#ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
.....“እህ • ውጤት እንዴት ነው ?” አለ ገና ሲያያት "
“ ኮንግራጁሌሽን ! አልፌአለሁ” አለችው በተቀመጠበት ልታቅፈው እየተንደረደረች
“ ወዳጅ ዘመድ ይኑር በይ ” አላት እርዳታውን ለመጠቀምም ።
“ ይኑር ! ” ብላ አንገቱ ላይ ተጠመጠመችና ጉንጬን ሳመችው
"ምን ምን ደኅና አገኘሽ ? ” ሲል ጠየቃት
“ ሒሳብ “ 203 ” ጎጆ ሠርቻለሁ
በዩኒቨርስቲ ውስጥ “F ያገኙበትን ትምህርት ባንዲራ ሰቅያለሁ” ሲባል “ A ? ያገኙበትን ትምህርት ደግሞ ፡ “ ጎጆ ሠርቻለሁ” ማለት የተለመደ ቋንቋ ሆኖአል
“ እሱማ የኔው ነው ” አላት እንደገና ባለውለታነቱን ለመጠቆም
“ እኮ ! ” አለችው እየቦረቀች ።
ታዲያ ጎጆውን የሰራው ማነው ? እኔ ነኝ ወይስ አንቺ ? ”
“ አንተ!” ብላው እንደገና ልትስመው ከንፈሯን ስታስጠጋው በሩ በድንገት ብርግድ አለ ። ሁለቱም እንደ ተቃቀፉ
ክው ብለው ቀሩ የገባው ሳምሶን ጉልቤው ነበር ። አውሬ መስሎ
ታያቸው
ሁኔታቸው የፊልም ትርኢት መሰለ ። እነሱ ዱብ ዕዳ እንደ ወረደባቸው ፍቅረኞቹ በጭንቀት ተቃቅፈው ሳምሶን ቆሞ በፍቅረኞቹ ላይ ሽጉጡን የደገነ ፥ " ቴክስ” ይመስል ነበር።
“ ምን ፈለግክ ? ” አለው ለማ ድንጋጤው ከበረደለት በኋላ በትዕቢት ድምፅ ። ሳምሶን ለእሱ አልመለሰለትም ።
“ አንቺ ሸርሙጣ!” አላት ቤተልሔም ላይ አፍጥጦ። እናንተ አስተማሪ እያወረዳችሁ ትኖራላችሁ ፤ እኛ ግን እንባረራለን ! ”
“ ወይኔ ! ” ብላ ቤተልሔም ለማ ሥር ሽጉጥ አለች። ሊውጣት የመጣ ነው የመሰላት ። ዐይኖቹ ውስጥ የሚንቀ
ለቀለው የንዴት እሳት አስፈራት። ሽንቷ አምልጧት ጭርር ሲል ተሰማትና ጭንና ጭኗን አጋጠመች ።
ለማና ሳምሶን ተፋጠጡ ። የአንበሳና የነብር ፍጥጫ መሰለ ። በጉልበቱ የሚተማመነው ሳምሶን ለማ ፊት እንደ
ቆመ ጡንቻውን ለመሰንዘር ምን እንዳገደው ለማሰብ ሞከረ፡ ሕግ ! የሰዎችን የስሜት ፈረስ ለጉሞ ሲይዝ ታየው ።
“ እንዴዬ ! አሁን ምንድነው የፈለግከው ? ” አለው "ከተቀመጠበት ለመነሣት እያሰላ
“ ምን አገባህ ! ” ብሎ ሳምሶን ሌላ መናገር ፈርቶ እንዳፈጠጠ'ያላየው ሰው ከኋላ መጥቶ በድንገት ትከሻውን
ጨመደደው ።
“ምን ማድረግህ ነው ሳምሶን ? ” አለው እስክንድር ትከሻውን እንደ ጨመደደ ከቢሮው ሊያስወጣው እየታገለ ።
ከእሱና ከአቤል ተለይቶአቸው መምጣቱ ከንክኖት ነበር እስክንድር እየሮጠ የደረሰበት ።
“ ልቀቀኝ ! ” አለው ሳምሶን መጋበዙ እልሁን አግሎበት ።
እስክንድር በግድ እየጎተት ከቢሮው ካወጣው በኋላ
“ ዕረፍ ሳምሶን ” አለው ፡ “ ነገሮችን ለማመዛዘን ሞክር ።ለማ ቤተልሔምን ይጠቅማት ይሆናል እንጂ አንተን አይ
ጎዳህም ። ምክንያቱም ቀድሞ የምትዋደዱበት ወይም የምትጣሉበት ምንም ግንኙነት አልነበራችሁም
“ እንጃልህ ! ” አለና እሱም ላይ አፈጠጠበት ። “ ወቼ ጉድ ! ዛሬስ ለእኔም አይመለስ ” አለና ቀስ ብሎ እያባበለሀው ይዞት ሔደ ።
እስክንድርና አቤል ፥ ሳምሶንን እያባበሉ ወደ መኝታ ክፍሉ ከወሰዱት በኋላ ስለ ራሳቸው ለማሰብ ተገደዱ። የሌላውን የፈተና ውጤት የሰማው ጆሮአቸው የራሳቸውን ለመስማት ተጣደፈ ። መውደቅና ማለፍ ሁለቱ ተቃራኒ ነገሮች
እስካሉ ድረስ ፥ መከሠታቸው የግድ ቢሆንም ፡ የማንም አእምሮ በቀላሉ አይቀበላቸውም ። ከሰዓት በኋላው ለእነአቤል በጣም ራቀባቸው ። በተለይ አቤል የትዕግሥትን ማለፍ ከሰማ በኋላ የራሱን ውጤት ለማወቅ ለምን እንደሚጓጓ ሊገባው አልቻለም ። ምናልባት ተአምር ይወርድ ይሆን ?
ሁለቱም፥ ውጤት ከሰማው ተማሪ ጋር መቀላቀል አልፈለጉም ። ግን ጆሮአቸውን በጥጥ አይደፍነት ነገር! ባለፉ ባገደሙበት ቦታ ተማሪው በቡድን ቆሞ አንዱን ሲያነሣ አንዱን ሲጥል መስማት እሰለቻቸው ። አንዱ በአንዱ ሲቀና ወይም ደግሞ መምህሩን ሲወነጅል ነው የሚሰማው ።
በዚህ ዓለም ላይ ማን ይሆን ለኅሊናው ሐቀኛ የሆነ ፍጡር ! ሁሌም የራሱን ማንነት ደብቆ ሌላውን ሲወነጅል
ነው የሚገኘው ሁሉም ። ተማሪው አስተማሪውን በማርክ አሰጣጥ ይወነጅላል።ሠራተኛ አለቃውን ይወነጅላል።አለቃም ድክመቱን በበታች ሠራተኛ ላይ ይለጥፋል ። ለዚህ ምንጩ
ምን ይሆን ? የአስተዳደጋችንና የአኗኗራችን ኋላቀርነት የፈጠረብን ችግር ይሆን እንዴ ? ምናለበት አንዱ ሌላውን ከመወንጀሉ በፊት ፡ « ለመሆኑ እኔ ማን ነኝ ? ” ብሎ ራሱን መጠየቅ ቢችል ? አንዱ ከሌላዉ ጋር የሚኖረው የግንኙነት መሠረት ሥራና የሀገር ፅድት ሆኖ ሳለ ፥ እርስ በርስ መቦጫጨቅ ቢቀር ምናለበት ? ማንም ከምድር በላይ ወይም
ከምድር በታች ላይኖር ለመበላለጥ በምናደርገው ቅናት የበዛበት ፉክቻና ግላዊ ርኩቻ የጋራችን የሆነችውን ምድር
ባንጎዳት ምናለበት ? እስክንድር በሸቀ ።
ከቀትር በኋላ፥ከነእስክንድርና ከአቤል ቀድሞ ውጤቱን የተመለከተው "ድብርት ” ነበር ።
“ ውጤት ወጥቷል ” አላቸው ፡ የራሱን አይቶ ወደ መኝታ ክፍሉ ከተመለሰ በኋላ ደስታ አፍኖት ሲያልጎመጉም ጥርሱን አሳይቶ አልሣቀም ።
"ያንተ እንዴት ነው ? ” አሉት ።
"ግሩም ነው !
“ ስንት ጎጆ ሠራህ ? ” አለው እስክንድር
ሦስቱን ጣቶቹን አሳያቸው ።
“ የጉልበት ዋጋ ነው !” አለ እስክንድር በልቡ የድብርት ” አጠናን ምንጊዜም የጉልበት ሥራ ያህል በመታገልና
ብዙ ሰዓት በማጥናት ስለሆነ፡በጉልበቱ ዩኒቨርስቲ መቆየቱን ሁሉም ያውቅለታል "
ወዲያው እስክንድርና አቤል ተያይዘው ወደ ሰሌዳው ሔዱ። የሦስተኛና የአራተኛ ዓመት ተማሪዎች ቁጥር ያን ያህል ብዛት ስለ ሌለው በቀላሉ ወደ ሰሌዳው ተጠግተው ተመለከቱ ። እስክንድር በጥሩ ውጤት ዐልፏል ። የአቤል
ውጤት ግን አልወጣም ። አቤል ራሱን ማመን አቅቶት የመታወቂያ ወረቀቱን
ከኪሱ አውጥቶ የመለያ ቁጥሩን ተመለከተ ። ያ ቁጥር ሰሌዳው ላይ የለም ማለፍም ሆነ መውደቅ የግድ ሰሌዳ ላይ
መውጣት አለበት ። እና የአቤል ከዚህ ከሁለቱ ውጭ ምን ሊሆን ይችላል ?
የእስክንድር ማለፍ ሲያስደስታቸው፡ በሌላ በኩል ደግሞ የአቤል ጉዳይ ሁለቱንም ግራ አጋባቸው ። እስክንድር
ልቡ ፈራ ። ስሜቱ መጥፎ ነገር ጠረጠረ ። ለማንኛውም ተያይዘው ውጤቱ ወደ ተዘጋጀበት ቢሮ ሒዱ ።
“ አቤት ! ምን ነበር ? " አለቻቸው ጸሐፊዋ ፡ የምታንቀጭቅጨውን ታይፕ አቋርጣ ። “ የእሱ ውጤት አልወጣም ። እና ... ብሎ እስክንድር ወደ አቤል እያመለከተ
ንግግሩን ሳይጨርስ አቋረጠችው ።
« ስሙ ማን ነው ? ”
“ አቤል ። የፍልስፍና ትምህርት ክፍል
“አሃ ! አቤል ሙሉዬ ፡ ያንተ ውጤት አልደረሰንም እስኪ ዮናታንን ሒደህ አነጋግራቸው አለችና ሥራዎን
ቀጠለች ።
“ውጤቱ ዮናታን ጋር ምን ያደርጋል?” አለ አቤል በልቡ።ዮናታንን ማየት አልፈለገም ነበር ። በዝጉ ውስጥ ሲሸሻቸው ነው የከረመው። ምክራቸውን አለመስማቱና ሕክምናውን ያለ መቀጠሉ እያሳፈሩት ከእሳቸው ለመራቅ ምክሮ ነበር።
የግዱን ከእስክንድር ጋር ሆኖ ወደ ዮናታን ቢሮ ሔደ።ዮናታን የሉም ። ቢሮኣቸው ተቆልፎአል ።
“ ምን ይሻላል ? ” አለ የእስክንድርን ዐይን ዐይን እያየ
“ ምን ይሻላል ? ” ብሎ እስክንድርም ቃሉን በትካዜ ድምፅ ከደገመ በኋላ ፥ “ እንግዲህ ነገ መጥተን እንጠይቃቸዋለን " መቼም ከአሁን በኋላ አይገቡም ” አለው እያስተዛዘነ።
ነገ እንዴት ይነጋ ይሆን ? የጭንቅ ምሽት ፤የመከራ ሕልም ሌሊት ።
በማግሥቱ ጠዋት አቤልና እስክንድር ዮናታንን ቀድመው ነበር፡ ከቢሮአቸው የደረሱት ።አቤል ዐይናቸውን ማየት
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
.....“እህ • ውጤት እንዴት ነው ?” አለ ገና ሲያያት "
“ ኮንግራጁሌሽን ! አልፌአለሁ” አለችው በተቀመጠበት ልታቅፈው እየተንደረደረች
“ ወዳጅ ዘመድ ይኑር በይ ” አላት እርዳታውን ለመጠቀምም ።
“ ይኑር ! ” ብላ አንገቱ ላይ ተጠመጠመችና ጉንጬን ሳመችው
"ምን ምን ደኅና አገኘሽ ? ” ሲል ጠየቃት
“ ሒሳብ “ 203 ” ጎጆ ሠርቻለሁ
በዩኒቨርስቲ ውስጥ “F ያገኙበትን ትምህርት ባንዲራ ሰቅያለሁ” ሲባል “ A ? ያገኙበትን ትምህርት ደግሞ ፡ “ ጎጆ ሠርቻለሁ” ማለት የተለመደ ቋንቋ ሆኖአል
“ እሱማ የኔው ነው ” አላት እንደገና ባለውለታነቱን ለመጠቆም
“ እኮ ! ” አለችው እየቦረቀች ።
ታዲያ ጎጆውን የሰራው ማነው ? እኔ ነኝ ወይስ አንቺ ? ”
“ አንተ!” ብላው እንደገና ልትስመው ከንፈሯን ስታስጠጋው በሩ በድንገት ብርግድ አለ ። ሁለቱም እንደ ተቃቀፉ
ክው ብለው ቀሩ የገባው ሳምሶን ጉልቤው ነበር ። አውሬ መስሎ
ታያቸው
ሁኔታቸው የፊልም ትርኢት መሰለ ። እነሱ ዱብ ዕዳ እንደ ወረደባቸው ፍቅረኞቹ በጭንቀት ተቃቅፈው ሳምሶን ቆሞ በፍቅረኞቹ ላይ ሽጉጡን የደገነ ፥ " ቴክስ” ይመስል ነበር።
“ ምን ፈለግክ ? ” አለው ለማ ድንጋጤው ከበረደለት በኋላ በትዕቢት ድምፅ ። ሳምሶን ለእሱ አልመለሰለትም ።
“ አንቺ ሸርሙጣ!” አላት ቤተልሔም ላይ አፍጥጦ። እናንተ አስተማሪ እያወረዳችሁ ትኖራላችሁ ፤ እኛ ግን እንባረራለን ! ”
“ ወይኔ ! ” ብላ ቤተልሔም ለማ ሥር ሽጉጥ አለች። ሊውጣት የመጣ ነው የመሰላት ። ዐይኖቹ ውስጥ የሚንቀ
ለቀለው የንዴት እሳት አስፈራት። ሽንቷ አምልጧት ጭርር ሲል ተሰማትና ጭንና ጭኗን አጋጠመች ።
ለማና ሳምሶን ተፋጠጡ ። የአንበሳና የነብር ፍጥጫ መሰለ ። በጉልበቱ የሚተማመነው ሳምሶን ለማ ፊት እንደ
ቆመ ጡንቻውን ለመሰንዘር ምን እንዳገደው ለማሰብ ሞከረ፡ ሕግ ! የሰዎችን የስሜት ፈረስ ለጉሞ ሲይዝ ታየው ።
“ እንዴዬ ! አሁን ምንድነው የፈለግከው ? ” አለው "ከተቀመጠበት ለመነሣት እያሰላ
“ ምን አገባህ ! ” ብሎ ሳምሶን ሌላ መናገር ፈርቶ እንዳፈጠጠ'ያላየው ሰው ከኋላ መጥቶ በድንገት ትከሻውን
ጨመደደው ።
“ምን ማድረግህ ነው ሳምሶን ? ” አለው እስክንድር ትከሻውን እንደ ጨመደደ ከቢሮው ሊያስወጣው እየታገለ ።
ከእሱና ከአቤል ተለይቶአቸው መምጣቱ ከንክኖት ነበር እስክንድር እየሮጠ የደረሰበት ።
“ ልቀቀኝ ! ” አለው ሳምሶን መጋበዙ እልሁን አግሎበት ።
እስክንድር በግድ እየጎተት ከቢሮው ካወጣው በኋላ
“ ዕረፍ ሳምሶን ” አለው ፡ “ ነገሮችን ለማመዛዘን ሞክር ።ለማ ቤተልሔምን ይጠቅማት ይሆናል እንጂ አንተን አይ
ጎዳህም ። ምክንያቱም ቀድሞ የምትዋደዱበት ወይም የምትጣሉበት ምንም ግንኙነት አልነበራችሁም
“ እንጃልህ ! ” አለና እሱም ላይ አፈጠጠበት ። “ ወቼ ጉድ ! ዛሬስ ለእኔም አይመለስ ” አለና ቀስ ብሎ እያባበለሀው ይዞት ሔደ ።
እስክንድርና አቤል ፥ ሳምሶንን እያባበሉ ወደ መኝታ ክፍሉ ከወሰዱት በኋላ ስለ ራሳቸው ለማሰብ ተገደዱ። የሌላውን የፈተና ውጤት የሰማው ጆሮአቸው የራሳቸውን ለመስማት ተጣደፈ ። መውደቅና ማለፍ ሁለቱ ተቃራኒ ነገሮች
እስካሉ ድረስ ፥ መከሠታቸው የግድ ቢሆንም ፡ የማንም አእምሮ በቀላሉ አይቀበላቸውም ። ከሰዓት በኋላው ለእነአቤል በጣም ራቀባቸው ። በተለይ አቤል የትዕግሥትን ማለፍ ከሰማ በኋላ የራሱን ውጤት ለማወቅ ለምን እንደሚጓጓ ሊገባው አልቻለም ። ምናልባት ተአምር ይወርድ ይሆን ?
ሁለቱም፥ ውጤት ከሰማው ተማሪ ጋር መቀላቀል አልፈለጉም ። ግን ጆሮአቸውን በጥጥ አይደፍነት ነገር! ባለፉ ባገደሙበት ቦታ ተማሪው በቡድን ቆሞ አንዱን ሲያነሣ አንዱን ሲጥል መስማት እሰለቻቸው ። አንዱ በአንዱ ሲቀና ወይም ደግሞ መምህሩን ሲወነጅል ነው የሚሰማው ።
በዚህ ዓለም ላይ ማን ይሆን ለኅሊናው ሐቀኛ የሆነ ፍጡር ! ሁሌም የራሱን ማንነት ደብቆ ሌላውን ሲወነጅል
ነው የሚገኘው ሁሉም ። ተማሪው አስተማሪውን በማርክ አሰጣጥ ይወነጅላል።ሠራተኛ አለቃውን ይወነጅላል።አለቃም ድክመቱን በበታች ሠራተኛ ላይ ይለጥፋል ። ለዚህ ምንጩ
ምን ይሆን ? የአስተዳደጋችንና የአኗኗራችን ኋላቀርነት የፈጠረብን ችግር ይሆን እንዴ ? ምናለበት አንዱ ሌላውን ከመወንጀሉ በፊት ፡ « ለመሆኑ እኔ ማን ነኝ ? ” ብሎ ራሱን መጠየቅ ቢችል ? አንዱ ከሌላዉ ጋር የሚኖረው የግንኙነት መሠረት ሥራና የሀገር ፅድት ሆኖ ሳለ ፥ እርስ በርስ መቦጫጨቅ ቢቀር ምናለበት ? ማንም ከምድር በላይ ወይም
ከምድር በታች ላይኖር ለመበላለጥ በምናደርገው ቅናት የበዛበት ፉክቻና ግላዊ ርኩቻ የጋራችን የሆነችውን ምድር
ባንጎዳት ምናለበት ? እስክንድር በሸቀ ።
ከቀትር በኋላ፥ከነእስክንድርና ከአቤል ቀድሞ ውጤቱን የተመለከተው "ድብርት ” ነበር ።
“ ውጤት ወጥቷል ” አላቸው ፡ የራሱን አይቶ ወደ መኝታ ክፍሉ ከተመለሰ በኋላ ደስታ አፍኖት ሲያልጎመጉም ጥርሱን አሳይቶ አልሣቀም ።
"ያንተ እንዴት ነው ? ” አሉት ።
"ግሩም ነው !
“ ስንት ጎጆ ሠራህ ? ” አለው እስክንድር
ሦስቱን ጣቶቹን አሳያቸው ።
“ የጉልበት ዋጋ ነው !” አለ እስክንድር በልቡ የድብርት ” አጠናን ምንጊዜም የጉልበት ሥራ ያህል በመታገልና
ብዙ ሰዓት በማጥናት ስለሆነ፡በጉልበቱ ዩኒቨርስቲ መቆየቱን ሁሉም ያውቅለታል "
ወዲያው እስክንድርና አቤል ተያይዘው ወደ ሰሌዳው ሔዱ። የሦስተኛና የአራተኛ ዓመት ተማሪዎች ቁጥር ያን ያህል ብዛት ስለ ሌለው በቀላሉ ወደ ሰሌዳው ተጠግተው ተመለከቱ ። እስክንድር በጥሩ ውጤት ዐልፏል ። የአቤል
ውጤት ግን አልወጣም ። አቤል ራሱን ማመን አቅቶት የመታወቂያ ወረቀቱን
ከኪሱ አውጥቶ የመለያ ቁጥሩን ተመለከተ ። ያ ቁጥር ሰሌዳው ላይ የለም ማለፍም ሆነ መውደቅ የግድ ሰሌዳ ላይ
መውጣት አለበት ። እና የአቤል ከዚህ ከሁለቱ ውጭ ምን ሊሆን ይችላል ?
የእስክንድር ማለፍ ሲያስደስታቸው፡ በሌላ በኩል ደግሞ የአቤል ጉዳይ ሁለቱንም ግራ አጋባቸው ። እስክንድር
ልቡ ፈራ ። ስሜቱ መጥፎ ነገር ጠረጠረ ። ለማንኛውም ተያይዘው ውጤቱ ወደ ተዘጋጀበት ቢሮ ሒዱ ።
“ አቤት ! ምን ነበር ? " አለቻቸው ጸሐፊዋ ፡ የምታንቀጭቅጨውን ታይፕ አቋርጣ ። “ የእሱ ውጤት አልወጣም ። እና ... ብሎ እስክንድር ወደ አቤል እያመለከተ
ንግግሩን ሳይጨርስ አቋረጠችው ።
« ስሙ ማን ነው ? ”
“ አቤል ። የፍልስፍና ትምህርት ክፍል
“አሃ ! አቤል ሙሉዬ ፡ ያንተ ውጤት አልደረሰንም እስኪ ዮናታንን ሒደህ አነጋግራቸው አለችና ሥራዎን
ቀጠለች ።
“ውጤቱ ዮናታን ጋር ምን ያደርጋል?” አለ አቤል በልቡ።ዮናታንን ማየት አልፈለገም ነበር ። በዝጉ ውስጥ ሲሸሻቸው ነው የከረመው። ምክራቸውን አለመስማቱና ሕክምናውን ያለ መቀጠሉ እያሳፈሩት ከእሳቸው ለመራቅ ምክሮ ነበር።
የግዱን ከእስክንድር ጋር ሆኖ ወደ ዮናታን ቢሮ ሔደ።ዮናታን የሉም ። ቢሮኣቸው ተቆልፎአል ።
“ ምን ይሻላል ? ” አለ የእስክንድርን ዐይን ዐይን እያየ
“ ምን ይሻላል ? ” ብሎ እስክንድርም ቃሉን በትካዜ ድምፅ ከደገመ በኋላ ፥ “ እንግዲህ ነገ መጥተን እንጠይቃቸዋለን " መቼም ከአሁን በኋላ አይገቡም ” አለው እያስተዛዘነ።
ነገ እንዴት ይነጋ ይሆን ? የጭንቅ ምሽት ፤የመከራ ሕልም ሌሊት ።
በማግሥቱ ጠዋት አቤልና እስክንድር ዮናታንን ቀድመው ነበር፡ ከቢሮአቸው የደረሱት ።አቤል ዐይናቸውን ማየት
👍2❤1
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
#ክፍል_ሶስት
#ትንሣኤ
በሁለቱ መንግስታት መካከል በተደረሰው ስምምነት መሠረት የምርኮኞች ልውውጥ የሚጀመርበት የመጀመሪያው ምዕራፍ......
የድሬዳዋ ከተማ አሸብርቃለች፡፡ ገንደቆሬ፣ ገንደገራዳ፣ መጋላ፣ ከዚራ፣ ለገሀሬ፣ ..... መንደሮች በሙሉ በደስታ ስቀዋል፡፡
በየመንገዱ ግራና ቀኝ ተተክለው ቀዝቃዛና፤ ነፋሻማ አየርን የሚረጩት ዛፎች በደስታ ተውጠው የሚደንሱ ይመስላሉ፡፡ በዚያች ምድር ላይ የተካሄደው ቀውጢ ጦርነት አልፎ፤ ያንን የመሰለ የሰላም አየር መተንፈስ መቻል ዳግማዊ ልደት ነው፡፡
በሐረርጌ ምድር፡፡ በደገሀቡር፣ ቀብሪደሀር፣ መራራሌ፣ በሺላቦ፣
ደቦይን፣ በቆራሄ አሸዋማ ሜዳ፣ በኦጋዴን በረሃ፣ በካራማራ ተራሮችና በሌሎችም ሺህ ሌሊት ሺህ መአልት የፈሰሰው ደም፣ የተከሰከሰው አጥንት፣ያስገኘው ውጤት፡፡
በዚያን ቀውጢ ሰዓት ላይ ለዳር ድንበር ሲሉ ከጠላት ጋር እየተናነቁ አኩሪ ገድል የፈጸሙት፤ በደማቸው ማህተም፤ በአጥንታቸው ክስካሽ፤ ምድሪቱን ያቀሉት...የመስዋዕትነት ፈርጦች! የሚጠበቁበት ዕለት......
ሰማዩ በዚያን ቀውጢ የጦርነት ወቅት በኢትዮጵያ አየር ሃይል የተሠራውን አስደናቂ ትርኢትና ተአምር አፍ አውጥቶ ሊናገር፣ የታሪክ ምስክርነቱን ሊሰጥ፣ የተዘጋጀ ይመስል አጉረመረመ፡፡ ለሚወዷት እናት አገራቸው ዳር ድንበር ሲሉ የተፋለሙና ልዩ ልዩ ጀብድ ከፈጸሙ በኋላ በጠላት እጅ ወድቀው በባእድ ሀገር በምርኮኝነትና፤ በእስረኝነት ለበርካታ
አመታት ከቆዩ በኋላ በሁለቱ መንግስታት መካከል በተደረሰው ስምምነት መሰረት ዛሬ ወደሚያፈቅሯትና፤ ወደሚወዷት፤ እናት አገራቸው የሚመለሱበት እለት ስለሆነ፤ እነዚህን ውድ የሀገር አለኝታዎችና፤ ጀግኖች፤በልዩና፤ በደማቅ አቀባበል ፤ ሊቀበል ህዝቡ የአውሮፕላን
ማረፊያውን አካባቢ አጥለቅልቆታል....
ማርሽ የሚያሰማው ሠራዊት በተጠንቀቅ ቆሞ ይጠባበቃል።ባንዲራዎች ይውለበለባሉ፡፡ ህዝቡ ይሯሯጣል፡፡ ይራወጣል። ሰማይ ሰማዩን እያንጋጠጠ ይመለከታል፡፡
አንዳንድ ጊዜ ትላልቅ አሞራዎች ያሳስታሉ፡፡ የሁሉም ልብ ተንጠልጥሏል፡፡ እነማን ይሆኑ?! ሞቱ ተብለው ደረት
የተመታላቸው፣ ተዝካር የተበላላቸው፣ ማን ያውቃል? በህይወት ሊገኙ
ይችሉ ይሆናል፡፡ ይህ ጦርነት በተካሄደባቸው ብዙ አገሮች በተደጋጋሚ
የታየ ክስተት ነው፡፡
ሰዓቱ ደረሰ፡፡ ሰማዩ እንደገና በከፍተኛ ድምፅ አጉረመረመ፡፡አውሮፕላኗ በርቀት ታየች፡፡ ከዚያም እየጐላች ፤እየጐላች፤ መጣችና፤በማረፊያው ላይ እየዞረች፤ ማንዣባብ ጀመረች።
የሰው ጩኸት ሁካታ... ግርግር... ትርምሱ...ሌላ ሆኗል፡፡ማርሽ በረጅሙ ይሰማል፡፡ አውሮፕላኗ አዘቀዘቀች..... ከዚያም አኮበኮበችና አረፈች፡፡
ጀግኖች የታደሙባት አውሮፕላን! ለዳር ድንበሯ ሱሉ ደማቸውን ያፈሰሱላትን፣ በእስር የማቀቁላትን፣ ጥለው የወደቁላትን፣ ታስረው የተገረፉላትን፣ የጦር ምርኮኞችን ይዛ ይሄውና አውሮፕላኗ መሬት ላይ አረፈች....
የአውሮፕላኗ በር ተከፍቶ አንድ ረጅም፧ ቀጭን፤ መነጽር ያደረገና በአየር ኃይሉ ውስጥ በጦር ጄት የጠላትን ሃይል ድባቅ
በመምታት በደማቅ ቀለም ታሪክ ያስመዘገበ ምርኮኛ ብቅ አለ፡፡ማርሹ ይሰማል፡፡ እልልታው ቀለጠ!! ግማሹ በሲቃ ያለቅሳል፣ይፈነድቃል፡፡ ምርኮኞቹን ለማየት ሰው በሰው ላይ ይንጠላጠላል፣
ትዕይንቱ ብዙ ነው፡፡ ከዚያም የተዘጋጀውን እቅፍ አበባ ምርኮኛው ተቀበለ፡፡
ምርኮኞቹ ከአውሮፕላኗ እንደወረዱ መሬቷን ይስማሉ። አፈሯን ይልሳሉ፡፡ ያለቅሳሉ፣ ይንከባለላሉ፡፡ የደስታ እንባ... የናፍቆት እንባ... የትዝታ እንባ...
ላለፉት አስራ አንድ ዓመታት ከአገር፤ ከወገን፣ ከቤተሰብ ጋር ተለያይተው ፤ የብቸኝነትንና የመከራ ኑሮን ሲገፉ ከቆዩ በኋላ፤የሚወዱትንና፤ የሚያፈቅሩትን፤ ህዝብና አገር መቀላቀል ዳግም መወለድ
ነውና፤ ምርኮኞች ዳግም የተወለዱ ያህል በደስታ ሰከሩ። እንደዚያ ዳር ድንበርዋን ሊያስከብሩላት፤ ከጠላት ጋር አንገት ለአንገት ተናንቀው፡ ሳንጃ ለሳንጃ ተሞዣልቀው፡ ጥለው የወደቁላት፡ የውድ ሀገራቸውን ለም አፈር ለማሽተት በመቻላቸው በደስታ የሚሆኑትን አጡ ...ህዝቡም በእልልታና በሆታ የጀግና አቀባበል አደረገላቸው፡፡ ደስ የሚል ከህሊና የማይጠፋ የአቀባበል ሥነ ሥርዓት......
ለተወሰኑ ቀናቶች በድሬዳዋ ከተማ እረፍት አድርገው ከቆዩና መንፈሳቸው ከተረጋጋ በኋላ፣ በየክፍለ ሀገሩ የሚገኙ ዘመዶቻቸውን ሊቀላቀሉ የቸኮሉት ቀድመው ተንቀሳቀሱ፡፡
እለተ ቅዳሜ! አዲስ አበባ!! የኢትዮጵያ ዋና ከተማ! ቀዝቃዛ ንፋስ ይነፍስባታል ። በተለይ የባህር ማዶው ዛፍ ለቅዝቃዜው የራሱን ከፍተኛ ድርሻ አበርክቷል፡፡
ባቡሩ መንገደኞቹን ጣቢያው አራገፈ፡፡ ግፊያው ለጉድ ነው፡፡ግማሹ ሲመጣ ግማሹ ሲሄድ... የገቢና ወጪ መንገደኞች ምልልስ የማያቋርጥበት አምባ......
ጊዜው ለዐይን ያዝ ማድረግ የጀመረበት ሰዓት ነው፡፡
አንድ ቁመቱ ረዘም ያለ፣ ሰውነቱ በበረሃ ግርፋትና በእስር ስቃይ ምክንያት የተለበለበ ግንድ ቢመስልም፤ በሰላሙ ጊዜ ማራኪ መልክና ቁመና እንደነበረው አሁንም በግልጽ የሚታየው ትክለ ሰውነቱ
ዐቢይ ምስክርነቱን የሚሰጥለት፤ ከሲታ ሰው ከባቡሩ ወረደ፡፡
ደረቱ ሰፋ ያለ፣ ፀጉረ ዞማና ዐይኖቹ ጐላ ጐላ ብለው የሚታዩ ረጅም ሰው ነው፡፡ ሻንጣ አንጠልጥሏል፡፡ ከተሰጠው የኪስ ገንዘብ ውስጥ አብዛኛውን ያዋለው ለሁለት ሴቶችና፤ ለአንድ ወንድ የሚሆኑ ልብሶችን በመግዛት ነው፡፡ ከባቡሩ ወርዶ፤ በአምባሳደር ቲያትር በኩል መጥቶ ፤ ወደ ኦርማ ጋራዥ አቀና፡፡ የሚራመደው በደመነፍስ ዐይነት ነው፡፡
በህልም ዓለም የሚራመድ ይመስላል፡፡
እሱ እራሱ የሚያየው ነገር እውነት መሆኑን ተጠራጥሯል።ግራና ቀኙን በዓይኑ ያማትራል፡፡ ሰዎችን ይቃኛል፡፡ ምናልባት የማውቀው ሰው ካገኘሁ በሚል ግምት ነው፡፡ ግን ማንም የሚያውቀው ሰው አላገኘም፡፡ ድሮ የሚያውቁት ሲያዩት እንኳን፤ በቀላሉ ሊለዩት አይችሉም፡፡ ተለውጧል፡፡ ተጉሳቁሏል፡፡
መንገዶቹ የጠበቡ፣ ቤቶቹም ከምዕተ ዓመት በፊት የነበሩ መስለው ታዩት፡፡ በየመንገዱ ላይ ከሚያያቸው ሰዎች ውስጥ ሶስት ሰዎችን ለማግኘት በናፍቆትና በጉጉት ደጋግሞ ይቃኛል፡፡
የሱ ብርቅዬ፤ ድንቅዬዎች፡፡ ልዩ የህይወቱ ቅመሞች፡፡ የተዳፈነ የናፍቆቱ እምቅ ሊፈነዳ ተቃረበ፡፡ ልቡ ተሸበረ... እየተቃረበ ሲመጣ ልቡ ድው ድው የሚል ድምጽ ሰጠ፡፡ ትንፋሽ አጠረው፡፡
እጅግ አስገራሚ ነው! አስደናቂ
የማይጠበቀው ሰው ፤ እንደዚህ ባልተጠበቀ ሰዓት ከች! ሲል፤ እነሱ
ከአንጀቱ የሚያፈቅራቸው፣ የሚወዳቸው፣ የሚሞትላቸው ቤተሰቦቹ እንዴት ሆነው ይሆን? የሚወዳት ሚስቱ፣ የሚወዳቸው ልጆቹ እንዴት ሆነው ይሆን? ሲለያቸው በነበራቸው ዕድሜ ላይ አስራ አንድ ዓመት ሲጨመርበት የትየለሌ ነው፡፡ ምን መስለው ይሆን?
አቤቱ ፈጣሪ ያንተ ተአምር እንዴት ተወርቶ ያልቅ ይሆን? አደራህን ሁሉንም ለአንድ ቀን እንኳን ቢሆን ዐይናቸውን አይቼው
እንድሞት እርዳኝ፡፡ አንተ ታውቃለህ፡፡
ወባ እንደያዘው ሰው እየተቃረበ መጣ፡፡ ቤቱ ጋ ሲደርስ ሰውነቱ ተንዘፈዘፈበት :: ልቡ በፍጥነት ይመታ ጀመር፡፡
ግቢው ...ያ ...ግቢ የሚወደው ግቢ...እዚያ ውስጥ ያሉት እነ.. መራመድ አልቻለም፡፡ ቆመ፡፡ እንደሀውልት ተገትሮ ቀረ፡፡ ከዚያም ለዘመናት በወስጡ ሲንተከተክ የነበረው እንባ በድንገት ገንፍሉ ወጣ፡፡
ከደስታ ብዛት ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ፡፡ ቤቱን አየው፡፡ ልጆቹን አቅፎ የሳመበትን፣ ከሚያፈቅራት ባለቤቱ ጋር ደስታን ያሳለፈበትን፣ በመጨረሻም ወደ ጦርነት ሲሄድ ከቤተሰቦቹ ጋር ተላቅሶ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
#ክፍል_ሶስት
#ትንሣኤ
በሁለቱ መንግስታት መካከል በተደረሰው ስምምነት መሠረት የምርኮኞች ልውውጥ የሚጀመርበት የመጀመሪያው ምዕራፍ......
የድሬዳዋ ከተማ አሸብርቃለች፡፡ ገንደቆሬ፣ ገንደገራዳ፣ መጋላ፣ ከዚራ፣ ለገሀሬ፣ ..... መንደሮች በሙሉ በደስታ ስቀዋል፡፡
በየመንገዱ ግራና ቀኝ ተተክለው ቀዝቃዛና፤ ነፋሻማ አየርን የሚረጩት ዛፎች በደስታ ተውጠው የሚደንሱ ይመስላሉ፡፡ በዚያች ምድር ላይ የተካሄደው ቀውጢ ጦርነት አልፎ፤ ያንን የመሰለ የሰላም አየር መተንፈስ መቻል ዳግማዊ ልደት ነው፡፡
በሐረርጌ ምድር፡፡ በደገሀቡር፣ ቀብሪደሀር፣ መራራሌ፣ በሺላቦ፣
ደቦይን፣ በቆራሄ አሸዋማ ሜዳ፣ በኦጋዴን በረሃ፣ በካራማራ ተራሮችና በሌሎችም ሺህ ሌሊት ሺህ መአልት የፈሰሰው ደም፣ የተከሰከሰው አጥንት፣ያስገኘው ውጤት፡፡
በዚያን ቀውጢ ሰዓት ላይ ለዳር ድንበር ሲሉ ከጠላት ጋር እየተናነቁ አኩሪ ገድል የፈጸሙት፤ በደማቸው ማህተም፤ በአጥንታቸው ክስካሽ፤ ምድሪቱን ያቀሉት...የመስዋዕትነት ፈርጦች! የሚጠበቁበት ዕለት......
ሰማዩ በዚያን ቀውጢ የጦርነት ወቅት በኢትዮጵያ አየር ሃይል የተሠራውን አስደናቂ ትርኢትና ተአምር አፍ አውጥቶ ሊናገር፣ የታሪክ ምስክርነቱን ሊሰጥ፣ የተዘጋጀ ይመስል አጉረመረመ፡፡ ለሚወዷት እናት አገራቸው ዳር ድንበር ሲሉ የተፋለሙና ልዩ ልዩ ጀብድ ከፈጸሙ በኋላ በጠላት እጅ ወድቀው በባእድ ሀገር በምርኮኝነትና፤ በእስረኝነት ለበርካታ
አመታት ከቆዩ በኋላ በሁለቱ መንግስታት መካከል በተደረሰው ስምምነት መሰረት ዛሬ ወደሚያፈቅሯትና፤ ወደሚወዷት፤ እናት አገራቸው የሚመለሱበት እለት ስለሆነ፤ እነዚህን ውድ የሀገር አለኝታዎችና፤ ጀግኖች፤በልዩና፤ በደማቅ አቀባበል ፤ ሊቀበል ህዝቡ የአውሮፕላን
ማረፊያውን አካባቢ አጥለቅልቆታል....
ማርሽ የሚያሰማው ሠራዊት በተጠንቀቅ ቆሞ ይጠባበቃል።ባንዲራዎች ይውለበለባሉ፡፡ ህዝቡ ይሯሯጣል፡፡ ይራወጣል። ሰማይ ሰማዩን እያንጋጠጠ ይመለከታል፡፡
አንዳንድ ጊዜ ትላልቅ አሞራዎች ያሳስታሉ፡፡ የሁሉም ልብ ተንጠልጥሏል፡፡ እነማን ይሆኑ?! ሞቱ ተብለው ደረት
የተመታላቸው፣ ተዝካር የተበላላቸው፣ ማን ያውቃል? በህይወት ሊገኙ
ይችሉ ይሆናል፡፡ ይህ ጦርነት በተካሄደባቸው ብዙ አገሮች በተደጋጋሚ
የታየ ክስተት ነው፡፡
ሰዓቱ ደረሰ፡፡ ሰማዩ እንደገና በከፍተኛ ድምፅ አጉረመረመ፡፡አውሮፕላኗ በርቀት ታየች፡፡ ከዚያም እየጐላች ፤እየጐላች፤ መጣችና፤በማረፊያው ላይ እየዞረች፤ ማንዣባብ ጀመረች።
የሰው ጩኸት ሁካታ... ግርግር... ትርምሱ...ሌላ ሆኗል፡፡ማርሽ በረጅሙ ይሰማል፡፡ አውሮፕላኗ አዘቀዘቀች..... ከዚያም አኮበኮበችና አረፈች፡፡
ጀግኖች የታደሙባት አውሮፕላን! ለዳር ድንበሯ ሱሉ ደማቸውን ያፈሰሱላትን፣ በእስር የማቀቁላትን፣ ጥለው የወደቁላትን፣ ታስረው የተገረፉላትን፣ የጦር ምርኮኞችን ይዛ ይሄውና አውሮፕላኗ መሬት ላይ አረፈች....
የአውሮፕላኗ በር ተከፍቶ አንድ ረጅም፧ ቀጭን፤ መነጽር ያደረገና በአየር ኃይሉ ውስጥ በጦር ጄት የጠላትን ሃይል ድባቅ
በመምታት በደማቅ ቀለም ታሪክ ያስመዘገበ ምርኮኛ ብቅ አለ፡፡ማርሹ ይሰማል፡፡ እልልታው ቀለጠ!! ግማሹ በሲቃ ያለቅሳል፣ይፈነድቃል፡፡ ምርኮኞቹን ለማየት ሰው በሰው ላይ ይንጠላጠላል፣
ትዕይንቱ ብዙ ነው፡፡ ከዚያም የተዘጋጀውን እቅፍ አበባ ምርኮኛው ተቀበለ፡፡
ምርኮኞቹ ከአውሮፕላኗ እንደወረዱ መሬቷን ይስማሉ። አፈሯን ይልሳሉ፡፡ ያለቅሳሉ፣ ይንከባለላሉ፡፡ የደስታ እንባ... የናፍቆት እንባ... የትዝታ እንባ...
ላለፉት አስራ አንድ ዓመታት ከአገር፤ ከወገን፣ ከቤተሰብ ጋር ተለያይተው ፤ የብቸኝነትንና የመከራ ኑሮን ሲገፉ ከቆዩ በኋላ፤የሚወዱትንና፤ የሚያፈቅሩትን፤ ህዝብና አገር መቀላቀል ዳግም መወለድ
ነውና፤ ምርኮኞች ዳግም የተወለዱ ያህል በደስታ ሰከሩ። እንደዚያ ዳር ድንበርዋን ሊያስከብሩላት፤ ከጠላት ጋር አንገት ለአንገት ተናንቀው፡ ሳንጃ ለሳንጃ ተሞዣልቀው፡ ጥለው የወደቁላት፡ የውድ ሀገራቸውን ለም አፈር ለማሽተት በመቻላቸው በደስታ የሚሆኑትን አጡ ...ህዝቡም በእልልታና በሆታ የጀግና አቀባበል አደረገላቸው፡፡ ደስ የሚል ከህሊና የማይጠፋ የአቀባበል ሥነ ሥርዓት......
ለተወሰኑ ቀናቶች በድሬዳዋ ከተማ እረፍት አድርገው ከቆዩና መንፈሳቸው ከተረጋጋ በኋላ፣ በየክፍለ ሀገሩ የሚገኙ ዘመዶቻቸውን ሊቀላቀሉ የቸኮሉት ቀድመው ተንቀሳቀሱ፡፡
እለተ ቅዳሜ! አዲስ አበባ!! የኢትዮጵያ ዋና ከተማ! ቀዝቃዛ ንፋስ ይነፍስባታል ። በተለይ የባህር ማዶው ዛፍ ለቅዝቃዜው የራሱን ከፍተኛ ድርሻ አበርክቷል፡፡
ባቡሩ መንገደኞቹን ጣቢያው አራገፈ፡፡ ግፊያው ለጉድ ነው፡፡ግማሹ ሲመጣ ግማሹ ሲሄድ... የገቢና ወጪ መንገደኞች ምልልስ የማያቋርጥበት አምባ......
ጊዜው ለዐይን ያዝ ማድረግ የጀመረበት ሰዓት ነው፡፡
አንድ ቁመቱ ረዘም ያለ፣ ሰውነቱ በበረሃ ግርፋትና በእስር ስቃይ ምክንያት የተለበለበ ግንድ ቢመስልም፤ በሰላሙ ጊዜ ማራኪ መልክና ቁመና እንደነበረው አሁንም በግልጽ የሚታየው ትክለ ሰውነቱ
ዐቢይ ምስክርነቱን የሚሰጥለት፤ ከሲታ ሰው ከባቡሩ ወረደ፡፡
ደረቱ ሰፋ ያለ፣ ፀጉረ ዞማና ዐይኖቹ ጐላ ጐላ ብለው የሚታዩ ረጅም ሰው ነው፡፡ ሻንጣ አንጠልጥሏል፡፡ ከተሰጠው የኪስ ገንዘብ ውስጥ አብዛኛውን ያዋለው ለሁለት ሴቶችና፤ ለአንድ ወንድ የሚሆኑ ልብሶችን በመግዛት ነው፡፡ ከባቡሩ ወርዶ፤ በአምባሳደር ቲያትር በኩል መጥቶ ፤ ወደ ኦርማ ጋራዥ አቀና፡፡ የሚራመደው በደመነፍስ ዐይነት ነው፡፡
በህልም ዓለም የሚራመድ ይመስላል፡፡
እሱ እራሱ የሚያየው ነገር እውነት መሆኑን ተጠራጥሯል።ግራና ቀኙን በዓይኑ ያማትራል፡፡ ሰዎችን ይቃኛል፡፡ ምናልባት የማውቀው ሰው ካገኘሁ በሚል ግምት ነው፡፡ ግን ማንም የሚያውቀው ሰው አላገኘም፡፡ ድሮ የሚያውቁት ሲያዩት እንኳን፤ በቀላሉ ሊለዩት አይችሉም፡፡ ተለውጧል፡፡ ተጉሳቁሏል፡፡
መንገዶቹ የጠበቡ፣ ቤቶቹም ከምዕተ ዓመት በፊት የነበሩ መስለው ታዩት፡፡ በየመንገዱ ላይ ከሚያያቸው ሰዎች ውስጥ ሶስት ሰዎችን ለማግኘት በናፍቆትና በጉጉት ደጋግሞ ይቃኛል፡፡
የሱ ብርቅዬ፤ ድንቅዬዎች፡፡ ልዩ የህይወቱ ቅመሞች፡፡ የተዳፈነ የናፍቆቱ እምቅ ሊፈነዳ ተቃረበ፡፡ ልቡ ተሸበረ... እየተቃረበ ሲመጣ ልቡ ድው ድው የሚል ድምጽ ሰጠ፡፡ ትንፋሽ አጠረው፡፡
እጅግ አስገራሚ ነው! አስደናቂ
የማይጠበቀው ሰው ፤ እንደዚህ ባልተጠበቀ ሰዓት ከች! ሲል፤ እነሱ
ከአንጀቱ የሚያፈቅራቸው፣ የሚወዳቸው፣ የሚሞትላቸው ቤተሰቦቹ እንዴት ሆነው ይሆን? የሚወዳት ሚስቱ፣ የሚወዳቸው ልጆቹ እንዴት ሆነው ይሆን? ሲለያቸው በነበራቸው ዕድሜ ላይ አስራ አንድ ዓመት ሲጨመርበት የትየለሌ ነው፡፡ ምን መስለው ይሆን?
አቤቱ ፈጣሪ ያንተ ተአምር እንዴት ተወርቶ ያልቅ ይሆን? አደራህን ሁሉንም ለአንድ ቀን እንኳን ቢሆን ዐይናቸውን አይቼው
እንድሞት እርዳኝ፡፡ አንተ ታውቃለህ፡፡
ወባ እንደያዘው ሰው እየተቃረበ መጣ፡፡ ቤቱ ጋ ሲደርስ ሰውነቱ ተንዘፈዘፈበት :: ልቡ በፍጥነት ይመታ ጀመር፡፡
ግቢው ...ያ ...ግቢ የሚወደው ግቢ...እዚያ ውስጥ ያሉት እነ.. መራመድ አልቻለም፡፡ ቆመ፡፡ እንደሀውልት ተገትሮ ቀረ፡፡ ከዚያም ለዘመናት በወስጡ ሲንተከተክ የነበረው እንባ በድንገት ገንፍሉ ወጣ፡፡
ከደስታ ብዛት ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ፡፡ ቤቱን አየው፡፡ ልጆቹን አቅፎ የሳመበትን፣ ከሚያፈቅራት ባለቤቱ ጋር ደስታን ያሳለፈበትን፣ በመጨረሻም ወደ ጦርነት ሲሄድ ከቤተሰቦቹ ጋር ተላቅሶ
👍2🔥1
#ቆንጆዎቹ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
...የሠራሁትን ጥፋት ለአገሬ መንግሥት እንደሚያሳውቁ እስጠነቀቁኝ፡፡ በዚህ
ላይ እንዳለን የጊኒና የሞሮኮ አታሼዎች ተገደሉ፡፡
“አየህ... እኔ ምስጢሩን ላወጣ አልፈለግሁም:: እርግጥ በአንድ
ወቅት በገዛ አገሬ ላይ ሰልያለሁ፡፡ በመላው አፍሪካ ላይ ይህን በደል
ልፈጽም አልቻልኩም፡፡ የምከዳው አንዲትን አገር ሳይሆን መላውን አፍሪካ
ነበር፡፡ እንዳስፈራሩኝ ከዚህ ቀደም የሰራሁትን ወንጀል ቢያወጡ: ደግሞ
ያለጥርጥር እንደጊኒና ሞሮኮ ወታደራዊ አታሼዎች መሰበሬ ሆነ:: ተሰወርኩ፡፡” ካልቨርት የያዘውን ግማሽ መለኪያ አረቄ ጨልጠው::
“የጊኒና የሞሮኮ አታሼዎች ምስጢር አውጥተው ነው ማለት ነው ለሞት የበቁት?” አለ ናትናኤል ፊቱን አኮማትሮ።
“በእርግጥ አላውቅም.… ግን ሊሆን ይችላል፡፡ አየህ.. ይኸው አካል
የተጠናከረ የመረጃ መረብ አለው:: ከፍተኛ ቁጥጥርም ያደርግብናል፡፡
ምንም እንኳን ቀደም ብሎ ስለ እያንዳንዳችን ጥልቅ ጥናት የተደረገ ቢሆንም አንዳንድ ያልታሰቡ ሁኔታዎች ለመቋቋም ሲባል ይከታተሉናል፡፡ አስፈላጊ ሲሆን ደግሞ በሁለቱ ኣታሼዎች ላይ ብቻ ሳይሆን በሌሎች ከፍተኛ የአፍሪካ ባላሥልጣናት ላይም የተፈጸመውን ግድያ ከመፈጸም ወደኋላ የሚል ኃይል አይደለም፡፡ብቻ ሁለቱ አታሼዎች ምሲጥር፡ አውጥተዋል ብዬ ስመናገር ያዳግተኛል አውጥተውት ቢሆን እስካሁን ብዙ መፍረክረኮች ይከተሉ ነበር፡፡ቢሆንም አመኔታ እስከታጣብን ድረስና የአንተ መኖር ለአፍሪካ ስጋት
እስከሆነ ድረስ ያለማመንታት ትወገዳለህ፡፡ ብዙዎቹ ተወግደዋል፡፡ ለዚህ ነው ከሁሉ የተሰርኩ፤ ከምደግፋቸውም ከምፀየፋቸውም የተሰወርኩ፡፡እኔም እንደሌላው አፍሪካዊ አፍሪካ አንድ ሆና ማየት እፈልጋለሁ፡፡”
"በመጀመሪያ ለሌላ ባዕድ ድርጅት መስራትህን እንዴት ሳይደርሱበት ቀሩ?”
“ስህተት ነው፡፡ ስህተት ነው የፈፀሙት፡፡ እርግጥ ጠንቃቃ ነበርኩ፤ ቢሆንም መሳሳታቸው በጊዜው እኔንም ያስደነገጠኝ ጉዳይ ነበር።”
“ከጠፋህስ ሰኋላ እንዴት ሊያገኙ አልቻሉም? ማለቴ መንግሥት የሚደግፋቸው እስከሆነ ድረስ አንተን ማደን ያን ያህል አስቸጋሪ አይሆንም...
ሌላውን ብንተወው እንኳን አድራሻህን እንድትነግራቸው የምሥራችን
ሊያስገድዷት ይችሉ ነበር፡፡ እኔ'ኮ ግራ የሆነብኝ ይህን ያህል በመላው አፍሪካ
እየተርመሰመስ ያለ ኃይል አድኖ ሊያገኘው ያልቻለውን ሰው እንዴት እኔ
ላገኝህ ቻልኩ?”
“ሊያገኙኝ ያልቻሉት ስላልሞከሩ ብቻ ነው፡፡ለመሰወር እንደቆረጥኩ
ከዚህ በፊት ያጠፋሁትን ጥፋት በገዛ አገሬ ላይ የሰራሁትን ወንጀል በሙሉ
ዘርዝሬ በጽሁፍ አስተላዕፍኩላቸው፡፡ይህንንም ያለፈ ጥፋቴን እንደማስፈ
ራሪያ በመጠቀም የባዕድ የስለላ ድርጅቶች ምስጢሩን ከእኔ ለማግኘት
በመጣር ላይ መሆናቸውንና ምስጢሩን አውጥቼ ከዳተኛ ከመሆን አለበለዚያም ነጮቹ ያለፈ ስራዬን ይፋ አውጥተው ለጥፋት ሳይዱርጉኝ በፊት ለመጥፋት መወሰኔን ገለጽኩላቸው፡፡ ሆኖም እኔን አድነው ለማግኘት ቢጥሩ ወይም የምሥራችን ለማስገደድ ቢሞክሩ ደብቄ የያዝኩት ምሥጢር የጋዜጦች ቆሎ እንደሚሆኝ እስፈራራኋቸው፡፡” ካልቨርት በቀኙ የጨበጠ ውን ባዶ መለኪያ አተኩሮ ተመለከተው፡፡ “ለዚህ ነው ሳይተናኮሉኝ ባለሁበት ሊተውኝ የመረጡት። ድምጼን አጥፍቼ ጭንቅላቴን ቀብሬ ሰዓቷ እስክትደርስ ከታገለኩ ከዚያ ወዲያ ሊበቀሉኝ እንደማይሞክሩ እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ ምክንያት አይኖራቸውማ፡፡ ለምስጢራቸው ደህንነት ስል ነዋ የተሰወርኩት፡፡”
“ታዲያ የምሥራችን ለምን ገደሏት?”
“እመነኝ እነሱ አይደሉም የገደሏት… ነጮቹ ናቸው፡፡”
“እነማን ናቸው ነጮቹ?”
“እንግሊዞቹ አስራኤላውያኑ… አላውቅም”
“እንዴት ለምን?”
“አየህ እንዳልኩህ ከመጥፋቱ በፊት በምሥራች ላይ አደጋ ሲደርስ
ምሥጢሩን እንደማመጣ ዝቼ ስለነበር ጥበቃ ይደረግላት ነበር በስውር፡፡”
“በማን?”
“በቆንጆዎቹ።”
“ማን እንዳይጎዳት?”
“በብስጭት ምሥጢሩን ይፋ እንዳደርገው ሲሉ ነኞቹ የምሥራችን
ሊያፍኗት ወይ ሊገሏት ይችላሉ ብለው በመፍራት ይመስለኛል። አንተም
ከሆቴሏ ድረስ ሄደህ አንድ ክፍል ውስጥ አስገብተሃት ስትዘጋ የነጮቹ
ቅጥረኛ መስለሃቸው አንድ ነገር እንዳታደርጋት በመፍራት ይሆናል
ቆንጆዎቹ ሊያቆሙህ የሞከሩት፡፡”
“ግን እንዴት ነው ነገሩ?” ናትናኤል ግራ ተጋባ፡፡ “ያ የባዕድ የሆነ የስለላ ድርጅት ኢትዮያውያንን መልምሎ አሰማርቷል ማለት ነው? የገደለቻት ሴት'ኮ ያለ ጥርጥር ኢትዮጵያዊት ነች::” አለ ናትናኤል ሲቲና ፊቱ ላይ ግጥም ስትልበት::
“አይደለም አይደለም::” አለ ካልቨርት የናትናኤል ውሱን እውቀት ነገሩን ሁሉእንዳዘበራረቀበት ሲረዳ፡፡ “ለነጮቹ የስለላ ድርጅት በአዲስ አበባ
ውስጥ የመስክ ስራ እየሠራላት ያለ ሞሳድ ነው፡፡ እሥራኤል ቀደም ሲል
ከዓመታት በፊት ኢትዮጵያ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ የኢትዮጵያ አይሁዳውያንን
መልሳ ወደ አዲስ አበባ በብዛት አስገብታ የመረጃ ስራ እያሰራቻቸው ነው::”
“ለምን?” ናትናኤል አቋረጠው፡፡ “እሥራኤል ለምን ብላ ለነጮቹ
ትሠራለች? ከኢትጵያ ጋር ያላት ግንኙነት መጥፎ አይደለም!እንደውም ግንኙነታችን ከመቼውም ጊዜ የተሻለ ነው::”
“የስለላ መረብ የምትዘረጋው በጠላትህ ላይ ብቻ አይደለም። ስለላ በአጭሩ መረጃዎችን መሰብሰቢያ መንገድ እንጂ የግድ አንዱ አንዱ ካለው
ጥላቻ የሚመነጭ አይደለም፡፡
አስታውስ እሥራኤል በ1980ዎቹ መጨረሻ በዋንኛ ደጋፊዋ በዩናይትድ ስቴትስ ላይ ሳይቅር ስለላ ስታካሂድ ተደርሶባታል፡፡ አይደለም፡፡ እሥራኤል ከኢትዮጵያ ጋር ካላት ግንኙነት ጋር የተያያዘ አይደለም::”
“ታዲያ ለምን?” ናትናኤል አፈጠጠ፡፡
“በመጀመሪያ ነገሩ የተለመደ ነው::የተለያዩ የመረጃ ቤቶች አንዱ
ለአንዱ ውለታ መፈጻጸሙና መረጃ መለዋለጠ የተለመደ ነው፡፡ ግን
እሥራኤል እዚህ ውስጥ አጇን የከተተችው ለራሷ ስትል ነው፡፡ አየህ
አፍሪካ ተባብራ ለመንቀሳቀስ ከቻለች ምናልባት በግብጽና በጥቂት የሰሜን
አፍሪካ አገሮች ገፋፊነት አጥፊ እርምጃ በእርሷ ላይ እንዳይፈጸም የሰጋች
ይመስለኛል ለዚህ ነው ሁኔታውን ከወዲሁ ለመከታተል የመረጠችው::”
“እና…. የምሥራችን የገደሏት…”
“ቆንጆዎቹ አይደሉም፡፡ የነጭ ጠላቶቻችን ናቸው::” አለ ካልቨርት አቋርጦ::
“ታዲያ እሁን ምን ልታደርግ ነው? ምሥጢሩን ልታወጣ ነው
ወይስ…?”
ካልቨርት ጭንቅላቱን ነቀነቀ፡፡
“ስታየኝ ጅል እመስላለሁ? በፍጹም! ሊያታልሉኝ ሲሞክሩ...
እንዳችንን በአንዳችን ላይ ሊያነሳሱ ሲሞክሩ እያየሁ እንዴት እጃጃላለሁ?”
“ጥሩ፡፡ አሁን ምንድነው ማድረግ ያለብን?” ናትናኤል ዙሪያው
ድቅድቅ ጨለማ ሆነበት፡፡
“መጠበቅ፡፡”
“ምኑን?”
“ቀኑን፡፡”
“የቱን ቀን?”
“የስብሰባውን ቀን፤ አፍሪካ አንድ የምትሆንበትን.…”
“አንችልም!” ናትናኤል ከተቀመጠበት ተፈናጥሮ ተነሳ።
“ለምንድነው የማንችለው.…የቀሩን ሦስት ቀናት ብቻ ናቸው፡፡ ከዚያ በኋላ ነፃ ነን፡፡”
“ይይዙናል!” አለ ናትናኤል በጭንቀት ተወጥሮ፡፡
“አያገኙንም፡፡”
“ያገኙናል፡፡ ባቡር ጣቢያው ድረስ ተከታትለውኛል ! አይቼዋለሁ፡፡
ሽጉጡኝ ከትከሻው በላይ ይዞ ሊቀጥፈኝ ሲንደረደር እነዛን አይኖቹን አይቻቸዋለሁ! ትሰማኛለህ? ! ድጋሚ ካገኘኝ ስሜን እንኳን አይጠራም፡፡ በጆሮ ግንዴ ነው የሚለቅብኝ! ትሰማኛለህ? ! መሞት አልፈልግም፡፡ በጤና ከቤቴ መመለስ ነው የምፈልገው!” ናትናኤል ሰውነቱ ሳይታወቀው ከቁጥጥሩ ውጭ ሲሆንበት ጭንቅላቱን በሁለት እጆቹ ግጥም አድርጎ ይዞ መሃል ወለሉ ላይ ቆመ፡፡
“ቁጭ በል…” አለ ካልቨርት
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
...የሠራሁትን ጥፋት ለአገሬ መንግሥት እንደሚያሳውቁ እስጠነቀቁኝ፡፡ በዚህ
ላይ እንዳለን የጊኒና የሞሮኮ አታሼዎች ተገደሉ፡፡
“አየህ... እኔ ምስጢሩን ላወጣ አልፈለግሁም:: እርግጥ በአንድ
ወቅት በገዛ አገሬ ላይ ሰልያለሁ፡፡ በመላው አፍሪካ ላይ ይህን በደል
ልፈጽም አልቻልኩም፡፡ የምከዳው አንዲትን አገር ሳይሆን መላውን አፍሪካ
ነበር፡፡ እንዳስፈራሩኝ ከዚህ ቀደም የሰራሁትን ወንጀል ቢያወጡ: ደግሞ
ያለጥርጥር እንደጊኒና ሞሮኮ ወታደራዊ አታሼዎች መሰበሬ ሆነ:: ተሰወርኩ፡፡” ካልቨርት የያዘውን ግማሽ መለኪያ አረቄ ጨልጠው::
“የጊኒና የሞሮኮ አታሼዎች ምስጢር አውጥተው ነው ማለት ነው ለሞት የበቁት?” አለ ናትናኤል ፊቱን አኮማትሮ።
“በእርግጥ አላውቅም.… ግን ሊሆን ይችላል፡፡ አየህ.. ይኸው አካል
የተጠናከረ የመረጃ መረብ አለው:: ከፍተኛ ቁጥጥርም ያደርግብናል፡፡
ምንም እንኳን ቀደም ብሎ ስለ እያንዳንዳችን ጥልቅ ጥናት የተደረገ ቢሆንም አንዳንድ ያልታሰቡ ሁኔታዎች ለመቋቋም ሲባል ይከታተሉናል፡፡ አስፈላጊ ሲሆን ደግሞ በሁለቱ ኣታሼዎች ላይ ብቻ ሳይሆን በሌሎች ከፍተኛ የአፍሪካ ባላሥልጣናት ላይም የተፈጸመውን ግድያ ከመፈጸም ወደኋላ የሚል ኃይል አይደለም፡፡ብቻ ሁለቱ አታሼዎች ምሲጥር፡ አውጥተዋል ብዬ ስመናገር ያዳግተኛል አውጥተውት ቢሆን እስካሁን ብዙ መፍረክረኮች ይከተሉ ነበር፡፡ቢሆንም አመኔታ እስከታጣብን ድረስና የአንተ መኖር ለአፍሪካ ስጋት
እስከሆነ ድረስ ያለማመንታት ትወገዳለህ፡፡ ብዙዎቹ ተወግደዋል፡፡ ለዚህ ነው ከሁሉ የተሰርኩ፤ ከምደግፋቸውም ከምፀየፋቸውም የተሰወርኩ፡፡እኔም እንደሌላው አፍሪካዊ አፍሪካ አንድ ሆና ማየት እፈልጋለሁ፡፡”
"በመጀመሪያ ለሌላ ባዕድ ድርጅት መስራትህን እንዴት ሳይደርሱበት ቀሩ?”
“ስህተት ነው፡፡ ስህተት ነው የፈፀሙት፡፡ እርግጥ ጠንቃቃ ነበርኩ፤ ቢሆንም መሳሳታቸው በጊዜው እኔንም ያስደነገጠኝ ጉዳይ ነበር።”
“ከጠፋህስ ሰኋላ እንዴት ሊያገኙ አልቻሉም? ማለቴ መንግሥት የሚደግፋቸው እስከሆነ ድረስ አንተን ማደን ያን ያህል አስቸጋሪ አይሆንም...
ሌላውን ብንተወው እንኳን አድራሻህን እንድትነግራቸው የምሥራችን
ሊያስገድዷት ይችሉ ነበር፡፡ እኔ'ኮ ግራ የሆነብኝ ይህን ያህል በመላው አፍሪካ
እየተርመሰመስ ያለ ኃይል አድኖ ሊያገኘው ያልቻለውን ሰው እንዴት እኔ
ላገኝህ ቻልኩ?”
“ሊያገኙኝ ያልቻሉት ስላልሞከሩ ብቻ ነው፡፡ለመሰወር እንደቆረጥኩ
ከዚህ በፊት ያጠፋሁትን ጥፋት በገዛ አገሬ ላይ የሰራሁትን ወንጀል በሙሉ
ዘርዝሬ በጽሁፍ አስተላዕፍኩላቸው፡፡ይህንንም ያለፈ ጥፋቴን እንደማስፈ
ራሪያ በመጠቀም የባዕድ የስለላ ድርጅቶች ምስጢሩን ከእኔ ለማግኘት
በመጣር ላይ መሆናቸውንና ምስጢሩን አውጥቼ ከዳተኛ ከመሆን አለበለዚያም ነጮቹ ያለፈ ስራዬን ይፋ አውጥተው ለጥፋት ሳይዱርጉኝ በፊት ለመጥፋት መወሰኔን ገለጽኩላቸው፡፡ ሆኖም እኔን አድነው ለማግኘት ቢጥሩ ወይም የምሥራችን ለማስገደድ ቢሞክሩ ደብቄ የያዝኩት ምሥጢር የጋዜጦች ቆሎ እንደሚሆኝ እስፈራራኋቸው፡፡” ካልቨርት በቀኙ የጨበጠ ውን ባዶ መለኪያ አተኩሮ ተመለከተው፡፡ “ለዚህ ነው ሳይተናኮሉኝ ባለሁበት ሊተውኝ የመረጡት። ድምጼን አጥፍቼ ጭንቅላቴን ቀብሬ ሰዓቷ እስክትደርስ ከታገለኩ ከዚያ ወዲያ ሊበቀሉኝ እንደማይሞክሩ እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ ምክንያት አይኖራቸውማ፡፡ ለምስጢራቸው ደህንነት ስል ነዋ የተሰወርኩት፡፡”
“ታዲያ የምሥራችን ለምን ገደሏት?”
“እመነኝ እነሱ አይደሉም የገደሏት… ነጮቹ ናቸው፡፡”
“እነማን ናቸው ነጮቹ?”
“እንግሊዞቹ አስራኤላውያኑ… አላውቅም”
“እንዴት ለምን?”
“አየህ እንዳልኩህ ከመጥፋቱ በፊት በምሥራች ላይ አደጋ ሲደርስ
ምሥጢሩን እንደማመጣ ዝቼ ስለነበር ጥበቃ ይደረግላት ነበር በስውር፡፡”
“በማን?”
“በቆንጆዎቹ።”
“ማን እንዳይጎዳት?”
“በብስጭት ምሥጢሩን ይፋ እንዳደርገው ሲሉ ነኞቹ የምሥራችን
ሊያፍኗት ወይ ሊገሏት ይችላሉ ብለው በመፍራት ይመስለኛል። አንተም
ከሆቴሏ ድረስ ሄደህ አንድ ክፍል ውስጥ አስገብተሃት ስትዘጋ የነጮቹ
ቅጥረኛ መስለሃቸው አንድ ነገር እንዳታደርጋት በመፍራት ይሆናል
ቆንጆዎቹ ሊያቆሙህ የሞከሩት፡፡”
“ግን እንዴት ነው ነገሩ?” ናትናኤል ግራ ተጋባ፡፡ “ያ የባዕድ የሆነ የስለላ ድርጅት ኢትዮያውያንን መልምሎ አሰማርቷል ማለት ነው? የገደለቻት ሴት'ኮ ያለ ጥርጥር ኢትዮጵያዊት ነች::” አለ ናትናኤል ሲቲና ፊቱ ላይ ግጥም ስትልበት::
“አይደለም አይደለም::” አለ ካልቨርት የናትናኤል ውሱን እውቀት ነገሩን ሁሉእንዳዘበራረቀበት ሲረዳ፡፡ “ለነጮቹ የስለላ ድርጅት በአዲስ አበባ
ውስጥ የመስክ ስራ እየሠራላት ያለ ሞሳድ ነው፡፡ እሥራኤል ቀደም ሲል
ከዓመታት በፊት ኢትዮጵያ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ የኢትዮጵያ አይሁዳውያንን
መልሳ ወደ አዲስ አበባ በብዛት አስገብታ የመረጃ ስራ እያሰራቻቸው ነው::”
“ለምን?” ናትናኤል አቋረጠው፡፡ “እሥራኤል ለምን ብላ ለነጮቹ
ትሠራለች? ከኢትጵያ ጋር ያላት ግንኙነት መጥፎ አይደለም!እንደውም ግንኙነታችን ከመቼውም ጊዜ የተሻለ ነው::”
“የስለላ መረብ የምትዘረጋው በጠላትህ ላይ ብቻ አይደለም። ስለላ በአጭሩ መረጃዎችን መሰብሰቢያ መንገድ እንጂ የግድ አንዱ አንዱ ካለው
ጥላቻ የሚመነጭ አይደለም፡፡
አስታውስ እሥራኤል በ1980ዎቹ መጨረሻ በዋንኛ ደጋፊዋ በዩናይትድ ስቴትስ ላይ ሳይቅር ስለላ ስታካሂድ ተደርሶባታል፡፡ አይደለም፡፡ እሥራኤል ከኢትዮጵያ ጋር ካላት ግንኙነት ጋር የተያያዘ አይደለም::”
“ታዲያ ለምን?” ናትናኤል አፈጠጠ፡፡
“በመጀመሪያ ነገሩ የተለመደ ነው::የተለያዩ የመረጃ ቤቶች አንዱ
ለአንዱ ውለታ መፈጻጸሙና መረጃ መለዋለጠ የተለመደ ነው፡፡ ግን
እሥራኤል እዚህ ውስጥ አጇን የከተተችው ለራሷ ስትል ነው፡፡ አየህ
አፍሪካ ተባብራ ለመንቀሳቀስ ከቻለች ምናልባት በግብጽና በጥቂት የሰሜን
አፍሪካ አገሮች ገፋፊነት አጥፊ እርምጃ በእርሷ ላይ እንዳይፈጸም የሰጋች
ይመስለኛል ለዚህ ነው ሁኔታውን ከወዲሁ ለመከታተል የመረጠችው::”
“እና…. የምሥራችን የገደሏት…”
“ቆንጆዎቹ አይደሉም፡፡ የነጭ ጠላቶቻችን ናቸው::” አለ ካልቨርት አቋርጦ::
“ታዲያ እሁን ምን ልታደርግ ነው? ምሥጢሩን ልታወጣ ነው
ወይስ…?”
ካልቨርት ጭንቅላቱን ነቀነቀ፡፡
“ስታየኝ ጅል እመስላለሁ? በፍጹም! ሊያታልሉኝ ሲሞክሩ...
እንዳችንን በአንዳችን ላይ ሊያነሳሱ ሲሞክሩ እያየሁ እንዴት እጃጃላለሁ?”
“ጥሩ፡፡ አሁን ምንድነው ማድረግ ያለብን?” ናትናኤል ዙሪያው
ድቅድቅ ጨለማ ሆነበት፡፡
“መጠበቅ፡፡”
“ምኑን?”
“ቀኑን፡፡”
“የቱን ቀን?”
“የስብሰባውን ቀን፤ አፍሪካ አንድ የምትሆንበትን.…”
“አንችልም!” ናትናኤል ከተቀመጠበት ተፈናጥሮ ተነሳ።
“ለምንድነው የማንችለው.…የቀሩን ሦስት ቀናት ብቻ ናቸው፡፡ ከዚያ በኋላ ነፃ ነን፡፡”
“ይይዙናል!” አለ ናትናኤል በጭንቀት ተወጥሮ፡፡
“አያገኙንም፡፡”
“ያገኙናል፡፡ ባቡር ጣቢያው ድረስ ተከታትለውኛል ! አይቼዋለሁ፡፡
ሽጉጡኝ ከትከሻው በላይ ይዞ ሊቀጥፈኝ ሲንደረደር እነዛን አይኖቹን አይቻቸዋለሁ! ትሰማኛለህ? ! ድጋሚ ካገኘኝ ስሜን እንኳን አይጠራም፡፡ በጆሮ ግንዴ ነው የሚለቅብኝ! ትሰማኛለህ? ! መሞት አልፈልግም፡፡ በጤና ከቤቴ መመለስ ነው የምፈልገው!” ናትናኤል ሰውነቱ ሳይታወቀው ከቁጥጥሩ ውጭ ሲሆንበት ጭንቅላቱን በሁለት እጆቹ ግጥም አድርጎ ይዞ መሃል ወለሉ ላይ ቆመ፡፡
“ቁጭ በል…” አለ ካልቨርት
👍1
#የፍቅር_ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
....ቤቨርሊ ሂል ውስጥ የሚገኘው የፎር ሲዝን ሆቴል የመሰብሰቢያ አዳራሽ
በሁለት የተከፈለ ነው፡፡ የአዳራሹ አንደኛው ጥግ ላይ ትልቅ የሚያምር
መድረክ አለው፡፡ የአዳራሹ ኮርኒስ መሀል ላይ ደግሞ በጣም ትልቅ እና
ጥልፍልፍ መብራት ተንጠልጥሏል፡፡ ከመደነሻው ወለሎች በላይ እና
የመደነሻውን ወለሎች ከበው የተዘጋጁት የእራት ጠረጴዛዎች በአበቦች እና
በተለያዩ ውድ መጠጦች አሸብርቀው ይታያሉ፡፡ መብራቱ የአዳራሹን
ወርቃማና ሰማያዊ ምንጣፍ ፏ አድርጎ ያሳያል፡፡
የዛሬው የበጎ አድራጎት ፕሮግራም ገቢን የሚያሰባስበው መሪ ቃል ደግሞ የአደንዛዥ ዕፅ ሱስን ማቆም' የሚል ነው፡፡ አዳራሹ ውስጥ በሥርዓቱ የተቀመጡት ረዣዥም እና ዓይን የሚስቡ አበባዎች ብቻ ወደ አንድ መቶ ሺ ዶላሮች ያወጣሉ፡፡ በየጠረጴዛዎቹ ላይ የሚገኙት ብርማ የሻማ መቅረዞችም ሲያበሩ ጠረጴዛው ላይ የተነጠፈውን ነጭ የጠረጴዛ ልብስ እና በሥርዓቱ ጠረጴዛው ላይ የተቀመጡትን ውብ ቅርጽ ያላቸውን
ብርጭቆዎች ውበት ልዩ አድርጎታል፡፡ አስራ ስምንት የሙዚቃ ተጫዋቾችም
መድረኩ ላይ ለስለስ ያሉ የኦርኬስትራ ሙዚቃዎችን እየተጫወቱ ውድ
ውድ የእራት ልብሶች ለብሰው ወደ አዳራሹ የሚገቡ የምሽቱን እንግዶች
ያጅባሉ።
ሁሉም አዳራሹ ውስጥ የሚገኙት ዝግጅቶች በውድ ዋጋ
መሰናዳታቸውን የሚመለከት ሰው፣ ዝግጅቱ ለድሆች እና ተስፋ ያጡ
ሱሰኞችን ለመርዳት መሆኑን ሲያስብ ይህ ሁሉ ገንዘብ በቀጥታ ለእነዚህ
ሰዎች ቢደርስ አይሻልም ነበር ወይ? የሚለውን ጥያቄ ሊጠይቅ ይችል
ይሆናል፡፡ ነገር ግን ኒኪ እነዚህ በውድ ገንዘብ አዳራሹን ማዘጋጀት ለምን
እንደሚጠቅሙ ከበፊት ልምዷ ግንዛቤን ወስዳ ስለነበር ትረዳዋለች፡፡ አዎን
“ገንዘብ ለመሰብሰብ ገንዘብ ማውጣት የሎስ አንጀለስ ከተማ ነዋሪዎች
መገለጫ እንደሆነ ስለምታውቅ በዚህ ቅሬታም ሆነ ጥያቄ ልታነሳ አትችልም፡፡ ምክንያቱም ፕሮግራሙ ላይ ለመታደም የአንድ ሰው የመግቢያ ቲኬት ከአንድ ሺ ዶላር በላይ እንደሚያወጣ፣ ጠረጴዛዎቹ ላይ ደግሞ ለመታደም ወደ ሃያ ሺ ዶላር እንደሚከፈልበት ስለምታውቅ አዳራሹ በዚህ መልኩ የመዋቡ ሚስጥር ይገባታል፡፡ በተጨማሪም በሚደረገው ጨረታም ከሰባት ዲጂት በላይ ገቢ እንደሚሰበሰብ ስለሚገባት
የፕሮግራሙ ምሽት ውጤታማ ሆኖ እንደሚጠናቀቅ አትጠራጠርም፡፡
"ኒኪ ውዴ! እንኳን ደህና መጣሽ!” ብሎ ሀዶን ዶፎ ግራ እና ቀኝ ጉንጫን ሳማት።
ሀዶን የአርማኒ ቶክሲዶ ሙሉ ልብስ እና ፈዛዛ ሰማያዊ ከራቫት አድርጎ አምሮበታል። ወደ እሱ ጠረጴዛም ክንዷን ከክንዱ አቆላልፎ እየወሰዳት
“በእውነት በመምጣትሽ ደስ ነው ያለኝ፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ ንግግር እንዳደርግ
ስለተጋበዝኩኝ ፍርሃት ፍርሃት ብሎኛል እና ብርታት ትሰጪኛለሽ፡፡ ንግግር
የማድረጉ ነገር ደግሞ የዶውግ እንጂ የእኔ ችሎታ አይደለም” አላት፡፡
“አይዞህ ትወጣዋለህ አትጨነቅ፡፡ ደግሞም ንግግር እንድታደርግ
ስለጋበዙህ ክብር ሊሰማህ ይገባል፡፡” አለችው ኒኪ፡፡
“ልክ ብለሻል ይኼን ነገር ደግሞ ልቀበለው ግድ ነው፡፡ የአደንዛዥ ዕፅ
ሱስን ማቆም የዚህ ዓመት ትልቁ ገቢን የምናሰባስብበት ፕሮግራም ነው”
አላት ሀዶን፡፡
በእሷ ትከሻ አሻግሮ አዳራሹ ውስጥ የሚገቡትን ታዳሚዎች እየተመለከተም “እኔ እንጃ ምናልባት ዶውግ በሕይወት ቢኖር ይህንን ነገር ላይቀበለው ይችል ይሆናል። ግን እነዚህ በአዳራሹ ውስጥ የሚገኙት እንግዶቻችን በጣም ብዙ ሊረዱን የሚችሉበት ገንዘብ አላቸው፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ ቬኒስ ላይ ለከፈትነው አዲሱ የበጎ አድራጎት ክሊኒካችን ገንዘብ
ያስፈልገናል።” አላት፡፡
ኒኪም ክንዱን ነክታ “ይህንን ልታብራራልኝ አይገባም፡፡” አለችው፡፡ ሀዶንም ከአጠገቡ ያለችውን ቀይ ከጀርባው እስከ ወገቧ ድረስ ክፍት የሆነው ረዥም የእራት ቀሚሷን፣ ጀርባዋ ላይ የተዘናፈለው ጸጉሯን እና ጆሮዋ ላይ ባደረገችው ተንጠልጣይ የአልማዝ የጆሮ ጌጥ ምክንያት የሚያበራው ፊቷን
እያየ አሁን ከሀዘኗ የተላቀቀች እና አዲስ ሕይወት ለመጀመር የተዘጋጀች
መስለኝ ብሎ በውስጡ አሰበ፡፡
እሷም ውስጡን እንዳነበበች ሁሉ “ዶውግ አሁን በህይወት የለም፡፡ስለዚህ ከዚህ በኋላ የምታደርገው ነገር ሁሉ ያንተ ውሳኔ ነው፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ ዶውግ ፍጹም አይደለም፤ የእሱ ውሳኔዎች ሁሉ ትክክል ናቸው ማለት አይቻልም”
“እውነት ብለሻል” ብሎ “አንቺም ዶውግን መምረጥሽ ትክክል አልነበረም”
ብሎም ለእሷ ያለውን መውደድ ሊገልጽላት እያሰበ እያለ ከአዳራሹ መግቢያ ላይ የእሷ መርማሪ የሆነውን ዴሬክ ዊሊያምስ ወደ ውስጥ ሲገባ
ተመለከተው፡፡ምን ሊሠራ መጣ ደግሞ? አለ በሃሳቡ፡፡
ሀዶን መርማሪዋ ቢሮ ድረስ መጥቶ እንዳወራው ሊነግራት አስቦ ነበር።
ነገር ግን ነገሩ ከእሷ ይምጣ ብሎ ትቶታል፡፡ ምናልባትም ዊሊያምስ እሱን
እንዳገኘ ለኒኪ ከነገራት ሀዶን የሞተው ባሏን ነፍስ እረፍት እንድትሰጠው፣
ስለ ሌንካም ለማወቅ የምታደርገውን ነገር እንድትተው ሊሞግታት ወስኗል፡፡
ኒኪ የሀዶንን ዓይን ተከትላ ወደ አዳራሹ መግቢያ አይኗን ስትልክ ዴሪክ
ዊሊያምስን አየችው እና ግንባሯን ቋጠረች፡፡ ዊሊያምስ ዝግጅቱ ላይ
እንደሚገኝ አልነገራትም፡፡ ምናልባትም ደግሞ እሷ እዚህ ዝግጅት ላይ
እንደምትመጣ አያውቅም፡፡ደግሞ ሉዊስ ሮድሪጌዝን ለማየት (ለማግኘት)
አስባ ነው በመጨረሻው ሰዓት ላይ ከእንግዶች የስም ዝርዝር ውስጥ
ልትካተት የቻለችው፡፡ ምናልባት ዴሬክ ሮድሪጌዝን ለማግኘት አስባ ይሆን
እዚህ የተገኘችው? መቼስ የእሷ የቅድሚያ ፍላጎቷን ስለሌንካ ማወቅ
መሆኑን ነግራዋለች እና ይህንን እንደማይረሳው ተስፋ አላት፡፡
በኋላ ላይ ጠረጴዛችን ላይ አገኝሻለሁ” ብሏት ሀዶን እሷን ትቶ ሌሎች
አዳራሹ ውስጥ ወደተጋበዙት እና የክብር እንግዶች እያመራ ሰላምታም
ይሰጣቸው ጀመር፡፡ ኒኪ ዊሊያምስን ለማግኘት ስትንቀሳቀስ ከአዳራሹ
መጨረሻ ቦታ ላይ አኔ ከአደንዛዥ ዕፅ ሱስን ማቆም የሚለው ፕሮግራም
ከመሰረተው ሰው ጋር በጥልቀት ስታወራ ተመለከተቻት እና ወደ እሷ አመራች።
አኔ ወሬዋን እስክትጨርስ ቆማ ጠበቀቻት እና ወሬዋን ስትጨርስ ወደ አኔ ቀርባ “ሃይ ሰላም ነው” አለቻት፡፡
ሚኪ!” አኔ ትንሽ ብስጭት ብላ በጥያቄ ተመለከተቻት፡፡ አኔ አጠር ያለ ጥቁር የሀር ቀሚስ ለብሳለች፡፡ ከወትሮው በተለየ መልክ ወጣትነቷ ጎልቶ ወጥቷል፡፡ ነጭ ፊቷም ትንሽ ውጥረት ይታይበታል፡፡
“እዚህ ደግሞ ምን ትሠሪያለሽ?” ብላ አኔ ጠየቀቻት፡፡
ኒኪ የአኔን የንዴት ስሜት ስትመለከት “ባክሽ ባለቀ ሰዓት የዶውግ የሥራ ባልደረባው ዶፎን ዶፎ ጠረጴዛውን እንድጋራው ጋብዞኝ ነው:: አለቻት፡፡
“ኦ” አለችና እና አኔ ከቁጣ ስሜቷ መለስ አለች፡፡ “እና በጣም ጥሩ ነዋ!"
አለቻት፡፡
“ደህና ነሽ አንቺ ግን? የሆነ ነገር ረብሾሻል አይደል?” አኔም በረዥም
ተንፍሳ “ሉዊስ አይመጣም” ብላ ፊቷ ላይ ትንሽ የመበሳጨት ነገር እየታየባትም “የሆነ ያልጠበቀው ነገር ስለተከሰተ መምጣት አልቻለም፡፡” አለቻት፡፡
ይህንን ከአኔ የሰማችው ኒኪም ቅር አላት፡፡ ቅሬታዋን ግን ፊቷ ላይ
አላሳየቻትም፡፡ ከአኔ ባል ጋር ፊት ለፊት ቢገናኙ ምን እንደሚሰማት
እርግጠኛ ባትሆንም ባላመምጣቱ ግን የተታለለች ዓይነት ስሜት ተሰማት፡፡
“ኦው አዝናለሁ፡፡ የዛሬን ምሽት አንቺ እንዴት እንደፈለግሽው ይገባኛል፡፡”
አኔ በጭንቀት ውስጥ ሆና በእጂ ጸጉሯን እየነካካች “ኡፍ እኔ አላውቅም የእሱን አለመምጣት ከሰማሁ በኋላ የእፎይታ ስሜት ይሁን ወይንም ደግሞ የብሽቀት ስሜት
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
....ቤቨርሊ ሂል ውስጥ የሚገኘው የፎር ሲዝን ሆቴል የመሰብሰቢያ አዳራሽ
በሁለት የተከፈለ ነው፡፡ የአዳራሹ አንደኛው ጥግ ላይ ትልቅ የሚያምር
መድረክ አለው፡፡ የአዳራሹ ኮርኒስ መሀል ላይ ደግሞ በጣም ትልቅ እና
ጥልፍልፍ መብራት ተንጠልጥሏል፡፡ ከመደነሻው ወለሎች በላይ እና
የመደነሻውን ወለሎች ከበው የተዘጋጁት የእራት ጠረጴዛዎች በአበቦች እና
በተለያዩ ውድ መጠጦች አሸብርቀው ይታያሉ፡፡ መብራቱ የአዳራሹን
ወርቃማና ሰማያዊ ምንጣፍ ፏ አድርጎ ያሳያል፡፡
የዛሬው የበጎ አድራጎት ፕሮግራም ገቢን የሚያሰባስበው መሪ ቃል ደግሞ የአደንዛዥ ዕፅ ሱስን ማቆም' የሚል ነው፡፡ አዳራሹ ውስጥ በሥርዓቱ የተቀመጡት ረዣዥም እና ዓይን የሚስቡ አበባዎች ብቻ ወደ አንድ መቶ ሺ ዶላሮች ያወጣሉ፡፡ በየጠረጴዛዎቹ ላይ የሚገኙት ብርማ የሻማ መቅረዞችም ሲያበሩ ጠረጴዛው ላይ የተነጠፈውን ነጭ የጠረጴዛ ልብስ እና በሥርዓቱ ጠረጴዛው ላይ የተቀመጡትን ውብ ቅርጽ ያላቸውን
ብርጭቆዎች ውበት ልዩ አድርጎታል፡፡ አስራ ስምንት የሙዚቃ ተጫዋቾችም
መድረኩ ላይ ለስለስ ያሉ የኦርኬስትራ ሙዚቃዎችን እየተጫወቱ ውድ
ውድ የእራት ልብሶች ለብሰው ወደ አዳራሹ የሚገቡ የምሽቱን እንግዶች
ያጅባሉ።
ሁሉም አዳራሹ ውስጥ የሚገኙት ዝግጅቶች በውድ ዋጋ
መሰናዳታቸውን የሚመለከት ሰው፣ ዝግጅቱ ለድሆች እና ተስፋ ያጡ
ሱሰኞችን ለመርዳት መሆኑን ሲያስብ ይህ ሁሉ ገንዘብ በቀጥታ ለእነዚህ
ሰዎች ቢደርስ አይሻልም ነበር ወይ? የሚለውን ጥያቄ ሊጠይቅ ይችል
ይሆናል፡፡ ነገር ግን ኒኪ እነዚህ በውድ ገንዘብ አዳራሹን ማዘጋጀት ለምን
እንደሚጠቅሙ ከበፊት ልምዷ ግንዛቤን ወስዳ ስለነበር ትረዳዋለች፡፡ አዎን
“ገንዘብ ለመሰብሰብ ገንዘብ ማውጣት የሎስ አንጀለስ ከተማ ነዋሪዎች
መገለጫ እንደሆነ ስለምታውቅ በዚህ ቅሬታም ሆነ ጥያቄ ልታነሳ አትችልም፡፡ ምክንያቱም ፕሮግራሙ ላይ ለመታደም የአንድ ሰው የመግቢያ ቲኬት ከአንድ ሺ ዶላር በላይ እንደሚያወጣ፣ ጠረጴዛዎቹ ላይ ደግሞ ለመታደም ወደ ሃያ ሺ ዶላር እንደሚከፈልበት ስለምታውቅ አዳራሹ በዚህ መልኩ የመዋቡ ሚስጥር ይገባታል፡፡ በተጨማሪም በሚደረገው ጨረታም ከሰባት ዲጂት በላይ ገቢ እንደሚሰበሰብ ስለሚገባት
የፕሮግራሙ ምሽት ውጤታማ ሆኖ እንደሚጠናቀቅ አትጠራጠርም፡፡
"ኒኪ ውዴ! እንኳን ደህና መጣሽ!” ብሎ ሀዶን ዶፎ ግራ እና ቀኝ ጉንጫን ሳማት።
ሀዶን የአርማኒ ቶክሲዶ ሙሉ ልብስ እና ፈዛዛ ሰማያዊ ከራቫት አድርጎ አምሮበታል። ወደ እሱ ጠረጴዛም ክንዷን ከክንዱ አቆላልፎ እየወሰዳት
“በእውነት በመምጣትሽ ደስ ነው ያለኝ፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ ንግግር እንዳደርግ
ስለተጋበዝኩኝ ፍርሃት ፍርሃት ብሎኛል እና ብርታት ትሰጪኛለሽ፡፡ ንግግር
የማድረጉ ነገር ደግሞ የዶውግ እንጂ የእኔ ችሎታ አይደለም” አላት፡፡
“አይዞህ ትወጣዋለህ አትጨነቅ፡፡ ደግሞም ንግግር እንድታደርግ
ስለጋበዙህ ክብር ሊሰማህ ይገባል፡፡” አለችው ኒኪ፡፡
“ልክ ብለሻል ይኼን ነገር ደግሞ ልቀበለው ግድ ነው፡፡ የአደንዛዥ ዕፅ
ሱስን ማቆም የዚህ ዓመት ትልቁ ገቢን የምናሰባስብበት ፕሮግራም ነው”
አላት ሀዶን፡፡
በእሷ ትከሻ አሻግሮ አዳራሹ ውስጥ የሚገቡትን ታዳሚዎች እየተመለከተም “እኔ እንጃ ምናልባት ዶውግ በሕይወት ቢኖር ይህንን ነገር ላይቀበለው ይችል ይሆናል። ግን እነዚህ በአዳራሹ ውስጥ የሚገኙት እንግዶቻችን በጣም ብዙ ሊረዱን የሚችሉበት ገንዘብ አላቸው፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ ቬኒስ ላይ ለከፈትነው አዲሱ የበጎ አድራጎት ክሊኒካችን ገንዘብ
ያስፈልገናል።” አላት፡፡
ኒኪም ክንዱን ነክታ “ይህንን ልታብራራልኝ አይገባም፡፡” አለችው፡፡ ሀዶንም ከአጠገቡ ያለችውን ቀይ ከጀርባው እስከ ወገቧ ድረስ ክፍት የሆነው ረዥም የእራት ቀሚሷን፣ ጀርባዋ ላይ የተዘናፈለው ጸጉሯን እና ጆሮዋ ላይ ባደረገችው ተንጠልጣይ የአልማዝ የጆሮ ጌጥ ምክንያት የሚያበራው ፊቷን
እያየ አሁን ከሀዘኗ የተላቀቀች እና አዲስ ሕይወት ለመጀመር የተዘጋጀች
መስለኝ ብሎ በውስጡ አሰበ፡፡
እሷም ውስጡን እንዳነበበች ሁሉ “ዶውግ አሁን በህይወት የለም፡፡ስለዚህ ከዚህ በኋላ የምታደርገው ነገር ሁሉ ያንተ ውሳኔ ነው፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ ዶውግ ፍጹም አይደለም፤ የእሱ ውሳኔዎች ሁሉ ትክክል ናቸው ማለት አይቻልም”
“እውነት ብለሻል” ብሎ “አንቺም ዶውግን መምረጥሽ ትክክል አልነበረም”
ብሎም ለእሷ ያለውን መውደድ ሊገልጽላት እያሰበ እያለ ከአዳራሹ መግቢያ ላይ የእሷ መርማሪ የሆነውን ዴሬክ ዊሊያምስ ወደ ውስጥ ሲገባ
ተመለከተው፡፡ምን ሊሠራ መጣ ደግሞ? አለ በሃሳቡ፡፡
ሀዶን መርማሪዋ ቢሮ ድረስ መጥቶ እንዳወራው ሊነግራት አስቦ ነበር።
ነገር ግን ነገሩ ከእሷ ይምጣ ብሎ ትቶታል፡፡ ምናልባትም ዊሊያምስ እሱን
እንዳገኘ ለኒኪ ከነገራት ሀዶን የሞተው ባሏን ነፍስ እረፍት እንድትሰጠው፣
ስለ ሌንካም ለማወቅ የምታደርገውን ነገር እንድትተው ሊሞግታት ወስኗል፡፡
ኒኪ የሀዶንን ዓይን ተከትላ ወደ አዳራሹ መግቢያ አይኗን ስትልክ ዴሪክ
ዊሊያምስን አየችው እና ግንባሯን ቋጠረች፡፡ ዊሊያምስ ዝግጅቱ ላይ
እንደሚገኝ አልነገራትም፡፡ ምናልባትም ደግሞ እሷ እዚህ ዝግጅት ላይ
እንደምትመጣ አያውቅም፡፡ደግሞ ሉዊስ ሮድሪጌዝን ለማየት (ለማግኘት)
አስባ ነው በመጨረሻው ሰዓት ላይ ከእንግዶች የስም ዝርዝር ውስጥ
ልትካተት የቻለችው፡፡ ምናልባት ዴሬክ ሮድሪጌዝን ለማግኘት አስባ ይሆን
እዚህ የተገኘችው? መቼስ የእሷ የቅድሚያ ፍላጎቷን ስለሌንካ ማወቅ
መሆኑን ነግራዋለች እና ይህንን እንደማይረሳው ተስፋ አላት፡፡
በኋላ ላይ ጠረጴዛችን ላይ አገኝሻለሁ” ብሏት ሀዶን እሷን ትቶ ሌሎች
አዳራሹ ውስጥ ወደተጋበዙት እና የክብር እንግዶች እያመራ ሰላምታም
ይሰጣቸው ጀመር፡፡ ኒኪ ዊሊያምስን ለማግኘት ስትንቀሳቀስ ከአዳራሹ
መጨረሻ ቦታ ላይ አኔ ከአደንዛዥ ዕፅ ሱስን ማቆም የሚለው ፕሮግራም
ከመሰረተው ሰው ጋር በጥልቀት ስታወራ ተመለከተቻት እና ወደ እሷ አመራች።
አኔ ወሬዋን እስክትጨርስ ቆማ ጠበቀቻት እና ወሬዋን ስትጨርስ ወደ አኔ ቀርባ “ሃይ ሰላም ነው” አለቻት፡፡
ሚኪ!” አኔ ትንሽ ብስጭት ብላ በጥያቄ ተመለከተቻት፡፡ አኔ አጠር ያለ ጥቁር የሀር ቀሚስ ለብሳለች፡፡ ከወትሮው በተለየ መልክ ወጣትነቷ ጎልቶ ወጥቷል፡፡ ነጭ ፊቷም ትንሽ ውጥረት ይታይበታል፡፡
“እዚህ ደግሞ ምን ትሠሪያለሽ?” ብላ አኔ ጠየቀቻት፡፡
ኒኪ የአኔን የንዴት ስሜት ስትመለከት “ባክሽ ባለቀ ሰዓት የዶውግ የሥራ ባልደረባው ዶፎን ዶፎ ጠረጴዛውን እንድጋራው ጋብዞኝ ነው:: አለቻት፡፡
“ኦ” አለችና እና አኔ ከቁጣ ስሜቷ መለስ አለች፡፡ “እና በጣም ጥሩ ነዋ!"
አለቻት፡፡
“ደህና ነሽ አንቺ ግን? የሆነ ነገር ረብሾሻል አይደል?” አኔም በረዥም
ተንፍሳ “ሉዊስ አይመጣም” ብላ ፊቷ ላይ ትንሽ የመበሳጨት ነገር እየታየባትም “የሆነ ያልጠበቀው ነገር ስለተከሰተ መምጣት አልቻለም፡፡” አለቻት፡፡
ይህንን ከአኔ የሰማችው ኒኪም ቅር አላት፡፡ ቅሬታዋን ግን ፊቷ ላይ
አላሳየቻትም፡፡ ከአኔ ባል ጋር ፊት ለፊት ቢገናኙ ምን እንደሚሰማት
እርግጠኛ ባትሆንም ባላመምጣቱ ግን የተታለለች ዓይነት ስሜት ተሰማት፡፡
“ኦው አዝናለሁ፡፡ የዛሬን ምሽት አንቺ እንዴት እንደፈለግሽው ይገባኛል፡፡”
አኔ በጭንቀት ውስጥ ሆና በእጂ ጸጉሯን እየነካካች “ኡፍ እኔ አላውቅም የእሱን አለመምጣት ከሰማሁ በኋላ የእፎይታ ስሜት ይሁን ወይንም ደግሞ የብሽቀት ስሜት
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ስለ ከዘራዎቹ ቀደም በለን ተነጋግረን ስለነበር ንቅንቄ አላለችም።
እናቴ በቅምጧ ውብነሽ በቁሟ ተንዘፈዘፉ። «አእምሮህ ብዙ ነገር
ይቋጥራል፥ በደንብ ታውቃታለህም ታስታውሳታለህም የጊዚ መርዘም ትዝታን ያመነምናታል እንጂ ፈጽሞ አይገድላትም፡፡ የዚህ ልጅ እናት የወዲያነሽ አሽናፊ ትባላለች። ባልተስተካከለና ባልተሟላ የፍቅር ሕይወት ውስጥ የተሠቃየችውና
የተንገላታችው የወዲያነሽና እኔ የተገናኘነው እዚህ ቤት ውስጥ ነው:: ሌላውን ሰፊ ሐተታና ዝብዝብ እንተወውና ከእኔ እንዳረገዘች ከዚህ ቤት ተባረረች። አነሆ እኔና እርሷ ከተፋቀርን ከስምንት ዓመታት በላይ ሆኗል» ብዬ ዝም ስል «ቀጥል! ተርክ!» ብሎ አንባረቀ፡፡
«ካንተ ቀደም ብለው ይህ ልጅ ልጂ መሆኑን የሰሙት የነባር
ምስጢሩንም ሥረ መሠረት የሚያውቁት እናቴና አጎቴ ናቸው። በከንቱ ልማዳዊ እምነት ታፍኜ ይህን መልካሙንና አስፈላጊውን ጉዳይ እንደ ነውር ቆጥሬ
ትክከለኛ የነበረውንና ያልነበረውንም ድርጊቴን አምቄው ኖሬያለሁ፡፡ አሁን ግን እውነት ራሷ ለመሰማትና ይፋ ለመውጣት በውስጤ በመብላላቷና በመብሰሷ እነሆ ይኸው አሁን በማስረዳት ላይ ነኝ፡፡ ይህ ልጅ የተረገዘው እዚህ ቤት ውስጥ
ነበር፡፡ ስለ አስተዳደጉ ግን ደረጃ በደረጃ እነግርሃለሁ:: ቆሞ ለመሔድ መዳህ ያስፈልጋል» ብዬ ንግግሬን እልባት ሳላደርግበት፥
«የት ነበር የተረዝው?» ብሎ መልሴን ለመስማት በሙሉ ስሜት
አሰፈሰፈ፡፡
«ደግሜ ላረጋግጥልሀ፤ እዚሁ ቤት ውስጥ!» ብዬ ወዲያውኑ ስለ መለስኩለት አጠገቡ የነበረውን አየር በፊቱ ስፋት ልክ ገፍቶ ወደ እናቴ ዞረ።
«የሚለውን ሰማሽ? ጉድሽ ተዘከዘከ! እውነት ከሆነ እውነት ነው በይ! ከዚህ ከዝብርቅርቅ ነገር ገላግይኝ፡ እዚህ ቤት ነገር አለ፡፡ ይኸ ዝም ዝም አያዛልቅም! ማን ነች በእርግዝናዋ ጊዜ ከዚህ ቤት የተባረረች? አውጡ! ተናገሩ!» ብሎ ቤቱን በቁጣ አናጋው::
የውብነሽ ውስጥ ውስጡን ከተጫናት ሐሳብ በድንጋጤ ባነነች፡፡ ፍርሃት አፈፍ አደረጋትና ጥቂት ወደ ኋላ አፈገፈገች።
እናቴ ጻእረ ሞት የተናነቀው ሰው መሰለች፡፡
የእኔ ሕሊና እያደር ሰላ፡፡ «እኔው ልናገር! እኔው ላስረዳ!» ብዬ
በሰፊው ለመናገር ወጠን ሳደርግ «በቃህ! ማን ጠየቀህ! ከልኩ የተረፈ ምላስ አላቸው፡፡ የእነርሱ መንታ ምላስ ምን ሆነና? ሾል ሾል አበዛህ! ከልኩ አለፈ!»
ብሎ ኩም አደረገኝ፡፡ የእናቴ ከንፈሮች በትንቅንቅ አንደሚከፈት አሮጌ የብረት በር ቀስ ብለው ከተላቀቀ በኋላ በፍርሃት የተስረቀረቁ ቃላት ማሰማት ጀመረች።
«ነገር ወዲያ ወዲህ ሆኖ አስቸግሮኝ ነው እንጂ የሱ ልጅ መሆኑን ካወቅሁ ይኸው ሁለት ሳምንት ሆነኝ፡፡ ልጁ ነው፡፡ ያቺ ያነዬ እዚህ ቤት ትሠራ
የነበረችው ሠራተኛችን እኛ ሳናውቅና ሳንሰማ ለካ ውስጥ ውስጡን» ብላ ተይው በቃሽ! አርደሽኛል! ገድለሽኛል! በቁሜ
ቀብረሽኛል!» ብሎ ከንፈሩን ነክሶ አቀረቀረ።
«ታዲያ ኑራ ኑራ የስንት ወር ነው ወንድሜ... ነፈሰ ጡር ከሆነችና ሆዷ ከለየ በኋላ ከጌታነህ ማርገዟን ቤት ዘግተን አስለፍልፈን ሰማን» ብላ ተነሣች።
ቀስ ብዬ ጋሻዬነህን በእጄ ጠቀስኩትና አጠገቤ መጥቶ ቆመ፡፡ «እግዚኦ የሰው ልብ! አንቺ አረመኔ! አንቺ ጨካኝ! ለምን
አልነገርሽኝም? ለምን ደበቅሽኝ? አንቺማ አልሠራም አልታዘዝም” ብላ በመጥገቧ አባረርኳት ነበር ያልሽኝ፡፡ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ይይልሽ! » ብሎ በደም ፍላት
ራሱን ነቀነቀ። የተለኮሰውን የትግል ችቦ አጥብቄ ያዝኩት፡፡ የእናቴና የየውብነሽ ሁኔታ በመጠኑ ስሳሳዘነኝ ምንም እንኳ እናቴ የምታምንበትን ሁሉ
የማላምንበትና የማልመራበት ቢሆንም የራሷንና የቤተሰባችንን የኖረ ክብር ስምና ዝና ለመጠበቅ ከፍተኛ ፍላጎት ስላላት በእርሷ ኣስተሳሰብ ማናቸውም
የቤተሰባችን ሰው ተልከስክሶ እንዲገኝ አትፈልግም፡፡ እኔ ግን አሁንም በግልጽ ልናገር! በሰዉ ልጅ እኩልነት ላይ ያላችሁን ፍፁም የተሳሳተ እምነት አላምንበትም! የእናቴንና የቤተሰቤን ፍላጎት ተጋፍቼና ጥሼ ማድረግ
'የማይገባኝን' ነገር ሁኔታው በማይፈቅድልኝና በማይደግፈኝ አካባቢ በመፈጸሜ ስሕተተኛ ነህ እባል ይሆናል፡፡ እኔ ግን አይደለሁም፡፡ የማላምንበትን ሁሉ
አልቀበልም፡፡ ተገዢነቷ ምክንያት ሆኖ ላደረስኩባት በደል በሕግና በሕሊና ችሎት ተጠያቂው እኔ ነኝ፡፡ ከዚህ በኋላ ግን እምነታችሁን ስለማላምንበትና ጨቋኝና ረጋጭ የሆነ ልማድና እምነትንም ስለማልቀበል ወንጀለኛ አይደለሁም ብዬ በመጠኑ ጊዜያዊ የመላቀቂያ ድጋፍ ሰጠኋቸው።» አባቴ ዐይኑን በርበሬ አስመስሎና ግንባሩን አኮፋትሮ «ያም ሆነ ይህ እስካሁን ድረስ የለፈለፍከው ምንም የሚጨበጥ ቁም ነገር የለበትም» ብሎ ጉልበቱን በቡጢ ደወለው።
«አዎ ከአንተ እምነት ውጪ የሆነ
በመሆኑ በቀላሉ አይጨበጥልሀም፡፡ ልብ ብለህ ስማኝ! ማንኛውም ጤነኛ ሰው በተለይም በወጣትነቱ ጊዜ ሥጋዊ ፍላጎትና ፍቅር ባንድ ላይ ተጣምረው እንደሚይዙትና
እንደሚያጠቁት የታወቀ ነው፡፡ ይህ የተፈጥሮ ሕግ ጊዜውን ጠብቆ ደርሶኛል።ያን ጊዜ ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃዋን ሳይሆን ወበቷን እድንቄና ከፈቃዱም
እንደማትወጣ ተማምኜ አግባባኋት፡፡ በሁኔታዎች የተከበበ ውስጣዊ ግዴታ ባማናትም ፍቅራዊ ግፊትና ውዴታም ነበራት» ብዩ ሐሳቡን ለማወቅ ዝም አልኩ፡፡
«ለምኑ ብላችሁ ነው፣ አሁን የምትጨቃጨቁት እኮ እንዲያው ነው፡፡ምነው አንተ ዝም ብትል ልጄ? አባትህም ሲሆን ይኸው ይኸን ሰሞን ጤና አላገኘም፡፡ ያመከረኛ የደም ብዛቱ እየተነሣ ቁም ስቅሉን ያሳየዋል፡፡ ምነው
የሚልህን ብትሰማ፡ ምነው እንደ ዱሮህ ይሁን ይሁን” ብትለው::»
በንግግሬ የተደሰተ ይመስል «ቀጥል፤ አብራራልኝ! አሁን ልንገናኝ ነው!» ብሎ እንድቀጥል አዘዘ። አሳርፍ እንደ ተባለ ወታደር እጅ እግሬን አፍታትቼ ተዝናናሁ፡፡
«የእኔና የእርሷ የጋራ ሥጋዊ ፍላጎት ውጤት በማሕፀኗ ውስጥ
እርግዝናን አስከተለ፡፡ ከዚያ በኋላ ነበር እናቴ ያን በአእምሮዎ ውስጥ ተዳፍኖ የኖረውን እምነቷን ይዛ በመነሣት የትውልዳችንን ክብርና ዝና ጨዋነትና ትልቅነት አስከብራለሁ በማለት በእርግዝናዋ ጊዜ ያባረረቻት። ያም ሆነ ይህ ሲወርድ ሲዋረድ መጥቶ በወረሰችው የተሳሳተ እምነት ተገድዳ የፈጸመችው
ስሕተት በመሆኑ እርሷ ብቻዋን በደለኛ አይደለችም፡፡ የስሕተቱ ቅርንጫፍ ሳይሆን ሥርና ምንጩን መቁረጥና መድፈን ያስፈልጋል፡፡ አንድን ሰው ብቻ መወንጀል ግን ከበሽታ ጠንቆች መካከል አንዷን ብቻ እንደ መግደል ይቆጠራል፡፡
ለወዲያነሽ ያለኝ ፍቅራዊ ታማኝነት ምንጊዜም ቢሆን የማይቀነስና በማንም የተቃውሞ አስተያየት የማይሻር ነው ! » አልኩና በዕለቱ ከሚፈፀመው ጉዳይ ውስጥ አብዛኛውን በድፍረትና በጥንቃቄ አጋመስኩት።
የአባቴ ንዴት ናረ፡፡ ወደ እናቴ ዞር ብሉ «ኧረ ይቺ የወዲያነሽ
የሚላትና እንዲህ የምታስወተውተው ማን ነች? የመቼዋ ነች? እስኪ ደኅና
አደርግሽ ንገረኝ? ምን ይለጉምሻል» አለ። እናቴ በፍርሃት ወለል ወለሉን እያየች «ያነዬ ነው ቆይቷል አንዲት ጠይም መልከ ቀና እዚህ እኛ ጋ አልነበረችም እንዴ? አንተ እንኳ ረጋ ያለች
ደርባባ ነች” ብለህ አመስግነሃት አልነበረም እንዴ? እሷን ነዋ የሚልህ። ከሷ ጋር ነው ይኸ ሁሉ» ብላ ወደ ዝምታዋ ተመለሰች። የአባቴ ዐይኖች ተውዘግዝገው
ጋሻዬነህ ላይ ተተከሉ። «እረግ! እረግ! እረግ! ተይው ተይው! አገኘኋት! ይኸ ልጅ የተወለደው ከእርሷ ነው ማለት ነው?» ብሎ ከሁላችንም መልስ ጠበቀ።
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ስለ ከዘራዎቹ ቀደም በለን ተነጋግረን ስለነበር ንቅንቄ አላለችም።
እናቴ በቅምጧ ውብነሽ በቁሟ ተንዘፈዘፉ። «አእምሮህ ብዙ ነገር
ይቋጥራል፥ በደንብ ታውቃታለህም ታስታውሳታለህም የጊዚ መርዘም ትዝታን ያመነምናታል እንጂ ፈጽሞ አይገድላትም፡፡ የዚህ ልጅ እናት የወዲያነሽ አሽናፊ ትባላለች። ባልተስተካከለና ባልተሟላ የፍቅር ሕይወት ውስጥ የተሠቃየችውና
የተንገላታችው የወዲያነሽና እኔ የተገናኘነው እዚህ ቤት ውስጥ ነው:: ሌላውን ሰፊ ሐተታና ዝብዝብ እንተወውና ከእኔ እንዳረገዘች ከዚህ ቤት ተባረረች። አነሆ እኔና እርሷ ከተፋቀርን ከስምንት ዓመታት በላይ ሆኗል» ብዬ ዝም ስል «ቀጥል! ተርክ!» ብሎ አንባረቀ፡፡
«ካንተ ቀደም ብለው ይህ ልጅ ልጂ መሆኑን የሰሙት የነባር
ምስጢሩንም ሥረ መሠረት የሚያውቁት እናቴና አጎቴ ናቸው። በከንቱ ልማዳዊ እምነት ታፍኜ ይህን መልካሙንና አስፈላጊውን ጉዳይ እንደ ነውር ቆጥሬ
ትክከለኛ የነበረውንና ያልነበረውንም ድርጊቴን አምቄው ኖሬያለሁ፡፡ አሁን ግን እውነት ራሷ ለመሰማትና ይፋ ለመውጣት በውስጤ በመብላላቷና በመብሰሷ እነሆ ይኸው አሁን በማስረዳት ላይ ነኝ፡፡ ይህ ልጅ የተረገዘው እዚህ ቤት ውስጥ
ነበር፡፡ ስለ አስተዳደጉ ግን ደረጃ በደረጃ እነግርሃለሁ:: ቆሞ ለመሔድ መዳህ ያስፈልጋል» ብዬ ንግግሬን እልባት ሳላደርግበት፥
«የት ነበር የተረዝው?» ብሎ መልሴን ለመስማት በሙሉ ስሜት
አሰፈሰፈ፡፡
«ደግሜ ላረጋግጥልሀ፤ እዚሁ ቤት ውስጥ!» ብዬ ወዲያውኑ ስለ መለስኩለት አጠገቡ የነበረውን አየር በፊቱ ስፋት ልክ ገፍቶ ወደ እናቴ ዞረ።
«የሚለውን ሰማሽ? ጉድሽ ተዘከዘከ! እውነት ከሆነ እውነት ነው በይ! ከዚህ ከዝብርቅርቅ ነገር ገላግይኝ፡ እዚህ ቤት ነገር አለ፡፡ ይኸ ዝም ዝም አያዛልቅም! ማን ነች በእርግዝናዋ ጊዜ ከዚህ ቤት የተባረረች? አውጡ! ተናገሩ!» ብሎ ቤቱን በቁጣ አናጋው::
የውብነሽ ውስጥ ውስጡን ከተጫናት ሐሳብ በድንጋጤ ባነነች፡፡ ፍርሃት አፈፍ አደረጋትና ጥቂት ወደ ኋላ አፈገፈገች።
እናቴ ጻእረ ሞት የተናነቀው ሰው መሰለች፡፡
የእኔ ሕሊና እያደር ሰላ፡፡ «እኔው ልናገር! እኔው ላስረዳ!» ብዬ
በሰፊው ለመናገር ወጠን ሳደርግ «በቃህ! ማን ጠየቀህ! ከልኩ የተረፈ ምላስ አላቸው፡፡ የእነርሱ መንታ ምላስ ምን ሆነና? ሾል ሾል አበዛህ! ከልኩ አለፈ!»
ብሎ ኩም አደረገኝ፡፡ የእናቴ ከንፈሮች በትንቅንቅ አንደሚከፈት አሮጌ የብረት በር ቀስ ብለው ከተላቀቀ በኋላ በፍርሃት የተስረቀረቁ ቃላት ማሰማት ጀመረች።
«ነገር ወዲያ ወዲህ ሆኖ አስቸግሮኝ ነው እንጂ የሱ ልጅ መሆኑን ካወቅሁ ይኸው ሁለት ሳምንት ሆነኝ፡፡ ልጁ ነው፡፡ ያቺ ያነዬ እዚህ ቤት ትሠራ
የነበረችው ሠራተኛችን እኛ ሳናውቅና ሳንሰማ ለካ ውስጥ ውስጡን» ብላ ተይው በቃሽ! አርደሽኛል! ገድለሽኛል! በቁሜ
ቀብረሽኛል!» ብሎ ከንፈሩን ነክሶ አቀረቀረ።
«ታዲያ ኑራ ኑራ የስንት ወር ነው ወንድሜ... ነፈሰ ጡር ከሆነችና ሆዷ ከለየ በኋላ ከጌታነህ ማርገዟን ቤት ዘግተን አስለፍልፈን ሰማን» ብላ ተነሣች።
ቀስ ብዬ ጋሻዬነህን በእጄ ጠቀስኩትና አጠገቤ መጥቶ ቆመ፡፡ «እግዚኦ የሰው ልብ! አንቺ አረመኔ! አንቺ ጨካኝ! ለምን
አልነገርሽኝም? ለምን ደበቅሽኝ? አንቺማ አልሠራም አልታዘዝም” ብላ በመጥገቧ አባረርኳት ነበር ያልሽኝ፡፡ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ይይልሽ! » ብሎ በደም ፍላት
ራሱን ነቀነቀ። የተለኮሰውን የትግል ችቦ አጥብቄ ያዝኩት፡፡ የእናቴና የየውብነሽ ሁኔታ በመጠኑ ስሳሳዘነኝ ምንም እንኳ እናቴ የምታምንበትን ሁሉ
የማላምንበትና የማልመራበት ቢሆንም የራሷንና የቤተሰባችንን የኖረ ክብር ስምና ዝና ለመጠበቅ ከፍተኛ ፍላጎት ስላላት በእርሷ ኣስተሳሰብ ማናቸውም
የቤተሰባችን ሰው ተልከስክሶ እንዲገኝ አትፈልግም፡፡ እኔ ግን አሁንም በግልጽ ልናገር! በሰዉ ልጅ እኩልነት ላይ ያላችሁን ፍፁም የተሳሳተ እምነት አላምንበትም! የእናቴንና የቤተሰቤን ፍላጎት ተጋፍቼና ጥሼ ማድረግ
'የማይገባኝን' ነገር ሁኔታው በማይፈቅድልኝና በማይደግፈኝ አካባቢ በመፈጸሜ ስሕተተኛ ነህ እባል ይሆናል፡፡ እኔ ግን አይደለሁም፡፡ የማላምንበትን ሁሉ
አልቀበልም፡፡ ተገዢነቷ ምክንያት ሆኖ ላደረስኩባት በደል በሕግና በሕሊና ችሎት ተጠያቂው እኔ ነኝ፡፡ ከዚህ በኋላ ግን እምነታችሁን ስለማላምንበትና ጨቋኝና ረጋጭ የሆነ ልማድና እምነትንም ስለማልቀበል ወንጀለኛ አይደለሁም ብዬ በመጠኑ ጊዜያዊ የመላቀቂያ ድጋፍ ሰጠኋቸው።» አባቴ ዐይኑን በርበሬ አስመስሎና ግንባሩን አኮፋትሮ «ያም ሆነ ይህ እስካሁን ድረስ የለፈለፍከው ምንም የሚጨበጥ ቁም ነገር የለበትም» ብሎ ጉልበቱን በቡጢ ደወለው።
«አዎ ከአንተ እምነት ውጪ የሆነ
በመሆኑ በቀላሉ አይጨበጥልሀም፡፡ ልብ ብለህ ስማኝ! ማንኛውም ጤነኛ ሰው በተለይም በወጣትነቱ ጊዜ ሥጋዊ ፍላጎትና ፍቅር ባንድ ላይ ተጣምረው እንደሚይዙትና
እንደሚያጠቁት የታወቀ ነው፡፡ ይህ የተፈጥሮ ሕግ ጊዜውን ጠብቆ ደርሶኛል።ያን ጊዜ ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃዋን ሳይሆን ወበቷን እድንቄና ከፈቃዱም
እንደማትወጣ ተማምኜ አግባባኋት፡፡ በሁኔታዎች የተከበበ ውስጣዊ ግዴታ ባማናትም ፍቅራዊ ግፊትና ውዴታም ነበራት» ብዩ ሐሳቡን ለማወቅ ዝም አልኩ፡፡
«ለምኑ ብላችሁ ነው፣ አሁን የምትጨቃጨቁት እኮ እንዲያው ነው፡፡ምነው አንተ ዝም ብትል ልጄ? አባትህም ሲሆን ይኸው ይኸን ሰሞን ጤና አላገኘም፡፡ ያመከረኛ የደም ብዛቱ እየተነሣ ቁም ስቅሉን ያሳየዋል፡፡ ምነው
የሚልህን ብትሰማ፡ ምነው እንደ ዱሮህ ይሁን ይሁን” ብትለው::»
በንግግሬ የተደሰተ ይመስል «ቀጥል፤ አብራራልኝ! አሁን ልንገናኝ ነው!» ብሎ እንድቀጥል አዘዘ። አሳርፍ እንደ ተባለ ወታደር እጅ እግሬን አፍታትቼ ተዝናናሁ፡፡
«የእኔና የእርሷ የጋራ ሥጋዊ ፍላጎት ውጤት በማሕፀኗ ውስጥ
እርግዝናን አስከተለ፡፡ ከዚያ በኋላ ነበር እናቴ ያን በአእምሮዎ ውስጥ ተዳፍኖ የኖረውን እምነቷን ይዛ በመነሣት የትውልዳችንን ክብርና ዝና ጨዋነትና ትልቅነት አስከብራለሁ በማለት በእርግዝናዋ ጊዜ ያባረረቻት። ያም ሆነ ይህ ሲወርድ ሲዋረድ መጥቶ በወረሰችው የተሳሳተ እምነት ተገድዳ የፈጸመችው
ስሕተት በመሆኑ እርሷ ብቻዋን በደለኛ አይደለችም፡፡ የስሕተቱ ቅርንጫፍ ሳይሆን ሥርና ምንጩን መቁረጥና መድፈን ያስፈልጋል፡፡ አንድን ሰው ብቻ መወንጀል ግን ከበሽታ ጠንቆች መካከል አንዷን ብቻ እንደ መግደል ይቆጠራል፡፡
ለወዲያነሽ ያለኝ ፍቅራዊ ታማኝነት ምንጊዜም ቢሆን የማይቀነስና በማንም የተቃውሞ አስተያየት የማይሻር ነው ! » አልኩና በዕለቱ ከሚፈፀመው ጉዳይ ውስጥ አብዛኛውን በድፍረትና በጥንቃቄ አጋመስኩት።
የአባቴ ንዴት ናረ፡፡ ወደ እናቴ ዞር ብሉ «ኧረ ይቺ የወዲያነሽ
የሚላትና እንዲህ የምታስወተውተው ማን ነች? የመቼዋ ነች? እስኪ ደኅና
አደርግሽ ንገረኝ? ምን ይለጉምሻል» አለ። እናቴ በፍርሃት ወለል ወለሉን እያየች «ያነዬ ነው ቆይቷል አንዲት ጠይም መልከ ቀና እዚህ እኛ ጋ አልነበረችም እንዴ? አንተ እንኳ ረጋ ያለች
ደርባባ ነች” ብለህ አመስግነሃት አልነበረም እንዴ? እሷን ነዋ የሚልህ። ከሷ ጋር ነው ይኸ ሁሉ» ብላ ወደ ዝምታዋ ተመለሰች። የአባቴ ዐይኖች ተውዘግዝገው
ጋሻዬነህ ላይ ተተከሉ። «እረግ! እረግ! እረግ! ተይው ተይው! አገኘኋት! ይኸ ልጅ የተወለደው ከእርሷ ነው ማለት ነው?» ብሎ ከሁላችንም መልስ ጠበቀ።
👍5❤1
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....በዚህ ላይ ደግሞ አቶ አባይነህ ስራቸው ተጋልጦ ከሥልጣናቸው ዝቅ እንዲሉ ምክንያት በመሆኑ እያቶኮቶኩ ነገር ያቀጣጥላሉ።
እውነትህን ነው ይሄ ጦሰኛ ጦሳችንን ይዞ ካልሄደ በስተቀር ምን ሰላም እናገኛለን?!” በማለት ብሶቱን ያባብሳሉ፡፡ በዚህ ምክንያት የምረቃ በአሉ ለጌትነት ለቤተሰቦቹና ለወዳጅ ዘመዶቹ ልዩ የደስታ ቀን ሆኖ ሲውል
ለልኡልሰገድ ግን መርዶ ነው የሆነበት። ይህንን መጥፎ ስሜቱን ለማብረድ ደግሞ ሰሞኑን ሲሯሯጥ ሰንብቷል። ትጉህ ሰራተኛነቱ እንኳንስ አብረውት በሚሰሩ የስራ ባልደረቦቹ ቀርቶ በሚጠሉት ሰራተኞች ጭምር
የታወቀ ነው፡፡ ዲግሪውን ይዞ ሲመጣ ያንን እንደቀላዋጭ ውሻ ከንፈሩን እየላሰ ሲጎመዥለት የኖረውን የሂሳብ ዋና ክፍል ሃላፊ ቦታ እንደ ሚወስደው የታወቀ ነው፡፡ በሱ እምነት ያንን እድገት ለማግኘት ጌትነት ከዚያ አካባቢ ገለል ማለት አለበት።እሱ ገለል እስካላለ ድረስ ሊረጋጋ አይችልም፡፡ አንዳንዱ ሰው እድገት ለማግኘት ሲል ከፊት ለፊቱ የቆመው ሰው በሆነ ምክንያት ገለል እንዲልለት ይመኛል። ፀሎት ያደርሳል፡በዚህ የተነሳ ከፊት ለፊቱ በሚታየው የተስፋ ጭላንጭል ላይ የተንጠለጠለ የምኞት እስረኛ ሆኖ ይቀራል።ከጭላንጭሉ በስተጀርባ ዕድል ደማቅ የብርሃን ውጋጋኗን አብርታ እየጠበቀችው መሆኑን በፍጹም አያስብም፡፡ በፈጠራት ጠባብ ዓለም ውስጥ ራሱን ወስኖ በማስቀረት ለትንሹ
ነገር ሲጓጓ የሱ የነበረው ትልቁና መልካሙ ነገር በድቅድቁ ጨለማ
ውስጥ ተውጦ ይቀራል። ልኡልሰገድም ተምሮ ራሱን በመለወጥ ከዚያ የተሻለ ወፍራም እንጀራ መብላት ሲችል የተመኛትን ትንሽ ሹመት እንዳይቀማው በመስጋት የጌትነትን ሞት ተመኘ፡፡ በምረቃ ስነ ስርአቱ ላይም ሳይገኝ ቀረ። ጌትነት አለቃው በጥሪው ቦታ ሳይገኝ በመቅረቱ ቅር ቢለውም ጥሪውን አክብረው የመጡ ጓደኞቹ እቅፍ አበባ እያበረከቱ ሲስሙት ተፅናና፡፡ እናቱን እቅፍ እያደረገ ከአማረች እና ከቤተሰቦቿ ጋር እንደዚሁም ከትምህርት ቤት ጓደኞቹና ከሽመልስ ጋር በርከት ያሉ ፎቶ
ግራፎችን ተነሱ፡፡ እናቱ እጮኛነቷን ባታውቅም የልጇ ፍቅረኛ መሆን
ዋን ገምታ ከአማረች ጋር በፍቅር እየተቃቀፈች በርከት ያሉ የማስታወሻፎቶግራፎችን ስትነሳ ዋለች::
የፎቶ ግራፍ ስነ ስርአቱ እንዳበቃ ጥሪውን አክብረው በመጡ ጓደኞቹ ታጅቦ ከእናትና ከእህቱ ጋርም ተያይዘው ወደ መኖሪያ ቤቱ ሄዱ። ጌትነት እምብዛም በማይወደው ሰፈር ውስጥ የተከራያት ጎጆውን የወደዳት ገና ዛሬ ነው፡፡ ዛሬ ከጓደኞቹና ከሚወዳቸው ቤተሰቦቹ ጋር ደማቅ የደስታ ጊዜ እያሳለፈባት ነውና ሰፈሩን ዘንግቶ ጎጆውን ቢወድ የሚደንቅ አይሆንም ጌትነት የተከራያት ቤት መሀሏ በመጋረጃ ተከፍሎ ከመጋረጃው ውስጥ
አንድ ሰፊ የሞዝቮልድ አልጋና ዘይኑ የምትተኛበት አንድ ታጣፊ
አልጋ አለ፡፡ የወዲህኛው ክፍል በሳሎንነት የሚጠቀሙበት ሲሆን አንድ ትልቅ ጠረጴዛና አራት የእንጨት ወንበሮች መሀል ላይ ጉብ ብለዋል።
ከጥግ ላይ አንድ አግዳሚ ወንበር አለ፡፡ ቤቱ ከውጭ እንደሚታየው
አይደለም፡፡ በዘይኑ ከፍተኛ ጥንቃቄና ጥረት ፅዳቱ ተጠብቆ ያምራል።
ዘይኑና እናቷ ላባቸውን ጠብ አድርገው የጠመቁት ጠላ ከውስኪ ያስንቃል።
"በሉ አረፍ በሉ!" አለች የጌትነት እናት ለመስተንግዶው ተፍ ተፍ
እያለች። ጌትነት ግን ልቡ ወደ አማረች በሯል። የሱን ደሳሳ ጎጆ የምታያት ዛሬ ነበር፡፡ከወዳጅ ዘመዱ ጋር በይፋ የሚያስተዋውቃትና በቅርቡ
የሚያገባት እጮኛው መሆንኗ የሚያበስርበት ቆንጆ አጋጣሚ ዛሬ በደስታው ቀን ነበር፡፡ ግን ምን ያደርጋል? እሷም ተመራቂ ነችና በወላጆቿ ቤት ከሠርግ መልስ ግብዣ ተደርጎ ዓለም እየታየ በመሆኑ አልተቻለም፡፡
“ሰውዬው በል እንጂ ምሳችንን ቶሎ አስቀርብልን፡፡ አንተ ልብህ ወዴት እንደኮበለለ አውቄዋለሁ"ባልቻ እየሳቀ በነገር ወጋ አደረገው፡፡
"አንተ ቡዳ! ምንድነው የምታውቀው ደግሞ?" እሱም ሳቀና ጎሽመው ባልቻ የአማረችና የጌትነትን ፍቅርን ጠንቅቆ የሚያውቅ የትምህርት ቤት
ጓደኛው ነው።እሱም የሚቀጥለው ዓመት ተመራቂ ነው፡፡
“ዘይንዬ! እባክሽ ገላግይኝ ሰዎቹ ጠላው አናታቸው ላይ እየወጣ ነው መስለኝ ምሳ! ምሳ!! ቶሎ በይ!” አለና ዘይኑን ተጣራ። ዘይኑ ከእናቷ ጋር ተጋግዛ በፍጥነት ምሳ አቀረበችና መመገብ ጀመሩ።
"እንግዲህ እርስዎም እዚሁ ከልጆችዎ ጋር መጠቃለል አለብዎት እማማ በመመላለስ ይጎዳሉ..." አለ ዘበነ፡፡
“አይ የኔ ልጅ እዚህ ከልጆቼ ጋር መቀመጡን ጠልቼው መሰለህ ? ደስታውን አልችለውም ነበር፡፡ እነሱን ተለይቼ የምኖረው ኑሮ አይደለም፡፡
በሬሳ ውስጥ አስሮ ያስቀመጠኝ የሟች አባታቸው ቃል ነው "
“እንዴ?! ለምን?” ባልቻና ዘበነ በአንድ ላይ ጠየቁ፡፡
“መኩሪያ አሁን ያለሁበትን ቤት ተአባቱ የወረሰው ነው። የአባቱ አስክሬን ከወጣበት ቤት ነው የሱም የወጣው፡፡ ታዲያ ሊሞት ሲያጣጥር ከዚች ቀዬ ንቅንቅ እንዳትይ መታመሚያሽ፣ መሞቻሽ መቀበሪያሽ እዚች ጎጆ እዚች መንድር ውስጥ ይሁን አደራ! ብሎ አስሮኝ ነው ያረፈው"
በሬሳን መልቀቅ የማትችልበትን ምክንያት አጫወተቻቸው። ለነገሩ በመኩሪያ ቃል አሳበበች እንጂ ያቺን ጎጆ መልቀቅ የማትፈልግበት እንዲህ ነው ብላ ልትገልፀው የማትችለው የራሷ ምክንያት ነበራት፡፡ጌትነት ሽመልስን ለእናቱ ሲያስተዋውቃት "እማዬ ሽመልስ ማለት እሱ ነው በህይወቴም ሆነ በህይወታችን ውስጥ ታላቅ ለውጥን ያስገኘልን ወንድሜ ነው፡፡
ስለ እውነት ሲል የተሟገተ፡፡ የገባውን ቃል ያከበረ.." ቃላት አጥረውት ስለ ሽመልስ ማንነት ገለፀላት፡፡
“እሰይ! እስይ! እግዚአብሔር የሱንም ኑሮ እንደዚሁ ያሳምርለት። ለሰው ደግ መስራት ከምድር ባይገኝ እሱ ፈጣሪ ውለታውን በሰማይ ይከፍለዋል" ሽመልስን አመሰገነችለት፡፡ በዚህ ሁኔታ በተሰባስቡ ወዳጅ ዘመዶቹና ጎረቤቶቹ የጌትነት ቤት ተጣባ ደስታውን ተደስተው ፅዋቸውን
እያነሱ ሲያጋጩ ሲጫወቱ ሲጨፍሩ ዋሉ.....
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የወይዘሮ ባንቺደሩ ጎጆ የሞት ጥላ እያንዣበበባት ነው። ጨካኙ
ሞት ህፃን፣ አዋቂ፣ ሴት፣ ወንድ አይመርጥም፡፡ እንደ ቋያ እሳት ያገ
ኘውን በእጁ የወደቀለትን ሁሉ እየበላ እያኘከ መሄድ ነው። ምህረት የለም፡፡ አሮጊቷ ወይዘሮ ባንቺደሩ በአንድ በኩል የዕድሜ ጫና በሌላ በኩል ደግሞ የሙት ልጆችና እናታቸው ጥላቸው የኮበለለች ሁለት ህፃናትን ለማሳደግ መከራቸውን እያዩ ናቸው፡፡ የአያትነት ግዴታ በላያቸው ወድቆ በስተርጅና የልጃቸውን ልጆች በህይወት ለማቆየት ብዙ ደከሙ፡፡ በበሽታ ክፉኛ የተደቆሰው ምትኬ እናቱንና አባቱን ክፉኛ እየናፈቀ አባቱን በአካል ሲያጣው እየተሳቀቀ እናቱ እንደ ድሮው እንድትሆንለት እየተመኘ እናቱ ስትጨክንበት፣ ሀሳብ አደቀቀውና፣ ተሳቀቀና ለጋ
የህፃንነት አዕምሮው በሀዘን ቆስለ። ቀስ በቀስ እየመነመነ በሽተኛ እየሆነ ሄደ፡፡ አሮጊቷ በአብዛኛው የሚሰጡት ርዳታ እንባቸውን ማፍሰስ ብቻ
ነበር። "አብዬ የኔ ጌታ አይዞህ!...እኔ ልጨነቅ. እኔ ልጠበብ እህ!...”ምትኬ ግን በሳቸው እንባ ሊጠነክርና ሊለመልም አልቻለም፡፡
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....በዚህ ላይ ደግሞ አቶ አባይነህ ስራቸው ተጋልጦ ከሥልጣናቸው ዝቅ እንዲሉ ምክንያት በመሆኑ እያቶኮቶኩ ነገር ያቀጣጥላሉ።
እውነትህን ነው ይሄ ጦሰኛ ጦሳችንን ይዞ ካልሄደ በስተቀር ምን ሰላም እናገኛለን?!” በማለት ብሶቱን ያባብሳሉ፡፡ በዚህ ምክንያት የምረቃ በአሉ ለጌትነት ለቤተሰቦቹና ለወዳጅ ዘመዶቹ ልዩ የደስታ ቀን ሆኖ ሲውል
ለልኡልሰገድ ግን መርዶ ነው የሆነበት። ይህንን መጥፎ ስሜቱን ለማብረድ ደግሞ ሰሞኑን ሲሯሯጥ ሰንብቷል። ትጉህ ሰራተኛነቱ እንኳንስ አብረውት በሚሰሩ የስራ ባልደረቦቹ ቀርቶ በሚጠሉት ሰራተኞች ጭምር
የታወቀ ነው፡፡ ዲግሪውን ይዞ ሲመጣ ያንን እንደቀላዋጭ ውሻ ከንፈሩን እየላሰ ሲጎመዥለት የኖረውን የሂሳብ ዋና ክፍል ሃላፊ ቦታ እንደ ሚወስደው የታወቀ ነው፡፡ በሱ እምነት ያንን እድገት ለማግኘት ጌትነት ከዚያ አካባቢ ገለል ማለት አለበት።እሱ ገለል እስካላለ ድረስ ሊረጋጋ አይችልም፡፡ አንዳንዱ ሰው እድገት ለማግኘት ሲል ከፊት ለፊቱ የቆመው ሰው በሆነ ምክንያት ገለል እንዲልለት ይመኛል። ፀሎት ያደርሳል፡በዚህ የተነሳ ከፊት ለፊቱ በሚታየው የተስፋ ጭላንጭል ላይ የተንጠለጠለ የምኞት እስረኛ ሆኖ ይቀራል።ከጭላንጭሉ በስተጀርባ ዕድል ደማቅ የብርሃን ውጋጋኗን አብርታ እየጠበቀችው መሆኑን በፍጹም አያስብም፡፡ በፈጠራት ጠባብ ዓለም ውስጥ ራሱን ወስኖ በማስቀረት ለትንሹ
ነገር ሲጓጓ የሱ የነበረው ትልቁና መልካሙ ነገር በድቅድቁ ጨለማ
ውስጥ ተውጦ ይቀራል። ልኡልሰገድም ተምሮ ራሱን በመለወጥ ከዚያ የተሻለ ወፍራም እንጀራ መብላት ሲችል የተመኛትን ትንሽ ሹመት እንዳይቀማው በመስጋት የጌትነትን ሞት ተመኘ፡፡ በምረቃ ስነ ስርአቱ ላይም ሳይገኝ ቀረ። ጌትነት አለቃው በጥሪው ቦታ ሳይገኝ በመቅረቱ ቅር ቢለውም ጥሪውን አክብረው የመጡ ጓደኞቹ እቅፍ አበባ እያበረከቱ ሲስሙት ተፅናና፡፡ እናቱን እቅፍ እያደረገ ከአማረች እና ከቤተሰቦቿ ጋር እንደዚሁም ከትምህርት ቤት ጓደኞቹና ከሽመልስ ጋር በርከት ያሉ ፎቶ
ግራፎችን ተነሱ፡፡ እናቱ እጮኛነቷን ባታውቅም የልጇ ፍቅረኛ መሆን
ዋን ገምታ ከአማረች ጋር በፍቅር እየተቃቀፈች በርከት ያሉ የማስታወሻፎቶግራፎችን ስትነሳ ዋለች::
የፎቶ ግራፍ ስነ ስርአቱ እንዳበቃ ጥሪውን አክብረው በመጡ ጓደኞቹ ታጅቦ ከእናትና ከእህቱ ጋርም ተያይዘው ወደ መኖሪያ ቤቱ ሄዱ። ጌትነት እምብዛም በማይወደው ሰፈር ውስጥ የተከራያት ጎጆውን የወደዳት ገና ዛሬ ነው፡፡ ዛሬ ከጓደኞቹና ከሚወዳቸው ቤተሰቦቹ ጋር ደማቅ የደስታ ጊዜ እያሳለፈባት ነውና ሰፈሩን ዘንግቶ ጎጆውን ቢወድ የሚደንቅ አይሆንም ጌትነት የተከራያት ቤት መሀሏ በመጋረጃ ተከፍሎ ከመጋረጃው ውስጥ
አንድ ሰፊ የሞዝቮልድ አልጋና ዘይኑ የምትተኛበት አንድ ታጣፊ
አልጋ አለ፡፡ የወዲህኛው ክፍል በሳሎንነት የሚጠቀሙበት ሲሆን አንድ ትልቅ ጠረጴዛና አራት የእንጨት ወንበሮች መሀል ላይ ጉብ ብለዋል።
ከጥግ ላይ አንድ አግዳሚ ወንበር አለ፡፡ ቤቱ ከውጭ እንደሚታየው
አይደለም፡፡ በዘይኑ ከፍተኛ ጥንቃቄና ጥረት ፅዳቱ ተጠብቆ ያምራል።
ዘይኑና እናቷ ላባቸውን ጠብ አድርገው የጠመቁት ጠላ ከውስኪ ያስንቃል።
"በሉ አረፍ በሉ!" አለች የጌትነት እናት ለመስተንግዶው ተፍ ተፍ
እያለች። ጌትነት ግን ልቡ ወደ አማረች በሯል። የሱን ደሳሳ ጎጆ የምታያት ዛሬ ነበር፡፡ከወዳጅ ዘመዱ ጋር በይፋ የሚያስተዋውቃትና በቅርቡ
የሚያገባት እጮኛው መሆንኗ የሚያበስርበት ቆንጆ አጋጣሚ ዛሬ በደስታው ቀን ነበር፡፡ ግን ምን ያደርጋል? እሷም ተመራቂ ነችና በወላጆቿ ቤት ከሠርግ መልስ ግብዣ ተደርጎ ዓለም እየታየ በመሆኑ አልተቻለም፡፡
“ሰውዬው በል እንጂ ምሳችንን ቶሎ አስቀርብልን፡፡ አንተ ልብህ ወዴት እንደኮበለለ አውቄዋለሁ"ባልቻ እየሳቀ በነገር ወጋ አደረገው፡፡
"አንተ ቡዳ! ምንድነው የምታውቀው ደግሞ?" እሱም ሳቀና ጎሽመው ባልቻ የአማረችና የጌትነትን ፍቅርን ጠንቅቆ የሚያውቅ የትምህርት ቤት
ጓደኛው ነው።እሱም የሚቀጥለው ዓመት ተመራቂ ነው፡፡
“ዘይንዬ! እባክሽ ገላግይኝ ሰዎቹ ጠላው አናታቸው ላይ እየወጣ ነው መስለኝ ምሳ! ምሳ!! ቶሎ በይ!” አለና ዘይኑን ተጣራ። ዘይኑ ከእናቷ ጋር ተጋግዛ በፍጥነት ምሳ አቀረበችና መመገብ ጀመሩ።
"እንግዲህ እርስዎም እዚሁ ከልጆችዎ ጋር መጠቃለል አለብዎት እማማ በመመላለስ ይጎዳሉ..." አለ ዘበነ፡፡
“አይ የኔ ልጅ እዚህ ከልጆቼ ጋር መቀመጡን ጠልቼው መሰለህ ? ደስታውን አልችለውም ነበር፡፡ እነሱን ተለይቼ የምኖረው ኑሮ አይደለም፡፡
በሬሳ ውስጥ አስሮ ያስቀመጠኝ የሟች አባታቸው ቃል ነው "
“እንዴ?! ለምን?” ባልቻና ዘበነ በአንድ ላይ ጠየቁ፡፡
“መኩሪያ አሁን ያለሁበትን ቤት ተአባቱ የወረሰው ነው። የአባቱ አስክሬን ከወጣበት ቤት ነው የሱም የወጣው፡፡ ታዲያ ሊሞት ሲያጣጥር ከዚች ቀዬ ንቅንቅ እንዳትይ መታመሚያሽ፣ መሞቻሽ መቀበሪያሽ እዚች ጎጆ እዚች መንድር ውስጥ ይሁን አደራ! ብሎ አስሮኝ ነው ያረፈው"
በሬሳን መልቀቅ የማትችልበትን ምክንያት አጫወተቻቸው። ለነገሩ በመኩሪያ ቃል አሳበበች እንጂ ያቺን ጎጆ መልቀቅ የማትፈልግበት እንዲህ ነው ብላ ልትገልፀው የማትችለው የራሷ ምክንያት ነበራት፡፡ጌትነት ሽመልስን ለእናቱ ሲያስተዋውቃት "እማዬ ሽመልስ ማለት እሱ ነው በህይወቴም ሆነ በህይወታችን ውስጥ ታላቅ ለውጥን ያስገኘልን ወንድሜ ነው፡፡
ስለ እውነት ሲል የተሟገተ፡፡ የገባውን ቃል ያከበረ.." ቃላት አጥረውት ስለ ሽመልስ ማንነት ገለፀላት፡፡
“እሰይ! እስይ! እግዚአብሔር የሱንም ኑሮ እንደዚሁ ያሳምርለት። ለሰው ደግ መስራት ከምድር ባይገኝ እሱ ፈጣሪ ውለታውን በሰማይ ይከፍለዋል" ሽመልስን አመሰገነችለት፡፡ በዚህ ሁኔታ በተሰባስቡ ወዳጅ ዘመዶቹና ጎረቤቶቹ የጌትነት ቤት ተጣባ ደስታውን ተደስተው ፅዋቸውን
እያነሱ ሲያጋጩ ሲጫወቱ ሲጨፍሩ ዋሉ.....
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የወይዘሮ ባንቺደሩ ጎጆ የሞት ጥላ እያንዣበበባት ነው። ጨካኙ
ሞት ህፃን፣ አዋቂ፣ ሴት፣ ወንድ አይመርጥም፡፡ እንደ ቋያ እሳት ያገ
ኘውን በእጁ የወደቀለትን ሁሉ እየበላ እያኘከ መሄድ ነው። ምህረት የለም፡፡ አሮጊቷ ወይዘሮ ባንቺደሩ በአንድ በኩል የዕድሜ ጫና በሌላ በኩል ደግሞ የሙት ልጆችና እናታቸው ጥላቸው የኮበለለች ሁለት ህፃናትን ለማሳደግ መከራቸውን እያዩ ናቸው፡፡ የአያትነት ግዴታ በላያቸው ወድቆ በስተርጅና የልጃቸውን ልጆች በህይወት ለማቆየት ብዙ ደከሙ፡፡ በበሽታ ክፉኛ የተደቆሰው ምትኬ እናቱንና አባቱን ክፉኛ እየናፈቀ አባቱን በአካል ሲያጣው እየተሳቀቀ እናቱ እንደ ድሮው እንድትሆንለት እየተመኘ እናቱ ስትጨክንበት፣ ሀሳብ አደቀቀውና፣ ተሳቀቀና ለጋ
የህፃንነት አዕምሮው በሀዘን ቆስለ። ቀስ በቀስ እየመነመነ በሽተኛ እየሆነ ሄደ፡፡ አሮጊቷ በአብዛኛው የሚሰጡት ርዳታ እንባቸውን ማፍሰስ ብቻ
ነበር። "አብዬ የኔ ጌታ አይዞህ!...እኔ ልጨነቅ. እኔ ልጠበብ እህ!...”ምትኬ ግን በሳቸው እንባ ሊጠነክርና ሊለመልም አልቻለም፡፡
#ያልታበሱ_እንባዎች
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
.....የምትለቀቀውማ እንደ ነገሩ ሁኔታ ዋስ ጠርተህ ነው» አለው መርማሪው ፖሊስ፣ ነገሩ የዕለት ግጭት በመሆኑ ብዙም ርቀት በማይሄድ ምርመራ እንደሚጠናቀቅ መርማሪው
ያስባል። የጠረጴዛ ደወል
አቃጨለና ረዳቱ ፖሊስ ሲቀርብለት ዓለሙን ወስዶ መብራቴ ባዩ የተባለ ሌላ
እስረኛ እንዲያቀርብለት አዘዘው።
ረዳቱም የተባለውን ፈፀመ፡
መብራቴ ባዩም በዕድሜው ብዙ አልገፋም ፣ ከሠላሳ ብዙ አያልፈውም፡፡ቀጠን ያለ ቀይ ዳማ ቢጤ ነው። መካከለኛ ቁመት አለው፡፡ ፀጉሩ አጠር፣ ከወደ አፉ
ሞጥሞጥ፣ ዓይኖቹ አነስ እነስ ያሉ ናቸው። እሱም በተመርማሪ ወንበር ላይ ተቀምጦ መርማሪውን በፍርሀት ይመለከተው ጀመር።
መርማሪው ፖሊስ ልክ በዓለሙ ላይ እንዳደረገው ሁሉ መብራቴን
መሠረታዊ መረጃዎችን እየጠየቀ ከመዘገበ በኋላ፡ «ከዓለሙ መርጋ ጋር ከአሁን በፊት ትተዋወቃላችሁ?» ሲል በቅድሚያ ጠየቀው።
«አይቸውም አላውቅ::»
«ምን አጣላችሁ ታዲያ?»
«እኔ ቀድሜ ገብቼ ባለሁበት ቤት መጥቶ ካልወጣህ ብሎ ሊያሳገድደኝ ሞከረ። አልወጣም ስለው በተቀመጥኩብት በጥፊ አቃጠለኝ ከዚያ በኋላ ነው
በደመነፍስ እጆቹን ይዤ ድረሱልኝ ብዬ የጮኩት።» አለው አይኖቹን እያቁለጨለጨ።
«በተጣላችሁበት ቤት ውስጥ ለምን ነበር ቀድመህ የገባኸው?»
«ቤቴ ነዋ!»
«ቤቴ ስትል? ሴትዮዋ ሚስትህ ናት?»
«ያው እንደ ሚሲቴ ናተ።»
«ለምን ያህል ጊዜ አብራችሁ ቆይታችኋል?»
«አረ ብዙ ነው።»
«እኮ በግምት?»
«ከአስራ አምስት ቀን በላይ አብረን አድረናል። ግን በተከታታይ
አደለም አልፎ አልፎ ነው፡፡ ከተዋወቅን ግን ቆይተናል፡፡»
«ወዳጅህ ስሟ ማን ይባላል?»
እየተገረመ ጠየቀው።
«ስሟ?»አለና መብራቴ ወደ ጣሪያ አንጋጠጠ፡፡ ግን ጠፋበት፡ ለማሰላሰል ሞከረና ሲያቅተው «ረሳሁት።» አለ የድንጋጤ ስሜት እየተነበበበት፡፡
«አሥራ አምስት ቀን ሙሉ የአቀፍካት ወዳጅህን» በማለት መርማሪው እየተገረመ ጠየቀው።
«በድንገት ስለሆነ የተገናኘነው ስሟ ይረሳኛል።»
መርማሪው ፖሊስ ጥርጣሬ ገባውና መብራቱን ትኩር ብሎ ተመለክተው።
መብራቴ የበለጠ የእፍረትና የድንጋጤ ስሜት ይነበብበት ጀመር።
«ዋሽተሃል አይደል?» አለው መርማሪው በትኩረት እየተመለከተው፡፡
«አጥፍቻለሁ ጌታዬ» አለ መብራቱ ሽቁጥቁጥ እያለ»
የመርማሪው ፖሊስ ልብ አሁንም እየተከረጢረ ሄደ ሆኖም ቃል
በያዘበት ወረቀት ላይ ከአስፈረመው በኋላ «የአንተንና የዓለሙን ጉዳይ በቀላሉ
ላለፈው አስቤ ነበር፡፡ ነገር ግን ተጠራጥሬአለሁ፡፡ የሁለታችሁንም ጉዳይ እንደገና
ኑነየው አልቀርም:: እለና ወደ እስር ቤት እንዲሄድ አሰናበተው፡፡
የመርማሪው ፖሊስ ጥርጣሬ ቀላል አልነበረም። ዓለሙን በሚጠይቅበት ወቅት ያያቸው ነነበሩ ሁኔታዎች እንደገና ትዝ አሉት። በስካር መንፈስ በአንዲት
ሴተኛ አዳሪ የተጣሉ መስለውት በእርግጥም ዋስ እያስጠራ በቀላሉ ሊሸኛቸው ነበር
አሳቡ:: አሁን ግን በጉዳዩ ላይ ጠለቅ ያለ ምርመራ ሊያደርግ ወሰነ። ለማንኛውም አለ በሆዱ
እስቲ ጋለሞታ የተባለችው ሴት ሌላ አጠራጣሪ ፍንጭ የምታወጣ
ከሆነ በቅድሚያ እሷን ላናጋግራት፡፡” አለና በረዳቱ ፖሲስ እንድትጠራ አደረገ።
ጋለሞታዋ ተጠርታ ወደ መርማሪው ፖሊስ ቢሮ በር ላይ ስትደርስ ሁለመናዋ በፍርሀት ይንቀጠቀጣል፡፡ እንባዋ ከዓይኗ ላይ እንደ በረዶ ይረግፋል።
መልኳ ደግሞ ይህ ቀረሽ የማትባል ወብ ናት። ዓይኖቿ እንደ ንጋት ኮከብ ያበራል። በዕድሜዋ ገና ወጣት ልጃገረድ ትመስላለች። “ጋለሞታ በሚለፈው የሴትነት መገለጫ አንዳች አመልካች ነገር አይታይባትም። ከንፈሮቿ እምቦጦች ይመስላሉ፡፡ የአፍንጫዋ አቀማመጥ ለቄንጥ የተሰራ ይመስላል። የቀይና ነጭ
ቡራቡራ ድሪያ ለብሳ በጡቶቿ ተገትሮ የአንጀቷን ድራሽ አጥፍቶታል።የመርማሪው ቢሮ በር ላይ ደርሳ ምን እንደምትባል ትዕዛዝ እየጠበቀች ሳለች
መርማሪው ፖሊስ ግን ይህንን ገፅታዋን ሲያይ ድንገት ተዘናግቶ ኖሮ ፐ! ይችስ ታደብድባለች አለ በሆዱ። ወዲያው ደግሞ «ምን ያስለቅስሻል?» ሲል ፈገግ ብሎ ጠየቃት ሁኔታዋ ሁሉ እያስገረመው። ግቢ ቁጭ በይ ማለቱን እንኳ እረሳው፡፡
«ፈርቼ» አለችው እንዳቀረቀረች::
«የሰራሽው ስራ አሳፈረሽ!»
«አረ እኔ ምንም አልሰራሁም!»
«እስቲ ግቢና ቁጭ በይ አላት» በእጁ አገጩን ያዝ አድርጎ አሁንም በትኩረት እየተመለከታት። ጋለሞታዋ ቁጭ አለችና አሁንም በፍርሃት ስሜት አቀርቅራ መሬት መሬት ታይ ጀመር።
«ምን አድርገሽ ነው የታሰርሽው?» ሲል ጠየቃት መርማሪው ፖላስ ቀስ እያለ ሊያግባባት ፈልጎ።
«ምንም» አለችና ለቅፅበት ያህል ቀና ብላ አየችው፡፡
«ዓለሙንና መብራቱን የት ነው የምታውቂያቸው?»
«እነማናቸው እነሱ?» አለች አሁንም፡፡ ለቅፅበት ያህል ቀና ብላ አይታው እንደገና እንጋቷን ደፋች::
«ጭራሽ አታወቂያቸውም?»
«አረ እኔ እንደዚህ የሚባሉ ሰዎች አላውቅም።»
«ሁለቱም ወዳጃችን ናት እያሉ እኮ ነው፡፡» አለና መርማሪው ከመቼውም ጊዜ ይበልጥ ለምላሿ ጓጉቶ ይጠባበቃት ጀመር፡፡
"ኣ"አለችና እሁንዎ ቀና ብላ አየት አረገችው፡፡
«ከማናቸውም ጋር አብረሽ አድረሽ አታውቂም?»
«እኔ ከወንድ ጋር ተኝቼ አላውቅም፡፡»
«አንድም ቀን?»
«አንድ ቀን ብቻ ከምወደው ሰው ጋር አድሬ አውቃለሁ፡፡ ግን ከንፈሬን ስሞታል እንጂ ሌላ ምንም አላደረገኝም::»
«ማነው እሱ ደግሞ?» ሲል ጠየቃት መርማሬው።
«እሱ እዚህ አገር የለም፣ ኤርትራ እሚባል አገር ከሄደ ቆይቷል፡፡»
«ኦ!» አለ መርማሪው ፖሊስ አንዳች የማያውቀው ስሜት መላ ሰውነቱን ድንገት ወርር እያረገው፡፡ «ማን ይባላል?» ሲል እንደገና ጠየቃት::
«አስቻለው ፍስሀ»
«አስቻለው ፍስህ ?» ሲል ደግሞ ጠየቃት፡፡
«አዎ፡፡» አለችውና እሷም ድንግጥ ብላ ቀና ብላ ታየው ጀመር፡፡
«እንዴ!» አለና «መርማሪው እንደገና አትኩሮ ያያት ጀመር። ስሜቱ እያደር ተለዋወጠ፡፡ አንቺ ስምሽ ማን ይባላል?» ሲል ጠየቃት የምትሰጠው መልስ ቀድሞ እያስፈራው።
«ሔዋን ተስፋዬ::»
«ምን?» ሰምቶ እንዳልሰማ፡፡
«ሔዋን ተስፋዬ እባላለሁ።»
መርማሪው ፖሊስ ፍዝዝ ብሎ ቀረ፡፡ የያዘው እስኪርቢቶ ከእጁ ላይ ሾልኮ ሲወድቅ ፈጽሞ አልታወቀውም፡፡ ዲላ ከተማ እየኖረ ስለመሆኑ እንደ አዲስ
ታወቀው፡፡ በሀሳብ ጥቅልል ብሎ አስመራ ከተማ ገባ፡፡
መርማሪው ፖሊስ የሀምሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ ይባላል። በሲዳሞ ክፍለ ሀገር በሀገረ ማሪያም ከተማ ተወልዶ ያደገ ነው። እዚያው በፖሊስነት ተቀጥሮ
እስከ ምክትል አሥር አለቅነት የደረሰና እሱም እንደ አስቻለው ፍሰሀ የዘመቻ ግዳጅ ተወስኖበት
ወደ ግንባር ዘምቶ በኤርትራ ምራባዊ የጦር ግንባሮች ለተከታታይ አምስት ዓመታት ሲዋጋ የቆየ ነው:: በጦር ግንባር የፈጸመው ጀብዱ የሀምሳ አለቅነት ማዕረግ ካገኘ በኋላ በቀጣይ የውጊያ ወቅት በደረሰበት ቁሰለት የተዋጊነት
ብቃቱ ቀንሶ ወደነበረበት የፖሊስ ሰራዊት አባልነቱ እንዲመለስ ተወስኖለት ወደ ሲዳም የተመለሰና ጊዜያዊ ምደባ ዲላ ውስጥ በመርማሪነት እየሰራ ያለ ፖሊስ ነው።
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
.....የምትለቀቀውማ እንደ ነገሩ ሁኔታ ዋስ ጠርተህ ነው» አለው መርማሪው ፖሊስ፣ ነገሩ የዕለት ግጭት በመሆኑ ብዙም ርቀት በማይሄድ ምርመራ እንደሚጠናቀቅ መርማሪው
ያስባል። የጠረጴዛ ደወል
አቃጨለና ረዳቱ ፖሊስ ሲቀርብለት ዓለሙን ወስዶ መብራቴ ባዩ የተባለ ሌላ
እስረኛ እንዲያቀርብለት አዘዘው።
ረዳቱም የተባለውን ፈፀመ፡
መብራቴ ባዩም በዕድሜው ብዙ አልገፋም ፣ ከሠላሳ ብዙ አያልፈውም፡፡ቀጠን ያለ ቀይ ዳማ ቢጤ ነው። መካከለኛ ቁመት አለው፡፡ ፀጉሩ አጠር፣ ከወደ አፉ
ሞጥሞጥ፣ ዓይኖቹ አነስ እነስ ያሉ ናቸው። እሱም በተመርማሪ ወንበር ላይ ተቀምጦ መርማሪውን በፍርሀት ይመለከተው ጀመር።
መርማሪው ፖሊስ ልክ በዓለሙ ላይ እንዳደረገው ሁሉ መብራቴን
መሠረታዊ መረጃዎችን እየጠየቀ ከመዘገበ በኋላ፡ «ከዓለሙ መርጋ ጋር ከአሁን በፊት ትተዋወቃላችሁ?» ሲል በቅድሚያ ጠየቀው።
«አይቸውም አላውቅ::»
«ምን አጣላችሁ ታዲያ?»
«እኔ ቀድሜ ገብቼ ባለሁበት ቤት መጥቶ ካልወጣህ ብሎ ሊያሳገድደኝ ሞከረ። አልወጣም ስለው በተቀመጥኩብት በጥፊ አቃጠለኝ ከዚያ በኋላ ነው
በደመነፍስ እጆቹን ይዤ ድረሱልኝ ብዬ የጮኩት።» አለው አይኖቹን እያቁለጨለጨ።
«በተጣላችሁበት ቤት ውስጥ ለምን ነበር ቀድመህ የገባኸው?»
«ቤቴ ነዋ!»
«ቤቴ ስትል? ሴትዮዋ ሚስትህ ናት?»
«ያው እንደ ሚሲቴ ናተ።»
«ለምን ያህል ጊዜ አብራችሁ ቆይታችኋል?»
«አረ ብዙ ነው።»
«እኮ በግምት?»
«ከአስራ አምስት ቀን በላይ አብረን አድረናል። ግን በተከታታይ
አደለም አልፎ አልፎ ነው፡፡ ከተዋወቅን ግን ቆይተናል፡፡»
«ወዳጅህ ስሟ ማን ይባላል?»
እየተገረመ ጠየቀው።
«ስሟ?»አለና መብራቴ ወደ ጣሪያ አንጋጠጠ፡፡ ግን ጠፋበት፡ ለማሰላሰል ሞከረና ሲያቅተው «ረሳሁት።» አለ የድንጋጤ ስሜት እየተነበበበት፡፡
«አሥራ አምስት ቀን ሙሉ የአቀፍካት ወዳጅህን» በማለት መርማሪው እየተገረመ ጠየቀው።
«በድንገት ስለሆነ የተገናኘነው ስሟ ይረሳኛል።»
መርማሪው ፖሊስ ጥርጣሬ ገባውና መብራቱን ትኩር ብሎ ተመለክተው።
መብራቴ የበለጠ የእፍረትና የድንጋጤ ስሜት ይነበብበት ጀመር።
«ዋሽተሃል አይደል?» አለው መርማሪው በትኩረት እየተመለከተው፡፡
«አጥፍቻለሁ ጌታዬ» አለ መብራቱ ሽቁጥቁጥ እያለ»
የመርማሪው ፖሊስ ልብ አሁንም እየተከረጢረ ሄደ ሆኖም ቃል
በያዘበት ወረቀት ላይ ከአስፈረመው በኋላ «የአንተንና የዓለሙን ጉዳይ በቀላሉ
ላለፈው አስቤ ነበር፡፡ ነገር ግን ተጠራጥሬአለሁ፡፡ የሁለታችሁንም ጉዳይ እንደገና
ኑነየው አልቀርም:: እለና ወደ እስር ቤት እንዲሄድ አሰናበተው፡፡
የመርማሪው ፖሊስ ጥርጣሬ ቀላል አልነበረም። ዓለሙን በሚጠይቅበት ወቅት ያያቸው ነነበሩ ሁኔታዎች እንደገና ትዝ አሉት። በስካር መንፈስ በአንዲት
ሴተኛ አዳሪ የተጣሉ መስለውት በእርግጥም ዋስ እያስጠራ በቀላሉ ሊሸኛቸው ነበር
አሳቡ:: አሁን ግን በጉዳዩ ላይ ጠለቅ ያለ ምርመራ ሊያደርግ ወሰነ። ለማንኛውም አለ በሆዱ
እስቲ ጋለሞታ የተባለችው ሴት ሌላ አጠራጣሪ ፍንጭ የምታወጣ
ከሆነ በቅድሚያ እሷን ላናጋግራት፡፡” አለና በረዳቱ ፖሲስ እንድትጠራ አደረገ።
ጋለሞታዋ ተጠርታ ወደ መርማሪው ፖሊስ ቢሮ በር ላይ ስትደርስ ሁለመናዋ በፍርሀት ይንቀጠቀጣል፡፡ እንባዋ ከዓይኗ ላይ እንደ በረዶ ይረግፋል።
መልኳ ደግሞ ይህ ቀረሽ የማትባል ወብ ናት። ዓይኖቿ እንደ ንጋት ኮከብ ያበራል። በዕድሜዋ ገና ወጣት ልጃገረድ ትመስላለች። “ጋለሞታ በሚለፈው የሴትነት መገለጫ አንዳች አመልካች ነገር አይታይባትም። ከንፈሮቿ እምቦጦች ይመስላሉ፡፡ የአፍንጫዋ አቀማመጥ ለቄንጥ የተሰራ ይመስላል። የቀይና ነጭ
ቡራቡራ ድሪያ ለብሳ በጡቶቿ ተገትሮ የአንጀቷን ድራሽ አጥፍቶታል።የመርማሪው ቢሮ በር ላይ ደርሳ ምን እንደምትባል ትዕዛዝ እየጠበቀች ሳለች
መርማሪው ፖሊስ ግን ይህንን ገፅታዋን ሲያይ ድንገት ተዘናግቶ ኖሮ ፐ! ይችስ ታደብድባለች አለ በሆዱ። ወዲያው ደግሞ «ምን ያስለቅስሻል?» ሲል ፈገግ ብሎ ጠየቃት ሁኔታዋ ሁሉ እያስገረመው። ግቢ ቁጭ በይ ማለቱን እንኳ እረሳው፡፡
«ፈርቼ» አለችው እንዳቀረቀረች::
«የሰራሽው ስራ አሳፈረሽ!»
«አረ እኔ ምንም አልሰራሁም!»
«እስቲ ግቢና ቁጭ በይ አላት» በእጁ አገጩን ያዝ አድርጎ አሁንም በትኩረት እየተመለከታት። ጋለሞታዋ ቁጭ አለችና አሁንም በፍርሃት ስሜት አቀርቅራ መሬት መሬት ታይ ጀመር።
«ምን አድርገሽ ነው የታሰርሽው?» ሲል ጠየቃት መርማሪው ፖላስ ቀስ እያለ ሊያግባባት ፈልጎ።
«ምንም» አለችና ለቅፅበት ያህል ቀና ብላ አየችው፡፡
«ዓለሙንና መብራቱን የት ነው የምታውቂያቸው?»
«እነማናቸው እነሱ?» አለች አሁንም፡፡ ለቅፅበት ያህል ቀና ብላ አይታው እንደገና እንጋቷን ደፋች::
«ጭራሽ አታወቂያቸውም?»
«አረ እኔ እንደዚህ የሚባሉ ሰዎች አላውቅም።»
«ሁለቱም ወዳጃችን ናት እያሉ እኮ ነው፡፡» አለና መርማሪው ከመቼውም ጊዜ ይበልጥ ለምላሿ ጓጉቶ ይጠባበቃት ጀመር፡፡
"ኣ"አለችና እሁንዎ ቀና ብላ አየት አረገችው፡፡
«ከማናቸውም ጋር አብረሽ አድረሽ አታውቂም?»
«እኔ ከወንድ ጋር ተኝቼ አላውቅም፡፡»
«አንድም ቀን?»
«አንድ ቀን ብቻ ከምወደው ሰው ጋር አድሬ አውቃለሁ፡፡ ግን ከንፈሬን ስሞታል እንጂ ሌላ ምንም አላደረገኝም::»
«ማነው እሱ ደግሞ?» ሲል ጠየቃት መርማሬው።
«እሱ እዚህ አገር የለም፣ ኤርትራ እሚባል አገር ከሄደ ቆይቷል፡፡»
«ኦ!» አለ መርማሪው ፖሊስ አንዳች የማያውቀው ስሜት መላ ሰውነቱን ድንገት ወርር እያረገው፡፡ «ማን ይባላል?» ሲል እንደገና ጠየቃት::
«አስቻለው ፍስሀ»
«አስቻለው ፍስህ ?» ሲል ደግሞ ጠየቃት፡፡
«አዎ፡፡» አለችውና እሷም ድንግጥ ብላ ቀና ብላ ታየው ጀመር፡፡
«እንዴ!» አለና «መርማሪው እንደገና አትኩሮ ያያት ጀመር። ስሜቱ እያደር ተለዋወጠ፡፡ አንቺ ስምሽ ማን ይባላል?» ሲል ጠየቃት የምትሰጠው መልስ ቀድሞ እያስፈራው።
«ሔዋን ተስፋዬ::»
«ምን?» ሰምቶ እንዳልሰማ፡፡
«ሔዋን ተስፋዬ እባላለሁ።»
መርማሪው ፖሊስ ፍዝዝ ብሎ ቀረ፡፡ የያዘው እስኪርቢቶ ከእጁ ላይ ሾልኮ ሲወድቅ ፈጽሞ አልታወቀውም፡፡ ዲላ ከተማ እየኖረ ስለመሆኑ እንደ አዲስ
ታወቀው፡፡ በሀሳብ ጥቅልል ብሎ አስመራ ከተማ ገባ፡፡
መርማሪው ፖሊስ የሀምሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ ይባላል። በሲዳሞ ክፍለ ሀገር በሀገረ ማሪያም ከተማ ተወልዶ ያደገ ነው። እዚያው በፖሊስነት ተቀጥሮ
እስከ ምክትል አሥር አለቅነት የደረሰና እሱም እንደ አስቻለው ፍሰሀ የዘመቻ ግዳጅ ተወስኖበት
ወደ ግንባር ዘምቶ በኤርትራ ምራባዊ የጦር ግንባሮች ለተከታታይ አምስት ዓመታት ሲዋጋ የቆየ ነው:: በጦር ግንባር የፈጸመው ጀብዱ የሀምሳ አለቅነት ማዕረግ ካገኘ በኋላ በቀጣይ የውጊያ ወቅት በደረሰበት ቁሰለት የተዋጊነት
ብቃቱ ቀንሶ ወደነበረበት የፖሊስ ሰራዊት አባልነቱ እንዲመለስ ተወስኖለት ወደ ሲዳም የተመለሰና ጊዜያዊ ምደባ ዲላ ውስጥ በመርማሪነት እየሰራ ያለ ፖሊስ ነው።
👍2
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ወዴት ነው የሚሄዱት?
ያን እለት ከቀኑ ወደ አሥር ሰዓት ገደማ ዣን ቫልዣ ብቸኝነት
ተሰምቶት ብቻውን ተቀምጧል፡፡ ኮዜትን ካየ ስለእርስዋ ብዙ አይጨነቅም፡፡በአንድ ወቅት ገጥሞት የነበረው መጥፎ አጋጣሚ እየተረሳው ሄዷል፡፡
ነገር ግን ከአንድ ወይም ከሁለት ሣምንት በፊት የገጠመው ነገር በጣም እያሳሰበው ሄዶአል:: አንድ ቀን አንድ አውራ ጉዳና ላይ ሲንሸራሸር ቴናድዬን ያየዋል:: የዚህ ክፉ ሰው ከዚያ በነፃ መለቀቅ እጅግ አደገኛ
መሆኑን ተገነዘበ፡፡ ይህም በጣም አስጨነቀው:: ከዚህም በላይ የፓሪስ ከተማ ሰላም ራቀው:: የፖለቲካ ብጥብጥ እያየለ መጣ፡፡ በዚህም የተነሳ ጸጥታ አስከባሪዎችና ፖሊሶች ክትትላቸውን አጠናከሩ፡፡ ዣን ቫልዣ በክትትል መጠናከር ሰበብ የሚያዝ ስለመሰለው በጣም ፈራ:: ዣን ቫልዣ ከሚፈለጉት
ሰዎች አንዱ እንደሆነ ልቡ ያውቃል:: ስለዚህ በአስቸኳይ ከፓሪስ መውጣት ነበረበት:: ከፓሪስ ከተማ ብቻ ሳይሆን ከፈረንሳይ መውጣት እንደሚሻል
አመነ:: ከፈረንሣይ አገር ከሄደ ወደ እንግሊዝ አገር መሄዱን ይመርጣል፡፡ በአንድ ሳምንት ውስጥ ከፈረንሣይ እንደሚወጡ ለኮዜት የነገራት በዚህ ጊዜ ነበር፡፡ የቴናድዬ፣ የፖሊስ ክትትል፣ የጉዞውና ፓስፖርት የማውጣቱ
ጉዳይ በጣም አስጨነቀው::
እነዚህ ነገሮች አስጨንቀውት ሳለ ያን እለት በቀን ግቢው ውስጥ
ሲንሸራሸር ከቤቱ ግድግዳ ላይ «ደ ፣ ላ፣ ቤራሪ ጉዳና የቤት ቁጥር 16» የሚል ጽሑፍ በምስማር ተጽፎ ያያል::
ጽሑፉ በቅርቡ ለመጻፉ ያስታውቃል:: ምናልባትም ጽሑፉ ከተጻፈ ቢበዛ አንድ ቀን ውሎ ይደር እንጂ ከዚያ እንደማይበልጥ ይገምታል:: ጽሑፉ ማን ይላል? የሰው አድራሻ ነው? አንድ ሰው ለማመልከት የተጻፈ ይሆን? ለዣን ቫልዣ የተሰጠ ማስጠንቀቂያ ነው? ምንም ይሁን ምን አንድ
ሰው ግቢውን ደፍሮአል፡፡
ይህን እያሰላሰለ ሰው በአካባቢው ለመኖሩ በጥላው አወቀ፡፡ ሰውዬው ድንገት ይቆማል። ዞር ብዬ ልይ በማለት ሲያስብ የተጠቀለለ ወረቀት
ከእግሩ ሥር ይወድቃል የወረቀታ አወዳደቅ ከላይ ወደታች እንጂ ከሩቅ በጎን የወረወሩት አይመስል
ወረቀቱን አንስቶ ዘረጋው «አስወግድ»የሚል ቃል በትልልቅ ጽሑፍ በእርሳስ ተጽፎ አነበበ::
ዣን ቫልዣ ዞር ዞር አለ፡፡ በዚያ አካባቢ ሰው አልነበረም፡፡ ግን
ግራጫ መልክ ያለው ሸሚዝና የወይን ጠጅ ቀለም ያለው ሰሪ የታጠቀ ልጅ አይሉት ትልቅ ሰው በአጥሩ ዘልሎ ወደ ዋናው ጎዳና ሲወጣ በሩቁ ተመለከተ።
ዣን ቫልዣ ቶሎ ብሎ ወደ ቤቱ ገባ። ከከባድ ጭንቀት ላይ ወደቀ።
ማሪየስ ከመሴይ ጊልኖርማንድ ቤት ከወጣ ቆይቷል:: በታላቅ ተስፋ የገባው ሰውዬ ከቤቱ ሲወጣ ከመጠን በላይ ተስፋ ቆርጦ ነው:: መከራና ስቃይ ያስጨነቀው ሰው እንደሚያደርገው ሁሉ እርሱም
በአሳብ ተውጦ እያቀረቀረ ነው የሚጓዘው:: ጭንቅላቱ ባዶውን ስለቀረ የሚያስበው ነገር አልነበረውም:: ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት ከጓደኛው ከኩርፌይራክ ቤት ደረሰ፡፡ ከነልብሱ ራሱን ከአልጋው ላይ ወረወረ፡፡
እስኪነጋ እንቅልፍ አልወሰደውም:: ፀሐይ እንደወጣ እንቅልፍ ወስዶት ኖሮ ክፉኛ አቃዠው::
ቅዠቱ ከእንቅልፉ ቀሰቀሰው:: ዓይኑን ገልጦ ሲያይ ከቤቱ ውስጥ
የነበሩት አራቱም ጓደኞቹ ለመሄድ ተዘጋጅተዋል፡፡
«ከጄኔራል ላማርክ ቀብር ትገኛለህ?» ሲል ጓደኛው ኩርፌይራክ ጠየቀው::
በቻይና ቋንቋ የሚያናግረው መሰለው:: ማሪየስ ጓደኞቹ ከቤት ከወጡ ጥቂት ቆይቶ ነው የወጣው፡፡ ዣቬር ከሰጠው ሽጉጥ አንዱን ኪሱ ውስጥ
አደረገ፡፡ ሽጉጡ ጥይት እንደጕረሰ ነው፡፡ ምን አስቦ ሽጉጡን እንደያዘ
ለማወቅ ያስቸግራል፡፡ የት እንደሚሄድ ሳያውቅ ቀኑን ሙሉ ከወዲያ ወዲህ ሲንቀዋለል
ዋለ፡፡ አንዳንዴ ዝናብ ቢያካፋም እርሱ አልተሰማውም:: ጦሙን እንዳያድር ለእራቱ የሚሆን ዳቦ ገዝቶ ኪሱ ውስጥ አደረገው፡፡ ግን ኪሱ ውስጥ እንዳለ ረስቶት ሳይበላው አደረ፡፡ ጊዜው ቶሎ አልመሽ ስላለው በጣም ተቁነጠነጠ፡፡ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ከኮዜት ጋር ቀጠሮ ስለነበረው ያቺን ሰዓት በጉጉት ይጠብቃል፡፡ ከተማው ውስጥ ከወዲያ ወዲህ ሲዞር በአሳብ ጭልጥ ይላል፡፡
ከአሳቡ ሲነቃ የተኩስ ድምፅ ስማ፡፡ «ውጊያ ቀጥለዋል ማለት ነው?» ሲል ራሱን ጠየቀ መሽቶ ሦስት ሰዓት ሲቃረብ ወደ ቀጠሮው ቦታ ሄደ፡፡ ኮዜትን ሳያይ
ሁለት ቀን ስላለፈ በጣም ናፍቆአታል:: ሰዓቱ በመድረሱ በጣም ደስ አለው፡፡ የምንጓጓለት ነገር ልብን ያስጨንቃል እንጂ ቶሎ ስለማይደርስ ደቂቃው እንደ ዓመት ይረዝማል፡፡
ማሪየስ በለመደው ቀዳዳ ከግቢው ውስጥ ገባ፡፡ ኮዜት በሌላ ጊዜ ከምትጠብቀው ሥፍራ የለችም፡፡ ምናልባት ከቤቱ አካባቢ ትጠብቀኝ ይሆናል ብሎ ወደዚያ አመራ:: ከዚያም አልነበረችም:: አንገቱን ቀና አድርጎ ሲያይ
የኮዜት መኝታ ቤት መስኮት ተዘግቷል፡፡ አካባቢው በጣም ጭር ብሏል፡፡ በፍቅር ያበደው፣ የነደደው፣ የተቃጠለውና የሰከረው ወጣት ከፍቅረኛው
መኝታ ቤት መስኮት ላይ አፈጠጠ፡፡ ከአሁን አሁን ተከፍቶ «ኮዜትዬ ብቅ ትላለች» ሲል አወጣ፤ አወረደ፡፡ ግን መስኮቱ እንደተዘጋ ቀረ፡፡ በጨለማ
ለማየት እስከቻለ ድረስ በዓይኑ አካባቢውን ቃኘ:: ማንም የለም:: ድንገት አባትዋ ብቅ ያለ እንደሆነ ‹‹ምን ትፈልጋለህ?» ብሎ ያፈጥብኛል በማለት ሳይፈራ ቤቱን ዞረው:: በመጨረሻ አላስችል ብሎት «ኮዜት» እያለ ደጋግሞ
ተጣራ:: መልስ አላገኘም:: አሁንም ደገመና ተጣራ:: መልስ የለም:: ቤቱ ውስጥ ሰው እንደሌለ አወቀ፡፡
ቤቱን ተስፋ በቆረጠ ዓይን አየው፡፡ ከመቃብር ቤት ይበልጥ ጭር
ብሎአል፡፡ ብዙ የደስታ ምሽቶችን ወዳሳለፈበት የድንጋይ መቀመጫ ሄደ:: ልቡ እየከበደው ከመቀመጫው ላይ ቁጭ አለ፡፡ ለኮዜት ያለውን ፍቅር
እያሰላሰለ ኮዜት ከሄደች ከመሞት በስተቀር ሌላ የተሻለ ምርጫ እንደሌለው አመነ፡፡
ከአጥር ውጭ ድንገት ድምፅ ሰማ
«መሴይ ማሪየስ!»
ከተቀመጠበት ብድግ አለ፡፡
‹‹ማነህ?» ሲል ተጣራ
«መሴይ ማሪየስ፣ አንተ ነህ?››
«አዎን፡፡»
«መሴይ ማሪየስ» አለ ድምፁ፣ «ጓደኞችህ ባሪኬድ ከተባለ ሥፍራ ይጠብቁሃል፡፡»
ድምፁ እንግዳ የሆነ ድምፅ አልነበረም፡፡ የኢፓኒንን ድምፅ ይመስላል፡፡ ቶሎ ብሎ ወደ አጥሩ ሄደና በቀዳዳ አየ:: አንድ ወጣት ሮጦ ሲሄድ ተመለከተ፡፡ ጨለማ ስለነበር ሊለየው አልቻለም::
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የመሴይ ማብዩፍ ኑሮ እያቆለቆለ ሄደ እንጂ አልተሻሻለም:: ባለፈው
ዓመት የሠራተኛቸውን ደመወዝ መክፈል አቅቶአቸው ነበር፡፡ በዚህ ዓመት ደግሞ የቤት ኪራይ መክፈል አቃታቸው፡፡ ቀስ በቀስ የቤቱን እቃ ሽጠው ጨረሱ፡፡ የጻፉትንም መጽሐፍ ገዢ ስላጣ እንደ አሮጌ መጽሐፍ ተቆጥሮ
በቅናሽ ሸጡት፡፡ ቀደም ሲል አልፎ አልፎ ሥጋ ይበሉ ነበር፡፡ ዛሬ ግን
ጠፍቶ የሚበሉት ደረቅ ዳቦና የተቀቀለ ድንች ሆነ፡፡ በመጨረሻ
የሚሽጡት ንብረት ሁሉ አልቆ የቀረው በደህና ዘመን የሰበሰብዋቸውና በጣም የሚወዷቸው መጻሕፍት ብቻ ነበሩ፡፡ መሴይ ማብዩፍ የሚያነዱት እንጨት ስላልነበራቸው ገና ጀምበር ስትጠልቅ ይተኛሉ፡፡ ከጊዜ በኋላማ በጣም እየደኸዩ ስለሄዱ ጎረቤት ሀሉ ይሸሻቸው ጀመር:: ሰዎች እንደሚሸሹዋቸው ስለገባቸው እርሳቸውም ይሸሿቸዋል:: በልጅ ስቃይ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ወዴት ነው የሚሄዱት?
ያን እለት ከቀኑ ወደ አሥር ሰዓት ገደማ ዣን ቫልዣ ብቸኝነት
ተሰምቶት ብቻውን ተቀምጧል፡፡ ኮዜትን ካየ ስለእርስዋ ብዙ አይጨነቅም፡፡በአንድ ወቅት ገጥሞት የነበረው መጥፎ አጋጣሚ እየተረሳው ሄዷል፡፡
ነገር ግን ከአንድ ወይም ከሁለት ሣምንት በፊት የገጠመው ነገር በጣም እያሳሰበው ሄዶአል:: አንድ ቀን አንድ አውራ ጉዳና ላይ ሲንሸራሸር ቴናድዬን ያየዋል:: የዚህ ክፉ ሰው ከዚያ በነፃ መለቀቅ እጅግ አደገኛ
መሆኑን ተገነዘበ፡፡ ይህም በጣም አስጨነቀው:: ከዚህም በላይ የፓሪስ ከተማ ሰላም ራቀው:: የፖለቲካ ብጥብጥ እያየለ መጣ፡፡ በዚህም የተነሳ ጸጥታ አስከባሪዎችና ፖሊሶች ክትትላቸውን አጠናከሩ፡፡ ዣን ቫልዣ በክትትል መጠናከር ሰበብ የሚያዝ ስለመሰለው በጣም ፈራ:: ዣን ቫልዣ ከሚፈለጉት
ሰዎች አንዱ እንደሆነ ልቡ ያውቃል:: ስለዚህ በአስቸኳይ ከፓሪስ መውጣት ነበረበት:: ከፓሪስ ከተማ ብቻ ሳይሆን ከፈረንሳይ መውጣት እንደሚሻል
አመነ:: ከፈረንሣይ አገር ከሄደ ወደ እንግሊዝ አገር መሄዱን ይመርጣል፡፡ በአንድ ሳምንት ውስጥ ከፈረንሣይ እንደሚወጡ ለኮዜት የነገራት በዚህ ጊዜ ነበር፡፡ የቴናድዬ፣ የፖሊስ ክትትል፣ የጉዞውና ፓስፖርት የማውጣቱ
ጉዳይ በጣም አስጨነቀው::
እነዚህ ነገሮች አስጨንቀውት ሳለ ያን እለት በቀን ግቢው ውስጥ
ሲንሸራሸር ከቤቱ ግድግዳ ላይ «ደ ፣ ላ፣ ቤራሪ ጉዳና የቤት ቁጥር 16» የሚል ጽሑፍ በምስማር ተጽፎ ያያል::
ጽሑፉ በቅርቡ ለመጻፉ ያስታውቃል:: ምናልባትም ጽሑፉ ከተጻፈ ቢበዛ አንድ ቀን ውሎ ይደር እንጂ ከዚያ እንደማይበልጥ ይገምታል:: ጽሑፉ ማን ይላል? የሰው አድራሻ ነው? አንድ ሰው ለማመልከት የተጻፈ ይሆን? ለዣን ቫልዣ የተሰጠ ማስጠንቀቂያ ነው? ምንም ይሁን ምን አንድ
ሰው ግቢውን ደፍሮአል፡፡
ይህን እያሰላሰለ ሰው በአካባቢው ለመኖሩ በጥላው አወቀ፡፡ ሰውዬው ድንገት ይቆማል። ዞር ብዬ ልይ በማለት ሲያስብ የተጠቀለለ ወረቀት
ከእግሩ ሥር ይወድቃል የወረቀታ አወዳደቅ ከላይ ወደታች እንጂ ከሩቅ በጎን የወረወሩት አይመስል
ወረቀቱን አንስቶ ዘረጋው «አስወግድ»የሚል ቃል በትልልቅ ጽሑፍ በእርሳስ ተጽፎ አነበበ::
ዣን ቫልዣ ዞር ዞር አለ፡፡ በዚያ አካባቢ ሰው አልነበረም፡፡ ግን
ግራጫ መልክ ያለው ሸሚዝና የወይን ጠጅ ቀለም ያለው ሰሪ የታጠቀ ልጅ አይሉት ትልቅ ሰው በአጥሩ ዘልሎ ወደ ዋናው ጎዳና ሲወጣ በሩቁ ተመለከተ።
ዣን ቫልዣ ቶሎ ብሎ ወደ ቤቱ ገባ። ከከባድ ጭንቀት ላይ ወደቀ።
ማሪየስ ከመሴይ ጊልኖርማንድ ቤት ከወጣ ቆይቷል:: በታላቅ ተስፋ የገባው ሰውዬ ከቤቱ ሲወጣ ከመጠን በላይ ተስፋ ቆርጦ ነው:: መከራና ስቃይ ያስጨነቀው ሰው እንደሚያደርገው ሁሉ እርሱም
በአሳብ ተውጦ እያቀረቀረ ነው የሚጓዘው:: ጭንቅላቱ ባዶውን ስለቀረ የሚያስበው ነገር አልነበረውም:: ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት ከጓደኛው ከኩርፌይራክ ቤት ደረሰ፡፡ ከነልብሱ ራሱን ከአልጋው ላይ ወረወረ፡፡
እስኪነጋ እንቅልፍ አልወሰደውም:: ፀሐይ እንደወጣ እንቅልፍ ወስዶት ኖሮ ክፉኛ አቃዠው::
ቅዠቱ ከእንቅልፉ ቀሰቀሰው:: ዓይኑን ገልጦ ሲያይ ከቤቱ ውስጥ
የነበሩት አራቱም ጓደኞቹ ለመሄድ ተዘጋጅተዋል፡፡
«ከጄኔራል ላማርክ ቀብር ትገኛለህ?» ሲል ጓደኛው ኩርፌይራክ ጠየቀው::
በቻይና ቋንቋ የሚያናግረው መሰለው:: ማሪየስ ጓደኞቹ ከቤት ከወጡ ጥቂት ቆይቶ ነው የወጣው፡፡ ዣቬር ከሰጠው ሽጉጥ አንዱን ኪሱ ውስጥ
አደረገ፡፡ ሽጉጡ ጥይት እንደጕረሰ ነው፡፡ ምን አስቦ ሽጉጡን እንደያዘ
ለማወቅ ያስቸግራል፡፡ የት እንደሚሄድ ሳያውቅ ቀኑን ሙሉ ከወዲያ ወዲህ ሲንቀዋለል
ዋለ፡፡ አንዳንዴ ዝናብ ቢያካፋም እርሱ አልተሰማውም:: ጦሙን እንዳያድር ለእራቱ የሚሆን ዳቦ ገዝቶ ኪሱ ውስጥ አደረገው፡፡ ግን ኪሱ ውስጥ እንዳለ ረስቶት ሳይበላው አደረ፡፡ ጊዜው ቶሎ አልመሽ ስላለው በጣም ተቁነጠነጠ፡፡ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ከኮዜት ጋር ቀጠሮ ስለነበረው ያቺን ሰዓት በጉጉት ይጠብቃል፡፡ ከተማው ውስጥ ከወዲያ ወዲህ ሲዞር በአሳብ ጭልጥ ይላል፡፡
ከአሳቡ ሲነቃ የተኩስ ድምፅ ስማ፡፡ «ውጊያ ቀጥለዋል ማለት ነው?» ሲል ራሱን ጠየቀ መሽቶ ሦስት ሰዓት ሲቃረብ ወደ ቀጠሮው ቦታ ሄደ፡፡ ኮዜትን ሳያይ
ሁለት ቀን ስላለፈ በጣም ናፍቆአታል:: ሰዓቱ በመድረሱ በጣም ደስ አለው፡፡ የምንጓጓለት ነገር ልብን ያስጨንቃል እንጂ ቶሎ ስለማይደርስ ደቂቃው እንደ ዓመት ይረዝማል፡፡
ማሪየስ በለመደው ቀዳዳ ከግቢው ውስጥ ገባ፡፡ ኮዜት በሌላ ጊዜ ከምትጠብቀው ሥፍራ የለችም፡፡ ምናልባት ከቤቱ አካባቢ ትጠብቀኝ ይሆናል ብሎ ወደዚያ አመራ:: ከዚያም አልነበረችም:: አንገቱን ቀና አድርጎ ሲያይ
የኮዜት መኝታ ቤት መስኮት ተዘግቷል፡፡ አካባቢው በጣም ጭር ብሏል፡፡ በፍቅር ያበደው፣ የነደደው፣ የተቃጠለውና የሰከረው ወጣት ከፍቅረኛው
መኝታ ቤት መስኮት ላይ አፈጠጠ፡፡ ከአሁን አሁን ተከፍቶ «ኮዜትዬ ብቅ ትላለች» ሲል አወጣ፤ አወረደ፡፡ ግን መስኮቱ እንደተዘጋ ቀረ፡፡ በጨለማ
ለማየት እስከቻለ ድረስ በዓይኑ አካባቢውን ቃኘ:: ማንም የለም:: ድንገት አባትዋ ብቅ ያለ እንደሆነ ‹‹ምን ትፈልጋለህ?» ብሎ ያፈጥብኛል በማለት ሳይፈራ ቤቱን ዞረው:: በመጨረሻ አላስችል ብሎት «ኮዜት» እያለ ደጋግሞ
ተጣራ:: መልስ አላገኘም:: አሁንም ደገመና ተጣራ:: መልስ የለም:: ቤቱ ውስጥ ሰው እንደሌለ አወቀ፡፡
ቤቱን ተስፋ በቆረጠ ዓይን አየው፡፡ ከመቃብር ቤት ይበልጥ ጭር
ብሎአል፡፡ ብዙ የደስታ ምሽቶችን ወዳሳለፈበት የድንጋይ መቀመጫ ሄደ:: ልቡ እየከበደው ከመቀመጫው ላይ ቁጭ አለ፡፡ ለኮዜት ያለውን ፍቅር
እያሰላሰለ ኮዜት ከሄደች ከመሞት በስተቀር ሌላ የተሻለ ምርጫ እንደሌለው አመነ፡፡
ከአጥር ውጭ ድንገት ድምፅ ሰማ
«መሴይ ማሪየስ!»
ከተቀመጠበት ብድግ አለ፡፡
‹‹ማነህ?» ሲል ተጣራ
«መሴይ ማሪየስ፣ አንተ ነህ?››
«አዎን፡፡»
«መሴይ ማሪየስ» አለ ድምፁ፣ «ጓደኞችህ ባሪኬድ ከተባለ ሥፍራ ይጠብቁሃል፡፡»
ድምፁ እንግዳ የሆነ ድምፅ አልነበረም፡፡ የኢፓኒንን ድምፅ ይመስላል፡፡ ቶሎ ብሎ ወደ አጥሩ ሄደና በቀዳዳ አየ:: አንድ ወጣት ሮጦ ሲሄድ ተመለከተ፡፡ ጨለማ ስለነበር ሊለየው አልቻለም::
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የመሴይ ማብዩፍ ኑሮ እያቆለቆለ ሄደ እንጂ አልተሻሻለም:: ባለፈው
ዓመት የሠራተኛቸውን ደመወዝ መክፈል አቅቶአቸው ነበር፡፡ በዚህ ዓመት ደግሞ የቤት ኪራይ መክፈል አቃታቸው፡፡ ቀስ በቀስ የቤቱን እቃ ሽጠው ጨረሱ፡፡ የጻፉትንም መጽሐፍ ገዢ ስላጣ እንደ አሮጌ መጽሐፍ ተቆጥሮ
በቅናሽ ሸጡት፡፡ ቀደም ሲል አልፎ አልፎ ሥጋ ይበሉ ነበር፡፡ ዛሬ ግን
ጠፍቶ የሚበሉት ደረቅ ዳቦና የተቀቀለ ድንች ሆነ፡፡ በመጨረሻ
የሚሽጡት ንብረት ሁሉ አልቆ የቀረው በደህና ዘመን የሰበሰብዋቸውና በጣም የሚወዷቸው መጻሕፍት ብቻ ነበሩ፡፡ መሴይ ማብዩፍ የሚያነዱት እንጨት ስላልነበራቸው ገና ጀምበር ስትጠልቅ ይተኛሉ፡፡ ከጊዜ በኋላማ በጣም እየደኸዩ ስለሄዱ ጎረቤት ሀሉ ይሸሻቸው ጀመር:: ሰዎች እንደሚሸሹዋቸው ስለገባቸው እርሳቸውም ይሸሿቸዋል:: በልጅ ስቃይ
👍18👎1
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
...“እኔስ ማሬ? እኔን አግኝተሻል። ቢያንስ የምትቀጥለዋ ቆንጆ እስክትመጣ ድረስ አለሁልሽ”
“እና እኔ ከሶፋው ጀርባ ሆኜ ይህንን ስሰማ በድንጋጤ ፈዘዝኩ። ሊያስመልሰኝ የተዘጋጀሁ መሰለኝ ግን ፀጥ ብዬ ተጋድሜ ጥንዶቹ ሶፋ ላይ ሆነው ሲያወሩ እያዳመጥኩ ነበር። ብድግ ብዬ በፍጥነት ወዳንቺና ወደኬሪ ሮጬ መምጣትና
ከመዘግየቱ በፊት ከዚህ ላስወጣችሁ ፈለግኩ።
“ግን ተይዣለሁ ብንቀሳቀስ ያዩኛል። በዛ ላይ ጆን ከሴት አያትየው ጋር
ዝምድና አለው፡ ጆን የአያትየው መተማመኛ ሳይሆን አይቀርም አለበለዚያ መኪናዎቿን እንዲጠቀም ያን ያህል ነፃነት አትሰጠውም ነበር። ካቲ፣
አይተሽው ታውቂያለሽ እኮ… የክሪስማስ ግብዣው ቀን የአገልጋዮች ልብስ ለብሶ የነበረው ?መላጣ ሰውዬ ነው” ማንን ማለቱ እንደሆነ አውቄያለሁ ግን የራሴ የመደንገጥ ድንዛዜ ተሰምቶኝ መናገር ስላቃተኝ፣ ማድረግ የቻልኩት ዝም ብዬ መጋደም ብቻ ነበር።
ክሪስ ቀጠለ። “ሶፋው ጀርባ እንደተደበቅኩ ጆንና ሰራተኛዋ መላፋት ጀመሩ። ልብሶቿን ማውለቅ ሲጀምርና እሷም የእሱን ልታወልቅ ስትጀምር እንቅስቃሴዎቻቸው ይሰማኛል።" “አንዳቸው የሌላኛቸውን ልብስ አወለቁ?” ስል ጠየቅኩት። “ልብሱን እንዲያወልቅ የምር አገዘችው?”
“እንደዛ ነው የተሰማኝ አለኝ በግድየለሽነት:
“አልጮኸችም፣ አልተቃወመችውም?”
“አልተቃወመችውም፡ እሷም ፈልጋ ነበር! አምላኬ ሆይ እና በጣም ረጅም ጊዜ ወሰደባቸው! ካቲ
የሚያወጡትን ድምፅ አታምኚም! ታቃስታለች፣ትጮሀለች አየር ያጠራት ትመስላለች፣ ታለከልካለች እና እሱ ደግሞ እንደ አሳማ ያጓራል ግን እዛ ላይ በጣም ጥሩ ሳይሆን እንደማይቀር እገምታለሁ::
ምክንያቱም በመጨረሻ ሠራተኛዋ እንዳበደ ሰው ነበር የጮኸችው። ከዚያ ሲያልቅ ጋደም ብለው ሲጋራ እያጨሱ እዚህ ቤት ስለሚደረገው ነገር እያወሩ ነበር። እመኚኝ የማያውቁት በጣም ጥቂት ነገሮችን ብቻ ነው። ከዚያ ለሁለተኛ
ጊዜ ፍቅር ሰሩ:"
“በአንድ ምሽት ሁለት ጊዜ?”
“ይቻላል።”
“ክሪስ ለምንድነው አነጋገርህ የተቀየረው?”
አመነታ፤ ትንሽ ራቅ አለና ፊቴን አጠና። “ካቲ እያዳመጥሽኝ አይደለም? ሁሉንም ነገር ልክ እንደሆነው አድርጌ ለአንቺ ለመንገር ትልቅ ህመም ውስጥ
ነኝ። አልሰማሽኝም?”
መስማት? አዎ ሰምቼያለሁ ሁሉንም:
የእናታችንን ጌጣጌጦች ለመዝረፍ ብዙ ጊዜ ጠበቀ።
እናታችንና ባሏ ሌላ ሽርሽር ሄዱ። ይሄ ምን አይነት ዜና ነው? ሁልጊዜ
ይመጣሉ… ይሄዳሉ፤ ከዚህ ቤት ለመውጣት ምንም ነገር ያደርጋሉ። እና እወቅሳቸዋለሁ ማለት አልችልም: እኛስ ተመሳሳይ ነገር ልናደርግ ተዘጋጅተን
የለ? ቅንድቦቼን ወደ ላይ ሰቅዬ ክሪስን በጥያቄ አስተያየት ተመለከትኩት ያልነገረኝ
የሆነ የሚያውቀው ነገር እንዳለ ግልፅ ነው: አሁንም እየተከላከለላት ነው። አሁንም ይወዳታል
ካቲ” ሲል ጀመረ፡ ድምፁ እየተቆራረጠ ነው
“ምንም አይደል ክሪስ፣ እየወቀስኩህ አይደለም ውዷ፣ ጣፋጯ፣ ደጓና አፍቃሪዋ እናታችን ከመልከመልካም ወጣት ባሏ ጋር ጌጣጌጣቸውን ሁሉ ይዘው ሌላ ሽርሽር ሄዳለች፡ በውጪው አለም ያለውን ጥበቃ ደህና ሁን
በለው: ግን አሁንም እሄዳለሁ! እንሰራለን ራሳችንን የምንደግፍበት መንገድ እንፈልጋለን፡ ከዚያ ኬሪ እንደገና ደህና እንድትሆን ለዶክተር እንከፍላለን፡ዠ ስለጌጣጌጦች አትጨነቅ፤ ስለ እናታችን ርህራሄ የለሽ ድርጊት አትጨነቅ።
የት እንደምትሄድ፣ መቼ እንደምትመለስ እንኳን አልነገረችንም: አሁን አስቀያሚ መጥፎ የማናስብ ቸልተኞች እንድንሆን ተትተናል፡ ታዲያ ይሄ
ሁሉ ዕንባ ለማን? ለምን?
"ካቲ!” ተቆጣ በእምባ የረጠበ ፊቱን ወደ እኔ መልሶ አይኖቼ ላይ አተኮረ:
“ለምንድነው የማታዳምጪውና የሆነ ነገር የማትይው? ጆሮሽ የት ነው? ያልኩትን ሰምተሽኛል? ወንድ አያታችን ሞቷል! ከሞተ አንድ አመት ገደማ ሆኖታል!”
ምናልባት በደንብ አልሰማሁትም፤ በጥንቃቄ አላዳመጥኩትም ማለት ነው ሀዘኑ ምንም ነገር እንዳልሰማ አድርጎኛል ማለት ነው አሁን ለመጀመሪያ ጊዜ ሙሉ በሙሉ መታኝ አያትየው በእውነት ከሞተ እጅግ መልካም ዜና ነው አሁን እናታችን ውርስ ታገኛለች… ሀብታም እንሆናለን…በሩን ትከፍትልናለች… ነፃ ታደርገናለች:: አሁን ለማምለጥ መሞከር የለብንም:
ሌሎች ሀሳቦች ጎረፉ አስደንጋጭ የጥያቄ ጎርፍ መጣብኝ። እናታችን አባቷ መሞቱን አልነገረችንም:: እነዚህ አመታት ለእኛ እንዴት ረጃጅም እንደሆኑ እያወቀች፣ ለምን በጨለማ ሁልጊዜ በመጠበቅ ውስጥ አስቀመጠችን? ለምን?
ግራ ተጋባሁ። ተደናገረብኝ፤ የትኛው ስሜት እንደሚሰማኝ አላውቅኩም። ደስታ ይሁን ሀዘን ሀሳቤን አለመቁረጤን ሽባ የሚያደርግ እንግዳ ፍርሀት
አስቆመኝ።
“ካቲ…” አለኝ ክሪስ በሹክሹክታ። ለምን ማንሾካሾክ እንዳለበት አላወቅኩም ኬሪ እንደሆነች አትሰማም: የእሷ አለም ከእኛ በእጅጉ ተለይቷል ኬሪ
በህይወትና በሞት መካከል ተንጠልጥላለች: በእያንዳንዱ ቅፅበት ወደ ኮሪ እየተጠጋች ነው: ራሷን በማስራብ ያለ ግማሽ አካሏ ለመኖር መፈለጓን ትታዋለች። “እናታችን ሆን ብላ አታላናለች: ካቲ አባቷ ሞቶ ከወራት በኋላ
ኑዛዜው ተነቧል። እና ሳትነግረን ፀጥ ብላ ሞታችንን እንድንጠብቅ እዚህ ተወችን፡ ከዘጠኝ ወራት በፊት ሁላችንም በዘጠኝ ወራት ጤናማ ነበርን! አባቷ የሞተ ጊዜ ከዚህ አስወጥታን ቢሆን ወይም ኑዛዜው የተነበበ ጊዜ እንኳን ወጥተን ቢሆን ኮሪ አሁን በህይወት ይኖር ነበር፡"
ስሜቴ ተጎድቶ እናታችን ልታሰምጠን የቆፈረችው ጥልቅ የክህደት ጉድጓድ ውስጥ ወደቅኩ። ማልቀስ ጀመርኩ።
“ዕንባሽን ለበኋላ አቆይው" አለ ክሪስ ራሱም እያለቀሰ ነው። “ሁሉንም ነገር አልሰማሽም ሌላም አለ። ብዙና የከፋ”
“ብዙ?” ሌላ ምን ብዙ ነገር ሊነገረኝ ይችላል? እናታችን ከእንግዲህ
ከማትወዳቸውና ከማትፈልጋቸው ልጆቿ ጋር መካፈል የማትፈልገውን
ንብረት በማካበት ሂደት ውስጥ ኮሪን የገደለች፣ውሽታም፣ አታላይና
ወጣትነታችንን የሰረቀች ሌባ መሆኗ ተረጋግጧል። በዚያ ምሽት ደስተኛ ባለመሆናችን ትንሽዋን ንስሀችንን ስትሰጠን ምን መጠበቅ እንዳለብን እንዴት አሳምራ እንዳብራራችልን! የዚያን ጊዜ አያታችን የሰራት አይነት
ሴት እንደምትሆን ታውቅ ወይስ ትገምት ነበር ይሆን? ክሪስ ክንዶች ላይ ወደቅኩና ደረቱን ተደገፍኩ “ከዚህ በላይ አትንገረኝ! የሰማሁት ይበቃኛል ከዚህ በላይ እንድጠላት አታድርገኝ! አልኩት።
“መጥላት. ጥላቻ ምን እንደሆነ ገና ማወቅ አልጀመርሽም ግን የቀረውን
ከመናገሬ በፊት ምንም ቢሆን ይህንን ቦታ ለቀን እንደምንሄድ አስቢ።እንዳቀድነው ወደ ፍሎሪዳ እንሄዳለን በፀሀይ ብርሀን ውስጥ እንኖራለን::እና ህይወታችንን በቻልነው ሁሉ በጣም ጥሩ እናደርገዋለን። ማን በመሆናችን ወይም በስራነው ለአንዲት ሰኮንድ እንኳን ሳናፍር እንኖራለን።
በመሀከላችን የተፈጠረው ነገር እናታችን ካደረገችው ጋር ሲነፀር ምንም ማለት አይደለም ከእኔ በፊት ብትሞቺም እንኳን፣ እዚህ ጣሪያ ስር ያለው ክፍል የነበረንን ህይወት ሁልጊዜ አስታውሰዋለሁ: በወረቀት አበባዎቹ ስር ስንደንስ አንቺ በጣም ግርማ ያለሽ እኔ ደግሞ ገልጃጃ ሆኜ የአቧራውንና የበሰበሰ እንጨቱን ሽታ ልክ እንደ ጣፋጭ ሽቶ አስታውሰዋለሁ ምክንያቱም
ህይወቴ ያላንቺ በጣም ቀፋፊና ባዶ ነው የሚሆነው። ፍቅር ምን ሊሆን
እንደሚችል የመጀመሪያውን ጣዕም ሰጥተሽኛል።
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
...“እኔስ ማሬ? እኔን አግኝተሻል። ቢያንስ የምትቀጥለዋ ቆንጆ እስክትመጣ ድረስ አለሁልሽ”
“እና እኔ ከሶፋው ጀርባ ሆኜ ይህንን ስሰማ በድንጋጤ ፈዘዝኩ። ሊያስመልሰኝ የተዘጋጀሁ መሰለኝ ግን ፀጥ ብዬ ተጋድሜ ጥንዶቹ ሶፋ ላይ ሆነው ሲያወሩ እያዳመጥኩ ነበር። ብድግ ብዬ በፍጥነት ወዳንቺና ወደኬሪ ሮጬ መምጣትና
ከመዘግየቱ በፊት ከዚህ ላስወጣችሁ ፈለግኩ።
“ግን ተይዣለሁ ብንቀሳቀስ ያዩኛል። በዛ ላይ ጆን ከሴት አያትየው ጋር
ዝምድና አለው፡ ጆን የአያትየው መተማመኛ ሳይሆን አይቀርም አለበለዚያ መኪናዎቿን እንዲጠቀም ያን ያህል ነፃነት አትሰጠውም ነበር። ካቲ፣
አይተሽው ታውቂያለሽ እኮ… የክሪስማስ ግብዣው ቀን የአገልጋዮች ልብስ ለብሶ የነበረው ?መላጣ ሰውዬ ነው” ማንን ማለቱ እንደሆነ አውቄያለሁ ግን የራሴ የመደንገጥ ድንዛዜ ተሰምቶኝ መናገር ስላቃተኝ፣ ማድረግ የቻልኩት ዝም ብዬ መጋደም ብቻ ነበር።
ክሪስ ቀጠለ። “ሶፋው ጀርባ እንደተደበቅኩ ጆንና ሰራተኛዋ መላፋት ጀመሩ። ልብሶቿን ማውለቅ ሲጀምርና እሷም የእሱን ልታወልቅ ስትጀምር እንቅስቃሴዎቻቸው ይሰማኛል።" “አንዳቸው የሌላኛቸውን ልብስ አወለቁ?” ስል ጠየቅኩት። “ልብሱን እንዲያወልቅ የምር አገዘችው?”
“እንደዛ ነው የተሰማኝ አለኝ በግድየለሽነት:
“አልጮኸችም፣ አልተቃወመችውም?”
“አልተቃወመችውም፡ እሷም ፈልጋ ነበር! አምላኬ ሆይ እና በጣም ረጅም ጊዜ ወሰደባቸው! ካቲ
የሚያወጡትን ድምፅ አታምኚም! ታቃስታለች፣ትጮሀለች አየር ያጠራት ትመስላለች፣ ታለከልካለች እና እሱ ደግሞ እንደ አሳማ ያጓራል ግን እዛ ላይ በጣም ጥሩ ሳይሆን እንደማይቀር እገምታለሁ::
ምክንያቱም በመጨረሻ ሠራተኛዋ እንዳበደ ሰው ነበር የጮኸችው። ከዚያ ሲያልቅ ጋደም ብለው ሲጋራ እያጨሱ እዚህ ቤት ስለሚደረገው ነገር እያወሩ ነበር። እመኚኝ የማያውቁት በጣም ጥቂት ነገሮችን ብቻ ነው። ከዚያ ለሁለተኛ
ጊዜ ፍቅር ሰሩ:"
“በአንድ ምሽት ሁለት ጊዜ?”
“ይቻላል።”
“ክሪስ ለምንድነው አነጋገርህ የተቀየረው?”
አመነታ፤ ትንሽ ራቅ አለና ፊቴን አጠና። “ካቲ እያዳመጥሽኝ አይደለም? ሁሉንም ነገር ልክ እንደሆነው አድርጌ ለአንቺ ለመንገር ትልቅ ህመም ውስጥ
ነኝ። አልሰማሽኝም?”
መስማት? አዎ ሰምቼያለሁ ሁሉንም:
የእናታችንን ጌጣጌጦች ለመዝረፍ ብዙ ጊዜ ጠበቀ።
እናታችንና ባሏ ሌላ ሽርሽር ሄዱ። ይሄ ምን አይነት ዜና ነው? ሁልጊዜ
ይመጣሉ… ይሄዳሉ፤ ከዚህ ቤት ለመውጣት ምንም ነገር ያደርጋሉ። እና እወቅሳቸዋለሁ ማለት አልችልም: እኛስ ተመሳሳይ ነገር ልናደርግ ተዘጋጅተን
የለ? ቅንድቦቼን ወደ ላይ ሰቅዬ ክሪስን በጥያቄ አስተያየት ተመለከትኩት ያልነገረኝ
የሆነ የሚያውቀው ነገር እንዳለ ግልፅ ነው: አሁንም እየተከላከለላት ነው። አሁንም ይወዳታል
ካቲ” ሲል ጀመረ፡ ድምፁ እየተቆራረጠ ነው
“ምንም አይደል ክሪስ፣ እየወቀስኩህ አይደለም ውዷ፣ ጣፋጯ፣ ደጓና አፍቃሪዋ እናታችን ከመልከመልካም ወጣት ባሏ ጋር ጌጣጌጣቸውን ሁሉ ይዘው ሌላ ሽርሽር ሄዳለች፡ በውጪው አለም ያለውን ጥበቃ ደህና ሁን
በለው: ግን አሁንም እሄዳለሁ! እንሰራለን ራሳችንን የምንደግፍበት መንገድ እንፈልጋለን፡ ከዚያ ኬሪ እንደገና ደህና እንድትሆን ለዶክተር እንከፍላለን፡ዠ ስለጌጣጌጦች አትጨነቅ፤ ስለ እናታችን ርህራሄ የለሽ ድርጊት አትጨነቅ።
የት እንደምትሄድ፣ መቼ እንደምትመለስ እንኳን አልነገረችንም: አሁን አስቀያሚ መጥፎ የማናስብ ቸልተኞች እንድንሆን ተትተናል፡ ታዲያ ይሄ
ሁሉ ዕንባ ለማን? ለምን?
"ካቲ!” ተቆጣ በእምባ የረጠበ ፊቱን ወደ እኔ መልሶ አይኖቼ ላይ አተኮረ:
“ለምንድነው የማታዳምጪውና የሆነ ነገር የማትይው? ጆሮሽ የት ነው? ያልኩትን ሰምተሽኛል? ወንድ አያታችን ሞቷል! ከሞተ አንድ አመት ገደማ ሆኖታል!”
ምናልባት በደንብ አልሰማሁትም፤ በጥንቃቄ አላዳመጥኩትም ማለት ነው ሀዘኑ ምንም ነገር እንዳልሰማ አድርጎኛል ማለት ነው አሁን ለመጀመሪያ ጊዜ ሙሉ በሙሉ መታኝ አያትየው በእውነት ከሞተ እጅግ መልካም ዜና ነው አሁን እናታችን ውርስ ታገኛለች… ሀብታም እንሆናለን…በሩን ትከፍትልናለች… ነፃ ታደርገናለች:: አሁን ለማምለጥ መሞከር የለብንም:
ሌሎች ሀሳቦች ጎረፉ አስደንጋጭ የጥያቄ ጎርፍ መጣብኝ። እናታችን አባቷ መሞቱን አልነገረችንም:: እነዚህ አመታት ለእኛ እንዴት ረጃጅም እንደሆኑ እያወቀች፣ ለምን በጨለማ ሁልጊዜ በመጠበቅ ውስጥ አስቀመጠችን? ለምን?
ግራ ተጋባሁ። ተደናገረብኝ፤ የትኛው ስሜት እንደሚሰማኝ አላውቅኩም። ደስታ ይሁን ሀዘን ሀሳቤን አለመቁረጤን ሽባ የሚያደርግ እንግዳ ፍርሀት
አስቆመኝ።
“ካቲ…” አለኝ ክሪስ በሹክሹክታ። ለምን ማንሾካሾክ እንዳለበት አላወቅኩም ኬሪ እንደሆነች አትሰማም: የእሷ አለም ከእኛ በእጅጉ ተለይቷል ኬሪ
በህይወትና በሞት መካከል ተንጠልጥላለች: በእያንዳንዱ ቅፅበት ወደ ኮሪ እየተጠጋች ነው: ራሷን በማስራብ ያለ ግማሽ አካሏ ለመኖር መፈለጓን ትታዋለች። “እናታችን ሆን ብላ አታላናለች: ካቲ አባቷ ሞቶ ከወራት በኋላ
ኑዛዜው ተነቧል። እና ሳትነግረን ፀጥ ብላ ሞታችንን እንድንጠብቅ እዚህ ተወችን፡ ከዘጠኝ ወራት በፊት ሁላችንም በዘጠኝ ወራት ጤናማ ነበርን! አባቷ የሞተ ጊዜ ከዚህ አስወጥታን ቢሆን ወይም ኑዛዜው የተነበበ ጊዜ እንኳን ወጥተን ቢሆን ኮሪ አሁን በህይወት ይኖር ነበር፡"
ስሜቴ ተጎድቶ እናታችን ልታሰምጠን የቆፈረችው ጥልቅ የክህደት ጉድጓድ ውስጥ ወደቅኩ። ማልቀስ ጀመርኩ።
“ዕንባሽን ለበኋላ አቆይው" አለ ክሪስ ራሱም እያለቀሰ ነው። “ሁሉንም ነገር አልሰማሽም ሌላም አለ። ብዙና የከፋ”
“ብዙ?” ሌላ ምን ብዙ ነገር ሊነገረኝ ይችላል? እናታችን ከእንግዲህ
ከማትወዳቸውና ከማትፈልጋቸው ልጆቿ ጋር መካፈል የማትፈልገውን
ንብረት በማካበት ሂደት ውስጥ ኮሪን የገደለች፣ውሽታም፣ አታላይና
ወጣትነታችንን የሰረቀች ሌባ መሆኗ ተረጋግጧል። በዚያ ምሽት ደስተኛ ባለመሆናችን ትንሽዋን ንስሀችንን ስትሰጠን ምን መጠበቅ እንዳለብን እንዴት አሳምራ እንዳብራራችልን! የዚያን ጊዜ አያታችን የሰራት አይነት
ሴት እንደምትሆን ታውቅ ወይስ ትገምት ነበር ይሆን? ክሪስ ክንዶች ላይ ወደቅኩና ደረቱን ተደገፍኩ “ከዚህ በላይ አትንገረኝ! የሰማሁት ይበቃኛል ከዚህ በላይ እንድጠላት አታድርገኝ! አልኩት።
“መጥላት. ጥላቻ ምን እንደሆነ ገና ማወቅ አልጀመርሽም ግን የቀረውን
ከመናገሬ በፊት ምንም ቢሆን ይህንን ቦታ ለቀን እንደምንሄድ አስቢ።እንዳቀድነው ወደ ፍሎሪዳ እንሄዳለን በፀሀይ ብርሀን ውስጥ እንኖራለን::እና ህይወታችንን በቻልነው ሁሉ በጣም ጥሩ እናደርገዋለን። ማን በመሆናችን ወይም በስራነው ለአንዲት ሰኮንድ እንኳን ሳናፍር እንኖራለን።
በመሀከላችን የተፈጠረው ነገር እናታችን ካደረገችው ጋር ሲነፀር ምንም ማለት አይደለም ከእኔ በፊት ብትሞቺም እንኳን፣ እዚህ ጣሪያ ስር ያለው ክፍል የነበረንን ህይወት ሁልጊዜ አስታውሰዋለሁ: በወረቀት አበባዎቹ ስር ስንደንስ አንቺ በጣም ግርማ ያለሽ እኔ ደግሞ ገልጃጃ ሆኜ የአቧራውንና የበሰበሰ እንጨቱን ሽታ ልክ እንደ ጣፋጭ ሽቶ አስታውሰዋለሁ ምክንያቱም
ህይወቴ ያላንቺ በጣም ቀፋፊና ባዶ ነው የሚሆነው። ፍቅር ምን ሊሆን
እንደሚችል የመጀመሪያውን ጣዕም ሰጥተሽኛል።
👍40❤3🥰3👎2😢2
#ሳቤላ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
በተከታዩ መጋቢት አንድ መንገደኛ ወደ ግረኖብል መጣ በጣም ንፋሳም ቀን ነበር ሰውየው እንግሊዛዊ ነበርና አንዱን ዕቃ ተሸካሚ ጥሩ ሆቴል የት እንደሚገኝ እንደ ነገሩ በሚችለው በእንግሊዛዊ ፈረንሳይኛ ጠየቀው "
ሰውየው አሰብ አደርገና በእርጋታና በትሕትና አንድ አካባቢ ላይ ሁለት
ጥሩ ሆቴሎች አሉ ትርዋ ዶፏ እና አምባሳዶሮች ከሁለቱም እኩል አገልግሎት ሊያገኙ ይችላሉ
እንግዳው ሰው ባጋጣሚ አምባሳደሮችን መረጠና ሔደ
ትንሽ ዐረፍ እንዳለ ወደ ግረኖብል አደባባይ የሚወስደውን መንገድ ጠየቀ እሱ እንኳን መሪ ተሰጥቶት
ነበር ግን ብቻውን መሔድ ፈለገ ከቦታው ደርሶ ወይዘሮ ሳቤላ ቬን ወደምትኖርበት ቤት ታጠፈ "
ሳቤላ አሁንም ሙቀቱን የእሳቱን ፍንጣሪ ጭምር ደጅ እየጠናች ልክ ባለፈው ታኅሣሥ ከነበረችበት ቦታና ሁኔታ እሳቷን አቅፋ ተቀምጣለች" እሳቱን ምን ያህል እንደ ተጠጋችው ለተመለከተ በነበልባሉ ልብሷ አለመያያዙ ያስገርመዋል " ክፍሉን
ቀና ብሎ ለሚያይ ሁሉም ነገር ሳይነካካ ስለ ነበር ባለፈው ታኅሣሥ ሳይሆን በትናንቱ ዕለት ያየው ይመስለው ነበር " በአልጋው አጐበር በከፊል የተጋረደውና
ሕፃኑ ተጠቅልሎ የተኛበት የልጅ አልጋ እንኳን ከነበረበት አልተለወጠም።
ወይዘሮ ሳቤላ አካላቸውንና አእምሮአቸውን በታመሙ ሰዎች ላይ እንደሚደርሰው ሁሉ የሷም ጤንነት ቶሎ አልመለስ አለ ከላይ በተባለው ዐይነት እንደ
ተቀመጠች ሱዛን ገብታ አንድ እንግሊዛዊ መኮንን መምጣቱን ነገረቻት "
ሳቤላ ደነገጠች እሷን የሚጠይቅ እንግሊዛዊ መኮንን ማን ይሆን ብላ ተጠራጠረች
“ መቸም እንግሊዛዊ ነው ” አለች ሱዛን ፈረንሳይኛውን ለመረዳት ተቸግራ ስለ ነበር" “ ረጅም መልከኛ ረጋ ያለ መስፍን የመሰለ ከባድ ሰው ነው ” ብላ
አብራራችላት "
ወይዘሮ ሳቤላ ይባሱን ደነገጠች ልቧ ጐኗን ሰንጥቆ ለመውጣት የፈለገ ይመስል እየዘለለ ይመታ ጀመር " የሱዛን ገለጻ የሚስተር ካርላይልን መልክ አመጣባት
ከተቀመጠችበት ተነሥታ ወደ ምድር ቤት ወርዳ መቀበል ተንገዳገደች " ሁኔታዋን ስታይ ጊዜ ሱዛንም ምላሷን ፈታች
“ እመቤት አበዱ ወይስ በጤናዎ ነው ” አለቻት " የፎቁን ደረጃ ስትወርድ እንደምትወድቅና ምናልባት ሆስፒታል ካልሔዶች በቀር ሰው እንደማትሆን በመገንዘብ „ “ሰውዬውም ሽበት የቀላቀለ ያምሳ ዓመት ሰው የሚሆን ነው.” ወጣት እንኳን አይዶለም • ስለዚሀ እርስዎ ከመኝታ ቤትዎ እንዳሉ እንግዳውን ወዲህ ባመጣው ምን ያስከፋል ? ”
አሁን ስለ እንግዳው የበለጠ ስታብራራላት ሚስተር ካርላይል አለመሆኑን ዐወቀችና ልቧ ረጋ " እንዲያውም እሱ ይሆናል ብላ በማሰቧም በራሷ የዋህነት
ሳቀች " ቀጠለችና ምናልባት ፍራንሲዝ ሌቪሰን ገንዘብ እንድትቀበል የሚያግባባ
ሰው ልኮባት ሳይሆን እንደማይቀር በመገመት ላለማነጋገር ቆረጠች »
ሱዛን .. በይ እንግዲያው ውረጅና የሰውዬውን ማንነትና የመጣበትን ቦታ ጠይቂው ” አለቻት
ሱዛን ወዲያው ወጥታ እንዲገባ ትጥራው ወይም ራሱን ይጋብዝ
አይታወቅም ሰውዬውን አስከትላ ብቅ አለች ሳቤላ ገና ስታየው እጆቿን ዘርግታ አራገበችና በኃፍረት የሚቃጠሉት ሁለቱን ጉንጮን እፍን አድርጋ ያዘች እንግዳው ሎርድ ማውንት እስቨርን ነበር !!
" ያለሁበትን በምን ዐውቀህ መጣህ ? "
በቅርቡ በተመለከትኳቸው አንዳንድ ነገሮች መለያየታችሁን የሚጠቁም ሁኔታዎች ስላየሁባቸው አንቺን ከምን እንዳደረሰሽ መጠየቅ አስፈላጊ ሆኖ አገኘሁትና ሰር ፍራንሲዝ ሌቪሰን ዘንድ ሔጄ አድራሻሽን ጠየቅሁት ”
“ ካለፈው ሐምሌ ጀምረን ተለያየን " በታኅሣሥ መጥቶ ነበር” ለአንድ ሰዓት በነገር ስንናቆር ቆይተን ተመልሶ ሔደ "
“ ስለሱ በቅርቡ ምን ሰምተሻል ? ”
“ ምንም ነገር አልሰማሁም » አሁን እኮ በአገራችን የሚደረገውን ነገር ምንም አላውቅም " ጋዜጣ የለኝም " ከማንም ጋር አልጻጻፍም " እሱም ቢሆን እስከዚህ ደፍሮ አይጽፍልኝም ”
“ እንግዲያውስ ስለሱ የሰማሁትን አንዳንድ ወሬ ብነግርሽ አላስደነግጥሽም ። ''
“ እኔ በጣም ልደነግጥና ሊዘገንነኝ የሚችለው እሱን ለማየት የምገደድ መሆኔን የሰማሁ እንደሆነ ብቻ ነው
“ እየውልሽ . . . በቅርቡ አገባ "
“ እሱን ያገባች ያልታደለች ናት ” አለችው እመቤት ሳቤላ ።
“ አሊስ ሻሎነርን ነው እኮ ያገባ ”
ራሷን ቀና አደረገችና እንደ መገረም ብላ“አሊስን? ብላንሽን አይደለም?” ብላ
ጠየቀችው ።
“ብላንሽን አታለላት እየተባለ ይወራል " እሷን እንደሚያገባት ተስፋ እየሰጠ ቆየና ሳታስብ ታናሽ እኅቷን ለማጨት ጠየቀ " እኔ ለራሌ ዝርዝር ነገሩን አላውቀውም ነበር " በቀደምለት ከክበብ ሳለን ሥርዓተ ተክሊሉን በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የሚፈጽም መሆኑን አንድ ጽሑፍ አየሁ " እኔም ከሱ ቀድሜ ቤተክርስቲያን ደረስኩና ምን እንዳደረገሽ የት እንዳለሽ አጥብቄ ስጠይቀው ይኸን አድራሻ
ሰጠኝ ከታኅሣሥ ወዲህ ተንቀሳቅስሽ እንደሆነ ግን የማያውቅ መሆኑን ነገረኝ
ረጂም ጸጥታ ሆነ " ኧርሉ ክፍሉን በዐይኑ እየቃኘ ነገር የሚያሰላስል ይመስል ነበር " ሳቤላ አንገቷን ደፍታ ተቀመጠች "
“ለምን ልትፈልገኝ መጣህ ? አሁን እኔ ምኔ ይፈለጋል ስምህን በአሳፋሪ ሥራዬ አሰነሣሁት እኔ አን† ልትፈልገኝ የሚገባኝ ሰው አይደለሁም "
የምትይው እውነት ነው ! የኔን ስም ብቻ ሳይሆን የባልሽንና የልጆችሽን ስም ጭምር ነው ያዋረድሽው አላት ነገር የማለባበስ ጠባይ ያልነበረው ሎርድ ማውንት እስቨርን" "ቢሆንም” አለ ነገሩን በመቀጠል, “አሁን እንደገና ብቸኛ ስትሆኝ ከባሰ ችግር እንዳትወድቂ የሚያስብልሽ ከኔ የቀረበ ዘመድ ስለሌለሽ አንቺን የመጠየቅና በምችለው ሁሉ የመደገፍ ኃላፊነት አለብኝ » አንድ ሺልንግ እንኳን የለሽም አሁን እንዴት ሆነሽ ለመኖር ታስቢያለሽ ? ”
እስካሁን እንኳን ጥቂት ገንዘብ አለኝ : በኋላም . .
የሱ ገንዘብ ” ብሎ አቋረጣት ቁጣና ኩራት በተሞላበት አነጋር "
የለም ! አለችው እሷም በንዴት " ያሉኝን ጌጦች እየሽጥኩ ነው እነሱ
ከማለቃቸው በፊት ግን በሆነ መንግድ ሠርቼ ለመተዳዶር እሞክራለሁ " ምናልባትም ሕፃናትን በማስተማር "
ጌጦች?” አለ ሎርድ ማውንት እስቨርን “ ከኢስት ሊን አንድም ነገር እንዳልወሰድሽ ሚስተር ካርላይል ነግሮኛል "
" እሱ ከሰጠኝ ውስጥ አንድም አላነሳሁም እነዚህ እሱን ሳላግባ የነበሩኝ
ናቸው " ሚስተር ካርላይልን አይተኸዋል?” አለችው እጅዋን ያዝ እንዳደረጋት
“ እንዴ ምን ማለትሽ ነው ? አንድ ዘመዴ የሆነ ሰው ላይ ይህን የመሰለ ከባድ
በደል ሲደርስበት ኢስትሊን ድረስ ሔጄ ኀዘኔን መግለጽ ይብዛብኝ? ሌላው ደግሞ
ከዚህ ሁሉ ለመድረስ የበቃሽበትን ምክንያት ለማወቅ እፈልግ ነበር " ይህ አሳዛኝ ወሬ ሲደርሰኝ ካላበድሽ በቀር እንደማታደርጊው ተከራከርኩ " አንቺን
አምንብሽ ነበረ ሔጄም ያወቅሁት ነገር የለም " ካርላይልም ቢሆን ነገሩ አልገባውም እንዲያው ምን ብትሆኝ ነው እንደዚህ ጉድ ያደረግሽው ?
አንገቷን ይበልጥ አቀረቀረች " ኃፍረቷ ትኩሳትና ክሳት በመጠጠው ፊቷ ታየባት በባሏ ላይ የፈጸመችው በደል ምሬቱና ግለቱ ተሰማት ሎርድ ማውንት እስቨርንም መጸጸቷን ከገጽታዋ ላይ አነበበው "
“ሳቤላ ” አላት ከበፊቱ ኃይለኛ አነጋገሩ በረድ ባለ ድምፅ " በዚህ ስሟ
ሲጠራት የመጀመሪያ ጊዜ ነበር "
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
በተከታዩ መጋቢት አንድ መንገደኛ ወደ ግረኖብል መጣ በጣም ንፋሳም ቀን ነበር ሰውየው እንግሊዛዊ ነበርና አንዱን ዕቃ ተሸካሚ ጥሩ ሆቴል የት እንደሚገኝ እንደ ነገሩ በሚችለው በእንግሊዛዊ ፈረንሳይኛ ጠየቀው "
ሰውየው አሰብ አደርገና በእርጋታና በትሕትና አንድ አካባቢ ላይ ሁለት
ጥሩ ሆቴሎች አሉ ትርዋ ዶፏ እና አምባሳዶሮች ከሁለቱም እኩል አገልግሎት ሊያገኙ ይችላሉ
እንግዳው ሰው ባጋጣሚ አምባሳደሮችን መረጠና ሔደ
ትንሽ ዐረፍ እንዳለ ወደ ግረኖብል አደባባይ የሚወስደውን መንገድ ጠየቀ እሱ እንኳን መሪ ተሰጥቶት
ነበር ግን ብቻውን መሔድ ፈለገ ከቦታው ደርሶ ወይዘሮ ሳቤላ ቬን ወደምትኖርበት ቤት ታጠፈ "
ሳቤላ አሁንም ሙቀቱን የእሳቱን ፍንጣሪ ጭምር ደጅ እየጠናች ልክ ባለፈው ታኅሣሥ ከነበረችበት ቦታና ሁኔታ እሳቷን አቅፋ ተቀምጣለች" እሳቱን ምን ያህል እንደ ተጠጋችው ለተመለከተ በነበልባሉ ልብሷ አለመያያዙ ያስገርመዋል " ክፍሉን
ቀና ብሎ ለሚያይ ሁሉም ነገር ሳይነካካ ስለ ነበር ባለፈው ታኅሣሥ ሳይሆን በትናንቱ ዕለት ያየው ይመስለው ነበር " በአልጋው አጐበር በከፊል የተጋረደውና
ሕፃኑ ተጠቅልሎ የተኛበት የልጅ አልጋ እንኳን ከነበረበት አልተለወጠም።
ወይዘሮ ሳቤላ አካላቸውንና አእምሮአቸውን በታመሙ ሰዎች ላይ እንደሚደርሰው ሁሉ የሷም ጤንነት ቶሎ አልመለስ አለ ከላይ በተባለው ዐይነት እንደ
ተቀመጠች ሱዛን ገብታ አንድ እንግሊዛዊ መኮንን መምጣቱን ነገረቻት "
ሳቤላ ደነገጠች እሷን የሚጠይቅ እንግሊዛዊ መኮንን ማን ይሆን ብላ ተጠራጠረች
“ መቸም እንግሊዛዊ ነው ” አለች ሱዛን ፈረንሳይኛውን ለመረዳት ተቸግራ ስለ ነበር" “ ረጅም መልከኛ ረጋ ያለ መስፍን የመሰለ ከባድ ሰው ነው ” ብላ
አብራራችላት "
ወይዘሮ ሳቤላ ይባሱን ደነገጠች ልቧ ጐኗን ሰንጥቆ ለመውጣት የፈለገ ይመስል እየዘለለ ይመታ ጀመር " የሱዛን ገለጻ የሚስተር ካርላይልን መልክ አመጣባት
ከተቀመጠችበት ተነሥታ ወደ ምድር ቤት ወርዳ መቀበል ተንገዳገደች " ሁኔታዋን ስታይ ጊዜ ሱዛንም ምላሷን ፈታች
“ እመቤት አበዱ ወይስ በጤናዎ ነው ” አለቻት " የፎቁን ደረጃ ስትወርድ እንደምትወድቅና ምናልባት ሆስፒታል ካልሔዶች በቀር ሰው እንደማትሆን በመገንዘብ „ “ሰውዬውም ሽበት የቀላቀለ ያምሳ ዓመት ሰው የሚሆን ነው.” ወጣት እንኳን አይዶለም • ስለዚሀ እርስዎ ከመኝታ ቤትዎ እንዳሉ እንግዳውን ወዲህ ባመጣው ምን ያስከፋል ? ”
አሁን ስለ እንግዳው የበለጠ ስታብራራላት ሚስተር ካርላይል አለመሆኑን ዐወቀችና ልቧ ረጋ " እንዲያውም እሱ ይሆናል ብላ በማሰቧም በራሷ የዋህነት
ሳቀች " ቀጠለችና ምናልባት ፍራንሲዝ ሌቪሰን ገንዘብ እንድትቀበል የሚያግባባ
ሰው ልኮባት ሳይሆን እንደማይቀር በመገመት ላለማነጋገር ቆረጠች »
ሱዛን .. በይ እንግዲያው ውረጅና የሰውዬውን ማንነትና የመጣበትን ቦታ ጠይቂው ” አለቻት
ሱዛን ወዲያው ወጥታ እንዲገባ ትጥራው ወይም ራሱን ይጋብዝ
አይታወቅም ሰውዬውን አስከትላ ብቅ አለች ሳቤላ ገና ስታየው እጆቿን ዘርግታ አራገበችና በኃፍረት የሚቃጠሉት ሁለቱን ጉንጮን እፍን አድርጋ ያዘች እንግዳው ሎርድ ማውንት እስቨርን ነበር !!
" ያለሁበትን በምን ዐውቀህ መጣህ ? "
በቅርቡ በተመለከትኳቸው አንዳንድ ነገሮች መለያየታችሁን የሚጠቁም ሁኔታዎች ስላየሁባቸው አንቺን ከምን እንዳደረሰሽ መጠየቅ አስፈላጊ ሆኖ አገኘሁትና ሰር ፍራንሲዝ ሌቪሰን ዘንድ ሔጄ አድራሻሽን ጠየቅሁት ”
“ ካለፈው ሐምሌ ጀምረን ተለያየን " በታኅሣሥ መጥቶ ነበር” ለአንድ ሰዓት በነገር ስንናቆር ቆይተን ተመልሶ ሔደ "
“ ስለሱ በቅርቡ ምን ሰምተሻል ? ”
“ ምንም ነገር አልሰማሁም » አሁን እኮ በአገራችን የሚደረገውን ነገር ምንም አላውቅም " ጋዜጣ የለኝም " ከማንም ጋር አልጻጻፍም " እሱም ቢሆን እስከዚህ ደፍሮ አይጽፍልኝም ”
“ እንግዲያውስ ስለሱ የሰማሁትን አንዳንድ ወሬ ብነግርሽ አላስደነግጥሽም ። ''
“ እኔ በጣም ልደነግጥና ሊዘገንነኝ የሚችለው እሱን ለማየት የምገደድ መሆኔን የሰማሁ እንደሆነ ብቻ ነው
“ እየውልሽ . . . በቅርቡ አገባ "
“ እሱን ያገባች ያልታደለች ናት ” አለችው እመቤት ሳቤላ ።
“ አሊስ ሻሎነርን ነው እኮ ያገባ ”
ራሷን ቀና አደረገችና እንደ መገረም ብላ“አሊስን? ብላንሽን አይደለም?” ብላ
ጠየቀችው ።
“ብላንሽን አታለላት እየተባለ ይወራል " እሷን እንደሚያገባት ተስፋ እየሰጠ ቆየና ሳታስብ ታናሽ እኅቷን ለማጨት ጠየቀ " እኔ ለራሌ ዝርዝር ነገሩን አላውቀውም ነበር " በቀደምለት ከክበብ ሳለን ሥርዓተ ተክሊሉን በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የሚፈጽም መሆኑን አንድ ጽሑፍ አየሁ " እኔም ከሱ ቀድሜ ቤተክርስቲያን ደረስኩና ምን እንዳደረገሽ የት እንዳለሽ አጥብቄ ስጠይቀው ይኸን አድራሻ
ሰጠኝ ከታኅሣሥ ወዲህ ተንቀሳቅስሽ እንደሆነ ግን የማያውቅ መሆኑን ነገረኝ
ረጂም ጸጥታ ሆነ " ኧርሉ ክፍሉን በዐይኑ እየቃኘ ነገር የሚያሰላስል ይመስል ነበር " ሳቤላ አንገቷን ደፍታ ተቀመጠች "
“ለምን ልትፈልገኝ መጣህ ? አሁን እኔ ምኔ ይፈለጋል ስምህን በአሳፋሪ ሥራዬ አሰነሣሁት እኔ አን† ልትፈልገኝ የሚገባኝ ሰው አይደለሁም "
የምትይው እውነት ነው ! የኔን ስም ብቻ ሳይሆን የባልሽንና የልጆችሽን ስም ጭምር ነው ያዋረድሽው አላት ነገር የማለባበስ ጠባይ ያልነበረው ሎርድ ማውንት እስቨርን" "ቢሆንም” አለ ነገሩን በመቀጠል, “አሁን እንደገና ብቸኛ ስትሆኝ ከባሰ ችግር እንዳትወድቂ የሚያስብልሽ ከኔ የቀረበ ዘመድ ስለሌለሽ አንቺን የመጠየቅና በምችለው ሁሉ የመደገፍ ኃላፊነት አለብኝ » አንድ ሺልንግ እንኳን የለሽም አሁን እንዴት ሆነሽ ለመኖር ታስቢያለሽ ? ”
እስካሁን እንኳን ጥቂት ገንዘብ አለኝ : በኋላም . .
የሱ ገንዘብ ” ብሎ አቋረጣት ቁጣና ኩራት በተሞላበት አነጋር "
የለም ! አለችው እሷም በንዴት " ያሉኝን ጌጦች እየሽጥኩ ነው እነሱ
ከማለቃቸው በፊት ግን በሆነ መንግድ ሠርቼ ለመተዳዶር እሞክራለሁ " ምናልባትም ሕፃናትን በማስተማር "
ጌጦች?” አለ ሎርድ ማውንት እስቨርን “ ከኢስት ሊን አንድም ነገር እንዳልወሰድሽ ሚስተር ካርላይል ነግሮኛል "
" እሱ ከሰጠኝ ውስጥ አንድም አላነሳሁም እነዚህ እሱን ሳላግባ የነበሩኝ
ናቸው " ሚስተር ካርላይልን አይተኸዋል?” አለችው እጅዋን ያዝ እንዳደረጋት
“ እንዴ ምን ማለትሽ ነው ? አንድ ዘመዴ የሆነ ሰው ላይ ይህን የመሰለ ከባድ
በደል ሲደርስበት ኢስትሊን ድረስ ሔጄ ኀዘኔን መግለጽ ይብዛብኝ? ሌላው ደግሞ
ከዚህ ሁሉ ለመድረስ የበቃሽበትን ምክንያት ለማወቅ እፈልግ ነበር " ይህ አሳዛኝ ወሬ ሲደርሰኝ ካላበድሽ በቀር እንደማታደርጊው ተከራከርኩ " አንቺን
አምንብሽ ነበረ ሔጄም ያወቅሁት ነገር የለም " ካርላይልም ቢሆን ነገሩ አልገባውም እንዲያው ምን ብትሆኝ ነው እንደዚህ ጉድ ያደረግሽው ?
አንገቷን ይበልጥ አቀረቀረች " ኃፍረቷ ትኩሳትና ክሳት በመጠጠው ፊቷ ታየባት በባሏ ላይ የፈጸመችው በደል ምሬቱና ግለቱ ተሰማት ሎርድ ማውንት እስቨርንም መጸጸቷን ከገጽታዋ ላይ አነበበው "
“ሳቤላ ” አላት ከበፊቱ ኃይለኛ አነጋገሩ በረድ ባለ ድምፅ " በዚህ ስሟ
ሲጠራት የመጀመሪያ ጊዜ ነበር "
👍19
#ጠላፊዎቹ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
ማርጋሬት ከእንቅልፏ ስትነቃ ሃሳብ ውስጥ ገባች፡: ዛሬ ለአባቴ ቁርጡን እነግረዋለሁ አለች በሆዷ አሜሪካ ሲደርሱ ከእነሱ ጋር
እንደማትኖር ከቤት ወጥታ ቤት ተከራይታ እና ስራ ይዛ ልትኖር እንደሆነ
ትነግራቸዋለች፡፡ መቼም አባቷ ይህን ሲሰሙ ኮረንቲ ይጨብጣሉ፡፡
ማርጋሬት ነገሩን ባሰበችው ቁጥር ፍርሃትና ሃፍረት ይሰማታል አባቷን ለመቃወም ስትነሳ የሚሰማት ይኸው ነው፡፡ አሁን አስራ ዘጠኝ ዓመቴ ነው፡፡ አሁን ልጅ አይደለሁም፡፡ ትናንት ከድንቅ ሰው ጋር ወሲብ
ፈጽሜያለሁ፡፡ ታዲያ ለምንድነው የምፈራው? ስትል ታስባለች፡
ለምን አባቷ ሁልጊዜ እንደ አውሬ በግርግም ውስጥ እንደሚዘጉባት አይገባትም፡ ኤልሳቤትንም እንዲሁ ነበር የሚያደርጓት፡፡ ፔርሱን ግን ለቀቅ አድርገውታል፡፡ ሴት ልጆቻቸውን እንደ ጌጣጌጥ ነው የሚቆጥሯቸው: አንድ
የሆነ ስራ እንስራ ብለው የተነሱ እንደሆን ቁጣቸው ለጉድ ነው፡፡ ለምሳሌ
ዋና እንዋኝ ወይም ብስክሌት እንንዳ ብለው ቢነሱ በቃ አለቀላቸው፡
ልብስ የፈለጉትን ያህል ቢያወጡ ምንም የማይሉትን ያህል መጽሐፍ
እንግዛ ቢሉ ጸጉራቸው ይቆማል፡
ማርጋሬት ይህን ባሰበች ቁጥር ሽንፈቷ አይደለም የሚያሳምማት፡፡አባቷ የእሷን ሀሳብ ውድቅ ለማድረግ የሚያወርዱባት የስድብ ውርጅብኝና
የፌዝ ጋጋታ እንጂ፡
ብዙ ጊዜ አባቷን ለማታለል ሞክራለች፡ የተሳካላት ግን ጥቂት ጊዜ ብቻ ነው፡፡
ሁልጊዜም ከአባቷ ትዕዛዝ ውጭ የምትፈጽመው በሌሎች እርዳታ
ነው:: ስለወሲብ ያስተማረቻት ዘመዷ ሞኒካ ናት፡፡ ፔርሲ ተኩስ አስተምሯታል፡፡ ሹፌራቸው መኪና መንዳት አስለምዷታል አሁን ደግሞ
ሄሪና ናንሲ ሌኔሃን ነጻነቷን እንድትቀዳጅ ይረዷት ይሆናል።
አሁን ለየት ያለ ስሜት እየተሰማት ነው፡፡ መኝታዋ ላይ ተጋድማ መላ አካላቷን ደባበሰችው፡፡ ከዚህ ቀደም ጸጉሯ የተንጨፈረረ ቅርጿ ደግሞ የማያምር አድርጋ ትገምት ነበር፡፡ አሁን ግን ገላዋን እየወደደችው
መጥታለች፡ ሄሪ ‹‹ቅርጽሽ ያምራል›› ብሏታል
አይሮፕላኑ ውስጥ የሰዎች ሹክሹክታና የዕቃ ኳኳታ ይሰማታል ተጓዦች ከመኝታቸው እየተነሱ ነው መጋረጃውን ገለጥ አድርጋ ስታይ ዱባው አስተናጋጅ ኒኪ የእናትና የአባቷን መኝታዎች ወደ መቀመጫነት እየቀየረ ነው፡፡ ሄሪ ሙሉ ልብሱን ለብሶ ቁጭ ብሎ በተመስጦ በመስኮት ወደ ውጭ ይመለከታል፡፡
እሱን ስታይ አፈረችና ሳያያት ወዲያው መጋረጃውን ዘጋችው::ከጥቂት ሰዓት በፊት በወሲብ ሲያብዱ ቢቆዩም አሁን ግን ሁኔታው
አሳፈራት።
ሌሎቹ ሰዎች የት ሄደው ይሆን?› ስትል አሰበች፡፡ ፔርሲና አባቷ ውጭ ወጥተው ይሆናል፡ አባቷ ለወትሮው በጧት ነው የሚነሱት፡ እናቷ
ግን በጧት መነሳት አይሆንላቸውም፡፡ ምናልባትም መታጠቢያ ቤት ይሆናሉ፡ ሚስተር መምበሪም በቦታው የለም፡፡
ማርጋሬት በመስኮት ስትመለከት ነግቷል፡፡ የሰማይ በራሪው አይሮፕላን
አንድ ትንሽ የወደብ ከተማ ዳርቻ ላይ ታስሮ ቆሟል፡ እንደገና መኝታዋ ላይ
ጋደም አለች፡፡ የለሊቱ ሁኔታ በዓይነ ህሊናዋ ድቅን አለ፡፡ የትናንቱ ቀን ድንግልናዋ የተወሰደበት ቀን አድርጋ ነው የቆጠረችው፡፡ ከኢያን ጋር ስትፈጽም የነበረው ወሲብ ችግር ያልተለየውና ጥድፍ ጥድፍ ያለ ነበር፡
ከእሱ ጋር ወሲብ ከፈጸመች በኋላ ሁልጊዜ በእፍረት ትሸማቀቃለች፡ትናንት ከሄሪ ጋር ያደረገችው ግን አስደስቷታል፡፡ እያንዳንዱ የስውነት ክፍሏ እየተቆጠረና እየተዳበሰ የተፈጸመ ወሲብ ነበር፡፡ ምንም እፍረት ያልነበረበት፡፡ እንደ ሴት ራሷን የቆጠረችበት ወቅት ነበር፡፡ እንዲህ አይነት ወሲብ ከሄሪ ጋር በተደጋጋሚ መፈጸም አለብኝ አለች ለራሷ፡ የትናንት ማታው ትዝታ የወሲብ ፍላጎቷን ቀሰቀሰባትና ሰውነቷን አወራጨች።
ሄሪ የክት ልብሱን ለብሶ መስኮቱ ጋ ተቀምጦ በተመስጦ ሲያይ ሰርቃ
አየችው:፡ የሆነ ነገር እያሰላሰለ መሆኑን መልከ መልካም ፊቱ ነገራት::
ልትስመው ዳዳት፡፡ መጋረጃውን ገለጥ አደረገችና ‹‹እንደምን አደርክ ሄሪ አለችው፡፡
ድንገት የሰማው ድምጽ ሲሰርቅ እንደተያዘ ሰው አስደነገጠውና ደንብሮ
ዞር አለ፡፡ ሲያያት አየችውና ፈገግታ ተለዋወጡ፡፡ እንደ ጅል ለረጅም ጊዜ ሲሳሳቁ ቆዩ፡፡ በኋላም ማርጋሬት አይኗን ሰበረችና ተነሳች።
አስተናጋጁ የእናቷን መቀመጫ ከሚያዘጋጅበት ቀና ብሎ ‹‹ደህና አደርሽ እመቤት ማርጋሬት ቡና ላምጣልሽ?›› አላት፡
‹‹ኒኪ ይቅርብኝ አመሰግናለሁ›› አለችው ሁኔታ እንደ ጭራቅ ለራሷ
አስፈራት፡፡ ጸጉሯ ተንጨፍርሯል፡፡ ልብስም በቅጡ አልለበሰችም፡፡ ሄሪ ግን ጢሙን ተላጭቶና ዘንጦ አዲስ ሳንቲም መስሏል
ብትስመው በወደደች፡፡
ነጠላ ጫማዋን እግሯ ላይ ሰካች፤ ሌሊት ለወሲብ ስትቻኮል ሄሪ አልጋ
ስር እንዴት እንደተወችውና አባቷ ሳያይዋት እንዴት አድርጋ አንስታ አልጋው ውስጥ እንደከተተችው እየታወሳት፡፡
የሌሊት ልብሷን ስትለብስ እርቃኗን ስለነበረች ሄሪ ጡቶቿ ላይ ዓይኑን
ተከለ፡፡ ቢያያትም ምንም አልመሰላትም፡፡ ሄሪ ጡቷን ሲያይ ደስ አላት፡ የሌሊት ልብሷን መቀነት ጠበቅ አደረገችና ጸጉሯን አሻሸች፡፡
ኒክ ስራውን ጨረሰ፡፡ ሄሪን መሳም ስለፈለገች ኒኪ ከዚያ ቦታ ቶሎ እንዲ ሄድላት ፈለገች፡፡ ኒኪ ግን የልቧን ፍላጎት ስላላወቀ መቀመጫውን ላዘጋጅልሽ?›› አላት
እሺ›› አለች ውስጧ በንዴት እየጨሰ፡፡ ሄሪን ድጋሚ የምትስምበት ጊዜ እንደሰማይ ራቃት፡፡ የመታጠቢያ ዕቃዎቿን የያዘችበትን ቦርሳዋን
አነሳችና ሄሪ በሀዘኔታ እያያት ተነስታ ሄደች፡፡
ሌላው አስተናጋጅ ዴቪ መብል ክፍሉ ውስጥ ምግብ እየደረደረ ነው፡፡
እግረ መንገዷን አንድ የእንጆሪ ፍሬ ሰርቃ አፏ ላይ አደረገች፡ ስትሄድ
ብዙዎቹ መኝታዎች
ወደ መቀመጫነት ተለውጠዋል አንዳንዶቹ
ተሳፋሪዎች ቡና እየጠጡ ነው፡ ሚስተር መምበሪ ከሳይንቲስቱና ከባሮን
ጋቦን ጋር ወሬ ይዟል፡፡
መታጠቢያ ክፍሉ ውስጥ ስትገባ እናቷ መስታወት ፊት ቁጭ ብለው ይዋባሉ፡፡ እሳቸውን ስታይ እፍረት ተሰማት፡ ‹እናቴ ካለችበት አንድ ሁለት ርምጃ ርቀት ላይ እንዴት እንዲህ ያለ ነገር አደርጋለሁ? አለች በሆዷ፡
ጉንጮቿ በእፍረት በርበሬ መስለዋል፡፡ ‹‹እንዴት አደርሽ እማማ›› አለች
‹‹ምን ሆነሽ ነው ፊትሽ እንደዚህ የቀላው? እንቅልፍ አልተኛሽም እንዴ?›› ሲሉ ጠየቋት፡፡
‹‹ኧረ በደምብ ተኝቻለሁ›› አለች ማርጋሬት፡፡ ‹‹አንዲት ፍሬ እንጆሪ ከጠረጴዛ ላይ አንስቼ ስለበላሁ ነው›› አለችና መጸዳጃ ቤት ጥልቅ አለች ከዚያም መታጠቢያው ላይ ውሃ ሞላችና ፊቷን ታጠበች፡:
ትናንት የለበሰችውን ልብስ ዛሬም በመልበሷ ደስ አላላትም፡፡ የታጠበ
ልብስ ብትለውጥ በወደደች: አንገቷ ስርና ጡቶቿ ውስጥ ሽቶ
አርከፈከፈች፡፡ ሽቶ ለይቶ የሚያውቅ ያየችው ወንድ ሄሪን ብቻ ነው፡፡
ረጅም ጊዜ ፈጅታ ጸጉሯን አበጠረች፡፡ ያላት ውበቷ ጸጉሯ ስለሆነ ለጸጉሯ የማትሆነው የለም፡፡ መልኬን ለማሳመር ስል ማድረግ ያለብኝ ሁሉ
አደርጋለሁ አለች ለራሷ፡ እስካሁን ስለመልኳ ተጨንቃ አታውቅም፡፡ ዛሬ ግን አስተሳሰቧ ተለውጧል፡፡ ገላዬን ልቅም አድርጎ የሚያሳይና ረጅም ታኮ
ጫማ ያስፈልገኛል፡፡ ከገላዬና ከጸጉሬ ከለር ጋር የሚሄድ ልብስ መምረጥ
አለብኝ፡፡› አሁን የለበሰችው ልብስ እንደ ሽክላ ቀይ ነው፡፡ እንዲያው ዝም ብሎ የወረደና ቅርጸ ቢስ መሆኑን በመስታወት አይታ ትከሻውጋ ቀጥ ያለና
ወገቡ ጋ በመቀነት ሸብ የሚደረግ ቢሆን ጥሩ ነበር ስትል ተመኘች።ሜክአፕ ባትቀባባም ያላት መልክ በቂ ነው፡ ጥርሶቿም አያሳጡም፡፡
‹‹ከሚስተር ቫንዴርፖስት ጋር ለመጫወት ልትሄጂ ነው አይደለም?››
አሉ እናት፡፡
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
ማርጋሬት ከእንቅልፏ ስትነቃ ሃሳብ ውስጥ ገባች፡: ዛሬ ለአባቴ ቁርጡን እነግረዋለሁ አለች በሆዷ አሜሪካ ሲደርሱ ከእነሱ ጋር
እንደማትኖር ከቤት ወጥታ ቤት ተከራይታ እና ስራ ይዛ ልትኖር እንደሆነ
ትነግራቸዋለች፡፡ መቼም አባቷ ይህን ሲሰሙ ኮረንቲ ይጨብጣሉ፡፡
ማርጋሬት ነገሩን ባሰበችው ቁጥር ፍርሃትና ሃፍረት ይሰማታል አባቷን ለመቃወም ስትነሳ የሚሰማት ይኸው ነው፡፡ አሁን አስራ ዘጠኝ ዓመቴ ነው፡፡ አሁን ልጅ አይደለሁም፡፡ ትናንት ከድንቅ ሰው ጋር ወሲብ
ፈጽሜያለሁ፡፡ ታዲያ ለምንድነው የምፈራው? ስትል ታስባለች፡
ለምን አባቷ ሁልጊዜ እንደ አውሬ በግርግም ውስጥ እንደሚዘጉባት አይገባትም፡ ኤልሳቤትንም እንዲሁ ነበር የሚያደርጓት፡፡ ፔርሱን ግን ለቀቅ አድርገውታል፡፡ ሴት ልጆቻቸውን እንደ ጌጣጌጥ ነው የሚቆጥሯቸው: አንድ
የሆነ ስራ እንስራ ብለው የተነሱ እንደሆን ቁጣቸው ለጉድ ነው፡፡ ለምሳሌ
ዋና እንዋኝ ወይም ብስክሌት እንንዳ ብለው ቢነሱ በቃ አለቀላቸው፡
ልብስ የፈለጉትን ያህል ቢያወጡ ምንም የማይሉትን ያህል መጽሐፍ
እንግዛ ቢሉ ጸጉራቸው ይቆማል፡
ማርጋሬት ይህን ባሰበች ቁጥር ሽንፈቷ አይደለም የሚያሳምማት፡፡አባቷ የእሷን ሀሳብ ውድቅ ለማድረግ የሚያወርዱባት የስድብ ውርጅብኝና
የፌዝ ጋጋታ እንጂ፡
ብዙ ጊዜ አባቷን ለማታለል ሞክራለች፡ የተሳካላት ግን ጥቂት ጊዜ ብቻ ነው፡፡
ሁልጊዜም ከአባቷ ትዕዛዝ ውጭ የምትፈጽመው በሌሎች እርዳታ
ነው:: ስለወሲብ ያስተማረቻት ዘመዷ ሞኒካ ናት፡፡ ፔርሲ ተኩስ አስተምሯታል፡፡ ሹፌራቸው መኪና መንዳት አስለምዷታል አሁን ደግሞ
ሄሪና ናንሲ ሌኔሃን ነጻነቷን እንድትቀዳጅ ይረዷት ይሆናል።
አሁን ለየት ያለ ስሜት እየተሰማት ነው፡፡ መኝታዋ ላይ ተጋድማ መላ አካላቷን ደባበሰችው፡፡ ከዚህ ቀደም ጸጉሯ የተንጨፈረረ ቅርጿ ደግሞ የማያምር አድርጋ ትገምት ነበር፡፡ አሁን ግን ገላዋን እየወደደችው
መጥታለች፡ ሄሪ ‹‹ቅርጽሽ ያምራል›› ብሏታል
አይሮፕላኑ ውስጥ የሰዎች ሹክሹክታና የዕቃ ኳኳታ ይሰማታል ተጓዦች ከመኝታቸው እየተነሱ ነው መጋረጃውን ገለጥ አድርጋ ስታይ ዱባው አስተናጋጅ ኒኪ የእናትና የአባቷን መኝታዎች ወደ መቀመጫነት እየቀየረ ነው፡፡ ሄሪ ሙሉ ልብሱን ለብሶ ቁጭ ብሎ በተመስጦ በመስኮት ወደ ውጭ ይመለከታል፡፡
እሱን ስታይ አፈረችና ሳያያት ወዲያው መጋረጃውን ዘጋችው::ከጥቂት ሰዓት በፊት በወሲብ ሲያብዱ ቢቆዩም አሁን ግን ሁኔታው
አሳፈራት።
ሌሎቹ ሰዎች የት ሄደው ይሆን?› ስትል አሰበች፡፡ ፔርሲና አባቷ ውጭ ወጥተው ይሆናል፡ አባቷ ለወትሮው በጧት ነው የሚነሱት፡ እናቷ
ግን በጧት መነሳት አይሆንላቸውም፡፡ ምናልባትም መታጠቢያ ቤት ይሆናሉ፡ ሚስተር መምበሪም በቦታው የለም፡፡
ማርጋሬት በመስኮት ስትመለከት ነግቷል፡፡ የሰማይ በራሪው አይሮፕላን
አንድ ትንሽ የወደብ ከተማ ዳርቻ ላይ ታስሮ ቆሟል፡ እንደገና መኝታዋ ላይ
ጋደም አለች፡፡ የለሊቱ ሁኔታ በዓይነ ህሊናዋ ድቅን አለ፡፡ የትናንቱ ቀን ድንግልናዋ የተወሰደበት ቀን አድርጋ ነው የቆጠረችው፡፡ ከኢያን ጋር ስትፈጽም የነበረው ወሲብ ችግር ያልተለየውና ጥድፍ ጥድፍ ያለ ነበር፡
ከእሱ ጋር ወሲብ ከፈጸመች በኋላ ሁልጊዜ በእፍረት ትሸማቀቃለች፡ትናንት ከሄሪ ጋር ያደረገችው ግን አስደስቷታል፡፡ እያንዳንዱ የስውነት ክፍሏ እየተቆጠረና እየተዳበሰ የተፈጸመ ወሲብ ነበር፡፡ ምንም እፍረት ያልነበረበት፡፡ እንደ ሴት ራሷን የቆጠረችበት ወቅት ነበር፡፡ እንዲህ አይነት ወሲብ ከሄሪ ጋር በተደጋጋሚ መፈጸም አለብኝ አለች ለራሷ፡ የትናንት ማታው ትዝታ የወሲብ ፍላጎቷን ቀሰቀሰባትና ሰውነቷን አወራጨች።
ሄሪ የክት ልብሱን ለብሶ መስኮቱ ጋ ተቀምጦ በተመስጦ ሲያይ ሰርቃ
አየችው:፡ የሆነ ነገር እያሰላሰለ መሆኑን መልከ መልካም ፊቱ ነገራት::
ልትስመው ዳዳት፡፡ መጋረጃውን ገለጥ አደረገችና ‹‹እንደምን አደርክ ሄሪ አለችው፡፡
ድንገት የሰማው ድምጽ ሲሰርቅ እንደተያዘ ሰው አስደነገጠውና ደንብሮ
ዞር አለ፡፡ ሲያያት አየችውና ፈገግታ ተለዋወጡ፡፡ እንደ ጅል ለረጅም ጊዜ ሲሳሳቁ ቆዩ፡፡ በኋላም ማርጋሬት አይኗን ሰበረችና ተነሳች።
አስተናጋጁ የእናቷን መቀመጫ ከሚያዘጋጅበት ቀና ብሎ ‹‹ደህና አደርሽ እመቤት ማርጋሬት ቡና ላምጣልሽ?›› አላት፡
‹‹ኒኪ ይቅርብኝ አመሰግናለሁ›› አለችው ሁኔታ እንደ ጭራቅ ለራሷ
አስፈራት፡፡ ጸጉሯ ተንጨፍርሯል፡፡ ልብስም በቅጡ አልለበሰችም፡፡ ሄሪ ግን ጢሙን ተላጭቶና ዘንጦ አዲስ ሳንቲም መስሏል
ብትስመው በወደደች፡፡
ነጠላ ጫማዋን እግሯ ላይ ሰካች፤ ሌሊት ለወሲብ ስትቻኮል ሄሪ አልጋ
ስር እንዴት እንደተወችውና አባቷ ሳያይዋት እንዴት አድርጋ አንስታ አልጋው ውስጥ እንደከተተችው እየታወሳት፡፡
የሌሊት ልብሷን ስትለብስ እርቃኗን ስለነበረች ሄሪ ጡቶቿ ላይ ዓይኑን
ተከለ፡፡ ቢያያትም ምንም አልመሰላትም፡፡ ሄሪ ጡቷን ሲያይ ደስ አላት፡ የሌሊት ልብሷን መቀነት ጠበቅ አደረገችና ጸጉሯን አሻሸች፡፡
ኒክ ስራውን ጨረሰ፡፡ ሄሪን መሳም ስለፈለገች ኒኪ ከዚያ ቦታ ቶሎ እንዲ ሄድላት ፈለገች፡፡ ኒኪ ግን የልቧን ፍላጎት ስላላወቀ መቀመጫውን ላዘጋጅልሽ?›› አላት
እሺ›› አለች ውስጧ በንዴት እየጨሰ፡፡ ሄሪን ድጋሚ የምትስምበት ጊዜ እንደሰማይ ራቃት፡፡ የመታጠቢያ ዕቃዎቿን የያዘችበትን ቦርሳዋን
አነሳችና ሄሪ በሀዘኔታ እያያት ተነስታ ሄደች፡፡
ሌላው አስተናጋጅ ዴቪ መብል ክፍሉ ውስጥ ምግብ እየደረደረ ነው፡፡
እግረ መንገዷን አንድ የእንጆሪ ፍሬ ሰርቃ አፏ ላይ አደረገች፡ ስትሄድ
ብዙዎቹ መኝታዎች
ወደ መቀመጫነት ተለውጠዋል አንዳንዶቹ
ተሳፋሪዎች ቡና እየጠጡ ነው፡ ሚስተር መምበሪ ከሳይንቲስቱና ከባሮን
ጋቦን ጋር ወሬ ይዟል፡፡
መታጠቢያ ክፍሉ ውስጥ ስትገባ እናቷ መስታወት ፊት ቁጭ ብለው ይዋባሉ፡፡ እሳቸውን ስታይ እፍረት ተሰማት፡ ‹እናቴ ካለችበት አንድ ሁለት ርምጃ ርቀት ላይ እንዴት እንዲህ ያለ ነገር አደርጋለሁ? አለች በሆዷ፡
ጉንጮቿ በእፍረት በርበሬ መስለዋል፡፡ ‹‹እንዴት አደርሽ እማማ›› አለች
‹‹ምን ሆነሽ ነው ፊትሽ እንደዚህ የቀላው? እንቅልፍ አልተኛሽም እንዴ?›› ሲሉ ጠየቋት፡፡
‹‹ኧረ በደምብ ተኝቻለሁ›› አለች ማርጋሬት፡፡ ‹‹አንዲት ፍሬ እንጆሪ ከጠረጴዛ ላይ አንስቼ ስለበላሁ ነው›› አለችና መጸዳጃ ቤት ጥልቅ አለች ከዚያም መታጠቢያው ላይ ውሃ ሞላችና ፊቷን ታጠበች፡:
ትናንት የለበሰችውን ልብስ ዛሬም በመልበሷ ደስ አላላትም፡፡ የታጠበ
ልብስ ብትለውጥ በወደደች: አንገቷ ስርና ጡቶቿ ውስጥ ሽቶ
አርከፈከፈች፡፡ ሽቶ ለይቶ የሚያውቅ ያየችው ወንድ ሄሪን ብቻ ነው፡፡
ረጅም ጊዜ ፈጅታ ጸጉሯን አበጠረች፡፡ ያላት ውበቷ ጸጉሯ ስለሆነ ለጸጉሯ የማትሆነው የለም፡፡ መልኬን ለማሳመር ስል ማድረግ ያለብኝ ሁሉ
አደርጋለሁ አለች ለራሷ፡ እስካሁን ስለመልኳ ተጨንቃ አታውቅም፡፡ ዛሬ ግን አስተሳሰቧ ተለውጧል፡፡ ገላዬን ልቅም አድርጎ የሚያሳይና ረጅም ታኮ
ጫማ ያስፈልገኛል፡፡ ከገላዬና ከጸጉሬ ከለር ጋር የሚሄድ ልብስ መምረጥ
አለብኝ፡፡› አሁን የለበሰችው ልብስ እንደ ሽክላ ቀይ ነው፡፡ እንዲያው ዝም ብሎ የወረደና ቅርጸ ቢስ መሆኑን በመስታወት አይታ ትከሻውጋ ቀጥ ያለና
ወገቡ ጋ በመቀነት ሸብ የሚደረግ ቢሆን ጥሩ ነበር ስትል ተመኘች።ሜክአፕ ባትቀባባም ያላት መልክ በቂ ነው፡ ጥርሶቿም አያሳጡም፡፡
‹‹ከሚስተር ቫንዴርፖስት ጋር ለመጫወት ልትሄጂ ነው አይደለም?››
አሉ እናት፡፡
👍23❤1🥰1
#ተአምረተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
//
የጊቢዋ አጸድ ውስጥ ባለ ወንበር ላይ ቁጭ ብላ የወፎችን ዝማሬ እና የዛፎችን ሽውሽውታ እየታዘበች በሀሳብ እየናወዘች ነው፡፡ያው በህይወቷ አዲስ ክስተት ተከስቷል … አንድ ሰው ላይ ለቀናቶች ሀሳቧ እንደተጣበቀ ነው….ያ ባሪያ ልጅ ልቧን ቅልጥ ሀሰቧን ውስውስ ነው ያደረገባት፡፡ሰሚራ ከምትባለው ፍቀረኛው ጋር ያለውን ታሪክ እና የፍቅር ትስሰር ሙሉውን ታሪክ ለመጨረስ እራሱ አቅም አነሳት...ስለሱ ከማሰብ የሚያሰንፋት መስሎ እየተሰማት ነው….‹‹ለማንኛውም እስቲ ታሪኩን ልጨርስ›› ብላ ተቀመጠች …ግን ታሪኩን ለመጨረስ ንስሯ ያስፈልጋታል..እንደምታየው ደግሞ አሁን ጊቢ ውስጥ ንስሯ አይታያትም …ብዙም ሳያስጠብቃት ከሄደበት ተመልሶ መጣ
ቀጥታ ወደዛ ወደተለከፈችበት ታሪክ አመራች …አእምሯዋን ከንስሯ አዕምሮ ጋር በተለመደው መንገድ አቆራኘችው..አዎ አገኘዋቸው…ከከተማ እንውጣ ብለው ላንጋኖ ነው የሄድት …በሀይቁ ዳር በታነፀ ላውንጅ የተዘጋ መኝታ ክፍል ውስጥ ናቸው፡፡
//////
ህይወት ልክ እንደካርታ ጫወታ ነች…ይበወዝና ተጫዋች ለሆኑት ኗዋሪዎቾ የሚታደል ዕጣ ፋንታ በሚሉት ምናባዊ ሀዲድ የምትሸረብ…አጋጣሚ በተባለ የህይወት ሰንሰለታማ ጉዞ ላይ በትክክለኛው ቦታ በትክክለኛው ጊዜ አንዱ ካንዱ በመገጣጠም መላተም እና በሌላ ገጽ ላይ በሰከንድ ሽርፍራፊ ሰከንድ መዘግየት ተፈጥሮ ተፈላልጎም ሳይገናኙ መተላለፍን በውስጧ የያዘች….
በጣርነው መጠን ማናገኝባት…ባመረትነው መጠን ማንሰበስብባት…በተመኘነው መንገድ ማንጓዝበት..እንደሎተሪ ዕጣ ብዙዎቻችን የምንከስርባት…የተወሰነው በማስተዛዘኛ የምንፅናናባት..ጥቂቶች ደግሞ እንደው ጠብታ ላባቸውን በአልማዝ ተመንዝሮ እጃቸው ላይ የሚቀመጥላቸው …ውጥናቸውን አለም ጠቅላላ ተረባርቦ ከግብ የሚያደርስልቸው ከእርጥብ እድል ጋር የተፈጠሩ…ንግግራቸውን በደቂቃ አለም የሚያደምጥላቸው…እነሱ ለተከዙት አለም ተንሰቅስቆ የሚያለቅስላቸው …እንዲሁ መርቆ የፈጠራቸው አሉ፡፡ … እና ህይወት የካርታ ጫወታ ነች…የጫወታውን ህግ ግን ተፈጥሮዊ ብቻ አይደለም..ሰው ሰራሽም ጭምር ነው …
ይሄንን ሀሳብ ያሰበችው ሰሚራ ነች ..ፍቅረኛዋ መላኩ ደረት ላይ ጋደም ብላ እያሰላሰለች የምትገኘው፡፡እንዴት እንዲህ ልሆን ቻልኩ....?እንዴት ከበሽተኛዬ ጋር ፍቅር ውስጥ ገባሁ…...?አጋጣሚው ነው ወደዛ የገፋኝ ወይስ እራሴ ነኝ ፈቅጄ እና አስቤ ወደዚህ ደረቱ ላይ ወደተጋደምኩት ልጅ ልብ ውስጥ የገባሁት…...?
‹‹ምን እያሰብሽ ነው..?››ድንገት በጠየቃት ጥያቄ ለውስጥ ጥያቄዋ መልስ ሳታገኝ አቋረጠችው፡፡
‹‹መቼ ጥለህኝ እንደምትሄድ እያሰብኩ ነው››አለችው…ለምን እንደዛ እንዳለችው ለራሷም አልተገለጸላትም… ..ምክንያም እያሰበች ያለችው ያንን እንዳልሆነ እሷና እግዚያብሄር ያውቃሉ….ሳታስብ ከንፈሯ ላይ የመጣላት ድንገታዊ መልስ የእውነት ስጋቷ አይደለም ማለት ግን አይቻልም…
‹‹የት ነው ጥዬሽ የምሄደው..?››
‹‹ወደኑሮህ ነዋ››
‹‹ኑሮ ማለት እኮ የህይወት ደስታሽ የሚመረትበት ቦታ ነው….ማንም ሰው በህይወቱ የሚባክነው ያንን ቦታ ፍለጋ ነው…የደስታው ምንጭ የሚፈልቅበትን ጥግ ለማግኘት …የሰው ልጅ ስኬትም የሚለካው በዚህ ነው…እና እኔ እድለኛ ነኝ .ብዙም ሳለፋ በተዐምራዊ አጋጣሚ አንቺን አግኝቼያለሁ….እንዳገኘውሽ ያወቅኩት ደግሞ በአሁኑ ጊዜ በቃ ስትስቂ ልቤ ትቀልጣለች…ትንፋሽሽን ወደውስጤ ስስበው በሰውነቴ ውስጥ በስብሰው ያበቃላቸው ሴሎቼ እንኳን መልሰው ህይወት ሲዘሩ ራሱ ይታወቀኛል…..ከጎኔ መኖርሽን ሳይ ዓለም ጠቅላላ ተሰብስባ ከእጄ የገባች ይመስለኝና ልቤ በኩራት አብጣ ልትፈነዳ ትደርሳለች..እና ከአንቺ ተለይቼ መሄድ ማለት ወደባዶነት ሸለቆ ተወርውሮ መከስከስ ማለት እንደሆነ ሚጠፋኝ ይመስልሻል …...?አሁን ባለሁበት ሁኔታ ከንቺ ውጭ ኑሮ ማለት ሲም ካርድ የሌለው ባዶ የሞባይል ቀፎ መሆን ማለት ነው…..››
ከትከት ብላ ሳቀች..ኪ…ኪ..ኪ…እንዴ ‹‹ነገሩን ሁሉ እኮ ስነጽሁፋዊ አደረከው…ከእኔ ከመገናኘትህ በፊት ነጋዴ ነበርኩ ብለሀኝ አልነበር እንዴ..?››
‹‹አዎ በጣም ጎበዝ ነጋዴ ነበርኩ…ምን ተፈጠረ..?››
‹‹አይ ንግግርህ የደራሲ እንጂ የነጋዴ አልመሰለኝ አለኛ…..››
‹‹አታውቂም እንዴ..? ፍቅር እና ችግር ያፈላስፋሉ እኮ….!!!››
‹‹አይ ጥሩ….ለማንኛውም የቀልድህንም ቢሆን በሰማሁት ነገር ደስ ብሎኛል….ምነው በተናገረው መጠን ሊያፈቅረኝ በቻለም ብዬ ተመኝቼያለሁ››
ከደረቱ ላይ ቀና አድርጎ አነሳትና እሱም ከተጋደመበት ቀና ብሎ ተቀመጠ… ወደእሷ ዞሮ አይን ዓይኗን እያየ‹‹አላመንሺኝም እንዴ ..? የምሬን ነው የተናገርኩት….በጣም ነው ያፈቀርኩሽ ..ወደፊት ማግባት የምፈልገው አንቺን ነው….የልጆቼ እናት ላደርግሽም እፈልጋለሁ….. ››
አንገቷን ወደእሱ ዘንበል አድርጋ እጆቾን በመዘርጋት ተጠመጠመችበት ..‹‹በጣም ነው የማፈቅርህ አንተን ስላገኘው እድለኛ ነኝ››
…..
‹‹እሺ አሁን ወጣ ብለን ቢች ዳር ዘና እንበል…..››አላት በሀሳቡ ተስማማችና ተያይዘው ወጡ…
ላንጋኖ ሀይቅ ላይ ያረፈችው የማታዋ ጀንበር ልዩ ህብረቀለም እየረጨች ስትታይ ለአካባቢው ልዩ ውበት አልብሳዋለች…. ቢች ዳር ኳስ የሚጫወቱ አሉ..ሀይቅ ውስጥ ገብተው የሚዋኙን የሚንቦጫረቁም ጥቂት አይደሉም…… በአካባቢው ደስታ ተመርቶ የሚታደል ወይንም ከንፋሱ ጋር ተቀላቅሎ አየሩን እየሞላው በስፍራው ያለው ሰው ሁሉ እየማገው የሚፈግና የሚደሰት ይመስላል፡፡
‹‹ትዋኚያለሽ …..?››
‹‹አረ ይቅርብኝ …ዝምብለን እዚህ ሳሩ ላይ ቁጭ እንበልና በማየት እንደሰት..ባይሆን ቆይቶ ከነሸጠኝ አብረን እንገባለን›› አለችውና ቁጭ አለች ..ተከትሎት ከጎኗ ቁጭ አለ…….
✨ይቀጥላል✨
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
//
የጊቢዋ አጸድ ውስጥ ባለ ወንበር ላይ ቁጭ ብላ የወፎችን ዝማሬ እና የዛፎችን ሽውሽውታ እየታዘበች በሀሳብ እየናወዘች ነው፡፡ያው በህይወቷ አዲስ ክስተት ተከስቷል … አንድ ሰው ላይ ለቀናቶች ሀሳቧ እንደተጣበቀ ነው….ያ ባሪያ ልጅ ልቧን ቅልጥ ሀሰቧን ውስውስ ነው ያደረገባት፡፡ሰሚራ ከምትባለው ፍቀረኛው ጋር ያለውን ታሪክ እና የፍቅር ትስሰር ሙሉውን ታሪክ ለመጨረስ እራሱ አቅም አነሳት...ስለሱ ከማሰብ የሚያሰንፋት መስሎ እየተሰማት ነው….‹‹ለማንኛውም እስቲ ታሪኩን ልጨርስ›› ብላ ተቀመጠች …ግን ታሪኩን ለመጨረስ ንስሯ ያስፈልጋታል..እንደምታየው ደግሞ አሁን ጊቢ ውስጥ ንስሯ አይታያትም …ብዙም ሳያስጠብቃት ከሄደበት ተመልሶ መጣ
ቀጥታ ወደዛ ወደተለከፈችበት ታሪክ አመራች …አእምሯዋን ከንስሯ አዕምሮ ጋር በተለመደው መንገድ አቆራኘችው..አዎ አገኘዋቸው…ከከተማ እንውጣ ብለው ላንጋኖ ነው የሄድት …በሀይቁ ዳር በታነፀ ላውንጅ የተዘጋ መኝታ ክፍል ውስጥ ናቸው፡፡
//////
ህይወት ልክ እንደካርታ ጫወታ ነች…ይበወዝና ተጫዋች ለሆኑት ኗዋሪዎቾ የሚታደል ዕጣ ፋንታ በሚሉት ምናባዊ ሀዲድ የምትሸረብ…አጋጣሚ በተባለ የህይወት ሰንሰለታማ ጉዞ ላይ በትክክለኛው ቦታ በትክክለኛው ጊዜ አንዱ ካንዱ በመገጣጠም መላተም እና በሌላ ገጽ ላይ በሰከንድ ሽርፍራፊ ሰከንድ መዘግየት ተፈጥሮ ተፈላልጎም ሳይገናኙ መተላለፍን በውስጧ የያዘች….
በጣርነው መጠን ማናገኝባት…ባመረትነው መጠን ማንሰበስብባት…በተመኘነው መንገድ ማንጓዝበት..እንደሎተሪ ዕጣ ብዙዎቻችን የምንከስርባት…የተወሰነው በማስተዛዘኛ የምንፅናናባት..ጥቂቶች ደግሞ እንደው ጠብታ ላባቸውን በአልማዝ ተመንዝሮ እጃቸው ላይ የሚቀመጥላቸው …ውጥናቸውን አለም ጠቅላላ ተረባርቦ ከግብ የሚያደርስልቸው ከእርጥብ እድል ጋር የተፈጠሩ…ንግግራቸውን በደቂቃ አለም የሚያደምጥላቸው…እነሱ ለተከዙት አለም ተንሰቅስቆ የሚያለቅስላቸው …እንዲሁ መርቆ የፈጠራቸው አሉ፡፡ … እና ህይወት የካርታ ጫወታ ነች…የጫወታውን ህግ ግን ተፈጥሮዊ ብቻ አይደለም..ሰው ሰራሽም ጭምር ነው …
ይሄንን ሀሳብ ያሰበችው ሰሚራ ነች ..ፍቅረኛዋ መላኩ ደረት ላይ ጋደም ብላ እያሰላሰለች የምትገኘው፡፡እንዴት እንዲህ ልሆን ቻልኩ....?እንዴት ከበሽተኛዬ ጋር ፍቅር ውስጥ ገባሁ…...?አጋጣሚው ነው ወደዛ የገፋኝ ወይስ እራሴ ነኝ ፈቅጄ እና አስቤ ወደዚህ ደረቱ ላይ ወደተጋደምኩት ልጅ ልብ ውስጥ የገባሁት…...?
‹‹ምን እያሰብሽ ነው..?››ድንገት በጠየቃት ጥያቄ ለውስጥ ጥያቄዋ መልስ ሳታገኝ አቋረጠችው፡፡
‹‹መቼ ጥለህኝ እንደምትሄድ እያሰብኩ ነው››አለችው…ለምን እንደዛ እንዳለችው ለራሷም አልተገለጸላትም… ..ምክንያም እያሰበች ያለችው ያንን እንዳልሆነ እሷና እግዚያብሄር ያውቃሉ….ሳታስብ ከንፈሯ ላይ የመጣላት ድንገታዊ መልስ የእውነት ስጋቷ አይደለም ማለት ግን አይቻልም…
‹‹የት ነው ጥዬሽ የምሄደው..?››
‹‹ወደኑሮህ ነዋ››
‹‹ኑሮ ማለት እኮ የህይወት ደስታሽ የሚመረትበት ቦታ ነው….ማንም ሰው በህይወቱ የሚባክነው ያንን ቦታ ፍለጋ ነው…የደስታው ምንጭ የሚፈልቅበትን ጥግ ለማግኘት …የሰው ልጅ ስኬትም የሚለካው በዚህ ነው…እና እኔ እድለኛ ነኝ .ብዙም ሳለፋ በተዐምራዊ አጋጣሚ አንቺን አግኝቼያለሁ….እንዳገኘውሽ ያወቅኩት ደግሞ በአሁኑ ጊዜ በቃ ስትስቂ ልቤ ትቀልጣለች…ትንፋሽሽን ወደውስጤ ስስበው በሰውነቴ ውስጥ በስብሰው ያበቃላቸው ሴሎቼ እንኳን መልሰው ህይወት ሲዘሩ ራሱ ይታወቀኛል…..ከጎኔ መኖርሽን ሳይ ዓለም ጠቅላላ ተሰብስባ ከእጄ የገባች ይመስለኝና ልቤ በኩራት አብጣ ልትፈነዳ ትደርሳለች..እና ከአንቺ ተለይቼ መሄድ ማለት ወደባዶነት ሸለቆ ተወርውሮ መከስከስ ማለት እንደሆነ ሚጠፋኝ ይመስልሻል …...?አሁን ባለሁበት ሁኔታ ከንቺ ውጭ ኑሮ ማለት ሲም ካርድ የሌለው ባዶ የሞባይል ቀፎ መሆን ማለት ነው…..››
ከትከት ብላ ሳቀች..ኪ…ኪ..ኪ…እንዴ ‹‹ነገሩን ሁሉ እኮ ስነጽሁፋዊ አደረከው…ከእኔ ከመገናኘትህ በፊት ነጋዴ ነበርኩ ብለሀኝ አልነበር እንዴ..?››
‹‹አዎ በጣም ጎበዝ ነጋዴ ነበርኩ…ምን ተፈጠረ..?››
‹‹አይ ንግግርህ የደራሲ እንጂ የነጋዴ አልመሰለኝ አለኛ…..››
‹‹አታውቂም እንዴ..? ፍቅር እና ችግር ያፈላስፋሉ እኮ….!!!››
‹‹አይ ጥሩ….ለማንኛውም የቀልድህንም ቢሆን በሰማሁት ነገር ደስ ብሎኛል….ምነው በተናገረው መጠን ሊያፈቅረኝ በቻለም ብዬ ተመኝቼያለሁ››
ከደረቱ ላይ ቀና አድርጎ አነሳትና እሱም ከተጋደመበት ቀና ብሎ ተቀመጠ… ወደእሷ ዞሮ አይን ዓይኗን እያየ‹‹አላመንሺኝም እንዴ ..? የምሬን ነው የተናገርኩት….በጣም ነው ያፈቀርኩሽ ..ወደፊት ማግባት የምፈልገው አንቺን ነው….የልጆቼ እናት ላደርግሽም እፈልጋለሁ….. ››
አንገቷን ወደእሱ ዘንበል አድርጋ እጆቾን በመዘርጋት ተጠመጠመችበት ..‹‹በጣም ነው የማፈቅርህ አንተን ስላገኘው እድለኛ ነኝ››
…..
‹‹እሺ አሁን ወጣ ብለን ቢች ዳር ዘና እንበል…..››አላት በሀሳቡ ተስማማችና ተያይዘው ወጡ…
ላንጋኖ ሀይቅ ላይ ያረፈችው የማታዋ ጀንበር ልዩ ህብረቀለም እየረጨች ስትታይ ለአካባቢው ልዩ ውበት አልብሳዋለች…. ቢች ዳር ኳስ የሚጫወቱ አሉ..ሀይቅ ውስጥ ገብተው የሚዋኙን የሚንቦጫረቁም ጥቂት አይደሉም…… በአካባቢው ደስታ ተመርቶ የሚታደል ወይንም ከንፋሱ ጋር ተቀላቅሎ አየሩን እየሞላው በስፍራው ያለው ሰው ሁሉ እየማገው የሚፈግና የሚደሰት ይመስላል፡፡
‹‹ትዋኚያለሽ …..?››
‹‹አረ ይቅርብኝ …ዝምብለን እዚህ ሳሩ ላይ ቁጭ እንበልና በማየት እንደሰት..ባይሆን ቆይቶ ከነሸጠኝ አብረን እንገባለን›› አለችውና ቁጭ አለች ..ተከትሎት ከጎኗ ቁጭ አለ…….
✨ይቀጥላል✨
👍129👎15❤14👏6😁2🔥1
#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ዶ/ር ሶፊያ ቢሮዋ ቁጭ ብላ የእለቱን ስራዋን በመስራት ላይ እያለች ፀሀፊዋ ወደእሷ መጣችና እንግዳ ሊያናግራት እንደሚፈልግ ነገረቻት.. እንድታስገባው ፍቃድ ሰጠቻት፡፡ እንግዳው ሲፈቀድለት ወደ ውስጥ ገባ ..ከመቀመጫዋ ተነስታ በክብር ጨብጣ ተቀበለችውና እንዲቀመጣም ጋዘችው፡፡
ለስራ ጉዳይ የመጣ መስሏት‹‹ምን ልታዘዝ ጌታዬ ..?››አለችው፡፡
‹‹የመጣሁት ለስራ ጉዳይ አይደለም ..ለግል ጉዳይ ነበር፡፡››
ግራ ገባት‹‹ይቅርታ ስለምን እንደሆነ ማወቅ እችላለሁ?›.›
‹‹አዎ በመጀመሪያ ግን እራሴን አላስተዋወቅኩም መሰለኝ ...ሁሴን እባላለሁ..
የትንግርት ባለቤት ነኝ፡፡››
ወንበሯ ላይ ወደኋላዋ በድንጋጤ ተለጠጠችና በረጅሙ ተነፈሰች.....ከዛ እራሷን እንደምንም አረጋጋታ <<ውጭ ሀገር ትምህርት ላይ መስለኸኝ ነበር?››
‹‹ከተመለስኩ 3 ቀን አለፈኝ፡፡››
‹‹ምነው በሰላም…?››
‹‹ምን ሰላም አለ ብለሽ ነው..የአንቺን ወደ ኢትየጵያ መመለስ ከዛም አልፎ ከትንግርት ጋር በአካል መገናኘት ስሰማ ተረጋቼ መማር አልሆነልኝም ..ስለዚህ ትምህርቱን አቋርጬ
‹‹ያን ያህል..?››
‹‹ከዛም በላይ...>>
‹‹እና አሁን ምን ልታዘዝ?››
‹‹እንድንነጋገር እፈልጋለሁ?››
‹‹ምንን በተመለከተ?
‹‹ዶ/ር ሶፊያ እኔ ትንግርትን በጣም አፈቅራታለሁ..በመሀከላችሁ ባለው የቀደመ ግንኙነት የተነሳ በህይወቷ ከበቂ በላይ መስዋዕትት ከፍላለች...ከዛ አዘቅት በከፍተኛ ጥረት ወጥታ በብዙ ትግል ነው ማገገም የቻለችው ፡፡ መልሳ ወደ እዛ ህይወት እንድትገባ በፍፁም አልፈልግም….ከዛ በላይ መሰቃየት አይገባትም፡፡ ለራሴ ብቻ አስቤ አይደለም እኔን ትተወኛለች ብዬ በመስጋት ቀንቼም አይደለም፤አንቺንም ጥፋተኛ ነበርሽ ብዬ ልኮንንሽ ወይም ልፈርድብሽም አይደለም…ግን በምንም አይነት ዳግመኛ ወደአንቺ ተመልሳ እንድትቀጥሉ ስለማልፈግ ነው፤ እሷን በሙሉ አቅሜ ከሚመጣው ጥፋት የመጠበቅ ኃላፊነት አለብኝ ....››
‹‹እና እኔ ምን ልተባበርህ?››
‹‹አሁን የስራ ቦታ ስለሆነ ሁሉን ነገር በተረጋጋ ሁኔታ ለመነጋገር ምቹ አይደለም ..እኔ እና አንቺ እንደሰለጠነ ሰው ቁጭ ብለን እንድንነጋገር ቦታ ንገሪኝ፡፡›› እፈልጋለሁ፤የሚመችሽን ጊዜና
ዶ/ር ሶፊያ ለደቂቃዎች እንደማሰብ አለችና በዚህ ጉዳይ ላይ መነጋገር ለእሷም የወደፊት ህይወት መረጋጋት እንደሚጠቅማት ስለገመተች በሀሳብ ተስማማችና ቢዝነስ ካርዷን አውጥታ ሰጠችው‹‹ነገ በተመቸህ ሰዓት ደውልልኝና ፕሮግራሜን አመቻችቼ የምንገናኝበትን ጊዜ እና ቦታ እነግርሀለሁ››
ከመቀመጫው ተነሳና ለስንብት እጁን እየዘረጋ‹‹በትህትና ስላስተናገድሺኝ አመሰግናለሁ፤ ይሄንን በመሀከላችን ያለውን ግንኙነት ትንግርት አታውቅም፤ምን አልባት የምትገናኙ ከሆነ ባትነግሪያት ደስ ይለኛል፡፡›› አላት፡፡
‹‹አትስጋ አቶ ሁሴን ..አልነግራትም፡፡›› አለችው ፤አንገናኝም ነበር ለማለት የፈለገችው... ግን እጅ መስጠት ስላልፈለገች አልነግራትም አለችው፡፡ደግሞ ሁሴንን ወዳላታለች... ‹‹ደስ የሚል ወንዳወንድ ቁመና ያለው አማላይ ባል ነው ያገኘችው፡፡››አለች እና የሆነ የመጐምዠት አይነት ስሜት ልቧን ጠቅ ሲያደርጋት ተሰማት….እንዴ ምን አይነት ነገር ነው እያሰብኩ ያለውት..? ብላ ራሷን ለመገሰፅ ሞከረች....ግን የሁሴንን ምስል ከአዕምሮዋ አውጥታ ጥላ ጀምራ የነበረውን ሰራ መቀጠል አልተቻላትም... በዚህም የተነሳ እራሷን ለማረጋጋት ቢሮዋን ለቃ ወጥታ ወደ ቤቷ አመራች፡፡
ከምሽቱ አንድ ሰዓት ተኩል ሰሎሞን እና ሁሴን ካሳንቺስ ከሚገኝ አንዱ ሆቴል ጥግ ይዘው ውስኪያቸውን እየተጐነጩ የናፍቆት ወሬ እያወሩ ናቸው፡፡
‹‹አንተ ደግሞ ቀላህ እኮ !! ከፈረንጅ ሀገር ዕውቀታቸውን ልትኮርጅ ሄደህ የቆዳ ቀለማቸውን ኮርጀህ መጣህ እንዴ?››
‹‹ምን ይደረግ ብለህ ነው...እንደሚታወቀው እኛ ኢትዬጵያውያን ኩረጃ ላይ ቀሺም ነን…..ግን ምን በጣም ናፍቆኝ እንደነበረ ታውቃለህ?››
‹‹አውቃለሁ.. እኔ ነኛ በጣም የናፈቅኩህ፡፡››
‹‹ጉረኛ…አንተ ደግሞ ጭቅጭቅህ ካለሆነ ሌላ ምን የሚናፍቅ ደህና ነገር አለህ ?እነዚህ ጠያይም ወዛና ያላቸው ልዕልት የሀገሬ ሴቶች በዓይኔ ላይ እየሄዱ ፈተና ነበር የሆኑብኝ፡፡››አለው ወደ አስተናጋጆቹ በአገጩ እያመለከተው፡፡
‹‹እንዴ!! እዛስ የፈረንጅ ቆንጆ ሞልቶልህ የለም እንዴ?››
‹‹የሰው ቆንጆ ለእኔ ምን ይሰራል? እኔ ምንም ብትለኝ ምንም እንደሀገሬ ሴት የተለየ ውበት ያላቸው የሉም ባይ ነኝ…የእኛ ሀገር ፉንጋዋ እንኳን የራሷ የሆነ ማግኔታዊ ደም ግባት
ይኖራታል ...ብቻ የትም ብትሄድ የትም የሀገሬ ሴቶች አንደኛ ናቸው፡፡››
‹‹ይሁንልህ... ይሄንን ዲስኩርህን ትንግርት ብቻ እንዳትሰማህ፡፡ >>
‹‹ብትሰማስ ምን አጠፋው ?ያሀገሬን ሴቶች ውበት ነው ያደነቅኩት፡፡››
‹‹አድናቆትህ ወሲባዊ ሆነብኛ፡፡››
‹‹የእኔ አድናቆት ሳይሆን ያንተ ጆሮ አደማመጥ ነው ወሲባዊ ያደረገው... ለማንኛውም ወደ ቁም ነገሩ እንግባ ዳግመኛ ወደ ሆቴልህ ተመለስክ አሉ፡፡››
‹‹አዎ ምን ላድርግ ?ሴቶች እና እኔ ልንገናኝ አልቻልንም፡፡ አገኘኋቸው ስል ይሾልኩብኛል አወቅኳቸው ስል ይጠፉብኛል.... ባክህ እነሱን በተመለከተ ግራ ግብት ብሎኛል፡፡
‹‹አይዞህ ጓዴ ...ይሄ ያንተ ችግር ብቻ አይደለም የአብዛኛው ወንድ ችግር ነው፡፡
ይኖራታል ...ብቻ የትም ብትሄድ የትም የሀገሬ ሴቶች አንደኛ ናቸው፡፡››
‹‹ይሁንልህ... ይሄንን ዲስኩርህን ትንግርት ብቻ እንዳትሰማህ፡፡ >>
‹‹ብትሰማስ ምን አጠፋው ?ያሀገሬን ሴቶች ውበት ነው ያደነቅኩት፡፡››
‹‹አድናቆትህ ወሲባዊ ሆነብኛ፡፡››
‹‹የእኔ አድናቆት ሳይሆን ያንተ ጆሮ አደማመጥ ነው ወሲባዊ ያደረገው... ለማንኛውም ወደ ቁም ነገሩ እንግባ ዳግመኛ ወደ ሆቴልህ ተመለስክ አሉ፡፡››
‹‹አዎ ምን ላድርግ ?ሴቶች እና እኔ ልንገናኝ አልቻልንም፡፡ አገኘኋቸው ስል ይሾልኩብኛል ..አወቅኳቸው ስል ይጠፉብኛል.... ባክህ እነሱን በተመለከተ ግራ ግብት ብሎኛል፡፡
‹‹አይዞህ ጓዴ ...ይሄ ያንተ ችግር ብቻ አይደለም የአብዛኛው ወንድ ችግር ነው፡፡
የአሁኑ ግን የእኔ ጥፋት ነው፡፡››
‹‹አንተ ደግሞ ምን አደረግክ…?››
‹‹እኔ ወደ ሀዋሳ ሂድ ባልልህ ይሄ ችግር አይፈጠርም ነበር፡፡››
‹‹ትቀልዳለህ እንዴ... እኔ ኖርኩም አልኖርኩም እርግዝናዋ ከመጨንገፍ ይድናል ብለህ ታስባለህ?፡፡››
‹‹እሱ ሊሆን ይችላል ...ምንም ሆነ ምንም ግን አጠገቧ ብትሆን ኖሮ እሷ እንዲህ አታመርም ነበር፤አንተም አኮ ትንሽ አጥፍተሀል››
‹‹ምን አድርጌ አጠፋሁ?››
‹‹ስደውልልህ የእሷን መታመም ብትነግረኝ ሌላ ሰው እልክ ነበር፡፡››
‹‹እሱ ሰበብ ነው.. እናቷ፣አባቷ፣ እህቷ.. ከአስር ሰው በላይ ዙሪያዋን ከቧት ነበር ..ደግሞ በጣም ተሸሏት ወደኖርማል ጤንነቷ
በተመለሰች ጊዜ ነው ተነስቼ የሄድኩት፡፡መልሳ እንደምትታመም እና ይሄ ነገር እንደሚፈጠር ጠንቋይ አልቀልብ በምን ላውቅ እችላለሁ? እንደውም ይሄንን ሰበብ አድርጋ ጋብቻውን ለማፈረስ በምክንያትነት ተጠቀመችበት እንጂ በፊቱኑም ከእኔጋ መኖር የሰለቻት ይመስለኛል፡፡ይሄን ያህል ይቅርታ የማያሰጥ ጥፋት አጥፍቼያለሁ ብዬ አላስብም፤ የጠፋው የእኔም ልጅ ነው፤ ወንድ ልጅ በመሆኑ እንዴት ተደስቼ እንደነበረ…እንዴት በናፍቆት ወደእዚህች ምድር የመምጫውን ቀን እጠብቅ እንደነበረ ከማንም በላይ ጠንቅቃ ታውቃለች፡፡ በተፈጠረው
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ዶ/ር ሶፊያ ቢሮዋ ቁጭ ብላ የእለቱን ስራዋን በመስራት ላይ እያለች ፀሀፊዋ ወደእሷ መጣችና እንግዳ ሊያናግራት እንደሚፈልግ ነገረቻት.. እንድታስገባው ፍቃድ ሰጠቻት፡፡ እንግዳው ሲፈቀድለት ወደ ውስጥ ገባ ..ከመቀመጫዋ ተነስታ በክብር ጨብጣ ተቀበለችውና እንዲቀመጣም ጋዘችው፡፡
ለስራ ጉዳይ የመጣ መስሏት‹‹ምን ልታዘዝ ጌታዬ ..?››አለችው፡፡
‹‹የመጣሁት ለስራ ጉዳይ አይደለም ..ለግል ጉዳይ ነበር፡፡››
ግራ ገባት‹‹ይቅርታ ስለምን እንደሆነ ማወቅ እችላለሁ?›.›
‹‹አዎ በመጀመሪያ ግን እራሴን አላስተዋወቅኩም መሰለኝ ...ሁሴን እባላለሁ..
የትንግርት ባለቤት ነኝ፡፡››
ወንበሯ ላይ ወደኋላዋ በድንጋጤ ተለጠጠችና በረጅሙ ተነፈሰች.....ከዛ እራሷን እንደምንም አረጋጋታ <<ውጭ ሀገር ትምህርት ላይ መስለኸኝ ነበር?››
‹‹ከተመለስኩ 3 ቀን አለፈኝ፡፡››
‹‹ምነው በሰላም…?››
‹‹ምን ሰላም አለ ብለሽ ነው..የአንቺን ወደ ኢትየጵያ መመለስ ከዛም አልፎ ከትንግርት ጋር በአካል መገናኘት ስሰማ ተረጋቼ መማር አልሆነልኝም ..ስለዚህ ትምህርቱን አቋርጬ
‹‹ያን ያህል..?››
‹‹ከዛም በላይ...>>
‹‹እና አሁን ምን ልታዘዝ?››
‹‹እንድንነጋገር እፈልጋለሁ?››
‹‹ምንን በተመለከተ?
‹‹ዶ/ር ሶፊያ እኔ ትንግርትን በጣም አፈቅራታለሁ..በመሀከላችሁ ባለው የቀደመ ግንኙነት የተነሳ በህይወቷ ከበቂ በላይ መስዋዕትት ከፍላለች...ከዛ አዘቅት በከፍተኛ ጥረት ወጥታ በብዙ ትግል ነው ማገገም የቻለችው ፡፡ መልሳ ወደ እዛ ህይወት እንድትገባ በፍፁም አልፈልግም….ከዛ በላይ መሰቃየት አይገባትም፡፡ ለራሴ ብቻ አስቤ አይደለም እኔን ትተወኛለች ብዬ በመስጋት ቀንቼም አይደለም፤አንቺንም ጥፋተኛ ነበርሽ ብዬ ልኮንንሽ ወይም ልፈርድብሽም አይደለም…ግን በምንም አይነት ዳግመኛ ወደአንቺ ተመልሳ እንድትቀጥሉ ስለማልፈግ ነው፤ እሷን በሙሉ አቅሜ ከሚመጣው ጥፋት የመጠበቅ ኃላፊነት አለብኝ ....››
‹‹እና እኔ ምን ልተባበርህ?››
‹‹አሁን የስራ ቦታ ስለሆነ ሁሉን ነገር በተረጋጋ ሁኔታ ለመነጋገር ምቹ አይደለም ..እኔ እና አንቺ እንደሰለጠነ ሰው ቁጭ ብለን እንድንነጋገር ቦታ ንገሪኝ፡፡›› እፈልጋለሁ፤የሚመችሽን ጊዜና
ዶ/ር ሶፊያ ለደቂቃዎች እንደማሰብ አለችና በዚህ ጉዳይ ላይ መነጋገር ለእሷም የወደፊት ህይወት መረጋጋት እንደሚጠቅማት ስለገመተች በሀሳብ ተስማማችና ቢዝነስ ካርዷን አውጥታ ሰጠችው‹‹ነገ በተመቸህ ሰዓት ደውልልኝና ፕሮግራሜን አመቻችቼ የምንገናኝበትን ጊዜ እና ቦታ እነግርሀለሁ››
ከመቀመጫው ተነሳና ለስንብት እጁን እየዘረጋ‹‹በትህትና ስላስተናገድሺኝ አመሰግናለሁ፤ ይሄንን በመሀከላችን ያለውን ግንኙነት ትንግርት አታውቅም፤ምን አልባት የምትገናኙ ከሆነ ባትነግሪያት ደስ ይለኛል፡፡›› አላት፡፡
‹‹አትስጋ አቶ ሁሴን ..አልነግራትም፡፡›› አለችው ፤አንገናኝም ነበር ለማለት የፈለገችው... ግን እጅ መስጠት ስላልፈለገች አልነግራትም አለችው፡፡ደግሞ ሁሴንን ወዳላታለች... ‹‹ደስ የሚል ወንዳወንድ ቁመና ያለው አማላይ ባል ነው ያገኘችው፡፡››አለች እና የሆነ የመጐምዠት አይነት ስሜት ልቧን ጠቅ ሲያደርጋት ተሰማት….እንዴ ምን አይነት ነገር ነው እያሰብኩ ያለውት..? ብላ ራሷን ለመገሰፅ ሞከረች....ግን የሁሴንን ምስል ከአዕምሮዋ አውጥታ ጥላ ጀምራ የነበረውን ሰራ መቀጠል አልተቻላትም... በዚህም የተነሳ እራሷን ለማረጋጋት ቢሮዋን ለቃ ወጥታ ወደ ቤቷ አመራች፡፡
ከምሽቱ አንድ ሰዓት ተኩል ሰሎሞን እና ሁሴን ካሳንቺስ ከሚገኝ አንዱ ሆቴል ጥግ ይዘው ውስኪያቸውን እየተጐነጩ የናፍቆት ወሬ እያወሩ ናቸው፡፡
‹‹አንተ ደግሞ ቀላህ እኮ !! ከፈረንጅ ሀገር ዕውቀታቸውን ልትኮርጅ ሄደህ የቆዳ ቀለማቸውን ኮርጀህ መጣህ እንዴ?››
‹‹ምን ይደረግ ብለህ ነው...እንደሚታወቀው እኛ ኢትዬጵያውያን ኩረጃ ላይ ቀሺም ነን…..ግን ምን በጣም ናፍቆኝ እንደነበረ ታውቃለህ?››
‹‹አውቃለሁ.. እኔ ነኛ በጣም የናፈቅኩህ፡፡››
‹‹ጉረኛ…አንተ ደግሞ ጭቅጭቅህ ካለሆነ ሌላ ምን የሚናፍቅ ደህና ነገር አለህ ?እነዚህ ጠያይም ወዛና ያላቸው ልዕልት የሀገሬ ሴቶች በዓይኔ ላይ እየሄዱ ፈተና ነበር የሆኑብኝ፡፡››አለው ወደ አስተናጋጆቹ በአገጩ እያመለከተው፡፡
‹‹እንዴ!! እዛስ የፈረንጅ ቆንጆ ሞልቶልህ የለም እንዴ?››
‹‹የሰው ቆንጆ ለእኔ ምን ይሰራል? እኔ ምንም ብትለኝ ምንም እንደሀገሬ ሴት የተለየ ውበት ያላቸው የሉም ባይ ነኝ…የእኛ ሀገር ፉንጋዋ እንኳን የራሷ የሆነ ማግኔታዊ ደም ግባት
ይኖራታል ...ብቻ የትም ብትሄድ የትም የሀገሬ ሴቶች አንደኛ ናቸው፡፡››
‹‹ይሁንልህ... ይሄንን ዲስኩርህን ትንግርት ብቻ እንዳትሰማህ፡፡ >>
‹‹ብትሰማስ ምን አጠፋው ?ያሀገሬን ሴቶች ውበት ነው ያደነቅኩት፡፡››
‹‹አድናቆትህ ወሲባዊ ሆነብኛ፡፡››
‹‹የእኔ አድናቆት ሳይሆን ያንተ ጆሮ አደማመጥ ነው ወሲባዊ ያደረገው... ለማንኛውም ወደ ቁም ነገሩ እንግባ ዳግመኛ ወደ ሆቴልህ ተመለስክ አሉ፡፡››
‹‹አዎ ምን ላድርግ ?ሴቶች እና እኔ ልንገናኝ አልቻልንም፡፡ አገኘኋቸው ስል ይሾልኩብኛል አወቅኳቸው ስል ይጠፉብኛል.... ባክህ እነሱን በተመለከተ ግራ ግብት ብሎኛል፡፡
‹‹አይዞህ ጓዴ ...ይሄ ያንተ ችግር ብቻ አይደለም የአብዛኛው ወንድ ችግር ነው፡፡
ይኖራታል ...ብቻ የትም ብትሄድ የትም የሀገሬ ሴቶች አንደኛ ናቸው፡፡››
‹‹ይሁንልህ... ይሄንን ዲስኩርህን ትንግርት ብቻ እንዳትሰማህ፡፡ >>
‹‹ብትሰማስ ምን አጠፋው ?ያሀገሬን ሴቶች ውበት ነው ያደነቅኩት፡፡››
‹‹አድናቆትህ ወሲባዊ ሆነብኛ፡፡››
‹‹የእኔ አድናቆት ሳይሆን ያንተ ጆሮ አደማመጥ ነው ወሲባዊ ያደረገው... ለማንኛውም ወደ ቁም ነገሩ እንግባ ዳግመኛ ወደ ሆቴልህ ተመለስክ አሉ፡፡››
‹‹አዎ ምን ላድርግ ?ሴቶች እና እኔ ልንገናኝ አልቻልንም፡፡ አገኘኋቸው ስል ይሾልኩብኛል ..አወቅኳቸው ስል ይጠፉብኛል.... ባክህ እነሱን በተመለከተ ግራ ግብት ብሎኛል፡፡
‹‹አይዞህ ጓዴ ...ይሄ ያንተ ችግር ብቻ አይደለም የአብዛኛው ወንድ ችግር ነው፡፡
የአሁኑ ግን የእኔ ጥፋት ነው፡፡››
‹‹አንተ ደግሞ ምን አደረግክ…?››
‹‹እኔ ወደ ሀዋሳ ሂድ ባልልህ ይሄ ችግር አይፈጠርም ነበር፡፡››
‹‹ትቀልዳለህ እንዴ... እኔ ኖርኩም አልኖርኩም እርግዝናዋ ከመጨንገፍ ይድናል ብለህ ታስባለህ?፡፡››
‹‹እሱ ሊሆን ይችላል ...ምንም ሆነ ምንም ግን አጠገቧ ብትሆን ኖሮ እሷ እንዲህ አታመርም ነበር፤አንተም አኮ ትንሽ አጥፍተሀል››
‹‹ምን አድርጌ አጠፋሁ?››
‹‹ስደውልልህ የእሷን መታመም ብትነግረኝ ሌላ ሰው እልክ ነበር፡፡››
‹‹እሱ ሰበብ ነው.. እናቷ፣አባቷ፣ እህቷ.. ከአስር ሰው በላይ ዙሪያዋን ከቧት ነበር ..ደግሞ በጣም ተሸሏት ወደኖርማል ጤንነቷ
በተመለሰች ጊዜ ነው ተነስቼ የሄድኩት፡፡መልሳ እንደምትታመም እና ይሄ ነገር እንደሚፈጠር ጠንቋይ አልቀልብ በምን ላውቅ እችላለሁ? እንደውም ይሄንን ሰበብ አድርጋ ጋብቻውን ለማፈረስ በምክንያትነት ተጠቀመችበት እንጂ በፊቱኑም ከእኔጋ መኖር የሰለቻት ይመስለኛል፡፡ይሄን ያህል ይቅርታ የማያሰጥ ጥፋት አጥፍቼያለሁ ብዬ አላስብም፤ የጠፋው የእኔም ልጅ ነው፤ ወንድ ልጅ በመሆኑ እንዴት ተደስቼ እንደነበረ…እንዴት በናፍቆት ወደእዚህች ምድር የመምጫውን ቀን እጠብቅ እንደነበረ ከማንም በላይ ጠንቅቃ ታውቃለች፡፡ በተፈጠረው
👍69