አትሮኖስ
279K subscribers
109 photos
3 videos
41 files
456 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ሰመመን


#ክፍል_አርባ_አንድ


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ


ተማሪ አንዱ በአንዱ ላይ እየተንጠራራ ከሰሌዳው ላይ የመለያ ቁጥሩን መፈለግ
ጀመረ።

እነ እስክንድር ግርግሩ መሀል ሲደርሱ እነ ማርታ ውጤታቸውን ለማየት ስለ ተበታተኑ ተሰወሩባቸው ። የአንደኛና የሁለተኛ ዓመት ተማሪዎች ውጤት ብቻ ነበር የወጣው ።

የአራተኛ ዓመቶች ውጤት አልደረሰም እንዴ ? ”
አለው እስክንድር ውጤቱን የለጠፈውን ሰውዬ ሲመለስ አግኝቶት።

"ከሰዓት በኋላ ” ብሎት ሰውዬው እየተደፈ ሐደ ።

“ እስቲ እኔም ጉዴን ልመልከት ”አለ ሳምሶን አስደንጋጭ ድምፁ ስልት አጥቶ እየተንቀጠ።

“ ቆይ ምን አስቸኮለህ ? ግርግሩ ተግ ይበልልህ! ” አለው እስክንድር ።

ሳምሶን አረ ባክህ ! ” ብሎት " ተማሪውን እየገፈታተረ ወደ ልለተኛ ዓመቶች የውጤት ሰሌዳ አመራ።

እቤልና እስክንድር ከግርግሩ መሀል ወጥተው ብቻ ቸውን ቆመው ቀሩ አንዳች ነገር ተጫጭኗቸዋል አይነጋገረም።

ግርግሩን አትረው ይመለከቱ ጀመር » ማንኛውም ነገር ውስጡ ሲሆኑበትና ከውጭ ሲታዘቡት የተለያየ ገፅታ አለው የፈተና ውጤት ግዜ እንዲህ ከሩቅ ሆነው ሲያዩት አሳዛኝ ትርኢት ይታይበታል ውጤቱ የድካም ውጤት ሳይሆን የብሔራዊ ሎተሪ እጣ ይመስላል አንዳንዱ እየሳቀ ሄዶ ውጤቱን አይቶ ሲመለስ ፊቱ ኮሶ ይመስላል በፍርሃት
እየተንቀጠለጠ ሔዶ እየቦረቀ የሚመለስም አለ ውጤቱ አስደንግጦት የቆመበት ዘፍ የሚልም አይታጣም አብዛኛው ተማሪ ስለ ራሱ የነበረው ግምትና አሁን ያገኘው ውጤት እየተራራቀበት ፊቱን አጨማዶ ሲመለስ ነው የሚታየው።
እኔስ ከየትኛው ዐይነት እሆን ? ” ሲል እስክንድር ራሱን ጠየቀ ። የውጤት ጊዜን ሁኔታ እንዲህ በሩቅ ታዝቦ አያውቅም ነበር ።

አንዲት ልጃገረድ በጓደኞቿ ተደግፋ እያለቀሰች በኣጠገባቸው ስታልፍ አይተው የአቤልም የእስክንድርም ልብ
አብሮ አለቀሰ።
አይዞሽ ፡ ዩኒቨርስቲ የሕይወት መጨረሻ አይደለም ” አላት እስክንድር ቀስ ብሎ።

ቀና ብላ አላየችውም ጓደኞቿ ግን ያሾፈባት መስሏቸው ዞረው ገላመጡት ። ግልምጫ ከዐፈር የሚደባልቅ ቢሆን የማይተዋወቁት ሰው ግልጫ ኦሆሆ ! ቶሎ ብሎ ዐይኑን ከአይናቸን አሸሸ ።

ዘወር ሲል ሚስተር ሆርስ ከሶስት ልጆች ጋር ሆኖ ቅልጥሙን እጥፍ እያረገ ፌቱ ፈክቶ ሲያልፍ አየው ።

“ እንዴት ነው ውጤት? ፊትህ ሁሉ ጥርስ ሆኖአል” አለው በሩቁ ከአኳኋኑ ማለፉን ተረድቶ

“ አልሞትንም ፤ ተርፈናል ። የዩኒቨርስቲ ሕይወታችንን አራዝመናል።

« እንኳን ደስ ያለህ ! ” አለውና ፥ “ በቀላሉ የሚደሰት ተፈጥሮ ጥሩ ነው ” አለ በልቡ በድንግት የአቤል ድምፅ አስደነገጠው።

“ ያቻት ትዕግስት"

አቤል ከርቀት ትዕግሥትንና ማርታን ሲያይ ሳያስበው ነው ስሟ ያመለጠው ። በድንጋጤ ስሟን ከመጥራቱ ሌላ
የሚጨምርበት ነገር አልነበረም ።

“ እህ ?” አለው እስክንድርም ደንግጦ "

አቤል ምንም አልመለሰም ። ፊቱ በቅጽበት ተለዋውጦ ከሰል መሰለ ከንፈሩ ተጣብቆ አልላቀቅ አለው ዐይኑ
ፈዞ ቀረ።

እስክንድርም መልስ አልጠበቀም ፥ የአቤልን ዐይን ተከትሎ ትዕግሥትንና ማርታን ተመለከታቸው ውጤታቸውን
አይተው በመመለስ ላይ ነበሩ ። ፊታቸው ዳምኗል ።በኀዘን ተውጠው አንዳችም ቃል ሳይለዋወጡ መሬት መሬት እያዩ ነው የሚሔዱት ። ለእነ አቤል ደግሞ የባሰ
ዳምነውና ተክዘው ታዩአቸው ።

ትዕግሥትና ማርታ እነ አቤልን ሲያዩዋቸውመንገዱቸውን አሳብረው በሌላ በኩል ሔዱ። በማርታ ግፊት ነበር
ይህ የተደረገው። ማንም ሳያያት ወደ መኝታ ክፍሏ መሔድ ነው የፈለገችው ።

አቤል መቆም ኣልቻለም ። ወገቡ የተቀነጠሰ መሰለው። ትዕግሥት ወድቃለች ማለት ነው ? ከዩኒቨርስቲው ልትባረርና ሊያጣት? ስለ ራሱ ውጤት አንዴም አላሰበ መለየት የሞት ያህል ሆኖ ታየው ።

ቃላት መተንፈስ ፈለገ ግን ከንፈሮቹ አልላቀቅ አሉት እርዳታ በሚጠይቅ አመለካከት እስክንድርን አየው ። ከተረታ ወይም ከደከመ ልብ ብቻ ነው የዚያን
ዐይነት እይታ የሚመነጨው።

“ ምን ልርዳህ ? ” አለው እስክንድር ' ሁኔታው ስለ ገባው።

አቤል ምንም ሳይመልስለት ፡ በሚስለመለም ዐይኖቹ እያየው ቀስ ብሎ አጠገቡ ያገኘው ነገር ላይ ቁጭ አለ።

እስክንድር በሐሳቡ አሁን ምን በወቅንና ነው ? ” አለ ። “ ምናልባት እነዚህ ልጆች ሳይወድቁ በዝቅተኛ ማርክ ብቻ እንደሆነስ የተከዙት ? ለምን ተከትዬአቸው ሔጂ አልጠይቃቸውም ? እነሱ ቢሸሹኝ ተናደው ይሆናል። እኔ
ግን ሔጄ ጠይቄአቸው ወድቀውም ከሆነ ማጽናናት አለብኝ ካለዚያ የመተዋወቅ ትርጕሙ ምንድን ነው ? ” አለና አቤልን የተቀመጠበት ትቶት ሔደ ።

ከሁለቱም ከማዘኑ ሌላ የእንድም ቀን የጫዋታ ትዝታ ቢሆን መጥፎ ነውና ከማርታ ጋር የመለያየቱ ነገር እሱንም ቅር ብሎት ነበር ።

ፈጥኖ ሔደ። ሲደርስባቸው ቀድማ ያየችው ትዕግሥት ነበረች ። በደካማ ፈገግታ ሰላምታ ሰጠችው ። ማርታም
እሷን ተከትላ ዘወር ስትል አየችው ። ሰላምታ ልትሰጠው ብትፈልግም ፈገግ ማለት አልቻለችም ።

እስክንድር አጠገባቸው ከደረሰ በኋላ ስለ ውጤታቸው መጠየቅ ፈርቶ ከንፈሩ ይንቀጠቀጥ ጀመር ።

“ እንዴት ነው ? ” አላቸው ፡ ሰላምታ ከተለዋወጡ በኋላ ፥ አንዴ ወደ ማርታ አንዴ ወደ ትዕግሥት እየተመለከተ ።

“ ዩኒቨርስቲያችሁን ለቀቅኩላችሁ እናንተው ኑሩበት!” አለችው ማርታ ቀድማ መንፈሷ ቢደክምም ምላሷ አልሞትም ነበር ።

“ ምነው ? ውጤቱ መጥፎ ነው እንዴ ? ”
ኤጭ ! ”
ከንፈሩን መጠጠና ወደ ትዕግሥት ዞሮ ' “ የአንቺስ ውጤት እንዴት ነው ? ” ሲል ጠየቃት ።

ጥሩ ነው ። በመካከለኛ ውጤት አልፌአለሁ ” አለችው በፈገግታ ።

“ እንኳን ደስ ያለሽ ! ዋናው ማለፍሽ ነው!!” አለና እሱም ፈገግ ብሎ እንደገና ጨበጣት ።

ማርታ ሁለቱንም በቅናት አስተያየት ላጠቻቸው "ዐይን የሚገድል ቢሆን ሁለቱም የቆሙበት ክው ብለው ቀርተው ነበር ።

እስክንድር ደስታና ኀዘን መሐል ገብቶ ወደ የትኛዋ 'እንደሚሆን ግራ ገባው ። “ ግማሽ ፊትን አጥቁሮ፡ ግማሽ ፊትን ማሣቅ ቢቻል እንዴት ጥሩ ነበር !” አለ በልቡ ።

ማርታን ፊት ለፊት ሊያያት አልደፈረም ። ቀስ ብሎ በስርቆሽ ተመለከታት የጠወለገች አበባ መስላለች ለካ ውበት የስሜት ነጸብራቅ ነው?” አለ በሐሳቡ ። ስሜቷ ከውስጥ ሲንድ ፡ሲቃጠል ሲብከነከን ታየው ድርብ የከንፈር ቀለሟ በመጠውለጉ ፊቷ ላይ ጎልቶ ምናምን
የላሰች አይጥ አስመስሏታል ። ቅንድቧ ብቻ እንደ ወትሮው ይርገበገባል ።

እስክንድር የቅንድቧን መርገብገብ አይቶ ወሬ እንደምትፈልግ ዐወቀ ። ግን ምን ዐይነት ወሬ ? በእሷ መውደቅ ምክንያት ተማሪውንና አስተማሪውን ማማት መቦጨቅ ? አይዞሽ ማርታ ዩኒቨርስቲ የሕይወት መጨረሻ አይደለም ” አላትና ፡ አንድ ቀን ያጫወተችውን አስታውሶ : “ ደሞም ከዚህ ወጥተሽ ስኮላርሽፕ መጠበቅ ትችያለሽ ” አላት ።

“እኔ ማርታ ጉዳዬም አይደል ! ብቻ እንኳን ዩኒቨርስቲ የምትሉትን አየሁላችሁ !
እስክንድር በልቡ “ እኛ ደሞ ምን አደረግንሽ ? " ብሎ ጭጭ።

“ የማትስ አስተማንሪኮ ነው ጉድ ያረገኝ ” አለች ትንሽ ቆየችና።

“ እሱ "F" ባይሰጠኝ ኖሮ ሌላ ትምህርት አልጎዳኝም ነበር።

“ ማነው እሱ? ” አላት ያስተዛዘናት መስሎት

“አቶ ኃይሉ የሚሉት አንድ ሽማግሌ አለ " ላውጣሽ ብሎኝ ስለ ዘጋሁት ቁጭቱን ተወጣብኝ ”

“ ያሳዝናል ! ” አለ እስክንድር ፡ ውሸቷ ኮርኩሮት በህዱ እየሳቀ።

ደሞ ከእሱ ጋር ልውጣ እንዴ? ቅሌታም ሽማግሌ ! ”፥

እስክንድር እንደገና ከንፈሩን
1
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_አርባ_አንድ


#ድርሰት_በትክክል_ገና

....አዜብና አንዱአለም አጠገቡ ናቸው፡፡ ከኪሱ ውስጥ የሆነ ነገር አወጣ፡፡ በትንሽ የፕላስቲክ ሳጥን ውስጥ የተቀመጠች..ውድ ነገር:: በመጠን በጣም ትንሽ፤ በቁም ነገር ግን እዚያ እላይ!! ቀለበት. የቃል ኪዳን ቀለበት ... ስለ እውነተኛ ፍቅር የተዘጋጀች ፤ የትዳር መጠንሰሻ:
የቃል መተሳሰሪያ፤ ቀለበት... በምህጻረ ቃል የሱና የሷ ስም የተጻፈበትን
ቀለበት አወጣና......

“በመንፈሰ ጠንካራነትሽ ለሰጠሽኝ ትልቅ ትምህርት፡ ለእውነተኛ ፍቅር ስትይ ለከፈልሽው መስዋዕትነት፣ በታማኝነት ፀንተሽ ኣብረን ለቆየንባቸው ጊዜያቶች ሁሉ ማስታወሻ እንድትሆን፡ ይህቺ ሁለት ዓመት ለቀሪ ህይወትሽ ትምህርት የምታገኝበት፣ እኔ ደግሞ ለሠርጋችንም ሆነ ከሠርጋችን በኋላ የትዳር ህይወታችንን በሰላም ለመምራት እንዲያስችለን የምዘጋጅበት እንዲሆንና፤ የማረፊያ ቤት ቆይታሽ፤ መጪውን ብሩህ
ተስፋ አሻግረሽ የምትመለከችበት የዕረፍት ጊዜ እንዲሆንልሽ በመመኘት፤
ያዘጋጀኋትን ገፀ በረከት፤ ይህችን የቃል ኪዳን ቀለበት፣ እንድትቀበይኝ” አለና ከጉልበቱ በርከክ ብሎ ሽቅብ ተመለከታት፡፡ ከዚያም ፍዝዝ ባለችበት
እንባዋ ጉንጮቿን እያቋረጠ፤ ቁልቁል መውረድ ሲጀምር፤ ቀልጠፍ ብሎ
የግራ እጇንና ቀለበቷን ወደ ላይ ከፍ አደረጋቸው፡፡

ከዚያ የከበበው ሰው በሙሉ በደስታና በሆታ አጨበጨበላቸው፡፡ ዕልልታውን አቀለጠላቸው፡፡ አንዱዓለምና አዜብ ተቃቀፉ፡ ሚስጥሩን የምታውቀው አዜብ ብቻ ነበረች፡፡ ቀለበቱንም የመረጠችለት እሷ ናት።
ለአንዱአለም ግን ሁኔታው ድንገተኛ ነበር፡፡ በፍርድ ቤቱ ቅጽር ግቢ ውስጥ ሌላ ተዓምር፡፡ ቃል ኪዳን ......ከዚያም
ቀለበቷን በጣቷ ውስጥ ሲያጠልቅ፤ አዜብና አንዱአለም በደስታ ሲቃ ተውጠው፤ እልልታቸውን፤ አቀለጡት፡፡
ያቺን ቀለበት በዚህ በዛሬው ዕለት ሊያደርግላት የወሰነበት ምክንያት ነበረው፡፡ ይህቺ የውሣኔ ዕለት፣ ይህቺ የፍርድ ቀን፡ በነፃ የምትለቀቅበት ሳይሆን፡ የህግ እስረኛ ሆና በማረፊያ ቤት እንድትቆይ የሚወሰንበት ዕለት መሆኗን አስቀድሞ ስለሚያውቅ፣ በዚህች ቀን የህግ እስረኛ በመሆንዋ፤ የመገለል ስሜት እንዳይሰማትና፤ የሞራል ውድቀት
እንዳይደርስባት፣ መታሰር ማለት፤ ከዚህ ዓለም መገለል ማለት ያለመሆኑን ተረድታ፤ በጥንካሬና በጽናት የእስር ዘመኗን እንድትጨርስ ለማድረግ፣ በዚያች የውሣኔ ዕለት፤ እስረኛ ብቻ ሳትሆን፤ የታጨች ሙሽራ መሆኗን ጭምር እንድታውቅ፣ የህይወት አጋር ፤የትዳር
ጓደኛው ! ከሷ ሌላ ማንም እንደሌለው ሊያረጋግጥላት፡፡ ሊያበረታታት፡፡
ስለወሰነ፤ የቀለበት ስነ ሥርዓቱን ባልጠበቀችው በዚያ ሁኔታ ሲፈጽምና
ቀለበቷን በጣቷ ላይ ሲያኖርላት፣ በደስታ ሲቃ ተውጣ፣ እስረኛ መሆኗን ፍጹም ረስታ፤ በሳቅ እየተፍለቀለቀች፣ ሻምበልን አንገቱ ላይ ተጠመጠመችበት፡፡ ሻምበል አደራውን ተወጣ! የፈራረሰ በድን አካሏ በወደቀበት ስፍራ በመቃብሯ ላይ ሳይሆን፤ ያቺን ውብ የፍቅር ጽጌረዳ
አበባ፤ አለንጋ በሚመስለው የቀለበት ጣቷ ላይ እና፤ በፍቅሩ ምክንያት ታላቅ ጉዳትና ስብራት በደረሰበት ልቧ ውስጥ በክብር አስቀመጠላት ::
ዶክተር ባይከዳኝ በዚያ በሚያየው ነገር ተደናግጦ እና ተገርሞ አፉን በሰፊው ከፍቶ በመቅረቱ ምክንያት፤ እጆቹን ማራገብ እንኳ ተስኖት!በተከፈተው አፉ
ውስጥ ይመላለሱ የነበሩ ዝንቦች ፤ ያለከልካይ ተዝናኑበት፡፡ ከዚያም እንደምንም ብሎ ከሰመመኑ ሲመለስ፤ የሆነ የቅናት መንፈስ ሰውነቱን ውርር አደረገው :: ያንን ያልጠበቀውን
ትእንግርት እያየ፤ አፉን ከፍቶ በቀረበት ቅጽበት ሌላ ነገር ተደገመ
“እኛ ደግሞ ለዛሬ የወርቅ ቀለበት ያላዘጋጀን ቢሆንም፧ ልክ አንቺ ከማረፊያ ቤት ወጥተሽ፤ የጋብቻ ስነ ስርዓታችሁን ስትፈጽሙ ፤
እኔና አዜቢና ደግሞ፧ የቃል ኪዳን ቀለበታችንን የምናስርበት ዕለት
ለመሆኑ ማረጋገጫው፤ የቃል ኪዳን ማህተሙ፤ ይኸው!” አለና ወንድሟ
አዜብን፡ የምታፈቅራት ጓደኛዋን፡ ወደ ደረቱ ሳብ፤ እቅፍ፤ አድርጉ አንገቷን ቀና በማድረግ፤ ከንፈሯን ግጥም አድርጎ ሲስማት፡ ይህ ሁሉ ተአምር በፍጹም ያልጠበቀችው ነበርና፤ ትህትና ከደስታዋ ብዛት የምትሆነውን አጣች፡፡ ያቺ ከልጅነት እስከ እውቀት፤ በሀዘንና፤ በችግሯ
አንድም ጊዜ ተለይታት የማታውቅ፤ እንደነፍሷ የምትወዳት ጓደኛዋ፤
ይሄውና የወንድሟ ሚስት ልትሆን፡ የሚወልዱዋቸው ልጆች የአክስቴ ፡
የአጎቴ፡ ልጅ ሊባባሉ ነው፡፡ የጓደኝነት ፍቅራቸው ወደ ስጋ ዝምድና ሊሸጋገር ነውና፤ አልቻለችም፡፡እንባዋ በድጋሜ ኮለል ብሎ ሲወርድ አሁንም ህዝቡ
ጭብጨባውን አቀለጠላቸው......

በሚያየው ተደጋጋሚ ትርኢት ተደንቆ፤ በሳቅ እያውካካ ዶክተር ባይከዳኝ ከህዝቡ ፈንጠር ብሎ ቆሞ ነበር፡፡ ያንን ሁሉ ትርኢት ተመልክቶ ካበቃ በኋላ ግን፤ የቅናት ስሜቱ እየተገፈፈ ሄዶ፤በምትኩ የደስታ ስሜት ይሰማው ጀመር፡፡ ምንም እንኳ የዛሬው የሻምበል እድል የሱ እንደነበረ ቢሰማውም፤ በራሱ ጥፋት እድሉን አበላሽቷልና፤ ይህቺ ለሱ ፍቅር ስትል ትልቅ ዋጋ የከፈለች ቆንጆ ልጅ
ከዚያ ሁሉ ችግር በኋላ ከጐኗ ቆሞ አይዞሽ የሚላት አጋር በማግኘቷ
ተደሰተ :: ትህትና ምንም በደል ያላደረሰችበት ልጅ መሆኗን ህሊናው
ደጋግሞ ስለጨቀጨቀው ይቅርታ ሊጠይቃትና እንኳን ደስ አለሽ ሊላት
ፈለገ፡፡ ከዚያም ጠጋ አለና.....
“ለተፈጸመው ስህተት ሁሉ አዝናለሁ፡፡ ላደረስኩብሽ በደልም ከልብሽ ይቅርታ እንድታደርጊልኝ እለምናለሁ :: በሰላም የእስር ዘመንሽን እንድትጨርሺና! መልካም የቀለበት ስነ ስርአት እንዲሆንልሽም ከልብ እመኝልሻለሁ
አላት፡፡
አንተም ፈቃደኛ ሆነህ እዚህ በመገኘትህና እውነቱን በማወቅህ
እኔም በጣም ተደስቻለሁ፡፡ አመሰግንሃለሁ፡፡ ያለፈውን ሁሉ
እረስቼዋለሁ፡፡ላንተም መልካሙ
ሁለ እንዲገጥምህ እመኝልሃለሁ፡፡ አዲስ ቀን ይመጣል : አዲስ ህይወት ይቀጥላል.በማለት አጸፋውን መለሰችለትና፣ ሻምበልን አየችው፡፡ ሻምበልም አያት::ከዚያም ሶስቱም እርስ በርሳቸው ተያይተው ፈገግ ሲሉ፤ አዜብም
ዶክተር ባይከዳኝን እያየች ፈገግ አለች፡፡ ሰራሁልህ ማለቷ ይሆን?

ለጊዜው ቢደብቋትም፤ ውሎ እያደር ለቅሶዋ ቢበዛና ውትወታዋ ቢያስጨንቃቸው፤ እውነቱን ነገሯት፡፡ እንደፈራችውም ልጇ በጤናዋ
እንዳልጠፋች ካወቀች ዕለት ጀምሮ፤ በበሽታዋ ላይ ሌላ በሽታ ተጨመረባት፡፡ ትህትና ከሆስፒታል ድና ብትወጣም እስር ቤት መግባቷን ሰማች፡፡ መርዶ... ትንሹ ልጇ አንዱአለም ደግሞ በእንጭጭነቱ ተለይቷት ለመሄድ መዘጋጀቱን ሰማች፡፡ ሌላ የልብ ስብራት... ያንን የምትወደው ባለቤቷን የነጠቀባት ጦርነት፤ አሁን ደግሞ ሮጦ ያልጠገበ አንድ ፍሬ ልጇን እንዳይነጥቅባት በሥጋት ተውጣ፤
ጠዋትና ማታ እዬዬ ብቻ ሆነ፡፡ሁለቱንም አለኝታዎቿን ከጐኗ ስታጣቸው፤ የወላድ መካን የሆነች መሰላት፡፡ ትህትና ከሆስፒታል ከወጣች በኋላም እቤቷ እንድትገባ ሳይሆን፤ ፍርድ ቤቱ በማረሚያ ቤት እንድትቆይ መወሰኑን ስትሰማ
ከዛሬ ነገ በነፃ ትለቀቅልኛለች ብላ በጉጉት እየተጠባበቀች ጭል፤ ጭል፤ትል የነበረች ተስፋዋ ድርግም ብላ ጠፋች፡፡
ይህ የጨለማ ህይወት ፍጹም ልትወጣው የማትችለው ሆነባት።የቤት ሰራተኛዋ እታፈራሁ የልጅ ያክል ብትንከባከባትና፤ ሻምበል ብሩክና አዜብም ልጆቿን ሊተኩላት ከጐኗ ሳይለዩ
ደፋ ቀና ቢሉም፤ሳይሆንላቸው ቀረ፡፡
ከዚህ በኋላ በሽታው በአንድ ወገን፤ የልጆቿ ናፍቆት በሌላው ወገን ሆነው፤ እየተጋገዙ፤ ስጋዋን እኝከው በመጨረስ፤ የሞት ድግሷን ያፋጥኑት ጀመር..
ትህትና ማረሚያ ቤት በቆየችበት ጊዜ ብቸኝነት፣ መታከት ተስፋ መቁረጥና
👍1
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_አርባ_አንድ


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ

....“ዝግጅቱ በተጀመረ በሦስተኛው ወር ምሥጢሩ አፈትልኮ ተገኘ፡፡ ማን አወጣው? እንዴት አወጣው? የሚታወቅ ነገር የለም፡፡ብቻ በእንግሊዞቹ
ኦብዘርሸርና በፈረንሳዮቹ አፍሪካን ዲፌንስ ላይ ያዕቅዱ ፍንጭ ታትሞ
ወጣ፡፡ እውነቱን ንገረኝ ካልካ ምሥጢሩን ያወጣው የዕቅዱ ጠንሳሽ እራሱ
ነበር፡፡”

“እንዴት? የዛ ምሥጢሩን ሰምን?”

“ቆይ… ዝም ብለህ ተከተለኝ.… እርግጥ ይህ የእኔ መላምት ነው… ግን ዳር ስንደርስ አንተ እራስህ ተመሳሳይ መላምት ላይ እንደምትደርስ እርግጠኛ ነኝ፡፡ እንዳልኩህ ምሥጢሩ አፈተለከ፡፡ ይህ እንደተሰማ የተለያዩ የአፍሪካ ባለሥልጣናት ከወዲያ ወዲህ ሲሯሯጡ ሰነበቱ፡፡ ውጤት ወታደራዊ ዝግጅቱ እራሱን በቻለ ምስጢራዊ መልክ እንዲካሄድና በማንኛውም አገር የሚገኝ ቅርንጫፍ ክፍል በቀጥታ ከዋናው ማዘዣ ካልሆነ በስተቀር በሚገኝበት አገር የመከላከያ ሚኒስቴርም ሆነ ሌላ መንግሥታዊ አካል ጣልቃ ገብ ቁጥጥርም ሆነ ተፅዕኖ እንዳይደረግበት ስምምነት ላይ ተደረሱ፡፡

“ዓላማው ዝግጅቱን አንድ ወጥ
በሆነ መልኩ ለማፋጠንና ምሥጢሩም እንዳይባክን ለመጠበቅ ተብሎ የተቀየሰ ነበር፡፡ በሌላ መልኩ ለተመለከተው ደግሞ ስምምነቱ አገሮች በተናጠል በክልላቸው ውስጥ በሚደረገው ወታደራቂ ዝግጅት ላይ መረጃ እንዳያገኙ የሚያግዳቸው ሆነ፡፡ ይህንን ስምምነት ተቃውሞ የሚቆም አገር ደግሞ ቀደም ሲል የተከሰተው አደነት የምሥጢር መዝረክረክ እንደማይፈጠር ማረጋገጫ ማቅረብ ሊኖርበት ሆነ፡፡ የዚህን ዓይነት ዋስትና መስጠት ደግሞ ለማንኛውም አገርዐአዳጋች ነው፡፡ ያም ሆነ ደሀ ምሥጢሩ በጨቅላ ደረጃው በማፈትለኩ ከዛ በኋላ የወታደራዊ አካሉ እቅሰቃሴ ሁሉ ከኣገሮች ቁጥጥር ውጭ በምስጢር
ለመሆን በቃ፡፡ ይሀን ነበር የፈለገው የዕቅዱ ባለቤት-እንቅስቃሴውን ያላታዛቢ
በቀጥታና በምስጢር መምሪት፡፡ ከዚያ ጊዜ በኋላ የአፍሪካ መሪዎች
የሚያጊንት መረጃ ሁሉ ከዋናው ማበዣ በሚተላለፉ በገባዎች ላይ ብቻ
የተወሰነ ሆነ፡፡

በሌላ ቋንቋ የአፍሪካ መሪዎች የሚያውቁት የእንቅስቃሴው መሪ እንዲያውቁ የሚፈቅድላቸውን ብቻ ሆነ:: ይህም እያንዳንዱ አገር አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኝ ኤምባሲው ባስቀመጠው የወታደራዊ አታሼው
በኩል ብቻ የሚፈጸም ነበር፡፡

“የወታደራዊ አካሉ መረብ እየሰፋና እየተጠላለፈ በመጣ ቁጥር
በየአገሩ የሚገኙ እውቀት ችሎታና ተሰሚነት ያላቸወ የጦር ባለሙያዎች
በጥንቃቄ እየተጠኑና አየተመዘኑ በዚሁ አካል ይዋጡ ጀመር፡፡ ብቻ ምን
ልበልህ..በሁለት ዓመታት ውስጥ እጅግ ጠንካራ፤ እጅግ ሰፊ፧ እጅግ ምስጢራዊ ወታደራዊ አካል አፍሪካ ውስጥ በስውር ተገንብቶ አበቃ:: አልፎ ኣልፎ አንዳንድ ባለስልጣኖች የወታደራዊ ኣካለን አለቅጥ ምስጢራዊ መሆንና መግዘፍ፡ የመቃወም ፍንጭ ሲያሳዩም ያለምንም ምህረት በተናጠል እየተለቀሙ ተወገዱ፡፡ ከዚህ ወዲያ ማንኛውም ምስጢሩን የሚያውቅ ባለሥልጣን ድምፁን ዝቅ እድርጎ መናገርን መረጠ፡፡”

ይህን 'አካል የምትለውን ማነው የሚመራው?” ናትናኤል ጠየቀው፡፡

“በትክክል እነማን እንደሆኑ አላውቅም...ግን ከአፍሪካ አገሮች ሁሉ
የተውጣጡ የጦር አዛዦች እንደሆነ አውቃለሁ፡፡”

“እሺ ቀጥል።”

“ሁኔታው በዚህ ላይ እንዳለ ከሁለት ወር በፊት ወደ አገሬ ተጠራሁ፡፡ አገሬ ውስጥ የቆየሁት ግን ለእራት ሰዓታት ብቻ ነበር፡፡
ሞንሮቪያ እንደደረስኩ ወደ መከላከያ ሚኒስቴር ተወስጀ ስለዚሁ ኣካል
መጠነኛ ገለፃ ከተደረገልኝ በኋላ ለሚቀጥሉት ሦስት ወራት ግልጋሎቴን
ለዚሁ አካል እንደምሰጥና ተጨማሪ መመሪያዎችንም ለመቀብል ወደ ሌላ
ስፍራ የምወሰድ መሆኑ ተነገረኝ፡፡

“እንዳልኩህ ሞንሮቪያ ከደረስክ ከአራት ሰዓታት በኋላ በሌላ አነስተኛ አውሮፕላን የሁለት ሰዓታት ጉዞ እድርጌ ከአንድ በረሃማ ቦታ አረፍን፡፡ ቦታው የቶ እንደሆነ ለመናገር ያስቸግራል። እርግጥ ባንዲራ
ተሰቅሉ ይውለበለባል ግን ባንዲራው አንድ ነው፤ የአፍሪካ አንድነት
ድርጅት ባንዲራ “ከአውሮፕላኑ እንደወረድኩ ማረፊያ ቦታ ተሰጠኝ፡፡ ከእኔ ቀደም ብለው የደረሱ ነበሩ፤ እኔ ከገባሁ በኋላም ሌሎች በተከታታይ ከተለያዩ
እገሮች በሄሊኮኘተሮችና በአነስተኛ አውሮፕላኖች እየተጫኑ ገቡ፡፡ በማግስቱ
ፕሮግራሙ ተጀመረ፡፡ በአጠቃላይ አስራ እንድ ነበርን፡፡ በኋላ እንደተረዳሁት
ሁላችንም በአዲስ አበባ በተለያዩ የአፍሪካ አገሮች ኤምባሲዎች ውስጥ
እንድንሰራ የተመረጥን ነበርን፡፡ እንደውም አንድ ሁለቱን ኤአዲስ ኣበባ ውስጥ ቀደም ብዬ አውቃቸው ስለነበር እዛ በረሃማ ቦታ በቆየሁባቸው ጥቂት
ቀናቶች ልቀርባቸው ችዬ ነበር፡፡ በነገራችን ላይ የሞሮኮ ወታደራዊ አታሼ የነበረው መሃመድ ባስሪ እኔ በነበርኩባቸው ቀናቶች እዛው ነበር፡፡ ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በወሩ ከጊነው ሰው ጋር ተገድሎ ተገኘ፡፡”

“ምን ላይ ነበር የኘሮግራሙ አትኩሮት?» ናትናኤል ወደፊት አዝምሞ ጠየቀው፡፡

“ዝርዝር ነጥቦች ውስጥ አልገባም፡፡ በአጠቃላይ የቆየነው ለሁለት ሳምንታት ነበር፡፡ በመጀመሪያው ሳምንት በአፍሪካ ወቅታዊ ችግር ላይ ነበር ያተኮርነው፡፡ በሁለተኛው ሳምንት ግን ስለ 'ቆንጆዎቹናሰ ስለዓላማው! ስለእን ቅስቃሴው ነበር በጥቅሉ፡፡ በአጭሩ ከመጪው የአፍሪካ መሪዎች ስብሰባ
በኋላ የአፍሪካ መንግሥታት እንደማይኖሩ ነበር የተገለጸልን፡፡››

“ምን ማለት ነው ይሄ?” ናትናኤል ግራ ገባው::
“ነገርኩህ'ኮ ከጥቂት ቀናት በኋላ የምትኖረው አፍሪካ አንድ አፍሪካ
ብቻ ትሆናለች::”

“እንዴት? አልገባኝም፡፡”ናትናኤል የሚያዳምጠው ቅዥት መሰለው፡፡

“የስብሰባው ጊዜ ሲደርስ ጠቅላላ የአፍሪካ መሪዎች ተጠቃለው
አዲስ አበባ ይገባሉ፡፡ ይህ ከተገባደደ በኋላ በመላው አፍሪካ በየአገሩ ያሉ
የአካሉ ቅርጫፍ ክፍሎች በያሉበት አገር ውስጥ መፈንቅለ መንግሥት
አድርገው ሥልጣን ይጨብጣሉ፡፡ ከዚያ በኋላ ማንኛውም መመሪያ ከአፍሪካ
አንድነት ድርጅት ይወጣል፡፡ በአዲስ አበባ በየአገሮች ኤምባሲዎች ውስጥ
በሚገኙ ወታደራዊ አታሼዎች አማካኝነት መመሪያዎች እንደአስፈላጊነቱ ለየአገሮች ይተላለፋሉ፡፡ አበቃ::”

“እንዴ! ስንት መፈንቅለ መንግሥት ማለት ነው?” ናትናኤል ካልቨርቶን አተኩሮ ተመለከተው፡፡ ሰውየው ድጋሚ የሰከረ መሰለው፡፡

“ሃምሳ ሦስት፡፡”
“የፈጣሪ ያለህ! ይህ'ኮ እልቂት ነው፤ ሃምሳ ሦስት አገሮች ውስጥ ጦርነት መፍጠር እኮ ማለት ነው::መቼም ሁሉም አሜን ብሎ አይቀበልም:: ጦርነት ይኖራል፡፡”

“እልቂት አይደለም፡፡ ይኽው አካል ተብትቦ ያልያዘው ወገን በዝብዞ
ያላወቀው ምስጢር በየትኛውም አገር አታገኝም፡፡ ውስጥ ውስጡን በየአገሩ
ጠንካራና ተሰሚ ደጋፊዎች አሉት፤ ውስጥ ውስጡን የየአገሩን ደካማ ጎን
አብጠርጥሮ ያውቃል፤እነማን መያዝ መታሰር.መወገድ አለባቸው? እነማን
ሊታመኑ ይገባል? እነማን ባንዳዎች ናቸው? እነማን ዲቃላዎች ናቸው?
እነማን ንፁህ አፍሪካውያን ናቸው? ሁሉ ይታወቃል።”

“አሁጉራዊ መከላከያ የተባለውስ? ማለቴ" ናትናኤል ግራ ገባው::

“ሽፋን ነው:: አየህ... ወታደራዊ አካሉ የአፍሪካ መንግሥታት እያወቁና ሙሉ ድጋፍ እየሰጡት በምስጢር ለመነቃነቅና የዚህን ዓይነት ስፋት ያለው ወታደራዊ ዝግጅት ለማድረግ በየአገሩ የሚገኙትን ከፍተኛ መኮንኖችን በስሩ ለማሰባሰብ አንድ ተቀባይነት ያለው ሽፋን ያስፈልገው
ነበር፡፡ አህጉራዊ የመከላከያ ሃይል ተስማሚ ሽፋን ነበረ፡፡”

“እና የአፍሪካ መንግሥታት ሁሉ ስለእንቅስቃሴው ምንም
አያውቁም ማለት ነው?''

“ያውቃሉ፡፡ዝግጅቱ ሁሉ: ተቀነባብሮ በየአገሩ ያሉ ቅርንጫፍ ኣካላት
👍3
#የፍቅር_ሰመመን


#ክፍል_አርባ_አንድ


#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን


#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው

...“እየተወዛገብኩኝ ነው መሰለኝ” አለች አኔ ቤታማን፡፡

አኔ ቤታማን ኒኪን እያየች እና በጭንቀት የታችኛውን ከንፈሯን እየነከሰች የኒክ ቢሮ ውስጥ ቁጭ ብላለች፡፡ ያኔ የኮንስርት አዳራሹ ልብስ መልበሻ ክፍል ውስጥ ከተጣሉ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ሁለቱ የተገናኙት፡፡ ስለዚህ ነገራቸው ሳይበላሽ በሰላም ማውራት ይፈልጋሉ፡፡

“ስለባሌ ማለቴ የቀድሞ ባሌ” ብላ አስተካከለችው እና “በቃ ምንም
ዓይነት ድምዳሜ ላይ ሳትደርሺ ስለእሱ የምነግርሽን ነገር እንደትሰሚኝ
እፈልጋለሁ፡፡”

“እሺ” አለች ኒኪ የእሷን እና የአኔን ፍርሃት ለማሸነፍ ራሷን እያዘጋጀች፡፡ አኔ የቀድሞ ባሌ' ብላ ማውራቷ ትንሽ ተስፋ ሰጥቷታል።ማለትም አኔ ባሏን ልትፈታው መንገድ እንደጀመረች ስለሚያሳያት ጥሩ
ስሜትን ሰጥቷታል፡፡ የአኔን ጉዳይ እንዴት መያዝ እንዳለባት ኒኪ ውሳኔ ላይ አልደረሰችም፡፡ ዊሊያምስ ስለ አኔ ባል የነገራትን ነገር ለአኔ ትንገራት? ባሏ እሷ እንደምታስበው ዓይነት ሰው እንዳልሆነ ታስጠንቅቃት? በመሃከላቸው ያለው ቅርበትን ደግሞ ይህንን እርግጠኛ ያልሆነችበትን ነገር ነግራ ልታበላሽው አትፈልግም፡፡ ስለዚህ ኒኪ ጊዜው አሁን አይደለም ብላ ዝምታን መረጠች፡፡

“እሺ ስለ እሱ ምንድነው የምትወዛገቢው?”

አኔ በረዥሙ አየር ሳበችና “እሱ እዚህ ሎስ አንጀለስ ውስጥ ነው የሚገኘው” ይኼ ለእሷ ምን ያህል ያሰጋታል? ፖሊሶቹ እና ዴሬክ ዊሊያምስስ እዚህ እንደሚገኝ ያውቃሉ?

“ዝም በይ ብላ ለራሷ ተናገረች እና “አኔ ራሷ ትናገር እና ወደ እኔ ትምጣ አለች በውስጧ፡፡
እሉ እዚህ የመጣሁት ለቢዝነስ ነው ቢለኝም እኔ ግን አላመንኩትም።
በተቃራኒው እሱ እዚህ የመጣው አኔን አሳምኖ ወደ ቤቱ ለመመለስ
እንደሆነ ነው የሚሰማኝ፡፡”

ጠባኝ አለቻት ኒኪ የተሰማትን የድንጋጤ ስሜት ሳታሳይ እሺ የት ነው ያገኘሽው?”

እኔ እኮ ፈልጌ አይደለም ያገኘሁት” ብላ አኔ ተኮሳተረችና “ከኋላዬ ተደብቆ መጥቶ ነው ያገኘኝ ላዚያውም እዚሁ የአንቺ ቢሮ ከሚገኝበት ሕንፃ ውጪ ነው፡፡ ያኔ ወደ አንቺ ለቴራፒ እየመጣሁ እያለሁ በነበረበት ቀን ላይ ነው ያገኘኝ፡፡”

ኒኪ ይህንን ስትሰማ ኒኪ እላይዋ ላይ ያሉት ፀጉሮች በፍርሃት ተነስተው
ቆሙ። ሮድሪጌዝ እዚህ ቅርቤ ነበር? ቢሮዬ ድረስ መጥቶ ነበር? ይኼ
በእውነት ነገር ፍለጋ ይመስላል።' ብላ አሰበች፡፡

“ያኔ ቀጠሮዬን ስሰርዝ ያልነገርኩሽ...” ብላ አኔ በጭንቀት ጣቶቿን እያቆላለፈች ስታሻቸው ቆየች እና “አንቺ ለእሱ ምን ዓይነት ነገር እንዳለሽ አውቃለሁ። ይህንን ነገርሽን ደግሞ ላባብስብሽ አልፈለግኩም፡፡ በእኛ መካከል ያለውን ነገር እንዳያበላሽ እፈልጋለሁ፡፡”

ኒኪም እጇን ልካ የአኔን እጅ ያዘች እና “እንደዚህ እንድታስቢ ስላደረግኩሽ ይቅርታ፡፡ አኔ ሁሌም አብሬሽ ነኝ፤ ይህንን ደግሞ ታውቂያለሽ አይደል?”

“አውቃለሁ”

“ስለ እሱ ብዙ ነገር ማወቅ እፈልጋለሁ” አለቻት ኒኪ አኔ ግልጽ ሆና ለመናገር በጥሩ ስሜት ላይ እንዳለች ስላየች፡፡

አኔም በኒኪ ጥያቄ ተገርማ “በእውነት ስለእሱ ምን ምን መስማት ትፈልጊያለሽ?”
ኒኪም ፈገግ ብላ “ማንኛውንም ነገር፡፡ ሙሉ ስሙን እንኳን ነግረሺኝ
አታውቂም፡፡”

“ስሙ ሉዊስ ሮድሪጌዝ ይባላል” አኔ መለሰች፡፡

“ታዲያ ለምንድነው የእሱን ስም ስታገቢው ያልወሰድሽው?”

“ይህንን አስቤበት አላውቅም” አለችና ሳቀች፡፡ በመሃከላቸው ያለው
ነገርም በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ እንዳለ ገምታ ደስ አላት እና እኔ የመድረክ
ላይ ሥራዎቼን ስሠራ ቤታማን በሚለው ተከታይ ስሜ ስለሆነ ይህንን
መቀየር ስላልፈለግኩኝ ነው” አለቻት፡፡
“መልካም፡፡ ሥራው የሪል ስቴት ነው ብለሽኝ ነበር አይደል?”
አኔም “አዎን” አለቻት፡፡
“እሱ ብቻ ነው ሥራው?” ብላ ኒኪ ቀለል አድርጋ ጠየቀቻት፡፡
እኔ እስከማውቀው ድረስ አዎ፡፡ ለዚያም ነው እሱ ለቢዝነስ ብዬ ነው
እዚህ የመጣሁት ያለኝን ነገር ያላመንኩት፡፡ ሁሉም የሪል ስቴት ሥራው
ሜክሲኮ ሲቲ ውስጥ ነው የሚገኙት፡፡ ታዲያ እኔን ለማግኘት ካልሆነ
ለምንድነው እዚህ የሚመጣው?” አለቻት፡፡
በየዋህነትና በንዴት መልሱን የመለሰችበት መንገድን የተመለከተችው
ኒኪ በእርግጥም ዊሊያምስ እንዳለው አኔ ባሏ ሉዊስ ሮድሪጌዝ የሚሠራውን
የአደንዛዥ ዕፅ ሥራን እንደማታውቅ ተረዳች፡፡

“ለማንኛውም እዚህ የአንቺ ቢሮ ሕንፃ ስር ያገኘኝ ጊዜ በጣም ነበር የደነገጥኩት፡፡ ጉልበተኛ ሆኖብኝ ነበር፡፡ ስለዚህም በድጋሚ እንዳገኘው ድርቅ ብሎ ጠየቀኝ፡፡ ሉዊስ በጣም ጠንካራ እና የፈለገውን ነገር እስኪያገኝ ድረስ
እስከጥግ ድረስ የሚታገል ሰው እንደሆነ አውቃለሁ፡፡ በቃ የፈለገውን ነገር
እስካላገኘ ድረስ የሚያቆም ሰው አይደለም፡፡”

“እሱ አንቺን ይፈልግሻል?” አለቻት ኒኪ፡፡

አኔም ድምጽዋን ወደ ሹክሹክታ ለውጣ “አዎን ይፈልገኛል”

ኒኪም ለሃያ ሰከንዶች ያህል ዝም ብላ ቆየች እና “እሺ አንቺስ? አኔ አንቺስ ምንድነው የምትፈልጊው?” ብላ ጠየቀቻት፡፡

“እኔ ነፃ መሆን ነው የምፈልገው” አኔ እንደዚህ ፍርጥም ብላ ትናገራለች
ብላ በማትጠብቀው ድምፅ ከመለሰችላት በኋላም “ግማሹ ልቤ ሁሌም ይወድደዋል ይኼንን አልክድም፡፡ ግን የራሴን ኑሮ መኖር እፈልጋለሁ።
ጀርባዬን በጥርጣሬ ቀን ከሌሊት እየተገላመጥኩኝ ማየት አልፈልግም፡፡”

“ከእሱ ጋር ለመለያየት ዝግጁ ነሽ?” ብላ ኒኪ ፈገግ ብላ ስትጠይቃት ሰውነቷ ደስታ እየወረረው ነበር፡፡ አኔ ነፃ ሆና እንድትኖር ትፈልጋለች።

እሷም ራሷ ነፃ መሆን ትፈልጋለች፡፡ አዎን ዴሬክ ዊሊያምስ፣ ነፍሰ ገዳዩን ካገኘ በኋላ፣ ስለ ዶውግ ውሽማ ማንነት ካሳወቃት በኋላ ደግሞ እሷም ነፃ
ሆና መኖር ትጀምራለች፡፡


poc camas
“አዎን ዝግጁ ነኝ፡፡ ያንንም ነበር ልነግርሽ የፈለግኩት፡፡ ግን እኔ
እንዲሄድ አስገድጄው ሳይሆን እራሱ አምኖበት እንዲሄድ ነው፡፡ በቃ እህል
ነው የምፈልገው፡፡ ይህንን ግን ማድረግ የሚቻለው እኔና እሱ ጓደኛሞች
ውሃትን እንዳበቃ እና አብረን መኖር እንደማንችል ራሱ አውቆ እንዲተወኝ
ለመሆን ከተስማማን ብቻ ነው::”
“ገባኝ” አለች ኒኪ ይህችን ጠንካራዋን አኔን እያየች፡፡
“ይህንን ነበር ልጠይቅሽ የፈለግኩት” ብላ የኒኪን እርዳታ በሚሻ መልክ
እያየቻትም “ከእሱ ጋር ነገ ማታ በፎር ሲዝን ሆቴል የአደንዛዥ ዕፅ ሱስን
ማስቆም' በሚል ርዕስ በተዘጋጀው የበጎ አድራጎት ፕሮግራም ላይ እንድገኝ
ስትጋብዘኝ መሄድ ያለብኝ ይመስለኛል።”
ኒኪ ይህንን ነገር ከአኔ ከሰማች በኋላ ውስጧን ሀዘን ተሰማት፡፡
ምክንያቱም በየዓመቱ ከሟች ባሏ ዶውግ ጋር በዚህ ፕሮግራም ላይ ይሳተፉ
ነበር።

“እና ከበፊት ባልሽ ጋር የፍቅር ቀጠሮ አለሻ?” ብላ ኒኪ ጠየቀቻት፡፡
“የፍቅር ቀጠሮማ አይደለም።”
“እና እንደሱ ካልሆነ ለምን ትሄጃለሽ?”
“በመሀከላችን ያለውን ነገር በጓደኝነት ልንቀይረው ስለፈለግኩኝ ነው።
ማለቴ ጓደኛሞች መሆናችንን ላሳየው፣ ያልተጣላንና አንዳችን ላንዳችን ቅርስ
እንደሆንን ነገር ግን በፍቅረኛነት መቀጠል እንደማንችል ላሳየው ስለፈለግኩኝ
ነው።” አለቻት፡፡
አኔ የምታወራው ነገር ሚዛን የሚደፋ ነገር ነው፡፡ ነገር ግን በኒኪ
አእምሮ ወስጥ የሆነ መጥፎ ነገር ሊፈጠር የሚችል ዓይነት ስሜት
ስለተሰማት ምቾት አልሰጣትም፡፡
“የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን መደገፍ እኔና ሉዊስን የመንፈስ እርካታ
የሚሰጠን ነገር ነው፡፡ ባይገርምሽ እሱ ሜክሲኮ ውስጥ በአደንዛዥ ዕፅ
በሚደርሱ ጉዳቶች በጣም ይጨነቃል፡፡ ታስታውሺ ከሆነ
👍3
#የወዲያነሽ


#ክፍል_አርባ_አንድ


#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል


...ዳፈና ውስጥ ተጎልቶ እየተቆሰቆሰ የሚበራ የማገዶ ብርሃን እንደሚጠባበቅ ሰው ሕሊናዬ በተመስጦና በጉጉት የሚጠባበቀው እሑድን እንጂ
ረቡዕንና ሐሙስን አልነበረም፡፡ እያንዳንዷ ቀን በዕጥፍ እየተቀመጠለች ብታጥር
ባልጠላሁ፡፡ ያም ሆነ ይህ ረቡዕና ሐሙስ እንዲሁም ዓርብ ተራ በተራ አለፉ፡፡የሕሊናዬ ጠቅላላ ዝግጅት ለእሑድ ትንቅንቅ ክተት አለ። የትግልና የቁም ነገር
ንፁህ ምርቴን የምሰበስብበት ዕለት እሑድ በመሆኑ ያ አብሮ አደጌ ፍርሃት በቁሜ እንዳያበክተኝ በማለት ተጨማሪ የክርክርና የሙግት ሸንጎ በራሴ ውስጥ
አዘጋጀሁ፡፡

ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ የሁለት እምነቶች የጦፈ ግጭት የሚደረግበት ዋዜማ ነበር፡፡ ምድረ-ግቢው መኻል ዕንጨት ወንበር ላይ ተቀመጥኩ፡፡ ከአባቴ
ጋር በማደርገው የአስተሳሰብ ጦርነት ላይ የሚገጥመኝ የመጨረሻ ውጤት ምን ይሆን እያልኩ ሳሰላስል እቆይና «ውጣልኝ! ውጣ! አሰዳቢ! ውርደተኛ ይዘሃት ገደል ግባ!» ብሎ የጮኸብኝ እንደሆነ ምን እመልስለታለሁ? በማለት ዝግጅቴን ለማጠናከርና ራሴን ለመፈተሽ ሀ ብዬ ነገሩን ወጠንኩ፡ ድንገት ከወንበሬ ላይ ተስፈንጥሬ ተነሣሁና ያስፈለገውን ይበል፥ ይራገም! ያውግዝ! ፍትሐ ብሔሩን
እየጠቀሰ ከሚመካበት የንብረቱ ውርስ ላይ ይንቀለኝ! ይሰርዘኝ! እኔ ግን ከወሰንኳት ሐሳቤ ላይ እንዲት ጋት እንኳን ወደኋላ አልነቃነቅም፡፡ አላፈገፍግም፡፡ወደፊት መሸከም የሚገባኝን የኃላፊነት ቀንበር መሸከም አለብኝ፡ በዚያው አንፃር
ደግሞ የተገዢነትንና የባርነትን ቀንበር መሰባበርና ማነኳኮት ይጠበቅብኛል፡፡እኔው አነጣጥሬ እኔው ቃታ መሳብ ይኖርብኛል! ስለ የወዲያነሽ ሰብአዊ እኩልነት ስለ ሁለታችን የሕሊና ነጻነት ስል የሚያጋጥመኝን ችግርና ማናቸውም ተቃውሞ ሁሉ እቋቋመዋለሁ፥ እደመስሰዋለሁ» ብዩ የአባቴን የሕሊና ምስል ፊት
ለፊት አቁሜ በቁጣ አፈጠጥኩበት ደመናው ውስጥ ድብብቆሽ ስትጫወት የቆየችው ፀሐይ የእኔን ቁጣና የሕሊና ረብሻ የፈራች ይመስል ደመና ውስጥ
ጠልቃ ቀረች፡፡ እኔም ወደ ቤት ገባሁ። ወዲያ ወዲህ ብመለከት ሰው በማጣቴ በቀጥታ ወደ መኝታ ቤት ዐለፍኩ፡፡ የወዲያነሽ የቀኝ እጅዋን ተንተርሳ ዐይኗን
ለእንቅልፍ ሳይሆን ለዕረፍት እንገርባዋለች። በንጹሕ የምንጭ ውሃ ላይ የምትሯሯጥ የውሃ እናት እንደሚመለከት ልጅ አሽቆልቁዬ አየኋት። ደርባባ ዝምታዋ የተንጣለለ ውበት ወለደ። አልጋው ጠርዝ ላይ ጋደም እንዳልኩ
እንቅልፍ ወሰደኝ፡፡ ኻያ ደቂቃ ያህል እንደ ተኛሁ ባንኜ ነቃሁ። በደመና ተሽፍና የነበረችው ፀሐይ መጥለቋን የተረዳሁት ክፍሉ ውስጥ በተተካው ድንግዝግዝ
ጨለማ ነበር። ዟ ብዩ አልጋው ላይ እንደ ተንጋለልኩ የወዲያነሽ ከያዘችው የጠርሙስ ውስጥ ውሃ እየቀነሰች ግንባሬ ላይ አንጠባጠበች።
በሐሳብ መጠመዱን አውቃ በሰበቡ አናጥባ ልትገላግለኝ ነበር፡፡ ከአልጋው ላይ ዘልዩ ትልቁ ክፍል ገባሁ፡፡ ተከትላኝ ገብታ አንድ ቦታ ላይ ቆማ እየዞረች
በምሮጥበት አቅጣጫ ሁሉ ረጨችብኝ፡፡ ሣቋ ሙዚቃዬ ነው። በናትሽ ቆይ በሞቴ ተይ! እባክሽ በሰበስኩ?» እያልኩ ክፍሉን ከአራት ጊዜ በላይ ዞርኩት።
ሰው ይመጣል ብለን ሳንጠረጥር የውብነሽ ድንገት መጥታ በመካከላችን ድንቅር
አለች።

«ኧረ በገላጋይ! ለእኔ ስትይ? ለእኔ ስትይ የዛሬን?» ብላ ጠርሙሱን
ተቀበለቻት። ከውሃው ቀነስ አድርጋ እጅዋ ላይ ስታቁር አይቼ «በቃ! አንቺ ደግሞ የምን ጭማሪ ነሽ» ብዩ ካንገት በላይ ተቆጣሁ፡፡ «ታዘብኩህ! ይኸን ያህል ታደላለህ?» ብላ እያሣቀች ተቀመጠች፡፡ ከጥቂት እንቶ ፈንቶ ወሬ በኋላ «እንግዲህ ነገ ያው ነው:: በእኔ በኩል የተለወጠና የሚለወጥ ነገር የለም» አልኳት
ምናልባት ያመጣችው አዲስ ወሬና ሐሳብ እንዳለ ለማወቅ፡፡ «እናታችን እንደሆነ ከአሁኑ መርበትበት ይዛለች፡፡ የቤቱ ዕቃ ሁሉ ያነቅፋታል። ነጋ ጠባ
ያቃዠኛል ነው የምትለው፣ እኔ እንጃላት» አለችና የትካዜዋን መጠን በወኪልነት
“ለማስረዳት የተላከች ይመስል የሚያሳዝን ባዶ ትካዜ ተከዘች። «ያለቀለት ጉዳይ ነው! ቃዠችም አለመችም አቀራረቤ አይለወጥም» በማለት ውክልናዋን እንደ ጨው አሟሟሁት። ነገሩን ቀዝቀዝ ባለ ሁኔታ የተመለከትኩት ለማስመሰል
«ይልቅስ መትተው ከማይመቱት ጋር ስለምፋጠጥ ምናልባት ተበሳጭቶ የተናደደ እንደሆነ በዚያ በከዘራ እንዳያንቆራጥጠኝና አሳሬን እንዳያስጨልጠኝ በአካባቢው ያለውን በትር ሁሉ ደብቂልኝ፡፡ ስለ ሌላው አትሥጊ» ብዬ የእሑዱን ተራ ሥጋቴን ለፍሥሐም ይሁን ለኀዘን ገለጽኩላት፡፡

እኅቴና ባለቤቴ ወሬ ሲያወሩ እኔ በዝምታ ወደ ውስጤ ሠረግሁ። በልቤ ውስጥ የተከሰከሰው የሐሳብ እቃቅማ ወጋኝ፡፡ ጋሻዬነህና ሠራተኛችን ከእኔ
አቅራቢያ ተቀምጠው ተረት ትተርትለታለች፡፡ የስድስቱም ተበሉና ያንዷ የሞኝ፤ ልጅ ብቻ ቀረ። ዝም ስለምትል ነው እንጂ ሞኝ አልነበረችም። ከዚያ በኋላ
የሰባቱንም ጡት ጠብቶ ሰባት ቀንድ አወጣ» አለችው ሁላችንም ካንገት በላይ እንቶፈንቶውን ሁሉ እያወራን ቤት ያፈራውን ተጋበዝን። የውብነሽን ለመሸኘት እንደ ወጣሁ በዚያው ወደ ጉልላት ቤት ጐራ ብዬ ስጫወት አመሽሁ። የውሳኔ ማሻሻያም ሆነ የሐሳብ ለውጥ አላደረግንም፡፡ ዝግጅቱ ተጠናቆ የሕሊና ጦርነት ክተት ታውጇል። የሚቀጥለው ተግባር ነፃነት ወይም ሞት ብቻ ነው። ነፃነት ግን ይቀድማል። ማታ የወዲያነሽን ጸጥታ እንዳልነሣ ሹልክ ብዩ ገብቼ ተቀመጥኩ።
መደበኛው አንጎሌ ብቻ ሳይሆን መላው አካሌ ሆኖ የሚያስብና
የሚያሰላስል፡ ምክንያት የሚያቀርብና የሚከራከር መሰለኝ፡፡ ሰካራም ባለቤት
በታላቅ ሥጋት እንደምትጠባበቅ ሴት ብቻዬን ተጎለትኩ። ይህን ረጂም ሌሊት ልገፋው የምችለው በንባብ ነው ብዪ ንባብ ቀጠልኩ። ደፋ ቀና እያልኩ ሁለት ሰዓት ያህል ጠረጴዛው ላይ ተኛሁ፡፡በየዕንጨቱ ስንጣቂ ጭላንጭል እየሾለካ
ሚገባው ቀዝቃዛ አየር ነቃ እንድል አስገደደኝ። ቀልቤን ሰብስቦ ያለማቋረጥ ሁለት ሰዓት ያህል ካነበብኩ በኋላ በስተምሥራቅ በኩል ያለውን መስኮት ከፍቼ
አካባቢውን ቃሁት። ጭልምልምታዉ ሙልጭ ብሉ ስላልጠራ ድፍርሱ ብርሃን
ዋና ትንቅንቅ ላይ ነበር። በጋቢዩ ውስጥ መጽሐፌን ደረቴ ላይ ለጥፌ የመስኮቱን ደፍ ተደግፌ ቆምኩ። አጥቢያ ኮከብ ልክ የቀኗ ሁለት ሰዓት ፀሐይ መዳረሻ ላይ
ደርሳ ትንተገተጋለች። ቀስ በቀስ ምሥራቃዊው አድማስ ከዳር እስከ ዳር ግምጃ ለበሰ። ከተራራው በስተጀርባ ያደባችው ፀሐይ ጮራዋን ሽቅብ ወደ ሰማይ
ሰደደችው። አሞሮችና ወፎች ከዚህም ከዚያም መብረር ጀመሩ፡፡ ከየአቅጣጫው
ሲያደነቁሩኝ ያደሩት አውራ ዶሮዎች ዐልፎ ዐልፎ መኮኮል ቀጥለዋል፡፡ ከንጋቱ ዐሥራ ሁለት ሰዓት ሞላና እሑድ ሆነ።

በማለዳው ቀዝቃዛ ጭጋግማ አየር ውስጥ የጋለ የብረት አሎሎ መስላ የምትታየዋ ፀሐይ ብቅ አለች፡፡ ደመና በማይታይበት
ሰማይ ላይ የወጣችው ጀንበር በየደቂቃው ኃይልና ግለት ትጨምር ይመስል ድምቀቷና ብርሃኗ አየለ። እንዲያ እንዲያ ስትል በባዶ ዐይን ከምትታይበት
ሁኔታ ዐልፋ ተንተግታጊ ደረጃ ላይ ደረሰች። እንደ ወህኒ ዘበኛ ከወዲያ ወዲህ በማለት ላይ እንዳለሁ የወዲያነሽ አጠገቤ መጥታ ቆመች። «እስኪ አሁን እንኳ ትንሽ ጋደም በል፤ ደግ አይደለም እኮ! በኋላ እኮ ይደነዝዝሃል! ይደብተሃል»
👍4🤔1
#የተወጋ_ልብ


#ክፍል_አርባ_አንድ


#ድርሰት_በትክክል_ገና


....አሜሪካን ግቢ፣ጌሾ ተራ፣ ዶሮ ማነቂያ፣ ሠራተኛ ሰፈር፣ እሪ በከንቱ በጎንቻ ቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡ የጆብሬና የጎንቻ ጓደኝነት ከሁለትነት ወደ አራትነት ተሸጋገረ። ጎንቻ ጀግንነቱን ለመጀመሪያ ጊዜ ያስመሰከረው
በፈጣን የአንገት ጥምዘዛ ነበር፡
አንድ ምሽት በሀብተ ጊዮርጊስ ድልድይ አካባቢ ለወሊድ የደረሰች ሚስቱን በሌሊት ሆስፒታል አድርሶ የመመለሻ መኪና አጥቶ ወደ ቤቱ ኩስ ኩስ የሚል ምስኪን አንገት እንደ ዶሮ ጠምዝዞ በመጣል ማንነቱን አሳየው።
ጆብሬ ፍጥነቱንና ቅልጥፍናውን የበለጠ አደነቀው።ከዚያን ግዜ ጀምሮ የበለጠ እያከበረውና እየፈራው መጣ፡፡ገንዘብ በሽበሽ ሆነ፡፡ ጆብሬ ኪስ ይዳብሳል።ጎንቻ ማጅራት ይመታል። ክርክር ከበዛ አንገት እንደ ፎጣ ጠምዝዞ ይጨምቅና ይበረብራል"ለካስ በከንቱ ኖሯል ኛሮ ኛሮ ያሰኘኝ?”
አለ፡፡ ኛሮን በአሜሪካ ግቢ ውስጥ፣ ኛሮን በጌሾ ተራ ውስጥ፣ ኛሮን በዶሮ ማነቂያ ውስጥ፣ ኛሮን በሠራተኛ ሰፈር ውስጥ፣ ኛሮን በእሪ በከንቱ ውስጥ አገኘው
ከኛሮ የቀረ የቀረበት ነገር ቢኖር
ዋሻውና የአውሬ ስጋው ብቻ ነበር፡፡በአዲስ አበባ ውስጥ የወላጆቹን ሃይማኖት ቀይሮ የዓለሚቱ ሃይማኖት ተከታይ ሆኖ አብረው ጮማ ይቆርጣሉ፡፡
አልኮል ይጨልጣሉ። ከዓለሚቱ ጋር በአረግራጊ ሽቦ አልጋ ላይ ያረገርጋሉ። ከዓላሚቱ ጋር እንደዚህ ዓለምን እየቀጩ በአዲስ አበባ ውስጥ መኖርን ቀስ በቀስ እየለመደው፣ እየወደደው መጣ፡፡ አዲስ አበባ ጣመችው፡፡ ጆብሬም
እውነተኛ ታማኝ ጓደኛነቱን አስመሰከረ ጎንቻን ጋሻ መከታው አደረገ፡፡ፀብ ከተነሳ ጎንቻ ገላጋይ መስሎ ተበዳይ ላይ ጉብ ነው፡፡ ጆብሬ የደነዘዘ ሰውነት ካገኘ ሞሽልቆ ያመልጣል። ከተነቃበትም ጎንቻ አለኝታው
ነው። ትርዒቱ ቀጠለ፡፡ አንደኛው የአደጋ ጣይ ቡድን ከሌላው ጋር
ተዋወቀ። በጎንቻ የበላይነት በዓለሚቱ ንብረት ተቀባይነትና አስቀማጭነት ወዳጅነቱ ተጧጧፈ።ሌሎቹ የቡድኑ አባላትም ዓለሚቱን በጥሩ አስተናጋጅነቷ ወደዷት። ፍቅር በፍቅር ሆኑ። መኖሪያ ቤታቸውንም ከእንጦጦ ወደ ዋናው መስሪያ ቤታቸው ወደ እሪ በከንቱ አዛወሩና አንድ ሰፊ ክፍል ቤት ተከራዩ።

በገንዘብ ላይ ገንዘብ ተጨመረ፡፡ እያለቀ፣ እየመነመነ የመጣው ገንዘብ ሲያሳስባት የቆየችው ዓለሚቱ ለመቁጠር እስከሚታክታት ድረስ ተንበሽበሸች፡፡ አራጣ በማበደር ሌላ የገቢ ምንጭ ከፈተች፡፡ በውበቷ ላይ ውበት፣
በጌጣጌጦቿ ላይ ጌጣጌጥ፣ በብር ላይ ብር አከማቸች።
ዛሬም በዓለሚቱ ካዳሚነት ጫት እየተቃመ የተዘረፈው ንብረት የሚቆጠርበት፣ ክፍፍል የሚደረግበት፣ እየተመረቀነ፣ እየተፈረሽ ውይይት የሚካ
ሄድበት፣ ተጨማሪ ዕቅድ የሚወጣበት፣ ስትራቴጂ የሚቀየስበትና ስልት
የሚነደፍበት ዕለት ነው፡፡ በቤቱ ውስጥ ያሉት ከዓለሚቱ ጋር አምስት ሲሆኑ ከጆብሬ ሌላ በቅፅል ስሙ “መቀስ" እየተባለ የሚጠራው አንበሴና
በጫት ምርቃና ላይ የሚንተፋተፈው አበራም ይገኙበታል። ጫት ከመጀመሩ በፊት ዓለሚቱ ሳር ጎዝጉዛ ፍራሽ አንጥፋ፣ ከሰል አያይዛ ሁሉን
ነገር አዘገጃጅታለች፡፡

የሜቱ ሥነ ሥርዓት የሚጠይቀው የቄጤማው ጉዝጓዝ ሰንደሉ ዕጣኑ
ሁሉ የተሟላ ነው፡፡ እውነተኛ ካዳሚነቷን አረጋግጣለች ማለት ይቻላል። የሰላም አምባሳደሮች፣ የሳይንስና ምርምር ፕሮፌሰሮች፣ የዕድገት መሀንዲሶች፣ ጥበበኞች እና ምሁራኖችን የምታስተናግድ ካዳሚ..እግሮቻቸውን አጣጥፈው ቦታ ቦታቸውን እንደያዙ ጎንቻ ግድግዳው ላይ ወዳን
ጠለጠለው ኮት ኪሱ ውስጥ ገባና በርካታ ነገሮችን ማውጣት ጀመረ።
በደም የተለወስ የአንገት ሀብል... ትላልቅ የጆሮ ጉትቻዎች… ከወርቅ
የተሰሩ የሴት የእጅ አምባሮች የተለያዩ የብር ኖቶች ያሉበት ትንሽ
ቦርሳ ያ ሁሉ ንብረት ከጥቂት ሰዓታት በፊት አንቆ የዘረፋት ሴት
ሀብት ነበር፡፡ ጆብሬ ዛሬ የሰራውን ሁለት መቶ ብር ከደረት ኪሱ ላጥ
አድርጎ አወጣና አስቀመጠ፡፡ አበራ አልቀናውም፡፡ አንበሴ ዛሬ እንደ አንበሳነቱ ሳይሆን ውርደት ቀምሶ ቡጢ ልሶ ነው የመጣው። ሁለቱ የሰሩትን ሲያወጡ ሁለቱ አፈጠጡ። ወላ ሀባ ጭቅጭቅ ንትርክ የለም። አንዱ ከቀናው ላልቀናው ያካፍላል ዛሬ ባይቀናው ነገ እንደሚክስ የታወቀ ነው፡፡
ይሁን እንጂ መቀስ በጣም አብዝቶታል። ያንን መልካም ቁመናውን ብቻ ዋቤ አድርጎ ዕይኖቹን ያስለመልምና ድርሻውን ላፍ አድርጎ መሰስ ይላል። የቀናው ዕለት እንኳ የረባ ነገር አበርክቶ አያውቅም። እፍኝ ቆሎ ይዞ ከአሻሮ መጠጋት አብዝቷል፡፡ በማንኪያ ሰጥቶ በአካፋ መዛቁን እየደጋገመ መጥቷል።

የተማመነው በማን ይሆን? ጎንቻ ጆብሬ ያስቀመጠውን አየና ወደ ሁለቱ ፊቱን አዙሮ በምልክት
እጃችሁ ከምን? ሲል በእንቅስቃሴ ጠየቃቸው፡፡ ያገኘው መልስ ግን የፈጠጡ አራት ዐይኖች ሲንከባሉና ሲቁለጨለጩ ከማየት ሊዘል አልቻለም።

“ስማ መቀስ ብዙ ብልጥ መሆን አያስፈልግም! የምታገኘውን ላፍ አድርገህ ትሄዳለህ፡፡ ይዘህ የምትመጣው የሰራኸውን ሳይሆን በብልጠት እየቀነጨብክለት መሆኑን ሁላችንም እናውቃለን። በመካከላችን ዋናው ቁም ነገር መተማመን ነው! አንተ ግን ሁኔታህን ደጋግሜ ስመለከ
ተው እምነት የጎደለህ ትመስላለህ፡፡ ሁል ጊዜ የሌላውን ድካም ጠባቂ መሆን ብልጥነት ብቻ ሳይሆን ዐይን አውጣነት ነው!” ተቆጣ፡፡ 'የአበራ ጉዳይ እንኳ ምንም አይደለም የታወቀ ነው። ቶሉ ቶሎ ባይቀናውም
አንዴ ከቀናው በሽ በሽ ስለሆነ ግድ የለም። አንተ ግን አበዛኸው። ከዚህ ውስጥ ምንም የሚደርስህ ነገር እንደማይኖር አረጋግጥልሀለሁ! በርጫህን ቅመህ ለጨብሲ የምትሆን አስር ብር በቂህ ስለሆነ ሌላውን እን
ዳትጠብቅ!" ቁርጡን ነገረው፡፡ ከጎንቻ ያላነሰ የአረመኔነት ባህሪ የነበረው መቀስ ለግላጋ ቁመቱና ወንዳወንድነቱ ከውጭ ለሚያየው ሰው የሚስብ ነው። መቀስ በጎንቻ አነጋገር ወሽመጡ ብጥስ አለ። በጉምዥት አፉን የሞላው ምራቅ በድንገት ደረቀ፡፡ ጎንቻ የበላይነቱን በመያዙ እኔስ ከማን አንሼ? በማለት ሊቀናቀነው የሚሞክር ሰው ነው። የቡድኑን የመሪነት ሥልጣን ለመውሰድ ከመመኘት ባለፈ በጎንቻ ላይ ንቀት ነበረው። ይህንን ንቀቱን በተግባር ለማሳየት ደግሞ ዓለሚቱን አጥምዷታል። ጎንቻ ያን የመሰለ አንጀት
የሚበጥስ ንግግር ሲናገረው ቀስ ብሎ ዓለሚቱን በቆረጣ ተመለከታት፡፡ እሷም የጎንቻን ዐይኖችና የሌሎቹንም
እንቅስቃሴ ጠብቃ ማንም ሳያያት ተደብቃ "ጥቅስ" አደረገችው። ፀብ አትፍጠር ማለቷ ነው፡፡ ምን አሳስበህ? ማለቷ ነው። ተረጋጋ....
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ከሶስት ዓመታት የላምበረት ኑሮ በኋላ ዘይኑን ዳግማዊ ሚኒሊክ ትምህርት ቤት አስገባት። ከላምበረት ዳግማዊ ሚኒሊክ ትምህርት ቤት ከምትመላለስ በአቅራቢያው ቤት መከራየት ፈለገና እሪ በከንቱ አካባቢ ሰራተኛ
ስፈር ሁለት ክፍል ያላት ቤት አግኝቶ ተከራየ፡፡ ዘይኑ ለትምህርት ቤቷ ቅርብ የሆነ ቤት አገኘች። ትንሽ ደስ ያላላት ላምበረት የትውልድ መንደሯን ዓይነት ፀጥታ የሰፈነበት ሲሆን እሪ በከንቱ ግን የተጨናነቀና ሁካታ የበዛበት መሆኑ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ረጅም መንገድ ከመመላለስ ታድጓታልና ጉዳቱን በጥቅሙ አካክሳ ተቀብላዋለች፡፡ ጌትነት እህቱን በቅርበት እየተከታተለ ለጥሩ ውጤት እንድትበቃ ማድረጉ፣ በትምህርት ቤት ተጀምሮ ለሁለት አመታት የዘለቀውና ውስጥ ውስጡን ሲያሰቃየው የኖረው ፍቅር መቋጫው አምሮ ከሚወዳት ከአማረች ጋር አስደሳች
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_አርባ_አንድ


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ


....የእልሁን ያህል ወለል ላይ የተጋደመ ፊቷን በጫማው ረግጦ ድፍጥጥ ካደረጋት በኋላ እዚያው እንደተዘረረች ትቷት ወደ በር አመራ።.
«ዘወር በል!» አለ ማንደፍሮ በር ላይ ተኮልኩሎ ሁኔታውን ይመለከት የነበረው ሰው ሁሉ።
ሳሎን ውስጥ መግባት የጀመሩትም በር ላይ የተኮለኮሉትም ሰዎች ግርር ብለው ወደ ውጭ ወጡ፡፡
ማንደፍሮ ግቢ ውስጥ እየተጯጯህ ይርመሰመስ የነበረው ህዝብ መሀል
እየተራመደ «ማንደፍሮ ገና ዛሬ ተደፈረ ተደፈረ ተደፈረ!» ካለ በኋላ “ዋይ ዋይ ዋይ" እያለ
ከግቢ ወጣ። ግራ ቀኝ ሳይመለከት ቀጥታ ወደ ከተማ ሄዴ፡፡ያ በወያዘሮ ዘነቡ ግቢ ውስጥ ይተረማመስ የነበረ ሕዝብ ሁሉ እየተጋፋ ወደ ሸዋዬ ቤት ገባ፡፡ ርቃነ ሥጋዋን ወለል ላይ ተጋድማ ስታለከልክ ላያት ሁሉ
የምትተርፍ አትመስልም ነበር። የወሳንሳ ተሸክመው አልጋዋ ላይ አጋደሟት፡፡ወይዘሮ ዘነቡ እፈቷ ቆመው «ኧረ እስቲ ውሃ! ኧረ እስቲ ውሃ!» እያሉ ጮሁ፡፡ ውሃ
በፍጥነት ቀረበላቸውና በአፍና በአፍንጫዋ ይወርድ የነበረ ደሟን ሲያጥቡ በነበረበት ወቅት ድንገት ሳታስብ ሔዋን ከተፍ አለች:: በትርምስምሱ ደንግጣ እንዳልነበረ ሁሉ ጭራሽ ወደ ቤት ገብታ የሸዋዬን ሁኔታ ስታይ የባሰ በመረበሽ «ወይኔ ጉዴ! እት አበባ ምንድነው?» እያለች በድንጋጤ ትርገበገብ ጀመር።
በዚህ ሰዓት ሸዋዬ በሌባ ጣቷ ወደ ሔዋን እያመለከተች ድክምክም ባለ ድምፆ «ያዙል...ኝ! ይቺን ሰው ያዙልኝ! ጎረምሳዋን ቤቴ ውስጥ ደብቃ ያስገደለችኝ እሷ ናት! ያዙልኝ!» እያለች ጥሪ ታስተላልፍ ጀመር፡፡
ሔዋን ክው ብላ ደነገጠች። በአካባቢው የነበሩትን ሰዎች አየት አየት እያረገች ወደኋላ ታፈገፍግ ጀመር። ከሔዋን የበለጠ
በውሃ ያጥቧት የነበሩት ወይዘሮ ዘነቡ ከመደንገጥ በተጨማሪ ንድድ አላቸውና፡
«ኣ! ምን እያልሽ ነው አንቺ?» አሏት በቁጣ።
ሸዋዬ ግን አሁንም «ያዙልኝ! እሷ ናት ያስገደለችኝ! ያዙል..ኝ»
ማለቷን ቀጠለች።
ሔዋን ጉዳዩ ስላልገባት ይበልጥ እየደነገጠች ሄደች። ከቤት ወጣችና ግቢ ውስጥ ቆም ብላ ስታዳምጥ ሸዋዬ አሁንም ያዘልኝ እያለች ስትናገር ስትሰማ ጭራሽ ከግቢው ወደ ውጭ ወጣች። ደግነቱ ማንም ሊይዛት አልቃጥም እሷ ግን ደንግጣና ፈርታ ገልመጥ ገልመጥ እያለች በቀጥታ ወደ ታፈሡ ቤት ገሰገሰች፡፡
ወይዘሮ ዘነቡ ንዴታቸው ባሰ፡፡ ያጥቧት የነበረቱን ትውት አደረጉና ወደ ውጭ እያተራመዱ በዙሪያቸው ለተሰበሰበው ሕዝብ በሚሰማ ድምፅ።
ጎረቤቶቹ የሆናችሁ ወገኖቼ የሆናችሁ ሁሉ፣ ይቺን መዘዘኛ ሴት ዛሬውኑ ከቤቴ አውጡልኝ ቶሎ በሉ ዕቃዋን አውጡልኝ ቶሎ በሉ ለእናቷ ልጅ እህቷ ያላዘነች ነገ ለኔም አትመለስ ቀጣፊ ናት ወልወልዳ ናት የተረገመች» አሉ
በማከታተል፡፡ ለዚያች ዕለት እንኳ ቢለመኑ እሻፈረኝ አሉ፡፡ በአካባቢው የተከበሩ ናቸውና ልመናቸው ተከበረ።
በቦታው በርካታ ወጣቶች ስለነበሩ የሸዋዬን ዕቃ አንድ ባንድ እየለቀሙ ወደ ውጭ ማውጣት ጀመሩ። ተባባሪው በርካታ ስለነበር
የሸዋዬን የማውጣት ስራ አፍታ
አላቆየም፡፡ ሁሉም ከአጥር ውጪ ወጣ:: ወይዘሮ እልፍነሽ ዕቃዋን
ደረደሩላት በመፍቀዳቸው ከእሳቸው ግቢ ውስጥ እየገባ ተቆለለ፡፡ ራሷ ሽዋዬም በሰዎች
እቅፍ ተይዛ ወደ እሳቸው ቤት ተወሰደች።
ዝቅዝቅ የዶሮ ሸክም እንዲሉ የሔዋንና የአስቻለውን ፍቅር አፍርሳ የራሷን ቤተ ልትገነባ ደፋ ቀና ስትል የነበረች ሸዋዬ ህልሟ ሁሉ ከንቱ ሆነ።
ድሮም የውሸት ቤት ነበርና እነሆ በአንድ ቀን ፈረሰ!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ከሶስተ ወር በኋላ ነው ፤ የጥር እና የካቲት ወራት መጋጠምያ
ሳምንት። በደንባራ በቅሎ እንዲሉ ወትሮም ግርግር የማይለያት ዲላ ከተማ ሰሞኑን ደግሞ በባስ ግርግር ውስጥ ሰንብታለች፣ የክፍለ ሀገሩ ስፖርት ሻምፒዮና ሲካሄድባት ሰንብቷል ። ከመላ የሲዳሞ ክፍለ ሀገር በርካታ ስፖርቱኞች መጥተው
ይርመሰመሱባታል፡፡ በተለይ በፈስቲቫሉ ማጠናቀቂያ ቀናት ስፖርተኞች በቡድን በቡድን እየሆኑ የመደባደብ አዝሚያሚያ ስለጀመሩ የፀጥታ ጥበቃውም በዚያው ልክ ተጠናክሯል በከተማዋ ውስጥ ያሉ ፖሊሶችና ሌሎች አጋር የፀጥታ ሐይሎች
በተጠንቀቅ ሆነው የከተማዋን ፀጥታ ይጠብቃሉ፡፡
ልከ ሻምፒዎናው በተጠናቀቃበት ቀን ፡ምሽቱ ሦስት ሰዓት አካባቢ
የተፈራው ሁከት የተነሳ መሰለ።
ከአንደኛ መንገድ በላይ ወደ አውራጃው አስተዳደር ፅህፈት ቤት መሄጃ አካባቢ ድንገት የእሪታና ኡኡታ ድምፅ ተሰማ። ወዲያው ደግሞ አንድ ጥይት ተተኮሰ። በርካታ የፀጥታ ሀይሎች ወደ አካባቢው መሮጥ ጀመሩ:: ስፖርተኞች የተጣሉ የመሰለው ህዝብና ሌሎች ስፖርተኞችም ወደዚያው ይጎርፍ ጀመር። ለዚያውምበሩጫና በጫጫታ ታጅቦ።
በርካታ ሰው እቦታው ሲደርስ ግን የጠቡ ዓይነትና መነሻው የተለየ ሆኖ ተገኘ የተጣሉቶ ስፖርተኞች ያልሆኑ ሁለት ሰዎች ናቸው መነሻው በአንዲት ሴት ምክንያት መሆኑ ይወራል ሰዎቹ ለድብድብ መጋበዛቸውን እንደ ቀጠሉ
ናቸው። አንዲት በዕድሜ ጠና ያሉ ሴት ደግሞ ከአንድ ቤት በር ላይ ቆመው ይለፈልፋሉ፡፡ «ያቺ ነውረኛ እኔ ደግሞ ደህና ሰው መስላኝ አንገት ደፊ አገር አጥፊ አሉ! ሆሆይ! የድሀ ቤቱን ልታስፈርሰው!» ይላሉ። ከሴትዮዋ አነጋገር በመነሳት አንድ ፖሊስ ጠጋ አላቸውና ‹‹ምንድነው ችግሩ የኔ እናት?» ሲል ጠየቃቸው።
አሪ በገዛ እጄ ጎትቼ ያመጣሁት ችግር ነው ልጄ ከሁለት ወር በፊት
ሳይሆን አይቀርም፤ አንዲት ሴትዮ መጥታ ቤት አከራይኝ ብላ መጣች፡፡ እኔ ደሞ ጨዋ መስላኝ አክራየኋት። ለካ ጋለሞታ ኖራ ይኸው ሁለት ወንዶችን በአንድ ጊዜ ቀጥራ ሰው ታፋጃለች::» አሉና እንደ እንዝርት በሚሾር ምላሳቸው እየተንጣጡ፡፡
«ጋለሞታዋ የታለች? » ሲል ጠየቃቸው ፖሊሱ::
ሴትዮዋ ከቆሙበት ቤት በታች ቀጥሎ ያለውን ክፍል በእጃቸው እየጠቆመው «እዚህ ቤት ውስጥ ናት ስራዋ አሳፍሯት ሳይሆን አይቀርም ቤት ዘግታ
ትነፋረቅልሀለች::» አሉት:: ፖሊሱ ወደ ተጠቆመው ቤት በር ጠጋ አለና እያንኳኳ
«ክፈች አንቺ! አለ።
«እምቢ! አንክፍትም!» የሚል ምላሽ ሰውስጥ ተሰጠው::
«ነገርኩሽ ብቻ! ፖሊስ ነኝ ክፈች!»
በሩ ተከፈተ፡ ሁለት ሴቶች ቆመው ያለቅሳሉ፡፡ ፖሊሱ በር ላይ ቆሞ ወደ ውስጥ እያየ ማንኛሽ ነሽ ጋለሞታዋ?» ሲል ጠየቀ::
«እዚህ ጋለሞታ የለም» አለች ከሁለቱ አንዷ፡፡ ሌላዋ አሁንም አጎንብሳ ታለቅሳለች እኒያ ላፍላፊዋ ሴትዮ ፖሊሱን ተከትለው ወደ በሩ ጠጋ ብለው ያዩ ነበርና
ነበርና ለፖሊሱ በእጃቸው እየጠቆሙ፡ «ይቺ አጎንብሳ የምትነፋረቀዋ ናት የማትረባ የቆንጆ በለል!» ካሉ በኋላ ወደ ኋላ መለስ እያሉ፡ «ይቺን ሁለት እጆቸን የፊጥኝ አስሮ አርባ መግረፍ ነበር እንጂ..»እያሉ ወደ መጡበት አቅጣጫ ተመለሱ።
ሕዝቡ ከዚያም ከዚህም እየጎረፈ አካባቢው በመደበላለቅ ላይ ነው፡፡
ፖሊሱ የተጠቆመችውን ጋለሞታ በቁጣ
«ነይ ውጪ” አላት በር ላይ እንደ ቆመ
«ለምን?» አለኝው በፍርሀት እየተንቀጠቀጠች፡፡
ፖሊሱ እንደ መናደድ አለና ገባ ብሉ በበይለኛ ጥፊ አንዴ አጮላት፡፡እንድና ከኋላ ዞሮ ወደ በሩ ይገፈትራት ጀመር፡ የቤቱን በር ወጣ እንዳለች ፖሊሱ አሁንም በሀይለኛ እርግጫ መቀመጨዋ ላይ ሲያሳርፍባት ወጀ ላይ ነጥራ.
👍18👎1
#ምንዱባን


#ክፍል_አርባ_አንድ


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ


....ምን እንደሚያደርጉ ሳይታወቃቸው ከንፈር ለከንፈር ይገናኛሉ፡፡ ዓይናቸው እምባ አቅርሮ አንዱ ሌላው ላይ ማፍጠጥ ሆነ፡፡ ማሪየስና ኮዜትም የፈጸሙት ተግባር ይኸው ነበር፡፡

የማሪየስ አያት በዚህ ጊዜ ዘጠና አንድ ዓመት ሆኖአቸዋል፡፡ አሁንም
ከዚያ ትልቅ ቤታቸው ውስጥ ከሴት ልጃቸው ጋር ነው የሚኖሩት:: በዚህ እድሜያቸው ወገባቸው ሳይጎብጥና ሀዘን ፊታቸውን ሳይሰባብር ቀጥ ብለው
የሚጓዙና ለምሳሌነት ሊቀርቡ የሚችሉ የእድሜ ባለፀጋ ናቸው::
ሽማግሌው ሠራተኞችን መደብደብና ምርኩዛቸውን ሳይዞ መንቀሳቀስ በተው ጊዜ ልጃቸው «አሁንስ አባቴ በእርግጥ አርጅቷል» እያለች ታስብ
ጀመር፡፡ በሐምሌ ወር የተጀመረው የፈረንሣይ አብዮት መጥፎ ስሜት
አሳድሮባቸዋል፡፡ ቢሆንም ሞራላቸው ብርቱ ስለነበር ለማንኛውም ነገር በቀላሉ አልተበገሩም፡፡ ነገር ግን ውስጥ ውስጡን መጎዳታቸው ሳይሰማቸው አልቀረም:: ከአራት ዓመት በኋላ እንኳን አንድ ቀን ማሪየስ ከቤታቸው ተመልሶ ከጫማዬ ሥር ወድቆ ይቅርታ ይጠይቀኛል የሚል እምነት
ነበራቸው:: ማሪየስ ተመልሶ ከቤት ሳይወጣ እሞታለሁ የሚል ሀሳብ
ከሕሊናቸው ውስጥ ገብቶ አያውቅም:: እንዲያውም በቅርበ ማሪየስ ይመለሳል የሚለው እምነታቸው እየጠነከረ ይሄዳል፡፡ ይህም ለውለታቢሱ የልጅ ልጃቸው የነበራቸው ፍቅር አጠነከረባቸው::

ይህ ልጅ ሰማይና ምድር ቀሚጨልምበት በክረምት ወራት ነበር ጥሎአቸው የሄደው:: ሽማግሌው በእርሳቸው በኩል ምንም ጥፋት እንደሌለና
ጥፋቱ የማሪየስ እንደሆነ በፍጹም ልቦናቸው ቢያምኑም ለልጁ የነበራቸው ፍቅር ግን አልተቀነሰም፡፡ በመጨረሻ ወደ ሞት መቃረባቸው ሲታወሳቸው
ለልጁ የነበራቸው ፍቅር ያይላል፡፡ ጥርሳቸው መርገፍ ጀምሯል:: ይህም ሀዘናቸውን ከፍ አደረገው::

አንድ ቀን ጉልበታቸውን አጣጥፈውና ዓይናቸውን በከፊል ጨፍነው ቁጭ ይላሉ፡፡ የተስፋ መቁረጥ ምልክት ከፊታቸው ላይ ይነበባል:: ሴት ልጃቸው ጥያቄ ጠየቀቻቸው:

"አባባ፣ አሁንም ልጁን እንደተቀየሙት ነው?»

ይህን ካለች በኋላ ለመቀጠል ስላልደፈረች ዝም አለች::

"ማንን ነው የምትዪው?» ሲሉ ጠየቅዋት::

«ያንን ምስኪን ማሪየስ፡፡»

የሽማግሌ ጭንቅላታቸውን ቀና አደረጉ:: ያንን የተሸበሸበወን
ክርናቸውን ከጠረጴዛ ላይ በማሳረፍ አገጫቸውን ደግፈው ያዙ፡፡ በጣም በተናደደና በተቆጣ አንደበት ተናገሩ፡፡

«ምስኪን ማሪየስ አልሽ? የማይረባ! እርሱ ብሎ ምስኪን፤ አጉራሹን የሚነክስ! የእኛ እልኸኛ! ልስቢስ፣ እንኳን ልብ ነፍስ የለውም::»

እምባ ያቀረረውን ዓይናቸው ልጃቸው እንዳታይ ከነበሩበት ፊታቸውን በማዞር ተነስተው ሄዱ:: ከሦስት ቀን በኋላ በዝምታ አራት ሰዓት ሙሉ ከአንድ ሥፍራ ተቀምጠው ከቆዩ በኋላ ሽማግሌ ልጃቸውን በመገሰጽ ይናገራሉ::

«ስለዚያ ልጅ ሁለተኛ እንዳታነሽብኝ ብዬ አልነበረም?»

በዚያው ሰሞን መሴይ ጊልኖርማንድ እሳት እየሞቁ አምሽተው ስለደከማቸው በጊዜ ልጃቸውን ደህና እደሪ ብለው ወደ መኝታ ክፍላቸው ሄዱ:: ልጃቸው ከሚቀጥለው ክፍል ውስጥ በሩን ክፍት አድርጋ ልብስ እየሰፋች ነበር:: ሽማግሌው እሳት ይሞቁ የነበረው ብቻቸውን ሲሆን
መጽሐፍ ለስሙ በእጃቸው ይዘው ነበር እንጂ አያነቡትም::
እሳት እየሞቀ ሳለ የልጅ ልጃቸው ማሪየስን አስታወሱት:: አሁንም
ቢሆን ውስጥ ውስጡን ይናፍቃቸዋል:: ሊታረቁት ፈለጉ፡፡ ግን ልባቸው ውስጥ የገነነው ኩራትና እልህ መንገዱን ዘጋባቸው:: እንዲያውም ከነአካቴው የመታረቅ አሳብ ኅሊናቸው ውስጥ ስለገባ መላ ሰውነታቸውን አንገሸገሸው::

«ምን?» ሲሉ ራሳቸውን ጠየቁ፡፡ ከአንገታቸው ቀና አሉ:: ከቤት
ውስጥ የገባ ስለመሰላቸው ተንገሸገሹ:: «ከዚህ ቤት ውስጥ ተመልሶ አይገባም» ሲሉ ለራሳቸው ቃል ገቡ:: ያ መላጣ ጭንቅላታቸው ነገር ስለከበደው ከደረታቸው ላይ ዘንበል ብሎ የወደቁ መሰላቸው:: ቀና ብለው
ከግድግዳ ላይ ከተሰቀለው ስእል ላይ አፈጠጡ:: በአሳብ ተውጠው ሳለ ባስክ የተባለ የቤት አሽከራቸው ይገባል፡፡

«ጌታዬ ማሪየስን ያነጋግሩታል?» ሲል ጠየቃቸው:: ሽማግሌው ቀና ብለው ተመለከቱ:: ከአሳባቸው ባንነው ሲነቁ በጣም
ካመደንገጣቸው የተነሳ ጀርባቻው ቀዘቀዛቸው::
‹‹ምን አልክ?» ማሪየስን ነው ያልከው?
«እኔ እንጃ» ሲል ባስክ እየፈራ መልስ ሰጠ፡፡ «እኔ እንኳን በዓይኔ
አላየሁትም:: ሠራተኛዋ ናት የነገረችኝ፡፡ ውጭ ግን አንድ ወጣት መቆሙ እርግጠኛ ነኝ፡፡ ምናልባት ማሪየስ ሊሆን ይችላል፡፡»

«ግባ ግባ ግባ በለው» አሉ እየተንተባተቡ፡፡ ልባቸው እንደከበሮ እየመታ ዓይናቸውን በር ላይ ተክለው ቀሩ፡፡ በሩ ተከፈተ:: አንድ ወጣት በሩን ከፍቶ ገባ፡፡ ማሪየስ ነበር፡፡

«ገባ በል እንጂ» በማለት እንዲጋበዝ የሚጠብቅ ይመስል ማሪየስ ከበሩ አጠገብ ቆም አለ፡፡ ጊዜው ጨልሞ ስለነበር የለበሰው አዳፋ ልብስ መቆሸሹ ብዙም አያስታውቅም፡፡ በሀዘን የተጨማለቀው ፊቱ ምንም እንኳን
ፀጥታ ቢሰፍንበትም መከፋቱን በግልጽ ያሳያል::

መሴይ ጊልኖርማንድ በደስታና በአድናቆት ልቡ እንደተነካ ሰው
ለጥቂት ጊዜ ዝም በማለት ሰማይ ሰማዩን አዩ፡፡ ማሪየስ እንደሆነ ለማረጋገጥ ሠርቀው አዩት::

በመጨረሻ! ከአራት ዓመት በኋላ! ደስታ አንደበታቸውን ዘግቶ ሽባ
አደረጋቸው:: ባለፉት አራት ዓመታት እንዲያው ሲያስቡት ቆንጆ፣ ረጋ ያለና ምራቁን የዋጠ የጨዋ ልጅ እንደሚሆን ገምተዋል:: ቢመለስ ልባቸው |
በደስታ ፈክቶና ስሜታቸው በሕሊና ዕረፍት ረክቶ እጆቻቸውን ዘርግተው እንደሚቀበሉት ልቦናቸው ተመኝቶ እንደነበር ልቦናቸው ቢያውቁም ያ ሰዓት ሊመጣ ሳያወቁት የማይሆን ቃል አንደበታቸው ውስጥ ይገባል።

«ለምንድነው የመጣኸው?»

ማሪየስ ሀፍረት እየተሰማው መለሰ፡፡

«ጌቶች...»

መሴይ ጊልኖርማንድ ከመቀመጫቸው ብድግ ብለው ቢያቅፉት ደስ ባላቸው፤ ግን ማሪየስ አስቀይሞአቸዋል፡፡ በአንድ ወቅት ራሳቸውም ቢሆኑ
በወሰዱት እርምጃ ቅር መሰኘታቸው አልቀረም:: ማሪየስ ቢያስቀይማቸውም መታገስ እንደነበረባቸው ያውቃሉ፡፡ ደግና እልኸኛ ሰው የልቡን ደግነት
በእልህና በኃይለ ቃል እየሸፈነ ወስጥ ውስጡን ይሰቃያል:: ምሬቱ ትዝ ብሉአቸው እንዲናገር እድል ሳይሰጡት ጣልቃ ገቡበት::

‹‹ንገረኝ እኮ፣ ለምንድነው የመጣኸው?»

ጉልበቴን ለመሳም ወይም አቅፈህ ጉንጩን በመሳም ይቅርታ ለመጠየቅ ካልሆነ ለምንድነው የመጣኸው ማለታቸው ነበር፡፡ ማሪየስ አያቱን አተኩር
ሲመለከታቸው ሀሞታቸው መፍሰሱን ተገነዘበ፡፡

ሽማግሌው አሁንም በኃይለ ቃል አቋረጡት::

«ይቅርታ ለመጠየቅ ነው የመጣኸው? ተጸጽተህ ነው?»
ወደ እርሳቸው እንዲመለስ በር መክፈታቸው ነበር፡፡ እጁን የሚሰጥና የሚርበተበት መሰላቸው:: እውነትም ማሪየስ በድንጋጤ ሰውነቱ ተርበተበተ፡፡
ዓይኑን ወደ መሬት ሰበረ፡፡ ቢሆንም በድፍረት መልስ ሰጠ፡፡

«የለም ጌቶች::»

«እና ምንድነው የምትፈልገው?» ሲሉ ሽማግሌው ንዴትና ምሬት
እየተናነቃቸው ተናገሩ፡፡ «አሁን ከእኔ የምትፈልገው ምንድነው?»
ማሪየስ ሁለት እጆቹን በኃይል በመጨበጥ አጋጫቸው አንድ
እርምጃ ወደፊት ተራመደ፡፡

እየፈራና እየተንቀጠቀጠ ንግግሩን ቀጠለ፡፡

«አባባ ይዘኑልኝ::»
👍18🥰1
#የጣሪያ_ስር_አበቦች


#ክፍል_አርባ_አንድ


#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ

...“እናታችንን መዝረፍ አለመቻሌ ሲገባኝ አያትየው ክፍል ሄጄ ለመስረቅ ወሰንኩ” አለኝ።

አምላኬ አይሆንም... ማድረግ አይችልም ግን ደግሞ በጣም ጥሩ በቀል ነው! ስል አሰብኩ። “ታውቂያለሽ… ጌጣጌጦች አሏት: ጣቶቿ ላይ ብዙ ቀለበቶች እና በዚያ ላይ የደንብ ልብሷ አንድ ክፍል እንደሆነ ሁሉ እድሜዋን
በሙሉ የምታደርገው የአልማዝ ጌጥ አላት እንደገናም በገና ግብዣው ላይ አድርጋቸው ያየናት እነዚያ አልማዞችም አሉ። እሷ የሚሰረቅ ብዙ ነገር እንዳላት አውቄያለሁ: በጨለማው መተላለፊያ አቋርጬ በጣቶቼ
እየተራመድኩ የአያትየው የተዘጋ ቢሮ ጋ ደረስኩ።”

ያንን ለማድረግ መድፈሩ እኔ መቼም በፍፁም . . .

“በበሩ ስር የሚታየው ቀጭን ቢጫ የብርሀን መስመር አሁንም እንቅልፍ
እንዳልተኛች እያስጠነቀቀኝ ነበር፡ ምርር አለኝ፡ መተኛት ነበረባት። ሁኔታዎቹ ያ ብርሀን እዛው እንድቆይና አሁን ካደረግኩት የባሰ አጉል ነገር እንዳላደርግ
አደረገኝ ወይም አሁን አንቺ የድርጊት ሰው ከሆንሽ በኋላ አንድ ቀን የቃልሽ ሰው ለመሆን እቅድ ስላለሽ “ድፍረት” ብለሽ ልትጠሪው ትችይ ይሆናል:"

“ክሪስ ከርዕሱ አትሽሽ! ቀጥል! ምን አይነት የእብደት ስራ እንደሰራህ ንገረኝ! አንተን ብሆን ኖሮ ፊቴን አዙሬ ቀጥታ ወደዚህ እመለስ ነበር!”

“እኔ አንቺን አይደለሁማ ካተሪን፣ እኔ እኔ ነኝ... ትንሽ ጥንቃቄ ተጠቅሜ
በቀስታ በሩን በትንሹ ከፈትኩ… በእያንዳንዷ ሰኮንድ ሲከፈት ድምፅ ያሰማል ብዬ ፈርቼ ነበር። ነገር ግን የሆነ ሰው መታጠፊያውን ዘይት አጥግቦታል:: እና እሷ ታየኛለች ብዬ ሳልፈራ በተከፈተው በር ወደ ውስጥ ተመለከትኩና ወደ ውስጥ ገባሁ:"

“እርቃኗን ሆና አየሀት?!” አቋረጥኩት።

“አይ!” ትዕግስት ባጣና በተናደደ አይነት መለሰልኝ፡ “እርቃኗን ሆና አላየኋትም እና በዚያም ደስ ብሎኛል፡ አልጋ ውስጥ ብርድ ልብሱ ስር ነበረች: እጅጌው ረጅም የምሽት ገዋን ለብሳ ተቀምጣ ነበር በትንሹ እርቃኗን ሆና አይቻታለሁ። ታውቂዋለሽ ያ የምንጠላው ብረት የሚመስለው ፀጉሯ
ጭንቅላቷ ላይ አልነበረም ሌሊት ድንገት አስቸኳይ ነገር ቢያጋጥም
አጠገቧ መሆኑን እርግጠኛ ለመሆን የፈለገች ይመስል ቅርብ ኮመዲኖ ላይ
ተቀምጧል"

“ዊግ ነው የምታደርገው?” ብዬ በመገረም ጠየቅኩት ግን ማወቅ ነበረብኝ

“አዎ ዊግ ታደርጋለች የክሪስማስ ግብዣው ዕለት ያደረገችውም ፀጉር ሳይሆን ዊግ ነበር። ጭንቅላቷ ላይ የቀረው ፀጉር የሳሳና ወደ ቢጫ የሚያደላ ነጭ ነው፡ እና ጭንቅላቷ ፀጉር የሌለባቸው ሰፋፊ ሮዝ ቦታዎች አሉት ረጅሙ አፍንጫዋ ጫፍ ላይ ጠርዝ የሌለው መነፅር ሰክታ ትልቅ ጥቁር መፅሀፍ ቅዱስ ታነባለች አሁን ከእሷ መስረቅ እንደማልችል ሳውቅ እየተመለከትኳት
መፅሀፍ ቅዱሱ ውስጥ ያቋረጠችበትን ቦታ በፖስት ካርድ ምልክት አድርጋ ኮመዲኖው ላይ አስቀመጠችና ከአልጋዋ ወርዳ ተንበረከከች ከዚያ አንገቷን አቀርቅራ እኛ እንደምናደርገው እጆቿን አገጯ ስር አደራርባ ረጅም ፀሎት ፀለየች:: ከዚያ ጮክ ብላ “ጌታ ሆይ ስለ ኃጢአቴ ይቅር በለኝ፡ ሁልጊዜ የምሰራው ጥሩ ነው ብዬ የማስበውን ነው እና ስህተቶች ከሰራሁ እባክህ ትክክል ለመስራት አስቤ እንደሆነ እመንልኝ በአንተ አይኖች ለዘለዓለም ፀጋ
ላግኝ አሜን ከተንበረከከችበት ተነስታ አልጋዋ ውስጥ ገባችና መብራቱን አጠፋች አዳራሽ ውስጥ ቆሜ ምን እንደማደርግ አሰብኩ ባዶ እጄን ወዳንቺ ተመልሼ መምጣት አልቻልኩም:: ምክንያቱም አባታችን ለእናታችን የሰጣትን ቀለበቶች እንደማንሽጣቸው ተስፋ አድርጌያለሁ "

ቀጠለ. አሁን እጆቹ ፀጉሬ ላይ ናቸው፡ ጭንቅላቴን እየዳበሱኝ ነው። “ ወደ ዋናው ክፍል ሄድኩና የወንድ አያታችንን ክፍል አገኘሁት፡ በሩን ከፍቼ ያንን እዚያ ተጋድሞ ከአመት አመት ሞቱን የሚጠብቀውን ሰው
የመጋፈጥ ድፍረት እንዳለኝ አላውቅም ነበር።

“ግን ይህ ብቸኛው እድሌ ነው: እጠቀምበታለሁ። የመጣው ይምጣ ብዬ

ልክ እንደ እውነተኛ ሌባ ድምፅ ሳላሰማ በደረጃው ወደ ታች ወረድኩ።ትልልቆቹን ውድ ክፍሎች አየሁ። በጣም ግዙፍና የሚያምሩ ነበሩ ልክ አንቺ እንደምታስቢው እኔም እንደዚህ አይነት ቤት ውስጥ ስለማደግ አሰብኩ
በብዙ ሰራተኞች ተከቦ ሁሉ ነገር በሰው ሲቀርብ ያለውን ስሜት አሰብኩ።
ኦ ካቲ፣ በጣም ቆንጆ ቤት ነው እቃዎቹ ከቤተመንግስት የመጡ መሆን አለባቸው: እናታችን ብዙ ጥያቄዎች ትጠይቂያት ስለነበር ወደ ቤተ መፃህፍት
የሚወስደውን መንገድ አውቄዋለሁ እና ምን እንደሆነ ታውቂያለሽ ካቲ?
ብዙ ጥያቄዎች በመጠየቅሽ በጣም ደስ ብሎኛል ባይሆን ኖሮ ከመሀሉ ተነስተው ወደ ግራና ወደቀኝ የሚታጠፉ ብዙ አዳራሾች ስለነበሩ ይጠፉብኝ ነበር:

“ግን ወደ ቤተመፃህፍቱ መሄድ በጣም ቀላል ነበር። ረጅም፣ ጨለማማ፣ በጣም ግዙፍ ክፍል ሆኖ ልክ እንደመቃብር ስፍራ ፀጥ ያለ ነው::"

ለመስማት የምናፍቀው የነበረውን ነገር እየነገረኝ ነው: በረጅሙ ተነፈስኩ።
መሳቢያዎቹ ውስጥ ገንዘብ እንደሚደበቅ ገምቻለሁ። ስለዚህ ባትሪዬን እያበራሁ
እያንዳንዱን መሳቢያ መፈተሽ ጀመርኩ አንዳቸውም አልተቆለፉም: እና ሁሉም ባዶ፣ ሙሉ በሙሉ ባዶ በመሆናቸው አለመቆለፋቸው አይገርምም እነዚያ ሁሉ ባዶ መሳቢያዎች፣ የወረቀት መያዣዎች፣ እርሳሶች፣
እስኪሪብቶዎች፣ ማስታወሻ ደብተሮች የመሳሰሉት ነገሮችን ለማስቀመጥ
ካልተጠቀሙባቸው መሳቢያው ለምን ይጠቅማል? ወደ ሀሳቤ የመጡት ጥርጣሬዎች ምን እንደሆነ አታውቂም: የዚያን ጊዜ ነው ከቤተመፃህፍቱ
ባሻገር ያለው የወንድ አያቴ ክፍል ለመግባት የወሰንኩት በመጨረሻ ላገኘው ነው... ከምጠላው አያቴ… እንዲሁም አጎቴ ጋር ፊት ለፊት ልገናኝ ነው:
“ግንኙነታችንን በሀሳቤ ሳልኩት እሱ አልጋ ላይ ነው ታሟል። ግን አሁንም
መብራቱን አበራዋለሁ: ከዚያ ያየኛል ትንፋሽ ያጥረዋል። ይለየኛል... ማን እንደሆንኩ ማወቅ አለበት: አንድ ጊዜ ሲያየኝ ወዲያውኑ ያውቃል፡ ከዚያ
እኔ “አያቴ… እንዲወለድ ያልፈለከው የልጅ ልጅህ እኔ ነኝ. እለዋለሁ:: ፎቁ ላይ በሰሜን በኩል ባለው የመኝታ ክፍል ውስጥ የተቆለፈባቸው ሁለት እህቶች አሉኝ በአንድ ወቅት ታናሽ ወንድምም ነበረኝ፡ አሁን ግን ሟቷል እንዲገድሉት ረድተሀቸዋል” ይሄ ሁሉ አእምሮዬ ውስጥ ነበር።ግን አንዳቸውንም ስለማለቴ ተጠራጥሬያለሁ። አንቺ ብትሆኚ ግን ጮኸሽ እንደምታወጪው ጥርጣሬ የለኝም:: ልክ ኬሪ ራሷን የምትገልፅበት ቃላት
ሲኖራት እንደምታደርው አይነት ማለቴ ነው አንቺ ግን ቃላቶቹ አሉሽ ምናልባት እናገረዋለሁ፣ ሲሸማቀቅ አይቼ እደሰት ይሆናል ወይም ምናልባት ሀዘኔታ ያሳይ ይሆናል ወይም በህይወት በመኖራችን የጋለ ብስጭት ያድርበት ይሆናል፡ ይህንን አውቃለሁ ከአሁን በኋላ ግን ለተጨማሪ አንድ ደቂቃ
እንኳን እስረኛ ሆኜ ኬሪም እንደ ኮሪ ስትሞት ማየትን መቋቋም አልችልም::

ትንፋሼን ዋጥኩ። አሁንም ሞቱን በሚጠብቅበት አልጋ ላይ ተጋድሞ፣ ያ ጠንካራ የመዳብ የሬሳ ሳጥን እስኪገባበት እየጠበቀው ቢሆንም የምንጠላውን
👍502
#ሳቤላ


#ክፍል_አርባ_አንድ


#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ


ታሣሥ ገብቷል » የአልፕስ ተራሮች በበረዶ ተሸፍነዋል ይህ የአየር ሁኔታ ለግሮነብል ከተማም ተረፋትና ቅዝቃዜ አመዳይና ድጥ ብቻ ሆናለች በአንዳንድ መንገዶች መኻል ለመኻል የሚያልፉት ቦዮች ያለ ወትሮአቸው ጠቁረዋል"ዐበቅዝቃዜው የተላቀቁት ሰዎች በጐዳናዎቹ ውር ውር ይላሎ " ወይዘሮ ሳቤላ ቬንን ከዚያ ብዙ መስኮቶችና በርች ካሎት ባለ ሰፊ ምድጃና ባለ ሰፊ የጢስ ማውጫ የፈረንሳይ መኝታ ቤት ወስጥ ከእሳቱ አጠገብ ተቀምጣ ትንቀጠቀጣለች ብርዱ ከየአቅጣጫው ይገባል " የበሽተኛ የራስ ቆብ ደፍታ ወፍራም የሱፍ ያንገት
ልብስ ደርባ ሰውነቷ ያለ ማቋረጥ ይንዘፈዘፋል ከእሳቱ በጣም ከመጠጋቷ የተነሳ ልብሷ በፍንጣሪው እንዳይቃጠል የፈራችው ሠራተኛዋ ከአጠገቧ ሁና ትጠብቃታች " ከሚንጣጣው ዕንጨት ፍንጣሪ ሲወረወር ብዙ ጊዜ እየዘለለች ትከለክልላት ነበር " ለሳቤላ ግን ምንም አልመሰላትም " የድንጋይ ሐውልት መስላ በአንድ አቅጣጫ እንደ ተቀመጠች አካሏ ከመንቀጥቀጡ በቀር አትነቃነቅም።

ጥቂት ሊሻላት የጀመረ ትመስላለች አንዳንድ ጊዜ ቀና እያለች መቀመጥ
ይዛለች ብዙ ቀን ታማ ሰንብታ አሁን ትኰሳቱ በረድ እያለላት ነው " ሠራተኞቿ
ግን እንደ ምንም ብላ ተነሥታ ብትንቀሳቀስ ሊሻላት እንደሚችል እርስ በርሳቸው ይንሾካሾካሉ " እሷም ከንፋሳሙ ክፍል ቁጭ ማለት ችላለች ነገር ግን ከመኝታ ቤቷ ወጣች አልወጣች ምንም ደንታ አልነበራትም ።

ዛሬ ቀን መቼም የእህል አምሮቷ ሙቷል ቀደም ብላ ራቷን ቀመሰችና ከባለ ድጋፍ ወንበርላይ ተቀምጣ ስታንጐላጅ ከውጭ የሠረገላ ድምፅ ሰምታ ነቃች።

“ ማነወ ? አለቻት ሞግዚቷን "

“ ጌቶች ናቸው .. እሜቴ! ፒየርም አብሮ አለ " እኔ እመቤቴን ብዙ ጊዜ እየመላለስኩ አይጨነቁ ጌቶች ይመጣሉ ስልዎ የነበረው አሁን እውነት ሆነ " አለመሳሳቴን ዐወቁት ? "

ወይዘሮ ሳቤላ ኮስተር ያለ ቆራጥ ገጽታ በፊቷ ተሰራጨ " ለዚህ አሁን ለመጣ ሰው በፊትም ሆነ አሁን ያልተጨነቀችለት መሆኗን የሚናገር ይመስል ነበር "ትዕግሥትና እርጋታ አይክዱኝ ! አሁን ነው እንግዲህ አለች ሳቤላ ለራሷ "

“ ጌቶች በጣም አምሮባቸዋል ”አለች ሠራተኛይቱ » በፎቅ መስኮት ቁማ ወደታች እየተመለከተች - ከሠረገላ ወረዱ እግራቸውን ከመሬት መታ መታ አደረጉ አለች

መውጣት ትችያለሽ ሱዛን” አለቻት ሳቤላ "

ሕፃኑ ቢነቃስ እመቤቴ ?

እጠራሻለሁ ”

ልጅቱ በሩን ዘግታ ወጣች ሳቤላ ተቀምጣ ሕፃኑን እየተመለከተች ትዕግሥት
እንዲሰጣትና እንዲያስችላት ራሷን በራሷ ስትመክር በሩ ብርግድ ብሎ ተhፈተ
ሰር ፍራንሲዝ ሌቪሰን ገባና ሰላም ሊላት ተጠጋት " መንፈሷ ተመርዞ ንዴቷ
ተቀጣጥሎ ድምጿን እንኳን ሳይቀር አሰለለውና ጮኻ መናገር ስላቃታት እንዳይቀርባት እጁዋን በማራገብ ከለከለችው ከፊት ለፊቷ ተቀምጦ የሚነደውን ዕንጨት
በጫማው እየገፋ ሳይመጣ የቆየው የሥራ ብዛት ከከተማ ሊያስወጣው ባለመቻሉ መሆኑን ነገራት "

አሁን ምን ልታደርግ መጣህ ?

'' ለምን መጣህ ?'' አለ የሷን አባባል ደገመውና “ እንዴ ! በዚሀ አሠቃቂ ቅዝቃዜ ይኸን ሁሉ አገር አቋርጦ ለመጣ ሰው ውለታው ይኸው ነው ማለት ነው?
እኔን በደስታ የምትቀበይኝ መስሎኝ ነበር . .ሳቤላ ”

“ ሰር ፍራንሲዝ” አለችው በሚያስደንቅ ያልተጠበቀ እርጋታ " እስከ መጨረሻው በዚሁ ዘለቀችው " የመልኳ ቶሎ ቶሎ መለዋወጥና ' የልቧን አመታት ለመቀነስ ይረዳት ይመስል አሁንም አሁንም ደረቷን በእጇ ስታስደግፍ ንዴቷን ለመቆጣጠር ከስሜቷ ጋር ምን ያህል እንደምትታገል ይታወቅባታል “ሰር ፍራንሲዝ
መምጣትህን ለአንድ ምክንያት በደስታ እቀበለዋለሁ በደንብ መግባባት አለብን ስለዚህ እዚህ በመገኘትህ በጣም ደስ ብሎኛል " ትንሽ ጠንከር ስል ልጽፍልህ ፈልጌ ነበር : ግን ያንተ መምጣት ከድካም አዳነኝ ያለ ገደብ ያለ ድብብቆሽ ያለምንም ድለላና ማታለል ግልጽልጽ አድርጌ መወያየት እፈልጋለሁ " አንተም
እንደዚሁ የኔን ምሳሌ እንድትከተል እጠይቅሃለሁ

ምን ማለትሽ ነው ?

“ግልጽ አድርጎ መነጋገር በአሁኑ ንግግራችን ግልጽ የሆነ እውነት መኖር
አለበት ”

“ አሳብሽ አልባኝም "

ምንም ሳንሸፋፍንና ሳንደባብቅ ሐቁን መነጋገር አለብን ነው የምልህ" ባለፈው ሐምሌ ስትሔድ በጋብቻችን በወቅቱ እንደምትመለስ ቃል ገብተህልኝ ነበር "
በወቅቱ ስል ምን ማለቴ እንደሆነ ታውቃለህ ነገር ግን . . .


“ በርግጥ ቃል ስገባልሽ ለመመለስ አስቤ ነበር ነገር ግን ለንደን እንደ ገባሁ
በሥራ ተዋጥኩ መምጣት አልቻልኩም አሁንም ቢሆን አጣዳፊ ሥራ ትቸ ስለ መጣሁ ከአንድ ሁለት ቀን የበለጠ አብሬሽ አልቆይም

“ እምነትህን እያፈረስክ ነው " ቃሎችህ የቅጥፈት እንጂ የእውነት ቃሎች አይደሉም ለጋብቻው በወቅቱ ለመመለስ አልፈለግህም : ከመሔድህ በፊት እንዲፈጸምም አልፈሰግህም

የምን ቅዠት ነው ከልብሽ የገባው !” አለ ፍራንሲዝ ሌቪሰን "

“ አንተ ከሔድህ ከትንሽ ጊዜ በኋላ” አለችው በረጋ አነጋገር “አንዷ ሠራተኛ ልብሶችህን ስታደራጅ ከአንዱ ኪስህ ደብዳቤ አግኝታ ሰጠችኝ ቀኑን
ሳየው ወደ ለንደን ነተነሣህ ለት ከደረሱክ ደብዳቤዎች አንዱ መሆኑን አወኩት
ደብዳቤው ፍቺው በሕግ መፈቀዱን የሚገልጽ ነበር ። ያን ጊዜ ባታታልለኝ ገና
ላልተወለደው ሕፃን ስል ብቻ የጓጓሁለት ተስፋ ከንቱ ከከንቱም የባሰ መና መሆኑን ብትነግረኝ ኖሮ ደግ ነበር ።

“እኔ በዚህ አላሰብኩትም።ያለመጠን ተናደሽ ሳይሽ ምንም ቁም ነገር ምንም ምክንያት ቢነግሩሽ በጥሞና የምታዳምጪ አልመሰለኝም
በዚህ አነጋገሩም የልቧ አመታት ጨመረ እሷ ግን እንደ ምንም ብላ ስሜቱን
ግታችው ።

“ የሰር ፍራንሲዝ ሌቪሰን ሚስት ለመሆን መመኘቴ በቂ ምክንያት ያለው አልመሰለህም?

በዚህ ጊዜ የሚነደውን ዕንጨት በጫማው ተረከዝ እየመታ ከተቀመጠበት
ብድግ አለና ፡ “ አየሽ ሳቤላ . . .በኔ ደረጃ ላለ ትልቅ ሰው አንዲት የፈታች ሴት ማግባት ተመሳሳይ የሌለው መሥዋዕት መሆኑን ማወቅ አለብሽ

“ እኔ እኮ መሥዋዕቱን እንድትከፍል የጠበቅሁህ ወይም የተመኘሁህ ለራሴ
ብዬ እንዳልሆነ ያኔም ነግሬህ ነበር ። ነገር ግን ሳይሆን ቀረ ልጁም የኃጢአትና የውርደት ወራሽ ሆነ ። ያውልህ እዚያ ተኝቷል

ሰር ፍራንሲዝ በጣቷ ወዳመለከተችው አንገቱን ዞር አድርጎ ሲመለhት
ከአልጋው ጐን አንድ የሕፃን መኝታ አየ ሔዶ ለማየት እንኳን አልሞከረም።

“እኔ እንግዲህ የአንድ ጥንታዊ ባለማረግ ቤተሰብ ወካይ እንደ መሆኔ
መጠን ” አላት በዚያ ባለፈው የልበ ቢስ ሰው ንግግሩ ተጸጽቶ ይቅርታ የሚጠይቅ በመሰለ ድምፅ አንችን ሚስት ባደርግ ቤተሰቤን ሁሉ አስቀይማለሁ ስለዚህ ...

“ ቆይ” አለችና ሳይጨርስ'' ግድ የለህም የማያስፈልግ ምክንያት ለመፍጠር ራስህን አታስጨንቅ ያሁኑ አመጣጥህ እኔን ሚስት ለማድረግ ቢሆን ኖሮ
ዛሬውኑ እንድንፈጽም የምትጠይቀኝ ቢሆን ኖሮ ሥርዓት አስፈጻሚ ቄስ ይዘህ መጥተህ ብትሆን ኖሮ ከምንም ቁም ነገር አልቈጥረውም ነበር የልጁ ጉዳት አይመለስም ስለራሴ የሆነ እንደሆነ ከአንተ ጋር እንድኖር ከመገደድ የከፋ ፈተና
ያ ገኘኛል ብዬ አላስብም።”

በኔ እንደዚህ ያለ ጥላቻ ካደረብሽ ምንም ማድረግ አይቻልም " ሆኖም
እንድክስሽ አጥብቀሽ በመለመን ከፍተኛ ሁከት ያኔ ፈጥረሽብኝ ነበር ” አላት አሁን አግባኝ ስላላለችው በሆዱ እየተደሰተ።
👍14👎1😁1
#ጠላፊዎቹ


#ክፍል_አርባ_አንድ


#በኬንፎሌት


#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ


hቦትውድ ወደ ሼዲያክ

ኤዲ ዲኪን የበረራ ባልደረቦቹ ወደ ጀልባው ሲገቡ ሲያይ ሊፈጽመው
ያሰበው ክህደት በዓይነ ህሊናው ድቅን አለበት፡ መቼም ሊያደርግ ያሰበውን
ቢያውቁ ዓይንህን ላፈር እንደሚሉት ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ ነዳጁ ባዶ መሆኑን እያወቀ አይሮፕላኑ ባህር ውስጥ ገብቶ ሁሉም እንዲያልቅ ሊያደርግ እንደነበር ያወቁበት መሰለው፡፡

የነዳጅ መጠኑን መቆጣጠር የበረራ መሀንዲሱ ስራ ነው፡፡ ስለዚህ ሰው በዚህ ምክንያት ቢያልቅ ተጠያቂ እሱ ነው፡፡

ሰሞኑን ያሳይ የነበረውን እንግዳ ባህሪ ቢያውቁ ምን ይላሉ? እነሱ በማያውቁት ነገር አዕምሮው ተወጥሮ ቆይቷል፡፡ ትናንት ማታ ራት ላይ ቶም ሉተርን ሲያስፈራራው ነው ያመሸው፡፡ የወንዶች መፀዳጃ ቤት ውስጥ
መስኮት ሲሰበር እሱ
እዚያው ነበር፡፡ ስለዚህ ኤዲን ቢጠረጥሩ
አይፈረድባቸውም፡፡ እንዲህ አይነት ነገር ቢታወቅ ወሬው በአንድ ጊዜ ነው
አይሮፕላኑ ውስጥ የሚዛመተው፡፡

የስራ ባልደረቦቹ በእሱ ላይ ከእንግዲህ እምነት ሊጥሉ እንደማይችሉ ማወቁ በራሱ የኮሶ መድኃኒት እንደመዋጥ ነው የሆነበት፡፡ ከሁሉም
የአይሮፕላኑ ሰራተኞች አቋመ ጽኑ መሆኑ ያኮራው ነበር፡ የሌሎችን ስህተት በቀላሉ ማለፍ ስለማይችል አንዳንዴ ሰዎች በግል ችግራቸው ምክንያት ግዴታቸውን መወጣት ሲያቅታቸው የሚሳደብበት ጊዜ አለ፡፡በይቅርታ ሊታለፍ አይችልም ይላቸዋል ስህተት ሲፈጽሙ ከተገኙ፡፡ አሁን ግን እሱ ራሱ የሚታመን ሰው አልሆነም፡፡

አሁን ለእንደዚህ አይነት ጉዳይ የሚጨነቅበት ጊዜ አይደለም፡፡ ሚስቱን
ለማዳን የማይፈነቅለው ድንጋይ የማይምሰው ጉድጓድ የለም፡፡ ስለዚህ
ሚስጥሩን በሆዱ ይዞ ለብቻው ሊፈጽም ቆርጦ ተነስቷል፡ ስለሌሎች ስሜት
አሁን መጨነቅ የለበትም፡፡ ሆነም ቀረ ህይወታቸውን አንዴ አደጋ ላይ ጥሏል፡፡ ውጤቱም እንዳሰበው ሊሆን ነው፡ አቋመ ጽኑው መሀንዲሱ ዲኪን
ወደማይታመነው ዲኪን መቀየሩ ነው፡፡

በርካታ ተሳፋሪዎች ትንሽ እንቅልፍ ብናገኝ ብለው አይሮፕላኑ ውስጥ
ቀርተዋል፡ የኤፍ.ቢ.አዩ ኦሊስ  ፊልድና  እስረኛው ፍራንክ ጎርዲኖም ከአይሮፕላኑ አልወረዱም፡፡ ቶም ሉተር ባለጸጉራም ጃኬቱን ለብሶና ቆቡን አናቱ ላይ ደፍቶ ጀልባው ላይ። ወጣ፡፡ ኤዲም ከኋላው መጣና ጠጋ ብሎ
‹‹የአየር መንገዱ ህንጻ ጋ ሂድና ስልኩ ያለበት ቦታ እወስድሃለሁ›› አለው፡

ቦትውድ ከእንጨት የተሰሩ ቤቶች የተገጠገጡባት ትንሽ ከተማ ስትሆን
የአይሮፕላኑ ተሳፋሪዎች በየሱቁ ብዙም የሚገዛ ነገር አላገኙም፡፡ መንደሪቱ
የስልክ አገልግሎት አላት፡፡ ኒውፋውንድ ላንድ አሁንም በእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ስር ስለሆነች መኪኖች የሚሄዱት ግራቸውን ይዘው ነው፡፡

ተሳፋሪዎቹ ወደ ፓን አሜሪካ አየር መንገድ ህንጻ ሄዱ፡፡ ኤዲ ከቦትውድ ሰላሳ ስምንት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ አየር ማረፊያ ላይ ካረፈ አይሮፕላን በሬዲዮ የተላከ የአየር ጠባይ መረጃ አነበበ፡፡ ከዚያም ለሚቀጥለው ጉዞ የሚያስፈልገውን የነዳጅ መጠን ስሌት ሰራ፡
ሲሰራ አፉን ደም ደም አለው፡፡ ከዚህ በኋላ የበረራ መሀንዲስ አይሆንም።

ካፒቴኑ የኤዲን የነዳጅ ፍላጎት መጠን ስሌት አምኖ መቀበል ይኖርበታል፡፡ የሰራው ስራ እንዲታመንለት ስሌቱን ሁለት ጊዜ ቼክ አደረገና
‹‹ሌላ ሰው ቢያጣራው እወድ ነበር›› ብሎ ለካፒቴኑ ሰጠው።

‹‹ችግር የለውም›› አለ ካፒቴኑ ለነገሩ ትኩረት ባለመስጠት፡ ‹‹እስቲ
ተናፍሼ ልምጣ›› አለና ወጥቶ ሄደ፡ ኤዲም ካፒቴኑን ተከትሎ ወጣና ቶም ሉተርን ፓን አሜሪካን ህንጻ አጠገብ ሁለት እጁን ኪሱ ከቶ አገኘው፡፡ ‹‹ወደ ስልኩ እንሂድና ከጓደኞችህ
ጋር እንድትነጋገር አድርጌ ቶሎ ወደ ስራዬ እመለሳለሁ›› አለው፡ ሉተር
በመጀመሪያ ጎተት እያለ ነበር የሚሄደው፡፡ በኋላ ግን የትናንት ማታውን
ግብግብ አስታወሰና ቶሎ ቶሎ መራመድ ጀመረ፡፡ ኤዲን እንደገና ማናደዱ
ትርፉ ራስን መጉዳት መሆኑን ተረድቷል፡፡
በመንገዳቸው ላይ መርቪንና ናንሲን አገኙና የአንገት ሰላምታ
ሰጥተዋቸው አለፉ፡፡ ሁለቱም አንድ ላይ በመሆናቸው የተደሰቱ ይመስላሉ፡ሰዎች እሱና ካሮል አን አንድ ላይ ሲሆኑ እንደሚያስቀኑ ይነግሩት ነበር፡ እሷን ሲያስታውስ ብስጭቱ እንደገና ተቀሰቀሰበት፡፡

ስልክ ቤት ገቡና ሉተር የስልክ ቁጥሩን በብጣሽ ወረቀት ጽፎ ለስልከኛው ሰጠው:፡ ኤዲ የሚናገረውን እንዲሰማ አልፈለገም፡፡ ኦፕሬተሩ እስኪያገናኛቸው ድረስ የስልክ መደወያው ክፍል ውስጥ ገብተው ጠበቁ ማለዳ በመሆኑ ብዙ ስልክ ደዋይ የለም፡፡

ኤዲ ካሮል አንን  አይሮፕላኑን የሚያሳርፍበት ቦታ ድረስ ይዘዋት እንዲመጡ ሉተር  እንደሚነግራቸው ገምቷል።
ካሮል አንን በእጁ ካስገባ
በኋላ ደግሞ ሌላ ያሰበውን ነገር ለመስራት ነጻነት ያገኛል ነገር ግን ምን
ሊያደርግ ነው ያሰበው? ወዲያው ለፖሊስ ማሳወቅ? ሉተር ከጠረጠረ ድረስ ደግሞ ዝም ብሎ መጠበቅ የግድ ነው፡፡ ታዲያ በዚህ ጊዜ ውስጥ የሬዲዮ መገናኛውን ከመስበር አይመለስም፡፡ የፖሊስ እርዳታ እስኪደርስ
ጎርዲኖና ሉተር ከአይሮፕላኑ ወጥተው በመኪና ያመልጡና አንዱ ጋ
ይሸጎጣሉ፡፡ ካናዳ ይግቡ አሜሪካ ማንም የሚያውቅ አይኖርም፡፡ ኤዲ
እንዳያመልጡ አስቀድሞ ለፖሊስ ቢነግር ደግሞ ከፖሊሶች ጋር ሲታኮሱ
የካሮል አን ህይወት አደጋ ላይ ይወድቃል፡፡ ኤዲ እንዲህ እንዲሆን
አይፈልግም::

ስልኩ ሲጮህ ሉተር አነሳና ‹‹እኔ ነኝ የዕቅድ ለውጥ መኖሩን ልነግራችሁ የደወልኩት፡፡ ሴትየዋን በጀልባ አይሮፕላኑ ድረስ ካላመጣችሁ የምትፈልጉትን አልፈጽምም ብሏል ሰውየው፡፡ እኔ በበኩሌ ያለውን አምኜ
ተቀብያለሁ፡ ስለዚህ ይዛችኋት እንድትመጡ›› አለና መልሳቸውን ጠበቀ፡፡
ከዚያም ‹‹ሊያናግሩህ ይፈልጋሉ›› አለው ኤዲን፡፡

ሉተር በመጀመሪያ ትዕዛዝ ሲሰጠው ልክ የወሮበሎቹ መሪ መስሎ ነበር የሚታየው፡፡ ካነጋገሩ ግን ካሮል አንን ወደ መገናኛቸው ቦታ እንዲያመጣለት
ለማዘዝ ስልጣን የሌለው ሆኖ ታየው፡፡

‹‹ሊያናግረኝ የሚፈልገው አለቃችሁ ነው?››

‹‹እኔ ነኝ አለቃ›› አለ ሉተር እየከበደው ‹‹ነገር ግን ግብረ አበሮች አሉኝ››

የሉተር ግብረ አበሮች  ካሮል አንን ቦታው ድረስ ማምጣት እንደማይፈልጉ ይታወቃል፡፡ ከእነሱ ጋር መነጋገሩ የሚፈይድለት ነገር አለ? የለም፡፡ ካሮል አንን ስልኩጋ ያመጡና አስለቅሰው የመንፈስ ጽናቱን ይፈታተኑታል፡፡ ‹‹ስትፈልጉ ገደል ግቡ  በላቸው›› አለ  ጮክ ብሎ
እንዲሰሙት፡፡

ሉተር የኤዲ አነጋገር አስደንግጦት እነዚህን ሰዎች እንዲህ ልትናገራቸው አትችልም›› አለ እሱም ጮክ ብሎ፡፡

ሉተር የወሮበሎቹ መሪ ከሆነ ምን አስፈራው? አሁን የሉተርን ስልጣን መገምገም አይረባውም፡፡ ዕቅዱን ማሳካት ነው ያለበት፡፡ ሉተርም ‹‹ወይ አናግራቸዋለሁ ወይም አላናግራቸውም በል›› አለው ኤዲን፡፡

ላናግራቸው እንደማልፈልግ ንገራቸው ለእነዚህ ድንጋይ ራሶች አለው።

አይ አምላኬ አለና ሉተር የስልኩን እጀታ አንስቶ ‹‹አላናግራችሁም
ብሏል፡፡ ሰውየው አስቸጋሪ ነው:›› ንግግሩን ቆም አደረገና ‹‹ጥሩ ሃሳብ ነው እነግረዋለሁ››ብሎ የስልኩን እጀታ እንደያዘ
‹‹ሚስትህ ቀርባለች
ታናግራታለህ?›› አለው ኤዲን፡፡

ኤዲ ስልኩን ሊቀበል እጁን ዘረጋና መልሶ ተወው፡፡ ከእሷ ጋር ከተነጋገረ ምህረት ጠያቂ ሊሆን ነው ነገር ግን ድምጿን ቢሰማ አይጠላም እንደማያነጋግራት በራስ ንቅናቄ ለሉተር አመለከተው፡፡

ሉተር ኤዲ ላይ አፈጠጠና ‹‹አላናግርሽም ብሏል ባልሽ፡፡ ዞር በይ አንቺ
ሸርሙጣ!›› አላት ካሮል አንን፡፡
👍141
#ባል_አስይዞ_ቁማር


#ክፍል_አርባ_አንድ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

ጎነኛው መቃብር ስር አንድ ሰው  እንደሀውልት ተገትሮ   ቆሟል...እዛ ያለ ይመስላል እንጂ በድኑ ብቻ እንዳለ ያስታውቃል። ሀዘኑ ሀዘኗን ቀሰበሰባት። ምኑ ይሆን የሞተበት"የማወቅ ጉጉት አደረባት።አንገቷን አሰገገችና ሀውልቱ ላይ የተፃፈውን ፁሁፍ አነበበች ወ/ሮ ቅድስት ሀምሳሉ 1980 ፡፡ 2015ዓ.ም ይላል።እድሜዋን በአእምሮዋ አሰላችው ።የሰውዬው  እድሜ ገመተች ..አርባ አመት ቢሆነው ነው በቃ ፍቅረኛው ወይም ሚስቱ ነች ስትል አሰበች።እንዲህ ካሠበች በኋላ ለሰውዬው  ያላት ሀዘኔታ ጨመረ፡፡

ለማታውቀው ሰው በዚህ መጠን ሰታዝን ይሄ የመጀመሪያ ገጠመኞ ነው። ምን አልባት እሷ  ገና ለገና ፍቅረኛ እንዲሆናት  የፈለገችው ሰው  ጥሏት ስለተሠወረ  እንዲህ እንቅሽቅሽ ካለች እሱ ደግሞ ፍቅረኛው ወይም ሚስቱ ለዘላለም ጥላው ሞታ ከምድር በታች አፈር ለብሳ ስትቀበር እንዴት ሊያዝን እንደሚችል አሰላችና ሰቀጠጣት...?ያው ለእሱ እያዘነች ቢመስላትም  በተዘዋዋሪ ለራሷ እያዘነች ነው። ወደኋላ  ተመለሰችና ለቃል አባት አምጥታ ሀውልቱ ላይ ካስቀመጥቻቸው አምስት የፅጌረዳ ዝንጣፊዎች መካከል ሁለቱን አነሳች ‹‹ይቅርታ በሚቀጥለው ስመጣ የእነዚህንም ፋንታ ይዤ መጣለሁ... ብድር ነው›› በማለት...ወደሰውዬው ሄደች.. አጠገቡ ቆመች...ከደቂቃዋች በኃላ ዞር ብሎ አያት አየችው.  ።

ጎንበስ አለችና አበባውን በሀውልቱ መሀከል ላይ አስቀመጠችው...፡፡ይደሰታል  ..ያመሰግነኛል ብላ ስትጠብቅ  በቅፅበታዊ ንዴት አይኖቹን አጉረጠረጠባት... ፊቱ በአንዴ ደም ለበሰ...አይኑ ውስጥ የሚንቀለቀል ከገሀነም እሳት የረገፈ ፍም ነው ያየችው..በዚህ መጠን ሰው አስፈርቷትም አስደንግጧትም አያወቅም....፡፡ጎንበስ አለና ያስቀመጠችውን አበባች አነሳና ብጥቅጥቅ አድርጓ ቆራረጣቸው፤ ተበታትነው መሬት ከመርገፍ የዳኑትን ወደ አፍ ከቶ  እያኘከና እየበጣጠቀ መትፍት ጀመረ…፡፡አንድ አምስት እርምጃ ወደ ኃላ ሸሸት አለችው...

‹‹እሷ አበባ ፈፅሞ አይገባትም.››."አሁን ይሄን መቃብር ብንከፍተው ስጋዋን እንዳለነው የምናገኘው..አፈር አይበላትም߹ ከበላትም ለአፈሩ አውዳሚ  አሲድ ነው የምትሆንበት ፤ምስጦችም አይበሏትም ከበሏትም ሰውነታቸው ተመርዞ ያልቃሉ"አላትና ጥሏት ሄደ...በህይወቷ በሞተ ሰው ላይ ሲሰነዘር የሰማችው በጣም መራርና አስከፊው  ወቀሳ ነው ፡፡በመሄዱ እፎይ አለች ..እዛ ከእሷና እሱ ውጭ  ሰው በሌለበት የቀብር ስፍራ  ሲጥ አድርጎ የሚገላግላት መስሏት በፍራቻ መንቀጥቀጥ ጀምራ ነበር ።አይ የሠው ልጅ ከደቂቃዎች በፊት   ለመኖር ያላት ጉጉት ተሟጦ አልቋል ስትል ነበር ..አሁን ደግሞ ህይወቷ ላይ ጥቃት እንዳይደርስ እየሠጋች ነው።እራሷን አረጋጋችና ኩስ ኩስ እያለች ከኋላ  ተከተለችው፡፡

ከመቃብር ቅጥር ጊቢ  ወጥቶ አስፓልት ጠርዝ ላይ ሲደርስ  እርምጃዋን ከእሱ እርምጃ ጋር ማስተካከል ቻለች....ዝም ብሎ መራመድን ቀጥሏል"ማኪያቶ ልጋብዝህ›› አለችው ..ሀሳብ ድንገት ነው የመጣላት፡፡

"አይ  ማኪያቶ አልወድም...አሁን  ጂን  ነው ምጠጣው"

‹‹ጥሩ ሀሳብ ነው.. እንደውም እኔም እሱን ብጠጣ ጥሩ ይመስለኛል።››

"ጥሩ"
"መኪናዬን ግን  ፊታችን ያለው ሆቴል ነው ያቆምኩት… እዛ ብንጠጣ ቅር ይልሀል..?."ዝም ብሎ አቅጣጫውን ወደነገረችው ሆቴል አስተካከለ።ያ ማለት በሀሳቧ መስማማቱን ማሳያ አድራጋ ወሰደችውና ተከተለችው፡፡እንደዛው ጎን ለጎን እየተራመዱ ምንም ሳያነጋገሩ  ሆቴል ደረሱ..  በፅድ ተክሎች የተከበች ከለል ያለች ቦታ መርጠው ተቀመጡ የሚቀመጡበትንም ቦታ የመረጠችው እሷ ነች..)እሱ ለመጠጡ እንጂ ለቦታው ግድም ያለው አይመስልም፡፡

"ስለደረሰብህ ሀዘን በጣም አዝናለሁ››አለችው ፈራ ተባ እያለች፡፡

የእሷን አስተያየት ችላ አለና"አባትሽ ናቸው?"ሲል ጠየቃት…ደነገጠች

"ምን? ማን?"

"ቀብሩን ነው ያልኩሽ"

"እ...የእጮኛዬ አባት ናቸው...ማለቴ የፍቅረኛዬ...   ማለቴ የማፈቀረው ልጅ አባት"

"በአንድ ፅኚ እንጂ..የምን መወነባበድ ነው?"

"ወድጄ ይመስልሀል"

"የት ነው"

"ማ ?"
"እሱ...የምታፈቅሪው ልጅ"

"ገዳም ገባ"

መልሷን ከሰማ በኃላ ያዝንልኝና  ያፅናናኛል ብላ ስትጠብቅ

‹‹ተገላገለ" ብሎ እርፍ።

"እንዴት እንደዛ ልትል ቻልክ?"

"ያው አንድ ቀን ልቡን ሰብረሺው  ስቃይ ውስጥ ከሚገባ እንዲ በደህናው ጊዜ ገዳም መግባቱ ይሻለዋል"

"እንዴት ልቡን ልሰበር እችላለሁ ከራሴ በላይ እኮ ነው የማፈቅረው"

"እዛ የተኛችው ማለት ቅድም አበባ  የሠጠሻት ሴትም ከአመታት በፊት እንዲሁ አንቺ ያልሺውን ቃል  መቁጠር ከምችለው ጊዜ በላይ ብላኝ ነበር"

"ታዲያ ምን ተፈጠረ?"

"ያው እንዳልኩሽ ነዋ የልብ መሠበር"

"ሁሉም ታሪኮች ፍፃሜያቸው እንደምታስበው አይደሉም"

"ናቸው..ቆይ አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ?"

"ጠይቀኝ"

"አሁን ጥሎሽ ገዳም ከገባው ልጅ በፊት ፍቅረኛ ነበረሽ"

"አዎ ነበረኝ"

"ታፈቅሪው ነበር?"

"በወቅቱ አዎ አፈቅረው ነበር"

"ጥሩ ...እንደምታፈቅሪውስ ነግረሽው አታውቂም"

"በወቅቱማ እንዴት አልነግረው ...ፍቅረኛዬ ነበር...እንደማፈቅረው ብዙ ጊዜ ነግሬው አውቃለሁ።"

"በቃ መልሴ ተመልሶልኛል"

ድንግርግሯ ወጣ ።ምን ለማለት እንደፈለገ ምንም አልገባትም።

‹‹የምኑ መልስ?"

"ያው መጨረሻውን አየሽው߹ ከዛ ፍቅረኛሽ ጋር አሁን አብረሽ የለሽም...የሌላ ወንድ ፍቅር ፍለጋ በየመቃብር ሀውልቱ ትዞሪያለሽ ߹ያ ፍቅረኛሽ ግን ምን እየተሠማው እንደሆነ ምን ያህል እንዳዘነ ?በምን ያህል መጠን እየናፈቅሽው እንደሆነ ?ምንም ትዝ ብሎሽ አያውቅም አይደል?።"

ለወንዶች ያለው ውግንናና ለሴቶች ያለው ጥላቻ ጠርዝ የወጣ ነው ብላ ስላሰበች አበሳጫት።

"ምን እያልክ ነው..?ቺት ስላረገብኝ እኮ ነው  የተለያየነው"

"እ እንደዛ ነው?" አለና  ጅኑን አንስቶ ተጋተው
‹‹ምነው?  በቂ ምክንያት አይደለም?"

"ለወንድ አዎ .ለሴት ግን አይደለም"

"አልገባኝም?

"ሴት  መጀመሪያውኑ  ለመለየት  አቀባብለ እየጠበቀች ካልሆነ በስተቀር ፍቅረኛዋ ችት ስላደረገባት ብቻ አታባርረውም"

ዝም አለች። ይሄ  የአስፈሪው እንግዳ ሰው ንግግር ለሌሎች ሴቶች ይስራ አይስራ ባታውቅም  እሷን በተመለከተ ዝንፈት የለበትም...እናም ገፍታ ልትከራከረው አቅም  አላገኘችም።ለተወሰነ ደቂቆች በዝምታ እያሰላሠለች ጅኑን መሳብ ጀመረች።ድንዝዝ እንዲላት ፈልጋለች። ለዛሬም ቢሆን እንኳን  ሁሉን ነገር መርሳት።

"እስቲ ስለራስህ ንገረኝ...ስለእሷ...አበሳጭታህ  ስለሞተችው ሴት"

‹‹እርግጠኛ ነሽ መስማት ትፈልጊያሽ?››

‹‹አዎ በደንብ›› አለችና ለመስማት አቆብቆበች….አቀማመጧን አስተካከለች…ማውራት ጀመረ

‹‹የሶስት አመት ፍቅረኛና የአራት አመት ባለቤቴ ነች፡፡ከባለጉዳይ ጋር ስዳረቅ እና ከሀለቃዬ ጋር ስጨቃጨቅ ቆይቼ በድካም ውልቅልቅ ብዬ ወደ ቤቴ ስመጣ  በገዛ አልጋዬ ላይ ከገዛ ጓደኛዬ ጋር ተኝታ ደረስኩ።ከመተኛቷ በላይ ያበሳጨኝ ከእኔ ጋር ስትተኛ ሰምቼው የማላውቀውን በደስታ የመቃተት ድምፅ መስማቴ ነው። የወሲብ ፊልም አክተሮች እራሱ እሷ እያለከለከች እንዳለው አያለከልኩም። ለማንኛውም በአፍላ ስሜት ነቅናቂ ሙዚቃ በታጀበ ተራክቦ ላይ እያሉ ደረስኩባቸው።

እሱ በመስኮት ዘሎ ፈረጠጠ..እሷን ያዝኳት..።
👍836😁2👏1
#ተአምረተ_ኬድሮን


#ክፍል_አርባ_አንድ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
//

በ25ኛው ቀን ጥዋት ቁርስ ከበሉ በኃላ

‹‹ዛሬማታ ልሄድ ነው››

‹‹የት ነው የምትሄደው…..?››ደንገጥ ብላ ጠየቀችው ሰሚራ

‹‹ከከተማ ወጣ ብዬ  ትንሽ ራቅ ብዬ ምን ማድረግ እንዳለብኝ ማሰብ እፈልጋለሁ….››

‹‹ስለምንድነው የምታስበው..…..?ክፉ ነገር አይደለም አይደል…..?››

‹‹እኔ እንጃ …ለጊዜው ምንም የመጣልኝ ነገረ የለም..እንደገደሉኝ ልግደላቸው…ወይስ ይቅር ልበላቸው …..?የማውቀው ነገር የለም…ገንዘቤን ግን ልጅነቴን የሰዋሁበትና ብዙ ፈተና ያየሁበት ስለሆነ ሰባራ ሳንቲም እንደማልተውላቸው እርግጠኛ ነኝ..ምን አልባት እስከዛው በደንብ ቢደሰቱበት  ጥሩ ነው››

‹‹እንዴት አድርገህ ታስመልሳቸዋለህ……..?አሁን እኮ ንብረትህ በእነሱ እጅ ነው..በህይወት መኖርህን ካወቁ ባለ በሌለ  ኃይላቸው ነው አሳደው የሚያስገድሉህ››

‹‹አይዞሽ አታስቢ… እጠነቀቃለሁ….ለዛም ነው ከዚህ ከተማ ራቅ ብዬ በጽሞና ምን ማድረግ እንደምችል ማሰብ አለብኝ የምልሽ››

‹‹ካልክ እሺ ..ቆይ መጣሁ›› ብላ ከነበሩበት ሳሎን ተነስታ ወደመኝታ ቤቷ ከሄደች ከ5 ደቂቃ በኃላ ተመልሳ መጣችና ቼክ እጁ ላይ አስቀመጠችለት፣..ግራ ገብቶት አንዴ የሰጠችውን ቼክ አንዴ ደግሞ እሷን በማፈራረቅና በመገረም ሲያያት  ከቆየ በኃላ

‹‹ምንድነው ይሄ…..?››ጠየቃት

‹‹የራስህ ብር ነው..አንተን እንድገድልላቸው የከፈሉኝ ነው…ሁኔታዎችን እስቲስተካከሉልህ ለመንቀሳቀሻ ይሆንሀል››

‹እንዴ ምን አይነት ሰው ነሽ….?እንዲህ አይነት ሰው እኮ በዚህ ጊዜ አይገኝም››

‹‹አይ እንደምታስበኝ ደግ ሴት ሆኜ አይደለም..ለአንተ ብቻ ነው እንዲህ የሆንኩት..››

በንግግሯ ውስጡ ተነካና‹‹ለእኔ ለምን…..?››ጠየቃት

‹‹እኔ እንጃ….. ›አለችው
..ከተቀመጠበት ተነሳና ስሯ ተንበረከከ..ደነገጠች፡፡ አቀፋት …አንገቷ ሰር ገብቶ ሳማት…. ውርርር አደረጋት፣..አላቆመም… ወደታች አስጎንብሶ ግንባሯን …አይኖቾን… ጉንጮቾን በመጨረሻ ከንፈሯ ላይ ተጣበቀባት…አይኗን ከመጨፈን እና ከንፎሯን ከማነቃነቅ ውጭ ምንም ተቃውሞ አላሰማችም…ደስ የሚሉ እልፍ መሰል ሁለት ደቂቆች አለፉ….

የሚያደርገውን አድርጎ ከተቀመጠበት ተነስቶ ሲቆም እሷ አፍራ  አቀረቀረች…
የሰጠችውን ቼክ መልሶ ጉልበቷ ላይ እያስቀመጠላት..ይሄ ምን አልባት እኔን ለገደልሽበት ቢከፍሉሽም.. አንቺ ግን እኔን ለማዳን ለህክምና ይሄን ቤት ለመከራየት ላወጣሽው ወጪ መሸፈኛ ይሁንሽ…ውለታሽ ግን በዚህ ብር የሚመለስ ወይም የሚጣጣ ፍጽም አይደለም…በሕወቴም ጭምር ከፍዬ አልጨርሰውም››

‹‹ህይወትህን ስፈልግ ያኔ  ትከፍለኛለህ …አሁን ግን ከእኔ ይልቅ አንተ ነህ ችግር ላይ ያለህው …  ደግሞ ከራሴ ገንዘብ ምንም ያወጣሁት ነገር የለም…ከዚህ በተጫማሪ መቶ ሺ ብር ቦነስ ብለው ሰጥተውኝ ነበር…እርግጥ ከላዩ ላይ አንተን ለማሸሽ እና የሬሳ ሳጥኑን ቀይረው ለሰጡኝ አቶ ተካ 50 ሺ ብር ከፍያለሁ..ሌላውን 50 ሺብር   ደግሞ እስከአሁን እየተጠቀምኩበት ነው ፡፡››

‹‹አይዞሽ ለእኔ አትስቢ አልኩሽ እኮ …እነሱም ሆነ ማንም የማያውቀው 5 ሚሊዬን ብር ባንክ አለኝ…..በዛ እጠቀማለሁ፡፡››

‹‹ግን ባረብሽህ ምትሄድበት ይዘህኝ ብትሄድ …..?››

‹‹አረ ደስ ይለኛል..ስራሽን ብዬ እኮ ነው…..?››

‹‹ስራው ይደርሳል››

‹‹በያ ተዘጋጂ….መኪና እንከራይ ››

‹‹ወደየት ነው ግን ምንሄደው…..?››

‹‹እግራችን ወደመራን….››

ይቀጥላል
👍1129👎5👏2
#ትንግርት


#ክፍል_አርባ_አንድ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

ዶ/ር ሶፊያ ግማሽ ልቧን ታዲዬስ ጋር ጥላ እሩብ ልቧን ወደ ትንግርት ልካ በሩብ ልቧ ነው ከሀዋሳ ተመልሳ ቤቷ የደረሰችው፡፡የሳሎኑን በር ከፍታ ስትገባ ፕሮፌሰር ዬሴፍ ሶፋ ላይ ጋደም ብሎ ፊልም እየተመለከተ ነበር፡፡ እንደገባች በፍቅር እና በመፍቀለቅለቅ ተጠመጠመባት ..ከንፈሯን ሳመት…ዝም ብላ ሳትስመው ተሳመችለት፡፡ ሰላምታውን ከጨረሱ በኃላ የፊቷን መገባበጥ ሲመከት በጣም ደነገጠ ‹‹እንዴ ቤቢ.… ምንድነው ይሄ.....? ምን አጋጠመሽ?::<<

‹‹ትንሽ የመኪና ግጭት ነው፡፡››ዋሸችው፡፡

‹‹ታዲያ ተረፍሽ..…?››

‹‹አዎ ቀላል ግጭት እኮ ነው ..ግን አንተ እንዴት መጣህ?››

‹‹አንቺ ጋር ነዋ፡፡››

‹‹እሱማ በስልክ ነገርከኝ ...ማለቴ እንምትመጣ አልገርከኝም ብዬ ነው?››

‹‹ሰርፕራይዝ ላደርግሽ ፈልጌ ነዋ፡፡››

‹‹እብድ እኮ ነህ.....ሰው እንኳን ከአሜሪካ ከደብረዘይት ሲመጣ ይናገራል…፡፡››

‹‹ልጅቷስ የት ሄደች ?››አለችው..ከመጣች ሰራተኛዋን ስላላየቻት ግራ ተጋብታ፡፡

‹‹አለች ..ቢራ እንድትገዛልኝ ልኬያት ነው፡፡››

‹‹ፍሪጅ ውስጥ የለም እንዴ?››

‹‹ጨረስኩታ... ከመጣው እኮ ሶስት ቀን ሆነኝ፡፡››

‹‹እስቲ መጣው በጣም ሞቆኛል... ሰውነቴን ለቅለቅ ልበል››አለችና ከተቀመጠችበት ተነስታ ወለሉ ላይ አስቀምጣ የነበረውን ሻንጣዋን እየጎተተች ወደ መኝታ ቤት ገባች፡፡

ዬሴፍ ከኃላዋ መላ አቋሟን እና የሚሞናደለውን መቀመጫዋን በአትኩሮት ተመልክቶ‹‹አማላይ ነሽ….›አለና ምራቁን ዋጠ፡፡ በእድለኝነቱም አምላኩን አመሰገነ፡፡ በአንድ ወር ውስጥ ደስ በሚል ሁኔታ ድል ባለ ሰርግ ያገባትና መልሶ ወደአሜሪካ ይዟት ይሄዳል..ወደአሜሪካ የመሄዱን ሀሳብ አልቀበልም ብትለው እንኳን ከእሷ የሚበልጥበት ነገር ስለሌለ እሱ ጓዙን ጠቅልሎ ወደ ሀገር ውስጥ ተመልሶ ከእሷ ጋር ይኖራል ..፡፡አሁን በሱ ህይወት የጎደለችው እሷ ብቻ ነች፡፡የሚፈልገውን አይነት ትምህርት ተምሯል፣የሚፈልገውን ዓይነት ስራ እየሰራ ነው፣የሚፈልገውን ያህል ገንዘብ አጠራቅሟል፣በዚህ ሁሉ ስኬት ላይ ሶፊን ማግባት ከቻለ…እሷ ደግሞ አንድ ወንድ እና አንድ ሴት ልጅ ከወለደችለት ..በቃ በዚህ ምድር ላይ ከእሱ በላይ ዕድለኛ ሰው ከየት ይገኛል?፡፡

ሶፊ መኝታ ቤቷ እንደገባች በቁሟ ነበር አልጋዋ ላይ የተዘረረችው፡፡የሶስት ዓመት
ፍቅረኛዋ በእሷ ትልቅ ተስፋ አድርጎ ውቅያኖስ ተሻግሮ በመምጣት ሳሎኗ ውስጥ ይገኛል፡፡ እሷ ግን በአካል ስታገኘው ውስጧን ደስታ አልተሰማትም…እንደውም በተቃራኒው የቅሬታና የመረበሽ ስሜት ነው በደም ስሯጰየተሰራጨው..በውስጧ የተፈጠረውን ስሜት ልትቆጣጠረው የምትችለው ዓይነት አይደለም፡፡ብቻ ውስጧ በነውጥ እየተናጋ ነው፡፡በልቧ ኃይለኛ ወጀብ ሲደበላለቅ ይሰማታል፡፡ከሚጡ ፣ከሰላም፣ ከሄለን ፣ከሀሊማ እና ከሙሴ ጀርባ የታዲዬስ ምስል በትልቁ ይታያታል፤ፅዬን ደግሞ እሱ ጭንቅላት ላይ ጉብ ብላ ስትደባብሰው.. በውስጧ የተፈጠረው ብስጭት ጭንቅላቷን አቃጠላት፤ከእዛ ሀሳብ ስትሸሽ ደግሞ ትንግርት ተቀበለቻት...ተፈናጥራ ከመኝታዋ ተነሳችና ልብሷን በማወላለቅ ወለሉ ላይ አዝረክርካ ወደ ሻወር አመራች ..የሰውነቷን ሙቀት ብቻ ሳይሆን በአዕምሮዋ የሚተረማመስ ሀሳብ ለማቀዝቀዝ፡፡
ፀጉሯን በላስቲክ ሸፍና ቧንቧውን ከፈተች፤ውሀው ካላይ እየተንፎለፎለ ሰውነቷን ሲያረጥበው ቀስ በቀስ የጋለው ገላዋን አቀዘቀዘላት..ያም ብቻ ሳይሆን የተረበሸ መንፈሷም እየተረጋጋላት መጣ፡፡ በመሀከል ‹‹ቤቢ..ቤብ››የሚለው የፕሮፌሰር ዬሴፍ የጥሪ ድምፅ ከነበረችበት የተመስጦ ድባብ አናጠባት፡፡

‹‹...ቤቢ አልጨረሽም እንዴ?››እያለ መኝታ ቤቱን አልፎ ወደ ሻወር ቤቱ ተጠጋ፡፡

እዛው እንዲጠብቃት በሚፈልግ ስሜት ‹‹ጨርሼያለሁ ...መጣሁ›› አለችው፡፡ እሱ ግን የሻወር ቤቱን መዝጊያ ገፋ አደረገና አንገቱን ወደውስጥ አሰገገ....ዕርቃን ሰውነቷን ሲያይ በህይወቱ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደተመለከታት ሁሉ ድንዝዝ በሚያደርግ ስሜት ተውጦ የፈጠጡ ዓይኖቹን እንደተከለባት ለደቂቃዎች ቆመ…፡፡ እሷን ግን ከበዳት፤ ለማታውቀው መንገደኛ ሰው ዕርቃን ሰውነቷን ያሰጣች መሰላት..የተቀሰሩት ጡቶቿን በእጆቿ ሸፈነቻቸው፡፡

‹‹ዬሲ መጣሁ አልኩህ እኮ..!! ሳሎን ጠብቀኝ››ሳታስበው እንደመቆጣት አለች፡፡

‹‹ሶሪ.…››አለና ከደነዘዘበት በመከራ ነቅቶ በራፉን ዘጋላትና በፍቅረኛው ያልተለመደ ሁኔታ ግራ እየተጋባ ወደ ሳሎን ተመለሰ..በፊት ቢሆን ጎትታ ነበር ወደ ውስጥ ምታስገባው.፡፡

.‹‹አይ ጥሩ ስሜት ላይ ስላልሆነች ይሆናል፡፡››ሲል እራሱን አፅናና፡፡

ሁሉን ነገር ጨርሳ ቢጃማዋን ለብሳ ሳሎን ስትመለስ...ሰራተኛዋ ሲኒ ደርድራ ቡና እየቆላች ነበር፡፡ ዬሴፍ ደግሞ እንደበፊቱ ሶፋው ላይ ጋደም ብሎ ቢራውን ይጐነጫል፡፡

‹‹ቤቢ መጣሽ..?›› አለት..ዩሴፍ በፊት

ከኢትጵያ ወደ አሜሪካ ሄዶ ከሶፊያ ጋር በተገናኙ እና ፍቅር በጀመሩበት ጊዜ ‹እናት› ብሎ ነበር የሚጠራት ...እናቴን ትመስያለሽ ለማለት..ከዓመታት በኃላ ግን አገሩን ሲላመድ እና የፈረንጆቹ ባህሪ ሲጋባበት..እናትን እረሳውና በቤቢ ቀየረው…ምሁራዊ የባህል ዕድገት …፡፡

‹‹አዎ ፡፡ >>አለችውና ከእሱ ፈንጠር ብላ ተቀመጠች፡፡

‹‹ቢራ ይከፈትልሽ ቤብ?››

‹‹አይ ይቅርብኝ ..ቡና ነው ያሰኘኝ፡፡››

‹‹እራት ቀርቦ በልተው የተፈላውን ቡና ጠጥተው አጠናቀቁና ተያይዘው ወደ መኝታ ቤት ገቡ፡፡ዮሴፍ ለ7 ወራት ያላገኘው ... በጣም የናፈቀውን ገላ ዳግም የሚያጣጥምበት ሰከንድ መቅረቡን ሲያስብ ውስጡ በደስታ ተጥለቀለቀ….የሰውነቱ ግለትም ለራሱ ተሰማው፡፡ከሁሉም በፊት ግን ያመጣላትን ስጦታ ሊያበረከትላት ፈለገ ፡፡
መኝታ ቤት አስገብቶ ካስቀመጣቸው 3 ሻንጣዎች ውስጥ ግዙፉን ሻንጣ ከፈተ‹‹ቤብ እነዚህ ልብሷች እና ጫማዎች ያንቺ ናቸው..ከግምቴ ትንሽ ወፈር ብለሽ ነው ያገኘሁሽ ስለዚህ አንዳንዶቹ ሊጠቡሽ ይችላሉ››አላት፡፡

ደስ እንዲለው ለቁጥር ከሚያዳግቱ ልብሶች መካከል አንድ ሶስቱን አንሳችና እንደነገሩ ሞከረች..ግን ውስጧን ደስ አላለውም... ‹ከሚያስፈልግሽ በላይ መሰብሰብ ስግብግብነት ነው፤፤››የሚለው የሰላም ንግግር አእምሮዋን ወቀራት፡፡አይደለም ባላት ላይ ተጨምሮ ይቅርና አሁን ፊት ለፊቷ በሻንጣው የታጨቀው ልብስ ብቻ ለሀያ ሴቶች በደንብ ይበቃል‹‹እውነትም ስግብግብነት…፡፡››አለች ..ሳይታወቃት ድምፅ አውጥታ፡፡

‹‹አናገርሽኝ ቤቢ..?››አላት ያናገረችው መስሎት፡፡
‹‹አይ... ያምራል ማለቴ ነው..ለማኛውም ሌሎቹን ነገ ተረጋግቼ እለካቸዋለሁ... አሁን ደክሞኛል፡፡››

‹‹አንደርእስታንድ አረግሻለሁ....ግን ከመተኛታችን በፊት ሌላ አንድ ነገር ላሳይሽ እፈልጋለሁ››

‹‹ምንድነው ዬሴፍ..አሳየኝ ?›አለችው ፡፡

ሁለተኛውን ሻንጣ ከፈተ..ውስጡ ያለውን አወጣ… በጣም ደነገጠች ‹‹..ምንድነው ?››

‹‹ለሰርጋችን ቀን የምትለብሽው ..ከፓሪስ በትዕዛዝ የተሰራ ልዩ ቬሎ..፡፡››

ሰውነቷ ዝልፍልፍ አለባት.. የምትለውን የምትናገረውን አጣች፡፡ዬሴፍም ግራ ገባው..በፊቷ ላይ ያረበበው ድንጋጤ የደስታ ነው ወይስ የቅሬታ? መለየት አልቻለው…፡፡

‹‹ቤብ..ምነው? ፈዘዝሽ እኮ!!!››

‹‹ይሄንን ከማድረግህ በፊት ልታማክረኝ ይገባ ነበር..እኔና አንተ እኮ ስለፍቅር እንጂ ስለጋብቻ አውርተን አናውቅም፡፡››
👍556