#ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
ከገና ማዕበል ያመለጠው ተማሪ፥ የዩኒቨርስቲ ውስጥ ዕድሜው መራዘሙን ካረጋገጠ በኋላ መረጋጋት ይታይበታል ። የሁለተኛው ሴሚስተር ትምህርት ቢጀመርም ገና ሞቅ ሞቅ ባለማለቱ አንገቱን መልሶ ቀለም ላይ የደፋ ተማሪ
እምብዛ!” ነው ። ሆኖም ፋታ ፈጥሮአቸው የነበሩት ቀልድ ፥ትችት።ውንጀላና ተረብ ተግ ብለዋል ።
ትዕግሥት ማጥናት አልጀመረችም ። የወረቀት ዘር ማየት ያስጠላት ትመስላለች ትምህርት ክፍሉ ውስጥ እንኳ ከመምህራኑ ገለጻ ሙሉ በሙሉ ማስታወሻ መውሰዷን ትጠራጠራለች ። ምክንያቱ አንዳንዴ ሐሳቧ እያመለጣት
ወደ ወጭ መብረር ጀምሯል ፤ በግልጽ ያልተከተላት ስሜት ሲፈታተናት ይሰማታል ከውስጧ አንዳች ነገር የጎደለ ይመስላታል። ምናልባት በቢልልኝ አገላለጽ ለፍቅር የተዘጋጀው ሥፍራ ሳይሆን አይቀርም የሚረብሻት ።
እቤል ሕመሙን አጋብቶባት እንደ ሄደ ለመገመት ብዙ ጊዜ አልወሰደባትም ። መኝታ ክፍሏ መግባት መውጣትም አስጠልቷታል ። ጸባይዋ ቢንቋሸሽም ፡ በመጠኑ ለምዳት የነበረችው ጓደኛዋ ማርታ ነበረች ። እሷ ከተባረረች ወዲህ በደንብ ቀርባ የምትጫወተውን የሴት ጓደኛ አላገኘችም ። ከቤተልሔም ጋር ዐልፎ ህልፎ ይገናኛሉ ። ሆኖም በግቢው ውስጥ የቤተልሔም ስም እየቆሸሽ ስለ መጣ ትዕግሥት አብራ እንዳትታማ በመፍራት ቀስ በቀስ እየራቀቻት
ነበር ። አቤል ግቢውን ለቅቆ ከወጣ ወዲህ ለዐይኗ ማሳረፊያ ያገኘችው ሰው እስክንድር ነው ፡ ሳታየዉ ወይም
አግኝታው የተለመደውን “ ታዲያስ ፥ ታዲያስ ” ሰላምታ ሳትለዋወጥ ውላ
አታውቅም ።
እስክንድርም ቢሆን፥የትዕግሥትን መግቢያና መውጪያ ሰዓት ጠብቆ ነው የሚገኛት ፥ ከመኝታ ክፍሉ ጠዋት
ሲወጣ ስለ አቤል ሁኔታ ፍርጥርጥ አርጎ አጫውቷት መፍትሔውን እንዲወያዩበት ሊለምናት ያስብና ፡ በሚያገኛት ጊዜ ልቡ ይከዳዋል ። በዮናታን ፊት የፎከረውንና እሷን ሲያገኛት ምላሱ መተሳስሩን ሲያመዛዝን ራሱን ታዘበው ።
“ አቤልስ ቢደነግጥላትም ቢፈራትም ወዷት ነው ፤እኔ ደግሞ ያሰብኩትን ልነግራት መፍራቴ ለምንድን ነው ? ” እያለ
ከራሱ ጋር መሟገቱ አልቀረም ። ግን ለእስክንድር አልታወቀውም እንጂ፥ ስለ አቤል ጠልቆ ሳያነሳባት ከትዕግሥት ጋር
ግንኙነቱን ማጠናከሩ ለዓላማው ጥሩ መንገድ አመቻችቶለት ነበር ። በአንዴ ነጥቡ ላይ ደርሶ ዱብ ዕዳ ከማውረድ ፥ ቀስ በቀስ አለማምዶ ከነጥቡ ላይ መድረሱን መልሱ የእሽታ እንዲሆን ይበልጥ ይረዳል ።
ትዕግሥትን ከአቤል ጋር ለማገናኘት አማራጭ መንገዶችን ዮናታንና ቢልልኝ ተነጋግረው ነበር ። ትዕግሥትን ድንገት ወስዶ አቤል ፊት ማቅረቡን ቢልልኝ አልደገፉትም ምናልባትም ካለፈው ልምዳቸው በመነሣት ሊሆን ይችላል።
አንዴ እንዲሁ ተመሳሳይ ችግር የገጠመው ተማሪ የሚፈልጋትን ልጅ አቅርበው እናስተዋውቅህ ሲሉት፡ ካልገደልኳት ብሎ የተጋበዘው ነገር ምንጊዜም አይረሳቸውም ። እና አሁን ያቀረቡት ሐሳብ በመጀመሪያ አቤል ስለ ትዕግሥት ቀና አመለካከት እንዲኖረው መኮትኮትና አጠገቡ ከመድረሷ በፊት በስልክ እንድታነጋግረው ወይም ደብዳቤ እንድትጽፍለት ማድረግ ነበር ። ደብዳቤ መጻፍዋ የተሻለ መንገድ ሆኖ ተመረጠ ። ይህን ለማስፈጸም በሙሉ ልብ ኃላፊነቱን
የወሰደው እስክንድር ነበር ። ታዲያ አሁን ተግባሩ ላይ ሲዲርስ የምን ወገቤን ያዙኝ ነው ?
ሲያምጥ ከርሞ፡አንድ ቀን እንደ ምንም ደፍሮ ሔደ ። ከመኝታ ክፍሏ አስጠራትና ፡ “ ለጥብቅ ጉዳይ እፈልግሻለሁ ” አላት ። በቆይታ የሚያወሩበት ቦታም ችግር ነበር
እነትዕግሥት ቀድሞ ያጠኑበት የነበረው ከዋናው ቤተ መጹሕፍት ጀርባ ያለው ዋርካ አካባቢ ታየው ። ግን ሁለታችንን
ብቻ እዚያ ዋርካ ሥር ሲያዩን ተማሪዎች ምን ይሉናል ? የሚል ሥጋት እደረበት በመጨረሻም ካወጣ ካወረደ በኋላ ሌላ ቦታ በማጣቱ “ ያሉትን ይበሉ ወደ
ዋርካው ሥር ይዟት ሔደ
እንዴት እንደሚጀምርላት ግራ ገብቶት ትንሽ ተጨነቀ። ግን ዝም ማለትም አልቻለም ። ዐይኖችዋ ውስጥ የጥያቄ
ምልክቶች ተደርድረው ያየ መሰለው ።
“ ሁለታችንም ሳንጠላው የምንሸሸው አርዕስት ነው አላት በድንገት ።
“ ምን ? ” አለችው ፥ ነገሩ ቢገባትም ከእሱው ይምጣ በሚል ስሜት ።
የእቤልን ነገር ሁለቱ በተገናኙ ቁጥር ዳር ዳር ሳይሉ ስለማይለያዩ አሁን ስለእሱ ሊያወራት መሆኑን ትዕግሥት አላጣቸውም ። ስሜቷን ደብቃ ነው እንጂ ወሬውን ለመስ ማት ቸኩላለች
ስለ አቤል በደንብ ላጫውትሽ ብዬ ነው ?” አላት ።
ፈቃደኛነቷን በአፏ ሳይሆን በዐይኖቿ ነው የግለጸችለት ።
አጫወታት ነው ረበሻት የሚባለው ? የለም ! ማጫወት ላይ ላዩን ሲሆን ነው ። ከሥር ከመሠረቱ ጀምሮ ልብን እያናጉ
መንፈስን እያወራጩ ፥ ቁስልን እየቀሰቀሱ ስሜትን እያንገላቱ የሚናገሩት ነገር፡ “ መረበሽ ” የሚለውን ቃል ቢይዝ ይሻላል ። እስክንድር እንደዚያ ነው ያደረገው ። ሳያስበው የእሱም ስሜት አርዕስተ ነገሩ ውስጥ ሰምጦ እየተንገላታ ስለ አቤል የሚያውቀውን ሁሉ ነገራት። እሷን ካየበት
ዕለት ጀምሮ በግሉ የተቀበለውን ሥቃይ አሁን የት እና በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ዘረዘረላት እያወራላት ገጽታዋን ገመገመ ከንፈሯ በቅጽበት ሲከስል ታየው ። ፊቷ በአንዴ ጠወለገ ። አዲስ ነገር ተናግሮ
አልረበሻትም ። አብዛኛው የምታውቀው ነገር ነው ። አብዛኛው ከአቤል ጋር አንድ ሴሚስተር ሙሉ በዐይናቸው የተለዋወጡት የጥናት ፥ የቁጣ ፥ የሥቃይና የእልህ ድምፅ አልባ
ግንኙነት ነው።
“ ታዲያ ጥፋተኛው ማነው ? ” አለችው ንግግሩን መጨረሱን ካረጋገጠች በኋላ
ዐይኖችዋ ያቀረሩትን ዕንባ ሲያይ ስሜትዋ ተጋባበት።ግን እሱ የማልቀስ ችግር አለበት ፤ዕንባው ቶሎ አይመጣለትም ።
ለፍርድ አስቸጋሪ ነው ። ሁለታችሁም ጥፋተኛች አይደላችሁም ። እየተፈላለጉ መራራቅን ፡ “ የፍቅር እንቆቅልሽ ” ብንለው ይሻላል ” አላት ።ዝም አለችው ። እሱም ዝም ብሎ ተመልከታት ። የአቤልን ስሜት ያደነዘዘውን የመልኳን ውበት ማጥናት ፈለገ ።ግን ከዳመነ ፊቷ ላይ ውበት ለማጥናት መሞከሩ አስቸጋሪ
ሆነበት ።
በረዥሙ ተነፈሰች የጭንቅ አተነፋፈስ ። የታባቱ !በሥቃይ የታመቀው አየር ወጣ ።
“ አሁን አንገብጋቢው “ ጥያቄ ጥፋተኛው ማነው?”ሳይሆን ፥ “ መፍትሔው ምንድነው ?” ይመስለኛል” አላት እስክንድር ።
“ ምን መፍትሔ አለው ? ” አለችው ፡ ተስፋ በቆረጠ ድምፅ።
“ አለው እንጂ ።አቤል ይወድሻል ፥ ይፈልግሻል ማወቅ የሚፈልገው ያንቺ ምላሽ ምን እንደሆን ነው ። ካንቺ
መረዳት እንደ ቻልኩት ደግሞ አንቺም ትፈልጊዋለሽ ፤ትወጂዋለሽ ። ይህን ስሜትሽን በደብዳቤ ብትገልጪለት
ችግሩ ይቃለላል ። ”
ደብዳቤ ”አለችው ; ሳይተዋወቁ የምትጽፍለት ደብዳቤ ምን እንደሚሆን ግር ብሏት ።
"አዎ ደብዳቤ !"
"ምን ብዬ ?"
“ በቃ ለእሱ ያለሽን ስሜት ነዋ ! ”
አሰበች ፤ደብዳቤ ። አዎ ጥሩ መንገድ ነው ስትጽፍ አጠገቧ የምታፍረው ወይም የምትፈራው አቤል አይኖርም ወረቀቱ ሳይ የምታሰፍራቸው ቃላት ፈንቅለዋት ማልቀስ ቢዳዳትም ማልቀስ ትችላለች ። ታዛቢ አይኖርባትም ። የምትጽፈው ነገር ከጭንቅላቷ ውስጥ እየፈለቀ ኣሁን አሁን
አሰኛት ።
“ ካልሆነም ረቂቁን እኔ ልጻፍልሽ ” አላት እስክንድር፡ ዝም ስትልበት ጊዜ የቸገራት መስሎት ።
ግድ የለም ፤ እኔው እሞክራለሁ ” አለችው ፥ በሐሳቧ የምትጽፍበትን ቦታ እየመረጠች ምቹ ቦታ የለም ።
የመኝታ ክፍል ጓደኞቿ ከተኙ በኋላ፥ ሌሊት ተነሥታ የመጻፍ ሐሳብ መጣላት ።
“ ጥሩ እንግዲህ ፥ ጸፊና ሰጪኝ ። እኔ አደርስልሻ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
ከገና ማዕበል ያመለጠው ተማሪ፥ የዩኒቨርስቲ ውስጥ ዕድሜው መራዘሙን ካረጋገጠ በኋላ መረጋጋት ይታይበታል ። የሁለተኛው ሴሚስተር ትምህርት ቢጀመርም ገና ሞቅ ሞቅ ባለማለቱ አንገቱን መልሶ ቀለም ላይ የደፋ ተማሪ
እምብዛ!” ነው ። ሆኖም ፋታ ፈጥሮአቸው የነበሩት ቀልድ ፥ትችት።ውንጀላና ተረብ ተግ ብለዋል ።
ትዕግሥት ማጥናት አልጀመረችም ። የወረቀት ዘር ማየት ያስጠላት ትመስላለች ትምህርት ክፍሉ ውስጥ እንኳ ከመምህራኑ ገለጻ ሙሉ በሙሉ ማስታወሻ መውሰዷን ትጠራጠራለች ። ምክንያቱ አንዳንዴ ሐሳቧ እያመለጣት
ወደ ወጭ መብረር ጀምሯል ፤ በግልጽ ያልተከተላት ስሜት ሲፈታተናት ይሰማታል ከውስጧ አንዳች ነገር የጎደለ ይመስላታል። ምናልባት በቢልልኝ አገላለጽ ለፍቅር የተዘጋጀው ሥፍራ ሳይሆን አይቀርም የሚረብሻት ።
እቤል ሕመሙን አጋብቶባት እንደ ሄደ ለመገመት ብዙ ጊዜ አልወሰደባትም ። መኝታ ክፍሏ መግባት መውጣትም አስጠልቷታል ። ጸባይዋ ቢንቋሸሽም ፡ በመጠኑ ለምዳት የነበረችው ጓደኛዋ ማርታ ነበረች ። እሷ ከተባረረች ወዲህ በደንብ ቀርባ የምትጫወተውን የሴት ጓደኛ አላገኘችም ። ከቤተልሔም ጋር ዐልፎ ህልፎ ይገናኛሉ ። ሆኖም በግቢው ውስጥ የቤተልሔም ስም እየቆሸሽ ስለ መጣ ትዕግሥት አብራ እንዳትታማ በመፍራት ቀስ በቀስ እየራቀቻት
ነበር ። አቤል ግቢውን ለቅቆ ከወጣ ወዲህ ለዐይኗ ማሳረፊያ ያገኘችው ሰው እስክንድር ነው ፡ ሳታየዉ ወይም
አግኝታው የተለመደውን “ ታዲያስ ፥ ታዲያስ ” ሰላምታ ሳትለዋወጥ ውላ
አታውቅም ።
እስክንድርም ቢሆን፥የትዕግሥትን መግቢያና መውጪያ ሰዓት ጠብቆ ነው የሚገኛት ፥ ከመኝታ ክፍሉ ጠዋት
ሲወጣ ስለ አቤል ሁኔታ ፍርጥርጥ አርጎ አጫውቷት መፍትሔውን እንዲወያዩበት ሊለምናት ያስብና ፡ በሚያገኛት ጊዜ ልቡ ይከዳዋል ። በዮናታን ፊት የፎከረውንና እሷን ሲያገኛት ምላሱ መተሳስሩን ሲያመዛዝን ራሱን ታዘበው ።
“ አቤልስ ቢደነግጥላትም ቢፈራትም ወዷት ነው ፤እኔ ደግሞ ያሰብኩትን ልነግራት መፍራቴ ለምንድን ነው ? ” እያለ
ከራሱ ጋር መሟገቱ አልቀረም ። ግን ለእስክንድር አልታወቀውም እንጂ፥ ስለ አቤል ጠልቆ ሳያነሳባት ከትዕግሥት ጋር
ግንኙነቱን ማጠናከሩ ለዓላማው ጥሩ መንገድ አመቻችቶለት ነበር ። በአንዴ ነጥቡ ላይ ደርሶ ዱብ ዕዳ ከማውረድ ፥ ቀስ በቀስ አለማምዶ ከነጥቡ ላይ መድረሱን መልሱ የእሽታ እንዲሆን ይበልጥ ይረዳል ።
ትዕግሥትን ከአቤል ጋር ለማገናኘት አማራጭ መንገዶችን ዮናታንና ቢልልኝ ተነጋግረው ነበር ። ትዕግሥትን ድንገት ወስዶ አቤል ፊት ማቅረቡን ቢልልኝ አልደገፉትም ምናልባትም ካለፈው ልምዳቸው በመነሣት ሊሆን ይችላል።
አንዴ እንዲሁ ተመሳሳይ ችግር የገጠመው ተማሪ የሚፈልጋትን ልጅ አቅርበው እናስተዋውቅህ ሲሉት፡ ካልገደልኳት ብሎ የተጋበዘው ነገር ምንጊዜም አይረሳቸውም ። እና አሁን ያቀረቡት ሐሳብ በመጀመሪያ አቤል ስለ ትዕግሥት ቀና አመለካከት እንዲኖረው መኮትኮትና አጠገቡ ከመድረሷ በፊት በስልክ እንድታነጋግረው ወይም ደብዳቤ እንድትጽፍለት ማድረግ ነበር ። ደብዳቤ መጻፍዋ የተሻለ መንገድ ሆኖ ተመረጠ ። ይህን ለማስፈጸም በሙሉ ልብ ኃላፊነቱን
የወሰደው እስክንድር ነበር ። ታዲያ አሁን ተግባሩ ላይ ሲዲርስ የምን ወገቤን ያዙኝ ነው ?
ሲያምጥ ከርሞ፡አንድ ቀን እንደ ምንም ደፍሮ ሔደ ። ከመኝታ ክፍሏ አስጠራትና ፡ “ ለጥብቅ ጉዳይ እፈልግሻለሁ ” አላት ። በቆይታ የሚያወሩበት ቦታም ችግር ነበር
እነትዕግሥት ቀድሞ ያጠኑበት የነበረው ከዋናው ቤተ መጹሕፍት ጀርባ ያለው ዋርካ አካባቢ ታየው ። ግን ሁለታችንን
ብቻ እዚያ ዋርካ ሥር ሲያዩን ተማሪዎች ምን ይሉናል ? የሚል ሥጋት እደረበት በመጨረሻም ካወጣ ካወረደ በኋላ ሌላ ቦታ በማጣቱ “ ያሉትን ይበሉ ወደ
ዋርካው ሥር ይዟት ሔደ
እንዴት እንደሚጀምርላት ግራ ገብቶት ትንሽ ተጨነቀ። ግን ዝም ማለትም አልቻለም ። ዐይኖችዋ ውስጥ የጥያቄ
ምልክቶች ተደርድረው ያየ መሰለው ።
“ ሁለታችንም ሳንጠላው የምንሸሸው አርዕስት ነው አላት በድንገት ።
“ ምን ? ” አለችው ፥ ነገሩ ቢገባትም ከእሱው ይምጣ በሚል ስሜት ።
የእቤልን ነገር ሁለቱ በተገናኙ ቁጥር ዳር ዳር ሳይሉ ስለማይለያዩ አሁን ስለእሱ ሊያወራት መሆኑን ትዕግሥት አላጣቸውም ። ስሜቷን ደብቃ ነው እንጂ ወሬውን ለመስ ማት ቸኩላለች
ስለ አቤል በደንብ ላጫውትሽ ብዬ ነው ?” አላት ።
ፈቃደኛነቷን በአፏ ሳይሆን በዐይኖቿ ነው የግለጸችለት ።
አጫወታት ነው ረበሻት የሚባለው ? የለም ! ማጫወት ላይ ላዩን ሲሆን ነው ። ከሥር ከመሠረቱ ጀምሮ ልብን እያናጉ
መንፈስን እያወራጩ ፥ ቁስልን እየቀሰቀሱ ስሜትን እያንገላቱ የሚናገሩት ነገር፡ “ መረበሽ ” የሚለውን ቃል ቢይዝ ይሻላል ። እስክንድር እንደዚያ ነው ያደረገው ። ሳያስበው የእሱም ስሜት አርዕስተ ነገሩ ውስጥ ሰምጦ እየተንገላታ ስለ አቤል የሚያውቀውን ሁሉ ነገራት። እሷን ካየበት
ዕለት ጀምሮ በግሉ የተቀበለውን ሥቃይ አሁን የት እና በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ዘረዘረላት እያወራላት ገጽታዋን ገመገመ ከንፈሯ በቅጽበት ሲከስል ታየው ። ፊቷ በአንዴ ጠወለገ ። አዲስ ነገር ተናግሮ
አልረበሻትም ። አብዛኛው የምታውቀው ነገር ነው ። አብዛኛው ከአቤል ጋር አንድ ሴሚስተር ሙሉ በዐይናቸው የተለዋወጡት የጥናት ፥ የቁጣ ፥ የሥቃይና የእልህ ድምፅ አልባ
ግንኙነት ነው።
“ ታዲያ ጥፋተኛው ማነው ? ” አለችው ንግግሩን መጨረሱን ካረጋገጠች በኋላ
ዐይኖችዋ ያቀረሩትን ዕንባ ሲያይ ስሜትዋ ተጋባበት።ግን እሱ የማልቀስ ችግር አለበት ፤ዕንባው ቶሎ አይመጣለትም ።
ለፍርድ አስቸጋሪ ነው ። ሁለታችሁም ጥፋተኛች አይደላችሁም ። እየተፈላለጉ መራራቅን ፡ “ የፍቅር እንቆቅልሽ ” ብንለው ይሻላል ” አላት ።ዝም አለችው ። እሱም ዝም ብሎ ተመልከታት ። የአቤልን ስሜት ያደነዘዘውን የመልኳን ውበት ማጥናት ፈለገ ።ግን ከዳመነ ፊቷ ላይ ውበት ለማጥናት መሞከሩ አስቸጋሪ
ሆነበት ።
በረዥሙ ተነፈሰች የጭንቅ አተነፋፈስ ። የታባቱ !በሥቃይ የታመቀው አየር ወጣ ።
“ አሁን አንገብጋቢው “ ጥያቄ ጥፋተኛው ማነው?”ሳይሆን ፥ “ መፍትሔው ምንድነው ?” ይመስለኛል” አላት እስክንድር ።
“ ምን መፍትሔ አለው ? ” አለችው ፡ ተስፋ በቆረጠ ድምፅ።
“ አለው እንጂ ።አቤል ይወድሻል ፥ ይፈልግሻል ማወቅ የሚፈልገው ያንቺ ምላሽ ምን እንደሆን ነው ። ካንቺ
መረዳት እንደ ቻልኩት ደግሞ አንቺም ትፈልጊዋለሽ ፤ትወጂዋለሽ ። ይህን ስሜትሽን በደብዳቤ ብትገልጪለት
ችግሩ ይቃለላል ። ”
ደብዳቤ ”አለችው ; ሳይተዋወቁ የምትጽፍለት ደብዳቤ ምን እንደሚሆን ግር ብሏት ።
"አዎ ደብዳቤ !"
"ምን ብዬ ?"
“ በቃ ለእሱ ያለሽን ስሜት ነዋ ! ”
አሰበች ፤ደብዳቤ ። አዎ ጥሩ መንገድ ነው ስትጽፍ አጠገቧ የምታፍረው ወይም የምትፈራው አቤል አይኖርም ወረቀቱ ሳይ የምታሰፍራቸው ቃላት ፈንቅለዋት ማልቀስ ቢዳዳትም ማልቀስ ትችላለች ። ታዛቢ አይኖርባትም ። የምትጽፈው ነገር ከጭንቅላቷ ውስጥ እየፈለቀ ኣሁን አሁን
አሰኛት ።
“ ካልሆነም ረቂቁን እኔ ልጻፍልሽ ” አላት እስክንድር፡ ዝም ስትልበት ጊዜ የቸገራት መስሎት ።
ግድ የለም ፤ እኔው እሞክራለሁ ” አለችው ፥ በሐሳቧ የምትጽፍበትን ቦታ እየመረጠች ምቹ ቦታ የለም ።
የመኝታ ክፍል ጓደኞቿ ከተኙ በኋላ፥ ሌሊት ተነሥታ የመጻፍ ሐሳብ መጣላት ።
“ ጥሩ እንግዲህ ፥ ጸፊና ሰጪኝ ። እኔ አደርስልሻ
#ቆንጆዎቹ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
....“ጥሩ እንዳትነቃነቅ::" አለ አራተኛው ሰው መሣሪያውን ደግኖ እንደያዘ ወደ ጭነት መኪናው እየተጠጋ፡፡ በእርጋታ ወደፊት እየተራመደ በዓይነ ጭነቱን ያዳብስ ጀመር፡
እራቅ ብለው ሁኔታውን በዝምታ ይከታተሉ የነበሩት ሦስት ሰዎች የመሃሉ ድንገት ተጣራና ጭንቅላቱን ወደኋላ መታ አደረገ፡፡ ወዲያው ወደ ጭነት መኪናው የተጠጋው አራተኛው ሰው ፊቱን መልሶ ወደ ጓደኞቹ ሮጥ ብሎ ተመለስና ሰብሰብ ብለው ይነጋገሩ ጀመር፡፡
“ጠዋት ምንያህል መኪናዎች ቀድመዋችሁ ወደ አዲስ አበባ
ተነስተዋል?” አለ አራተኛው ሰው ፊቱን ወደ ጭነት መኪናው ሹፌር
መልሶ ድምፁን ከፍ አድርጎ፡፡
“አንድ ሶስት አራት ይሆናሉ፡፡” አለ ከጭነት መኪናው ወርዶ የቆመው ሹፌር፡፡
ወዲያው አራቱ ሰዎች ሮጥ ሮጥ እያሉ ሬንጅሮቨራቸው ውስጥ ገቡና በአዲስ አበባ አቅጣጫ በረሩ፡፡
“ኡፍ .…ፍ!!” አለ ካልቨርት ጭንቅላቱን በተኛበት ጆንያ ላይ ጥሎ፡፡
“ሄዱ? ” አሉ ናትናኤል ሽራውን እንደተከናነበ በሹክሹክታ፡፡
“አዎ፡፡ ያለቀልን መስሎኝ ነበር::”
የጭነት መኪናው ሹፌር መኪናው ውስጥ ገብቶ ሲንቀሳቀሱ በተቻላቸው መጠን መንፈሳቸውን አረጋግተው መመካከር ያዙ፡፡
“ያላጥርጥር በየከተሞቹ ኬላዎች ላይ ይጠብቁናል፡፡ በተለይ ወደ አዲስ አበባ እየቀረብን ስንመጣ አስቸጋሪ ነው የሚሆንብን፡፡” እለ ናትናኤል፡፡
“አዎ፡፡ : ካአሁን ወዲያ ወደየትኛውም ከተማ መግባት የለብንም፡፡ ወደ ከተሞች ስንቀርብ እየወረድን ከጀርባ በግማሽ ክብ ቅርፅ በእግር ማለፍ ነው ያለን አማራጭ፡፡”
“ከናዝሬት ወዲያ ያለውን አካባቢ አውቀዋለሁ! መንገዱን በሩቅ
እይታ እስከተከተልን ድረስ ችግር አይገጥመንም::አለ ናትናኤል፡፡
ናዝሬት ከተማ ሲደርሱ እንድ አምስት ኪሎ ሜትር ሲቀራቸው ከተደበቁበት ሸራ ውስጥ ብቅ ብቅ እያሉ ከኋላና ከፊት ሌላ ተሽከርካሪ አለመኖሩን ካረጋገጡ በኋላ በጭነት፡ ላይ እየዳሁ ወደ መኪናወ ኋላ ተጠጉ፡፡
ሸራው የተጠፈረባቸውን ወፋፍራሃም ገመዶች የሙጢኝ ጨምድደው ይዘው
ቁልቁል ተንጠለጠሉ፡፡
“ተጠንቀቅ፡፡ አስፋልቱ ላይ ኣንዳታርፍ፡፡ በሁለት እግሮችህ ለማረፍና ለመቆም አትሞክር፤ ከዘለልክ በኋላ ጭንቅላትህን ቀብረህ ተንከባለል፡፡ እኔ ስዘል ተመልከት፡፡” አለ ካልቨርት በወጣትነት ዘመኑ በአገሩ ውስጥ ያሳለፋቸውን የኮማንዶ ህይቱን እያስታወሰ፡፡ "
በሰላሳ ሜትር ርቀት ልዩነት ሁለቱም የተንጠላጠሉባቸውን ገመዶች እየለቀቁ ከጭነት መኪናው ላይ ተፈናጠሩ፡፡ ካልቨርት አልተጎዳም፤ ናትናኤል ግን ግራ ክንዱ ክፉኛ ተገሸለጠ፡፡
“አስፋልቱ ላይ አትረፍ፡ እያልኩህ እንዲያውም ተርፈሃል፡፡ወደጎን
ባትንከባለል ኖሮ ይሄ አስፋልት ጭንቅላትህን ነበር የሚፈረክስልሀ፡፡” አለ
ካልቨርት እየሮጠ መጥቶ ናትናኤልን ደግፎ እያነሳው፡፡
አውራ መንገዱን እየራቁ፤ እየሸሹ የናዝሬትን ከተማ በስተቀኝ
ጀርባዋ ዞሯት::
"መንገዱ ወደቀኝ የሚታጠፍ፡ ስለሆነ ከዚህ በኋላ በቀጥታ መስመር ብንሄድ ወይም በሃያ አምስት ኪሎ ሜትር ላይ በዱከምና በሞጆ መሃል መንገድ ላይ ብቅ እንላለን፡፡ አለ ካልቨርት ካርታውን አውጥተው ሲያጠኑት ከቆዩ በኋላ፡፡
እንዳለው ከሦስት ሰዓት ተኩል የእግር ጉዞ በኋላ በሞጆ ከተማ አልፈው ከአውራ ጎዳናው ጋር ተገናኙ:: ብዙም ሳይቆዩ አነስተኛ የሕዝብ ማመላለሻ የገጠር አውቶቡስ አስቁመው ተሳፈሩ፡፡
“አዲስ ፈለጥ!“ ይላሉ አውቶብሱ ውስጥ ከሹፌሩ ጀርባ የተቀመጡ አዛውንት ድምፃቸውን ከፍ አድርገው፡፡ “ከአውቶብሱ ገብቶ
መፈተሽ የአባት... “ቆብህን አውልቅ፤ ክንብንብህን አውርድ ብሎ ነገር
ምንድነው? ወቸጉድ!”
“የሚፈልጉት ሰው አለ መሰለኝ::” አለ ባሻገር የተቀመጠ ልጅ እግር፡፡
ታድያ ቢኖርስ ባለፍንበት ከተማ ሁሉ እየቆምን ቆብና ክንብንባችንን መገፈፍ የአባት ነው?ልማድ ነው? ወይ ፈጣሪ?” ሽማግሌው ተቆጠ፡፡
“ምንድነው?” አላቸው ናትናኤል ከጎኑ የተቀመጡትን ሴትዮ::
“እንጃ! ባለፍንበት ከተማ ሁሉ መሣሪያ ደግነው እንደ ሽፍታ ሲበረብሩን ቆዩ፡፡” አሉት ሴትየዋ መደነቃቸውን፣ መገረማቸውን ለማሳየት እጃቸውን አፋቸው ላይ ጣል አድርገው፡፡
“እነማን ናቸው?” ናትናኤል ግራ የተጋባ መስሎ ጠየቃቸው፡፡
“ምኑን አወቄው ብቻ ከወለንጭቲ የጀመሩ ሰባቴ እያስቆሙ ሁለት
ሁለት፥ሦስት ሦስት እየሆኑ እንዲህ እንዲህ እያደረጋቸው ሲበረብሩን ዋሉ፡፡
ሆ! እንደ አነሳሳችንኮ ገና ቅድም ታዲስ አበባ ደርስን ነበር ጊዮርጊስ ይይላቸው”
ናትናኤል ዞር ብሎ ካልቨርትን ሹክ አለው::
ደብረዞይት ሊደርሱ ትንሽ ሲቀራቸው ተጠቃቀሱና መጀመሪያ ካልቨርት እራቅ ብሎ ደግሞ ናትናኤል ተከታትላው ወረዱ፡፡
“ምንድነው?” አለ ካልቨርት አውቶቡሱ ውስጥ የተባለውን ሁሉ አጣርቶ ለመረዳት ጓጉቶ፡፡
ናትናኤል አውቶቡሱ ውስጥ የሰማውን ሁሉ ዘርዝሮ ነገረው፡፡
“ከአሁን ወዲያ መኪና ላይ መውጣት የለብንም::” አለ ካልቨርት፡፡
“ታዲያ እንዴት አናደርጋለን?”
“አሁን ሁለታችንም የተዳከምን ይመስለኛል፡፡ ለጊዜው ከመንገድ
ፈቀቅ ብለን እንረፍና ከጨለመ ወዲያ ሌሊቱን መንገዱን ተከትለን በእግራችን እንቀጥላለን፡፡ ከበረታንና ሰሰዓት አምስት ኪሎ ሜትር ብንጓዝ እንኳን ከምሽቱ አንድ እስከ ጠዋቱ አንድ ሰዓት ስልሳ ኪሎ ሜትር ሽፈንን ማለት ነው:: ፀሐይ ስለማይበረታብን የምንሸነፍ፡ አይመስለኝም፡፡”
ከመንገዱ በስተቀኝ እርቀው ገብተው
ለብቻዋ በቆመች የግራር ዛፍ ስር በደረታቸው ተደፍተው ለማረፍ
ሞከሩ::እየጠለቀች ያለችው ፀሐይ እንደጌጥ ብታብረቀርቅም ሙቀቷ እየከዳት መጣ፡፡ አውላላ ሜዳ ላይ ብቻውን እየተመላለሰ የሚጋልበው ቀዝቃዛ ነፋስ ሰውነታቸውን ጠዘጠዘው፤ ምግብ ሳያገኝ ሁለተኛ ቀኑን የያዘው
ሰውነታቸውም ከፊት የተደቀነውን መንገድ ቁጭ አድርጎ ተዳከመ፡፡ ቢሆንም ፀሐይ ልትሸሽግ ሲዳዳት ከተኙበት ተነስተው የመንገዱን ጥግ ይዘው በአዲስ አበባ አቅጣጫ ጉዞአቸውን በእግር ተያያዙት፡፡
“እርምጃህን አትቀያይር በአንድ ዓይነት ፍጥነት አንድ አይነት ስፋት ተራመድ አለበለዚያ ይደክምሃል፡፡” አለ ካልቨርት እጆቹን እያወናጨፈ፤ “ከጎን ከጎኑ የሚንቶሰቶሰውን ናትናኤልን ዞር ብሎ
ተመልክቶ፡፡
አልፎ አልፎ በሩቁ የመኪና መብራት ሲታያቸው ፈጠን ብለህ ከአውራ መንገዱ እራቅ እያሉ መሬቱ ላይ በደረታቸው አየተኙ እያሳለፉ መንገዳቸውን ያለንግግር ቀጠሉ፡፡ ሁለት ጊዜ ጅቦች ሲያጋጥሟቸውም ሁለቱንም ጌዜ የካልቨርት ሽጉጥ የጥይት ጩኹት አተረፋቸው፡፡
እንዳሰሱት እስከጠዋቱ አንድ ሰዓት ድረስ አልተጓዘም፡፡ ከጠዋቱ አስራ አንድ ሰዓት አካባቢ አቃቂ ከተማ እንደደረስ ያለዕረፍት መቀጠል እንደማይችሉ ስለተረዱ ከመንገዱ ወጥቶ እራቅ ካለ ጫካ ውስጥ ገብተው ካልቨርት እንቅልፍ ይዞት ጭልጥ አለ፡፡ናትናኤል እስካሁን ያሳለፋውን ሁኔታዎች አንድ በአንድ በህሊናው እየመላለሰ ይቃኝ ጀመር፡፡ ርብቃ…
አብርሃም… የቢሮ አለቃው.… ወታደራዊ አታሼዎቹ… ነጭዋ ሲትሮይን
የምሥራች ዘውዲቱ… አዲስ አበባ ድሬዳዋ…ካልቨርት ይህ ሁሉ ውጣ
ውረድ ከርብቃ ስቃይና ከእርግዝናዋ ጋር እየተሰባጠረ ይታየው ጀመር፡፡
ርብቃን ለማዳን ምን ማድረግ አለበት? አወሬዎቹን መጋፈጥ? ከአውሬዎቹ
ጋር መደራደር? ካልቨርት ምስጢሬን ይዤ ልሙት ባይ ነው፡፡ ካልቨርትን እንደገና ማግባባትና ማሳመን ይቻላል? ወይስ የሞተ ፡ ነገር ነው? ለማናቸውም ለካልቨርት ምንም ፍንጭ ማሳየት የለበትም… ማናቸውንም ጉዳይ ከካልቨርት መደበቅ ይኖርበታል፡፡
የተጫናቸው ድካም በዙሪያቸው ከነበረው የማለዳ ውርጭ የከበደ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
....“ጥሩ እንዳትነቃነቅ::" አለ አራተኛው ሰው መሣሪያውን ደግኖ እንደያዘ ወደ ጭነት መኪናው እየተጠጋ፡፡ በእርጋታ ወደፊት እየተራመደ በዓይነ ጭነቱን ያዳብስ ጀመር፡
እራቅ ብለው ሁኔታውን በዝምታ ይከታተሉ የነበሩት ሦስት ሰዎች የመሃሉ ድንገት ተጣራና ጭንቅላቱን ወደኋላ መታ አደረገ፡፡ ወዲያው ወደ ጭነት መኪናው የተጠጋው አራተኛው ሰው ፊቱን መልሶ ወደ ጓደኞቹ ሮጥ ብሎ ተመለስና ሰብሰብ ብለው ይነጋገሩ ጀመር፡፡
“ጠዋት ምንያህል መኪናዎች ቀድመዋችሁ ወደ አዲስ አበባ
ተነስተዋል?” አለ አራተኛው ሰው ፊቱን ወደ ጭነት መኪናው ሹፌር
መልሶ ድምፁን ከፍ አድርጎ፡፡
“አንድ ሶስት አራት ይሆናሉ፡፡” አለ ከጭነት መኪናው ወርዶ የቆመው ሹፌር፡፡
ወዲያው አራቱ ሰዎች ሮጥ ሮጥ እያሉ ሬንጅሮቨራቸው ውስጥ ገቡና በአዲስ አበባ አቅጣጫ በረሩ፡፡
“ኡፍ .…ፍ!!” አለ ካልቨርት ጭንቅላቱን በተኛበት ጆንያ ላይ ጥሎ፡፡
“ሄዱ? ” አሉ ናትናኤል ሽራውን እንደተከናነበ በሹክሹክታ፡፡
“አዎ፡፡ ያለቀልን መስሎኝ ነበር::”
የጭነት መኪናው ሹፌር መኪናው ውስጥ ገብቶ ሲንቀሳቀሱ በተቻላቸው መጠን መንፈሳቸውን አረጋግተው መመካከር ያዙ፡፡
“ያላጥርጥር በየከተሞቹ ኬላዎች ላይ ይጠብቁናል፡፡ በተለይ ወደ አዲስ አበባ እየቀረብን ስንመጣ አስቸጋሪ ነው የሚሆንብን፡፡” እለ ናትናኤል፡፡
“አዎ፡፡ : ካአሁን ወዲያ ወደየትኛውም ከተማ መግባት የለብንም፡፡ ወደ ከተሞች ስንቀርብ እየወረድን ከጀርባ በግማሽ ክብ ቅርፅ በእግር ማለፍ ነው ያለን አማራጭ፡፡”
“ከናዝሬት ወዲያ ያለውን አካባቢ አውቀዋለሁ! መንገዱን በሩቅ
እይታ እስከተከተልን ድረስ ችግር አይገጥመንም::አለ ናትናኤል፡፡
ናዝሬት ከተማ ሲደርሱ እንድ አምስት ኪሎ ሜትር ሲቀራቸው ከተደበቁበት ሸራ ውስጥ ብቅ ብቅ እያሉ ከኋላና ከፊት ሌላ ተሽከርካሪ አለመኖሩን ካረጋገጡ በኋላ በጭነት፡ ላይ እየዳሁ ወደ መኪናወ ኋላ ተጠጉ፡፡
ሸራው የተጠፈረባቸውን ወፋፍራሃም ገመዶች የሙጢኝ ጨምድደው ይዘው
ቁልቁል ተንጠለጠሉ፡፡
“ተጠንቀቅ፡፡ አስፋልቱ ላይ ኣንዳታርፍ፡፡ በሁለት እግሮችህ ለማረፍና ለመቆም አትሞክር፤ ከዘለልክ በኋላ ጭንቅላትህን ቀብረህ ተንከባለል፡፡ እኔ ስዘል ተመልከት፡፡” አለ ካልቨርት በወጣትነት ዘመኑ በአገሩ ውስጥ ያሳለፋቸውን የኮማንዶ ህይቱን እያስታወሰ፡፡ "
በሰላሳ ሜትር ርቀት ልዩነት ሁለቱም የተንጠላጠሉባቸውን ገመዶች እየለቀቁ ከጭነት መኪናው ላይ ተፈናጠሩ፡፡ ካልቨርት አልተጎዳም፤ ናትናኤል ግን ግራ ክንዱ ክፉኛ ተገሸለጠ፡፡
“አስፋልቱ ላይ አትረፍ፡ እያልኩህ እንዲያውም ተርፈሃል፡፡ወደጎን
ባትንከባለል ኖሮ ይሄ አስፋልት ጭንቅላትህን ነበር የሚፈረክስልሀ፡፡” አለ
ካልቨርት እየሮጠ መጥቶ ናትናኤልን ደግፎ እያነሳው፡፡
አውራ መንገዱን እየራቁ፤ እየሸሹ የናዝሬትን ከተማ በስተቀኝ
ጀርባዋ ዞሯት::
"መንገዱ ወደቀኝ የሚታጠፍ፡ ስለሆነ ከዚህ በኋላ በቀጥታ መስመር ብንሄድ ወይም በሃያ አምስት ኪሎ ሜትር ላይ በዱከምና በሞጆ መሃል መንገድ ላይ ብቅ እንላለን፡፡ አለ ካልቨርት ካርታውን አውጥተው ሲያጠኑት ከቆዩ በኋላ፡፡
እንዳለው ከሦስት ሰዓት ተኩል የእግር ጉዞ በኋላ በሞጆ ከተማ አልፈው ከአውራ ጎዳናው ጋር ተገናኙ:: ብዙም ሳይቆዩ አነስተኛ የሕዝብ ማመላለሻ የገጠር አውቶቡስ አስቁመው ተሳፈሩ፡፡
“አዲስ ፈለጥ!“ ይላሉ አውቶብሱ ውስጥ ከሹፌሩ ጀርባ የተቀመጡ አዛውንት ድምፃቸውን ከፍ አድርገው፡፡ “ከአውቶብሱ ገብቶ
መፈተሽ የአባት... “ቆብህን አውልቅ፤ ክንብንብህን አውርድ ብሎ ነገር
ምንድነው? ወቸጉድ!”
“የሚፈልጉት ሰው አለ መሰለኝ::” አለ ባሻገር የተቀመጠ ልጅ እግር፡፡
ታድያ ቢኖርስ ባለፍንበት ከተማ ሁሉ እየቆምን ቆብና ክንብንባችንን መገፈፍ የአባት ነው?ልማድ ነው? ወይ ፈጣሪ?” ሽማግሌው ተቆጠ፡፡
“ምንድነው?” አላቸው ናትናኤል ከጎኑ የተቀመጡትን ሴትዮ::
“እንጃ! ባለፍንበት ከተማ ሁሉ መሣሪያ ደግነው እንደ ሽፍታ ሲበረብሩን ቆዩ፡፡” አሉት ሴትየዋ መደነቃቸውን፣ መገረማቸውን ለማሳየት እጃቸውን አፋቸው ላይ ጣል አድርገው፡፡
“እነማን ናቸው?” ናትናኤል ግራ የተጋባ መስሎ ጠየቃቸው፡፡
“ምኑን አወቄው ብቻ ከወለንጭቲ የጀመሩ ሰባቴ እያስቆሙ ሁለት
ሁለት፥ሦስት ሦስት እየሆኑ እንዲህ እንዲህ እያደረጋቸው ሲበረብሩን ዋሉ፡፡
ሆ! እንደ አነሳሳችንኮ ገና ቅድም ታዲስ አበባ ደርስን ነበር ጊዮርጊስ ይይላቸው”
ናትናኤል ዞር ብሎ ካልቨርትን ሹክ አለው::
ደብረዞይት ሊደርሱ ትንሽ ሲቀራቸው ተጠቃቀሱና መጀመሪያ ካልቨርት እራቅ ብሎ ደግሞ ናትናኤል ተከታትላው ወረዱ፡፡
“ምንድነው?” አለ ካልቨርት አውቶቡሱ ውስጥ የተባለውን ሁሉ አጣርቶ ለመረዳት ጓጉቶ፡፡
ናትናኤል አውቶቡሱ ውስጥ የሰማውን ሁሉ ዘርዝሮ ነገረው፡፡
“ከአሁን ወዲያ መኪና ላይ መውጣት የለብንም::” አለ ካልቨርት፡፡
“ታዲያ እንዴት አናደርጋለን?”
“አሁን ሁለታችንም የተዳከምን ይመስለኛል፡፡ ለጊዜው ከመንገድ
ፈቀቅ ብለን እንረፍና ከጨለመ ወዲያ ሌሊቱን መንገዱን ተከትለን በእግራችን እንቀጥላለን፡፡ ከበረታንና ሰሰዓት አምስት ኪሎ ሜትር ብንጓዝ እንኳን ከምሽቱ አንድ እስከ ጠዋቱ አንድ ሰዓት ስልሳ ኪሎ ሜትር ሽፈንን ማለት ነው:: ፀሐይ ስለማይበረታብን የምንሸነፍ፡ አይመስለኝም፡፡”
ከመንገዱ በስተቀኝ እርቀው ገብተው
ለብቻዋ በቆመች የግራር ዛፍ ስር በደረታቸው ተደፍተው ለማረፍ
ሞከሩ::እየጠለቀች ያለችው ፀሐይ እንደጌጥ ብታብረቀርቅም ሙቀቷ እየከዳት መጣ፡፡ አውላላ ሜዳ ላይ ብቻውን እየተመላለሰ የሚጋልበው ቀዝቃዛ ነፋስ ሰውነታቸውን ጠዘጠዘው፤ ምግብ ሳያገኝ ሁለተኛ ቀኑን የያዘው
ሰውነታቸውም ከፊት የተደቀነውን መንገድ ቁጭ አድርጎ ተዳከመ፡፡ ቢሆንም ፀሐይ ልትሸሽግ ሲዳዳት ከተኙበት ተነስተው የመንገዱን ጥግ ይዘው በአዲስ አበባ አቅጣጫ ጉዞአቸውን በእግር ተያያዙት፡፡
“እርምጃህን አትቀያይር በአንድ ዓይነት ፍጥነት አንድ አይነት ስፋት ተራመድ አለበለዚያ ይደክምሃል፡፡” አለ ካልቨርት እጆቹን እያወናጨፈ፤ “ከጎን ከጎኑ የሚንቶሰቶሰውን ናትናኤልን ዞር ብሎ
ተመልክቶ፡፡
አልፎ አልፎ በሩቁ የመኪና መብራት ሲታያቸው ፈጠን ብለህ ከአውራ መንገዱ እራቅ እያሉ መሬቱ ላይ በደረታቸው አየተኙ እያሳለፉ መንገዳቸውን ያለንግግር ቀጠሉ፡፡ ሁለት ጊዜ ጅቦች ሲያጋጥሟቸውም ሁለቱንም ጌዜ የካልቨርት ሽጉጥ የጥይት ጩኹት አተረፋቸው፡፡
እንዳሰሱት እስከጠዋቱ አንድ ሰዓት ድረስ አልተጓዘም፡፡ ከጠዋቱ አስራ አንድ ሰዓት አካባቢ አቃቂ ከተማ እንደደረስ ያለዕረፍት መቀጠል እንደማይችሉ ስለተረዱ ከመንገዱ ወጥቶ እራቅ ካለ ጫካ ውስጥ ገብተው ካልቨርት እንቅልፍ ይዞት ጭልጥ አለ፡፡ናትናኤል እስካሁን ያሳለፋውን ሁኔታዎች አንድ በአንድ በህሊናው እየመላለሰ ይቃኝ ጀመር፡፡ ርብቃ…
አብርሃም… የቢሮ አለቃው.… ወታደራዊ አታሼዎቹ… ነጭዋ ሲትሮይን
የምሥራች ዘውዲቱ… አዲስ አበባ ድሬዳዋ…ካልቨርት ይህ ሁሉ ውጣ
ውረድ ከርብቃ ስቃይና ከእርግዝናዋ ጋር እየተሰባጠረ ይታየው ጀመር፡፡
ርብቃን ለማዳን ምን ማድረግ አለበት? አወሬዎቹን መጋፈጥ? ከአውሬዎቹ
ጋር መደራደር? ካልቨርት ምስጢሬን ይዤ ልሙት ባይ ነው፡፡ ካልቨርትን እንደገና ማግባባትና ማሳመን ይቻላል? ወይስ የሞተ ፡ ነገር ነው? ለማናቸውም ለካልቨርት ምንም ፍንጭ ማሳየት የለበትም… ማናቸውንም ጉዳይ ከካልቨርት መደበቅ ይኖርበታል፡፡
የተጫናቸው ድካም በዙሪያቸው ከነበረው የማለዳ ውርጭ የከበደ
👍1
#የፍቅር_ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
....ከኮቱ ውስጥም ሽጉጥ መዝዞ በአይኗ መሀል ላይ ደቀነባት።
...ሚክ ጆንሰን ፖሊሷ ላቲሻ ሆልን ልክ እንደ ቆሻሻ እየተመለከታት
“ጉድማን በቶሎ ይፈልግሃል ብለሺኝ ነበር የመጣሁት” አላት፡፡
“አዎን መርማሪ ፖሊስ ጉድማን እንደዚያ ብለሽ ነው ደውይለት ያለኝ ጌታዬ” ብላ መለሰችለት።
ላቲሻ ከጉድማን ይልቅ ጆንሰን በጣም ንዴተኛ እንደሆነ ስለምታውቅ በጣም
ተጠንቅቃ በትህትና ነበር መልስ የምትሰጠው።ሁሉምዐየዲፓርትመንቱ ሰራተኞች ከሚክ ጆንሰን ጋር ፊት ለፊት መጋፈጥ እንደሚያዋርድ ያውቃሉ። በተለይ ደግሞ የሚጋፈጠው ሰው አይሪሽ ካቶሊክ ነጭ እና ወንድ ከሆነ ጉዱ ነው የሚፈላው፡፡
“እና የታለ እሱ?” ብሎ ጆንሰን ጥርሱን ነክሶ ጠየቃት፡፡
“አላውቅም ጌታዬ!”
“አታውቂም?!” ብሎ ጆንሰን በሹፈት መልክ ድምፁን ቀንሶ ጠየቃት::ክፍሉ ውስጥ ከሚገኘው ሶፋ ወንበር ላይም ሰምጦ ከተቀመጠ በኋላ አይኑን
በመጨፈን ንዴቱን ተቆጣጠረ። ለእሷ አስቦ ሳይሆን ሀይሉን መቆጠብ
ስላለበት ነው ንዴቱን ያላሳያት። አሁን ነገሮች በጣም አደገኛ ሆነዋል።
ስለዚህ አሁን ማወቅ ያለበት ጉድማን የት እንደሚገኝ ብቻ ነው።
ሁለቱ መርማሪ ፖሊሶች እየተወሻሹ እስከ አሁን ድረስ ዘልቀዋል። ዛሬ ላይ ደግሞ ጆንሰን የሽጉጥ ድምፅ አፋኝ የሚሸጡ ሰዎችን ሲያፈላልግ እንዳልዋለ ሁሉ ጉድማንም የመተግበሪያ አፕሊኬሽን ፈቃዱ የማን እንደሆነ ሲመረምር እንደዋለ ያውቃል። ጆንሰን የካርተር በርክሌን ባንክ ወደ ሆነው በርክሌይ ሀሞንድ ሩድ ባንክ ሄዶ ለምርመራ የሚፈልገውን ፋይል ኮፒ ሲያስደርግ በነበረበት ጊዜ ነበር በአስቸኳይ እንደሚፈለግ ይህቺ ደነዝ ሴት
ደውላ የነገረችው፡፡
ዛሬ በርክሌይ ቢሮ ውስጥ ሆኖ ነበር ጉድማን እየዋሸው ሁለቱንም ባሳወራቸው የማይገባው ዓለም ውስጥ አብሮት እንደሚሰራ የገባው። እርግጥ
ነው ገና ይሄንን ጉዳይ አብረው ምርመራ ማድረግ ከጀመሩበት ጊዜ ጀምሮ
ደመ ነፍሱ ጉድማንን እንደማያምነው ሲነግረው ነበር።
“መርማሪ ፖሊስ ጉድማን እዚህ አንተን እየጠበቀ ባለበት ጊዜ ላይ ነበር
ስልክ የተደወለለት::” አለች እና ላቲሻ በመቀጠልም “የደወለለትን ሰው ማንነት ባላውቅም ስልኩን ካወራ በኋላ ልክ ከሲኦል ተመንጥቆ እንደወጣ የሌሊት ወፍ በፍጥነት ነበር ከዚህ ቢሮ የወጣው። ፊቱ ላይ የሚታየው ነገርን ሳልጨምር ማለት ነው”
የጆንስን አዕምሮ የተለያዩ ነገሮችን እያሰበ ሆዱን ፍርሃት ፍርሀት አለው።
ላቲሻን ከእሱ እና ጉድማን የጋራ ቢሮ አስወጣት እና በሩን ዘግቶ የጉድማን ወንበር ላይ ቁጭ አለ።
አሁን ነገሩ እየከረረ ነው ፤ ነገር ግን ተስፋ መቁረጥ አይኖርበትም፡፡
አስብ!”
የጉድማን ዴስክ ሁሌም ጥርት ያለ እና የተደራጀ ነው። የዶክተር ሮበርትስ አድራሻ ከጀርባው የተፃፈበት ኤንቨሎፕ እና የጉድማን ስልክ ዴስኩ ላይ ይገኛሉ። ይሄ ደግሞ ጉድማን በጣም በከፍተኛ ተስፋ መቁረጥ ውስጥ በመሆኑ የተነሳ ነው እንጂ ጉድማን ስልኩን ረስቶ መቼም እንደማይሄድ ያውቀዋል። ጆንሰን ኤንቨሎፕን አንስቶ የዊሊያምስን ደረሰኝ እና ከጀርባው የተፃፈውን የኒኪን እጅ ፅሁፍ ማስታወሻውን በጥንቃቄ ሲመለከት ቆየ።
በተለይ ደግሞ የእሱን ስም ከኤንቨሎፕ ላይ ሲያነብ ልቡን አፈነው። ጆንሰን
እዚህ ነገር ውስጥ እስከ አንገቱ ነው ያለበት! የማትረባ ሴት! አንገት ድረስ
መጥለቅ ምን ማለት እንደሆነ ሊያሳያት ነበር።
ኤንቨሎፕን ኪሱ ውስጥ ከተተ እና የጉድማንን ስልክ አንስቶ ከበፊት
ጀምሮ ሸምድዶ የያዘውን የስልኩን ኮድ ቁጥር ፃፈ እና ከፈተው።የመልዕክት ሳጥኑን እና የደወላቸውን ቁጥሮች በጣቱ ወደ ታች ሲያደርግ ቆይቶ በመጨረሻ ላይ የሚፈልገውን ነገር አገኘ።
ወደ ራሱ ስልክም ከጉድማን ስልክ ላይ ያለውን መረጃ አዘዋወረ እና የተላከ መልዕክት የሚለው ቦታ ላይ ገብቶም መረጃውን አጠፋ:: ሰዓቱን ሲመለከትም ልቡ በፍርሃት መደለቅ ጀመረች፡፡ 12:20 ይላል! ይሄ እንዴት ሊሆን ቻለ? ምናልባት ዘግይቶ ቢሆንስ?
ሽጉጡን እና ተጨማሪ የሽጉጡ ካርታዎች ቀልሃቸው ሙሉ መሆኑን አረጋግጦም በሩን ከፍቶ እየሮጠ ወጣ፡፡
አሁን ይህንን የተረገመ ምርመራ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ መጨረስ ይኖርበታል።
ኒኪ አይኗን ጨፍና ህይወቷን የሚያሳጣትን ጥይት ድምፅ እየጠበቀች
ነው። የዊሊን ሬሳ ስታይ የተሰማት ከፍተኛ ፍርሃት በንኖ ጠፋ እና በተስፋ መቁረጥ ተተካ፡፡ በተለይ ደግሞ ለማወቅ የምትፈልጋቸውን ነገሮች ሳታውቅ
መሞቷን ስታስብ ድንዛዜ ተቆጣጠራት፡፡
የምትጠብቀው የጥይት ድምፅን መስማት አልቻለችም። አይኗን
ስትገልፅም የሮድሪጌዝ አይኖች ላይ ጭካኔን እና መገረምን ተመለከተች፡፡
“ምን ያስቸኩልሻል ዶክተር ሮበርትስ፡፡ ወደ ፈጣሪሽ ከመሄድሽ በፊት ማውራት አትፈልጊም እንዴ?” አላት፡፡
“ዊሊ ባደንን አንተ ነህ የገደልከው?” ብላ በእርጋታ ጠየቀችው። እርግጥ ነው ሊገድላት ነው። ግን ከመሞቷ በፊት መልሶችን መስማት ትፈልጋላች፡፡
“ታዲያስ?” ብሎ ምስጋና የሚሰጣት ይመስል አጎነበሰ፡፡
“ለምን?
“ለምን አልገድለውም?” ብሎ ሳቀባት እና “እንዴ ያደረግኩትን ሥራ እንዳልወደድሽው እያየሁ እንዳይሆን ብቻ! የሆነ አጭበርባሪ አሳማ ነገር እኮ
ነው።”
“ለምን?”
“ተስገበገበአ!” አላት እና በመቀጠልም “አብረን በምንሰራው ቢዝነስ ውስጥ
ሜክሲኮ ውስጥ ከተስማማነው ውጪ ብዙ ገንዘብ ከእኔ ላይ መውሰድ
ጀመረ። ሜክሲኮ እያለን ጠንቃቃ ነበር፡፡ እዚህ ሎስ አንጀለስ ከመጣ በኋላ
ግን ራሱን አይነኬ አድርጎ መቁጠር ጀመረ፡፡” አላት እና ወደ ዊሊ ሬሳ ዞሮ
“ይህ ሀሳቡ ደግሞ የማይረባ እና ስህተት እንደሆነ ላሳየው ፈለግኩኝ። ማንም ሰው ከእኔ ጋር ጠላትነት ውስጥ ከገባ የትም ቢገባ ፈልጌ አገኘዋለሁ::” ካላት በኋላ በጣም በሚያስፈራ ሁኔታ አፍጥጦ ሲያያት ኒኪ ወዲያውኑ ተኩሶ የሚገድላት መስላት:: “እሺ ሌላ ጥያቄ አለሽ?” አላት፡፡
“እኔን ምንድነው ያደረግካት?”
ሮድሪጌዝም በጥያቄዋ ተገርሞ አያት እና
“እኔን እሷ እንዲደረግባት ከምትፈልጋቸው ነገሮች ውጪ ምንም ነገር አላደረኳትም” አለ እና ፈገግ ብሎም
“ሚስቴ ሰዎች እንዲጫኗት ትፈልጋለች። ዶክተር ሮበርትስ አንቺ ይሄ የሚስቴ ነገር ለምን እንዳልገባሽ አላውቅም። አሁንም ቢሆን ይሄ ነገር አይገባሽም። ምክንያቱም አኔን ከእኔ በላይ አታውቂያትም።”
“በጣም እንደምትፈራህ አውቃለሁ” አለችው እና ኒኪ በመቀጠልም
አንተ ሸሽታ ወደ እዚህ የመጣችው አንተ አስረሃት የምትኖረው ኑሮ ከአቅሟ በላይ ስለሆነባት ነው” ስትለው ፈገግታው ጨለመ::
አንቺ ስለ እሷ ስትከራከሪላት ሳይ በጣም ይገርመኛል፡፡ እንዴ! ወደዚህ
ልታስገድልሽ እንደሆነ እያወቅሽ መሆኑ ደግሞ የባሰ አስደምሞኛል።” አላት፡፡
“ምክንያቱም ስላስገደድካት ነው! የዊሊ ባድንን ግድያ አስገድደህ እንድታየው እንዳደረካት ሁሉ ማለት ነው።” አለችው፡፡
ሊዊስም ራሱን በአሉታ ነቅንቆ “ዶክተር ሮበርትስ ነገሩ እስካሁን አልገባሽም ማለት ነው? እሷ ይህንን ነገር የምታደርግልኝ እኮ በጣም
ስለምትወደኝ ነው። ላንቺ ምንም አይነት ስሜት ቢኖራትም በመጨረሻ ላይ
አኔ እኔን ለመከላከል ስትል ማንኛውንም ነገር ታደርግልኛለች። ምንም እንኳን በመካከላችን ያለውን ፍቅር ልታጠፊ ያላደረግሽው ነገር ባይኖርም
አኔ ልቧ አሁንም ከእኔ ጋር ነው።”
“ውሸት!” ብላ ኒኪ ከመለሰችለት በኋላ ግን ደውላ ወደዚህ እንዳስመጣቻትና እንዲሁም ደግሞ በዊሊ ባደን ግድያ ላይ ስለነበራት ድርሻ ምን ይሆን? ብላ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
....ከኮቱ ውስጥም ሽጉጥ መዝዞ በአይኗ መሀል ላይ ደቀነባት።
...ሚክ ጆንሰን ፖሊሷ ላቲሻ ሆልን ልክ እንደ ቆሻሻ እየተመለከታት
“ጉድማን በቶሎ ይፈልግሃል ብለሺኝ ነበር የመጣሁት” አላት፡፡
“አዎን መርማሪ ፖሊስ ጉድማን እንደዚያ ብለሽ ነው ደውይለት ያለኝ ጌታዬ” ብላ መለሰችለት።
ላቲሻ ከጉድማን ይልቅ ጆንሰን በጣም ንዴተኛ እንደሆነ ስለምታውቅ በጣም
ተጠንቅቃ በትህትና ነበር መልስ የምትሰጠው።ሁሉምዐየዲፓርትመንቱ ሰራተኞች ከሚክ ጆንሰን ጋር ፊት ለፊት መጋፈጥ እንደሚያዋርድ ያውቃሉ። በተለይ ደግሞ የሚጋፈጠው ሰው አይሪሽ ካቶሊክ ነጭ እና ወንድ ከሆነ ጉዱ ነው የሚፈላው፡፡
“እና የታለ እሱ?” ብሎ ጆንሰን ጥርሱን ነክሶ ጠየቃት፡፡
“አላውቅም ጌታዬ!”
“አታውቂም?!” ብሎ ጆንሰን በሹፈት መልክ ድምፁን ቀንሶ ጠየቃት::ክፍሉ ውስጥ ከሚገኘው ሶፋ ወንበር ላይም ሰምጦ ከተቀመጠ በኋላ አይኑን
በመጨፈን ንዴቱን ተቆጣጠረ። ለእሷ አስቦ ሳይሆን ሀይሉን መቆጠብ
ስላለበት ነው ንዴቱን ያላሳያት። አሁን ነገሮች በጣም አደገኛ ሆነዋል።
ስለዚህ አሁን ማወቅ ያለበት ጉድማን የት እንደሚገኝ ብቻ ነው።
ሁለቱ መርማሪ ፖሊሶች እየተወሻሹ እስከ አሁን ድረስ ዘልቀዋል። ዛሬ ላይ ደግሞ ጆንሰን የሽጉጥ ድምፅ አፋኝ የሚሸጡ ሰዎችን ሲያፈላልግ እንዳልዋለ ሁሉ ጉድማንም የመተግበሪያ አፕሊኬሽን ፈቃዱ የማን እንደሆነ ሲመረምር እንደዋለ ያውቃል። ጆንሰን የካርተር በርክሌን ባንክ ወደ ሆነው በርክሌይ ሀሞንድ ሩድ ባንክ ሄዶ ለምርመራ የሚፈልገውን ፋይል ኮፒ ሲያስደርግ በነበረበት ጊዜ ነበር በአስቸኳይ እንደሚፈለግ ይህቺ ደነዝ ሴት
ደውላ የነገረችው፡፡
ዛሬ በርክሌይ ቢሮ ውስጥ ሆኖ ነበር ጉድማን እየዋሸው ሁለቱንም ባሳወራቸው የማይገባው ዓለም ውስጥ አብሮት እንደሚሰራ የገባው። እርግጥ
ነው ገና ይሄንን ጉዳይ አብረው ምርመራ ማድረግ ከጀመሩበት ጊዜ ጀምሮ
ደመ ነፍሱ ጉድማንን እንደማያምነው ሲነግረው ነበር።
“መርማሪ ፖሊስ ጉድማን እዚህ አንተን እየጠበቀ ባለበት ጊዜ ላይ ነበር
ስልክ የተደወለለት::” አለች እና ላቲሻ በመቀጠልም “የደወለለትን ሰው ማንነት ባላውቅም ስልኩን ካወራ በኋላ ልክ ከሲኦል ተመንጥቆ እንደወጣ የሌሊት ወፍ በፍጥነት ነበር ከዚህ ቢሮ የወጣው። ፊቱ ላይ የሚታየው ነገርን ሳልጨምር ማለት ነው”
የጆንስን አዕምሮ የተለያዩ ነገሮችን እያሰበ ሆዱን ፍርሃት ፍርሀት አለው።
ላቲሻን ከእሱ እና ጉድማን የጋራ ቢሮ አስወጣት እና በሩን ዘግቶ የጉድማን ወንበር ላይ ቁጭ አለ።
አሁን ነገሩ እየከረረ ነው ፤ ነገር ግን ተስፋ መቁረጥ አይኖርበትም፡፡
አስብ!”
የጉድማን ዴስክ ሁሌም ጥርት ያለ እና የተደራጀ ነው። የዶክተር ሮበርትስ አድራሻ ከጀርባው የተፃፈበት ኤንቨሎፕ እና የጉድማን ስልክ ዴስኩ ላይ ይገኛሉ። ይሄ ደግሞ ጉድማን በጣም በከፍተኛ ተስፋ መቁረጥ ውስጥ በመሆኑ የተነሳ ነው እንጂ ጉድማን ስልኩን ረስቶ መቼም እንደማይሄድ ያውቀዋል። ጆንሰን ኤንቨሎፕን አንስቶ የዊሊያምስን ደረሰኝ እና ከጀርባው የተፃፈውን የኒኪን እጅ ፅሁፍ ማስታወሻውን በጥንቃቄ ሲመለከት ቆየ።
በተለይ ደግሞ የእሱን ስም ከኤንቨሎፕ ላይ ሲያነብ ልቡን አፈነው። ጆንሰን
እዚህ ነገር ውስጥ እስከ አንገቱ ነው ያለበት! የማትረባ ሴት! አንገት ድረስ
መጥለቅ ምን ማለት እንደሆነ ሊያሳያት ነበር።
ኤንቨሎፕን ኪሱ ውስጥ ከተተ እና የጉድማንን ስልክ አንስቶ ከበፊት
ጀምሮ ሸምድዶ የያዘውን የስልኩን ኮድ ቁጥር ፃፈ እና ከፈተው።የመልዕክት ሳጥኑን እና የደወላቸውን ቁጥሮች በጣቱ ወደ ታች ሲያደርግ ቆይቶ በመጨረሻ ላይ የሚፈልገውን ነገር አገኘ።
ወደ ራሱ ስልክም ከጉድማን ስልክ ላይ ያለውን መረጃ አዘዋወረ እና የተላከ መልዕክት የሚለው ቦታ ላይ ገብቶም መረጃውን አጠፋ:: ሰዓቱን ሲመለከትም ልቡ በፍርሃት መደለቅ ጀመረች፡፡ 12:20 ይላል! ይሄ እንዴት ሊሆን ቻለ? ምናልባት ዘግይቶ ቢሆንስ?
ሽጉጡን እና ተጨማሪ የሽጉጡ ካርታዎች ቀልሃቸው ሙሉ መሆኑን አረጋግጦም በሩን ከፍቶ እየሮጠ ወጣ፡፡
አሁን ይህንን የተረገመ ምርመራ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ መጨረስ ይኖርበታል።
ኒኪ አይኗን ጨፍና ህይወቷን የሚያሳጣትን ጥይት ድምፅ እየጠበቀች
ነው። የዊሊን ሬሳ ስታይ የተሰማት ከፍተኛ ፍርሃት በንኖ ጠፋ እና በተስፋ መቁረጥ ተተካ፡፡ በተለይ ደግሞ ለማወቅ የምትፈልጋቸውን ነገሮች ሳታውቅ
መሞቷን ስታስብ ድንዛዜ ተቆጣጠራት፡፡
የምትጠብቀው የጥይት ድምፅን መስማት አልቻለችም። አይኗን
ስትገልፅም የሮድሪጌዝ አይኖች ላይ ጭካኔን እና መገረምን ተመለከተች፡፡
“ምን ያስቸኩልሻል ዶክተር ሮበርትስ፡፡ ወደ ፈጣሪሽ ከመሄድሽ በፊት ማውራት አትፈልጊም እንዴ?” አላት፡፡
“ዊሊ ባደንን አንተ ነህ የገደልከው?” ብላ በእርጋታ ጠየቀችው። እርግጥ ነው ሊገድላት ነው። ግን ከመሞቷ በፊት መልሶችን መስማት ትፈልጋላች፡፡
“ታዲያስ?” ብሎ ምስጋና የሚሰጣት ይመስል አጎነበሰ፡፡
“ለምን?
“ለምን አልገድለውም?” ብሎ ሳቀባት እና “እንዴ ያደረግኩትን ሥራ እንዳልወደድሽው እያየሁ እንዳይሆን ብቻ! የሆነ አጭበርባሪ አሳማ ነገር እኮ
ነው።”
“ለምን?”
“ተስገበገበአ!” አላት እና በመቀጠልም “አብረን በምንሰራው ቢዝነስ ውስጥ
ሜክሲኮ ውስጥ ከተስማማነው ውጪ ብዙ ገንዘብ ከእኔ ላይ መውሰድ
ጀመረ። ሜክሲኮ እያለን ጠንቃቃ ነበር፡፡ እዚህ ሎስ አንጀለስ ከመጣ በኋላ
ግን ራሱን አይነኬ አድርጎ መቁጠር ጀመረ፡፡” አላት እና ወደ ዊሊ ሬሳ ዞሮ
“ይህ ሀሳቡ ደግሞ የማይረባ እና ስህተት እንደሆነ ላሳየው ፈለግኩኝ። ማንም ሰው ከእኔ ጋር ጠላትነት ውስጥ ከገባ የትም ቢገባ ፈልጌ አገኘዋለሁ::” ካላት በኋላ በጣም በሚያስፈራ ሁኔታ አፍጥጦ ሲያያት ኒኪ ወዲያውኑ ተኩሶ የሚገድላት መስላት:: “እሺ ሌላ ጥያቄ አለሽ?” አላት፡፡
“እኔን ምንድነው ያደረግካት?”
ሮድሪጌዝም በጥያቄዋ ተገርሞ አያት እና
“እኔን እሷ እንዲደረግባት ከምትፈልጋቸው ነገሮች ውጪ ምንም ነገር አላደረኳትም” አለ እና ፈገግ ብሎም
“ሚስቴ ሰዎች እንዲጫኗት ትፈልጋለች። ዶክተር ሮበርትስ አንቺ ይሄ የሚስቴ ነገር ለምን እንዳልገባሽ አላውቅም። አሁንም ቢሆን ይሄ ነገር አይገባሽም። ምክንያቱም አኔን ከእኔ በላይ አታውቂያትም።”
“በጣም እንደምትፈራህ አውቃለሁ” አለችው እና ኒኪ በመቀጠልም
አንተ ሸሽታ ወደ እዚህ የመጣችው አንተ አስረሃት የምትኖረው ኑሮ ከአቅሟ በላይ ስለሆነባት ነው” ስትለው ፈገግታው ጨለመ::
አንቺ ስለ እሷ ስትከራከሪላት ሳይ በጣም ይገርመኛል፡፡ እንዴ! ወደዚህ
ልታስገድልሽ እንደሆነ እያወቅሽ መሆኑ ደግሞ የባሰ አስደምሞኛል።” አላት፡፡
“ምክንያቱም ስላስገደድካት ነው! የዊሊ ባድንን ግድያ አስገድደህ እንድታየው እንዳደረካት ሁሉ ማለት ነው።” አለችው፡፡
ሊዊስም ራሱን በአሉታ ነቅንቆ “ዶክተር ሮበርትስ ነገሩ እስካሁን አልገባሽም ማለት ነው? እሷ ይህንን ነገር የምታደርግልኝ እኮ በጣም
ስለምትወደኝ ነው። ላንቺ ምንም አይነት ስሜት ቢኖራትም በመጨረሻ ላይ
አኔ እኔን ለመከላከል ስትል ማንኛውንም ነገር ታደርግልኛለች። ምንም እንኳን በመካከላችን ያለውን ፍቅር ልታጠፊ ያላደረግሽው ነገር ባይኖርም
አኔ ልቧ አሁንም ከእኔ ጋር ነው።”
“ውሸት!” ብላ ኒኪ ከመለሰችለት በኋላ ግን ደውላ ወደዚህ እንዳስመጣቻትና እንዲሁም ደግሞ በዊሊ ባደን ግድያ ላይ ስለነበራት ድርሻ ምን ይሆን? ብላ
👍1
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገ
...አፍንጫ ጎራዳነቷ ውበቷን አደመቀው እንጂ አላደበዘዘውም፡፡ ስላማዊት ብዙ ሰው ቢረባረብባትም ከሁሉ የበለጠ የምትቀርበውና ወዳጇ
መሆኑ በብዙዎቹ ዘንድ እየታወቀ የመጣው ታደሰ ነው። ታደሰ መልኩ ጥቁር ሆኖ ረዘም ያለ ጉብል ነው፡፡ እሱ ሲመጣ ሰላማዊት ማንንም አታነጋግርም፡፡ ሄዳ እሱ ላይ ጥብቅ ነው። ይሄ ሁኔታ በፅጌ አማካኝነት ለሰፈሩ ሴተኛ አዳሪዎች ሁሉ ስለተወራ ታደሰ ብቅ ማለቱን ሲያዩ ስሟን
እንደማስቲካ ሲያኝኩት ይውላሉ።
“አሳበዳት እንጂ! ነፍሷን አጠፋላት!ታደሰን አታውቂውም እንዴ? ደላላ ነው እኮ! ኸረ በሌላም የሚጠረጠር ሰው ነው አሉ። አንዱ ውሽማዬ ስለሱ ነግሮኛል።ነጭ ለባሽ ነው ተብሎ ይጠረጠራል ብሎ አጫውቶኛል”
“አረ እባክሽ?! ነጭ ለባሽ ?ምን አስነክቷት ይሆን እንደዚህ በፍቅር የከነፈችለት?”
“ትቀልጃለሽ እንዴ? ያቅማታላ! ብር እንደ አሸዋ ይበትንላታላ! እስቲ ይታይሽ? ደላላ ነው። በዚህ ላይ ደግሞ በነጭ ለባሽነቱ መንግሥት ይከፍለዋል! ገንዘብ ካለ በሰማይ መንገድ አለ ነው
“ምን እያቀመሰቻቸው ይሆን ወንዶቹ ሁሉ እንደዚህ በሷ ላይ የሚረባረቡት በናትሽ?”
“ወረት ነው እባክሽ! ወረት! አዲስ ጀማሪ አይደለችም? በወረት ነው እንደ ንብ የሚከቧት”
የታደሰ ደግሞ ባሰ፡፡ ፍቅር ድብን አድርጎ ገድሎታል እኮ፡፡ ምን ማለትሽ ነው? አሁን አሁንማ ግንባሯን ሳይሳለም አይውልምኮ! እኔም ሳላየው የዋልኩበት ቀን የለም”
“ምን ታደርጊዋለሽ አጅሬ የወረት ፍቅር ነዋ!” ተንሾካሾኩባት። እውነትም ከዚያ ሁሉ የወንድ መንጋ መካከል ለታደስ ልዩ ፍቅር ነበራት። ታደሰ ፍቅሩን በብዙ መልኩ የሚገለፅላትና የሚያስፈልጋትን ሁሉ የሚያሟላላት የስካር ሳይሆን እውነተኛ ጓደኛዋ ነበር።
ዛሬም እንደ ወትሮው ካፖርቱን ከላይ ጣል አድርጉ ባርኔጣውን ደፍቶ አንገቱ ላይ ሻርፕ ጠምጥሞ ተፍተፍ የሚለው ወደሷ ነበር፡፡ ከሁለተኛ ፖሊስ ጣቢያ ወደ ቀኝ ተገንጥሎ ወደ እሪ በከንቱ የሚወስደውን ቀጭን የአስፋልት መንገድ ተከትሎ ወደ ፍቅረኛው ወደ ሰላማዊት ለመድረስ እየተጣደፈ ነበር፡፡
ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ሆኗል። በአላፊ አግዳሚ ላይ ዐይኖቻቸውን እያፈጠጡ የሚያስፈራሩ ሴተኛ አዳሪዎች ብቅ ብቅ ማለት ጀምረዋል። በዚህ
ሰዓት እብዱ ምንሽንሽ ከአካባቢው አይታጣም ነበር፡፡ አንዴ ወዲህ አንዴ ወዲያ እየዘለለ ድንጋይ እያነሳ ድንጋይ እየጣለ ይሯሯጥ ነበር፡፡ ሣንቲም
ይለምናል። ከሰጡት ይቀበላል፡፡ ዝም ካሉት ደንታም የለው። የሱ ቁም ነገር መዝለል፣ መዝለል፣ ድንጋይ መፈንቀል፣ ድንጋይ ማንሳት ድንጋይ መጣል ብቻ ነው፡፡ ዛሬ ግን በሱ ምትክ ሰካራሙ ታከለ ያንን የማያስከፍል ድራማውን እያሳየ ለሴተኛ አዳሪዎች መሳለቂያና መደበሪያ ሆኖላቸው ነበር፡፡ መጀመሪያ ቀይ አጣብቂኝ ሱሪ ለብሳ ፀጉሯን እንደ ገዳይ ጐፈሬ ወዳቆመችው ሴት ቤት ጥልቅ ብሎ ገባ..
ሰካራሙ ታከለ ትዳሩን በመጠጥ ምክንያት ካፈረሰ በኋላ መቅኖ አጥቶ በደሞዝ ሰሞን ሲጠጣ፣ያገኘውን ሲጋብዝ፣ ሲሸልም፣ ሲበትን ይከርምና
ባዶ ኪሱን ጨረቃ አስመስሎ መውጣት ልማዱ ነው። እንደምንሽንሽ ሲለይለት አንድ ሀሙስ ብቻ ነው የቀረው፡፡ ሴትዮዋ በሯን ዘጋችና...
“እሺ ሂሣብ በቅድሚያ!” አለችው።
“ም. ን. ድ. ነው... ቅርሚያ ቅርሚያ! የምትይው? እኔን አታ..
አታምኝ.. ኝ.. ኝምምም?” አላት ልፍድድ ባለ የስካር ንግግር።
“ኡፋ! ሰውዬ ወሬ አታብዛ ! የምትከፍል ከሆነ በቅድሚያ ክፈልና እሺ። አለበለዚያ ውጣልኝ!ገበያዬን አትዝጋ!” አለችና አንባረቀችበት። ታከለ በጠጅና በአረቄ ብዛት የደነበሹ ዐይኖቹን ብልጥጥ አድርጎ ሲመለከታት ተንኮል የቋጠረ አመፀኛ ዝንጀሮ እንጂ ለጉዳይ የገባ እንግዳ አይመስልም ነበር።
በል ተናገር?! ያለበለዚያ ውጣ!” የዘጋችውን በር መልሳ እየከፈተች ጭኽችበት።
“ቆይ .. እ- ሺ ቆይ! ቆይ!” አለና ወደ ኪሱ ገባ፡፡ ያገኘው ሰላሳ አምስት ሣንቲም ብቻ ነበር።
እሺ ያው..ልሽ!
አትፈልጊምምም.?” እየተንተባተበ፡፡ ብልጭ አለባት።
ከኋላው አሽቀንጥራ ስትወረውረው ከፊት ለፊቱ ካለው ቆሻሻ ውሃ ከሚ ወርድበት ቦይ ውስጥ ሂዶ ተወተፈ፡፡ ከዚያም እየተውተረተረ ተነሳና ሣንቲምቹን መለቃቀም ጀመረ፡፡ እንደምንም ብሎ ሃያ አምስት ሣንቲም አገኘ።
ትርዒቱን እያዩ ወደሚሳሳቁት ግራና ቀኙን ወደተኮለኮሉ ሴተኛ አዳሪዎች እየተመለከተ“ይህቺን... ፈላጊ!.. ይህቺን... ይህቺን.” እያለ ሳንቲ ሞቹን ሽክ... ሽክ... ሽክ ሲያደርጋቸው የበለጠ በሳቅ ፈነዱ።
“አንተ ጠንባራ ሰካራም ድራሽህ ይጥፋ! የቀረችህ እሷ ናት። ሂድና ለሚስትህ ቀሚስ ግዛበት ፉዞ!” የስድብ መአት አወረዱበት። እሱም እየተንገዳገደ ቁልቁል ወረደ። ታደሰ ይህ ትርዒት የሚካሄድበትን አካባቢ
አልፎ ወደ ሰላማዊት ዘንድ ሊደርስ ትንሽ ቀርቶታል። አስፋልቱን ከመሻገሩ በፊት ግን ቆም ብሎ ምን ይዞላት እንደሚሄድ አሰላሰለ። እንደ
ሴተኛ አዳሪነቷ ሳይሆን እንደ ሚስቱ ያስብላት ስለጀመረ ወደ መኖሪያ ቤቱ የሚሄድ አባወራ እንጂ ወደ መሸታ ቤት የሚሄድ ጠጪ አይመስልም ነበር፡፡ ሰላማዊትም ከልቧ ስለምትወደው እሱ ከመጣ ሌላው ጠጪ
ሰው መስሎ አይታያትም፡፡ እንደሚጨነቅላት ስለምታውቅ አፀፋውን ፍቅር እየሰጠችው ነው፡፡ ታደስ ከእማማ ወደሬ ቤት ከፍ ብሎ ወደሚገኘው ሉካንዳ ቤት ገባና ከሽንጥ ሥጋ ላይ ሁለት ኪሎ ግራም አስቆርጦ አስጠቅልሎ ሄደ። ወይዘሮ ወደሬ የታደሰ ውለታ እየከበዳቸው ስለመጣ በሱ ምክንያት ሰላማዊትን ማክበርና መፍራት ጀምረዋል። ታደሰ ወደ ቤት ሊገባ ካለ በኋላ ምናምን እንዳቋረጠው ሰው ወደ ኋላው ሰግጠጥ አለና ቆመ፡፡ቀስ ብሎ በጓሮ በኩል ዞረ። የጓሮውን በር ያለሱ የሚደፍረው የለም።
“ሰላምን ጥሪያት” አላት ላፅጌ። ሰላማዊት ፅጌ ስትነግራት ሮጣ መጣች።
“ውይ ታዴ!”እቅፍ አድርጋ ሳመችውና በእጁ የያዘውን ተቀበለችው።
በጓሮ በኩል ዞሮ የገባው የያዘውን ሊሰጣት መሰላት። ድርጊቱ የበለጠ ገረማት። ማንም እሱ የሚያደርገውን አያደርግላትም። የፈለገውን ያክል ገንዘብ አስታቅፈዋት ቢሄዱ ታደሰ የሚያስበውን ያክል አስበውላት አያውቁም፡፡ በበዓላት ቀን ሹልክ ብሎ ይመጣና ገንዘብ ይሰጣታል። እንዳይደብርሽ እያለ ትያትርና ሙዚቃ ቤት ወስዶ ያዝናናታል፡፡
“አይ ታደሰ?አሁንስ አበዛው ምነው እሱ እንዲህ ተጨነቀ? እኔ ውለታ
ሲበዛብኝ ደስ አይለኝም፡፡ ይከብደኛል። ከሌላው የተለየ ለሱ ምን የተደረገለት ነገር አለ?” ወይዘሮ ወደሬ ስለታደሰ ተጨነቁ፡፡
“ታድዬ እቤት ትገባለህ ወይስ እዚሁ ጠላ ይዤልህ ልምጣ?” ስትል ጠየቀችው።
“እቤት አልገባም እዚችው ጓሮ ቁጭ ብለን ትንሽ አጫውቺኝና ጠላ ጠጥቼ እሄዳለሁ” አሁን አሁን የገባው ጠጪ ሁሉ እንደፈለገው እየጎተተ ሲያሻሻት፣ ሲያቅፋት፣ ሲስማት፣ ሲደባብሳት ማየት እያስጠላው መጥቷል።
“እሺ የኔ ቆንጆ ይዤልህ ልምጣ” አለችና ተመልሳ ገባች።
“ታዴ ወደ ቤት አይገባም እንዴ ሰላም?” አሉ ወይዘሮ ወደሬ።
“ውጭ ይሻለኛል ብሉኝ እኮ ነው”
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገ
...አፍንጫ ጎራዳነቷ ውበቷን አደመቀው እንጂ አላደበዘዘውም፡፡ ስላማዊት ብዙ ሰው ቢረባረብባትም ከሁሉ የበለጠ የምትቀርበውና ወዳጇ
መሆኑ በብዙዎቹ ዘንድ እየታወቀ የመጣው ታደሰ ነው። ታደሰ መልኩ ጥቁር ሆኖ ረዘም ያለ ጉብል ነው፡፡ እሱ ሲመጣ ሰላማዊት ማንንም አታነጋግርም፡፡ ሄዳ እሱ ላይ ጥብቅ ነው። ይሄ ሁኔታ በፅጌ አማካኝነት ለሰፈሩ ሴተኛ አዳሪዎች ሁሉ ስለተወራ ታደሰ ብቅ ማለቱን ሲያዩ ስሟን
እንደማስቲካ ሲያኝኩት ይውላሉ።
“አሳበዳት እንጂ! ነፍሷን አጠፋላት!ታደሰን አታውቂውም እንዴ? ደላላ ነው እኮ! ኸረ በሌላም የሚጠረጠር ሰው ነው አሉ። አንዱ ውሽማዬ ስለሱ ነግሮኛል።ነጭ ለባሽ ነው ተብሎ ይጠረጠራል ብሎ አጫውቶኛል”
“አረ እባክሽ?! ነጭ ለባሽ ?ምን አስነክቷት ይሆን እንደዚህ በፍቅር የከነፈችለት?”
“ትቀልጃለሽ እንዴ? ያቅማታላ! ብር እንደ አሸዋ ይበትንላታላ! እስቲ ይታይሽ? ደላላ ነው። በዚህ ላይ ደግሞ በነጭ ለባሽነቱ መንግሥት ይከፍለዋል! ገንዘብ ካለ በሰማይ መንገድ አለ ነው
“ምን እያቀመሰቻቸው ይሆን ወንዶቹ ሁሉ እንደዚህ በሷ ላይ የሚረባረቡት በናትሽ?”
“ወረት ነው እባክሽ! ወረት! አዲስ ጀማሪ አይደለችም? በወረት ነው እንደ ንብ የሚከቧት”
የታደሰ ደግሞ ባሰ፡፡ ፍቅር ድብን አድርጎ ገድሎታል እኮ፡፡ ምን ማለትሽ ነው? አሁን አሁንማ ግንባሯን ሳይሳለም አይውልምኮ! እኔም ሳላየው የዋልኩበት ቀን የለም”
“ምን ታደርጊዋለሽ አጅሬ የወረት ፍቅር ነዋ!” ተንሾካሾኩባት። እውነትም ከዚያ ሁሉ የወንድ መንጋ መካከል ለታደስ ልዩ ፍቅር ነበራት። ታደሰ ፍቅሩን በብዙ መልኩ የሚገለፅላትና የሚያስፈልጋትን ሁሉ የሚያሟላላት የስካር ሳይሆን እውነተኛ ጓደኛዋ ነበር።
ዛሬም እንደ ወትሮው ካፖርቱን ከላይ ጣል አድርጉ ባርኔጣውን ደፍቶ አንገቱ ላይ ሻርፕ ጠምጥሞ ተፍተፍ የሚለው ወደሷ ነበር፡፡ ከሁለተኛ ፖሊስ ጣቢያ ወደ ቀኝ ተገንጥሎ ወደ እሪ በከንቱ የሚወስደውን ቀጭን የአስፋልት መንገድ ተከትሎ ወደ ፍቅረኛው ወደ ሰላማዊት ለመድረስ እየተጣደፈ ነበር፡፡
ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ሆኗል። በአላፊ አግዳሚ ላይ ዐይኖቻቸውን እያፈጠጡ የሚያስፈራሩ ሴተኛ አዳሪዎች ብቅ ብቅ ማለት ጀምረዋል። በዚህ
ሰዓት እብዱ ምንሽንሽ ከአካባቢው አይታጣም ነበር፡፡ አንዴ ወዲህ አንዴ ወዲያ እየዘለለ ድንጋይ እያነሳ ድንጋይ እየጣለ ይሯሯጥ ነበር፡፡ ሣንቲም
ይለምናል። ከሰጡት ይቀበላል፡፡ ዝም ካሉት ደንታም የለው። የሱ ቁም ነገር መዝለል፣ መዝለል፣ ድንጋይ መፈንቀል፣ ድንጋይ ማንሳት ድንጋይ መጣል ብቻ ነው፡፡ ዛሬ ግን በሱ ምትክ ሰካራሙ ታከለ ያንን የማያስከፍል ድራማውን እያሳየ ለሴተኛ አዳሪዎች መሳለቂያና መደበሪያ ሆኖላቸው ነበር፡፡ መጀመሪያ ቀይ አጣብቂኝ ሱሪ ለብሳ ፀጉሯን እንደ ገዳይ ጐፈሬ ወዳቆመችው ሴት ቤት ጥልቅ ብሎ ገባ..
ሰካራሙ ታከለ ትዳሩን በመጠጥ ምክንያት ካፈረሰ በኋላ መቅኖ አጥቶ በደሞዝ ሰሞን ሲጠጣ፣ያገኘውን ሲጋብዝ፣ ሲሸልም፣ ሲበትን ይከርምና
ባዶ ኪሱን ጨረቃ አስመስሎ መውጣት ልማዱ ነው። እንደምንሽንሽ ሲለይለት አንድ ሀሙስ ብቻ ነው የቀረው፡፡ ሴትዮዋ በሯን ዘጋችና...
“እሺ ሂሣብ በቅድሚያ!” አለችው።
“ም. ን. ድ. ነው... ቅርሚያ ቅርሚያ! የምትይው? እኔን አታ..
አታምኝ.. ኝ.. ኝምምም?” አላት ልፍድድ ባለ የስካር ንግግር።
“ኡፋ! ሰውዬ ወሬ አታብዛ ! የምትከፍል ከሆነ በቅድሚያ ክፈልና እሺ። አለበለዚያ ውጣልኝ!ገበያዬን አትዝጋ!” አለችና አንባረቀችበት። ታከለ በጠጅና በአረቄ ብዛት የደነበሹ ዐይኖቹን ብልጥጥ አድርጎ ሲመለከታት ተንኮል የቋጠረ አመፀኛ ዝንጀሮ እንጂ ለጉዳይ የገባ እንግዳ አይመስልም ነበር።
በል ተናገር?! ያለበለዚያ ውጣ!” የዘጋችውን በር መልሳ እየከፈተች ጭኽችበት።
“ቆይ .. እ- ሺ ቆይ! ቆይ!” አለና ወደ ኪሱ ገባ፡፡ ያገኘው ሰላሳ አምስት ሣንቲም ብቻ ነበር።
እሺ ያው..ልሽ!
አትፈልጊምምም.?” እየተንተባተበ፡፡ ብልጭ አለባት።
ከኋላው አሽቀንጥራ ስትወረውረው ከፊት ለፊቱ ካለው ቆሻሻ ውሃ ከሚ ወርድበት ቦይ ውስጥ ሂዶ ተወተፈ፡፡ ከዚያም እየተውተረተረ ተነሳና ሣንቲምቹን መለቃቀም ጀመረ፡፡ እንደምንም ብሎ ሃያ አምስት ሣንቲም አገኘ።
ትርዒቱን እያዩ ወደሚሳሳቁት ግራና ቀኙን ወደተኮለኮሉ ሴተኛ አዳሪዎች እየተመለከተ“ይህቺን... ፈላጊ!.. ይህቺን... ይህቺን.” እያለ ሳንቲ ሞቹን ሽክ... ሽክ... ሽክ ሲያደርጋቸው የበለጠ በሳቅ ፈነዱ።
“አንተ ጠንባራ ሰካራም ድራሽህ ይጥፋ! የቀረችህ እሷ ናት። ሂድና ለሚስትህ ቀሚስ ግዛበት ፉዞ!” የስድብ መአት አወረዱበት። እሱም እየተንገዳገደ ቁልቁል ወረደ። ታደሰ ይህ ትርዒት የሚካሄድበትን አካባቢ
አልፎ ወደ ሰላማዊት ዘንድ ሊደርስ ትንሽ ቀርቶታል። አስፋልቱን ከመሻገሩ በፊት ግን ቆም ብሎ ምን ይዞላት እንደሚሄድ አሰላሰለ። እንደ
ሴተኛ አዳሪነቷ ሳይሆን እንደ ሚስቱ ያስብላት ስለጀመረ ወደ መኖሪያ ቤቱ የሚሄድ አባወራ እንጂ ወደ መሸታ ቤት የሚሄድ ጠጪ አይመስልም ነበር፡፡ ሰላማዊትም ከልቧ ስለምትወደው እሱ ከመጣ ሌላው ጠጪ
ሰው መስሎ አይታያትም፡፡ እንደሚጨነቅላት ስለምታውቅ አፀፋውን ፍቅር እየሰጠችው ነው፡፡ ታደስ ከእማማ ወደሬ ቤት ከፍ ብሎ ወደሚገኘው ሉካንዳ ቤት ገባና ከሽንጥ ሥጋ ላይ ሁለት ኪሎ ግራም አስቆርጦ አስጠቅልሎ ሄደ። ወይዘሮ ወደሬ የታደሰ ውለታ እየከበዳቸው ስለመጣ በሱ ምክንያት ሰላማዊትን ማክበርና መፍራት ጀምረዋል። ታደሰ ወደ ቤት ሊገባ ካለ በኋላ ምናምን እንዳቋረጠው ሰው ወደ ኋላው ሰግጠጥ አለና ቆመ፡፡ቀስ ብሎ በጓሮ በኩል ዞረ። የጓሮውን በር ያለሱ የሚደፍረው የለም።
“ሰላምን ጥሪያት” አላት ላፅጌ። ሰላማዊት ፅጌ ስትነግራት ሮጣ መጣች።
“ውይ ታዴ!”እቅፍ አድርጋ ሳመችውና በእጁ የያዘውን ተቀበለችው።
በጓሮ በኩል ዞሮ የገባው የያዘውን ሊሰጣት መሰላት። ድርጊቱ የበለጠ ገረማት። ማንም እሱ የሚያደርገውን አያደርግላትም። የፈለገውን ያክል ገንዘብ አስታቅፈዋት ቢሄዱ ታደሰ የሚያስበውን ያክል አስበውላት አያውቁም፡፡ በበዓላት ቀን ሹልክ ብሎ ይመጣና ገንዘብ ይሰጣታል። እንዳይደብርሽ እያለ ትያትርና ሙዚቃ ቤት ወስዶ ያዝናናታል፡፡
“አይ ታደሰ?አሁንስ አበዛው ምነው እሱ እንዲህ ተጨነቀ? እኔ ውለታ
ሲበዛብኝ ደስ አይለኝም፡፡ ይከብደኛል። ከሌላው የተለየ ለሱ ምን የተደረገለት ነገር አለ?” ወይዘሮ ወደሬ ስለታደሰ ተጨነቁ፡፡
“ታድዬ እቤት ትገባለህ ወይስ እዚሁ ጠላ ይዤልህ ልምጣ?” ስትል ጠየቀችው።
“እቤት አልገባም እዚችው ጓሮ ቁጭ ብለን ትንሽ አጫውቺኝና ጠላ ጠጥቼ እሄዳለሁ” አሁን አሁን የገባው ጠጪ ሁሉ እንደፈለገው እየጎተተ ሲያሻሻት፣ ሲያቅፋት፣ ሲስማት፣ ሲደባብሳት ማየት እያስጠላው መጥቷል።
“እሺ የኔ ቆንጆ ይዤልህ ልምጣ” አለችና ተመልሳ ገባች።
“ታዴ ወደ ቤት አይገባም እንዴ ሰላም?” አሉ ወይዘሮ ወደሬ።
“ውጭ ይሻለኛል ብሉኝ እኮ ነው”
#ያልታበሱ_እንባዎች
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
....«ይቅርታ የኔ ወንድም» ብሎ ጉዳዩን አጠር እድርጎ እስረዳው፡፡
ወጣቱ ርምጃውን ቀጠለ፡፡ በልሁ ግን እዚያው ባለበት አቀርቅሮ
ቆመ ወጣቱ አስቻለውን በዓይን እንደሚያውቀው ተረድቷል ፡፡ ነገር ግን የሰራተኞች በመኪና መግባትና መውጣት ጉዳይ መኖሪያቸው የግድ በዚያ
አካባቢ ላይሆን እንደሚችል አመሰከተው፡፡ በዚያው ልክ በልሁ ተስፋ ቆረጠ፡፡በነገው ዕቅዱ ላይ ብቻ አተኮረ፡፡ ሲያስብበት ውሉ ሲያስብበትም አደረ፡፡
ሰኞ ዕለት ጠዋት ከረፋፍዶ ከመኝታው ተነሳ፡፡ አለባበሱንም ለየት አደረገው፡፡ ዲላ ውስጥ ለሰርግ ወይም ለየት ባለ ድግስ ካልሆነ በቀር አዘውትሮ
የማይለብሰውን ደብዘዝ ያለ ሰማያዊ ሙሉ ልብስ ለብሶ የጥቁርና የነጭ ቡራቡሬ ክራባት አሰረ፡፡ ጥሩ ቁርስ በላ፡፡ ትናንት ቦታውን አጥንቶት ወደነበረው የክፍለ ሀገሩ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አመራ ከጠዋቱ ሶስት
ሰዓት አካባቢ ከቅጥር ግቢው ውስጥ ገባ፡፡ የአስተዳደር ምክትል ሰራ አስኪያጅ የሚል ጽሁፍ ወዳለበት ቢሮ ልቡ አደላ፣ በፀሐፊዋ በኩል ከመራና በር ላይ ቆሞ
«ጤና ይስጥልኝ» አላት፡፡
«አብሮ ይስጠን» አለችና ፀሃፊዋ ከመቀመጫዋ ብድግ አለች፡፡ አጠር ብላ ወፈር የምትል፡ የቀይ መልከ መልካም የሆነች ዕድሜዋ ወደ አርባ የሚጠጋት ሴት ወይዘሮ ናት፡፡ አጠር ያለ ፀጉሯን ጆንትራ አበጥራለች፡፡
«ሃላፊውን ማነጋገር እችላለሁ?»
«ስለምን ጉዳይ?»
በልሁ የልቡን መዘርዘር አልፈለገም ያን ጉዳይ ካነሳ ይህ አይመለከታቸውም ልትለው እንደምትችል አሰባና «የግል ጉዳይ ነው፡» አላት።
በኋላ፡ የምታዝንለት መስሎት «የመጣሁትም ከሲዳሞ ነው» ሲል ገለጸላት፡፡
ፀሐፊዋ ወንበር እያሳየችው ይቀመጡ» ብላ ወደ አለቃዋ ቢሮ
ገባች፡፡ ብዙ ፡ ሳትቆይ ወዲያው ተመለሰችና "ይግቡ አለችው "
የሃላፊው ቢሮ ለየት ያለ ነው፡፡ መጠነ ሰፊ ወለሉ በአረንጓዴ ቀለም ምንጣፍ የተሸፈነ መስኮቱ በነጭ ስስ እና ቀይ ወፍራም መጋረጃ የተከለለ ከስድስት የማያንሱ ወንበሮች ያሉት ትልቅ የእንግዳ ጠረጴዛ የተንጣለለበት
ግድግዳው ሹሯማ ቀለም የተቀባና ደስ የሚያሰኝ ገፅታ ያለው ነው፡፡
ሃላፊው አቶ ካህሳይ ገብሩም መልካ መልካም ነው፡፡ ድምቅ ብሎ ቀይ ጥቁር ሰማያዊ ሙሉ ልብስ በነጭ ሸሚዝና ጥቁሩ በዛ ያለበት ቡራቡሬ ካራባት ያደረገ፣ አፍንጫው ሰልከክ ዓይኖቹ ጎላ ያሉና ዕድሜው ከአርባ አምስት
ዓመት የማያንሰው ጎልማሳ ነው።
«ጤና ይስጥልኝ አለ በልሁ ወደ ውስጥ ገብቶ ሃላፊውን እጅ እየነሳ
«አብሮ ይስጠን» ብሎ ካህሳይ ከወንበሩ ብድግ ብሎ ተቀበለው፡፡
ስማቸውን በመለዋወጥ እጅ ለእጅ ተጨባበጡና በካህሳይ ግብዣ በልሁ ከእንግዳ መቀበያ ወንበር ላይ ተቀመጠ።
«ምን ልርዳዎት አቶ በልሁ?» ሲል ካህሳይ በልሁን ጠየቀው፡፡
«ችግር ገጥሞኝ ነው አቶ ካህሳይ»
«ምን ዓይነት ችግር?
በልሁ የመጣበትን አገርና ለምን ወደ አስመራ እንደመጣ በአጭሩ
ከአስረዳ በኋላ «ወንድሜ በሚሲዮኖች ክሊኒክ ውስጥ ይሰራ እንደነበር ተጠቁሜ ነበር ።
የሚሰኒዮቹን የስራ ቦታ አጠያይቄ ባገኘውም ነገር ግን ከአንድ ዓመት በፊት ከዛ ቦታ እንደለቀቁ ሰማሁ፡፡ ምናልባት ከሙያ አንጻርና
የምታውቸው ከሆነና አሁን የሚገኙበትን ቦታ ትጠቁሙኝ ከሆነ ብዩ ነበር፡፡» አለና በልሁ ካህሳይን ቀና ብሎ ተመለከተው፡፡
«የት አካባቢ የነበሩት ናቸው?» ሲል ካህሳይ በልሁን ጠየቀው::
«ቀበሌውን በትክክል አላወኩትም፡፡ ነገር ግን አባ ሻውል ከሚባለው ቦታ ወረድ ብሎ በምዕራባዊ የከተማዋ ዳርቻ የሚገኝ ክሊኒክ እንደ ነበር ማወቅ ችያለሁ።
ካህሳይ ሚሲዮኖቹን ያወቃቸው ይመስላል፡፡ አንገቱን ነቅነቅ ነቅነቅ ካደረገ በኋላ «ታዲያ እኮ እነሱ አስመራ ውስጥ አይደሉም ቦታ የቀየሩት ጠቅላላ ከሀገር ተባርረዋል አለውደ
«ተባርረዋል?» ሲል ጠየቀ በልሁ፡፡ ዓይኖቹ ፍጥጥ ብለው
በካህሳይ ላይ ተተከሉ፡፡
«ከዓመት በላይ ሆናቸው»
«በምን ምክንንያት ተባረሩ አቶ ካህሳይ? ምናልባት ወንድሜም አብሮ ተባሮ ይሆን?» ሲል በስጋት ስሜት ውስጥ ሆና ጠየቀው፡፡
ወንድምክ እንኳ ከብሮ ሊባረር የሚችልበት ሁኔታ የለም፡፡ እነሱ የተባረሩት በሀገር ውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ገቡ ተብሎ ነው፡፡»
«በፖለቲካ?»
«በመሆኑ ነዋ ለነገሩ እነርሱም አያርፉ ነገሮች ሁሉ እንደራሳቸው
ሀገር እየመሰላቸው የኛ መንግስት አካሄድ ሳይጥማቸው ሲቀር በአገኙት አጋጣሚ ሁሉ ወጋ ማድረግ ይወዳሉ፡፡ አለ ካህሳይ ፈገግ ብሎ የበላሁን ምላሽ እየጠበቀ።
በልሁ ፈጥኖ ለካህሳይ መልስ መስጠት አልፈለገም ወይም አልቻለም ዓይኑን ብቻ ትክል አድርጎ ካህሳይን ያየው ጀመር፡፡ እንዲያውም ቀስ በቀስ ዓይኖቹ በእንባ ይሞሉ ጀመር፡፡
«ምነው አቶ በልሁ?» ሲል ካህሳይ የበልሁ ስሜት መለዋወጥ አስገርሞት ጠየቀው፡፡
በልሁ አሁንም መልስ ከመስጠት ይልቅ ፊቱን በካህሳይ ላይ መልሶ
ወደ ጠረጴዛው በማጎንበስ በእንባ የሞላውን ዓይኑን በመሀረብ ይጠርግ ጀመር፡፡
«አቶ በልሁ» አለ ካህሳይ ይበልጥ እየደነገጠ፡፡
«ሆዴ አዘነ አቶ ካህሳይ!»
«ምነው? ወንድምህ አብሮ የተባረረ መሰሎህ?
«አይደለም አቶ ካህሳይ የዕድሉ ነገር እሳዝኖኝ ነው ፡፡" አለና ንግግሩን በማራዘም «አዩ አቶ ካህሳያ፣ ወንድሜ የጤና ባለሙያ እንጂ ፖለቲከኛ አልነበረም፡፡ ነገር ግን በሄደበት ቦታ ሁሉ የፖለቲካ መዘዝ አልለቀው አለው
አሁንም የዓይኖቹን እንባ እየጠራረገ፡፡
«ማለት?»
«ወንድሜ ገና ልጅ ሳለ የሚረዳው ወንድሙ በፖለቲከኞች ተገደለበት
በችግር ተማረ፡፡ በስንት ስቃይ ትምህርቱን ጨርሶ ስራ ከያዘም በኋላ አሁንም ፖለቲከኞች ሰላም ነስተው ሲያዋከቡት ኖሩ፡፡ የኋላ ኋላም በግፍና በተፀዕኖ ወደዚህ ክፍለ ሀገር በ እናት ሀገር ጥሪ ሽፋን እስገድደው ላኩት፡፡ በእነሱ ጦስ አካሉን አጣ፡፡ እዚሁ ከተማ ውስጥ እየተውትሮ ያርፍባት የነበረችው ሰራዩ መናፈሻ ደግሞ ከፖለቲካ ጋር በተያያዘ መዘጋቷን ሰማሁ፡፡ እነሆ አሁን ደግሞ
እርስዎም አሰሪዎቹ በፖለቲካ ጉዳይ ከሀገር መባረራቸውን እየነገሩኝ ነው፡፡ ይህ የፖለቲካ ጉዳይ እኔም እንዳላገኘው ምክንያት ሊሆን ነው፡፡ ታዲያ ይሄ
አያሳዝንም እቶ ካህሳይ?» ሲል በልሁ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ለካህሳይ ገለፀለት::
ካህሳይ ገብሩ በሰማው ታሪክ፣ በበልሁ አለቃቀስና የነገሮች አገላለፅ የእሱም ልብ ነካ፡፡ በልሁን ያህል ግርማ ሞገሱ ግጥም ያለ የወጣት ጠንበለል ከፊቱ ቁጭ ብሎ እንባውን እያፈሰሰ ብሶቱን ሲገልጽላት የእሱም አንጀት
ተላወሰ፡፡ ወንድ ልጅ ሲከፋው እንባው ምን ያህል ቅርብ እንደሆነ ከመቼውም ጊዜ በላይ ሲረዳ ሆዱ ተንቦጫቦጨ በሀዘን ሰሜት ራሱን ደጋግሞ ወዘወዘና በልሁን ትኩር ብሎም ተመለከተው። በልሁ አሁንም ንግግሩን ቀጠለ
«በቃ እኮ አቶ ካህሳይ ከእንግዲህ ወንድሜን ላላገኘው ነው።አለው እንባው በአይኖቹ ላይ ተቋጥሮ ሰማይ እየመሰለ።
ካህሳይ ገብሩ አሁንም ላፍታ ያህል በሀዘን ዓይን ከተመለከተው በኋላ ራሱን ለረጅም ግዜ ወዝውዞ በረጅሙ ተነፈሰና «ለመሆኑ የወንድምህ ስም ማን ይባላል?» ሲል ጠየቀው።
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
....«ይቅርታ የኔ ወንድም» ብሎ ጉዳዩን አጠር እድርጎ እስረዳው፡፡
ወጣቱ ርምጃውን ቀጠለ፡፡ በልሁ ግን እዚያው ባለበት አቀርቅሮ
ቆመ ወጣቱ አስቻለውን በዓይን እንደሚያውቀው ተረድቷል ፡፡ ነገር ግን የሰራተኞች በመኪና መግባትና መውጣት ጉዳይ መኖሪያቸው የግድ በዚያ
አካባቢ ላይሆን እንደሚችል አመሰከተው፡፡ በዚያው ልክ በልሁ ተስፋ ቆረጠ፡፡በነገው ዕቅዱ ላይ ብቻ አተኮረ፡፡ ሲያስብበት ውሉ ሲያስብበትም አደረ፡፡
ሰኞ ዕለት ጠዋት ከረፋፍዶ ከመኝታው ተነሳ፡፡ አለባበሱንም ለየት አደረገው፡፡ ዲላ ውስጥ ለሰርግ ወይም ለየት ባለ ድግስ ካልሆነ በቀር አዘውትሮ
የማይለብሰውን ደብዘዝ ያለ ሰማያዊ ሙሉ ልብስ ለብሶ የጥቁርና የነጭ ቡራቡሬ ክራባት አሰረ፡፡ ጥሩ ቁርስ በላ፡፡ ትናንት ቦታውን አጥንቶት ወደነበረው የክፍለ ሀገሩ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አመራ ከጠዋቱ ሶስት
ሰዓት አካባቢ ከቅጥር ግቢው ውስጥ ገባ፡፡ የአስተዳደር ምክትል ሰራ አስኪያጅ የሚል ጽሁፍ ወዳለበት ቢሮ ልቡ አደላ፣ በፀሐፊዋ በኩል ከመራና በር ላይ ቆሞ
«ጤና ይስጥልኝ» አላት፡፡
«አብሮ ይስጠን» አለችና ፀሃፊዋ ከመቀመጫዋ ብድግ አለች፡፡ አጠር ብላ ወፈር የምትል፡ የቀይ መልከ መልካም የሆነች ዕድሜዋ ወደ አርባ የሚጠጋት ሴት ወይዘሮ ናት፡፡ አጠር ያለ ፀጉሯን ጆንትራ አበጥራለች፡፡
«ሃላፊውን ማነጋገር እችላለሁ?»
«ስለምን ጉዳይ?»
በልሁ የልቡን መዘርዘር አልፈለገም ያን ጉዳይ ካነሳ ይህ አይመለከታቸውም ልትለው እንደምትችል አሰባና «የግል ጉዳይ ነው፡» አላት።
በኋላ፡ የምታዝንለት መስሎት «የመጣሁትም ከሲዳሞ ነው» ሲል ገለጸላት፡፡
ፀሐፊዋ ወንበር እያሳየችው ይቀመጡ» ብላ ወደ አለቃዋ ቢሮ
ገባች፡፡ ብዙ ፡ ሳትቆይ ወዲያው ተመለሰችና "ይግቡ አለችው "
የሃላፊው ቢሮ ለየት ያለ ነው፡፡ መጠነ ሰፊ ወለሉ በአረንጓዴ ቀለም ምንጣፍ የተሸፈነ መስኮቱ በነጭ ስስ እና ቀይ ወፍራም መጋረጃ የተከለለ ከስድስት የማያንሱ ወንበሮች ያሉት ትልቅ የእንግዳ ጠረጴዛ የተንጣለለበት
ግድግዳው ሹሯማ ቀለም የተቀባና ደስ የሚያሰኝ ገፅታ ያለው ነው፡፡
ሃላፊው አቶ ካህሳይ ገብሩም መልካ መልካም ነው፡፡ ድምቅ ብሎ ቀይ ጥቁር ሰማያዊ ሙሉ ልብስ በነጭ ሸሚዝና ጥቁሩ በዛ ያለበት ቡራቡሬ ካራባት ያደረገ፣ አፍንጫው ሰልከክ ዓይኖቹ ጎላ ያሉና ዕድሜው ከአርባ አምስት
ዓመት የማያንሰው ጎልማሳ ነው።
«ጤና ይስጥልኝ አለ በልሁ ወደ ውስጥ ገብቶ ሃላፊውን እጅ እየነሳ
«አብሮ ይስጠን» ብሎ ካህሳይ ከወንበሩ ብድግ ብሎ ተቀበለው፡፡
ስማቸውን በመለዋወጥ እጅ ለእጅ ተጨባበጡና በካህሳይ ግብዣ በልሁ ከእንግዳ መቀበያ ወንበር ላይ ተቀመጠ።
«ምን ልርዳዎት አቶ በልሁ?» ሲል ካህሳይ በልሁን ጠየቀው፡፡
«ችግር ገጥሞኝ ነው አቶ ካህሳይ»
«ምን ዓይነት ችግር?
በልሁ የመጣበትን አገርና ለምን ወደ አስመራ እንደመጣ በአጭሩ
ከአስረዳ በኋላ «ወንድሜ በሚሲዮኖች ክሊኒክ ውስጥ ይሰራ እንደነበር ተጠቁሜ ነበር ።
የሚሰኒዮቹን የስራ ቦታ አጠያይቄ ባገኘውም ነገር ግን ከአንድ ዓመት በፊት ከዛ ቦታ እንደለቀቁ ሰማሁ፡፡ ምናልባት ከሙያ አንጻርና
የምታውቸው ከሆነና አሁን የሚገኙበትን ቦታ ትጠቁሙኝ ከሆነ ብዩ ነበር፡፡» አለና በልሁ ካህሳይን ቀና ብሎ ተመለከተው፡፡
«የት አካባቢ የነበሩት ናቸው?» ሲል ካህሳይ በልሁን ጠየቀው::
«ቀበሌውን በትክክል አላወኩትም፡፡ ነገር ግን አባ ሻውል ከሚባለው ቦታ ወረድ ብሎ በምዕራባዊ የከተማዋ ዳርቻ የሚገኝ ክሊኒክ እንደ ነበር ማወቅ ችያለሁ።
ካህሳይ ሚሲዮኖቹን ያወቃቸው ይመስላል፡፡ አንገቱን ነቅነቅ ነቅነቅ ካደረገ በኋላ «ታዲያ እኮ እነሱ አስመራ ውስጥ አይደሉም ቦታ የቀየሩት ጠቅላላ ከሀገር ተባርረዋል አለውደ
«ተባርረዋል?» ሲል ጠየቀ በልሁ፡፡ ዓይኖቹ ፍጥጥ ብለው
በካህሳይ ላይ ተተከሉ፡፡
«ከዓመት በላይ ሆናቸው»
«በምን ምክንንያት ተባረሩ አቶ ካህሳይ? ምናልባት ወንድሜም አብሮ ተባሮ ይሆን?» ሲል በስጋት ስሜት ውስጥ ሆና ጠየቀው፡፡
ወንድምክ እንኳ ከብሮ ሊባረር የሚችልበት ሁኔታ የለም፡፡ እነሱ የተባረሩት በሀገር ውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ገቡ ተብሎ ነው፡፡»
«በፖለቲካ?»
«በመሆኑ ነዋ ለነገሩ እነርሱም አያርፉ ነገሮች ሁሉ እንደራሳቸው
ሀገር እየመሰላቸው የኛ መንግስት አካሄድ ሳይጥማቸው ሲቀር በአገኙት አጋጣሚ ሁሉ ወጋ ማድረግ ይወዳሉ፡፡ አለ ካህሳይ ፈገግ ብሎ የበላሁን ምላሽ እየጠበቀ።
በልሁ ፈጥኖ ለካህሳይ መልስ መስጠት አልፈለገም ወይም አልቻለም ዓይኑን ብቻ ትክል አድርጎ ካህሳይን ያየው ጀመር፡፡ እንዲያውም ቀስ በቀስ ዓይኖቹ በእንባ ይሞሉ ጀመር፡፡
«ምነው አቶ በልሁ?» ሲል ካህሳይ የበልሁ ስሜት መለዋወጥ አስገርሞት ጠየቀው፡፡
በልሁ አሁንም መልስ ከመስጠት ይልቅ ፊቱን በካህሳይ ላይ መልሶ
ወደ ጠረጴዛው በማጎንበስ በእንባ የሞላውን ዓይኑን በመሀረብ ይጠርግ ጀመር፡፡
«አቶ በልሁ» አለ ካህሳይ ይበልጥ እየደነገጠ፡፡
«ሆዴ አዘነ አቶ ካህሳይ!»
«ምነው? ወንድምህ አብሮ የተባረረ መሰሎህ?
«አይደለም አቶ ካህሳይ የዕድሉ ነገር እሳዝኖኝ ነው ፡፡" አለና ንግግሩን በማራዘም «አዩ አቶ ካህሳያ፣ ወንድሜ የጤና ባለሙያ እንጂ ፖለቲከኛ አልነበረም፡፡ ነገር ግን በሄደበት ቦታ ሁሉ የፖለቲካ መዘዝ አልለቀው አለው
አሁንም የዓይኖቹን እንባ እየጠራረገ፡፡
«ማለት?»
«ወንድሜ ገና ልጅ ሳለ የሚረዳው ወንድሙ በፖለቲከኞች ተገደለበት
በችግር ተማረ፡፡ በስንት ስቃይ ትምህርቱን ጨርሶ ስራ ከያዘም በኋላ አሁንም ፖለቲከኞች ሰላም ነስተው ሲያዋከቡት ኖሩ፡፡ የኋላ ኋላም በግፍና በተፀዕኖ ወደዚህ ክፍለ ሀገር በ እናት ሀገር ጥሪ ሽፋን እስገድደው ላኩት፡፡ በእነሱ ጦስ አካሉን አጣ፡፡ እዚሁ ከተማ ውስጥ እየተውትሮ ያርፍባት የነበረችው ሰራዩ መናፈሻ ደግሞ ከፖለቲካ ጋር በተያያዘ መዘጋቷን ሰማሁ፡፡ እነሆ አሁን ደግሞ
እርስዎም አሰሪዎቹ በፖለቲካ ጉዳይ ከሀገር መባረራቸውን እየነገሩኝ ነው፡፡ ይህ የፖለቲካ ጉዳይ እኔም እንዳላገኘው ምክንያት ሊሆን ነው፡፡ ታዲያ ይሄ
አያሳዝንም እቶ ካህሳይ?» ሲል በልሁ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ለካህሳይ ገለፀለት::
ካህሳይ ገብሩ በሰማው ታሪክ፣ በበልሁ አለቃቀስና የነገሮች አገላለፅ የእሱም ልብ ነካ፡፡ በልሁን ያህል ግርማ ሞገሱ ግጥም ያለ የወጣት ጠንበለል ከፊቱ ቁጭ ብሎ እንባውን እያፈሰሰ ብሶቱን ሲገልጽላት የእሱም አንጀት
ተላወሰ፡፡ ወንድ ልጅ ሲከፋው እንባው ምን ያህል ቅርብ እንደሆነ ከመቼውም ጊዜ በላይ ሲረዳ ሆዱ ተንቦጫቦጨ በሀዘን ሰሜት ራሱን ደጋግሞ ወዘወዘና በልሁን ትኩር ብሎም ተመለከተው። በልሁ አሁንም ንግግሩን ቀጠለ
«በቃ እኮ አቶ ካህሳይ ከእንግዲህ ወንድሜን ላላገኘው ነው።አለው እንባው በአይኖቹ ላይ ተቋጥሮ ሰማይ እየመሰለ።
ካህሳይ ገብሩ አሁንም ላፍታ ያህል በሀዘን ዓይን ከተመለከተው በኋላ ራሱን ለረጅም ግዜ ወዝውዞ በረጅሙ ተነፈሰና «ለመሆኑ የወንድምህ ስም ማን ይባላል?» ሲል ጠየቀው።
👍9
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....የሞቱት ሰዎች አስከሬን
ከመውጫው ላይ ተቆልሎ ስለነበር በችግር ነው ያለፉት:: የሰው ሬሣ እንደ ድንጋይ ተቆልሎ ማየቱም በጣም አሰቃቂ ነበር፡፡
ቁና ዣቬር በረጋ መንፈስ «ይህችን ልጅ አውቃት ነበር» ሲል ድምፁን ዝቅ አድርጎ የኢፖኒን የተገላለጠ ጡትና ገላ እያየ ይናገራል፡፡ ከዚያም ወደ
ዣን ቫልዣ ዞር አለ፡፡"
ዣን ቫልዣ ቃል ሳይናገር ዝም ብሎ በማፍጠጥ አየው:: ደግሞ
መናገርም አያስፈልግም ነበር፡፡ አስተያየቱ ብቻ ዣቬር እኔው ነኝ!» ለማለቱ ግልጽ ነበር፡፡
ዣቬር ንግግሩን ቀጠለ፡፡
«አሁን ልትበቀለኝ ትችላለህ::»
ዣን ቫልዣ ሽጉጡን ከኪሱ ከከተተ በኋላ ሰንጢውን አወጣ፡፡ ሰንጢውን ዘረጋው፡፡
«ወይ ጉድ!» አለ ዣቬር፡፡ «ልክ ነህ፣ እሱ ይሻልሃል»
«ፊትህን አዙር» ሲል ዣቬርን አዘዘው:: ዣቬርም ፊቱን ወደ
ግድግዳው አዞረ:: ከዚያም ዣን ቫልዣ ጠላቱ የፍጥኝ የታሠረበትን ገመድ ይቆርጥ ጀመር፡፡ እጁንና እግሩን አላቀቀለት:: እግሮቹ የታሠሩባቸውን ገመድ ቆርጦ እንደጨረሰ እዚያው ከመሬት ሆኖ ዣቬርን ቀና ብሎ አያየ
«መሄድ ትችላለህ» አለው::
ዣቬር ግራ ተጋብቶ አፉን እንደከፈተ ቀረ:: ዣን ቫልዣ ንግግሩን ቀጠለ፡፡
«እኔ ግን ከዚሁ ማለት ከምሽጉ ውስጥ እቆያለሁ፡፡ ምናልባት በአጋጣሚ በሕይወት ከወጣሁ አድራሻዬን ልስጥህ» ብሎ የቤቱን አድራሻ ሰጠው።ዣቬር በመገረም እያየውና ከንፈሩን በግድ አላቅቆ «ራስህን ጠብቅ» ሲል መከረው::
«ለማንኛውም ሂድ ብያለሁ፤ ቶሎ ብለህ ከዚህ ጥፋ» ሲል ዣን
ቫልዣ በተራው መከረው::
ዣቬር አድራሻውን ለማረጋገጥ «ሆም አርሚ ጐዳና የቤት ቁጥር
ሰባት ነው ያልከኝ?» ሲል ጠየቀው::
«በደምብ ይዘኸዋል» ሲል ዣን ቫልዣ መለሰለት::
ዣቬር ልብሱን አስተካክሎና በአንድ እጁ ጉንጩን ይዞ መንገዱን ቀጠለ፡፡ ዣን ቫልዣ ከዚያው እንደቆመ በዓይኑ ተከተለው:: ዣቬር ጥቂት
ከተጓዘ በኋላ ወደ ኋላ መለስ ብሎ «አናደድከኝ፣ ለምን አልገደልከኝም ነበር»ሲል ተናገረው:: «ሂድ ብያለሁ፤ ሂድ» ሲል ዣን ቫልዣ መለሰለት።
ዣቬር በዝግታ እየተራመደ ጉዞውን ቀጠለ፡፡ ኩርባ ላይ ሲደርስ ወደ ግራ ታጠፈ::ዣቬር ከዓይኑ ሲሰወር ዣን ቫልዣ ሁለት ጊዜ ወደ ሰማይ ተኩሰ፡፡ ከዚያም ወደ ምሽጉ ተመልሶ «እርምጃው ተወስዷል» ሲል ሪፖርቱን አቀረበ።
«አጥቃ» የሚለው የከበሮ ምልክት እንደገና በኃይል ተመታ፡፡ ማጥቃቱ እርምጃ ከማዕበል የከፋ ነበር፡፡ እግረኛው ጦር ጠመንጃን ወድሮ በቀጥታ ወደ ምሽጉ ገሠገሠ፡፡ መለከቱና ከበሮው ተንጣጣ፡፡ የእግረኛው እርምጃ መሬቱን አነቃነቀው::
ከምሽጉ ውስጥ በሕይወት የቀሩት አድመኞች ጠመንጃቸውን
አንጣጡት:: ኢንጆልራስ በአንድ ፊት ማሪየስ በሌላ በኩል አጋሮቻቸውን ለማነቃቃት ይጮሃሉ፡፡ ጦሩ እየቀረባቸው መጣ፡፡ ከአጠገባቸው የደረሰው
እየተንገዳገደ ከእግራቸው ስር ይወድቃል:: ኃይለኛ የመከላከያ ምሽግን ተገን አድርጎ በቀዳዳ የሚዋጋን ጦር ቶሎ ለመጣል ያዳግታል። ሆኖም ! የነበረው
ምንም እንኳን የምሽጉ አቀማመጥ ቢረዳቸውም በመጨረሻ ለመቋቋም አልቻሉም።
እህል ከቀመሱና የእንቅልፍ ዓይን ካዩ ሃያ አራት ሰዓታት ኣልፈዋል።
ቁጥራቸው አንድ ስልሣ ይሆናል:: የነበራቸው ጥይት እየተሟጠጠ ነው።ከመካከላቸው ያልቆሰለ ቢኖር በጣም ጥቂት ነው፡፡ የመንግሥት ጦር ከምሽጉ ለመግባት አሥር ጊዜ ያህል ሞክሮአል፡፡ በዚህ ጊዜ ሁሉ ደረት
ለደረት በጠብመንጃና በጎራዴ በመከላከል በሙሉ ልብ ተዋጉ፡፡ በዚህ ውጊያ እነኩርፌይራክ፣ ቦሌይና ሌሎችም ሲሞቱ ኮምብፌሬ በሳንጃ ደረቱ ላይ
ከሦስት ቦታ ተወግቷል፡፡ እሱም ቢሆን ከተወጋ በኋላ ብዙ አልቆየም፧ ሕይወቱ አለፈች፡፡ ማሪየስ እስከመጨረሻው ቢዋጋም ቆስሉ ስለነበር እየደከመ
ሄደ፡፡ ኢንጆልራስ ብቻ ነበር ያልተነካው::
በየአቅጣጫው ጥግ ይዞ ይዋጋ የነበረው ሰው ቀስ በቀስ አንዱ
ከሌላው ቀጥሎ ስለተመታና ስለወደቀ ወደ ምሽጉ የሚያስገባ ቀዳዳ እየሰፋ ሄደ፡፡ የመንግሥት ጦርም ከምሽጉ መሃል ለመግባት ቻለ፡፡ ሰው ሲያልቅ የምሽጉ የውጭ ግምብም በመሣሪያ ኃይል ተናደ፡፡ በዚህ ጊዜ ነበር በሕይወት የቆዩት እጅግ ጥቂት አድመኞች የመጨረሻውን መንፈራገጥ ያሳዩት።በዚህች የመጨረሻ ደቂቃ ነው የሰው ልጅ የመኖር ፍላጎቱ የሚያይልበትና
የእንስሳ ባሕርዩ የሚጎላው:: ያቺን ሰዓት ለማለፍ የማያስበው ዘዴና
የማያልመው መላ አይኖርም፡፡ ወደ ፎቅ የሚሮጠውን የተዘጋ በር ለመክፈት የሚታገለው፤ ተከፍቶ የነበረውን በር ላመቀርቀር የሚሽቀዳደመው ሲታይ
በጣም አሳዛኝ ትርዒት ነበር::
በዚያች ቀውጢ ሰዓት በድንጋጤ መንፈሱ ተረብሾ ወደ ስርቆቱ በር
የሚወስደውን መንገድ በጉልህ ያስታወሰ ኢንጆልራስ ብቻ ነበር፡፡ በአንድ እጁ ጠመንጃውን በሌላው ጎራዴ ይዞ ከፊት ለፊት የሚመጣውን ጦር እየተከላከለ በሕይወት የቀሩትን ሰዎች ወደ ውስጥ እንዳስገባ ወታደሮች
ደርሰው የብረቱን በር ለመግፋት ይታገላሉ:: አድመኞቹ ከውስጥ ወታደሮች ከውጭ ሆነው በሩን ሲገፉ አንድ ወታደር ጣቱ በበሩ በመቀርጠፉ ይጮሃል፡፡
ማሪየስ በመመታቱ በበሩ አላለፈም:: እንዲያውም ከነአካቴው ሕሊናውን ስቶ ይወድቃል፡፡ ልክ ሲወድቅ አንድ ሰው መጥቶ ሲይዘው
ይታወቀው እንጂ ከዚያ በኋላ የሆነውን አያውቅም:: ከዚያ ጥቂት ቀደም ብሎ እንደ ተመታ ኮዜት ትዝ ብላው «ስለቆሰልኩ እማረካለሁ፤ ከዚያም
በጥይት ተደብድቤ እሞታለሁ» ሲል ያስባል፡፡ ልክ ኮዜት አጠገቡ እንዳለች ቆጥሮ ነበር ታሪኩን የሚነግራት::
እነ ኢንጂልራስ ከውስጥ ወታደሮች ከውጭ ሆነው ከአንደኛ ፎቅ ላይ የነበረውን ክፍል በር በጥይት አጋዩት:: በዚያች ሰዓት የነበረው ጩኸት ! የነበረው ዋይታና የስቃይ እንጉርጉር በቃላት ለመግለጽ እጅግ በጣም
ስለሚያዳግት እንዲያው ዝም ይሻላል፡፡
በመጨረሻ በሩ ተበርግዶ ሲከፈት በሕይወት የቆየው ኢንጂልራስ
ብቻ ነበር፡፡ ኢንጆልራስ ጥይት አልቀበት ሰውነቱ በደም ተበክሎና ልብሱ ተቦጫጭቆ ጥግ ይዞ ቆሞአል፡፡ ጠመንጃውን ግን በእጁ እንደያዘ ነው።አንድ ሰው ገና ሲያየው በኃይል እየጮኸ ይናገራል::
«መሪው እሱ ነው፡፡ ያንን መልከ መልካም ወጣት የገደለ እርሱ
ነው:: እዚህቹ ከቆመበት በሉት::»
«ግደሉኝ» አለ ኢንጆልራስ ረጋ ብሎ ደረቱን እየገለበጠ፡፡
አሥራ ሁለት ወታደሮች ኢንጆልራስ ላይ ለመተኰስ ጥግ ይዘው
ጠመንጃቸውን አቀኑ።
የሃምሣ አለቃ «ለመተኩስ ተዘጋጁ» ሲል ትእዛዝ ሰጠ::
የሃምሳ አለቃው ጩኸት ግራናትዬን ከእንቅልፉ ቀሰቀሰው:: ግራናትዬ ከሰካራሞቹ አንዱ ነው:: ከመጠጥ ቤቱ ተኝቶ እንቅልፍ የወሰደው ከአንድ ቀን በፊት ነበር::
እንደሚታወቀው ሰካራም አንዴ እንቅልፍ ከወሰደው እንቅልፉን
ካልጨረሰ በቀር ምንም ዓይነት ድምፅ አይቀሰቅሰውም፡፡ ከእንቅልፉ እንደነቃ በእንቅልፍ ልቡ «ሪፑብሊኩ ለዘላለም ይኑር፤ እኔም የዚያው አባል ነኝ
በማለት ጮክ ብሉ ሲናገር ወታደሮቹ ደንግጠው ወደ ግራናትዬ ፊታቸውን
አዞሩ፡፡
ሰካራሙ ከተኛበት ብድግ ይላል:: ሁለም አፍጥጦ ያየዋል፡፡
የሚያናግረው ግን የለም::
«ሪፑብሊኩ ለዘላለም ይኑር» ይላል በድጋሚ፡፡ በቀጥታ ወደ ኢንጆልራስ ሄዶ ከአጠገቡ ቆመ::
«በአንድ ጥይት ሁለት ሰው» ይላል:: ከዚያም ወደ ኢንጆልራስ ዞር ብሎ ረጋ ባለ መንፈስ «አብሬህ ብሞት ትፈቅድልኛህ?» ሲል ጠየቀው።
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....የሞቱት ሰዎች አስከሬን
ከመውጫው ላይ ተቆልሎ ስለነበር በችግር ነው ያለፉት:: የሰው ሬሣ እንደ ድንጋይ ተቆልሎ ማየቱም በጣም አሰቃቂ ነበር፡፡
ቁና ዣቬር በረጋ መንፈስ «ይህችን ልጅ አውቃት ነበር» ሲል ድምፁን ዝቅ አድርጎ የኢፖኒን የተገላለጠ ጡትና ገላ እያየ ይናገራል፡፡ ከዚያም ወደ
ዣን ቫልዣ ዞር አለ፡፡"
ዣን ቫልዣ ቃል ሳይናገር ዝም ብሎ በማፍጠጥ አየው:: ደግሞ
መናገርም አያስፈልግም ነበር፡፡ አስተያየቱ ብቻ ዣቬር እኔው ነኝ!» ለማለቱ ግልጽ ነበር፡፡
ዣቬር ንግግሩን ቀጠለ፡፡
«አሁን ልትበቀለኝ ትችላለህ::»
ዣን ቫልዣ ሽጉጡን ከኪሱ ከከተተ በኋላ ሰንጢውን አወጣ፡፡ ሰንጢውን ዘረጋው፡፡
«ወይ ጉድ!» አለ ዣቬር፡፡ «ልክ ነህ፣ እሱ ይሻልሃል»
«ፊትህን አዙር» ሲል ዣቬርን አዘዘው:: ዣቬርም ፊቱን ወደ
ግድግዳው አዞረ:: ከዚያም ዣን ቫልዣ ጠላቱ የፍጥኝ የታሠረበትን ገመድ ይቆርጥ ጀመር፡፡ እጁንና እግሩን አላቀቀለት:: እግሮቹ የታሠሩባቸውን ገመድ ቆርጦ እንደጨረሰ እዚያው ከመሬት ሆኖ ዣቬርን ቀና ብሎ አያየ
«መሄድ ትችላለህ» አለው::
ዣቬር ግራ ተጋብቶ አፉን እንደከፈተ ቀረ:: ዣን ቫልዣ ንግግሩን ቀጠለ፡፡
«እኔ ግን ከዚሁ ማለት ከምሽጉ ውስጥ እቆያለሁ፡፡ ምናልባት በአጋጣሚ በሕይወት ከወጣሁ አድራሻዬን ልስጥህ» ብሎ የቤቱን አድራሻ ሰጠው።ዣቬር በመገረም እያየውና ከንፈሩን በግድ አላቅቆ «ራስህን ጠብቅ» ሲል መከረው::
«ለማንኛውም ሂድ ብያለሁ፤ ቶሎ ብለህ ከዚህ ጥፋ» ሲል ዣን
ቫልዣ በተራው መከረው::
ዣቬር አድራሻውን ለማረጋገጥ «ሆም አርሚ ጐዳና የቤት ቁጥር
ሰባት ነው ያልከኝ?» ሲል ጠየቀው::
«በደምብ ይዘኸዋል» ሲል ዣን ቫልዣ መለሰለት::
ዣቬር ልብሱን አስተካክሎና በአንድ እጁ ጉንጩን ይዞ መንገዱን ቀጠለ፡፡ ዣን ቫልዣ ከዚያው እንደቆመ በዓይኑ ተከተለው:: ዣቬር ጥቂት
ከተጓዘ በኋላ ወደ ኋላ መለስ ብሎ «አናደድከኝ፣ ለምን አልገደልከኝም ነበር»ሲል ተናገረው:: «ሂድ ብያለሁ፤ ሂድ» ሲል ዣን ቫልዣ መለሰለት።
ዣቬር በዝግታ እየተራመደ ጉዞውን ቀጠለ፡፡ ኩርባ ላይ ሲደርስ ወደ ግራ ታጠፈ::ዣቬር ከዓይኑ ሲሰወር ዣን ቫልዣ ሁለት ጊዜ ወደ ሰማይ ተኩሰ፡፡ ከዚያም ወደ ምሽጉ ተመልሶ «እርምጃው ተወስዷል» ሲል ሪፖርቱን አቀረበ።
«አጥቃ» የሚለው የከበሮ ምልክት እንደገና በኃይል ተመታ፡፡ ማጥቃቱ እርምጃ ከማዕበል የከፋ ነበር፡፡ እግረኛው ጦር ጠመንጃን ወድሮ በቀጥታ ወደ ምሽጉ ገሠገሠ፡፡ መለከቱና ከበሮው ተንጣጣ፡፡ የእግረኛው እርምጃ መሬቱን አነቃነቀው::
ከምሽጉ ውስጥ በሕይወት የቀሩት አድመኞች ጠመንጃቸውን
አንጣጡት:: ኢንጆልራስ በአንድ ፊት ማሪየስ በሌላ በኩል አጋሮቻቸውን ለማነቃቃት ይጮሃሉ፡፡ ጦሩ እየቀረባቸው መጣ፡፡ ከአጠገባቸው የደረሰው
እየተንገዳገደ ከእግራቸው ስር ይወድቃል:: ኃይለኛ የመከላከያ ምሽግን ተገን አድርጎ በቀዳዳ የሚዋጋን ጦር ቶሎ ለመጣል ያዳግታል። ሆኖም ! የነበረው
ምንም እንኳን የምሽጉ አቀማመጥ ቢረዳቸውም በመጨረሻ ለመቋቋም አልቻሉም።
እህል ከቀመሱና የእንቅልፍ ዓይን ካዩ ሃያ አራት ሰዓታት ኣልፈዋል።
ቁጥራቸው አንድ ስልሣ ይሆናል:: የነበራቸው ጥይት እየተሟጠጠ ነው።ከመካከላቸው ያልቆሰለ ቢኖር በጣም ጥቂት ነው፡፡ የመንግሥት ጦር ከምሽጉ ለመግባት አሥር ጊዜ ያህል ሞክሮአል፡፡ በዚህ ጊዜ ሁሉ ደረት
ለደረት በጠብመንጃና በጎራዴ በመከላከል በሙሉ ልብ ተዋጉ፡፡ በዚህ ውጊያ እነኩርፌይራክ፣ ቦሌይና ሌሎችም ሲሞቱ ኮምብፌሬ በሳንጃ ደረቱ ላይ
ከሦስት ቦታ ተወግቷል፡፡ እሱም ቢሆን ከተወጋ በኋላ ብዙ አልቆየም፧ ሕይወቱ አለፈች፡፡ ማሪየስ እስከመጨረሻው ቢዋጋም ቆስሉ ስለነበር እየደከመ
ሄደ፡፡ ኢንጆልራስ ብቻ ነበር ያልተነካው::
በየአቅጣጫው ጥግ ይዞ ይዋጋ የነበረው ሰው ቀስ በቀስ አንዱ
ከሌላው ቀጥሎ ስለተመታና ስለወደቀ ወደ ምሽጉ የሚያስገባ ቀዳዳ እየሰፋ ሄደ፡፡ የመንግሥት ጦርም ከምሽጉ መሃል ለመግባት ቻለ፡፡ ሰው ሲያልቅ የምሽጉ የውጭ ግምብም በመሣሪያ ኃይል ተናደ፡፡ በዚህ ጊዜ ነበር በሕይወት የቆዩት እጅግ ጥቂት አድመኞች የመጨረሻውን መንፈራገጥ ያሳዩት።በዚህች የመጨረሻ ደቂቃ ነው የሰው ልጅ የመኖር ፍላጎቱ የሚያይልበትና
የእንስሳ ባሕርዩ የሚጎላው:: ያቺን ሰዓት ለማለፍ የማያስበው ዘዴና
የማያልመው መላ አይኖርም፡፡ ወደ ፎቅ የሚሮጠውን የተዘጋ በር ለመክፈት የሚታገለው፤ ተከፍቶ የነበረውን በር ላመቀርቀር የሚሽቀዳደመው ሲታይ
በጣም አሳዛኝ ትርዒት ነበር::
በዚያች ቀውጢ ሰዓት በድንጋጤ መንፈሱ ተረብሾ ወደ ስርቆቱ በር
የሚወስደውን መንገድ በጉልህ ያስታወሰ ኢንጆልራስ ብቻ ነበር፡፡ በአንድ እጁ ጠመንጃውን በሌላው ጎራዴ ይዞ ከፊት ለፊት የሚመጣውን ጦር እየተከላከለ በሕይወት የቀሩትን ሰዎች ወደ ውስጥ እንዳስገባ ወታደሮች
ደርሰው የብረቱን በር ለመግፋት ይታገላሉ:: አድመኞቹ ከውስጥ ወታደሮች ከውጭ ሆነው በሩን ሲገፉ አንድ ወታደር ጣቱ በበሩ በመቀርጠፉ ይጮሃል፡፡
ማሪየስ በመመታቱ በበሩ አላለፈም:: እንዲያውም ከነአካቴው ሕሊናውን ስቶ ይወድቃል፡፡ ልክ ሲወድቅ አንድ ሰው መጥቶ ሲይዘው
ይታወቀው እንጂ ከዚያ በኋላ የሆነውን አያውቅም:: ከዚያ ጥቂት ቀደም ብሎ እንደ ተመታ ኮዜት ትዝ ብላው «ስለቆሰልኩ እማረካለሁ፤ ከዚያም
በጥይት ተደብድቤ እሞታለሁ» ሲል ያስባል፡፡ ልክ ኮዜት አጠገቡ እንዳለች ቆጥሮ ነበር ታሪኩን የሚነግራት::
እነ ኢንጂልራስ ከውስጥ ወታደሮች ከውጭ ሆነው ከአንደኛ ፎቅ ላይ የነበረውን ክፍል በር በጥይት አጋዩት:: በዚያች ሰዓት የነበረው ጩኸት ! የነበረው ዋይታና የስቃይ እንጉርጉር በቃላት ለመግለጽ እጅግ በጣም
ስለሚያዳግት እንዲያው ዝም ይሻላል፡፡
በመጨረሻ በሩ ተበርግዶ ሲከፈት በሕይወት የቆየው ኢንጂልራስ
ብቻ ነበር፡፡ ኢንጆልራስ ጥይት አልቀበት ሰውነቱ በደም ተበክሎና ልብሱ ተቦጫጭቆ ጥግ ይዞ ቆሞአል፡፡ ጠመንጃውን ግን በእጁ እንደያዘ ነው።አንድ ሰው ገና ሲያየው በኃይል እየጮኸ ይናገራል::
«መሪው እሱ ነው፡፡ ያንን መልከ መልካም ወጣት የገደለ እርሱ
ነው:: እዚህቹ ከቆመበት በሉት::»
«ግደሉኝ» አለ ኢንጆልራስ ረጋ ብሎ ደረቱን እየገለበጠ፡፡
አሥራ ሁለት ወታደሮች ኢንጆልራስ ላይ ለመተኰስ ጥግ ይዘው
ጠመንጃቸውን አቀኑ።
የሃምሣ አለቃ «ለመተኩስ ተዘጋጁ» ሲል ትእዛዝ ሰጠ::
የሃምሳ አለቃው ጩኸት ግራናትዬን ከእንቅልፉ ቀሰቀሰው:: ግራናትዬ ከሰካራሞቹ አንዱ ነው:: ከመጠጥ ቤቱ ተኝቶ እንቅልፍ የወሰደው ከአንድ ቀን በፊት ነበር::
እንደሚታወቀው ሰካራም አንዴ እንቅልፍ ከወሰደው እንቅልፉን
ካልጨረሰ በቀር ምንም ዓይነት ድምፅ አይቀሰቅሰውም፡፡ ከእንቅልፉ እንደነቃ በእንቅልፍ ልቡ «ሪፑብሊኩ ለዘላለም ይኑር፤ እኔም የዚያው አባል ነኝ
በማለት ጮክ ብሉ ሲናገር ወታደሮቹ ደንግጠው ወደ ግራናትዬ ፊታቸውን
አዞሩ፡፡
ሰካራሙ ከተኛበት ብድግ ይላል:: ሁለም አፍጥጦ ያየዋል፡፡
የሚያናግረው ግን የለም::
«ሪፑብሊኩ ለዘላለም ይኑር» ይላል በድጋሚ፡፡ በቀጥታ ወደ ኢንጆልራስ ሄዶ ከአጠገቡ ቆመ::
«በአንድ ጥይት ሁለት ሰው» ይላል:: ከዚያም ወደ ኢንጆልራስ ዞር ብሎ ረጋ ባለ መንፈስ «አብሬህ ብሞት ትፈቅድልኛህ?» ሲል ጠየቀው።
👍18❤2
#ሳቤላ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
ከበረዶው ማዕበል በኋላ ብራ የሆነ ጧት ተተካ ሰማዩ ፍንትው ብሎ ጠርቶ
ፀሐይ ደምቃ ስታበራ ሲጥል ያደረው በረዶ ግን ከመሬት እንደ ተቆለለ ነበር
ሚስዝ ሔር በወንበር ተቀምጣ የቀኑን ድምቀት እያየች ትደሰታለች የማስተር ካርላይልም
አጠገቧ ቆሟል ከባርባራ ጋር የመለያየቷን ነገር ስታስበው ኀዘኑ ለሷ አቻዋ የሆነ ባል በማግኘቷ ደስታው ሁለቱ ስሜቶች ተጋጭተው ሲያስጨንቋት ዐይኖቿ የኀዘንና የደስታ እንባ አቀረሩ ።
“አርኪባልድ . . . ይህች ልጅ ከኛ ጋር ሁና ደስተኛ ነበረች አንተ ዘንድም የለመደችውን ደስታ ታገኘው ይመስልሃል ?
“ እኔ በምችለው ሁሉ።"
“ ታዝንላታለህ ? ትንከባከባታለህ ?
ሚስዝ ሔር ... ደኅና አድርገው
ስለሚያውቁኝ የሚጠራጠሩኝ አይመስለኝም ነበር " አሁንም ባለኝ አቅም ሁሉ በሙሉ ልቤ እሷን ለማስደሰት እሞክራለሁ " "
“ አንተን አልጠረጥርህም ! በደንብ አምንሃለሁ ዓለም ሁሉ ከባርባራ እግር ቢወድቅ አንተን እንድትመርጥልኝ እጸልይ ነበር ግን አርኪባልድ የኮርንሊያ ነገርስ እንዴት ይሆናል ? እኔ እንኳን ባንተ ጉዳይ ወይም አንተና ባርባራ ተስማምታችሁ በምትፈጽሙት ለመግባት ሳይሆን ባልና ሚስት ብቻቸውን ቢሆኑ የማሻል መስሎኝ ነው "
"እሷ የፊተኛዋ ሚስቴ ሳለችም ብዙ ጊዜ ጣልቃ እየገባች ታስቸግራት እንደ ነበረ ለማወቅ ችያለሁ ይህን ነገር በጊዜው ብሰማ ኖሮ አንድ ቀን አላሳድራትም ነበር " አሁን ግን ይህ ነገር አይደገምም " በርግጥ ገና አልነገርኳትም እንጂ ኮርኒሊያ ከኢስት ሊን ለቃ ከቤቷ ትገባለች " በዚህ ምንም አያስቡ "
“ኧረ ለመሆኑ ባርባራ ስንቱን ሰው ስትመልስ ኖራ አንተን እንዴት እሺ አለችህ ? አለ ቀደም ሲል በነገሩ መደስቱንና ስምምነቱን የገለጸው ሚስተር ጀስቲስ ሔር "
“ ምናልባት መስተፋቅር አድርጌባት ይሆናል ” አለ ሣቅ ብሎ "
“ እንዲያውም ይኸው መጣች ” አለና አባትየው።
“ ኧረ እንዲያው ለነገሩ ካርላይልን ከሌሎች የተለየ ምን ብልጫ አየሽበት ? አላት "
ጉንጮቿ ፍም በመምሰል መልሱን ተናገሩላት “ “ አባባ .... ሚስተር ኦትዋይ ቤቴል ከደጅ ሊያነጋግርህ ይፈልጋል " ጃስፐር እንዶፈደ ነገረኝ ከሆነ ለመግባት አልፈለገም አለችው።
“ እኔም ብሆን በዚህ ብርድ አልወጣለትም " ሚስተር ኦትዌይ ... ግባ እንጂ
ምን አስፈራህ ? አለው
“ቀጠሯችሁ ከሰባት ሰዓት ወደ ስምንት ሰዓት ቢለወጥ የሚመችዎ እንደሆነ ኮሎኔል ጠይቅ ብለውኝ ነው የመጣሁት " አንድ ያልታሰበ እንግዳ ስለ መጣባቸውና እሱም ዛሬ በስምንት ሰዓቱ ባቡር ተመልሶ ስለሚሔድ ነው ” አለው "
“ እኔምን ከፋኝ ! በሰባትም ሆን በስምንት ግድ የለኝም ” አለው ሚስተር ሔር"
“እሺ! እንግዲያው ይኸንኑ ለሔርበትና ለፒነር ልንገራቸው " ለመሆኑ ሙቶ ስለ ተገኘው ሰውዬ ሰምተዋል ?
" የምን ሰው ነው ?
“ እንግዲህ አንዱ መንገድ የጠፋው ወይም ደክሞት ከበረዶው የወደቀና በዚያው እንዳለ የቀረ ይሆናል እንጂ ከሆሊጀን ቤት መዞሪያ አጠገብ ካለው ጐድጓዳ ሥፍራ ነው ከመንገዱ ዳር ሞቶ የተገኘው "
ብዙ ስዎች ወደዚያ ሲጎርፉ
አየሁና እኔም ሄጄ አየሁት" አለው።
“ ማነው እሱ ?” አለ ጀስቲስ ሔር ።
“ የሚታወቅ ሰው አልመሰለኝም ! ፊቱን አይቸ ላውቀው አልቻልኩም "
የሥራ ካፖርት ለብሷል ። በጣም ጢማም የሆነ ልጅ እግር ነው ” አለ ኦትዌይ ቤቴል »
“ ትናንት ጃንጥላውን በስተፊቱ ገትሮ እየተደናበረ ሲያልፈኝ ጃንጥላዬን
ሊሰብርብኝ የነበረው ሰው ሳይሆን አይቀርም » አንድ
የሥራ ካፖርት የደረበ ሪዙ ችምችም ያለ ልጅ እግር ነበር ሰውዬው ጤነኛ አልመሰለኝም " ተናደድኩና
ስጮህበት ጊዜ የድንጋጤውን ያህል ጮኸና እንደ ጥይት ሽው ብሎ ሔደ እና ኦትዌይ ይህ የምትለው ሰው እሱ ይሆናል ” አለ ሚስተር ሔር ።
“ ሊሆን ይችላል ጌታዬ " አለው ።
የሚስተር ሔር ገለጻ ' ከሪቻርድ ጋር የሚመሳሰል ስለ ነበር ባርባራ በበኩሏ
ሪቻርድ ይሆናል ብላ ተጨነቀች ሚስተር ካርላይልም ገባው "
ሚስተር ካርላይል ክፍሉን አቋርጦ ወደ በሩ ሲያልፍ እንደ ምንም ብሎ አንድ
ነገር በጆሮዋ ሹክ አላት "
ሔጄ አይቸ ወሬውን አመጣልሻለሁ እስከዚያው ቻይው የኔ ፍቅር"
“መሔድህ ነው አርኪባልድ ? አለችው ሚስዝ ሔር "
ይህን ቤቴል የሚለውን ሰውዬ አይቸ ለመምጣት ነው " መቸም ለወሬ መጓጓት ነው "
ሚስተር ካርላይል በአትክልቱ ቦታ አቋርጦ ወርዶ ሔደ ባርባራ በዐይኗ እስከ በሩ ተከተለችው
በጣም ተጨነቀች ካርላይል ተመልሶ ነው ወይም አይደለም የሚል መልስ እስኪሰጣት ድረስ እንዴት ትቆይ በጣም ተቸገረች ሪቻርድ ነው ብሎ አንድ ነገር እንደነገራት ተሰማት ኦትዌይ ቤቴልም ሔዶ ጀስቲስ ሔርም ሰው ሠራሽ ጸጉሩንና ኮቱን ማለፈያ ማለፊያውን መርጦ ለባበስና ተከትሎት ወጣ እሱም ሞተ የተባለውን ሰውዩ ለማየት ፈለገ ዌስት ሊንን በመሰለ ትንሽ ከተማ
ጥቃቅኑ ነገር ሁሉ እንደ ብርቅ ይታያል በትልልቅ ከተሞች ከቁም ነገር የማይገባው ሁሉ እዚህ ሲሆን በጣም ይጋነናል " ሕዝቡ ያደንቀዋል "
ባርባራ ከበረንዳ ቁማ በጭንቀት በጕጕት ስትጠባበቅ ካርላይልን ሲመለስ ከሩቅ አየችው ዶርሶ እስኪነግራት መቸኮሏን ተረድቶ ጥቂት ቀረብ አንዳለ ራሱን በመነቅነቅ የፈግታ ምልክት አሳያት ልቧ መምታቱን ባይቀንስላትም በፈገግታው ትንሽ ጠንከር አለች
«እንዲያው ነው የተደናገጥነው .... ባርባራ » አንድ መንግድ ጠፍቶት ይንከራተት የነበረ ማንም የማያውቀው መንገደኛ ነው " ሪዙ ቀይ ነው » በምኑም ሪቻርድን አይመስልም።
«ያን ለት ማታ ሚስ ካርላይል ጉንፋኗ ቀሏት ነበር " ራት ተበላና ሚስተር ካርላይል ስለ ጋብቻው ሊያጫውታት ጀመረ።
“ ኮርኒሊያ... እመቤት ሳቤላ ቬንን ሳገባ አስቀድሜ ስለአልነገርኩሽ በጣም ተቆጥተሽ ነበር "
« ማንም ሰው ድረግ እንደሚገባው አስቀድመህ ብታማክረኝ ኖሮማ
የደረሱት ነገሮች ሁሉ ሌላ መልክ ይኖራቸው ነበር " በዚህ ቤት ላይ የወረደው ውርደትና ፈተና አይደርስም ነበር ” አለችው እየተቆጣች "
“አሁንም ያለፈውን ትተን ስለ ወደፊቱ እናስብ " እንደ ከዚህ ቀደሙ በተሣሣመሳሳይ ሁኔታ ዳግመኛ ላስቀይምሽ ሐሳብ እንደሌለኝ ልነግርሽ ፊልጌ ነው " እንደ ሚመስለኝ ከልብሽ ይቅር አላልሽኝም"
“ ወደፊትም ከልቤ ይቅር አልልህም ” አለችው “እንደዚህ መናቅ አይገባኝም ነበር "
ስለዚህ እኔ ራሴ በቁርጥ እንዳወቅሁት ወዲያው ከሐቁ ጋር ላስተዋውቅሽ
እፈልጋለሁ " ኮርኒሊያ አሁን ሁለተኛ ላገባ አስቤአለሁ ”
ሚስ ካርላይል ክው ብላ ደነገጠችና ቀና ስትል መነጽሯ ከአፍንጫዋ ወደቀ
ስትሠራው የነበረውን ክር የያዘችበት ባኮ ከጉልበቷ ላይ ስለ ነበር ተንሸራትቶ ከመሬት ዐረፈ ።
ምን ምን ” አልክ ?”
“ አሁን በቅርቡ ማግባቴ ነው ”
“አንተ !?
“ አዎን እኔ ... ምነው ? ምን የሚያስገርም ነገር አገኘሽ ?”
“ በል በል አሁን ደግሞ በገዛ እጅህ ገብተህ አትጃጃል " አንድ ጊዜ ያየኸውዐአይበቃህም ? አሁን ደግሞ ዐይንህ እያየ ባንገትህ ሸምቀቆ ታስገባለህ ?
“ ኮርኒሊያ ... እኔ የምነግርሽን ሁሉ አንቺ በዚህ ዐይነት ስትቀበይው
እያየሁ እንዲህ ያሉትን ነገሮች ባልነግርሽ ሊገርምሽ ይገባል ? አንቺ እኔን ልክ እንደ ሕፃንነቴ ጊዜ ነው የምታይኝ " ይኸ ደግሞ ከፍተኛ የዋህነት ነው”
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
ከበረዶው ማዕበል በኋላ ብራ የሆነ ጧት ተተካ ሰማዩ ፍንትው ብሎ ጠርቶ
ፀሐይ ደምቃ ስታበራ ሲጥል ያደረው በረዶ ግን ከመሬት እንደ ተቆለለ ነበር
ሚስዝ ሔር በወንበር ተቀምጣ የቀኑን ድምቀት እያየች ትደሰታለች የማስተር ካርላይልም
አጠገቧ ቆሟል ከባርባራ ጋር የመለያየቷን ነገር ስታስበው ኀዘኑ ለሷ አቻዋ የሆነ ባል በማግኘቷ ደስታው ሁለቱ ስሜቶች ተጋጭተው ሲያስጨንቋት ዐይኖቿ የኀዘንና የደስታ እንባ አቀረሩ ።
“አርኪባልድ . . . ይህች ልጅ ከኛ ጋር ሁና ደስተኛ ነበረች አንተ ዘንድም የለመደችውን ደስታ ታገኘው ይመስልሃል ?
“ እኔ በምችለው ሁሉ።"
“ ታዝንላታለህ ? ትንከባከባታለህ ?
ሚስዝ ሔር ... ደኅና አድርገው
ስለሚያውቁኝ የሚጠራጠሩኝ አይመስለኝም ነበር " አሁንም ባለኝ አቅም ሁሉ በሙሉ ልቤ እሷን ለማስደሰት እሞክራለሁ " "
“ አንተን አልጠረጥርህም ! በደንብ አምንሃለሁ ዓለም ሁሉ ከባርባራ እግር ቢወድቅ አንተን እንድትመርጥልኝ እጸልይ ነበር ግን አርኪባልድ የኮርንሊያ ነገርስ እንዴት ይሆናል ? እኔ እንኳን ባንተ ጉዳይ ወይም አንተና ባርባራ ተስማምታችሁ በምትፈጽሙት ለመግባት ሳይሆን ባልና ሚስት ብቻቸውን ቢሆኑ የማሻል መስሎኝ ነው "
"እሷ የፊተኛዋ ሚስቴ ሳለችም ብዙ ጊዜ ጣልቃ እየገባች ታስቸግራት እንደ ነበረ ለማወቅ ችያለሁ ይህን ነገር በጊዜው ብሰማ ኖሮ አንድ ቀን አላሳድራትም ነበር " አሁን ግን ይህ ነገር አይደገምም " በርግጥ ገና አልነገርኳትም እንጂ ኮርኒሊያ ከኢስት ሊን ለቃ ከቤቷ ትገባለች " በዚህ ምንም አያስቡ "
“ኧረ ለመሆኑ ባርባራ ስንቱን ሰው ስትመልስ ኖራ አንተን እንዴት እሺ አለችህ ? አለ ቀደም ሲል በነገሩ መደስቱንና ስምምነቱን የገለጸው ሚስተር ጀስቲስ ሔር "
“ ምናልባት መስተፋቅር አድርጌባት ይሆናል ” አለ ሣቅ ብሎ "
“ እንዲያውም ይኸው መጣች ” አለና አባትየው።
“ ኧረ እንዲያው ለነገሩ ካርላይልን ከሌሎች የተለየ ምን ብልጫ አየሽበት ? አላት "
ጉንጮቿ ፍም በመምሰል መልሱን ተናገሩላት “ “ አባባ .... ሚስተር ኦትዋይ ቤቴል ከደጅ ሊያነጋግርህ ይፈልጋል " ጃስፐር እንዶፈደ ነገረኝ ከሆነ ለመግባት አልፈለገም አለችው።
“ እኔም ብሆን በዚህ ብርድ አልወጣለትም " ሚስተር ኦትዌይ ... ግባ እንጂ
ምን አስፈራህ ? አለው
“ቀጠሯችሁ ከሰባት ሰዓት ወደ ስምንት ሰዓት ቢለወጥ የሚመችዎ እንደሆነ ኮሎኔል ጠይቅ ብለውኝ ነው የመጣሁት " አንድ ያልታሰበ እንግዳ ስለ መጣባቸውና እሱም ዛሬ በስምንት ሰዓቱ ባቡር ተመልሶ ስለሚሔድ ነው ” አለው "
“ እኔምን ከፋኝ ! በሰባትም ሆን በስምንት ግድ የለኝም ” አለው ሚስተር ሔር"
“እሺ! እንግዲያው ይኸንኑ ለሔርበትና ለፒነር ልንገራቸው " ለመሆኑ ሙቶ ስለ ተገኘው ሰውዬ ሰምተዋል ?
" የምን ሰው ነው ?
“ እንግዲህ አንዱ መንገድ የጠፋው ወይም ደክሞት ከበረዶው የወደቀና በዚያው እንዳለ የቀረ ይሆናል እንጂ ከሆሊጀን ቤት መዞሪያ አጠገብ ካለው ጐድጓዳ ሥፍራ ነው ከመንገዱ ዳር ሞቶ የተገኘው "
ብዙ ስዎች ወደዚያ ሲጎርፉ
አየሁና እኔም ሄጄ አየሁት" አለው።
“ ማነው እሱ ?” አለ ጀስቲስ ሔር ።
“ የሚታወቅ ሰው አልመሰለኝም ! ፊቱን አይቸ ላውቀው አልቻልኩም "
የሥራ ካፖርት ለብሷል ። በጣም ጢማም የሆነ ልጅ እግር ነው ” አለ ኦትዌይ ቤቴል »
“ ትናንት ጃንጥላውን በስተፊቱ ገትሮ እየተደናበረ ሲያልፈኝ ጃንጥላዬን
ሊሰብርብኝ የነበረው ሰው ሳይሆን አይቀርም » አንድ
የሥራ ካፖርት የደረበ ሪዙ ችምችም ያለ ልጅ እግር ነበር ሰውዬው ጤነኛ አልመሰለኝም " ተናደድኩና
ስጮህበት ጊዜ የድንጋጤውን ያህል ጮኸና እንደ ጥይት ሽው ብሎ ሔደ እና ኦትዌይ ይህ የምትለው ሰው እሱ ይሆናል ” አለ ሚስተር ሔር ።
“ ሊሆን ይችላል ጌታዬ " አለው ።
የሚስተር ሔር ገለጻ ' ከሪቻርድ ጋር የሚመሳሰል ስለ ነበር ባርባራ በበኩሏ
ሪቻርድ ይሆናል ብላ ተጨነቀች ሚስተር ካርላይልም ገባው "
ሚስተር ካርላይል ክፍሉን አቋርጦ ወደ በሩ ሲያልፍ እንደ ምንም ብሎ አንድ
ነገር በጆሮዋ ሹክ አላት "
ሔጄ አይቸ ወሬውን አመጣልሻለሁ እስከዚያው ቻይው የኔ ፍቅር"
“መሔድህ ነው አርኪባልድ ? አለችው ሚስዝ ሔር "
ይህን ቤቴል የሚለውን ሰውዬ አይቸ ለመምጣት ነው " መቸም ለወሬ መጓጓት ነው "
ሚስተር ካርላይል በአትክልቱ ቦታ አቋርጦ ወርዶ ሔደ ባርባራ በዐይኗ እስከ በሩ ተከተለችው
በጣም ተጨነቀች ካርላይል ተመልሶ ነው ወይም አይደለም የሚል መልስ እስኪሰጣት ድረስ እንዴት ትቆይ በጣም ተቸገረች ሪቻርድ ነው ብሎ አንድ ነገር እንደነገራት ተሰማት ኦትዌይ ቤቴልም ሔዶ ጀስቲስ ሔርም ሰው ሠራሽ ጸጉሩንና ኮቱን ማለፈያ ማለፊያውን መርጦ ለባበስና ተከትሎት ወጣ እሱም ሞተ የተባለውን ሰውዩ ለማየት ፈለገ ዌስት ሊንን በመሰለ ትንሽ ከተማ
ጥቃቅኑ ነገር ሁሉ እንደ ብርቅ ይታያል በትልልቅ ከተሞች ከቁም ነገር የማይገባው ሁሉ እዚህ ሲሆን በጣም ይጋነናል " ሕዝቡ ያደንቀዋል "
ባርባራ ከበረንዳ ቁማ በጭንቀት በጕጕት ስትጠባበቅ ካርላይልን ሲመለስ ከሩቅ አየችው ዶርሶ እስኪነግራት መቸኮሏን ተረድቶ ጥቂት ቀረብ አንዳለ ራሱን በመነቅነቅ የፈግታ ምልክት አሳያት ልቧ መምታቱን ባይቀንስላትም በፈገግታው ትንሽ ጠንከር አለች
«እንዲያው ነው የተደናገጥነው .... ባርባራ » አንድ መንግድ ጠፍቶት ይንከራተት የነበረ ማንም የማያውቀው መንገደኛ ነው " ሪዙ ቀይ ነው » በምኑም ሪቻርድን አይመስልም።
«ያን ለት ማታ ሚስ ካርላይል ጉንፋኗ ቀሏት ነበር " ራት ተበላና ሚስተር ካርላይል ስለ ጋብቻው ሊያጫውታት ጀመረ።
“ ኮርኒሊያ... እመቤት ሳቤላ ቬንን ሳገባ አስቀድሜ ስለአልነገርኩሽ በጣም ተቆጥተሽ ነበር "
« ማንም ሰው ድረግ እንደሚገባው አስቀድመህ ብታማክረኝ ኖሮማ
የደረሱት ነገሮች ሁሉ ሌላ መልክ ይኖራቸው ነበር " በዚህ ቤት ላይ የወረደው ውርደትና ፈተና አይደርስም ነበር ” አለችው እየተቆጣች "
“አሁንም ያለፈውን ትተን ስለ ወደፊቱ እናስብ " እንደ ከዚህ ቀደሙ በተሣሣመሳሳይ ሁኔታ ዳግመኛ ላስቀይምሽ ሐሳብ እንደሌለኝ ልነግርሽ ፊልጌ ነው " እንደ ሚመስለኝ ከልብሽ ይቅር አላልሽኝም"
“ ወደፊትም ከልቤ ይቅር አልልህም ” አለችው “እንደዚህ መናቅ አይገባኝም ነበር "
ስለዚህ እኔ ራሴ በቁርጥ እንዳወቅሁት ወዲያው ከሐቁ ጋር ላስተዋውቅሽ
እፈልጋለሁ " ኮርኒሊያ አሁን ሁለተኛ ላገባ አስቤአለሁ ”
ሚስ ካርላይል ክው ብላ ደነገጠችና ቀና ስትል መነጽሯ ከአፍንጫዋ ወደቀ
ስትሠራው የነበረውን ክር የያዘችበት ባኮ ከጉልበቷ ላይ ስለ ነበር ተንሸራትቶ ከመሬት ዐረፈ ።
ምን ምን ” አልክ ?”
“ አሁን በቅርቡ ማግባቴ ነው ”
“አንተ !?
“ አዎን እኔ ... ምነው ? ምን የሚያስገርም ነገር አገኘሽ ?”
“ በል በል አሁን ደግሞ በገዛ እጅህ ገብተህ አትጃጃል " አንድ ጊዜ ያየኸውዐአይበቃህም ? አሁን ደግሞ ዐይንህ እያየ ባንገትህ ሸምቀቆ ታስገባለህ ?
“ ኮርኒሊያ ... እኔ የምነግርሽን ሁሉ አንቺ በዚህ ዐይነት ስትቀበይው
እያየሁ እንዲህ ያሉትን ነገሮች ባልነግርሽ ሊገርምሽ ይገባል ? አንቺ እኔን ልክ እንደ ሕፃንነቴ ጊዜ ነው የምታይኝ " ይኸ ደግሞ ከፍተኛ የዋህነት ነው”
👍13🥰1
#ጠላፊዎቹ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
‹‹እሺ›› አለ ቪንቺኒ ወደ ጀልባዋ ፊቱን አዞረና ‹‹ጆ መጀመሪያ አንተ ና
ቀጥሎ ትንሹ ልጅ በመጨረሻ የኤዲ ሚስት፡፡›› ወደ ውስጥ ሲያዩ ካፒቴኑ ወደ አይሮፕላን መንጃው ክፍል ሲሄድ አየው፡፡ በዚህ ጊዜ ቪንቺኒ ሽጉጡን
መዘዘና ‹‹አንተ ባለህበት ቁም›› ሲል አዘዘው ቤከርን፡፡
ኤዲም ካፒቴን እንደሚልህ አድርግ እባክህ እነዚህ ሰዎች ቀልድ አያውቁም›› አለ ቤከር ባለበት ቆመና እጁን ወደ ላይ አነሳ፡፡
ጆ የተባለው ወሮበላ ‹‹እዚህ ውስጥ ብወድቅ መዋኘት አልችልም›› አለ
ከጀልባው ወደ አይሮፕላኑ መዝለል ፈርቶ፡፡
‹‹መዋኘት አያስፈልግም›› አለ ኤዲ እጁን ዘረጋለት፡፡
ጆም እንደምንም ዘለለና አይሮፕላኑ ውስጥ ገባ፡፡
ከእሱ በፊት ሁለት ሰዎች በደህና መዝለላቸውን አይቶ ትንሹ ልጅ ኮራ ብሎ ዘለለ፤ ነገር ግን ሲዘል ሚዛኑን ሳተና ወደኋላው ሊወድቅ ሲል ኤዲ የልጁን ቀበቶ ይዞ አዳነው ‹‹አመሰግናለሁ›› አለ ልጁ፡፡
አሁን የካሮል አን ተራ ደረሰ ለመዝለል ፈርታ የኤዲን አይን አይን ታያለች በተፈጥሮዋ ፈሪ ሆና ሳይሆን ከእሷ በፊት ትንሹ ልጅ ተንገዳግዶ ባህር ውስጥ ሊገባ ሲል ስላየች ነው የፈራችው፡፡ ኤዲም ፈገግ አለና
‹‹እንደነሱ ዝለይ ማርዬ›› አለ ‹‹አይዞሽ ውሃ ውስጥ አትወድቂም::››
ኤዲ በፍርሃት ልቡ እየደለቀ በጉጉት ጠበቀ ሚስቱ እስክትዘል፡፡ ካሮል
አን መዝለል መቻሏን ተጠራጠረች፡፡ ‹‹ተዘጋጂና ዝለይ!›› አላት እሱም የእሷ
ፍርሃት ተጋብቶበት፡፡
ካሮል አን ጥርሷን ነክሳ እንደ ምንም ዘለለች፤ ነገር ግን ግማሽ አካሏ ባህሩ ውስጥ ሆኖ ገመዱን ለመያዝ ተፍጨረጨረች፤ ‹‹ገመዱን አጥብቀሽ
ያዥ አይዞሽ›› አለ ወደ ባህሩ የምትወድቅ ከሆነ ለመዝለል ተዘጋጅቶ
ኤዲ ተንበረከከና እጇን ለመያዝ እጁን ሰደደ፤ ሆኖም ሚዛኑን ሳተና ወደ
ባህሩ ሲወድቅ እጇን መያዝ አልቻለም፤ የባህሩ ሞገድ ጎትቶ ውሃ ውስጥ
ሲያስቀራት በተስፋ መቁረጥ ጮኸች፡፡
ያለ የሌለ ሀይሏን ተጠቅማ ወደ ኤዲ እየዋኘች ተጠጋች፤ ኤዲ ጥርሷ
ሊንገጫገጭ አየ፧ እንደ ምንም ብሎ እግሯን ያዘ፤ ሆኖም የባህሩ ሞገድ
ሃይለኛ በመሆኑ ከእጁ አፈተለከችና እንደገና ባህሩ ላይ ወደቀች፤ ካሮል አን
እየሰመጠች ነው እሱም እጁን ሰደደና ወገቧን ያዘ፡፡
‹‹አይዞሽ የኔ ማር ይዤሻለሁ›› አለና እንደምንም ተሸክሞ ወደ
አይሮፕላኑ አስገባት፡፡ ካሮል አን ባሏ እቅፍ ውስጥ ገብታ ማንባቷን ቀጠለች፡፡ እምባ ቢተናነቀውም እንደምንም ዋጥ አደረገው፡፡የምትንቀጠቀጠውን
ሚስቱን ለማረጋጋት አጥብቆ ደረቱ ላይ ለጠፋት
‹‹ደህና ነሽ የኔ ማር? እነዚህ ሰዎች አንገላቱሽ?›› ሲል ጠየቃት
‹‹ደህና ነኝ›› አለች ጥርሷ እየተንገጫገጨ፡፡
የካፒቴኑን ዓይን ለማየት ፈርቶ እየሰረቀ ያየዋል፡፡ ቤከር ወደ ካሮል
አን አማተረና
‹‹ያደረግኸው ሁሉ ለምን እንደሆነ አሁን እየገባኝ መጣ›› አለ፡፡
‹‹ይበቃል የምንሰራው ስራ አለን›› አለ ቪንቺኒም፡፡
ኤዲ ካሮል አንን ለቀቃትና ‹‹እሺ ወደምትፈልጉት ሰው እወስዳችኋለሁ››
‹‹እሺ›› አለ የወሮበሎቹ መሪ፡
‹‹ተከተሉኝ›› አላቸውና ወደ ውስጥ ገቡ፡ ሰራተኞቹ ምንም ነገር ለማድረግ እንዳይሞክሩ ኤዲ አስጠነቀቃቸው:
‹‹ሁላችሁም አደብ ግዙ፡፡ እነዚህ ሰዎች አድርጉ የሚሏችሁን ማድረግ
ብቻ ነው ያለባችሁ አለበለዚያ በጥይት ከመግደል ወደ ኋላ የሚሉ ሰዎች አይደሉም፡ ሰው እንዲጎዳ አልፈልግም፡ ካፒቴኑም ይህንኑ ነው የሚላችሁ አለ ኤዲ፡
‹‹ትክክል ነው›› አለ ካፒቴኑ ‹‹ጎበዝ! እነዚህ ሰዎች መሳሪያ የያዙ ናቸው፤ ብትወራጩ በጥይት ነው የሚሏችሁ ››
ኤዲ ወደ ቪንቺኒ ዞረና ‹‹እንሂድ እንግዲህ፤ ካፒቴን ተሳፋሪዎቹን ማረጋጋት ይኖርብሃል›› አለ፡፡
ቪንቺኒ በኤዲ አባባል መስማማቱን በራሱ ንቅናቄ አሳየ፡
‹‹ካሮል አን ከአይሮፕላኑ ሰራተኞች ጋር ሁኚ፧ እሺ›› አላት፡፡
ኤዲ ሚስቱ ከወሮበሎቹ ጥይት መራቋን ወዶታል፡ በተጨማሪም ባሏ
ለምን እነዚህን ሰዎች ሊተባበር እንደወሰነ ለተሳፋሪዎቹ ታስረዳለታለች፡
ኤዲ ቪንቺኒን ‹‹እባክህ ጠመንጃህን ከተሳፋሪዎች ብታርቅልኝ፧ ይፈራሉ››
‹‹ተነፋ!›› አለ ቪንቺኒ ‹‹እንሂድ›› ሲል አዘዘ ጓደኞቹን፡ ኤዲ ትከሻውን
በንዴት ነቀነቀ፡፡ ሁሉም ቦታ ቦታቸው ላይ እንደተቀመጡ ነው፡፡ ሁለቱ አስተናጋጆች ምንም እንዳልተፈጠረ ሁሉ ለማረጋጋት ጥረት እያደረጉ ነው፡፡
ኤዲ አይሮፕላኑ ውስጥ እየተዘዋወረ ሲያይ መብል ክፍሉ ትርምስምስ
ብሏል፡፡ ወለሉ በሸክላ እና በብርጭቆ ስብርባሪ ተሸፍኗል። ምግብ ተበልቶ
ስላለቀና ተሳፋሪዎች እየጠጡ ስለሆነ የተደፋፋ ነገር አይታይም፡:
ተሳፋሪዎቹ የቪንቺኒን ሽጉጥ ሲያዩ በፍርሃት ድምጻቸውን አጠፉ፡፡ ካፒቴን
ቤከር ወደ ፊት መጣና ‹‹ክቡራንና ክቡራት ለተፈጠረው ችግር ይቅርታ
እጠይቃለሁ፡ ከመቀመጫችሁ እንዳትነሱ፡ አሁን ያለው ችግር ከተወሰነ
ደቂቃ በኋላ መፍትሄ ያገኛል›› አለ፡፡
ኦሊስ ፊልድና ፍራንኪ ጎርዲኖ አብረው ቁጭ ብለዋል አሁን ነፍሰ
ገዳይ እንዲያመልጥ ላደርግ ነው አለ ኤዲ ለራሱ፡ ወደ ጎርዲኖም ጣቱን እየጠቆመ ‹‹ያውልህ ሰውዬህ ውሰደው›› አለ፡፡
ኦሊስ ፊልድ ከተቀመጠበት ተነሳና ‹‹ይሄ የኤፍ ቢ አይ መርማሪ ቶሚ ማክ አርድል ነው›› አለ ‹‹ፍራንኪ ጎርዲኖ ትላንት በመርከብ ኒውዮርክ ደርሶ ወህኒ ገብቷል››
‹‹የአምላክ ያለህ!›› ሲል ኤዲ በግርምት ጮኸ፡፡ ይህን ሁሉ እኩይ ተግባር ሲፈጽም የነበረው ለአስመሳይ ሰው ነው?!
‹‹እኛ ከፍራንኪ ጉዳይ የለንም፡፡ ጀርመናዊው ሳይንቲስት የታለ?›› አለ ቬኒቺኒ
ኤዲ ተገርሞ ቪንቺኒ ላይ አፈጠጠ፡፡ ጎርዲኖን አይፈልጉትም፡፡ ታዲያ
ማንን ነው የሚፈልጉት?ተ
የቶም ሉተር ድምፅ ተሰማ ‹‹እዚህ ነው ያለው፤ በእኔ ቁጥጥር ስር ነው›› አለ ሉተር ሃርትማን ላይ ሽጉጡን እየደገነ፡፡ተ
ኤዲ የበለጠ እንቆቅልሽ ሆነበት፡፡ የፓትሪያርካ ማፊያ ቡድን ለምንድን ነው ካርል ሃርትማንን ማገት የፈለገው?› ‹‹ሳይንቲስቱን ለምንድን ነው የምትፈልጉት?› ሲል ጠየቀ፡፡
ቀበል አድርጎ ‹‹ተራ ሳይንቲስት እንዳይመስልህ የኒኩሊየር ፊዚስት
ነው›› አለ ሉተር፡
‹‹እናንተ ናዚ ናችሁ?›› ሲል ጠየቀ ኤዲ፡፡
‹‹አይደለንም፧ እኛ ዲሞክራቶች ነን፡፡ እነሱ ሳይንቲስቱን አግተን
እንድንሰጣቸው ስራ አዘውን ነው፡ ረብጣ ገንዘብ ይከፍሉናል›› አለና ቪንቺኒ
ተንከተከተ፡
ሉተርም ‹‹እኔ ዲሞክራት አይደለሁም፡፡ የጀርመን አሜሪካን ትብብር
ማህበር አባል ነኝ፡፡ ይህ ማህበር በናዚ መንግስት የገንዘብ ድጋፍ
የሚንቀሳቀስ ድርጅት ነው፡፡ ሂትለር ራሱ ነው ከአገር አምልጦ የወጣውን
ሳይንቲስት አፍኜ ወደ ጀርመን እንዳመጣው ያዘዘኝ›› አለ፡፡ ሉተር ይህን
ሲናገር በኩራት ነው፡፡ ‹‹እነዚህ ሰዎች ከፍዬ የማሰራቸው እኔ ነኝ፡፡ ስለዚህ ዶክተር ፕሮፌሰር ሃርትማንን ወደ ጀርመን መልሼ እወስደዋለሁ፡
ሳይንቲስቱ እዚያ በጣም ይፈለጋል›› አለ፡
ኤዲ ከሃርትማን ጋር ዓይን ላይን ግጥም አለ፡፡ ሰውዬው ፍርሃት
ጨምድዷቸዋል፡ ኤዲ ወዲያው ፀፀት ገባው፡፡ ሳይንቲስቱ ወደ ጀርመን
ሊመለሱ ነው፡፡ ይሄ ደግሞ የኤዲ ጥፋት ነው፡፡
‹‹ምን ላድርግ ባለቤቴን ስላገቱብኝ ነው የተባበርኳቸው›› አለ፡፡
የሃርትማን አስተያየት ተለወጠ ‹‹ይገባኛል›› አሉ ሳይንቲስቱ ‹‹እንደዚህ
አይነት ክህደቶችን ጀርመን ውስጥ ለምደናቸዋል፡ አንዱን ለማዳን ስትል
ሌላውን አሳልፈህ ትሰጣለህ፡ ምንም ምርጫ አልነበረህም፡፡ በዚህ ራስህን አትውቀስ›› አሉት፡፡
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
‹‹እሺ›› አለ ቪንቺኒ ወደ ጀልባዋ ፊቱን አዞረና ‹‹ጆ መጀመሪያ አንተ ና
ቀጥሎ ትንሹ ልጅ በመጨረሻ የኤዲ ሚስት፡፡›› ወደ ውስጥ ሲያዩ ካፒቴኑ ወደ አይሮፕላን መንጃው ክፍል ሲሄድ አየው፡፡ በዚህ ጊዜ ቪንቺኒ ሽጉጡን
መዘዘና ‹‹አንተ ባለህበት ቁም›› ሲል አዘዘው ቤከርን፡፡
ኤዲም ካፒቴን እንደሚልህ አድርግ እባክህ እነዚህ ሰዎች ቀልድ አያውቁም›› አለ ቤከር ባለበት ቆመና እጁን ወደ ላይ አነሳ፡፡
ጆ የተባለው ወሮበላ ‹‹እዚህ ውስጥ ብወድቅ መዋኘት አልችልም›› አለ
ከጀልባው ወደ አይሮፕላኑ መዝለል ፈርቶ፡፡
‹‹መዋኘት አያስፈልግም›› አለ ኤዲ እጁን ዘረጋለት፡፡
ጆም እንደምንም ዘለለና አይሮፕላኑ ውስጥ ገባ፡፡
ከእሱ በፊት ሁለት ሰዎች በደህና መዝለላቸውን አይቶ ትንሹ ልጅ ኮራ ብሎ ዘለለ፤ ነገር ግን ሲዘል ሚዛኑን ሳተና ወደኋላው ሊወድቅ ሲል ኤዲ የልጁን ቀበቶ ይዞ አዳነው ‹‹አመሰግናለሁ›› አለ ልጁ፡፡
አሁን የካሮል አን ተራ ደረሰ ለመዝለል ፈርታ የኤዲን አይን አይን ታያለች በተፈጥሮዋ ፈሪ ሆና ሳይሆን ከእሷ በፊት ትንሹ ልጅ ተንገዳግዶ ባህር ውስጥ ሊገባ ሲል ስላየች ነው የፈራችው፡፡ ኤዲም ፈገግ አለና
‹‹እንደነሱ ዝለይ ማርዬ›› አለ ‹‹አይዞሽ ውሃ ውስጥ አትወድቂም::››
ኤዲ በፍርሃት ልቡ እየደለቀ በጉጉት ጠበቀ ሚስቱ እስክትዘል፡፡ ካሮል
አን መዝለል መቻሏን ተጠራጠረች፡፡ ‹‹ተዘጋጂና ዝለይ!›› አላት እሱም የእሷ
ፍርሃት ተጋብቶበት፡፡
ካሮል አን ጥርሷን ነክሳ እንደ ምንም ዘለለች፤ ነገር ግን ግማሽ አካሏ ባህሩ ውስጥ ሆኖ ገመዱን ለመያዝ ተፍጨረጨረች፤ ‹‹ገመዱን አጥብቀሽ
ያዥ አይዞሽ›› አለ ወደ ባህሩ የምትወድቅ ከሆነ ለመዝለል ተዘጋጅቶ
ኤዲ ተንበረከከና እጇን ለመያዝ እጁን ሰደደ፤ ሆኖም ሚዛኑን ሳተና ወደ
ባህሩ ሲወድቅ እጇን መያዝ አልቻለም፤ የባህሩ ሞገድ ጎትቶ ውሃ ውስጥ
ሲያስቀራት በተስፋ መቁረጥ ጮኸች፡፡
ያለ የሌለ ሀይሏን ተጠቅማ ወደ ኤዲ እየዋኘች ተጠጋች፤ ኤዲ ጥርሷ
ሊንገጫገጭ አየ፧ እንደ ምንም ብሎ እግሯን ያዘ፤ ሆኖም የባህሩ ሞገድ
ሃይለኛ በመሆኑ ከእጁ አፈተለከችና እንደገና ባህሩ ላይ ወደቀች፤ ካሮል አን
እየሰመጠች ነው እሱም እጁን ሰደደና ወገቧን ያዘ፡፡
‹‹አይዞሽ የኔ ማር ይዤሻለሁ›› አለና እንደምንም ተሸክሞ ወደ
አይሮፕላኑ አስገባት፡፡ ካሮል አን ባሏ እቅፍ ውስጥ ገብታ ማንባቷን ቀጠለች፡፡ እምባ ቢተናነቀውም እንደምንም ዋጥ አደረገው፡፡የምትንቀጠቀጠውን
ሚስቱን ለማረጋጋት አጥብቆ ደረቱ ላይ ለጠፋት
‹‹ደህና ነሽ የኔ ማር? እነዚህ ሰዎች አንገላቱሽ?›› ሲል ጠየቃት
‹‹ደህና ነኝ›› አለች ጥርሷ እየተንገጫገጨ፡፡
የካፒቴኑን ዓይን ለማየት ፈርቶ እየሰረቀ ያየዋል፡፡ ቤከር ወደ ካሮል
አን አማተረና
‹‹ያደረግኸው ሁሉ ለምን እንደሆነ አሁን እየገባኝ መጣ›› አለ፡፡
‹‹ይበቃል የምንሰራው ስራ አለን›› አለ ቪንቺኒም፡፡
ኤዲ ካሮል አንን ለቀቃትና ‹‹እሺ ወደምትፈልጉት ሰው እወስዳችኋለሁ››
‹‹እሺ›› አለ የወሮበሎቹ መሪ፡
‹‹ተከተሉኝ›› አላቸውና ወደ ውስጥ ገቡ፡ ሰራተኞቹ ምንም ነገር ለማድረግ እንዳይሞክሩ ኤዲ አስጠነቀቃቸው:
‹‹ሁላችሁም አደብ ግዙ፡፡ እነዚህ ሰዎች አድርጉ የሚሏችሁን ማድረግ
ብቻ ነው ያለባችሁ አለበለዚያ በጥይት ከመግደል ወደ ኋላ የሚሉ ሰዎች አይደሉም፡ ሰው እንዲጎዳ አልፈልግም፡ ካፒቴኑም ይህንኑ ነው የሚላችሁ አለ ኤዲ፡
‹‹ትክክል ነው›› አለ ካፒቴኑ ‹‹ጎበዝ! እነዚህ ሰዎች መሳሪያ የያዙ ናቸው፤ ብትወራጩ በጥይት ነው የሚሏችሁ ››
ኤዲ ወደ ቪንቺኒ ዞረና ‹‹እንሂድ እንግዲህ፤ ካፒቴን ተሳፋሪዎቹን ማረጋጋት ይኖርብሃል›› አለ፡፡
ቪንቺኒ በኤዲ አባባል መስማማቱን በራሱ ንቅናቄ አሳየ፡
‹‹ካሮል አን ከአይሮፕላኑ ሰራተኞች ጋር ሁኚ፧ እሺ›› አላት፡፡
ኤዲ ሚስቱ ከወሮበሎቹ ጥይት መራቋን ወዶታል፡ በተጨማሪም ባሏ
ለምን እነዚህን ሰዎች ሊተባበር እንደወሰነ ለተሳፋሪዎቹ ታስረዳለታለች፡
ኤዲ ቪንቺኒን ‹‹እባክህ ጠመንጃህን ከተሳፋሪዎች ብታርቅልኝ፧ ይፈራሉ››
‹‹ተነፋ!›› አለ ቪንቺኒ ‹‹እንሂድ›› ሲል አዘዘ ጓደኞቹን፡ ኤዲ ትከሻውን
በንዴት ነቀነቀ፡፡ ሁሉም ቦታ ቦታቸው ላይ እንደተቀመጡ ነው፡፡ ሁለቱ አስተናጋጆች ምንም እንዳልተፈጠረ ሁሉ ለማረጋጋት ጥረት እያደረጉ ነው፡፡
ኤዲ አይሮፕላኑ ውስጥ እየተዘዋወረ ሲያይ መብል ክፍሉ ትርምስምስ
ብሏል፡፡ ወለሉ በሸክላ እና በብርጭቆ ስብርባሪ ተሸፍኗል። ምግብ ተበልቶ
ስላለቀና ተሳፋሪዎች እየጠጡ ስለሆነ የተደፋፋ ነገር አይታይም፡:
ተሳፋሪዎቹ የቪንቺኒን ሽጉጥ ሲያዩ በፍርሃት ድምጻቸውን አጠፉ፡፡ ካፒቴን
ቤከር ወደ ፊት መጣና ‹‹ክቡራንና ክቡራት ለተፈጠረው ችግር ይቅርታ
እጠይቃለሁ፡ ከመቀመጫችሁ እንዳትነሱ፡ አሁን ያለው ችግር ከተወሰነ
ደቂቃ በኋላ መፍትሄ ያገኛል›› አለ፡፡
ኦሊስ ፊልድና ፍራንኪ ጎርዲኖ አብረው ቁጭ ብለዋል አሁን ነፍሰ
ገዳይ እንዲያመልጥ ላደርግ ነው አለ ኤዲ ለራሱ፡ ወደ ጎርዲኖም ጣቱን እየጠቆመ ‹‹ያውልህ ሰውዬህ ውሰደው›› አለ፡፡
ኦሊስ ፊልድ ከተቀመጠበት ተነሳና ‹‹ይሄ የኤፍ ቢ አይ መርማሪ ቶሚ ማክ አርድል ነው›› አለ ‹‹ፍራንኪ ጎርዲኖ ትላንት በመርከብ ኒውዮርክ ደርሶ ወህኒ ገብቷል››
‹‹የአምላክ ያለህ!›› ሲል ኤዲ በግርምት ጮኸ፡፡ ይህን ሁሉ እኩይ ተግባር ሲፈጽም የነበረው ለአስመሳይ ሰው ነው?!
‹‹እኛ ከፍራንኪ ጉዳይ የለንም፡፡ ጀርመናዊው ሳይንቲስት የታለ?›› አለ ቬኒቺኒ
ኤዲ ተገርሞ ቪንቺኒ ላይ አፈጠጠ፡፡ ጎርዲኖን አይፈልጉትም፡፡ ታዲያ
ማንን ነው የሚፈልጉት?ተ
የቶም ሉተር ድምፅ ተሰማ ‹‹እዚህ ነው ያለው፤ በእኔ ቁጥጥር ስር ነው›› አለ ሉተር ሃርትማን ላይ ሽጉጡን እየደገነ፡፡ተ
ኤዲ የበለጠ እንቆቅልሽ ሆነበት፡፡ የፓትሪያርካ ማፊያ ቡድን ለምንድን ነው ካርል ሃርትማንን ማገት የፈለገው?› ‹‹ሳይንቲስቱን ለምንድን ነው የምትፈልጉት?› ሲል ጠየቀ፡፡
ቀበል አድርጎ ‹‹ተራ ሳይንቲስት እንዳይመስልህ የኒኩሊየር ፊዚስት
ነው›› አለ ሉተር፡
‹‹እናንተ ናዚ ናችሁ?›› ሲል ጠየቀ ኤዲ፡፡
‹‹አይደለንም፧ እኛ ዲሞክራቶች ነን፡፡ እነሱ ሳይንቲስቱን አግተን
እንድንሰጣቸው ስራ አዘውን ነው፡ ረብጣ ገንዘብ ይከፍሉናል›› አለና ቪንቺኒ
ተንከተከተ፡
ሉተርም ‹‹እኔ ዲሞክራት አይደለሁም፡፡ የጀርመን አሜሪካን ትብብር
ማህበር አባል ነኝ፡፡ ይህ ማህበር በናዚ መንግስት የገንዘብ ድጋፍ
የሚንቀሳቀስ ድርጅት ነው፡፡ ሂትለር ራሱ ነው ከአገር አምልጦ የወጣውን
ሳይንቲስት አፍኜ ወደ ጀርመን እንዳመጣው ያዘዘኝ›› አለ፡፡ ሉተር ይህን
ሲናገር በኩራት ነው፡፡ ‹‹እነዚህ ሰዎች ከፍዬ የማሰራቸው እኔ ነኝ፡፡ ስለዚህ ዶክተር ፕሮፌሰር ሃርትማንን ወደ ጀርመን መልሼ እወስደዋለሁ፡
ሳይንቲስቱ እዚያ በጣም ይፈለጋል›› አለ፡
ኤዲ ከሃርትማን ጋር ዓይን ላይን ግጥም አለ፡፡ ሰውዬው ፍርሃት
ጨምድዷቸዋል፡ ኤዲ ወዲያው ፀፀት ገባው፡፡ ሳይንቲስቱ ወደ ጀርመን
ሊመለሱ ነው፡፡ ይሄ ደግሞ የኤዲ ጥፋት ነው፡፡
‹‹ምን ላድርግ ባለቤቴን ስላገቱብኝ ነው የተባበርኳቸው›› አለ፡፡
የሃርትማን አስተያየት ተለወጠ ‹‹ይገባኛል›› አሉ ሳይንቲስቱ ‹‹እንደዚህ
አይነት ክህደቶችን ጀርመን ውስጥ ለምደናቸዋል፡ አንዱን ለማዳን ስትል
ሌላውን አሳልፈህ ትሰጣለህ፡ ምንም ምርጫ አልነበረህም፡፡ በዚህ ራስህን አትውቀስ›› አሉት፡፡
👍12
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
/////
ወደሸገር ተመልሰዋል..ማለት እሷ እና ንስሯ ፡፡ለእናቷ በመጨረሻው ቀን ተመልሳ እንደምታያትና ወደአባቷ ዘመዶችም በምትሄድበት ቀን አጠገቧ እንድትሆን እንደምትፈልግ ነግራትና ቃል ገብታላት ነው የመጣችው፡፡
እስከዛው ያሉትን ቀጣዬቹን በስስት እየተሸራረፉ በመርገፍና በማለቅ ላይ ያሉትን ቀሪ 5 የሰቀቀን ቀናቶችን ሸገር ልታሳልፍ ወስናለች….ምን አልባትም አይታውቅም… በመሀል ሀሳቧን ልትቀይር ትችላለች፡፡
ግን አሁን ተረጋግታ እቤቷ መቀመጥ አልቻለችም … ሰዓቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ቢያልፍም ልትቆጣጠረው የማትችለው ከውስጧ ሚመነጭ ስውር ስሜት ውጪ ውጪ ይላት ጀመር….ልብሷን ቀያየረችና መኪናዋን ወዳለችበት መራመድ ከጀመረች በኃላ ሀሳቧን ቀየረችና ስልኳን አውጥታ ደወለች..አዎ ነፃ መሆን ነው የምትፈልገው….ላዳ ያለው የምታውቀው ልጅ ጋር ነው የደወለችው፡፡
‹‹ሄሎ››
‹‹ሰላም ነው… .ፈልጌህ ነበር…የት ነህ ያለኸው?››
‹‹ይቅርታ ዛሬ ስራ ላይ አይደለሁም መኪናዬ ተበላሽታ ገራዥ ነች››
‹‹በቃ አንተ ናልኛ ..የእኔ መኪና ስላለች ትይዝልኛለህ …ጥሩ ስሜት ላይ ስላልሆንኩ መንዳት አልፈለኩም››
‹‹ደስ ይለኝ ነበር.. ግን ያው ስራ የለኝም ብዬ ከከተማ ወጣ ብያለሁ…..ከፈለግሽ አንድ ጓደኛዬን ልልክልሽ እችላለሁ››
‹‹ደስ ይለኛል››
‹‹በቃ ንገረውና ቁጥርሽን ሰጠዋለሁ…ይደውልልሻል››
‹‹እሺ አመሰግናለሁ››ስልኳን ዘጋችውና ጊቢዋ ውስጥ እየተዘዋወረች እስኪደወልላት መጠበቅ ጀመረች….፡፡
ብዙም ሳይቆይ ስልኳ ላይ የማታውቀው ቁጥር ተንጫረረ …አነሳችው..አናገረችው ….በ15 ደቂቃ እንደሚደርስ ነገራት…..መጠበቅ ጀመረች…..
‹‹አዎ በዚህ ለሊት ምን አልባት ለመጨረሻ ጊዜ ማበድ እፈልጋለሁ..አዎ ብዙ ነገር ማድረግ አምሮኛል…የማሰብ አቅሜን አዳክሞ ጭንቀቴን የሚቀንስልኝን ማንኛውንም ነገር ለማድረግ እፈልጋለሁ…..መጠጣትና መስከር …መቁላላትና መዋሰብ እፈልጋለሁ…መጣላትና መደባደብም ካገኘሁ አልጠላም…››
እግዜር ይስጠው የመኪና ጥሩንባ ድምጽ ሰማች...ጎበዝ ልጅ ነው… በነገረችው ምልክት መሰረት ሳይሳሳት መምጣቱ አስደሰታት… በራፍን ከፈተችና ወጣች…በምልክት ጠራት … የላዳውን በራፍ ከፈተላትና ገባች፡፡
‹‹ወዴት ልውሰድሽ….?››
‹‹መጠጣት ነው የምፈልገው››አለችው፡፡
‹‹መጠጣት›› አላት ግራ ተጋብቶ፡፡
‹‹መጠጣት ስልህ …ብሽቅጥ እስክል መጠጣት ነው የምፈልገው…የፈለከውን ያህል ከፍልሀለሁ እስከንጋትም ቢሆን አብረኸኝ ትቆይና እቤቴ ታስገባኛለህ››
‹‹ይመችሽ ››አላት….
እንዲሁ ወደደችው…አንድን ሰው አይተን በውስጣችን ስለሰውዬው ደስ የሚል ስሜት ሲሰማን ውቃቢዬ ወዶታል የምንለው ነገር አለ አይደል..….? እሷም ይሄን የላዳ ሹፌር እንዳየችው እንደዛ ነው የተሰማት፡፡
‹‹ምርጫሽ የት አካባቢ ነው?››
‹‹የፈለክበት ውሰደኝ ››
‹‹ቺቺኚያ ይመችሻል››
‹‹ይመችህ››
ነዳው….ንስሯ አምኗት እቤት ሊቀር አልቻለም …ከፊት ለፊታቸው በላዳዋ ፍጥነት መጠን ሲበር በመኪናዋ መስታወት አሻግራ አየችው….
ደረሱና መኪናዋን ምቹ እና ደህንነቱ የተጠበቀበት ቦታ ፓርክ አድርገው አንዱ ጭፈራ ቤት ገቡ……እሷ ደረቅ አልኮለሏን ስታዝ እሱ ዉሀ አዘዘ..
‹‹ለምን ትንሽ አትሞከርም….? ››
‹‹አይ …የሞያዬ ስነምግባር አይፈቅድልኝም›› ሲል መለሰላት በቀልድ መልክ
..ዝም አለችው… በላይ በላዩ መለጋቱን ቀጠለች….የሙዚቃው ከጣሪያ በላይ ጩኸት…የለሊት ንገስታቶች በገዢ መሳይ ወንዶች ዙሪያ መሽከርከር፤ በስካር የሚናውዙና የሚደንሱ ወንዶችና ሴቶች የሆቴሉን ወለል መሙላት…የሆነ ትርምስምስ ያለ ነገር ነው የሚታየው….በዛ ላይ መብራቱ በአምስት አይነት ቀለም በመፈራረቅ ቦግ ብልጭ ሲል እይታን ብዥ ያደርጋል…….ግን በምትፈልገው መጠን ባይሆንም ተመችቷታል ፡፡ቢሆንም ደስታዋን ሙሉ ማድረግ ፈለገች…
‹‹ሌላ ጓደኛ የለህም….?››ድንገት ከመሬት ተነስታ ጠየቀችው፡፡
‹‹ምን አይነት….?››
‹‹ሹፌር››..
‹‹ምን ያደርግልሻል….?››
‹‹ያንተን መኪና የሚነዳልን››
‹‹እኔስ….?››አላት በጥያቄዋ ግራ ተጋብቶ
‹‹አይ አንተማ እንድታጣጣኝ ፈልጌ ነው..ብቻዬን ደበረኝ››
‹‹እ ..ቆይ እስኪ ደዋውዬ ልሞክር››አለና ስልኩን እየጎረጎረ ከሆቴሉ ወጣ..ሲወጣ ከጀርባው ሳታየው ነበር…ቁመናው መስጧታል..በቃ የተለመደው ችግሯ እያገረሸባት ነው..ጭኗ መካከል አሳከካት…ምን አይነት መጥፎ አመል ነው…እዛም አባቷ አለም ስትሄድ እንዲህ የሚበላት ነገር ወቅት እየጠበቀ ይፈታተናት ይሆን እንደዛ ከሆነ ምንድነው የምታደርገው….….?
ሀሳቧን ሳትጨርስ መጣና መቀመጫው ላይ ተመልሶ እየተቀመጠ..‹‹ተሳክቶል…ተቀላቅዬሻለሁ››አላት
በደስታ እየፈገገች‹‹ምን ይምጣልህ..?››ሥትል ምርጫውን ጠየቀችው፡፡
‹‹አንቺ የያዝሺውን…››
ሙሉ ጠርሙስ አዘዙ…መጣላቸው…… ይገለብጡት ጀመረ…እየደነሱ እየተቀመጡ …ደግሞ ተመልሰው በመነሳት እየደነሱ ..ውልቅልቃቸው እስኪወጣ ድረስ አስነኩት‹‹ …አቤት ዳንሱ !!ፕሮፌሽናል ነው ፡፡ልቤን ስልብ ነው ያደረገኝ…›አለች በዳንስ ችሎታው ተመስጣ፡፡ይበልጥ ሰውነቱ ላይ ተለጥፋ በተሸሻችው መጠን የጭኗ መብላላ አደብ እየነሳት ነው…በትርምሱ መካከል በዳንስ ስልት በማሳበብ እጣቷን ወደጭኗ በመስደድ ይሉኝታ እስክታጣ ድረስ እያሻሸች ነው..ደግነቱ ሁሉም በመጠጥ የደመቀ እና በመብራቱ ቦግ ብልጭ ብዥ ያለበት መሆኑ በጃት …
ከለሊቱ አምስት ሰዓት አካባቢ ሲሆን ግን ተዳከሙ…
‹‹ቤት እንቀይር ….?››አለችው… ቤት መቀየር የፈለገችው ሙዳችውንም ጭምር መቀየር ስለፈለገች ነው… ተስማማ ..ሂሳብ ዘግተው ወጡ…
‹‹ጭፈራ ቤት ሳይሆን ዝም ብለን የምንጠጣበት ቦታ ነው የምፈልገው…››
ወደላዳዋ ይዟት ሄደ …ቅድም ተጠርቶ የመጣው ጓዳኛውን ገቢና ቁጭ ብሎ ጫቱን ሲቀመቅም አገኙት..ሁለቱም ተደጋግፈው ከኃላ ገቡ… ላዳዋ ተንቀሳቀሰች… በመስኮቱ አንጋጣ ሰማዮን ሰታይ ንስሯን ቀድሟት ለመብረር ሲያኮበኩብ አየችው…ሰካራሙ ጓደኛው እይታዋን ተከትሎ ወደውጭ በተመሳሳይ ሁኔታ ካየ በኃላ‹‹ አይገርምም ይሄ አሞራ ቅድምም ስንመጣ ከፊት ለፊታችን ሲበር ነበር….እርግጠኛ ነኝ የተለየ ከለር ስላለው አስተውዬው ነበር››አለ
‹‹አሞራ አይደለም..ንስር ነው››አረመችው
‹‹እንዴ.. አዎ ንስር ነው ትክክል ..አንቺ ግን እንዴት አወቅሽ….?››
‹‹የእኔ ነው››በልበ ሙሉነት መለሰችለት፡፡
‹‹የእኔ ነው ስትይ….?››ያዝ ያዝ በሚያደርገው የስካር አንደበት ጠየቃት
‹‹ወንድሜ ነው››
ሁለቱም ተንከትክተው ሳቁ
‹‹..ቀልደኛ ነሽ..ይበልጥ ስትጠጪ ደግሞ ይብልጥ ቀልደኛ የመሆን ተስፋ አለሽ ማለት ነው››አላት፡፡
….አስረድቶ ማሰማንም ሆነ ተከራክሮ ማሸንፈ እንደማትችል ስለተረዳች‹‹ይሁንልህ›› አለችው ፡፡
መገናኛ አካባቢ ደርሱ… ብዙም ትርምስ የሌለበት እሷ የማታውቀው ሁለቱ ግን የሚያውቁት ሆቴል ይዘዋት ገቡ..ሹፌሩ ከላዳዋ አልወረደም…‹‹ጫቴን ብቅም ይሻለኝል›› ብሎ ቀረ …እነሱ ተያይዘው ገቡና የተገነጠለ እና ከታዳሚ የራቀ ወንበር ይዘው ተቀመጡ፡፡
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
/////
ወደሸገር ተመልሰዋል..ማለት እሷ እና ንስሯ ፡፡ለእናቷ በመጨረሻው ቀን ተመልሳ እንደምታያትና ወደአባቷ ዘመዶችም በምትሄድበት ቀን አጠገቧ እንድትሆን እንደምትፈልግ ነግራትና ቃል ገብታላት ነው የመጣችው፡፡
እስከዛው ያሉትን ቀጣዬቹን በስስት እየተሸራረፉ በመርገፍና በማለቅ ላይ ያሉትን ቀሪ 5 የሰቀቀን ቀናቶችን ሸገር ልታሳልፍ ወስናለች….ምን አልባትም አይታውቅም… በመሀል ሀሳቧን ልትቀይር ትችላለች፡፡
ግን አሁን ተረጋግታ እቤቷ መቀመጥ አልቻለችም … ሰዓቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ቢያልፍም ልትቆጣጠረው የማትችለው ከውስጧ ሚመነጭ ስውር ስሜት ውጪ ውጪ ይላት ጀመር….ልብሷን ቀያየረችና መኪናዋን ወዳለችበት መራመድ ከጀመረች በኃላ ሀሳቧን ቀየረችና ስልኳን አውጥታ ደወለች..አዎ ነፃ መሆን ነው የምትፈልገው….ላዳ ያለው የምታውቀው ልጅ ጋር ነው የደወለችው፡፡
‹‹ሄሎ››
‹‹ሰላም ነው… .ፈልጌህ ነበር…የት ነህ ያለኸው?››
‹‹ይቅርታ ዛሬ ስራ ላይ አይደለሁም መኪናዬ ተበላሽታ ገራዥ ነች››
‹‹በቃ አንተ ናልኛ ..የእኔ መኪና ስላለች ትይዝልኛለህ …ጥሩ ስሜት ላይ ስላልሆንኩ መንዳት አልፈለኩም››
‹‹ደስ ይለኝ ነበር.. ግን ያው ስራ የለኝም ብዬ ከከተማ ወጣ ብያለሁ…..ከፈለግሽ አንድ ጓደኛዬን ልልክልሽ እችላለሁ››
‹‹ደስ ይለኛል››
‹‹በቃ ንገረውና ቁጥርሽን ሰጠዋለሁ…ይደውልልሻል››
‹‹እሺ አመሰግናለሁ››ስልኳን ዘጋችውና ጊቢዋ ውስጥ እየተዘዋወረች እስኪደወልላት መጠበቅ ጀመረች….፡፡
ብዙም ሳይቆይ ስልኳ ላይ የማታውቀው ቁጥር ተንጫረረ …አነሳችው..አናገረችው ….በ15 ደቂቃ እንደሚደርስ ነገራት…..መጠበቅ ጀመረች…..
‹‹አዎ በዚህ ለሊት ምን አልባት ለመጨረሻ ጊዜ ማበድ እፈልጋለሁ..አዎ ብዙ ነገር ማድረግ አምሮኛል…የማሰብ አቅሜን አዳክሞ ጭንቀቴን የሚቀንስልኝን ማንኛውንም ነገር ለማድረግ እፈልጋለሁ…..መጠጣትና መስከር …መቁላላትና መዋሰብ እፈልጋለሁ…መጣላትና መደባደብም ካገኘሁ አልጠላም…››
እግዜር ይስጠው የመኪና ጥሩንባ ድምጽ ሰማች...ጎበዝ ልጅ ነው… በነገረችው ምልክት መሰረት ሳይሳሳት መምጣቱ አስደሰታት… በራፍን ከፈተችና ወጣች…በምልክት ጠራት … የላዳውን በራፍ ከፈተላትና ገባች፡፡
‹‹ወዴት ልውሰድሽ….?››
‹‹መጠጣት ነው የምፈልገው››አለችው፡፡
‹‹መጠጣት›› አላት ግራ ተጋብቶ፡፡
‹‹መጠጣት ስልህ …ብሽቅጥ እስክል መጠጣት ነው የምፈልገው…የፈለከውን ያህል ከፍልሀለሁ እስከንጋትም ቢሆን አብረኸኝ ትቆይና እቤቴ ታስገባኛለህ››
‹‹ይመችሽ ››አላት….
እንዲሁ ወደደችው…አንድን ሰው አይተን በውስጣችን ስለሰውዬው ደስ የሚል ስሜት ሲሰማን ውቃቢዬ ወዶታል የምንለው ነገር አለ አይደል..….? እሷም ይሄን የላዳ ሹፌር እንዳየችው እንደዛ ነው የተሰማት፡፡
‹‹ምርጫሽ የት አካባቢ ነው?››
‹‹የፈለክበት ውሰደኝ ››
‹‹ቺቺኚያ ይመችሻል››
‹‹ይመችህ››
ነዳው….ንስሯ አምኗት እቤት ሊቀር አልቻለም …ከፊት ለፊታቸው በላዳዋ ፍጥነት መጠን ሲበር በመኪናዋ መስታወት አሻግራ አየችው….
ደረሱና መኪናዋን ምቹ እና ደህንነቱ የተጠበቀበት ቦታ ፓርክ አድርገው አንዱ ጭፈራ ቤት ገቡ……እሷ ደረቅ አልኮለሏን ስታዝ እሱ ዉሀ አዘዘ..
‹‹ለምን ትንሽ አትሞከርም….? ››
‹‹አይ …የሞያዬ ስነምግባር አይፈቅድልኝም›› ሲል መለሰላት በቀልድ መልክ
..ዝም አለችው… በላይ በላዩ መለጋቱን ቀጠለች….የሙዚቃው ከጣሪያ በላይ ጩኸት…የለሊት ንገስታቶች በገዢ መሳይ ወንዶች ዙሪያ መሽከርከር፤ በስካር የሚናውዙና የሚደንሱ ወንዶችና ሴቶች የሆቴሉን ወለል መሙላት…የሆነ ትርምስምስ ያለ ነገር ነው የሚታየው….በዛ ላይ መብራቱ በአምስት አይነት ቀለም በመፈራረቅ ቦግ ብልጭ ሲል እይታን ብዥ ያደርጋል…….ግን በምትፈልገው መጠን ባይሆንም ተመችቷታል ፡፡ቢሆንም ደስታዋን ሙሉ ማድረግ ፈለገች…
‹‹ሌላ ጓደኛ የለህም….?››ድንገት ከመሬት ተነስታ ጠየቀችው፡፡
‹‹ምን አይነት….?››
‹‹ሹፌር››..
‹‹ምን ያደርግልሻል….?››
‹‹ያንተን መኪና የሚነዳልን››
‹‹እኔስ….?››አላት በጥያቄዋ ግራ ተጋብቶ
‹‹አይ አንተማ እንድታጣጣኝ ፈልጌ ነው..ብቻዬን ደበረኝ››
‹‹እ ..ቆይ እስኪ ደዋውዬ ልሞክር››አለና ስልኩን እየጎረጎረ ከሆቴሉ ወጣ..ሲወጣ ከጀርባው ሳታየው ነበር…ቁመናው መስጧታል..በቃ የተለመደው ችግሯ እያገረሸባት ነው..ጭኗ መካከል አሳከካት…ምን አይነት መጥፎ አመል ነው…እዛም አባቷ አለም ስትሄድ እንዲህ የሚበላት ነገር ወቅት እየጠበቀ ይፈታተናት ይሆን እንደዛ ከሆነ ምንድነው የምታደርገው….….?
ሀሳቧን ሳትጨርስ መጣና መቀመጫው ላይ ተመልሶ እየተቀመጠ..‹‹ተሳክቶል…ተቀላቅዬሻለሁ››አላት
በደስታ እየፈገገች‹‹ምን ይምጣልህ..?››ሥትል ምርጫውን ጠየቀችው፡፡
‹‹አንቺ የያዝሺውን…››
ሙሉ ጠርሙስ አዘዙ…መጣላቸው…… ይገለብጡት ጀመረ…እየደነሱ እየተቀመጡ …ደግሞ ተመልሰው በመነሳት እየደነሱ ..ውልቅልቃቸው እስኪወጣ ድረስ አስነኩት‹‹ …አቤት ዳንሱ !!ፕሮፌሽናል ነው ፡፡ልቤን ስልብ ነው ያደረገኝ…›አለች በዳንስ ችሎታው ተመስጣ፡፡ይበልጥ ሰውነቱ ላይ ተለጥፋ በተሸሻችው መጠን የጭኗ መብላላ አደብ እየነሳት ነው…በትርምሱ መካከል በዳንስ ስልት በማሳበብ እጣቷን ወደጭኗ በመስደድ ይሉኝታ እስክታጣ ድረስ እያሻሸች ነው..ደግነቱ ሁሉም በመጠጥ የደመቀ እና በመብራቱ ቦግ ብልጭ ብዥ ያለበት መሆኑ በጃት …
ከለሊቱ አምስት ሰዓት አካባቢ ሲሆን ግን ተዳከሙ…
‹‹ቤት እንቀይር ….?››አለችው… ቤት መቀየር የፈለገችው ሙዳችውንም ጭምር መቀየር ስለፈለገች ነው… ተስማማ ..ሂሳብ ዘግተው ወጡ…
‹‹ጭፈራ ቤት ሳይሆን ዝም ብለን የምንጠጣበት ቦታ ነው የምፈልገው…››
ወደላዳዋ ይዟት ሄደ …ቅድም ተጠርቶ የመጣው ጓዳኛውን ገቢና ቁጭ ብሎ ጫቱን ሲቀመቅም አገኙት..ሁለቱም ተደጋግፈው ከኃላ ገቡ… ላዳዋ ተንቀሳቀሰች… በመስኮቱ አንጋጣ ሰማዮን ሰታይ ንስሯን ቀድሟት ለመብረር ሲያኮበኩብ አየችው…ሰካራሙ ጓደኛው እይታዋን ተከትሎ ወደውጭ በተመሳሳይ ሁኔታ ካየ በኃላ‹‹ አይገርምም ይሄ አሞራ ቅድምም ስንመጣ ከፊት ለፊታችን ሲበር ነበር….እርግጠኛ ነኝ የተለየ ከለር ስላለው አስተውዬው ነበር››አለ
‹‹አሞራ አይደለም..ንስር ነው››አረመችው
‹‹እንዴ.. አዎ ንስር ነው ትክክል ..አንቺ ግን እንዴት አወቅሽ….?››
‹‹የእኔ ነው››በልበ ሙሉነት መለሰችለት፡፡
‹‹የእኔ ነው ስትይ….?››ያዝ ያዝ በሚያደርገው የስካር አንደበት ጠየቃት
‹‹ወንድሜ ነው››
ሁለቱም ተንከትክተው ሳቁ
‹‹..ቀልደኛ ነሽ..ይበልጥ ስትጠጪ ደግሞ ይብልጥ ቀልደኛ የመሆን ተስፋ አለሽ ማለት ነው››አላት፡፡
….አስረድቶ ማሰማንም ሆነ ተከራክሮ ማሸንፈ እንደማትችል ስለተረዳች‹‹ይሁንልህ›› አለችው ፡፡
መገናኛ አካባቢ ደርሱ… ብዙም ትርምስ የሌለበት እሷ የማታውቀው ሁለቱ ግን የሚያውቁት ሆቴል ይዘዋት ገቡ..ሹፌሩ ከላዳዋ አልወረደም…‹‹ጫቴን ብቅም ይሻለኝል›› ብሎ ቀረ …እነሱ ተያይዘው ገቡና የተገነጠለ እና ከታዳሚ የራቀ ወንበር ይዘው ተቀመጡ፡፡
👍86❤11😁2👎1🤔1😱1😢1
# ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
እንግዶቹ ሳሎን ውስጥ እንደከተሙ ቢራ የሚጠጣው ቢራ የተቀረው ለስላሳ እየተጎነጩ እየተጫወቱ ነው፡፡
‹‹ታዲ ለዛ ጉዳይ ነው የመጣሀው?››
‹‹አዎ.. ስትጨቀጭቁኝ ጊዜ ደጋግሜ አሰብኩበት...የእኔ እና የልጆቼ ታሪክ በሌላው ዜጋ ላይ መነሳሳት ፈጥሮ ብዙ ወላጅ አልባና ችግረኛ ህፃናቶችን አጋዥ ሚያስገኝላቸው ከሆነ ለኢ.ቢ.ኤስ ቶክሾው የቴሌቨዠን ፕሮግራም
እኔም ሆንኩ ልጆቼ ቃለ መጠየቁን ብናደርግ አይከፋም ብዬ ነው፡፡በዛ ላይ ያው እነ ሄለንም በሙዚቃው .....እነ ሰላምም በስዕሉ በሞራል እየሰሩ ለመዝለቅ ከህዝብ ጋር በይበልጥ
መተዋወቅ የስራቸውን ውጤት ለህዝብ ማቅረብ ስላለባቸው ለዛ ደግሞ ሚዲያው ወሳኝ መሆኑን
አምኜበት ነው..ስለዛ ነው ሀሳቤን ቀይሬ የተስማማሁት፡፡››
‹‹በእውነት ጥሩ ወስነሀል..ይህ ነገር መስፋፋት አለበት... ባይገርምህ እኔም ፕሮፖዛሌን ጨርሼ እንቅስቃሴም ጀምሬያለሁ፡፡››አለችው ዶ/ር ሶፊያ፡
‹‹ምንድነው እኛም እንሳተፍበት ይሆናል... ገለጽለፅ አድርጉልን እንጂ?››አለ ሰሎሞን፡፡
‹‹እሺ ፕሮፖዛሌ በድህነት ምክንያት የሚባክኑ ሕፃናትን ከኢትዬጵያ ማጥፋት ነው.. ሀሳቡን የወሰድኩት ሙሉ በሙሉ ከታዲዬስ ነው፡፡እሱ ብቻውን አምስት ልጆችን እያሳደገ ..ማሳደግ ሲባል ደግሞ ማንም ኢትዬጵያዊ ልጁን ከሚያሳድገው እጅግ በሚበልጥ እና ለማንም ምሳሌ በሆነ መልኩ ነው፡፡ ሄለን ሀይለኛ ፒያኒስት ነች፣ሀሊማ ጊታሩን ታናገረዋለች..በዛ ላይ ድምጸ መረዋ ነች፣ሚጡ ከአሁኑ አሪፍ ገጣሚ ነች፣ሰላም የሚያማልል ስዕሎች ትስላለች፣ሙሴ የእሱን አትጠይቁኝ..የዬፎ አይነት ጭንቅላት ያለው ድንቅ የልጅ ሳይንቲስት ነው፤ እስቲ ተመልከቱ ከእነዚህ ልጆች መካከል አንድም የባከነ ይታያችኋል....?
ማንም ሰው የተትረፈረፈ ሀብት ኖሮት አምስት ልጆች ቢወልድ ቢያንስ ሁለቱ ወይም ሶስቱ ዝም
ብለው እየቦዘኑ መኖራቸው የሚጠበቅ ነው…
ታዲዬስ ጋር ግን ይሄ አይሰራም …እኔ እንደተረዳሁት ልዩ ፍጡሮችን መሰብሰብ ስለቻለ ሳይሆን ..ማንም ሰው ሲፈጠር አብሮት ወደ እዚህ ምድር ይዞት የመጣው ልዩ ስጦታ
ወይም ከሌላው በተሻለ የሚችለው ነገር አለው
ብሎ ያምናል፡፡ ..የታዲዬስ ልዩ ብቃት ደግሞ
አንድ ህጻን ሲድህ ጀምሮ እየተከታተለ የህይወት
መስመሩን ብዙም ሳይለፍ እንዲያገኝ ማድረግና
ማገዝ መቻሉ ነው፡፡ታዲዬስ እኮ ለልጆቹ ምግብና መጠለያ መስጠቱ ብቻ በጣም
ሚያስወድሰው ሰናይ ተግባር ነው... እሱ ግን ከከርሳቸው መሙላት በላይ ለአዕምሮቸው
መጎልበት ነው አብዝቶ የሚጨነቀው፡፡››..
የውብዳር ለዚህ ወሬም ሆነ ስለታዲዬስ ታሪክ አዲስ ስለሆነች ግራ ተጋባች፤ ታዲዬስና ልጆቹን ካየች ጀምሮ ጥያቄ በውስጧ ተቀብሮ ነበር፡፡፡
ዳ/ር ንግግሯን አራዘመች << እንግዲህ የእኔ ፕሮፕዛል ቀንጨብ አድርጌ ለማብራራ...›› ስትል
ከወደ ጓዲያ ጠንከር ያለ ድምጽ ሲሰማ ንግግሯን አቆመች፡
‹‹ምንድነው ሰዎቹ እራት ጋብዘውን ማእድ ቤት ተከተው ቀሩኮ..ዶ/ር ይቅርታ የፕሮፖዛልሽን ሀሳቡ በጣም መስማት ስለምፈልግ እስክመጣ አቆይልኝ አይቻቸው ልምጣ፡፡›› ብሎ ከመቀመጫው ተነሳና ወደ ማዕድ ቤት ሊያመራ መንገድ ሲጀምር ዶ/ር ሶፊያ‹‹ይቅርታ አቶ ሰሎሞን እኔ ብሄድ ይሻላል›› ብል ተነሳች ፡፡
ታዲዬስ ግራ ገባው‹‹...እሱ ቢሄድ አይሻልም፡፡››
‹‹ግድ የለም ካልደፈረሰ አይጠራም ብሎኝ ነው ሁሴን ይዞኝ የመጣው..ልሂድና በደንብ ይደፍርስ… ከጠራ እመጣለሁ››
‹‹አይ.... አሁንም ተፈነካክታችሁ እራታችንን ሳንበላ በለሊት ሆስፒታል ለሆስፒታል እንዳታንከራተቱን፡፡››
‹‹ከሆነም መቻል ነው››በማለት አሻፈረኝ ብላ እነ ትንግርት ወደሚገኙበት በመሄድ ዘው ብላ ስትገባ ፎዚያ ፈዛ ቆማ ትንግርትን ስትለምናት ነበር የደረሰችው.... ሁሴን ደግሞ ጉልበቷ ላይ ተደፍቶ ‹‹የእኔ ፍቅር እኔ እኮ ምክንያቷን ሰምቼ ስላሳመነችኝ... እኔን ያሳመነኝ ምክንያት ደግሞ አንቺንም ያሳምንሻል ብዬ በእርግጠኝነት ስላመንኩ ነው፤ ተማምኜብሽ ነው ይዤያት የመጣሁት ..የዛሬን››
‹‹ደህና አመሸሽ ትንግርት››...ስድስት ያፈጠጡ ዓይኖች ግንባሯ ላይ ሲተከልባት ሚጥሚጣ በዓይኑ ገብቶ እንደለበለበው ሰው የራሷን ዓይን አርገበገበች ‹‹ይቅርታ ለድፍረቴ... ሁሴን እና ፎዚያ እኛ እንነጋገር አንዴ ወደ ሳሎን ትሄዱልን፡፡››
‹‹ችግር የለም ዶ/ር አንቺ ሳሎን ሁኚ ...>>
<<ኖ ሁሴን እመነኝ እንደፈለገች ታድርገኝ...5 ደቂቃ ላናግራት እና ፤ካልሆነ እኔ ወደቤቴ ሄዳለሁ በእኔ ምክንያት ይሄን የመሰለ ዝግጅት መበላሸት የለበትም፡፡››
‹‹ይሻላል ፍቅር? ››አላት ወደ ትንግርት እያየ በመለማመጥ፡፡
ትንግርትም በግንባሯ ንቅንቅታ እንደሚሻል አረጋገጠችለት..ሁሴንና ፎዚ ግራ በገባው ሁኔታ ማዕድ ቤቱን ለቀው ወጡላቸው፡፡እንደወጡ ዶክተር ሶፊያ ከውስጥ ቀረቀረችው…ሁሴን ዶ/ ር ሶፊን በመጋበዙ የጥፋተኝነት ስሜት እየተሰማው ለሚፈጠረው ችግር ሁሉ ኃላፊነቱን የራሱ እንደሆነ እያሰብ ሳሎን ሄዶ ከእንግዶቹ ጋር ተቀላቀለ ፡፡ ፎዚያ በጭንቀት ኮርደሩ ላይ ወዲህና ወዲያ ትንጎራደድ ጀመር፡፡
‹‹እንዴ ጥለሀቸው መጣህ እንዴ?››ሰሎሞን ነው የጠየቀው፡፡
‹‹አዎ ምርጫ የለኝም ፡፡>>
‹‹አጠገባቸው ፎዚያ አለች አይደል?››
‹‹ኧረ እሷንም አስወጥተው እራሳቸው ላይ ቆልፈዋል፡፡››
ሰሎሞን ብድግ አለ ..መልሶ ቁጭ አለ‹‹አብደሀል እንዴ..?ወይኔ የውብ መክሰስ በልተን እንሂድ ስልሽ እንቢ ብለሽ አሩጠሸ አምጥተሸኝ...በቃ አሁን እኮ ቀጥታ አንድ በደም የተሸፈነ ሰው ይዘን ሆስፒታል መሄዳችን አይቀሬ ነው፡፡››
‹‹ቆይ አልገባኝም... ይሄን ያህል አንዷ ያንዷን አባት ገድላለች እንዴ….?ግራ አጋባሀኝ እኮ!!›› አለችው የውብዳር ፡፡
‹‹ኧረ ከዛም በላይ ናቸው ..ቅድም ዶ/ር ግንባር ላይ ጠባሳ አላየሽም፤ባለፈው ትንግርት በቢራ ጠርሙስ በርግዳት ነው አኮ፡፡ አሁን ደግሞ... ለመሆኑ ማዕድ ቤት ውስጥ ቢላዋ ፊት ለፊት አለ?»
‹‹አይ ብዙም የለ... አንድ አራት ወይም አምስት ብቻ ቢሆን ነው››አለው ሁሴን ጥያቄው አበሳጭቶት፡፡
በዚህ ጊዜ ከታዲዬስ ጎን የተቀመጠው ሙሴ ከመቀመጫው ተነሳና ወደውጭ ሲሄድ ታዲዬስ ተከተለው ፡፡
‹‹ወዴት ነው?››ኤልያስ ነው ጠያቂው፡፡
‹‹ሙሴ ትንሽ በግርግሩ ሳይጨናነቅ አይቀርም አብሬው ውጭ ነኝ... ለማንኛውም አትጨነቁ ከዛ ክፍል በሰላም ተግባብተው ነው የሚወጡት፡፡ >>
‹‹እንደአፍህ ያድርግልን >>አሉት ሁሉም በአንድነት፡፡
ከአስጨናቂ የ15 ደቂቃ ቆይታ በኃላ የማዕድ ቤቱ በራፍ ተከፈተ ...ቀድማ የወጣችው ዶ/ር ሶፊያ ነች ..በተፍለቀለቀ ፊት በሚያበራ ፈገግታ ወደ ሳሎን ገባች፡፡
ፊቷና ሁኔታዎ ግን ለየቅል ነበር... ከላይ
የለበሰችው ሽሮ መልክ ቲሸርት የሰላምን ጅምር የስዕል መሳያ ሸራ መስሏል ፡፡በርግጠኝነት
አንድ ሙሉ ጎድጓዳ ሰሀን ቀይ ወጥ ነው እላይዋ ላይ የተደፋው ፡፡ሁሴን ተንደርድሮ
ከመቀመጫው በመነሳት ስሯ ደረሰና‹‹ ምን ሆንሽ ...?ምን ተፈጠረ? ››እያለ በድንጋጤ ዙሪያወን ሲሽከረከር ትንግርት ከኃላው ደረሰችና‹‹ደህና ነች ባክህ›› ብላ የሶፊያን እጆች
ይዛ ወደ መኝታ ቤት ይዛት ገባች...... እሱም እንደፈዘዘ መሀል ሳሎን ላይ ተገትሮ ቀረ ፡፡
‹‹አቦ ይሄ ድራማ መች ነው የሚያልቀው ..?አኔ እኮ በርሀብ ልሞት ነው››ሰሎሞን ተነጫነጨ፡፡
‹‹ኧረ ዛሬ እንኳን ስለከርስህ ማሰብ አቁም፡፡››አለው ሁሴን በብስጭት፡፡
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
እንግዶቹ ሳሎን ውስጥ እንደከተሙ ቢራ የሚጠጣው ቢራ የተቀረው ለስላሳ እየተጎነጩ እየተጫወቱ ነው፡፡
‹‹ታዲ ለዛ ጉዳይ ነው የመጣሀው?››
‹‹አዎ.. ስትጨቀጭቁኝ ጊዜ ደጋግሜ አሰብኩበት...የእኔ እና የልጆቼ ታሪክ በሌላው ዜጋ ላይ መነሳሳት ፈጥሮ ብዙ ወላጅ አልባና ችግረኛ ህፃናቶችን አጋዥ ሚያስገኝላቸው ከሆነ ለኢ.ቢ.ኤስ ቶክሾው የቴሌቨዠን ፕሮግራም
እኔም ሆንኩ ልጆቼ ቃለ መጠየቁን ብናደርግ አይከፋም ብዬ ነው፡፡በዛ ላይ ያው እነ ሄለንም በሙዚቃው .....እነ ሰላምም በስዕሉ በሞራል እየሰሩ ለመዝለቅ ከህዝብ ጋር በይበልጥ
መተዋወቅ የስራቸውን ውጤት ለህዝብ ማቅረብ ስላለባቸው ለዛ ደግሞ ሚዲያው ወሳኝ መሆኑን
አምኜበት ነው..ስለዛ ነው ሀሳቤን ቀይሬ የተስማማሁት፡፡››
‹‹በእውነት ጥሩ ወስነሀል..ይህ ነገር መስፋፋት አለበት... ባይገርምህ እኔም ፕሮፖዛሌን ጨርሼ እንቅስቃሴም ጀምሬያለሁ፡፡››አለችው ዶ/ር ሶፊያ፡
‹‹ምንድነው እኛም እንሳተፍበት ይሆናል... ገለጽለፅ አድርጉልን እንጂ?››አለ ሰሎሞን፡፡
‹‹እሺ ፕሮፖዛሌ በድህነት ምክንያት የሚባክኑ ሕፃናትን ከኢትዬጵያ ማጥፋት ነው.. ሀሳቡን የወሰድኩት ሙሉ በሙሉ ከታዲዬስ ነው፡፡እሱ ብቻውን አምስት ልጆችን እያሳደገ ..ማሳደግ ሲባል ደግሞ ማንም ኢትዬጵያዊ ልጁን ከሚያሳድገው እጅግ በሚበልጥ እና ለማንም ምሳሌ በሆነ መልኩ ነው፡፡ ሄለን ሀይለኛ ፒያኒስት ነች፣ሀሊማ ጊታሩን ታናገረዋለች..በዛ ላይ ድምጸ መረዋ ነች፣ሚጡ ከአሁኑ አሪፍ ገጣሚ ነች፣ሰላም የሚያማልል ስዕሎች ትስላለች፣ሙሴ የእሱን አትጠይቁኝ..የዬፎ አይነት ጭንቅላት ያለው ድንቅ የልጅ ሳይንቲስት ነው፤ እስቲ ተመልከቱ ከእነዚህ ልጆች መካከል አንድም የባከነ ይታያችኋል....?
ማንም ሰው የተትረፈረፈ ሀብት ኖሮት አምስት ልጆች ቢወልድ ቢያንስ ሁለቱ ወይም ሶስቱ ዝም
ብለው እየቦዘኑ መኖራቸው የሚጠበቅ ነው…
ታዲዬስ ጋር ግን ይሄ አይሰራም …እኔ እንደተረዳሁት ልዩ ፍጡሮችን መሰብሰብ ስለቻለ ሳይሆን ..ማንም ሰው ሲፈጠር አብሮት ወደ እዚህ ምድር ይዞት የመጣው ልዩ ስጦታ
ወይም ከሌላው በተሻለ የሚችለው ነገር አለው
ብሎ ያምናል፡፡ ..የታዲዬስ ልዩ ብቃት ደግሞ
አንድ ህጻን ሲድህ ጀምሮ እየተከታተለ የህይወት
መስመሩን ብዙም ሳይለፍ እንዲያገኝ ማድረግና
ማገዝ መቻሉ ነው፡፡ታዲዬስ እኮ ለልጆቹ ምግብና መጠለያ መስጠቱ ብቻ በጣም
ሚያስወድሰው ሰናይ ተግባር ነው... እሱ ግን ከከርሳቸው መሙላት በላይ ለአዕምሮቸው
መጎልበት ነው አብዝቶ የሚጨነቀው፡፡››..
የውብዳር ለዚህ ወሬም ሆነ ስለታዲዬስ ታሪክ አዲስ ስለሆነች ግራ ተጋባች፤ ታዲዬስና ልጆቹን ካየች ጀምሮ ጥያቄ በውስጧ ተቀብሮ ነበር፡፡፡
ዳ/ር ንግግሯን አራዘመች << እንግዲህ የእኔ ፕሮፕዛል ቀንጨብ አድርጌ ለማብራራ...›› ስትል
ከወደ ጓዲያ ጠንከር ያለ ድምጽ ሲሰማ ንግግሯን አቆመች፡
‹‹ምንድነው ሰዎቹ እራት ጋብዘውን ማእድ ቤት ተከተው ቀሩኮ..ዶ/ር ይቅርታ የፕሮፖዛልሽን ሀሳቡ በጣም መስማት ስለምፈልግ እስክመጣ አቆይልኝ አይቻቸው ልምጣ፡፡›› ብሎ ከመቀመጫው ተነሳና ወደ ማዕድ ቤት ሊያመራ መንገድ ሲጀምር ዶ/ር ሶፊያ‹‹ይቅርታ አቶ ሰሎሞን እኔ ብሄድ ይሻላል›› ብል ተነሳች ፡፡
ታዲዬስ ግራ ገባው‹‹...እሱ ቢሄድ አይሻልም፡፡››
‹‹ግድ የለም ካልደፈረሰ አይጠራም ብሎኝ ነው ሁሴን ይዞኝ የመጣው..ልሂድና በደንብ ይደፍርስ… ከጠራ እመጣለሁ››
‹‹አይ.... አሁንም ተፈነካክታችሁ እራታችንን ሳንበላ በለሊት ሆስፒታል ለሆስፒታል እንዳታንከራተቱን፡፡››
‹‹ከሆነም መቻል ነው››በማለት አሻፈረኝ ብላ እነ ትንግርት ወደሚገኙበት በመሄድ ዘው ብላ ስትገባ ፎዚያ ፈዛ ቆማ ትንግርትን ስትለምናት ነበር የደረሰችው.... ሁሴን ደግሞ ጉልበቷ ላይ ተደፍቶ ‹‹የእኔ ፍቅር እኔ እኮ ምክንያቷን ሰምቼ ስላሳመነችኝ... እኔን ያሳመነኝ ምክንያት ደግሞ አንቺንም ያሳምንሻል ብዬ በእርግጠኝነት ስላመንኩ ነው፤ ተማምኜብሽ ነው ይዤያት የመጣሁት ..የዛሬን››
‹‹ደህና አመሸሽ ትንግርት››...ስድስት ያፈጠጡ ዓይኖች ግንባሯ ላይ ሲተከልባት ሚጥሚጣ በዓይኑ ገብቶ እንደለበለበው ሰው የራሷን ዓይን አርገበገበች ‹‹ይቅርታ ለድፍረቴ... ሁሴን እና ፎዚያ እኛ እንነጋገር አንዴ ወደ ሳሎን ትሄዱልን፡፡››
‹‹ችግር የለም ዶ/ር አንቺ ሳሎን ሁኚ ...>>
<<ኖ ሁሴን እመነኝ እንደፈለገች ታድርገኝ...5 ደቂቃ ላናግራት እና ፤ካልሆነ እኔ ወደቤቴ ሄዳለሁ በእኔ ምክንያት ይሄን የመሰለ ዝግጅት መበላሸት የለበትም፡፡››
‹‹ይሻላል ፍቅር? ››አላት ወደ ትንግርት እያየ በመለማመጥ፡፡
ትንግርትም በግንባሯ ንቅንቅታ እንደሚሻል አረጋገጠችለት..ሁሴንና ፎዚ ግራ በገባው ሁኔታ ማዕድ ቤቱን ለቀው ወጡላቸው፡፡እንደወጡ ዶክተር ሶፊያ ከውስጥ ቀረቀረችው…ሁሴን ዶ/ ር ሶፊን በመጋበዙ የጥፋተኝነት ስሜት እየተሰማው ለሚፈጠረው ችግር ሁሉ ኃላፊነቱን የራሱ እንደሆነ እያሰብ ሳሎን ሄዶ ከእንግዶቹ ጋር ተቀላቀለ ፡፡ ፎዚያ በጭንቀት ኮርደሩ ላይ ወዲህና ወዲያ ትንጎራደድ ጀመር፡፡
‹‹እንዴ ጥለሀቸው መጣህ እንዴ?››ሰሎሞን ነው የጠየቀው፡፡
‹‹አዎ ምርጫ የለኝም ፡፡>>
‹‹አጠገባቸው ፎዚያ አለች አይደል?››
‹‹ኧረ እሷንም አስወጥተው እራሳቸው ላይ ቆልፈዋል፡፡››
ሰሎሞን ብድግ አለ ..መልሶ ቁጭ አለ‹‹አብደሀል እንዴ..?ወይኔ የውብ መክሰስ በልተን እንሂድ ስልሽ እንቢ ብለሽ አሩጠሸ አምጥተሸኝ...በቃ አሁን እኮ ቀጥታ አንድ በደም የተሸፈነ ሰው ይዘን ሆስፒታል መሄዳችን አይቀሬ ነው፡፡››
‹‹ቆይ አልገባኝም... ይሄን ያህል አንዷ ያንዷን አባት ገድላለች እንዴ….?ግራ አጋባሀኝ እኮ!!›› አለችው የውብዳር ፡፡
‹‹ኧረ ከዛም በላይ ናቸው ..ቅድም ዶ/ር ግንባር ላይ ጠባሳ አላየሽም፤ባለፈው ትንግርት በቢራ ጠርሙስ በርግዳት ነው አኮ፡፡ አሁን ደግሞ... ለመሆኑ ማዕድ ቤት ውስጥ ቢላዋ ፊት ለፊት አለ?»
‹‹አይ ብዙም የለ... አንድ አራት ወይም አምስት ብቻ ቢሆን ነው››አለው ሁሴን ጥያቄው አበሳጭቶት፡፡
በዚህ ጊዜ ከታዲዬስ ጎን የተቀመጠው ሙሴ ከመቀመጫው ተነሳና ወደውጭ ሲሄድ ታዲዬስ ተከተለው ፡፡
‹‹ወዴት ነው?››ኤልያስ ነው ጠያቂው፡፡
‹‹ሙሴ ትንሽ በግርግሩ ሳይጨናነቅ አይቀርም አብሬው ውጭ ነኝ... ለማንኛውም አትጨነቁ ከዛ ክፍል በሰላም ተግባብተው ነው የሚወጡት፡፡ >>
‹‹እንደአፍህ ያድርግልን >>አሉት ሁሉም በአንድነት፡፡
ከአስጨናቂ የ15 ደቂቃ ቆይታ በኃላ የማዕድ ቤቱ በራፍ ተከፈተ ...ቀድማ የወጣችው ዶ/ር ሶፊያ ነች ..በተፍለቀለቀ ፊት በሚያበራ ፈገግታ ወደ ሳሎን ገባች፡፡
ፊቷና ሁኔታዎ ግን ለየቅል ነበር... ከላይ
የለበሰችው ሽሮ መልክ ቲሸርት የሰላምን ጅምር የስዕል መሳያ ሸራ መስሏል ፡፡በርግጠኝነት
አንድ ሙሉ ጎድጓዳ ሰሀን ቀይ ወጥ ነው እላይዋ ላይ የተደፋው ፡፡ሁሴን ተንደርድሮ
ከመቀመጫው በመነሳት ስሯ ደረሰና‹‹ ምን ሆንሽ ...?ምን ተፈጠረ? ››እያለ በድንጋጤ ዙሪያወን ሲሽከረከር ትንግርት ከኃላው ደረሰችና‹‹ደህና ነች ባክህ›› ብላ የሶፊያን እጆች
ይዛ ወደ መኝታ ቤት ይዛት ገባች...... እሱም እንደፈዘዘ መሀል ሳሎን ላይ ተገትሮ ቀረ ፡፡
‹‹አቦ ይሄ ድራማ መች ነው የሚያልቀው ..?አኔ እኮ በርሀብ ልሞት ነው››ሰሎሞን ተነጫነጨ፡፡
‹‹ኧረ ዛሬ እንኳን ስለከርስህ ማሰብ አቁም፡፡››አለው ሁሴን በብስጭት፡፡
👍81❤5🥰1👏1😁1