞ ቦርሳን ከጀርባሞ አዝላለች ሶራም እንደ እሷ ትጥቁን እያስመረ ስማዩን ቀና ብሎ
አየው ጠቁሯል
ጀልባዋን ውሃው ላይ ካሳረፉ በኋላ ድንኳናቸው
ምግባቸውን የማብሰያ እቃቸውን… ከጀልባው መሀል አስቀምጠው
በጣም አስፈላጊ የሆነውን ቁሳቁስ በጀርባ ቦርሳቸው አዘሉት፡፡ ከዚያ “አድሪፍት" የምትለው ጀልባ ላይ ያለውን ረጅም ገመድ ወገባቸው ላይ ካለው ሰፊ ቀበቶ ጋር አያያዙት፡፡
ጀልባዋ ላይ ወጥተው ሚዛናቸውን ለመጠበቅ ከኋላ በኩል ግራና ቀኙ ተቀመጡና መቅዘፊያቸውን አንስተው አውራ ጣታቸውን
በማንሳት ዝግጁ ተባባሉና ወደ ኦሞ ወንዝ መሃል ሄደው ቁልቁል ቀዘፉ
ሰማዩ እንደ ተቆጣ ነብር ማጉረምረም ጀመረ። ድንገት ሰማዩ በቀጫጭን የብርሃን ዝግዛግ እየተሰነጣጠቀ ብልጭታው
ይታይና ብራቁ ድብልቅልቅ ብሎ መጮሁ እየጨመረ ሄደ፡፡
“ኮንችት!” ብሎ ጠርቶ አያት፡፡ ቶሎ ቶሎ ትቀዝፋለች ለማምለጥ፡፡ ድክም ያላት መሆኑ በዚያ ቆፈን የሚወርደው ላቧ ያስታውቃል፡፡ ሶራ አዘነላት፡፡ ምን ሊያደርግላት እንደሚችል አሰበ፡፡
መላው አጥጋቢ አልመሰለውም፡፡ ይሻል ይሆናል ብሎ ገመተና ጮክ
በማለት ደግሞ ጠራት፡-
“ኮንችት…….” ሲል ሰማዩ ብልጭልጭ አለና የጆሮ
ታንቡራቸው የተነደለ እስኪመስል ብራቁ ጮኸ፡፡ሁለቱም በደመነፍስ ዝቅ አሉ በድንጋጤ፡፡
ኮንቺት አያቷ ትዝ አላት አደራው ተጭኗት ኖሯል፡፡
ማንኛውንም መስዋዕትነት ከፍላ አደራውን መፈፀም መቻል አለበት፡፡ህሊናዋ ከዚህ ግዴታዋ ውልፍት እንድትል አይፈቅድላትም፡፡ የዚያ ምስኪን ኢትዮጵያዊ አያቷን ዘመዶች ከመፈለግ ከአቅሟ በላይ በሆነ
ችግር ሞት ጥፍሩን አሽሎ መጣሁ' እያለ ቢያስፈራራትም እንኳ
ላለመሽሽ ለራሷ ቃል ገብታለች፡፡ ብዙ ጊዜ በዚህ ጉዳይ ላይ አስባ
ከማያዳግም ውሳኔ ላይ ደርሳለች፡፡
ብራቁ ካለፈ በኋላ ማጉረምረሙ እየበዛ የመጣውን ሰማይ ቀና ብሎ አየና ሶራ ኮንችትን አያት፡፡ ከዝያቡ ሊያድናት ፈለገ
ስለዚህ ጮክ ብሎ ጠራት
ኮንችት ለምን ጉዞውን አቁመን እንጠለልም፡፡ ከዚያ…" ብሎ ሃሣቡን ሳይጨርስ ገሃነም ግባ እሽ ቦቅቧቃ ፈሪ ነህ! ወደፈለግበት መሄድ
ትችላለህ! እኔን ግን አትጥራኝ ደደብ!" አለችው፡ ሶራ መብረቁ ጭንቅላቱ ላይ እንደወደቀ ሁሉ ክው አለ። ስላዘነላት ነበር የጠየቃት እሷ ግን አውሬ ሆነችበት ።
ሶራ እንደተወጋ አውሬ ሸቅሽቆት ውስጡ የገባው አነጋገሯ አደነዘዘው አበሸቀው።
ዝናቡ ህፃናት የሚጫወቱበትን ብይ እያካከለ ዥጉድጉድ
ብሎ መውረድ ጀመረ፡፡ ኮንችትና ሶራ ማየት እንኳ ተሳናቸው፡፡የመዋኛ መነፅራቸውን አደረጉ: ጉሙ እየሸፈነ ይበልጥ ማየት
ተሳናቸው፡ ቀስ እያለ ደግሞ አዙሪቱ ሰማያዊ ጀልባዋን ወደ ታች ሳይሆን እንባለሌ ያዞራት ጀመር፡፡
ሁለቱም ባለ ሃይላቸው ቀዘፉ አዙሪቱ ደግሞ እነሱን
ይበልጥ እያሽከረከረ ቀዘፋቸው፡፡ ቁልቁልና ሽቅቡ ዳሩና መሃሉ እስኪጠፋቸው ድረስ ከላይ ዝናቡ ከታች ዙሪቱ ልባቸውን
አጠፈው፡
ድንገት ደግሞ ዥው ብለው በአየር ላይ ሲንሳፈፉ እነሱ
ከሥር ጀልባዋና ውሃው ከላይ ሆኑ፡፡ ከሁሉም የከፋው አዲስ መከራ
ተጀመረ፡፡ ኮንችትና ሶራ ውሃው ያላጋቸዋል ያሰጥማቸዋል። ዝናቡ
ከላይ ዶፉን ያወርደዋል፡፡ ወገባቸው ላይ ገመዷን ያሰሯት ጀልባም
ወዲህ ወዲያ ትመነጭቃቸዋለች በጀልባዋ ወለል የነበረውን
ጓዛቸውንም ኦሞ ሰለቀጠው፡፡
ሰማዩ አልበቃውም ያጉረመርማል ይጮሃል፤
ይወርዳል. ኦሞ ወንዝም እርጋታው ጠፍቶ ይደነፋል ይሽከረከራል እላይ ደርሶ ይፈርጣል አሶች አዞዎችና ጉማሬዎች የሚሉትና
የሆኑት አይታወቅም፡፡ ኮንችትና ሶራ ግን አበሳቸውን ያያሉ። በኒያ
ወጣቶች መሃል ውሃ ገባ በቅጽበት እንደ ተራራ የገዘፈ ችግርና መከራ ላያቸው ላይ ተከመረ ይባስ ብሎ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ አካባቢውን ፅልመት አለበሰው፡፡ ኮንችት መከራው ሲበዛባት ያመለጠች መስሏት የጀልባዋን ገመድ ከጎኗ ፈታችው፡፡ ከዚያ ከሶራና ከጀልባዋ ተጠፋፋች… እሪ ይላል ሰማዩ፡- አካባቢው
በእሮሮ በእግዚኦታ ተዋጠ፡፡
ሶራ ጀልባዋ እየጎተተችው ብዙ ከተጓዘ በኋላ በጭንቅ ወደ ዳር ወጣ፡፡ የይወት ማዳኛ ጃኬቱና ሄልሜቱ ነፍሱን አተረፋት፡ ዝናቡ ቆሟል ቀና ብሉ ሰማዩን አየ፡፡ ሰማዩ ጠርቷልı ጨረቃ ወጥታለች ከዋክብት ብልጭ ድርግም ይላሉ፡፡ ሶራ የሆነውን ሁሉ
ለማሰብ ሞከረ፡፡
ጀልባዋ ከሱ ጋር ነች፡፡ ኮንችት ግን አብራው የለችም፡ ያች መለሎዋ ያች ኢትዮጵያዊት ደፋርና የፍቅር ልዕልቱ አጠገቡ
የለችም፡፡ ከጀልባዋ ጋር ያያዘችው ገመድ ተበጥሷል፡፡
ሶራ ኦሞን ዞር ብሉ አየው፡፡
“ኦሞ አላማ ያለውን ሰው እውን ትበላለህ?” ብሎት ማልቀስ ጀመረ ሶራ። ጮኸ “ፍቅሬን ምሳሌዬን… ተነጠቅሁ” ብሎ ቀና
ብሎ ሰማዩን እያዬ ተማፀነ፡፡
እኔንም መብላት አለብህ ኦሞ፡፡ልትነጣጥለን አይገባም ሲሆን እኔን ማስቀደም ነበረብህ…” እየተንቀጠቀጠ አለቀሰ፡፡
“ምነው እግዚአብሔር... ምነው! የኦሞ ወንዝ ዳርን ጭቃ እያፈሰ ፊቱን እየቀባ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ ለአምላኩ
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ+ነበረ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////
ትንፋሽ ወሰድኩና ከመተኛቴ በፊት ከአያቴ ጋር ለማውራት አፌን ከፈትኩ…አያቴ እንዳልተኙ በመብራቱ አለመጥፋት እና በዕቃ መንኳኳት ማወቅ ችያለሁ፡፡
‹‹አያቴ ጉዴን እየሰሙ ነው አይደል?››
መልስ የለም
‹‹አያቴ ይሰሙኛል?››
መልስ የለም
‹‹እንዴ..ያን የተለመደ ዝምታቸውን ጀመሩ ማለት ነው..?አሁን በዚህ ከእሳቸው ጋር ማውራት በፈለኩ ቀን ዝም ይላሉ..››ብዬ ተሰፋ በመቁረጥ ልተኛ ልብሴን ማውለቅ ስጀምር በጆሮዬ ደምፅ ሰማሁ፣፣
‹ምንድነው… አያቴ ሙዚቃ…?››ወደግድግዳው ተጠጋሁና ጆሮዬን ቀስሬ አዳመጥኩ….ውይ እለተ ምፅአት ደርሶል መሰለኝ…ከአያቴ ቤት የሲሊንዲዮን ዘፈን እየተሰማ ነው…፡፡
‹‹አያቴ እኔ አላምንም…ሰሞኑን በጣም እያስደመሙኝ ነው..ከቤት ለመውጣት መወሰኖት ሳያንስ ጭራሽ የፈረንጅ ሙዚቃ….በአንዴ ግን እንዲህ አይነት ለውጥ አይከብድም.?
አሁንም ፀጥታ ነው….
‹‹አያቴ ምንም የማያናግሩኝ ከሆነ በፊት ለፊት በራፍ ዞሬ መምጣቴ ነው..››
‹‹በፊት ለፊት በራፍ… ተው ይቅርብህ..አታድርገው››
‹‹ምን ?››የባሰ አለ ጆሮዬን ማመን አልቻልኩም
‹‹ሰምተሀል››
አዎ በደንብ ሰምቼያለሁ… አያቴ ቤት ሴት….አረ አይደረግም…እያናገረችኝ ያለችው ሴት ነች..ወጣት ሴት፡፡
‹‹አያቴ የሉም እንዴ?››
‹‹አያትህ የለም››ለስላሳ ለጋ የሴት ድምፅ መልስ ሰጠኝ፡፡
‹‹ይቅርታ ማን ልበል….?››ግራ በመጋባት ተሞልቼ ጠየቅኩ፡፡
‹በዚህ ውድቅት ለሊት ከአዲስ ሰው ጋር መተዋወቅ አይክብድም..?ይቅርታ ጥዋት እንተዋወቃለን… ባይሆን አሁን የአያትህን መልዕክት ተቀበለኝ..››
ከአያቴ ጋር እቃ ወደምንቀባበልበት ስንጥቅ አመራሁ...ለግላጋ ጠይም የእጅ እጣት ብጣሽ ወረቀት አቀበለኝ.. .ተቀበልኳት እና ወደአልጋው ተመለስኩ… ገለጥኩና ማንበብ ጀመርኩ፡፡
ልጄ ሳልነግርህ ይህን በማድረጌ ይቅርታ..ለአንድ ወር ወደገዳም ሄጄያለሁ…ትንሽ በፅሞና ከእግዚያብሄር ጋር ማውራት አምሮኛል…ልክ የዛሬ ወር ተመልሼ እመጣለሁ...እስከዛ የምወዳት የልጅ ልጄ ማራናታ ካንተ ጋር እንድትቆይልኝ እፈልጋለሁ፡፡ያው ከሰሎሞን ሚስት ማለት ከእንጀራ እናቷ ጋር አምርራ ስለማትስማማ እነሱ ጋር መቀመጥ አትችልም…እኔ ወደገዳም መሄዱን ቀድሜ የያዝኩት ቀጠሮ ነው… ከእግዚያሄር ጋር የያዝኩትን ቀጠሮ ማስተጓጎል አልችልኩም…እሷ ደግሞ ድንገት መጣችብኝ….ግን ያው አንተ ልጄን ከእራሴ በላይ ስለማምንህ ልክ እንደእኔ አረገህ ከእኔም በላይ እንደምትጠብቃትና እንደምትንከበከባት ቅንጣት ጥርጣሬ አይገባኝም…ቀንም ስራም ሆነ ሌላ ቦታ ስትሄድ ይዘሀት ሂድ…ማታም ጥለሀት ውጭ እንዳታድር..ነግሬሀለው አንተ ወሽካታ..ደግሞ ለእሷም እንዳታስቸግርህ ነግሬያታለሁ...አደራ አንተ ቀልማዳ እናንተ ሁለታችሁ በአለም ላይ እጅግ የምወዳችሁ የልጅ ልጆቼ ናችሁና ተመልሼ እስክመጣ በመደጋገፉ ጊዜችሁን በጥሩ ሁኔታ አሳልፉ.፡፡
ያንተው አያት ሙሉአለም ነኝ፡፡
‹‹እህት ይቅርታ ማራናታ ይሄ ምንድነው..?አያቴ ምንድነው የሰሩት?››
‹‹ያው አያትህ የሰራው እንዳነበብከው ነው›
‹‹እያሾፍሽ ነው እንዴ?››
‹አንተ እንዴት ነው የምታናግረኝ እንግዳህ እኮ ነኝ…ከደበረህ ነገ ጥዋት ተነስቼ ወደ ሀገሬ እበራለሁ..››
‹‹አረ በፈጣሪ ..ነገሩ ዱብ እዳ ሆኖብኝ እንጂ እንደዛ ማለቴ አይደለም...አሁን እራት በልተሻል..?››
‹‹አዎ በልቼያለሁ››
‹‹ሌላ የምትፈልጊው ነገር አለ….?››
‹‹አዎ አንድ ጠርሙስ ቢራ ባገኝ ደስ ይለኝ ነበር..››
‹‹እሺ አሁን አመጣልሻለሁ.››.ከአልጋዬ ተነሳሁና ጫማዬን ማድረግ ጀመርኩ
‹‹ምነው አለህ እንዴ?››ጠየቀችኘ
‹‹አይ የለኝም ግን አታስቢ አሁን ገዝቼ መጠለሁ. ምንድነው ሚመችሽ ማለት ጊርጊስ፤ በደሌ፤ሀረር ..››
‹‹አራት ሰዓት እኮ አልፏል..የእውነት አሁን በዚህ ሰዓት ሄደህ ልትገዛልኝ ነው?›
‹‹አራት ሰዓት አይደለም ስድስት ሰዓትስ ቢሆን ምን ችግር አለው…የአያቴ አደራ እኮ ነሽ…››
‹‹በል ስቀልድ ነው..አሁን አልፈልግም ነገ ትጋብዘኛለህ››
‹‹እውነተሽን ነው…?››
‹‹.አዎ አሁን ስለደከመኝ እንቅልፌ መጥቷል …ቻው ደህና እደር..››
‹‹ደህና እደሪ …ለሊት በማንኛውም ሰዓት የምትፈልጊው ምንም ነገር ቢኖር ንገሪኝ..››
‹‹ለሊት ምንም ነገር ብፈልግ?››ሳቅ ባፈነው ድምፅ
‹‹አዎ ምንም ነገር ብትፈልጊ..››
‹‹እሺ ነግርሀለሁ.. .አሁን ደህና እደር››
‹‹ደህና እደሪ›› ብዬ ሳደርግ የነበረውን ጫማ መልሼ አወለቅኩና ወደ አልጋዬ ወጣሁ...ከልጅቷ ጋር በግድግዳ ወዲህ ማዶና ወዲያ ማዶ ሆነን የተነጋገርናቸውን ነገሮች መልሼ ሳስብ...ልጅቷ ልክ እንደ አያቴ ተንኮለኛ ቢጤ ነች መሰለኝ ስል አሰብኩና ፈገግ አልኩ…
ስለእዚህች ልጅ አያቴ ለብዙ ቀን አውርተውኛል..በየ15 ቀኑም ደብደቤ እየጻፉ እየሰጡኝ ለረጂም ጊዜ ፖሰታ ቤት ወስጄ የማስገባላቸው አኔ ስለሆንኩ ስለእሷ በመጠኑ አውቃለሁ..…ለምሳሌ የድሬደዋ ልጅ መሆኗን..ከእናቷ ጋር እንደምትኖርና… ጋሽ ሰለሞን የአሁኗን ሚስቱን ከማግባቱ በፊት እናትዬውን አግብቶ እሷን ከወለደ በኃላ እንደተፋቱ ከዛ እናትዬው ልጆን ይዛ ቤተሰቦቾ ጋር ድሬደዋ እንደገባች አውቃለሁ…አያቴም ከቤት አልወጣም ብለው እራሳቸውን ኳራንቲን ከማስገባቸው በፊት ቢያንስ በስድስት ወር አንዴ እየሄዱ እንደሚጠይቋት እሷም አልፎ አልፎ እየመጣች ትጠይቃቸው እንደነበረ መረጃው አለኝ ….ከልጃቸው ከጋሽ ሰለሞን በላይ ከእሷ ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንዳላቸውም አውቃለሁ....ሌላው በ1987 ዓ.ምህረት እንደተወለደች ነግረውኛል…ያ ማለት ይህቺ የሚቀጥለው ክፍል ውስጥ ያለች ወጣት አሁን 25 ዓመቷ ነው፡ በትምህርቷ በአካውንቲንግ ዲግሪ አላት…የእናቷ ቤተሰቦች ሀብታም ነጋዴዎች ስለሆኑ የራሷ ቡቲክ ከፍተውላት እየሰራች እንደሆነም አውቃለሁ...በቃ ስለእሷ የማውቀው ይሄንን ያህል ብቻ ነው ፡፡በተረፈ ቀጭን ትሁን ወፍራም..ቀይ ትሁን ጥቁር..ረጀም ትሁን አጭር ….ትሁት ትሁን መሰሪ ምንም አላውቅም….ምንም ፡፡ ግን ምንም ትሁን ምንም ለአንድ ወር የእኔ ኃላፊት ነች.. ፡፡ ያንን ኃላፊነት ደግሞ ያለምንም ማቅማማት በፍጽም ትዕግስት እና ብቃት እወጣለሁ...ምክንያቱም ያዘዙኝ አያቴ ናቸው..አሁን ልተኛ….ነገ ምን አልባት ረጅም ቀን ሊሆን ይችላል፡፡
✨ይቀጥላል✨
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////
ትንፋሽ ወሰድኩና ከመተኛቴ በፊት ከአያቴ ጋር ለማውራት አፌን ከፈትኩ…አያቴ እንዳልተኙ በመብራቱ አለመጥፋት እና በዕቃ መንኳኳት ማወቅ ችያለሁ፡፡
‹‹አያቴ ጉዴን እየሰሙ ነው አይደል?››
መልስ የለም
‹‹አያቴ ይሰሙኛል?››
መልስ የለም
‹‹እንዴ..ያን የተለመደ ዝምታቸውን ጀመሩ ማለት ነው..?አሁን በዚህ ከእሳቸው ጋር ማውራት በፈለኩ ቀን ዝም ይላሉ..››ብዬ ተሰፋ በመቁረጥ ልተኛ ልብሴን ማውለቅ ስጀምር በጆሮዬ ደምፅ ሰማሁ፣፣
‹ምንድነው… አያቴ ሙዚቃ…?››ወደግድግዳው ተጠጋሁና ጆሮዬን ቀስሬ አዳመጥኩ….ውይ እለተ ምፅአት ደርሶል መሰለኝ…ከአያቴ ቤት የሲሊንዲዮን ዘፈን እየተሰማ ነው…፡፡
‹‹አያቴ እኔ አላምንም…ሰሞኑን በጣም እያስደመሙኝ ነው..ከቤት ለመውጣት መወሰኖት ሳያንስ ጭራሽ የፈረንጅ ሙዚቃ….በአንዴ ግን እንዲህ አይነት ለውጥ አይከብድም.?
አሁንም ፀጥታ ነው….
‹‹አያቴ ምንም የማያናግሩኝ ከሆነ በፊት ለፊት በራፍ ዞሬ መምጣቴ ነው..››
‹‹በፊት ለፊት በራፍ… ተው ይቅርብህ..አታድርገው››
‹‹ምን ?››የባሰ አለ ጆሮዬን ማመን አልቻልኩም
‹‹ሰምተሀል››
አዎ በደንብ ሰምቼያለሁ… አያቴ ቤት ሴት….አረ አይደረግም…እያናገረችኝ ያለችው ሴት ነች..ወጣት ሴት፡፡
‹‹አያቴ የሉም እንዴ?››
‹‹አያትህ የለም››ለስላሳ ለጋ የሴት ድምፅ መልስ ሰጠኝ፡፡
‹‹ይቅርታ ማን ልበል….?››ግራ በመጋባት ተሞልቼ ጠየቅኩ፡፡
‹በዚህ ውድቅት ለሊት ከአዲስ ሰው ጋር መተዋወቅ አይክብድም..?ይቅርታ ጥዋት እንተዋወቃለን… ባይሆን አሁን የአያትህን መልዕክት ተቀበለኝ..››
ከአያቴ ጋር እቃ ወደምንቀባበልበት ስንጥቅ አመራሁ...ለግላጋ ጠይም የእጅ እጣት ብጣሽ ወረቀት አቀበለኝ.. .ተቀበልኳት እና ወደአልጋው ተመለስኩ… ገለጥኩና ማንበብ ጀመርኩ፡፡
ልጄ ሳልነግርህ ይህን በማድረጌ ይቅርታ..ለአንድ ወር ወደገዳም ሄጄያለሁ…ትንሽ በፅሞና ከእግዚያብሄር ጋር ማውራት አምሮኛል…ልክ የዛሬ ወር ተመልሼ እመጣለሁ...እስከዛ የምወዳት የልጅ ልጄ ማራናታ ካንተ ጋር እንድትቆይልኝ እፈልጋለሁ፡፡ያው ከሰሎሞን ሚስት ማለት ከእንጀራ እናቷ ጋር አምርራ ስለማትስማማ እነሱ ጋር መቀመጥ አትችልም…እኔ ወደገዳም መሄዱን ቀድሜ የያዝኩት ቀጠሮ ነው… ከእግዚያሄር ጋር የያዝኩትን ቀጠሮ ማስተጓጎል አልችልኩም…እሷ ደግሞ ድንገት መጣችብኝ….ግን ያው አንተ ልጄን ከእራሴ በላይ ስለማምንህ ልክ እንደእኔ አረገህ ከእኔም በላይ እንደምትጠብቃትና እንደምትንከበከባት ቅንጣት ጥርጣሬ አይገባኝም…ቀንም ስራም ሆነ ሌላ ቦታ ስትሄድ ይዘሀት ሂድ…ማታም ጥለሀት ውጭ እንዳታድር..ነግሬሀለው አንተ ወሽካታ..ደግሞ ለእሷም እንዳታስቸግርህ ነግሬያታለሁ...አደራ አንተ ቀልማዳ እናንተ ሁለታችሁ በአለም ላይ እጅግ የምወዳችሁ የልጅ ልጆቼ ናችሁና ተመልሼ እስክመጣ በመደጋገፉ ጊዜችሁን በጥሩ ሁኔታ አሳልፉ.፡፡
ያንተው አያት ሙሉአለም ነኝ፡፡
‹‹እህት ይቅርታ ማራናታ ይሄ ምንድነው..?አያቴ ምንድነው የሰሩት?››
‹‹ያው አያትህ የሰራው እንዳነበብከው ነው›
‹‹እያሾፍሽ ነው እንዴ?››
‹አንተ እንዴት ነው የምታናግረኝ እንግዳህ እኮ ነኝ…ከደበረህ ነገ ጥዋት ተነስቼ ወደ ሀገሬ እበራለሁ..››
‹‹አረ በፈጣሪ ..ነገሩ ዱብ እዳ ሆኖብኝ እንጂ እንደዛ ማለቴ አይደለም...አሁን እራት በልተሻል..?››
‹‹አዎ በልቼያለሁ››
‹‹ሌላ የምትፈልጊው ነገር አለ….?››
‹‹አዎ አንድ ጠርሙስ ቢራ ባገኝ ደስ ይለኝ ነበር..››
‹‹እሺ አሁን አመጣልሻለሁ.››.ከአልጋዬ ተነሳሁና ጫማዬን ማድረግ ጀመርኩ
‹‹ምነው አለህ እንዴ?››ጠየቀችኘ
‹‹አይ የለኝም ግን አታስቢ አሁን ገዝቼ መጠለሁ. ምንድነው ሚመችሽ ማለት ጊርጊስ፤ በደሌ፤ሀረር ..››
‹‹አራት ሰዓት እኮ አልፏል..የእውነት አሁን በዚህ ሰዓት ሄደህ ልትገዛልኝ ነው?›
‹‹አራት ሰዓት አይደለም ስድስት ሰዓትስ ቢሆን ምን ችግር አለው…የአያቴ አደራ እኮ ነሽ…››
‹‹በል ስቀልድ ነው..አሁን አልፈልግም ነገ ትጋብዘኛለህ››
‹‹እውነተሽን ነው…?››
‹‹.አዎ አሁን ስለደከመኝ እንቅልፌ መጥቷል …ቻው ደህና እደር..››
‹‹ደህና እደሪ …ለሊት በማንኛውም ሰዓት የምትፈልጊው ምንም ነገር ቢኖር ንገሪኝ..››
‹‹ለሊት ምንም ነገር ብፈልግ?››ሳቅ ባፈነው ድምፅ
‹‹አዎ ምንም ነገር ብትፈልጊ..››
‹‹እሺ ነግርሀለሁ.. .አሁን ደህና እደር››
‹‹ደህና እደሪ›› ብዬ ሳደርግ የነበረውን ጫማ መልሼ አወለቅኩና ወደ አልጋዬ ወጣሁ...ከልጅቷ ጋር በግድግዳ ወዲህ ማዶና ወዲያ ማዶ ሆነን የተነጋገርናቸውን ነገሮች መልሼ ሳስብ...ልጅቷ ልክ እንደ አያቴ ተንኮለኛ ቢጤ ነች መሰለኝ ስል አሰብኩና ፈገግ አልኩ…
ስለእዚህች ልጅ አያቴ ለብዙ ቀን አውርተውኛል..በየ15 ቀኑም ደብደቤ እየጻፉ እየሰጡኝ ለረጂም ጊዜ ፖሰታ ቤት ወስጄ የማስገባላቸው አኔ ስለሆንኩ ስለእሷ በመጠኑ አውቃለሁ..…ለምሳሌ የድሬደዋ ልጅ መሆኗን..ከእናቷ ጋር እንደምትኖርና… ጋሽ ሰለሞን የአሁኗን ሚስቱን ከማግባቱ በፊት እናትዬውን አግብቶ እሷን ከወለደ በኃላ እንደተፋቱ ከዛ እናትዬው ልጆን ይዛ ቤተሰቦቾ ጋር ድሬደዋ እንደገባች አውቃለሁ…አያቴም ከቤት አልወጣም ብለው እራሳቸውን ኳራንቲን ከማስገባቸው በፊት ቢያንስ በስድስት ወር አንዴ እየሄዱ እንደሚጠይቋት እሷም አልፎ አልፎ እየመጣች ትጠይቃቸው እንደነበረ መረጃው አለኝ ….ከልጃቸው ከጋሽ ሰለሞን በላይ ከእሷ ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንዳላቸውም አውቃለሁ....ሌላው በ1987 ዓ.ምህረት እንደተወለደች ነግረውኛል…ያ ማለት ይህቺ የሚቀጥለው ክፍል ውስጥ ያለች ወጣት አሁን 25 ዓመቷ ነው፡ በትምህርቷ በአካውንቲንግ ዲግሪ አላት…የእናቷ ቤተሰቦች ሀብታም ነጋዴዎች ስለሆኑ የራሷ ቡቲክ ከፍተውላት እየሰራች እንደሆነም አውቃለሁ...በቃ ስለእሷ የማውቀው ይሄንን ያህል ብቻ ነው ፡፡በተረፈ ቀጭን ትሁን ወፍራም..ቀይ ትሁን ጥቁር..ረጀም ትሁን አጭር ….ትሁት ትሁን መሰሪ ምንም አላውቅም….ምንም ፡፡ ግን ምንም ትሁን ምንም ለአንድ ወር የእኔ ኃላፊት ነች.. ፡፡ ያንን ኃላፊነት ደግሞ ያለምንም ማቅማማት በፍጽም ትዕግስት እና ብቃት እወጣለሁ...ምክንያቱም ያዘዙኝ አያቴ ናቸው..አሁን ልተኛ….ነገ ምን አልባት ረጅም ቀን ሊሆን ይችላል፡፡
✨ይቀጥላል✨
#ባል_አስይዞ_ቁማር
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
ጊፍቲ ሕይወት ቀፏታል.. ሁሉ ነገር ጭልምልም ካለባትና ክፉ በሆነ በሀይለኛ እራስ ምታት በታጀበ ድባቴ ውስጥ ከገባች ሳምንት ሞላት
…..በዚህ ሀዘን ላይ በጣላት ክስተት ማንን ተወቃሽ እንደምታደርግ አለማወቋ ነው ይበልጥ ህመሟን ያጠነከረባት…ሰው ሰውን ሲቀየምና ሲጠላ ምንም አይደል…ሰው አምላኩን ቢቀየምም ምንም አይደል(ምክንያቱም አምላክ ለምን ተቀየማችሁኝ ብሎ እልክ በመጋባት ጥበቃውን አያቋርጥም)…. ሰው ራሱን ከተቀየመና ከጠላ ግን አደገኛ ነው…እራሱን የጠላ ሰው ለምንም ነገር ደንታ አይኖረውም.. እራሱን የጠላ ሰው ነገሮችን በቀና ሁኔታ የማስተካከል ተነሳሽነቱ ዜሮ ነው…. እራሱን የጠላና የተጠየፈ ሰው አለምን እንዳለ ለማጥፋት እና ለማውደም ዝግጁ ነው፡፡ ጊፍቲም በአሁኑ ጊዜ እንደዛ ነው የሆነችው..እራሷን ነው የጠላችው..እራሷን ነው የተጠየፈችው፡፡
ጊፍቲ ከደነዘዘችበት መቀመጫ ላይ ተስፈንጥራ ተነሳችና ወደ መኝታ ክፍሏ አመራች፡፡ አልጋው ላይ በጀርባው ተዘርራ አይኗን ጣሪያዋ ላይ ተክላ ምስቅልቅል ሀሳቧቾን ታስብ ጀመር ..ደግሞም ተነሳችና ኮሞዲኖ ላይ የተቀመጠውን የውስኪ ጠርሙስ አነሳችና ከእነ ጠርሙሱ አፏ ላይ ደቅና አንደቀደቀችው………. የንዴት እና ሽንፈት አጠጣጥ ነበር፡፡እሩብ ያህሉን አጋምሳና ቀሪውን ይዛ ወደ መስኮቱ ተጠጋችና በጨለማው እየተሸነፈ ያለውን ውጭ እየቃኘች ምን ማድረግ እንዳለባት ማሰብ ቀጠለች‹‹ህይወቷን እንዴት ማስተካከል ትችላለች…?ከቃልስ ጋር እስከወዲያኛው ተለያይታ እንዴት ትችለዋለች? …. ሰውነቷ በላብ ወረዛ‹‹መሆን የለበትም በፍጹም አይደረግም ቃልዬን አጥቼ መኖር የለብኝም አዎ እራሴን ማጥፋት አለብኝ.. እናቴ ወደላችበት መቃብር እራሴን እልካለሁ ››በውሳኔዋ ረካች…. እና ከት ብላ ሳቀች..የንዴት ሳቅ…..የመበለጥ ሳቅ….የተሸናፊነት ሳቅ…ተስፋ የመቁረጥ ሳቅ..የእብደት ሳቅ ››
በዚህ ወቅት እቤቷ ተንኳኳ…ዝም ባለች ቁጠር የማንኳኳቱ ኃይል እየጨመረ ሲመጣ እንደምንም እግሯን እየገተች ሄዳ ከፈተችው…ስትከፍት ያገኘችው ሰው ግን ፍፅም ያልጠበቀችውና ስትሸሸወ የነበረ ሰው ነው፡፡
‹‹ውይ ምነው? ምን አደረኩህ?››
‹‹እኔስ ምን አደረኩሽ…?››
‹‹በራፉን ትታ ፊቷን ወደውስጥ መለሰችና እንዳመጣጧ እግሯን በመጎተት ተራምዳ መቀመጫ ይዛ ተቀመጠች.እሱም ወደውስጥ በመግባት በራፉን ዘጋና ተከትሏት ከፊት ለፊቷ ተቀመጠና ማውራት ጀመረ…
‹‹ስልክ አይሰራም…ስትረጋጊ ትደውያለሽ ወይም ወደቤት ትመጪያለሽ ብዬ ጠበቀኩ ጠበቅኩ..ሲያቅተኝ መጣሁ .
‹‹ስልኬን የዘጋሁት እኮ ሰው ማግኘት ስለማልችል ነው…በተለይ አንተን››አይኖቹን ማየት አቅቷት አንገቷን ደፍታ የቤቱን ወለል እያየች መለሰችለት፡፡
‹‹ተይ እንጂ ጊፍቲ…እራስሽን መቅጣትስ ሳያንስሽ እኔንም ለምን ትቀጪኛለሽ..በጣም እኮ ነው የናፈቅሺኝ››
‹‹ቃል አይገባህም እንዴ ?እንዴት ብዬ ነው አንተን ለማግኘት ድፍረቱ ሚኖረኝ…?በጣም እኮ ነው የቆሸሽኩት …›
‹‹ሰው ሊሰራ የማይችለውን ምን የተለየ ተአምር ስራሸ …በዛ ላይ እንደሰማሁት በወቅቱ ሁላችሁም በጣም ጠጥታችሁና እስከመጨረሻው ሰክራችሁ ነበር….ለወደፊቱ ተመሳሳይ ስህተት ላለመስራት ከክስተቱ ትምህርት መውሰድ እንጂ እንዲህ እቤት ውስጥ እራስን እስረኛ በማድረግና አምርሮ በመቆዘም የሚቀየር ነገር የለም፡፡››
‹‹አሁን ጥፋቴን ቀለል አድርጎ በማቅረብ የምትደልለኝ ይመስልሀል?››
‹‹አይ እየደልኩሽ አይደለም..የሚሰማኝን እውነት እየነገርኩሽ ነው…በውስጥሽ ያለውን ጨላማ ሀሳብ አስወግጂ
….በመሀከላችሁ ስር የሰደደ ጥላቻ መቼም ሊኖር አይችልም..እስኪ ነገሩን በራስሽ ገልብጠሸ አስቢው …አሁን አንቺ የሰራሁት የምትይውን ስህተት እኔ ሰርቼው ቢሆን ኖሮ አይንህ ላፈረ ብለሽ እስከወዲያኛው ፊትሽን ታዞሪብኝ ነበር፡፡ ምንስ ነገር ብበድልሽ አምርረሽ ልትጠይኝ ትችያለሽ.?ለዛ አቅሙ አለሽ?››
‹‹ቃል እንዲሁ አትድከም….ምንም ብትል መፅናናት አልችልም….በሰራሁት ቀሺም ስህተት ምክንያት በውስጤ የሚሰማኝ ህመምና .ህሙም ያሳደረብኝን ቁስለት ሊረዳልኝ የሚችል አንድ ሰው በዚህ አለም ላይ አይኖርም…?ከአሁን በኃላ ህመሜን ብቻዬን ስታመም እኖራለሁ..ምን አልባት የመከራዬ መግል ሽታ የእኔ የሆኑትን ሰዎች እየከረፋቸው ስለሚቸገሩ ቀስ በቀስ ከጎኔ ሊጠፉ ይችላሉ….››ንግግሯን አቋረጠችና እየተንሰቀሰቀች መነፍረቅ ጀመረች……ቃል መቀመጫውን ለቆ ተነሳና ከጎኗ ተቀመጠ...ቃላት ሳይጠቀም ወደደረቱ ጐተታትና አቀፎ ግንባሯን በመሳምና ፀጉሯን በማሻሸት ያጽናናት ጀመረ፡፡
‹‹ቃልዬ›› ለስለስ ባለ ድምጽ ጠራችው
‹‹ወዬ ጊፍቲ››
‹‹በፈጠረህ አንድ ነገር ላስቸግርህ፡፡››
‹‹ምንደነው የፈለግሺውን››አላት
በውስጡ ግን አሁን ይቅር በለኝና ዛሬውኑ እንጋባ ብትለኝ ምን መልስ እሰጣታለሁ? እያለ መሳቀቅ ጀምሮ ነበር፡
‹‹እስቲ ስደበኝ…ሸርሙጣ ነሽ፤ከዳተኛና አዋራጅ ሴት ነሽ… ብለህ ስደበኝ ..ከተቻለህም በጥፊ አጠናግረኝ…ምራቅህንም ሀክ እንትፍ ብለህ ግንባሬ ላይ በመትፋት ጥለኸኝ ሂድ..ያዛን ጊዜ ትንሽ ቀለል ይለኝ ይሆናል፡፡››በማለት ያልጠበቀውን ንግግር ተናገረች፡፡አሳዘነችው፡በውስጡም የጥፋተኝነት ስሜት ያሰቃየው ጀመር፡፡
‹‹እንደዛ መቼም እንደማላደርግ ታውቂያለሽ…አንቺ ለእኔ እኮ ፍቅረኛዬ ብቻ አይደለሽም እህቴም ጭምር ነሽ…››
‹‹ይሄው እንደገመትኩት ክፉ እኮ ነህ..ሰውን የምትቀጣበት መንገድ መራር ነው…ያንተ ቅጣት ነፍስ ላይ ነው ጠባሳ ሚጥለው፡፡››
‹‹ስለተበሳጨሽ ነው እንዲህ የምትይው…ጊዜ የውስጥን ቁስል ይፈውሳል…ለራስሽ ጊዜ ስጪና ለመረጋጋት ሞክሪ…ሰው ስለሆንሽ ሰው ሚሰራውን ነገር ነው የሰራሽው ስህተት ቢሆን እንኳን ይቅር የማይባልና የማይስተካከል ስህተት የለም፡፡››
‹‹እንዴት ..?እስኪ ንገረኝ ብልቴ ውስጥ ሲዋኝ ያደረውን ብልቱን እንዴት አድርጌ እንዳልተፈጠረ ማድረግ እችላለሁ…?ዕድሜ ልኬን ላንተ እንኳን ከመስጠት ሰስቼ ሳሽሞነሙነው የነበረውን ድንግልናዬንስ እንዴት አድርጌ ወደቦታው ልመልሰው እችላለሁ..?ነው ወይስ ሰርጀሪ ላሰራው?፡፡››
‹‹ጊፍቲ ኮ… ተይ እንጂ.. አንቺ እኮ በጣም ጠንካራ ልጅ ነሽ ፡፡ በህይወትሽ ብዙ ከዚህ በጣም የከፉ አስቸጋሪ መከራዎች አጋጠጥመውሽ በትግስትና በብልሀት አልፈሻቸዋል…አሁንም ንም ትወጪዋለሽ…ታውቂያለሽ እኔም ከጎንሽ ነኝ፡፡››
‹‹ተው ቃል ….በዚህ ልክ የህይወቴን መስመር ድብልቅልቁን የሚያወጣ መከራ ገጥሞኝ አያውቅም ወደፊትም አይገጥመኝም…ልፋ ሲልህ የማይሰራ ምክር ነው እየመከርከኝ ያለኸው...ተመልከተኝ እስኪ ክስተቱ ልቤን አድቅቆታል፤ ውስጤን በታትኖታል…፡፡አዎ ሞራሌን ተሰባብሯል …ሰባአዊነቴንም አክስሞብኛል… የሚቧጥጥ ጥፍርና..ያገጠጡ ስል ጥርሶች ያሉት የሚዘነጣጥልና የሚሸረካክት አውሬ በውስጤ እየተፈጠረ ይመስለኛል….እኔ በጣም መጥፎ ሰው ነኝ …? መጥፎነት ፈፅሞ አይግልጻውም..ፈፅሞ…››መለፍለፎን ማቆረጥ አልቻለችም፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
ጊፍቲ ሕይወት ቀፏታል.. ሁሉ ነገር ጭልምልም ካለባትና ክፉ በሆነ በሀይለኛ እራስ ምታት በታጀበ ድባቴ ውስጥ ከገባች ሳምንት ሞላት
…..በዚህ ሀዘን ላይ በጣላት ክስተት ማንን ተወቃሽ እንደምታደርግ አለማወቋ ነው ይበልጥ ህመሟን ያጠነከረባት…ሰው ሰውን ሲቀየምና ሲጠላ ምንም አይደል…ሰው አምላኩን ቢቀየምም ምንም አይደል(ምክንያቱም አምላክ ለምን ተቀየማችሁኝ ብሎ እልክ በመጋባት ጥበቃውን አያቋርጥም)…. ሰው ራሱን ከተቀየመና ከጠላ ግን አደገኛ ነው…እራሱን የጠላ ሰው ለምንም ነገር ደንታ አይኖረውም.. እራሱን የጠላ ሰው ነገሮችን በቀና ሁኔታ የማስተካከል ተነሳሽነቱ ዜሮ ነው…. እራሱን የጠላና የተጠየፈ ሰው አለምን እንዳለ ለማጥፋት እና ለማውደም ዝግጁ ነው፡፡ ጊፍቲም በአሁኑ ጊዜ እንደዛ ነው የሆነችው..እራሷን ነው የጠላችው..እራሷን ነው የተጠየፈችው፡፡
ጊፍቲ ከደነዘዘችበት መቀመጫ ላይ ተስፈንጥራ ተነሳችና ወደ መኝታ ክፍሏ አመራች፡፡ አልጋው ላይ በጀርባው ተዘርራ አይኗን ጣሪያዋ ላይ ተክላ ምስቅልቅል ሀሳቧቾን ታስብ ጀመር ..ደግሞም ተነሳችና ኮሞዲኖ ላይ የተቀመጠውን የውስኪ ጠርሙስ አነሳችና ከእነ ጠርሙሱ አፏ ላይ ደቅና አንደቀደቀችው………. የንዴት እና ሽንፈት አጠጣጥ ነበር፡፡እሩብ ያህሉን አጋምሳና ቀሪውን ይዛ ወደ መስኮቱ ተጠጋችና በጨለማው እየተሸነፈ ያለውን ውጭ እየቃኘች ምን ማድረግ እንዳለባት ማሰብ ቀጠለች‹‹ህይወቷን እንዴት ማስተካከል ትችላለች…?ከቃልስ ጋር እስከወዲያኛው ተለያይታ እንዴት ትችለዋለች? …. ሰውነቷ በላብ ወረዛ‹‹መሆን የለበትም በፍጹም አይደረግም ቃልዬን አጥቼ መኖር የለብኝም አዎ እራሴን ማጥፋት አለብኝ.. እናቴ ወደላችበት መቃብር እራሴን እልካለሁ ››በውሳኔዋ ረካች…. እና ከት ብላ ሳቀች..የንዴት ሳቅ…..የመበለጥ ሳቅ….የተሸናፊነት ሳቅ…ተስፋ የመቁረጥ ሳቅ..የእብደት ሳቅ ››
በዚህ ወቅት እቤቷ ተንኳኳ…ዝም ባለች ቁጠር የማንኳኳቱ ኃይል እየጨመረ ሲመጣ እንደምንም እግሯን እየገተች ሄዳ ከፈተችው…ስትከፍት ያገኘችው ሰው ግን ፍፅም ያልጠበቀችውና ስትሸሸወ የነበረ ሰው ነው፡፡
‹‹ውይ ምነው? ምን አደረኩህ?››
‹‹እኔስ ምን አደረኩሽ…?››
‹‹በራፉን ትታ ፊቷን ወደውስጥ መለሰችና እንዳመጣጧ እግሯን በመጎተት ተራምዳ መቀመጫ ይዛ ተቀመጠች.እሱም ወደውስጥ በመግባት በራፉን ዘጋና ተከትሏት ከፊት ለፊቷ ተቀመጠና ማውራት ጀመረ…
‹‹ስልክ አይሰራም…ስትረጋጊ ትደውያለሽ ወይም ወደቤት ትመጪያለሽ ብዬ ጠበቀኩ ጠበቅኩ..ሲያቅተኝ መጣሁ .
‹‹ስልኬን የዘጋሁት እኮ ሰው ማግኘት ስለማልችል ነው…በተለይ አንተን››አይኖቹን ማየት አቅቷት አንገቷን ደፍታ የቤቱን ወለል እያየች መለሰችለት፡፡
‹‹ተይ እንጂ ጊፍቲ…እራስሽን መቅጣትስ ሳያንስሽ እኔንም ለምን ትቀጪኛለሽ..በጣም እኮ ነው የናፈቅሺኝ››
‹‹ቃል አይገባህም እንዴ ?እንዴት ብዬ ነው አንተን ለማግኘት ድፍረቱ ሚኖረኝ…?በጣም እኮ ነው የቆሸሽኩት …›
‹‹ሰው ሊሰራ የማይችለውን ምን የተለየ ተአምር ስራሸ …በዛ ላይ እንደሰማሁት በወቅቱ ሁላችሁም በጣም ጠጥታችሁና እስከመጨረሻው ሰክራችሁ ነበር….ለወደፊቱ ተመሳሳይ ስህተት ላለመስራት ከክስተቱ ትምህርት መውሰድ እንጂ እንዲህ እቤት ውስጥ እራስን እስረኛ በማድረግና አምርሮ በመቆዘም የሚቀየር ነገር የለም፡፡››
‹‹አሁን ጥፋቴን ቀለል አድርጎ በማቅረብ የምትደልለኝ ይመስልሀል?››
‹‹አይ እየደልኩሽ አይደለም..የሚሰማኝን እውነት እየነገርኩሽ ነው…በውስጥሽ ያለውን ጨላማ ሀሳብ አስወግጂ
….በመሀከላችሁ ስር የሰደደ ጥላቻ መቼም ሊኖር አይችልም..እስኪ ነገሩን በራስሽ ገልብጠሸ አስቢው …አሁን አንቺ የሰራሁት የምትይውን ስህተት እኔ ሰርቼው ቢሆን ኖሮ አይንህ ላፈረ ብለሽ እስከወዲያኛው ፊትሽን ታዞሪብኝ ነበር፡፡ ምንስ ነገር ብበድልሽ አምርረሽ ልትጠይኝ ትችያለሽ.?ለዛ አቅሙ አለሽ?››
‹‹ቃል እንዲሁ አትድከም….ምንም ብትል መፅናናት አልችልም….በሰራሁት ቀሺም ስህተት ምክንያት በውስጤ የሚሰማኝ ህመምና .ህሙም ያሳደረብኝን ቁስለት ሊረዳልኝ የሚችል አንድ ሰው በዚህ አለም ላይ አይኖርም…?ከአሁን በኃላ ህመሜን ብቻዬን ስታመም እኖራለሁ..ምን አልባት የመከራዬ መግል ሽታ የእኔ የሆኑትን ሰዎች እየከረፋቸው ስለሚቸገሩ ቀስ በቀስ ከጎኔ ሊጠፉ ይችላሉ….››ንግግሯን አቋረጠችና እየተንሰቀሰቀች መነፍረቅ ጀመረች……ቃል መቀመጫውን ለቆ ተነሳና ከጎኗ ተቀመጠ...ቃላት ሳይጠቀም ወደደረቱ ጐተታትና አቀፎ ግንባሯን በመሳምና ፀጉሯን በማሻሸት ያጽናናት ጀመረ፡፡
‹‹ቃልዬ›› ለስለስ ባለ ድምጽ ጠራችው
‹‹ወዬ ጊፍቲ››
‹‹በፈጠረህ አንድ ነገር ላስቸግርህ፡፡››
‹‹ምንደነው የፈለግሺውን››አላት
በውስጡ ግን አሁን ይቅር በለኝና ዛሬውኑ እንጋባ ብትለኝ ምን መልስ እሰጣታለሁ? እያለ መሳቀቅ ጀምሮ ነበር፡
‹‹እስቲ ስደበኝ…ሸርሙጣ ነሽ፤ከዳተኛና አዋራጅ ሴት ነሽ… ብለህ ስደበኝ ..ከተቻለህም በጥፊ አጠናግረኝ…ምራቅህንም ሀክ እንትፍ ብለህ ግንባሬ ላይ በመትፋት ጥለኸኝ ሂድ..ያዛን ጊዜ ትንሽ ቀለል ይለኝ ይሆናል፡፡››በማለት ያልጠበቀውን ንግግር ተናገረች፡፡አሳዘነችው፡በውስጡም የጥፋተኝነት ስሜት ያሰቃየው ጀመር፡፡
‹‹እንደዛ መቼም እንደማላደርግ ታውቂያለሽ…አንቺ ለእኔ እኮ ፍቅረኛዬ ብቻ አይደለሽም እህቴም ጭምር ነሽ…››
‹‹ይሄው እንደገመትኩት ክፉ እኮ ነህ..ሰውን የምትቀጣበት መንገድ መራር ነው…ያንተ ቅጣት ነፍስ ላይ ነው ጠባሳ ሚጥለው፡፡››
‹‹ስለተበሳጨሽ ነው እንዲህ የምትይው…ጊዜ የውስጥን ቁስል ይፈውሳል…ለራስሽ ጊዜ ስጪና ለመረጋጋት ሞክሪ…ሰው ስለሆንሽ ሰው ሚሰራውን ነገር ነው የሰራሽው ስህተት ቢሆን እንኳን ይቅር የማይባልና የማይስተካከል ስህተት የለም፡፡››
‹‹እንዴት ..?እስኪ ንገረኝ ብልቴ ውስጥ ሲዋኝ ያደረውን ብልቱን እንዴት አድርጌ እንዳልተፈጠረ ማድረግ እችላለሁ…?ዕድሜ ልኬን ላንተ እንኳን ከመስጠት ሰስቼ ሳሽሞነሙነው የነበረውን ድንግልናዬንስ እንዴት አድርጌ ወደቦታው ልመልሰው እችላለሁ..?ነው ወይስ ሰርጀሪ ላሰራው?፡፡››
‹‹ጊፍቲ ኮ… ተይ እንጂ.. አንቺ እኮ በጣም ጠንካራ ልጅ ነሽ ፡፡ በህይወትሽ ብዙ ከዚህ በጣም የከፉ አስቸጋሪ መከራዎች አጋጠጥመውሽ በትግስትና በብልሀት አልፈሻቸዋል…አሁንም ንም ትወጪዋለሽ…ታውቂያለሽ እኔም ከጎንሽ ነኝ፡፡››
‹‹ተው ቃል ….በዚህ ልክ የህይወቴን መስመር ድብልቅልቁን የሚያወጣ መከራ ገጥሞኝ አያውቅም ወደፊትም አይገጥመኝም…ልፋ ሲልህ የማይሰራ ምክር ነው እየመከርከኝ ያለኸው...ተመልከተኝ እስኪ ክስተቱ ልቤን አድቅቆታል፤ ውስጤን በታትኖታል…፡፡አዎ ሞራሌን ተሰባብሯል …ሰባአዊነቴንም አክስሞብኛል… የሚቧጥጥ ጥፍርና..ያገጠጡ ስል ጥርሶች ያሉት የሚዘነጣጥልና የሚሸረካክት አውሬ በውስጤ እየተፈጠረ ይመስለኛል….እኔ በጣም መጥፎ ሰው ነኝ …? መጥፎነት ፈፅሞ አይግልጻውም..ፈፅሞ…››መለፍለፎን ማቆረጥ አልቻለችም፡፡
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
‹‹በነገራችን ላይ ወደሀገር የገባሁትም የዛሬ ወር አካባቢ ነው፡፡ላለፉት ሶስት አመታት ሳውዲ ነበርኩ…በህገወጥ መልኩ ስለሄድኩ በመሹለክለክ ነበር የኖርኩት… የቀን ጎዶሎ ግን ከሶስት ወር በፊት ከቀጣሪዬ ማዳም ጋር ተጣላሁና አስያዘችኝ››
‹‹በባሏ ጠርጥራሽ ነው አይደል …?››ያው እኔ ሳላስበው ነው ቀደም ቀድም የምለው ….ምክንያቱም እሷ ታሪኳን በቃላት አቀናብራ ለሶፊ ከመናገሯ በፊት እሷ ቀድሞ ይታያታል…ንስሯ የበራፍ በረንዳ ላይ ሶፊ ከለቀቀችበት ወንበር ላይ ተፈናጦ ክፍት በሆነው በራፍ ወደውስጥ አጨንቁሮል ….እርግጥ ልጅቷ ጀርባውና ስለሰጠችው እስከአሁን አላየችውም… እሷ ግን ፊት ለፊት ይታያታል ሁለቱም የልጅቷን ታሪክ ላይ አተኩረዋል …ለዛ ነው ቀደም ቀደም የምትለው….ያ ደግሞ ልጅቷን ግራ እያጋባት ስለሆነ መረጋጋት እንዳለባት ለራሷ እየነገረች ነው፡፡
‹‹አዎ ትክክል ነሽ…ብታይ ጭራቅ ሴት ነች፡፡ቅናቷ አያድረስ ነው፡፡በቃ ሰይጣናዊ የቅናት ዛር ነው የሰፈረባት፡፡ኑሮዬን ሁሉ ሲኦል ነው ያደረገችው፡፡››
‹‹ሙሉውን ሶስት አመት እዛው ነው የኖርሺው…?››
‹‹አዎ ሶስት አመት ሙሉ አንድ ቤት ነበርኩ…እርግጥ መጀመሪያውን አንድ አመት አካባቢ ጥሩ ሴት ነበረች…ሁሉ ነገር መልካም ነበር… ደሞዜን በስርአቱ ትከፍለኛለች..እርግጥ እስከመጨረሻውም ደሞዜን ከልክላኝ ወይም አቋርጣብኝ አታውቅም…ለቤተሰቦቼ የምልከው ተጨማሪ ብር ሁሉ ትሰጠኝ ነበር፡፡ከዛ ድንገት ፀባይዋ ተቀያየረ….ለዓይኖቾ ተጠየፈችኝ….
‹‹ለምን ታዲያ አትለቂም ነበር..?ማለት ሌላ ማዳም ጋር ቀይረሽ መስራት ትቺይ ነበር…››
‹‹ያው እንደነገርኩሽ በህገወጥ መንገድ ነው የሄድኩት.. እንደልቤ ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሼ ስራ ማማረጥ አልችልም..ሌላው …››ብላ ዝም አለች ..ላውራ ወይስ ይቅርብኝ እያለች ከራሷ ጋ ሙግት የገጠመች መሆኑን አውቃባታለች…
‹‹ሌላው ምን…?››
‹‹ሰውዬው በጣም መልካም ሰው ነው…ልጆቹንም በጣም ነው የምወዳቸው….ለእነሱ ስል ነው ታግሼያት የኖርኩት››
ፈገግ አለች‹‹መጨረሻ ታዲያ እንዴት ሆነ?››
‹‹ቅናቷ ከቁጥጥር በላይ ሆነብኛ››
‹‹ያው ምታደርጉትን እኮ ስለምታይ ነው››
‹‹ማለት…? እንዴት ታውቃለች……?›.
‹‹እርግጥ የእሷን አለመኖር እየጠበቃችሁ ነው ፍቅራችሁን የምትወጡት… ግን እሷ በደንብ ታውቃለች ..እንደውም ጥሩ ሰው ነች››አለቻት
ልጅቷ ግራ ገባት ..ከድንጋጤዋ የተነሳም ከተቀመጠችበት ተነስታ ቤቱን ሁሉ ለቃ መውጣት ፈልጋለች..…
‹‹አይዞሽ አትደንግጪ …እሷን ለማስቀየም ወይም ለመበደል ብለሽ ሳይሆን ፍቅር ላይ ስለወደቅሽ ነው እንደዛ ያደረግሽው…ያ ደግሞ ከሰውዬው ቀረቤታ እና መልካምነት የተነሳ ነው..በዛ ላይ በጣም ቆንጆ እና ዘናጭ ነው…እንደምትወጂው አውቃለሁ ፡፡እሱም በደንብ ነው የሚያፈቅርሽ፡፡በጣም የከፋው ነገር ግን ቅናተኛ ላልሻት ሴት ደግሞ ሰውዬው ሁለመናዋ ነው…እናንተ እርስ በርስ ከምትዋደዱት በላይ እሷ እሱን ትወደዋለች፡፡እና ሴትዬዋ በተፈጥሮዋ መጥፎ ሆና አንቺን በማሰቃየት የምትረካ ስለሆነች ሳይሆን ባሏን ላለማጣት የምታደረግው መፋለም እና ጥረት ነበር፡፡እንደውም አንቺን ባሰቃየች ቁጥር እሱንም የምታስከፋው እና የምታጣው መስሎ ስለሚሰማት በጣም ትጨናነቅ እና ትጠነቀቅ ነበር…አንቺን ጎድታኛለች ብለሽ ከምታወሪው በላይ እሷ እራሷን አሰቃይታለች ….የጨጋራ በሽተኛ ሆናለች….››
‹‹ቆይ አንቺ ይሄን ሁሉ እንዴት ልታውቂ ቻልሽ…?››
እሱን ልታስረዳት አልቻለችም ‹‹..ትኩረት ከሰጠው አንዳንድ ነገሮችን ማየት እችላለሁ፡፡
በውስጥሽ ይህቺ ልጅ ጠንቆይ ነች እንዴ…? እያልሽ እያሰብሽ እንደሆነ አውቃለሁ..እንደዛ በይው ችግር የለውም››
‹‹አይ ማለቴ ….ልዋሽሽ አልችልም እንዳልሽው ነበር እያሰብኩ ያለሁት…ይገርማል ያልሻቸውን ብዙውን ነገሮች ትክክል ነሽ››
‹‹ምንድነው ትክክል ያልሆንኩት…?››
‹‹እሷ ስለእኛ ግንኙነት በእርግጠኝነት ማወቋን እና..ከእኔ በላይ እሱን ማፍቀሯን››
‹‹ሁለታችሁ ፍቅር የምትሰሩት አንቺ ክፍል አይደል…?››
‹‹አዎ ግን እሷ ስራ በምትሆንበት እና ከቤት እርቃ በሄደችበት ጌዜ ጠብቀንና ተጠንቅቀን ነው››
‹‹አዎ ትክክል ነሽ …በሁለታችሁ ያልተለመደ መቀራረብ ጥርጣሬ ካደረባት በኃላ ግን ክፍልሽ ውስጥ በስውር ካሜራ ስላስቀመጠች የተቀዳውን በፈለገችው ጌዜ ከፍታ ታየው ነበር፡፡››
‹‹ያማ አይሆንም..…?እንዴት ተደርጎ…?››
‹‹እንደዛ ነበር የሆነው…ከእኔ በላይ አታፈቅረውም ያልሺው ደግሞ ያው በራስሽ ሚዛን ስለምትመዝኚው ነው እንደዛ የምታስቢው እንጂ እንቺ በእሷ ቦታ ብትሆኚ እርግጠኛ ነኝ ወይ ጥለሺው ትሄጂያለሽ ..ወይ ሌላ እርምጃ ትወስጂያለሽ ….እሷ ግን ካንቺ ጋር ብትጨቃጨቅም ….አንቺን ላይ ችግር ለመፍጠር ብትሞክርም አንድ ቀን እንኳን እሱ ላይ ተነጫንጫበት ወይንም ጉዳዩን አንስታበትና ወቅሳው አታውቅም..ለእሷ እሱ ብቸኛው ፍቅሯ ነው..ለአንቺ ግን የመጀመሪያ ምርጫሽ አይደለም..ስለምታፈቅሪው ብቻ ሳይሆን ማዳሞ ከምታውቀው ሌላ ተጨማሪ ብር ስለሚሰጥሽ ነው ..ፍቅርሽ ብቻ ሳይሆን የገንዘብ ምንጭሽም ስለሆነ ነው…ለእሷ ግን እንደዛ አልነበረም…››
‹‹እሱስ እውነትሽን ነው….የእውነት ካሜራው ኖሮ የምናደርገውን ሁሉ እያየች በትዕግስት አልፋን ከሆነ የሚገርም ነው…እኔ ብሆን ልገድለው ሁሉ እችላለሁ…አረ ሁለቱንም ነው በተቃቀፉበት የማጠፋቸው››
‹‹አየሽ..ሴትየዋ የምታስቢያትን ያህል ክፉ አልነበረችም….ከዚህም በላይ ልታሰቃይሽ ምክንያቱን ሰጥተሻት ነበር…ግን እሷ በተቻላት መጠን እራሷን ለመቆጣጠር ሞክራለች፡፡››
‹‹አዎ አንቺ ይገርማል… አሁን ሳስበው በህይወት ስላለውም እድለኛ ነኝ….››
‹‹እና እዚህ ስትመጪ ደግሞ ሌላ ታሪክ አጋጠመሽ››
‹‹አዎ በጣም የሚያንገበግበው እና ስብርብር ያደረገኝ ደግሞ ይሄኛው ነው›› አለች …..አሁን በፍራቻ እና በአድናቆት ነበር የምትመልስልኝ
የተወሰነ ትንፋሽ ወሰደችና ቀጠለች‹‹መቼስ ታውቂዋለሽ…አንድ ቀን ወደ ሀገሬ ስመለስ ቤት ይኖረኛል….አገባዋለሁ..ልጅ ወልድለታለሁ ብዬ ደሞዜንም .ሰውዬው ይሰጠኝ የነበረውንም ብር እልክለት ነበር…ቤት እየሰራው ነው ይለኛል….የቤት ዕቃ እያሞለው ነው ይለኛል..ምን አለፋሽ ከሶስት መቶ ሺ ብር በላይ ነው የላኩለት …..ግን ስደርስ ሌላ ሴት አግብቶ አንድ ልጅ ወልዶ ጠበቀኝ…..ከዛ ምን ልንገርሽ ሁሉ ነገር አስጠላኝ …ክፍለሀገር ወደ ቤተሰቦቼም መሄድ አልፈለግኩም እንዴት ብዬ ምን ይዤ ሄዳለሁ…?……..
‹‹አዎ ለእሱ ያልሽውን ሶስት መቶ ሺብር ስትልኪለት ለቤተሰቦችሽ የላክሺው ብር ሲደመር 50 ሺ ብርም አይሞላም..››
‹‹አዎ ትክክል ነሽ..የሚያንገበግበኝ እና ሞራሌን እንክትክት ያደረገው እና ዛሬ እዚህ ያስገኘኝ ይሄው ነው….
አይዞሽ እናስተካክለዋለን ..በእኔ ተማመኚ..አልኳትና የደረሰውን ቁርስ አቅርቤ መብላት ጀመርን›…
✨ይቀጥላል✨
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
‹‹በነገራችን ላይ ወደሀገር የገባሁትም የዛሬ ወር አካባቢ ነው፡፡ላለፉት ሶስት አመታት ሳውዲ ነበርኩ…በህገወጥ መልኩ ስለሄድኩ በመሹለክለክ ነበር የኖርኩት… የቀን ጎዶሎ ግን ከሶስት ወር በፊት ከቀጣሪዬ ማዳም ጋር ተጣላሁና አስያዘችኝ››
‹‹በባሏ ጠርጥራሽ ነው አይደል …?››ያው እኔ ሳላስበው ነው ቀደም ቀድም የምለው ….ምክንያቱም እሷ ታሪኳን በቃላት አቀናብራ ለሶፊ ከመናገሯ በፊት እሷ ቀድሞ ይታያታል…ንስሯ የበራፍ በረንዳ ላይ ሶፊ ከለቀቀችበት ወንበር ላይ ተፈናጦ ክፍት በሆነው በራፍ ወደውስጥ አጨንቁሮል ….እርግጥ ልጅቷ ጀርባውና ስለሰጠችው እስከአሁን አላየችውም… እሷ ግን ፊት ለፊት ይታያታል ሁለቱም የልጅቷን ታሪክ ላይ አተኩረዋል …ለዛ ነው ቀደም ቀደም የምትለው….ያ ደግሞ ልጅቷን ግራ እያጋባት ስለሆነ መረጋጋት እንዳለባት ለራሷ እየነገረች ነው፡፡
‹‹አዎ ትክክል ነሽ…ብታይ ጭራቅ ሴት ነች፡፡ቅናቷ አያድረስ ነው፡፡በቃ ሰይጣናዊ የቅናት ዛር ነው የሰፈረባት፡፡ኑሮዬን ሁሉ ሲኦል ነው ያደረገችው፡፡››
‹‹ሙሉውን ሶስት አመት እዛው ነው የኖርሺው…?››
‹‹አዎ ሶስት አመት ሙሉ አንድ ቤት ነበርኩ…እርግጥ መጀመሪያውን አንድ አመት አካባቢ ጥሩ ሴት ነበረች…ሁሉ ነገር መልካም ነበር… ደሞዜን በስርአቱ ትከፍለኛለች..እርግጥ እስከመጨረሻውም ደሞዜን ከልክላኝ ወይም አቋርጣብኝ አታውቅም…ለቤተሰቦቼ የምልከው ተጨማሪ ብር ሁሉ ትሰጠኝ ነበር፡፡ከዛ ድንገት ፀባይዋ ተቀያየረ….ለዓይኖቾ ተጠየፈችኝ….
‹‹ለምን ታዲያ አትለቂም ነበር..?ማለት ሌላ ማዳም ጋር ቀይረሽ መስራት ትቺይ ነበር…››
‹‹ያው እንደነገርኩሽ በህገወጥ መንገድ ነው የሄድኩት.. እንደልቤ ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሼ ስራ ማማረጥ አልችልም..ሌላው …››ብላ ዝም አለች ..ላውራ ወይስ ይቅርብኝ እያለች ከራሷ ጋ ሙግት የገጠመች መሆኑን አውቃባታለች…
‹‹ሌላው ምን…?››
‹‹ሰውዬው በጣም መልካም ሰው ነው…ልጆቹንም በጣም ነው የምወዳቸው….ለእነሱ ስል ነው ታግሼያት የኖርኩት››
ፈገግ አለች‹‹መጨረሻ ታዲያ እንዴት ሆነ?››
‹‹ቅናቷ ከቁጥጥር በላይ ሆነብኛ››
‹‹ያው ምታደርጉትን እኮ ስለምታይ ነው››
‹‹ማለት…? እንዴት ታውቃለች……?›.
‹‹እርግጥ የእሷን አለመኖር እየጠበቃችሁ ነው ፍቅራችሁን የምትወጡት… ግን እሷ በደንብ ታውቃለች ..እንደውም ጥሩ ሰው ነች››አለቻት
ልጅቷ ግራ ገባት ..ከድንጋጤዋ የተነሳም ከተቀመጠችበት ተነስታ ቤቱን ሁሉ ለቃ መውጣት ፈልጋለች..…
‹‹አይዞሽ አትደንግጪ …እሷን ለማስቀየም ወይም ለመበደል ብለሽ ሳይሆን ፍቅር ላይ ስለወደቅሽ ነው እንደዛ ያደረግሽው…ያ ደግሞ ከሰውዬው ቀረቤታ እና መልካምነት የተነሳ ነው..በዛ ላይ በጣም ቆንጆ እና ዘናጭ ነው…እንደምትወጂው አውቃለሁ ፡፡እሱም በደንብ ነው የሚያፈቅርሽ፡፡በጣም የከፋው ነገር ግን ቅናተኛ ላልሻት ሴት ደግሞ ሰውዬው ሁለመናዋ ነው…እናንተ እርስ በርስ ከምትዋደዱት በላይ እሷ እሱን ትወደዋለች፡፡እና ሴትዬዋ በተፈጥሮዋ መጥፎ ሆና አንቺን በማሰቃየት የምትረካ ስለሆነች ሳይሆን ባሏን ላለማጣት የምታደረግው መፋለም እና ጥረት ነበር፡፡እንደውም አንቺን ባሰቃየች ቁጥር እሱንም የምታስከፋው እና የምታጣው መስሎ ስለሚሰማት በጣም ትጨናነቅ እና ትጠነቀቅ ነበር…አንቺን ጎድታኛለች ብለሽ ከምታወሪው በላይ እሷ እራሷን አሰቃይታለች ….የጨጋራ በሽተኛ ሆናለች….››
‹‹ቆይ አንቺ ይሄን ሁሉ እንዴት ልታውቂ ቻልሽ…?››
እሱን ልታስረዳት አልቻለችም ‹‹..ትኩረት ከሰጠው አንዳንድ ነገሮችን ማየት እችላለሁ፡፡
በውስጥሽ ይህቺ ልጅ ጠንቆይ ነች እንዴ…? እያልሽ እያሰብሽ እንደሆነ አውቃለሁ..እንደዛ በይው ችግር የለውም››
‹‹አይ ማለቴ ….ልዋሽሽ አልችልም እንዳልሽው ነበር እያሰብኩ ያለሁት…ይገርማል ያልሻቸውን ብዙውን ነገሮች ትክክል ነሽ››
‹‹ምንድነው ትክክል ያልሆንኩት…?››
‹‹እሷ ስለእኛ ግንኙነት በእርግጠኝነት ማወቋን እና..ከእኔ በላይ እሱን ማፍቀሯን››
‹‹ሁለታችሁ ፍቅር የምትሰሩት አንቺ ክፍል አይደል…?››
‹‹አዎ ግን እሷ ስራ በምትሆንበት እና ከቤት እርቃ በሄደችበት ጌዜ ጠብቀንና ተጠንቅቀን ነው››
‹‹አዎ ትክክል ነሽ …በሁለታችሁ ያልተለመደ መቀራረብ ጥርጣሬ ካደረባት በኃላ ግን ክፍልሽ ውስጥ በስውር ካሜራ ስላስቀመጠች የተቀዳውን በፈለገችው ጌዜ ከፍታ ታየው ነበር፡፡››
‹‹ያማ አይሆንም..…?እንዴት ተደርጎ…?››
‹‹እንደዛ ነበር የሆነው…ከእኔ በላይ አታፈቅረውም ያልሺው ደግሞ ያው በራስሽ ሚዛን ስለምትመዝኚው ነው እንደዛ የምታስቢው እንጂ እንቺ በእሷ ቦታ ብትሆኚ እርግጠኛ ነኝ ወይ ጥለሺው ትሄጂያለሽ ..ወይ ሌላ እርምጃ ትወስጂያለሽ ….እሷ ግን ካንቺ ጋር ብትጨቃጨቅም ….አንቺን ላይ ችግር ለመፍጠር ብትሞክርም አንድ ቀን እንኳን እሱ ላይ ተነጫንጫበት ወይንም ጉዳዩን አንስታበትና ወቅሳው አታውቅም..ለእሷ እሱ ብቸኛው ፍቅሯ ነው..ለአንቺ ግን የመጀመሪያ ምርጫሽ አይደለም..ስለምታፈቅሪው ብቻ ሳይሆን ማዳሞ ከምታውቀው ሌላ ተጨማሪ ብር ስለሚሰጥሽ ነው ..ፍቅርሽ ብቻ ሳይሆን የገንዘብ ምንጭሽም ስለሆነ ነው…ለእሷ ግን እንደዛ አልነበረም…››
‹‹እሱስ እውነትሽን ነው….የእውነት ካሜራው ኖሮ የምናደርገውን ሁሉ እያየች በትዕግስት አልፋን ከሆነ የሚገርም ነው…እኔ ብሆን ልገድለው ሁሉ እችላለሁ…አረ ሁለቱንም ነው በተቃቀፉበት የማጠፋቸው››
‹‹አየሽ..ሴትየዋ የምታስቢያትን ያህል ክፉ አልነበረችም….ከዚህም በላይ ልታሰቃይሽ ምክንያቱን ሰጥተሻት ነበር…ግን እሷ በተቻላት መጠን እራሷን ለመቆጣጠር ሞክራለች፡፡››
‹‹አዎ አንቺ ይገርማል… አሁን ሳስበው በህይወት ስላለውም እድለኛ ነኝ….››
‹‹እና እዚህ ስትመጪ ደግሞ ሌላ ታሪክ አጋጠመሽ››
‹‹አዎ በጣም የሚያንገበግበው እና ስብርብር ያደረገኝ ደግሞ ይሄኛው ነው›› አለች …..አሁን በፍራቻ እና በአድናቆት ነበር የምትመልስልኝ
የተወሰነ ትንፋሽ ወሰደችና ቀጠለች‹‹መቼስ ታውቂዋለሽ…አንድ ቀን ወደ ሀገሬ ስመለስ ቤት ይኖረኛል….አገባዋለሁ..ልጅ ወልድለታለሁ ብዬ ደሞዜንም .ሰውዬው ይሰጠኝ የነበረውንም ብር እልክለት ነበር…ቤት እየሰራው ነው ይለኛል….የቤት ዕቃ እያሞለው ነው ይለኛል..ምን አለፋሽ ከሶስት መቶ ሺ ብር በላይ ነው የላኩለት …..ግን ስደርስ ሌላ ሴት አግብቶ አንድ ልጅ ወልዶ ጠበቀኝ…..ከዛ ምን ልንገርሽ ሁሉ ነገር አስጠላኝ …ክፍለሀገር ወደ ቤተሰቦቼም መሄድ አልፈለግኩም እንዴት ብዬ ምን ይዤ ሄዳለሁ…?……..
‹‹አዎ ለእሱ ያልሽውን ሶስት መቶ ሺብር ስትልኪለት ለቤተሰቦችሽ የላክሺው ብር ሲደመር 50 ሺ ብርም አይሞላም..››
‹‹አዎ ትክክል ነሽ..የሚያንገበግበኝ እና ሞራሌን እንክትክት ያደረገው እና ዛሬ እዚህ ያስገኘኝ ይሄው ነው….
አይዞሽ እናስተካክለዋለን ..በእኔ ተማመኚ..አልኳትና የደረሰውን ቁርስ አቅርቤ መብላት ጀመርን›…
✨ይቀጥላል✨
#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ዶ/ር ሶፊያ ከአራት ወራት ቆይታ በኃላ ነበር ለሌላ ስራ ወደ ሀዋሳ የተመለሰችው፡፡ዛሬ አምስተኛ ቀኗ ነው፡፡መቼስ የሀዋሳ ውበት
ይበልጥ ፈክቶ ይበልጥ ጎልቶ የሚታየው በገዛ
እግር በዝግታ እየተጓዙ ሲያጣጥሙት ነው፡፡
ዶ/ር ሶፊያም ይሄንን እውነት በመገንዘብ
የእለቱን ስራዋን ካጠናቀቀች በኃላ የምሽቱን
አየር ነፋሻማነትና ተስማሚነትንም ከግምት
በማስገባት በእግር ዞር ዞር ለማለት ወሰነችና መኪናዋን ሆቴል ግቢ ውስጥ ትታ በእግሯ ወጣች፡፡ለ3ዐ ደቂቃ በከተማው ተሸከረከረች፡፡
ጉዞዋ አስደሳችና መንፈሷን ያረጋጋላት ቢሆንም ደከማት፤ ወደ ካፌ ጎራ ብላ እረፍት ለመውሰድ ከወሰነች በኃላ መልሳ ሀሳቧን
ቀየረችና ጫማዋን እያስጠረገች ወጪ
ወራጁን መቃኘት እንደሚሻላት አመነች፡፡
ባለችበት አስፓልት አቅጣጫ ጠርዝ ላይ
ወዳለው ሊስትሮ አመራች፡፡ ሊስትሮው ከጐኑ በግምት መቶ የሚሆኑ መፅሀፎች ለሽያጭ ዘርግቷል፡፡እሱም ሊስትሮ ወንበሩ ላይ ቁጭ ብሎ በተመስጦ እያነበበ ነው፡፡ተጠጋችው ፤ግንብ አጥር ተደግፎ የሚገኘው አግዳሚ ወንበር ላይ ቁጭ አለች፡፡
‹‹አንተ ነህ የምትጠርገው?››
ቀና ሳይል <<አዎ እኔ ነኝ፡፡ግን አሁን ስራ ስለያዝኩ እዛ ማዶ ያለው ልጅ ጋር ብታስጠርጊ››አላት በትህትና፡፡
ደነገጠች<< ...አዋ እራሱ ነው፡፡››አወቀችው ፡፡ የዛሬ ወር ሚኒባስ ውስጥ 2ዐዐ ብር ያበደራት ልጅ፡፡ ደነቃት፡፡ በምንም አይነት ሊስትሮና መፅሀፍ ሻጭ ይሆናል ብላ አልገመተችም
ነበር::
<<ችግር የለም ጨርስና ትጠርግልኛለህ ... አልቸኩልም፡፡››አለችው፡፡
ንባቡን እንደቀጠለ ‹‹እንደተመቸሽ፡፡››አላት ፡፡
ከአስር ደቂቃ ጥበቃ በኃላ የሚያነበውን መፅሀፍ አጥፎ አስቀመጠና ቀናም ብሎ ሳያያት ወደ መሬት ወርዶ እግሯን የሊስትሮ ዕቃው ላይ እስክታስቀምጥ ጠብቆ ጫማዋን ያፀዳላት ጀመር፡፡
‹‹‹ይቅርታ የምንተዋወቅ መሰለኝ?››አለችው፡፡
ቀናም ብሎ ሳያያት ‹‹ይሆናል፡፡››
‹‹አስታወስከኝ ግን?››
‹‹ስለአንቺ እያሰብኩ ስላልነበረ አላስታወስኩሽም፡፡››
‹‹አንድ ቀን ከአዲስአባ ስንመጣ ሚኒባስ ውስጥ ብር አበድረኸኝ ነበር››
ማንነቷን ለማረጋገጥ ቀናም ብሎ ሳያያት ስራው ላይ እንዳቀረቀረ ‹‹አስታወስኩ፡፡››አላት፡፡
‹‹እንዴት እንደዛ ትሸውደኛለህ ግን?››
‹‹መስሎሽ ነው፡፡››
<< መስሎኝማ አይደለም፡፡በወቅቱ አንተን ለማግኘት እኮ ሀዋሳን ቀላል አላሰስኮትም፡፡››
‹‹እኔን ለመፈለግ እኮ የዛን ያህል መልፋት አልነበረብሽም፡፡እኔ ማለት ያ ዕብድ ነኝ፣እኔ ማለት ያቺ ሁለት ልጆች ስሯ አስተኝታ የምትለምነው እናት ትታይሻለች ..እሷ ማለት ነኝ፣እኔ ማለት የተራበ ጨቅላ፣የታረዘ አዛውንት ማለት ነኝ፡፡››
‹‹እሱ ገብቶኛል፡፡ባልከው መንገድም ለማድረግ ሞክሬያለው ግን ደግሞ አንተንም አግኝቼ ማመስገን ውስጤ በጣም ፈለገ፡፡››
‹‹እሺ ይሁን፤ምስጋናውን ተቀብዬለሁ፡፡››
‹‹እንደዚህማ በደረቁ አይሆንም፤ ቢያንስ እራት ጋብዤህ ነው ማመስገን የምፈልገው፡፡››
‹‹ደስ ይለኝ ነበር ፤እኔ ግን እራት የምበላው ከጓደኞቼ ጋር ነው፡፡ >>
‹‹‹ምን ችግር አለው ታዲያ ፤ደውልላቸውና ይምጡ፤አብረን እንበላለን፡፡›› በቀላሉ ልትለቀው አልፈለገችም፡፡
‹‹ስልክ የለኝም፤እነሱም የላቸውም፤ቤት ነው ሚጠብቁኝ፡፡››
<<በቃ ችግር የለውም ፤አብረን እንሄድና ይዘናቸው እንወጣለን፡፡››
‹‹ለምን ትቸገሪያለሽ?››
‹‹አልተቸገርኩም፡፡››
<<እኛ የምንበላው እዛው ሰፈር ነው፤ያ ደግሞ ላንቺ የሚመችሽ ቦታ አይደለም፡፡››
‹‹ግድ የለም ይመቸኛል፡፡››
‹‹እንግዲያው እኔ አንድ ሰዓት ነው ከዚህ የምነሳው፤አሁን 12 ሰዓት ነው ፤ለአንድ ሰዓት ሩብ ጉዳይ አካባቢ ተመልሰሽ ነይ፡፡ >>
‹‹አይ እዚሁ እጠብቅሀለው፡፡››አለችው፡፡
አፍጥጦ አያት፡፡ሰው እንደዚህ ችክ ሲልበት አይወድም፡፡‹‹ ግን ምን ቸገረኝ፤የራሷ ጉዳይ... መቀመጡ ሲደክማት ተነስታ ትሄድ የለ›› ብሎ ወደ ንባቡ ተመለሰ፡፡እሷም ወጪ ወራጁን እያየች ስለ እሱ ማሰብ ጀመረች ፡፡በአጋጣሚ በእጇ ገብቶማ ዳግመኛ አያመልጣትም፡፡ 12፡ 3ዐ ላይ ስልኳ ጮኸ ፡፡ አነሳችው፡፡ የቅርንጫፍ መስሪያ ቤቱ ስራ አስኪያጅ ነው፡፡
‹‹ሄሎ ልዑል፡፡››
‹‹አመሰግናለሁ..ሌላ ቀጠሮ አለብኝ፡፡››
‹‹አዎ ፡፡አንድ የድሮ የልብ ጓደኛዬን በአጋጣሚ አግኝቼ እራት ካልጋበዝኩሽ ስላለ ከእሱ ጋር ነው የማመሸው፡፡››
‹‹እሺ..ቻው አመሰግናለሁ፡፡››
ለአንድ እሩብ ጉዳይ መፅሀፎቹን ሰበሰበና በቦርሳውን ጠቀጠቃቸው፡፡ አንዱን በአንድ ተከሻው ሌላውን በሌላ ትከሻው አነገተና የሊስትሮ ሳጥኑን በቀኝ እጁ በመያዝ
መንገዱን ቀጠለ፡፡ተከተለችው፡፡እሷ እሱ የገረማትን ያህል እሱም ገርማዋለች፡፡ እንዲህ ችኮ ሴት ገጥሞት አያውቅም፡፡.
ወደ እሱ ቤት ጉዞ ጀምረው ግማሽ መንገድ ላይ እንደደረሱ‹‹ስሜን አልጠየቅከኝም?›› አለችው ፡፡
‹‹ስላላስፈለገኝ ነው ያልጠየቅኩሽ›› አላት፡፡
‹‹መተዋወቅ እኮ ክፋት የለውም፡፡››
‹‹ክፋት አለው መች ወጣኝ?፡፡››
‹‹ሶፊያ እባላለሁ...ያንተስ?››
‹‹ከዚህ በፊት በፈለገሽው ስም ልትጠሪኝ ትችያለሽ ብዬሽ እንደነበር አስታውሳለሁ፡፡ስም መለያ ነው፣እኔነቴን አይወክልም፡፡ አንቺ እኔን ከሌላ የሰው ልጅ ለይተሸ ለመጥራት ያስፈልገኛል ካልሽ የሚመችሽን ተጠቀሚ፡፡››
‹‹ሶቅራጦስ ይመችሀል?››
‹‹ዋናው ላንቺ ይመችሽ፡፡ይሄን ስም በፊት አንድ ታላቅና ቅዱስ ሰው ተጠቅሞበታል፡፡››
‹‹አውቃለሁ፤እኔም ለዛ ነው የመረጥኩት።
‹‹ደግ›› ይሄንን ሁሉ ሲያወሩ ብዙ የዉስጥ ለውስጥ መንገዶችን አልፈው ነበር፡፡ ግንብ አጥር ያለው ቤት ጋር ሲደርሱ የሊስትሮውን ዕቃ መሬት አስቀመጠና ከኪሱ በማውጣት መክፈት ጀመረ፡፡
‹‹5 ደቂቃ ጠብቂኝ መጣሁ፡፡ ››ብሏት እንደተገተረች ጥሏት ወደ ውስጥ ገባ ብትፈራም ጭለማ ውስጥ ቆማ መጠበቅ ጀመረች፡፡ ሰዓቱ አንድ ሰዓት ከሩብ ሆኗል በአራት ህፃናት ተከቦ መጣ፡፡ ሁሉም እየቧረቁ ስሩ ኩስ ኩስ ይላሉ፡፡የሁሉዎ ተቀራራቢ ነው በ7 እና በ12 ዓመት መሀል ሲሆን ከአራቱ ሦስቱ ሴቶች ናቸው
‹‹ጓደኞችህስ?››
‹‹እኚው›› አላት ወደ ልጆቹ እየጠቆመ፡፡
ከፈለግሽ ተከተይን በማለት ከእነሱ ጋር በፈገግታ እያወራና እየተሳሳቀ ቀድሟት መንገዱን ቀጠለ፡፡ ብዙም ከማይርቅ አንድ መንገድ ዳር ካለ ደከም ያለ ምግብ ቤት ገቡ ፡፡ ተከትለቻቸው፡፡አንድ ጠረጴዛ ከበው ተቀመጡ፡፡አንድ ለእሷም ሳበላት ፤ ተቀመጠች፡፡
እርጅና የተጫጫናቸው አሮጊት ከጓዲያ ወጡና‹‹ ... ልጆቼ መጣችሁ? በስንት ጊዜያችሁ ፤ናፍቃችሁኝ ነበር፡፡››
‹‹ሰላም ኖት ማዘር?››ታዲዬስ ነው፡፡
‹‹ሰላም ነኝ ፤ይመስገነው፡፡ደግሞ እንግዳ ይዛችሁ ነው የመጣችሁት?››
‹‹አዎ... ምግብ ቤት አጥታ ስትንከራተት መንገድ ላይ አግኝተናት ነው ይዘናት የመጣነው፡፡››
‹‹በሞትኩት.. ለሀገሩ እንግዳ ነቻ?››መጣሁ ብለው ተመልሰው ወደ ውስጥ ገቡ፡፡
‹‹ስምሽ ማን ነው? አለቻት ጎኗ የተቀመጠችውን ትንሽ ልጅ ፡፡
‹‹ሶፊያ..ያንቺስ?››
<<ሚጣ ነው?»
‹‹ሚጣ ታዲዬስ››
‹‹እሱ ምንሽ ነው? አለቻት በጣቷ እየጠቆመች፡፡እሱን ቀጥታ ጠይቃ ማይሆን መልስ ሰጥቷት ከምትበሳጭ በጎን ትክክለኛ ስሙን ለማወቅ መሞከሯ ነበር፡፡
በተኮላተፈ አንደበት‹‹አባቴ›› ብላ መለሰችላት
‹‹አንቺስ እናት ስምሽ ማነው?››
<<ሄለን>>
<<ሄለን ማ?>>
‹‹ሄለን ታዲወስ››
‹‹አባትሽ ታዲወስ የታለ?››
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ዶ/ር ሶፊያ ከአራት ወራት ቆይታ በኃላ ነበር ለሌላ ስራ ወደ ሀዋሳ የተመለሰችው፡፡ዛሬ አምስተኛ ቀኗ ነው፡፡መቼስ የሀዋሳ ውበት
ይበልጥ ፈክቶ ይበልጥ ጎልቶ የሚታየው በገዛ
እግር በዝግታ እየተጓዙ ሲያጣጥሙት ነው፡፡
ዶ/ር ሶፊያም ይሄንን እውነት በመገንዘብ
የእለቱን ስራዋን ካጠናቀቀች በኃላ የምሽቱን
አየር ነፋሻማነትና ተስማሚነትንም ከግምት
በማስገባት በእግር ዞር ዞር ለማለት ወሰነችና መኪናዋን ሆቴል ግቢ ውስጥ ትታ በእግሯ ወጣች፡፡ለ3ዐ ደቂቃ በከተማው ተሸከረከረች፡፡
ጉዞዋ አስደሳችና መንፈሷን ያረጋጋላት ቢሆንም ደከማት፤ ወደ ካፌ ጎራ ብላ እረፍት ለመውሰድ ከወሰነች በኃላ መልሳ ሀሳቧን
ቀየረችና ጫማዋን እያስጠረገች ወጪ
ወራጁን መቃኘት እንደሚሻላት አመነች፡፡
ባለችበት አስፓልት አቅጣጫ ጠርዝ ላይ
ወዳለው ሊስትሮ አመራች፡፡ ሊስትሮው ከጐኑ በግምት መቶ የሚሆኑ መፅሀፎች ለሽያጭ ዘርግቷል፡፡እሱም ሊስትሮ ወንበሩ ላይ ቁጭ ብሎ በተመስጦ እያነበበ ነው፡፡ተጠጋችው ፤ግንብ አጥር ተደግፎ የሚገኘው አግዳሚ ወንበር ላይ ቁጭ አለች፡፡
‹‹አንተ ነህ የምትጠርገው?››
ቀና ሳይል <<አዎ እኔ ነኝ፡፡ግን አሁን ስራ ስለያዝኩ እዛ ማዶ ያለው ልጅ ጋር ብታስጠርጊ››አላት በትህትና፡፡
ደነገጠች<< ...አዋ እራሱ ነው፡፡››አወቀችው ፡፡ የዛሬ ወር ሚኒባስ ውስጥ 2ዐዐ ብር ያበደራት ልጅ፡፡ ደነቃት፡፡ በምንም አይነት ሊስትሮና መፅሀፍ ሻጭ ይሆናል ብላ አልገመተችም
ነበር::
<<ችግር የለም ጨርስና ትጠርግልኛለህ ... አልቸኩልም፡፡››አለችው፡፡
ንባቡን እንደቀጠለ ‹‹እንደተመቸሽ፡፡››አላት ፡፡
ከአስር ደቂቃ ጥበቃ በኃላ የሚያነበውን መፅሀፍ አጥፎ አስቀመጠና ቀናም ብሎ ሳያያት ወደ መሬት ወርዶ እግሯን የሊስትሮ ዕቃው ላይ እስክታስቀምጥ ጠብቆ ጫማዋን ያፀዳላት ጀመር፡፡
‹‹‹ይቅርታ የምንተዋወቅ መሰለኝ?››አለችው፡፡
ቀናም ብሎ ሳያያት ‹‹ይሆናል፡፡››
‹‹አስታወስከኝ ግን?››
‹‹ስለአንቺ እያሰብኩ ስላልነበረ አላስታወስኩሽም፡፡››
‹‹አንድ ቀን ከአዲስአባ ስንመጣ ሚኒባስ ውስጥ ብር አበድረኸኝ ነበር››
ማንነቷን ለማረጋገጥ ቀናም ብሎ ሳያያት ስራው ላይ እንዳቀረቀረ ‹‹አስታወስኩ፡፡››አላት፡፡
‹‹እንዴት እንደዛ ትሸውደኛለህ ግን?››
‹‹መስሎሽ ነው፡፡››
<< መስሎኝማ አይደለም፡፡በወቅቱ አንተን ለማግኘት እኮ ሀዋሳን ቀላል አላሰስኮትም፡፡››
‹‹እኔን ለመፈለግ እኮ የዛን ያህል መልፋት አልነበረብሽም፡፡እኔ ማለት ያ ዕብድ ነኝ፣እኔ ማለት ያቺ ሁለት ልጆች ስሯ አስተኝታ የምትለምነው እናት ትታይሻለች ..እሷ ማለት ነኝ፣እኔ ማለት የተራበ ጨቅላ፣የታረዘ አዛውንት ማለት ነኝ፡፡››
‹‹እሱ ገብቶኛል፡፡ባልከው መንገድም ለማድረግ ሞክሬያለው ግን ደግሞ አንተንም አግኝቼ ማመስገን ውስጤ በጣም ፈለገ፡፡››
‹‹እሺ ይሁን፤ምስጋናውን ተቀብዬለሁ፡፡››
‹‹እንደዚህማ በደረቁ አይሆንም፤ ቢያንስ እራት ጋብዤህ ነው ማመስገን የምፈልገው፡፡››
‹‹ደስ ይለኝ ነበር ፤እኔ ግን እራት የምበላው ከጓደኞቼ ጋር ነው፡፡ >>
‹‹‹ምን ችግር አለው ታዲያ ፤ደውልላቸውና ይምጡ፤አብረን እንበላለን፡፡›› በቀላሉ ልትለቀው አልፈለገችም፡፡
‹‹ስልክ የለኝም፤እነሱም የላቸውም፤ቤት ነው ሚጠብቁኝ፡፡››
<<በቃ ችግር የለውም ፤አብረን እንሄድና ይዘናቸው እንወጣለን፡፡››
‹‹ለምን ትቸገሪያለሽ?››
‹‹አልተቸገርኩም፡፡››
<<እኛ የምንበላው እዛው ሰፈር ነው፤ያ ደግሞ ላንቺ የሚመችሽ ቦታ አይደለም፡፡››
‹‹ግድ የለም ይመቸኛል፡፡››
‹‹እንግዲያው እኔ አንድ ሰዓት ነው ከዚህ የምነሳው፤አሁን 12 ሰዓት ነው ፤ለአንድ ሰዓት ሩብ ጉዳይ አካባቢ ተመልሰሽ ነይ፡፡ >>
‹‹አይ እዚሁ እጠብቅሀለው፡፡››አለችው፡፡
አፍጥጦ አያት፡፡ሰው እንደዚህ ችክ ሲልበት አይወድም፡፡‹‹ ግን ምን ቸገረኝ፤የራሷ ጉዳይ... መቀመጡ ሲደክማት ተነስታ ትሄድ የለ›› ብሎ ወደ ንባቡ ተመለሰ፡፡እሷም ወጪ ወራጁን እያየች ስለ እሱ ማሰብ ጀመረች ፡፡በአጋጣሚ በእጇ ገብቶማ ዳግመኛ አያመልጣትም፡፡ 12፡ 3ዐ ላይ ስልኳ ጮኸ ፡፡ አነሳችው፡፡ የቅርንጫፍ መስሪያ ቤቱ ስራ አስኪያጅ ነው፡፡
‹‹ሄሎ ልዑል፡፡››
‹‹አመሰግናለሁ..ሌላ ቀጠሮ አለብኝ፡፡››
‹‹አዎ ፡፡አንድ የድሮ የልብ ጓደኛዬን በአጋጣሚ አግኝቼ እራት ካልጋበዝኩሽ ስላለ ከእሱ ጋር ነው የማመሸው፡፡››
‹‹እሺ..ቻው አመሰግናለሁ፡፡››
ለአንድ እሩብ ጉዳይ መፅሀፎቹን ሰበሰበና በቦርሳውን ጠቀጠቃቸው፡፡ አንዱን በአንድ ተከሻው ሌላውን በሌላ ትከሻው አነገተና የሊስትሮ ሳጥኑን በቀኝ እጁ በመያዝ
መንገዱን ቀጠለ፡፡ተከተለችው፡፡እሷ እሱ የገረማትን ያህል እሱም ገርማዋለች፡፡ እንዲህ ችኮ ሴት ገጥሞት አያውቅም፡፡.
ወደ እሱ ቤት ጉዞ ጀምረው ግማሽ መንገድ ላይ እንደደረሱ‹‹ስሜን አልጠየቅከኝም?›› አለችው ፡፡
‹‹ስላላስፈለገኝ ነው ያልጠየቅኩሽ›› አላት፡፡
‹‹መተዋወቅ እኮ ክፋት የለውም፡፡››
‹‹ክፋት አለው መች ወጣኝ?፡፡››
‹‹ሶፊያ እባላለሁ...ያንተስ?››
‹‹ከዚህ በፊት በፈለገሽው ስም ልትጠሪኝ ትችያለሽ ብዬሽ እንደነበር አስታውሳለሁ፡፡ስም መለያ ነው፣እኔነቴን አይወክልም፡፡ አንቺ እኔን ከሌላ የሰው ልጅ ለይተሸ ለመጥራት ያስፈልገኛል ካልሽ የሚመችሽን ተጠቀሚ፡፡››
‹‹ሶቅራጦስ ይመችሀል?››
‹‹ዋናው ላንቺ ይመችሽ፡፡ይሄን ስም በፊት አንድ ታላቅና ቅዱስ ሰው ተጠቅሞበታል፡፡››
‹‹አውቃለሁ፤እኔም ለዛ ነው የመረጥኩት።
‹‹ደግ›› ይሄንን ሁሉ ሲያወሩ ብዙ የዉስጥ ለውስጥ መንገዶችን አልፈው ነበር፡፡ ግንብ አጥር ያለው ቤት ጋር ሲደርሱ የሊስትሮውን ዕቃ መሬት አስቀመጠና ከኪሱ በማውጣት መክፈት ጀመረ፡፡
‹‹5 ደቂቃ ጠብቂኝ መጣሁ፡፡ ››ብሏት እንደተገተረች ጥሏት ወደ ውስጥ ገባ ብትፈራም ጭለማ ውስጥ ቆማ መጠበቅ ጀመረች፡፡ ሰዓቱ አንድ ሰዓት ከሩብ ሆኗል በአራት ህፃናት ተከቦ መጣ፡፡ ሁሉም እየቧረቁ ስሩ ኩስ ኩስ ይላሉ፡፡የሁሉዎ ተቀራራቢ ነው በ7 እና በ12 ዓመት መሀል ሲሆን ከአራቱ ሦስቱ ሴቶች ናቸው
‹‹ጓደኞችህስ?››
‹‹እኚው›› አላት ወደ ልጆቹ እየጠቆመ፡፡
ከፈለግሽ ተከተይን በማለት ከእነሱ ጋር በፈገግታ እያወራና እየተሳሳቀ ቀድሟት መንገዱን ቀጠለ፡፡ ብዙም ከማይርቅ አንድ መንገድ ዳር ካለ ደከም ያለ ምግብ ቤት ገቡ ፡፡ ተከትለቻቸው፡፡አንድ ጠረጴዛ ከበው ተቀመጡ፡፡አንድ ለእሷም ሳበላት ፤ ተቀመጠች፡፡
እርጅና የተጫጫናቸው አሮጊት ከጓዲያ ወጡና‹‹ ... ልጆቼ መጣችሁ? በስንት ጊዜያችሁ ፤ናፍቃችሁኝ ነበር፡፡››
‹‹ሰላም ኖት ማዘር?››ታዲዬስ ነው፡፡
‹‹ሰላም ነኝ ፤ይመስገነው፡፡ደግሞ እንግዳ ይዛችሁ ነው የመጣችሁት?››
‹‹አዎ... ምግብ ቤት አጥታ ስትንከራተት መንገድ ላይ አግኝተናት ነው ይዘናት የመጣነው፡፡››
‹‹በሞትኩት.. ለሀገሩ እንግዳ ነቻ?››መጣሁ ብለው ተመልሰው ወደ ውስጥ ገቡ፡፡
‹‹ስምሽ ማን ነው? አለቻት ጎኗ የተቀመጠችውን ትንሽ ልጅ ፡፡
‹‹ሶፊያ..ያንቺስ?››
<<ሚጣ ነው?»
‹‹ሚጣ ታዲዬስ››
‹‹እሱ ምንሽ ነው? አለቻት በጣቷ እየጠቆመች፡፡እሱን ቀጥታ ጠይቃ ማይሆን መልስ ሰጥቷት ከምትበሳጭ በጎን ትክክለኛ ስሙን ለማወቅ መሞከሯ ነበር፡፡
በተኮላተፈ አንደበት‹‹አባቴ›› ብላ መለሰችላት
‹‹አንቺስ እናት ስምሽ ማነው?››
<<ሄለን>>
<<ሄለን ማ?>>
‹‹ሄለን ታዲወስ››
‹‹አባትሽ ታዲወስ የታለ?››
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
"አዎ ገብቶኛል....ግን ይቀረፃል ያልሺው?"
"አዎ ይሄንን በከፍተኛ ሚስጥር ነው....ድንገት ተስቶሽ በህልምሽ እንኳን ብታወሪ ህይወትሽን ያስከፍልሻል።ምክንያቱም ደንበኞቻችን እንደሚቀረፁ ቢያውቁ እዚህች ቤት ዳግመኛ ዝር አይሉም።እኛ ግን በጣም ምስጢራዊና ማንም በቀላል ፍተሻ ማግኘት በማይችልበት ቦታዎች ካሜራዎች አሉን።ይሄ በዎናነት ሰራተኞቻችንን ከአደጋ ለመጠበቅ ነው። ማንኛውም ሰው አጉል እመል ኖሮት ጥቃት ልፈፅም ቢል በፈጥነን እንደርሳለን፡፡ ከእንደገና ሰውዬው በሂደት ከእኛ ጋር ተቃቅሮ ድርጅታችንን ሊያጠቃ ቢንቀሳቀስ ያ ሚስጥር መከላከያ ጋሻችን ነው።
"አሁን ገባኝ"
"አዎ...ግን ላስጠንቅቅሽ...ስራ ስትጀምሪ ፈፅሞ ስለካሜራው በአእምሮሽ ማሰብ የለብሽም...ልክ አንድ የፊልም ተዋናይ ስትተውን ፊት ለፊቷ ስለተደቀነው ካሜራ ቁብ እንደማይሰጣት ሁሉ አንቺም ተመሳሳዩን ማድረግ አለብሽ፤ ይሄንንን ከመጀመሪያው ቀን ጀምረሽ መልመድ አለብሽ"
"እሺ እንዳልሺኝ አደርጋለሁ።
"እሺ አሁን ጨርሰናል...ክፍልሽን ያሳዩሻል ግቢና እረፊ... ልክ 9.30 ላይ ከክፍልሽ ወደማሳጅ ቤቱ ይወስድሻል። አስር ሰዓት ላይ የመጀመሪያ ደንበኛሽ ይመጣል። ዝግጁ ሆነሽ ጠብቂው ።ከእኔ ጋር ነገ ጠዋት እንገናኛለን ብላ ከመቀመጫዋ ተነሳችና ጉንጯን ስማት በተቀመጠችበት ጥላት ሄደች።
ሳባ በህይወቷ ዘመኗ የከፋው ፍርሀት ነው በመላ ሰውነቷ ተሰራጭቶ እያንዘፈዘፍት ያለው እርግጥ ይህ ፍራቻ ገና ጠዋት ስለፕሮግራሙ ከተነገራት ጀምሮ ነው ሲረብሻት የዋለው ። ሰአቱ ሲቃረብ እንዲያደፋፍራት መድሀኒት ነገር ወይም መጠጥ ጠጣ ጠጣ አድርጋ ለመሄድ ፈልጋ ነበር።ግን ስልጠና ላይ እንደተነገራት ወደስራ መጠጥ ጠጥቶ አይደለም ቀምሶ እንኳን መግባት አይቻልም።ባይሆን በስራ ላይ እያለች ደንበኛው መጠጥ እንዲቀርብለት ካዘዘና ለእሷም ከጋበዛት የዛኔ ነፃ እንደሆነች ነው የተማረችው።በመጀመሪያ ቀን የሙከራ ጊዜዎ ደግሞ ስህተት በመስራት ልትጀምረው አልፈለገችም። ቢያንስ እያወቀች መሳሳት አትፈልግም"ሰገን
ሰገን ነች ማሳጅ መስጫ ክፍል ድረስ ይዛት የሄደችው። እያንዳንዱ ለማሳጅ የምትገለገልበት እቃ የት የት እንዳለ ምን ማድረግ እንዳለባት ምን አለማድረግ እንዳለባት ከ20 ደቂቃ በላይ ክፍል ውስጥ እየተንጎራደደች አንድን ዕቃ እየያዘች መልሳ እያስቀመጠች አብራራችላትና መልካም እድል ተመኘችላትና ተሰናብታት ወጣች።
ጥላት ከሄደች ከ10 ደቂቃ በኃላ በራፍ ተቆረቆረ ከተቀመጠችበት በመበርገግ ቆመች...መልሳ ቁጭ አለች...የኋላ መውጫ በር ቢኖረው በራ ለመውጣት ሁሉ ተመኘች።
ደግሞ በራፍ ተቆረቆረ..እንደምንም መቀመጫዋን ለቃ ወደበሩ ተራመደች ከፈተችው…በድንጋጤ ላይ ድንጋጤ የሚጨምር ሁኔታ ተከሰተ በራፋ ላይ የገጠማት አንድ ግዙፍ አስፈሪ መልክና ኮስታራ ፊት ያለው ሰው ፊቷ ተጋረጠ" ወይኔ በጌታ አሁን ይሄ ምኑ ይታሻል?"ስትል በቅፅበት ውስጥ አሰበች"አሽቀንጥሮ.ገፈተራትና.ወደውስጥ.ገባ።በድንጋጤ.አይኖቿን.በለጠጠች።
በየክፍሉ እየገባ ይፈትሽ ጀመር።ቁም ሳጥኖቹን ሁሉ እያንዳንድን መሳቢያ ሳይቀር እየከፈተ እየዘጋ ማየቱን ቀጠለ
"ይሄ ምን የሚሉት ደንበኛ ነው? "ስትል በውስጧ አሰበች። በሁኔታው ተበሳጨች፤ስትበሳጭ.በመጠኑ.ፍራቻዋ.ቀነስ.አለላት።
"ጌታዬ ምን ፈልገው ነው?"
መሀል ወለል ላይ ቆመና ዙሪያ ገባውን ኮርኒሱንም ሳይቀር በጥንቃቄ ካየ በኋላ ለእሷ ጥያቄ ምንም መልስ ሳይሰጥ እንደ አመጣጡ መልሶ ወጣ። ይበልጥ ግራ ተገባች፡፡ ይሄ ጠረንገሎና አስቀያሚ እዛ የማሳጅ ጠረጴዛ ላይ ተኝቶ እሺኝ ስላላላት እግዚያብሄር ይመስገን ብላ አመስግና ሳትጨርስ በራፍ ተከፈተና ያው ሰውዬ መልሶ አንገቱን አሰገገ...ሀሞቷ ፍስስ አለ...በራፉን ሙሉ በሙሉ ከፈተው ሌሎች ሰዎች ታያት።ሶስት መሆናቸውን አየች።
"በአንዴ ሶስት ሰው ማሸት ይቻላል እንዴ? እንዲህ አይነት ነገር እንዳለ አልተነገረኝም...ምን ነካቸው ቢያንስ ለተለማማጅ ሰራተኛ እንደዚህ ማድረግ ይገባል?"በውስጧ አጉረምርማ ሳትጨርስ ግራና ቀኝ የነበሩ ሁለት ወጠምሾች መሀል ያለውን ሰውዬ ወደውስጥ አስገቡትና እነሱ ወደኋላ ሸሽተው ከክፍሉ ወጡ። በራፉ ከውጭ ተዘጋ።
ግድግዳውን ተለጥፋ እንደቆመች ሰውዬው ላይ አፈጠጠችበት። ሰውዬውን ታውቀዋለች..አዎ በደንብ ታውቀዋለች። ሮጣ ሄዳ ልትጠመጠምበት ነበር።ትዝ ሲላት ለካ የምታውቀው በመገናኛ ብዙሀን ነው።ማን ነበር..አዎ አስታወሰችው። እንዴ እዚህ ምን ይሰራል?"
‹‹ጤና ይስጥልኝ ቆንጆ?››አላት በሚያምር ግን አስገምጋሚ በሆነ ድምፅ።
በፍጥነት ወደቀልቧ ለመመለስ ጥረት አደረገች። ፊቷን በፈገግታ አደመቀችና እጇን ለሰላምታ ዘረጋች….በተመሳሳይ ድምቀት ጨበጣት ...
‹‹ጌታዬ ትንሽ አረፍ ትላለህ...ወይስ?››
"ቆይ ትንሽ ትንፋሼን ልሰብስብ... ካንቺም ጋር በደንብ ልተዋወቅ።"አለና ወደሶፋው ሄደና ተቀመጠ፡፡
"ጌታዬ ቀለል እንዲልህ ኮትህን ታወልቀው?"
"አዎ ትክክል ነሽ..››ብሎ በተቀመጠበት ሶፋ ሆኖ ኮቱን አወለቀ.. በፍጥነት ተቀብላ ወደመስቀያው ሄደችና በጥንቃቄ ሰቀለችና ወደ ሰውዬው ተመለሰችና ፊት ለፊቱ ተቀመጠች።
‹‹ስምሽን ማን ልበል?›› ጠየቃት፡፡
‹‹ቬሮኒካ"አለችው፡፡ ይሄ ስም ድንገት አፏ ላይ የመጣላት ስም ነው…ለዚህ ስራ ትክክለኛ ስምን መጠቀም አግባብ መስሎ ስላልተሰማት ነው እንዲህ ያደረገችው፡፡
‹‹የእኔ ክብሮም››አላት ሰውዬው፡
‹‹ጌታዬ አንተን የማያውቅ ኢትዬጴያዊ ማን አለ?››
‹‹እንደዛ ከሆነ ጥሩ...››አለና ከኪሱ ሞባይሉን አወጣና ደወለ፡፡
"የሚጠጣ አስመጣልን እስቲ"አለና ትዕዛዝ ካስተላለፈ በኃላ ሞባይሉን ዘግቶ ቦታው መለሠና።
"ከነገሩኝ በላይ ቆንጆ ነሽ"አላት
ከት ብላ ሳቀች.‹‹..እንዴ ማነው እንዲህ አይነት ጥብቅ ሚስጥር ያሾለከው?" አለችው፡፡
"የውስጥ ሰላይ አለኝ...ከዛሬ ጀምሮ ሙሉ ስራው ያንቺን እንቅስቃሴ መከታተል ይሆናል››
"እንግዲህ እኛም ቀዳሚ ስራችን ውስጣችንን ከሰላዬችና ከሰርጎ ገቦች ማፅዳት ይሆናል" ስትለው በራፍ ተቆረቆረ ፡፡ መቀመጫዋን ለቃ ተንቀሳቀሰችና ከፈተች፡፡ ከጋርዶቹ አንዱ ነው። በሰርቪስ ትሪ ሙሉ ጠርሙስ ውስኪ ከሁለት ብርጭቆ ጋር ይዟል። አልፏት ወደ ውስጥ ገባና ጠረጴዛ ላይ አስቀምጦ ወጥቶ ሄደ ...ተከትላው ሄደችና በራፉን ከውስጥ በመቀርቀር ወደ ጠረጴዛው ተመለሰች። ውስኪውን ጠርሙስ ከፈተችና በአንድ ብርጭቆ በመቅዳት አቀረበችለትና ቦታዋ ተመልሳ ቁጭ አለች።
"እንዴ ላንቺስ?"
"እኔማ ስራ ላይ ነኝ...ሰክሬ ሰውነትህን ብቦጫጭቅህስ? "
"ነፍሴን አትቦጫጭቂያት እንጂ ለቆዳዬ ችግር የለም...በሰርጀሪ ይድናል "
"አረ ተው ...አንተን ማሳከም አይደለም ከእኔ ከድርጅቴም አቅም በላይ ነው"
"አልገባኝም...ቆዳ ቆዳ ነው?ምኑ ነው የሚከብድ››
‹‹ኸረ ጌታዬ ቆዳ ሁሉማ ቆዳ አይደለም..››
ራሱ ተነሳና ጠርሙሱን አንስቶ በባዶው ብርጭቆ ቀዳና "በይ እንደውም ጠጪና የምታደርጊኝን አድርጊኝና የሚሆነውን አብረን እናያለን....እግረ መንገዴንም የእኔ ቆዳ እንዴት የተለየ እንደሆነ እንዳውቅ ታደርጊያለሽ።
"ጌታዬ በአንድ ምስኪን ላይማ ይሄን ያህል አትጨክንባት››
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
"አዎ ገብቶኛል....ግን ይቀረፃል ያልሺው?"
"አዎ ይሄንን በከፍተኛ ሚስጥር ነው....ድንገት ተስቶሽ በህልምሽ እንኳን ብታወሪ ህይወትሽን ያስከፍልሻል።ምክንያቱም ደንበኞቻችን እንደሚቀረፁ ቢያውቁ እዚህች ቤት ዳግመኛ ዝር አይሉም።እኛ ግን በጣም ምስጢራዊና ማንም በቀላል ፍተሻ ማግኘት በማይችልበት ቦታዎች ካሜራዎች አሉን።ይሄ በዎናነት ሰራተኞቻችንን ከአደጋ ለመጠበቅ ነው። ማንኛውም ሰው አጉል እመል ኖሮት ጥቃት ልፈፅም ቢል በፈጥነን እንደርሳለን፡፡ ከእንደገና ሰውዬው በሂደት ከእኛ ጋር ተቃቅሮ ድርጅታችንን ሊያጠቃ ቢንቀሳቀስ ያ ሚስጥር መከላከያ ጋሻችን ነው።
"አሁን ገባኝ"
"አዎ...ግን ላስጠንቅቅሽ...ስራ ስትጀምሪ ፈፅሞ ስለካሜራው በአእምሮሽ ማሰብ የለብሽም...ልክ አንድ የፊልም ተዋናይ ስትተውን ፊት ለፊቷ ስለተደቀነው ካሜራ ቁብ እንደማይሰጣት ሁሉ አንቺም ተመሳሳዩን ማድረግ አለብሽ፤ ይሄንንን ከመጀመሪያው ቀን ጀምረሽ መልመድ አለብሽ"
"እሺ እንዳልሺኝ አደርጋለሁ።
"እሺ አሁን ጨርሰናል...ክፍልሽን ያሳዩሻል ግቢና እረፊ... ልክ 9.30 ላይ ከክፍልሽ ወደማሳጅ ቤቱ ይወስድሻል። አስር ሰዓት ላይ የመጀመሪያ ደንበኛሽ ይመጣል። ዝግጁ ሆነሽ ጠብቂው ።ከእኔ ጋር ነገ ጠዋት እንገናኛለን ብላ ከመቀመጫዋ ተነሳችና ጉንጯን ስማት በተቀመጠችበት ጥላት ሄደች።
ሳባ በህይወቷ ዘመኗ የከፋው ፍርሀት ነው በመላ ሰውነቷ ተሰራጭቶ እያንዘፈዘፍት ያለው እርግጥ ይህ ፍራቻ ገና ጠዋት ስለፕሮግራሙ ከተነገራት ጀምሮ ነው ሲረብሻት የዋለው ። ሰአቱ ሲቃረብ እንዲያደፋፍራት መድሀኒት ነገር ወይም መጠጥ ጠጣ ጠጣ አድርጋ ለመሄድ ፈልጋ ነበር።ግን ስልጠና ላይ እንደተነገራት ወደስራ መጠጥ ጠጥቶ አይደለም ቀምሶ እንኳን መግባት አይቻልም።ባይሆን በስራ ላይ እያለች ደንበኛው መጠጥ እንዲቀርብለት ካዘዘና ለእሷም ከጋበዛት የዛኔ ነፃ እንደሆነች ነው የተማረችው።በመጀመሪያ ቀን የሙከራ ጊዜዎ ደግሞ ስህተት በመስራት ልትጀምረው አልፈለገችም። ቢያንስ እያወቀች መሳሳት አትፈልግም"ሰገን
ሰገን ነች ማሳጅ መስጫ ክፍል ድረስ ይዛት የሄደችው። እያንዳንዱ ለማሳጅ የምትገለገልበት እቃ የት የት እንዳለ ምን ማድረግ እንዳለባት ምን አለማድረግ እንዳለባት ከ20 ደቂቃ በላይ ክፍል ውስጥ እየተንጎራደደች አንድን ዕቃ እየያዘች መልሳ እያስቀመጠች አብራራችላትና መልካም እድል ተመኘችላትና ተሰናብታት ወጣች።
ጥላት ከሄደች ከ10 ደቂቃ በኃላ በራፍ ተቆረቆረ ከተቀመጠችበት በመበርገግ ቆመች...መልሳ ቁጭ አለች...የኋላ መውጫ በር ቢኖረው በራ ለመውጣት ሁሉ ተመኘች።
ደግሞ በራፍ ተቆረቆረ..እንደምንም መቀመጫዋን ለቃ ወደበሩ ተራመደች ከፈተችው…በድንጋጤ ላይ ድንጋጤ የሚጨምር ሁኔታ ተከሰተ በራፋ ላይ የገጠማት አንድ ግዙፍ አስፈሪ መልክና ኮስታራ ፊት ያለው ሰው ፊቷ ተጋረጠ" ወይኔ በጌታ አሁን ይሄ ምኑ ይታሻል?"ስትል በቅፅበት ውስጥ አሰበች"አሽቀንጥሮ.ገፈተራትና.ወደውስጥ.ገባ።በድንጋጤ.አይኖቿን.በለጠጠች።
በየክፍሉ እየገባ ይፈትሽ ጀመር።ቁም ሳጥኖቹን ሁሉ እያንዳንድን መሳቢያ ሳይቀር እየከፈተ እየዘጋ ማየቱን ቀጠለ
"ይሄ ምን የሚሉት ደንበኛ ነው? "ስትል በውስጧ አሰበች። በሁኔታው ተበሳጨች፤ስትበሳጭ.በመጠኑ.ፍራቻዋ.ቀነስ.አለላት።
"ጌታዬ ምን ፈልገው ነው?"
መሀል ወለል ላይ ቆመና ዙሪያ ገባውን ኮርኒሱንም ሳይቀር በጥንቃቄ ካየ በኋላ ለእሷ ጥያቄ ምንም መልስ ሳይሰጥ እንደ አመጣጡ መልሶ ወጣ። ይበልጥ ግራ ተገባች፡፡ ይሄ ጠረንገሎና አስቀያሚ እዛ የማሳጅ ጠረጴዛ ላይ ተኝቶ እሺኝ ስላላላት እግዚያብሄር ይመስገን ብላ አመስግና ሳትጨርስ በራፍ ተከፈተና ያው ሰውዬ መልሶ አንገቱን አሰገገ...ሀሞቷ ፍስስ አለ...በራፉን ሙሉ በሙሉ ከፈተው ሌሎች ሰዎች ታያት።ሶስት መሆናቸውን አየች።
"በአንዴ ሶስት ሰው ማሸት ይቻላል እንዴ? እንዲህ አይነት ነገር እንዳለ አልተነገረኝም...ምን ነካቸው ቢያንስ ለተለማማጅ ሰራተኛ እንደዚህ ማድረግ ይገባል?"በውስጧ አጉረምርማ ሳትጨርስ ግራና ቀኝ የነበሩ ሁለት ወጠምሾች መሀል ያለውን ሰውዬ ወደውስጥ አስገቡትና እነሱ ወደኋላ ሸሽተው ከክፍሉ ወጡ። በራፉ ከውጭ ተዘጋ።
ግድግዳውን ተለጥፋ እንደቆመች ሰውዬው ላይ አፈጠጠችበት። ሰውዬውን ታውቀዋለች..አዎ በደንብ ታውቀዋለች። ሮጣ ሄዳ ልትጠመጠምበት ነበር።ትዝ ሲላት ለካ የምታውቀው በመገናኛ ብዙሀን ነው።ማን ነበር..አዎ አስታወሰችው። እንዴ እዚህ ምን ይሰራል?"
‹‹ጤና ይስጥልኝ ቆንጆ?››አላት በሚያምር ግን አስገምጋሚ በሆነ ድምፅ።
በፍጥነት ወደቀልቧ ለመመለስ ጥረት አደረገች። ፊቷን በፈገግታ አደመቀችና እጇን ለሰላምታ ዘረጋች….በተመሳሳይ ድምቀት ጨበጣት ...
‹‹ጌታዬ ትንሽ አረፍ ትላለህ...ወይስ?››
"ቆይ ትንሽ ትንፋሼን ልሰብስብ... ካንቺም ጋር በደንብ ልተዋወቅ።"አለና ወደሶፋው ሄደና ተቀመጠ፡፡
"ጌታዬ ቀለል እንዲልህ ኮትህን ታወልቀው?"
"አዎ ትክክል ነሽ..››ብሎ በተቀመጠበት ሶፋ ሆኖ ኮቱን አወለቀ.. በፍጥነት ተቀብላ ወደመስቀያው ሄደችና በጥንቃቄ ሰቀለችና ወደ ሰውዬው ተመለሰችና ፊት ለፊቱ ተቀመጠች።
‹‹ስምሽን ማን ልበል?›› ጠየቃት፡፡
‹‹ቬሮኒካ"አለችው፡፡ ይሄ ስም ድንገት አፏ ላይ የመጣላት ስም ነው…ለዚህ ስራ ትክክለኛ ስምን መጠቀም አግባብ መስሎ ስላልተሰማት ነው እንዲህ ያደረገችው፡፡
‹‹የእኔ ክብሮም››አላት ሰውዬው፡
‹‹ጌታዬ አንተን የማያውቅ ኢትዬጴያዊ ማን አለ?››
‹‹እንደዛ ከሆነ ጥሩ...››አለና ከኪሱ ሞባይሉን አወጣና ደወለ፡፡
"የሚጠጣ አስመጣልን እስቲ"አለና ትዕዛዝ ካስተላለፈ በኃላ ሞባይሉን ዘግቶ ቦታው መለሠና።
"ከነገሩኝ በላይ ቆንጆ ነሽ"አላት
ከት ብላ ሳቀች.‹‹..እንዴ ማነው እንዲህ አይነት ጥብቅ ሚስጥር ያሾለከው?" አለችው፡፡
"የውስጥ ሰላይ አለኝ...ከዛሬ ጀምሮ ሙሉ ስራው ያንቺን እንቅስቃሴ መከታተል ይሆናል››
"እንግዲህ እኛም ቀዳሚ ስራችን ውስጣችንን ከሰላዬችና ከሰርጎ ገቦች ማፅዳት ይሆናል" ስትለው በራፍ ተቆረቆረ ፡፡ መቀመጫዋን ለቃ ተንቀሳቀሰችና ከፈተች፡፡ ከጋርዶቹ አንዱ ነው። በሰርቪስ ትሪ ሙሉ ጠርሙስ ውስኪ ከሁለት ብርጭቆ ጋር ይዟል። አልፏት ወደ ውስጥ ገባና ጠረጴዛ ላይ አስቀምጦ ወጥቶ ሄደ ...ተከትላው ሄደችና በራፉን ከውስጥ በመቀርቀር ወደ ጠረጴዛው ተመለሰች። ውስኪውን ጠርሙስ ከፈተችና በአንድ ብርጭቆ በመቅዳት አቀረበችለትና ቦታዋ ተመልሳ ቁጭ አለች።
"እንዴ ላንቺስ?"
"እኔማ ስራ ላይ ነኝ...ሰክሬ ሰውነትህን ብቦጫጭቅህስ? "
"ነፍሴን አትቦጫጭቂያት እንጂ ለቆዳዬ ችግር የለም...በሰርጀሪ ይድናል "
"አረ ተው ...አንተን ማሳከም አይደለም ከእኔ ከድርጅቴም አቅም በላይ ነው"
"አልገባኝም...ቆዳ ቆዳ ነው?ምኑ ነው የሚከብድ››
‹‹ኸረ ጌታዬ ቆዳ ሁሉማ ቆዳ አይደለም..››
ራሱ ተነሳና ጠርሙሱን አንስቶ በባዶው ብርጭቆ ቀዳና "በይ እንደውም ጠጪና የምታደርጊኝን አድርጊኝና የሚሆነውን አብረን እናያለን....እግረ መንገዴንም የእኔ ቆዳ እንዴት የተለየ እንደሆነ እንዳውቅ ታደርጊያለሽ።
"ጌታዬ በአንድ ምስኪን ላይማ ይሄን ያህል አትጨክንባት››
#ጉዞ_በፀሎት
(አቃቂ እና ቦሌ)
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ድክምክም ብሎታል፡፡ግን ደግሞ አልጋው ላይ ተኝቷ በሀሳብ እየተንገላታ ነው፡፡ ሰለሞን በሁለት በኩል ስለት ባለው ሰይፍ የሚጫወት ህፃን አይነት ሰው እንደሆነ እየተሰማው ነው፡፡ሞያውን በተመለከተ ለሶስት አመት በከፍተኛ የፕሮፌሽናል ደረጃ በምድረ-አሜሪካ ሲሰራ አንድም ጊዜ እንደዚህ አይነት ክፍተት ተከስቶበት አያውቅም..በዛም በራሱ ሲመካና ሲኮራ ኖሮ ነበር፡፡አሁን ግን ወደሀገሩ ተመልሶ ባጋጠሙት የመጀመሪያ ደንበኞቹ ከፍተኛ የሚባል ሽንቁር ተከስቶበታል፡፡አንድ ባለሞያ የሞያውን ስነምግባር አክብሮ ስራውን መስራት የሚገደደው ለደንበኞች ደህንነትንና ጥቅም ሲባል ብቻ አይደለም…ለራሱ ለሞያው ክብርና ተቀባይነትም እያንዳንዱ ባለሞያ የስራ-አፈፃፀም ሁኔታ ትልቅ ድርሻ አለው፡፡በሙስናና በጥቅማጥቅም የሚታለሉ ዳኞችና አቃቢ-ህጎች በሞሉበት ሀገር ፍርድቤት ሊከበርና ሊታመን አይችልም፡፡ሌላውም ሞያ እንደዛው ነው፡፡ ይህን ስራ ከጀመረ ያጋጠመችው ትልቋ ደንበኛው በፀሎት ነች፡፡እርግጥ ቀጥታ ደንበኛው እሷ ሳትሆን ወላጆቾ ናቸው፡፡ከእነሱ ጋር እየሰራ ያለውን ስራ የሞያው ስነምግባር በሚፈቅደው መንገድ ጥርትና ጥልል አድርጎ እየሰራ ነው፡፡ቢሆንም ቀጥታ ቀጣሪው ልጃቸው በፀሎት ነች፡፡እሷ ፍላጎቱን ተረድታ አፈቅርሀለው ብትለው እንኳን ፍቅሯ እሱ ለወላጆቾ በሚያደርገው የሞያ ድጋፍ ተፅዕኖ ስር የወደቀ ወይንም በይሉኝታ ስሜት የተቀነበበ ሊሆን ይችላል…ይሄንን ማንም በእርግጠኝነት ማወቅ አይችልም…በዚህም ምክንያት ከእሷ ጋር ደግሞ ያለው ግንኙነት እየሄደ ያለበት መንገድ ትክክል እንዳልሆነ ያውቃል፡፡ከሞያ ስነምግባር ውጭም እንደሆነ ያምናል፡፡ይሄ ጉዳይ ነው በጣም እያስጨነቀው ያለው፡፡ ከበፀሎት ጋር የፍቅር ስሜት በተሰማበት ቅፅበት ሁለት ምርጫ ነበረው፡፡አንድም በእሷ ቀጣሪነት ወላጆቾን ለማከም የተዋዋለውን የስራ ውል አፍርሶ ነፃ መውጣትና.. ከልሆነም ልቡን ገስፆ እና ፍቅሩን በውስጡ አክስሞ ስራው ላይ ብቻ አትኩሮ መቀጠል፡፡ቢያንስ ስራውን በተዋዋለው መሰረት ሙሉ በሙሉ አጠናቆ እስኪጨርስ ድረስ እንደዛ ነበር ማድረግ ያለበት፡፡ግን ይሄው ሁለቱንም ማድረግ አልቻለም፡፡ ‹‹ግን እኮ ይሄ በስራ አለም ቆይታዬ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈፀምኩት የሞያ ስነምግባር ጥሰት ነው››ሲል እራሱን ለማፅናናት ሞከረ…..፡፡ንግግሩ ግን እራሱንም ሊያሳምነው አልቻለም፡፡ ‹‹ስህተት የመጀመሪያም ሆነ የመጨረሻ ያው ስህተት ነው››የገዛ አእምሮ መልሶ የነገረው ነበር፡፡ ‹‹አሁን ወደኃላ መመለስ አልችልም…ይሄንን ጉዳይ ከዳር ላድርስና ..ከእሷ ጋር ያለኝ የፍቅር ግንኙነት የሚደርስበትን ከፍታ አይቼ ውጤታማ የሚሆን ከሆነ ምን አልባት ሞያውን በክብር ብለቅና ወደሌላ ዘርፍ ብሸጋገር እንኳን ያዋጣኛል››ሲል ለጊዜው የታየውን መፍትሄ አስቀመጠ…የገዛ አእምሮው ግን ወዲያው ነበር አፍራሽ የሆነ ሀሳብ የሰጠው‹‹ሰውዬ ምን ነካህ..?ይሄንን ሞያ ለቀህ…ነጋዴም ብትሆን …ወይም ደራሲ… ሁሉም ሞያ አይነቱ እና ተጋላጭነቱ በመጠኑ ይለያይ እንደሆን እንጂ የራሱ ህጋዊም ሆኑ ሞራላዊ የስነምግባር ገደቦች አሉበት…በተለይ ፍቅርን በተመለከተ ሁሉም ሞያ ይፈተናል…አስተማሪ ብትሆን ተማሪህ ላይ አይንህን መጣል የለብህም…ማናጀር ሆነህ ፀሀፊህን መጎነታተል ስህተት ነው፡፡ሞያህን ሳይሆን አመለካከትህን ነው መቀየር ያለብህ… ራስህን አታሞኝ፡፡››አለው…. ለጊዜው በዚህ ጉዳይ ላይ ከዚህ በላይ ማሰብ አልፈለገም….ጉዳዩን ለጊዜ አሳልፎ ሰጠና ብድርብሱን ተከናንቦ እራሱን ለእንቅልፉን አሳልፎ ሰጠ ....ወዲያው ነበር ያሸለበው…የሚገርመው ደግሞ አይኖቹ በተከደኑ ከሁለት ደቂቃ በኃላ ነበር በፀሎት ነጭ ቬሎ ለብሳ ጭንቅላቷ ላይ የሚያብረቀርቅ የወርቅ አክሊል አጥልቃ ግራና ቀኝ ጎኗ ላይ የበቀሉ ውብ ክንፏቾን እያማታች ከሰማዩ ላይ ሰንጥቃ መጥታ እቅፉ ውስጥ ስትገባ በህልሙ ያየው፡፡
///
በፀሎትና ለሊሴ ከወንጪ ከተመለሱ ሁለት ቀን ሆኗቸዋል፡፡መሽተዋል…አንድ ሰዓት ተኩል አካባቢ ነው…በፀሎት እና ፊራኦል ግቢው ውስጥ ካለ ግዙፍ የመንጎ ዛፍ ስር ጎን ለጎን ቁጭ ብለው እያወሩ ነው፡፡
‹‹እንዴት ነበር ወንጪ?››
‹‹ውይ ሲዊዘርላድ በለው፡፡››
‹‹እኔ ወንጪን እንጂ ሲዊዘርላንድን አላውቃትም፡፡››
‹‹አኔ ደግሞ አውቃታለዋ ለዛ ነው ያነፃፀርኩልህ..ደግሞ ዘመዶቻችን እንዴት ደግና ቀሽት መሰሉህ?፡፡››
‹‹የእኔም ዘመዶች እኮ ናቸው አውቃቸዋለው››
‹‹አይ ቢሆንም ..አንተ ምንአልባት ከልጅነትህ ጀምሮ ስለምታውቃቸው …ብዙም ጣእም ላይሰጥህ ይችላል..ማለት ሁለም ሰው እንደእነሱ አይነት ዘመድ ያለው ስለሚመስልህ ተራ ነገር አድርገህ ልትቆጥረው ትችላለህ….እንደእኔ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደዛ አይነት ዘመድ ሲኖርህ ግን በቃ ..ከአሁኑ እንዴት እንደናፈቁኝ ብታውቅ››
‹‹ገና በሁለት ቀን››
‹‹አዎ በሁለት ቀን››
‹‹አሁን ከእኛ ስትለይና ወደቤትሽ ስትሄጂ እንናፍቅሻለን ..?ማለት እኔ ናፍቅሻለሁ?››ለቀናት በውስጡ ሲያብሰለስለው የነበረውን ጥያቄ ጠየቃት፡፡
‹‹ምን ማለት ነው….?ወደየትኛው ቤቴ ነው የምሄደው?››
‹‹ወደቦሌው ቤትሽ››
‹‹ምን….ለሊሴ ነገረችህ››
‹‹እሷ ታውቃለች እንዴ?››
‹‹እሷ ካልነገረችሽ ታዲያ ማን ነገረህ?››
‹‹እራሴ ነኝ የደሰረስኩበት ..ወደ ወንጪ ከመሄዳችሁ በፊት ነው ያወቅኩት››
‹‹እኮ እንዴት ልታውቅ ቻልክ?››
‹‹ያው እንዳልኩሽ የእህቴን ልብ ከተቀበልሽ በኃላ በሩቅ ሆኜ ለረጅም ጊዜ ስከታተልሽ ነበር..ስለዚህ በደንብ አውቅሻለው…እዚህ ቤት ከመጣሽ ከሳምንት በኃላ ጀምሮ ከፍተኛ ጥርጣሬ አድሮብኝ ነበር..ከዛ ምን አደረኩ አንድ ቀን ስትተኚ ሻርፕሽን ሙሉ በሙሉ ከፊትሽ ላይ ገፍፌ ተመለከትኩሽ…እና ኦርጅናለዋ በፀሎት መሆንሽን አረጋገጥኩ፡፡
‹‹ትገርማለህ..ከዛ ፀጥ አልክ?››
‹‹ምን ላድርግ…ምንም ማለትና ምን ማድረግ እንዳለብኝ አላወቅኩም ነበር፡፡››
‹‹አሁንስ አወቅክ?››
‹‹አይ….አንቺ ንገርኝ እስኪ …ምን ልታደርጊ ነው…?እስከመቼ ነው ከወላጆችሽ ምትደበቂው?››
‹‹ወላጆቼን በቀደም አግኝቼቸዋለው..እዚህ መሆኔን ያውቃሉ››ብላ ያልጠበቀውን ዜና ነገረችው፡፡
‹‹ጥሩ..እሺ እነአባዬን እንዴት ልታደርጊ ነው….?እንደዋሸሻቸው ሲያውቅ በጣም ነው የሚያዝኑብሽ…በአንቺ ብቻ ሳይሆን እኛም አውቀን ከነሱ ደብቀን ዝም በማለታችን ምን እንደሚወጥን አላውቅም? በጣም ጨንቆኛል›ብሎ እውነተኛ ስሜቱን ነገራት፡፡
‹‹ይቅርታ ፊራኦል..እንደዚህ አይነት ነገር ውስጥ ስላስገባዋችሁ በጣም አዝናልው…ግን በዚህ ሁለት ሶስት ቀን ውስጥ እፈተዋለው…ማለት እናንተ ቀድማችሁ እንደምታውቁ ሳላሳውቅ እፈተዋለው››
‹‹እስኪ እናያለን…››
‹‹እኔ የእህትህን ልብ የተሸክምኩ በፀሎት መሆኔን እርግጠኛ ስትሆን ምን ተሰማህ?››
‹‹ግማሽ ሀዘን ግማሽ ደስታ››
‹‹አልገባኝም››
‹‹ለረጂም ጊዜ ላናግርሽና ቀርቤ ላወራሽ የምመኝሽ የእህቴን ከፊል አካል የተሸከምሽው በፀሎት የገዛ ቤቴ መጥተሸ ከእኔ ጋር አንድ መአድ እየቆረሽ መሆንሽን ሳውቅ ፍጽም ድስታ ነው የተሰማኝ…በሌላ ጎኑ ደግሞ ያችኛዋን በፀሎት አፍቅሬት ስለነበር….ሌላ በፀሎት እንዳልሆንሽ ሳውቅ ቅር ብሎኛል››
‹‹ከመቀመጫዋ ተነሳችና እላዩ ላይ ተጠምጥማ ጉንጩን እየሳመችው‹‹….የእኔ ወንድም
(አቃቂ እና ቦሌ)
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ድክምክም ብሎታል፡፡ግን ደግሞ አልጋው ላይ ተኝቷ በሀሳብ እየተንገላታ ነው፡፡ ሰለሞን በሁለት በኩል ስለት ባለው ሰይፍ የሚጫወት ህፃን አይነት ሰው እንደሆነ እየተሰማው ነው፡፡ሞያውን በተመለከተ ለሶስት አመት በከፍተኛ የፕሮፌሽናል ደረጃ በምድረ-አሜሪካ ሲሰራ አንድም ጊዜ እንደዚህ አይነት ክፍተት ተከስቶበት አያውቅም..በዛም በራሱ ሲመካና ሲኮራ ኖሮ ነበር፡፡አሁን ግን ወደሀገሩ ተመልሶ ባጋጠሙት የመጀመሪያ ደንበኞቹ ከፍተኛ የሚባል ሽንቁር ተከስቶበታል፡፡አንድ ባለሞያ የሞያውን ስነምግባር አክብሮ ስራውን መስራት የሚገደደው ለደንበኞች ደህንነትንና ጥቅም ሲባል ብቻ አይደለም…ለራሱ ለሞያው ክብርና ተቀባይነትም እያንዳንዱ ባለሞያ የስራ-አፈፃፀም ሁኔታ ትልቅ ድርሻ አለው፡፡በሙስናና በጥቅማጥቅም የሚታለሉ ዳኞችና አቃቢ-ህጎች በሞሉበት ሀገር ፍርድቤት ሊከበርና ሊታመን አይችልም፡፡ሌላውም ሞያ እንደዛው ነው፡፡ ይህን ስራ ከጀመረ ያጋጠመችው ትልቋ ደንበኛው በፀሎት ነች፡፡እርግጥ ቀጥታ ደንበኛው እሷ ሳትሆን ወላጆቾ ናቸው፡፡ከእነሱ ጋር እየሰራ ያለውን ስራ የሞያው ስነምግባር በሚፈቅደው መንገድ ጥርትና ጥልል አድርጎ እየሰራ ነው፡፡ቢሆንም ቀጥታ ቀጣሪው ልጃቸው በፀሎት ነች፡፡እሷ ፍላጎቱን ተረድታ አፈቅርሀለው ብትለው እንኳን ፍቅሯ እሱ ለወላጆቾ በሚያደርገው የሞያ ድጋፍ ተፅዕኖ ስር የወደቀ ወይንም በይሉኝታ ስሜት የተቀነበበ ሊሆን ይችላል…ይሄንን ማንም በእርግጠኝነት ማወቅ አይችልም…በዚህም ምክንያት ከእሷ ጋር ደግሞ ያለው ግንኙነት እየሄደ ያለበት መንገድ ትክክል እንዳልሆነ ያውቃል፡፡ከሞያ ስነምግባር ውጭም እንደሆነ ያምናል፡፡ይሄ ጉዳይ ነው በጣም እያስጨነቀው ያለው፡፡ ከበፀሎት ጋር የፍቅር ስሜት በተሰማበት ቅፅበት ሁለት ምርጫ ነበረው፡፡አንድም በእሷ ቀጣሪነት ወላጆቾን ለማከም የተዋዋለውን የስራ ውል አፍርሶ ነፃ መውጣትና.. ከልሆነም ልቡን ገስፆ እና ፍቅሩን በውስጡ አክስሞ ስራው ላይ ብቻ አትኩሮ መቀጠል፡፡ቢያንስ ስራውን በተዋዋለው መሰረት ሙሉ በሙሉ አጠናቆ እስኪጨርስ ድረስ እንደዛ ነበር ማድረግ ያለበት፡፡ግን ይሄው ሁለቱንም ማድረግ አልቻለም፡፡ ‹‹ግን እኮ ይሄ በስራ አለም ቆይታዬ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈፀምኩት የሞያ ስነምግባር ጥሰት ነው››ሲል እራሱን ለማፅናናት ሞከረ…..፡፡ንግግሩ ግን እራሱንም ሊያሳምነው አልቻለም፡፡ ‹‹ስህተት የመጀመሪያም ሆነ የመጨረሻ ያው ስህተት ነው››የገዛ አእምሮ መልሶ የነገረው ነበር፡፡ ‹‹አሁን ወደኃላ መመለስ አልችልም…ይሄንን ጉዳይ ከዳር ላድርስና ..ከእሷ ጋር ያለኝ የፍቅር ግንኙነት የሚደርስበትን ከፍታ አይቼ ውጤታማ የሚሆን ከሆነ ምን አልባት ሞያውን በክብር ብለቅና ወደሌላ ዘርፍ ብሸጋገር እንኳን ያዋጣኛል››ሲል ለጊዜው የታየውን መፍትሄ አስቀመጠ…የገዛ አእምሮው ግን ወዲያው ነበር አፍራሽ የሆነ ሀሳብ የሰጠው‹‹ሰውዬ ምን ነካህ..?ይሄንን ሞያ ለቀህ…ነጋዴም ብትሆን …ወይም ደራሲ… ሁሉም ሞያ አይነቱ እና ተጋላጭነቱ በመጠኑ ይለያይ እንደሆን እንጂ የራሱ ህጋዊም ሆኑ ሞራላዊ የስነምግባር ገደቦች አሉበት…በተለይ ፍቅርን በተመለከተ ሁሉም ሞያ ይፈተናል…አስተማሪ ብትሆን ተማሪህ ላይ አይንህን መጣል የለብህም…ማናጀር ሆነህ ፀሀፊህን መጎነታተል ስህተት ነው፡፡ሞያህን ሳይሆን አመለካከትህን ነው መቀየር ያለብህ… ራስህን አታሞኝ፡፡››አለው…. ለጊዜው በዚህ ጉዳይ ላይ ከዚህ በላይ ማሰብ አልፈለገም….ጉዳዩን ለጊዜ አሳልፎ ሰጠና ብድርብሱን ተከናንቦ እራሱን ለእንቅልፉን አሳልፎ ሰጠ ....ወዲያው ነበር ያሸለበው…የሚገርመው ደግሞ አይኖቹ በተከደኑ ከሁለት ደቂቃ በኃላ ነበር በፀሎት ነጭ ቬሎ ለብሳ ጭንቅላቷ ላይ የሚያብረቀርቅ የወርቅ አክሊል አጥልቃ ግራና ቀኝ ጎኗ ላይ የበቀሉ ውብ ክንፏቾን እያማታች ከሰማዩ ላይ ሰንጥቃ መጥታ እቅፉ ውስጥ ስትገባ በህልሙ ያየው፡፡
///
በፀሎትና ለሊሴ ከወንጪ ከተመለሱ ሁለት ቀን ሆኗቸዋል፡፡መሽተዋል…አንድ ሰዓት ተኩል አካባቢ ነው…በፀሎት እና ፊራኦል ግቢው ውስጥ ካለ ግዙፍ የመንጎ ዛፍ ስር ጎን ለጎን ቁጭ ብለው እያወሩ ነው፡፡
‹‹እንዴት ነበር ወንጪ?››
‹‹ውይ ሲዊዘርላድ በለው፡፡››
‹‹እኔ ወንጪን እንጂ ሲዊዘርላንድን አላውቃትም፡፡››
‹‹አኔ ደግሞ አውቃታለዋ ለዛ ነው ያነፃፀርኩልህ..ደግሞ ዘመዶቻችን እንዴት ደግና ቀሽት መሰሉህ?፡፡››
‹‹የእኔም ዘመዶች እኮ ናቸው አውቃቸዋለው››
‹‹አይ ቢሆንም ..አንተ ምንአልባት ከልጅነትህ ጀምሮ ስለምታውቃቸው …ብዙም ጣእም ላይሰጥህ ይችላል..ማለት ሁለም ሰው እንደእነሱ አይነት ዘመድ ያለው ስለሚመስልህ ተራ ነገር አድርገህ ልትቆጥረው ትችላለህ….እንደእኔ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደዛ አይነት ዘመድ ሲኖርህ ግን በቃ ..ከአሁኑ እንዴት እንደናፈቁኝ ብታውቅ››
‹‹ገና በሁለት ቀን››
‹‹አዎ በሁለት ቀን››
‹‹አሁን ከእኛ ስትለይና ወደቤትሽ ስትሄጂ እንናፍቅሻለን ..?ማለት እኔ ናፍቅሻለሁ?››ለቀናት በውስጡ ሲያብሰለስለው የነበረውን ጥያቄ ጠየቃት፡፡
‹‹ምን ማለት ነው….?ወደየትኛው ቤቴ ነው የምሄደው?››
‹‹ወደቦሌው ቤትሽ››
‹‹ምን….ለሊሴ ነገረችህ››
‹‹እሷ ታውቃለች እንዴ?››
‹‹እሷ ካልነገረችሽ ታዲያ ማን ነገረህ?››
‹‹እራሴ ነኝ የደሰረስኩበት ..ወደ ወንጪ ከመሄዳችሁ በፊት ነው ያወቅኩት››
‹‹እኮ እንዴት ልታውቅ ቻልክ?››
‹‹ያው እንዳልኩሽ የእህቴን ልብ ከተቀበልሽ በኃላ በሩቅ ሆኜ ለረጅም ጊዜ ስከታተልሽ ነበር..ስለዚህ በደንብ አውቅሻለው…እዚህ ቤት ከመጣሽ ከሳምንት በኃላ ጀምሮ ከፍተኛ ጥርጣሬ አድሮብኝ ነበር..ከዛ ምን አደረኩ አንድ ቀን ስትተኚ ሻርፕሽን ሙሉ በሙሉ ከፊትሽ ላይ ገፍፌ ተመለከትኩሽ…እና ኦርጅናለዋ በፀሎት መሆንሽን አረጋገጥኩ፡፡
‹‹ትገርማለህ..ከዛ ፀጥ አልክ?››
‹‹ምን ላድርግ…ምንም ማለትና ምን ማድረግ እንዳለብኝ አላወቅኩም ነበር፡፡››
‹‹አሁንስ አወቅክ?››
‹‹አይ….አንቺ ንገርኝ እስኪ …ምን ልታደርጊ ነው…?እስከመቼ ነው ከወላጆችሽ ምትደበቂው?››
‹‹ወላጆቼን በቀደም አግኝቼቸዋለው..እዚህ መሆኔን ያውቃሉ››ብላ ያልጠበቀውን ዜና ነገረችው፡፡
‹‹ጥሩ..እሺ እነአባዬን እንዴት ልታደርጊ ነው….?እንደዋሸሻቸው ሲያውቅ በጣም ነው የሚያዝኑብሽ…በአንቺ ብቻ ሳይሆን እኛም አውቀን ከነሱ ደብቀን ዝም በማለታችን ምን እንደሚወጥን አላውቅም? በጣም ጨንቆኛል›ብሎ እውነተኛ ስሜቱን ነገራት፡፡
‹‹ይቅርታ ፊራኦል..እንደዚህ አይነት ነገር ውስጥ ስላስገባዋችሁ በጣም አዝናልው…ግን በዚህ ሁለት ሶስት ቀን ውስጥ እፈተዋለው…ማለት እናንተ ቀድማችሁ እንደምታውቁ ሳላሳውቅ እፈተዋለው››
‹‹እስኪ እናያለን…››
‹‹እኔ የእህትህን ልብ የተሸክምኩ በፀሎት መሆኔን እርግጠኛ ስትሆን ምን ተሰማህ?››
‹‹ግማሽ ሀዘን ግማሽ ደስታ››
‹‹አልገባኝም››
‹‹ለረጂም ጊዜ ላናግርሽና ቀርቤ ላወራሽ የምመኝሽ የእህቴን ከፊል አካል የተሸከምሽው በፀሎት የገዛ ቤቴ መጥተሸ ከእኔ ጋር አንድ መአድ እየቆረሽ መሆንሽን ሳውቅ ፍጽም ድስታ ነው የተሰማኝ…በሌላ ጎኑ ደግሞ ያችኛዋን በፀሎት አፍቅሬት ስለነበር….ሌላ በፀሎት እንዳልሆንሽ ሳውቅ ቅር ብሎኛል››
‹‹ከመቀመጫዋ ተነሳችና እላዩ ላይ ተጠምጥማ ጉንጩን እየሳመችው‹‹….የእኔ ወንድም
#የድንግሊቷ_አፍቃሪዎች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
================
አለማየሁ በቀጠሮው መሰረት ከአላዛርና አለማየሁ ጋር ከተገናኘ በኋላ ‹‹እሺ ባላና ሚስቶች ለምንድነው የፈለጋችሁኝ….?ለጥሩ ነገር እንደሚሆን እገምታለሁ፡፡››ሲል የመጀመሪያ ጥያቄ ጠየቃቸው፡፡
ሁለቱም እርስ በርስ ተያዩ..አንተ ንገረው አንቺ ንገሪው እየተባባሉ የሚገባበዙ ይመስላል አላዛር ቅድሚያውን ወሰደ‹‹በሚቀጥለው ሳምንት ሁሴን እንደሚመጣ ታውቃለህ አይደል?››
ያልጠበቀውን ርዕስ ነው ያነሳበት‹‹ትክክለኛውን ቀን አላውቅም እንጂ እንደሚመጣ አዎ በቀደም ደውሎልኝ ነበር..››
‹‹ጥሩ እንግዲህ ..እናቱም አባቱም እንደሞቱ ታውቃለህ…..እዚህ ሌላ ዘመድ የለውም ..ከፋም ለማም የልጅነት ጓደኞቹና የቅርቡ ሰዎች እኛ ሶስታችን ነን››
በውስጡ ‹‹የራሷ አሮባት የሰው ታማስላለች›› የሚለውን ተረት እየተረተበት ‹‹አዎ ትክክል››ሲል መለሰ፡፡
‹‹እና እንዴት እንቀበለው የሚለውን ለመነጋገር ነው፡፡››
‹‹በጣም ጥሩ ሀሳብ ነው፡፡ይሄ የድሮ ጓደኛችንን የመቀበል ጉዳይ ብቻ ሳይሆን እኛም መልሰን ለአመታት ተራርቀን ከቆየንበት ለመቀራረብና መልሰን ጓደኝነታችንን ለማደስ ያግዘናል….››አለ
…እንደዛ ሲል በውስጡ ያለው ከአላዛር ወይም ከሁሴን ጋር ይበልጥ ተቀራርቦ ድሮ ጓፈደኛነታችው የመመለስ ጉጉት ኖሮት አይደለም..ከዛ ይልቅ ስለሰሎሜ በውስጡ እያሰበ ነው፡፡
‹‹በጥሩ ሁኔታ ብንቀበለው ደስ ይለኛል…እኔ የሚጠበቅብኝን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ ነኝ….ዝግጅቱን እኔ ቤት ማድረግ እንችላለን››አለ…
‹‹አይ ከአንተ ቤት የእኛ ቤት ይሻል ይመስለኛል….ማለት የወንደላጤን ቤት ማድመቅ ይከብዳል›› ሰሎሜ ነች ተናጋሪዋ፡
‹‹እሺ እንዳልሽ…እኔ ቤት ብንቀበለው በዛውም የራሱን ነገር እስከሚያመቻች አኔ ጋር መቆየት ይችላል ብዬ ነው፡፡››
‹‹እኛ ጋርስ ለመቆየት ምን ይከለክለዋል…?እቤታችን እንደሆነ እንኳን እሱንና አንተም ብትጨመር በቂ ክፍት ክፍሎች አሉን ….እንደምታውቀው እዛ አፓርታማ ቤት ውስጥ እኔና እሱ ብቻ ነን....ልጅ የለን ምን የለን››
በሰሎሜ ንግግር አላዛር ሽምቅቅ አለ..ሆነ ብላ አስባበት የተናገረችው እንደሆነ ያውቃል….ግን ዋጥ አድርጎ በትዕግስት ከማሳለፍ ውጭ ምርጫ እንደሌለው ያውቃል፣ያደረገውም እንደዛ ነው፡፡
አለማየሁ‹‹በቃ እሺ እጅ ሰጥቼለው››ሲል በሀሳባቸው ተስማማ፡፡
‹‹ጥሩ በቃ …እንደዛ ከሆነ በፊታችን እሁድ ቤት ናና ስለዝርዝሩ እንነጋገርበታለን››
‹‹ጥሩ..እንደውም በሰበቡ ቤታችሁን አያለሁ››
‹‹አዎ ››
ከዛ በኃላ ብዙም ያወሩት ነገረ የለም ፡፡ተሰነባብተው ተለያዩ፡፡
‹‹አላዛር እና ሰሎሜ በአንድ መኪና ገብተው ወደቤታቸው እየተጓዙ ወሬ ጀመሩ‹‹ግን እርግጠኛ ነህ..?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹ምኑን?››
‹‹ማለቴ የሁሴን እኛ ቤት ማረፍ….ነው ወይስ አንድ ሁለት ቀን እኛ ጋር ካደረ በኃላ ሌላ ማረፊያ ፈልግ ልንለወው ነው፡?››
‹‹ለምን …አንቺን ካልደበረሽ እቤታቸን ሰፊ ነው…ሁሴን የማናውቀው ሰው አይደለም ….ለሁለታችንም ቅርብ የሆነ ሰው ነው፡፡››
‹‹ገባኝ….በደንብ አስበህበታል ወይ ለማለት ነው…?.እኔማ ደስ ይለኛል..ግን እወቅ እንደነገረኝ ከሆነ እስከሶስት ወር ሊቆይ ይችላል፡፡››
‹‹ችግር የለውም..ታውቂያለሽ የሆነ የእኛ የምንለው ሰው አብሮን እንዲኖር እንዴት እፈልግ እንደነበረ…እህቶቼም ሁለቱም ስላገቡ ወደቤታችን ላመጣቸው አልቻልኩም…የአንቺም እናት አሻፈረኝ ብላለች..እስኪ አሁን በጓደኛችን እንሞክረው፡፡››
‹‹እማዬ እኮ ከእናንተ ጋር አልኖርም አላለችም..እሷ ያለችው ልጅ ስትወልዱ እሱን ለማሳደግ መጣለሁ…አሁን ግን መጥቼ የእናንተ ሞግዚት መሆን አልፈልግም ነው ያለችው››።
‹‹እና በሞግዚት ኑሪ እንጂ ሞግዚት ሁኚን መች አልናት?››
‹‹ተወው አሁን… ለምን የማይሆን ጭቅጭቅ ውስጥ እንገባለን…ቁርጥ አድርጋ አቋሟን አሳውቃለች…መውለድ ስንችል ትመጣለች››
‹‹ይሁን እሺ… ለማንኛውም ስለሁሴን አትጨነቂ… ሁኔታዎች ካልተመቹት እኮ እራሱ አማራጭ ይፈልጋል፡፡››በማለት የተጣመመውን ርእስ እንደምንም ብሎ አቃናው፡፡
‹‹ጥሩ..ለእኛም ከብቸኝነት ጋር ከመታገል በተወሰነ መንገድ ይታደገናል…›› ስትል መለሰች፡፡
‹‹እኔም እሱን አስቤ ነው ››አላት..ግን ሁለቱም ስጋታቸው ሌላ እንደሆነ ግልፅ ነው…ሁሴን ልክ እንደአላዛር ሁሉ የሰሎሜ የልጅነት አፍቃሪዎ እንደሆነ ሁለቱም ያውቃሉ፡፡ለሁለቱም እኩል ጓደኛቸው ቢሆንም ለእሷ ግን በተለየ መልኩ አፍቃሪዋም ጭምር ነው…እና አሁን አንድ ቤት እሱን ጎትቶ ማምጣት ለዛውም አሁን ባልና ሚስቶቹ ባሉበት ሁኔታ ላይ አደጋ እንዳለውና የልታሰበ መዘዝ ሊያመጣ እንደሚችል…ለሁለቱም ግልፅ ነው….እና ሰሎሜ ደጋግማ ስለውሳኔው እርግጠኝነት እየጠየቀችው ያለው..ነገ አንድ ነገር ቢከሰት ኃላፊነቱን እንዲወስድ በማሰብ ነው፡፡
እሷ ያላወቀችው ግን የእሱን እቅድ ነው…እሱ ሁሴን ወደቤት እንዲመጣ ሲወስን መዘዙንም አስቦና አስልቶ ነው፡፡ምን አልባት የጀመረው የህክምና ጉዳይ ባይሳካለት ሊያደርግ የሚችለውን እቅድ አስቦና አስልቶ ጨርሷል..በቃ እራስ ወዳድ መሆን እንደሌለበት ገብቶታል…እየወደደም ቢሆን ከሰሎሜን ህይወት ሾልኳ መውጣት እንዳለበት ወስኗል.. ከህይወቱ ሲሸኛት ግን በተሰበረ ልብ ሆና ስነልቦናዋ ተጎድቶ መሆን እንደሌለበትም ነው የሚያምነው..ለእሱ መሆን ካልቻለች ከሁለት የልጅነት ጓደኞቾና ከልብ ከሚያፈቅሯት መቼም ቢሆን ሊጎዶት ለማይችሉት ለአንዱ ሊያስረክባት ነው ያሰበው….ለዛም ጥሪጊያ መንገድ ለመፍጠር ሁሴን በእንግድነት እሱ ቤት ማረፍ እንዳለበት ማድረግ እንዳለበት ተሰምቶታል፡፡፡ያንን ካደረገ ደግሞ አለማየሁም በተደጋጋሚ ወደእሱ ቤት ለመመላለስና ከሰሎሜ ጋር በተደጋጋሚ ጊዜ የመገናኘት እድል ይኖራዋል፣በሂደት ከሁለት አንዱ ከእሷ ጋር በተሻለ መቀራረብ ይፈጥሩና ልቧን ማግኘት ይችሉ ይሆናል….ከዛ አንዱ ያገኛታል ማለት ነው፡፡ከዛ እሱ ሀዘኑን ለብቻው ያዝናል..ማጣቱን በማስታመም ቀሪ የብቸኝነት ዘመኑን ይገፋል…….፡፡እግዚያብሄር ቀንቶት ከተፈወሰ ደግሞ በቃ ምን ይፈልጋል…እና አሁን እያደረገ ያለው ቅድመ ዝግጅት ነው፡፡ይሄ ነው ሰሎሜን ያልገባት፡፡
ይሄ ጉዳይ ደግሞ ከሰሎሜ ይልቅ አለማየሁን ነው ፍፅም ግራ ያጋባው‹‹ሰውዬው ምን እየሰራ ነው?››የሚለው ሀሳብ በውስጡ መጉላላት የጀመረው ገና ከእነሱ እንደተለየ ነው፡፡እና ደግሞ አልተመቸውም….በመጀመሪያ ደረጃ በዚህ ወሳኝ ወቅት የሁሴን ወደሀገር ቤት ተመልሶ መምጣት ደስ አላሰኘውም ነበር፡፡፡በእሱ እምነት አላዛር ካልተሳካለት ቀጥታ ሰሎሜን የእሱ የማድረጉን ትግል በብቸኝነት ለመወጣት ነበር ዕቅዱም ምኞቱም..ሁሴን ደውሎ እንደሚመጣ ከነገረው በኋላ ግን ሌላ ተፋላሚ እየመጣበት እንደሆነ ነው ወዲያው የገባው…እንደውም መምጣቱ እራሱ ያጋጣሚ ነገር ሳይሆን ሆነ ብሎ የታሰበበት እንደሆነ ነው የሚጠረጥረው…ሰሎሜ አላዛርን ከማግባቷ በፊት ከእሱ ጋር ለረጅም ጊዜ እንደምትደዋወል ነግራዋለች..በእሷ እና በባሏ መካከል ያለውን ቦንብ ሚስጥር ለእሱ በተገናኙበት በመጀመሪያው ቀን ከነገረችው…ለረጅም ጊዜ ስትደዋወል ለነበረው ለዛውም ከባህር ማዶ ላለው ሁሴን ላትነግረው የምትችልበት ምክንያት ምንም እየታየው አይደለም…እንደጠረጠረው ነግራው ከሆነ ደግሞ በተለይ የሰሞኑን ግር ግር አብራርታለት ከሆነ የሆነ ምክንያት ፈጥሮ አጋጣሚውን ለመጠቀም እንደመጣ ነው የሚያምነው..እና ከእሱ ጋር
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
================
አለማየሁ በቀጠሮው መሰረት ከአላዛርና አለማየሁ ጋር ከተገናኘ በኋላ ‹‹እሺ ባላና ሚስቶች ለምንድነው የፈለጋችሁኝ….?ለጥሩ ነገር እንደሚሆን እገምታለሁ፡፡››ሲል የመጀመሪያ ጥያቄ ጠየቃቸው፡፡
ሁለቱም እርስ በርስ ተያዩ..አንተ ንገረው አንቺ ንገሪው እየተባባሉ የሚገባበዙ ይመስላል አላዛር ቅድሚያውን ወሰደ‹‹በሚቀጥለው ሳምንት ሁሴን እንደሚመጣ ታውቃለህ አይደል?››
ያልጠበቀውን ርዕስ ነው ያነሳበት‹‹ትክክለኛውን ቀን አላውቅም እንጂ እንደሚመጣ አዎ በቀደም ደውሎልኝ ነበር..››
‹‹ጥሩ እንግዲህ ..እናቱም አባቱም እንደሞቱ ታውቃለህ…..እዚህ ሌላ ዘመድ የለውም ..ከፋም ለማም የልጅነት ጓደኞቹና የቅርቡ ሰዎች እኛ ሶስታችን ነን››
በውስጡ ‹‹የራሷ አሮባት የሰው ታማስላለች›› የሚለውን ተረት እየተረተበት ‹‹አዎ ትክክል››ሲል መለሰ፡፡
‹‹እና እንዴት እንቀበለው የሚለውን ለመነጋገር ነው፡፡››
‹‹በጣም ጥሩ ሀሳብ ነው፡፡ይሄ የድሮ ጓደኛችንን የመቀበል ጉዳይ ብቻ ሳይሆን እኛም መልሰን ለአመታት ተራርቀን ከቆየንበት ለመቀራረብና መልሰን ጓደኝነታችንን ለማደስ ያግዘናል….››አለ
…እንደዛ ሲል በውስጡ ያለው ከአላዛር ወይም ከሁሴን ጋር ይበልጥ ተቀራርቦ ድሮ ጓፈደኛነታችው የመመለስ ጉጉት ኖሮት አይደለም..ከዛ ይልቅ ስለሰሎሜ በውስጡ እያሰበ ነው፡፡
‹‹በጥሩ ሁኔታ ብንቀበለው ደስ ይለኛል…እኔ የሚጠበቅብኝን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ ነኝ….ዝግጅቱን እኔ ቤት ማድረግ እንችላለን››አለ…
‹‹አይ ከአንተ ቤት የእኛ ቤት ይሻል ይመስለኛል….ማለት የወንደላጤን ቤት ማድመቅ ይከብዳል›› ሰሎሜ ነች ተናጋሪዋ፡
‹‹እሺ እንዳልሽ…እኔ ቤት ብንቀበለው በዛውም የራሱን ነገር እስከሚያመቻች አኔ ጋር መቆየት ይችላል ብዬ ነው፡፡››
‹‹እኛ ጋርስ ለመቆየት ምን ይከለክለዋል…?እቤታችን እንደሆነ እንኳን እሱንና አንተም ብትጨመር በቂ ክፍት ክፍሎች አሉን ….እንደምታውቀው እዛ አፓርታማ ቤት ውስጥ እኔና እሱ ብቻ ነን....ልጅ የለን ምን የለን››
በሰሎሜ ንግግር አላዛር ሽምቅቅ አለ..ሆነ ብላ አስባበት የተናገረችው እንደሆነ ያውቃል….ግን ዋጥ አድርጎ በትዕግስት ከማሳለፍ ውጭ ምርጫ እንደሌለው ያውቃል፣ያደረገውም እንደዛ ነው፡፡
አለማየሁ‹‹በቃ እሺ እጅ ሰጥቼለው››ሲል በሀሳባቸው ተስማማ፡፡
‹‹ጥሩ በቃ …እንደዛ ከሆነ በፊታችን እሁድ ቤት ናና ስለዝርዝሩ እንነጋገርበታለን››
‹‹ጥሩ..እንደውም በሰበቡ ቤታችሁን አያለሁ››
‹‹አዎ ››
ከዛ በኃላ ብዙም ያወሩት ነገረ የለም ፡፡ተሰነባብተው ተለያዩ፡፡
‹‹አላዛር እና ሰሎሜ በአንድ መኪና ገብተው ወደቤታቸው እየተጓዙ ወሬ ጀመሩ‹‹ግን እርግጠኛ ነህ..?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹ምኑን?››
‹‹ማለቴ የሁሴን እኛ ቤት ማረፍ….ነው ወይስ አንድ ሁለት ቀን እኛ ጋር ካደረ በኃላ ሌላ ማረፊያ ፈልግ ልንለወው ነው፡?››
‹‹ለምን …አንቺን ካልደበረሽ እቤታቸን ሰፊ ነው…ሁሴን የማናውቀው ሰው አይደለም ….ለሁለታችንም ቅርብ የሆነ ሰው ነው፡፡››
‹‹ገባኝ….በደንብ አስበህበታል ወይ ለማለት ነው…?.እኔማ ደስ ይለኛል..ግን እወቅ እንደነገረኝ ከሆነ እስከሶስት ወር ሊቆይ ይችላል፡፡››
‹‹ችግር የለውም..ታውቂያለሽ የሆነ የእኛ የምንለው ሰው አብሮን እንዲኖር እንዴት እፈልግ እንደነበረ…እህቶቼም ሁለቱም ስላገቡ ወደቤታችን ላመጣቸው አልቻልኩም…የአንቺም እናት አሻፈረኝ ብላለች..እስኪ አሁን በጓደኛችን እንሞክረው፡፡››
‹‹እማዬ እኮ ከእናንተ ጋር አልኖርም አላለችም..እሷ ያለችው ልጅ ስትወልዱ እሱን ለማሳደግ መጣለሁ…አሁን ግን መጥቼ የእናንተ ሞግዚት መሆን አልፈልግም ነው ያለችው››።
‹‹እና በሞግዚት ኑሪ እንጂ ሞግዚት ሁኚን መች አልናት?››
‹‹ተወው አሁን… ለምን የማይሆን ጭቅጭቅ ውስጥ እንገባለን…ቁርጥ አድርጋ አቋሟን አሳውቃለች…መውለድ ስንችል ትመጣለች››
‹‹ይሁን እሺ… ለማንኛውም ስለሁሴን አትጨነቂ… ሁኔታዎች ካልተመቹት እኮ እራሱ አማራጭ ይፈልጋል፡፡››በማለት የተጣመመውን ርእስ እንደምንም ብሎ አቃናው፡፡
‹‹ጥሩ..ለእኛም ከብቸኝነት ጋር ከመታገል በተወሰነ መንገድ ይታደገናል…›› ስትል መለሰች፡፡
‹‹እኔም እሱን አስቤ ነው ››አላት..ግን ሁለቱም ስጋታቸው ሌላ እንደሆነ ግልፅ ነው…ሁሴን ልክ እንደአላዛር ሁሉ የሰሎሜ የልጅነት አፍቃሪዎ እንደሆነ ሁለቱም ያውቃሉ፡፡ለሁለቱም እኩል ጓደኛቸው ቢሆንም ለእሷ ግን በተለየ መልኩ አፍቃሪዋም ጭምር ነው…እና አሁን አንድ ቤት እሱን ጎትቶ ማምጣት ለዛውም አሁን ባልና ሚስቶቹ ባሉበት ሁኔታ ላይ አደጋ እንዳለውና የልታሰበ መዘዝ ሊያመጣ እንደሚችል…ለሁለቱም ግልፅ ነው….እና ሰሎሜ ደጋግማ ስለውሳኔው እርግጠኝነት እየጠየቀችው ያለው..ነገ አንድ ነገር ቢከሰት ኃላፊነቱን እንዲወስድ በማሰብ ነው፡፡
እሷ ያላወቀችው ግን የእሱን እቅድ ነው…እሱ ሁሴን ወደቤት እንዲመጣ ሲወስን መዘዙንም አስቦና አስልቶ ነው፡፡ምን አልባት የጀመረው የህክምና ጉዳይ ባይሳካለት ሊያደርግ የሚችለውን እቅድ አስቦና አስልቶ ጨርሷል..በቃ እራስ ወዳድ መሆን እንደሌለበት ገብቶታል…እየወደደም ቢሆን ከሰሎሜን ህይወት ሾልኳ መውጣት እንዳለበት ወስኗል.. ከህይወቱ ሲሸኛት ግን በተሰበረ ልብ ሆና ስነልቦናዋ ተጎድቶ መሆን እንደሌለበትም ነው የሚያምነው..ለእሱ መሆን ካልቻለች ከሁለት የልጅነት ጓደኞቾና ከልብ ከሚያፈቅሯት መቼም ቢሆን ሊጎዶት ለማይችሉት ለአንዱ ሊያስረክባት ነው ያሰበው….ለዛም ጥሪጊያ መንገድ ለመፍጠር ሁሴን በእንግድነት እሱ ቤት ማረፍ እንዳለበት ማድረግ እንዳለበት ተሰምቶታል፡፡፡ያንን ካደረገ ደግሞ አለማየሁም በተደጋጋሚ ወደእሱ ቤት ለመመላለስና ከሰሎሜ ጋር በተደጋጋሚ ጊዜ የመገናኘት እድል ይኖራዋል፣በሂደት ከሁለት አንዱ ከእሷ ጋር በተሻለ መቀራረብ ይፈጥሩና ልቧን ማግኘት ይችሉ ይሆናል….ከዛ አንዱ ያገኛታል ማለት ነው፡፡ከዛ እሱ ሀዘኑን ለብቻው ያዝናል..ማጣቱን በማስታመም ቀሪ የብቸኝነት ዘመኑን ይገፋል…….፡፡እግዚያብሄር ቀንቶት ከተፈወሰ ደግሞ በቃ ምን ይፈልጋል…እና አሁን እያደረገ ያለው ቅድመ ዝግጅት ነው፡፡ይሄ ነው ሰሎሜን ያልገባት፡፡
ይሄ ጉዳይ ደግሞ ከሰሎሜ ይልቅ አለማየሁን ነው ፍፅም ግራ ያጋባው‹‹ሰውዬው ምን እየሰራ ነው?››የሚለው ሀሳብ በውስጡ መጉላላት የጀመረው ገና ከእነሱ እንደተለየ ነው፡፡እና ደግሞ አልተመቸውም….በመጀመሪያ ደረጃ በዚህ ወሳኝ ወቅት የሁሴን ወደሀገር ቤት ተመልሶ መምጣት ደስ አላሰኘውም ነበር፡፡፡በእሱ እምነት አላዛር ካልተሳካለት ቀጥታ ሰሎሜን የእሱ የማድረጉን ትግል በብቸኝነት ለመወጣት ነበር ዕቅዱም ምኞቱም..ሁሴን ደውሎ እንደሚመጣ ከነገረው በኋላ ግን ሌላ ተፋላሚ እየመጣበት እንደሆነ ነው ወዲያው የገባው…እንደውም መምጣቱ እራሱ ያጋጣሚ ነገር ሳይሆን ሆነ ብሎ የታሰበበት እንደሆነ ነው የሚጠረጥረው…ሰሎሜ አላዛርን ከማግባቷ በፊት ከእሱ ጋር ለረጅም ጊዜ እንደምትደዋወል ነግራዋለች..በእሷ እና በባሏ መካከል ያለውን ቦንብ ሚስጥር ለእሱ በተገናኙበት በመጀመሪያው ቀን ከነገረችው…ለረጅም ጊዜ ስትደዋወል ለነበረው ለዛውም ከባህር ማዶ ላለው ሁሴን ላትነግረው የምትችልበት ምክንያት ምንም እየታየው አይደለም…እንደጠረጠረው ነግራው ከሆነ ደግሞ በተለይ የሰሞኑን ግር ግር አብራርታለት ከሆነ የሆነ ምክንያት ፈጥሮ አጋጣሚውን ለመጠቀም እንደመጣ ነው የሚያምነው..እና ከእሱ ጋር