አትሮኖስ
280K subscribers
109 photos
3 videos
41 files
459 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ሰመመን


#ክፍል_ሃምሳ_አንድ


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ


...ማሰብና መጀመር የተለያዩ ሆነውበት ተቸግሯል አቤል ። ሐሳቡ በጣም ይመጥቅበታል ።ሊጽፍ ያሰበው ነገር መጽሐፍ ይሆንበታል ። ለሐሳቡ ወግ የሚያግኝለትም አይመስለው ። ወረቀቱን ይዞ ቁጭ ሲል ግን ከብዕሩ ጠብ የሚል ነገር ይጠፋል ። ባዶ ወረቀት ላይ ማን ፎር ሂምሰልፍ” ከሚል አርዕስት ጋር መፋጠጥ ብቻ !

“ችግሩ ከቋንቋው ይሆን ? ” ሲል አሰበ ። በሰው ቋንቋ ከምቸገር ሓሳቤን እንደ ልቤ ላንቆረቁርበት በምችለው በራሴ ቋንቋ ለምን አልፅፍም?።

ባዶውን ወረቀት ከአጠገቡ አገለለና መጽሐፍ ገለጠ ለጽሑፉ የሚጠቅመውትን መጽሐፎች መርጦ አውጥቶ ጠረጴዛው ላይ ከምሯል ። መጻፍ ከመጀመሩ በፊት በዚህ አርዕስት
ጐዳይ ላይ የተጻፉ ብዙ መጽሐፎች ማንበብ እንዳለበት ስለ ተረዳ፡ ሰሞኑን እያነበበ ነበር። ችግሩ ግን አለ ከሚያነበው መጽሐፍ ላይ ብዙ ሰዓት መቆየት አለ መቻሉ ነው ከመጽሐፉ ውስጥ ጠቃሚ ሐሳብ ሲያገኝ የእሱ ሐሳብ ቀድሞ ይሐጥቅና ጻፍ ጻፍ ይለዋል

አሁንም ከተቀመጠበት ተነሥቶ ትንሽ ተንጎራደደ ። ከመንጐራደዱ ጋርም የሚጽፈው ነገር ብልጭ አለለት
ሰው ከራሱ ጋር የሚጣላው ለምንድነው ? በግል ምኞትና ግብ አእምሮው ተወጥሮ ሲጨነቅ ነው ። ነገር ግን የሰው ልጅ የመጨረሻ ግቡ እኛ እንጂ እኔ መሆን የለበትም ከራሱ ጋር ሊታረቅ የሚችለው በዚህ እምነት ተጠምቆ ከግሉ ይልቅ ለማኅበራዊ ችግር ክብደት ሲሰጥና ደስታውን ከኅብረተሰቡ ጣፋጭ ሕይወት ውስጥ ለማግኘት ሲሞክር ነው ። ሰው በመጀመሪያ ለሕያውነቱ ከፍተኛ ግምት መስጠትና ማድነቅ አለበት ። ይህን ካመነ ደግም ማናቸውም በውስጡ የሚከሠቱ ነገሮች የሕያውነቱ ነጸብራቆች ስለሆኑ
እንዳመጣጣቸው ተቀብሎ መፍታት እንጂ ለችግሮች ምረታት የለበትም ። ሰው በትግሉ በተጸጥሮ ላይ ፍጹም የበላይነቱን መቀዳጀት አለበት ።

እቤል መጻፍ የፈለገውን መቋጠሪያ ሐሳብ ያገኝ መሰለው ደስ ደስ አለው። በአንጻሩ ግን ከውስጡ አዘናጊ ስሜት ይታግለው ነበር ። " አይ አቤል ፤ አሁንስ ጅል ሆንክ አዲስ ሐሳብ ያፈለቅክ መስሎህ ነው ? ስንት ፈላስፋዎች ብለውት ብለውት የበቃውን ነገር እንዴት እንደ አዲስ ታነሳዋለህ ? እባክህ ይልቅ ያልተሳበ አዲስ ነገር ፈልግ ።ለዚያውስ በዚህ ዓለም ላይ ምን ያልተባለ ነገር አለ ?”

አቤል የራሱ ስሜት አስጠላው ለምንድነው ስሜቱን ገንቢውን ትቶ አፍራሹ ላይ የሚሮጠው? አዲሱ ሰው ሁሉን ነገር “ ተብሏል” እያለ ራሱን የሚያዘናጋ ከሆነና እጁን አጣምሮ ከተቀመጠ ነገር ተበላሸ ከአሁን በፊትም ማንም ቢሆን ፍጹም አዲስ ነግር ይዞ አልተሄዶም ። ሁሉም እውቀቱን የቀመረው በተከሠረት ወይም በተባለ ነገር ላይ እየቆመ ነው።እና አቤል አቤልሽ ! ይልቅ ደፍረህ ጀምር የአቅምህን ሞክር ፤ ጫር ! ” አለና እንደገና ቁጭ አለ።

እንዴት እንደሚጀምረው ቁልጭ ብሎ ታየው " ሰፊ አርዕስት ነው የያዘው ፤ስለዚህ በንዑስ ርዕስ ከፋፍሎ እያንዳንዷን ንዑስ ክፍል በጽሑፍ ማስረጃና በሕይወት ገጠመኝ
አስደግፎ ማስኬድ ! ሰውነቱን አንዳች የደስታ ስሜት ወረረው ። ሐሳቡ ካለበት መጥቆ ሲሮጥ ንዑስ ርዕሱ ልጓም ሆኖ
ያዘለት ። ሰው የራሱ ወዳጅ የሚሆንበትን ሐሳብ ከመደርደሩ በፊት ከራሱ ጋር የሚጣላባቸውን ሁኔታዎች ለመደርደር ተገደደ ። እዚህ ላይ ለመድረስ ደግሞ፥ ሰው በተፈጥሮ ይዟቸው የሚወጣውንና ከአካባቢው የሚቀስማቸውን ዐብይት ጸባያት ይዞ መነሣት ነበረበት ። የጅማሬ ሐሳቡን በዚህ ንዑስ ርዕስ ሥር አጠቃልሎ ፥ “ በዚህ ዓለም ላይ ታላቅና
ክቡር ፍጡር ነው” ሲል ጀመረ ።

በተመስጦ እየጻፈና ደጋፊ ሐሳቦች ፍለጋ መጽሐፎች እያገላበጠ ትንሽ እንደ ቆየ ፡ ሞኒካ ሻይ ይዛለት መጣች።

የአምስት ሰዓት ሻይ ነበር ። ጊዜው ከምኔው እንደ ሮጠ ገረመው
“ ጽሑፉን ጀመርኩት “ ኮ ” አላት ፡ ገና እየገባች ሳለች ።

“ ዳስ ኢስት ሸን ” አለችው ሞኒካ • ፈገግ ብላ ደስታዋን በመግለጽ ።

አቤል ይህንኑ “ ጀመርኩት ” የሚለውን ቃል ለዮናታንም ለመንገር ተቻኮለ ። እንዲያመጡለት የጠየቃቸውን የቀድሞ የተበላሹ የጥናት ጽሑፎቹን ባመጡለት ጊዜ ፥ የገባላቸው ቃል ትዝ አለው ። ወረቀቶቹን ተቀብሎ ፊታቸው በክ
ብሪት ካቃጠለ በኋላ ፥ አሁን ከፊትዎ የቆመው አዲሱ አቤል ነው ። አዲስ ጽሑፍ አዘጋጅቶ ያሳይዎታል ” ብሏ
ቸው ነበር ። አሁን ዮናታን የሚመጡበት የምሳ ሰዓት ራቀበት።

ሞኒካ አሁን እቤል ያለበትን ጥሩ ስሜት ካረጋገጠች በኋላ፥ ወደ መኝታ ክፍሏ ሔዳ አንድ ጉርድ ፎቶግራፍና የታሸገ
ኢንቬሎፕ ይዛ ተመለሰች ።

“ ይህችን ልጅ ታውቃታለህ ? ” አለችው ፥ ፎቶውን ዐይኑ ሥር አቅርባ ።ፉት ብሎ የነበረውን ሻይ ቶሎ መዋጥ አቃተው
የልብ ትርታ የሚቀሰቅስ ምስል ! አስደንግጦ የሚያስደስት ምስል ! “ ማወቅ ብቻ ነው!? አምልኬባታለሁ እንጂ!” ሊላት ፈለገ። የሞኒካ ቶሎ መልስ መፈለግ ግን፥ አቤል ነገሩን አመዛዝኖ እንዲናገር ጊዜ አልሰጠውም ።

አዎ ! አላት ፥ ሌላውን ስሜቱን ዋጥ አድርጎ
“ የት ? ”
“ ዩኒቨርስቲ ውስጥ አንድ ሴሚስተር ሙሉ በዐይን ፍቅር የማቀቅኩላት ናት” አላት ቃናው በተለወጠ ድምፅ ።

“ ከዚህ ፎቶዋ ጋር ደብዳቤ ልካልሃለች ” አለችና የታሸገውን ፖስታ ሰጠችው። ፈጥኖ ተቀበላት ። ነገር ግን ፈጥኖ መቅደድ አልቻለም ። አንዳች ነገር እጁን የያዘው ይመስል ተንቀጠቀጠ ።

በሚያነብበት ጊዜ ነጻ እንዲሆን በማሰብ ሞኒካ ክፍሉን ለቅቃለት ወጣች ። ደብዳቤዉንና ፎቶዉን ከእስክንድር
ከተቀበሰች ሁለት ቀን አልፎአል ።ለአቤል ወድያውኑ ያልሰጠችው እንዲህ ጥሩ ስሜት እስኪታይበት በመጠበቅ ነበር።

አቤል ደብዳቤዉን ግልጾ ማንበብ ጀመረ፡-

አቤል፥ ስምህን ደብዳቤ ላይ ለመጀሪያ ጊዜ ስጽፈው የተሰማኝን ስሜት ልገልጽልህ አልችልም ። የምወደውንና
የምፈልጎውን ቃል መጥራት ለምን እንደሚያስፈራኝ ሊገባኝ አልቻለም ። የዚህን ደብዳቤ ረቂቅ ብታየው ትግረማለህ ። ስርዝ፤ ድልዝዝ ብቻ ነው። ከስሜቴ ጋር ክፉኛ መታገሌን በዚህ መገመት ትችላለህ ።

ይህን ደብዳቤ እንድጽፍልህ ያደፋፈረኝ እስክንድር ነው ። ጥሩ ጓደኛ ነው ያለህ እሱ ባይገፋፋኝ ኖሮ እንዲሁ ስሜቴን አምቄ ውስጥ ውስጤን እሠቃያለሁ እንጂ ከቶም አልሞክረውም ነበር ። አንተ በእኔ የተነሣ የተቀበልከውን ስቃይ ስሰማ ለብቻዬ ተደብቄ ስቅስቅ ብዬ ነው ያለቀስኩት ፤ግን ጥፋተኛው ማን ነው ? አየህ አቤል ! እኔ መቼም ሴት ነኝ ፤ደፍሬ መጥቼ እንዳነጋግርህ የአካባቢ ተጽዕኖ
አለብኝ ። አንተ ግን በሩቅ ከምትሠቃይ ቀርበህ ! ብታነጋረኝና እወድሻለሁ ብትለኝ ምን ነበረበት ።

“ሕመምህ ጠልቆ የተሰማኝ አሁን ነው ። ለካስ ፍቅር ተገጣጥሞ ካልሰመረ ሥቃይ ነው። በካምፓስ ውስጥ አንተን በዐይኔ ካጣሁበት ጊዜ ጀምሮ ያለሁበትን ሁኔታ ልገልጽልህ አልችልም ። አንተን ለማየት እናፍቃለሁ ፣ ብቸኝነት ያሰቃየኛል ፥ አካባቢዩ ያስጠላኛል ፤ጥናት ያንገሸግሸኛል ፣ሁሉ ነገር ከብዶና መርሮ ይታየኛል ። እውነቴን ነው የምልህ
የተፈጥሮ ክሥተት ባይሆን ኖሮ፡ አፍላ ፍቅር ፈጽሞ እያስመኝም
“ በመጀመሪያው ሴሚስተር ከትምህርቴ እንዳልሰናከል እፈራ ስለ ነበር፡ ፍቅርህን ክፉኛ ተቃውሜዋለሁ›
አሁን የተረዳሁት ነገር ቢኖር ግን ፥ ፍቅር ታግለው የሚጥሉት ነገር አለመሆኑን ነው ። ገና መጀመሪያ የዩኒቨርስቲውን ግቢ ስረግጥ ካየኸኝ ጀምሮ በዐይን እንደምትከተለኝ ያልተረዳሁልህ እንዳይመስልህ እያንዳንዷ እይታ ከንግግር የበለጠ ተሰምታኛለች። እንዲያውም አንዳንዴ ቃላት
1👍1🥰1
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሃምሳ_አንድ


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ


....ከዋናው መንገድ ብዙም ሳይርቁ የመኖሪያ ቤቶች ከተደረደሩበት
የሠፈር ውስጥ መንገድ ዳር አንድ ጥግ ላይ መኪናቸውን አቆሙ፡፡

መኪናዋ ጥግ ይዛ እንደቆመች ፡ ናትናኤል የመኪናዋን ሬድዮ ከፈተው፡፡ ጎርናና የጋዜጠኛ ድምፅ መኪናዋ ውስጥ አስተጋባ፡፡

እንዲሁም የአንጎላና የሞሮኮ የሴኔጋልና የቡሩንዲ መሪዎች ከሰዓት በኋላ አቀባበል ሲደረግላቸው እስካሁን ወደ አፍሪካዋ ያልገቡት ሦስት የአፍሪካ መሪዎች ማለትም የሴራሊዮን የጋቦንና
የቡርኪናፋሶ መሪዎች ምሽቱን ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በወጣው ኘሮግራም መሠረት ዛሬ ሰኞ መስከረም አራት ምሽት በሁለት ሰዓት ተኩል ያልገቡት ሦስት የአፍሪካ መሪዎች ማለትም የሴራሊዮን የጋቦንና የቡርኪናፋሶ መሪዎች ምሽቱን ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በወጣው
ፕሮግራም መሠረት ዛሬ ሰኞ መስከረም አራት ምሽት በሁለት ሰዓት ተኩል
ላይ ጠቅላላ ፡ የአፍሪካ መሪዎች የሚገኙበት ስብሰባ ሲከፈት ይቅርታ
አድማጮቻችን አሁን ዘግይቶ የደረሰን ዜና አለ የሴራሊዮኑን መሪ
የያዘችው አውሮኘላን አዲስ አበባ ኢንተርናሽናል አውሮኘላን ማረፊያ
አርፋለች ኘሬዚዳንቱ፡ የክብር ሰላምታ ላቀረበላቸው.. አፀፋውን..…”

ናትናኤል ሬዲዮኑን ዘጋው፡፡
“ሁለት ቀሩ::” አለ ናትናኤል አይኖቹን አቦዝዞ ለራሱ እንደሚናገር ሁል፡፡

ጊዜው እየሄደ . ሰዓቱ እየቀረበ ሲመጣ ተራርቀው የዋሉት ደመናዎች እየተጠራሩ እጅ ለእጅ መያያዝ ጀመሩ:: ቀኑን ሙሉ ማን አለብኝ ብላ ያለርህራሄ ምድሪቷን ስትወቃት የዋለችው ፀሃይ የተባበሩትን
ደመናዎች ማለፍ ሲያቅታት ዙሪያው ቀዝቅዝ ተንፈስ አለ፡፡ ንፋሱ ብቻ
እንደ ወሬ ነጋሪ ከወዲያ ወዲህ ይመላለስ ጀመር፡፡

ሁለት ሰዎች የጫነች የቴሌኮሙኒኬሽን የጥገና መኪና ከአስመራ መንገድ ተነስታ በላይኛው ቤተመንግስት አድርጋ ፒያሳን ለሁላት ከፍላ ሲኒማ ኢትዮጵያ አጠገብ ስትደርስ ሊመሻሽ ተቃርቦ ነበር፡፡ መኪናዋ
አደባባዩን ዞረችና ቁልቁል ወረደች፡፡ ብዙም ሳትርቅ ከአንድ አፓርትመንት
ህንፃ የአጥር በር ፊት ለፊት ቆመች፡፡

“አቤት::” አለ አፈርማ ካፖርት የደረቡ የአፖርትመንቱ የማታ ዘበኛ የብረቱን በር ከፈት አድርገው ብቅ አሉና፡፡

“አንዴ ይክፈቱልን እባክዎት፡፡” አለ ከሾፌሩ ጎን የተቀመጠው ሰው ጭንቅላቱን በመስኮት ብቅ አድርጎ። “ስልከኞች ነን.… የተበላሸ ስልክ
ለመጠገን ነው፡፡”

ሽማግሌው እያቅማሙ የብረቱን በር ወለል አድርገው ከፈቱት፡፡
የቴሌኮሙኒኬሽኗ መኪና ወደ አፖርታማው ግቢ ገብታ ጥግ ይዛ ቆመች፡፡ወዲያው ካኪ ቱታ የለበሱ ሠራተኞች ፈጠን ብለው ከመኪናዋ ወርደው የጥገና መሣሪያዎቻቸውን የያዙባቸውን ቦርሳዎቻቸውንና ሌሎችንም
ዕቃዎቻቸውን አንግበው ወደ አፖርትመንቱ በር ተጣደፉ፡፡

ከመጀመሪያው ደርብ እንደደረሱ ወደግራ ብለው በጠባቡ መተላለፊያ ፊትና ኋላ ራመድ ራመድ እያሉ ቀጠሉ፡፡ 21 የተላጠፈበት በር አጠገብ እንደደረሱ ተያዩ:: ወዲያው በሩን አልፈው 22 የሚል ቁጥር የተለጠፈበትን የሚቀጥለውን በር አንኳኩ፡፡
“አቤት"አለች በሩን የከፈተችው ልጅ እግር ሴት ህፃን ልጅ እንደታቀፈች፡፡

“ከቴሌኮሙኒኬሽን ነው፡፡ በአካባቢው የተበሳሹ ስልኮች አሉ፡፡ የናንተንም ለማየት ነበር፡፡አላት ቀጠን ቀላ ያለው፡፡

“ደህና ነው የኔ ስልክ፡፡” አለች ሴትየዋ በተራ እያየቻቸው፡፡
“ገብተን እንየው?” አላት የመጀመሪያው ሰው፡፡
“ግቡ ግቡ፡፡“ አለች ሴትያዊ የታቀፈቻትን ህፃን ከመሬት አውርዳ በሩን በሰፊው እየከፈታችላቸው::

ካኪ ቱታ የለበሱት ሁለት ሰዎች ተከታትለው ገቡ፡፡
“ቅድም ስንደውል ያነጋገሩን እርሶ ኖት?” አላት ቀጠን ያለው፡፡
“አይ እዚህ አልደወላችሁም::”
“ምናልባት ሌላ ሰው አንስቶት እንዳይሆን…”
“እኔ ብቻ ነኝ ያለሁት በቤቱ፤ ከሷ በስተቀር፡፡” አለች ሴትየዋ ፈገግ
ብሳ የህፃን ልጇን ጭንቅላት እየደባበሰች፡፡ “እዚህ አልደወላችሁም፡፡”
ሰውየው የፈለገውን ያገኘ ይመስል ጊዜ ሳይወስድ ከቱታው ከስ ውስጥ ሽጉጥ አውጥቶ ሴትየዋ ላይ ደገነባት፡፡ ከጎኑ ቆሞ የነበረው ጥቁር ስው ያንጠለጠለውን የሸራ ቦርሳ ወደጎን ጥሎ በሚያስደንቅ ፍጥነት አፏን አፍኖ ወንበር ላይ አስቀመጣት፡፡ ሽጉጥ የያዘው ሰው ማልቀስ የዳዳትን ህፃን ልጅ ከመሬት አንስቶ ታቀፋት።

“ኣይዞሽ አንቺንም ሆነ ልጅሽን የመጉዳት ሃሳብ የለንም:: ነገር ግን ለመጮህ ወይ ለመሮጥ ብትሞክሪ ጥሩ አይሆንም ውጤቱ፡፡” አለ መሣሪያ የያዘው ሰው የሽጉጡን አፈሙዝ ህፃኗ ለስላሳ አንገት ውስጥ እያፍተለተለ፡፡

ሽጉጡን የያዘው ሰው ምልክት ሲሰጠው ኣፍዋን አፍኖ የያዛት ሰው ለቀቃት::

“ምንድነው የምትፈልጉት? የምትፈልጉትን ያዙና ውጡልኝ፡፡” አለች ልጇ አንጎት ስር የተሸጎጠውን ሽጉጥ የተመለከተችው እናት እየተርበተበተች::

“ሌቦችና ቀማኞች እይደለንም፡፡ ጉዳት ልናደርስብሽም አይደለም የመጣነው፡፡ እርዳታሽን ብቻ ነው የምንፈልገው፡፡” አላት ቀጠን ያለው ሰው ህፃኗን እንደታቀፈ ከተቀመጠችበት ወንበር አጠገብ በርከክ ብሎ፡፡
ምንድነው የምትፈልጉት?” አለች ሴትየዋ ኣይኖቿን በሁለቱ አፋኞች ላይ ተራ እያንከራተተች፡፡

እዚህ ጎረቤትሽ 21 ቁጥር ውስጥ ያለችውን ሴት ታውቂያታለሽ?"
አለ ልጇን የታቀፈው ሰውዬ ማልቀስ የጀመረችውን ህፃን በማባበል እየጣረ

“አዎ… ርብቃ ትባላለች… ልጄን ልቀቅልኝ፡፡”

ሀዋኗን የታቀፈው ሰው እየተቁነጠነጠች ያስቸገረችውን ህፃን ለእናቷ ካቅበለ በኋላ ወንበር ስቦ አጠገቧ ተቀመጠ፡፡

“ይህን ሰሞን አይተሻታል?” “ አለ የያዘውን መሣሪያ ከቱታው ኪስ
ውስጥ እየጨመረ::

“ኣሳየኋትም፡፡ ረጅም ጊዜ ነው ካየኋት.. ግን ሌሎች ሰዎች ወደ ክፍሏ ሲገቡና ሲወጠ አይቻለሁ፡፡ ምንድነው የምትፈልጉት ከኔ?” ሴትየዋ ልጇን እቅፍ አድርጋ ይዛ እየደባበሰች አፈጠሰችበት፡፡
“ምን ያህል ይሆናሉ ሰዎቹ?" ጠየቃት፡፡
“የቶቹ ሰዎች?” መልሳ ጠየቀችኑ፡፡
“ክፍሏ ውስጥ ያሉት ሰዎች፡፡"
“እኔ እንጁ ሲገቡና ሲወጡ ነው ያየኋቸው.. ውስጥ ይኑሩ አይኖሩ አላውቅም።

ቀጠን ያለው ሰው በርከክ ካለበት ተነስቶ በፀጥታ ከቆመው ጓደኛው ጋር በእንግሊዝኛ ቋንቋ በሹክሸከታ ያወራ ጀመር፡፡ ወዲያው ፊቱን ወደ
ሴትየዋ መለሰ፡፡

“እንዳልኩሽ እርዳታሽን እንፈልጋለን፡፡ ጉዳት ላይ እንድትወድቂ አንፈልግም። የምልሽን ያለማወላወል መፈጸም አለብሽ፡፡ አለበለዚያ ግን ያልጠበቅነው አደጋ ሊደርስ ይችላል፡፡”

“ምንድነው የምትፈልጉት?” አለች ሴትየዋ ግራ ተጋብታ፡፡ ተራ ሌቦችና ቀማኞች አለመሆናቸውን ስታረጋግጥ ድፍረቷ ተሰባስበላት፡፡ ኮስተር ብላ ተመለከተችው።

“አብረሽን ወደሚቀጥለው ክፍል ትሄጅና በሩን ታንኳኪያለሽ፡፡”
“እኔ የማላውቀው ሰው ቤት ሄጄ ኣላንኳኳም::” አለች ነገሩ ያልጣማት ሴትዮ የልጇን ጭንቅላት ጡቶቿ መሃል ቀብራ፡፡
“ምርጫ የለም፡፡ እምቢ ካልሽን እኛም የማንወደውን እንድንፈጽም እንገደዳለን፡፡” አለ ሽጉጡን የያዘው ሰው ጎንበስ ብሉ የህፃን ልጇን ጭንቅላት እየደባበሰ፡፡ “ተነሽ የፍርሃት መልክ አታሳዬ፡ በሯን
ካንኳኳሽ በኋላ ትጠባበቂያለሽ፡፡ በሩ ሲከፈት…” ማድረግ የሚገባትን ሁሉ
አንድ በአንድ እያስረዳ ክንዷን ይዞ ከተቀመጠችበት አስነሳት፡፡

ሴትየዋ ህፃን ልጇን እንደታቀፈች ከሁለቱ አፋኞቿ ጋር ክክፍሏ ወጥታ ጭር ባለው መተላለፊያ ወደሚቀጥለው ክፍል አመራች፡፡ ከጎረቤቷ ክፍል መዝጊያ እንደደረሱ ሁለቱ ሰዎች በበሩ ግራና ቀኝ ጀርባቸውን ለጥፈው ቆሙ:: ቀጠን ያለው ሰው ሽጉጡን አውጥቶ ደረቱ ላይ ለጥፎ
ያዘው በስተግራዋ ያለው ሰው ደግሞ ከሽራ
👍2
#የፍቅር_ሰመመን


#ክፍል_ሃምሳ_አንድ


#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን


#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው

...የብረቱን መሰላል ይዞ ወደ ላይ መውጣት ጀመረ፡፡

ሉዊስ ሮድሪጌዝ የኮሪደሩ መብራቶች በሙሉ ሲበሩ አይኑን ሽጉጥ በያዘበት እጁ ከለለ፡፡ ከታች ስሙ ሲጠራ ሰምቷል። የእነርሱን ጉዳይ የኒኪን ጉዲይ ከጨረሰ በኋላ ያስኬደዋል። አሁን ግን ኒኪን መግደል አለበት፡፡ እሷን የመግደሉ ሀሳብ በጣም አስደስቶታል። ከተቀመጠበት ተነስቶ ቆለጡ ላይ የሚሰማውን ህመም ችላ ብሎ ለእሳት አደጋ መውጫ ወደ ተሠራው የብረት ደረጃ አመራ።

እየመጣሁልሽ ነው አላት በዜማ ድምፅ እና ወደ ላይ ደረጃውን መውጣት ጀመረ። “የት ነው ያለሺው ነይ ወደ እዚህ!” እያለ ደረጃው ላይ የተንጠባጠበውን ጥቁር ደም እየተመለከተም ከደረጃው ጫፍ ላይ ከሚገኘው በር ላከ ደረሰ።

ሙሉ በሙሉ የበሩት የህንፃው መብራቶች ኒኪን ከእንቅልፏ አነቋት፡፡
ግን ተመልሳ ለዘላለም እንድታንቀላፋ ትደረጋለች፡፡ አዎን ልክ ዊሊ ባደንን
እንደገደለው እሷንም ያለችበት ቦታ ድረስ መጥቶ ሉዊስ ሮድሪጌዝ ይገድላታል። በቃ ከዚያ በኋላ ከባሏ ዶውግ ጋር ትገናኝ እና መልስ ላልተገኘላቸው ጥያቄዎቿ እራሱ መልስ ይሰጣታል። እውነታውንም
ታውቃለች ማለት ነው፡፡

“በጣም ነው የደከመኝ

ወደ ታች አይኗን ልካ በጥይት የተመታው እግሯን ተመለከተች፡፡ እንደ ቅድሙ ሀይለኛ ህመም አይሰማትም፡፡ ከዚያ ይልቅ ግን ቀዝቃዛ ውቅያኖስ
ውስጥ እንዳለች ሁሉ እግሯን በጣም ደንዝዟታል።

ከላይ በኩል ያለው የእሳት አደጋ መውጫ በር ተከፈተ እና የሮድሪጌዝን
ጭካኔ የተሞላበት የሹፈት ጥሪን ማዳመጥ ጀመረች።

“ዶክተርዬ የት ነሽ? እየመጣሁልሽ ነው እኮ” ይላታል፡፡

ፍርሃቷ ተመልሶ መጣባት፡፡ ከህመሟ የሚበልጠው ጥልቅ የመኖር ጉጉትም ውስጧን ተናነቃት፡፡ ስለሆነም ወደ ኋላ ወደ ጓዳው ግድግዳ እየተንፏቀቀች ተጠጋች እና ኮንክሪቱ ጋ ስትደርስ ተደግፋው ቁጭ አለች። ከተቀመጠችበት ቦታ ሆና በመጀመሪያ ጥቁሩን እና በደንብ ተደርጎ የተወለወለውን ጫማውን ተመለከተች፡፡ በመቀጠል ደግሞ እግሩን እና ሱሪውን፡ ከንፈሯም በፍርሃት የሆነ የልመና ድምፅ ሲያወጣ ይታወቃታል።

ይሄው አገኘሁሽ የኔ ውድ” አላት አጠገቧ እንደ ጅብራ ተገትሮ እንደቆመ፡፡ ሽጉጡን አዘቅዝቆ ይዞታል፡፡ ቀና ብለሽ ተመልከቺኝ” አላት፡፡ ኒኪም እንዳጎነበሰች ራሷን በአሉታ ነቀነቀች፡፡

ቀና ብለሽ እይኝ አንቺ ሸርሙጣ!” ብሎ ሲጮህባት ግን ኒኪ የግዷን ቀና
ብላ አየችው።

አቤት አይኖቹ! ውስጣቸው ያለው ጭካኔ ይታይባቸው ኖሮ እንዴት ያምሩ ነበር፡፡ ግን እነዚያ ቡናማ ውብ አይኖቹ ውስጥ የሚታዩት ጭካኔ ምህረት አልባነት እና ጥላቻ ስለሆነ ውበቱን አደብዝዞታል፡፡

ሽጉጡን ቀስ ብሎ ወደ እሷ ጭንቅላት አስጠግቶ በስስ ከንፈሮቹ ፈገግ
እያለ ተመለከታት።

“ሮድሪጌዝ መሳሪያህን ጣል ፖሊስ ነኝ
እንዳትተኩስባት!” የሚለው የጉድማን ድምፅ እንደ ህልም ሆኖ ይሰማት ጀመር፡፡
ሉዊስም ቢሆን ልክ እሷ የተሰማት አይነት ስሜት ነበር የተሰማው::
የሽጉጡን አፈሙዝ ግምባሯ ላይ ለጠፈው።

“ከኋላህ ነኝ ሉዊስ እንዳትተኩስባት” አለው፡፡

ኒኪም ጉድማን መሰላሉን ወርዶ ከሉዊስ ጀርባ ላይ ሽጉጡን እንዳነጣጠረ ተመለከተች፡፡ የደንብ ልብሱን ባይለብስም ሁሉ ነገሩ ግን በራስ
መተማመኑን እና ስልጣን ያለው መሆኑን ያሳያሉ። ግጥም ያለ መንጋጋው
እና ትዕዛዝ የሚሰጥበት ድምፁ ደግሞ ለዚያ ማሳያ ናቸው።

'የእኔ ህይወት ሊታደግልኝ ነው እዚህ ድረስ የመጣው! እና ጥልቅ የሆነ እፎይታ ሰውነቷን ወረራት።

ሮድሪጌዝም መሳሪያውን ወለሉ ላይ ጣላ እና ወደ ጉድማን ዞረ፡፡

ዘና ብሎ ጉድማንን ልክ በፊት እንደሚያውቀው ሰውም ያናግረው
ጀመር፡፡ “ፖሊስዬ አየህ አልገደልኳትም፡፡ ስለዚህ ለእሷ ያለህን ፍቅር ማሳየት ችለሃል” አለው እና ትንሽ ስቆ
“እሺ ከዚህ ቀጥሎስ ልታስረኝ ነው?” ብሎ ሁለቱን ክንዶቹን ወደ
ጉድማን ዘረጋ፡፡

ይሄ ሰውዬማ ዕብድ ነገር ነው፡፡ ብላ ኒኪ አሰበች። በቃ መጥፎ ብቻ ሳይሆን ዕብድ የአእዕምሮ ሆስፒታል ውስጥ ገብቶ ህክምና መከታተል የሚገባው ሰው ነው አለች በውስጧ፡፡

ጉድማንን ቀና ብላ እየተመለከተች በእስረኛው እጅ ላይ የእጅ ሰንሰለት
(ካቴና) ከማስገባቱ በፊት ለእስረኛው ስለመብቱ የሚናገረው ነገር ካለ ብላ
ጠበቀች፡፡ አዎን ሮድሪጌዝ ታስሮ ከአጠገቧ እስካልሄደ ድረስ ፍፁም ሰላም
አይሰማትም። መሳሪያ ባይዝ እንኳ በባዶ እጁ እንደሚጨርሳት..

ድው' የሚለው ብቸኛ የጥይት ድምፅ ተሰማት።
የሮድሪጌዝን ጭንቅላት አፈነዳው። የጭንቅላቱ የተበታተኑ አጥንቶች
እና አንጎሉም በብረት መሰላሉ ላይ፣ በኒኪ ልብስ ላይ፣ በኒኪ ፊት ላይ እና
እጆች ላይ ከደም ጋር ተቀላቅለው ተበታተኑ።

በዝግታ የጉድማንን ሬሳ ተሻግሮ ኒኪ ወደምትገኝበት ግድግዳ ተጠጋ እና
ለስላሳ እጁን ደም የነካውን ጉንጫ ላይ አሳረፈ።

“ልታስረው አልፈለግክም!”

“አዎን አልፈለግኩም!” ብሎ መለሰላት፡፡

ይሄኔም ኒኪ በሀይል መንቀጥቀጥ ጀመረች። በመቀጠልም በጣም
እየተንሰቀሰቀች አልቅሳ ተረጋጋች
“አመሰግናለሁ!” አለችው እና በሁለቱ እጆቿ አንገቱን አቅፋ ልጥፍ አለችበት።

ለጥቂት ጊዜ ያህል አቅፋው ከቆየች እና የደህንነት ስሜት ከተሰማት በኋላ ከእቅፉ ተላቅቃ ግድግዳውን ተደገፈች። እግሯ ሙሉ በሙሉ ደንዝዟል። ወደ ሆስፒታል በቶሎ መሄድ ይኖርባታል፡፡

“ህይወቴን ስላተረፍክልኝ እጅግ በጣም አመሰግናለሁ።” አለች እና በአይኗ አይኑን ፈለገችው፡፡

እሱም አይኑን መልሶ አይኗን ሲያያት ግን ለሰከንዶች ያህል ኒኪ ግራ ተጋባች:: አይኑ ውስጥ ቅድም ሮድሪጌዝ ሊገድላት ሲል ያየችውን ነገር ተመለከተች። ሰይጣንን፡፡

“በጣም የምትገርሚ ደደብ ሴት ነሽ” አላት እና ሽጉጡን ጭንቅላቷ ላይ
ደገነባት፡፡

ከዚያም ከፍተኛ ፍንዳታ ተሰማ እና ሁሉም ነገር ፀጥ አለ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ፊዮና ማክ ማን በጉድ ሰማርቲያን ሆስፒታል ውስጥ የምትሰራውን ስራ ትወደዋለች ፊዮና ነርስነትን እንደ ሥራ ሳይሆን እንደ የእጅ ሙያ ነው የምትቆጥረው፡፡ ማለትም ሌሎችን ለማገልገል በፈጣሪ ጥሪ እንደተደረገለት የቤተክርስቲያን አገልጋይ ነው የምታየው። “ጥሪያችንን ተከትለን በምንሥራው ሥራ አይደል እንዴ ገቢያችንን የምናገኘው?” እያለች እናቷ ጆኒ ትቀልድባታለች፡፡

እንደ ዕድል ሆኖ ደግሞ ሆስፒታሉ የሚከፍላት ክፍያ በጣም ጥሩ ነው።
በየቀኑ በጣም ጥሩ ሀኪሞች እና ነርሶች ጋር ነው የምትሰራው። በዚያ ላይ
ደግሞ የምታክማቸው ሰዎች የተለያዩ መሆናቸው ያዝናናታል። አንድ
አንዶቹ በጣም ህመም መቋቋም የሚችሉ ሰዎች ሲሆኑ፣ ሌሎች ደግሞ
ደጎች እና ሰዎችን አክባሪ ናቸው። አለ አይደል ለተደረገላቸው አገልግሎት
ምስጋናን የሚያቀርቡ ናቸው፡፡ በእርግጥ ሌሎችም አይነት ሰዎች አሉ::
የሚያመናጭቁ ሱሰኞች፣ በሽታቸው በጣም የሚያስቃያቸው ሰዎች ወይንም
ደግሞ ቁስላቸው እና በሽታቸው ሊታከምላቸው የማይችሉ ሰዎችም
ይገጥሟታል፡፡

ፊዮና የክፍሉን መጋረጃ ገልጣ ፀሐይ እንዲገባ ካደረገች በኋላ ዞር ብላ
አልጋው ላይ የተኛችውን ታካሚ ተመለከተቻት፡፡ እግሯ ላይ በጥይት
ተመታ እና ብዙ ደም ከፈሰሳት በኋላ ነው ወደዚህ ሆስፒታል ሌሊቱን ይዘዋት የመጡት፡፡ በጥሩ ሁኔታ የቀዶ ጥገና ከተደረገላቸውም በኋላ ቢሆን
አንድ አንድ በሽተኞች በጣም ሊጎዱ ወይንም ደግሞ ልባቸው ላይ ጉዳት
ሊደርስባቸው ይችላል፡፡ ወይንም ደግሞ ለሰዓታት፣ ለቀናት ወይም ደግሞ
ሳምንታት ያህል በደረሰባቸው አደጋ ሊሰቃዩ አዕምሮአቸው ሊረበሽ ይችላል
👍3
#የተወጋ_ልብ


#ክፍል_ሃምሳ_አንድ


#ድርሰት_በትክክል_ገና


...ከምሽቱ አምስት ሰዓት ተኩል ሆኗል፡፡ ሀብተ ጊዮርጊስ ድልድይ ከአስፋልቱ መንገድ ፈንጠር ብሎ
ከአቡነ ጴጥሮስ ሀውልት ወደ መርካቶ በሚወስደው መንገድ ላይ በስተቀኝ በኩል እርስ በርሳቸው ተደጋግፈው
ከቆሙት የጭቃ ቤቶች መካከል በአንደኛዋ ዳንኪራው ጦፏል፡፡
ቀን ቀን ቡና ቤት ውስጥ በገንዘብ ተቀባይነት በምትሰራውና ማታ ማታ ደግሞ በመኖሪያ ቤቷ ውስጥ የአልኮል መጠጦች እየሸጠች እንግዶቿን
በምታስተናግደው በማህሌት ቤት እየተደነከረ፣ እየተጨፈረ ነው።
ማህሌት በዚያ አጭር ቁመቷ ላይ የለበሰችው ጮማ ተከምሮ በድንገት ስትታይ የምትገላበጥ እንጂ የምትራመድ መሆኗ የሚያጠራጥር ቀይ አፍንጫ ጎራዳ ሴት ናት። ማህሌት ወደዚያ ስትሄድ ወደዚህ የመጣች እየመሰላቸው ቁጭ ብለው የጠበቋት ጓደኞቿን ብዙ ቀን ጉድ
ያደረገች ጉደኛ ሰው ነች።በዚች ጠባብ ቤቷ ውስጥ የመሽኛ ግብዣ የተደረገላቸው ሰዎች ተሸኝተዋል። በመሥሪያ ቤት እድገት ያገኙ ሠራተኞች ማህሌት ቤት እያሉ እየተቀጣጠሩ ፅዋቸውን አንስተዋል፡፡ ለእንኳን
ደህና መጣችሁ እንግዶች ተጋብዘዋል፡፡ የተለያዩ የግብዣ ሥነ ሥርዓቶች በተለያዩ ጊዜያትና አጋጣሚዎች ተካሂደዋል፡፡ ማለፊያ ገንዘብ እስከተከፈላት ድረስ ማህሌት የሚያምሩ ጥርሶቿን ፍልቅቅ፣ ትሙክ፣
ትሙክ የሚሉ ጉንጮቿን ስርጉድ እያደረገች በጥሩ አስተናጋጅነት እንግዶቿን አስደስታ ሽኝታበታለች። ዛሬ በታደሰ አስተባባሪነት የመሸኛ ይሁን የመዝናኛ ውሉ ያልታወቀ ግብዣ እንድታዘጋጅ ተነግሯት አልኮል በያይነቱ ቀርቦ ጮማ እየተቆረጠ ሊጠጣ... ሊዘለል... ሊጨፈር... የጠየቀችው ሞቅ ያለ ክፍያ ተከፍሏታል። በዚህ የግብዣ ሥነ ሥርዓት ላይ የሚገኙት አምስት ወንዶች ናቸው።
ሙዚቃው ጦፏል!ተጋባዦቹ ከሙቀቱና ከሙዚቃው ጋር እንደ ውሃ የሚጨልጡት አልኮል ተጨምሮበት መስከር ብቻ ሳይሆን እብደት ቀረሽ ዝላይ እየዘለሉ ናቸው። በስካር ላይ ስካር የሚጨምረው የሚያብረከርከው ሙዚቃ ደግሞ በረጅሙ ተለቋል...
አንቺ ከቶ ግድ የለሽም፣
ስለፍቅር አልገባሽም፣
ሁሉን ነገር እረስተሽው፣
ችላ ብለሽ ስለተውሽው፣
ቻልኩት ፍቅርን... ለብቻዬ፣
ስለዚህ ትቼሻለሁ ይቅር፣
ስላልገባሽ የፍቅር ሚስጥር፣
ትቼሻለሁ አትምጪ ይቅር፣
እችክ፣ እችክ፣ እችክ፣ እችክ፣እችክ.....
ወገብ ብጥስ ቅንጥስ ይላል፡፡ አንዳንዱ ደናሽ ሳይሆን ዳንግላሳ የሚመታ ፈረስ ይመስላል፡፡ ማህሌት የወንዶቹ ጭፈራና ዝላይ ፈንቅሏት እዚያ እመሀላቸው ገብታ እንደ ግንድ እየተገላበጠች ነው።መቼም ከጭንቅላት ቀጥሎ ያለው የሰው ልጅ አካል በማህሌት ዘንድ አለ ለማለት የሚያስደፍር አልነበረም፡፡ ያቺኑ አንገት ተብዬ እየወዘወዘች ከትከሻዋ እየ
ተርገፈገፈች እያሳበደቻቸው ነው። በአምስት ወንዶች መካከል የተገኘች ብርቅዬ... ሞናሊዛ ሆናላቸው ደብለል. ደብለል.. ዞር ዞር...ደግሞ ከትከሻዋ መታ መታ ወረድ... ቀና... እያለች ልባቸውን እያጠፋችላቸው ነው፡፡
ከታደሰ በስተቀር ሌሎቹ በደስታ ብዛት የሚሆኑትን አሳጥቷቸዋል።
አራቱም በየልባቸው ማህሌትን ተመኝተዋታል፡፡ ምን ችግር አለ? የራሳቸውን ስሜት የሚያረኩበት ብቻ ሳይሆን የሌላ ሰው ስሜት ጭምር የሚማርኩበት ረብጣ ገንዘብ ተይዟል። በዚሁ መካከል ግን ሰዓቱ እየበረረ ነበር። ማህሌት ወደ ታደሰ ጆሮ ጠጋ አለችና.....
“ታደስ እስከ ስድስት ሰዓት ብቻ አልነበረም እንዴ የተነጋገርነው? ሩብ ጉዳይ ሆነ እኮ! ሁኔታችሁን ስመለከተው ሙሉ ሌሊት የሚበቃችሁ አልመስለኝም” አለችው።ታደሰ እጇን ሳብ አደረገና
ወደ ጓዳዋ ውስጥ ይዟት ገባ።
“ማህሌት ከስድስት ሰዓት አንድ ደቂቃ ቢያልፍ የተነጋገርንበትን ዋጋበእጥፍ እከፍልሻለሁ፡፡ በዚህ በኩል በፍፁም ሃሳብ አይግባሽ፡፡ በኔ ተይው። ሰዓት አልፏል ብለሽ ጨዋታሽን እንዳትቀንሺባቸው ፊት እንዳትነሻቸው፡፡ እንደ ልባቸው ይጨፍሩ ይዝለሉ። ዛሬ የመዝለያ የመጨፈሪያ ቀናቸው ስለሆነ ሌላ ንግግር ተናግረሽ እንዳታስቀይሚያቸው”
ለስለስ ደግሞም ኮስተር ባለ አነጋገር አስጠነቃቃት። ልቧ ተረጋጋና ተያይዘው ወደ ጭፈራው መሃል ገቡ... አንዱ በአንዱ ላይ እየወጣ እየቦረቀ ለጤናችን እያለ መለኪያ ለመለኪያ እያጋጨ ተዝናና። ለሁሉም ነገር
ድፍረትና ወኔ የሚስጠውን አልኮል በብዛት ወስዶ ሰውነቱን በሚገባ
ወደ ሁለተኛዋ ክፍል አሟሟቀ፡፡ ታደሰ ወጣ ገባ እያለ አካባቢውን ያጠናል።
“የሙዚቃ ድምፅ ይቀነስ... ጩኸት ቀንሱ” እያለ የአካባቢው ነዋሪ እንዳይረበሽ ማስጠንቀቂያ እየስጠ ብቅ ጥልቅ ይላል።በዚያ ሀድራው በሚጨስበት፣ሙቀቱ ጨፋሪዎቹን በትኩስ ላብ በሚዘፍቅበት፣ ሙዚቃው
ልብ እየነጠቀ እንደ ጋላቢ ውሃ ሽቅብ በሚያዘልልበት፣ አልኮል እንደ ፏፏቴ በሚፈስበት፣ የሚገኘው የወደፊት ብሩህ ተስፋ የሚቆጠረው የገንዘብ ብዛት በሚያጓጓበት አስደሳች ዓለም ውስጥ እያሉ ልክ ስድስት
ሰዓት አናቱ ላይ ሲሆን “እጅ ወደ ላይ!” የሚል ድምፅ ሲሰማና በሩ ሲበረገድ አንድ ሆነ፡፡

ማህሌት ከድንጋጤዋ የተነሳ ያ ዝሆን የሚያክለው ግዙፍ ሰውነቷ እንደ ባሉን ቀላላትና እንደ ህፃን ልጅ ሮጣ አልጋዋ ስር ገብታ ተደበቀች።ከሁሉ ቀድሞ እጁን ያነሳው ታደሰ ነበር።

አለቃቸው እጅ መስጠቱን ሲያስተውሉ ሁሉም ተስፋ ቆረጡና እጆቻቸውን ወደ ሰማይ ሰቀሉ።በየኪሳቸውና በጉያቸው የደበቋቸውን ሰንጢዎች፣ ስንስለቶች፣ መሰርሰሪያ ለመሽሽግ ወይንም ለመወርወር ፋታ ኣላገኙም ነበር፡፡ ፖሊሶቹ እጅግ ቅልጥፍና በተሞላበት መንገድ ኪሶቻቸውን ፈተሹና መሳሪያዎቹን በቁጥጥር ስር አዋሉ፡፡ ብዛት ያለው ገንዘብና
ከታደሰ ኪስ የተገኘው አንድ ሽጉጥም በቁጥጥር ስር እንዲውል ተደረገ፡፡በዚህ ሁሉ ትርምስ ውስጥ ግን ያ ሽለምጥማጥ አበራ በጓዳ በር በኩል ተሽሎክሉኮ በር በርግዶ አጥር ጥሶ አጥር ዘሎ ሲያመልጥ ከታደስ ጋር አራቱ ተያዙ።

ፖሊሶቹ ወሮበሎቹን በቁጥጥር ሥር በማዋላቸው ምክንያት ዛሬ በሌሊት ቤቱን ሰብረው በመግባት ህይወቱን ለማጥፋት ቀብድ የተቀበሉበት የቡና ነጋዴው የአደም ሁሴን ህይወት ተረፈች። አስር ሺህ ብር ከአደም ላይ
የተበደረው ኡስማን አብደላ የተበደረውን ገንዘብ ለመመለስ ፈቃደኛ ሆኖ አልተገኘም። ጫማው ላይ ወድቆ ምሎ ተገዘቶ የተበደረውን ገንዘብ ከለከለው።
"ኡስማን ገንዘቡን ስትቀበለኝ የነበረህን ሁኔታ ታስታውሳለህ አይደለም?
ዘመድ አዝማድ ልከህ ደጅ ጠንተህ ከነወለዱ ለመክፈል ተስማምተህ ነበር። የኔ ፍላጎት ወለዱ ቀርቶ ዋናውን ብቻ እንድትመልስልኝ ነው፡፡
ከገባኸው ውለታ ውጪ አራት ወር ከአስራ አምስት ቀን ጠብቄሃለሁ።
እምቢ የምትለኝ ከሆነ ግን በህግ ልጠይቅህ እገደዳለሁ” ሲል አስጠንቅ ቆት ነበር።
ኡስማን የአደምን ማስጠንቀቂያ ከሰማ በኋላ አደም ገንዘቡን ስታበድረኝ የጽሁፍም ሆነ የሰው ማስረጃ እንዳለህ አውቃለሁ። እኔም ገንዘብህን ላለ
መስጠት ሳይሆን ሀጃዬ ስላልሞላልኝ ነው። እባክህ ትንሽ ጊዜ ስጠኝ?"በማለት ዋሽቶት ነበር። ጊዜ ስጠኝ ያለው ዕዳውን ለመክፈል ሳይሆን ነፍሰ ገዳዮችን በሁለት ሺህ ብር ገዝቶ አደምን ለማስገደልና ስምንት ሺህ
ብር ለማትረፍ ነበር፡፡ በዚሁ መሰረት እነኝህ ኡስማን የገዛቸው የወሮበላ ቡድን አባላት ለወንጀል መፈፀሚያ ከያዟቸው መሳሪያዎች በተጨማሪ ወንጀሉን ለመፈፀም የተቀበሉት ቀብድ ታደስ በሰጠው መረጃ መሠረት በቡድኑ አባል በጥጋቡ ኪስ ተገኘ፡፡ ታደስም ከወሮበሎቹ ጋር አብሮ እየተነዳ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ሄደ፡፡
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_ሃምሳ_አንድ


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ


...«እታች ቡና ቤት ውስጥ ሻይ እየጠባሁ እጠብቅሀለሁ፡» ተረጋግተህ ለባብስና ና
በዚሁ ተስማምተው ስዩም ከፎቁ ላይ ወደ ታች ወደ ቡና ቤቴ ወረደ.
በልሁ ግን ከመደናገጡና ከመቸኮሉ የተነሳ የአለባበስ ቅደም ተከተሉ ሁሉ ጠፋበት። ሳይፀዳዳና ሳይተጣጠብ ልብሱን ለባባሰ ሲያስታውስ የሚቀሩት ነገሮች አሉ።እንደገና መፀዳጃ፡ ከዚያም ወደ ፀጉር ማበጠር ግን ሁሉም ነገር በችኮላና በጥድፍያ ነው።
ሁሉንም ነገር እንደምንም ጨራርሶ ወደ ሆቴሌ ተንደርድሮ ሲወርድ ስዩም ያዘዘውን ሻይ ጠጥቶ ጨርሷል ፡፡ በልሁም” እንዲጠጣ ጋበዘው በልሁ ግን እሺ አላለም"፡ ይልቁንም የስዩምን የሻይ ሂሳብ ለመክፈል ተሽቀዳደመና ከፈለ፡፡ ከቡና ቤቱ ወጡና በስተግራ በኩል ወደ አባ ሻውል በሚወስደው ሰፊ
የአስፋልት መንገድ ላይ ወደ አስቻለው ቤት ጉዞ ተጀመረ፡፡ ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ተኩል አካባቢ ሆኗል፥
በልሁ ከስዩም ጋር አብሮ እየተራመደ ሳለ እግሮቹ በፍርሀት
ይንቀጠቀጣሉ፡፡ ከንፈሮቹ እየደረቁ ደጋግሞ በምላሱ ያርሳቸዋል፡፡ ጭራሽ ከስዩም እኩል ከጎኑ ሆኖ ለመራመድ እየፈራ ወደ ኋላ ቀረት ቀረት ይላል፡፡ብዙ ከተጓዙ በኋላ አንዲት የሀገር ልብስ የለበሱ ሴት ወይዘሮ አንዲት ልጅ እግር ቢጤ ሴት ዘንቢል አስይዘው ከፊትለፊት ሲመጡ አዩአቸው:: ከጥቂት ርምጃዎች በኋላ ይበልጥ ተቀራረቡ፡፡በኋላም ተገናኙ
«በጠዋት ወዴት እማማ አብረኸት?» ሲል ስዩም ቀድሞ ጠየቃቸው፡፡
«ለገበያ ወደ ኣባ ሻውል፡፡» አሉት ወይዘሮ አብረኸት በእጃቸው
ስዩምን ሰላም እያሉ በአይናቸው ደግሞ በልሁን እየተመለከቱ።
የት እንደሚያውቁት የሚያሰላስሉ ይመስላሉ፡፡
«የተዋወቁት፣ የአገር ወዳድ ወንድም ነው::»አላቸው ስዩም ፈገግ ብሎ ሁለቱንም ተራ በተራ እየተመለከታቸው፡፡
«አገር ወዳድ የኛ?» አሉ ወይዘሮ አብረኸት አሁንም በልሁን ትኩር
ብለው እያዩት::
«አዎ»
«ከአሁን ቀደም አላየሁህም እንዴ የኔ ልጅ?» ሲሉ ጠየቁት በልሁን::
«አይተውኛል፡፡ ከጥቂት ቀናት በፊት ከቤትዎ ጠላ ጠጥቻለሁ፡፡
«እኮ የሚሲዮኖችን ሀኪም ቤት የጠየከኝ?»
«አዎ»
«ዋይ የአገር ወዳድ ወንድም ኖረሀል እንደ? ታዲያ ገልፀህ አትነግረኝም" ኖሯል እንዴ ልጄ ቤቱን እኮ አሳይህ ነበር። ከኔም ጋር ብዙም አንራራቅ፣ ያው የጎረቤት ያህል ነው።
«አላወቅሁን የኔ እናት»
ወይዘሮ አብረኸት ወደ ስዩም ፊታቸውን መለስ አድርገው «ግን አገር ወዳድ ከኔ ቤት እልም ብሎ
መጥፋቱ ምን ሆና ይሆን ስዩሜ»? ለወትሮው እንኳ እኔ ጋር
ብቅ ሳይል አይውል አያድርም ነበር፡፡ ወይስ ያ ያመኛል የሚለው ነገር እየጠናበት ሄደ? ይኸው ዓይኑን ከአየሁት ሶስት ወይም አራት ወር ሊሞላኝ ነው።»አሉት
«እያመመው ነው እማማ አብረኸት»
«በቃ ደከመው?»
«መሰለኝ፡፡» አለ ስዩም በዓይኑ ሰረቅ አድርጎ በልሁን እያየ፡፡
የወይዘሮ አብረኸትና የስዩም ቃለ ምልልስ ለበልሁ የመርዶ ያህል
አስደንጋጭ ነበር፡፡ ብቻ ጣልቃ መግባት አልፈልግም፡፡ የሆዱን በሆዱ እምቅ አድርጎ የመጨረሻውን ለማየት በፍርሀት ይጠብቃል፡፡
ወይዘሮ አብረኸት ደረታቸውን በቡጢ መታ መታ እያደረጉ «ልጄን!ልጄን! ልጄን » ካሉ በኋላ «እስኪ ከተመቸኝ ዛሬ ከሠዓት በኋላ ብቅ እላለሁ፡አሊያም ነገ መጥቼ አየዋለሁ፡፡» ብለው ተሰናብተዋቸው ወደ ግቢያቸው አመሩና ስዩምና በልሁም መንገዳቸውን ቀጠሉ፡፡
በልሁና ስዩም የያዙትን የኮረንኮች መንገድ በመቀጠል ወደ ታች
ሲወርዱ ከወይዘሮ አብረኸት ቤት መድረሳቸውን በልሁ ልብ አለ፡፡ በዚያው ልክ ወደ አስቻለው ቤት መቃረባቸውን ተረዳና ልቡ የድንጋጤና የፍርሃት ከበሮ ይመታ ጀመር፡፡ የወይዘሮ አብረኸትን ቤት አልፈው ጥቂት ከተጓዙ በኋላ
ስዩም በግራ በኩል የሚገኝ አንድ አቋራጭ መንገድ ይዞ ታጠፈ፡፡ በልሁም ተከተለ፡፡ ጥቂት ከተራመዱ በኋላ ስዩም አሁንም በሌላ የግራ ኣቅጣጫ በሚወስድ መንገድ ይዞ ወደ ላይ ታጠፈ፡፡ በልሁ አሁንም ተከተለ፡፡ በፕላን
የተሰሩ አምስት ቤቶችን አልፈው ስዩም የስድስተኛውን ቤት የውጭ በር አንኳኳ፡፡
በዚህ ጊዜ በልሁ ሁለመናውን ላብ አጠለቀው፡፡ ትንፋሹ በረከተ፡፡
ደረቱ ወጣ ገባ ሆዱ ሞላ ሞሽሽ ይል ጀመር፡፡ በሩ እስኪከፈት ድረስ ሽንጥና ሽንጡን ይዞ በመቆም አንዴ ወደ መሬት ሌላ ጊዜ ወደ ሰማይ እያየ ተቅበጠበጠ፡፡ የአስቻለው መገኘት ነገር እንደ ህልም እልም ብሎ ይጠፋ
እየመሰለው ልቡ ቷ ቷ ቷ ይል ጀመር፡፡
የውጪው በር ተከፈተ፡፡ ፊትለፊት ከጥርብ ድንጋይ የተሰራ ዘመናዊ
ቪላ ቤት ለዓይናቸው ገጭ አለ፡፡ በረንዳው በብረት ፍርግርግ ተሰርቶ ነጭ ቀለም የተቀባ፡ የበርና መስኮቶቹ መስታወት ነጣ ባለ መጋረጃ አሸብርቀው የጥሩ
ኗሪዎች መኖሪያ የሚመሰል ነው:: ግቢው ተስተካክሎ የተደለደለ፡ በየአጥሩ አጠገብ የአበባ ተክሎች
የሚታዩበት እምር ድምቅ ያለ ነው።
ስዩም ወደ ዢላው አላመራም። በስተግራ በኩል ወደ ጓሮ በሚወስድ ቀጭን የእግር መንገድ ይዞ ተራመደ። በልሁም ተከተለው። በጓሮ በኩል አራት ክፍሎች ያሉት ረጅም የስነርቪስ ቤት አለ፡፡ የተሰራው ከጥርብ
ድንጋይ ቢሆንም ነገር ግን ሲሚንቶ የሌለው ደረቅ ካብ ነው፡፡ የአራቱም ሰርቪስ ክፍሎች በር መዝጊያቸው የቆርቆሮ ነው ስዩም መካከል ላይ ከሚገኙት ክፍሎች
ወደ አንዷ ተራመደና ገና በሩ ላይ እንደደረሰ «እንዴት አደርክ አገር
ወዳድ? ሲል ወደ ውስጥ ተናገረ፡፡ ቤቱ ገርበብ ብሎ" ተከፍቷል።
ከውስጥ በኩል ለስዩም ሰላምታ የተሰጠው የምላሽ ድምጽ ግን በተለይ ለበልሁ እጅጉን አስደንጋጭ ነበር እጅግ የደከመ እጅግ የሰለለና የአስቻለው ሊሆን ይችላል ብሎ ለማመን በጣም የሚያስቸግር ነበር፡፡ «ይመስገነው፡፡ ደህና ነኝ ስዩሜ!» የሚል ድምፅ ወጣ ከውስጥ በኩል፡ ግን ደግሞ ድምጽ እንደሚወጣ ላልጠበቀ ሰው ፍፁም ሊሰማ የማይችል ሁኔታ። የበልሁ ጆሮ ቀድሞ ባይ ኖሮ ሰው የተናገረ ሰለመሆኑ ባልታወቀው ነበር።
«እንዴት ነው ሻል አላለህ?» እያለ ስዩም ወደ ውስጥ ገባ በልሁ
ምንም አልተሻለኝም ስዩሜ፣ አሁንማ ከመኝታዬም ለመነሳት ሰው ሊያስፈልገኝ ነው፡፡ እየደከመኝና እያቃተኝ ሄደ፡፡ » የሚል ድምጽ ከውስጥ
ተሰማ፡፡ በዚህ ሰዓት በልሁ በር ላይ ቆሞ በፍርሀት ዓይን ወደ ውስጥ አየት ያደርግ ጀመር፡፡ ከራስጌው በኩል ክራንች ግድግዳ ተደግፎ አየ፡፡ በራስጌ ኮመዲኖ ላይ የምግብ ሳሀኖች ይታያሉ፡፡ ቀጥታ ወደ ታማሚው ሲያይ በግራ ፊቱ ላይ ጠባሳ ታየው፡፡ ነገር ግን ትራስ ላይ ካረፈው የታማሚው ጭንቅላት
በቀር ወደ ታች ያለተ ሰውነቱ ፍጹም ያለ አይመስልም፡፡ ከድምጹ መድከምና መሰለል በተጨማሪ የታማሚው ሰውነት ኣልቆ ከእልጋው ላይ የመጥፋቱ ነገር
ያ ሰው በእርግጥ አስቻለው ስለመሆኑ የበልሁ ልብ ሊያምን አልቻለም፡፡
«ስማ አገር ወዳድ! ዛሬ ደግሞ ዘመድ ዘዳድ ይዤልህ መጥቻለሁ፣ እስቲ እንደ ምንም ብለሀ ቀና በል፡ : " አለ ስዩም አልጋው ስር ቆሞ ታማሚውን
በተኛበት ቁልቁል እያየ::
«የኔ ዘመዶች እዚህ ድረስ አይመጡም፡፡» አለ ታማሚው ከውስጥ፡፡
👍8
#ምንዱባን


#ክፍል_ሃምሳ_አንድ


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ

...ሐኪሙ እስኪመጣ ማሪየስ ከተኛበት አልተንቀሳቀሰም:: አክስቱ ግን ከመኝታዋ ተነስታ ከአጠገቡ ቁጭ ብላለች:: «ወይኔ ጉዴ ፧ አምላኬ ከዚህ አውጣኝ» ብሎ ከማልቀስና ከወዲያ ወዲህ ከመንቆራጠጥ ሌላ ያደረገችው
ነገር አልነበረም::

ሐኪሙ ማሪየስን መረመረው:: እስትንፋሱ አለች፡፡ በጀርባው አስተኝቶ ቁስል እንደሌለበት ተረዳ፡፡ ልብሱንተ ሲያወልቁለት አክስትየው ወደ ውጭ ወጣች:: መቁጠሪያዋን ይዛ ትጸልይ ጀመር፡፡

ከጎድኑ ላይ ቁስል አለ፡፡ ግን በጣም ወደ ውስጥ የገባ ቁስል አይደለም::እጁም ላይ በጐራዴ ተመትቶአል፡፡ ከጭንቅላቱም ላይ እንዲሁ በመወጋቱ የደማ ቁስል አለ፡፡ ከግምባሩ ላይ አጥንቱ ተሰብሮ እንደሆነ ሐኪሙ በዝግታ
ነካካው:: ለመለየት አቃተው:: ሆኖም ሐኪሙን ከዚህ ሁሉ ይበልጥ ያሳሰበው የማሪየስ ነፍስ አለማወቅ ነበር፡፡ ብዙ ጊዜ ወንዶች ነፍሳቸውን ከሳቱ በዚያው ይቀራሉ እንጂ አይነቁም:: አሁን ታዲያ ማሪየስ ይነቃል ወይስ አይነቃም ሲል ተጨነቀ:: ብዙ ደም ስለፈሰሰው ሰውነቱ ዝሉአል::

ሴቶቹ የማሪየስን ቁስል ካጣጠቡ በኋላ ሐኪሙ እያዠ የሚወጣውን
ደም አቆመው፡፡ ጭንቅላቱን በቃገቃዛ ውሃና ሳሙና አጠቡት፡፡ ሐኪሙ የማሪየስን ግምባር እያሻሸ ሲጠራርግ በር ተከፈተ፡፡ በጣም ደነገጠና የገረጣ
ፊት ብቅ አለ፡፡

አያቱ ነበሩ፡፡ ሰውነታቸው እየተንቀጠቀጠ አንገታቸውን ብቻ ወደ ውስጥ በማስገባት ተመለከቱ፡፡ የሌሊት ልብስ ነው የለበሱት:: መቃብር
እንጂ ደህና ነገር የሚያዩ አይመስሉም፡፡ ማሪየስ አልጋ ላይ ተዘርሮና አዓይኑን ጨፍኖ ነው ያዩት:: እስከ መታወቂያው ራቁቱን ነው የተኛው::በጥፊ እንደ ተመታ ሰው ክው እንዳሉ ወደ አልጋው ተጠጉ:: ልባቸው በኃይል ይመታል፡፡

«ማሪየስ!» ሲሉ በዝግታ ተጣሩ፡፡

«አባባ» አለች አንደኛዋ ሠራተኛ «አሁን ነው ሰዎች ይዘውት
የመጡት:: ከጦርነቱ ቦታ ነበር ብለዋል፡፡›

«ሞቷል!» ሲሉ ሽማግሌው መጮህ ጀመሩ:: «ዶክተር» አሉ፤ «አንተ ነህ ሁሉንም የምታውቀው:: አንድ ነገር ብቻ ንገረኝ:: ሞቷል ፤ አይደል?»

ሐኪሙ በጣም ተጨንቆ ስለነበር መልስም አልሰጣቸውም::

ሽማግሌው እያጨበጨቡ ይስቁ ጀመር፡፡ ተደጋግሞ እንደተባለው
«ማሽላ እያረረ ይስቃል» ይሉ የለ!
«ሞቷል! ሞቷል! ከዚያ ከምሽጋቸው ወስጥ ነው የተገደለው! ሳንታረቅ! በጥላቻ ዓይን እየተመለከተኝ ነዋ ሕይወቱ ያለፈችው! ይኼ ርኩስ! ሞቶ ሬሣው ይምጣልኝ! ይኼ ነዋ የእኔ እጣ ፋንታ! ሞቷል! ሞቷል!»
ሐኪመ ማሪየስን ትቶ ወደ መሴይ ጊልኖርማንድ ሄደ:: ሰውዬውም
ዞር ብለው በአበጠ ዓይናቸው ተመለከቱት::

«ይቅርታህን ዝም እላለሁ፡፡ ምንም እንኳን ብዘ ሰው ከአጠገቤ
ሲለይ ባይም የአሁኑ በዚህ እድሜዬ አላስችል ስላለኝ ነው:: ብቻ በማያገባቸው ነገር ይገቡ፤ ይለፈልፉና ውጤታቸው ይሄ በመሆኑ አሳዘነኝ፡፡ ይጽፋሉ፤
ይናገራሉ፤ ወደፊት፤ ወደኋላ፤ አዲስ ሕይወት፧ ነፃነት፣ መብት፧ ሌላም ሌላም እያሉ ይጮሁና ሬሣ ይዘውልን ይመጣሉ፡፡ ብቻ ምን ይሆናል ይቅር! ልቻለው፤ አይ ልጄ ማሪየስ! ገደለህ፤ ከእኔ በፊት ሞትክ፣ ያሳደግሁት ልጄ እኮ ነው! ገና አንድ ፍሬ ሆኖ ሳለ እኮ ነው እኔ ያረጀሁት:: ታዲያ እኔ
ቆሜ እርሱ ይሙት:: እርሱ የፈጨውን አፈር እኮ አብረን አብኩተናል፡፡ እርሱ በሕፃንነቱ እኔ በስተርጅናዬ! ብቻ ምን ይሆናል ተዉት፡፡ ጠዋት ጠዋት ከመኝታ ክፍሌ እየሮጠ ሲመጣ፣ ስቆጣው፣ እርሱ ሲስቅ፣ የማታ
ማታውማ ከላዬ ላይ ካልወጣሁ ሲል «ኧረ እኔ አልችልም» እያልኩ
ስቆጣው ፧ የጨዋታ መሆኑ እየገባው አይቆጣ! ኧረ ስንቱን ላንሳው! የሕይወቴ ብርሃን ነበር፡፡ እንደዚህ ልጅ የሚወደድ ፧ አንጀት የሚበላ ሰው አጋጥሞኝ አያውቅም::»

ጠጋ ብለው አዩት:: አሁንም ነቅነቅ አይልም:: «እነዚህ አረመኔዎች»
ሲሉ ጮሁ:: የማሪየስ የዓይን ሽፋን ተነቃነቀ፡፡ በፈዘዘ ዓይን አያቸው፡፡
«ማሪየስ» ሲሉ ሽማግሌው ተናገሩ፡: «ማሪየስ፤ የእኔ ጌታ! ልጄ! ሕይወትህ አለ? አየኸኝ እኮ! ተመስገን፣ ተመስገን አምላኬ!»
ነፍሳቸውን ስተው ከመሬት ተዘረሩ::
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ዣቬር መስመር ሲለቅ

ዣቬር እያዘገመ ከገዣን ቫልገዣ ቤት ወጥቶ ሄደ:: የሚራመደው
እያቀረቀረ ነው:: በሕይወቱ ለመጀመሪያ ጊዜ እጁን ወደኋላ አድርጎ ተራመደ:: ፀጥ ካለው አውራ ጎዳና ውስጥ ደረሰ፡፡ ዝም ብሉ ብቻ ወደፊት ነው የሚሄደው:: ወደ ሳይን ወንዝ የሚወስደውን መንገድ ይዞ ነው የሚጓዘው::
ትልቅ ድልድይ ካለበት ስለደረሰ የድልድዩን አግዳሚ ብረት ተደግፎ
ቆመ:: በጣቶቹ ሪዙን እያፍተለተለ አገጩን በእጆቹ ደግፎ ነው የቆመው::በሀሳብ ነጉዷል።

ሰውነቱ ውስጥ አዲስ ነገር፣ አንድ ዓይነት ለውጥ፣ እረፍት የሚነሳ
ስቃይ እየተፈራረቀ ነው:: ራሱን ማለት የግል ሕይወቱን ይመረምር
ጀመር፡፡

በሚያሳዝን ሁኔታ ዣቬር እየተሰቃየ ነው:: ዣቬር ልክ አልነበረም::ጥቂት ሰዓት አለፈ:: አንጎሉ ተረበሽ፣ ሁለም ነገር ተመስቃቀለበት::ስለሥራው የነበረው ደንዳና እምነት ላላ፡፡ ህሊናው ውስጥ የነበረው
የማይደፈር ሥልጣን ዋዠቀ፡፡ ይህን ሁኔታ ከራሱ ሊሸሽገው አልቻለም:: ይች ካልጠበቀው ቦታና ባላሰበው ጊዜ ዣን ቫልዣን ከወንዞ ዳር አገኘው:: ዣን
ቫልዣን ሲያገኘው ጥምቡን መልሶ እንዳገኘ ተኩላ ወይም የጠፋበትን ጌታ እንዳገኘ ውሻ ዓይነት ስሜት ነበረው::

ሁለት ዋና መንገዶችን አየ:: ከሁለቱ ዋና መንገዶች የትኛው ነው ! እውነተኛ? ልቡ ፈራ:: እድሜ ልኩን ያየው የነበረውና ትክከለኛ ነው ብሎ የሚያምንበት አንድ መንገድ ብቻ ነበር፡፡ አሁን ግን ሁለት ሆኑበት፡፡ ጨርሶ ግራ ተጋባ፡፡ ለማንኛውም ከህሊናው ውስጥ ምን ይተራመስ እንደነበር
አረጋግጦ ለመጻፍ ትንሽ ያስቸግራል::

አንድ ነገር ግን በጣም አስገርሞታል፡፡ ይኸውም የእርሱ ሕይወት በዣን ቫልዣ ምክንያት መትረፉንና የዣን ቫልዣ ሕይወት ደግሞ ከእርሱ ምህረት ማግኘቱ ነበር፡፡ የት ነው ያለው? አሁን ምን ይሥራ? ዣን ቫልዣን ይርዳው? ትክክል ሥራ አይሆንም:: ዣን ቫልዣ ነፃ ይውጣ? ስህተት ይሆናል፡፡ ታዲያ ከከፍተኛ ማዕረግ ላይ ያለ ሰው ከአንድ እስረኛ
ይነስ? በሌላ አንፃር ደግሞ ወንጀለኛ ከሕግ በላይ ሆኖ ሕግን ሲረግጥ? በሁለቱም መንገድ ቢሆን ለእርሱ ለዣቬር ውርደት ነው::

በሕይወት ዘመናችን የምንደርስባቸወ እንደዚህ ያለ ምርጫ የሚያሳጡና መፍትሔ ከሌለው ነገር ጫፍ የሚያደርስ አጋጣሚዎች አሉ:: እነዚህ አጋጣሚዎች መያዣ ወይም መጨበጫ የሚያሳጡ ናቸው::
ዣቬር ከእንደዚያ ያለ ፈተና ውስጥ ነበር የገባው::

የጭንቀቱ መነሻ ከአሳብ ውስጥ እንዲገባ መገደዱ ነው:: እነዚያ
ተቃራኒ አሳቦች ናቸው እንዲጨነቅና እንዲያስብ ያደረጉት: አሳብና ጭንቀት
ለእርሱ እንግዳ ነገሮች ናቸው:: አዲስ በመሆናቸውም አሰቃዩት፡፡ እርሱ የለመደው አንድን አሳብ «ወደፊት» ማራመድ ብቻ ነበር:: አሳብ ጭንቅላታችን ውስጥ በሚገባበት ጊዜ ለአንድ ድርጊት የሚገፋፋን የአመፅ ስሜት በውስጣችን አለ፡፡ ይህ ዓይነት ስሜት ስላደረበት ዣቬር ተናደደ፡፡

ታዲያ ከምን ውሳኔ ላይ ይድረስ? ያለው ምርጫ አንድ ሲሆን
ይኸውም ወደ ዣን ቫልዣ ቤት ተመልሶ ሄዶ ዣን ቫልዣን ማሰር ነው፡፡ ከአንድ የፖሊስ አዛዥ የሚጠበቀውም ይኸው ነው፡፡ ግን እንዴት አድርጎ! አይችልም፡፡ ይህን እንዳይፈጽም መንገዱን የዘጋበት ነገር አለ፡፡
👍16
#ሳቤላ


#ክፍል_ሃምሳ_አንድ


#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ


ከአንድ ዓመት በላይ ዐለፈ።

የጀርመን ያባሕር ዳርቻ መዝናኛዎች በመከሩ ወራት ጀመሪ ላይ በሕዝብ
ተጨናንቀዋል " እነዚህ ቦታዎች በዚሀ ወራት በብዛት እየጉረፉ በሚመጡ እንግሊዞች መሞላታቸው የተለመደ ነው ከጥቂት ጊዜ በኋላ እንደገና ወደ አገራቸው ይመለሳሉ " ስታልከንበርግ በተለይ በዚያ ዓመት በእንግዶች ጢም ብላ ተሞልታለች
ከተማይቱ ስሟን ዝናዋን ሌላም የሷ የሆነ ነገር ሁሉ ያገኘችው ከባላባቱ ከባሮን ቮን እስታልከንበርግ ነው ባርኑ ትክለ ቁመናው ግዙፍና ጠንካራ ጢሙና የራስ ጸጉሩ ሽበት የቀላቀለ ከዕድሜውም ገፋ ያለ በሥን ምግባሩ በአደን
ከሚገድላቸው ከርከሮዎች ያልተሻለ ስድ ነበር በግዝፈት ባባታቸው መጠን የወጡ አራት ወንዶች ልጆች ነበሩት » የመጀመሪያ ልጁ አብዛኛውን ጊዜ ትንሹ ባሮን
ሲባል ሶስቱ ግን የስታልከን በርግ ካውንቶች በሚል የማዕረግ ስም ይጠራሉ » ስለዚህ አንዱን ከሌላው መለየት የሚቻለው በክርስትና ስማቸው ነው ሁለቱ ወታደሮች ሆነው ሔደዋል የመጀመሪያውና የመጨረሻው ልጆች ግን ከአባታቸው ጋር እስታልከን በርግ ግምብ ውስጥ ይኖራሉ ይህ የወላለቀ አሮጌ ግምብ የሚገኘው
ከእስታልከንበርግ ከተማ አንድ ማይል ያህል ወጣ ብሎ ነው " ወጣቱ ባሮን ለማግባት ነፃ ነበር » ሦስቱ ግን ራሷንና ባለቤቷን ማስተዳዶር የሚያስችል ሀብት ያላት ሚስት ካላገኙ በቀር ትዳር ለመያዝ አልፈለጉም ።

እስታልከንበርግ መሰሎቿ ከሆኑት ሌሎች የመዝናኛ ሥፍራዎች የምትለይበት የላትም የሚያምሩ ዛፎች ደስ የሚል ጠቅላላ ትዕይንት የዳንስ የሙዚቃ
ትዕይንት በትእዛዝ የሚዘጋጅ ምግብ ሕዝብ የሚራኮትባቸው የቁማር ጠረጴዛዎች የእግር መንሸራሸሪያ ቦታዎችና የመታጠቢያ ጸበሎች አሏት በተለይ ጸበሎቹ በብዛት ከታጠቡባቸው ማንኛውም ዐይነት በሕሊና የታሰበ በአካል የደረሰ በሽታ ሁሉ ማለት ከሚጥል ሕመም እስከ ፍቅር ትኰሳት ድረስ ይፈውሳሉ እየተባለ በሰፊው ይነገርላቸዋል ይታመንባቸዋል " ለብዙዎቹም እንደ እምነታቸው ተሳክቶላቸዋል

ወጣቱ ባሮን ካባቱ ጋር በማስተያየት ወጣት ተባለ እንጂ ዐርባ አንድ ዓመት
ሞልቶታል በመልኩና በአውሬ አዳኝነቱ ስመ ጥር ሰው ነው " በተለይ የከርከሮና የተኩላ ፀር መሆኑ በስፋት ይነገርለታል ከወንድሙ በዐሥራ አንድ ዓመት ያንስ የነበረው ካውንት ኦቶፎን እስታልክንበርግ ሪዙን በማፍተልተል በመብላትና
በመጠጣት ልማድ ካልሆነ በቀር ሌላ የሚታወቅበት ሙያ የለውም ሽማግሌው
ባሮንም ሆነ ወራሹና የመጀመሪያ ልጁ ወጣቱ ባሮን ስለ መዝናናትና ስለ ቅንጦት ተጨንቀው አያውቁም " የእስታልክንበርግ ግንብ ምግብ እምብዛም
እንደነበር ይነገርለታል ስለዚህ ካውንት ኦቶ ጋባዥ ባገኘ ቁጥር ከሆቴሉ እየሔደ ለመመገብ
ዐይኑን አያሽም ካውንት ኦቶ እስቶልከንበርግ ሙሉ ባለቤትና አስተዳዳሪ በመሆኑ በራሱ ከባድ ማዕረግና ባባቱ ሙሉ ባለሥልጣንነት በመጠቀም በየጊዜው እየተጋበዘ ከሆቴሉ ይመጣል ።

በቦታው የሚገኘው የታወቀው ሆቴል ሉድቢግባድ ይባላል " ሚስተር ክሮ ሰቢ የተባለ ሰው ሚስቱንና ተከታይ የሌላት አንዲት ልጁን የሷን አስተማሪና ሁለት ወይም ሦስት የቤት ሠራተኞችን ይዞ ከዚሁ ሆቴል ዐርፋል
ኢንግላንድ ውስጥ የሰራው
ነገር ወይም የደረሰበት በደል አይታወቅም እሱ ግን ወደ ትውልድ አገሩ ሊመለስ ቀርቶ አስቦት አያውቅም » በውጭ አግር ከቦታ ወደ ቦታ እየተዘዋወረ መኖር ከጀመረ ብዙ ዘመን ሆኖታል

ሚስዝ ክሮስቢይ የደስ ደስ ያላት ተጫዋች ሴት ስትሆን ልጂዋ ሑሌና ክሮስቢም
ደስ የምትል ያሥራ ሰባት ዓመት ቆንጆ ናት ልጂቱ በመልኳም በጠባይዋም ሆነ በአካሏ መዳበር የትልቅ ሰው ሁኔታ ስለሚታይባት ላላወቃት ሰው በዕድሜዋም የበሰለች ትመስላለች » ከዚህም በላይ አንድ አጎቷ ሲሞት ባመት ሠላሳ ሺህ ፓውንድ የሚያስገኝ ውርስ ትቶላታል እናቷ ስትሞት ደግሞ የዐሥር ሺህ ፓውንድ
ያመት ገቢ ውርስ ትጠብቃለች » ካውንት
ኦቶ ፎን እስታልከንበርግ ስለ ሠላላ ሺህ ፓውንድ ውርስ ሲሰማ ፊቱን ወደ ሚስ ሔሌና መለሰ "

“ እንዴ ሠላሳ ሺ ፓውንድና ቆንጆ ልጅ ! ታዲያ እኔስ ከዚህ ሌላ ምን ስጠብቅ ኑሬአለሁ ! አለ ለራሱ "

ስለ ሀብቷ የሰማው ወሬ ትክክለኛ መሆኑን አረጋገጠ " ከዚያ ወዲህ ከክሮስቢ
ቤተሰብ ጋር መቃረብ ጀመረ የዘወትር ጠያቂያቸው ሆነ እሱ ከነሱ ባይለይ ደስ እንደሚለው እነሱም የሱን ቀረቤታ ወደዱት ሌሎች የእስታልከንበርግ እንግዶች ቀኑበት እነሱም ያችን መሳይ ቆንጆ ካለችበት ቤተሰብ ጋር መወዳጀትን ተመኙ " ሚስተር ክሮስቢ ግን ወጣቱን ካውንት ልጁና ሚስቱ ባዩት ዐይን አይቶት
እንደሆነ አይታወቅም " በትሕትና ሲቀርበው እሱም በደስታ ይቀበለዋል "

አንድ ቀን ሽማግሌዉ የእስታልንከንበርግ ባሮን በሠረገላ መጣ " መቸም የሠረገላው ቅርጽና የብር ጌጦች ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ ታይቶ አይታወቅም " የአያቶቹ ኩራትና ቅርስ ሆኖ በክብር ተቀምጧል ኑሮ ኑሮ አንዳንድ ጊዜ ካልሆነ በቀር
ከተቀመጠበት አይነቃነቅም በብር ያጌጠ አረንጓዴ ልብስ የለበሱ ምርጥ አሽከሮች አጅበውት ከሎድቪግ ባድ ሆቴል በራፍ ተጠግቶ ቆመ የሆቴሉ ኗሪ በየመስኮቱ
ሆኖ ለማየት ግልብጥ ብሎ አሰፈሰፈ " ሽማግሌዉ መኮንን የመጣው ሚስተር ክሮስቢ ዘንድ ስለሆነ እሱም በታላቅ አክብሮት ተቀብሎ ወደ ሳሎን አስገባው “ ኃያሉ ባሮን ከዚያ ወይም ከዚ Oረፍ ይበሉ ! አለው …

“ ኃያሉ ባሮን የመጣው ክሮስቢን ከሚስቱና ከልጁ ጋር ግብዣ ሊጠራው
ነው " በባሮኑ ቤተ ግምብ ከዚያ በፊት ያልታየ ታላቅ ድግስ ካለፈ ጥቂት ቀኖች
ቆይቶ ካውንት ኦቶፎን እስታልከንበርግ ልጂቱን ሔሌናን ለሚስትነት ለመነ "
ጥያቄውም ተቀባይነት አላጣም ።"

“ ገና ልጅ ናትኮ ” አለ ሚስተር ክሮስቢ በቅሬታ ሁለት ዓመት ብቻ ቢጠብቁ ስለ ጥያቄዎቹ ምንም ተቃውሞ አይኖረኝም ነበር

“ እንዴ እንዴ ! ሁለት ዓመት ይጠብቅ ብለን ሌሎች ይውሰዱብን ብለህ ነው
አይሆንም ተው እነዚህ የእስታልከንበርግ ካውንቶች እኮ አይታመኑም ” አለችው ሚስቱ።

ታድያ ቢሆንሳ ! እሱ በማዕረጉና በሐረጉ ቢመካ ሔሌና ደግሞ በገንዘቧ ትመካለች።

እንግዲያ በደንብ ተመጣጥነዋል ማለት ነው " እኔ ደግሞ እሱን አላሰብኩትም ካውንቴስ ፎን እስታልከንበርግ ሲል ብቻ ለጆሮ ደስ ሲል አዳምጠውማ !

“ ያን ቀፋፊ ሪዙን ወዲያ ቢጥለው ደስ ባለኝ ” አለ ሚስተር ክሮስቢ "

“አንተ ደሞ የማያሳስበው ጥቃቅኑ ነገር ሁሉ ያሳስብሀል ሔሌና እንደ
ሆነች በጣም ወዳለታለች » አሁን የቸገረን ያስተማሪዋ ነገር ነው።

"የሷ ደግሞ ምንድነው ችግሯ ?

እኔ የቀጠርኳት እስከ ገና ስለሆነ ሌላ ስራ ካላገኘሁላት እስከዚያ ድራስ
ደሞዝ መክፈል ሊኖርብኝ ነው "

“እንደ እኔስ ሄሊና አሁን ከምታገባ ከአስተማሪዋ ጋር ብትቆይ ይሻል ነበር"
ሴቶች ልጆች በትንሽነታቸው ሲያገቡ ደስ አይለኝም " አሁን እዚህ ያሉ እንግሊዞች
ምን እንደሚሉ አላውቅም ።

አንተ ካልተናገርክ በቀር ስለ ዕድሜዋ ማንም አያውቅም ዛሬ እሷ ለራሷ ሙሉ ሴት እንጂ ልጅ አትመስልም እንግሊዞችማ እንደዚያ ያለ ዕድል ለነሱ ስላልገጠማቸው በቅናት ከመብሰልሰል በቀር ሌላ ምን ሊሉ ኖረዋል?

ሚስተር ክሮስቢ ተቃውሞው ሁሉ እየከሸፈ ሲያስቸግረው ዝም አለ "
በዚህ መነታረኩ ዋጋ እንደሌለው ዐወቀው "

ሔሌና ክሮስቢ ደሞ በበኩሏ ወደ አስተማሪዋ እየሮጠች ሒዳ ! ማዳም ማዳም ባል ላገባ እኮ ነው ! " አለቻት "

ማዳም ጥውልግ ያለውን ፊቷን ቀና አድርጋ አየቻትና እውነት !” አለቻት
👍152
#ጠላፊዎቹ


#ክፍል_ሃምሳ_አንድ


#በኬንፎሌት


#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ


ጎረምሳውና ጆ ውሃ ውስጥ እየሰጠሙ ስታይ ጮኸች፡፡
ወጣቱ ልጅ ወደ ላይ ለመውጣት ሲሞክር ጆ ደግሞ ህይወቱን ለማትረፍ ወጣቱን ወደ ታች ይጎትታል፡፡ በጣም አስፈሪ ሁኔታ ነው የሚታየው፡፡
ማርጋሬት መጮኋን ሰምቶ ሉተር በመስኮት ተመለከተና ‹‹ባህሩ ውስጥ ወድቀዋል››› ሲል ጮኸ በጭንቀት፡፡

‹‹እነማ ናቸው?›› አለ ቪንቺኒ፡፡

‹‹ጎረምሳውና ጆ›› አለ ሉተር፡

የጀልባው ነጂ ገመድ ቢወረውርላቸውም ሁለቱ ሰዎች አላዩትም፡፡ እነሱ
የሚይዙትን አጥተው በፍርሃት ውሃ ውስጥ እየተንቦራጨቁ ሲሆን ጆ
ጎረምሳውን ልጅ ወደ ባህሩ ውስጥ እየደፈቀው ነው፡፡

‹‹እባክህ እርዳቸው›› አለ ሉተር እሱም በፍርሃት እየተንቀጠቀጠ፡፡

‹‹ምን?›› አለቪንቺኒ ‹‹ምንም ልንረዳቸው የምንችለው ነገር ያለ
አይመስለኝም፡ እነሱም ራሳቸውን ለማዳን አቅም የላቸውም፡፡›› በመጨረሻም
ሁለቱን ሰዎች ጨካኙ ባህር ሰለቀጣቸው፡

‹‹እንዴት ሊሆን ቻለ?›› ሲል ጠየቀ ሉተር ‹‹በመጀመሪያ ውሃ ውስጥዐእንዴት ሊወድቁ ቻሉ?››

‹‹ምናልባት የሆነ ሰው ገፍቷቸው ይሆናል›› አለ ቪንቺኒ፡

‹‹ማን?››

‹‹እዚህ አይሮፕላን ውስጥ የሆነ ሌላ ሰው ይሆናል፡›› ማርጋሬት የሁለቱን ሰዎች ንግግር ስትሰማ ስለነበር ሄሪ ሊሆን ይችላል› ስትል
ገመተች፡ ሄሪ ጀልባው ውስጥ ይኖር ይሆን?
ፖሊሶቹ አይሮፕላኑን
ሲፈትሹ እሱ የሆነ ቦታ ተደብቆ አይሮፕላኑ ባህሩ ላይ ሲያርፍ ከተደበቀበት
ወጥቶ ይሆን? ሁለቱን ወሮበሎች ውሃ ውስጥ ገፍቶ የጨመራቸው እሱ
ይሆን? እያለች መልስ የሌለው ጥያቄ በአዕምሮዋ ተጉላላ፡፡

በኋላ ደግሞ ወንድሟ ትዝ አላት ፔርሲ የወሮበሎቹ ጀልባ ከአይሮፕላኑ ጋር በሚታሰርበት ጊዜ ነው የጠፋው፡፡ ‹ምናልባትም መጸዳጃ ቤት ሄዶ ግርግሩ እስኪያልቅ እዚያው ሊቆይ አስቦ ይሆናል› አለች በሆዷ፡
እሱ ደግሞ እንዲህ አይነት ባህሪ የለውም፡፡ እሱ እንደውም ሁሉን ነገር
ለማወቅ ስለሚፈልግ ችግር አይፈራም፡፡

ሉተር ‹‹ሁሉ ነገር ከእጃችን እየወጣ ነው ምን ብናደርግ ይሻላል?›› ሲል ጠየቀ፡

‹‹አሁን በመጣችው አይሮፕላን እንሄዳለን እንዳቀድነው፡፡ አንተ፣ እኔና
ሳይንቲስቱ›› አለ ቪንቺኒ፡ ‹‹መንገዳችንን ሊያሰናክል የሚሞክር ሰው ካለ
በሆዱ ጥይት ልቀቅበት፡ አሁን ረጋ ብለን እንውጣ፡፡››
ማርጋሬት ወሮበሎቹ ፔርሲን ደረጃው ላይ ያገኙትና በሆዱ ጥይት
ይለቁበታል ብላ ሰጋች፡
ሶስቱ ሰዎች ከምግብ ቤቱ ሲወጡ የፔርሲ ድምጽ ከበስተኋላቸው
ተሰማ፡፡ ድምጹንም ከፍ አድርጎ ‹‹እንዳትነቃነቁ!›› አለ፡፡
ፔርሲ ቪንቺኒ ላይ ሽጉጡን መደገኑን ስታይ ማርጋሬት ዓይኗን ማመን አቃታት፡፡ የሽጉጡን አፈሙዝ አይታ ካፒቴኑ ከኤፍ.ቢ.አዩ ሰውዬ
ላይ የነጠቀው መሆኑን ገመተች፡

ቪንቺኒ ቀስ ብሎ ወደ ፔርሲ ዞረ፡፡

ማርጋሬት የወንድሟ ህይወት አደጋ ላይ ቢሆንም በፔርሲ ኮራች፡፡

የመብል ክፍሉ በሰው
ተሞልቷል፡፡ ከቪንቺኒ ኋላ ማርጋሬት ከተቀመጠችበት አጠገብ ሉተር በሃርትማን ላይ ሽጉጡን ደግኗል፡ በሌላኛው በኩል ናንሲ፣ መርቪን፣ ዳያና፣ ኤዲ እና ካፒቴኑ ቆመዋል ቪንቺኒ ፔርሲን ዘለግ ላለ ጊዜ አየውና ‹‹ልጅ ከዚህ ጥፋ›› አለው፡፡

‹‹ሽጉጥህን ጣል!›› ሲል ፔርሲ አዘዘ፡፡

በመሃል አንድ ጥይት ጮኸች፡፡ የጥይቱ ድምጽ ጆሮ ያደነቁራል፡
ማርጋሬት ጩኸቷን አቀለጠችው: ማን ማን ላይ እንደተኮሰ አላወቀችም:: ፔርሲ ምንም አልሆነም፡፡ ትንሽ ቆይቶ ቪንቺኒ ከደረቱ ላይ ደም እየተንፎለፎለ ተንገዳገደና መሬት ዘፍ አለ፡፡ በዚህ ጊዜ ቦርሳው
ሲወድቅ ተበረገደና ብሮቹ በደም ታጠቡ፡

ፔርሲ ቪንቺኒን ሲያይ ሽጉጡን ጣለ፡፡ ደንግጧል፡
ሁሉም ሰው ሽጉጥ የያዘው የመጨረሻው ወሮበላ ላይ አፍጧል፡

ካርል ሃርትማን በተፈጠረው
ሁኔታ ከተዘናጋው ሉተር መንጭቀው ራሳቸውን ነጻ አደረጉና መሬት ያዙ ማርጋሬት ሳይንቲስቱን ይገድላቸዋል ብላ ሰግታለች ፔርሲንም እንዲሁ፡ ነገር ግን ወዲያው የሆነው ግን
አስደንግጧታል፡፡

ሉተር አፈፍ አድርጎ ያዛት፡ ከወንበሯ ጎትቶ አነሳትና ጭንቅላቷ ላይ ሽጉጡን ደገነባት፡፡ በዚህ ጊዜ ሁሉም በድንጋጤ በድን ሆኑ።

ማርጋሬት ፍርሃት ስለገባት መንቀሳቀስ መጮህ አልቻለችም፡ የሉተር
ሽጉጭ ጭንቅላቷን እየወጋት ነው፡ ሉተር ራሱ ይንቀጠቀጣል፡፡ ከዚያም
ሳይንቲስቱን ‹‹ውጣና ጀልባ ውስጥ ግባ፡፡ ትዕዛዜን ካልፈጸምክ ልጅቷ
ጭንቅላት ላይ ጥይት እቀረቅርበታለሁ›› አለ፡፡
ወዲያው ፍርሃቷ ሲለቃት ታወቃት፡፡ ሉተር  ብልህ መሆኑን ተገንዝባለች፡፡ ሽጉጡን ሃርትማን ላይ ደግኖ ቢሆን ኖሮ ሃርትማን ግደለኝ ጀርመን አገር ከምመለስ ሞቴን እመርጣለሁ› እንደሚሉ እርግጠኛ ሆኗል፡ አሁን ግን የእሷ ህይወት አደጋ ላይ ነው፡ ሃርትማን ምናልባት
ህይወታቸውን ለመስጠት ዝግጁ ይሆኑ ይሆናል፡፡

ሃርትማን ቀስ ብለው ተነስተው ቆሙ፡፡

ሁሉም ነገር በማርጋሬት ላይ የተጣለ ነበር፡ ራሷን ሰውታ ማዳን ትችላለች፡ ሆኖም ይህ አድራጎት ጥሩ አይደለም፡፡ እሷም ይህን አደርጋለሁ ብላ አልጠበቀችም፡፡ ለዚህ ራሴን አላዘጋጀሁም፡፡ ማድረግ አልችልም› አለች
በሆዷ፡
ከአባቷ ጋር ዓይን ላይን ግጥም አሉ፡፡ አባቷ በጣም ደንግጠዋል ሲያበሻቅጧት እንደኖሩ ምን ያህል
አቅመቢስ እንደሆነች ጦሩንም ተቀላቅላ አንድ ቀን እንኳን እንደማትቆይ
የነገሯት ሁሉ ትዝ አላት፡፡
አባቴ ያለው እውነት ይሆን?› አለች ለራሷ፡
ስለዚህ አንድ ነገር ማድረግ እንዳለባት ወሰነች፡፡ ሉተር ሊገላት ይችላል ነገር ግን አንድ ነገር ከማድረጉ በፊት ሌሎች ሰዎች ዘለው ይረባረቡበታል ጊዜው እየሄደ ነው፤ አንድ ነገር ማድረግ አያቅተኝም, አለች በሆዷ፡

ከዚያም ‹‹ሁላችሁም ደህና ሁኑ›› አለች፡፡ አፍታም ሳይቆይ የሄሪን ድምጽ ከኋላዋ ሰማች፡፡

‹‹ሚስተር ሉተር ጠላቂው መርከብህ ደርሷል›› አለ፡፡

ሁሉም ሰው በአይሮፕላኑ መስኮት ተመለከተ፡፡ ማርጋሬት ሄሪ በተናገረው ነገር ሉተር ልቡ መወሰዱን አወቀች፡፡ ከዚያ አንድ ጥይት ጮኸች፤ እሷ ግን ምንም አልሆነችም፡፡ ሁሉም አንድ ጊዜ ተንቀሳቀሰ፡፡ ኤዲ ዘለለና እንደ ተቆረጠ ዛፍ ሉተር ላይ ወደቀበት፡፡ ሄሪ የሉተርን ሽጉጥ
መንጭቆ ወሰደ፡፡

ፔርሲ ወደ ማርጋሬት ሄደና አቀፈችው፡፡ ‹‹አንተ ግን ደህና ነህ?››ቸ ስትል ጠየቀችው፡፡

‹‹አዎ ይመስለኛል››
‹‹በጣም ጎበዝ ነህ››
‹‹አንቺም እንዲሁ››
‹አዎ እኔ ጎበዝ ነኝ አለች ለራሷ፡
ፀጥ ብሎ የቆየው ተሳፋሪ ሁሉ በአንድ ጊዜ ተንጫጫ፡፡ በዚህ ጊዜ
ካፒቴኑ ‹‹ፀጥታ እባካችሁ ዝም በሉ›› አለ፡፡
ማርጋሬት ዙሪያውን ቃኘች፡፡
ሉተር ኤዲ እና ሄሪ ላዩ ላይ ወጥተውበት ከመሬቱ ላይ እንደተደፋ ነው፡፡ አይሮፕላኑ ውስጥ ያንዣበበው አደጋ ተወግዷል፡ ሃርትማንና
ሉተርን ሊወስድ የመጣው ጠላቂ መርከብ ተንሳፎ ይታያል፡

ካፒቴኑም የባህር ኃይል መርከብ በቅርብ ርቀት ይታያል፡ ‹‹ጠላቂ
መርከብ እዚህ እንዳለ የሬዲዮ መልእክት እናስተላልፋለን፡፡››
‹‹ቤን›› ሲል ተጣራ፡
‹‹አቤት ጌታዬ›› አለ የሬዲዮ ኦፕሬተሩ ‹‹የጠላቂው መርከብ አዛዥ
ሬዲዮ መልእክት ማስተላለፋችንን ካወቀ ወደ እኛ ሊተኩስ እንደሚችል
ተገንዝበኸዋል?›› አለ ቤን፡፡

‹‹ደህና ይቅር›› አለ ካፒቴኑ ‹‹ተሳፋሪዎቻችን እስካሁን የደረሰባቸው መከራ
ይበቃል፡››
ጠላቂው መርከብ መግቢያው እንደተዘጋ ነው አዛዡ  አንድ ነገር
ይሆናል ብሎ እየጠበቀ ነው፡፡

‹‹ቤከር አንድ ያልተያዘ ወሮበላ  ይቀረናል፡ እዚህ እንዲመጣ እፈልጋለሁ፡፡ የጀልባዋ ነጂ፡ ኤዲ ሂድና ቪንቺኒ እንደሚፈልገው ንገረው አለው
👍192🔥2🥰2🤔1
#ተአምራተ_ኬድሮን


#ክፍል_ሃምሳ_አንድ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///

መኝታ ቤቷ ገብታ ልብሷን ከቀያየረች በኋላ የጀመሩትን አይነት መጠጥ  አምጥታ ለሁለቱም ቀዳችና ወደጫወታቸውን እዲመለሱ ተመቻቸች..

‹‹እሺ አሁን ካቆምክበት ጀምርልኝ››

‹‹ምን….? ››አለት ሁሉን ነገር የረሳው ይመስላል

‹‹ታሪክህን እየነገርከኝ ነበር››

‹‹እ..አዎ…ግን የት ላይ  ነበር ያቆምኩት….?››

‹‹ስለፍቅረኛህ ጀምረህልኝ ነበር..በህይወት የምትኖርበት ምክንያት እሷን አንድ ቀን አገኛት ይሆናል በሚል ጉጉት ምክንያት እንደሆነ ነግረኸኝ ነበር ያቆምከው››

‹‹አዎ….አይገርምሽም …

እስከጥቂት ቀናት ድረስ እኮ ምንም አይነት ተስፋ አልነበረኝም…››
‹‹ቆይ ጠይቀሀት እንቢ ብላህ ነው….?››

‹‹አረ መጠየቅ…ትቀልጂያለሽ እንዴ ….?ቀና ብዬ እንኳን ሰላምታ ልሰጣት ድፍረቱ የለኝም.››

‹‹ግን እኮ እንደዛ አይነት ሰው አትመስልም..በጣም ደፋር ግልጽ እና በራስ መተማመን ያለህ ሰው ነህ››አለችው ከልቧ..

‹‹እኔም እንደዛ ነኝ ብዬ አምናለሁ..ፍቅር የሚባለው ነገር ግን ዋና ባህሪው ያልሆንሺውን ሆነሽ እንድትገኚ ማድረግ ይመስለኛል…እጅግ ክፉ የነበርሽው ሰው በፍቅር ውስጥ ስትሆኚ ስጋዬን ግፈፉት እስከማለት ድርስ የሚደርስ ደግነት ያጓናጽፍሻል….ደንዳናና ኮስታራ የነበርሽው፤አልቃሽና ተርበትባች ሆነሽ ቁጭ….ፍቅር እንደዛ  አይነት በሽታ ነው፡፡››

‹‹ቢሆንም ….ይህን ያህል ካፈቀርካት የሆነ ነገር ማድረግ ነበረብህ ..ለመሆኑ የት ነው የምትኖረው….?››

‹‹የሚገርመው እሱ ነው..በእሷ ቤት እና በእኔ ቤት መካከል ያለሁ እርቀት ግማሽ ኪሎ ሜትር አይሆንም…. ሁለታችንም ሳሪስ  በአንድ ሰፍር ተወልደን እዛው አንድ ሰፈር ያደግን ነን…ቤተሰቦቻን የአንድ እድር አባል ሆነው፤አንድ የጽዋ ማህበር መስርተው ዕድሜያቸውን በጉርብትና  የኖሩ ናቸው….አንድ ቄስ ትምህር ቤትፊደል መቁጠር ጀምረን   .አብረን ኤለመንተር የገባን የእድሜ እኩዬች ነን››

‹‹ይገርማል!!››

‹‹እውነትሽን ነው በጣም ይገርማል…. ከ1ኛ ክፍል አንስቶ እስከ አስረኛ ክፍል አብረን ነበር  የተማርነው…በተለይ ዘጠነኛ ክፍል አንድ ወንበር ላይ ነበር የምንቀመጠው…ግን በወቅቱ እኔ  ግማሽ ልቤ ነበር ክፍል ውስጥ የሚገኘው… እሷ ደግሞ አካሏም ነፍሶም ትምርቱ ላይ የተጣበቀ ነበር፡፡ግን የሚያመሳስለን አንድ ነገር ቢኖር  ሁለታችንም ተአምር ካልተፈጠረ በስተቀር ከትምህርት ቤት አንቀርም ነበር..››

‹‹ለምን ….?››አለችው ገለጻው ገርሞት

‹‹እሷ ለትምህርት ባላት ፍቅር የተነሳ እኔ   ደግሞ ለእሷ ካለኝ ፍቅር  የተነሳ….››

አሳቃት….ብርጭቆውን አንስቶ ከተጎነጨለት በኃላ ቀጠለ

‹‹እሷ እንደማንኛውም የክፍል ጓደኛ ግን ደግሞ ከዛም ትንሽ ከፍ ባለ የሰፈር ልጅነት እና አብሮ አደግነት ነው የምትቀርበኝ…እኔ ደግሞ በዚህ አለም ላይ ሁለት ሴቶች ብቻ ናቸው ያሉኝ.. እናቴ እና እሷ ብቻ..በቃ..ያኔ  አብሬት በምማርበት  በዛ ጊዜ ብቻ አልነበረም እንደዛ የሚሰማኝ.. አገር ለቅቄ  በስደትም እያለው እንደዛ ነበር  እምነቴ…የሆነች ሴት በሆነ ነገሮቾ ትንሽም እንኳን ከእሷ ጋር ካልተመሳሰለችልኝ..የሆነ የእሷን ነገር እንዳስታውስ  ካላደረገችኝ አንድ ደቂቃም ላወራት ወይም አጠገቧ ልቀመጥ አይቻለኝም….ከአስር አመት መለያየት በኃላ ከ10 ዓመት ናፍቆት በኃላ እሷን እና እናቴን አንዴ አይቼ ለመሞት ወስኜ  ወደሀገሩ ስመጣ…እሷን በተመለከተ ጭራሽ ተስፋ የሚያስቋርጥ ነገር ነው ያጋጠመኝ…፡፡አፍላ ልጃገረድ ገና አጎጠጎጤ ሆና ጥያት የሄድኳት  ልጅ አድጋና ፈክታ ሙሉ ሴት ሆና ጠበቀችኝ…፡፡የ10ኛ ክፍል ተማሪ ሆና የተለየኋት  ልጅ ዶክተር ተብላ ትልቅ ሆስፒታል ውስጥ ትልቅ  ባለሞያ ሆና አገኘኋት..እና የሩቅ ህልሜ የነበረችው ልጅ ጭራሽ መቼም የማትፈታ ቅዠቴ እንደሆነች አሰብኩ…ሳያት በሩቅ መሸሽ ጀመርኩ፡፡ድንገት መንገድ ላይ ስንገጣጠም እንኳን   ቅንድቤን ከፍ ዝቅ በማድረግ አንገቴን አቀርቅሬ  ሰላምታ  ለመስጠት ከመሞከር ውጭ እሷ እንኳን ለሰላምታዬ አፀፋውን መመለሷ እና አለመመለሷን  እርግጠኛ ሆኜ አላውቅም፡፡ይህቺ ልጅ የእኔ ልጅነቴ ነች….የሩቅ እሩቅ ትዝታዬ …ብዙ ብዙ ለሊቶች በህልሜ ያየኋት… ብዙ ብዙ ታሪክ ያጫወተችኝ….ብዙ ብዙ ነገር ያወጋኋት…ያወጋችኝ..፡፡እንደዛ ብቻ ሳይሆን ደጋግሜ ያገባኋት…ብዙ ብዙ ልጆች የወለደችልኝ…ብዙ የሳምኳት፤ ብዙ የሳመችኝ…ብዙ ያፈቀርኳት፤ብዙ የወደደቺኝ…ግን ሁሉም በህልሜ የሆነ ነበር …››

‹‹ምን አይነት ፍቅር ነው..ስል አሰብኩ ደግሞ ከዚህች ልጅ ጋር የሚያመሳስለኝ አንድ ነገር ይኖር  ይሁን .. ….?አዎ መኖርማ አለበት ….እደዛ ቢሆን ነው ይሄን ሁሉ ሰዓት አብሮኝ ያሳለፈው…እቤቴ ድረስ ተከትሎኝ በለሊት የመጣው…አዎ እንደዛ ቢሆን ነው ሚስጥሩን ዘክዝኮ የሚነግረኝ…››ስትል የራሷን ግምት ወሰደች…ግምቷ እውነት ሆኖ  እስከአልጋ መዋደቅና መዋሰብ ድረስ ያደርሷቸው እንደሆነ አሁንም በውስጧ እያሳላሳላች ነው ፡
ቀጠለ እሱ…‹‹እና ይገርምሻል ከሶስት ቀን በፊት  ያልጠበቅኩት አጋጣሚ ተከሰተ…››

‹‹ምን ተከሰተ….?››

‹‹ወደሀገሬ ከተመለስኩ ከሁለት ዓመት ተኩል በኃላ   ትናንት….ድብር እና ጭፍግግ ብሎኝ ሰፈር ላዳዬ  አቁሜ እኔም ላዳዬ  ውስጥ ወንበሬን ወደኃላ ለጥጬ መፅሀፍ በማንበብ በተመስጦ ላይ እያለሁ...በሀይለኛው የላዳው የኃላዋ በራፍ ሲንኳኳ የሆነ  የእብድ ድርጊት መስሎኝ  በርግጌ ተነሳሁና  አንገቴን በመስኮት አስግጌ  ወደ ኃላው ተመለከተኩ…

‹‹እንዴ ሰላም…!!!!!››

‹‹ክፈትልኝ››

‹‹እሺ ››ተረብትብቼ ከፈትኩላት..ተስፈንጥራ ገባች…የሆነ ሰው ከኃላ እያባረራት ይመስላል..ፀጉሯ ሁሉ ጭብርር ብሏል…የአይኖቾ ደም መልበስ ምን አልባት ለቀናት ስታለቅስ እንደቆየች ምስክር ናቸው…..አለባበሶም እንደነገሩ እና ያልታሰበበት ነው….››የአመታት ህልሜ የሆነች ልጅ በእንዲህ አይነት ያልታሰበበት አጋጣሚ ላዳዬ ውስጥ ትገባለች ብዬ እንኳን ማሰብ አልሜ እንኳን አላውቅም…..

‹‹ንዳው ››አለችኝ
ህልም ውስጥ ያለሁ ነበር የመሰለኝ ፡፡ ትዛዞን ተቀብዬ  …ሞተሬን አንቀሳቀስኩ እና  ነደሁት

‹‹-የትኛው ፖሊስ ጣቢያ እንሂድ….?››ጠየቅኳት

‹‹የምን ፖሊስ ጣቢያ….?›› አለችን ግራ በመጋባት

-‹‹አይ እንዲሁ ነገር ስራሽን ስገመግመው  የሆንሽው ነገር ያለ ስለመሰለኝ ነው..››

‹‹ሆኜያለሁ...አዎ የሆነ ነገር ሆኜያለሁ… መች አልሆንኩም አልኩህ …ግን ወደ  ፖሊስ ጣቢያ መሄድ ምን ይፈይድልኛል..….?››አለቺኝ.‹‹ይቅርታ እሺ የት ልወስድሽ..….?››አልኳት
በመለማመጥ..እወነቴን ነው በዛች ላዳ ጆሀንስበርግ  አድርሰኝ ብትለኝ እንኳን እድሜ ልክ ይውሰድብኝ እንጂ እንቢ አልላትም…በምን አቅሜ…በእሷ መታዘዝ እኮ ለእኔ እድል ነው…የአለምን ህዝብ አጥፋልኝ ብትለኝ እንኳን ባልችልም  ከመሞከር ወደኃላ አልልም፡፡ 
‹‹እኔ እንጃ የሆነ ሰው እንደእኔ ሲሆን የት ነው የሚሄደው..….?ወይም የት ነው መሄድ ያለበት..››በቀላሉ ልመልሰው የማልችለውን ውስብስብና  ግራአጋቢ ጥያቄ ጠየቀችኝ ‹‹እኔ እንጃ ምን አልባት ቤተክሪስትያን ልውሰድሽ….?››ይሻል የመሰለኝን አማራጭ አቀረብኩላት ፡
👍858😁2👏1
#ትንግርት


#ክፍል_ሃምሳ_አንድ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


የዶ/ርን ስልክ እንደዘጋ ርብቃ ጋር ነው የደወለው<<መቼስ እሁድ ስለሆነ ቤት ትኖሪያለሽ ብዬ ነው?››

‹‹አዎ ቤት ነኝ ..እየመጣህ ነው እንዴ?››

‹‹አዎ ፈልጌሽ ነበር?››

<<ና አለውልህ››አለችው፡፡ ስልኩን ዘጋውና ታክሲ ውስጥ ገባ፡፡

ሲደርስ ቆንጆ ቁርስ ሰርታ ጠበቀችው፤ በጣም የገረመው ያገኛት በህልሙ የመጣችበት ጊዜ የለበሰችውን ቀሚስ ለብሳ ነበር ፡፡

ከቁርስ በኃላ

‹‹አረፍ እንበል እንዴ? >> አለችው በአገጯ ወደ መኝታ ቤቷ እየጠቆመችው….፡፡

‹‹አይ እስቲ መጀመሪያ እዚሁ ሳሎን ሆነን እንነጋገር።

<<እንነጋገር?>>

‹‹አዎ ምነው?››

‹‹እኔ እንጃ እኔና አንተ እንነጋገር ብለን ተነጋግረን አናውቅም ብዬ ነዋ ..እኔ እንነጋገር ሲሉኝ ይጨንቀኛል...፡፡ የሆነ ችግር..የሆነ የተበላሸ ነገር ያለ መስሎ ነው የሚሰማኝ…ይገርምሀል እናትና አባቴ ሁል ጊዜ እንነጋገር እንዳሉና በጠረጴዛ ዙሪያ እንደተቀመጡ ነው... ግን አንድም ቀን በመግባባት አጠናቀውት አያውቁም...እና ቃሉ ያስጠላኛል፡፡››

‹‹እና ካልፈለግሽ ልተወው?››

‹‹አይደለም ..ዝም ብለህ በፊት እንደምታደርገው ቀለል አድርገህ በጨዋታ መልክ አውራኝ ነው ያልኩህ››

‹‹እሺ›› አለ ፈገግ ብሎ‹‹…ባለፈው አንድ ጨዋታ በስልክ ጀምሬልሽ ነበር….ስለ እኔ እና ስለ ፅዮን››

‹‹አስታወስኩት….፡፡››

‹‹እንድንጋባ ትፈልጋለች፡፡››

‹‹በጣም አፍቅራሀለች ማለት ነው ?አደራ ግን እዳትጎዳት... አንተ በጣም ምርጥ ጓደኛ መሆን እንደምትችል እኔ ምስክር ነኝ ..ለእሷ ደግሞ ምርጥ ባል ለመሆን ሞክር፡፡››

‹‹እሞክራለሁ….ከዛ በፊት ግን አንቺ ብታገቢኝ ምን አለበት ብዬ ልጠይቅሽ ነበር የመጣሁት››

<<እኔ....? ጋብቻ>>

‹‹አዎ ጋብቻ...ካፈቀርሺኝ ማለቴ ነው?››

‹‹ስለማፈቅርህማ ነው የማላገባህ..አየህ ታዲ እኔ ስላንተ ምንም አይነት ቆሻሻ ትዝታ እንዲኖረኝ አልፈልግም..7 አመት ሙሉ ህይወቴን በፍቅር አጣፍጠህልኛል...አንተን በማግኘቴ በጣም እጅግ በጣም እድለኛ ሰው ነኝ... ወደ ጋብቻ ¶ይዤህ ገብቼ የሆነ ነገር ታስቀይመኝና ይሄንን ስለአንተ ስገነባ የኖርኩትን የፍቅር ሀውልቴን ታፈርስብኛለህ ብዬ እሰጋለሁ.. ስለዚህ ይቅርብኝ፡፡››

‹‹በቃ የመጨረሻ ውሳኔሽ ይሄ ነው?››

‹‹አዎ ከዚህ በፊት አንተን ለማግባት ሁለት ሶስት ጊዜ አስቤ ነበር፤ቀድሜ ሁሉ ልጅ ልወልድልህ ፈልጌም ነበር፤ከዛ እንድታገባኝ ማለት ነው››

<<ሎጅ?>>

‹‹አዎ ልጅ ልወልድልህ ....ከዛ ላገባህ፡፡››

‹‹እና ሀሳብሽን ለምን ቀየርሽ?››

‹‹ተረጋግቼ ሳስበው የጅል ሴት ዘዴ ሆኖ አገኘሁት..አይህ ወንድ ልጅ እንዲያገባህ የተሳሳትክ መስለህ ማርገዝ ትክክለኛ ዘዴ አይደለም ፡፡ምን አልባት አፍሮ፣ይሉኝታ ይዞት፣አዘኔታ አንጀቱን አላውሶት..ወይም ለልጁ ካለው ፍቅር አንፃር በሁኔታዎች አስገዳጅነት ወደ ጋብቻ ተስማምቶ ሊገባ ይችል ይሆናል..ነገር ግን ቆየት ብሎ ጋብቻው ችግር ላይ መውደቁ አይቀርም፤አይደለም በሆነ ሰበብ አስገዳጅነት ይቅርና በፍፁማዊ ፍቀር እና በሙሉ ፍላጐት የገቡበት ጋብቻ እንኳን አስተማማኝ አይደለም፡፡››

«እና?»

‹‹እናማ ሀሳቤን ሰረዝኩ፡፡››

‹‹ለእኔ ልጅ የመውለዱን?››

‹‹....ኧረ አንተን ማግባቱንም ጭምር፡፡››

‹‹አሁን ግን እኮ ልጅ አርግዘሽልኛል፡፡››

‹‹የምን ልጅ?››

‹‹ልጅ ነዋ... እርጉዝ ነሽ፡፡››

‹‹አንተ እኮ ምላስህ ጥቁር ነው..በእናትህ አታሟርትብኝ፡፡››

‹‹ማሟረት አይደለም.. የእውነቴን ነው…፡፡አሁን የለበስሽውን ቀሚስ ለብሰሽ በህልሜ መጥተሸ ነበር..ለዚህ ነው በጥዋት ወደአንቺ የመጣሁት፡፡››

‹‹ይሄንን ቀሚስ አታውቀውም እኮ ከሶስት ቀን በፊት ነው የገዛሁት..በዚህ ሶስት ቀናት ውስጥ ደግሞ ካንተ ጋር አልተገናኘሁም፡፡››

‹‹እኔም የገረመኝ እሱ ነው..ጥምዝ የወርቅ ሀብል በፍቅር አጠለቅሺልኝ.. ስሜቴ እንደሚተረጉምልኝ ከሆነ ልጅ ሳታረግዢልኝ አልቀረሺም፡፡ >>

‹‹እንዴ ሀብል አጠለቅኩልህ ማለት እሺ እንዳልከው ልጅ ይሁን ..ከፅዬን እንደሆነስ ..? የግድ እኔ ስላጠለቅኩልህ ከእኔ ነው ማለት ይቻላል?››

‹‹አይ ከፅዮን ጋር መዋሀድ እንደማንችል አይቼያለሁ..በዛ ላይ ሀብሉ ሁለት ተመሳሳይ አንድ ላይ የተጠቀለለ ነበር ...አንዱን እራስሽ አንገት ላይ ስታጠልቂ አንዱን እኔ አንገት ላይ ነው ያደረግሽው፡፡››

‹‹ጥሩ ህልም ነው ፤ግን አንድ የዘነጋሀው ነገር ቢኖር እኔ በየሶስት ወሩ ሳላሰልስ የወሊድ መከላከያ መርፌ እንየተወጋው መሆኔን ነው፡፡››

‹‹አውቃለሁ.... ያ ማለት ግን ላለማርገዝሽ መቶ ፐርሰንት ማስተማመኛ ነው ማለት አይደለም..እዚህ ሰፈር በቅርብ ክሊኒክ አለ?››

‹‹አዎ ምነው ጠየቅከኝ?››

‹‹ተነሽ ሄደን ቼክ እናድርግ?››

‹‹ምኑን?››

‹‹ማርገዝ አለማርገዝሽን >>

‹‹የምርህን ነው እንዴ?›› አለችው በፍራቻም በመጠራጠርም ጭምር.. ምክንያቱም ከዚህ በፊት ታዲዬስ ተመሳሳይ ከህልም የመነጩ ትንቢቶችን ነግሯት እሱ እንዳለው ተግባራዊ ሲሆኑ ደጋግማ ታዝባለች፡፡

‹‹ተነሽ እንጂ፡፡››ትንሽ ካቅማማች በኃላ ተስማምታ ተነሳች.... ተያይዘው ወጡ፡፡

ከአንድ ሰአት በኃላ..ወደቤት ተመልሰው ፊት ለፊት ተፋጠው ተቀምጠዋል፡፡

‹‹..ጭራሽ የሶስት ወር እርጉዝ?››በንዴት ተንጨረጨረች፡፡

‹‹ርብቃ አይዞኝ ተረጋጊ እንጂ፡፡››

‹‹እንዴት ልረጋጋ..?እኔ ገና ለገና ስራና ገንዘብ ስላለኝ ብቻ አባት የሌለው ልጅ መውለድ አልፈልገውም፡፡>>

‹‹ምን ማለት ነው? አባቱ እኮ አለሁ... እኔ ነኝ::››

‹‹አንተማ የሌላ ሰው ባል ልትሆን ነው››

‹‹እርሺው ..እኔ እንኳን ልጅ ኖሮኝ ቀድሞውንም ያንቺን ፍላጐት ላክብር ብዬ ነው እንጂ የማፈቅረው ማግባትም የምፈልገው አንቺን ብቻ ነው››...አፍጥጣ በአድናቆት አየችውና‹‹ፅዮንስ?››ስትል ጠየቀችው፡፡

‹‹አስረዳታለዋ››

‹‹ምን ብለህ …?ሞራሏ እኮ ሊነካ ይችላል?››

‹‹ጋብቻ የሰው ሞራል ለመገንባት ወይም ለይሉኝታ ሲባል የሚገባበት አይደለም፡፡››

‹‹ቢሆንም እኔ እንጃ ምን ማለት እንዳለብኝ እንኳን ማወቅ አልቻልኩም››

‹‹አባት የመሆን ብቃቴ ተጠራጥረሽ ነው አይደል፡፡››

አይ እሱን እንኮን ፍፁም ልጠራጠር አልችልም..ያንተን አባት የመሆን ብቃት ከተጠራጠርኩማ እኔ የአለም ትልቋ ደደብ ነኝ ማለት ነው..አንተ እኮ የአለም ምርጥ አባትነት ብትወዳደር እንደምታሸንፍ አውቃው››

‹‹እና ምንድነው ችግሩ››

ችግሩማ ምንም እንኳን በአባትነትህ ቅንጣት ጥርጣሬ ባይኖረኝም በባልነትህ ግን እኔ እንጃ..አንተ የትዳር ሰው ይወጣሀል ብዬ ማሰብ ይከብደኛል፡፡

ይቀጥላል

ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።

#Share #like and #subscribe my #YouTube 

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍7516😱3🔥2🥰2👎1