አትሮኖስ
280K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
459 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ሰመመን


#ክፍል_አርባ_አራት


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

....ለጥያቄዋ መልስ በመጠበቅ ዐይነት ሦስቱንም ተመለከተቸቻው ፡ ዐይኖቿ አንድ ቦታ እይረጐም በነጭ ቆዳዋ
ላይ ሰማያዊ መሳይ ሥራሥሮቿ ዐልፎ ዐልፎ ይታያሉ ።ገጽታዋ ላይ ፍቅርና ትሕትና ይነበባል ።

ዮናታንና እስክንድር ቡና ሲመርጡ እቤል ሻይ አለ ።ሚስታቸው ወደ ጓዳ ከመሔዷ በፊት ዮናታን ክንዷን ይዘው እጅዋ ላይ ሳም እያረጓት ። ለመልካም መስተንግዶዋ
ምስጋናቸውን የሚገልጹበት መንገድ ነበር

እስክንድር ዐይኑን ማመን አቃተው ወይም ያየው ነገር ሕልም መሰለው ። እውነት ፍቅር ይሆን ? አለ በልቡ ።የትዳር ዕድሜአቸውን ለማወቅ ጓጓ አፍላ ፍቅረኞች ካልሆኑ በስተቀር ተጋብተው በቆዩ ሰዎች መሐል አይቶ የማያውቀውን ሁኔታ ማየቱ ነው ያስደነቀው ያውም በእንግዳ ፊት !

“ ሊብሊንግ ሚስቴም እናቴም ናት ። የሕይወት ጣእም የሚታወቀኝ እሷን አጠገቤ ሳገኛት ነው አሉ ዮናታን ፥
ሚስታቸው ወደ ጓዳ ከገባች በኋላ ። “ ሰውን ማስደሰት መቻል ቀላል ነገር አይደለም ። ሊብሊንግ ይህን ችሎታ በተፈጥሮዋ ታድላዋለች ። ሁል ጊዜ ደስተኛ ነች እንደሚገባኝ ፡ ደስታዋን የምታገኘው ሰዎችን በማስደሰት ነው ።
አቤል ሁኔታዎች እስኪመቻቹለት ከእኛ ጋር እንዲኖር ሐሳቡን ቀድማ ያቀረበችልኝ እሷ ናት ።

አቤል በጥያቄ መልክ ዐይኑን እቁለጨለጨ ።

ከአሁን በፊት የት ታውቀኛለች ?ብሎ ነበር ራሱን የጠየቀው ። ማንኛውም ነገር በዮናታን ሊደርሳት እንደሚችል ወዲያው ገመተ። ወደዚህ ቤት የመምጣቱ ሐሳብ ከእሷ መመንጨቱን ሲሰማ በልቡ ውስጥ ለሴትዮዋ ልዩ ስሜት ተፈጠረበት

“ ከተጋባችሁ ? ” ሲል እስክንድር ፈራ ተባ በሚል ድምፅ ጠየቀ ።

“ ኦ! ስድስት ዓመት ያህል ሆኖአል ። በርሊን በነበርኩበት ጊዜ፡አንዴ ታምሜ ተኝቼ ሐኪም ቤት ውስጥ አስታማሚዬ ሆና ነው ያገኘኋት ። ”

ዮናታን ይህን ሲናገሩ ድምፃቸው የተለየ ቃና ነበረው ።የፍቅረኞች የመጀመሪያ ትውውቅ በልባቸው ታላቅ ትውስት
ጥሎ ያልፋል ። ዮናታንም ለእስክንድር በሰጡት መልስ ሳቢያ ከስድስት ዓመት በፊት የተፈጸመ ትውስት ውስጥ ገቡ .....
ዮናታን በምሥራቅ ጀርመን ውስጥ በሚገኘው ትልቅ ዩኒቨርስቲ የድኅረ ምረቃ ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ለተወሰኑ ዓመታት በምቦልት ዩኒቨርስቲ የፍልስፍና መምህር ሆነው አገልግለው ነበር ። እዚያ ሳሉ አንድ ጊዜ የሆድ ውስጥ ሕመም ያድርባቸውና በርሊን ቤክ እሚባለው
ሆስፒታል ይገባሉ ።

በርሊን ቤክ ፣ ከመሃል ከተማው ሀያ ኪሎ ሜትር ያህል ይርቃል ። ውስጡ በአምስት ግቢዎች ተከፍሎ ፡ በጠቅላላ
ዐሥር ሺህ አልጋዎች ያሉት ሰፊ ሆስፒታል ነው ። ዮናታን የተኙት፡“ታይል አይንስ” በሚባለው ግቢ፡ “ እስታስዩን አይን ሁንደርት ሲ ” ክፍል ውስጥ ነበር ።
በማገገም ላይ እንዳሉ አንዲት ነርስ ሲያዩ ልባቸው ይደነግጣል ። ይህች ነርስ ፊቷ ላይ ፈገግታ የተሳለ እንጂ እንደ ሌላው ሰው አንዳንድ ጊዜ ብቻ የምትሥቅ አትመስልም ። ሕሙማንን ለመጎብኘት ስትገባ በሕመም የደከመ ስሜታቸውን በፈገግታ ታነቃቃዋለች ። በውስጥ ቁስል
የዳመነ ፊታቸውን ፈገግታዋ ብርሃን ሆኖ ያፈካዋል ። መስተንግዶዋ ፍቅር የሞላበት በመሆኑ'በክፍሏ ሕሙማን ዘንድ ተወዳጅ ነበረች ። ወደ በሽተኞቹ ክፍል ለመግባት የጉብኝት ወይም የመድኃኒት ዕደላ ሰዓት እስኪደርስ ወይም እነሱ በደወል እስኪጠሩዋት አትጠብቅም ። ብቅ ጥልቅ እንዳለች
ነው የምትውለው ። ልማድ ሆኖባት ሁሌ ትቸኩላለች ።እናም አንድ ቦታ ቆማ አትቆይም ።

ዮናታን ልባቸው ከደነገጠላት ጊዜ ጀምሮ ይህን ችኮላዋን አልወደዱላትም ። ክፍላቸው ገብታ ስትወጣ ፀሐይ
ብልጭ ብላ ድርግም ያለች ያህል ስሜታቸው ይከፋ ጀመር ።

ሥራዋን ጨርሳ ወደ ቤትዋ ልትሔድ በሽተኞቹን ስትሰናበታቸው። የዮናታን ልብ ይረበሽ ነበር ።ሌሊት አልመዋት አድረው ጠዋት ዐይኗን የሚያዩበትን ጊዜ መናፈቅ ሲጀምሩ ልባቸው ፍቅር ፍለጋ ዳዴ እያለ መሆኑን ገመቱ ። ሞኒካ የሚለው ስም አሁንም አሁንም ጆሮአቸው፡ ውስጥ ይደውል ጀመር ።

አንድ ቀን ከሥራ በኋላ እንደ ልማዷ ልትሰናበታቸው ወደ ክፍላቸው ስትግባ ዮናታን እጅዋን ያዝ አድርገው ቅሬታቸውን ተነፈሱላት ።

"ቆይ እንጂ አትቸኩዪ ። ትንሽ አጫውችኝ ሁሌ መቸኮል ምንድነው ?” አሏት ።

ሞኒካ ፈገግ ብላ ፍቃዳቸውን ለመፈጸም አልጋቸው አጠገብ ትንሽ ቆመች ።

“ እውነት ለምንድነው እንዲህ የምትቸኩዬው ” ሲሉ ጠየቋት ።

“ ልማድ ሆኖብኝ ነው ። በምሰራበት ጊዜ ፍጥነቴ አይታወቀኝም ” አለችና : ትንሽ አሰብ አድርጋ ! “ በዚህ በአራት ዓመት ውስጥ ያፈራሁት ጸባይ ነው” አለቻቸው ።

“ ግን ምነው ! ለምን ? ” አሏት ።

“ለአፍላ ፍቅሬ ያገኘሁት ማካካሻ ራሴን ከይዲያ ወዲህ በማራወጥ ዕረፍት መንሣት ነበር ” አለቻችው ሰሜቷን
ግልጽ አድርጋ።

ከዚህ ንግግሯ ጋር ፊቷ ፍም ሲመስል ተመለከቱት ። ስሜቷ መጨፍገጉን አገጽታዋ ላይ አጠኑ ሰው ሠራሽ
የሚመስሉት ዐይኖችዋ፡በቅርቧ ያለውን ነገር ለማየት የተከለከሉ ይመስል በመስኮቱ ማዶ ከሚታየወው ባዶ ሰማይ ላይ ዐረፉ ።

“ ነገሩ እንዲህ ነው ” ስትል ቀጠለች ። “ ከአራት ዓመት በፊት አፈቅረው የነበረው ወጣት የመጀመርያዬ ነበር ። በመሆንም እጭር ጊዜ ውስጥ ሙሉ ልቤንና ፍቅሬን ሰጥቼው ነበር ለማለት እደፍራለሁ ። ነገር ግን ሁለት ዓመት ባልሞላው ጊዜ ውስጥ ጥሎኝ ጠፋ” አለችና ዝም !

“ የት ነው የጠፋው ?” አሏት ዮናታን ፥ ተመስጠው ።

“ ወደ ምዕራብ ጀርመን። እኔ የሰማሁት ጠፍቶ ከሔደ በኋላ ነው እንጂ ምንም ያማከረኝ ነገር አልነበረም ። በእርግጥ
ልቡ መሸፈቱን በአንዳንድ ንግግሮቹ ገምቼ ነበር ። አብዛኛውን ጊዜ በአስተሳሰብ እንጋጫለን ። እኔ በፋሽስቶች ላይ ከፍተኛ ጥላቻ አለኝ ። በሂትለር ዘመን በናዚዎች ታስሮ የማቀቀው አባቴ ቆስሎ በእኔም ላይ ከባድ ተጽዕኖ ነበረው ።ፍቅረኛዬ ግን ያለፈው ትውልድ በፋሺዝም ምን ያህል
እንደ ተሠቃየ ለማጤን ደንታ አልነበረውም በኣፍላ ስሜት ግፊት እኔደሚነቃነቅ እገምት በር ። እናም መጨረሻውን እንደዚያ አደረገወ ። ”

ዮናታን በኀዘን ከንፈራቸውን መጠጡ።

“አያሳዝነኝም ። ልቤን አሳዝኖት ነው የሔደው ”አለች ሞኒካ ፥ ራሷን እየነቀነቀች “ ነገር ግን እሱን ብጠላውም ልቤ ውስጥ የተተከለውን ፍቅር በቀላሉ መንቀል
አልቻልኩም ነበር። ስለዚህ ራሴን በሥራ በማዋከብ ልረሳው ሞከርኩ ። በሚረባውም ፥ በማይረባውም ነገር ነበር ራሴን የማደክመው ። በማያሰፈልግበት ቦታ እፈጥን ነበር ። እየቆየ ሲሔድ ይህ ልማድ እውስጤ ሥር እየሰደያ መጣ። አሁን ያለ ሥራ ለአጭር ጊዜም ቢሆን መቀመጥ አልችልም ። መንፈሴም የሚረካው ፈጠን ፈጠን እያልኩ ከሠራሁ ነው ”አለቻቸውና ፥ ደመናውን ከፊቷ አባርራ ፈገግ አለች ።

ታሪኳ ዮናታንን አጥንታቸውን ሰርስሮ ገብቶ ወደ ፍቅር መዳህ የጀመረ ልባቸውን እደፋፍረው። ነገር ግን ፥
በአፍላነቱ የተጎዳወን የሞኒካን ልብ ለማዳን መቻላቸውን እርግጠኛ አልነበሩም እድሜአቸውን ለማመዛዘን ሞከሩ ።
በዐሥር ዓመት ያህል ይበልጧታል ። ይህ ሁሉ የእንምሮ ማመንታት ነው እንጂ ፥ ፍቅሩ ያለ ምንም ፍርሃት በልባቻው ውስጥ እያደገ መጥቷል ።

ሞኒካም ዮናታን ታሪኳን በተመስጦና በትካዜ ካዳመጡዋት ጊዜ ጀምሮ ስሜታቸውን በማጤን ልቧ ውስጥ ለየት
ያለ አዲስ ስሜት ሲያብብ ተሰማት እና የእሷም ልብ እንደ እሳቸው ልብ ወደ ፍቅር በመዳህ ላይ ሳለ መንገድ ላይ ተገናኙ።

የዘመን መለወጫ በዓል ሲከበር፡ ዮናታን እዚያው ሐኪም ቤት ውስጥ
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_አርባ_አራት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ

....ናትናኤል ባለበት እንደቆመ በእልህ የሚርገበውን ካልቨርትን ሲመለከት የፈጸመው ስህተት ወለል ብሎ ታየው፡፡

“እጇን እየጠመዘዙ ሲያስጮኋት መፈረካከስ ጀመርክ.. እዬዬዋን
ስትሰማ ስለሰጡህ ቃልኪዳን መስበክ አማረህ… ናትናኤል የሚወዱት ሰው
አደጋ ላይ ሲወድቅ ምን እንደሚሰማ አውቀዋለሁ፡፡ እንዳንተ ለደቂቃዎች
ሳይሆን ለቀናት ለሳምንታት አብሮኝ ከርሟል። ይህ ብቻ አይደለም፤
የሚወዱትን ማጣት ምን ምን እንደሚልም ቀምሼዋለሁ። አሁን ድንገት
ወጣ ብለህ የፍቅረኛህን ለቅሶ አዳምጠህ ስለመጣህ ካንተ ጋር በአንድ ሲባጎ ተሸብቤ ወደ መቃብራ እንድነዳ ትጠይቀኛለህ? !ኦ ! ኢየሱስ!”

ናትናኤል ድምፅ ሳያሰማ ባለበት እንደቆመ ቆየ።

“ኣብረኸኝ ትጠፋለህ ወይስ እጅህን ትሰጣለህ? ” አለ ካልቨርት የሴት
ነጠላ ጫማውን ኣጥልቆ ሰፊ የሴት ቦርሳውን ዚፕ ከመዝጋቱ በፊት ድንገት
ቀና ብሎ እየተመለከተው፡፡

አብሬህ እጠፋለሁ፡፡” አለ ናትናኤል ጥርሱን ነክሶ እንባውን እየታገለ፡፡

“ትረፍ ሲልህ ጥሩ መንገድ መርጠሃል” አለ ካልቨርት ከስፊው ቦርሳው ውስጥ አንድ ትንሽ ሽጉጥ አውጥቶ እየፈተሽ፡፡ “እጅህን ልትሰጥ ብትወስን ኖሮ እዚሁ ጨርሼህ ልሄድ ነበር የወሰንኩት፡፡ መቼም አይኔ እያየ እየመራህ እንድታሲዘኝ ልተውህ አልችልም፡፡ በል ቶሎ እንውጣ፡፡” አለ ካልቨርት ሽጉጡን ፈትሾ አቀባብሎ መጠበቂያውን ብቻ ባለበት ትቶ መልሶ
ቦርሳው ውስጥ እየከተተው፡፡

ካልቨርት የሴት ልብስ ለብሶ በላዩ ላይ ድሪያውን ተከናንቦ ናትናኤል ደግሞ ከወገቡ በታች ሽርጡን እንዳሸረጠ በነጭ ሸሚዝ ከትንሿ ክፍል ተከታትለው ወጡ፡፡

“ወዴት ልትሄዱ ነው?” አሉ የየምሥራች እናት ድምፅ ሰምተው ከጓዳ ብቅ እያሉ፡፡
“ሰላም ነው፡፡ወደ አዲስ አበባ ነው የምንሄደው በላቸው፡፡” አለ
ካልቨርት በእንግሊዝኛ ቋንቋ ፈጠን ብሎ፡፡ “እና ስላደረጉልኝ ሁሉ በደንብ
አመስግንልኝ፡፡”

ናትናኤል ካልቨርት ያለውን በአማርኛ ተርጉሞ ለሴትየዋ ተናገረ፡፡

“ውዴታዲያ ብትሄዱስ በዓመት በዓል ነው እንዴ! ምነው ዋል አደር ብትሉ፡፡” አሉ የተከፉ የሚመስሉት ሴትዮ ካልቨርት ለብሶት የመጣውን የሴት ልብስ ድጋሚ ለብሶ ሲያዩ ምስጢሩ እያጓጓቸው፡፡

“ብንሄድ ይሻላል፡፡ የምሥራች ትጠብቀናላች:: ዛሬ ከሰዓት መግባት
አለብን፡፡”

“በአውሮፕላን ነው የምትሄዱ?” አሉ ሴትየዋ፡፡
“አዎ፡፡” አላቸው ናትናኤል፡፡
“ውይ አፈር በበላሁ! ደብዳቤ እንኳን ሳልጥፍ!” ኣሉ ሴትየዋ
እጃቸውን ሽርጣቸው ሳይ እየጠራረጉ “ማነሽ እመ… እመቤት ወረቀት
ወዲህ በይ ...ቶሎ...”
“አይ… ” አቋረጣቸው ናትናኤል እንዳያዘገይዋቸው ሰግቶ፡፡ “ሰሞኑን
ከቻልኩ ተመልሼ እመጣለሁ ከምሥራች ጋር፡፡ መልዕክት ግን እነግሮለታለሁ፡፡ አሁን ቶሎ መሄድ አለብን፡፡”

ሊወጡ ሲሉ ካልቨርት ከቦርሳው ውስጥ በርካታ ገንዘብ አውጥቶ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ምሥጋና እየደረደረ ለሴትየዋ ዘረጋላቸው፡፡

“በቁልቢው! ኧረ እኔ'ቴ! እዚህም ሆኖ የተቀበልኩት'ኮ ሁሉን ላሟላበት አቅም ስለሌለኝ እንጂ. ደግሞ የምን ክፍያ አመጣችሁብኝ? የልጄ ባልንጀሮች ልጆቼም አይደላችሁ? ግድ የለም 'እግዜር ይስጥህ የኔ ልጅ በልልኝ በኣ
አፉ በቋንቋው፡፡” አሉ ሴትየዋ ፊታቸውን ወደ ናትናኤል መልሰው፡፡

የምሥራች እናት ቤት ወጥተው ብዙም ሳይርቁ ከአንድ አነስተኛ ቡና ቤት ገቡና ጥግ ላይ ጨለምለም ያለ ቦታ መርጠው ተቀመጡ፡፡

“አዲስ አበባ ነው ለመሄድ ያሰብኩት::” አለ ካልቨርት ቦታ ይዘው እንደተቀመጡ፡፡ “በዚህ ሰዓት ተመልሰው እመህላችን ይገባሉ ብለው አይጠረጥሩንም:: ወደዚያው ማምራታችንን በትክክል እስካልደረሱበት ደግሞ ሠላም ልናገኝ የምንችለው አዲስ አበባ ውስጥ ብቻ ነው፡፡”

“ታዲያ ለምን ለየምሥራች እናት እውነቱን እንድነግራቸው ነገርከኝ?” አለ ናትናኤል፡፡

“አውቄ ነው:: ተባራሪ የሚሄድበትን፤ የሚሽሽበትን በትክክል አይናገርም። ሴትየዋ ቢያወሩም ዋጋ የሚሰጠው የለም፡፡ ይልቅ እንዴት አድርገን ወደ አዲስ አበባ መሄድ እንደምንችል ነው ያልተገለፀልኝ፡፡”

“ሦስት አማራጭ ነው ያለን አውሮፕላን- ባቡር መኪና፡፡”

“አውሮፕላኑን እርሳው:: ባቡር አንድ አማራጭ ነው:: ቢሆንም በጣቢያዎች ላይ ሰዎች ሊኖሩአቸው ይችላል፡፡ አውቶቡስ ጣቢያዎችም ተመሳሳይ ናቸው”

“እያቆራረጥን መጓዝ እንችላለን፡፡” አለ ናትናኤል ዝም ብለው ተቀምጠው ያዘዙትን ሻይ ሲጠጡ ከቆዩ በኋላ፡፡

“እንዴት?”
“ለጊዜው ክድሬዳዋ ብእግርም ቢሆን መውጣት.… ከዛ በኋላ የጭነት
መኪናዎችና የቤት መኪናዎች እየተከራየን እያቆራረጥን መጓዝ
እንችላለን፡፡”

“በእግር እስከየት ድረስ እንሄዳለን?” አለ ካልቨርት ትክሻው ላይ ካነገበው ከሰፊው የሴት ባርሳው ውስጥ አነስተኛ የአገር ጎብኚ ካርታ አውጥቶ እመሃል ካለው ጠረጴዛ ላይ እየዘረጋ፡፡ «እዚህ ነው ያለነው፡፡ አለ ካልቨርት የሌባ ጣቱን ድሬዳዋ ላይ ተክሎ፡፡ «እዚህ ነው መድረስ ያለብን፡፡ጣቱን ከድሬዳዋ አንስቶ አዲስ አበባ ላይ ጫነው፡፡

“እዎ..ይኽውልህ አንደኛው መንገድ በሐረር አቅጣጫ አድርጎ አለማያ ከመድረሱ በፊት ወደ ግራ ታጥፎ አሰበ ተፈሪ ይገባና ከዚያ ወዲያ በሚኤሶ አድርጎ ወደ አዲስ አበባ ይደርሳል፡፡ የተለመደው መንገድ ይህ ይመስለኛል፡፡”

“ይመስለኛል? አታውቀውም እንዴ?” አለ ካልቨርት ደንገጥ ብሎ፡፡

“እውነቱን ለመናገር አላውቀውም.. የመጀመሪያ ጊዜዬ ነው ድሬዳዋ ስመጣ፡፡”

“በእየሱስ! ከኔ አትሻልማ!” አለ ካልቨርት ወደኋላ ወንበሩ ላይ ተደግፎ፡፡

“አታስብ አማርኛ እስከተናገርኩ ድረስ የትም ይዤህ መሄድ እችላለሁ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ፡፡ ይኸውልህ... ሌላው አማራጭ ደግሞ ከሞላ ጎደል ከባበር ሃዲዱ ጋር ጎን ለጎን የሚሄደው የየረር ጎታ መስመር ነው፡፡ ይታይሃል በዚህ እድርጎ.” . ናትናኤል ወደ አዲስ አበባ ሊያመሩ
የሚችሉባቸውን ሁለት የመኪና መንገዶች አንድ በአንድ ለካልቨርት አሳየው፡፡

እኔ ሁለተኛውን እመርጣለሁ፡፡ እንዴልከው ብዙም የማይዘወትር ከሆነ አለ ካልቨርት፡፡

“ጥሩ፡፡ ግን ከዚያ በፊት ልብሶቻችንን መቀየር አለብን። ቤት ስንመጣ የምሥራች እናት እይተውናል፡፡አዳኞቻችን ከጠነከሩባቸው ፈርተው
ሊናገሩ ይችላሉ፡፡”

መዝድ ከመጀመራቸው በፊት ናትናኤል ከአንድ የልብስና የጫማ ሱቅ ገብቶ ለካልቨርት የሚሆን ሽርጥናጫማ፣ ለሁለቱም ደግሞ የእስላም ቆቦች ገዝቶ ተመለሰ፡፡ ከአንድ ቡና ቤት መጸዳጃ ቤት ውሰጥ ካልቨርት የለበሰውን የሴት ልብስ በአዲሱ ሼርጥ ከቀየረ በኋላ የወንድ ጫማውን ተጫምቶ መኪና ፍለጋ ወጡ።

“ጎን ለጎን ባንሄድ ጥሩ ነው። የሚፈልጉት ሁለት ሰዎችን ስለሆነ ዓይናቸው ጥንድ መንገደኞች ላይ ይበልጥ ጠንቃቃ ይሆናል፡፡አንተ ከፊት ከፊቴ ሂድ፡ እኔ በቅርብ ርቀት እከተልሃለሁ።” አለ ካልቨርት፡፡

"እንጠፋፋለና።”

“አንጠፋፋም፡፡ ብቻ አተ ከጀርባህ መኖሬን ለማረጋገጥ አትገላመጥ፡፡ ኣማርኛ የምትናገር አንተ ስለሆንክ በተቻለ መኪናውን ቶሉ ለማግኘት ብቻ ሞክር፡፡ እኔ እከተልሃለሁ። አታስብ፡፡ ለአት እዲስ ነው እንጂ እኔ የኖርኩበት ዓለም ነው ድብብቆሽ፡፡” አላ ካልቨርት፡፡
«እ..ናትናኤል ሊይዙን ቢችሉም ቀድመው የሚይዙት አንዳችንን ነው…አንተን ከያዙህ ዕሩቅ ስለማይህ ችግር የለውም! አመልጣለሁ፡፡ እኔን ከያዙኝ ግን የጥይት ድምፅ ስትሰማ ሳትገላመጥ ሳትደናገጥ ለማምለጥ ሞክር፡፡አንተንም ከያዙህ የምመክርህ የገዛ ሕይወትህን እንድታጠፋ ነው፡፡ አለበለዚያ
የሚከተለውን ለመሸከም መምረጥህ ነው፡፡”

“መሣሪያ እኮ
👍2
#የፍቅር_ሰመመን


#ክፍል_አርባ_አራት


#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን


#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው

....ኬቨን ቮስ በሴዳይ ሳናይ ሆስፒታል ውስጥ በሚገኘው የሆስፒታሉ ካፌ
ውስጥ ቁጭ ብሎ የፕላስቲክ ጠረጴዛውን በጣቱ እየቆረቆረ ነው::

የግል መርማሪው ደውሎ ቀጠሮ ያስያዘው ከጠዋቱ 12 ሰዓት ላይ ነው::
አሁን 12:10 ይላል፡፡ 12:11 ሲል ደግሞ ኬቨን ቀጠሮው የውሸት መሰለው::
ምክንያቱም የሆነ ሰው ስለ ዶክተር ዶውግ ሮበርትስ እና ስለ ውሽማው
የምታውቀውን ነገር ከነገርከኝ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዶላሮችን እሰጥሃለሁ
ብሎት ነው እዚህ የቀጠረው። እርግጥ ነው ኬቨን ስለ እነርሱ ብዙ የሚናገረው ነገር የለም። አብዛኞቹ ነገሮች ወንድ እና ሴት ነርሶች ሲያወሯቸው የነበሩ የሐሜት ወሬዎች ናቸው። ኬቨን ቮስ ዕዳ ስላለበት
ክሬዲት ካርዱ እና ሌሎች ነገሮችም ሁሉ ባዶ ስለሆኑበትና የግድ ብሩ
ስለሚያስፈልገው ነበር ሰውዬውን ለማግኘት የተስማማው። በዚያ ላይ ደግሞ የወንድ ጓደኛው ኢንዞ በነርስነቱ ከሚከፈለው በላይ በጣም ብዙ ብሩን ግጦትባዶና ስላደረገው ነበር።

“ኤቨን?” አለው አንድ ወፍራም ሰው ወደ ካፍቴሪያው ተንደርድሮ እየገባ እና ኬቨን ወደ ተቀመጠበት ቦታ እየመጣ፡፡ አጠገቡ ደርሶም ላባማ እጆቹን ለሰላምታ እየዘረጋ ራሱን አስተዋወቀው:: ደግነቱ ቦታው ጭር ያለ ስለሆነ ኬቨን ደስ አለው::

ነርሱ ዙሪያውን ከቃኘ በኋላ እጁን ጨብጦ እንዲቀመጥ በአይኑ ጋበዘው።

“እዚህ ካፌ ምንድነው ጥሩ ምግባቸው?” ዊሊያም ከጠየቀ በኋላ “ማታ ቆይቼ ነበር እና ጥሩ ቁርስ እፈልጋለሁ::”
ኬቨን የዊሊያምስን ከብብቱ ሥር ያለውን ሸሚዝ ቅፍፍ እያለው አይን አይኑን እየተመለከተ “ብቻዬን ልታገኘኝ ነበር የፈለግከው።” አለው በሹክሹክታ፡፡

“አዎን ደግሞም እኮ እዚህ ማንም የለም::” ብሎ ዊሊያምስ ገለፈጠ እና
ሁለት የብሉ ቤሪ ዳቦ እና አንድ ትልቅ ላቴ አዝዞ ወደ ኬቨን በመመለስ
"እዚህ ስለ እኛ ደንታ ያለው ሰው የለም እመነኝ፡፡ ደግሞም እኮ እያወራን
ያለነው ስለ ድሮ ጓደኛዬ ስለሆነ ህገወጥ የሆነ ነገር አይደለም::”

እሺ” ብሎ ነርሱ የግዱን ፈገግ አለ እና ይሄ ዊሊያምስ የእውነት የዶ/ር
ሮበርትስ ጓደኛ ይሆን? ብሎ አሰበ።
ለማንኛውም ገንዘቡ የግድ ስለሚያስፈልገው የግድ ያወራዋል።

“ያን ያህል በጣም የቅርብ ጓደኛማቾች አይደለንም” ብሎ የመጣለትን ቁርስ አንድ ጊዜ አብዝቶ ጎርሶም የሆነ ጊዜ ላይ አብረን እንሰራ ነበር።እወደውም ነበር። ብዙ ሰዎች ይወዱታል” አለው፡፡

“እሺ ማን ነበር የማይወደው የነበረው?” ብሎ ዊሊያምስ ቡናውን በረዥሙ ድምፅ እያሰማ ፉት አለው።

“ምን ማለትህ ነው አልገባኝም?”
“ብዙ ሰዎች ይወዱት ነበር ብለኸኛል። ብዙ ማለት ደግሞ ሁሉም ማለት አይደለም። ስለዚህ እሱን የማይወድ ሰው ነበር?”

ኬቨን ፊቱን አጥቁሮ “በቃ ፀባዩ ተቀየረ ከሆነች ሴት ጋር ግንኙነትም ጀመረ። ሩሲያዊ ናት:: ከዚያ በኋላ ሁሉ ነገሩ ተቀየረ”

“ተቀየረ ስትል?” ብሎ ዊሊያምስ ጠየቀው ምግቡ ላይ አቀርቅሮ፡፡

የሩሲያኖች ሥም ነው ያላት። ሥሟ አሁን ተረሳኝ። ሞስኮ ነበር ትኖር የነበረው። ግን ሁሉ ነገሯ አሜሪካዊ ነበር ይመስል የነበረው:: ስታወራ ደግሞ እንግሊዝኛ ዘዬዋ የአሜሪካውያን ነበር፡፡ ብቻ ዶክተር ሮበርትስ በእሷ መተት የተሰራበት ይመስል ነበር። ደግሞ እኮ ያን ያህል
ቆንጆ አልነበረችም:: የሆነች የአለምን ሸክም የተሸከመች ነበር የምትመስለው።
እንዲያውም በወጣትነቷ የሚጠብሳት ወንድ ሁሉ ያለ አይመስለኝም፡፡ በጣም
ረዥም ናት” ብሎ በማስከተልም “ከዚያ በዘለለ ግን ከሚስቱ ጋር ስትነፃፀር
እዚህ ግቢ የሚባል የሴት ውበት ያላት አልነበረችም” አለው፡፡

ዊሊያምም በኬቨን ሀሳብ መስማማቱን ራሱን ነቀነቀ፤ በተለይ ደግሞ ደብዛዛ የሌንካ ጎርዴቪችን ፎቶዎች ሲመለከት ሌንካ ከኒኪ በዕድሜ ማነሷ
ብቻ ይበልጥ ወጣት እንድትመስል ያደርጋታል፡፡ ከዚያ በተረፈ
የፈለገቻቸውን ውድ ውድ ልብሶችን
ምንም እንኳን ብትለብስም
የማያምርባት ሴት እንደሆነች ለመረዳት ችሏል።

ዊሊያምስ ስለ እሷ የኋላ ህይወት ለማወቅ ያልቆፈረው ድንጋይ
ባይኖርም እንዳሰበው ስለ እሷ ማወቅ አልቻለም። ይሄው ከአከራይዋ ጀምሮ
እሷን አስመልክቶ ጥያቄን ቢጠይቅም ስለ ቤተሰቧ ስለ ስራዋ፣ ስለ ስራ
ቅጥሯ ወይንም ደግሞ ስለ ትምህርት ደረጃዋ አንድም አይነት መረጃና
ለማግኘት አልቻለም፡፡

ሀዶን ዶፎ ኒው ዮርክ ውስጥ በሚገኝ የአደንዛዥ ዕፅ አስወጋጅ የግብረ
ሰናይ ድርጅት ውስጥ ነው የምትሰራው ቢለውም እዚያ ቦታ ላይ ይሰሩ
የነበሩ ሰዎችን ባወራቸው ጊዜ ስለ እሷ አንድም ነገር እንደማያውቁ
ነግረውት ነበር። ብቻ ሴትየዋ የሆነች መንፈስ ናት እንዴ? ብሎ እስከማሰብ
ደርሷል።

“አግኝተሃት ታውቅ ነበር?” “ለተወሰኑ ጊዜያት ያህል አዎ፡፡” ነርሱም ራሱን በአዎንታ ወዝውዞ “ብዙ ጊዜ ወደ ሆስፒታል ትመጣ ነበር፡፡ እዚህ
ካፌ ውስጥም ነበር ብዙውን ጊዜ ምሳቸውን ይበሉ የነበሩት። ይሄ ደግሞ
ያልተለመደ ነገር ነው:: ምክንያቱም የፍቅር ግንኙነታቸው በይፋ ነበር፡፡
ለሆስፒታሉ ሠራተኛ በሙሉ ነበር በግልፅ ያሳዩ የነበረው።” ይሄ ደግሞ
ብዙውን ጊዜ ዶክተር ዶፎ እና ዶክተር ሮበርትስ ያጣላቸው ነበር። “አዎን
በእሷ በሌንካ ምክንያት እንደሚጨቃጨቁ እርግጠኛ ነኝ። አሁን ሥሟ መጣልኝ ሌንካ ነው ሥሟ” አለው ኬቨን ስሟን በማግኘቱ ደስ እያለው፡፡

“ዶውግ ሮበርትስ እና ሌንካ እንዴት ነበር የተገናኙት?”

ኬቨን ለጥቂት ጊዜ ሲያስበው ቆየና “ኒውዮርክ ላይ ይመስለኛል። የሆነ
የበጎ አድራጎት የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ላይ። ዶክተር ሮበርትስ የሆነ
በነፃ አገልግሎት የሚስጥ ክሊኒክ...” ብሎ

“እሱን አውቃለሁ” አለው እና ካቋረጠው በኋላ “ስራዋ ምን እንደነበር
ታውቅ ነበር?”

“እሱን አላውቅም” ብሎ ኬቨን መቶዎቹ ዶላሮች በዚህ ምክንያት የሚያመልጠው ይመስል እየተጨነቀም “ግን እሷ በጣም ሀብታም ነበረች። ምናልባት ይሄ ይሆናል ያቀራረባቸው:: ግን አየህ ፕላቲንየም እና አልማዝ ያለባቸውን የእጅ ሰዓቶች ነበር የምታደርገው፡፡ አዎን ቶፓርድ!” አለው እና
በመቀጠልም “ማለቴ ሰዓቶቿ ቢያንስ ከአሥራ አምስት ሺ እስከ ሃያ ሺ
ዶላር የሚያወጡ ናቸው። ሁሌም ሄርሜስ ቦርሳዎችን ነው ይዛ የማያት።የሆነ ጊዜ ላይ ደግሞ እጅግ በጣም ውድ የሆነ ጃኬት አድርጋ መምጣቷን አስታውሳለሁ። ምክንያቱም ዶክተር ሮበርትስ ይህንን ለብሳ በመምጣቷ ተቆጥቷት ስለነበር ነው።”

“ምን ብሎ ነው የተቆጣት?”

“ማምለጥ ብትፈልጊም ሆነ ባትፈልጊ ይህንን ልብስ ለብሰሽ አትምጪ!”
ብሎ በጣም ተናድዶ ነበር የተናገራት::

እሺ እሷስ ምን መለሰችለት?” ብሎ ዊሊያምስ ጠየቀው፡፡ የተለየ ነገር
የሚገኝበት መስሎት እየጓጓ።

አለቀሰች” ብሎ ኬቨን ከመለሰለት በኋላም “ግን ያው እንደ ሁልጊዜውም
ወድያው ተረጋጋች”

“ከእሷ ሌላ ውሽማዎች ነበሩት?”

ኬቨን ራሱን በአሉታ ነቅንቆ “ከሌንካ ጋር ግንኙነት ከመጀመሩ በፊት
እንደምትፈልገው በጣም የምትፈልገው አይመስለኝም፡፡ ገባህ አይደል?”
ሁሌም ከሚስቱ ጋር ነበር፡፡ ግን አየህ ሚስቱም ዶክተር ስለሆነች ሩሲያዊቷ
ዊሊያምም እንደገባው ለማሳወቅ ራሱን በአዎንታ ወዘወዘለትና የማስታወሻ ደብተሩ ላይ ነገሮችን መፃፍ ጀመረ::

ከሆኑ አደገኛ ሰዎች ጋርም ግንኙነት እንዳላት ሰምቼ ነበር?” ብሎ ኬቨን ድምፁን ቀነሰና “ማለቴ በጣም ሀይለኛ ከሆኑ ሰዎች ጋር”

“ምን አይነት ሰዎች?” ብሎ ዊሊያምስ ጠየቀው፡፡

“አላውቅም” አለ እና ኬቨን በመቀጠልም “ዶውግ ሮበርትስ እነዚህን
👍3
#የተወጋ_ልብ


#ክፍል_አርባ_አራት


#ድርሰት_በትክክል_ገና


...ጭንቀት በጭንቀት ሆነች። ብቅ ጥልቅ ወጣ ገባ.አበዛች። ለመጀመሪያ ጊዜ ማምሸቱ ያሳሰባት ዘይኑ የምትሆነውን አጣች። ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ተኩል ጀምሮ ነበር መጠባበቅ የጀመረችው። እንደበፊቱ ትምህርት ቤት እንዳትል ትምህርቱን ጨርሷል። ምን ነክቶት ይሆን? ተርበተበተች፡፡ ስዓቱ እየገፋ እየሄደ ነው። ስጋት ከጀመረችበት ጊዜ ጀምሮ ጌትነት
አደጋ ላይ እስከወደቀበት እስከ ምሽቱ አራት ሰዓት ተኩል ድረስ...
ከዚያም ሙሉውን ለሊት ስታምጥ አነጋች፡፡ ወንድም ጋሻዋ..ድምጡ
ጠፋ፡፡ የውሃ ሽታ ሆነ፡፡ ለሊቱን ተቅማጥ ሲያጣድፋት አደረ። ጎረቤታቸው ወይዘሮ ጤናዳም ደግሞ ሲያፅናኗት አነጉ።

"ምንም አይደለም ወንድ ልጅ አንዳንድ ጊዜ አመሉ ነው። አይዞሽ ጠዋት ይመጣልሻል"እያሉ ሞራል ሲሰጧት አደሩ። መንጋት አይበለው እንደ ምንም ነጋላት። ወንድም ጋሻዋን የበላችባት ወፍ ግን ድምጿን አላሰማ አለች፡፡ እዬዬ... ኡኡታ... ዋይታ…ቁጭ ብድግ.. በዚያች እሷ በጭንቀት በምትሸበርባት ማለዳ አንድ ሰው ወደ ስራ በማምራት ላይ እያለ እሪ በከንቱ ዳገቱ ላይ ወደተፈጠረው ትርምስ ጎራ አለ።

ታደሰ ገብረማሪያም ይባላል። በአሰቃቂ ሁኔታ የተደበደበውን ወጣት ሲመለከት ዐይኖቹ በእንባ ተሞሉ፡፡ አደጋውን ለፖሊስ ቀድሞ ሪፖርት ያደረገው እሱ ነበር፡፡ ፖሊስ ከስፍራው ሲደርስ ነፍሱ አልወጣችም እንጂ ያ ወጣት የሞት ያክል ከባድ ጉዳት ደርሶበት ተገኘ፡፡ ወጣቱ በአንቡላንስ ወደ ዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል ከተወሰደ በኋላ ታደስ ወደ መስሪያ
ቤቱ ቢያመራም የእለት ተግባሩን በአግባቡ መከወን ተስኖት ነበር። ገና በጠዋቱ ከቤቱ እንደወጣ ባየው አሰቃቂ አደጋ ቀኑን ሙሉ ሲረበሽ ውሎ ሲመሽ ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡
ታደሰ የጨለማ ድባብ በዋጣት ጠባብ ክፍሉ ውስጥ ብረቱ የዛገ የሽቦ አልጋውን ተንተርሶ በሃሳቡ ጭልጥ ብሎ ሄደ። የዚያ በደም ተለውሶ የተንጋላለ ወጣት ሁኔታ ከፊቱ እየተመላለሰ ሰላም አየነሳው ነበር።
መንግሥትና ህግ ባሉበት አገር ውስጥ እዚያ ጥግ የደረሰ አስከፊ ወንጀል በአደባባይ መፈፀሙ እያስቀጨነቀው፣ የቀማኞችና የነፍሰ በላዎች መሸሽጊያ ዋሻ እሪ በከንቱ የሚፀዳበት ጊዜ እየናፈቀው እንቅልፍ የሚባል ነገር
በአይኑ ሳይዞር ሰማይና ምድር ተላቀቁ።

ታደሰ በጠዋቱ ተነሳና ወንበር ላይ አጣጥፎ ያስቀመጣቸው ልብሶቹን
ለባብሶ በየማዕዘኑ ሸረሪት ያደራባት ጎጆውን ከውጪ ቆለፈና እንደ ልማዱ ወደ መስሪያ ቤቱ የሚያደርሰውን ሰርቪስ ለመያዝ ወጣ፡፡ያ አሳዛኝ ወጣት ወድቆበት የነበረውን አካባቢ በጥላቻ ወደ ጎን እየተመለከተ ወደ ፊት በር አቀና፡፡

አንገቱን አቀርቅሮ እጆቹን እያወራጨ ሲራመድና ለራሱ ሲያወራ የተመለከተ ሰው ከአዕምሮው ጤነኛ አለመሆኑን ቢጠራጠር የሚፈረድበት
አይሆንም፡፡ ለሰው ልጅ ህይወት ደንታ ሳይኖራቸው እየነጠቁና ደም
እያፈሰሱ በእሪ በከንቱ ዋሻ ውስጥ ተደብቀው የሚኖሩ ግፈኞች ጉዳይ በእጅጉ እያሳስበውና ነገ ከነገ ወዲያ የዚያ ወጣት እጣ ፈንታ በሱ ላይ
የማይደርስ ስለመሆኑ ዋስትና በማጣት ጭምር እየተጨነቀ ነው። ታደሰ ይሄ ጉዳይ ክፉኛ ስላሳሰበው አቅሙ በፈቀደ መጠን ወንጀልና ወንጀለኞችን ለመፋለም ለራሱ ቃል ገብቷል። "ምነው ታዴ እንደ እብድ ብቻሽን ታወሪ ጀመር እንዴ ?" አለው ጓደኛው አማኑኤል፡፡
"እብደት አልከኝ አማኑኤል? ልክ ነህ አእምሮ ጫና ሲበዛበትና ፊውዙ ሲቃጠል ተከታዩ እብደት ሊሆን ይችላል። የኔ አዕምሮ ፊውዝ ግን የነሱን ሳያቃጥል በቀላሉ አይቃጠልም!!" ፊቱን ቅጭም አደረገ፡፡ አማኑኤል በታደሰ አነጋገር ግራ ተጋባ፡፡
"እነማንን ነው የምትለው ታዴ?"
"እነዚያን የሰውን ልጅ ህይወት በጩቤ ጀልባ እየቀዘፉ በደም ውቅያኖስ ውስጥ የሚዋኙትን፣ እነዚያን የንፁሃንን ጉሮሮ ያለርህራሄ የሚበጥሱትን፣ እነዚያን ሳይሐፉ፣ሳይደክሙ በደም የተለወሰ እንጀራ የሚበሉትን!"

አማኑኤል ከዩኒቨርስቲ ተመርቆ ስራውን ከጀመረ ሁለት ዓመት እንኳን አልሞላውም ነበር፡፡ ከታደስ ጋር በዚህ መስሪያ ቤት ውስጥ ከተዋወቁበት ጊዜ ጀምሮ ተግባብተውና ተሳስቀው ስራቸውን በትጋት ከማከናወን
ባለፈ የዚህ ዓይነቱን የመረረ ሁኔታ አይቶበት አያውቅም ነበር ።
አስቃቂ ድርጊትም አከለለት።
“ባልና ሚስትን ደብድበው ንብረታቸውን ዘርፈው ተሰወሩ፣ እገሌን ማጅራቱን መቱት፣ የለበሰውን ልብስ ገፈው ቱቦ ውስጥ ጥለውት ሄዱ፤
እገሌን ሃንግ አደረጉ..." ሌላም ሌላም፡፡ በዚያ ወጣት ላይ ደርሶ ያየውን አሰቃቂ ድርጊት አከለለት

“ይሄ አረመኔነት የተጠናወተው ሰይጣናዊ ተግባር ነው። ይሄ እኩይ መቆሚያ ካልተበጀለት የእያንዳንዳችን ጉሮሮ ተራ በተራ መታነቁ የማይቀር ነው" አለ በብስጭት።
"አቦ ተወና ታዴ! ያልበላህን እያከክ ነው እንዴ?! እሱ የኛ ችግር አይደለም! ይሄ ለዚሁ ተግባር የተሰማሩ የፖሊሶች ስራ ነው፡፡ የሰው ስራ አትሻማ!” አለው።

“እንደሱ አይደለም አማኑኤል!.….በፍፁም አትሳሳት!…አንዱ ለሌላው ፖሊስ ሊሆን ይገባል፡፡ የኛ ድጋፍ፣ የኛ ትብብር በሌለበት ፖሊስ ብቻውን ተአምር ሊፈጥር አይችልም፡፡ የሌላው ቤት ሲፈተሽ፣ ሲበረበር፣ ሌላው አንገቱ ሲመታ፣ሲታነቅ እንደ ዶሮ ሲጠመዘዝ እያየን እንዳላየ ፊታችንን አዙረን የመሄዱን አስከፊ ልማድ እስካልቀየርነው ድረስ የደህንነት ዋስትናችን አደጋ ላይ መውደቁ የማይቀር ነው፡፡ የሰው ልጅ ጥሮ ግሮ ያፈራው አንጡራ ሀብቱን በገሃድ መነጠቁ አንሶ ህይወቱ መጥፋት የለበትም። በየሜዳውና በየድልድዩ ውስጥ መደፋት የለበትም፡፡ ወንጀለኞቹ
ገንዘብ ብቻ ዘርፈው አይሄዱም እኮ! እሱ ብቻውን አያረካቸውም፡፡የሚያረካቸው ደሙ ሲንዠቀዠቅ፣ እስትንፋሱ ስትቆም ማየት ነው"
እና መፍትሄው ምንድን ነው ታዴ ? ምንስ ማድረግ ትችላለህ?"
ከዚች ደቂቃና ሴኮንድ ጀምሮ ምሽጋቸውን ለመናድ ከተደራጀው ሰራዊት ጎን ቆሜ እኩይ ተግባራቸውን ለማስቆም የበኩሌን ጥረት አደርጋለሁ” አለው በፅናት፡፡

'ተው እንጂ ታደስ? ለምን በአንገትህ ላይ ሸምቀቆ ታስገባለህ? ለምን ራስህን ለአደጋ ተጋልጣለህ?ፖሊስ የሚፋለማቸውኮ በተገቢው ትጥቅ ተደራጅቶ ነው፡፡ አንተ ግን ባዶ እጅህን ነህ በባዶ እጅ ያዋጣል? እንኳን በባዶ እጅ በትጥቅም አልተቻሉም ወዳጄ!.."
ተራህ እስከሚደርስ ቁጭ ብለህ ጠብቃቸው እያልከኝ ነው?"
“ታዴ ብቻህን ተቆርቋሪ በመሆንህ ወይንም ራስህን ለጥቃት በማጋለጥህ ለችግሩ መፍትሄ ትሆናለህ ብዬ ስለማላምን ነው። ጨለምተኛ እንዳትለኝ እንጂ መፍትሄው ያለው በመንግሥት እጅ ብቻ ነው።ማጅራት መቺው፣ ቤት ሰርሳሪው፣ ኪስ አውላቂው ሁሉ የየራሳቸው የሆነ የተለያየ ታሪክ ያላቸውና በተለያዩ ጊዜያት ተይዘው እስር ቤት የገቡ፣ የተገረፉ፣ የተደበደቡ ጭምር ናቸው፡፡ ምክንያታቸው ደግሞ የስራ መስክ አልተፈጠረልንም፣ ሰርተን የምንኖርበት ሁኔታ አልተመቻቸልንም የሚል ነው።
ዘላቂ መፍትሄ የሚገኘው እነሱን በማጥፋት ብቻ ሳይሆን እነሱን
የሚፈለፍለውን የኋላ ቀርነት ማሽን ከስር መሰረቱ በማጥፋት ነው።
ወንጀልና ወንጀለኛን መከላከል የሚቻለው ስራ አጥነትን፣ የትምህርት እድል እጦትን፣ ረሃብን ፣ በሽታን ፣ ድንቁርናን በአጠቃላይ በድህነት ሰፊ ማህፀን ውስጥ የሚፀነሱ ችግሮችን በመዋጋት ነው። ለዚህ ደግሞ በቂ የስራ እድል በመፍጠር፣ ህብረተሰቡ ለስራ ያለውን ዝቅተኛ አመለካከቱን እንዲለውጥ በማስተማር፣ መሃይምነትን በመታገል እና ሌሎች ተመሳሳይ ስራዎችን በመስራት እንጂ ወንጀለኛን በማሳደድ ብቻ ማስቆም የሚቻል አይሆንም፡፡ ይሄ እጅግ ሰፊ አገራዊ ችግርና አጀንዳ ስለሆነ
👍1
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_አርባ_አራት


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ


...እንደ ሀምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ከትዝታ ጋር የተቀላቀለ አይሁን እንጂ መርዕድ እሽቴም በደረቅ ጭንቀት ተወጥሮ ነው ያረፈደው የጀመረው ደግሞ ጠዋት ሁለት ሰዓት በፊት፡፡ መኖሪያው በዜሮ ሁለት ቀበሌ የታችኛው ጥግ ሲሆን የሚያስተምረው ደግሞ የዲላ ከተማ የላይኛው ጫፍ
በሆነ ቀበሌውስጥ በማገኘው
የአፄ ዳዊት ትምህርት ቤት ውስጥ ነው። ሔዋንና ትርፊ የተከራዬት መንገዱ ላይ በመሆኑ ሲወጣም ሲወርድም ጎራ እያለ ይጠይቃቸው ነበር፡፡ ዛሬ ጠዋት ግን ወደ ሥራው ሲሄድ ያ ቤት በጠዋት ከውጭ ተዘግቶ አየው ወዴት እንደሄዱ የጎረቤት ስዎችን ሲጠይቅ ማታ ሲሆንና ሲባል ያመሸው ሁሉ ሁሉ የዝርዝር ተነገረው።
በሰማው ወሬ የተሰማው ድንጋጤ ጭራሽ ራስ ምታት ለቀቀበት። ዛሬ
ቢቸግረው ወደ በልሁ ቢሮ ሮጠ፡፡ ነገር ግን ዘንግቶ ነበር እንጂ በልሁ
ለመስክ ስራ ወጥቷል መስሪያ ቤት ደርሶ ይኸው ሲነግረው ያለ ውጤት ተመለሰ።
እንደገና ወደ ታፈሠ ቤት ላሮጥ አሰበ፡፡ ግን ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ክፍለ ጊዜ አስተምሮ ሌሎቹን ክፍለ ጊዜያት ነፃ እንደሆነ አስታወሰና በአንድ ፊት ስራውን
አጠናቆ ለመሄድ ወስኖ እየተጨነቀም ቢሆን ወደ ትምህርት ቤት አመራ፡
ልክ ከጠዋቱ አራት ሰዓት ላይ ሥራውን ጨርሶ ወደ ታፈሡ ቤት
በመገስገስ ላይ ሳለ አስፋልቱን አቋርጦ ሊያልፍ ሲል ከይርጋ ጨፌ አቅጣጫ ትመጣ የነበረች ቶዮታ መኪና ደጋግማ ክላክስ ስታደርግ ሰማ። ዞር ብሎ ሲመለከት የበልሁ የመስክ መኪና ናት:: በክላክስ ያስጠራውም ራሱ በልሁ ኖሯል፡፡ በአለበት ላይ ቆሞ መኪናዋን ጠበቀ።
«ዛሬ ስራ የለም እንዴ?» ሲል ጠየቀው በልሁ አጠገቡ ሲደርስ አንገቱን በመስኮት አውጥቶ መርዕድን እየተመለከተ፡፡
«እስቲ ና ውረድ!» አለ መርዕድ ፊቱ በድንጋጤ ጭምትርትር እንዳለ።በልሁም የመርዕድ ሁኔታ ገና ሲያየው እስደንግጦታል። «ምነው? ምን ሆነካል?
«ችግር አለ፡፡»
በልሁ ከመኪናዋ ላይ ዱብ ብሎ ወደ መርዕድ በመጠጋት ምንድን ነው ችግሩ? ሲል ጠየቀው።
«ሔዋን ታስራለች!»
«ምን አድርጋ?»
መርዕድ ከሰው የሰማውን በሙሉ ነገረው::
«ያምሀል እንዴ አንተ ሰው?»
«የነገሩኝን ነው እኔ የምነግርህ?»
“ከታሰረች ጠይቀሃታል?»
« አሁን ወዚያው እየሄድኩ ነበር፡፡»
ለነበሩበት ቦታ ፖሊስ ጣቢያው ቅርብ ነው፡፡ በልሁ ሾፈሩን ወደ ቤቱ እንዲሄድ አሰናበተውና ከመርዕድ ጋር ወደ ፖሊስ ጣቢያው ገሰገሱ፡፡ እርምጃቸው
ፈጣን ስለነበር ከአምስት ደቂቃ በላይ አልወሰደባቸውም።
ትርፌ ገና በጠዋት ለሔዋን ቁርስ ይዛ እንደሄደች አልተመለሰችም ኖሯል፡እንዲያውም በእስረኞች ግቢ እንድትገባ ተፈቅዶላት ኖሮ ፊት ለፊት ሔዋን ጋር አብረው ተቀምጠው በልሁና መርዕድን ከሩቅ ሲያዩአቸው ተንጫጬ «በልሁ! መርዕድ! በልሁ! መርዕድ!» በማለት።
በልሁና መርዕድ ጣቢያው በር ላይ እንደ ደረሱ አንድ ፖሊስ ጠጋ
አላቸውና ««ከእናንተ ወስጥ በልሁ ተገኒ የሚባል ማነው?» ሲል ጠየቃቸው፡፡
«እኔ!» አለው በልሁ በሌባ ጣቱ ወደ ራሱ እያመለከተ፡፡
«ሃምሳ አለቃ ይፈልጉሃል።»
«በሰላም?»
«አላወቅሁም አለና ፖሊስ ወደ እነ ሔዋን ዞር ብሎ አየት አደረገና ፊቱን ወደ በልሁ በመመለስ ከልጅቷ ጋር ሳይገናኝ ወደኔ አምጡት ነው ያሉት» አለው።
«ቢሮው የት ነው?» አለ በልሁ ቁና ቁና እየተነፈሰ፡፡
«ተከተለኝ! አለና ፖሊስ በልሁን ከፊት ከፊት እየመራ ወስዶ ካሃምሳ አለቃው ቢሮ አስገባው፡፡
የሃምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ጆሮግንዶቹን በእጆቹ ይዞ
ጠረጴዛው ላይ በማቀርተር ሀሳብ ውስጥ ገብቶ ሳለ ፖሊስ በልሁን ይዞ በመድረስ «አቶ በልሁ
እኒህ ናቸው አለው፡፡ ሃምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ለካ በልሁን ከተማ ውስጥ በዓይን ያወቀው ኖሯል:: እንዲያውም በአለባበስ፣ በተክለ ሰውነቱና አጠቃላይ አቋሙ
ያደንቀው የነበረ ሰው ሆኖ ሲያገኘው ‹‹በልሁ ተገኒ ማለት አንተ ኖረሀል እንዴ?
እያለ ብድግ ብሎ ጨበጠው::
«አዎ ነኝ» አለ በልሁ ቁና ቁና እየተነፈሰ፡፡
«ቁጭ በል እስቲ! ሁለቱም ፊት ለፊት ተቀመጡና ተፋጠጡ፡፡
«የተበሳጨህ ትመስላለህ!» አለው የሃምሣ አለቃ፡፡
«አዎ እጅግ በጣም ተናድጃለሁ፡፡
«ምነው?»
«የማትታሰር ሰው አስራችኋላ» አለው በልሁ ቁጭ እንዳለ በቀኝ
ሽንጡን በመያዝ ሃምሳ አለቃውን እየተመለከተ።
«ወንጀል ፈጽማ እንሆነስ» አለ ሃምሳ አለቃው ፈገግ እያለ።
«የተባለው ከሆነ አላምንም።» አለና በልሁ የሃምሳ አለቃውን ጠረጴዛ መታ መታ እያደረገ «ቀድሞ ነገር የተሰራ ሁሉ ወንጀለኛ የአሰረ ሁሉ ዳኛ ነው ብዬ ማመን ከተውኩ ቆይቼአለሁ።» አለው።
«አይፈረድብህም»
«አሁን ለምን ፈለከኝ።» ሲል በልሁ ዓይኑን ፈጠጥ አድርጎ ጠየቀው።
«ለብርቱ ጉዳይ !» አለና ሃምሳ አለቃ በረጅሙ ተንፍሶ "ግን አቶ በልሁ አሁን የምነግርህ ጉዳይ ሔዋን ለምትባል ልጅ ፈፅሞ መነገር የለበትም ባይሆን
ለአንተና ለቅርብ ጓደኞችህ ከነገርኳችሁ በኋላ አስባችሁበት የሚሆን ነገር ነው።"
«ምንድነው እሱ?»
«አስቻለው ፍስሀ የሚባል ጓደኛ እንደነበረህ ሰማው።»
«አሁንም አለኝ::»
«አብራችሁ ያላችሁ አይመስለኝም።»
«ከልቤ አይወጣምና ምንጊዜም አብረን የምንኖር ይመስለኛል»
«በአካል ማለቴ ነው፡፡»
«ክፉዎች አለያይተውናል፡፡ አሁን የትና በምን ሁኔታ ላይ እንዳለ
አላውቅም።» ካለ በኋላ በልሁ «ለአንተ ማን ነገረህ? ሲል ጠየቀን
«በህይወት አለ ብልህ ታምናለህ?
«የት አገር?»
«እዚሁ ኢትዮጵያ ውስጥ፡፡»
«ኦ?» አፉ ተከፍቶ ቀረ ዓይኖቹ በሃምሳ አለቃው ላይ ተተከሉ
«እስቲ ከሚቀርበህ ሰዎች ጋር በመሆን ተሰባሰቡልኝና ስለ እሱ ሁኔታ በጋራ ላናጋገራችሁ፡፡ እኔ የማውቀው ነገር አለኝ፡፡
«ዛሬ ማታ ቢሆንስ?»
«ይቻላል»
«ቦታና ሰአት ወስነው ተለያዩ፡፡»
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

የሃምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ፖሊስ ሆኖ ከተቀጠረ ጀምሮ አሁን
ያጋጠመውን ዓይነት አስደሳች ሥራ እግኝቶ አያውቅም። የሔዋንና በእሷ ምክንያት ተጣላን ያሉ ሰዎችን ጉዳይ እንደ የመንግስት ተቀጣሪነቱ ሳይሆን ልክ እንደ ራሱ
ገዳይ በተለየ ስሜትና ትኩረት ሊከታተለው ወሰነ።
የስራው የመጀመሪያ ዕቅድ የሔዋንን ድንግልና በሐኪም ማረጋገጥ ነበር።በእርግጥም ፈፀመው ሔዋን ያልተሟሸ ገላ ባለቤት ሆና አገኛት። የምስክር
ወረቀቱንም በእጁ ያዘ፡፡ ለምርመራው የሚያወመቹ በርካታ ፍንጮችን ከእነበልሁ አግኝቷል፡፡ የምርመራው ሂደት በዚያው አቅጣጫ እንዲጓዝ አድርጎ እቅድና
ስልቱንም ቀይሶታል፡፡ ስለ አስቻለው ሁኔታ ታፈሡን በልዑንና መርዕድን ሲያነጋግር ባመሽበት ሶስተኛ ቀን ላይ ዓለሙ መርጋንና መብራቴ ባዩን ሁለቱንም በአንድ ጊዜ ከቢሮው አስቀረባቸውና «ልብ ብላችሁ አድምጡኝ» ሲል ሀምሳ አለቃ አስጠነቀቃቸው፥ ዓለሙና መብራቴ ከፊቱ ተቀምጠው የሚሆኑት ሁኔታ በራሱ ውስጣቸውን ያስነብበዋል።
«ሔዋን ተስፋዬ የምትባል ሴት ወዳጃችሁ እንደሆነች ቃል በሰጣችሁበት ወረቀት ላይ ፊርማችሁን አኑራችኋል ነው ወይስ እይደለም?» ሲል ጠየቃቸው።
👍12🔥1
#ምንዱባን


#ክፍል_አርባ_አራት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ

...እውነትም ቦታው እስትራቴጂካዊ ነበር በአንድ በኩል ወደቤቱ ሚያስገባው መንገድ ሰፊ ነው:: በጓሮ በኩል ቀደም ሲል እንደተገለጸው ቀጭን የጨለማ መንገድ አለው:: ማንኛውም አጥቂ ጦር በሴንት ዴኒስ
ጎዳና በኩል ባለው ሰፊ ጎዳና እንጂ በጓሮ በኩል ደፍሮ ሊገባ አይችልም::ስለዚህ የፊት ለፊቱን አጥብቀው ከያዙ የኋላውን በቀላሉ መመከት ይቻላል።
ድንገት ማፈግፈግም ቢመጣ በጓሮ በኩል የማምለጥ እድል አለ::

ያ ሁሉ ሕዝብ ሆ እያለ መለስ ሲል መንገዱ ሁሉ ጨነቀው::
ባለሱቅ ቶሎ ብሎ ሱቁን ዘጋ:: ከግራና ከቀኝ የነበሩ ሴቶች ሁሉ የውጭ በር ካላቸው የውጭ በራቸውን፣ አለዚያም የየቤታቸውን በርና መስኮት ቀረቀሩ፡፡ ለወሬ ሞትኩ ባይ መስኮቱን ከፍቶ በትንሹ ያያል፡፡ አላስችል
ያለውና «ምን ይቀርብኛል ብሎ ተስፋ የቆረጠው ከሰልፈኛው ጋር
ይደባለቃል፡፡

አንዲት በጣም የተደናገጠች አርጊት ምን አደረገች? ቶሎ ብላ አሮጌ ፍራሽ ከውጭ በኩል በገመድ በማንጠልጠል መስኮትዋን ሸፈነችው:: ሌላ
ፍራሽ ደግሞ ከውስጥ በኩል በማቆም ጋረደችው፡፡ ከዚያም ከመስኮቱ በር ወለል ላይ ለጥ ብላ ተኛች:: ጥይት ሲተኮስ እንዳይመታት ነበር፡፡

በዚያ አካባቢ በርና መስኮቱ የተከፈተ ቤት ሲኖር ያ መሸታ ቤትና ምግብ ቤት ብቻ ነበር:: ይሄ ደግሞ ያለ ምክንያት አልነበረም:: ትርምሱ፣ ጩኸቱ፣ ስድቡና
መዝሙሩ ድብልቅል ያለ ስለነበር የምጽዓት ቀን የመጣ
ስላስመሰለው ነው::

“ወያኔ ፣ ወይኔ፣ አምላኬ የዛሬን! ከዛሬው ብቻ ሰውረኝ» አሉ ማዳም ኻሽሉፕ ፡
ወዲያው በሃያ ደቂቃ ውስጥ ከሴትዮዋ መጠጥና ምግብ ቤት ምሽግ ተሠራ፡፡ በርሜሎች ተለቃቅመው በአሸዋና ጠጠር ተሞሉ፡፡ ጋብሮች በርሜል በማንከባለል ረዳ፡፡ በርሜል ሊሸፍነው ያልቻለውን ቦታ በአፈርና
በድንጋይ ቁልል ታጠረ፡፡ ኤንጂልራስ በጓሮው በኩል ወዳለው ጨለማ መንገድ የሚወስደውን በር ወለል አድርጎ ከፈተው:: ከዚያም ከቤቱ በር
ወደሚገኘው እቃ ማስቀመጫ ክፍል ወረደ:: ከምድር ቤቱ ውስጥ ወደሚገኘው ጥቂት በርሜሎችን አገኘ፡፡ እነርሱንም ለምሽግ ሥራ ተጠቀሙባቸው::መቼም እጅ ከተባበረ የማይሠራው ሥራ የለምና «ብዙ ቀናት ፈጅቷል
ተብሎ ሊገመት የሚችል ምሽግ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቀቀ፡፡ በዚያች አጭር ሰዓት ያ ቤት ከቡናና ምግብ ቤትነት ወደ ጦር ካምፕ ተሸጋገረ::

አንድ ጋሪ ሴቶችን ጭኖ በዚያ በኩል ለማለፍ ይመጣል፡፡ ከሰልፈኞቹ መሪ አንደኛው ሮጦ ሄዶ ባለጋሪውንና ሴቶችን ካስወረደ በኋላ ሴቶቹን
ከይቅርታ ጋር አሰናበታቸው:: የፈረሱን ልጓም ይዞ በመጐተት ጋሪውን ወደ ምሽጉ ወሰደው::

«ጋሪ ደግሞ በዚህ ሰዓት፣ በዚህ መንገድ ምን ያደርጋል?» ሲል
ጠየቀ፡፡ «ከአሁን ቀደም በዚህ መንገድ ጋሪ አልፎ አያውቅም» ብሎ ከተናገረ በኋላ ፈረሱን ከጋሪው አላቅቆ አባረረው:: ፈረሱ ከሄደ በኋላ ጋሪውን በጎን
በማጋደም ያንን መንገድ ለመዝጋት ተጠቀመበት::

ማዳም ኸሽሉፕ ተናደዱ፣ የሚያደርጉትን ስላጡ ከአንደኛው ፎቅ ቁጭ ብለው ቀሩ፡፡ ዓይናቸው ከወዲያ ወዲህ ይቅበዘበዛል፡፡ፀ ሳይታወቃቸው እንባቸው በጉንጫቸው እንደ ጎርፍ ይወርዳል፡፡ ድምፅ አሰምተው ለማልቀስ ተሰብረዋል
አልደፈሩም::

«ምፅዓት ነው ይሄ» ሲሉ አጉረመረሙ::

ከሰካራሙ አንደኛው መጥቶ ጉንጫቸውን ከሳመ በኋላ «መቼም
እንደ ሴት ጉንጭ የሚለሰልስ ነገር የለም» ይላል፡፡

ቫውደር የተባለች ሠራተኛ እነርሱ ከነበሩበት ክፍል ገባች:: ከሰካራሞች ሌላው በሳቅ እየተፍነከነከ የሴትዮዋን ጨርቅ በመጎተት ወደ መስኮት
ወሰዳቸው:: ወደ ጆሮአቸው ተጠግቶ አናገራቸው::
«ቫውደር እኮ በጣም ፉንጋ ናት:: መቼስ ለፉንጋዎች ምሳሌ ሆና |
ልትቀርብ የምትችል ናት:: »

ወዲያው ኤንጆልራስ ጮክ እያለ ተናገረ፡፡

«እናንተ ሰካራሞች የምሽጉን ስም አታጉድፉ:: ቶሎ እንዲበርድላቸው

ከዚህ ሂዱና ከምትተኙበት ተኙ፡፡ ይህ ሥፍራ በአገር ፍቅር ለነደዱ እንጂ ለሰካራሞቹ አይደለም

ከሰካራሞቹ ማለትም ብዙም ያልጠነበዘው በዚህ ስድብ
ከተሞላበት ንግግር ስሜቱ በጣም ስለተነካ ውሃ በጣሳ አንስቶ ፊቱ ላይ ቸለበሰ፡፡ የውሃው ቅዝቃዜ እውነትም ስካሩን ትንሽ አበረደለት:: ወደ መስኮቱ ሄዶ ኢንጆልራስን ጥያቄ ጠየቀው::

«ከዚሁ ልተኛ?»

የለም፣ ከምትተኛበት ሂድና ተኛ እንጂ ከዚህ መተኛት አይቻልም::»
«እባካችሁ ነፍሴ እስክትወጣ ከዚሁ ልተኛ» ሲል ሰካራሙ በለዘበ አነጋገር ተናገረ፡፡

ኢንጆልራስ በንቀት ዓይን አየው:: ሰካራሙም የሚባለውን ሳይሰማ
ጥቂት ከተንተባተበ በኋላ አጠገቡ ከነበረው ጠረጴዛ ላይ ጭንቅላቱን አስደግፎ ብዙም ሳይቆይ እንቅልፍ ይዞት ጭልጥ አለ፡፡ቸ

ዝናቡ ቆሞአል፡፡ ተጨማሪ ሰልፈኛ የተለያየ መሳርሪያ እየያዘ መጣ፡፡
በሩቁ የምትታይ አንዲት የመንገድ መብራት ብቻ ነበረች:: እስዋም ብዙ አልቆየችም፤ ሰልፈኞቹ ሰበርዋት:: የተቀሩት መብራቶች ቀደም ሲል
ተሰብረዋል፡፡

ኢንጆልራስ፣ ካምብፌራና ከርፌይራክ ለሰልፈኛው አመራር መስጠት ጀመሩ፡፡ መንገዱ በሁለቱም አቅጣጫ በምሽግ ተዘጋ:: የጦር መሣሪያ የያዙ
ሁሉ ቦታ ቦታቸውን ያዙ:: አንዳንዶቹ ቆብ መሳይ ነገር አጥልቀዋል::አንዳንዱ በአጭር ታጥቆ ጎራዴ ሲይዝ ሌላው ጠብመንጃ አንግቷል።
መሣሪያ ይዞ ፈረስ ላይ የተቀመጠም አለ፡፡ አንዳንዱ የመጨረሻው ሰው እስከቀረ ድረስ እንዋጋለን» እያለ ይፎክራል፡፡ ሌላው ጥይት ሲያልቅ
በድንጋይ እንማታለን» ይላል:: አንዱ ያቅራራል፣ ሌላው ይሸልላል::አንዳንዱም እነርሱ ሲጠቁ የከተማው ሰው እንደሚደርስላቻው እርስ በእርስ
ይወያያል፡፡ ሁሉም በየፊናው ይነጋገራል፤ ይቻኮላል፤ ሥራ ለመሥራትና ቦታ ለመያዝ ይጣደፋል፡፡ ሰካራሞቹና የቡና ቤቱ ባለቤት የሚያደርጉትን
አጥተው ከአንድ ክፍል ውስጥ ተፋጥጠው ቁጭ ብለዋል::
ከቁመቱ፡ ዘለግ ያለውና የሰልፈኛው መሪ የሆነው ሰው ከሰልፈኛው መካከል ገብቶ ምሽግ ይሠራል:: ጋብሮችም ከምሽጉ ጫፍ ላይ ከወዲያ ወዲህ ይሯሯጣል:: ማሪየስን የጠየቀውና ኩርፊያሪክን ጠብቀኝ
ያለው የሴት መልክ ያለው ግለሰብ ግን ከዚያ አልነበረም፡፡ ጋብሮትች
ከደስታው ብዛት ከወዲህ ወዲያ የሚለው እየዘፈነ ስለነበር አብዛኛው ሰልፈኛ ለይቶታል:: እንዲያውም ከነአካቴው ሰው ሁሉ የእርሱን ንቃትና ሞራል እያየ በጣም ተደፋፈረ፣ ሰነፉንና ዳተኛውን አነቃቃ:: ለፈሪውም
ልብ ዋጀለት። ለተደነባበረውም መንገድ ከፈተለት።

ጋብሮች ከአሮጊትዋ በነጠቀው ሽጉጥ ስላልረካ «ጠብመንጃ
እፈልጋለሁ፣ ምነው ብትሰጡኝ» እያለ ይጠይቃል::

«ጠብመንጃ ለአንተ ነው ወይስ ለማነው?» ሲል ካምብፌሪ ጠየቀው
«ምነው?» ሲል ጋብሮች ጥያቄን በጥያቄ ይመልሳል፡፡ «ምን ይጉድለኛል? ድሮ እኮ እንዴት ያለ ጠብመንጃ ነበረኝ» ሲል ይሸልላል::
ኢንጆልራስ ይስቃል፡፡
«አዋቂዎቹ ሲዳረሳቸው ለልጆች ይሰጣል::»
ጋብሮች በቁጣ ዞር ብሎ ይመልሳል፡፡
«አንተን ከእኔ በፊት ከገደሉህ እኔ እኮ ነኝ አንተን የምተካው:: ላከወ
«ጉረኛ» ሲል በቀልድ መልክ ኢንጆልሪስ መለሰለት::

«ጉረኛ አልከኝ?» ሲል ጋቭሮች ቃሉን ደገመ:: ይህን እንደጠየቀ
አንድ ሰው ከሰልፉ ወጥቶ ያያል:: ሮጦ ሄዶ «ከሰልፈኛው ተለይተው
አይሄዱ፤ ለዚህች ምስኪን አገር የሚውሉት ውለታ ቢኖር አሁን ነው፤ ስለዚህ አይሂዱ» ሲል ይማጠናቸዋል፡፡ ሰውየው ግን ፈጠን ብለው በመራመድ
ይሄዳሉ፡፡
👍12
#የጣሪያ_ስር_አበቦች


#ክፍል_አርባ_አራት


#ትርጉሜ_ሀኒም_ኤልያስ


በፍሎሪዳ ወርቃማ የፀሀይ ብርሃን ውስጥ ደስተኛ ህይወት እንደሚኖረን ያቀድነውን እቅድ በቀስታ እየነገርኳት ነበር።

ክሪስ ልብሶቹን በደንብ ለብሶ በሚወዛወዘው ወንበር ላይ የኮሪን ጊታር እየነካካ ተቀምጧል። በቀስታ እያንጎራጎረ ነበር፡ ድምፁ መጥፎ አይደለም: ምናልባት ኬሪ ተሽሏት እንደገና እንደበፊቱ ከሆነች ሶስታችን አብረን ሙዚቀኞች እንሆን ይሆናል።

እጄ ላይ ያሰርኩት ስዊዘርላንድ ውስጥ የተሰራ ባለ ሀያ አራት ካራት የወርቅ
ሰዓት አለ። መቼም እናታችንን ብዙ ገንዘብ ሳያስወጣት አልቀረም፤ ክሪስም ሠዓት አለው ጊታር አለን፣ የክሪስ ካሜራና የውሀ ቀለሞችም አሉ… ስለዚህ እነሱን መሸጥ እንችላለን በዚያ ላይ አባታችን ለእናታችን ሰጥቷት የነበሩት
ቀለበቶችም አሉ።

ነገ ማለዳ የማምለጫ ቀናችን ሆኖ ተይዟል ግን የሆነ አስፈላጊ ነገር የረሳሁ
እንደሆነ አድርጌ የማስበው ለምንድነው?

ከዚያ ድንገት የሆነ ነገር አስተዋልኩ! እኔም ክሪስም ችላ ያልነው ነገር አያትየው የተዘጋውን በር ከፍታ እኛ ሳናያት በፀጥታ መቆም ከቻለች ሌላም ጊዜ እንደዚህ ታደርግ ይሆን? የምታደርግ ከነበረ አሁን እቅዳችንን አውቃ ሊሆን ይችላል። የእኛን ማምለጥ ለማስቆም የራሷን አቅድ አዘጋጅታ ሊሆን
ይችላል!

ይህንን መናገር ይገባኝ እንደሆን እያሰብኩ ወደ ክሪስ ተመለከትኩ አሁን
በማመንታት እንድንቆይ ምክንያት አልፈልግም: ስለዚህ ጥርጣሬዬን
ነገርኩት። ምንም ሳይረበሽ ጊታሩን መነካካቱን ቀጠለ “እሷን ባየሁበት ደቂቃ
ያ ሀሳብ አእምሮዬ ውስጥ ብልጭ ብሎ ነበር።” አለኝ: “ያንን ጆን የተባለ
ሠራተኛ ልትተማመንበት እንደምትችል አውቃለሁ። እንዳናመልጥ በማሰብ
ደረጃው ላይ እንዲጠብቀን ልታደርግ ትችል ይሆናል። ተይው ይሞክር! ምንም ነገር ሆነ ማንም ነገ ጠዋት ከመሄድ አያቆመንም!”
የአያትየውና የሰራተኛው ደረጃው ስር የመጠበቅ ሀሳብ ሰላም ሊሰጠኝ
አልቻለም። ኬሪ አልጋው ላይ እንደተኛች ክሪስም የሚወዛወዘው ወንበር ላይ
ተቀምጦ ጊታሩን እየነካካ ትቻቸው ለመሰናበት ጣሪያው ስር ወዳለው ክፍል ወጣሁ።

በሚወዛወዘው አምፑል ስር ቆሜ ዙሪያውን ተመለከትኩ፡ ሀሳቤ ወደዚህ ወደመጣንበት የመጀመሪያ ቀን ተጓዘ... እኛን... አራታችንን. እጅ ለእጅ
እንደተያያዝን ግዙፉን የጣሪያ ስር ክፍልና ውስጡ ያሉትን ጣዕረሞት
የሚመሳስሉ እቃዎቹን በመገረም ዙሪያውን ስንመለከት፣ ክሪስ ለመንትዮቹ ዥዋዥዌ ለመስራት ራሱን አደጋ ላይ ሊጥል የነበረበትን ሁኔታ በሀሳቤ ተመለከትኩ ከዚያ ወደ መማሪያው ክፍል ገብቼ መንትዮቹን አስቀምጠን
የነበረውን በሀሳቤ እየተመለከትኩ ሳለ ክሪስ በደረጃው በኩል ተጣራ ካቲ
መሄጃችን ደርሷል።"


ማንበብና መፃፍ ያስተማርንባቸውን መቀመጫዎች አየሁ። ብቻዬን ስደንስ

ፈጠን ብዬ ወደ መማሪያ ክፍሉ ተመለስኩና በጥቁር ሰሌዳው ላይ በጠመኔ
በትልልቁ እንዲህ ብዬ ጻፍኩ…

ጣራው ስራ ባለው ክፍል እንኖር ነበር።

እኔ፣ ክሪስቶፈር፣ ኮሪና ኬሪ።

አሁን ሶስት ብቻ ነን።

ከዚያ ስሜንና ቀኑን ፃፍኩ። በልቤ የአራታችን መንፈስ ከዚህ ጣራው ስር
ያለው መማሪያ ክፍል ውስጥ ተዘግቶባቸው የነበሩ የሌሎች ልጆችን መንፈስ እንደሚበልጥ አውቃለሁ የሆነ ሰው ወደፊት እንዲፈታው አንድ እንቆቅልሽ ትቻለሁ።

የሞተውን አይጥ ከሁለቱ የተመረዙ ዶናቶች ጋር ኪስ ወረቀት ውስጥ ከትተን ክሪስ በኪሱ እንዲይዘው ተደረገ፡ ከእንጨት በተሰራው ቁልፍ የእስር
ቤታችንን በር ለመጨረሻ ጊዜ ከፈተ። አያትየውና ሠራተኛው ታች እየጠበቁን
ከሆነ እስከሞት እንታገላለን ክሪስ ልብሶቻችንና ዕቃዎቻችን የተሞሉባቸውን
ሁለት ሻንጣዎች ያዘ ትከሻው ላይ ደግሞ የኮሪን ጊታር አንጠለጠለ፡ ጨለም
ባለው አዳራሽ ውስጥ እየመራ በጀርባ ወዳለው ደረጃ ወሰደን። ኬሪ በከፊል
እንደተኛች አቅፌያታለሁ ትንሽ ከበድ ትላለች። ነገር ግን ከሶስት አመታት
በፊት በእነዚህ ደረጃዎች ላይ ተሸክሜያት ስወጣ ከነበራት ክብደት ምንም
ያህል አልጨመረችም። ወንድሜ የያዛቸው ሁለቱ ሻንጣዎች ልጆች ሳለን
በጣም አፍቃሪና ሰውን የምናምን በነበረበት ወቅት፣ ከረጅም ጊዜ በፊት በዚያ
ቀፋፊ ምሽት እናታችን ያሸከመችን ሻንጣዎች ነበሩ።

በልብሶቻችን ስር በሁለት ትንንሽ ቦርሳዎች ከእናታችን የሰረቅናቸውን ገንዘቦች
እኩል ለእኩል ተከፋፍለን ይዘናል የተካፈልናቸው ምናልባት የሆነ ነገር
ተፈጥሮ እኔና ክሪስ ብንለያይ አንዳችን ባዶ እጃችንን እንዳንቀር ለማድረግ ነበር። ኬሪ ደግሞ በእርግጠኝነት ከአንዳችን ጋር ትሆናለች በሁለቱ ሻንጣዎች
ውስጥም እንደዚሁ ሳንቲሞቹን እኩል ቦታ ከፍለን በሁለት ቦርሳዎች ውስጥ አድርገናል

እኔና ክሪስ ሁለታችንም ውጪ ምን እንደሚጠብቀን አውቀናል። ረጅም ጊዜ ቴሌቭዥን ማየታችን የዋህና ምንም ለማያውቁ ሰዎች የአለም ጨካኝ
ውሸቶች እንደሚጠብቋቸው አስተምሮናል። ልጆች፣ ተጠቂዎች፣ ደካሞችና
በከፊል የታመምን ነን ነገር ግን ከአሁን በኋላ የዋህ ወይም ምንም የማናውቅ
አይደለንም።

ክሪስ የጀርባውን በር እስኪከፍት ስጠብቅ የሆነ ሰው ሊያስቆመን እየመሰለኝ በእያንዳንዷ ሰኮንድ በፍርሀት ልቤ ቀጥ ብላ ነበር። ወደ እኔ ዞር ብሎ ፈገግ እያለ ወደ ውጪ ወጣ:

ውጪው ይበርዳል። መሬቱ ላይ እየቀለጠ ያለ በረዶ ይታያል: ግራጫው
ሰማይ በረዶ እንደገና ሊጥል እንደሆነ ይጠቁማል ቢሆንም ግን ጣራው ስር
ካለው ክፍል በላይ አይቀዘቅዝም፡ መሬቱ ከእግራችን ስር ያሙለጨልጫል።
ለብዙ አመታት ጠንካራና የተስተካከለ የእንጨት ወለል ብቻ ረግጠን
የምናውቅ በመሆኑ፣ መሬት ላይ መራመድ እንግዳ ስሜት አሳድሮብናል።
ደህንነት አልተሰማኝም: ምክንያቱም ጆን ሊከተለንና ሊመልሰን ይችላል
ወይም ይሞክራል ብዬ ፈርቻለሁ።

ንፁሁንና ጠንካራውን የተራራ አየር ለመሳብ ጭንቅላቴን ቀና አደረግኩ።
ትንሽ እስክንሄድ ድረስ ኮሪን አቅፌያት ነበር። ከዚያ በእግሮቿ አቆምኳት።
እርግጠኛ ባለመሆን እየተንገዳገደች ዙሪያውን አማተረች: ግራ የተጋባችና
የተገረመች ትመስላለች።
ትንሽና ቆንጆ ቅርፅ ያላትን የቀላች አፍንጫዋን ጠረገች። አምላኬ! ብርድ
ያማት ይሆን? ካቲ…” ሲል ክሪስ ተጣራ። “ሁለታችሁ መፍጠን አለባችሁ!
ገና ረጅም መንገድ ከፊታችን ስላለ ኬሪ ከደከማት እቀፊያት” አለ፡ ትንሽዬ እጇን ይዤ እጎትታት ጀመር። “ኬሪ ጥልቅና ረጅም ትንፋሽ ውሰጂ!
ሳታውቂው ንፁህ አየር፣ ጥሩ ምግብና የፀሀይ ብርሃን እንደገና ጠንካራና
ደህና ያደርግሻል:” አልኳት

ትንሽዋን የገረጣችውን ፊቷን ወደ እኔ ቀና አደረገች: በመጨረሻ ያቺ ተስፋ
አይኖቿ ውስጥ አንፀባረቀች: “ኮሪን ልናገኘው ነው?"

የኮሪን መሞት ካወቅንበት አሳዛኝ ቀን በኋላ የጠየቀችው የመጀመሪያ ጥያቄ ነው። የውስጥ ፍላጎቷ ኮሪ መሆኑን ስለማውቅ አተኩሬ ተመለከትኳት የተስፋ ብልጭታዋን ላጠፋባት ስላልፈለግኩ አይደለም ማለት አልቻልኩም
ኮሪ ከዚህ በጣም በጣም ሩቅ ቦታ ነው ያለው: አባታችንን የሚያምር
የአትክልት ቦታ ውስጥ አየሁት ብዬ ሳወራ አልሰማሽኝም? አባታችን ኮሪ እንዳቀፈውና አሁን እሱ እየተንከባከበው እንደሆነ ስናገር አልሰማሽም እነሱ እዚያ እየጠበቁን ነው: አንድ ቀን እንደገና እናገኛቸዋለን፡፡ ግን በቅርብ አይደለም" አልኳት።
👍43😢13🥰61🔥1
#ሳቤላ


#ክፍል_አርባ_አራት


#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ

አንዳፍታ ወደ ሳቤላ እንመለስ ዓመቱ እየተዋግደ ሲሔድ እሷም እየበረታች
እየተሻላት መጣች የበጋው መገባደጃ ሲቃረብ ግረኖብልን ለመልቀቅ ተዘጋጀች መኖሪያዋን የት እንደምታደርግ ወይም ምን እንደምትሠራ ግን አላወቀችም ከሥቃይዋ ብርታት ከኀዘኗ ብዛት ከጸጸቷ ጥናት የተነሣ በራሷ ላይ ሊደርስባት ስለሚችል ነገር ማሰቡን ትተዋለች የመጣው ቢመጣባት ግድ አልበራትም እንደምኟቷማ እጅግ ከራቀው የዓለም ዳርቻ የሠለጠነ ሰው ያልረገጠው ትንሽ ሥፍራ
ብታገኝ ትወድ ነበር ። ግን እንደዚህ ያለ ቦታ እንዴት ታግኘው ?

ሱዛን ግሮኖብል ውስጥ ፍቅረኛ አበጀችና ከዚያ ለመልቀቅ አልፈለገችም
ስለዚህ ሳቤላ በሷ ምትክ አንዲት ልጅ እግር ገጠሬ በሞግዚትነት ቀጥራ ልጅዋን ይዛ የሚስማማትን ፍለጋ ተነሣች በግድ ከሚያስፈልጓት ነገሮች በቀር የነበራትን ዕቃ በሙሉ እሷ ሌላ ትእዛዝ እስክትሰጥ ድረስ ከመጋዘን እንዲቀመጥ አስቀድማ
ወደ ፓሪስ ልካዋለች ከግረኖብል ስትወጣ ቀኑ በጣም ደስ የሚል ነበር ።
መምሸት ጀምሮ ለዐይን እስኪይዝ ድረስ ሳቤላ አንድ ሁለት ቀን ልታድርበት አስባው ከነበረው ካመር ከተባለው ቦታ እስኪጠጋ ድረስ ባቡሩ በደኅና ተጓዘ የፈረንሳይ የባቡር አደጋዎች የእንግሊዝ አገርን ያህል አይበዙም እንጂ ኑረው ኑረው ሲደርሱ ግን የሚያስከትሉት ጉዳት ለጆሮ የሚቀፍ ነው። ትዝታው እስከ ዕድሜ ልክ ከአእምሮ አይጠፋም ። ባቡሩ ከጣቢያው ሊደርስ ጥቂት ሲቀረው የምጽአት ቀን የመሰለ ድንገተኛ ግጭትና ነወጥ ደረስ የባቡሩ ሠረገላዎችና መንገደኞች አንድነት ተደባልቀው ከአንድ ትልቅ ግድብ ሥር ወደቁ።

እየከበደ የመጣ ጨለማ አሠቃቂውን ሽብርና ድብልቅልቅ አባባሰው ። ሳቤላ ከልጅዋና ከሠራተኛዋ ጋር የተሳፈሩበት የባቡር ሠረገላ በብዙ ናዳና ስብርባሪ ሥር ወደቀ " ሦስቱም በብዙ ድካም ከተዳፈኑበት ተፈልገው በመጨረሻም ከወጡት መንገደኞች ውስጥ ነበሩ ምስኪኑ ሕፃንና ሞግዚቱ ሙተው ተገኙ ሳቤላ ግን አልሞተችም እንዲያውም በደንብ ነፍሷን ታውቅ ነበር ባስቸኳይ ተጠርተው የመጡ የሕክምና ሰዎች ካዬዋት በኋላ እሷ እግሯን ብትቆረጥ እንኳን እንደማትርፍ ሌላ ሕክምናም ሊደረግላት እንደ
ማይችል ቀዶ ጥገና ደደደ ዳ መሞቷ ዴ ዳዳደ
ሰማቻቸው ከሷ የተሻለ ተስፋ የነበራቸው ሥቃይተኞችን ለመርዳት ጥለዋት ሲሔዱ አየቻቸው ጉዳቷ ከፊቷ የታችኛው ክፍልና አንድ እግሯ ላይ ነበር ከደረሰባት የኑሮ ሥቃይ ለመላቀቅ ብዙ ጊዜ ሞትን ተመኝታለች።ነገር ግን እንደዚህ የመሰለ አስጨናቂ ሥቃይ አስከትሎ ይመጣል ብላ አላሰበችውም መንቀሳቀስ አትችልም የደረሰባት ከባድ ነውጥ ስሜቷን አደንዝዞታል ሕመም ገና አልተሰማትም ከሁሉ የሚያስደንቀው ግን አእምሮዋ ዝንፍ አላለም ላጭር ጊዜ አስተካክላ ማዳመጥና መመለስ ትችል ነበር አንዲት የበጎ አድራጎት ገዳም አባል የሆነች መነኰሲት ሳቤላ ወደተኛችበት የቁስለኛ ማንሻ አልጋ ተጠግታ ውሃ
ሰጠቻት ሳቤላ ተቀብላ ልክክ አድርጋ ጠጣችው

“ ሌላ የማደርግልሽ ነገር የለም ? ” አለች መነኩሴይቱ

ሕፃኑ ልጄና ሞግዚቱ አብረውኝ ተሳፍረው ነበር ። ተገኝተው እንደ ሆነ ልጄም ሞቶ እንደሆነ ንግሪኝ
መነኩሲይቱም በዚያ ሁሉ ግርግርና ጩኽት መኻል ፍለጋ ሔደች። የአንድ ሕፃን አስከሬን ሳቤላ ከነበረችበት ብዙም ሳይርቅ ከባቡር ጣቢያው መጠለያ አኑረውት አገኘች ቀስ አድርጋ አንሥታ ወሰደችውና “ልጅሽ ይኸ ነው ? አለቻት።

ያ ያልታደለው የሳቤላ ልጅ ነበር ። ትንሿን ፊቱን ከደረቷ እቅፍ አደረችና በመጀመሪያ ወደፊት ከሚጠበቀው አሰቃቂ ኑሮ አስቀድሞ በመላቀቄ ከልቧ አመሰገነች እሷም ከጥቂት ሰዓቶች በኋላ እንደምከተለው ታወቃት ስለዚህ ሞት ሲመጣ ብዙ ጊዜ
እንደሚከሰተው ሁሉ ከዚህ ዓለም ሕይወት ጋር የተያያዘውን ጥሪት ቸል የሚላት ስሜት ቀስ በቀስ ተዳደራት “ድሮውንም ልመኝለት የሚገባኝ እንዲህ ሆኖ እንዲገላገል ነበር ” ብላ እንድታነሣው ምልክት ሰጠቻት "

ያቺ ደግ መነኩሲት ሐኪሞች ስለ ቁስለኛይቱ የተናገሩትን ሰምታ ስለ ነበር
“ምናልባት ለዘመድ ወዳጆችሽ የምታስተላልፊው መልእክት ቢኖርሽና የምታምኚኝ ከሆነ ፍላጐትሽን እፈጽማለሁ ከኋላ ለሚቀሩ ሰዎችሽ የምትተይላቸው መልክት
ካለሽ አሁን አእምሮሽ እንደ ተስተካከለ አንደበትሽ ሰልቶ ሳለ ብትነግሪኝ ጥሩ ነው ' አለቻት ።

“ እኔን የሚያውቁ ሁሉ መሞቴን ሲሰሙ ደስ ይላቸዋል " ከኀዘንና ከኃፍረት ለከተትኩዋቸው ዘመዶቼ የምሰጣቸው ካሳ ሞቴን ብቻ ነው " እኔ ከባድ በደለኛ ነበርኩ ”

“ሞትን እንደ በደል ዋጋ አድርገሽ ለመቀበል ሞክሪ መከራዎቻችንም እንደ ደስታዎቻችን ተሰጥዋችን ናቸውና።

“እሺ እርስዎ እንደሚሉኝ አደርጋለሁ ” አለች ሳቤላ ሕመሙ ሊሰማት ስለ
ጀመረ ድምጿ ድክምክም እያለ

"ንገሪኝ ለምትፈልጊው ልጻፍልሽ"

ወረቀቱን ከያዙልኝ ሐሳቤም ግልጽ እጆቼም ደህና ስለሆኑ እኔ ልሞክረው
እችላለሁ ስትላት መነኩሲቱ እንዳለቻት አመቻችታ ያዘችላት " መጀመሪያ አድራሻውን ለሎርድ ማውንት እስቨርን በማድረግ እንደ ተጋደመች ጥቂት ቃላት መሞነጫጨር ጀመረች በባቡር አደጋ ምክንያት በደረሰባት ከባድ ጉዳት ከሞት አፋፍ መሆንዋን ልጂዋና ሞግዚቷ መሞታቸውን ጻፈች ሎርድ ማውንት እስቨርን ለዋለላት በጐ ተግባር ሁሉ አመሰግና ለሱና ለሌሎችም ወገኖች ሁሉ ማፈሪያ ከምትሆንባቸው ሙታ ማረፉን እንደምትወድ ገለጸችለት "

ሚስተር ካርላይል ዘንድ ሒድና ብላ በመቀጠል “ ይቅር እንዲለኝ በትሕትና መለመኔን ንገረው እንደዚሁም ልጆቼ አድገው ምን ያህል እንደ በደል
ኳቸው ሲያውቁ እንዳይረግሙኝ ይቅርታቸውን መለመኔን ንገረው በራሴ ማዘኔን እርር ድብን ብዬ ስሜቴን የምገልጽበት ቋንቋ እስኪያጥረኝ ድረስ መጸጸቴን ንገረው ብላ ከጻፈች በኋላ የሕመሙ ሥቃይ ጀመራትና እያባሰባት ሔደ እንደ ምንም ብላ ተጠናክራ“ ሳቤላን ይቅር በልዋት ብላ ሞጭራ ስታበቃ “ይበሉ
እንግዲህ ከሞትኩ በኋላ በፊት አይደለም ጥቂት የማረጋገጫ ቃላት ጨምረው ይላኩት ”
አለቻት

ኋላ ቆይተው ሳቤላ የደረሰባትን ጉዳት ምንና ምን ያህል እንደሆነ በዝርዝር ለመመርመር የቀዶ ጥግና ሐኪሞች በመጨረሻ ሲመጡ ፈጽማ ነፍሷን ስታ አገኟት ስለዚህም መሞቷን አምነው ይኽንኑ ከጐኗ ተንበርክካ ከሥጋዋ ለምትለየው ነፍስ
ስትጸልይላት ለነበረችው መነኰሲት ነገርዋት ጸሎቷን ጨርሳ እርዳታዋን ወደ ሚያስፈልጋቸው ወደ ሌሎች ቁስለኞች ሔደች "
ከዚያ በኋላም ሞታለች ብላ
ወደ ሳቤላ አልተመለሰችም " ደብዳቤውንም እንደ ነገረቻት የማረጋገጫ ቃላት ጨምራ ላከችው። የሞቱት ተቀበሩ ከሞት የተረፉት ቁስለኞች ወደ ሆስፒታል ተላኩ

ሳቤላ ቀስ በቀስ ነፍሷን አወቀች ከአንድ ሆስፒታል መደዳ ክፍል ከአንድ
አልጋ ብጤ ርብራብ ላይ መተኛቷንም ተረዳች የደረሰባትን ነገር ስታስታውስ አለመሞቷንም ሳታረጋግጥ ብዙ ጊዜ ቆየች ሐኪሞቹም እየቆየ ባደረጉት ምርመራ የተሰባበረው ሰነቷ ነፍስ እንዳልተለየው ተገነዘቡ ለሞት ባያደርስም ጉዳቱ ግን ከባድና የመዳኑም ተስፋ የመነመነ መሆኑን አዩ ከነበረችበት አሥጊ ሁኔታ
የሚያበረታታ ውጤት ማየት ጀመሩ ሳቤላ አሁንም ገና በሕይወትና በሞት መካከል ብቅ እልም ስትል ቆየችና ቀስ በቀስ ሕይወት እየዘራች ሔደች ከአደጋው ጀምሮ እስከ ሦስት ወር ድረስ የነበረችበት ሁኔታ ከሞት ያልተሻለ ነበር" ምንምን
ብሎ ከስቶ ገርጥቶ : የወላለቀው ሰውነት የሳቤላ ቬን ነው የሚል አይገኝም ነበር"
👍19
#ጠላፊዎቹ


#ክፍል_አርባ_አራት


#በኬንፎሌት


#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ


አይሮፕላኑ ወደ ማረፊያው ሼዲያክ ቤይ ለማረፍ እየወረደ እያለ ሄሪ የሌዲ ኦክሰንፎርድን ጌጣ ጌጦች መስረቅ ወይም አለመስረቅ ሃሳቡን እልባት ለመስጠት ተቸግሯል፡ ጌጡን ለመስረቅ የነበረው ጉጉት በማርጋሬት
ምክንያት ቀንሷል፡ ቦስተን ይዟት ሄዶ ቤት ተከራይቶ እየኖሩና ራሷን እንድትችል እየረዳት በ ይበልጥ ከእሷ ጋር ሊላመድ ይፈልጋል፡ ደስታዋ ያስደስተዋል፡ ቀለል ያለ ኑሮ ለመኖር ያላትን ጉጉት ይጋራል፡

እናቷን ከዘረፈ ግን ይህ ሁሉ ያከትመለታል፡፡
በአንጻሩ ኒውዮርክ ከመድረሳቸው በፊት የመጨረሻ ማረፊያቸው ከተማ ሼዲያክ ስለሆነ በዚህ ጉዳይ ላይ ቶሎ መወሰን አለበት፡ ሻንጣ   ክፍሉም የመግባት የመጨረሻ ዕድሉ ይሄ ብቻ ነው፡

ማርጋሬትንም ዕንቁውንም በእጁ ማድረግ የሚችልበትን መንገድ እያሰበ ነው፡ በመጀመሪያ ዕንቁው ቢጠፋ እሱ የሰረቀ መሆኑን ታውቅ ይሆን? ሌዲኦክፎርድ  ዕንቁው መጥፋቱን የሚያውቁት ኒውዮርክ ከደረሱ በኋላ
ልዶርፍ አስቶሪያ ሆቴል ውስጥ ሻንጣቸውን ሲከፍቱ ነው: ዕንቁው 'የጠፋው አይሮፕላኑ ውስጥ፣ በፊት ወይም በኋላ መሆን አለመሆኑን ማንም
አያውቅም፡፡ ማርጋሬት ሄሪ ሌባ መሆኑን ስለምታውቅ እሱ ነው የሰረቀው
ብላ ትጠረጥር ይሆናል። እኔ አልሰረቅሁም ቢላት ታምነዋለች? ታምነው
ይሆናል።

ከዚህ በኋላስ? እሱ ባንክ ውስጥ አንድ መቶ ሺ ዶላር ወሽቆ በድህነት ይኖራሉ! በዚህ አይነት ብዙ ዓመት ሊገፉ አይችሉም፡፡ ወደ እንግሊዝ አገር ትመለስና ሴት ወታደሮችን ትቀላቀላለች፡ ሄሪ ደግሞ ካናዳ ሄዶ የአየር
ኃይል ፓይለት ይሆናል፡፡ ጦርነቱ ሲያበቃ ገንዘቡን ከባንክ ያወጣና መኖሪያ
ቤት ይገዛል፧ እሷም አሜሪካ ትመጣና አብረው መኖር ይጀምራሉ፤ አብረው
ሲኖሩም ይህን ሁሉ ገንዘብ ከየት እንዳመጣ ትጠይቀዋለች።
የሆነውን ሁሉ ወዲያው ወይም ቆይቶ ይነግራት ይሆናል፡ በኋላ ቢነግራት ነው ግን የሚሻለው፡፡

አይሮፕላኑ ሼዲያክ ላይ ሲያርፍ ሁሉም ሲወጡ እሱ የሚቆይበትን ምክንያት መንገር አለበት፡፡ አመመኝ ቢላት አብሬህ እሆናለሁ የምትለው በመሆኑ ሁሉም ነገር ተበላሸ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ከሰዎቹ ጋር ወጥታ
መሄዷን ማረጋገጥ አለበት፡
ሄሪ ማርጋሬትን አሻግሮ ያያታል፡፡ የመቀመጫ ቀበቶዋን እያጠበቀች
ነው፡ በዓይነ ህሊናው ደግሞ ራቁቷን ሆና አጎጠጎጤዋ ፈጦ ወጥቶ እና እግሮቿ ከፈት ብለው ብልቷ ዙሪያ ያከፈከፈው ጸጉር ይታየዋል፡፡ ይችን
የመሰለች ቆንጆ ለዕንቁ መለወጡ ጅል የሆነ አያስመስለውም? ታዲያ

እነዚህን ዕንቁዎች መተው ማለት ዘወትር የሚመኘውን የባለጸጋ ኑሮ ሊያደርግ ያሰበውን ነገር ነገራት እንበል፡፡ የናትሽን ዕንቁ ብሰርቅ ምን ይመስልሻል? ቢላት ጥሩ ሃሳብ ነው፤ ይቺ አሮጊት እነዚህ ዕንቁዎች
አይገቧትም ብላ እንደማትመልስለት  ያውቃል፡ በፖለቲካ  አመለካከቷ ተራማጅ  በመሆኗ በፍትሃዊ ክፍፍል ታምናለች፡፡ ይሄ ደግሞ በጽንለ ሃሳብ ደረጃ ነው፡፡ ሄሪ እናትና አባቷ ያላቸውን አንድ ዕንቁ ቢወስድባቸው በጣም በጣም ትበሳጫለች በዚህም ምክንያት ለእሱ ያላት ፍቅር ሁሉ ይተናል።

ይህን በአዕምሮው ሲያሰላስል ከእሷ ጋር ዓይን ላይን ግጥም አሉና
ፈገግ አለች፡ እሱም በእፍረት ፈገግ አለና ፊቱን ወደ መስኮቱ አዞረ፡፥

አይሮፕላኑ ባህር ዳርቻው ላይ ለማረፍ ዝቅ እያለ ነው። ዙሪያዋን የተበታተኑ መንደሮች የተገጠገጡ ሲሆን ከመንደሮቹ ጀርባ የእርሻ ቦታ ይታያል፡ ወደ ማረፊያቸው እየተጠጉ ሲመጡ በመንደሮቹ መሃል እንደ እባብ እየተሹለከለከ እስከ ወደቡ የተዘረጋው የባቡር ሃዲድ ከሩቅ ተለይቶ
ይታያል በባህሩ ዳርቻ ላይ በርካታ መርከቦችና አንድ የአየር በራሪ ጀልባ መልህቃቸውን ጥለዋል።ከወደቡ በስተምስራቅ እዚህም እዛም የበጋ መዝኔኛ
ቤቶች ፈንጠቅጠቅ ያሉበት አሸዋማ የባህር ዳርቻ ይታያል፡ ሄሪ እንደዚህ
ያለ የበጋ መዝናኛ ቤት እንዲኖረው ይፈልጋል፡፡ ይህንንማ በእጄ ካላስገባሁ
ሞቻለሁ! ሀብታም እሆናለሁ› ሲል በሆዱ ተመኘ፡፡

አይሮፕላኑ ባህሩ ዳርቻ ላይ በሰላም አረፈ፡ ሄሪ አሁን ተረጋግቷል፡ በአይሮፕላን መብረርንም ተላምዷል፡
‹‹ስንት ሰዓት ነው?›› ሲል ሄሪ ፔርሲን ጠየቀው፡
‹‹ብአገሩ ሰዓት አቆጣጠር ከቀኑ አምስት ሰዓት ነው፡፡ አንድ ሰዓት ዘግይተን ነው የደረስነው››

‹‹ሼዲያክ ላይ ስንት ሰአት እንቆያለን?››

‹‹አንድ ሰዓት››

ሄሪ ማርጋሬት ቀድማ እንድትሄድና ከጥቂት ጊዜ በኋላ እንደሚከተላት
ይነግራታል እሷም ካንተ ጋር እቆያለሁ ብላ እንደማታስቸግር ገምቷል፡፡
አንድ አስተናጋጅ የአይሮፕላኑን በር ሲከፍት ተሳፋሪዎች ልብሶቻቸውን
ደረቡ: የኦክስንፎርድ ቤተሰብ ከአይሮፕላን ለመውጣት ተነሳ፡፡ እስካሁን
አፉን ለጉሞ የቀረው ክላይቭ መምበሪም ከመቀመጫው ተነሳ፡
ማርጋሬትን ‹‹አንቺ ሂጂና እኔ እከተልሻለሁ›› አላትና ወደ መጸዳጃ ቤት ሄደ።

ሰው እስኪወጣ የሆነ ነገር ልስራ ብሎ ጸጉሩን አበጣጠረ እጁንም ታጠበ፡፡ አንድ የአይሮፕላኑ ሰራተኛ በደረጃው ወርዶ አልፎ ሲሄድ አየ፡፡
ሰዓቱን አየና ተጨማሪ ሁለት ደቂቃ ለመጠበቅ ወስነ፡፡ሁሉም ወጥተው እንደሆነ ለማየት ዙሪያ ገባውን አማተረ፡፡ ቦትውድ ላይ ሁሉም አሸልበው  ነበር
አሁን ግን ብዙዎቹ እግሮቻቸውን ለማፍታታተና ንጹህ አየር ለመቀበል እየወጡ ነው፡፡ ኦሊስ ፊልድና እስረኛው እስካሁን ሲያደርጉ እንደነበረው አይሮፕላኑ ላይ ይቆያሉ፡፡
መምበሪ ፍራንኪን እንዲጠብቅ የተመደበ ከሆነ ከአይሮፕላኑ ወጥቶ መሄዱ እንግዳ ነገር ነው፡፡ ሄሪን አሁንም ግርምት ውስጥ የከተተው ሙሉ ልብስ የለበሰው ሰው ነው።
ቲም ሉተር።

የጽዳት ሰራተኞች ወዲያውኑ እየተግተለተሉ መምጣታቸው አይቀርም
ብሎ ጆሮውን ቀስሮ አዳመጠ፡፡ በበሩ በኩል የሚመጣ ድምጽ የለም፡፡ በሩን ትንሽ ከፈት አደረገና አየ፡ ምንም ነገር አለመኖሩን አረጋገጠና ኮቴ ሳያሰማ ወጣ።

ከወጣበት በር ትይዩ ኩሽና ያለ ሲሆን ሰው የለበትም፡፡ ወደ ሌላው የአይሮፕላኑ ክፍልም ዘው ሲል የሰው ዘር አይታይም ወደ ሳሎኑ ሲገባ መጥረጊያ የያዘች ሴት ጀርባዋን ሰጥታው ቆማለች፡፡ ደረጃውን ወጣ፡፡
Lያለምንም መጠራጠር ኮቴ ሳያሰማ ደረጃውን ቀስ ብሎ ወጣ፡፡ ደረጃው መጠምዘዣ ላይ ሲደርስ ቆም አለና ዓይኑን ወረወረ፡ ማንም የለም ወደፊት ሊሄድ ሲል አንድ ሰው ደረጃው ስር ሲሄድ አየና ከመቅጽበት
ኮሪደሩ ላይ ልጥፍ ብሎ ዓይኑን አጮልቆ ሲያይ ባለፈው ጊዜ ሻንጣ
ሲበረብር ያየው ሚኪ ፊን ነው፡፡ ሰውየው የበረራ መሃንዲሱ ቦታ ሲደርስ
ዞር ብሎ አየ፡፡ ሄሪ በዚህ ጊዜ እንዳይታይ ግድግዳው ላይ ልጥፍ አለና አዳመጠ፡ ይሄ ሰው የት ነው የሚሄደው? ሲል መልስ
የሌለው ጥያቄ ጠየቀ የሰውየው ኮቴ እየራቀ ሲሄድ ጸጥታ ሰፈነ፡፡

በደረጃው ወጣ፡፡ ደረጃውን ወጥቶ እንደጨረሰ አሻግሮ ሲመለከት ሰው የለም፡ በቀጥታ ያመራው ወደ ሻንጣዎቹ መቀመጫ ክፍል ነው፡፡ እዚያም ገብቶ በሩን ቀስ ብሎ ዘጋና ትንፋሹን በረጅሙ ለቀቀው፡፡
ሻንጣዎቹን ሲቃኝ አንድ ትልቅ ሳጥን ላይ ዓይኑ ተተከለ፡፡የሌዲ ኦክሰንፎርድ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ጠጋ ብሎ ሲያይ ኦክሰንፎርድ የሚል ስም ተለጥፎበታል፡፡
👍14🔥2🥰1
#ታምራተ_ኬድሮን


#ክፍል_አርባ_አራት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


////
እየሄደች ነው… ልታናግረው…፡፡ ለምን እሱን ማናገር እንደፈለገች አታውቅም፡፡ ምን አልባት ዳግመኛ አጠገቡ ልትቆምና ያንን ወንዳወንድ ቁመናው እና ቆንጅዬ ባሪያ የሆነ መልኩን በቅርበት ለማየት ፈልጋ ሊሆን ይችላል….ናፍቋትም ሊሆን ይችላል፡፡ 

ንስሯ የት እዳለ በነገራት መሰረት ቀጥታ ቤቱ ነው የሄደችው..የውጩን የጊቢ በር መጥሪያ ስትጫን ዘበኛው ነበር የከፈተላት…‹‹ከመላኩ ጋ ቀጠሮ ነበረኝ ቤት እየጠበኩሽ ነው ብሎ ደውሎልኝ ነበር..?››ብላ ቀላመደች… ዘበኛው ያልተለመደ ነገር ሆኖበት .. ግራ እንደመጋባት አለና በመጠኑ ካቅማማ በኃላ እንድትገባ  ፈቀደላት…
ቀጥታ ቤተኛ እንደሆነ ሰው የተንጣለለውን ግቢ ሰንጥቃ ባለአንድ ፎቅ ከሆነው ዘመናዊ መኖሪያ ቤት  በረንዳው ላይ ደረሰች… የሳሎኑን በር ገፋ ስታደርገው ተከፈተ…የቀኝ እግሯን አስቀድማ ግራዋን አስከትላ ወደውስጥ ከገባች በኃላ  ወደኃላ ዞሯ በራፉን አንኳኳችው…
‹ከገቡ በኃላ ማንኳኳት ከገደሉ በኃላ ማዘን አይነት አይደለም እንዴ…..?››እራሷው በራሷ ነው የጠየቀችው
መላኩ የሳሎኑ መአከላዊ ስፍራ ላይ  ካለችበት ወደውስጥ 4 ወይም 5 ሜትር ያህል ርቆ በመገረም አፍጥጦ እያያት ነበር….
ማንኳኳቷን ስትቀጥል

‹‹አቤት››የሚል ድምጽ አሰማ

‹‹መግባት ይቻላል..?››

‹‹ገብተሻል እኮ ››

‹‹እሺ ካልክ›› ብላ ቀጥታ የሳሎኑን በር መልሳ ዘግታ ወደእሱ አቅጣጫ አመራች ….በተገተረበት ስለማንነቷ በመመራመር ይመስለል ፈዞ እንደቆመ በስሩ አልፋ ልክ እንደቤተኛ ሶፋው ላይ ዘና ብላ ተቀመጠች….መጣና ከፊት ለፊቷ ተቀመጠ

‹‹አውቅሻለሁ ልበል..?››

‹‹እኔን የመሰለች ቆንጆ ልጅ እንዴት ልትረሳ ትችላለህ..?››

‹‹ማለት..?››

‹‹ጎበዝ የዋና ተማሪህ ነበርኩ ብዬ ነዋ››

…ድንገት እንደበራለት ሰው በመደነቅ ‹‹እንዴ አንቺ እብድ ..እቤቴን ደግሞ ማን አሳየሽ..?›› አለት ‹‹ቀላል ሰው  አይደለሁም ብዬህ ነበርኮ..?››

‹‹አረባክሽ.. ፉከራሽን እኮ አየነው..እኔማ አንተን ማሳሳት ካቀተኝ እንጠለጠላለው ብለሽ ስለነበረ..በቃ ይቺ ልጅ አልሆንላት ሲል እራሷን አጥፍትለች ማለት ነው..ምን አይነት ለቃሏ ታማኝ ልጅ ነች ብዬ ሳደንቅሽ ነበር የሰነበትኩት፤ለካ ዝም ብለሽ ጉረኛ ነገር ነሽ..?››

‹‹አንተን ማውጣት አቅቶኝ ሳይሆን አሳዝነኸኝ ነው የተውኩህ ››

ግድግዳውን ሰንጥቆ በመውጣት ውጭ ድረስ ለመሰማት ኃይል ባለው አይነት አንቧራቂ ሳቅ ሳቀ‹‹አሳዘንኩሽ…..?ቀልደኛ ነሽ››

‹‹ቀልድ አይደለም…የዛን ቀን የሄደክው ከፍቅረኛህ ጋር ወደሆቴል አልነበር…..?ስለ ጋብቻ ስታወሩ አልነበር....?እንድታገባህ ስትለምናት አልነበር…..?እሷ መጋባቱ ቀርቶባችሁ እስክትሞት ድረስ የቀራትን ህይወት እንደዚሁ እንድታሳልፉ ስትለምንህ አልነበር…..?ከመሞቷ በፊት ካላገባችህ እና መጽናኝ የሚሆን ልጅም ካልወለደችልህ በሞተች ቀን አብረሀት እንደምትሞት እየነገርካት ስትላቀሱ አልነበር……..?››

ይሄንን ስትነግረው እነዛ የኮከብ ክፋይ የሚመስሉ  ደማቅ አይኖቹን ከወዲህ ወዲያ በመገረም እያሽከረከራቸው ነበር…..

‹‹አንቺ ክፍል ውስጥ ተደብቀሽ ስታዳምጪኝ ነበር እንዴ..?››በንዴት ጡንቻው ውጥርጥር ሲልና … ልነቃት አልነቃት እያለ ከውስጡ ጋር ሙግት እንደገተመ ከሁኔታው ያስታውቃል….

‹‹አይደለም …ክፍል ውስጥ አልነበርኩም…ግን በአካል ባይሆንም ክፍል ውስጥ ገብቼ  እናንተን ምታዘብበት ሌላ ዘዴ ነበረኝ››

‹‹ምን ..?ካሜራ ..?››
‹‹አይደለም…ምንነቱን ቀስ ብዬ ነግርሀለሁ…አሁን ወደመጣሁበት ጉዳይ እንግባ››

‹‹ወደመጣሁበት ጉዳይ .. ..?በይ ሳትዋረጄ በመጣሽበት እግርሽ ሹልክ ብለሽ ቤቴን ለቀሽ ውጪ..››ከመቀመጨው ቀድሞ ተነሳ…

‹‹ሁለተኛ እንኳን እቤቴ እኔ ባለሁበት አካባቢ  በድንገት ባገኝሽ እወነቴን ነው አጠፋሻለሁ…ሲጥ አድርጌ ነው የምገልሽ….››

ዘና ብላ እንደተቀመጠች መልስ መመለሷን ቀጠለች  ‹‹ዝም ብለህ አትፎክር…በቁጣ እያንቧረቁ መናገር እና ፊትን ማጨማደድ የምትለውን አይነት ጭካኔ እንዲኖርህ አያግዝህም››

‹‹ምን ማለት ነው..?››

‹‹እንኳን እኔን ምንህም  ላይ ያልደረስኩትን ልጅ ይቅርና ሰላምን እንኳን እንደዛ በድላህ ፍቅህን ረግጣ የገዛ ወንድምህን በማግባት ስታወድምህ   ለህግ አሳልፎ ከመስጠት ውጭ ምንም ልታደርጋት  አቅም አላገኘህም፡፡››
ተንደርድሮ ወደእሷ ቀረበና  ተንበርክኮ አንገቷን በማነቅ እያረገፈገፋ‹‹ማነሽ …....?አንቺን ማነው የላከብኝ....?ማነው ንገሪኝ..?››

‹‹ማንም …ምን አልባት የምታመልከው አምላክ ሊታረቅህ ፈልጎ ይሆናል…ምን አልባት እስዛሬ የፀለይከው ፀሎት አምላክ መንበር ደርሶ መልስ የማግኛህ ጊዜ ደርሶም ሊሆን ይችላል…››
፣እጁን ከአንገቷ ላይ መንጭቃ በማላቀቅ ገፈተረችውና …ዝርፍጥ ብሎ ወለሉ ላይ በቂጡ ቁጭ አለ …እዛው ባለበት አፍጦ እሷን ከማየት በስተቀር ለመነሳት አልሞከረም

‹‹ሰሚራን ባድንልህ ምን  ታደርግልኛለህ..?››

‹‹ምን  እየቀባጠርሽ ነው…...?ደግሞ በእሷ ልትቀልጂብኝ ነው..?››

‹‹አይደለም ..ካዳንኩልህ ምን ታደርግልኝለህ..?››

‹‹ቅጠል አሽተሸ በመቀባት የምታድኚው ቁስል… ምች መድሀኒት ወይንም ጅንጅብል ጨቅጭቀሽ ከሻይ ጋር አፍልቶ በመጋት  የምታድኚው  ጉንፋን በሽታ  ያመማት መሰለሽ  እንዴ..?››
‹‹አውቃለሁ…ለአመታት በጭንቅላቷ ቆይቶ የነበረው ጥይት እና የጭንቅላት እጢ ተከትሎ…….››
አላስጨረሳትም ‹‹…በፈጠረሽ ማን ነሽ ?ምንድነው ምትፈልጊው....?ይሄን ሁሉ ገበናችኝን ስንት አመት ብትሰልይን ነው ማወቅ የቻልሺው..?››

ጥያቄውን ችላ በማለት  የራሷን ጥያቄ ደግማ ጠየቀችው

‹‹ካዳንኩልህ ምን ታርግልኛለህ..?››

‹‹ እኮ እንዴት ነው የምታዲኚያት…..?የጀርመንና አሜሪካ ጠበብቶች ያቃታቸውን አንቺ እንዴት ብለሽ..?››

‹‹እኔ የተለየ መንፈሳዊ ስጦታ አለኝ …››

‹‹አላምንሽም››

‹‹እንድታምነኝ…አንድ አንተ ብቻ የምታውቀው ታሪክ ልንገርህ…እንደውም ለምን ዛሬ ያየኸውን ህልም አልነግረህም ..…››

ንገሪኝም ተይው ማለት አቅቶት በግራ መጋባት ስሜት እየዋለለ ዝም ብሎ እንዳፈጠጠባት ፈዞ ቀረ…

ጣና ሀይቅ መሀል ላይ ያለች ትንሽ ደሴት ትመስልሀለች….እሷን ከብዙ የሀገሪቷ ሀብታሞች ጋር ተወዳደረህ በጫረታ በማሸነፍ ትገዛና …በጣም ውብ የሆነ በባህላዊ መንገድ እጽብ ድንቅ ተደርጎ የታነፀ ቤት ትሰራበታለህ…በዛች ደሴት ላይ አንተ ከሰራሀት ቤት ውጭ ምንም አይነት ሌላ ቤት የለም፤ደሴቱ ሙሉውን በቡና ተክል፣በሙዝ፣በብርቱካን፣በመንደሪን፣በአፕል እና  በመሰሰሉት የሚበሉ ፍራፍሬዋች የተሞላች ነች…አዕዋፍት እና የዱር እንስሳትም  ከደኑ ጋር ስመም ፈጥረው ተፈጥሮን አድምቀው እና በተፈጥሮም ደምቅው የሚኖርበት ቦታ በመሆኑ ልዩ ድስታ ተሰምቶህ ይሄንን ስጦታ ላዘጋጀህላት ለሰሚራ ትሰጣታለህ…

‹‹ሰሚርዬ ቀሪ ህይወትሽን ምንም እንኳን አጭር ብትሆንም በደስታ የተሞላች እድትሆን ፈልጋለሁ…በዛ ላይ እዚህ ከእኔ እና ከተፈጥሮ ውጭ ምንም አይነት የሰው ልጅ ወደ ሌለበትና ወደማይኖርበት ቦታ ሳመጣሽ ቀሪ ዘመንሽን የብቻዬ ብቻ እንድትሆኚ በመፈለግ እና በመሰሰት ነው…ይቺ ስፍራ የእኔ እና የአንቺ ገነት ነች››ትላታለህ፡
👍766😁3🥰2
#ትንግርት


#ክፍል_አርባ_አራት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


ፅዮን እና ታዲዬስ እሁድ ከምሽቱ 12 ሰዓት ሀዋሳ ሴንትራል ሆቴል ቁጭ ብላው እሷ ለስላሳ እሱ ቢራ አዛው እየተጐነጩ ያዘዙትን መክሰስ በመጠባበቅ ላይ ናቸው፡፡የምረቃ በዓሉ ካለፈ በኃላ በሣምንታቸው ዛሬ መገናኘታቸው ነው፡፡‹‹እሺ ፅዮን ለምን ግን ወይን ነገር አትሞክሪም ነበር?››

<<አንደኛ አልኮል የሚባል ነገር ሞክሬ አላውቅም ...ሁለተኛ የማያየው ዓይኔ ሳያንስ ጠጥቼ እምሮዬንም እንዳያይ አድርጌ እንዴት ልሆን ነው?››

‹‹አይ ሳታበዢ ማለቴ እኮ ነው፡፡››

‹‹ያው መጠጣት ከጀመርኩ ቢያንስ አንድ ብርጭቆ መጨረሴ ይቀራል..ያ ማለት ደግሞ እኔን ለማስከር በቂ መጠን ነው…ግድ የለህም ለስላሳው ይብቃኝ፡፡››

‹‹ያው ብትሰክሪም እኮ እኔ አብሬሽ አለሁ ብዬ ነው፡፡››

‹‹አይ እኔ በራሴ ድክመት እራሴን ጥዬ ሰውን ደግፉኝ ማለት አይመቸኝም፡፡››

‹‹ተቀብያለሁ››አለ በጠንካራ መንፈሷ ተደስቶባት፡፡

‹‹ፂ ስለበቀደሙ ጉዳይ እንድናወራ ነው ዛሬ የቀጠርኩሽ››ወደዋናው ቁምነገር ድንገት ገባ።

‹‹ይመቸኛል..እኔም እንደዛ እንደሆነ ተስፋ በማድረግ ነው የመጣሁት..ቀጥል፡፡››

‹‹እንዴት እንደምቀጥል አላውቅም፤ብቻ…..››

‹‹ታዲ ..እኔ የ28 ዓመት ወጣት ነኝ፤በህይወቴ ብዙ ውጣ ውረድ ያየው ሰው ነኝ.. ህይወት ነጩንም ሆነ ጥቁሩን ክፍሎቿን በማፈራረቅ አሳይታኛለች፡፡አንድን ነገር ፈልጌዋለሁና የግድ አገኘዋለሁ ማለት እንዳልሆነ አውቃለሁ፡፡››

‹‹በህይወትማ ምንም ነገር ከልብሽ አገኘዋለሁ ብለሽ ካሰብሽ ታገኚዋለሽ፡፡››

‹‹አውቃለሁ....የሆነ ነገር አገኛለሁ ብለህ ከልብህ ከተመኘህ፤ ምኞትህንም ለማሳካት በሙሉ ጉልበትህ ከተንቀሳቀስክ የማይሳካልህ ነገር እንደሌለ እኔም አምናለሁ፤ይሄ ግን ፍቅር ላይ ሲሆን ከሚሰራበት ጊዜ ይልቅ የማይሰራበት ጊዜ ይበልጣል፡፡››

‹‹እንዴት እንዲህ ልትይ ቻልሽ…?ከፍቅር አምላክ ጋር ትንሽ የተቀያየማችሁ ይመስላል፡፡››

‹‹ትንሽ አልከው...ምን ትንሽ ብቻ ...ለአምስት አመት ተኮራርፈን በደረሰበት ላልደርስ ተማምለን… ሳይደርስብኝ ሳልደርስበት ጥሩ ጊዜ አሳልፈን ነበር ፡፡››

‹‹ታዲያ እንዴት ሆናችሁ?››

‹‹ምን እንዴት ሆናችሁ አለው... አንተን ሳገኝ መሀላዬን አፍርሼ ደጅ እየፀናሁ እያየኸኝ?››

‹‹ደጅ ጽናት አልሽው፤ለማንኛውም እስኪ በምን ተኮራርፋችሁ እንደነበረ ብትነግሪኝ ? ማለት ደስ ካለሽ…..››

ዝም አለች... ጭንቅላቷ ወደታች ተደፋ‹‹…ምን መሰለህ......››ብላ ልትቀጥል ስትል ያዘዙት መክሰስ መጣና ቀረበላቸው፡እየተጎራረሱ በሉ..ከጨረሡ በኃላ አብረው ወደ እጅ መታጠቢያው በመሄድ ታጠቡና ወደመቀመጫቸው ተመለሱ፡፡ታዲዬስ ሁለተኛ ቢራውን አዘዘ..ዛሬ ካለወትሮው ጠጣ ጠጣ አሰኝቶታል፡፡

‹‹ምነው ዝም አልከኝ ...?››አለችው ልትጀምርለት የነበረውን ታሪኳን እንድትቀጥልለት ባለመጠየቁ ቅር ብሏት...

‹‹ኧረ ዝም አላልኩሽም ….ዝም ስላልሽ እኮ ዝምታሽን ላለመረበሽ ብዬ ነው፤እኔ ዝምታዬን ከሚረቡሹኝ ንግግሬን ቢያቋርጡኝ ይሻለኛል፡፡››

‹‹እሱስ እውነትህን ነው….ግን አሁን ዝምታ ውስጥ ስላልሆንኩ አትረብሸኝም

...ይሄውልህ ታዲ እኔ የሻሸመኔ ልጅ ነኝ፡፡ ትውልዴ እስከተወሰነ ጊዜም እድገቴም እዛ ነው፡፡ አባቴን እና እናቴን አላውቃቸውም ማለቴ በአካል አላውቃቸውም...ያሳደገችኝ የአባቴ እናት አያቴ ነች ... እናቴ ገና አንድ አመት ሳይሞላኝ ነው አባቴ ክንድ ላይ ጥላኝ ሀገሩን ጥላ የጠፋችው፡፡ ከአንድ አመት በኃላ አባቴም በተራው ሁኔታዎች ስልችት ሲሉት እኔን ለእናቱ ሰጥቶኝ ውትድርና ተቀጥሮ ለጦርነት ወደ ሰሜን ይሄዳል፡፡

ከዛ በኃላ አያቴ ያለቻትን አንድ ክፍል ቤት በደባልነት አንድ ደደፎ ለሚባል ከገጠር ለትምህርት ለመጣ ልጅ አከራይታ ከእሱ ከምታገኘው ገቢ በተጨማሪም በደካማ አቅሟ ጠላ እየጠመቀች አንዳንዴም አረቄ እያወጣች በመሸጥ እኔን ማሳደግ ትጀምራለች ፡፡ስምንት ዓመት ሲሞላኝ ግን ያልታሰበ ችግር ተፈጠረ..

ዓይኖቼን ይጋርደኝ ጀመር ..በወቅቱ አያቴ እንኳን ለህክምና ለሆዴም መሙያ የሚሆን ሳንቲም ለማግኘት በመከራ ነበር ሚሳካላት…፡፡

ባቅሟ የቻለችውን ፀበሉንም የባህል መድሀኒቱንም ብትሞክርልኝም ከቀን ወደቀን እየባሰብኝ መጥቶ ከአንድ አመት በኃላ ሙሉ በሙሉ ሁለቱም አይኖቼ ታወሩ..ከዛ ትምህርቴንም ከሁለተኛ ክፍል ግማሽ ላይ አቆረጥኩ፡፡አያቴ ግራ ገባት ፡፡በሚመጣው አመት ግን ያ እቤታችን በደባልነት ይኖር የነበር ያልኩህ ተማሪው ልጅ ሚሽኖቹ ጋር ተሯሩጦ በአዳሪነት አስገባኝ፡፡ ይገርምሀል አያቴን ልክ እንደእናቱ ነበር የሚወዳት... እሷም ከእኔ ለይታ አታየውም ነበር እንዲሁ ስሙ ተከራይ ተባለ እንጂ እኛ የምንበላውን ይበላል እሱ የሚበላውን እንበላለን ስናጣ አብረን እንራባለን፡

እኔ ሚሽን በአዳሪነት ከገባሁ በኃላ አያቴ ጋር እኖር ከነበረው ኑሮ በተሻለ ሁኔታ እኖር ጀመር፤ ትምህርቴንም በጥሩ ሁኔታ መከታተል ጀመርኩ፤ድንገት ግን ምን እንደተፈጠረ ታውቃለህ? ብቸኛ ዘመዴ የሆነችው አያቴ ሞተች፡፡በወቅቱ የ5ተኛ ክፍል ተማሪ ነበርኩ… ዕድሜዬም ወደ 14 አካባቢ ተጠግቶ ነበር ..በጣም ነው የከበደኝ፡፡ ለመጽናናት በጣም አስቸግሬ ነበር፡፡ይገርምሀል እቤታችንን ተከራይቶ ነበር ያልኩህ ልጅ በወቅቱ አስረኛ ክፍል ደርሶ ነበር፡፡በአያቴን ሞት በጣም ነበር ያዘነው…፡፡

ከዛ እኔን መንከባከብ የእሱ ኃላፊነት እንደሆነ ነበር የሚያስበው፤ በሳምንት ሁለት ቀን እየመጣ ይጠይቀኝ ነበር፤ደግሞ ሲመጣ ባዶ እጁን አይመጣም..ደብተር፣እስኪሪብቶ፣የፀጉር ቅባት፣ማበጠሪያ፣ፓንት ...ብቻ የማይገዛልኝ ነገር አልነበረም፤ካጣ ካጣ የ 25 ሳንቲም ማስቲካም ቢሆን ይዞልኝ ይመጣል..ደግሞ እኮ የሚገርመው እሱም ምንም የሌለው የደሀ ገበሬ ልጅ መሆኑ ነው፡፡ ግማሽ ቀን ይማራል ኑሮውን ለመደጎም ደግሞ ግማሽ ቀን ጋራዥ ይሰራል...ከዛ በሚያገኛት ሽርፍራፊ ገንዘብ ነበር ለእኔ የሚያስፈልገኝን ነገር ይገዛልኝ የነበርው፡፡

በዛ ላይ የቤት ኪራዬን በየወሩ ቀን እንኳን ሳያስተጎጉል አምጥቶ ይሰጠኛል…ተወው ይቅር አያስፈልገኝም ብለውም አይሰማኝም...‹ነገ ብትቸገሪ ለአንድ ነገር ይሆንሻል.. አስቀምጪው >> ይለኛል...እኔ ደግሞ የተለየ ወጪ ስለሌለኝ እጄ ላይ እየተጠራቀመ ሲበዛብኝ አንድ የምወዳት አስተማሪዬ ጋር ማስቀመጥ ጀመርኩ፡፡

እንዲህ እንዲህ እያለ ቀናቶች እየነጐዱ እኔም እያደግኩ በትምህርቴም እየገፋሁ መጣሁ..በነገራችን ላይ ሙዚቃ መሳሪያ መነካካት የጀመርኩት እዛው ሻሸመኔ አይነስውራን ትምህርት ቤት እያለሁ ነበር፡፡

ስምንተኛ ክፍል ስደርስ ደደፎ 12ተኛ ክፍል ጨርሶ ነጥብ ስላልመጣለት መንጃ ፍቃድ አውጥቶ ሹፌር ሆነ፡፡በዚህን ጊዜ በሳምንት ሁለት ቀን መምጣቱን አቁሞ በሳምንት አንዴ
..አንዳንዴም በአስራአምስት ቀን አንዴ ይመጣ
ጀመር፡፡ሲመጣ ታዲያ ይዞልኝ የሚመጣውን
ነገር አትጠይቀኝ ... ምንም የሚቀረው ነገር
አልነበረም፤ለእኔ አይደለም ለጓደኞቼ እራሱ ይተርፍ ነበር፡፡ የጽዮን ወንድም መጣ ከተባለ ጓደኞቼ በሙሉ ጥርስ በጥርስ ነበር
👍728