#ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
አቤል ካምፓሱን በለቀቀ ማግሥት ሳምሶንም ጓዙን ይዞ ስለ ወጣ እስክንድር ፊቱን ወደ ዩኒቨርስቲው ማዞር አስጠልቶት ሦስት ቀን ያህል መኖሪያ ቤቱ ነበር የሰነበተው ። እዚያም ሆኖ የአቤልን ጉዳይ ለማስፈጸም ወዲያ ወዲህ
ማለቱ አልቀረም ። ብርቅነሽን አነጋግሮአት አቤል ያካፈላትን ምስጢር ለቢልልኝ እንድትነግራቸው አድርጓል ። መጀመሪያ ብርቅነሽ ፍርድ ቤት የመቅረብ ያህል ቆጥራው እምቢ ብላ አስቸግራው ነበር ። በብዙ ውትወታና ማሳመን ነው ወደ ቢልልኝ የወሰዳት ። ከእሷም ሌላ አቤል ቀድሞ በርቀት ካስተዋወቀው ሰዎች መሐል ለሥነ ልቡናው ምርምር ጥቂት
ይረዳሉ ብሎ የገመታቸውን ከቢልልኝ ጋር በመመካከር አነጋግሮአቸዋል ። እሱም እንደ ዮናታን በጓደኛው በአቤል ጉዳይ ውስጥ እጁን ማስገባቱና አንዳንድ ጠቃሚ ውጤቶች ማስገኘቱ አስደስቶት የበለጠ እንዲገፋበት እያደረገው
ነበር ።
በአራተኛው ቀን ወደ ካምፓስ ሲገባ ሁለት ሴቶች በጥብቅ ሲፈልጉት እንደ ሰነበቱ ድብርት ነገረው ። ቶሎ ሐሳቡ ውስጥ የመጣችበት ማርታ ነበረች ።
” ምን ዐይነት ሴቶች ? ” አለው ፡ ለማወቅ ቸኩሎ።
“ አንዷ ወፍራም ቀይ ፡ አንዷ መጠነኛ ወይም ሁለቱም አጭሮች ” ካለው በኋላ ፥ የነገሩትን ስም አስታውሶ ።ድብርት“ ቤተልሔምና ትዕግሥት የሚባሉ” አለው
“ አሃ ! ” አለ እስክንድር ። የተፈለገበት ምክንያት ምን እንደሆነ ለመገመት ጊዜ አልወሰደበትም ። ነገር ግን በጣም የጓጓው ስለ አቤል የሚቀርብለት ጥያቄ ከትዕግሥት ከራሷ አፍ ይወጣ እንደሆን ለመስማት ነበር ።
ሁለቱም በምሳ ሰዓት ወደ መመገቢያው አዳራሽ ሊገቡ ሲሉ አገኛቸው ።
በእግር በፈረስ ስትፈለግ የት ነው እንዲህ የጠፋኸው ? ” አለችው ቤተልሔም ።
በመኪና ብትፈልጉ ፡ ታገኙኝ ነበር ! ” ሁለቱም ሴቶች በቀልዱ ሣቁ ።
“ ማርታኮ ፡ ሔደች ! ” አለችው ቤተልሔም ሣቋን ገታ አድርጋ
“ የት?” አላት የደመ ነፍሱን ።
“ ወድቃ ፡ ትላንት ሻንጣዋን ይዛ ግቢውን ለቀቀች ። ”
"እና? እና እኔ ታዲያ እኔ ምኗ መሰልኳት የማርታን መርዶ የጨዋታ መክፈቻ የምታደርግልኝ ”አለ እስክንድር በልቡ ።
“ በራሷ ጥፋት ነው ” አለች ቤተልሔም ፡ ከእስክንድር መልስ ስታጣ ።
“ እንዴት ? ”
"ጸባይ የላትም ። ጸባይ ቢኖራት ኖሮ ህእ ! ” አለችው ፥ እንደ ሕፃን ልጅ ለምቦጭዋን ጥላ ።
“ ጸባይ ወይስ ጭንቅላት ?” እለ እስክንድር በሐሳቡ ።ምን ለማለት እንደ ፈለገች ገብቶታል ። ወዲያው ትዝ ያለው
ማርታ ለማን አጥላልታ ያወራችለት ነገር ነበር ።
“ ያንተስ ጓደኞች ?” አለችው ትዕግሥት በድንገት ።ስለ አቤል ለማወቅ ካላት ጉጉት የተነሣ፥ ሌላውን ጨዋታ
ለስማት ትዕግሥት አጥታ ነበር ።
“ ሳምሶን ወድቆ ተባረረ” አላትና አቋረጠ
ቤተልሔም የሳምሶንን ስም ሲጠራ እሱ ራሱ አጠገቧ የቆመ ያህል ሽምቅቅ አለች ከፍርሀቷ ብዛት ተደብቃው ከርማ ግቢውን ለቅቆ መሔዱን ካረጋገጠች በኋላ ነበር
ከመኝታ ክፍሏ መውጣት የጀመረችው ።
እስክንድር የሳምሶንን መባረር ብቻ ተናግሮ ስለ አቤል ምንም ነገር ሳያነሣ ያቋረጠው ሆነ ብሎ ነበር ። ትዕግሥት
ደፍራ ትጠይቀው እንደሆን ሊፈትናት ፈልጎ ነበር ትዕግሥት ዐይን ዐይኑን አየችው የምትፈልገውን እንዲነግራት በዐይኗ ለመነችው ። ነገር ግን ከእስክንድር አፍ ጠብ ያለ ነገር ኣልነበረም ።
“አቤልስ ? ” አለችው ደፍራ ። ድምጿ ግን ድክምክም ብሎ ነበር።
እስክንድር ደስ አለው ። ትዕግሥት ለመጀመሪያ ጊዜ የአቤልን ስም በጓደኛው ፊት መጥራቷ በእርግጥም ትልቅ ለውጥ ነበር ። ደስታዊው ስላስደነገጠው ቶሎ መልስ አልሰጣትም ። እሱም ድምፅ እንደ እሷው እንዳይደካክም መጠ ንቀቅ ነበረበት ።
“ አበል እንኳ አልወደቀም ። ግን እሱም ካምፓሱን ለቅቆ ወጥቶአል ” አላት ።
እስክንድር ይህን ሲናገር ከትዕግሥት ፊት ላይ የጠበቀውን ለውጥ አልተመለከተም አቤል ግቢውን መልቀቁ ያስደነግጣታል ብሎ ነበር ። ነገር ግን ትዕግሥትም ሆነች
ቤተልሔም ለነዚህ ዜና እንግዳ አልነበሩም ። አቤል በዮናታን መኪና ሻንጣውን ጭኖ የወጣ ዕለት ነበር ያዩት ተማሪዎች ወሬውን ቀምመው ሲያራቡ ነው የሰነበቱት ። እና አሁን የትዕግሥት ጉጉት የአቤል መውደቅ ትክክለኛ መሆኑን
ማረጋገጥ ብቻ ነበር ።
“ ታዲያ ካልወደቀ ለምን ካምፓሱን ለቅቆ ወጣ ? " አለችወ ትዕግሥት በጥርጣሬ ።
“ በሌላ ምክንያት ነው ”አላትና እስክንድር ለአመላለስ ተቸግሮ ፡ “ ሰፊ ነው ነገሩ ፣ በቁም ጨዋታ የሚያልቅ አይደለም ” አለ።
አላመነችውም ፊቷ ላይ ጥርጣሬ አነበበ የተከፋው ገጽታዋ አቤል ወድቋል ብላ እንደ ደመደመች ይናገራል ።ይህ እስክንድርን ብዙ አላስጨነቀውም ጊዜውን ጠብቆ ሁሉን ነገር እንድታውቀው ይደረጋል ። ዋናው ነገር በሩ መከፈቱ ነውጅ የአቤልን ስም እንስታ በግልጽ መጫወት ጀምራለች።
"ግን ምን ይሆን ' ወይስ ማን ይህን ያደፋፈራት ?? ሲል አሰበ ።
ከደስታው የተነሣ ምሳውን በሚበላበት ጊዜ ጉዳይ እንዳለበት ሰው እየተጣደፈ ቶሎ ቶሎ ነበር የጎረሰው ምግቡን ቶሎ ጨርሶ ያንን ሰው የበዛበት አዳራሽ ለቅቆ ወጥቶ ብቻውን ከሐሳቡ ጋር እየተሣሣቀ ለመፈንደቅ ካልሆነ በስተቀር ፡ ሌላ የሚሔድበት ቦታ አልነበረውም ።
መኝታ ክፍሉ ገብቶ እንደ ወትሮው አጭር የቀን እንቅልፍ ለመተኛት ቢሞክርም አልሆነለትም ከውጭ ይዞት የገባው ደስታ ጠፍቶ ትካዜ ተጫጫነው ። ከክፍሉ ውስጥ አቤልንና ሳምሶንን ማጣቱ ቅር ቅር አሰኘው ወና ቤት ውስጥ የገባ ይመስል ሰውነቱን ቀፈፈው ። ለሚቀጥሉት አራት ወራት በዚህ ክፍል ውስጥ የሚያሳልፈው ሕይወት
በጣም ብቸኛ ሆኖ ታየው ። በእርግጥ አጠንቡ ድብርት አለ ግን ድምፁ ከማይሰማ ሰው ጋር እንዴት ይኖራል ?
ሳምሶን "ጉልቤው" መኝታ ክፍሉን ምን ያህል ያደምቀው እንደ ነበር የገባው አሁን ነው » እየፈሳም ሆነ እየዘለለ ወይም ድብርትን እያበሽቀ ክፍሉን ሕይወት ይሰጠው ነበር ። መቼም መለያየት ክፉ ነው» ፤ እንደዚያ የሚያበሽቀው ድብርት እንኳ ሳምሶን ሲባረር ተገላገልኩ አላለም
ከልቡ ነበር ያዘነላት እስክንድር እንደ ተጋደመ ስለ ሳምሶን ሲያስብ የተለያዩበት ቀን ትዝ አለው ። በሰላም አልነበረም የተለያዩት ።
ሳምሶን ሰው ሳያየው ተደብቆ ካምፓሱን ለመልቀቅ ከለሊቱ አስራ አንድ ሰዓት አካባቢ ዕቃውን ሲያሰነዳዳ እስክንድር ድንገት ከእንቅልፉ ባነነ ። ሆኖም አዝማሚያው ስለገባው እስከ መጨረሻው ልመልከት ብሎ ፊቱን ከአንሶላው ውስጥ ሳያወጣ ጭጭ ብሎ ያዳምጥ ጀመር። ሻንጣውን አዘገጃጅቶ ጨርሶ ሲወጣ በሩጋ ሲደርስ ከአንሶላው ውስጥ አሾልቆ ተመለከተውና ፡ “ ሳምሶን ! ” ብሎ በኃይለ ቃል ጠራው።
"ምነው ? ! ”አለ ሳምሶን ዘወር ብሎ ከቁጣ ባልተናነሰ ድምፅ ስለተነቃበት ተናዶ ነበር።
"ምን ሆነሃል ? ”
"መሄዴ ነው"
“ ታዲያ እንዲህ ነው እንዴ የሚኬደው ? ምነው ሳምሶን ? የተወሰነ ጊዜም ቢሆን በጓደኝነት አሳልፈናል ። ቻው ብለኸን በሰላም ሸኝተንህ ፥ ብንለያይ ምናለበት ? መውደቅ በአንተ አልተጀመረ ! ” አለው እስክንድር ፥ ሆድ ብሶት ።
“ ሸኝ አልፈልግም ! ያው ሰፈር እንገናኛለን” ! ብሉ ጥሎት ሔደ ።
ሰው ለምን ድክመቱን ለመሸፈን ሲል እውሬ ይሆናል?” አለ እስክንድር በልቡ ። በሳምሶን አልበሸቀበትም " እንዲያውም ፡ “ በዚህ በንዴቱ ሰዓት ምግብ ቢቀርብለት
እንደ ቀድሞው ይበላ ይሆን ? ” ብሎ አስቦ ሣቅ አለ ። “ ጥርሳሞች ! ” ሲል በሐሳቡ ታየው ።ሰው
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
አቤል ካምፓሱን በለቀቀ ማግሥት ሳምሶንም ጓዙን ይዞ ስለ ወጣ እስክንድር ፊቱን ወደ ዩኒቨርስቲው ማዞር አስጠልቶት ሦስት ቀን ያህል መኖሪያ ቤቱ ነበር የሰነበተው ። እዚያም ሆኖ የአቤልን ጉዳይ ለማስፈጸም ወዲያ ወዲህ
ማለቱ አልቀረም ። ብርቅነሽን አነጋግሮአት አቤል ያካፈላትን ምስጢር ለቢልልኝ እንድትነግራቸው አድርጓል ። መጀመሪያ ብርቅነሽ ፍርድ ቤት የመቅረብ ያህል ቆጥራው እምቢ ብላ አስቸግራው ነበር ። በብዙ ውትወታና ማሳመን ነው ወደ ቢልልኝ የወሰዳት ። ከእሷም ሌላ አቤል ቀድሞ በርቀት ካስተዋወቀው ሰዎች መሐል ለሥነ ልቡናው ምርምር ጥቂት
ይረዳሉ ብሎ የገመታቸውን ከቢልልኝ ጋር በመመካከር አነጋግሮአቸዋል ። እሱም እንደ ዮናታን በጓደኛው በአቤል ጉዳይ ውስጥ እጁን ማስገባቱና አንዳንድ ጠቃሚ ውጤቶች ማስገኘቱ አስደስቶት የበለጠ እንዲገፋበት እያደረገው
ነበር ።
በአራተኛው ቀን ወደ ካምፓስ ሲገባ ሁለት ሴቶች በጥብቅ ሲፈልጉት እንደ ሰነበቱ ድብርት ነገረው ። ቶሎ ሐሳቡ ውስጥ የመጣችበት ማርታ ነበረች ።
” ምን ዐይነት ሴቶች ? ” አለው ፡ ለማወቅ ቸኩሎ።
“ አንዷ ወፍራም ቀይ ፡ አንዷ መጠነኛ ወይም ሁለቱም አጭሮች ” ካለው በኋላ ፥ የነገሩትን ስም አስታውሶ ።ድብርት“ ቤተልሔምና ትዕግሥት የሚባሉ” አለው
“ አሃ ! ” አለ እስክንድር ። የተፈለገበት ምክንያት ምን እንደሆነ ለመገመት ጊዜ አልወሰደበትም ። ነገር ግን በጣም የጓጓው ስለ አቤል የሚቀርብለት ጥያቄ ከትዕግሥት ከራሷ አፍ ይወጣ እንደሆን ለመስማት ነበር ።
ሁለቱም በምሳ ሰዓት ወደ መመገቢያው አዳራሽ ሊገቡ ሲሉ አገኛቸው ።
በእግር በፈረስ ስትፈለግ የት ነው እንዲህ የጠፋኸው ? ” አለችው ቤተልሔም ።
በመኪና ብትፈልጉ ፡ ታገኙኝ ነበር ! ” ሁለቱም ሴቶች በቀልዱ ሣቁ ።
“ ማርታኮ ፡ ሔደች ! ” አለችው ቤተልሔም ሣቋን ገታ አድርጋ
“ የት?” አላት የደመ ነፍሱን ።
“ ወድቃ ፡ ትላንት ሻንጣዋን ይዛ ግቢውን ለቀቀች ። ”
"እና? እና እኔ ታዲያ እኔ ምኗ መሰልኳት የማርታን መርዶ የጨዋታ መክፈቻ የምታደርግልኝ ”አለ እስክንድር በልቡ ።
“ በራሷ ጥፋት ነው ” አለች ቤተልሔም ፡ ከእስክንድር መልስ ስታጣ ።
“ እንዴት ? ”
"ጸባይ የላትም ። ጸባይ ቢኖራት ኖሮ ህእ ! ” አለችው ፥ እንደ ሕፃን ልጅ ለምቦጭዋን ጥላ ።
“ ጸባይ ወይስ ጭንቅላት ?” እለ እስክንድር በሐሳቡ ።ምን ለማለት እንደ ፈለገች ገብቶታል ። ወዲያው ትዝ ያለው
ማርታ ለማን አጥላልታ ያወራችለት ነገር ነበር ።
“ ያንተስ ጓደኞች ?” አለችው ትዕግሥት በድንገት ።ስለ አቤል ለማወቅ ካላት ጉጉት የተነሣ፥ ሌላውን ጨዋታ
ለስማት ትዕግሥት አጥታ ነበር ።
“ ሳምሶን ወድቆ ተባረረ” አላትና አቋረጠ
ቤተልሔም የሳምሶንን ስም ሲጠራ እሱ ራሱ አጠገቧ የቆመ ያህል ሽምቅቅ አለች ከፍርሀቷ ብዛት ተደብቃው ከርማ ግቢውን ለቅቆ መሔዱን ካረጋገጠች በኋላ ነበር
ከመኝታ ክፍሏ መውጣት የጀመረችው ።
እስክንድር የሳምሶንን መባረር ብቻ ተናግሮ ስለ አቤል ምንም ነገር ሳያነሣ ያቋረጠው ሆነ ብሎ ነበር ። ትዕግሥት
ደፍራ ትጠይቀው እንደሆን ሊፈትናት ፈልጎ ነበር ትዕግሥት ዐይን ዐይኑን አየችው የምትፈልገውን እንዲነግራት በዐይኗ ለመነችው ። ነገር ግን ከእስክንድር አፍ ጠብ ያለ ነገር ኣልነበረም ።
“አቤልስ ? ” አለችው ደፍራ ። ድምጿ ግን ድክምክም ብሎ ነበር።
እስክንድር ደስ አለው ። ትዕግሥት ለመጀመሪያ ጊዜ የአቤልን ስም በጓደኛው ፊት መጥራቷ በእርግጥም ትልቅ ለውጥ ነበር ። ደስታዊው ስላስደነገጠው ቶሎ መልስ አልሰጣትም ። እሱም ድምፅ እንደ እሷው እንዳይደካክም መጠ ንቀቅ ነበረበት ።
“ አበል እንኳ አልወደቀም ። ግን እሱም ካምፓሱን ለቅቆ ወጥቶአል ” አላት ።
እስክንድር ይህን ሲናገር ከትዕግሥት ፊት ላይ የጠበቀውን ለውጥ አልተመለከተም አቤል ግቢውን መልቀቁ ያስደነግጣታል ብሎ ነበር ። ነገር ግን ትዕግሥትም ሆነች
ቤተልሔም ለነዚህ ዜና እንግዳ አልነበሩም ። አቤል በዮናታን መኪና ሻንጣውን ጭኖ የወጣ ዕለት ነበር ያዩት ተማሪዎች ወሬውን ቀምመው ሲያራቡ ነው የሰነበቱት ። እና አሁን የትዕግሥት ጉጉት የአቤል መውደቅ ትክክለኛ መሆኑን
ማረጋገጥ ብቻ ነበር ።
“ ታዲያ ካልወደቀ ለምን ካምፓሱን ለቅቆ ወጣ ? " አለችወ ትዕግሥት በጥርጣሬ ።
“ በሌላ ምክንያት ነው ”አላትና እስክንድር ለአመላለስ ተቸግሮ ፡ “ ሰፊ ነው ነገሩ ፣ በቁም ጨዋታ የሚያልቅ አይደለም ” አለ።
አላመነችውም ፊቷ ላይ ጥርጣሬ አነበበ የተከፋው ገጽታዋ አቤል ወድቋል ብላ እንደ ደመደመች ይናገራል ።ይህ እስክንድርን ብዙ አላስጨነቀውም ጊዜውን ጠብቆ ሁሉን ነገር እንድታውቀው ይደረጋል ። ዋናው ነገር በሩ መከፈቱ ነውጅ የአቤልን ስም እንስታ በግልጽ መጫወት ጀምራለች።
"ግን ምን ይሆን ' ወይስ ማን ይህን ያደፋፈራት ?? ሲል አሰበ ።
ከደስታው የተነሣ ምሳውን በሚበላበት ጊዜ ጉዳይ እንዳለበት ሰው እየተጣደፈ ቶሎ ቶሎ ነበር የጎረሰው ምግቡን ቶሎ ጨርሶ ያንን ሰው የበዛበት አዳራሽ ለቅቆ ወጥቶ ብቻውን ከሐሳቡ ጋር እየተሣሣቀ ለመፈንደቅ ካልሆነ በስተቀር ፡ ሌላ የሚሔድበት ቦታ አልነበረውም ።
መኝታ ክፍሉ ገብቶ እንደ ወትሮው አጭር የቀን እንቅልፍ ለመተኛት ቢሞክርም አልሆነለትም ከውጭ ይዞት የገባው ደስታ ጠፍቶ ትካዜ ተጫጫነው ። ከክፍሉ ውስጥ አቤልንና ሳምሶንን ማጣቱ ቅር ቅር አሰኘው ወና ቤት ውስጥ የገባ ይመስል ሰውነቱን ቀፈፈው ። ለሚቀጥሉት አራት ወራት በዚህ ክፍል ውስጥ የሚያሳልፈው ሕይወት
በጣም ብቸኛ ሆኖ ታየው ። በእርግጥ አጠንቡ ድብርት አለ ግን ድምፁ ከማይሰማ ሰው ጋር እንዴት ይኖራል ?
ሳምሶን "ጉልቤው" መኝታ ክፍሉን ምን ያህል ያደምቀው እንደ ነበር የገባው አሁን ነው » እየፈሳም ሆነ እየዘለለ ወይም ድብርትን እያበሽቀ ክፍሉን ሕይወት ይሰጠው ነበር ። መቼም መለያየት ክፉ ነው» ፤ እንደዚያ የሚያበሽቀው ድብርት እንኳ ሳምሶን ሲባረር ተገላገልኩ አላለም
ከልቡ ነበር ያዘነላት እስክንድር እንደ ተጋደመ ስለ ሳምሶን ሲያስብ የተለያዩበት ቀን ትዝ አለው ። በሰላም አልነበረም የተለያዩት ።
ሳምሶን ሰው ሳያየው ተደብቆ ካምፓሱን ለመልቀቅ ከለሊቱ አስራ አንድ ሰዓት አካባቢ ዕቃውን ሲያሰነዳዳ እስክንድር ድንገት ከእንቅልፉ ባነነ ። ሆኖም አዝማሚያው ስለገባው እስከ መጨረሻው ልመልከት ብሎ ፊቱን ከአንሶላው ውስጥ ሳያወጣ ጭጭ ብሎ ያዳምጥ ጀመር። ሻንጣውን አዘገጃጅቶ ጨርሶ ሲወጣ በሩጋ ሲደርስ ከአንሶላው ውስጥ አሾልቆ ተመለከተውና ፡ “ ሳምሶን ! ” ብሎ በኃይለ ቃል ጠራው።
"ምነው ? ! ”አለ ሳምሶን ዘወር ብሎ ከቁጣ ባልተናነሰ ድምፅ ስለተነቃበት ተናዶ ነበር።
"ምን ሆነሃል ? ”
"መሄዴ ነው"
“ ታዲያ እንዲህ ነው እንዴ የሚኬደው ? ምነው ሳምሶን ? የተወሰነ ጊዜም ቢሆን በጓደኝነት አሳልፈናል ። ቻው ብለኸን በሰላም ሸኝተንህ ፥ ብንለያይ ምናለበት ? መውደቅ በአንተ አልተጀመረ ! ” አለው እስክንድር ፥ ሆድ ብሶት ።
“ ሸኝ አልፈልግም ! ያው ሰፈር እንገናኛለን” ! ብሉ ጥሎት ሔደ ።
ሰው ለምን ድክመቱን ለመሸፈን ሲል እውሬ ይሆናል?” አለ እስክንድር በልቡ ። በሳምሶን አልበሸቀበትም " እንዲያውም ፡ “ በዚህ በንዴቱ ሰዓት ምግብ ቢቀርብለት
እንደ ቀድሞው ይበላ ይሆን ? ” ብሎ አስቦ ሣቅ አለ ። “ ጥርሳሞች ! ” ሲል በሐሳቡ ታየው ።ሰው
👍1
#ቆንጆዎቹ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
....ደውዬ አነጋግራቸዋለሁ። እስካልለቀቋትና በሰላም እስካልተዋት
ድረስ ዕቅዳቸውን እንደማወጣ አስጠነቅቃቸዋለሁ፡፡”
“እንበልና ሊለቋት ባይስማሙስ?”
“አዝረከርከዋለኋ ጉዳዩን! እየተለቀመ ይጎባታል፡፡” ናትናኤል ንዴት ወረረው::
“አየህ... እዚህ ላይ ነው የማንስማማው:: ልንገርህ... ይህን ምስጢር ልታወጣ ብትሞክር ቀድሜ የምቀነጥስህ እኔ ነኝ፡፡” አለ ካልቨርት ሽጉጥ የከተተበትን ኪሱን በቀኝ እጁ መታ መታ እያደረገ፡፡
“ምን ለማለት ነው?” አለ ናትናኤል ዓይኖቹን አጥብቦ፡፡
“ሰምተኸኛል፡፡ ባጭሩ ምስጢሩን ለማውጣት ብትሞክር ቀድሜ
እገድልሃለሁ፡፡ ናትናኤል ኣንድ ተስፋ ቢኖረን... አንድ ጭላንጭል ቢታየን
እሱንም ልታጨልመው ስትሞክር ዝም ብዬ አልመለከትህም::” ቆፍጠን አለ
ካልቨርት፡፡
“ተስፋ… ተስፋ አትበልብኝ ሰባቴ…” ናትናኤል የተሰማውን ንዴት መደበቅ አልቻለም የነፍሰ ገዳዮች ጥርቅም...““ የወንበዴዎች ሆያሆዬ አይደለም ተስፋ
የሚፈነጥቅብኝ ተስፋ አይደለም፡፡ የሚታየኝ..እልቂት ነው ጥፋት ውድቀት፡፡”
“ታዲያ ለምኑ ፈራህ? ለአፍሪካዊ እልቂትና ፍጅት፣ ጥፋትና ዉድቀት ከመቼ ወዲህ ባዳ ሆነበት? በዘርና በጎሳ፣ በፖለቲካና በሃያማኖት ሰበብ የገዛ ወንድሙን በየጫካው በጥይት እየጠዘጠዘ እየቆላ ላለ አዳኝ ታዳኝ ሕዝብ እልቂትና ፍጅት እዲስ ናቸው? የገዛ መንጋጋው ሊያላምጠው የሌለው የገዛ ጨጓራው ሊሰለቅጠው የሌለው ነጋ ጠባ ከኣውሮፓ ኣራጣ አበዳሪዎች ጓዳ ለማይጠፋ ድሀ ህዝብ ወድቀት ብርቅ ሆነ? ለምነ ፈራህ ..ምን እንዳይመጣ ሰጋህ? ከዜሮ በታች ቁጥር አለ? ከአፍሪካ በታች ገሃነም አለ? ብንሻውም እንኳን ከዚህ በታች የምንወርድበት የምናዘቅጥበት ስፍራ የለም አትስጋ፡፡”
“አንዱ የተፋጀ ዝንተ ዓለም ቢፋጅ… አንዴ የወደቀ ዘለአለም ቢወድቅ ምን ገዶኝ ማለትህ ነው?" አለ ናትናኤል በሃሳሱ የመጣችበት ግን ዘውዲቱ ነበረች… ተጎድቸ ያላቀልኝ ሸርሙጣ… ምኔ ይጎዳል?
“አላልኩም፡፡ ለደዌአቸው መድሃኒቱ እዚያው እመህላቸው አፍሪካ ውስጥ መሆኑን መቀበል ተስኗቸወ ከባዕድ ጋር እየተመሳጠሩ ከመጤ ጋር እየተሻረኩ የገዛ ወንድሞቻቸውን ዕልቂት የሚያራቡ አፍሪካውያን ናቸው፡፡ አፍሪካ አንድ መሆን አለባት።”
“እንድነት'ኮ በዘፈቀደ በአየር ላይ አይመስረትም፡፡” አለ ናትናኤል
ስሜቱን ለማስረዳት ተቸግሮ። “እኔ'ኮ ውህደትን አልተቃወምኩም፡፡ ግን
ፖለቲካዊ አንድነት የኤኮኖሚያዊና የማህበራዊ ዕድገት ጥንቅር ውጤት
ነው፡፡ ከዚያ ውጭኮ ውህደት ጭፍን ውህደት ዲሞክራሲን ችላ ማለት ብቻ
ሳይሆን ኢሳይንሳዊ ነው፡፡”
“ፐ! ኢሳይንሳዊ ሳይንሳዊ ቅራቅንቦ! በአፍሪካ ውስጥ ከነፃነት ወዲህ ስንት ሳይንሳዊ ፖሊሲዎችና ሳይንሳዊ ዕቅዶች በወረቀት እንደሰፈሩ አንድ ፈጣሪ ብቻ ነው የሚያውቅ፡፡ የየትኛው አፍሪካዊ አገር ኤኮኖሚ ሲያብብ ሲፈካ… የየትኛው አፍሪካዊ አገር ማህበራዊ ኑሮ ሲለመልምና ሲምነሸነሽ ታየ? በላ ንገረኝ!”
“ታዲያ እኮ የዚህ ምክንያቱ ዲሞክራሲያዊ ሂደት ስለሌለ ነው፡፡
ዲሞክራሲና ሠላም በሌለበት ዕድገት የለም…” አለ ናትናኤል፡፡
“ውህደት ነው መልሱ!” ዕልህ ያጨናነቀው የካልቨርት ድምፅ
አቋረጠው:: “ልክ እንዳንተ በርካታ አፍሪካውያን ከፖለቲካ ውህደት በፊት
ኤኮኖሚያዊ ግንባታ ሊቀድም እንደሚገባና የፖለቲካን ውህደት ወደፊት
ልንቀዳጀው የምንችል ግብ አድርገው ያቀርቡታል፡፡ ነገር ግን ማስተዋል
የሚገባን የምንጓጓለት ኤኮኖሚያዊ ጥንካሬ ሊፈጠር የሚችለው ሙሉ
ፈቃደኝነት የተሞላበት መደጋገፍና መረዳዳት በአፍሪካ አገሮች መሃከል
ሲሰፍን ብቻ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ መደጋገፍና መረዳዳት በቅድሚያ
የሚጠይቀው ነገር አለ የጋራ ፖለቲካዊ መድረክ፡፡”
“አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ…” አለ ናትናኤል አቋርጦት፡፡ “አፍሪካውያንን፤ ምንድነው ሊያስተሳስረን የሚችል? የአፍሪካ አንድነትና በሥነ ስርዓቱ የተደከመበት ዓላማ ነው፡፡ አልሆነም እንጂ፡፡”
“ከባድ ጥያቄ!” ካልቨርት ጭንቅላቱን ወደኋላ ጥሎ የማሾፍ ሳቅ ሳቀ። “ምንድነው የውህደታችን መሠረት? በእየሱስ ምን እንድልህ ትፈልጋለህ? የሴንጎር ኒግሪትዩድ? የሴኩትሬ አፍሪካዊ ብሄረተኝነት?የንክሩማን የቅኝ ግዛት እስክ ቁስል ጠባሳ? አይደለም፡፡ ለእኔ ባዶ ሆዳችን ነው አንድ የሚያደርገን! የመሰንበትና ያለመሰንበት ጥያቄ ነው
የሚያስተባብረን፡፡ ተነጣጥለን ልንሞላው ያልቻልነውን ከርሳችንን .. ለየብቻ
ቆመን ልናረጋግጠው ያቃተንን ሰላምና ደህንነታችንን እጅ ለእጅ ተያይዘን
ልንጋፈጠው ይገባል! በእኔና በአንተ እግር ላይ የወደቀን ቋጥኝ ለማንሳት የእኔና ያንተን የዝምድና ግንድ መቁጠርና መመርመር አያሻንም።
በመጀመሪያ እግሮቻችን ከመጨፍለቃቸው ፡ በፊት ተረዳድተን ቋጥኙን ከላያችን ማንሳት አለብን፡፡ አለቀ፡፡ የአፍሪካ ውህደት የተደከመበት ነው ላልከው... እርሳው:: ለእኔ አይዋጥልኝም:: በቆንጆ ቆንጆ ከተሞች ቆንጆ ቆንጆ ህንፃዎች እየገነቡ የአፍሪካ ድርጅት'፤ 'የአፍሪካ… ኮሚሽን የአፍሪካ...
ኢንስቲትዩት እያሉ ስም ማውጣት ትንሽ ትንሽ እየሰሩ ብዙ ብዙ የሚከፈላቸውና በሽንጠ ረጃጅም ቆንጆ ቆንጆ የአውሮፓ መኪናዎቻቸው ቆንጆ . ቆንጆ ኮረዶችን እየጫነ መዞር ሥራቸው የሆነ : ውድ ውድ
ኤክስፐርቶችን ማሰባሰብ አፍሪካን አንድ አያደርጋትም::”
“እኔኮ ሊገባኝ ያልቻለው…" ናትናኤል የጀመረውን ሳይጨርስ ለጥቂት ሰኮንዶች ዝም አሉ፡፡ “እሺ ሆነ እንበል፡፡ እንዲያው ድንገት አፍሪካ አንድ ሆናለች ብለህ በመገናኛ መስመሮች ስትለፈልፍ፡ ሌላውን ተወው አፍሪካውያን እራሳቸው ምን ይላሉ? ፍጹም ያላሰበበትና በማኀበራዊና ኢኮኖሚያዊ ህብረት ያላለፉብት ወንድማማችነታቸውን አጠናክረው በሚገባ ያልተዋወቁበት… ድንገተኛ ዱብ ዕዳ ሲመጣባቸው ምን ይላሉ?
“ምን ይላሉ?” ካልቨርት መልሶ ጠየቀ፡፡ “አየህ… ኣንተ በተላያዩ የአፍሪካ አገሮች ያለውን ህዝብ የፖለቲካ አመለካከት አልተረዳህም:: አፍሪካ ውስጥ ፖለቲካ ግለሰብአዊ ነው፡፡ ግለሰቦች ፖለቲካን ይፈጥሩታል እንጂ የፖለቲካ አመለካከት ግለሰቦችን አይቀርጽም ምክንያቱም ፖለቲካ ራስን መጠበቂያ መሣሪያ ነው
አፍሪካ ውስጥ ጥያቄው የትኛው የፖለቲካ መስመር ለእድገት ይበጃል
አይደለም:: ጥያቄው የትኛው የፖለቲካ መስመር ሥልጣን ላይ ያሰነብተኛል ነው ለዚህ ነው ፖለቲካ ግለሰብአዊ ነው
የምልህ፡ ነፃ አፍሪካ አንድ ብትሆን አፍሪካውያን የሚሉት 'አፍሪካ አንድ
ሆነች ነው:: በቃ::”
ያሉባት መኪና ድንገት ፍጥነቷን አብርዳ ከኋላዋ የአቧራ ቁልል አንስታ፡፡ ወደ ቀኝ ስትታጠፍ፡ ቤኬ መገንጠያ ላይ ደርሰናል ብለው አሰቡ፡፡ ለአንድ አፍታ ተያዩ፡፡ ወዲያው ካልቨርት ወደጎን አዝምሞ ከሹፌሩ ጀርባ ያለችውን ትንሽ መስኮት እየደበደበ ሹፌሩ መኪናዋን እንዲያቆም በምልክት ይወተውተው ጀመር፡፡
“ምንድነው? ምንድነው የምታደርገው?” አለ ናትናኤል የካልቨርት ፈሊጥ አልገባህ ሲለው፡፡
“አቁም በለው፡፡ እቃ ጥለሃል በለው::” አለ ካልሸርት ፊቱን ወደ ናትናኤል መልሶ፡፡
ናትናኤል ወደ መስኮቱ ተጠግቶ ለሹፌሩ ዕቃ መጣሉን በምልክት ሲያስረዳው ሹፌሩ መኪናውን አብርዶ ጥግ አስያዛት፡፡
“ምን ሆናችኋል?” ጮኸ ሹፌሩ ጭንቅላቱን ጠምዝዞ፡፡
“ምንድነው የፈለከው? አለ ናትናኤል በተራው ፊቱን ወደ ካልቨርት መልሶ::
"መጣሁ፡፡” አለ ካልቨርት:: ከጭነት መኪናዋ ጀርባ ዘሎ ወረደና ወደ ሹፌሩ ሄደ፡፡ የሽፌሩን በር ከፍቶ ያለሃተታ የሹፌሩን ክንድ ጨመደደና ጎትቶ አወረደው፡፡ የሚነጫነጨው
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
....ደውዬ አነጋግራቸዋለሁ። እስካልለቀቋትና በሰላም እስካልተዋት
ድረስ ዕቅዳቸውን እንደማወጣ አስጠነቅቃቸዋለሁ፡፡”
“እንበልና ሊለቋት ባይስማሙስ?”
“አዝረከርከዋለኋ ጉዳዩን! እየተለቀመ ይጎባታል፡፡” ናትናኤል ንዴት ወረረው::
“አየህ... እዚህ ላይ ነው የማንስማማው:: ልንገርህ... ይህን ምስጢር ልታወጣ ብትሞክር ቀድሜ የምቀነጥስህ እኔ ነኝ፡፡” አለ ካልቨርት ሽጉጥ የከተተበትን ኪሱን በቀኝ እጁ መታ መታ እያደረገ፡፡
“ምን ለማለት ነው?” አለ ናትናኤል ዓይኖቹን አጥብቦ፡፡
“ሰምተኸኛል፡፡ ባጭሩ ምስጢሩን ለማውጣት ብትሞክር ቀድሜ
እገድልሃለሁ፡፡ ናትናኤል ኣንድ ተስፋ ቢኖረን... አንድ ጭላንጭል ቢታየን
እሱንም ልታጨልመው ስትሞክር ዝም ብዬ አልመለከትህም::” ቆፍጠን አለ
ካልቨርት፡፡
“ተስፋ… ተስፋ አትበልብኝ ሰባቴ…” ናትናኤል የተሰማውን ንዴት መደበቅ አልቻለም የነፍሰ ገዳዮች ጥርቅም...““ የወንበዴዎች ሆያሆዬ አይደለም ተስፋ
የሚፈነጥቅብኝ ተስፋ አይደለም፡፡ የሚታየኝ..እልቂት ነው ጥፋት ውድቀት፡፡”
“ታዲያ ለምኑ ፈራህ? ለአፍሪካዊ እልቂትና ፍጅት፣ ጥፋትና ዉድቀት ከመቼ ወዲህ ባዳ ሆነበት? በዘርና በጎሳ፣ በፖለቲካና በሃያማኖት ሰበብ የገዛ ወንድሙን በየጫካው በጥይት እየጠዘጠዘ እየቆላ ላለ አዳኝ ታዳኝ ሕዝብ እልቂትና ፍጅት እዲስ ናቸው? የገዛ መንጋጋው ሊያላምጠው የሌለው የገዛ ጨጓራው ሊሰለቅጠው የሌለው ነጋ ጠባ ከኣውሮፓ ኣራጣ አበዳሪዎች ጓዳ ለማይጠፋ ድሀ ህዝብ ወድቀት ብርቅ ሆነ? ለምነ ፈራህ ..ምን እንዳይመጣ ሰጋህ? ከዜሮ በታች ቁጥር አለ? ከአፍሪካ በታች ገሃነም አለ? ብንሻውም እንኳን ከዚህ በታች የምንወርድበት የምናዘቅጥበት ስፍራ የለም አትስጋ፡፡”
“አንዱ የተፋጀ ዝንተ ዓለም ቢፋጅ… አንዴ የወደቀ ዘለአለም ቢወድቅ ምን ገዶኝ ማለትህ ነው?" አለ ናትናኤል በሃሳሱ የመጣችበት ግን ዘውዲቱ ነበረች… ተጎድቸ ያላቀልኝ ሸርሙጣ… ምኔ ይጎዳል?
“አላልኩም፡፡ ለደዌአቸው መድሃኒቱ እዚያው እመህላቸው አፍሪካ ውስጥ መሆኑን መቀበል ተስኗቸወ ከባዕድ ጋር እየተመሳጠሩ ከመጤ ጋር እየተሻረኩ የገዛ ወንድሞቻቸውን ዕልቂት የሚያራቡ አፍሪካውያን ናቸው፡፡ አፍሪካ አንድ መሆን አለባት።”
“እንድነት'ኮ በዘፈቀደ በአየር ላይ አይመስረትም፡፡” አለ ናትናኤል
ስሜቱን ለማስረዳት ተቸግሮ። “እኔ'ኮ ውህደትን አልተቃወምኩም፡፡ ግን
ፖለቲካዊ አንድነት የኤኮኖሚያዊና የማህበራዊ ዕድገት ጥንቅር ውጤት
ነው፡፡ ከዚያ ውጭኮ ውህደት ጭፍን ውህደት ዲሞክራሲን ችላ ማለት ብቻ
ሳይሆን ኢሳይንሳዊ ነው፡፡”
“ፐ! ኢሳይንሳዊ ሳይንሳዊ ቅራቅንቦ! በአፍሪካ ውስጥ ከነፃነት ወዲህ ስንት ሳይንሳዊ ፖሊሲዎችና ሳይንሳዊ ዕቅዶች በወረቀት እንደሰፈሩ አንድ ፈጣሪ ብቻ ነው የሚያውቅ፡፡ የየትኛው አፍሪካዊ አገር ኤኮኖሚ ሲያብብ ሲፈካ… የየትኛው አፍሪካዊ አገር ማህበራዊ ኑሮ ሲለመልምና ሲምነሸነሽ ታየ? በላ ንገረኝ!”
“ታዲያ እኮ የዚህ ምክንያቱ ዲሞክራሲያዊ ሂደት ስለሌለ ነው፡፡
ዲሞክራሲና ሠላም በሌለበት ዕድገት የለም…” አለ ናትናኤል፡፡
“ውህደት ነው መልሱ!” ዕልህ ያጨናነቀው የካልቨርት ድምፅ
አቋረጠው:: “ልክ እንዳንተ በርካታ አፍሪካውያን ከፖለቲካ ውህደት በፊት
ኤኮኖሚያዊ ግንባታ ሊቀድም እንደሚገባና የፖለቲካን ውህደት ወደፊት
ልንቀዳጀው የምንችል ግብ አድርገው ያቀርቡታል፡፡ ነገር ግን ማስተዋል
የሚገባን የምንጓጓለት ኤኮኖሚያዊ ጥንካሬ ሊፈጠር የሚችለው ሙሉ
ፈቃደኝነት የተሞላበት መደጋገፍና መረዳዳት በአፍሪካ አገሮች መሃከል
ሲሰፍን ብቻ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ መደጋገፍና መረዳዳት በቅድሚያ
የሚጠይቀው ነገር አለ የጋራ ፖለቲካዊ መድረክ፡፡”
“አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ…” አለ ናትናኤል አቋርጦት፡፡ “አፍሪካውያንን፤ ምንድነው ሊያስተሳስረን የሚችል? የአፍሪካ አንድነትና በሥነ ስርዓቱ የተደከመበት ዓላማ ነው፡፡ አልሆነም እንጂ፡፡”
“ከባድ ጥያቄ!” ካልቨርት ጭንቅላቱን ወደኋላ ጥሎ የማሾፍ ሳቅ ሳቀ። “ምንድነው የውህደታችን መሠረት? በእየሱስ ምን እንድልህ ትፈልጋለህ? የሴንጎር ኒግሪትዩድ? የሴኩትሬ አፍሪካዊ ብሄረተኝነት?የንክሩማን የቅኝ ግዛት እስክ ቁስል ጠባሳ? አይደለም፡፡ ለእኔ ባዶ ሆዳችን ነው አንድ የሚያደርገን! የመሰንበትና ያለመሰንበት ጥያቄ ነው
የሚያስተባብረን፡፡ ተነጣጥለን ልንሞላው ያልቻልነውን ከርሳችንን .. ለየብቻ
ቆመን ልናረጋግጠው ያቃተንን ሰላምና ደህንነታችንን እጅ ለእጅ ተያይዘን
ልንጋፈጠው ይገባል! በእኔና በአንተ እግር ላይ የወደቀን ቋጥኝ ለማንሳት የእኔና ያንተን የዝምድና ግንድ መቁጠርና መመርመር አያሻንም።
በመጀመሪያ እግሮቻችን ከመጨፍለቃቸው ፡ በፊት ተረዳድተን ቋጥኙን ከላያችን ማንሳት አለብን፡፡ አለቀ፡፡ የአፍሪካ ውህደት የተደከመበት ነው ላልከው... እርሳው:: ለእኔ አይዋጥልኝም:: በቆንጆ ቆንጆ ከተሞች ቆንጆ ቆንጆ ህንፃዎች እየገነቡ የአፍሪካ ድርጅት'፤ 'የአፍሪካ… ኮሚሽን የአፍሪካ...
ኢንስቲትዩት እያሉ ስም ማውጣት ትንሽ ትንሽ እየሰሩ ብዙ ብዙ የሚከፈላቸውና በሽንጠ ረጃጅም ቆንጆ ቆንጆ የአውሮፓ መኪናዎቻቸው ቆንጆ . ቆንጆ ኮረዶችን እየጫነ መዞር ሥራቸው የሆነ : ውድ ውድ
ኤክስፐርቶችን ማሰባሰብ አፍሪካን አንድ አያደርጋትም::”
“እኔኮ ሊገባኝ ያልቻለው…" ናትናኤል የጀመረውን ሳይጨርስ ለጥቂት ሰኮንዶች ዝም አሉ፡፡ “እሺ ሆነ እንበል፡፡ እንዲያው ድንገት አፍሪካ አንድ ሆናለች ብለህ በመገናኛ መስመሮች ስትለፈልፍ፡ ሌላውን ተወው አፍሪካውያን እራሳቸው ምን ይላሉ? ፍጹም ያላሰበበትና በማኀበራዊና ኢኮኖሚያዊ ህብረት ያላለፉብት ወንድማማችነታቸውን አጠናክረው በሚገባ ያልተዋወቁበት… ድንገተኛ ዱብ ዕዳ ሲመጣባቸው ምን ይላሉ?
“ምን ይላሉ?” ካልቨርት መልሶ ጠየቀ፡፡ “አየህ… ኣንተ በተላያዩ የአፍሪካ አገሮች ያለውን ህዝብ የፖለቲካ አመለካከት አልተረዳህም:: አፍሪካ ውስጥ ፖለቲካ ግለሰብአዊ ነው፡፡ ግለሰቦች ፖለቲካን ይፈጥሩታል እንጂ የፖለቲካ አመለካከት ግለሰቦችን አይቀርጽም ምክንያቱም ፖለቲካ ራስን መጠበቂያ መሣሪያ ነው
አፍሪካ ውስጥ ጥያቄው የትኛው የፖለቲካ መስመር ለእድገት ይበጃል
አይደለም:: ጥያቄው የትኛው የፖለቲካ መስመር ሥልጣን ላይ ያሰነብተኛል ነው ለዚህ ነው ፖለቲካ ግለሰብአዊ ነው
የምልህ፡ ነፃ አፍሪካ አንድ ብትሆን አፍሪካውያን የሚሉት 'አፍሪካ አንድ
ሆነች ነው:: በቃ::”
ያሉባት መኪና ድንገት ፍጥነቷን አብርዳ ከኋላዋ የአቧራ ቁልል አንስታ፡፡ ወደ ቀኝ ስትታጠፍ፡ ቤኬ መገንጠያ ላይ ደርሰናል ብለው አሰቡ፡፡ ለአንድ አፍታ ተያዩ፡፡ ወዲያው ካልቨርት ወደጎን አዝምሞ ከሹፌሩ ጀርባ ያለችውን ትንሽ መስኮት እየደበደበ ሹፌሩ መኪናዋን እንዲያቆም በምልክት ይወተውተው ጀመር፡፡
“ምንድነው? ምንድነው የምታደርገው?” አለ ናትናኤል የካልቨርት ፈሊጥ አልገባህ ሲለው፡፡
“አቁም በለው፡፡ እቃ ጥለሃል በለው::” አለ ካልሸርት ፊቱን ወደ ናትናኤል መልሶ፡፡
ናትናኤል ወደ መስኮቱ ተጠግቶ ለሹፌሩ ዕቃ መጣሉን በምልክት ሲያስረዳው ሹፌሩ መኪናውን አብርዶ ጥግ አስያዛት፡፡
“ምን ሆናችኋል?” ጮኸ ሹፌሩ ጭንቅላቱን ጠምዝዞ፡፡
“ምንድነው የፈለከው? አለ ናትናኤል በተራው ፊቱን ወደ ካልቨርት መልሶ::
"መጣሁ፡፡” አለ ካልቨርት:: ከጭነት መኪናዋ ጀርባ ዘሎ ወረደና ወደ ሹፌሩ ሄደ፡፡ የሽፌሩን በር ከፍቶ ያለሃተታ የሹፌሩን ክንድ ጨመደደና ጎትቶ አወረደው፡፡ የሚነጫነጨው
👍2
#የፍቅር_ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
....ቲናን አይኗን በፍርሃት ጎልጉላ እያየችው “ሚ/ር ዊሊያምስ እኔ ህይወቴን እፈልገዋለሁ። እንደ ድሮ ነፃ ሆኜ መኖር እፈልጋለሁ።” አለችው፡፡
አድሬኒ እንደነገረችው ከንቲባው ሴትየዋን በወሲብ የሚተነኩስበት አቋም የላትም። ባይሆን ቆንጆ እና ብልህ አዕምሮ እንዳላት ታስታውቃለች፡፡
“ብዙ ጊዜ ከቦታ ቦታ ቤት እየቀየርሽ ትዘዋወሪያለሽ?” ብሎ ጠየቃት፡፡
መልሷን ቢያውቀውም “አዎን። ምክንያቱም አንድ ቦታ ላይ ለብዙ ጊዜያት
መቆየት ለደህንነቴ ያሰጋኛል።” አለችው።
“ይሄ ደግሞ በጣም ወጪ ያበዛብሻል።” አላት እና በቀጥታ “ደንበኛዬ አንቺ ለምትሰጪኝ መረጃዎች በሙሉ ልትከፍልሽ ፈቃደኛ ናት” አላት፡፡
ቲና በእጇ ሀሳቡን አጣጣለችበት እና በመቀጠልም “አመሰግናለሁ ዴሪክ፡፡
ግን እውነቱን ስለተናገርኩ ብቻ ክፍያ መቀበሌ ምቾት አይሰጠኝም። አንተ
ጥሩ ሰው ትመስላለህ፡፡ ደምበኛህም ታማኝ ሳትሆን አትቀርም”
“ልክ ነሽ” አላት፡፡
“አንተ እንዳልከው እኛን አንድ አይነት ሰዎች የሚያስፈራሩን ከሆነ ከማን ጋር እየታገላችሁ እንደሆነ ጠንቅቃችሁ የምታውቁ አልመሰለኝም” አለችው፡፡
“ከሩሲያኖቹ ጋር ነው” አላት፡፡
ቲና ሥማቸውን እንኳን ገና ስትሰማ አይኗ በድንጋጤ ፈጠጠ፡፡
“አዎን” አላት በሹክሹክታ ድምፅ “ስለዚህ ደምበኛህን ከአካባቢው ዞር እንድትል ምከራት” ዊሊያም ስለ ኒኪ አሰበ እና ፈገግ ብሎ
“ይሄንን ያንቺን ምክር የምትቀበለው አይመስለኝም። እሷ በጣም ግትር
ሰው ናት” ብሎ መለሰላት፡፡
ይሄ እኮ ጨዋታ አይደለም” ብላ ቲና እየተቆጣች “ሰዎች እየሞቱ ነው፡፡
እኔ ያናገርኩት የኤልኤታይምስ ጋዜጣ ሪፖርተር እንኳን ሞቷል
”ዊሊያምስ ማስታወሻውን መውሰድ ጀመረ፡፡
“እነርሱ በልብ በሽታ ነው የሞተው ይላሉ:: ግን ገና የ33 ዓመት ወጣት
እና እንደ ፈረስ ጠንካራ ነበር።”
“ቲና አሁንም ሰዎች እየተገደሉ ነው” አላት እና ዊሊያምስ በመቀጠልም
“እኔም እዚህ የተገኘሁት በዚህ ምክንያት ነው” አላት፡፡
በመቀጠልም ስለ ሊዛ ፍላንገንን እና ትሬይ ሬይሞንድ ግድያ ሟቾቹ
ከኒኪ ሮበርትስ እና ከባሏ ዶውግ ጋር ስላላቸው ግንኙነት ሮበርትስ ስላለው
ከአደንዛዥ ዕፅ ጋር ስለሚገናኝ የበጎ አድራጎት ሥራዎቹ እና በሎስ አንጀለስ
ላይ የበላይነቱን ለመያዝ ሩስያኖቹ እና ሜክሲካኖቹ ስለሚያደርጉት ግብግብ
ጭምር ነገራት፡፡
“ዶውግ ሮበርትስ ባለፈው ዓመት ነው በአደጋ ህይወቱን ያጣው:: ከጎኑ
ደግሞ ለከንቲባ ፋንቴስን መኪና ከሚሰጡት ሩስያውያን ጋር ግንኙነት ያላት
ሴት ነበረች። እሷም በአደጋው ሞታለች” አላት፡፡
ቲናም እጇን አንስታ “ሙስና ነው ያልከው? አድሬኒ ናት ይህንን የነገረችህ? በእግዚአብሔር ሥም ይህቺ ልጅ በቅርቡ ትገደላለች እመነኝ:: ደግሞ የሚገርመው ነገር እኮ እሷ ስለጉዳዩ ምንም የምታውቀው ነገር ያለመኖሩ ነው::” አለችው፡፡
“ልክ ብለሻል እኔም እንደ አንቺ ነው የማስበው” አላት ዊሊያምስ፡፡
“በመጀመሪያ ደረጃ እኔ ፋንቴስ በግሉ ጉቦ ይቀበላል አይደለም ያልኩት።
ግን ማዘጋጃ ቤቱ ለእሱ ባወጣለት የባንክ አካውንት በኩል የተለያየ አይነት
ገንዘቦች ይገቡለታል ነው ያልኩት። የማወራህ ስለ ትልቅ ክፍያዎች ሲሆን
ክፍያውን ደግሞ የሚፈፅሙት ሩሲያዎኖቹ ናቸው”
ዊሊያምስም ማስታወሻ ደብተር ላይ እየፃፈ “ምን ያህል? እና ደግሞ
የትኞቹ ሩሲያኖች?”
“መጠኖቹ በየጊዜው ይለያያሉ።” አለች እና ቲና በመቀጠልም
“አምስት መቶ ሺ ዶላር መቶ አምሳ ሺ ዶላር እና አንድ ጊዜ ደግሞ አንድ ሚሊዩን ዶላር፡፡ ብቻ በየአራት እና በየስድስት ሳምንቱ የተለያዩ ቼኮች
ይመጣሉ፡፡ ለማንኛውም ባጠቃላይ ወደ ሦስት ሚሊዩን ዶላር ይሆናል።”
“እሺ ክፍያውን የሚፈፅሙትን የሩሲያኖችን ሥም ታውቂዋለሽ?”
አላት፡፡
“አላውቅም” ብላ ወደ ወለሉ
ተመለከተች:: ዊሊያምስ ቲና በጣም
እንደፈራች ተመልክቶም
“እነርሱን የምትገልጪበት አካላዊ ሁኔታቸው? በአካልስ አግኝተሻቸው
ታውቂያለሽ?” ብሎ ጠየቃት። ቲናም ራሷን በአሉታ በሀይል ካወዛወዘች
በኋላ ከንፈሯን ነክሳ “ይቅርታ ይህንን ልነግርህ አልችልም” አለችው፡፡
የስልክ ጥሪዎችን ቢያንስ ተቀብለሽ ታውቂያለሽ? ወንዶች ናቸው ሴቶች?
ሁለት ናቸው ወይንስ ሃያ?”
“አይገባህም እኮ...”
ሌንካ ጎርደቪስኪ የምትባል ሴት ታውቂያለሽ?” ብሎ አይፎን ስልኩን
አወጣና የጎርዴቪስኪን ፎቶ አሳያት። የቲና አይን ላይ ሌንካን እንዳስታወሰች
የሚያሳብቅ ዕይታን ዊሊያምስ ተመለከተ።
“ዴ.ሪክ ስለዚህ ነገር መናገር አልችልም። እስከ አሁንም በጣም ብዙ ነገር
ነው የተናገርኩት”
“ቢያንስ የአንድ ካምፓኒ ሥምን ንገሪኝ፤ ያላወቅኩትን እንቆቅልሽ የምፈታበትን አንድ ነገርን እንኳን ንገሪኝ” ሲላት ጊዜ አናቷን በሀይል ወዝውዛ ይገድሉኛል!” አለችው፡፡
ዊሊያምም ለጥቂት ጊዜ ያህል አፍጥጦ ሲያያት ቆየና በቀስታ “ምናልባት ይገድሉሽ ይሆናል። ምናልባት ሁለታችንንም ይገድሉን ይሆናል፤ ግን አንቺ የያዝሺው ሚስጥር እንደወጣ በማሰብ ሌሎች ሰዎች እየተገደሉ ቢሆንስ? ይህንን ግድያቸውን የሚያስቆመው ደግሞ አንቺ
የያዝሺውን ሚስጥር ይፋ በማውጣት ነው። ይህንን ነገር አምነሽ አይደል
እንዴ ለሮቢን ሳንፎርድ ስልክ የደወልሺው?”
“አዎን” አለች እና ቲና ታፋዋ ላይ ያስቀመጠችው እጇ ይንቀጠቀጥባት
ጀመር፡፡ “በጣም እንደፈራሽ አውቃለሁ። እኔም እኮ በጣም ፈርቻለሁ፤ ቲና
ግን ይሄንን እኛ ካልተናገርን ማን ይናገራል እሺ?”
ዴሪክ ዊሊያምስ ከጎኑ በተቀመጠችው ሴትዮ ውስጥ የሚካሄደውን የሀሳቦች ፍልሚያን አሰበ። ቲና ድሬይተን በጣም ደፋር ሴት ነች። ይህንን ደግሞ አንድ ጊዜ ለማረጋገጥ ችሏል። ግን ሁሉም ሰው የድፍረት ገደብ አለው።
“እሺ” አለች እና በመጨረሻም “እነግርሃለሁ። ግን ከዚህ በኋላ እኔን ዳግመኛ በፍፁም ለማግኘት እንዳትሞክር፡፡ በፍፁም! ለማንኛውም ምክንያት ቢሆን።
ዊሊያምም ወንበሩ ላይ ተመልሶ ቁጭ አለ እና
“ይሄው ቃሌን እሰጥሻለሁ” ብሏት እስክሪብቶውን አወጣ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ኒኪ እና ግሬቸን ገና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች እያሉ ይሄዱበት ወደ
ነበረው የኮሪያውያን ፍልውሃ ውስጥ ራቁታቸውን ሆነው ሰውነታቸውን
እያደሱ ነው። ግሬቸን የወረዱ ጡቶቿን ከኒኪ ብርትኳን ከሚያካክሉ ጡቶች
ጋር፣ ሽንትርትር ያለውንና ዘልዘል ያለ ሆዷን ደግሞ ልጥፍ ካለው የኒኪ
ጡቶች ጋር አነፃፀረች፡፡ ጡቶቿ ሦስት ልጆችን ያጠባ እና ሆዷም ሦስት
ልጆችን የተሸከመ በመሆኑ የተነሳ እንደዚህ እንደሆነ አሰበች እና ተፅናናች::
ኒኪ ውሃው ውስጥ ሙሉ በሙሉ ሰምጣ ከወጣች በኋላ የሴት ወሬያቸውን ጀመረች “ባለፈው የነበረው የእራት ግብዣ ላይ ሀዶን አስገድዶ ሳመኝ፤ ከበፊት ጀምሮም እወድሻለሁ አለኝ” አለች ኒኪ ላግሬቸን፡፡
ግሬቸንም “እኮ የኛ ሀዶን ነው?” ብላ ተገርማ ጠየቀቻት፡፡
“አዎን፣ ግን ጥሩ ስሜት አልተሰማኝም። ምክንያቱም እሱ እኮ ለዶውግ
ልክ እንደ ወንድሙ ነበር፡፡
“አአ ልክ እንደ ኦሪት ዘመን ነዋ? ማለትም አንዲት ሴት ቧሏ ከሞተ ወንድምዬው እንደሚጠቀልላት አይነት ነገር መሆኑ ነዋ” ብላ ግሬቸን አሾፈችባት፡፡
ኒኪም በግሬቸን ሹፈት ትንሽ ተከፍታ ዝም አለች። ግሬቸን ይሄ የኒኪ ጥቁር ደመና እስኪያልፍ ድረስ ዝም ብላት ውሃው ውስጥ ብቅ ጥልቅ ስትል ቆየች፡፡
ከጥቂት ጊዜ በኋላም ኒኪ “ይሄውልሽ ግሬች እኔ ችግር ሳይኖርብኝ
አይቀርም፡፡ ምንም አይነት የወሲብ ፍላጎት እንኳን የለኝም”
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
....ቲናን አይኗን በፍርሃት ጎልጉላ እያየችው “ሚ/ር ዊሊያምስ እኔ ህይወቴን እፈልገዋለሁ። እንደ ድሮ ነፃ ሆኜ መኖር እፈልጋለሁ።” አለችው፡፡
አድሬኒ እንደነገረችው ከንቲባው ሴትየዋን በወሲብ የሚተነኩስበት አቋም የላትም። ባይሆን ቆንጆ እና ብልህ አዕምሮ እንዳላት ታስታውቃለች፡፡
“ብዙ ጊዜ ከቦታ ቦታ ቤት እየቀየርሽ ትዘዋወሪያለሽ?” ብሎ ጠየቃት፡፡
መልሷን ቢያውቀውም “አዎን። ምክንያቱም አንድ ቦታ ላይ ለብዙ ጊዜያት
መቆየት ለደህንነቴ ያሰጋኛል።” አለችው።
“ይሄ ደግሞ በጣም ወጪ ያበዛብሻል።” አላት እና በቀጥታ “ደንበኛዬ አንቺ ለምትሰጪኝ መረጃዎች በሙሉ ልትከፍልሽ ፈቃደኛ ናት” አላት፡፡
ቲና በእጇ ሀሳቡን አጣጣለችበት እና በመቀጠልም “አመሰግናለሁ ዴሪክ፡፡
ግን እውነቱን ስለተናገርኩ ብቻ ክፍያ መቀበሌ ምቾት አይሰጠኝም። አንተ
ጥሩ ሰው ትመስላለህ፡፡ ደምበኛህም ታማኝ ሳትሆን አትቀርም”
“ልክ ነሽ” አላት፡፡
“አንተ እንዳልከው እኛን አንድ አይነት ሰዎች የሚያስፈራሩን ከሆነ ከማን ጋር እየታገላችሁ እንደሆነ ጠንቅቃችሁ የምታውቁ አልመሰለኝም” አለችው፡፡
“ከሩሲያኖቹ ጋር ነው” አላት፡፡
ቲና ሥማቸውን እንኳን ገና ስትሰማ አይኗ በድንጋጤ ፈጠጠ፡፡
“አዎን” አላት በሹክሹክታ ድምፅ “ስለዚህ ደምበኛህን ከአካባቢው ዞር እንድትል ምከራት” ዊሊያም ስለ ኒኪ አሰበ እና ፈገግ ብሎ
“ይሄንን ያንቺን ምክር የምትቀበለው አይመስለኝም። እሷ በጣም ግትር
ሰው ናት” ብሎ መለሰላት፡፡
ይሄ እኮ ጨዋታ አይደለም” ብላ ቲና እየተቆጣች “ሰዎች እየሞቱ ነው፡፡
እኔ ያናገርኩት የኤልኤታይምስ ጋዜጣ ሪፖርተር እንኳን ሞቷል
”ዊሊያምስ ማስታወሻውን መውሰድ ጀመረ፡፡
“እነርሱ በልብ በሽታ ነው የሞተው ይላሉ:: ግን ገና የ33 ዓመት ወጣት
እና እንደ ፈረስ ጠንካራ ነበር።”
“ቲና አሁንም ሰዎች እየተገደሉ ነው” አላት እና ዊሊያምስ በመቀጠልም
“እኔም እዚህ የተገኘሁት በዚህ ምክንያት ነው” አላት፡፡
በመቀጠልም ስለ ሊዛ ፍላንገንን እና ትሬይ ሬይሞንድ ግድያ ሟቾቹ
ከኒኪ ሮበርትስ እና ከባሏ ዶውግ ጋር ስላላቸው ግንኙነት ሮበርትስ ስላለው
ከአደንዛዥ ዕፅ ጋር ስለሚገናኝ የበጎ አድራጎት ሥራዎቹ እና በሎስ አንጀለስ
ላይ የበላይነቱን ለመያዝ ሩስያኖቹ እና ሜክሲካኖቹ ስለሚያደርጉት ግብግብ
ጭምር ነገራት፡፡
“ዶውግ ሮበርትስ ባለፈው ዓመት ነው በአደጋ ህይወቱን ያጣው:: ከጎኑ
ደግሞ ለከንቲባ ፋንቴስን መኪና ከሚሰጡት ሩስያውያን ጋር ግንኙነት ያላት
ሴት ነበረች። እሷም በአደጋው ሞታለች” አላት፡፡
ቲናም እጇን አንስታ “ሙስና ነው ያልከው? አድሬኒ ናት ይህንን የነገረችህ? በእግዚአብሔር ሥም ይህቺ ልጅ በቅርቡ ትገደላለች እመነኝ:: ደግሞ የሚገርመው ነገር እኮ እሷ ስለጉዳዩ ምንም የምታውቀው ነገር ያለመኖሩ ነው::” አለችው፡፡
“ልክ ብለሻል እኔም እንደ አንቺ ነው የማስበው” አላት ዊሊያምስ፡፡
“በመጀመሪያ ደረጃ እኔ ፋንቴስ በግሉ ጉቦ ይቀበላል አይደለም ያልኩት።
ግን ማዘጋጃ ቤቱ ለእሱ ባወጣለት የባንክ አካውንት በኩል የተለያየ አይነት
ገንዘቦች ይገቡለታል ነው ያልኩት። የማወራህ ስለ ትልቅ ክፍያዎች ሲሆን
ክፍያውን ደግሞ የሚፈፅሙት ሩሲያዎኖቹ ናቸው”
ዊሊያምስም ማስታወሻ ደብተር ላይ እየፃፈ “ምን ያህል? እና ደግሞ
የትኞቹ ሩሲያኖች?”
“መጠኖቹ በየጊዜው ይለያያሉ።” አለች እና ቲና በመቀጠልም
“አምስት መቶ ሺ ዶላር መቶ አምሳ ሺ ዶላር እና አንድ ጊዜ ደግሞ አንድ ሚሊዩን ዶላር፡፡ ብቻ በየአራት እና በየስድስት ሳምንቱ የተለያዩ ቼኮች
ይመጣሉ፡፡ ለማንኛውም ባጠቃላይ ወደ ሦስት ሚሊዩን ዶላር ይሆናል።”
“እሺ ክፍያውን የሚፈፅሙትን የሩሲያኖችን ሥም ታውቂዋለሽ?”
አላት፡፡
“አላውቅም” ብላ ወደ ወለሉ
ተመለከተች:: ዊሊያምስ ቲና በጣም
እንደፈራች ተመልክቶም
“እነርሱን የምትገልጪበት አካላዊ ሁኔታቸው? በአካልስ አግኝተሻቸው
ታውቂያለሽ?” ብሎ ጠየቃት። ቲናም ራሷን በአሉታ በሀይል ካወዛወዘች
በኋላ ከንፈሯን ነክሳ “ይቅርታ ይህንን ልነግርህ አልችልም” አለችው፡፡
የስልክ ጥሪዎችን ቢያንስ ተቀብለሽ ታውቂያለሽ? ወንዶች ናቸው ሴቶች?
ሁለት ናቸው ወይንስ ሃያ?”
“አይገባህም እኮ...”
ሌንካ ጎርደቪስኪ የምትባል ሴት ታውቂያለሽ?” ብሎ አይፎን ስልኩን
አወጣና የጎርዴቪስኪን ፎቶ አሳያት። የቲና አይን ላይ ሌንካን እንዳስታወሰች
የሚያሳብቅ ዕይታን ዊሊያምስ ተመለከተ።
“ዴ.ሪክ ስለዚህ ነገር መናገር አልችልም። እስከ አሁንም በጣም ብዙ ነገር
ነው የተናገርኩት”
“ቢያንስ የአንድ ካምፓኒ ሥምን ንገሪኝ፤ ያላወቅኩትን እንቆቅልሽ የምፈታበትን አንድ ነገርን እንኳን ንገሪኝ” ሲላት ጊዜ አናቷን በሀይል ወዝውዛ ይገድሉኛል!” አለችው፡፡
ዊሊያምም ለጥቂት ጊዜ ያህል አፍጥጦ ሲያያት ቆየና በቀስታ “ምናልባት ይገድሉሽ ይሆናል። ምናልባት ሁለታችንንም ይገድሉን ይሆናል፤ ግን አንቺ የያዝሺው ሚስጥር እንደወጣ በማሰብ ሌሎች ሰዎች እየተገደሉ ቢሆንስ? ይህንን ግድያቸውን የሚያስቆመው ደግሞ አንቺ
የያዝሺውን ሚስጥር ይፋ በማውጣት ነው። ይህንን ነገር አምነሽ አይደል
እንዴ ለሮቢን ሳንፎርድ ስልክ የደወልሺው?”
“አዎን” አለች እና ቲና ታፋዋ ላይ ያስቀመጠችው እጇ ይንቀጠቀጥባት
ጀመር፡፡ “በጣም እንደፈራሽ አውቃለሁ። እኔም እኮ በጣም ፈርቻለሁ፤ ቲና
ግን ይሄንን እኛ ካልተናገርን ማን ይናገራል እሺ?”
ዴሪክ ዊሊያምስ ከጎኑ በተቀመጠችው ሴትዮ ውስጥ የሚካሄደውን የሀሳቦች ፍልሚያን አሰበ። ቲና ድሬይተን በጣም ደፋር ሴት ነች። ይህንን ደግሞ አንድ ጊዜ ለማረጋገጥ ችሏል። ግን ሁሉም ሰው የድፍረት ገደብ አለው።
“እሺ” አለች እና በመጨረሻም “እነግርሃለሁ። ግን ከዚህ በኋላ እኔን ዳግመኛ በፍፁም ለማግኘት እንዳትሞክር፡፡ በፍፁም! ለማንኛውም ምክንያት ቢሆን።
ዊሊያምም ወንበሩ ላይ ተመልሶ ቁጭ አለ እና
“ይሄው ቃሌን እሰጥሻለሁ” ብሏት እስክሪብቶውን አወጣ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ኒኪ እና ግሬቸን ገና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች እያሉ ይሄዱበት ወደ
ነበረው የኮሪያውያን ፍልውሃ ውስጥ ራቁታቸውን ሆነው ሰውነታቸውን
እያደሱ ነው። ግሬቸን የወረዱ ጡቶቿን ከኒኪ ብርትኳን ከሚያካክሉ ጡቶች
ጋር፣ ሽንትርትር ያለውንና ዘልዘል ያለ ሆዷን ደግሞ ልጥፍ ካለው የኒኪ
ጡቶች ጋር አነፃፀረች፡፡ ጡቶቿ ሦስት ልጆችን ያጠባ እና ሆዷም ሦስት
ልጆችን የተሸከመ በመሆኑ የተነሳ እንደዚህ እንደሆነ አሰበች እና ተፅናናች::
ኒኪ ውሃው ውስጥ ሙሉ በሙሉ ሰምጣ ከወጣች በኋላ የሴት ወሬያቸውን ጀመረች “ባለፈው የነበረው የእራት ግብዣ ላይ ሀዶን አስገድዶ ሳመኝ፤ ከበፊት ጀምሮም እወድሻለሁ አለኝ” አለች ኒኪ ላግሬቸን፡፡
ግሬቸንም “እኮ የኛ ሀዶን ነው?” ብላ ተገርማ ጠየቀቻት፡፡
“አዎን፣ ግን ጥሩ ስሜት አልተሰማኝም። ምክንያቱም እሱ እኮ ለዶውግ
ልክ እንደ ወንድሙ ነበር፡፡
“አአ ልክ እንደ ኦሪት ዘመን ነዋ? ማለትም አንዲት ሴት ቧሏ ከሞተ ወንድምዬው እንደሚጠቀልላት አይነት ነገር መሆኑ ነዋ” ብላ ግሬቸን አሾፈችባት፡፡
ኒኪም በግሬቸን ሹፈት ትንሽ ተከፍታ ዝም አለች። ግሬቸን ይሄ የኒኪ ጥቁር ደመና እስኪያልፍ ድረስ ዝም ብላት ውሃው ውስጥ ብቅ ጥልቅ ስትል ቆየች፡፡
ከጥቂት ጊዜ በኋላም ኒኪ “ይሄውልሽ ግሬች እኔ ችግር ሳይኖርብኝ
አይቀርም፡፡ ምንም አይነት የወሲብ ፍላጎት እንኳን የለኝም”
👍4
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...ሰሞኑን ያየችው ህልም ክፉኛ ያስደነገጣት እናት አመዱን ይነሰንስባት ጀምሯል። የወትሮ ህልሟ ተስፋን የሚያበስር መሆኑን ስለምታውቅ ፊቷ እንደ ፀሀይ እያበራ በደስታ መንፈስ ለቡና ማህበረተኞቿ ታወራላቸው ነበር፡፡ ከማህበርተኞቿ ውስጥ ደግሞ በህልም ፈቺነታቸው ወይዘሮ
ተዋበችን የሚደርስባቸው የለም፡፡ ህልም ሲፈቱ እንከን አይወጣላቸውም ተብሎ በአብዛኛው ነዋሪ ስለሚታመንባቸው ህልም ለመፍታት ኩራታቸው አይጣል ነው። ትንሽ ካላስለመኑ ህልም አይፈቱም፡፡ ከልመና በኋላ ግን መተንተን ይጀምራሉ፡፡
ሲሳይ ነው! ዓለም ነው!አቤት ደስታ! ልጅ ልትወልጂ ነው...ስለትሽ ሊደርስ ነው፣ በዚህ ሊገባ በዚህ ሊወጣ ነው፡፡ የተጣላው ሊታረቅ፣ የደለው ሊሞላ.. ብቻ ጥሩ ጥሩውን ሁሉ ልታገኙ ነው እያሉ አላሚውን
ተስፋ በተስፋ ያደርጉታል፡፡ ከሁሉ የበለጠ የህልም ደንበኛቸው ግን
አስካለ ነበረች። ያየችውን ህልም ስትነግራቸው ሁሌም የሚያያይዙት ከልጆቿ ጋር ነው፡፡
አቤት! አቤት! በውነት ህልም አይደለም ያየሽለት ራዕይ ነው፡፡ ጉድ! ደሞዙ ከፍ ሥልጣኑም ከፍ ሊል ነው፡፡ ጥሩ ደረጃ ላይ ሊደርስልሽ ነው! ትንሿም ደስ ብሏታል ያንቺ ናፍቆት አለባት መሰለኝ እዚህ ጋ ትንሽ ቅር
እንዳላት አያለሁ፡፡ ይሁን ግድ የለም ትምህርት ቤት ሲዘጋ ትመጣለች።
ጥሩ ህልም ነው ይሏታል የቡናው አሻራ ያረፈበትን ባዶ ስኒ ዘቅዝቀው እየተመለከቱ፡፡ ከዚያም አስካለ በደስታ መፈንደቅ ነው። በዚህ ሁሉ ቆንጆ ቆንጆ ህልሞቿ ጣልቃ ስሞኑን ያየችው መጥፎ ህልም ግን ክፉኛ አስደንግጧታል
ለማንም ሳትናገር ፍርሃትና ሃሣብ ውስጥ ውስጡን ሲያካት ቆይቶ በትንሽ ጊዜ ውስጥ ወዛም ነበረ ፊቷ ላይ አመዱን ይነዛበት ገባ።
"ተነሳብሽ ደግሞ አንቺ ሴት! ለመሆኑ ሄደሽ ከመጣሽ ሁለት ወር እንኳ ይሞላዋል እንዴ? ናፈቁኝ ነው ወይስ ምን አዲስ ነገር ተገኘና ነው እንዴዚህ ነጭ እስከምትሆኚ ድረስ ራስሽን መጣል ያመጣሽው?” ለመሽፋፈን ጥረት ብታደርግም ሃሳብ እየወዘወዛት መሆኑ የገባቸው ወይዘሮ ተዋቡ ተቆጡ።አስካለ የመጀመሪያ መጥፎ ህልሟን አይታ መረበሽ ከጀመረች
በኋላ ጭንቀቱ ነው መሰል በላይ በላዩ የሚያስፈራራ ህልም እየደጋገመ አስቸገራት። የአሁኑ ደግሞ ፍፁም የተለየ ሆነባት።
ጌትነት ይመስላታል፡፡ እንደ ልጅነቱ አብሯት እንጨት ለቀማ ይሄዳሉ።
ከአንዱ ዛፍ ወደ ሌላው ዛፍ እየዘለለ ጥሩ ጥሩውን እንጨት እየሰበረ ኢያቀበላት የቆመበት ቅርንጫፍ ተገንጥሎ መሬት ላይ ይወድቃል። ከዚያም
ይንከባለላል. በዚያው እንደ ሙቀጫ ጅው ብሎ ተንከባሎ ቁልቁል ይወርዳል። ለካስ ከስሩ ገደል ነበር፡፡ ከታች ገደል መኖሩን፣ ልጅዋ አደጋ ላይ መውደቁን ያየች እናት ኡኡ! ልጄን! ልጄን!.. ልጄን! እየጮኸች አብራው ልትገባ ወደ እሱ ትሮጣለች። ጌትነት ገደሉ ውስጥ ተወርውሮ ከመግባት ለትንሽ የተረፈው የሆነ ቁጥቋጦ ነገር እጁ ውስጥ ስለገባ ነበር፡፡
ከዚያም እናቱ ጉዳት ላይ እንዳትወድቅበት ውትወታውን ይቀጥላል።
“እማዬ! እማዬ!ደህና ነኝ! ምንም አልሆንኩም! እዚያው ቁሚ! መጣሁ! መጣሁ! መጣሁ!" ወደሱ ስትሮጥ ወድቃ እንዳትሰበር ፈርቶ ይጮሀል። እሷ ደግሞ አሻፈረኝ ብላ ወደ ገደሉ እየሮጠች ትመጣና ገደሉ ጫፍ ላይ
ሆና “ጌትዬ! ተረፍክ የኔ ጌታ?!” ቁልቁል እያየችው ትጠይቀዋለች::
"ተርፌአለሁ! ተርፌአለሁ!አይዞሽ! ምንም አልሆንኩም በቃ እዚያው ጋ ሁኚ!" ይላትና በአንድ ትልቅ ቋጥኝ ላይ ተጋድሞ በተንጠለጠለ ወፍራም
ሀረግ አማካኝነት እየተሳበ ሽቅብ መውጣት ጀመረ። ወጣ ወጣ...
ወጣና አጠገቧ ሊደርስ ትንሽ ቀረው። ደክሞታል። አልቦታል። ..
“አይዞህ ጌትዬ በርታ የኔ ልጅ... ቆይ እጅህን ልያዝልህ" ጐንበስ
ትላለች።
“ተይ !ተይ! እማዬ ተይ! እንዳያንሸራትትሽ !እኔ ቀስ እያልኩ እወጣ ለሁ ተይ!!"
“ግዴለህም ይልቁንስ እጅህን አቀብለኝ" ትለውና ሄዳ ከገደሉ ጫፍ ላይ ተንጠልጥላ የቀኝ እጇን ትልክለታለች። አልደርስብሽ ይላታል። እንደገና ብሃይል ወደሱ ተንጠራርታ እጇን ልትስጠው ጐንበስ ትላለች። በግራ እጅዋ አንድ ትልቅ ጉቶ ይዛ ነበር፡፡ አሁንም አልደርስብሽ ይላታል።
ጭንቅቱ አስጨንቋት ቶሎ ልታወጣው ቸኩላለች። እሱም አወጣዋለሁ ብላ ስትፍጨረጨር ጉዳት ላይ እንዳትወድቅ ፈርቶ እጅዋን ቶሎ ለመያዝ ይንደፋደፋል። ተቃረበ ። ሊይዛት ትንሽ ብቻ ቀረው። በጣም
ተንጠራራ። እጇን ልታስይዘው አብዛኛው ሚዛኗን በገደሉ አፋፍ ላይ ወጥራ በሃይል ተንጠራራች። ጣቶቻቸው ሊነካኩ የስንዝር ያክል ልዩነት ብቻ ነበር የቀራቸው። በዚሁ መሀል ግን ከየት መጣ ሳይባል አንድ ትልቅ ጭልፊት አሞራ ይመጣና ፊቷን በጥፊ ይላታል። ደንግጣ አሞራውን ለማየት ቀና ስትል ጌትነት የተንጠለጠለበት ሀረግ ቷ!! ብሎ ከመስረቱ ተነቀለና ቁልቁል እየተምዘገዘገ ይዞት ሲወርድ አየች።
ገደሉ ርቀት ነበረው። ጌትነት ጥረቱ ሳይሳካለት ቀረና ሄዶ በአናቱ ተደፋ። ጭንቅላቱ ያረፈው አለት ድንጋይ ላይ ነበር፡፡ በጀርባው እንደተዘረረ ደሙ እንደ ምንጭ ውሃ ቡልቅ! ሲል እናቱ ተመለከተች፡፡
“ወይኔ..ልጄን!እኔ ልደፋ!” ባለ በሌለ ሀይሏ ወደ ገደሉ ራሷን ወረወረች... ከእንቅልፏ እየተወራጨች የባነነችው በዚህ አስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ እያለች ነበር፡፡ በዚህ እጅግ አሰቃቂ በሆነ ህልሟ ምክንያት ሰውነቷ ይንዘፈዘፍ፣ ወባ እንደተነሳበት ስው ይንቀጠቀጥ ጀመር፡፡
እውን... እውን መሰላት። ከአልጋዋ ላይ ተነሳችና መንታ መንታውን
አወረደችው። ስቅስቅ ብላ አለቀሰች፡፡ ማልቀስ ካቆመች ረጅም ጊዜ ሆኗት ነበር፡፡ የተጠራቀመ እምባዋን እንደ ጐርፍ ለቀቀችው
"ወይኔ ጉዴ?! ወይኔ ልጆቼ?! ምን ዓይነት ህልም ነው? የኔ ደም
ክንብል ይበል። ዛሬ ፈጣሪዬ ምኑን አሳየኽኝ? ደግሞ የምን ጭልፊት
ነው? ዐይኔን ሊያጠፋው ነበረኮ! እስቲ አንተ ታውቃለህ? " ከዚህ አሰቃቂ ህልሟ በኋላ መንፈሷ በፍፁም አልረጋጋ አላት። ጭንቀቱ እረፍት ነሳትና ዳቦ ቆሎ መቁረጥ ጀመረች። በሌላ ጊዜ ደግሞ ትልቅ እባብ ሲያባርረው አየች። ይሄንን ግን ለወይዘሮ ተዋበች አልደበቀቻቸውም፡፡
“ምቀኛ ነው! ምቀኛ! ለመሆኑ ነደፈው?" ብለው ጠየቋት።
የለም! የለም! አልነደፈውም ብቻ ሲያባርረው ሮጦ አመለጠው'
ባለመነደፉ ነው ህልሟን የተናገረችው እንጂ ነድፎት ቢሆን ኖሮ አትነግራቸውም ነበር፡፡
“ጐሽ!...ጎሽ! እባብ ምቀኛ ነው። ምቀኞቹን ሁሉ ድል አድርጓል ማለት ነው፡፡ ቢነድፈው ኖሮ ጥሩ አልነበረም፡፡ ካመለጠው እንኳ ከጠላት፣ ከምቀኛ ተንኮል አምልጧል ማለት ነው፡፡ ማለፊያ ህልም ነው ያየሽለት!”
ሲሉ አጽናኗት። የወላድ አንጀት፣ የልብ ፍቅር እውነትም አንዳንድ ጊዜ ሹክ የሚለው መንፈስ አለ፡፡ ጌትነት የዚያን አይነት አሳዛኝ አደጋ ሊደርስበት ሳምንት ሲቀረው ጀምሮ በሃሣብና በጭንቀት ተወጥራ እየተብሰለሰላች በሆነ ባልሆነው ልቧ ድንግጥ ድንግጥ እያለባት እንቅልፍ እንቢ እያላት
እያቃዣት ሰውነቷ መጨማደድ ጀመረና በጥቂት ቀናት ውስጥ
ተለወጠች፡፡ ለተመልካች ግራ እስከሚገባው ድረስ በአንድ ጊዜ ቆረቆዘች።ጉዷን ያላወቀች እናት። በሷ ቤት የሳምንት ተጓዥ መንገደኛ ናት።የስንቅ ጣጣዋን ጨርሳ ወደ ልጅዋ ለመሄድ ዝግጅቷን በማጠናቀቅ ላይ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...ሰሞኑን ያየችው ህልም ክፉኛ ያስደነገጣት እናት አመዱን ይነሰንስባት ጀምሯል። የወትሮ ህልሟ ተስፋን የሚያበስር መሆኑን ስለምታውቅ ፊቷ እንደ ፀሀይ እያበራ በደስታ መንፈስ ለቡና ማህበረተኞቿ ታወራላቸው ነበር፡፡ ከማህበርተኞቿ ውስጥ ደግሞ በህልም ፈቺነታቸው ወይዘሮ
ተዋበችን የሚደርስባቸው የለም፡፡ ህልም ሲፈቱ እንከን አይወጣላቸውም ተብሎ በአብዛኛው ነዋሪ ስለሚታመንባቸው ህልም ለመፍታት ኩራታቸው አይጣል ነው። ትንሽ ካላስለመኑ ህልም አይፈቱም፡፡ ከልመና በኋላ ግን መተንተን ይጀምራሉ፡፡
ሲሳይ ነው! ዓለም ነው!አቤት ደስታ! ልጅ ልትወልጂ ነው...ስለትሽ ሊደርስ ነው፣ በዚህ ሊገባ በዚህ ሊወጣ ነው፡፡ የተጣላው ሊታረቅ፣ የደለው ሊሞላ.. ብቻ ጥሩ ጥሩውን ሁሉ ልታገኙ ነው እያሉ አላሚውን
ተስፋ በተስፋ ያደርጉታል፡፡ ከሁሉ የበለጠ የህልም ደንበኛቸው ግን
አስካለ ነበረች። ያየችውን ህልም ስትነግራቸው ሁሌም የሚያያይዙት ከልጆቿ ጋር ነው፡፡
አቤት! አቤት! በውነት ህልም አይደለም ያየሽለት ራዕይ ነው፡፡ ጉድ! ደሞዙ ከፍ ሥልጣኑም ከፍ ሊል ነው፡፡ ጥሩ ደረጃ ላይ ሊደርስልሽ ነው! ትንሿም ደስ ብሏታል ያንቺ ናፍቆት አለባት መሰለኝ እዚህ ጋ ትንሽ ቅር
እንዳላት አያለሁ፡፡ ይሁን ግድ የለም ትምህርት ቤት ሲዘጋ ትመጣለች።
ጥሩ ህልም ነው ይሏታል የቡናው አሻራ ያረፈበትን ባዶ ስኒ ዘቅዝቀው እየተመለከቱ፡፡ ከዚያም አስካለ በደስታ መፈንደቅ ነው። በዚህ ሁሉ ቆንጆ ቆንጆ ህልሞቿ ጣልቃ ስሞኑን ያየችው መጥፎ ህልም ግን ክፉኛ አስደንግጧታል
ለማንም ሳትናገር ፍርሃትና ሃሣብ ውስጥ ውስጡን ሲያካት ቆይቶ በትንሽ ጊዜ ውስጥ ወዛም ነበረ ፊቷ ላይ አመዱን ይነዛበት ገባ።
"ተነሳብሽ ደግሞ አንቺ ሴት! ለመሆኑ ሄደሽ ከመጣሽ ሁለት ወር እንኳ ይሞላዋል እንዴ? ናፈቁኝ ነው ወይስ ምን አዲስ ነገር ተገኘና ነው እንዴዚህ ነጭ እስከምትሆኚ ድረስ ራስሽን መጣል ያመጣሽው?” ለመሽፋፈን ጥረት ብታደርግም ሃሳብ እየወዘወዛት መሆኑ የገባቸው ወይዘሮ ተዋቡ ተቆጡ።አስካለ የመጀመሪያ መጥፎ ህልሟን አይታ መረበሽ ከጀመረች
በኋላ ጭንቀቱ ነው መሰል በላይ በላዩ የሚያስፈራራ ህልም እየደጋገመ አስቸገራት። የአሁኑ ደግሞ ፍፁም የተለየ ሆነባት።
ጌትነት ይመስላታል፡፡ እንደ ልጅነቱ አብሯት እንጨት ለቀማ ይሄዳሉ።
ከአንዱ ዛፍ ወደ ሌላው ዛፍ እየዘለለ ጥሩ ጥሩውን እንጨት እየሰበረ ኢያቀበላት የቆመበት ቅርንጫፍ ተገንጥሎ መሬት ላይ ይወድቃል። ከዚያም
ይንከባለላል. በዚያው እንደ ሙቀጫ ጅው ብሎ ተንከባሎ ቁልቁል ይወርዳል። ለካስ ከስሩ ገደል ነበር፡፡ ከታች ገደል መኖሩን፣ ልጅዋ አደጋ ላይ መውደቁን ያየች እናት ኡኡ! ልጄን! ልጄን!.. ልጄን! እየጮኸች አብራው ልትገባ ወደ እሱ ትሮጣለች። ጌትነት ገደሉ ውስጥ ተወርውሮ ከመግባት ለትንሽ የተረፈው የሆነ ቁጥቋጦ ነገር እጁ ውስጥ ስለገባ ነበር፡፡
ከዚያም እናቱ ጉዳት ላይ እንዳትወድቅበት ውትወታውን ይቀጥላል።
“እማዬ! እማዬ!ደህና ነኝ! ምንም አልሆንኩም! እዚያው ቁሚ! መጣሁ! መጣሁ! መጣሁ!" ወደሱ ስትሮጥ ወድቃ እንዳትሰበር ፈርቶ ይጮሀል። እሷ ደግሞ አሻፈረኝ ብላ ወደ ገደሉ እየሮጠች ትመጣና ገደሉ ጫፍ ላይ
ሆና “ጌትዬ! ተረፍክ የኔ ጌታ?!” ቁልቁል እያየችው ትጠይቀዋለች::
"ተርፌአለሁ! ተርፌአለሁ!አይዞሽ! ምንም አልሆንኩም በቃ እዚያው ጋ ሁኚ!" ይላትና በአንድ ትልቅ ቋጥኝ ላይ ተጋድሞ በተንጠለጠለ ወፍራም
ሀረግ አማካኝነት እየተሳበ ሽቅብ መውጣት ጀመረ። ወጣ ወጣ...
ወጣና አጠገቧ ሊደርስ ትንሽ ቀረው። ደክሞታል። አልቦታል። ..
“አይዞህ ጌትዬ በርታ የኔ ልጅ... ቆይ እጅህን ልያዝልህ" ጐንበስ
ትላለች።
“ተይ !ተይ! እማዬ ተይ! እንዳያንሸራትትሽ !እኔ ቀስ እያልኩ እወጣ ለሁ ተይ!!"
“ግዴለህም ይልቁንስ እጅህን አቀብለኝ" ትለውና ሄዳ ከገደሉ ጫፍ ላይ ተንጠልጥላ የቀኝ እጇን ትልክለታለች። አልደርስብሽ ይላታል። እንደገና ብሃይል ወደሱ ተንጠራርታ እጇን ልትስጠው ጐንበስ ትላለች። በግራ እጅዋ አንድ ትልቅ ጉቶ ይዛ ነበር፡፡ አሁንም አልደርስብሽ ይላታል።
ጭንቅቱ አስጨንቋት ቶሎ ልታወጣው ቸኩላለች። እሱም አወጣዋለሁ ብላ ስትፍጨረጨር ጉዳት ላይ እንዳትወድቅ ፈርቶ እጅዋን ቶሎ ለመያዝ ይንደፋደፋል። ተቃረበ ። ሊይዛት ትንሽ ብቻ ቀረው። በጣም
ተንጠራራ። እጇን ልታስይዘው አብዛኛው ሚዛኗን በገደሉ አፋፍ ላይ ወጥራ በሃይል ተንጠራራች። ጣቶቻቸው ሊነካኩ የስንዝር ያክል ልዩነት ብቻ ነበር የቀራቸው። በዚሁ መሀል ግን ከየት መጣ ሳይባል አንድ ትልቅ ጭልፊት አሞራ ይመጣና ፊቷን በጥፊ ይላታል። ደንግጣ አሞራውን ለማየት ቀና ስትል ጌትነት የተንጠለጠለበት ሀረግ ቷ!! ብሎ ከመስረቱ ተነቀለና ቁልቁል እየተምዘገዘገ ይዞት ሲወርድ አየች።
ገደሉ ርቀት ነበረው። ጌትነት ጥረቱ ሳይሳካለት ቀረና ሄዶ በአናቱ ተደፋ። ጭንቅላቱ ያረፈው አለት ድንጋይ ላይ ነበር፡፡ በጀርባው እንደተዘረረ ደሙ እንደ ምንጭ ውሃ ቡልቅ! ሲል እናቱ ተመለከተች፡፡
“ወይኔ..ልጄን!እኔ ልደፋ!” ባለ በሌለ ሀይሏ ወደ ገደሉ ራሷን ወረወረች... ከእንቅልፏ እየተወራጨች የባነነችው በዚህ አስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ እያለች ነበር፡፡ በዚህ እጅግ አሰቃቂ በሆነ ህልሟ ምክንያት ሰውነቷ ይንዘፈዘፍ፣ ወባ እንደተነሳበት ስው ይንቀጠቀጥ ጀመር፡፡
እውን... እውን መሰላት። ከአልጋዋ ላይ ተነሳችና መንታ መንታውን
አወረደችው። ስቅስቅ ብላ አለቀሰች፡፡ ማልቀስ ካቆመች ረጅም ጊዜ ሆኗት ነበር፡፡ የተጠራቀመ እምባዋን እንደ ጐርፍ ለቀቀችው
"ወይኔ ጉዴ?! ወይኔ ልጆቼ?! ምን ዓይነት ህልም ነው? የኔ ደም
ክንብል ይበል። ዛሬ ፈጣሪዬ ምኑን አሳየኽኝ? ደግሞ የምን ጭልፊት
ነው? ዐይኔን ሊያጠፋው ነበረኮ! እስቲ አንተ ታውቃለህ? " ከዚህ አሰቃቂ ህልሟ በኋላ መንፈሷ በፍፁም አልረጋጋ አላት። ጭንቀቱ እረፍት ነሳትና ዳቦ ቆሎ መቁረጥ ጀመረች። በሌላ ጊዜ ደግሞ ትልቅ እባብ ሲያባርረው አየች። ይሄንን ግን ለወይዘሮ ተዋበች አልደበቀቻቸውም፡፡
“ምቀኛ ነው! ምቀኛ! ለመሆኑ ነደፈው?" ብለው ጠየቋት።
የለም! የለም! አልነደፈውም ብቻ ሲያባርረው ሮጦ አመለጠው'
ባለመነደፉ ነው ህልሟን የተናገረችው እንጂ ነድፎት ቢሆን ኖሮ አትነግራቸውም ነበር፡፡
“ጐሽ!...ጎሽ! እባብ ምቀኛ ነው። ምቀኞቹን ሁሉ ድል አድርጓል ማለት ነው፡፡ ቢነድፈው ኖሮ ጥሩ አልነበረም፡፡ ካመለጠው እንኳ ከጠላት፣ ከምቀኛ ተንኮል አምልጧል ማለት ነው፡፡ ማለፊያ ህልም ነው ያየሽለት!”
ሲሉ አጽናኗት። የወላድ አንጀት፣ የልብ ፍቅር እውነትም አንዳንድ ጊዜ ሹክ የሚለው መንፈስ አለ፡፡ ጌትነት የዚያን አይነት አሳዛኝ አደጋ ሊደርስበት ሳምንት ሲቀረው ጀምሮ በሃሣብና በጭንቀት ተወጥራ እየተብሰለሰላች በሆነ ባልሆነው ልቧ ድንግጥ ድንግጥ እያለባት እንቅልፍ እንቢ እያላት
እያቃዣት ሰውነቷ መጨማደድ ጀመረና በጥቂት ቀናት ውስጥ
ተለወጠች፡፡ ለተመልካች ግራ እስከሚገባው ድረስ በአንድ ጊዜ ቆረቆዘች።ጉዷን ያላወቀች እናት። በሷ ቤት የሳምንት ተጓዥ መንገደኛ ናት።የስንቅ ጣጣዋን ጨርሳ ወደ ልጅዋ ለመሄድ ዝግጅቷን በማጠናቀቅ ላይ
👍2
#ያልታበሱ_እንባዎች
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
....በድሉ ከመደንገጡ የተነሳ በዓይኑ መግቢያ ቀዳዳ የሚፈልግ ይመስል ወደ ላይ ወደ ታች፣ ወደ ቀኝ ወደ ግራ ዓይኑን እያማተረ ይቁነጥነጥ ጀመር።
«በምን ተገናኝታችሁ ነው ያስደበደበችህ?
«እወዳታለሁ!»
«ለምን ወደድከኝ ብላ አስደበደበችህ?»
«መሰለኝ::»
«ስለዚህ ልትበቀላት ፈለክ?»
«የራሷ እህት ናት የገፋፋችኝና መላውን የፈጠረችልኝ::»
«ስሟን ጥራታ!»
«ሸዋዬ::» አለና በድሉ እነዚያን ገጣጣ ጥርሶቹን የባስ ግጥጥ አደረጋቸው፡፡
ላብ ላብ ብሎት ጭንቀቱ ይታወቅበታል።.
“ 'ተደበደበ ሰው ቢደበድብ ወይም ቢያስደበድብ ድርጊቱ ወንጀል ቢሆንም ነገር ግን ስም አለው:: «ግን ወንድ አደባደበች» ብሎ ማስወራቱ ምንድንነው
ዓላማው? ሲል ጠየቀው፡፡
«ስሟን ለማጥፋት::»
«ማለት?»
«ልጅቷ አስመራ ሄዶ የቀረ እጮኛ' አላት፡፡»
«እሺ»
«እዚህ ያሉት ጓደኞቿ ግን ከማንም ጋር እንዳትገናኝ ይጠብቋታል፡፡
እሷም ትፈራቸዋለች። ወንድ አደባደበች ተብሎ ከተወራባት ግን እነሱ ያርቋታል፡፡እሷም ተስፋ ትቆርጥና የኔን ጥያቄ ትቀበላለች ብዬ በማሰብ ነው፡፡» አለና በድሉ
በተቀመጠበት ላይ ተቁነጠነጠ፡፡
«ስማ » አለው የሃምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ቁጣ በተቀላቀለበት አነጋገር።
«አቤት»
«እዚሁ እንዳለህ የሴራ መሀንዲስህን አስጠራታለሁ፡፡ እጥር ምጥን ባለ ቃል
ሁሉን ነገር እንደተናገርንክ ትነግራታለህ። ነገር አደፋፍናለሁ ካልክ ጠብክ ከመንግስት ጋር ብቻ ሳይሆን ከእኔም ጋር በግል እንደሚሆን እወቅ!!»
«ኧረ እነግራታለሁ!»።
ሃምሳ አለቃ ረዳቱን በደውል ጠራና እንደቀረበለት ሽዋዬን እንዲያመጣ አዘዘው። ረዳቱ ሸዋዬን ወዲያው አቀረባት። በበድሉ ፊትለፊት
እንድትቀመጥ ታዝዛ አለፍ ብላ ተቀመጠች፡፡ ከመርማሪው ፖሊስ ይልቅ በድሉን በፍርሀት ዓይን ታየው ጀመር።
«ቀጥላ!» አለ ሃምሣ አለቃው በድሉ ላይ በማፍጠጥ::
በድሉ ከተቀመጠበት ብድግ አለና ወደ ሽዋዬ ጣቱን ቀስሮ «የቀይ ሽብሩን ጉዳይ ሙልጭ አድርጌ ተናግሬያለሁ፡፡ ብትዋሽ ውርድ ከራሴ!» አላትና ተመልሶ ቁጭ አለ። የሃምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ቀይ ሽብር የሚለውን ቃል ሲሰማ መላ ሰውነቱን አንቀጠቀጠው፡፡ አጠገቡ ያሉት ሰዎች ነፍሰ ገዳዮች መስለው ታዩት። ልክ በቀይ ሽብር ጊዜ እንደተፈጸመው ሁሉ እሱም እነዚህን ሰዎች ዘቅዝቆ ቢለበልባቸው ደስ ባለው ነበር። ግን ደሞ ጨካኞች የፈፀሙትን የጭካኔ ተግባር መድገም የባስ አረመኔነት መሆኑን ይገነዘባልና በቁጭት ራሱን ወዝውዞ ተወው።
ወድያው ረዳቱን በደውል ጠራ። በድሉን ወደ እስር ቤት አስወሰደና ሸዋዬን ብቻዋን አገኛት።
ሽዋዬ በዕለቱ አጠር ያለ ሰማያዊ ጉርድ ቀሚስና ቡናማ ሹራብ ለብሳለች፡፡
ቀላ ያለች ስካርፍ አንገቷ ላይ ጣል አድርጋለች:: ሳታስበው ታስራ በማደሯ ፀጉሯ አላበጠረቾም፣ አልተቀባባችም:: አመዷ ወጥቷል፡፡ ማንደፍሮ ሜዳ ላይ የደፈጠጠው ፊቷ ጠባሳው አልጠፋም፡፡ ተዥጎርጉራለች። ያ አጭር ፀጉሯ ተንጨፍሯል፡፡
ቀጫጭን እግርቿን ስታክካቸው አድራ መስመር ሰርተዋል። በድንጋጤ ዓይኗ ፍጥጥ ብሎ የሴትነት ጥላዋ ተገፏል። ታስጠላለች::
«መምሀርት ሸዋዬ!» ሲል ጠራት የሀምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ሁለት እጆቹ ላይ አገጩን አስደግፎ ዘንበል ብሎ እየተመለከታት፡፡
«አቤት!»
«ሙያሽን ምን ያህል ትወጅዋለሽ?»
«በጣም እወደዋለሁ፣ አከብረዋለሁ፣ ተማሪዎቼም በጣም ይወዱኛል::»
«ምን እያስተማርሻቸው እንደሆነ ስለሚገባቸው ይሆናላ!» አላት በምፀት።
«ትንትን ብትንትን አድርጌ ነው የማስተምራቸው»
የሃምሳ አለቃው በረጅሙ ተነፈሰና ወደ ጠረጴዛው ጎንበስ አለ።
ራሱን ወዝወዝ አድርጎ ብዕርና ወረቀቱን ከአመቻቸ በኋላ «እስቲ እኔም እንደተማሪዎችሽ እንድወድሽ ስለ ቀይ ሽብሩ ጉዳይ ትንትን ብትንትን አድርጎአል ንገሪኝ፡፡» አላት።
ሽዋዬ የደረቀ ከንፈሯን በምላሷ እያራሰች ወደ ላይ ወደ ታች በማየት ከተቅበጠበጠች በኋላ «ቀይ ሽብሩኮ» ብላ ልትጀምር ስትል እንደገና ወደ ሃምሳ አለቃው
ዞር ብላ «በድሉ ነግሮህ የለ?»
አለችው።
ሀምሳ አለቃው በሸዋዩ አስተሳሰብ እንደ መገረም ብሎ ድንገት ፈገግ እንደ ማለት አለና እሱ ብቻ ሳይሆን ዓለሙም መብራቴም በሰፊው ዘርዝረውታል ግን መጀመርያ ሀሳቡን ያፈለቅሽው አንቺ ስለሆንሽ ከባለቤቷ መስማት ፈልጌ ነው::
እግረ መንገዴን ምን ያህል እውነተኛ እንደሆነሽ ለማወቅ ፈልጌ ነው፡፡» ብሎ አየት ሲያደርጋት ሸዋዬ ቀጠለች።
«እኔ እኮ ውሽት አላቅም!» አለችው ቀበጥበጥ እያለች
«እኔስ መች ወጣኝ? በይ እውነቱን ንገሪኝ።»
«ቀይ ሽብር ማለት ያው ቀይ ሽብር ማለት ነው አለችው አይኖቿን በዓይኖቹ ላይ እያንከባለለች።
«ነገርኩሽ አንቺ ሴትዮ አላት ተናዶ፡፡ ምኗ ደነዝ ናት በሆዱ።
«ምን ልበል ታዲያ?» ሽዋዬ ድንግጥ አለች። ተጨነቀችም።
«ዝርዝር ሂደቱን ንገሪኝ ነው ያልኩሽ አለና «ቀይ ሽብርስ ምን አስፈለ»
«ሔዋን አስቸገረችኝ::»
«ምን አድርጊኝ ብላ?
«በቃ! እሷ እያለች ባልም ትዳርም ሌኖረኝ አልቻሉም፡፡»
«ነጠቀችሽ ወይስ አፋታችሽ?»
«ሁለቱንም።»
«እንዴት እያረገች?»
«መጀመሪያ በልቤ የወደድኩትን ሰው ውስጥ ለውስጥ ሄዳ በጎን
ጠለፈችብኝ፡፡» እንደገና ብላ ልትቀጥል ስትል ሃምሣ አለቃ ቀደማት።
«የነጠቀችሽ ሰው ማን ይባላል?»
«አስቻለው ፍሰህ ይባል ነበር፡፡»
«እንዴ!» አለ ሃምሣ አለቃ በመገረምም በመደነቅም ዓይነት ትኩር ብሎ ሸዋዬን ሲመለከታት ከቆየ በኋሳ አስቻለውን ትወጂው ነበር?» ሲል ጠየቃት፡፡
«ነፍሴ እስክትወጣ!»
ሃምሣ አለቃ ግራ ገባው፡፡ ልክ ሔዋንን ያነጋገረ ዕለት እንደሆነው ሁሉ እስኪርብቶውን ወረቀት ላይ ጣል አደረገና ጉንጮቹን ደግፎ ወደ ጠረጴዛው አቀረቀረ፡፡ በዚያው ሀሳብ ውስጥ እንዳለ ሸዋዬ በልቤ የወደድኩትን… ያለችውን አስታወሰና ቅናት ከአጎመነበሰበ ቀና በማለት
«እሺ፣ ደግሞ ከማን አፋታችሽ?» ሲል ጠየቃት።
««ያን እንኳ ባናወራው ይሻላል::»
«ለምን?»
«ደስ አይልማ!»
«ሀምሣ አለቃ የሸዋዬ ባዶነት አስገረመውና አሁንም ጎንበስ ብሎ እንደ መሳቅ አለና። እንደገና ቀና ብሎ “ታዲያ ለኔ የሚያስደስተኝ ደስ የማይለውን ነገር ማወቅ መሆኑን አጣሽው? ወይስ ፖለስ ጣቢያ ውስጥ መሆንሽን ረሳሽው አለና ወረቀቶች ብድግ አድርጎ «ታሪክሽ ሁሉ እኮ እዚህ ላይ ተዘርዝሯል መደበቁ ያዋጣሽ መሰለሽ?» አላት። በእርግጥ ስለ ፍቺ ነገር የተጠቀሰ ነገር አልነበረም፡፡ ነገር ግን ሸዋዬን ለማስፈራራትና ለማስወትወት ተጠቀመበት፡፡
«ሰዎቹ ያንንም አውታዋል? »አለች ሽዋዬ ደንግጣ ብላ፡፡
«በእነሱ ላይ ጨምሮ ቀድሉ አጋልጦሻል::»
«ቅሌታም ነው።»
የሀሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ ድንገት ቂቂቂቂቂ...» ብሎ ሳቀ፡፡ ሸዋዬ ፊደል ከመቁጠሯ በቀር
ምንም እንዳልተማረች ታስበው፡፡፦ እውቀት" ሥርዓትም አጣባት።
በዚያ ምትክ የክፋትና የተንኮል ሰው መሆኗን በውል ተገነዘበና
«ጊዜዬን እትግደያ መምህርት ሸዋዬ!» ሲል ቆጣ ብሎ ተናገራት፡፡ በዚያኑ ልክ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
....በድሉ ከመደንገጡ የተነሳ በዓይኑ መግቢያ ቀዳዳ የሚፈልግ ይመስል ወደ ላይ ወደ ታች፣ ወደ ቀኝ ወደ ግራ ዓይኑን እያማተረ ይቁነጥነጥ ጀመር።
«በምን ተገናኝታችሁ ነው ያስደበደበችህ?
«እወዳታለሁ!»
«ለምን ወደድከኝ ብላ አስደበደበችህ?»
«መሰለኝ::»
«ስለዚህ ልትበቀላት ፈለክ?»
«የራሷ እህት ናት የገፋፋችኝና መላውን የፈጠረችልኝ::»
«ስሟን ጥራታ!»
«ሸዋዬ::» አለና በድሉ እነዚያን ገጣጣ ጥርሶቹን የባስ ግጥጥ አደረጋቸው፡፡
ላብ ላብ ብሎት ጭንቀቱ ይታወቅበታል።.
“ 'ተደበደበ ሰው ቢደበድብ ወይም ቢያስደበድብ ድርጊቱ ወንጀል ቢሆንም ነገር ግን ስም አለው:: «ግን ወንድ አደባደበች» ብሎ ማስወራቱ ምንድንነው
ዓላማው? ሲል ጠየቀው፡፡
«ስሟን ለማጥፋት::»
«ማለት?»
«ልጅቷ አስመራ ሄዶ የቀረ እጮኛ' አላት፡፡»
«እሺ»
«እዚህ ያሉት ጓደኞቿ ግን ከማንም ጋር እንዳትገናኝ ይጠብቋታል፡፡
እሷም ትፈራቸዋለች። ወንድ አደባደበች ተብሎ ከተወራባት ግን እነሱ ያርቋታል፡፡እሷም ተስፋ ትቆርጥና የኔን ጥያቄ ትቀበላለች ብዬ በማሰብ ነው፡፡» አለና በድሉ
በተቀመጠበት ላይ ተቁነጠነጠ፡፡
«ስማ » አለው የሃምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ቁጣ በተቀላቀለበት አነጋገር።
«አቤት»
«እዚሁ እንዳለህ የሴራ መሀንዲስህን አስጠራታለሁ፡፡ እጥር ምጥን ባለ ቃል
ሁሉን ነገር እንደተናገርንክ ትነግራታለህ። ነገር አደፋፍናለሁ ካልክ ጠብክ ከመንግስት ጋር ብቻ ሳይሆን ከእኔም ጋር በግል እንደሚሆን እወቅ!!»
«ኧረ እነግራታለሁ!»።
ሃምሳ አለቃ ረዳቱን በደውል ጠራና እንደቀረበለት ሽዋዬን እንዲያመጣ አዘዘው። ረዳቱ ሸዋዬን ወዲያው አቀረባት። በበድሉ ፊትለፊት
እንድትቀመጥ ታዝዛ አለፍ ብላ ተቀመጠች፡፡ ከመርማሪው ፖሊስ ይልቅ በድሉን በፍርሀት ዓይን ታየው ጀመር።
«ቀጥላ!» አለ ሃምሣ አለቃው በድሉ ላይ በማፍጠጥ::
በድሉ ከተቀመጠበት ብድግ አለና ወደ ሽዋዬ ጣቱን ቀስሮ «የቀይ ሽብሩን ጉዳይ ሙልጭ አድርጌ ተናግሬያለሁ፡፡ ብትዋሽ ውርድ ከራሴ!» አላትና ተመልሶ ቁጭ አለ። የሃምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ቀይ ሽብር የሚለውን ቃል ሲሰማ መላ ሰውነቱን አንቀጠቀጠው፡፡ አጠገቡ ያሉት ሰዎች ነፍሰ ገዳዮች መስለው ታዩት። ልክ በቀይ ሽብር ጊዜ እንደተፈጸመው ሁሉ እሱም እነዚህን ሰዎች ዘቅዝቆ ቢለበልባቸው ደስ ባለው ነበር። ግን ደሞ ጨካኞች የፈፀሙትን የጭካኔ ተግባር መድገም የባስ አረመኔነት መሆኑን ይገነዘባልና በቁጭት ራሱን ወዝውዞ ተወው።
ወድያው ረዳቱን በደውል ጠራ። በድሉን ወደ እስር ቤት አስወሰደና ሸዋዬን ብቻዋን አገኛት።
ሽዋዬ በዕለቱ አጠር ያለ ሰማያዊ ጉርድ ቀሚስና ቡናማ ሹራብ ለብሳለች፡፡
ቀላ ያለች ስካርፍ አንገቷ ላይ ጣል አድርጋለች:: ሳታስበው ታስራ በማደሯ ፀጉሯ አላበጠረቾም፣ አልተቀባባችም:: አመዷ ወጥቷል፡፡ ማንደፍሮ ሜዳ ላይ የደፈጠጠው ፊቷ ጠባሳው አልጠፋም፡፡ ተዥጎርጉራለች። ያ አጭር ፀጉሯ ተንጨፍሯል፡፡
ቀጫጭን እግርቿን ስታክካቸው አድራ መስመር ሰርተዋል። በድንጋጤ ዓይኗ ፍጥጥ ብሎ የሴትነት ጥላዋ ተገፏል። ታስጠላለች::
«መምሀርት ሸዋዬ!» ሲል ጠራት የሀምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ሁለት እጆቹ ላይ አገጩን አስደግፎ ዘንበል ብሎ እየተመለከታት፡፡
«አቤት!»
«ሙያሽን ምን ያህል ትወጅዋለሽ?»
«በጣም እወደዋለሁ፣ አከብረዋለሁ፣ ተማሪዎቼም በጣም ይወዱኛል::»
«ምን እያስተማርሻቸው እንደሆነ ስለሚገባቸው ይሆናላ!» አላት በምፀት።
«ትንትን ብትንትን አድርጌ ነው የማስተምራቸው»
የሃምሳ አለቃው በረጅሙ ተነፈሰና ወደ ጠረጴዛው ጎንበስ አለ።
ራሱን ወዝወዝ አድርጎ ብዕርና ወረቀቱን ከአመቻቸ በኋላ «እስቲ እኔም እንደተማሪዎችሽ እንድወድሽ ስለ ቀይ ሽብሩ ጉዳይ ትንትን ብትንትን አድርጎአል ንገሪኝ፡፡» አላት።
ሽዋዬ የደረቀ ከንፈሯን በምላሷ እያራሰች ወደ ላይ ወደ ታች በማየት ከተቅበጠበጠች በኋላ «ቀይ ሽብሩኮ» ብላ ልትጀምር ስትል እንደገና ወደ ሃምሳ አለቃው
ዞር ብላ «በድሉ ነግሮህ የለ?»
አለችው።
ሀምሳ አለቃው በሸዋዩ አስተሳሰብ እንደ መገረም ብሎ ድንገት ፈገግ እንደ ማለት አለና እሱ ብቻ ሳይሆን ዓለሙም መብራቴም በሰፊው ዘርዝረውታል ግን መጀመርያ ሀሳቡን ያፈለቅሽው አንቺ ስለሆንሽ ከባለቤቷ መስማት ፈልጌ ነው::
እግረ መንገዴን ምን ያህል እውነተኛ እንደሆነሽ ለማወቅ ፈልጌ ነው፡፡» ብሎ አየት ሲያደርጋት ሸዋዬ ቀጠለች።
«እኔ እኮ ውሽት አላቅም!» አለችው ቀበጥበጥ እያለች
«እኔስ መች ወጣኝ? በይ እውነቱን ንገሪኝ።»
«ቀይ ሽብር ማለት ያው ቀይ ሽብር ማለት ነው አለችው አይኖቿን በዓይኖቹ ላይ እያንከባለለች።
«ነገርኩሽ አንቺ ሴትዮ አላት ተናዶ፡፡ ምኗ ደነዝ ናት በሆዱ።
«ምን ልበል ታዲያ?» ሽዋዬ ድንግጥ አለች። ተጨነቀችም።
«ዝርዝር ሂደቱን ንገሪኝ ነው ያልኩሽ አለና «ቀይ ሽብርስ ምን አስፈለ»
«ሔዋን አስቸገረችኝ::»
«ምን አድርጊኝ ብላ?
«በቃ! እሷ እያለች ባልም ትዳርም ሌኖረኝ አልቻሉም፡፡»
«ነጠቀችሽ ወይስ አፋታችሽ?»
«ሁለቱንም።»
«እንዴት እያረገች?»
«መጀመሪያ በልቤ የወደድኩትን ሰው ውስጥ ለውስጥ ሄዳ በጎን
ጠለፈችብኝ፡፡» እንደገና ብላ ልትቀጥል ስትል ሃምሣ አለቃ ቀደማት።
«የነጠቀችሽ ሰው ማን ይባላል?»
«አስቻለው ፍሰህ ይባል ነበር፡፡»
«እንዴ!» አለ ሃምሣ አለቃ በመገረምም በመደነቅም ዓይነት ትኩር ብሎ ሸዋዬን ሲመለከታት ከቆየ በኋሳ አስቻለውን ትወጂው ነበር?» ሲል ጠየቃት፡፡
«ነፍሴ እስክትወጣ!»
ሃምሣ አለቃ ግራ ገባው፡፡ ልክ ሔዋንን ያነጋገረ ዕለት እንደሆነው ሁሉ እስኪርብቶውን ወረቀት ላይ ጣል አደረገና ጉንጮቹን ደግፎ ወደ ጠረጴዛው አቀረቀረ፡፡ በዚያው ሀሳብ ውስጥ እንዳለ ሸዋዬ በልቤ የወደድኩትን… ያለችውን አስታወሰና ቅናት ከአጎመነበሰበ ቀና በማለት
«እሺ፣ ደግሞ ከማን አፋታችሽ?» ሲል ጠየቃት።
««ያን እንኳ ባናወራው ይሻላል::»
«ለምን?»
«ደስ አይልማ!»
«ሀምሣ አለቃ የሸዋዬ ባዶነት አስገረመውና አሁንም ጎንበስ ብሎ እንደ መሳቅ አለና። እንደገና ቀና ብሎ “ታዲያ ለኔ የሚያስደስተኝ ደስ የማይለውን ነገር ማወቅ መሆኑን አጣሽው? ወይስ ፖለስ ጣቢያ ውስጥ መሆንሽን ረሳሽው አለና ወረቀቶች ብድግ አድርጎ «ታሪክሽ ሁሉ እኮ እዚህ ላይ ተዘርዝሯል መደበቁ ያዋጣሽ መሰለሽ?» አላት። በእርግጥ ስለ ፍቺ ነገር የተጠቀሰ ነገር አልነበረም፡፡ ነገር ግን ሸዋዬን ለማስፈራራትና ለማስወትወት ተጠቀመበት፡፡
«ሰዎቹ ያንንም አውታዋል? »አለች ሽዋዬ ደንግጣ ብላ፡፡
«በእነሱ ላይ ጨምሮ ቀድሉ አጋልጦሻል::»
«ቅሌታም ነው።»
የሀሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ ድንገት ቂቂቂቂቂ...» ብሎ ሳቀ፡፡ ሸዋዬ ፊደል ከመቁጠሯ በቀር
ምንም እንዳልተማረች ታስበው፡፡፦ እውቀት" ሥርዓትም አጣባት።
በዚያ ምትክ የክፋትና የተንኮል ሰው መሆኗን በውል ተገነዘበና
«ጊዜዬን እትግደያ መምህርት ሸዋዬ!» ሲል ቆጣ ብሎ ተናገራት፡፡ በዚያኑ ልክ
👍15🥰1😁1
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...«ዣቬር ይህ ሁሉ ሲሆን ድምፅ አላሰማም፡፡ ከቋሚ ብረት ጋር
በመታሠሩ መነቃነቅ አይችልም፡፡ እነኩርፌይራክና ኮምብፌሬ ተመለከቱት።
«ሰላይ ነው» ሲል ኢንጆልራስ ኋላ ለመጡት ጓደኞቹ አስረዳቸው::
ወደ ዣቬር ዞር ብሉ «ምሽጋችን ከተያዘ ትገደላለህ» አለው::
«ለምን አሁኑኑ አትጨርሱኝም» ሲል ቁጣ በተሞላበት እንደበት
ዣቬር ጠየቃቸው::
«ጥይት እንዳይባክን» ሲሉ መለሱለት::
«ለምን በቢላዋ አንገቴን አትቆርጡትም፡፡»
«አንተ ሰላይ» አለ መልኩመልካሙ ኢንጆልራስ፡፡ «እኛ ዳኞች ነን እንጂ ቅጥር ነፍሰ ገዳዮች አይደለንም፡፡»
ከዚያም ጋቭሮችን ጠራው፡፡
«አንቺ፣ ሂጅና የተላክሽበትን ፈጽሚ፡፡ የነገርኩርህን ፈጽመህ በቶሎ ተመለስ፡፡»
«መሄዱ ነው» ብሎ ጮክ ብሎ ተናገረ፡፡
ሊወጣ ሲል መለስ ብሎ «በነገራችን ላይ የሰውዬውን ጠብመንጃ ለእኔ አትሰጡኝም?» ሲል ጠየቀ፡፡ «ሙዚቀኛው ለእናንተ፣ ዋሽንቱ ግን
ለእኔ ቢሆን መልካም ነው፡፡)
ሁሉም ሳቅ አሉ ከዣቬር በስተቀር፡
ጋቭሮች ወጥቶ እንደሄደ የሆነውን አሳዛኝ ታሪክ ባይነገር ሕዝባዊ
እንቅስቃሴ በሚካሄድበት ጊዜ ምን ዓይነት ድርጊት እንደሚፈጸም አንባቢ ሊያውቅ አይችልም፡፡ ቢያውቅም እውቀቱ የተሟላ አይሆንም፡፡
ሕዝባዊ እንቅስቃሴ በበረዶ ሊመሰል ይችላል፡፡ አንድ ዓይነት
እንቅስቃሴ በሚነሳበት ጊዜ ሕዝብ ከየት መጣ ሳይባል እንደ ክረምት በረዶ ይቆለላል፤ ይሰበሰባል፡፡ ሰዎቹ ከየት እንደመጡ አይጠያየቁም። ዝም
ብለው ይሰበሰባሉ፡፡ በዚህ ዓይነት ከተሰበሰቡት ሰዎች መካከል ከየት እንደመጣ የማይታወቅ አንድ ወዝ አደር ነበር፡፡ የለበሰው ጃኬት ከክርኑ ላይ ተቀድዷል፡፡ አጢነው ሲመለከቱት የሰካራም መልክ ነው ያለው፡፡ ይህ
ሰው አብሮአቸው ከቆሙት ሌሎች ሰዎች መካከል የሚያውቀው የለም፡፡ ከዚያ እንደቆመ ሲናገር እንደ ሰካራም ወይም ሳይሰክር አውቆ የሰከረ ለመምሰል እንደሚንተባተብ ሰው ይንተባተባል፡፡ በድንገት ወደ ዋናው አውራ ጎዳና እያየ በሰካራም አንደበት ይናገራል::
«ጓደኞች፣ ታውቃላችሁ? የመጀመሪያውን ተኩስ የምንከፍተው ከዚያች
ማዶ ከምትታይ ቤት ውስጥ ሆነን መሆን አለበት:: የመስኮቱን ጥግ ይዘን ከተኮስን በማንም አንበገርም::»
« ቤቱን እንዲከፍቱ ማንኳኳት ነዋ!»
«ቢንኳኳም አይከፍቱም::»
«እኔ አስከፍተዋለሁ» በማለት ያ ሰው ራሱ ወደ ጠቆመው ቤት
አቅጣጫ አመራ:: ከበሩ ላይ ሆኖ አንኳኳ፡፡ ቤቱ አልተከፈተም። ደግሞ በኃይል አንኳኳ፡፡ ጥቂት ቆይቶ ለሦስተኛ ጊዜ በድፍረት በኃይል አንኳኳ፡፡ አሁንም ዝምታ ሆነ፡፡
«ቤቶች! እዚህ ቤት! ሰው የለም እንዴ?» ሲል በጣም ጮክ ብሎ
ተናገረ:: የሚንኳኳ ድምፅ ወይም የሚንቀሳቀስ ፍጡር አልነበረም:: በያዘው ጠብመንጃ ሰደፍ በሩን በኃይል ቀጠቀጠው:: ከድብደባው ብዛት ቤቱ የተነቃነቀ
መሰለ፡፡ ይህ ሲሆን ከመስኮቶቹ አንደኛው በጥቂቱ ተከፈተ:: ከውስጥ የሻማ ብርሃን ታየ:: ፀጉራቸው የሸበተ ሽማግሌ ሰው አንገታቸውን ብቅ አደረጉ።
በር ደብዳቢው መደብደቡን አቆመ::
“ምን ይፈልጋሉ ጌቶች?»
«በሩን ክፈትልን» ሲል መለሰላቸው::
«ጌታዬ ፣ ይህ ሊሆን አይችልም::
«ክፈት ብያለሁ፤ በሩ ቢከፈት ይሻላል::»
«አልችልም ጌታው::»
ጨለማ ስለነበር መሣሪያውን ሲያነጣጥርባቸው አላዩትም::
«እሺ ወይስ እምቢ?
አትከፍትም?» ሲል እንደገና የቤቱን ጌታ ጠየቃቸው
«እምቢ፣ አልከፍትም» ሲሉ መለሰሉት::
ሸ
«እምቢ አልክ?»
«አዎን የእኔ ጀግ…»
የሚሰጡትን መልስ ሳይጨርሱ ጠብመንጃው ተተኩሶ ግንባራቸውን ተረተረው:: ጥይቱ ከፊት ገብቶ ከኋላ በኩል ወጣ፡፡ ሰውዬው ጩኸት ሳያሰሙ መስኮቱ ላይ ተደፉ፡፡ ደማቸው ከመሬት ላይ ተንጠባጠበ:: ከመስኮቱ ላይ ሲወድቁ ሻማውን ነክተውት ኖሮ ከወለል ላይ ወድቆ መብራቱ ስለጠፋ ቤቱን ጨለማ ወረረው::
«ወንዱ» ሲል ገዳዩ ፎከረ፡፡ የጠመንጃውን አፈሙዝ ወደ መሬት እየመለሰ፡፡ ይህን ቃል ከአፉ አውጥቶ ሳይጨርስ አንድ ሰው ከኋላው መጥቶ ትከሻውን ጨምድዶ ያዘው::
«እጅ ወደ ላይ!» አለው::
ገዳዩ ፊቱን ቢያዞር ኢንጀልራስ እንደሆነ አወቀ፡፡ ጣቱን ከያዘው
ሽጉጥ ላይ አሳርፎአል:: የጠመንጃው ድምፅ ሰምቶ ነው ሲሮጥ የመጣው። ግስላ መስሎአል፡፡
«እጅ ወደ ላይ!» ሲል በድጋሚ ተናገረ፡፡
የሃያ ዓመቱ ወጣት በድንጋጤ እጁን ወደ ላይ ከዘረጋ በኋላ ከጭቃ ላይ ተንበረከከ፡ በአንድ ጊዜ ፊቱ ቀላ:: ሲደነግጡ የፈረንጅ ገላ መቅላት
የተለመደ ነው፡፡ ከዚያ የተሰበሰበው ሰው ዓይን ሁሉ ከእርሱ ላይ አረፈ፡፡
ሰው ሁሉ ዝም አለ፡፡ ገዳዩም ለመከላከል ወይም ለመናገር አልደፈረም።
ኢንጆልራስ ትከሻውን ለቅቆ ከመሬቱ ላይ በግንባሩ ደፋው፡፡
«አሳብህን ሰብስብ» አለው:: «ጸሉት ማድረስ ከፈለግህ መጸለይ ትችላለህ፡፡ ሌላም የምታስበው ነገር ካለ አስብ፡፡ ያለህ ጊዜ አንድ ደቂቃ ብቻ
ነው፡፡»
ማረኝ ይቅርታ አድርግልኝ፤ ተሳስቼአለሁ» ሲል ተንተባተበ፡፡
ከዚያም እንጀልሪስ እግር ላይ ተደፋ::
ኢንጂልራስ ዓይኑን ከወጣቱ ዓይን ላይ አላነሳም፡፡ ለአንድ ደቂቃ ጊዜ
ጠበቀው:: አንድ ደቂቃ ሲሞላ ከእግሩ ስር ይንደፋደፍ የነበረውን ሰው ፀጉር ይዞ ከጎተተው በኋላ እንደገና ወደ መሬት ወረወረው:: የያዘውን ሽጉጥ ቃታ ሳብ በማድረግ ጆሮው ላይ ለቀቀበት፡፡ ከዚያ የነበሩ ሰዎች ሁሉ
ወደመሬት አቀረቀሩ፡፡ ሟቹ ከጭቃው ላይ ተደፋ፡፡ ኢንጆልራስ ለመሞት የሚያጣጥረውን ሰው በእግሩ ከገፈተረ በኋላ የሚክተለውን ተናገረ፡፡
«ይህን ጥምብ ከምሽግ ውጭ ወርውሩና ጣሉት::»
ሶስት ሰዎች የሚያጣጥረውን ወጣት ከመሬት አንስተው ከምሽጉ ውጭ አውራ ጎዳና ላይ ወርውረው ጣሉት::
ኢንጆልራስ በአሳብ ተመስጦ ጥቂት ከቆየ በኋላ ከአሳቡ ይነቃል፡፡ራሱን ሰብሰብ አድርጎ ጸጥታውን በንግግር አደፈረሰ፡፡
«ጓዶች›› አለ ኢንጀልራስ፧ «ይህ ሰው የፈጸመው ተግባር አስጸያፊ
ሲሆን እኔ የወሰድኩበት እርምጃ ደግሞ አስከፊ ነው:: የሰው ሕይወት ስላጠፋ ነው የገደልኩት:: ይህን ቅጣት የፈጸምኩት ተገድጄ እንጂ ወድጄ
አይደለም:: እንቅስቃሴያችን ሥርዓት እንዲኖረው ያስፈልጋል:: የሰውን ሕይወት ማጥፋት ታላቅ ወንጀል ነው:: የአብዮታችን ዓይን እንደሚያየን መርሳት የለብንም:: እኛ የሪፑብሊክ ቄሶች ነን:: ኃላፊነት ስላለብን ፍልሚያችን በማንም መታወክ የለበትም:: በዚህ ምክንያት ነው ይህ ሰው
የፍርድ ውሳኔ የተበየነበትና አስፈላጊወም እርምጃ የተወሰደበት:: ፍርዱን የበየንኩት በዚህ ሰው ብቻ ላይ ሳይሆን በራሴም ላይ የፈረድኩ ስለሆነ
ውጤቱን ወደፊት የምታዩት ይሆናል::
የመጨረሻውን አነጋገር የሰሙ ሁሉ ተሸበሩ፡፡
«በአንተ ላይ የሚደርሰውን ሁሉ እኩል እንካፈላለን» ሲል ኮምብፌራ በጩኸት ተናገረ::
«ይሁና» ሲል ኢንጀልራስ መለሰለት:: «አንድ ነገር አለ ደግሞ:: የዚህን ሰው ብያኔ በማስፈጸም የሚጠበቅብኝን ግዴታ ነው የተወጣሁት::»
የወጣቱ ነፍስ ከወጣች በኋላ ልብሱ ሲመረመር ከኪሱ ውስጥ የፖሊስ አዛዥ ካርድ ተገኘ፡፡ ይህ ሰው ቆይቶ እንደተደረሰበት ከማሪየስ ቤት መጥቶ ማሪየስ የት እንዳለ ኩርፌይራን የጠየቀው ወጣት እንደሆነ ታውቋል፡፡
ማሪየስ ከጥላው ሥር ተደበቀ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...«ዣቬር ይህ ሁሉ ሲሆን ድምፅ አላሰማም፡፡ ከቋሚ ብረት ጋር
በመታሠሩ መነቃነቅ አይችልም፡፡ እነኩርፌይራክና ኮምብፌሬ ተመለከቱት።
«ሰላይ ነው» ሲል ኢንጆልራስ ኋላ ለመጡት ጓደኞቹ አስረዳቸው::
ወደ ዣቬር ዞር ብሉ «ምሽጋችን ከተያዘ ትገደላለህ» አለው::
«ለምን አሁኑኑ አትጨርሱኝም» ሲል ቁጣ በተሞላበት እንደበት
ዣቬር ጠየቃቸው::
«ጥይት እንዳይባክን» ሲሉ መለሱለት::
«ለምን በቢላዋ አንገቴን አትቆርጡትም፡፡»
«አንተ ሰላይ» አለ መልኩመልካሙ ኢንጆልራስ፡፡ «እኛ ዳኞች ነን እንጂ ቅጥር ነፍሰ ገዳዮች አይደለንም፡፡»
ከዚያም ጋቭሮችን ጠራው፡፡
«አንቺ፣ ሂጅና የተላክሽበትን ፈጽሚ፡፡ የነገርኩርህን ፈጽመህ በቶሎ ተመለስ፡፡»
«መሄዱ ነው» ብሎ ጮክ ብሎ ተናገረ፡፡
ሊወጣ ሲል መለስ ብሎ «በነገራችን ላይ የሰውዬውን ጠብመንጃ ለእኔ አትሰጡኝም?» ሲል ጠየቀ፡፡ «ሙዚቀኛው ለእናንተ፣ ዋሽንቱ ግን
ለእኔ ቢሆን መልካም ነው፡፡)
ሁሉም ሳቅ አሉ ከዣቬር በስተቀር፡
ጋቭሮች ወጥቶ እንደሄደ የሆነውን አሳዛኝ ታሪክ ባይነገር ሕዝባዊ
እንቅስቃሴ በሚካሄድበት ጊዜ ምን ዓይነት ድርጊት እንደሚፈጸም አንባቢ ሊያውቅ አይችልም፡፡ ቢያውቅም እውቀቱ የተሟላ አይሆንም፡፡
ሕዝባዊ እንቅስቃሴ በበረዶ ሊመሰል ይችላል፡፡ አንድ ዓይነት
እንቅስቃሴ በሚነሳበት ጊዜ ሕዝብ ከየት መጣ ሳይባል እንደ ክረምት በረዶ ይቆለላል፤ ይሰበሰባል፡፡ ሰዎቹ ከየት እንደመጡ አይጠያየቁም። ዝም
ብለው ይሰበሰባሉ፡፡ በዚህ ዓይነት ከተሰበሰቡት ሰዎች መካከል ከየት እንደመጣ የማይታወቅ አንድ ወዝ አደር ነበር፡፡ የለበሰው ጃኬት ከክርኑ ላይ ተቀድዷል፡፡ አጢነው ሲመለከቱት የሰካራም መልክ ነው ያለው፡፡ ይህ
ሰው አብሮአቸው ከቆሙት ሌሎች ሰዎች መካከል የሚያውቀው የለም፡፡ ከዚያ እንደቆመ ሲናገር እንደ ሰካራም ወይም ሳይሰክር አውቆ የሰከረ ለመምሰል እንደሚንተባተብ ሰው ይንተባተባል፡፡ በድንገት ወደ ዋናው አውራ ጎዳና እያየ በሰካራም አንደበት ይናገራል::
«ጓደኞች፣ ታውቃላችሁ? የመጀመሪያውን ተኩስ የምንከፍተው ከዚያች
ማዶ ከምትታይ ቤት ውስጥ ሆነን መሆን አለበት:: የመስኮቱን ጥግ ይዘን ከተኮስን በማንም አንበገርም::»
« ቤቱን እንዲከፍቱ ማንኳኳት ነዋ!»
«ቢንኳኳም አይከፍቱም::»
«እኔ አስከፍተዋለሁ» በማለት ያ ሰው ራሱ ወደ ጠቆመው ቤት
አቅጣጫ አመራ:: ከበሩ ላይ ሆኖ አንኳኳ፡፡ ቤቱ አልተከፈተም። ደግሞ በኃይል አንኳኳ፡፡ ጥቂት ቆይቶ ለሦስተኛ ጊዜ በድፍረት በኃይል አንኳኳ፡፡ አሁንም ዝምታ ሆነ፡፡
«ቤቶች! እዚህ ቤት! ሰው የለም እንዴ?» ሲል በጣም ጮክ ብሎ
ተናገረ:: የሚንኳኳ ድምፅ ወይም የሚንቀሳቀስ ፍጡር አልነበረም:: በያዘው ጠብመንጃ ሰደፍ በሩን በኃይል ቀጠቀጠው:: ከድብደባው ብዛት ቤቱ የተነቃነቀ
መሰለ፡፡ ይህ ሲሆን ከመስኮቶቹ አንደኛው በጥቂቱ ተከፈተ:: ከውስጥ የሻማ ብርሃን ታየ:: ፀጉራቸው የሸበተ ሽማግሌ ሰው አንገታቸውን ብቅ አደረጉ።
በር ደብዳቢው መደብደቡን አቆመ::
“ምን ይፈልጋሉ ጌቶች?»
«በሩን ክፈትልን» ሲል መለሰላቸው::
«ጌታዬ ፣ ይህ ሊሆን አይችልም::
«ክፈት ብያለሁ፤ በሩ ቢከፈት ይሻላል::»
«አልችልም ጌታው::»
ጨለማ ስለነበር መሣሪያውን ሲያነጣጥርባቸው አላዩትም::
«እሺ ወይስ እምቢ?
አትከፍትም?» ሲል እንደገና የቤቱን ጌታ ጠየቃቸው
«እምቢ፣ አልከፍትም» ሲሉ መለሰሉት::
ሸ
«እምቢ አልክ?»
«አዎን የእኔ ጀግ…»
የሚሰጡትን መልስ ሳይጨርሱ ጠብመንጃው ተተኩሶ ግንባራቸውን ተረተረው:: ጥይቱ ከፊት ገብቶ ከኋላ በኩል ወጣ፡፡ ሰውዬው ጩኸት ሳያሰሙ መስኮቱ ላይ ተደፉ፡፡ ደማቸው ከመሬት ላይ ተንጠባጠበ:: ከመስኮቱ ላይ ሲወድቁ ሻማውን ነክተውት ኖሮ ከወለል ላይ ወድቆ መብራቱ ስለጠፋ ቤቱን ጨለማ ወረረው::
«ወንዱ» ሲል ገዳዩ ፎከረ፡፡ የጠመንጃውን አፈሙዝ ወደ መሬት እየመለሰ፡፡ ይህን ቃል ከአፉ አውጥቶ ሳይጨርስ አንድ ሰው ከኋላው መጥቶ ትከሻውን ጨምድዶ ያዘው::
«እጅ ወደ ላይ!» አለው::
ገዳዩ ፊቱን ቢያዞር ኢንጀልራስ እንደሆነ አወቀ፡፡ ጣቱን ከያዘው
ሽጉጥ ላይ አሳርፎአል:: የጠመንጃው ድምፅ ሰምቶ ነው ሲሮጥ የመጣው። ግስላ መስሎአል፡፡
«እጅ ወደ ላይ!» ሲል በድጋሚ ተናገረ፡፡
የሃያ ዓመቱ ወጣት በድንጋጤ እጁን ወደ ላይ ከዘረጋ በኋላ ከጭቃ ላይ ተንበረከከ፡ በአንድ ጊዜ ፊቱ ቀላ:: ሲደነግጡ የፈረንጅ ገላ መቅላት
የተለመደ ነው፡፡ ከዚያ የተሰበሰበው ሰው ዓይን ሁሉ ከእርሱ ላይ አረፈ፡፡
ሰው ሁሉ ዝም አለ፡፡ ገዳዩም ለመከላከል ወይም ለመናገር አልደፈረም።
ኢንጆልራስ ትከሻውን ለቅቆ ከመሬቱ ላይ በግንባሩ ደፋው፡፡
«አሳብህን ሰብስብ» አለው:: «ጸሉት ማድረስ ከፈለግህ መጸለይ ትችላለህ፡፡ ሌላም የምታስበው ነገር ካለ አስብ፡፡ ያለህ ጊዜ አንድ ደቂቃ ብቻ
ነው፡፡»
ማረኝ ይቅርታ አድርግልኝ፤ ተሳስቼአለሁ» ሲል ተንተባተበ፡፡
ከዚያም እንጀልሪስ እግር ላይ ተደፋ::
ኢንጂልራስ ዓይኑን ከወጣቱ ዓይን ላይ አላነሳም፡፡ ለአንድ ደቂቃ ጊዜ
ጠበቀው:: አንድ ደቂቃ ሲሞላ ከእግሩ ስር ይንደፋደፍ የነበረውን ሰው ፀጉር ይዞ ከጎተተው በኋላ እንደገና ወደ መሬት ወረወረው:: የያዘውን ሽጉጥ ቃታ ሳብ በማድረግ ጆሮው ላይ ለቀቀበት፡፡ ከዚያ የነበሩ ሰዎች ሁሉ
ወደመሬት አቀረቀሩ፡፡ ሟቹ ከጭቃው ላይ ተደፋ፡፡ ኢንጆልራስ ለመሞት የሚያጣጥረውን ሰው በእግሩ ከገፈተረ በኋላ የሚክተለውን ተናገረ፡፡
«ይህን ጥምብ ከምሽግ ውጭ ወርውሩና ጣሉት::»
ሶስት ሰዎች የሚያጣጥረውን ወጣት ከመሬት አንስተው ከምሽጉ ውጭ አውራ ጎዳና ላይ ወርውረው ጣሉት::
ኢንጆልራስ በአሳብ ተመስጦ ጥቂት ከቆየ በኋላ ከአሳቡ ይነቃል፡፡ራሱን ሰብሰብ አድርጎ ጸጥታውን በንግግር አደፈረሰ፡፡
«ጓዶች›› አለ ኢንጀልራስ፧ «ይህ ሰው የፈጸመው ተግባር አስጸያፊ
ሲሆን እኔ የወሰድኩበት እርምጃ ደግሞ አስከፊ ነው:: የሰው ሕይወት ስላጠፋ ነው የገደልኩት:: ይህን ቅጣት የፈጸምኩት ተገድጄ እንጂ ወድጄ
አይደለም:: እንቅስቃሴያችን ሥርዓት እንዲኖረው ያስፈልጋል:: የሰውን ሕይወት ማጥፋት ታላቅ ወንጀል ነው:: የአብዮታችን ዓይን እንደሚያየን መርሳት የለብንም:: እኛ የሪፑብሊክ ቄሶች ነን:: ኃላፊነት ስላለብን ፍልሚያችን በማንም መታወክ የለበትም:: በዚህ ምክንያት ነው ይህ ሰው
የፍርድ ውሳኔ የተበየነበትና አስፈላጊወም እርምጃ የተወሰደበት:: ፍርዱን የበየንኩት በዚህ ሰው ብቻ ላይ ሳይሆን በራሴም ላይ የፈረድኩ ስለሆነ
ውጤቱን ወደፊት የምታዩት ይሆናል::
የመጨረሻውን አነጋገር የሰሙ ሁሉ ተሸበሩ፡፡
«በአንተ ላይ የሚደርሰውን ሁሉ እኩል እንካፈላለን» ሲል ኮምብፌራ በጩኸት ተናገረ::
«ይሁና» ሲል ኢንጀልራስ መለሰለት:: «አንድ ነገር አለ ደግሞ:: የዚህን ሰው ብያኔ በማስፈጸም የሚጠበቅብኝን ግዴታ ነው የተወጣሁት::»
የወጣቱ ነፍስ ከወጣች በኋላ ልብሱ ሲመረመር ከኪሱ ውስጥ የፖሊስ አዛዥ ካርድ ተገኘ፡፡ ይህ ሰው ቆይቶ እንደተደረሰበት ከማሪየስ ቤት መጥቶ ማሪየስ የት እንዳለ ኩርፌይራን የጠየቀው ወጣት እንደሆነ ታውቋል፡፡
ማሪየስ ከጥላው ሥር ተደበቀ
👍9
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
“ቆንጅዬ ልጅ ይዘሻል” አለ ረጅሙ ፖስተኛ በፍርሀት ቀሚሴን ጥብቅ አድርጋ የያዘችውን ኬሪን በአሳዛኝ አይን እየተመለከተ። “ይህንን ስናገር ቅር
ካላላችሁ ትንሽ ያመማት ትመስላለች።”
“አሟት ነበር” ክሪስ አረጋገጠለት፡ “ግን አሁን ይሻላታል” አለው። ፖስተኛው ጭንቅላቱን ነቀነቀ፤ የነገርነውን ያመነ ይመስላል።
“ትኬት ይዛችኋል?”
“ገንዘብ ይዘናል፤ ለትኬቱ ክፍያ የሚበቃ ገንዘብ ይዘናል” አለ
“ስጠኝ ልጄ፤ የአስራ አንድ ሰአት ከአርባ አምስት ደቂቃው ባቡር መጥቷል”
አለው በዚያ ማለዳ ወደ ቻርለትስቪል በሚወስደው ባቡር ስንጓዝ የፎክስወርዝ ግዙፍ ቤት በኮረብቶቹ ላይ ከፍ ብሎ እያየነው ነበር። እኔና ክሪስ አይኖቻችንን
ከእሱ ላይ መንቀል አልቻልንም: እስር ቤታችን ከአይናችን እስኪሰወር ድረስ ውጪ እየተመለከትነው ነበር በተለይ በጥቁር መጋረጃ የተዘጉትን የጣሪያ
ስር ክፍል መስኮቶች እያየናቸው ነበር
ከዚያ ትኩረቴ በሰሜን አቅጣጫ ባለው የሁለተኛው ፎቅ የመጨረሻ ክፍል ሄደ ከባዱ መጋረጃ ተከፍቶና ጥላ የሚመስል ከሩቅ የሚታይ የግዙፍ
አሮጊት ሴት ምስል ወጥቶ ሲፈልገንና… ከዚያ ሲጠፋ ታይቶኝ ክሪስን ጎነተልኩት።
እርግጥ ነው ባቡሩን ማየት ትችላለች: ግን እዚያ ሆነን መንገዶቹን ማየት
እንደማንችለው ሁሉ እሷም እንደማታየን አውቀናል። ቢሆንም ግን እኔና
ክሪስ መቀመጫችን ላይ እንዳለን ወደ ታች ሸርተት አልን፡
“በዚህ ጠዋት ምን ትሰራ ይሆን?” ስል ክሪስን በሹክሹክታ ጠየቅኩት።
“በተለምዶ እስከ አስራ ሁለት ሰአት ተኩል ድረስ ምግባችንን ይዛ አትመጣም”
ሳቀ። የምሬት ሳቅ ይመስላል። “ምናልባት የሆነ ኃጢአት ወይም የተhለከለ ነገር ስንሰራ ለመያዝ ጥረት እያደረገች ይሆናል” አለ። ይሆን ይሆናል። ግን እዚያ ክፍል ውስጥ ገብታ ባዶ ሆኖ ስታገኘውና ልብሶቻችንም ማስቀመጫው ውስጥ ያለመኖሩን ስታይ፣ ከዚያ ስትጣራ፣ ምንም አይነት ድምፅም ሆነ ሮጦ
የሚመጣ የእግር ኮቴ ሳትሰማ ስትቀር የምታስበውንና የሚሰማትን ባውቅ ደስ ይለኝ ነበር።
ቻርለትስቪል ስንደርስ ወደ ሳሪሶታ የሚያደርሰንን የአውቶቢስ ቲኬት ስንገዛ
ወደ ደቡብ የሚሄደውን አውቶቢስ ለመያዝ ሁለት ሰአት መጠበቅ እንዳለብን
ተነገረን።
በሁለት ሰአት ውስጥ ጆን ጥቁሩን ሊሞዝን ይዞ ቀርፋፋውን ባቡር
ይቀድመዋል!” አልኩ
“አታስቢ” አለ ክሪስ፡ “ስለ እኛ ለእሱ የምትነግረው ሞኝ አይደለችም ምናልባት
በራሱ መንገድ ካላወቀ በስተቀር" እንዲከተለን ከተላከም እንዳያገኘን ምርጡ መንገድ አለመቆም እንደሆነ አሰብን ዕቃ ማስቀመጫ ተከራይተን ሁለቱን ሻንጣዎቻችንንና ጊታሩን አስቀመጥን ኬሪን መሀከል አድርገን እጅ ለእጅ ተያይዘን ዋና ዋና መንገዶች
ተከትለን የፎክስወርዝ ሰራተኞች በእረፍት ቀናቸው ዘመድ ለመጠየቅ ዕቃ ለመግዛትና ሲኒማ ለመግባት ወይም በሌሎች መንገዶች ራሳቸውን ለማስደሰት የሚመርጡትን ከተማ በደንብ አየነው። ሀሙስ ቢሆን ኖሮ በጣም
ያስፈራ ነበር። ግን እሁድ ነው።
በልካችን ያልሆኑ ልብሶቻችን፣ ጫማዎቻችን፣ ያልተስተካከለው የፀጉር
ቁርጣችንና የገረጣው ፊታችን ከሌላ አለም የመጡ ጎብኚዎች መስሎኝ ነበር። ግን እንደፈራሁት ማንም አላፈጠጠብንም ልክ የሰው ዘር እንደሆንን ነው የተቀበሉን እንግዳ ፍጡር አልመሰልናቸውም ብዙ ሰዎች ወዳሉበት ቦታ መመለሳችን በጣም ጥሩ ነበር: የተለያዩ ፊቶች ያሉበት ቦታ መሆን።
“ሁሉም እየፈጠነ ወዴት እንደሚሄድ አይገርምም?” ስል ክሪስን ጠየቅኩት:
መወሰን አቅቶን ጥግ ላይ ቆምን፡ ኮሪ የተቀበረው ከዚህ ብዙም ሳይርቅ
እንደሆነ ገመትኩ። መቃብሩን ፈልጌ አበባ ማስቀመጥ በጣም ፈለግኩ።በሌላ ቀን ቢጫ አበቦች ይዘን ተመልሰን እንመጣና ይጥቀምም አይጥቀም ተንበርክከን ፀሎት እናደርስለታለን፡ ለአሁኑ ግን ኬሪን ከአደጋ ለመጠበቅ ወደ ዶክተር ከመውሰዳችን በፊት . . . ከቨርጂኒያ ርቀን በጣም ርቀን መሄድ አለብን
የዚያን ጊዜ ነው ክሪስ በኪስ ወረቀት የያዘውን የአይጥ ሬሳና ስኳር
የተነሰነሰባቸውን ዶናቶች ከጃኬት ኪሱ ያወጣው ኮስታራ አይኖቹ ከአይኖቼ
ጋር ተገናኙ ኪስ ወረቀቱን ፊት ለፊቴ ይዞ ፊቴን እያጠና በአይኖቹ “አይን ላጠፋ አይን?” እያለ ጠየቀኝ፡
“ወደ ፖሊስ ጣቢያ ሄደን ታሪካችንን መናገር እንችላለን" አለ ክሪስቶፈር
አይኖቹን ከእኔ እያሸሸ፡ “መንግስት ለአንቺና ለኬሪ ማደጎ ቤት ይፈልግላችኋል።
ስለዚህ መኮብለል አይጠበቅባችሁም: ለእኔ ደግሞ አላውቅም . . .
ክሪስ የሆነ ነገር ካልደበቀኝ በስተቀር አይኖቼን ሳያይ አያወራም: ያ የተለየ ነገር ከፎክስወርዝ አዳራሽ እስክንወጣ መቆየት የነበረበት ነገር መሆን አለበት።“እሺ ክሪስ አሁን አምልጠናል ምንድነው የደበቅከኝ ተናገር!
ኬሪ ብዙ መኪናዎች ወዲያ ወዲህ ሲሉና አንዳንድ ሰዎች ፈገግ እያሉላት
እየፈጠኑ ሲያልፉ አይኖቿ በአድናቆት ፈጥጠው ወደ እኔ ተጠግታ ቀሚሴን
ስትይዝ ክሪስ አንገቱን ደፋ አደረገ።
እናታችን ናት” አለ ዝቅ ባለ ድምፅ:: ከአባቷ ለመውረስ እንድትችል እሽታውን ለማግኘት ምንም ነገር እንደምታደርግ ስትናገር ታስታውሻለሽ? ምን ቃል እንዳስገባት አላውቅም ካቲ፣ ግን ሠራተኞቹ ሲያወሩ ሰምቻለሁ።
ወንድ አያታችን ከመሞቱ ጥቂት ቀናት በፊት፣ ኑዛዜው ውስጥ ተጨማሪ ቃል ገብቷል። ያስገባው ቃል የሚለው እናታችን ከመጀመሪያው ባሏ ልጆች እንዳሏት ከተረጋገጠ የወረሰችውን ንብረት በሙሉ በቅጣት መልክ ትመልሳለች
በገንዘቡ የገዛቻቸውን ነገሮች ሁሉ፣ ልብሶቿን ጌጣጌጦቿንና ዋጋ የሚያወጡ ነገሮችን በሙሉ ትመልሳለች። ያ ብቻ አይደለም: ያፃፈው
ኑዛዜ ውስጥ ከሁለተኛ ትዳሯ ከወለደችም ሁሉንም ነገር ታጣለች: እና
እናታችን ይቅር እንዳላት ታስባለች። ይቅር አላላትም፣ አልረሳምም፣ መቃብር
ውስጥ ሆኖ እንኳን እየቀጣት ነው::”
ነገሮችን ሳገጣጥም አይኖቼ በድንጋጤ ፈጠጡ። “ማለት እናታችን . . . ?
እናታችን ናት አያትየው አልነበረችም?”
ሊሰማው እንደሚችል ባውቅም ግን ልክ ግድ እንደሌለው ሁሉ ትከሻውን
ሰበቀ: “ያቺ አሮጊት አልጋዋ አጠገብ ሆና ስትፀልይ ሰምቻታለሁ። ክፉ ናት፣ ግን ዶናቶቹ ላይ መርዝ መጨመሯን እጠራጠራለሁ።ወደ እኛ
ይዛቸው ትመጣለች... እንደምንበላቸውም ታውቃለች ግን እንዳንበላቸው ታስጠነቅቀን ነበር።"
“ግን ክሪስ፣ እናታችን ልትሆን አትችልም ዶናቶቹ በየቀኑ መምጣት ሲጀምሩ
እሷ የጫጉላ ሽርሽር ላይ ነበረች”
ፈገግታው የመምረርና የመጠየፍ ነበር “አዎ ግን ከዘጠኝ ወር በፊት ኑዛዜው
ተነቦ ነበር፤ ከዘጠነኛ ወር በፊት እናታችን ተመልሳ ነበር። ከወንድ አያታችን
ኑዛዜ የምትጠቀመው እናታችን ብቻ ናት ሴት አያታችን አይደለችም እሷ
የራሷ ገንዘብ አላት፡ የእሷ ስራ በየቀኑ ቅርጫቱን ማምጣት ብቻ ነበር።"
መጠየቅ የምፈልጋቸው ብዙ ጥያቄዎች ነበሩኝ፡ ግን ኬሪ ነበረች: ቀሚሴን
ይዛ አተኩራ እያየችኝ ነበር ኬሪ በተፈጥሮ ሞት መሞቱን እንጂ ሌላ ምንም
ነገር እንድታውቅ አልፈለግኩም: የዚያን ጊዜ ነው ክሪስ ማስረጃ የሆነውን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
“ቆንጅዬ ልጅ ይዘሻል” አለ ረጅሙ ፖስተኛ በፍርሀት ቀሚሴን ጥብቅ አድርጋ የያዘችውን ኬሪን በአሳዛኝ አይን እየተመለከተ። “ይህንን ስናገር ቅር
ካላላችሁ ትንሽ ያመማት ትመስላለች።”
“አሟት ነበር” ክሪስ አረጋገጠለት፡ “ግን አሁን ይሻላታል” አለው። ፖስተኛው ጭንቅላቱን ነቀነቀ፤ የነገርነውን ያመነ ይመስላል።
“ትኬት ይዛችኋል?”
“ገንዘብ ይዘናል፤ ለትኬቱ ክፍያ የሚበቃ ገንዘብ ይዘናል” አለ
“ስጠኝ ልጄ፤ የአስራ አንድ ሰአት ከአርባ አምስት ደቂቃው ባቡር መጥቷል”
አለው በዚያ ማለዳ ወደ ቻርለትስቪል በሚወስደው ባቡር ስንጓዝ የፎክስወርዝ ግዙፍ ቤት በኮረብቶቹ ላይ ከፍ ብሎ እያየነው ነበር። እኔና ክሪስ አይኖቻችንን
ከእሱ ላይ መንቀል አልቻልንም: እስር ቤታችን ከአይናችን እስኪሰወር ድረስ ውጪ እየተመለከትነው ነበር በተለይ በጥቁር መጋረጃ የተዘጉትን የጣሪያ
ስር ክፍል መስኮቶች እያየናቸው ነበር
ከዚያ ትኩረቴ በሰሜን አቅጣጫ ባለው የሁለተኛው ፎቅ የመጨረሻ ክፍል ሄደ ከባዱ መጋረጃ ተከፍቶና ጥላ የሚመስል ከሩቅ የሚታይ የግዙፍ
አሮጊት ሴት ምስል ወጥቶ ሲፈልገንና… ከዚያ ሲጠፋ ታይቶኝ ክሪስን ጎነተልኩት።
እርግጥ ነው ባቡሩን ማየት ትችላለች: ግን እዚያ ሆነን መንገዶቹን ማየት
እንደማንችለው ሁሉ እሷም እንደማታየን አውቀናል። ቢሆንም ግን እኔና
ክሪስ መቀመጫችን ላይ እንዳለን ወደ ታች ሸርተት አልን፡
“በዚህ ጠዋት ምን ትሰራ ይሆን?” ስል ክሪስን በሹክሹክታ ጠየቅኩት።
“በተለምዶ እስከ አስራ ሁለት ሰአት ተኩል ድረስ ምግባችንን ይዛ አትመጣም”
ሳቀ። የምሬት ሳቅ ይመስላል። “ምናልባት የሆነ ኃጢአት ወይም የተhለከለ ነገር ስንሰራ ለመያዝ ጥረት እያደረገች ይሆናል” አለ። ይሆን ይሆናል። ግን እዚያ ክፍል ውስጥ ገብታ ባዶ ሆኖ ስታገኘውና ልብሶቻችንም ማስቀመጫው ውስጥ ያለመኖሩን ስታይ፣ ከዚያ ስትጣራ፣ ምንም አይነት ድምፅም ሆነ ሮጦ
የሚመጣ የእግር ኮቴ ሳትሰማ ስትቀር የምታስበውንና የሚሰማትን ባውቅ ደስ ይለኝ ነበር።
ቻርለትስቪል ስንደርስ ወደ ሳሪሶታ የሚያደርሰንን የአውቶቢስ ቲኬት ስንገዛ
ወደ ደቡብ የሚሄደውን አውቶቢስ ለመያዝ ሁለት ሰአት መጠበቅ እንዳለብን
ተነገረን።
በሁለት ሰአት ውስጥ ጆን ጥቁሩን ሊሞዝን ይዞ ቀርፋፋውን ባቡር
ይቀድመዋል!” አልኩ
“አታስቢ” አለ ክሪስ፡ “ስለ እኛ ለእሱ የምትነግረው ሞኝ አይደለችም ምናልባት
በራሱ መንገድ ካላወቀ በስተቀር" እንዲከተለን ከተላከም እንዳያገኘን ምርጡ መንገድ አለመቆም እንደሆነ አሰብን ዕቃ ማስቀመጫ ተከራይተን ሁለቱን ሻንጣዎቻችንንና ጊታሩን አስቀመጥን ኬሪን መሀከል አድርገን እጅ ለእጅ ተያይዘን ዋና ዋና መንገዶች
ተከትለን የፎክስወርዝ ሰራተኞች በእረፍት ቀናቸው ዘመድ ለመጠየቅ ዕቃ ለመግዛትና ሲኒማ ለመግባት ወይም በሌሎች መንገዶች ራሳቸውን ለማስደሰት የሚመርጡትን ከተማ በደንብ አየነው። ሀሙስ ቢሆን ኖሮ በጣም
ያስፈራ ነበር። ግን እሁድ ነው።
በልካችን ያልሆኑ ልብሶቻችን፣ ጫማዎቻችን፣ ያልተስተካከለው የፀጉር
ቁርጣችንና የገረጣው ፊታችን ከሌላ አለም የመጡ ጎብኚዎች መስሎኝ ነበር። ግን እንደፈራሁት ማንም አላፈጠጠብንም ልክ የሰው ዘር እንደሆንን ነው የተቀበሉን እንግዳ ፍጡር አልመሰልናቸውም ብዙ ሰዎች ወዳሉበት ቦታ መመለሳችን በጣም ጥሩ ነበር: የተለያዩ ፊቶች ያሉበት ቦታ መሆን።
“ሁሉም እየፈጠነ ወዴት እንደሚሄድ አይገርምም?” ስል ክሪስን ጠየቅኩት:
መወሰን አቅቶን ጥግ ላይ ቆምን፡ ኮሪ የተቀበረው ከዚህ ብዙም ሳይርቅ
እንደሆነ ገመትኩ። መቃብሩን ፈልጌ አበባ ማስቀመጥ በጣም ፈለግኩ።በሌላ ቀን ቢጫ አበቦች ይዘን ተመልሰን እንመጣና ይጥቀምም አይጥቀም ተንበርክከን ፀሎት እናደርስለታለን፡ ለአሁኑ ግን ኬሪን ከአደጋ ለመጠበቅ ወደ ዶክተር ከመውሰዳችን በፊት . . . ከቨርጂኒያ ርቀን በጣም ርቀን መሄድ አለብን
የዚያን ጊዜ ነው ክሪስ በኪስ ወረቀት የያዘውን የአይጥ ሬሳና ስኳር
የተነሰነሰባቸውን ዶናቶች ከጃኬት ኪሱ ያወጣው ኮስታራ አይኖቹ ከአይኖቼ
ጋር ተገናኙ ኪስ ወረቀቱን ፊት ለፊቴ ይዞ ፊቴን እያጠና በአይኖቹ “አይን ላጠፋ አይን?” እያለ ጠየቀኝ፡
“ወደ ፖሊስ ጣቢያ ሄደን ታሪካችንን መናገር እንችላለን" አለ ክሪስቶፈር
አይኖቹን ከእኔ እያሸሸ፡ “መንግስት ለአንቺና ለኬሪ ማደጎ ቤት ይፈልግላችኋል።
ስለዚህ መኮብለል አይጠበቅባችሁም: ለእኔ ደግሞ አላውቅም . . .
ክሪስ የሆነ ነገር ካልደበቀኝ በስተቀር አይኖቼን ሳያይ አያወራም: ያ የተለየ ነገር ከፎክስወርዝ አዳራሽ እስክንወጣ መቆየት የነበረበት ነገር መሆን አለበት።“እሺ ክሪስ አሁን አምልጠናል ምንድነው የደበቅከኝ ተናገር!
ኬሪ ብዙ መኪናዎች ወዲያ ወዲህ ሲሉና አንዳንድ ሰዎች ፈገግ እያሉላት
እየፈጠኑ ሲያልፉ አይኖቿ በአድናቆት ፈጥጠው ወደ እኔ ተጠግታ ቀሚሴን
ስትይዝ ክሪስ አንገቱን ደፋ አደረገ።
እናታችን ናት” አለ ዝቅ ባለ ድምፅ:: ከአባቷ ለመውረስ እንድትችል እሽታውን ለማግኘት ምንም ነገር እንደምታደርግ ስትናገር ታስታውሻለሽ? ምን ቃል እንዳስገባት አላውቅም ካቲ፣ ግን ሠራተኞቹ ሲያወሩ ሰምቻለሁ።
ወንድ አያታችን ከመሞቱ ጥቂት ቀናት በፊት፣ ኑዛዜው ውስጥ ተጨማሪ ቃል ገብቷል። ያስገባው ቃል የሚለው እናታችን ከመጀመሪያው ባሏ ልጆች እንዳሏት ከተረጋገጠ የወረሰችውን ንብረት በሙሉ በቅጣት መልክ ትመልሳለች
በገንዘቡ የገዛቻቸውን ነገሮች ሁሉ፣ ልብሶቿን ጌጣጌጦቿንና ዋጋ የሚያወጡ ነገሮችን በሙሉ ትመልሳለች። ያ ብቻ አይደለም: ያፃፈው
ኑዛዜ ውስጥ ከሁለተኛ ትዳሯ ከወለደችም ሁሉንም ነገር ታጣለች: እና
እናታችን ይቅር እንዳላት ታስባለች። ይቅር አላላትም፣ አልረሳምም፣ መቃብር
ውስጥ ሆኖ እንኳን እየቀጣት ነው::”
ነገሮችን ሳገጣጥም አይኖቼ በድንጋጤ ፈጠጡ። “ማለት እናታችን . . . ?
እናታችን ናት አያትየው አልነበረችም?”
ሊሰማው እንደሚችል ባውቅም ግን ልክ ግድ እንደሌለው ሁሉ ትከሻውን
ሰበቀ: “ያቺ አሮጊት አልጋዋ አጠገብ ሆና ስትፀልይ ሰምቻታለሁ። ክፉ ናት፣ ግን ዶናቶቹ ላይ መርዝ መጨመሯን እጠራጠራለሁ።ወደ እኛ
ይዛቸው ትመጣለች... እንደምንበላቸውም ታውቃለች ግን እንዳንበላቸው ታስጠነቅቀን ነበር።"
“ግን ክሪስ፣ እናታችን ልትሆን አትችልም ዶናቶቹ በየቀኑ መምጣት ሲጀምሩ
እሷ የጫጉላ ሽርሽር ላይ ነበረች”
ፈገግታው የመምረርና የመጠየፍ ነበር “አዎ ግን ከዘጠኝ ወር በፊት ኑዛዜው
ተነቦ ነበር፤ ከዘጠነኛ ወር በፊት እናታችን ተመልሳ ነበር። ከወንድ አያታችን
ኑዛዜ የምትጠቀመው እናታችን ብቻ ናት ሴት አያታችን አይደለችም እሷ
የራሷ ገንዘብ አላት፡ የእሷ ስራ በየቀኑ ቅርጫቱን ማምጣት ብቻ ነበር።"
መጠየቅ የምፈልጋቸው ብዙ ጥያቄዎች ነበሩኝ፡ ግን ኬሪ ነበረች: ቀሚሴን
ይዛ አተኩራ እያየችኝ ነበር ኬሪ በተፈጥሮ ሞት መሞቱን እንጂ ሌላ ምንም
ነገር እንድታውቅ አልፈለግኩም: የዚያን ጊዜ ነው ክሪስ ማስረጃ የሆነውን
👍50👎1🔥1
#ጠላፊዎቹ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
ናንሲ ባህሩ ዳር ቁጭ ብላለች፡፡ መርቪን ላቭሴይ አጠገቧ ተቀምጧል፡፡
የባህሩ ውሃ በማዕበል እየተገፋ ይመጣል፣ ይመለሳል፡፡ ናንሲ ዓይኗን
ጨፍናለች፡ ሌሊት በደምብ አልተኛችም:: መርቪንና እሷ
እሷ ማታ መጋጨታቸው ትዝ አላትና ፈገግ አለች ከእሱ ጋር የምር ግንኙነት
አለመመስረቷ ደስ ብሏታል፡ ለወሲብ መቻኮሉ ጥሩ
አይደለም፡፡የመጣችበትን ዓላማ ከግብ ማድረስ አለባት፡፡
ሼዲያክ የዓሳ ማጥመጃ ፤መንደርና የባህር ዳር መዝናኛ ከተማ ናት፡፡
በባህሩ ዳርቻ ላይ የዓሳ
ማጥመጃ ጀልባዎች፣ መርከቦች፣ ሌሎች ሁለት
አይሮፕላኖችና እነሱ የመጡበት አይሮፕላን ይታያል፡፡ ብዙዎቹ የአይሮፕላኑ ተሳፋሪዎች በባህሩ ዳርቻ ላይ ወዲያ ወዲህ ይላሉ፡፡
ሁለት የፖሊስ መኪኖች እየበረሩ መጥተው ጎማቸውን ሲጢጥ
አድርገው ሲቆሙ የአካባቢው ፀጥታ ታወከ፡፡ ከመኪኖቹም ውስጥ ሰባት
ስምንት ያህል ፖሊሶች እየዘለሉ ወጡ፡፡ በቀጥታ ወደ ተሳፋሪዎቹ
ማስተናገጃ ሲያመሩ የሆነ ሰው ሊይዙ የመጡ ይመስላል›› አለች ናንሲ፡
እሱም በመስማማት ራሱን ነቀነቀና ‹‹ማንን ይሆን?›› አለ፡፡
‹‹ምናልባትም ፍራንኪ ጎርዲኖን››
‹ሊሆን አይችልም እሱ እንደሆነ እንደታሰረ ነው፡፡››
አይሮፕላን ውስጥ ሲገቡ ሁለቱ ወደ ባህሩ ዳርቻ ሲያመሩ ሁለቱ ደግሞ
ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ፖሊሶቹ ከመናኸሪያው ወጡና ሶስቱ መንደሩ ውስጥ መንጎራደድ ጀመሩ፡፡
ፖሊሶቹ የሆነ ሰው እንደሚፈልጉ ያስታውቅባቸዋል፡ አንዱ
የአይሮፕላኑ ሰራተኛ ከአይሮፕላኑ ሲወጣ አየችና ናንሲ ‹ፖሊሶቹ ማንን ነው የሚፈልጉት?›› ስትል ጠየቀች:
ሰውየው ምስጢር ለማውጣት እየተጠራጠረ ሄሪ ቫንዴርፖስት
የተባለውን ሰው ነው የሚፈልጉት፤ ስሙ የሀሰት ነው›› አለ፡፡
ናንሲ ግንባሯን ከሰከሰችና ይሄ ልጅ ከኦክሰንፎርድ ቤተሰብ ጋር ተቀምጦ የነበረው ነው፡ ልጁ የማርጋሬትን ልብ ሳይሰርቅ አልቀረም›› ስትል
ገመተች ናንሲ፡
መርቪን ‹‹ከአይሮፕላኑ ወጥቶ ሄዷል እንዴ? እኔ ከአይሮፕላኑ ሲወጣ
አላየሁትም›› አለ፡፡
‹‹እኔም አላስተዋልኩም›› አለች ናንሲ፡
‹‹ልጁ አጭበርባሪ ይመስላል››
‹‹እውነት?›› አለች ናንሲ፡ እሷ ልጁ ከጥሩ ቤተሰብ የተገኘ ነበር የመሰላት፡ ‹‹ጥሩ ባህሪ አይቼበታለሁ: ማርጋሬት ከልጁ ጋር ፍቅር ሳይዛት አልቀረችም፡፡ ፖሊስ እንደሚፈልገው ስታውቅ ታዝናለች›› አለች
‹‹ወላጆቿ ፖሊስ እጅ መውደቁ ደስ ሳያሰኛቸው አይቀርም›› አለ
መርቪን፡፡ናንሲ ስለወላጆቿ ግድ የላትም፡ በአይሮፕላኑ መብል ክፍል ውስጥ
ሎርድ ኦክሰንፎርድ ያሳዩት የነበረው ጋጠወጥ ባህሪ መርቪንና ናንሲ
ያስታውሳሉ፡ ለእንደዚህ አይነት ሰው ውርደት ሲያንሰው ነው ናንሲ ከእንደዚህ አይነት ወመኔ ጋር ማርጋሬት ፍቅር ስለያዛት አዘነችላት፡
መርቪንም ቀጠለና ‹‹እኔ ስለሌላ ሰው ማውራት አልፈልግም›› አለ፡
ናንሲ ጆሮዋን ቀሰረች፡
መርቪን ቀጠለና ‹‹የተገናኘነው ከጥቂት ሰዓታት በፊት ስለሆነ በደምብ ላውቅሽ እፈልጋለሁ፡›› ናንሲም እርግጠኛ መሆን አትችልም አንተ ደደብ አለች በሆዷ
ሆኖም ይህን ማለቱ አስደስቷታል፡ ምንም መልስ አልሰጠችውም፡፡
‹‹ብፊት አንቺን ኒውዮርክ አድርሼ ወደ ማንቼስተር መመለስ ነበር የማስበው፡፡ አሁን ግን አላደርገውም›› አላት፡
ናንሲ ፈገግ አለች ይህን እንዲል ነበር ስትጠብቅ የነበረው:፡ እጇን ሰደደችና እጁን ያዝ አደረገች፡፡ ‹‹ይህን ስላልክ ደስ ብሎኛል›› አለችው፡
‹‹ደስ ብሎሻል? ችግሩ ከዚህ በኋላ አትላንቲክን ማቋረጡ የሚቻል አይሆንም፡፡ የጦር መርከቦች ብቻ ናቸው ይህን ማድረግ የሚችሉት፡››ናንሲ በመስማማት ራሷን ነቀነቀች፡
አሁን ከተለያየን ምናልባትም የምንገናኘው ከብዙ ጊዜ በኋላ ነው፡፡።
እኔ ግን ላጣሽ አልፈልግም›› አለ መርቪን፡፡
‹‹እኔም እንደዚያው›› አለች ናንሲ፡፡
‹‹ከእኔ ጋር ኢንግላንድ ትሄጃለሽ?›› ሲል ጠየቃት፡፡
ናንሲ ፈገግታዋ ከፊቷ ላይ ጠፋ፡፡ ‹‹ምን አልክ?››
‹‹ከእኔ ጋር ወደ ኢንግላንድ እንመለስ፡፡ ሆቴል ውስጥ ትቆያለሽ ወይም ቤት ትገዣለሽ ወይም አፓርትማ ትከራያለሽ››
ናንሲ ያቀረበላት ሃሳብ በጣም አስቆጣት፡፡ ጥርሷን በንዴት አፋጨች፡፡
‹‹አብደሃል እንዴ?›› አለችው፡፡ መርቪንን ፊት ለፊት ማየት ጠልታ
ፊቷን አዞረች፡፡ በእጅጉ አዘነችበት፡፡
መርቪን አባባሏ አስደነገጠው ግራ አጋባው፡፡ ‹‹ምነው?›› ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹እኔ አሜሪካ ውስጥ የራሴ ኑሮ፣ ቤት፣ ሁለት ልጆችና በሚሊዮንዐየሚቆጠር ዶላር ገቢ የሚያስገኝ ፋብሪካ አለኝ፡፡ አንተ እንዴት ይህን ሁሉ እርግፍ አድርጌ ትቼ በማንቼስተር ሆቴል እንድቀመጥ ትጠይቀኛለህ?››
‹‹ይህን ካልፈለግሽ ከእኔ ጋር ተጠቃለይ››
‹‹እኔ እኮ ባገሬ የተከበርኩ ሴት ነኝ እንደ ቅምጥ ልኖር አልችልም፡››
‹‹ይኸውልሽ ልንጋባ እንችላለን፤ ይህን አረጋግጥልሻለሁ፧ እኔ አሁን
በዚህ ደቂቃ ውስጥ እንድትወስኚ አይደለም የጠየቅሁሽ››
‹‹ይህ አይደለም ዋናው ነጥብ መርቪን›› አለች ‹‹እኔን የገረመኝ ሁሉን
ጣጥለሽ ተከትለሽኝ ኢንግላንድ ነይ ያልከኝ ነው፡፡››
‹‹ታዲያ እንዴት ነው አንድ ላይ ልንኖር የምንችለው?››
‹‹ታዲያ ጥያቄውን መጠየቅ ሲገባህ ወደ መልሱ ሄድክ››
‹‹አንድ መልስ ስላለ ብቻ ነው ይህን ያልኩት››
‹‹ሶስት መልሶች ናቸው ያሉት፤ አንተ እንዳልከው አንተን ተከትዬ ወደ
ኢንግላንድ መመለስ ወይም አንተ ወደ አሜሪካ መጥተህ ከእኔ ጋር መኖር
ወይም ሌላ ቦታ ለምሳሌ ቤርሙዳ እንኖራለን›› አለች፡፡
በአባባሏ አልተደሰተም፡፡ ‹‹አገሬ ጦርነት ላይ ነች፤ እኔም የድርሻዬን ማበርከት አለብኝ፤ ጦርነት ውስጥ ገብቼ ለመዋጋት እድሜዬ ቢያልፍም ለአየር ኃይሉ የአይሮፕላን ሞተሮች ሰርቼ አቀርባለሁ፡፡ በእዚህ መስክ ከእኔ የተሻለ እውቀት ያለው የለም፡፡ አገሬ በጣም ትፈልገኛለች››
አሁን ያላት ነገሩን አባባሰው፡ ‹‹ለምንድነው የእኔ አገር እኔን
እንደማትፈልገኝ አድርገህ የምታስበው?›› አለች እኔ የወታደር ጫማ አመርታለሁ፡፡ አሜሪካ ጦርነቱ ውስጥ ከገባች ብዙ የወታደሮች ጫማ
ያስፈልጋታል››
‹‹እኔ ማንቼስተር ውስጥ ፋብሪካ አለኝ››
‹‹እኔ ደግሞ ቦስተን ውስጥ ካንተ የበለጠ ፋብሪካ አለኝ››
‹‹ታዲያ ሴት እንደ ወንድ እኮ አይደለችም››
‹ሴት ከወንድ እንዴት ታንሳለች አንተ ጅል!›› ብላ ጮኸችበት፡፡
ጅል› ማለቷ ወዲያው ጸጸታት፡፡ ፊቱ ቅጭም ሲል ታያት፡፡ በጣም
እንዳበሳጨችው ገባት፡፡ ከወንበሩ ተነሳ፡፡ እንደከፋው እንዳይሄድ አንድ ነገር
ማለት ብትፈልግም ትክክለኛው ቃል አልመጣላት አለ፡፡ እሱም አፍታም ሳይቆይ ጥሏት ሄደ፡፡
ምን ማለቴ ነው? አለች ምርር ብሏት፡ አባባሉ ቢያበሳጭም ስላስከፋችው ደግሞ ተናደደች፡፡ በዚህ ሁኔታ እንዲርቃት አልፈለገችም ወዳዋለች፡ ወንዶችን ፊት ለፊት በመጋፈጥ ለውጥ ማምጣት እንደማይቻል
እያደር ገብቷታል፡፡ ወንዶች ከወንዶች በኩል
የሚመጣውን ጠብ ለምደውታል፡ ከሴቶች የሚመጣውን ግን መቀበል ይከብዳቸዋል፡፡ በንግድ
ስራዋ ላይ ከሰራተኞች የሚመጣ ችግር ሲገጥማት ድምጿን አለስልሳና
አለዝባ ትመልሳቸዋለች እንጂ አታካሮ አትገጥምም፡፡ አሁን ግን ያ ባህሪዋ ሸሽቷት በአስር ዓመት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ልቧን የወሰደውን ሰው
አበሳጭታ አባረረችው፡
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
ናንሲ ባህሩ ዳር ቁጭ ብላለች፡፡ መርቪን ላቭሴይ አጠገቧ ተቀምጧል፡፡
የባህሩ ውሃ በማዕበል እየተገፋ ይመጣል፣ ይመለሳል፡፡ ናንሲ ዓይኗን
ጨፍናለች፡ ሌሊት በደምብ አልተኛችም:: መርቪንና እሷ
እሷ ማታ መጋጨታቸው ትዝ አላትና ፈገግ አለች ከእሱ ጋር የምር ግንኙነት
አለመመስረቷ ደስ ብሏታል፡ ለወሲብ መቻኮሉ ጥሩ
አይደለም፡፡የመጣችበትን ዓላማ ከግብ ማድረስ አለባት፡፡
ሼዲያክ የዓሳ ማጥመጃ ፤መንደርና የባህር ዳር መዝናኛ ከተማ ናት፡፡
በባህሩ ዳርቻ ላይ የዓሳ
ማጥመጃ ጀልባዎች፣ መርከቦች፣ ሌሎች ሁለት
አይሮፕላኖችና እነሱ የመጡበት አይሮፕላን ይታያል፡፡ ብዙዎቹ የአይሮፕላኑ ተሳፋሪዎች በባህሩ ዳርቻ ላይ ወዲያ ወዲህ ይላሉ፡፡
ሁለት የፖሊስ መኪኖች እየበረሩ መጥተው ጎማቸውን ሲጢጥ
አድርገው ሲቆሙ የአካባቢው ፀጥታ ታወከ፡፡ ከመኪኖቹም ውስጥ ሰባት
ስምንት ያህል ፖሊሶች እየዘለሉ ወጡ፡፡ በቀጥታ ወደ ተሳፋሪዎቹ
ማስተናገጃ ሲያመሩ የሆነ ሰው ሊይዙ የመጡ ይመስላል›› አለች ናንሲ፡
እሱም በመስማማት ራሱን ነቀነቀና ‹‹ማንን ይሆን?›› አለ፡፡
‹‹ምናልባትም ፍራንኪ ጎርዲኖን››
‹ሊሆን አይችልም እሱ እንደሆነ እንደታሰረ ነው፡፡››
አይሮፕላን ውስጥ ሲገቡ ሁለቱ ወደ ባህሩ ዳርቻ ሲያመሩ ሁለቱ ደግሞ
ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ፖሊሶቹ ከመናኸሪያው ወጡና ሶስቱ መንደሩ ውስጥ መንጎራደድ ጀመሩ፡፡
ፖሊሶቹ የሆነ ሰው እንደሚፈልጉ ያስታውቅባቸዋል፡ አንዱ
የአይሮፕላኑ ሰራተኛ ከአይሮፕላኑ ሲወጣ አየችና ናንሲ ‹ፖሊሶቹ ማንን ነው የሚፈልጉት?›› ስትል ጠየቀች:
ሰውየው ምስጢር ለማውጣት እየተጠራጠረ ሄሪ ቫንዴርፖስት
የተባለውን ሰው ነው የሚፈልጉት፤ ስሙ የሀሰት ነው›› አለ፡፡
ናንሲ ግንባሯን ከሰከሰችና ይሄ ልጅ ከኦክሰንፎርድ ቤተሰብ ጋር ተቀምጦ የነበረው ነው፡ ልጁ የማርጋሬትን ልብ ሳይሰርቅ አልቀረም›› ስትል
ገመተች ናንሲ፡
መርቪን ‹‹ከአይሮፕላኑ ወጥቶ ሄዷል እንዴ? እኔ ከአይሮፕላኑ ሲወጣ
አላየሁትም›› አለ፡፡
‹‹እኔም አላስተዋልኩም›› አለች ናንሲ፡
‹‹ልጁ አጭበርባሪ ይመስላል››
‹‹እውነት?›› አለች ናንሲ፡ እሷ ልጁ ከጥሩ ቤተሰብ የተገኘ ነበር የመሰላት፡ ‹‹ጥሩ ባህሪ አይቼበታለሁ: ማርጋሬት ከልጁ ጋር ፍቅር ሳይዛት አልቀረችም፡፡ ፖሊስ እንደሚፈልገው ስታውቅ ታዝናለች›› አለች
‹‹ወላጆቿ ፖሊስ እጅ መውደቁ ደስ ሳያሰኛቸው አይቀርም›› አለ
መርቪን፡፡ናንሲ ስለወላጆቿ ግድ የላትም፡ በአይሮፕላኑ መብል ክፍል ውስጥ
ሎርድ ኦክሰንፎርድ ያሳዩት የነበረው ጋጠወጥ ባህሪ መርቪንና ናንሲ
ያስታውሳሉ፡ ለእንደዚህ አይነት ሰው ውርደት ሲያንሰው ነው ናንሲ ከእንደዚህ አይነት ወመኔ ጋር ማርጋሬት ፍቅር ስለያዛት አዘነችላት፡
መርቪንም ቀጠለና ‹‹እኔ ስለሌላ ሰው ማውራት አልፈልግም›› አለ፡
ናንሲ ጆሮዋን ቀሰረች፡
መርቪን ቀጠለና ‹‹የተገናኘነው ከጥቂት ሰዓታት በፊት ስለሆነ በደምብ ላውቅሽ እፈልጋለሁ፡›› ናንሲም እርግጠኛ መሆን አትችልም አንተ ደደብ አለች በሆዷ
ሆኖም ይህን ማለቱ አስደስቷታል፡ ምንም መልስ አልሰጠችውም፡፡
‹‹ብፊት አንቺን ኒውዮርክ አድርሼ ወደ ማንቼስተር መመለስ ነበር የማስበው፡፡ አሁን ግን አላደርገውም›› አላት፡
ናንሲ ፈገግ አለች ይህን እንዲል ነበር ስትጠብቅ የነበረው:፡ እጇን ሰደደችና እጁን ያዝ አደረገች፡፡ ‹‹ይህን ስላልክ ደስ ብሎኛል›› አለችው፡
‹‹ደስ ብሎሻል? ችግሩ ከዚህ በኋላ አትላንቲክን ማቋረጡ የሚቻል አይሆንም፡፡ የጦር መርከቦች ብቻ ናቸው ይህን ማድረግ የሚችሉት፡››ናንሲ በመስማማት ራሷን ነቀነቀች፡
አሁን ከተለያየን ምናልባትም የምንገናኘው ከብዙ ጊዜ በኋላ ነው፡፡።
እኔ ግን ላጣሽ አልፈልግም›› አለ መርቪን፡፡
‹‹እኔም እንደዚያው›› አለች ናንሲ፡፡
‹‹ከእኔ ጋር ኢንግላንድ ትሄጃለሽ?›› ሲል ጠየቃት፡፡
ናንሲ ፈገግታዋ ከፊቷ ላይ ጠፋ፡፡ ‹‹ምን አልክ?››
‹‹ከእኔ ጋር ወደ ኢንግላንድ እንመለስ፡፡ ሆቴል ውስጥ ትቆያለሽ ወይም ቤት ትገዣለሽ ወይም አፓርትማ ትከራያለሽ››
ናንሲ ያቀረበላት ሃሳብ በጣም አስቆጣት፡፡ ጥርሷን በንዴት አፋጨች፡፡
‹‹አብደሃል እንዴ?›› አለችው፡፡ መርቪንን ፊት ለፊት ማየት ጠልታ
ፊቷን አዞረች፡፡ በእጅጉ አዘነችበት፡፡
መርቪን አባባሏ አስደነገጠው ግራ አጋባው፡፡ ‹‹ምነው?›› ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹እኔ አሜሪካ ውስጥ የራሴ ኑሮ፣ ቤት፣ ሁለት ልጆችና በሚሊዮንዐየሚቆጠር ዶላር ገቢ የሚያስገኝ ፋብሪካ አለኝ፡፡ አንተ እንዴት ይህን ሁሉ እርግፍ አድርጌ ትቼ በማንቼስተር ሆቴል እንድቀመጥ ትጠይቀኛለህ?››
‹‹ይህን ካልፈለግሽ ከእኔ ጋር ተጠቃለይ››
‹‹እኔ እኮ ባገሬ የተከበርኩ ሴት ነኝ እንደ ቅምጥ ልኖር አልችልም፡››
‹‹ይኸውልሽ ልንጋባ እንችላለን፤ ይህን አረጋግጥልሻለሁ፧ እኔ አሁን
በዚህ ደቂቃ ውስጥ እንድትወስኚ አይደለም የጠየቅሁሽ››
‹‹ይህ አይደለም ዋናው ነጥብ መርቪን›› አለች ‹‹እኔን የገረመኝ ሁሉን
ጣጥለሽ ተከትለሽኝ ኢንግላንድ ነይ ያልከኝ ነው፡፡››
‹‹ታዲያ እንዴት ነው አንድ ላይ ልንኖር የምንችለው?››
‹‹ታዲያ ጥያቄውን መጠየቅ ሲገባህ ወደ መልሱ ሄድክ››
‹‹አንድ መልስ ስላለ ብቻ ነው ይህን ያልኩት››
‹‹ሶስት መልሶች ናቸው ያሉት፤ አንተ እንዳልከው አንተን ተከትዬ ወደ
ኢንግላንድ መመለስ ወይም አንተ ወደ አሜሪካ መጥተህ ከእኔ ጋር መኖር
ወይም ሌላ ቦታ ለምሳሌ ቤርሙዳ እንኖራለን›› አለች፡፡
በአባባሏ አልተደሰተም፡፡ ‹‹አገሬ ጦርነት ላይ ነች፤ እኔም የድርሻዬን ማበርከት አለብኝ፤ ጦርነት ውስጥ ገብቼ ለመዋጋት እድሜዬ ቢያልፍም ለአየር ኃይሉ የአይሮፕላን ሞተሮች ሰርቼ አቀርባለሁ፡፡ በእዚህ መስክ ከእኔ የተሻለ እውቀት ያለው የለም፡፡ አገሬ በጣም ትፈልገኛለች››
አሁን ያላት ነገሩን አባባሰው፡ ‹‹ለምንድነው የእኔ አገር እኔን
እንደማትፈልገኝ አድርገህ የምታስበው?›› አለች እኔ የወታደር ጫማ አመርታለሁ፡፡ አሜሪካ ጦርነቱ ውስጥ ከገባች ብዙ የወታደሮች ጫማ
ያስፈልጋታል››
‹‹እኔ ማንቼስተር ውስጥ ፋብሪካ አለኝ››
‹‹እኔ ደግሞ ቦስተን ውስጥ ካንተ የበለጠ ፋብሪካ አለኝ››
‹‹ታዲያ ሴት እንደ ወንድ እኮ አይደለችም››
‹ሴት ከወንድ እንዴት ታንሳለች አንተ ጅል!›› ብላ ጮኸችበት፡፡
ጅል› ማለቷ ወዲያው ጸጸታት፡፡ ፊቱ ቅጭም ሲል ታያት፡፡ በጣም
እንዳበሳጨችው ገባት፡፡ ከወንበሩ ተነሳ፡፡ እንደከፋው እንዳይሄድ አንድ ነገር
ማለት ብትፈልግም ትክክለኛው ቃል አልመጣላት አለ፡፡ እሱም አፍታም ሳይቆይ ጥሏት ሄደ፡፡
ምን ማለቴ ነው? አለች ምርር ብሏት፡ አባባሉ ቢያበሳጭም ስላስከፋችው ደግሞ ተናደደች፡፡ በዚህ ሁኔታ እንዲርቃት አልፈለገችም ወዳዋለች፡ ወንዶችን ፊት ለፊት በመጋፈጥ ለውጥ ማምጣት እንደማይቻል
እያደር ገብቷታል፡፡ ወንዶች ከወንዶች በኩል
የሚመጣውን ጠብ ለምደውታል፡ ከሴቶች የሚመጣውን ግን መቀበል ይከብዳቸዋል፡፡ በንግድ
ስራዋ ላይ ከሰራተኞች የሚመጣ ችግር ሲገጥማት ድምጿን አለስልሳና
አለዝባ ትመልሳቸዋለች እንጂ አታካሮ አትገጥምም፡፡ አሁን ግን ያ ባህሪዋ ሸሽቷት በአስር ዓመት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ልቧን የወሰደውን ሰው
አበሳጭታ አባረረችው፡
👍19
#ታምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////
‹‹ግን ምን አይነት ዳቢሎስ ነሽ..?››ሙትት ባለ ድምጽ
‹‹ዳቢሎስ እንኳን አይደለሁም…. ምን አልባት የዳቢሎስ ልጅ ልሆን እችላለሁ…ግን የምትወዳትን ልጅ ላድንልህ እኮ ነው እያልኩህ ያለሁት .. ..?እንደዚህ አይነት በጎ ተግባር ዳቢሎስ ያሰኛል እንዴ..?››
‹‹አዎ ዳቢሎስ ፍቅር አያውቅም..ፍቅር የማያውቅ ደግሞ ምንም ነገር በነፃ መስጠት አይችልበትም፤ለሰጠሸ ጥሩ የሚመስል ነገር ሁሉ ተመጣጣኝ የሆነ መከራና ስቃይ ያስከፍሉሻል…››
‹‹አልገባኝም..?››
‹‹ለምሳሌ …ያለፋሽበትን ገንዘብ ተመኝተሸ ስጠኝ ብትይው በደስታ ነው የሚሰጥሽ፤የገንዘብን ባለቤት ግደይና ነጥቀሺው ውስጂ ብሎ መንገድን እና ብልሀቱን ያሳይሻል…ከዛ ትገድይና ገንዘብን ታገኚያለሽ ሀብታም እና በፀፀት የሚሰቃይ ሰው ትሆኚያለሽ፡፡አንቺም ፍቅረኛህን ላድንልህ..እና ልንጠቅህ እያልሺኝ ነው…፡፡ያው እኮ ነው በስጋ ከመሞት ታድኛታለሽ ከዛ ፍቅርን በመንጠቅ በመንፈስ ትገያታለሽ…እኔንም እንደዛው፤ታዲያ አንቺ ዳቢሎስ ካልሆንሽ ማን ይሆናል....?››አላት ምርር ባለ የመጠየፍ ንግግር፡
‹‹እሺ እንግዲያው ይቅርብህ…ሁለተኛ አረብሽህም፤ደህና ሁን››ብላ ከመቀመጫዋ ተነሳችና እንደ አመጣጧ ሳሎኑን ሰንጥቃ በርፍን ከፍታ ወጣች እና መልሳ ዘግታ መንገዶን ቀጠለች…የግቢው አማካይ ስፍራ ስትደርስ ነበር የበር መከፈት እና ‹‹ማን ነበር ስምሽ..?››የሚል ከሙታን መንፈስ የወጣ የሚመስል ድምጽ ከጀርባዋ የተሰማው
እርምጃዋን ገታችና ቀኝ ኋላ ዞራ ‹‹ሶፊያ››ስትል መለሰችለት
‹‹ከቻልሽ አድርጊው..አድኚልኝ ፤ተስማም..ቼ…ያ….ለሁ››አላትና ከእሷ ምንም አይነት መልስ ሳይጠብቅ ፊቱን መልሶ ወደውስጥ በመግባት በራፉን በመዝጋት ከእይታዋ ተሰወረ ..
‹‹እውነትም ዳቢሎስ ነገር ነኝ እንዴ..?….ምን እያረግኩ ነው…...?››ስትል አሰበች፡፡ቅድም እዚህ እሱ ጋር ስትመጣ ይሄንን ለማድረግ አልነበረም…ዝም ብላ ፍቅረኛው እደምታድንለት ልትነግረው እና በተስፋ ልታስፈነጥዘው ብቻ ነበር ፍላጎቷ…ያደረገችው ግን ተቃራኒውን ነው..በደስታ እና ሀዘን መካከል ነፍሱ ተንጠልጥላ እዲሰቃይ ፈረደችበት …
‹‹የእውነት ግን ያልኩትን አደርገዋለሁ…..?እሷን አድኜ እሱን ነጥቄያት አገባዋለሁ…..?.ማግባትስ በእውነት እኔ የምፈልገው ነገር ነው....?ወይስ በስቃዩ ለመደሰት…..?››ብላ ተደራራቢ ጥያቄ እራሷን ጠየቀች፡
ለማንኛውም ዛሬ ማታ ከንስሯ ጋር ለመብረር አቅዳለች….ለልጅቷ የሚሆን መድሀኒት የት እደሚገኝ ፍንጩን አግኝታለች ….ቦረና ባሌ መካከል መዳ ወላቡ አካባቢ ነው ለሰሚራ ፈውስ የሚሆነው መድሀኒት ሚገኘው….፡፡
የየትኛውም ሀገር አቨዬሽን የማይቆጣጠረው በረራ ላይ ነች፡፡ግን ደህንነቱ ፍፅም የተረጋገጠ በረራ ….ከየትኛውም አይሮፕላን ጋር እጋጫለሁ ወይም አሞራና ወፎች ተላትመውብን አቅጣጫ ያስቀይሩናል…ነዳጅ አልቆ ወይም ሞተር ጠፍቶ ችግር ላይ እንወድቃለን ብላ የማትሰጋበት ዥዋዝዌ የመጫወት ያህል ዘና የሚያደርግ በረራ…. ይሄን አይነት በረራ ሳታካሂድ ሶስት ወራት ስላለፋት ናፍቆት ነበር…
እየሄድ ያለው ከአዲስ አበባ ወደ መዳወላቡ ነው ፡፡መዳወላቡ የት እንደምትኝ መገመት ካቃታችሁ..ኬንያ ድንበር አካባቢ ብትሉት አካባውን ለመገመት ይቀላችኋል ፡፡እየበረሩን ያለነው ከንስሯ ጋር ነው…፡፡እሱ ክንፎች መሀከል ዘና ብሎ ቁጭ ብላለች….
ከመሬት ያሉበትንን ከፍታ ገምታ ለመናገር አትችልም ..…ግን ትንሽ ግልፅ ለማድረግ ምሳሌ ለመስጠት ያህል በዚህ ሰዓት ( ከምሽቱ ሶስት ሰዓት አካባቢ ነው) ሻሸመኔ ከተማ አካባቢ ደርሰዋል..እላይ ባሉበት ከፍታ ላይ ሆነው ከተማዋ ቁልቁል ስያዮት ከእሷ ቤት ጊቢ ብዙም ሰፍታ አይታያትም….ጭልጭል የሚሉ አንድ ቦታ የተሰበሰቡ መብራቶች ናቸው እንደምልክት የሚታዩት..
የሚፈልገበት ቦታ ላይ ከምሽቱ አራት ሰዓት አካባቢ ነው የደረሱት…ከአውሬ ድምጽ እና ከጥቅጥቅ ጨለማ በተጨማሪ ብዙ ድምጽ ይሰማል..የደረቁ ቅጠሎች በንፋስ ተገፍተው ከዛፍ ሲወድቁ ይሰማል…..ካረፍበት ተራራ ወገብ ላይ እየፈለቀ ቁልቁል ወደ ታች እየተምዘገዘገ የሚወርድው አረፋ ደፋቂ ፏፏቴ ድምጽ በጣም ይሰማል…የብዙ አውሬዎች መጣራራት እና ማስካካተ ድምጽ ይሰማል…. ….
‹‹የቱ ነው መድሀኒቱ….?››ጠየቀችው ንስሯን
አንድ ከእሷ ቁመት ብዙም የማትበልጥ ቋጥኝ ላይ ዘና ብሎ ቁጭ በማለት ዝም አለት
የሚያስበውን ማወቅ ስለፈለገች..‹‹አዕመሮህን ክፈትልኝ…..….?››ስትል ጠየቀችው… ቁልፍ አደረገና ችላ አለት ..አንዳንዴ እንዲህ ግግም ብሎ ያስቸግራታል..
‹‹ምን እያሰብክ ነው… ….?ለሊቱን እዚሁ ጫካ ውስጥ ከአውሬ ጋር እናሳልፍ እንዴ…….?››ጠየቀችው
አዕምሮው ውስጥ ሰርስሯ እንዳትገባ እንደከረቸመባት በሹፈት መልክ አንገቱን አሸከረከረባትና ጀርባውን ሰጣት…በቃ ምንም ማድረግ አልችለችም …እስኪለቀው ድረስ መጠበቅ እንዳለባት ስለተረዳች እራሷን አረጋጋች..የሆነ የሚጠብቀው ወይም ለጊዜው ያልጣመው ነገር አለ ማለት ነው ስትል አሰበች..ተወችውና አካባቢውን በመቃኘት ዘና ማለት ጀመረች..
ጥቅጥቅ ያለውን ጫካ ስታይ.. በአካባቢው በቅርብ ርቀት ከሚገኙ የገጠር መንደሮች ጭል ጭል የሚሉትን የኩራዝና የፍኖስ መብራቶችን ..ወደ ላይ አንጋጣ የዘወትር አጫዋቾን ጨረቃን ስትመለከት ሰዓቱ ከምሽቱ አምስት ሰዓት ሆነ …ንስሯ ፀባይ ላይ ምንም የተለወጠ ነገር የለም …አሁንም የነበረበት ቋጥኝ ላይ በተመስጦ… አረ እንደውም የፀሎት በሚመስል ሁኔታ ያለእንቅስቃሴ አንገቱን ወደጨረቃዋ አንጋጦ ተደምሟል ..
የተቀመጠችበት የወደቀ የግንድ ጉማጅ ቂጧን ስላሳመመት ተነሳችና ቀስ እያለች እሾህ እንዳይቧጭራ እና አውሬ ጉድጋድ ውስጥ ተንሸራታ እንዳትገባ እየተጠነቀቀች ወደ ፏፏቴው ተራመደች… እንደደረሰች ሙሉ ልብሷን ፓንቷንም ሳታስቀር ውልቅልቅ አድርጋ ገባችበት… ፏፏቴው ከላይ ከአለቱ እየተላተመ መቶ ጭንቅላቷ ላይ ሲያርፍ ያለውን ኃይል መቋቋም አቅቶት ልትወድቅ ነበር.. ለጥቂት ነው በአቅራቢያዋ የጋጠማትን የግንድ ቅርንጫፍ ይዛ የተረፈችው‹‹..ደግሞ ውሀው እንዴት አባቱ ይሞቃል…….?››አለችና ድክም እስኪላት ድረስ ሰውነቷን እየተገለባበጠች አስመታችውና ወጥታ ልብሷን ለብሳ ወደ ንስሯ ተመለሰች፡፡
ስሩ እንደደረሰች ከፊት ለፊቱ ቆማ በትኩረት አየችው…መልኩ ተለየባት… የሆነ አመድ ላይ የተንከባለለ አህያ መስሏል..እንዴ ምን ላይ ተንከባሎ ነው….?..እዚህ ሰውነት ላይ ነው እንዴ ተጭኜ የመጣሁት…….?ነው ወይስ እኔ ውሀ ውስጥ ሳለው የሆነ ነገር ከሰማይ አመድ ነፋበት..….?አረ አመድ ብቻ አይደለምል አንገቱንም መሸከም አቅቶታል…››ስለንስሷ ቴና ሀሳ ገብቷት መነብሰልሰል ጀመረች
‹‹ምን ሆንክ….?››
አዕምሮውን ቀስ እያለ ከፈተላት፡፡እሷም እንደምንም እራሷን ለማረጋጋት ሞከረችና ወደአዕምሮው ገባች…አዎ መድሀኒቷን አየቻት …እሷ ካለችበት በ5 ሜትር ያህል ርቀት ላይ ትገኛለች…የተለየች አይነት ልዩ ተክል ነች ….?የአንድ ሰው የማህል ጣትን ነው የምታክለው…የበቀለችው ሌላ ትልቅ የብሳና ዛፍ ላይ ጥገኛ ሆና ነው….የሆነ ሀመራዊ አይነት የተለየ ብርሀን ትረጫለች…
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////
‹‹ግን ምን አይነት ዳቢሎስ ነሽ..?››ሙትት ባለ ድምጽ
‹‹ዳቢሎስ እንኳን አይደለሁም…. ምን አልባት የዳቢሎስ ልጅ ልሆን እችላለሁ…ግን የምትወዳትን ልጅ ላድንልህ እኮ ነው እያልኩህ ያለሁት .. ..?እንደዚህ አይነት በጎ ተግባር ዳቢሎስ ያሰኛል እንዴ..?››
‹‹አዎ ዳቢሎስ ፍቅር አያውቅም..ፍቅር የማያውቅ ደግሞ ምንም ነገር በነፃ መስጠት አይችልበትም፤ለሰጠሸ ጥሩ የሚመስል ነገር ሁሉ ተመጣጣኝ የሆነ መከራና ስቃይ ያስከፍሉሻል…››
‹‹አልገባኝም..?››
‹‹ለምሳሌ …ያለፋሽበትን ገንዘብ ተመኝተሸ ስጠኝ ብትይው በደስታ ነው የሚሰጥሽ፤የገንዘብን ባለቤት ግደይና ነጥቀሺው ውስጂ ብሎ መንገድን እና ብልሀቱን ያሳይሻል…ከዛ ትገድይና ገንዘብን ታገኚያለሽ ሀብታም እና በፀፀት የሚሰቃይ ሰው ትሆኚያለሽ፡፡አንቺም ፍቅረኛህን ላድንልህ..እና ልንጠቅህ እያልሺኝ ነው…፡፡ያው እኮ ነው በስጋ ከመሞት ታድኛታለሽ ከዛ ፍቅርን በመንጠቅ በመንፈስ ትገያታለሽ…እኔንም እንደዛው፤ታዲያ አንቺ ዳቢሎስ ካልሆንሽ ማን ይሆናል....?››አላት ምርር ባለ የመጠየፍ ንግግር፡
‹‹እሺ እንግዲያው ይቅርብህ…ሁለተኛ አረብሽህም፤ደህና ሁን››ብላ ከመቀመጫዋ ተነሳችና እንደ አመጣጧ ሳሎኑን ሰንጥቃ በርፍን ከፍታ ወጣች እና መልሳ ዘግታ መንገዶን ቀጠለች…የግቢው አማካይ ስፍራ ስትደርስ ነበር የበር መከፈት እና ‹‹ማን ነበር ስምሽ..?››የሚል ከሙታን መንፈስ የወጣ የሚመስል ድምጽ ከጀርባዋ የተሰማው
እርምጃዋን ገታችና ቀኝ ኋላ ዞራ ‹‹ሶፊያ››ስትል መለሰችለት
‹‹ከቻልሽ አድርጊው..አድኚልኝ ፤ተስማም..ቼ…ያ….ለሁ››አላትና ከእሷ ምንም አይነት መልስ ሳይጠብቅ ፊቱን መልሶ ወደውስጥ በመግባት በራፉን በመዝጋት ከእይታዋ ተሰወረ ..
‹‹እውነትም ዳቢሎስ ነገር ነኝ እንዴ..?….ምን እያረግኩ ነው…...?››ስትል አሰበች፡፡ቅድም እዚህ እሱ ጋር ስትመጣ ይሄንን ለማድረግ አልነበረም…ዝም ብላ ፍቅረኛው እደምታድንለት ልትነግረው እና በተስፋ ልታስፈነጥዘው ብቻ ነበር ፍላጎቷ…ያደረገችው ግን ተቃራኒውን ነው..በደስታ እና ሀዘን መካከል ነፍሱ ተንጠልጥላ እዲሰቃይ ፈረደችበት …
‹‹የእውነት ግን ያልኩትን አደርገዋለሁ…..?እሷን አድኜ እሱን ነጥቄያት አገባዋለሁ…..?.ማግባትስ በእውነት እኔ የምፈልገው ነገር ነው....?ወይስ በስቃዩ ለመደሰት…..?››ብላ ተደራራቢ ጥያቄ እራሷን ጠየቀች፡
ለማንኛውም ዛሬ ማታ ከንስሯ ጋር ለመብረር አቅዳለች….ለልጅቷ የሚሆን መድሀኒት የት እደሚገኝ ፍንጩን አግኝታለች ….ቦረና ባሌ መካከል መዳ ወላቡ አካባቢ ነው ለሰሚራ ፈውስ የሚሆነው መድሀኒት ሚገኘው….፡፡
የየትኛውም ሀገር አቨዬሽን የማይቆጣጠረው በረራ ላይ ነች፡፡ግን ደህንነቱ ፍፅም የተረጋገጠ በረራ ….ከየትኛውም አይሮፕላን ጋር እጋጫለሁ ወይም አሞራና ወፎች ተላትመውብን አቅጣጫ ያስቀይሩናል…ነዳጅ አልቆ ወይም ሞተር ጠፍቶ ችግር ላይ እንወድቃለን ብላ የማትሰጋበት ዥዋዝዌ የመጫወት ያህል ዘና የሚያደርግ በረራ…. ይሄን አይነት በረራ ሳታካሂድ ሶስት ወራት ስላለፋት ናፍቆት ነበር…
እየሄድ ያለው ከአዲስ አበባ ወደ መዳወላቡ ነው ፡፡መዳወላቡ የት እንደምትኝ መገመት ካቃታችሁ..ኬንያ ድንበር አካባቢ ብትሉት አካባውን ለመገመት ይቀላችኋል ፡፡እየበረሩን ያለነው ከንስሯ ጋር ነው…፡፡እሱ ክንፎች መሀከል ዘና ብሎ ቁጭ ብላለች….
ከመሬት ያሉበትንን ከፍታ ገምታ ለመናገር አትችልም ..…ግን ትንሽ ግልፅ ለማድረግ ምሳሌ ለመስጠት ያህል በዚህ ሰዓት ( ከምሽቱ ሶስት ሰዓት አካባቢ ነው) ሻሸመኔ ከተማ አካባቢ ደርሰዋል..እላይ ባሉበት ከፍታ ላይ ሆነው ከተማዋ ቁልቁል ስያዮት ከእሷ ቤት ጊቢ ብዙም ሰፍታ አይታያትም….ጭልጭል የሚሉ አንድ ቦታ የተሰበሰቡ መብራቶች ናቸው እንደምልክት የሚታዩት..
የሚፈልገበት ቦታ ላይ ከምሽቱ አራት ሰዓት አካባቢ ነው የደረሱት…ከአውሬ ድምጽ እና ከጥቅጥቅ ጨለማ በተጨማሪ ብዙ ድምጽ ይሰማል..የደረቁ ቅጠሎች በንፋስ ተገፍተው ከዛፍ ሲወድቁ ይሰማል…..ካረፍበት ተራራ ወገብ ላይ እየፈለቀ ቁልቁል ወደ ታች እየተምዘገዘገ የሚወርድው አረፋ ደፋቂ ፏፏቴ ድምጽ በጣም ይሰማል…የብዙ አውሬዎች መጣራራት እና ማስካካተ ድምጽ ይሰማል…. ….
‹‹የቱ ነው መድሀኒቱ….?››ጠየቀችው ንስሯን
አንድ ከእሷ ቁመት ብዙም የማትበልጥ ቋጥኝ ላይ ዘና ብሎ ቁጭ በማለት ዝም አለት
የሚያስበውን ማወቅ ስለፈለገች..‹‹አዕመሮህን ክፈትልኝ…..….?››ስትል ጠየቀችው… ቁልፍ አደረገና ችላ አለት ..አንዳንዴ እንዲህ ግግም ብሎ ያስቸግራታል..
‹‹ምን እያሰብክ ነው… ….?ለሊቱን እዚሁ ጫካ ውስጥ ከአውሬ ጋር እናሳልፍ እንዴ…….?››ጠየቀችው
አዕምሮው ውስጥ ሰርስሯ እንዳትገባ እንደከረቸመባት በሹፈት መልክ አንገቱን አሸከረከረባትና ጀርባውን ሰጣት…በቃ ምንም ማድረግ አልችለችም …እስኪለቀው ድረስ መጠበቅ እንዳለባት ስለተረዳች እራሷን አረጋጋች..የሆነ የሚጠብቀው ወይም ለጊዜው ያልጣመው ነገር አለ ማለት ነው ስትል አሰበች..ተወችውና አካባቢውን በመቃኘት ዘና ማለት ጀመረች..
ጥቅጥቅ ያለውን ጫካ ስታይ.. በአካባቢው በቅርብ ርቀት ከሚገኙ የገጠር መንደሮች ጭል ጭል የሚሉትን የኩራዝና የፍኖስ መብራቶችን ..ወደ ላይ አንጋጣ የዘወትር አጫዋቾን ጨረቃን ስትመለከት ሰዓቱ ከምሽቱ አምስት ሰዓት ሆነ …ንስሯ ፀባይ ላይ ምንም የተለወጠ ነገር የለም …አሁንም የነበረበት ቋጥኝ ላይ በተመስጦ… አረ እንደውም የፀሎት በሚመስል ሁኔታ ያለእንቅስቃሴ አንገቱን ወደጨረቃዋ አንጋጦ ተደምሟል ..
የተቀመጠችበት የወደቀ የግንድ ጉማጅ ቂጧን ስላሳመመት ተነሳችና ቀስ እያለች እሾህ እንዳይቧጭራ እና አውሬ ጉድጋድ ውስጥ ተንሸራታ እንዳትገባ እየተጠነቀቀች ወደ ፏፏቴው ተራመደች… እንደደረሰች ሙሉ ልብሷን ፓንቷንም ሳታስቀር ውልቅልቅ አድርጋ ገባችበት… ፏፏቴው ከላይ ከአለቱ እየተላተመ መቶ ጭንቅላቷ ላይ ሲያርፍ ያለውን ኃይል መቋቋም አቅቶት ልትወድቅ ነበር.. ለጥቂት ነው በአቅራቢያዋ የጋጠማትን የግንድ ቅርንጫፍ ይዛ የተረፈችው‹‹..ደግሞ ውሀው እንዴት አባቱ ይሞቃል…….?››አለችና ድክም እስኪላት ድረስ ሰውነቷን እየተገለባበጠች አስመታችውና ወጥታ ልብሷን ለብሳ ወደ ንስሯ ተመለሰች፡፡
ስሩ እንደደረሰች ከፊት ለፊቱ ቆማ በትኩረት አየችው…መልኩ ተለየባት… የሆነ አመድ ላይ የተንከባለለ አህያ መስሏል..እንዴ ምን ላይ ተንከባሎ ነው….?..እዚህ ሰውነት ላይ ነው እንዴ ተጭኜ የመጣሁት…….?ነው ወይስ እኔ ውሀ ውስጥ ሳለው የሆነ ነገር ከሰማይ አመድ ነፋበት..….?አረ አመድ ብቻ አይደለምል አንገቱንም መሸከም አቅቶታል…››ስለንስሷ ቴና ሀሳ ገብቷት መነብሰልሰል ጀመረች
‹‹ምን ሆንክ….?››
አዕምሮውን ቀስ እያለ ከፈተላት፡፡እሷም እንደምንም እራሷን ለማረጋጋት ሞከረችና ወደአዕምሮው ገባች…አዎ መድሀኒቷን አየቻት …እሷ ካለችበት በ5 ሜትር ያህል ርቀት ላይ ትገኛለች…የተለየች አይነት ልዩ ተክል ነች ….?የአንድ ሰው የማህል ጣትን ነው የምታክለው…የበቀለችው ሌላ ትልቅ የብሳና ዛፍ ላይ ጥገኛ ሆና ነው….የሆነ ሀመራዊ አይነት የተለየ ብርሀን ትረጫለች…
👍71❤12😁1
#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
እሁድ ቀን ነው 8 ሰአት ከካባቢ ደደፎ እንግዳ ይዞ ቤት መጣ፤ምን ዓይነት እንግዳ መሰለህ ? ... የሚያስጠላ ቀፋፊ ድምፅ ያላት፤ሾካካ አረማመድ የምትራመድ፤ባለ ሻካራ ድምፅ ሴት፡፡ ምን አልባት ያልኳትን አይነት ሴት ላትሆን ትችላለች፤በወቅቱ ለእኔ የተሰማኝ ግን እንደዛ ዓይነት ሴት እንደሆነች ነበር፡፡››
‹‹ኪያ ተዋወቂያት ፀዳለ ትባላለች..ፀዳለ እሷ ደግሞ ጽዮን ትባላለች እህቴ ነች፡፡ ››አላት፡፡
‹‹ተዋወቅንና ቁጭ አሉ…ውይ ኪያ ሳልነግርሽ ….ከፀዳለ ጋር አንድ መስሪያ ቤት ነው
የምንሰራው አሁን ግን….››ብሎ ንግግሩን አንጠልጥሎ ተወው፡
እኔም የልጅቷን ድምጽ ከሰማሁበት ደቂቃ ጀምሮ የሆነ ቅፍፍ ብሎኛልና‹‹አሁን ግን ምን…?››ብዬ ጠየቅኩት፡፡
‹‹ፍቅረኛዬ ሆናለች….እሺ ካለቺኝ በቅርብ እንጋባና ትቀላቀለናለች፡፡››አለኝ፡፡
መሀከል ወለል ላይ ቆሜ ነበር የሚያወራውን ሳዳምጥ የነበረው ... ወዲያው ግን ብዥ አለብኝ...ልቤን ሲያጥወለውለኝ ወደ ጓዳ ለመግባት ቀኝ እግሬን አነሳሁና መልሼ መሬት ለማሳረፍ ስሞክር መሬቱ የጥልቅ ገደል ያህል በኪሎ ሜትሮች ራቀብኝ፡፡ከዛ ዥው ብዬ ወደ ኃላዬ እየወደቅኩ ሳለ ደፎ ተንደርድሮ ከመሬቱ ከመላተሜ በፊት ሲታደገኝ..ከዛ ማንነቴም ሲጠፋኝ፡፡
ከደቂቃዎች በኃላ ስነቃ ደደፎ በድንጋጤ በፎጣ ውሃ እየነከረ እራሴን ልቤን ሲያቀዘቅዝልኛል ሴትዬዋ በዛ ቀፋፊ ድምጿ < አይዞህ ይሻላታል …አትደንግጥ፡፡›› እያለች ስታፅናናው ሰማሁ ፡፡ የእሷን ድምጽ
የማልሰማበት የት ልሂድ....? ደሞ ያበሳጨኝ የእኔ መታመም ሳይሆን የእሱ ለእኔ መጨነቅ ስላስጨነቃት ነበር ፡፡ እንደምንም አንደበቴን አላቅቄ‹‹.. ደፍ ሰላም ነኝ እራሴን ስላመመኝ ትንሽ ልተኛበት ..ይተወኛል› አልኩት፡፡
በመናገሬ ደስ እያለው ብርድልብሱን አለባበሰኝና ያቺን ባለቀፋፊ ድምፅ ሴት
ከመኝታ ቤት ይዞልኝ ወጣ፡፡እኔም የምፈልገው
እሱን ነበር፡፡ግን ምን ነካኝ….?የእሱ ፍቅረኛ
መያዝ እኔን እራሴን እስክስት ድረስ እንዴት
ሊያደርሰኝ ቻለ... ? ለእኔ ወንድሜ አይደል እንዴ..?አይደለም፡፡ ለእኔ ዘመዴ አይደለ እንዴ….? አይደለም፤እና አፈቅረዋለው ማለት ነው...?. መጠርጠሩስ፡፡ በቃ የልቤን ጥያቄ እና የአዕምሮዬን መልስ ስሰማ ሰማይ ምድሩ
ተደበላለቀብኝ፤ምን ይሻለኛል….?እንዴት ነው
ለዓመታት እሱን አቅፌ የሰላም እንቅልፍ
በተኛሁበት አልጋ ላይ ሌላ ሴት መጥታ እኔን
ሳሎን ወዳለው ፍራሽ ላይ ወርውራኝ እሷ እሱን
አቅፋ የምትተኛው…? በፍፅም አይሆንም፡፡
ይሄንን ቤት ለቅቄ መውጣት አለብኝ…? ወጥቼ ወዴት ነው የምሄደው? አለሜ ጠቅላላ ..ዘመዴ መሸሸጊያ እሱው ነው፡፡ ቢሆንም እሱን ከሌላ ሴት ጋር እያየሁ መኖር አልችልም ::
መቻል አለብሽ... እሱ እኮ እንደ ታናሽ እህቱ አይቶሽ ነው በህይወቱ ሙሉ ሲንከባከብሽ የኖረው ፡፡ታዲያ ውለታውን እንዲህ ነው እንዴ የምትመልሺው..… ?ዕድሜሽን በሙሉ ያንን ሁሉ በምንም የማይለካ ደስታ ሲመግብሽ ቆይቶ ዛሬ አንቺ ውለታውን እንዲህ ነው የምትመልሺው...? የእሱ ደስታ እንዴት ነው እንዲህ ሊያበሰጭሽ የቻለው..? እስከመቼ ሳያፈቅር እና ሳያገባ ላንቺ ሲል ተቆራምዶ ይኖራል…?››አይምሮዬና ልቤ ጦርነት ጀመሩ ግን ቆረጥኩ… በቃ፡፡
ቢያንስ አሁን ትልቅ ሰው ነኝ.. ከአያቴ ቤት ኪራይ ለዓመታት የተጠራቀመልኝ 5ዐሺ ብር ባንክ ቤት አለኝ ፤ በዛ ላይ ከቸገረኝ የአያቴን ቤት እሸጠዋለሁ፡፡ያ ደግሞ ትምህርቴን እስክጨርስ በርግጠኝነት ይበቃኛል.. ለጊዜው
የሚከራይ ቤት እስካገኝ ጓደኞቼ ጋር አርፋለሁ ፡፡ከዚህ ቤት ግን ዛሬውኑ መልቀቅ አለብኝ፡፡ አዎ አሁን ሊሸኛት ሄዷል ፤ ከመምጣቱ በፊት መፍጠን አለብኝ > አልኩና ከተኛሁበት ተነስቼ ሻንጣዬን በዳበሳ ፈለግኩና ፊት ለፊት ያገኘሁትን እና መሰብሰብ የቻልኳቸውን የእኔ የሆኑ እቃዎችን ከታተትኩና ሻንጣዬን በአንድ እጅ የገንዘብ ቦርሳዬን በትከሻዬ፤ ዘንጌን በሌላው እጄ ይዤ ከመኝታ ቤት አልፌ የሳሎኑን ደጃፋ በጥበብ ተሸግሬ ቤቱን ሙሉ በሙሉ ለቅቄ ልወጣ ስል‹‹እንዴ ወዴት ነው?››የሚለው የደደፎ ድምጽ አንዱን እገሬን በአየር ላይ ተንከርፍፎ እንዲቀር አደረገው፡፡ ተንደርድሮ መጣና ክንዴን አጥብቆ ያዘኝ፡፡
‹‹ኪያ ምን እየሰራሽ ነው?›› ሲጠይቀኝ ሰውነቱ ሁሉ እየተንቀጠቀጠ እንደሆነ በያዘኝ እጆቹ ንዝረት ተረዳሁ፤ አሳዘነኝ፡፡
‹‹ንገሪኝ እንጂ የት ነው?››
‹‹በቃ ልታገባ አይደል እንዴ? ቤቱን ልለቅልህ ነዋ፡፡››
በጥፊ አላሰኝ... አቤት የደነገጥኩት ድንጋጤ ..አቤት የተደሰትኩት መደሰት..አቤት የተሰማኝ ቅብዥርዥር ስሜት፡፡ ከተዋወቅንበት ቀን አንስቶ እንኳን ሊመታኝ ክፉ ቃል እንኳን ተናግሮኝ አያውቅም ...የደነገጥኩት ለዛ ነው፡፡ የተደሰትኩት ደግሞ የመታኝ ስለሚፈልገኝ ነው የሚል ስሜት ስለተሰማኝ ነበር፡፡ከዛ ቦርሳውንም ሻንጣውንም ነጥቆኝ እየገፈተረ ወደ ውስጥ አስገባኝ እና ወንበር ላይ ገፍትሮ አስቀመጠኝ..››
‹‹እየሰማኸኝ ነው አይደል ታዲ?››
‹‹በጣም እየሰማሁሽ ነው.፡፡ በሰው ወሬ መካከል እሺ ..ከዛስ ..ምናምን ማለት ስለማልወድ ነው..፡፡››
ከዛ እየተንዘረዘረ‹‹እኔ አንቺን ከቤት አስወጥቼ ነው ሚስት የማገባው?እንዴት እንዴት ነው የምታስቢው…? በቀላሉ እንድታገባ አልፈልግም አትይኝም?››
‹‹እንድታገባ አልፈልግም ብልህ እሺ ትለኛለህ?››
‹‹በትክክል እልሻለው፡፡››
‹‹እንግዲያው እንድታገባ አልፈልግም..አንተን ከሌላ ሴት ጋር እንዳይህ ፈጽሞ አልፈልግም››አልኩት፡፡ ፀጥ አለኝ ፡፡ ፀጥታው አስር ለሚሆኑ ደቂቃዎች ነው የቆየው... ግን የአስር ሺ አመትን ያህል ርዝመት ነበረው፡፡ ግራ የሚያጋባ የሚያስደነግጥ ፀጥታ….ነፍስን የሚያፍን ፀጥታ እንደምንም ያለኝን ጉልበት አጠራቅሜ‹‹ይሄው አላልኩህም… እሺ አትልም አላልኩህም .. ?እኔ እዚህ ቤት መኖር አልፈልግም በቃ…››ተንጣጣሁበት፡፡
‹‹ባክሽ ዝም በይ፤እሺ ብዬሻለሁ፤በቃ ትቼያታለሁ፡፡ ፍቅረኛዬም እንዳልሆነች
እንደማላገባትም ነገ እነግራታለሁ...አሁን ለምቦጭሽን አትጣይብኝ፡፡›› አለኝ፡፡
ከተቀመጥኩበት ተንደርድሬ በመነሳት ተጠምጥሜበት ልስመው ስል አንድ ኩርሲ ነገር አደናቀፈኝና ልዘረገፍ ስል በአየር ላይ ተቀበልኝ ...በአንድ ቀን ለሁለተኛ ጊዜ ከመፈጥፈጥ ታደገኝ፡፡ ለዛም ምስጋና እንዲሆንልኝ ወደራሴ ጎትቼ ጉንጩን ሳምኩት…፡፡
ከዛ .... ከአንድ ወር በኋላ ነበር ነገሩን አንስተን ዳግም የተነጋገርንበት፡፡
እንዲሁ ከመሬት ተነስቶ‹‹ኪያ ታፈቅሪኛለሽ እንዴ?›› አለኝ፡፡
‹‹አንተ ምን ይመስልሀል?››
‹‹እኔ እንጃ ግራ ገብቶኝ እኮ ነው የጠየቅኩሽ .. ምን አልባት አንቺ ድሮ አይንሽ በሚያይበት ወቅት ጎረምሳ ስለነበርኩ አሁንም ልክ እንደዛው አድርገሽ ስለሺኝ ተሸውደሽ እንዳይሆን ....ቢያንስ ከአስር አመት በላይ በዕድሜ እበልጥሻለሁ... አረጅብሻለሁ፡፡››
‹‹እንጂ ታፈቅረኝ ነበር.?
‹‹.እኔማ በጣም ነው ማፈቅርሽ….ግን ደግሞ ሳስብ በብዙ ነገር የምገባሽ አይደለሁም፡፡ እኔ አንድ ተራ ሹፌር ነኝ..አንቺ ደግሞ ነገ ብሩህ ሕይወት የሚጠብቅሽ በጣም ዝነኛ የመሆን ዕድል ያለሽ ሴት ነሽ፡፡ አየሽ ነገ ይሄ በውለታ አስሯት አታሏት ህይወቷን አበላሸባት፤ደግሞ ሽማግሌ እኮ ነው!!! በዛ ላይ፤ እያሉ እንዲሳለቁብኝ እና አንቺም ወይኔ ብለሽ እንድትፀፀቺ ስለማልፈልግ እንጂ እኔማ መች አንቺን ሳላፈቅር ቀርቼ አውቃለሁ፡፡››ብሎ ቁጭ አለ፡፡… አቤት የዛን ቀን የተደሰትኩት መደሰት፣አቤት
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
እሁድ ቀን ነው 8 ሰአት ከካባቢ ደደፎ እንግዳ ይዞ ቤት መጣ፤ምን ዓይነት እንግዳ መሰለህ ? ... የሚያስጠላ ቀፋፊ ድምፅ ያላት፤ሾካካ አረማመድ የምትራመድ፤ባለ ሻካራ ድምፅ ሴት፡፡ ምን አልባት ያልኳትን አይነት ሴት ላትሆን ትችላለች፤በወቅቱ ለእኔ የተሰማኝ ግን እንደዛ ዓይነት ሴት እንደሆነች ነበር፡፡››
‹‹ኪያ ተዋወቂያት ፀዳለ ትባላለች..ፀዳለ እሷ ደግሞ ጽዮን ትባላለች እህቴ ነች፡፡ ››አላት፡፡
‹‹ተዋወቅንና ቁጭ አሉ…ውይ ኪያ ሳልነግርሽ ….ከፀዳለ ጋር አንድ መስሪያ ቤት ነው
የምንሰራው አሁን ግን….››ብሎ ንግግሩን አንጠልጥሎ ተወው፡
እኔም የልጅቷን ድምጽ ከሰማሁበት ደቂቃ ጀምሮ የሆነ ቅፍፍ ብሎኛልና‹‹አሁን ግን ምን…?››ብዬ ጠየቅኩት፡፡
‹‹ፍቅረኛዬ ሆናለች….እሺ ካለቺኝ በቅርብ እንጋባና ትቀላቀለናለች፡፡››አለኝ፡፡
መሀከል ወለል ላይ ቆሜ ነበር የሚያወራውን ሳዳምጥ የነበረው ... ወዲያው ግን ብዥ አለብኝ...ልቤን ሲያጥወለውለኝ ወደ ጓዳ ለመግባት ቀኝ እግሬን አነሳሁና መልሼ መሬት ለማሳረፍ ስሞክር መሬቱ የጥልቅ ገደል ያህል በኪሎ ሜትሮች ራቀብኝ፡፡ከዛ ዥው ብዬ ወደ ኃላዬ እየወደቅኩ ሳለ ደፎ ተንደርድሮ ከመሬቱ ከመላተሜ በፊት ሲታደገኝ..ከዛ ማንነቴም ሲጠፋኝ፡፡
ከደቂቃዎች በኃላ ስነቃ ደደፎ በድንጋጤ በፎጣ ውሃ እየነከረ እራሴን ልቤን ሲያቀዘቅዝልኛል ሴትዬዋ በዛ ቀፋፊ ድምጿ < አይዞህ ይሻላታል …አትደንግጥ፡፡›› እያለች ስታፅናናው ሰማሁ ፡፡ የእሷን ድምጽ
የማልሰማበት የት ልሂድ....? ደሞ ያበሳጨኝ የእኔ መታመም ሳይሆን የእሱ ለእኔ መጨነቅ ስላስጨነቃት ነበር ፡፡ እንደምንም አንደበቴን አላቅቄ‹‹.. ደፍ ሰላም ነኝ እራሴን ስላመመኝ ትንሽ ልተኛበት ..ይተወኛል› አልኩት፡፡
በመናገሬ ደስ እያለው ብርድልብሱን አለባበሰኝና ያቺን ባለቀፋፊ ድምፅ ሴት
ከመኝታ ቤት ይዞልኝ ወጣ፡፡እኔም የምፈልገው
እሱን ነበር፡፡ግን ምን ነካኝ….?የእሱ ፍቅረኛ
መያዝ እኔን እራሴን እስክስት ድረስ እንዴት
ሊያደርሰኝ ቻለ... ? ለእኔ ወንድሜ አይደል እንዴ..?አይደለም፡፡ ለእኔ ዘመዴ አይደለ እንዴ….? አይደለም፤እና አፈቅረዋለው ማለት ነው...?. መጠርጠሩስ፡፡ በቃ የልቤን ጥያቄ እና የአዕምሮዬን መልስ ስሰማ ሰማይ ምድሩ
ተደበላለቀብኝ፤ምን ይሻለኛል….?እንዴት ነው
ለዓመታት እሱን አቅፌ የሰላም እንቅልፍ
በተኛሁበት አልጋ ላይ ሌላ ሴት መጥታ እኔን
ሳሎን ወዳለው ፍራሽ ላይ ወርውራኝ እሷ እሱን
አቅፋ የምትተኛው…? በፍፅም አይሆንም፡፡
ይሄንን ቤት ለቅቄ መውጣት አለብኝ…? ወጥቼ ወዴት ነው የምሄደው? አለሜ ጠቅላላ ..ዘመዴ መሸሸጊያ እሱው ነው፡፡ ቢሆንም እሱን ከሌላ ሴት ጋር እያየሁ መኖር አልችልም ::
መቻል አለብሽ... እሱ እኮ እንደ ታናሽ እህቱ አይቶሽ ነው በህይወቱ ሙሉ ሲንከባከብሽ የኖረው ፡፡ታዲያ ውለታውን እንዲህ ነው እንዴ የምትመልሺው..… ?ዕድሜሽን በሙሉ ያንን ሁሉ በምንም የማይለካ ደስታ ሲመግብሽ ቆይቶ ዛሬ አንቺ ውለታውን እንዲህ ነው የምትመልሺው...? የእሱ ደስታ እንዴት ነው እንዲህ ሊያበሰጭሽ የቻለው..? እስከመቼ ሳያፈቅር እና ሳያገባ ላንቺ ሲል ተቆራምዶ ይኖራል…?››አይምሮዬና ልቤ ጦርነት ጀመሩ ግን ቆረጥኩ… በቃ፡፡
ቢያንስ አሁን ትልቅ ሰው ነኝ.. ከአያቴ ቤት ኪራይ ለዓመታት የተጠራቀመልኝ 5ዐሺ ብር ባንክ ቤት አለኝ ፤ በዛ ላይ ከቸገረኝ የአያቴን ቤት እሸጠዋለሁ፡፡ያ ደግሞ ትምህርቴን እስክጨርስ በርግጠኝነት ይበቃኛል.. ለጊዜው
የሚከራይ ቤት እስካገኝ ጓደኞቼ ጋር አርፋለሁ ፡፡ከዚህ ቤት ግን ዛሬውኑ መልቀቅ አለብኝ፡፡ አዎ አሁን ሊሸኛት ሄዷል ፤ ከመምጣቱ በፊት መፍጠን አለብኝ > አልኩና ከተኛሁበት ተነስቼ ሻንጣዬን በዳበሳ ፈለግኩና ፊት ለፊት ያገኘሁትን እና መሰብሰብ የቻልኳቸውን የእኔ የሆኑ እቃዎችን ከታተትኩና ሻንጣዬን በአንድ እጅ የገንዘብ ቦርሳዬን በትከሻዬ፤ ዘንጌን በሌላው እጄ ይዤ ከመኝታ ቤት አልፌ የሳሎኑን ደጃፋ በጥበብ ተሸግሬ ቤቱን ሙሉ በሙሉ ለቅቄ ልወጣ ስል‹‹እንዴ ወዴት ነው?››የሚለው የደደፎ ድምጽ አንዱን እገሬን በአየር ላይ ተንከርፍፎ እንዲቀር አደረገው፡፡ ተንደርድሮ መጣና ክንዴን አጥብቆ ያዘኝ፡፡
‹‹ኪያ ምን እየሰራሽ ነው?›› ሲጠይቀኝ ሰውነቱ ሁሉ እየተንቀጠቀጠ እንደሆነ በያዘኝ እጆቹ ንዝረት ተረዳሁ፤ አሳዘነኝ፡፡
‹‹ንገሪኝ እንጂ የት ነው?››
‹‹በቃ ልታገባ አይደል እንዴ? ቤቱን ልለቅልህ ነዋ፡፡››
በጥፊ አላሰኝ... አቤት የደነገጥኩት ድንጋጤ ..አቤት የተደሰትኩት መደሰት..አቤት የተሰማኝ ቅብዥርዥር ስሜት፡፡ ከተዋወቅንበት ቀን አንስቶ እንኳን ሊመታኝ ክፉ ቃል እንኳን ተናግሮኝ አያውቅም ...የደነገጥኩት ለዛ ነው፡፡ የተደሰትኩት ደግሞ የመታኝ ስለሚፈልገኝ ነው የሚል ስሜት ስለተሰማኝ ነበር፡፡ከዛ ቦርሳውንም ሻንጣውንም ነጥቆኝ እየገፈተረ ወደ ውስጥ አስገባኝ እና ወንበር ላይ ገፍትሮ አስቀመጠኝ..››
‹‹እየሰማኸኝ ነው አይደል ታዲ?››
‹‹በጣም እየሰማሁሽ ነው.፡፡ በሰው ወሬ መካከል እሺ ..ከዛስ ..ምናምን ማለት ስለማልወድ ነው..፡፡››
ከዛ እየተንዘረዘረ‹‹እኔ አንቺን ከቤት አስወጥቼ ነው ሚስት የማገባው?እንዴት እንዴት ነው የምታስቢው…? በቀላሉ እንድታገባ አልፈልግም አትይኝም?››
‹‹እንድታገባ አልፈልግም ብልህ እሺ ትለኛለህ?››
‹‹በትክክል እልሻለው፡፡››
‹‹እንግዲያው እንድታገባ አልፈልግም..አንተን ከሌላ ሴት ጋር እንዳይህ ፈጽሞ አልፈልግም››አልኩት፡፡ ፀጥ አለኝ ፡፡ ፀጥታው አስር ለሚሆኑ ደቂቃዎች ነው የቆየው... ግን የአስር ሺ አመትን ያህል ርዝመት ነበረው፡፡ ግራ የሚያጋባ የሚያስደነግጥ ፀጥታ….ነፍስን የሚያፍን ፀጥታ እንደምንም ያለኝን ጉልበት አጠራቅሜ‹‹ይሄው አላልኩህም… እሺ አትልም አላልኩህም .. ?እኔ እዚህ ቤት መኖር አልፈልግም በቃ…››ተንጣጣሁበት፡፡
‹‹ባክሽ ዝም በይ፤እሺ ብዬሻለሁ፤በቃ ትቼያታለሁ፡፡ ፍቅረኛዬም እንዳልሆነች
እንደማላገባትም ነገ እነግራታለሁ...አሁን ለምቦጭሽን አትጣይብኝ፡፡›› አለኝ፡፡
ከተቀመጥኩበት ተንደርድሬ በመነሳት ተጠምጥሜበት ልስመው ስል አንድ ኩርሲ ነገር አደናቀፈኝና ልዘረገፍ ስል በአየር ላይ ተቀበልኝ ...በአንድ ቀን ለሁለተኛ ጊዜ ከመፈጥፈጥ ታደገኝ፡፡ ለዛም ምስጋና እንዲሆንልኝ ወደራሴ ጎትቼ ጉንጩን ሳምኩት…፡፡
ከዛ .... ከአንድ ወር በኋላ ነበር ነገሩን አንስተን ዳግም የተነጋገርንበት፡፡
እንዲሁ ከመሬት ተነስቶ‹‹ኪያ ታፈቅሪኛለሽ እንዴ?›› አለኝ፡፡
‹‹አንተ ምን ይመስልሀል?››
‹‹እኔ እንጃ ግራ ገብቶኝ እኮ ነው የጠየቅኩሽ .. ምን አልባት አንቺ ድሮ አይንሽ በሚያይበት ወቅት ጎረምሳ ስለነበርኩ አሁንም ልክ እንደዛው አድርገሽ ስለሺኝ ተሸውደሽ እንዳይሆን ....ቢያንስ ከአስር አመት በላይ በዕድሜ እበልጥሻለሁ... አረጅብሻለሁ፡፡››
‹‹እንጂ ታፈቅረኝ ነበር.?
‹‹.እኔማ በጣም ነው ማፈቅርሽ….ግን ደግሞ ሳስብ በብዙ ነገር የምገባሽ አይደለሁም፡፡ እኔ አንድ ተራ ሹፌር ነኝ..አንቺ ደግሞ ነገ ብሩህ ሕይወት የሚጠብቅሽ በጣም ዝነኛ የመሆን ዕድል ያለሽ ሴት ነሽ፡፡ አየሽ ነገ ይሄ በውለታ አስሯት አታሏት ህይወቷን አበላሸባት፤ደግሞ ሽማግሌ እኮ ነው!!! በዛ ላይ፤ እያሉ እንዲሳለቁብኝ እና አንቺም ወይኔ ብለሽ እንድትፀፀቺ ስለማልፈልግ እንጂ እኔማ መች አንቺን ሳላፈቅር ቀርቼ አውቃለሁ፡፡››ብሎ ቁጭ አለ፡፡… አቤት የዛን ቀን የተደሰትኩት መደሰት፣አቤት
👍81❤9🥰8😁3