አትሮኖስ
279K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
458 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ሰመመን


#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

....በማግሥቱ ጠዋት ከቀጠሮው ሰዓት ቀድሞ ጆሊ ባር የተገኘው እስክንድር ነበር። ያደረበት ቤት ስላልተስማማው
በሌሊት ነበር ሾልኮ የወጣው ። የቤቱ አለ መስማማት ብቻ ሳይሆን የሰው ዐይን ፍራቻም ነው “ አላሁ አክብር” ሳይል ያስወጣው ። የገዛ ኅሊናው ዐይን ሲያለቅስ እንባውን አድርቆ ሲልከሰከስ እያደረ ' የሌሎችን ዐይን ለምን እንደ
ሚፈራ ሁሌም ይገርመዋል ። ባደረበት ቤት አንግቶ፡ ተዝናንቶ ቆይቶ አያውቅም ።

ይህን ልምድ ከየት ይሆን የቀዳነው ? ” ሲል አሰበ በዩኒቨርስቲው ውስጥ በትምህርት ወራት ቀለም ላይ ተደፍቶ
መክረም ፡ በዕረፍት ሳምንታት ደግሞ ኪስ እስከ ተቻለ ድረስ በአልኮል ማበድና በየበረንዳው ማደር ፈሊጥ እየሆነ መምጣቱ ነበር ያሳሰበው ። በዛሬው ዕለት እንኳ እንደ እሱው የሰው ዐይን እየፈሩ ከያደሩበት በረንዳ በሌሊት እየተሾለኩ " ጸጉራቸው እንደ ተንጨፈረረ ወደ ካምፓስ ቢሮ ያያቸው ተማሪዎች ቁጥር ትንሽ አልነበረም ።

ሁኔታው በትምህርት ተጨንቆ የከረመን አዕምሮ የማዝናናት አዝማሚያ ይመስላል” ሲል ሐሳቡን ቀጠለ
“ ታዲያ ከሰው ዐይንም ; ከዛ ኅሊናም የማይሸሹበት ሌላ መዝናኛ መፍጠር አይቻልም ወይ ? ተማሪው ከተባበረ ከፈተና በኋላ ባለው የዕረፍት ጊዜ ውስጥ እንደየዓቅሙ ገንዘብ አዋጥቶ ' የሙዚቃና ሌሎች የተለያዩ ትርኢቶችን እንዲሁም አዝናኝና አነቃቂ ውድድሮችን ማዘጋጀት፥ በቡድን ሆኖ ከከተማ ወጣ እያሉ ብርቅና ድንቅ ቦታዎችን መጐብኘትና የመሳሰሉት ልምዶች ቢዳብሩ ጤናማ መዝናኛ ይሆኑ
ነበር ። ታዲያ ይህን በጐ ተግባር ለማስተባበር የግንባሩን ቦታ ማን ይውሰድ ? ?

በራሱ ሣቀና ሲጋራ ለመፈለግ ኪሱን ይደባብስ ጀምር ትላንት ማታ ሌላ፡ ዛሬ ጠዋት ሌላ መሆኑ ነው ያሣቀውም
የአንድ ሰው ሁለት ልክ ? አለ በልቡ።

ሣቁ ከፊቱ ላይ ሳይጠፋ ሳምሶን ጉልቤው ደረሰ። ፊቱን ጭፍግግ አድርጐታል • እሱነቱ አስጠልቶት ራሱን የሚጥልበት ቦታ ያጣ ሰው ይመስላል "

“ ታድያስ ? ” አለው እስክንድር ፈገግ እያል ።

ሳምሶን አፉ መናገር እንዳቃተው ሁሉ “ መቼም አልሞትኩም ! ” በማለት ዐይነት አፍንጫውን አጣሞ አንገቱን ወደ ግራ አዘነበለ እጆቹን ኪሶቹ ውስጥ እንደ
ከተተ ሊቀመጥ ሲል ሱሪው የመተርተር ድምፅ አሰማ።

“ እናትክን ! ” አለው ሱሪውን ።

ጥርሳም እንዳትለው ሱሪው ጥርስ የለው አለና እስክንድር ቀለደበት ።

ሳምሶን ፈገግም አላለም "ቢኮረኩሩትም የሚሥቅ አይመስልም

“ ምነው ደበረህ ?” አለው እስክንድር ሣቁን እየዋጠ ።
“ ምን እባክህ ነጭ ናጫ ሴት ነች የገጠመችኝ፡እንዲሁ ስንበጣበጥ ነው ያደርነው "

አይዞህ አንድ ነን ። እኔም ቀዝቃዛ አሮጌት ይዤ ነው ያደርኩት መጠጥ ምን የማይሠራው አለ? ብቻ አትፍረድባቸው ። የእንጀራ ጉዳይ ሆኖባቸው ነው እንጂ ሰልችቶቸዋል "

“ ጥርሳሞች ! ” አላቸው ሳምሶን በልቡ ። ከእስክንድር ጋር መከራከርም መጫወትም አልፈለገም ። መላ ሰውነቱ
ደክሞአል " ለመፍታታት ያህል እንኳ የጠዋት ስፖርት አልሠራም። ሕይወትን የመሰላቸት ስሜት ተሰማው ፡ ፊቱን
በመስታወት ባያየውም በስሜቱ ጠውልጎ ታየው ። የጠጣበትን ቡና ቤት ያጠጣውን ገንዘብና አብሯት ያደረችውን ሴት በልቡ እየረገመ ጠረጴዛውን በቡጢ ደበደበ "

“አቤት!ምን ልታዘዝ?” ሲልአሳላፊው ከተፍ አለ ።
"አንድ ጠርውስ ቀዝቃዛ አምቦ ውሃ ”
“ አዎ ጎሽ ፡ የተቃጠለ አንጀት ለማራስ” አለ እስክንድር ተደርቦ ።

አምቦ ውሃው ቀርቦላቸው እየጠጡ በመጫወት ላይ ሳሉ አቤልን በውጭው መስተዋት በኩል አዩት። ከኋላው
የሚያባርሩትን ያህል በፍጥነት ነበር ወደ እነሱ የሚገሰግሰው ። የእስክንድርና የሳምሶን የተደበረ ስሜት አቤልን
ሲያዩ ተነቃቃ ። ወሬውን ለመስማት አጠገባቸው እስኪደርስ ተቻኮሉ። እሱም ከውጭ ሲያያቸው ዐይናቸውን አፍሮ
በሆዱ አቀርቅሮ ነበር የተጠጋቸው» ማታ በቅዠት መልክ የሰማውን “ ብር አምባር ሰበረልዎ ” አሁን ለቱ ሰበውን የሚሉት መሰስው ።

“ እህሳ ? ሌሊቱ እንዴት ነበር ? ” አለው ሳምሶን' ቀድሞ ሊጨብጠው እጁን እየዘረጋ።

ጥሩ ነበር” አለ አቤል ሁለቱንም ከጨበጣቸው በኋላ ጠርሙሱ ውስጥ የተረፈውን አምቦ ውሃ በብርጭቆ
እየቀዳ ። ጠጥቶ እንደ ጨረሰ በእርካታ ተንፍሶ፡ “እንሒድ እባካችሁ ” አላቸው ።

"ቁጭ በልና ተጫወት እንጂ ” አለው ሳምሶን ለወሬው ጓጉቶ ። አቤል ግን መቀመጥ አልፈለገም ። ወደ ካምፓስ ለመሔድ ቸኩሎአል ። በዩኒቨርስቲም ግቢ ውስጥ አንዳች ነገር ጥሎ ያደረ ይመስል ልቡ ተሰቅሎአል ። እስክንድርም ይህን ስሜቱን ስለ ተረዳለት ለመሔድ ተነሣ።

ወደ ስድስት ኪሎ ሲጓዙም ሳምሶን ከእቤል የመስማት “ጥማቱ እንደ ቀጠለ ነበር ። በዝምታ ትንሽ እንደ ተራመዱ "

“ ታዲያስ ፡ እንዴት ነበር ? ” ሲል ይጠይቀዋል የሴት ተግባሩን አስጐልጉሎ ለማናዘዝ በሚጥር ጥልቅ ስሜት ።

“ ደኅና ነበር ይላል አቤል ነገሩን ቸል ብሎ ለማሳጠር በሚጥር ስሜት ። ሳምሶን በዚህ መልስ አይረካም

"ብርቅነሽ እንዴት ነች ? ” ሲል ደግሞ ሊያወጣጣ ይሞክራል ።

“ ብርቅነሽ ጥሩ ሴት ነች” ሲል አቤል ነገሩን በአጭሩ ይደመድመዋል ።

አቤል ከብርቅነሽ ጋር ምን ዐይነት የመጀመሪያ ሌሊት እንዳሳለፈ ለመስማት ሳምሶን ብቻ ሳይሆን እስክንድርም
ጓጉቶ ነበር ። የብርቅነሽ ጥሬነት ፡ ግልጽነትና ጣፋጭነት ሳያስቡት በሁሉም ልብ ውስጥ ግልጽ ያልሆነ የፍቅር
ስሜት አሳድሮባቸው ነበር። ያም ሆነ ይህ፡ አቤል እንደ ጠበቁት በሰፊው የሚያወራላቸው አልሆነም ። ጓደኛሞች እንዲህ ዐይነት ሌሊት አሳልፈው ጠዋት ሲገናኙ ስለ አዳራቸው ሁኔታ ወይም አብረዋት ስላደሩት ሴት ማውራት
የተለመደ ቢሆንም ፥ ለአቤል እንግዳ ነገር ነበር ። ስለ አዳሩ እንዳይናዘዝ የፍረትና የቁጥብነት ስሜት ኅሊናውን
ጨምድዶ ያዘው ።

ብርቅነሽ የትዕግሥትን ቦታ ባትወስድም በአቤል ልብ ውስጥ የተወሰነ ዳርቻ ይዛ ነው ያደረችው ። ለወሲብ የመጀመሪያ ሴቱ በመሆንዋ ብቻም አይደለም ። እስዋም ራስዋ ሁኔታውን በማየትና ሳምሶን የነገራትን በማገናዘብ
ለአቤል ቀና ስሜት ስለ ነበራት በባነነ ቁጥር አብራው ስትባንን ነው ያደረችው ። የልቧን አጫውታው የልቡን ምስጢር ወስዳለች ። ግልጽነቷና ፍቅራዊ መስተንግዶዋ አስገድዶት አቤልም ስለ ትዕግሥት ሲያጫውታት ነው ያደረው።
የትዕግሥትን ጉዳይ ለብርቅነሽ ግልጽ ማውጣቴ የቆረቆረው ጠዋት ከተለያት በኋላ ነው ። በግትርነት ተወጥሮ የነበረው መንፈሱ እየላላ መምጣቱ ለራሱም ተሰማው ። ምስጥሬ ብሎ ደብቆ የያዘውን የትዕግሥትን ነገር በመጀመሪያ ለሐኪሙ ፡ በትላንቱ ምሽት በመጠጥ ኃይል ለእስክንድር ሌሊቱን ደግሞ ለብርቅነሽ መናዘዙን ሲያስታውስ የመንፈሱ መላላት ታወቀው ።

ሳምሶንም ሆነ እስክንድር የጓጉትን ያህል ሳያወራቸው ከዩኒቨርስቲው በር ደረሱ ። ግቢው ጭር ብሎአል ።ለወትሮው ቢሆን ይህ ሰዓት ወደ ትምህርት ክፍል መግቢያ ጊዜ በመሆኑ መራወጥ ይታይበት ነበር።ዛሬ ግን ገና ከእንቅልፉ ያልተነሣም ኘለ ። የሚነቃነቅ ተማሪ አይታይም ።

እነ አቤል ግቢ ውስጥ ከገቡ በኋላ፥ወደ መኝታ ቤታቹኑ የሚወስደውን ጠምዛዛ መንገድ ሲይዙ አራት ልጃገረዶች
ከሩቅ ተመለከቱ ። ልጃገረዶቹ ሻንጣ ሻንጣቸውን ይዘው ከግቢው በመውጣት ላይ ነበሩ ። ሦስቱ፡ ልጃገረዶች እነማን
እንደሆኑ ሦስቱም ወንዶች ከመቅጽበት ለዩኣቸው ትዕግሥት፡ ማርታና ቤተልሔም ነበሩ ። ሁሉም ያላወቋት አንዷ ልጃገረድ የቤቴልሔም የመኝታ ክፍል ጓደኛ ነበረች
አቤል ደነገጠ
👍1
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት


#ድርሰት_በትክክል_ገና


#ከሁለት_ወራት_በኋላ

እንደሻው በቀለንና ራሷን በጥይት አቁስላ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ውስጥ ህክምናዋን ስትከታተል ከቆየች በኋላ በሁለተኛው ወሯ ሙሉ ለሙሉ ዳነች፡፡
በዚያ ጥይት ምክንያት ከላይኛው መንጋጋ ጥርሶቿ ላይ ሁለቱን አጥታለች፡፡ የግራ ጆሮዋ በመስማት በኩል ትንሽ ቅር ቢለውም ሙሉ ለሙሉ አልደነቆረም፡፡
ጥይቶቹ በተከታታይ ሾልከው የወጡበት ቀዳዳ መጠነኛ ጠባሳን ጥሉባት አለፈ እንጂ፤ ውበቷን እምብዛም የሚፈታተነው አልነበረም፡፡
ከዚህ ሁሉ ሥቃይ በኋላ ግን እቤቷ ገብታ አላረፈችም፡፡ ወንጀለኛ ናትና በቀጥታ በማረፊያ ቤት እንድትቆይ ተደረገ፡፡
የወንጀል ክሱ በዐቃቤ ህግ ከሳሽነት ለከፍተኛው ፍርድ ቤት ቀረበ፡፡
ከሳሽ ዐቃቤ ህግ ተከሳሽ ወይዘሪት ትህትና ድንበሩ የክሱ ምክንያት ሰው የመግደል ሙከራ ወንጀል ዐቃቤ ህጉ ተከሳሽ ሆን ብላ ተዘጋጅታ ወጣት እንደሻው በቀለ ከሚሰራበት የንግድ ሱቅ ድረስ በመሄድ በአራት ጥይቶች ያቆሰለችው መሆኑንና እራሷንም ለመግደል ሙከራ ማድረጓን ከገለፀ በኋላ፤ የወንጀለኛ መቅጫ ህግና አንቀጽ ጠቅሶ አስፈላጊው ቅጣት እንዲወሰንባት
የተመሰረተ ክስ መሆኑን በማተት አቀረበ፡፡
ትህትና ድንበሩ ተከሳሽ ሆና ለመጀመሪያ ጊዜ ፍርድ ቤት በቀረበችበት ዕለት፤ ታናሽ ወንድሟ በችሎቱ ላይ በመገኘት ክሱን
አብሯት አዳመጠ፡፡
ፍርድ ቤቱ ለተከሳሽ የሚከተለውን ጥያቄ አቀረበላት፡፡
ስምሽ?”
“ትህትና ድንበሩ”
“ዕድሜሽ?”
"አሥራ ሰባት ዓመት”
“አድራሻ?”
“አዲስ አበባ
“ሥራሽ?”
“ሥራ ፈላጊ”
“ወላጆችሽ በህይወት አሉ?”
“አባቴ ሞቷል እናቴም የአልጋ ቁራኛ ነች”
ይህንንና መሰል ጥያቄዎችን ከተጠየቀች በኋላ “የክሱ ቻርጅ ደርሶሻል?” የሚል ጥያቄ ቀረበላት፡፡
“አዎን ደርሶኛል”
ከዚያም የመሐል ዳኛው መነጽራቸውን ዝቅ አድርገው በግንባራቸው ዐይዋትና........
“ወይዘሪት ትህትና ለተመስረተብሽ ክስ እራስሽ ትከራከሪያለሽ ወይስ?
ጠበቃ ታቆሚያለሽ?” የሚል ጥያቄ አቀረቡላት፡፡
ቀስ ብላ ሻምበል ብሩክን አየችው፡፡ የመከራትን አስታወሰች፡፡
“ድሃ ስለሆንኩ መንግስት ጠበቃ ያቁምልኝ?” የሚል መልስ ሰጠች፡፡
ይህንን መልስ ስትሰጥ በተቻላት መጠን ድምጿ እንዲሰማ ጮክ ብላ ነበር፡፡
ፍርድ ቤቱ በጥብቅና ሙያው የታወቀው አቶ ምንውዬለት ተዘራ ለተከሳሽ ጠበቃ እንዲሆንላት ትዕዛዝ ሰጠ፡፡ አቶ ምንውዬለትም ትእዛዙን በደስታ ተቀበለ፡፡
ይህ ከሆነ በኋላ ተከሳሽ የተከሰሰችበት ወንጀል በንባብ እንዲሰማ ተደረገ፡፡
“በተመሰረተብሽ ወንጀል ጥፋተኛ ነሽ አይደለሽም?” ተብላ ተጠየቀች፡፡
በዚህ ጊዜ ጠበቃው አቶ ምንውዬለት ጥቁር ካባውን እንደለበሰ
ብድግ ብሎ ቆመ፡፡
“ጥፋተኛ አይደለችም ክቡር ፍርድ ቤቱ” ሲል መልስ ሰጠ፡፡ ዳኛው መልሱን ከመዘገቡ በኋላ፤ ጠበቃው “ክቡር ፍርድ ቤቱ ተከሳሽ የዋስ መብቷ ተጠብቆ እንድትከራከር ይፍቀድልኝ” ሲል ጥያቄ አቀረበ፡፡
ፍርድ ቤቱ ግን ጥያቄውን ውድቅ በማድረግ፤ ተከሳሽ በማረፊያ
ቤት ቆይታ እንድትከራከር በመወሰንና፤ ዐቃቤ ህጉ አሉኝ የሚላቸውን ማስረጃዎች እንዲያቀርብ ቀጠሮ በመስጠት ችሎቱ አበቃ፡፡
ትህትና እዚያ የተከሳሽ ሳጥን ውስጥ
ቆማ ስትቁለጨለጭ፣እንዳንድ ጊዜ በፍርሃት ተውጣ ሰውነቷ ሲንቀጠቀጥ፣
ድምጿ ሲርገበገብ፣ ሲያልባት፡ እያየች አዜብ እንባ እየተናነቃት ነበር፡፡ ሆኖም አልቅሳ ልትረብሻት አልፈለገችም፡፡ ይልቁንም ሳቅ ፈገግ እያለች ሞራል ልትሰጣት ሞከረች፡፡
እውነትም እንደዚያ ሰውነቷ በፍርሃት ሲሸበርባት፣ ልቧ ድው ድው ሲል፣ ሻምበል ብሩክን፣ ወንድሟንና አዜብን ቀስ ብላ ታያቸዋለች፡፡ እነሱ ፈገግ ይሉና በ“አይዞሽ” ምልክት ሲያበረታቷት “አይዞኝ” በሚል ስሜት እራሷን ስታጠናክር ከቆየች በኋላ ችሎቱ ሲያበቃ በአጃቢ ፓላስ ታጅባ ወጣች፡፡
ከዚያም በአንዱአለም ጠያቂነት አብረው ምሣ ይበሉ ዘንድ ሻምበል ብሩክ አጃቢ ፓሊሱን አነጋገረውና አብረው ምሣ ለመብላት ፈቃድ ስለ አገኙ ፤ እዚያው አካባቢ በሚገኝ ወደ አንድ ሆቴል ገቡ፡፡
አንዱአለም የዛሬውን ምሣ ለመጋበዝ የፈለገበት ምክንያት ነበረው፡፡ የሚፈለገው ምግብና መጠጥ ታዘዘ፡፡
ከባህር ኃይሉ የተሰጠው የኪስ ገንዘብ ስለነበረው ምሣ የጋበዘው እሱ ነበር፡፡ አንዱአለምን ብሎ ጋባዥ በመገኘቱ እየተሳሳቁ፣እየተጨዋወቱ፣ ግብዣውን በደስታ ተቀበሉት፡፡ አጃቢ ፓሊሱ በሻምበል ብሩክ ላይ እምነት ስለጣላ እስረኛዋ ታመልጣላች የሚል ሥጋት አላደረበትም፡፡ እንደዚሁ እየተጨዋወቱ ከቆዩ በኋላ.......
“አንድ ጊዜ” አለና አንዱአለም ትንፋሹን ሰብሰብ፣ ምራቁን ዋጥ አደረገ፡፡
አራቱም በፀጥታ ይመለከቱት ጀመር፡፡ ከወትሮው ለየት ያለ ስሜት ይታይበታል፡፡ እነሱ ከተቀመጡበት አካባቢ ትንሽ ራቅ ብለው በርከት ያሉ እየተጨዋወቱ የሚሳሳቁ ሰዎች ድምጽ ብቻ ይሰማል፡፡
“ይህቺ የምሣ ግብዣ በአንድ በኩል እታለም ለመጀመሪያ ጊዜ
ፍርድ ቤት በቀረበችበት ቀን ተገኝቼ እውነተኛ ፍትህን አግኝታ በነፃ
እንድትለቀቅ መልካም ምኞቴን የምገልጽበት ሲሆን፤ በሌላ በኩል ደግሞ
ለራሴ መሸኛ በማድረግ በግል ውሣኔዬ መሠረት ለነገው ጉዞዬ መቃናት
እንድትመርቁኝና፤ የወጪ እንድላችሁ በማሰብ የተደረገች ግብዣ ነች”
አለ፡፡ ስለምን እንደሚያወራ ቶሎ ማወቅ አልቻሉም :: “የምን ጉዞ? የምን መሸኛ?. “ምንድነው የምትለው አንዱዬ?” በድንጋጤና በጥርጣሬ ተውጣ አዜብ ጠየቀችው፡፡ “ ሁሉንም ቅድመ ዝግጅት አጠናቅቄአለሁ፡፡
ከአንድ ሣምንት በፊት በኢትዮጵያ ባህር ኃይል ውስጥ ተቀጥሬ ለስልጠና
መሄዱ ነው” ሲል ቁርጡን ነገራቸው፡፡ በዚያ ጨዋታ መካከል ይህንን መርዶ አምጥቶ ሲጥልባቸው ልባቸው ክፉኛ አዘነ፡፡ በተለይ ትህትና የተሰማትን ስሜት መግለጽ ያስቸግራል፡፡ ጭውው አለባት፡፡ ግማሽ አካሏ፣ የምትወደው ታናሽ ወንድሟ ምንም እንኳን እስረኛ ብትሆንም በየጊዜው እየመጣላት ዐይኖቹን ስታየው
የምትጽናናበት አለኝታዋ ነበር፤ በሁኔታው መሪር ሀዘን ተሰምቷት አለቀሰች፡፡
አዜብም እንደዚያው፡ ሻምበል ብሩክም ክፉኛ ነበር የደነገጠው፡፡
ይህ ትንሽ ልጅ የዚህ ዐይነት ከባድ ውሣኔ ላይ ይደርሳል ብሎ ጭራሽ አልገመተም ነበር፡፡ የሱ ፍላጐት አንዱአለም በትምህርቱ ጠንክሮ ዩኒቨርስቲ
እንዲገባ እንጂ እንደዚህ በመሀሉ አቋርጦ ወደ ጦር ሜዳ እንዲሄድ አልነበረም፡፡ ከረጅም ፀጥታ በኋላ......
“እንደሱ ይሻላል አልክ አንዱአለም?” አለው ሻምበል በትካዜ አንደበት።
ትህትና እና አዜብ በእንባ ይንፈቀፈቃሉ፡፡ አጃቢ ፓሊሱ ግራ ተጋብቶ ሁሉንም በዐይኑ ይቃኛል፡፡
“በቃ ብንሄድስ” የሚል ፍላጉት አድሮበታል፡፡ ሞትም ቢሆን በተሰማበት ቅጽበት በድንጋጤ ያደርቃል እንጂ፤ ቀስ በቀስ መለመዱ አይቀርምና፤
ውስጥ ውስጡን እየተቃጠሉ፤ እንባቸውን እየጠራረጉ፤ዐይን፤ ዐይኑን፧ ይመለከቱት ጀመር፡፡ ውሣኔው የፀና፣ ጉዳዩ ያበቃለት መሆኑን ቁርጥ አድርጉ ነገራቸው፡፡
እስከዛሬ ድረስ የቆየው እህቱ ፍርድ ቤት ስትቆምና የተከሰሰችበት ወንጀል ሲሰማ አብሯት ለመገኘት ፍቃድ በመውሰድ መሆኑን፣ ነገ በጠዋት በዋናው መሥሪያ ቤት ተገኝቶ ወደ ማሰልጠኛው ጉዞ የሚጀምርከ መሆኑን፣ለሻምበል ሲያስረዳው ለትህትና እና ለአዜብ ደግሞ የመርዶ ያህል ካረዳቸው በኋላ በአጃቢ ፓሊሱ አሳሳቢነት ተነስተው ወጡ፡፡
“እሺ አሥር አለቃ ስለተባበርከኝ በጣም ነው የማመሰግንህ አለው ሻምበል የአጃቢ ፓሊሱን ትከሻ ቸብ ቸብ እያደረገ፡፡
“እሺ ጌታዬ አኔም የርስዎ ነገር ሆኖብኝ እንጂ፤ ህግ መጋፋቴን አልዘነጋሁትም” አሥር አለቃ ጥላዬ እግረ መንገዱን ውለታውን
👍1
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ

"ከየት ነው ?" አለች ሴትየዋ በመገረም ቃና።

“ከዚሁ ነው ከድሬዳዋ እባኳት አንዴ ቢያገናኙኝ፡፡” ልቡ ተንጠለጠለ፡፡

“ይቅርታ ተሳስተዋል::” አለች ሴትየዋ ለመናገር ያልፈለገችው ነገር እንዳለ ሁሉ እያቅማማች፡፡
“ቆይ፤ ቆይ!” አለ ስልኩን እንዳትዘጋበት ተሽቀዳድሞ፡፡ የስልክ ቁጥሩን በእርጋታ እየጠራ ትክክል መሆኑን ጠየቃት፡፡

“ቁጥሩ ትክክል ነው:: ግን…” አቅማማችበት፡፡
“አቶ ይልማ የሉም? ” ጭንቅላቱ በጭንቀት ተወጠረ፡፡
“እንደዛ የሚባል ሰው የለም::” ስልኩን ጆሮው ላይ ዘጋችበት፡፡

ሊሆን አይችልም! ነገሩ ሁሉ ተደበላለቀበት፡፡ የስልኩን መነጋገሪያ
ከቦታው መልሶ ወደ ወንበሩ ተመለሰ፡፡ አለቀ፡፡ ካልቨርትን ለማግኘት የነበረው ተስፋ : ከእጅ ያመለጠ እንቁላል ሆነበት፡፡ ህ!… አስራ ሶስት ብር ይዞ ሽሽት ታየው:: አስራ ሶስት ብር ወደ አዲስ አበባ ለመመለስ እንኳን በቂ አይደለም፡፡ ምንም ምርጫ የለውም! መስረቅ ካለበት ይስቃል! ማጅራት መምታት ካለበት ይመታል ግን አዲስ አበባ አይመለስም! ካልቨርት ያለው እዚህ ነው፡፡ የምሥራች ነግራዋለች፡፡ ካልቨርት ድሬዳዋ ነው! ካልቨርት አፍንጫው ስር ነው!” ጠረጴዛውን በቡጢ ደወለው፡፡

በቡና ቤቱ አዳራሽ የተቀመጡ ሰዎች ጠረጴዛውን ሲጠልዘው ሲሰሙ ቀና ቀና አያሉ እየተገላመጡ ያዩት ጀመር፡፡በዛ ድርጊቱ ተደናገጠ፡፡
ጥንቃቄ!…. መረጋጋት! መረጋጋት! ሻዩን አንስቶ ፉት አለው፡፡ ቀዝቅዟል፡፡ አልተወውም፡: በእርጋታ ደጋግም ፉት እያለ ጨረሰው፡፡ ቢደግም አይጠላም
ነበር፡፡ ኪሱ ውስጥ ያለውን ገንዘብ ሲያስታውሰው ተወው፡፡

በተቀመጠበት ዓይኖቹን ባዘዝ አድርጎ አእምሮውን ለማስራት ሞከረ
…ካልቨርት የት ነው?- «እማዪጋ ድሬዳዋ…እማዬ…የአቶ ይልማ ገዛኸኝ
ባለቤት… ኣቶ ይልማ ገዛኸኝ .. ይልማ ይልማ ምንድን ነበር ያለችው ስልኩን ያነሳችው ሴት ይልማ ምን? …ይልማ ጋራዥ… ጋራዥ…

የቡና ቤቱን አስተናጋጅ ጠቀሳት፡፡መጣች።

“እባክሽ የኔ ቆንጆ ይልማ ጋራዥ የሚባል ታውቂያለሽ ድሬዳዋ ውስጥ? ” የአንድ ጋራዥ ስም ጠርቶ ውለዱ ሲል እራሱን አስገረመው፡፡

“ይልማ…ይልማ…እንትንጋ ነው… ማነው? ...በቃ ከአሸዋ ሜዳ ከድልድዩ ሳይደርሱ ወዲህ ከባንኩ ትንሽ አለፍ እንዳሉ…” የማያውቀውን ከተማ ትተርክለት ጀመር፡፡

“እይው...” አለ ድምፁን አለዝቦ አቋረጣት፡ “ለድሬዳዋ አዲስ
ስለሆንኩ ነው::”

“የሚያሳይዎት ልጅ ልጥራሉት? ቅርብ ነው::” አለች፡፡
“ጥሩ ጥሩ፡፡” ጭንቅላቱን እየወዘወዘ መስማማቱን ገለፀላት፡፡

ጋራዡን ከሚያሳየው ልጅ ጋር ካገኘችው በኋላ በደረቅ ምሥጋና ተሰናብቷት ከልጁ ጋር ተፈተለከ፡፡ ጉርሻ ቢሰጣት ደስ ባለው ነበር… ግን...፡፡

“ይልማ ጋራዥ ነው አይደል? ኑ” ይለዋል ከፊት ለፊቱ ቱስ ቱስ የሚለው ህፃን ልጅ፡፡ ዕድሜው ከአስር አመት አይበልጥም፡፡ ያደረጋት የላስቲክ ነጠላ ጫማ ተበጣጥሳለች፡፡ በተራመደ ቁጥር ወደ ኋላ ልትቀር ታስባለች፡፡ ልጁ ግን ትቷት ሊሄድ ፈቃደኛ አይመስልም፡፡ በእግሮቹ ጣቶች ቆንጠጥ አድርጎ ይዞ ወደፊት ይጎትታታል፡፡ ትንሽ ይሄድና “…ይልማ
ጋራዥ ነው አይደል? ኑ” ይለዋል፡፡

ናትናኤል ላቡ በጆርባው እየተንቆረቆረ ከልጁ ኋላኋላ ይጣደፋል፡፡

“ያው! ይሄ ነው ይልማ ጋራዥ:: ሜካኒኮቹን ልጥራሎት?” አለ ልጁ ተስፋ ያደረገውን ጉርሻ በሆዱ ይዞ መስተንግዶውን እያጧጧፈ፡፡

“አይ ተወው፡፡” አለ ናትናኤል ከኪሱ አስር ሳንቲም አውጥቶ ለልጁ
እየዘረጋለት::

አቦ ይጨምሩ! ከለገሃሬ ድረስ አምጥተውኝ” አለ ልጁ አስር
ሳንቲሟን ሲያይ ፊቱ በቅያሜ ተንጠልጥሎ፡፡

“ሌላ ጊዜ እሰጥሃለሁ፡፡” ኣለ ናትናኤል አስር ሳንቲሟን ገፋ አድርጎ፡፡

“እስር አልወስድም!” አለ ልጁ በብስጭት::

ናትናኤል አልተግደረደረም ሳንቲሟን ኪሱ ከቶ ወደ ጋራዡ በር ተጣደፈ፡፡ልጁ ከጀርባው እናቱን ተሳድቦ ሲሮጥ ሰማው። ግድ አልበረውም፡፡ የጋራዡ ግቢ ስፋት ያለው ቢሆንም ከውስጥ የተሰገሰጉት በርካታ መኪናዎች ጠባብ አስመስለውታል፡፡ ደማቅ ሰማያዊ ቱታ የለበሱ የጋራዥ ሠራተኞች ኮፈናቸው በተበረገዱ መኪናዎች ዙሪያ ተፍ ተፍ ይላሉ።

· “የት ነው?” አሉት ከበሩ ጥግ በተደራረቡ ድንጋዮች ላይ የተቀመ
ጡት ሽበት ያሸፈናቸው ዘበኛ ከተቀመጡበት ወገባቸውን ይዘው እየተነሱ፡፡የከንፈሮቻቸውን ጥግና ጥግ በጎረሱት ጫት አረንጓዴ ሆኗል፡፡

“እንደምን ዋሉ.…አቶ ይልማን ነበር፡፡” አላቸወ ጠጋ ብሎ::

ሰውየው ግራ በመጋባት መልክ ትክ ብለው ተመለከቱት፡፡ መልስ አልሰጡም ብቻ እብድ እንደሆነ ሁሉ አፍጥጠው አዩት::

“እ..ቀጠለ“ልጃቸው ከአዲስ አበባ ልካኝ ነው፡፡ ይኖሩ ይሆን?”

“አቶ አደፍርስ ማለትህ ነው?” አሉ ሽማግሌው የፀሃይዋን ጨረር
በመዳፋቸው ከልለው::

“አይ አቶ ይልማን ነው::”
ሰውየው ጤነኛ እንዳልሆነ ጭንቅላታቸውን ነቀነቁበት፡፡

“የአቶ ይልማ ጋራዥ አይደል እንዶ ይሄ?” አለ ናትናኤል ተስፋው እየተሟጠጠ፡፡

“ክፉው ሞት ሳይወስዳቸው በፊት አዎ፡፡" አሉት ሰውየው ተመልሰው በተደራረቡት ድንጋዮች ላይ እየተቀመጡ፡፡

“ምን አሉኝ?” አለ ደንገጥ ብሎ፡፡
“የኔ ወንድም አቶ ይልማ ከሞቱ መጪው ህዳር ሁለተኛ ዓመታቸዉ ነው::” አሉት ሽማግሌው ከጎናቸው በኮካኮላ ጠርሙስ ካስቀመጡት ውሃ እየተጎነጩ፡፡

ናትናኤል ለጥቂት ደቂቃዎች ፈዞ ቆየ፡፡

“እባኮት ባለቤታቸው የሚኖሩበትን ያውቁ ይሆን?”

ሽማግሌው ችላ ብለውት በዝምታ ጭንቅላታቸውን ነቀነቁበት፡፡
ወሬው የጣማቸው አይመስልም፡፡

“እባኮት ስለባለቤታቸው የሚያውቅ ሰው ካለ ላስቸግርዎት...”ናትናኤል የሽማግሌውን ፊት ሲመለከት ቶሎ ኪሱ ገባና ሁለት ብር መዞ ተመለሰ፡፡

“እስቲ ግባና ባለቤትየውን አነጋግር፡፡ ወንድም ናቸው::” አሉት ሽማግሌው ዘበኛ ሁለት ብራቸውን ኪሳቸው እየጨመሩ።

“የማን ወንድም? ”
“የአቶ ይልማ ወንድም::አቶ ኣደፍርስ ብለህ ጠይቅ::
ናትናኤል ሹማግሌውን አመስግኖ ወደ ውስጥ ገባ፡፡
“ይቅርታ ወንድም አቶ አደፍርስን ፈልጌ ነበር፡፡” አንዱን የጋራዥ ሰራተኛ አስቁሞ ጠየቀው::

“እኛውልህ፡፡” አለው በዘይት የተጨማለቀ እጁን ዘርግቶ እያመለከተው::

ናትናኤል ወደ ሰውየው አመራ ተጠግቶ በአክብሮት ሠላምታ ሰጣቸው፡፡ በጣም አጭርና ሆዳቸው ወደፊት የገፋ ናቸው፡፡ ሙልጭ ካለው መላጣቸው ጎንና ጎን ከጆሮዎቻቸው በላይ ቡፍ ቡፍ ያሉ ጥቂት የማቆጠሩ የፀጉር ብናኞች ይታያሉ፡፡ የጋራዥ ባለቤት ሳይሆን የሆቴል ወጥቤት ኃላፊ ነው የሚመስሉት::

“እንደምን ዋሉ፡፡ እባኮት ላስቸግርዎት፡፡ ከአዲስ አበባ ነው የመጣሁት።”

“አላህ ይስጥህ አላህ ይስጥህ!” በሚያስገመግም ድምፅ ጮሁና
እጃቸውን እያወናጨፉ ፊታቸውን አዞሩበት፡፡

“አይደለም ጌታዬ፡፡ ለእርዳታ አይደለም፡፡ መልዕክት ይዤ ነው የመጣሁት፡፡”

“የምን መልዕክት?” በዚያው ሃይለኛ ድምፃቸው ጠየቁት ፊታቸውን
ከስክሰው::

“የምሥራች ነበረች የላከችኝ እናቷጋ፡፡ጽፋ የሰጠችኝ ኣድራሻ ጠፋብኝና የአባቷን ስም አውቀው ስለነበረ ማዞሪያ ስጠይቅ የእርስዎን አድራሻ ሰጡኝ፡፡”

“አንተ ግም፣ ያችን መኪና ፍታት አላልኩም? ጥሩ አውደልድል
ሳምንት ይድረስና ከጎንህ ታገኘዋለህ! ” ሰውየው ተቆጥተው ሲጮሁ የጋራዥ
ሠራተኞች ሁሉ ጭልፊት እንዳዩ ጫጩቶች በየስርቻው አንገታቸውን
ይቀብራሉ፡፡ “የማነች የምሥራች?” አሉት ድንገት በቁጣ የተለዋወጠ ፊታቸው ወደ ናትናኤል መልሰው፡፡

“የአቶ ይልማ ልጅየምሥራች ይልማ፡፡”
ለመጀመሪያ ጊዜ ሰውየው ረጋ ብለው አትኩረው
2👍1
#የፍቅር_ሰመመን


#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት


#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን


#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው


ኒኪ ከዊሊያምስ ቢሮ ወጥታ ጥቂት መቶ ሜትሮችን መኪናዋን ካሽከረከረች በኋላ ከኋላዋ ብልጭ ብልጭ የሚል የመኪና መብራትን የሚያሳያት መኪና እንዳለ ለማየት ቻለች፡፡ ያው የሎስ አንጀለስ መንገድ የተጨናነቀ ስለሆነ ምናልባትም የቀደመችው ሹፌር ንዴቱን ለማሳየት
በመብራት እየሰደባት እንደሆነ በመገመት ላይ እያለች ግን የፖሊስ ሳይረን
ድምጽ ስለሰማች መኪናዋን ጥግ አስይዛ ከመንገዱ ዳር በንዴት አቆመች እና
መስታወቱን ዝቅ አድርጋ “ፖሊስ ምን ያጠፋሁት ነገር አለ... እንዴ! አንተ
ነህ እንዴ?” አለችው በመስኮቱ ስር ቀና ብላ ከመኪናዋ በር አጠገብ የቆመውን መርማሪ ፖሊስ ጉድማንን ስትመለከት፡፡ የጉድማን ቆንጆ ፊትም በፈገግታ እንደ በራ “ከዴሪክ ዊሊያምስ ቢሮ ወጥተሽ መንገድ ከጀመርሽ ጀምሮ እንድታይኝ ያላደረግኩት ጥረት አልነበረም፡፡”

ኒኪም በስጨት ብላ “ስለ ዊሊያም ደግሞ እንዴት አወቅክ? ስትከታተለኝ
ነበር እንዴ?” ብላ ጠየቀች “አትበሳጪ” ብሏት ጉድማን በማስከተልም “ስራዬ
እኮ ነው፡፡ ማለቴ አንዱ የስራ እድል ነው፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ አንቺ እራስሽን
አላማ ያደረጉ የግድያዎች ሙከራዎች የተደረጉብሽ ሰው ስለሆንሽ እንደ
አንድ መርማሪ አንቺን መከታተሌ ክፋት የለውም እላለሁ።” አላትና በሰማያዊ አይኖቹ ሰርስሮ ሲመለከታት አፈረችና “ይቅርታ” ብላ ተንተባተበች፡፡ “በመቀጠልም ልወነጅልህ ፈልጌ አይደለም፡፡ አንተ ስራህን እየሰራህ እንደሆነ አውቃለሁ፡፡ ግን በድንገት ስላገኘሁህ ተገርሜ ነው።”

“አሁን ወዴት እየሄድሽ ነው?”
“ወደ ቤት”
“እራት በልተሻል?”
የሚለው ጥያቄው ትንሽ የነፃነት ስሜት ሰጣትና እስከ አሁን አልበላሁም” ብላ መለሰችለት፡፡

“መልካም ተከተይኝ” ብሎ ጉድማን የእሷን ሀሳብ ሳይጠይቅ በመወሰን
“የሆነ የግሪኮች ምግብ ቤት ከዚህ በትንሽ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ የምትወጂው ይመስለኛል፡፡ በዚያ ላይ እናወራለን” ሲላት ኒኪ አብራው ለመሄድ ስታመነታ በማየቱ “ስለ አዲሱ ወዳጅሽ ስለ ሚ/ር ዊሊያምስ እናወራለን፡፡ ስለ እሱም ልታውቂያቸው የሚገቡ አንዳንድ ነገሮች አሉ፡፡” አላት፡፡

ከአስር ደቂቃ በኋላ ከግሪኮቹ ሬስቶራንት ውስጥ ከጉድማን ፊት ለፊት ዘና ብላ ተቀምጣ ራሷን አገኘችው፡፡ የጉድማን የሸሚዙ የላይኞቹ ሁለት ቁልፎች ተከፍተዋል፡፡ እጅጌውን ስለጠቀለለው ጡንቻማ እጁ ይታያል፡፡ቆዳው ለስላሳ እና ልጥፍ ያለ ነው፡፡ ፈገግ ሲል ደግሞ ነጫጭ ጥርሶቹ በግልፅ ይታያሉ፡፡ እርግጥ ነው ጉድማን ምንም አይነት እሷን የማማለል ድርጊቶችን በግልፅ ባያሳይም ባለፈው ማታ አብረው እየጠጡ በነበሩበት ሰዓት ላይ ለጥቂት ነው አብራው ከማደር የተረፈችው፡፡

“እስቲ ሀሳብሽን ሰብስቢ” አላት እና ጉድማን ውሃ እና አፒታይዘር
ለአስተናጋጁ አዝዞ ከጨረሰ በኋላም “አንዲት ሴት ላይ የራሴን ተፅዕኖ
በማድረግ ልወነጅል አልፈልግም” አላት የውስጧን ሀሳብ ያነበበ ይመስላል፡፡

ይህንን ሲላት የወሲብ ውጥረት በመሀከላቸው ተፈጠረ፡፡ ነገር ግን
ይህንን ስሜቷን ሆነ ብላ ችላ አለችው፡፡ ህይወቷ በፍቅር የተነሳ ተዘበራርቆባታል፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ ውስጧ ያለው የፍቅር ስሜት ሦስት አራተኛው ጉልበቷ ከእኔ ቤታ ማን ጋር ይገኛል፡፡ ከዚህም በላይ ደግሞ የባሏን ሀዘን አልጨረሰችም፡፡ እናም ለወሲብ ዝግጁ አይደለችም፡፡

“እሺ ስለዴሪክ ዊሊያምስ ምንድነው ማወቅ ያሉብኝ ነገሮች?” ብላ
ጠየቀችው፡፡

“እሱ የሴራ ፅንስ ሀሳቦችን እና ሁሌም የራሱን ካርድ ይዞ የሚጫወት ሰው ከመሆኑ በተጨማሪ ማለትሽ ነው?” ጉድማን ጠየቃት፡፡
“ዊሊያምስ ጥሩ ሰው ነው ደስ ብሎኛል” አለችው ኒኪ፡፡
“ብለሽ ነው?” ብሎ ጉድ ማን በቀልድ ስሜት ውስጥ በመሆን
“ለምን?” ብሎ ጠየቃት፡፡
“እውነተኛ ሰው ነው...”
“እውነተኛ ሰው ነው ...” ብሎ ጉድማን የእሷን ቃል ደገመው እና በቃሉ
እየተደመመ “መልካም ይሄን እንግዲህ እኔ በዚህ መልኩ ነው የማስቀምጠው፡፡ የእኛ ዲፓርትመንት በሚገለፅበት መልኩ
በእርግጥ እውነተኛ ያስመስለዋል፡፡”

“ለምን ይመስልሀል ግን?” ብላ ኒኪ ጠየቀችው፡፡ ዴሪክ ስለ ኤል.ኤ.ፒ.ዲ
መጥፎ ነገሮችን ሊያወራ የቻለበትን ምክንያት ከጉድማን ለማወቅ ፈለገች::

ጉድማን አንዴ ከመጠጡ ተጎነጨና “እሱ እኛ ሙሰኞች፣ ሰነፎች እና ደደቦች እንደሆንን አድርጎ ሊነግርሽ ይችላል፡፡” አላት እና “እውነቱ ግን ሌላ ነው፡፡ የራሱ መራር መሆን ነው እንደዚህ እንዲያስብ ያደረገው:: ወጣት እያለ የፖሊስ ሀይሉን ለመቀላቀል ማመልከቻ አስገብቶ ነበር፤ ለዚያውም ለብዙ ጊዜ፡፡ ግን ሊቀጥሩት ፍቃደኛ አልነበሩም።”

“በምን ምክንያት?” ብላ ኒኪ ጠየቀችው እና “ንገሪኝ ካልከኝ እሱ ለምርመራ ሥራ የተፈጠረ ሰው ነው” አለችው፡፡

“ስለ እሱ እንኳን የማውቀው ጉዳይ የለም፡፡ ግን ምናልባት መጥፎ ባህሪ
ስላለው? በጣም ችኩል እና በስሜት የሚገፋፋ ስለሆነም ይሆናል? ብቻ
ባጠቃላይ ዴሪክ ዊሊያምስ ለቡድን ሥራ የሚሆን ሰው አይደለም፡፡ ነገሮችን
ሁሉ ከራሱ ጋር የሚያያዝ ሰው ነው፡፡ ስለሆነም ብዙውን ጊዜ ለዲፓርትመንቱ የጭቃ እሾህ ሆኖ ነው የቆየው፡፡ ባይገርምሽ የፀረ አደንዛዥ ዕፅ
ቡድን ቢሮ ውስጥ ፎቶው ቦርድ ላይ በስፒል ተሰቅሏል፡፡ምክንያቱም በጣም ብዙ ጉዳዮቻቸው ውስጥ ጣልቃ እየገባ እነርሱ መርምረው ነገሮችን እንዳይደርሱባቸው ሲያደርግ የነበረ ሰው ነው” አላት፡፡

ኒኪ ግራ ተጋብታለች:: ጉድማን ጥሩ ግልፅ ሰው መሆኑ ብታምንም
ዴሪክ ዊሊያምስ ጨለምተኛ እና የተጣመመ አመለካከት ያለው ሰው ነው
እያለ ነው የሚነግራት፡፡ ይህ ደግሞ እሷ ስለዊሊያምስ ከምታውቀው በጣም
የተለየ ነው የሆነባት፡፡

“እሱን በዚህ መልኩ መፈረጁ ምቾት ላይሰጥሽ ይችላል። ስለ እኛ ዲፓርትመንት የነገረሽ ነገሮች በሙሉ የጥላቻ እና የቂም በቀል ናቸው፡፡ ግን
አንድ ነገር ልንገርሽ እሱ ገንዘብን በተመለከተ ደምሽን ነው የሚመጥሽ፡፡
ይሄ የአንቺ ጉዳይ እንደሆነ አውቃለሁ፡፡ ግን እስኪ እስከአሁን ስንት ነው
ያስከፈለሽ?” ብሎ ጉድማን ጠየቃት፡፡

ኒኪ ለዴሪክ የከፈለችውን በግማሹ አሳንሳ ለጉድማን ብትነግረውም
በጣም ብዙ እየከፈለችው እንደሆነ ነገራት፡፡

“ይሄውልሽ ቆንጆ ጉዳዩ ያንቺ ቢሆንም ሰውዬው እስስት አይነት ነገር ስለሆነ ለእሱ የምትነግሪያቸው ነግሮች ላይ ጥንቃቂ አድርጊ፡፡” አላት እና
በኒኪ ውስጥ ትንሽም ቢሆን ዴሪክ ዊሊያምስን ለመጠራጠር የሚያስችል
የጥርጣሬ ዘርን በመዝራቱ ደስ እያለው የሚያወሩትን ርዕስ ቀየረ፡፡ “ይልቅ
አንድ ነገር ልጠይቅሽ ፈልጌ ነበር” አላት፡፡
“እሺ” አለችው፡፡

“ብራንዶ ግሮልሽ” ብሎ ስሙን ሞቅ አድርጎ ጠራና “አውቃለሁ እሱን
አክመሽ እንደማታውቂ ነግረሽናል፡፡ ግን እሱ በጣም የሄሮይን ዕፅ ተጠቃሚ
ስለሆነ ምናልባት ለህክምና የባለቤትሽ ክሊኒክ መጥቶ ሊሆን አይችልም
ብለሽ ታስቢያለሽ?”

“መጥቶ ታክሞ ሊሆን ይችላል፡፡ ምክንያቱም ዶውግ እና ዶፎ እንደርሱ
አይነት ችግር ውስጥ የሚገኙ በጣም ብዙ ሰዎችን ሲያክሙ ነበር፡፡” ብላ መለሰችለት ኒኪ።

ግን ስለ ታካሚዎቻቸው ማንነት መረጃዎችን ያስቀምጣሉ አይደል?"

የአንዳንዶቹን አዎን” ብላ ኒኪ ትንሽ አመነታች እና በመቀጠልም የእነርሱ አሠራር ከእኔ ይለያል፡፡ እዚያ ለህክምና የሚመጡ ሰዎች ቤት አልባ ሰዎች፣ ምንም አይነት የመታወቂያ ወረቀት የሌላቸው ሰዎች፣ ምንም አይነት የኑሮ ዋስትና እና ጡረታ የሌላቸው ሰዎች ናቸው፡፡ ስለዚህ አንድ ሰው ከእነዚህ አይነት ሰዎች ውስጥ ማግኘት ከገለባ ውስጥ
👍1
#የወዲያነሽ


#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት


#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል


...አስታውሳለሁ ግን እኮ ታዲያ...” ብዩ ሙሉ ሐሳቤን ሳልገልጽላት ዝም አልኩ።የዝምታዬ መነሾና ጥጥር ምክንያት ግን አዲሱ እኔ በመሆኑ እሷ ልታውቀው
አትችልም፡፡

«ና በል እንሒድ ቶሉ እንመለሳለን» አለችና ተነሣች። የእኔ ጉዳይ
በእርሷና በእናቴ መካከል ተመክሮበት ያለቀ በመሆኑ እንግዲህ አደራሽን እንደዚያቹ እንደ ምክራችን አድርገሽ ንገሪው፡፡ እኔና አንቺ እንደ ተባባልነው
ቢሆን ይሻላል፡፡ ከዚያ በኋላ ደግሞ እኔ ደኅና አድርጌ እነግረዋለሁ፤ አደራሽን አደራችሁን» ብላ እናቴ በዐይኗ ሸኘችኝ፡፡ «ሂዱ» የምትለን ወደ እኔ ቤት መሆኑን አወቅሁ፡፡ የወዲያነሽን ለመጠበቅ ቆምኩ። «ሂዱ እንጂ ምን ቀረህ?
እናቷ እኮ ነኝ! ሌላ እናት ያላት መሰለህ? አይዞህ! ለሌላ ሰው አልሰጥብህም፣ እሷም በጀ አትልም» ብላ ስቃ አሣቀችኝ፡፡ የወዲያነሽ እናቴን በዐይኗ እየጠበቀች 'የሂዱ' ምልክት በጣቷ አሳየችኝ። ምርቱን እንደከተተ ሰው ተደስቼ ወጣሁ፡፡ወደ እኔ ቤት የመሄዱን ነገር ሰርዘን መኪና ውስጥ ተቀመጥን።

«አባቴ ስለ አንተና ስለ የወዲያነሽ ምንም ነገር ፈጽሞ እንዳልሰማና እስከ ዛሬም እንዳላወቀ ታውቃለህ:: ምስጢሩን የቀበርነው ሁላችንም ስለ ፈራነው ነው»
በማለት ንግግሯን ጀመረች፡፡ ጠንቃቃነቴንና ለጉዳዩ ያለኝን ከፍተኛ ግምት በግልጽ ለማስረዳት «አንቺና እማማስ ብትሆኑ ካባረራችኋት በኋላ ስለ እርሷ ምን የምታውቁት ነገር ነበር? ምስጢሩ ያልተነዛው ከእርሷ ጋር በመባረሩና እስር ቤት
በመውረዱ ነበር» ብዩ ተራ ለቀቅሁ፡፡

«ነገሩን በብልሃትና በዘዴ ካላስኬድነው በስተቀር ከአባታችን ጋር ብዙ ንትርክና ጭቅጭቅ እንደሚነሳ የታወቀ ነው፡፡ እኛ ግን ስለ ነገሩ ፍንጭ አግኝቶ
እንዲጠራጠር በማድረግ ጉዳዩን ለመጀመር አስበናል፡፡ ከዚያ በኋላ ደግሞ አንተም እኛም ጥሩ ጥሩ ሽማግሌዎች መርጠን...» ብላ ሳትጨርስ «የብልሃቴ አቀነባባሪ እኔ ነኝ፡፡ የአዲሱ ሕይወቴ ጎዳና ቀያሽና ደልዳይ ራሴ ነኝ።
እያስፈልግም፡ በቃኝ! አባቴንም እንደ እናቴ በማስማልና በፍርሃት
እየተርበደበድኩ በመጠጋት የሚለኝንና የሚወስንብኝን ሁሉ አቀርቅሬ በመስማት ዕድል ለሚሏት አጋጣሚ ነገር አልንበረከክም! መጠራጠር ማለት ስለ አንድ ነገር ቢያንስ በጥቂቱ ማወቅ ወይም መገመት ማለት ነው። የትላንቱን ስሕተቴን ዛሬና
ነገ መድገም የለብኝም፡፡ አታስቡ! እኔ ለአባቴ የራሴ ዝግጅት አለኝ፡፡ በቀጥታ ቀርቤ ፊት ለፊት አስረዳዋለሁ፡፡ ለጥያቄዎቹም መልስ እሰጣለሁ» በማለት ጣልቃ
ገብቼ ተናገርኩ። ድንገት ደሟ ፈላና «ከንትርክና ብዙ ጣጣን ከሚያስከትል ጭቅጭቅ ይልቅ መግባባት ይበልጣል። በንትርክና በአሻፈረኝ ባይነት የምታገኘው
ድል አድራጊነት ሁሉ እስከ መጨረሻው አያረካህም፡፡ አባቴ በመጀመሪያ ጋሻዬነን አይቶ ከተደሰተና የሐሳቡ አቅጣጫ ካማረ ሁሉም ነገር ይሳካልናል።
የወዲያነሽንና የአንተን ግንኙነት፣ የደረሰባትን መከራና ሥቃይ ሁሉ ቀስ በቀስ እተርክለታለሁ፡፡ ልቡ ካዘነና መንፈሱ በርህራሄ ከተነካ፡ በሉ ሂዱና አምጧት ይላል” ብላ ነገሯን ልታራዝም ስትል «አይቻልም! ማን አስተርጓሚ አደረገሽና!
መሸሸግም ሆነ መደበቅ የለበትም፡፡ አልለማመጥም:: እጅግ አርኪው ድል አድራጊነትም ከትግልና ከሥቃይ በኋላ የሚገኝ ድል አድራጊነት ነው፡፡ እኔና
የወዲያነሽ ጋሻዬነህን አስከትለን ባንድ ላይ እንቀርባለን፡፡ ይህ ከመሆኑ በፊት “እንቺም ሆንሽ እናቴ አንዲት ቃል መናገርም ሆነ ማሰማት የለባችሁም፡፡ በምንቀርብበት ቀን እንግዶች ቢኖሩም ባይኖሩም ግድ የለኝም። እንዲያውም ወሬው እንዲስፋፋና እንዲዛመት ብዙ ሰዎች ቢኖሩ በጣም ጥሩ ነው:: በዚህ ብትስማሙ ተስማሙ፡ አለበለዚያ ግን የማደርገውንና የማላደርገውን እኔ ራሴ አውቃለሁ፡፡ እኔ የምፈልገው እንዲያውቅ ብቻ እንጂ እንዲስማማ ወይም መርቆ
እንዲቀበለን አይደለም፡፡ ከባለቤቴ ጋር ባለን ግንኙነት ውስጥ ጣልቃ ገብቶ አስተያየትም ሆነ ሌላ ሐሳብ እንዲያቀርብ አይደለም» በማለት ቀጥ እንዳለ አቀበት ስትፈራው የቆየችውን ጉዳይ አውላላ ሜዳ አደረግሁላት፡፡ በእኔ ላይ የነበራት ግምትና አስተሳሰብ ሁሉ ነፋስ እንደ መታው ልም ዱቄት ተበተነ፡፡በሁለታችን መካከል በጣም ግዙፍ የሆነ የሐሳብ ልዩነት ተፈጠረ፡፡ በእኔ ላይ የሐሳብ በላይነት ለማግኘት ባለመቻሏ ተከዘች። ምክራቸውንና መላቸውን ሁሉ ባለምቀበሌ ንዴቷ ናረ። የመዥገር ሞት ያህል አላሳዘነችኝም፡፡ ቁርጡን ለማወቅ
የጓጓው አእምሮዋ ራሱ የዘጋውን የዝምታ በር ከፈተው፡፡ «እኔ እና የግሌን የአቀራረብ መንገድና ሐሳብ አዘጋጃለሁ እንጂ የእናንተን አልቀበልም ማለትህ ነው?» ብላ ሁኔታዬንም አብራ ለመረዳት ፊቷን ወደ እኔ አዞረች፡፡

ባጭሩና በቀላሉ ”አዎ” አልኩና ተጨማሪ ምክንያትና ማብራሪያ
ለማቅረብ ስዘጋጅ «በቃኝ አያስፈልገኝም! አልሰማም ቀኙን ሲያሳዩህ ግራ ግራውን ትመርጣለህ፡፡ እኔን ያናደደኝ ያንተ እምቢታና የመጣው ይምጣ ባይነት ሳይሆን በዚሀ ይሻላል በዚያ፡ ይኸ ያዋጣል ያኛው ይበልጣል እያልኩ ከእናቴ ጋር
ስነታረክና ስከራከር መሰንበቴ ነው» ብላ ፊቷን አዞረች።

አልደነገጥኩም፡፡ «የአንቺም ይሁን የእናቴ ርዳታ እያስፈልገኝም፡፡ ጥገና እና ድረታ አልፈልግም፡ ጥገና አይዋጥልኝም! ጥገና ማለት ውስጠ ሰባራ ማለት ነው፡፡
ከሆነላችሁ እናንተም ተደርባችሁ በጥያቄና መልስ አዋከቡኝ! ዝግጁ ነኝ። ነገር ግን እኔ በማልገኝበት ወቅት አባቴን እንድትለምኑልኝና እኔን፣ ባለቤቴንና ልጄን ዝቅ አድርጋችሁ እንድትለማመጡልኝ አልፈልግም፡፡ እኔ ራሴ ባለጉዳዩ ፍላጎቴንና ውሳኔዩን ለማስረዳት በሚገባ ዝግጁ ሆኛለሁ» ብዬ ፋታ ሰጠሁ፡፡

«አያዋጣም እንጂ ቢያዋጣማ ጥሩ ነው:: ለፍተህ ለፍተህ እዚህ ከደረስክ በኋላ እንዴት እንዲህ በቀላሉ ትገነፍላለህ?» ብላ ራሷን ነቀነቀች።

«በቃኝ ነው የምልሽ! በሐሳቤና በእምነቴ እንድትስማሚ አላስገድድሽም። የገዛ መብቴን አልመፀወትም:: የሕሊናዬን ቁስል የማድንበትን መድኃኒት ቀስ በቀስ እያወቅሁ ነው:: ከአባቴ መሠረተቢስ እምነት ጋር እንድጋጭና እንድታተር
እንጂ እንደ ከዚህ ቀደሙ አንገቴን ሰብሬ የሚኖረው የሚያቀርበውን
ዝባዝንኪ ሐሳብ ሁሉ ያለ አንዳች ክርክር እንድቀበል አልፈልግም! ጨቋኝ ግዴታውን አልቀበልም:: ሐሳባችሁንም ሰርዙ። ከዚህ አሁን ከነገርኩሽ አፈጻጻም ውጪ አንዳችም የምቀበለውና የምስማማበት ሐሳብ ስለ ሌለ ነገር ሳናንዛዛ ወደ ቤት እንግባ» አልኩና ለጠላቱ የመጭረሻ ማስጠንቀቂያ እንደሚሰጥ
ሰው የማያወላዳውን ነገርኳት። ለወለላ ገሥግላ ፊት ዛቀች!

ያለውን ይበል ብላ እንዴት አታስብም? እንዴት አይገባህም? ነገሩን ረጋ ብለህ ተመልከተው፡ ራስህን ብቻ አትውደድ፡ ይኸማ ይበጣበጡ' ይጣሉ፡ ይጋደሉ ማለትህ እኮ ነው? ስንትና ስንት ዓመት ሙሉ ምስጢሩን ደብቀህ
ከኖርክ በኋላ አሁን በመጨረሻ ጣጣን አመጣህ። ለካስ በጄም በግሬም ገብተህ የተለማመጥከኝ እንዲህ ለመሆን ኖሯል? አሁን አንተ በምትለው ሁኔታ ከሆነ
አገር ምድሩን እንደሚበጠብጥ አውቃለሁ፡፡ እናቴ ግን ያን ሁሉ አድራጎት ያደረገችው ላንተው ስትል እንደነበር ታውቃለህ» ብላ ፊት ለፊት ወደ ጨለማው
👍3
#የተወጋ_ልብ


#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት


#ድርሰት_በትክክል_ገና


.....አምናን ካቻምናን ከዚያ በፊት የተቆጠሩ ዓመታትን ጨምሮ ለብዙ ጊዜ የደከሙበት ትምህርት የሚቋጨው ዘንድሮ ነው። ጌትነትና አማረች ከጓደኞቻቸው ጋር በቡድን በቡድን ሆነው እያሽመቁ ጥናታቸውን ሲለበልቡ የከረሙበት ላለፉት ረጅም አመታት ትምህርታቸውን በመከታተልና የሚሰጣቸውን አድካሚ የቤት ስራዎችን ከመደበኛ ሥራቸው ጋር አጣምረው በመስራት ከፍተኛ ዋጋ የከፈሉበት የነዚያ ሁሉ አመታት ልፋት ድምር ውጤት የሚደመደምበትና የሚመረቁበት አመት ዘንድሮ ነው።
ሁለቱ ፍቅረኛሞች በአዋሳ ላንጋኖ ሃይቅ ውስጥ ተክለው ያለመለሙት ፍቅራቸው የሚያስቀና ሆኗል። ጌትነት የመልካሙ ተበጀ አዋሳ ላንጋኖ
ዘፈን አስቀድሞ የሚወደው ቢሆንም ለሱ የተዘፈነለት እስከሚመስለው ድረስ በይበልጥ የወደደውና አብሮ ማቀንቀን የጀመረው ከላንጋኖ ሽርሽር
በኋላ ነው።
አዋሳ ላንጋኖ ለሽርሽር ሄጄ ያየሁሽ፣
የሲዳሞ ቆንጆ እንዴት ነሽ?
ሽንጥና ተረከዝ ዳሌና ጡትሽ...
አዲስ አበባ ውስጥ ለሁለት አመታት ሲመኛት ቢኖርም በፍቅር ያወቃት በአዋሳ ላንጋኖ ሀይቅ ውስጥ ነበረና ያንን ዘፈን ሲሰማ የአዋሳ ላንጋኖው ሃይቅና ያ ውብና ምንጊዜም ከህሊና የማይጠፋ አስደሳች ዓለም ከነሙሉ
ጓዙ ተጠቅልሎ በሃሳቡ እየመጣበት ዘፈኑን ነፍሱ ምንጥቅ ብላ እስከምትወጣ ድረስ ወደደው። በዚህ የተነሳ የሲዳሞ ቆንጆ በሚለው ምትክ የአዲስ አበባ ቆንጆ እንዴት ነሽ በሚል ተክቶ ከዘፋኙ ጋራ አብሮ ሲያቀነቅን የሚሰማው ስሜት የተለዬ ነበር፡፡ አማረች ለሁለት አመታት ስትመኘው የነበረው ጉዳይ በመሳካቱ እጅግ ደስተኛ ከመሆኗ በላይ ከምትወደው ልጅ ጋር በትዳር ተሳስራ በመኖር የወላጆቿን ፍላጎት ለማሟላት
የሚያስችላት መልካም አጋጣሚ መፈጠሩ በአንድ ጠጠር ሁለት ወፍ ሆኖላታል። ወላጆቿ ልጃቸው ትዳር እንድትይዝላቸው ከፍተኛ ጉጉት አላቸው፡፡ “መቼ ይሆን የአያትነት ወግ ማእረግ የምታሳይኝ ልጄ? እንግዲህ ጀርባዬ ሳይጎብጥ ጉልበቴ ሳይዝል ጥሩ እስክስታ እንድመታልሽ ከፈለግሽ ይሄን ጊዜ ነው ጉልበቴን መሻማት” እያሉ የሚወተውቷት አባቷ
ይህንን ውሳኔዋን ሲሰሙ ደስታቸው ወደር እንደማይኖረው ጥርጥር አልነበራትም፡፡እናቷ አማረችን የሚያይዋት እንደ ልጃቸው ሳይሆን እንደ ታናሽ እህታቸው ነው። አማረችም እናቷን እንደ ታላቅ እህት እንጂ
እንደ እናት አይደለም የምታያቸው፡፡ ታሪኩን ያጫወተቻቸውም እሳቸው
በነገር ወጋ አድርገዋት ነው፡፡

“አማሩዬ? እኔ የምለው? እኛ የምናመጣልሽ ባል እንደማይኖር
በጠዋቱ አስጠነቀቅሽን
አንቺ የምታመጭውን ብንጠብቅ ደግሞ የማሚታይ ነገር ጠፋ።
ምን ይሻላል ልጄ? የሁልጊዜ ምክንያትሽ ትምህርቴን ልጨርስ ነው። ትዳር ተይዞ መማርን ምን ይከለክለዋል? አባትሽ ትዳር ትዳር እያልኩ ስጨቀጭቃት ሸክም ሆንሽብኝ ያልኳት እንዳይመስላት እንዳትሳቀቅብኝ እያለ እየፈራ እንጂ ከኔ የበለጠ የቸኮለ እሱ ነው፡፡ እንዲያው ለጤናው ያድርግለት ችኩል ብሏል”
የትዳሯ ነገር ያጓጓቸው፤ የሰርጉ ቀን የናፈቃቸው መሆኑን አጫወቷት።አማረች ቀኝ ክንዷን በቀኝ ጉልበቷ ላይ አገጯን በመዳፏ ደገፍ አድርጋ
በፍቅር ዐይን ዐይናቸውን እየተመለከተች ነበር የምታዳምጣቸው፡፡

ፊቷ ወይን ጠጅ መስሏል፡፡ ከረጅም ጊዜ ሚስጥር በኋላ እጮኛ ያላት መሆኑን ወላጆቿ ያላወቁት የትዳር ጥንስስ በልቧ ውስጥ ተጠንስሶ መቆየቱን ልትነግራቸው ፈለገች። ከዘንድሮ ምረቃ በኋላ ለትዳር የወጠነቸው
ጓደኛ ያላት መሆኑን ለእናቷ ለማብሰር ፈለገችና ጥርት ያለው ፊቷ በእፍረት ሲቀላባት የወይን ጠጅ መልክ እየያዘ ሄደ።

ከአማረች የመኝታ ክፍል ውስጥ ሆነው ነበር የሚጨዋወቱት፡፡ አማረች ስለፍቅረኛዋ ማስረዳቱን ቀጠለች፡፡ የዐይነ ህሊናዋ ካሜራ በጌትነት ላይ አነጣጥሮ ያሳለፉትን ጣፋጭ የፍቅር ጊዚያት አንድ በአንድ እንደ ፊልም
እየቀረፀና የአዋሳው ትዝታ ፊቷ ላይ ድቅን እያለ፡ “ትንሽ ነው የቀረኝ በጣም ትንሽ ጊዜ፡፡ በጣት የሚጠለቀውን ቀለበት አላጠለኩም እንጂ ታጭቻለሁ። ለረጅም ጊዜ የተዋወቅኩት የምወደው ፍቅረኛ አለኝ፡፡ እስከ አሁን በደንብ ተጠናንተናል። ተግባብተናል። ተዋደናል። ያንቺና የአባዬ ብቻ ሳይሆን በትዳር የመኖሩ ጉጉት በኔ ብሷል። ዩኒቨርስቲ አብሮኝ የሚማር
ልጅ ነው፡፡ ላንቺም ለአባዬም የማስተዋውቅበት ጊዜው ደርሷል። ሁላታችንም በዚህ ዓመት እንመረቃለን፡፡ እስከዛሬም የደበቅኩሽ ትምህርቴን
ከመጨረሴ በፊት ሠርጉ ይፋጠን የሚል ጥያቄ እንዳታቅርቡልኝ ነው።አሁንም ቢሆን ላንቺ ብቻ ነው የምነግረው፡፡ ለአባዬ ጊዜው ሲደርስ አንቺ ትነግሪዋለሽ” የአማረች እናት ልባቸው በደስታ ዘለለች። እንኳን የተማረ! እንኳን ያፈቀረችውን ይቅርና ሱሪ ይልበስ እንጂ እሷ ተመችቶኛል ትዳር
መያዝ እፈልጋለሁ ብላ ፈቃደኝነቷን ከገለፀች ከማንም ጋር ቢሆን ድል ባለ ሠርግ ሊድሯት ሁሌም የሚቃዡበት ምኞታቸው ነበረና፣ እንደ
ዕድሜ እኩዮቻቸው “ልጃችንን ዳርናት” እያሉ አፋቸውን ሞላ አድርገው ለመናገርና እርጅና ከመምጣቱ በፊት የአያትነት ወግ ማእረግ ሊያገኙ ነውና የሰሙት የምስራች እንደ ትንሽ ልጅ እያስቦረቃቸው የባለቤታቸውን ደስታ ጭምር አገላብጠው ሳሟት፡፡

“ለምን የፈለገው አይሆንም አማሩዬ? ይህችን አሁን ያሰማሽኝን የምስራች ይቺን እኔ የሰማኋትን ሚስጥር እሱም ቢሰማ ኖሮ በደስታ አስር
ዓመት ወደ ኋላ ያስቆጥር ነበር” በዜናው እጅግ ተደስተው ወደር የማይገኝለት የእናትነት ፍቅራቸውን እቅፍ አድርገው በመሳም ገለፁላት።አባቷ የሚወዷት የመጀመሪያ ልጃቸው ትምህርቷን ጨርሳ በዲግሪ ተመርቃ
የምትወደውን ፀባየ ሸጋና ጠንበለል ልጅ ይዛላቸው ከተፍ ስትልሳቸው ከደስታቸው የተነሳ ቦሌ አካባቢ ያሰሩትን አምስት ክፍል ቪላ ቤት ጀባ እንደሚሏቸው ጥርጥር የለውም፡፡ ይህንን ጠንቅቃ ስለምታውቅ ጌትነትና ስለመኖሪያ ቤት እያነሳ ሲጨናነቅ በልቧ ትስቅ ነበር። አማረች የምስራቹን ለእናቷ ባደረሰችበት በመመረቂያቸው ዓመት ላይ ጌትነትና እሷ የዓመት ዕረፍት ፈቃዳቸውን ወስደው ለመጨረሻው ፈተና እየተዘ
ጋጁ ነበር።

ትናንትና ለእናቷ የነገረቻቸውን ልትነግረው ፈለገች። አሁንም እንደ
አማረች በሆነ ባልሆነው “ጌትሽ ድረስ!” ሆኗል ዜማዋ፡፡ ዕቃ ሲሰበር አዲስ ፊቷ በእፍረት እየተለወጠ እየቀላ ሄደ፡፡ አሁን አሁን ደግሞ “ጌትዬ ድረስ!" ሆኗል ዜማዋ ምናምን ካስደነገጣት ጌትሽ” ብቻ ለሁሉም ነገር "ጌትሽ
ነጠላ ዜማ ሆኗል፡፡ ይሄ ነገር እናቷንም ግራ ሲያጋባቸው የኖረ ጉዳይ ነበር፡፡ በመጨረሻው ላይ እቅጩን ነገረቻቸው እንጂ ደጋግመው ስምተዋታል "ጌትዬ! ጌትዬ" ስትል፡፡

በዩኒቨርስቲው የመማሪያ ክፍል ውስጥ ከሁለቱ በስተቀር ማንም አልነበረም፡፡ባዶ ነው።ኃይለኛ ንፋስ መስኮቱን ጓ! አደረገና አላጋው። እንደልማዷ”ጌትሽ ድረስ!” በማለት ሄዳ ልጥፍ አለችበትና” ለማዘር ነገርኳት እኮ!"
አለችው እየተፍነከነከች።የመስኮቱ ጩኸት እፍረቷን አቡንኖታል።
“ምኑን?" ፈገግ እንዳለ ዘቅዝቆ እየተመለከታት፡፡
“በቃ ላስተዋውቅህ መሆኑን? እና እንትኔ መሆንህን፡ ባሌ መሆንህን!" አንገቱን እቅፍ አድርጋ ከንፈሩን ሳመችው። ቅብጥ ስትል ያለማጋነን ደስ ትላለች። የአንዳንዱ ቅብጠት ያስጠላል። አማረች ግን የቅብጠት ቅመሙን ጣል አድርጐባት ነው መሰል ቅብጥብጥ ስትል የበለጠ
👍31
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ

...አስራ ስድስት ወራትን በክብረ መንግስት አሳልፋ ወዴ ዲላ የተመስሰችው ሔዋን ብዙ አካባቢያዊ ለውጥ ሊገጥማት እንደሚችል ገምታ ነበር፡፡ነገር ግን ከሽዋዬ ቤት በዘመናዊ የቤት እቃዎች መሞላትና ወንድ ወንድ ከመሽተት በቀር ሁሉም ነገር ያው ነው።በሸዋዬ ቤት የወንድ ኮትና ጃኬት ግድግዳ ላይ ተሰቅለው የወንድ ጫማ በአልጋ ሥር ተቀምጦና ትልቅ የወንድ ፎቶ ግራፍ ብፌ ላይ ስታይ ሸዋዬ ባል ያገባች መስሎ ተሰማት። በእርግጥም “ማንዴፍሮን ገና የገባች እለት ተዋወቀችው።
ማንደፍሮ መልኩ ጥቁር ፊቱ ጉሩድረድ ያለና አካሉ ግዙፍ
ከመሆኑ ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ ሲጨብጣት የእጁ አከባበድ የሚያስፈራ ሆኖባት ቢሆንም እያደር ስትግባባው ግን ባህሪው ቀላል የሆነ ሰው ነው። ይስቃል
ይጫወታል። ቀልዶቹ ይጥማሉ፡፡ እየሰነበተች ስታየው እንዲያውም በእሱ መኖር ቤቱ ድምቅ ሲል መንፈሷም ዘና እያለ መጣ፡፡ «የኔ ፍልቅልቅ» በማለት እያጫወተም ይበልጥ ያፍለቀልቃት ጀመር።
ዲላ እንደገባች በአፍንጫዋ የገባው አየር በአስቻለው የሰቀቀን ትዝታ የተለወሰው ነበር፡፡ ሆዷን ባር ባር እያለው እንባዋም ያለ ገደብ ፈስሷል። ያም ሆኖም
በተለይ ታፈሡን፣ በልሁን መርዕድንና ትርፌን አግኝታቸው በጋራ አልቅሰውና አንብተው እፎይ ካሉ ወዲህ ከፊል የመንፈስ መረጋጋትም እያደረባት ሄደ። ሸዋዬም ለአባትና ለእናቷ የገባችውን ቃል ያከበረች መሰለች! ሔዋን በማንኛውም ሰዓት ወደ
ታፈሡ ቤት ሄዳ የቱንም ያህል ጊዜ ቆይታ ብትመለስ የት ነበርሽ ምን አስቆየሽ?” አትላትም፡፡ ለሔዋን ከምንም በላይ የተመቻት ይህ የሸዋዬ ቃል ማከበር ነው።

ለአንድ አስራ አምስት ቀናት ያህል በዚህ አይነት እንፃራዊ የመንፈስ
መራጋጋት ውስጥ የሰነበተችው ሔዋን ሦስተኛው ሳምንት ሲጀመር ግን ያ በሸዋዬ ቤት የመኖር ሥጋቷ የልቧን ግድግዳ ማንኳኳት ጀመረ፣ በድሉ አሸናፊ ማንደፍሮን እየተከተለ በዚያ ቤት ውስጥ ገባ ወጣ ማለት ጀመረ፡፡ ማንደፍሮ ስለ ሔዋን ብዙ ነገር ሲነገረው ከርሟል። ከአስቻለው ጋር የነበራት ግንኙነት፣ በድሉ ሔዋንን ለመቅረብ ያደረገዉ ጥረትና የሰጠችው ምላሽ፣ በአሁኑ ወቅት አስቻለው ስለሚገኝበት ሁኔታና ሌሎችም ሁኔታዎች በዝርዝር ተገልፀውለታል፡፡ ወደፈት
የበድሉንና የሔዋንን ጉዳይ እንዲጨርስም አደራ ተጥሎበታል፡፡
ምንም እንኳ በአስቻለውና በሔዋን መካከል የነበረው ግንኙነት በተዛባ ሁኔታ የተነገረው የተሳሳተ መንገድ እንዲከተል የተገፋፋ ቢሆንም ማንደፍሮ ግን
ሆዱን ፍርሃት ፍርሃት ይለው ነበር። ሁኔታው ምንም ይሁን ምን አንድ ነገር ተገንዝቧል። ሔዋን የምታፈቅረው ሰው አላት። ያ ሰው ለጊዜው በአካባቢው ባይኖረም በተስፋ እየጠበቀችው እንደሆነ ልብ ብሏል። የተጣለበት አደራ ደግሞ ይህን ተስፋ በጥሶ ሌላ እንዲቀጥል ነው። እናም ለህሊናው እየከበደው ውስጥ ውስጡን ይጨነቃል።
በሌላ በኩል ደግሞ ጉዳዩ የበድሉ ነው፣ የሥራ ዋስትናው። እንዲሁም የሸዋዬም ጭምር ነው፤ የአፍላ ፍቅረኛው፡፡ በዚህና በመሳሰሉት ሁኔታዎች እየተገፋፋ የተጣለበትን አደራ መወጣት የሚያስችሉ መላዎችን ሲፈጥር ሰንብቷል።አንድ ቀን በተለመደው
ሁኔታ በድሉና ማንደፍሮ በሽዋዬ ቤት ጫት ለመቃም አቅደው ከሸዋዬ ጋር በተደረገ ምክክር ቤቱ በልዩ ሁኔታ ተዘጋጅቷል። ከቀኑ ስምንት ሰዓት አካባቢ ከቤቷ ሲደርሱ ማንደፍሮ ከቤቱ ወለል ላይ ቆሞ ለየት ያለ ሀሳብ አቀረበ
«ዛሬ ከምንም ነገር በፊት አንድን ነገር መፈፀም አለበት።» አለ በዚያ ሰዓት ጓዳ ውስጥ ለነበረችው ሔዋን በሚሰማ ሁኔታ ድምፁን ከፍ በማድረግ።
«ምን?» አለች ሽዋዩ እንደማታውቅ ሆና፡፡
«ሔዋን የለችም እንዴ?» ሲል ማንደፍሮ እንደገና ጠየቃት፡፡
«አለች። ጓዳ ውስጥ ናት፡፡»
«ኑ ሁላችንም ወደ እሷ እንሂድ፡፡» አለና ማንደፍሮ ቀድሞ ወደ ጓዳ
ተራመደ። በድሉና ሸዋዬም ተከተሉት::
«የኔ ፍልቅልቅ» ሲል ጠራት ማንደፍሮ ሔዋንን፡፡
«አቤት» አለች ሔዋን ድንግጥ እያለች፡፡ የዚያን ዕለት ደግሞ የልብ
ህመሟ ዘወር ብሎባት ፍራሽ ላይ ጋደም ብላለች፡፡
«አንድ ጊዜ ብድግ ብትይ!»
ሔዋን በድንጋጤ ዓይኗ ፍጥጥ እንዳለ ተነስታ በዚያው ፍራሻ ላይ
ቆመችና ከፊት ለፊቷ የተኮለኮሉትን ሁሉ ተራ በተራ ታያቸው ጀመር፡፡
«ዛሬ ዛሬ ሁሉም ነገር ገብቶኛል፡፡» አለ ማንደፍሮ ሳቅ ብሎ። “ይህ ሰውዬ!» ሲል ቀጠለ ወደ በድሉ እያመለከተ ወደዚህ ቤት በመጣ ቁጥር ስሜትሽ ለምን እንደሚቀያየር ተረድቻለሁ። ያለ ፍላጎትሽ እየጎነተለ ሲያስቀይምሽ እንደቆየ ገብቶኛል።አሁን አሁን ጥፋት መሆኑን አምኖ ተቀብሏል፡፡ ይቅርታም ሊጠይቅሽ ተዘጋጅቷል።ይቅርታውን ተቀብለሽ እንድትታረቁና ልክ እንደ አንድ ቤተሰብ እየተያየን እንድንኖር ፈልጌለሁ።» አላት።
ሔዋን ያላሰበችውና ያልጠበቀችው አቀራረብ ነበር። ለጊዜው ግን ድንግጥ ተብላ ወደ መሬት ከማቀርቀር በቀር ያለችው ነገር አልነበረም። ማንደፍር ወደ በድሉ ዞር አለና ቆጣ ባለ አነጋገር «በል እግሯ ላይ ውደቅ!» ሲል አዘዘው፡፡ በድሉ ኮቱን ወደ ኋላ መለስ አድርጎ በሔዋን እግር ላይ ወደቀ፡፡
«እልልልል» አለች ሽዋዬ። ማንደፍሮም ብቻውን አጨበጨበ። ለሔዋን ግን ትልቅ የእረብሻና የግርግር ጩኸት ወስጥ የገባች መሰላት፡፡ በድሉ በእግሯ ላይ ወድቆ ለአፍታ ሲቆይ ለመግደርደር ያህል እንኳ በቃ ተነስ አላለችውም። ሲበቃው ራሱ ተነሳ::
«ቀጥል!» አለ ማንደፍሮ ነገሩን በማሟሟቅ ዓይነት ፈንደቅ እያለ፡፡
በድሉ ቀኝ እጁን በኮቱ ኪስ አስገብቶ አንዲት በብልጭልጭ ወረቀት የተጠቀለለች ነገር አወጣ፡፡ ወረቀቱን ቀዶ ጣለ፡፡ ከማይካ የተስራች ነጭ ሙዳይ
ብቅ አለች፡፡ እሷንም ከፈታት። በቅድሚያ ጥጥ መሳይ ነገር ታየ። ቀጠለና በግምት አሥራ አራት ግራም የሚሆን የክርስቶስ የስቅለት ተምሳሌት ማጫዎች
የተንጠለጠለበት የወርቅ ሀብል አወጣና በአንገት ውስጥ ለማስገባት የተዘጋጀ በሚመስል ሁኔታ ከያዘ በኋላ ፈገግ እያለ ማንደፍርን አየት አደረገው::
«ቀጥላ! ምን ታየኛለህ?» አለ ማንደፍሮ፡፡ በድሉ እነዚያን አራት ገጣጣ ጥርሶቹን ገልፈጥ አድርጎ ወደ ሔዋን ጠጋ ሲል ሔዋን ግን ድንገት ጮኸች::
«አልፈልግም!»
«ተይ እንጂ የኔ ፍልቅልቅ አለ ማንደፍሮ እሱም ደንግጥ አያለ፡፡
«እምቢ! አልፈልግም» ሔዋን አሁንም፡፡ ፊቷን ክስክስ አድርጋ በድሉን በጥላቻ ዓይን ታየው ጀመር።
«አይ እንግዲህ!" አለና ማንደፍሮ ሔዋንን ወደ ራሱ ጎተት አደረገና ሁለት እጆቿን ያዝ በማድረግ «አጥልቅላት » አለው በድሉን።
በድሉ የሔዋን እጆቿ እንደተያዙለት ሀብሉን በአንገቷ ላይ የመጣል ያህል አስገብቶ ወደ ኋላው ፈግፈግ አለ።ማንደፍሮና ሸዋዬ አጨበጨቡ፡፡ ማንደፍሮ በሔዋን አንገት ላይ ያረፊቱን ሀብል በእጁ ያዝ አድርጎ ወርቁንም ሔዋንንም
ተራ በተራ እየተመለከተ«አንቺን ለመሰለች ቆንጆ የሚገባ ልዩ ስጦታ!» አላት።
ሔዋን ግን ዓይኖቿ በእንባ ሞሉ፡፡ ግንባሯን በከንዷ ጋርዳ ወደ መሬት
በማቀርቀር ታለቅስ ጀመር።
«ሔዋን እንዳንቀያየም» አላት ማንደፍሮ። ሔዋን መልስ አልሰጠችውም፡፡አሁንም አጎንብሳ ታለቅስ ጀመር፡፡
👍8😱1
#ምንዱባን


#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ

መጨረሻው እንደ አጀማመሩ አልሆነም

ጊዜ እያለፈ ሲሄድ ኮዜት ከሀዘንዋ እያገገመች መጣች:: የጊዜው
መርዘም፣ ወጣትነትዋ፣ የአባትዋ ፍቅርና የአካባቢዋ ማማር ቀስ በቀስ ሀዘንዋን እንድትረሳ ረዱዋት:: ቀን አልፎ ቀን ሲተካ፧ ወር አልፎ ወር ሲተካ የፍቅርዋ ሙላት በየቀኑ በጠብታዎች እየጎደለ ሄደ:: ወላፈኑ በርዶ
ወደ መጥፋት ተቃረበ፡፡ ሆኖም ረመጠ ጨርሶ ስላልጠፋ ማቃጠሉ፣ ማስጨነቁና ማሰቃየቱን ትቶአታል እንጂ ጨርሶ አልተወገደም::

አንድ ቀን በድንገት ማሪየስ ታወሳት:: «ምን!» አለች:: «ደግሞ ከየት መጣ? ረስቼው አልነበረም እንዴ!» በማሪየስ በኩል ደግሞ «ምነው ከመሞቴ በፊት አንድ ጊዜ ብቻ ባየኋት!» የሚልበት ወቅት ነበር፡፡

የማን ጥፋት ነው? የማንም::

አንዳንድ ሰው ከገባበት ወጥመድ በቀላሉ መውጣት አይችልም፡፡
ማሪየስ የዚያ ዓይነት ሰው ነው:: ከደረሰበት ሀዘን እንደ ኮዜት በቀላሉ ሊላቀቅ አልቻለም:: ሀዘን ውስጥ ገብቶ እዚያው ነው ተዘፍቆ የቀረው።

አንድ አጋጣሚ ይከተላል፡፡ በትልቁ በር በኩል ከአንድ ግቢ ውስጥ
አንድ እንደ መቀመጫ የሚያገለግል ጥርብ ድንጋይ ነበር፡፡ እንደ ሴት ጎፈሬ
የተከረከመ የዛፍ አጥር በአጠገቡ ስለነበር ማንም ሰው በመንገድ ሲያልፍ ወደ ውስጥ ማየት አይችልም፡፡ ነገር ግን ከውስጥ ያለ ሰው ከፈለገ እጁን
በአጥሩ ቀዳዳ በማበጀት አሾልኮ በውጭ የሚያልፈውን ሰው ማየትና መጨበጥ ይችላል፡፡

አንድ ቀን ማታ ዣን ቫልዣ ወደ ውጭ ወጥቶ ነበር፡፡ አየሩ ጥሩ
ስለነበር መሸት ሲል ኮሴት ከዚያ ድንጋይ ላይ ተክዛ ቁጭ ብላለች፡፡ የጥንት ትዝታዋ ተቀሰቀሰባት፡፡ ጊዜው ጨለምለም ብሏል፡፡ የእናትዋ መንፈስ ከዚያ ያለ መሰላት፡፡ ከተቀመጠችበት ብድግ ብላ ሄደች::

ቀደም ሲል ዝናብ ዘንቦ ስለነበር ሳሩ ያቀዘቅዛል፡፡ «ይህስ ጉንፋን
ያሲዛል ፧ ብቀመጥ ይሻላል» ብላ ወደ ድንጋዩ መቀመጫ ስትመለስ
መቀመጫው ላይ አንድ ነገር አየች:: አንድ እጥፍጥፍ ብላ የተጠቀለለ ነገር ከትንሽ ጠጠር ጋር ተያይዟል:: ከመቀመጫው ተነስታ ስትሄድ ከዚያ
አልነበረም::

ኮዜት ገርሞኣት «ምንድነው እሱ?» ስትል ራስዋን ጠየቀች:: መቼም ሰው ካላስቀመጠው በራሱ ኃይል ሊመጣ እንደማይችል ተረዳች:: ፍርሃት፣ፍርሃት፣ አላት፡፡ ድንጋዩን መንካት አልደፈረችም:: ወደኋላ ሳታይ ቤትዋ ሮጠች፡፡ ቤትዋ ከገባች በኋላ በርና መስኮት ዘጋጋች፡፡ መቀርቀሪያዎቹን
ሁሉ ቀረቀረች:: ከጥቂት ጊዜ እረፍት በኋላ ‹አባባ ተመልሷል እንዴ?»
ስትል ቱሴይን ጠየቀቻት::

«ኧረ አልተመለሰም» አለቻት::

ክፍሎቹ በሙሉ ተዘግተው እንደሆነና ከቤት ውስጥ ሰው እንዳለ እንድታይ ቱሴይን አዘዘቻት:: አጎንብሳ ከአልጋዋ ስር እንዲሁም ቁም ሣጥንዋን ከፍታ ሰው እንዳለና እንደሌለ አጣራች:: ከተኛች በኋላ ያ ያየችው
ጠጠር ተራራ አክሉ በውስጡ ዋሻ እንዳለበት አለመች::

ጠዋት ፀሐይ ስትወጣና ጨለማ ለብርሃን ቦታዋን ስትለቅ ማታ
እንደዚያ ያስፈራሩን ነገሮች እንደሚያስቁን ይታወቃል:: ኮዜት ስትነቃ ማታ እንደዚያ ያስፈራት ነገር ቅዠት መስሎ ታያት:: ስለምን ነበር የምቃዠው?» ስትል ራስዋን ጠየቀች::

ልብስዋን ለብሳ ወደ አትክልቱ ቦታ ሄደች:: ስትፈራኛ ስትቸር ማታ
ተቀምጣበት ወደነበረው የድንጋይ መቀመጫ ሄደች:: የተጠቀለለው ነገር ከዚያው ቁጭ ብሉአል:: በመጀመሪያ ትንሽ ፈርታ ነበር:: በኋላ ግን ፍርሃቱ ተወገደላት:: ደግሞም በጨለማ የሸሸነወ ነገር በብርሃን እንጓጓለታለንና ምን እንደሆነ ለማየት ቸኩለች፡፡

«አይ ምን አስፈራኝ፤ ፈትቼ ልየዋ» አለች ለራስዋ:: የተጠቀለለውን
ነገር አንስታ ከፈታታችው በኋላ አብሮ ታስሮ የነበረውን ድንጋይ ጣለችው::

አድራሻ ያልተጻፈበትና በውስጠ ወረቀት ያለው እንደ ደብዳቤ ያለ ነገር መሆኑን ተገነዘበች:: ወረቀቱን ከውስጡ ሳታወጣ አገላብጣ አየችው:: አሁን መፍራትዋ ቀርቶ «ከውስጡ ምን አለ» በማለት በመጓጓት ለማወቅ ፈለገች::
ፖስታውን ከፍታ ከውስጡ የነበረውን ወረቀት አወጣች:: በጥሩ የእጅ ጽሑፍ እንደ ጥቅስ ያሉ ነገሮች ተጽፎበታል፡፡ የገጹ ብዛት ከአንድ በላይ ነው:: እያንዳንዱ ገጽ ላይ ቁጥር ተጽፎበታል:: ሆኖም እያንዳንዱ ገጽ ሞልቶ የተጻፈበት ሳይሆን መሐሉ ላይ ብቻ ነው የተጻፈው:: የመጻፊያ ቦታ እያለ ወደ ሚቀጥለው ገጽ ይዞራል::

ፊርማ ወይም ስም ካለበት በሚል በችኮላ ፈለገች፤ ግን አላገኘችም::
ለማነው የተጻፈው? ለራስዋ እንደሆነ ጠረጠረች፡፡ ምክንያቱም እርስዋ ተቀምጣበት ከነበረው ሥፍራ ነው የተገኘው፡፡ ታዲያ ማነው ጸሐፊው?
ግራ ገባት:: በመገላመጥ አካባቢዋን ቃኘች፡፡ ከርግቦች በስተቀር ምንም ነገር የለም:: ወረቀቱን ማንበብዋን ቀጠለች::
ቀጥሎ የተመለከተው ነበር በወረቀቶቹ ላይ የተጻፈው::

«ዓለም ተጨብጣ አንዲት ትንሽ ነገር ስትሆን፧ አንዲት ትንሽ ነገር
ደግሞ ተነፍታ እግዚአብሔርን ስታክል ፍቅር ትባላለች፡፡ ፍቅር ነፍስን ትመስላለች፤ አፈጣጠራቸው አንድ ነው፡፡ እንደ ነፍስ የመንፈስ ቅዱስ
ብልጭታ ኣለባት፡፡ እንደ ነፍስ ግን አትገድፍም፣ አትነጣጠልም
አትጠፋም፡፡ የእሳት ረመጥ ስትሆን በውስጣችን አለች፤ ዘላለማዊ ናት..ማለቂያና መደምደሚያ የላትም፡፡ ረመጥዋ በምንም ነገር አይጠፋም::
ከአጥንታችን ውስጥ እንኳን ገብታ ስትፋጅ ይሰማናል:: እንዲሁም ከሰማየ ሰማያት ወርዳ፧ ከአካል ውስጥ ዘልቃ ትገባለች፡፡ ሆኖም ስታንፀባርቅ አካላችን ውስጥ በጉልህ እናያታለን፡፡

«ፍቅር! አድናቆት! የሁለት የሚግባቡ አእምሮዎች ፣ የሁለት
የሚወሳሰቡ ልቦች፣ የሁለት አካልን ሰነጣጥቀው የሚገቡ ዓይኖች ያላት ብርሃን! አንቺ ደስታ ወደ እኔ ትመጪያለሽ ወይስ አትመጪም! ፍቅር
ብቸኝነትን ሲያጠቃ አብሮ የሚጓዝ፤ የሚንሸራሽር! የተባረኩ ቀኖች! የሰዎችን እድል፣ የሰዎችን እጣ ፈንታ ለመካፈል መላእክት ከሰማየ ሰማያት ወርደው
በዚህች ምድር ሲኖሩ በሕልሜ ያየኋቸው ነው የመሰለኝ፡፡ አይ ፍቅር!

«ዘላለማዊ ከማድረግ በስተቀር ማንም ከሁለት ከሚዋደዱ ፍጡሮች ደስታ ላይ የሚጨምረው ነገር የለም፡፡ በእርግጥ የፍቅር ዘላለማዊነት
ከፍቅር ዘመን በኋላ የሚታከል ነው:: ግን የፍቅርን መጠን፣ የፍቅርን ግለት ለማሳደግ ከፍቅረኞቹ ከራሳቸው በስተቀር ማንም ሊያስቀረው አይቻለውም፡፡ ፍቅር የሰዎች ፍጹምነት ይታይበታል፡፡

«ከዋክብትን የምናይበት ምክንያት ሁለት ነው:: ይኸውም
ስለሚያብረቀርቁ ወይም ምንነታቸውን ስለማናውቅ! ከጎናችን ግን ከከዋክብት
ይበልጥ ምሥጢሩ ያልታወቀ የላመ፣ የለሰለሰና የሚያንፀባርቅ ፍጡር አለ... ሴት::

«ድንጋይ ከሆንክ ትልቅ ድንጋይ ሁን፤ የዛፍና የቅጠላቅጠል ዘር
ከሆንክ ስሜት፤ ሰው ከሆንክ ደግሞ ፍቅር ይኑርህ::

«ወደ ሽርሽሩ ቦታ ትመጣለች? የለም ጌታዬ! በየሳምንቱ እሑድ ወደ ቤተክርስቲያን ትመጣ የለ? የለም መምጣቱን ትታለች:: አሁን ከዚሁ ቤት ውስጥ ነው የምትኖረው? የለም ለቅቃለች፡፡ አሁን ከየት ሰፈር ገባች?
አድራሻዋ አይታወቅም፡፡ ስትሄድ አልተናገረችም? አልነገረችንም:: ምን ዓይነት የተዳፈነ ጨለማ ነው እባካችሁ የአንድን ነፍስ አድራሻ አለማወቅ!

በፍቅር ምክንያት የምትጨነቅ፣ የምትሰቃይ ነፍስ! አሁንም ውደድ፤ በይበልጥ አፍቅር፡፡ በፍቅር መሞት ማለት በፍቅር መኖር ማለት ነውና፡፡
👍17😱1
#የጣሪያ_ስር_አበቦች


#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት


#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ


ቀኖቹን ሁላ ሰማያዊ ስትቀባ አንዱን ለጥቁር ተወው።

በማንኛውም ቀን ልንሄድ ነው፡፡ እናታችን በምሽት ወጣ እላለሁ እንዳለች፣
መጓጓዝ የሚችሉ ውድ ንብረቶቿም ከእሷ ይወጣሉ። ወደ ግላድስተን
አንመለስም እዚያ አሁን ክረምት ገብቷል። ገና እስከ ግንቦት ይቆያል።ሰርከስ የሚሰሩ ሰዎች ወደሚኖሩበት ወደ ሳራሶታ እንሄዳለን፡ እዚያ ያሉ
ሰዎች ለየት ያለ የኋላ ታሪክ ላላቸው ሰዎች ደግነት በማሳየት የሚታወቁ
ናቸው ክሪስና እኔ ከፍ ያለ ቦታ ማለትም ጣራ ላይ ስለኖርን ምሰሶዎቹ
ላይ ብዙ ገመዶች የታሰሩበት በመሆኑ ለክሪስ “የዥዋዥዌ ትርኢት የምንሰራ እንሆናለን” አልኩት እየተፍለቀለቅኩ። በመጀመሪያ የሞኝ ሀሳብ እንደሆነ አስቦ ፈገግ አለ፤ ቀጥሎ ግን መንፈስን የሚቀሰቅስ ሀሳብ ብሎ ጠራው።

ኮሪ ጭንቅላቱን ቀና አደረገ፡፡ ሰማያዊ አይኖቹ በፍርሀት ፈጥጠዋል።

“አይሆንም!” አለች ኬሪ “እቅዳችሁን አልወደድነውም እንድትወድቁ አንፈልግም::”

“አንወድቅም” አለ ክሪስ፡ “እኔና ካቲ የማንቻል ቡድን ነን፡" አሻግሬ ወደ እሱ
እየተመለከትኩ መማሪያ ክፍሉ ውስጥ ከዚያም ጣሪያው ላይ ሆነን “ከአንቺ
በስተቀር ማንንም አላፈቅርም፣ ካቲ አውቀዋለሁ... እንደዚያ አይነት ስሜት ነው ያለኝ... ሁልጊዜ እኛ ብቻ:" ያለኝን አስታወስኩና በተለየ ሁኔታ ሳቅኩ። “ሞኝ አትሁን፣ በዚያ መንገድ እንደማትወደኝ ታውቃለህ፡ እና ጥፋተኝነት
ሊሰማህ ወይም ልታፍር አይገባም: የእኔም ጥፋት ነው: እንዳልተፈጠረ
ማስመሰልና በድጋሚ እንዳይፈጠር እርግጠኛ መሆን ነው ያለብን፡"

"ግን ካቲ....."

“አንቺና እኔ ሌሎች ሰዎች ሲኖሩን፣ በፍፁም… በፍፁም እርስ በርሳችን በዚህ መንገድ እንዲሰማን አይሆንም''

“እኔ ግን ስላንተ በዚህ መንገድ እንዲሰማኝ ነው የምፈልገው። እና ለእኔ ሌላ
ሰው ለማመንና ለመውደድ በጣም ዘግይቷል።”

ክሪስን መመልከት… ከዚያ መንትዮቹን. ለሁላችንም እቅድ ሳወጣና እንዴት
እንደምንሄድ ሳወራ ትልቅ የሆንኩ አይነት ስሜት ፈጠረብኝ፡ ለመኖር
የትኛውንም ነገር ለመስራት እንደምንገደድ ባውቅም እንኳን መንትዮቹ ሰላም
እንዲሰማቸው መፅናኛ ነገሮች አወራቸዋለሁ።

መስከረም አልፎ ጥቅምት ተተካ። በቅርቡ በረዶ መጣል ይጀምራል:
“ዛሬ ማታ” አለ ክሪስ፡ እናታችን በሩጋ ቆም ብላ ዞራ እንኳን ሳታየን
በግዴለሽነት ደህና ሁኑ ብላን ሄደች:: አሁን እኛን መመልከት እንኳን
መቋቋም አቅቷታል። አንዱን የትራስ ልብስ ሌላኛው ላይ ደርበን ጠንhር እንዲል አደረግን፡ በዚያ ትራስ ጨርቅ ውስጥ ክሪስ የእናታችንን ውድ
ጌጣጌጦች ሁሉ ከትቶ ያመጣል፡ እኔም ሁለት ሻንጣዎችን አሽጌ እናታችን
አሁን ወደዚያ ስለማትሄድ ጣራው ስር ያለው ክፍል ውስጥ ደብቄያለሁ።

ቀኑ መምሸት ሲጀምር ኮሪ ማስመለስ ጀመረ። እየደጋገመ ያስመልሰው
ጀመር። በመድኃኒት ማስቀመጫው ውስጥ ለሆድ የሚሆን መድኃኒት ነበረን የገረጣውን፣ የሚያንቀጠቅጠውን፣ የሚያስለቅሰውን አሰቃቂ ማስመለስ ያደረግነው ጥረት ሁሉ ሊያስቆመው አልቻለም ከዚያ ክንዶቹን በአንገቴ ዙሪያ ጠምጥሞ “እማዬ ደህና አይደለሁም::” ሲል አንሾካሾከ።

“እንዲሻልህ ምን ላድርግልህ ኮሪ?” ስል በጣም ልጅ መሆኔና ልምድ የሌለኝ መሆኔ እየተሰማኝ ጠየቅኩ።

“ሚኪ” አለ ያላመደውንና ጓደኛ ያደረገውን አይጥ በደካማ ድምፅ እየተጣራ
“ሚኪ እኔ ጋር እንዲተኛ እፈልጋለሁ”

“ግን ስትገለበጥ ላዩ ላይ ትተኛበትና ይሞትብሀል፡ እንዲሞትብህ አትፈልግም
አይደል?”

“አልፈልግም” አለ ሀሳቡ ራሱ ያስደነገጠው መሰለ፡ ከዚያ ያ አሰቃቂ መጓጠጥ
እንደገና ጀመረውና ክንዶቼ ላይ እንደያዝኩት እየቀዘቀዘ መጣ፡ በላብ የረጠበ
ፀጉሩ ግንባሩ ላይ ተለጥፏል ሰማያዊ አይኖቹ ፊቴ ላይ ተተክለው እየደጋገመ እናቱን ይጣራል። “እማዬ፣ እማዬ፣ አጥንቶቼን አሞኛል” “አይዞህ” አልኩት።
የተበላሸውን ፒጃማውን ለመቀየር ተሸክሜ ወደ አልጋው እየወሰድኩት ነው።
ሆዱ ውስጥ የቀረ ምንም ነገር ሳይኖር እንዴት ሊያስመልሰው ይችላል?
ክሪስ ይረዳሻል አትጨነቂ!” ሲለኝ ከጎኑ ጋደም ብዬ ደካማና የሚንቀጠቀጥ
ሰውነቱን በክንዶቼ አቀፍኩት::

ክሪስ ጠረጴዛው ጋ ተቀምጦ የኮሪ የህመም ምልክቶች የሚያሳየውን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያንዳንችንን ሊያጠቃን የሚችለውን ሚስጥራዊ በሽታ ለማወቅ
የሀክምና መፅሀፍ ላይ ተደፍቷል አሁን አስራ ስምንት አመት እየሆነው
ነው እኔንና ኬሪን ትታችሁን አትሂዱ! ሲል ለመነኝ፡ ጮክ ባለ ድምፅ “ክሪስ አትሂድ እዚህ ቆይ!” አለ።

ምን ማለቱ ነው? እንድናመልጥ አይፈልግም? ወይስ ለመስረቅ እንደገና
ወደ እናታችን ክፍል አትሂድ ማለቱ ይሆን? እኔና ክሪስ መንትዮቹ የምናደርጋቸውን ነገሮች በመረዳት ይመለከታሉ ብለን ያመንነው ለምንድነው?
በእርግጠኝነት እሱና ኬሪ ትተናቸው እንደማንሄድ ያውቃሉ ያንን ከማድረግ
ብንሞት ይሻለናል።

ኬሪ ነጭ ልብስ የለበሰች ትንሽ ጥላ መስላ ወደ አልጋው መጣችና በረጠቡት ትላልቅ ሰማያዊ አይኖቿ መንትያ ወንድሟን አተኩራ እየተመለከተች
ቆመች: ትንሽ ናት። በጨለማ ክፍል ውስጥ መንምና በአጭር ቀርታ ያደገች ትንሽዬ ተክል ናት።

“ከኮሪ ጋ መተኛት እችላለሁ? ምንም መጥፎ ወይም ክፉ ወይም ቅዱስ
ያልሆነ ነገር አንሰራም: እሱ አጠገብ መሆን ስለፈለግኩ ብቻ ነው” አለች።

አያትየው ትምጣና መጥፎ የምትለውን ነገር ታድርግ! ኬሪን ከኮሪ ጋር አስተኛኋት። ከዚያ እኔና ክሪስ ከትልቁ አልጋ ግራና ቀኝ ቆመን በሀዘን ተሞልተን ኮሪ ረፍት ባጣ ሁኔታ ሲቅበጠበጥና ለመተንፈስ ሲታገል እንዲሁም በቅዠት ሲጣራ እየተመለከትን ነው
እናቱንና አባቱን፣ ክሪስንና እኔን ይፈልጋል እምባዬ በሌሊት ልብሴ ኮሌታ
ላይ እየወረደ ነው ክሪስንም ስመለከተው ጉንጮቹ በእምባዬ ረጥበዋል። “ኬሪ
ኬሪ... ኬሪ የታለች?" ሲል በመደጋገም ጠየቀ እንቅልፍ ከወሰዳት ትንሽ
ቆይታለች: ፊቶቻቸው ተጠጋግተው ነበር። ቀጥታ ወደ እሷ እየተመለተ
ቢሆንም እያያት አይደለም

ቅጣት እንደሆነ አሰብኩ፡፡ እግዚአብሔር እኔና ክሪስ ስለሰራነው ነገር እየቀጣን
ነው አያትየው አስጠንቅቃን ነበር. እስክተገረፍንበት ቀን ድረስ በየቀኑ
ታስጠነቅቀን ነበር ሌሊቱን ሙሉ እኔ ክፍሉ ውስጥ ስንጎራደድ፣ ክሪስ ደግሞ ከአንዱ የህክምና መፅሀፍ ወደ ሌላው እየሄደ ሲያነብ ነበር።

በመጨረሻ ደም የመሰሉ አይኖቹን ቀና አድርጎ “የምግብ መመረዝ ነው::
ወተቱ ተበላሽቷል ማለት ነው” አለ።

“ስቀምሰውም፣ ሳሸተውም ደህና ነበር” ስል መለስኩለት ሁልጊዜ የትኛውንም ምግብ ለክሪስና ለመንትዮቹ ከማቅረቤ በፊት በጥንቃቄ አሽትቼና ቀምሼ ነበር። በሆነ ምክንያት ሁሉንም ነገር ከሚወደውና ምንም ነገር ከሚበላው
ክሪስ የተሻለ የመቅመስ ችሎታ እንዳለኝ አስባለሁ።

“ሀምበርገሩ ይሆናል፡ ለየት ያለ ጣዕም ነበረው”

“አረ ጣዕሙ ለእኔ ደህና ነበር” አልኩት ለእሱም ደህና የነበረ ይመስለኛል::
ምክንያቱም ቀኑን ሙሉ ኮሪ ምንም መብላት ስላልፈለገ የኬሪን ግማሽ ሀምበርገር ጨምሮ የኮሪንም ፋንታ ነበር የበላው ኮሪ ቀኑን ሙሉ ምንም መብላት አልፈለገም ነበር።

“ካቲ አንቺም ቀኑን ሙሉ ምንም እንዳልበላሽ አስተውያለሁ አንቺም እንደ
መንትዮቹ ያህል ከስተሻል፡ የምታመጣልን ምግብ በቂ ነው ራስሽን መበደል
አይጠበቅብሽም” አለኝ፡
👍342🥰1
#ሳቤላ


#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት


#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ


ደቂቃዎች በረሩ ላራት ሰዓት ሩብ ጕዳይ አራት ተሩብ አሁንም ሪቻርድ ሔር ከእናቱ ጋር እንዳለ ነው " ሚስተር ካርላይልና ባርባራም በአትክልቱ ቦታ መኽል ባለዉ እግር መንገድ እስከዚያ ሰዓት ድረስ በትዕግሥት ይመላለሳሉ አራት ሰዓት ተሩብ ላይ ሪቻርድ ሔር ከናቱ ተሰናብቶ መጣ " ባርባራም ዕንባዋን እያወረደች ተሰናበተችው በመጣበት ለመሔድ ወደ ዐፀዱ ገባ "

“ በይ ባርባራ . . . ደኅና እደሪ " በጣም ስለመሸ ሚስዝ ሔርን አልተሰናበትኳቸውም " ሆኖም ሁሉ ነገር ደኅና በመሳካቱ የተሰማኝን ደስታ ንገሪልኝ ”ብሏት ሔደ እሱ በሰው እየተራመደ ወደ ቤቱ ሲገሠግሥ ባርባራ ብሶቷ በዕንባ እስኪወጣላት ድረስ ከበሩ ብረት ተደግፋ ማንም
ሳያቋርጣት እያነባች ዐሥር ደቂቃ ያህል ቆየች " እናቷም የራሷን የውስጥ ብሶት ስታስተነትን ፈጽማ ረስታት ኖሯል። ባርባራ ከዚያ እንደ ቆመች ፈጣን የእግር ዳና ስትሰማ በጣም ድንግጥ አለች ወዲያው ግን ሚስተር ካርላይል መሆኑን ዐወቀችው "

“ በውስጡ አንድ ብራና የያዘ ጥቅል ትቼ ነበር እባክሽ አምጭልኝ” ባርባራ
ስትበር ሔዳ አመጣችለት ሚስተር ካርላይልም ተቀበለና ባጭሩ አመስግኖ ወደ ቤቱ ገሠገሠ ። እሷም እንደ ነበረችው ከበሩ ተደግፋ በካርላይል መምጣት ተቋርጦ
የነበረውን ዕንባዋን ትለቀው ጀመር በወንድሟ ነገር አንጀቷ አሯል ይሆናል ተብሎ የተጠበቀው ካፒቴን ቶርን ሳይሆን በመቅረቱ የባሰውን በግናለች አሁንም ግና የአባቷ ዳና አልተሰማም እሷም ቁማ መጠበቋን ቀጠለች » ትንሽ ቆይታ በቁጥቋጦቹ ታኮ አንድ ስው ከሩቅ ታያት " እሷም የድንጋጤ ሀይኖቿን አፍጣ ተመለከተች " ልቧ ነጥሮ የሚወጣ እስኪመስል ይመታ ጀመር " ሪቻርድ መሆኑን ስታውቅ
ምን ጉዳይ አሳብዶ እንደ መለሰው ገረማት አሁንም ከደጅ ሲያገኛት ጊዜ ያባቱን
አለመግባት አረጋገጠና ያለ ሥጋት ተጠጋ " የሠራ አካላቱ እየተንቀጠቀጠ ትንፋሹ ቁርጥ ቁርጥ እያለ የሚሆነው ጠፍቶታል "

“ ባርባራ ! ባርባራ !.... ” አላት በኃይል እየቃተተ “ቶርንን አየሁት !
ራሱን ቶርንን በአካል አገኘሁት ”

ባርባራ እንግዳ ነገር ሆነባትና አፍጣ ታየው ጀመር

“ልክ ከዚህ እንደ ወጣሁ ሰው ስለማይበዛበት ከዚህኛው መንገድ ይሻላል
በማለት ወደ ቢን ሌን አቋርጨ ስሔድ አንድ ሰው ከሩቅ ሲመጣ አየሁ ምንም እንኳን ሌላ ለመምሰል ብሞክርም ማንም እንዲያገኘው ስለ አልፈለግሁ ወደ ዛፎቹ
ዘወር አልኩ እሱ መኻል መንገዱን ይዞ ወዶ ዌስትሊን ሲሔድ አየሁት ግና ከአጠገቤ ሳይደርስ ዐወቅሁት "

የሠራ አካላቴን ወረረኝ " እያንዳንዷ የደሜ ጠብታ የምትሯሯጥብኝ መሰለኝ" ዘለህ እነቀው የሆሊጆን ገዳይ ነው ብለህ አስይዘው የሚል ሐሳብ መጣብኝ
ሁኔታውን ገምግሜ ቀጥቅጦ እንዳይገለኝ ፈራሁና ተውኩት አየሽ... ደሞኮ አንድ ጊዜ ነፍስ ያጠፋ ሰው ሁለተኛ ለመድገም ወደ ኋላ አይልም አላት። "

«ሪቻርድ እርግጠኛ ነህ ? ስለ ቶርን ብዙ ስለምትናገር እንዲያው በሐሳብህ
መጥቶብህ እንዳይሆን ?አለችው "

ምን ነካሽ ... ባርባራ ሐሳብ? ከዚህ ተቀርጿል አላልኩሽም ? አላት ወደ
ልቡ እያመለከተ " በየጥላው ሥር ቶርንን አየሁ የምል ሰው በለበት ሰው የሚታየኝ ሕፃን መሰልኩሽ ወይንስ ዕብድ? በአንድ እጁ ባርኔጣውን ይዞ በሌላው ፀጉሩን ከግንባሩ የኋሊት እያስተኛ አሁንም አሁንም ጸጕሩን የኋሊት የመግፋት
ልምድ አለው በጣም እየተጣደፈ ይራመድ ነበር ጸጉሩን እንደዚያ ወደ ኋላ
በሚመልስበት ጊዜ የጣቱ አልማዝ በጨረቃው ብርሃን ይፈልቅ ነበር " ምንም አትጠራጠሪ።

ባርባራ በደንብ ካዳመጠችው በኋላ እሷም እንደሱ ስሜቷ ተቀሰቀሰ ድንጋጤዉ እንቅቃጤዉ ጥድፊያዉ ጉጉቱ እንዳለ ተጋባባት ። ማሰብ ማማዘን
ቦታ ለቀቁ።

በግብታዊ ስሜት ብቻ ተነዳች " የሪቻርድ አባባል ሙሉ በሙሉ እንዳመነችቐት
ምን እንደምታደርግ በማሰብ ጊዜ ማባከን አልፈለገችም :

ምናልባት በዚያ ሰዓት ሰው ቢያገኛት ምን እንደሚላት በመዘንጋት አባቷ ከቤት ሲገባ ቢያጣት ምን እንደሚል በመርሳት ሪቻርድ ሔር ቀስ ብሎ ዙሪውን እያስተዋለ በሩቁ እየተከተላት ወደ ሚስተር ካርላይል እየሮጠች ሔዶች ገና ኢስትሊን በር ሊገባ ሲል ደረሰችበት "

“ባርባራ. . . ምን ነው በደኅናሽ ነው ?”

“ አርኪባልድ ! አርኪባልድ ! አለች ከትንፋሿ ጋር እየተናነቀች " እሱስ
ደኅና ነኝ' አንድ ጊዜ ሪቻርድን አነጋግረው ቶርንን አይቶታል ”

ሚስተር ካርላይል ምልስ አለና ወደ ቁጥቋጦች ዘወር ብለው ሪቻርድ ያየውን
ነገር ዝርዝር አድርጎ አጫወተው እሱም ምናልባት ሪቻርድን ላለማስከፋት ብሎ
እንደሆነም አይታወቅም : ልክ እንደ ባርባራ ሙሉ በሙሉ ሳይጠራጠር ያመነው መሰለ "

“ ሪቻርድ ... ዛሬ ማታ ከቢሮዬ ካየኸው ሰው በቀር በዚህ አካባቢ ቶርን የሚባል ሰው ጭራሽ የለም” አለው ካርላይል ትንሽ ካሰበ በኋላ “ የሚገርም ነገር ነው …”

“ አሁን ያገኘሁት ሰው ቶርን ለመሆኑ አልጠራጠርም ምናልባት እሱ እዚ
ያለው በሌላ ስም ሊሆን ይችላል።

አለባበሱ ምን ይመስል ነበር ? አለው ካርላይል።

እንደ ፈለገ ቢለብሰው ሰውየው አያሳስትም ” አለ ሪቻርድ “ የማታ ልብስ ለብሶ ቀጭን ካፖርት ብጤ ትከሻው ላይ ጣል አድርጎ ነበር " ለባርባራ እንደነገርኳት ጸጉሩን ከግንባሩ ወደ ኋላው በመግፋት ልምዱ ብቻ በቀላሉ ዐውቀዋለሁ
በተጨማሪ ደግሞ ለስላሳ ነጭ የሆነው እጁና የሚያንጸባርቀው የአልማዝ
ቀለበቱ ዋና ምልክቶች ናቸው ”

"በል እንግዲያው ሪቻርድ ... እኔ አሁን የምመክርህ ከዚህ አንድ
ቀን ሰንብትና ይህን ሰውዬ ፈልገው » ድንገት ያየኸው እንዪሆነ የት እንደሚገባ
ተከታተለው ከተቻለ የዚህን ሰው ማንነት ማወቅ በጣም አስፌላጊ ነው አለው
በሚስተር ካርይል

"ብገኝ የሚጠብቀኝ አደጋሳ ?”

አንተ ደግሞ በጣም ስለ ተለዋወጥክ ቀን ለቀን በአደባባይ ብትሔድ እንኳን
የሚያውቅህ አይገኝም : "

ሪቻርድ በሚስተር ካርይል አነጋገር ሊተማመን ስለ አልቻለ ስለአየው ሰውዬ
ምልክት ዝርዝር አድርጎ ከገለጸላቸው በኋላ ለማንኛውም አስፈላጊ ነገር
የሎንዶን አድራሻውን ሰጥቶ ሔደ "

“ በይ እንግዲሀ ልሸኝሽ እንጂ .. ባርባራ ” አለ ሚስተር ካርላይል "

“ በጭራሽ አይሆንም ! እንደዚህ ጊዜው መሽቶ አንተ ደክሞህ እያለህ ሁለተኛ መንገድ አላስመታህም " አሁንም ስመጣ ብቻዬን ነበርኩ " ሪቻርድም እንኳን አብሮኝ አልነበረም ።

ስትመጭ ምንም ነገር ማድረግ ባልችልም አሁን ከሌሊቱ እምስት ሰዓት
ላይ በአውራ ጐዳና ብቻሽን ስትሔጅ ዝም ብዬ አላይሽም ” አለና ክንዱን ዘረጋላት " ተያይዘው ጉዞ ጀመሩ "

“አቤት ይህን ያህል አምሽተህ ስትገባ እቤት ሳቤላ ምን ትልህ ይሆን?”

“ እስካሁን ከግብዣው የምትመለስ አይመስለኝም ደሞም አንዴ ብቻ በአንድ ምክንያት ማምሸቴ ይህን ያህልም አይደለም ”

ከበሩ አድርሷት ተመለሰ እሷ ከቤት ስትገባ አባቷ አሁንም ገና አልመጣም
ነበር "

ሚስተር ካርይል ከቤቱ ሲደርስ ሳቤላ ከመልበሻ ክፍሏ ውስጥ ተቀምጣ ስትጽፍ አገኛት " ስለ ግብዣው አንዳንድ ነገር ጠይቋት ባጭሩ ቁርጥ ቁርጥ እያደረገች
መለሰችለት " በመጨረሻም ለምን እንደማትተኛ ጠየቃት

“ እንቅልፌ አልመጣም ”

“ እኔ ግን ቶሎ መተኛት አለብኝ " ... ሳቤላ ሙትት ብዬ ደክሜአለሁ ”

" ትችላለህ ” አለችው "

ሊስማት ጐንበስ ሲል ፊቷን በዘዴ ዞር አደረገችበት ወደ ግብዣው አብሯት ባለመሔዱ የተቆጣች መሰለውና እጁን ከትከሻዋ ጣል አድርጎ ፈገግ አለ "
👍12
#ጠላፊዎቹ


#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት


#በኬንፎሌት


#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ


ወጀቡ እስኪጠፋ ወለሉ ላይ ተቃቅፈው ቆዩና ‹‹መርቪን አልጋው ላይ
እንውጣ ከወለሉ ይልቅ እዚያ ይመቸናል›› አለ፡
ናንሲ በመስማማት ራሷን ነቀነቀች፡፡ ከዚያም በጉልበቷ እየዳኸች
አልጋው ላይ ወጣች፡፡ መርቪንም ተከተላትና አልጋው ላይ አብሯት ወጣ፡፡
እሱም እቅፍ አድርጎ ያዛት፡፡
በወጀቡ ምክንያት አይሮፕላኑ በተናወጠ ቁጥር ልክ መርከበኛ የጀልባ
ውን ምሰሶ እንደሚይዝ ሁሉ ናንሲ መርቪንን ጭምቅ አድርጋ ትይዛለች፡፡
ወጀቡ ሲቀንስና ዘና ስትል እሱም ሰውነቷን በፍቅር ይነካካቸዋል ከዚያ ትንሽ ቆየችና እንቅልፍ ይዟት ሄደ፡፡.
በሩ ተቆርቁሮ «አስተናጋጅ መቷል» የሚል ድምፅ ስትሰማ ከእንቅልፏ ነቃች።
ዓይኖቿን ስትከፍታቸው መርቪን ደረት ላይ መተኛቷን አወቀች
‹ወይ አምላኬ! አለች እየተርበተበተች፡

መርቪን ከተኛችበት እንድትነሳ በእጁ ገፋ አደረጋትና ‹‹ትንሽ ጠብቀን
አስተናጋጅ›› አለ፡፡

ከበሩ ውጭ የቆመው አስተናጋጅ በተደናገጠ ድምፅ እሺ ጌታዬ
እጠብቃለሁ›› አለ፡፡

መርቪን ከአልጋው ወረደና በአልጋ ልብስ ናንሲን ሸፈናት::

በዚህ አድራጎቱ በሆዷ አመሰገነችው፡፡ አስተናጋጁ እንዳያያት ፊቷን ወደ ግድግዳው አዞረች፡፡

መርቪን በሩን ሲከፍት አስተናጋጁ ገባና ‹‹እንዴት አደራችሁ›› አለ በፈገግታ፡፡

የትኩስ ቡና መዓዛ ናንሲን አወዳት፡፡ ‹‹በእንግሊዝ የሰዓት አቆጣጠር
የሶስት ሰዓት ተኩል ወደ ኋላ ነው ማለት ነው?›› አለ አስተናጋጁን

‹‹ልክ ነው ጌታዬ የኒውፋውንድ ላንድ የሰዓት አቆጣጠር ከግሪንዊች
የሰዓት አቆጣጠር  ሶስት ሰዓት ተኩል ወደ ኋላ ይዘገያል፡››

‹‹መቼም የአየር መንገዶችን የጉዞ መርሃ ግብር ለሚያዘጋጁ ሰዎች ይህ  የሰዓት አቆጣጠር  ችግር
ሳይፈጥርባቸው አይቀርም፡፡ ባህር ላይ ለማረፍ ምን
ያህል ሰዓት ይቀረናል?›› ሲል ጠየቀ መርቪን

‹‹ከግማሽ ሰዓት በኋላ እናርፋለን፡ ከመርሃ ግብሩ አንድ ሰዓት ጉዟችን
የዘገየው በወጀቡ ምክንያት ነው›› አለና አስተናጋጁ በሩን ዘግቶ ወጣ፡

ናንሲ በሩ ከተዘጋ በኋላ ‹የመስኮቱን መጋረጃ ክፈተው፡ ነግቷል››
አለችው:፡ መርቪን ቡና ሲቀዳ የትናንት ምሽት አዳራቸው ፊቱ ላይ መጥቶ
ድቅን አለ፡፡ ወጀቡ በተነሳ ቁጥር መርቪን እጇን የሚይዛት፣ ወለሉ ላይ
የሚወድቁት፣ የመርቪን እጆች ጡቶቿን ሲጨብጥ፣ አይሮፕላኑ ሲናወጥ፣
እሱ ደረት ላይ ልጥፍ የምትለውና እየደባበሰ የሚያስተኛት ትዝ አላት:
ይህን ሰው በጣም ወድጄዋለሁ› አለች በሆዷ።

‹‹ቡና እንደወረደ ወይስ ከወተት ጋር ነው የምትፈልጊው?›› ሲል
ጠየቃት፡፡

‹‹ጥቁር ቡና ይሁንልኝ፡ ስኳር አልፈልግም››
‹‹እንደ እኔ›› አለና ቡናዋን አቀበላት ናንሲ አመስግና ቡናዋን ጠጣች፡፡

ናንሲ ስለ መርቪን በደንብ ማወቅ ፈለገች፡፡ ቡናውን እየጠጣ ስለእሱ ልማዶች ግምቷን አስቀመጠች፡፡ ቴኒስ ይጫወታል፣ ልብ ወለድ ብዙ ማንበብ አይወድም፣ ገበያ መሄድም እንደዚሁ፣ ቁማር ጨዋታ የሚሳካለት ይመስላል፣ ዳንስ ግን የሚችል አይመስልም፡፡›
‹‹ምንድን ነው የምታውጠነጥኚው?›› ሲል
ጠየቀ ለሕይወት  ኢንሹራንስ አደገኛ እንደሆንኩ አድርገሽ የምታይኝ መሰለኝ፡፡››

ናንሲ ቀልዱ አሳቃት፡፡ ‹‹ምን አይነት ሙዚቃ ነው የምትወደው?›› ለሙዚቃ ጆሮ አልሰጥም›› አለ ‹‹መደነስ ባልጠላም ጥሩ ደናሽ ግን አይደለሁም፡፡ አንቺስ?››

እኔ ድሮ ደንሼያለሁ፡መደነስም ነበረብኝ፡፡ እሁድ እሁድ ሱፍ ከሚለብሱ ወንዶች ልጆች ጋር በዳንስ ትምህርት ቤት ዳንስ እማር ነበር፡፡ከላይኛው መደብ የቦስተን ማህበረሰቦች ጋር ለመግባባት ብቸኛው መንገድ ይህ ብቻ እንደሆነ እናቴ ትነግረኝ ነበር፡ እኔ ግን ከዛ ማህበረሰብ ውስጥ
ብገባ ባልገባ ግድ አልነበረኝም፡: የኔ ቀልብ ያለው ከአባቴ ፋብሪካ ጋር ነው፡፡ እናቴ ደግሞ ይሄን ባህሪዬን አትወደውም ነበር፡››

ሁለቱ አዲስ ፍቅረኛሞች ተያዩ፡፡ መርቪንም ትናንት ማታ እንዴት ሲላፉና ሲላላሱ እንዳመሹ እንደሚያስብ ነቃችበት፡፡ ይህም ሀሳብ እፍረት
ውስጥ ከተታትና ፊቷን ወደ መስኮቱ ስታዞር መሬት ታያት፡፡ አይሮፕላኑ
ቦትውድ ሲያርፍ ህይወቷን የሚለውጠውን የስልክ ጥሪ ማድረግ እንዳለባት ትዝ አላት፡ ‹‹ደርሰናል›› አለችና ከመኝታዋ ዘላ ተነሳች ‹‹ልብሴን ልልበስ›› አለች፡፡
‹‹እኔ ቀድሜ ልውጣ›› አለ መርቪን ‹‹ለአንቺ ጥሩ ነው››
እሺ፧ አሁንስ ምን ቀልብ አለኝ አለች በሀሳቧ። ይህን ለእሱ አልነገረችውም፡፡ መርቪን ልብሱን ስበሰበ፡፡ በሩን ከፍቶ ሊወጣ ሲል
ተጠራጠረና ቆመ፡፡ እሷም እንደገና ሊስማት እንደፈለገ አውቃ ወደ እሱ ሄደችና ከንፈሯን ሰጠችው፡፡ ‹‹ሌሊቱን በሙሉ እቅፍ አድርገህ ስላስተኛኸኝ
አመሰግንሃለሁ›› አለችው:

መርቪን ከአንገቱ ዝቅ አለና ሳማት፡፡ አሳሳሙ ልስልስ ያለ ነበር፡ አፏን በአፉ ግጥም አድርጎ ነው የሳማት፡፡ እየተሳሳሙ ትንሽ ቆዩና ተላቀቁ፡፡

ናንሲ በሩን ከፍታ ያዘችለትና ወጥቶ ሄደ፡፡

በሩን እንደዘጋች የደስታ ሲቃ ተናነቃት፡ ከዚህ ሰው ፍቅር ሊይዘኝ ነው አለች፡ በመስኮቱ ስታማትር አይሮፕላኑ ቀስ በቀስ እየወረደ ነው፡፡

መፍጠን አለባት፡፡

መስታወቱ ፊት ቆማ ፀጉሯን ቶሎ አሰረችና የመዋቢያ ዕቃዎቿን ይዛ የሙሽሮቹ ክፍል አጠገብ ወደሚገኘው ወደ ሴቶች መታጠቢያ ቤት ሄደች፡፡እዚያ ሉሉ ቤልንና አንድ ሌላ ሴት አገኘች፡፡ የመርቪን ሚስት ግን የለችም:

ናንሲ ፊቷን እየታጠበች ጧት ከመርቪን ጋር ያደረገችውን ውይይት
አስታወሰች፡፡ እሱን ስታስብ ደስታ ቢሰማትም ደስታው የተሟላ ባለመሆኑ
ከጭንቀት ሊገላግላት አልቻለም፡፡ ስለሚስቱ ምንም አላለም፡፡ ትናንት ማታ ስለእሷ ስትጠይቀው ድንግርግር እንዳለው ነው የነገራት፡፡ ከዚያ በኋላ ግን
ይወዳት ይሆን? ትናንት ማታ ሌሊቱን ሙሉ ደረቱ ላይ ለጥፎ ነው ያሳደራት ይህ ብቻውን ጋብቻን ይፍቃል ማለት ግን አይደለም፡
እኔ የምፈልገው ምንድን ነው? ስትል ራሷን ጠየቀች፡፡ ‹መርቪንን እንደገና ማግኘት እፈልጋለሁ ከእሱ ጋር ድብቅ ወዳጅነት  ልመስርት?ታዲያ ለኔ ብሎ ጋብቻውን እንዲያፈርስ እፈልጋለሁ? ከአንድ  ሌሊት
ወሲባዊ ልፊያና መሳሳም በኋላ ይህን እንዴት ማወቅ እችላለሁ?
ሊፕስቲክ ለመቀባት መስታወቱ ላይ አፈጠጠች ናንሲ መጠራጠርሽን አቁሚ
ስትል ለራሷ አሳሰበች እውነታውን ታውቂዋለሽ፤ ይሄን ሰው በጣም ፈልገሽዋል፧ ከአስር ዓመት ወዲህ እጅሽን የሰጠሸው ለዚህ ሰው ነው፡:
አሁን አርባ አመትሽን ደፍነሻል፡ አሁን ተገቢውን ሰው አግኝተሻል፡ እዚህ
እዚያ መርገጥሽን ትተሽ ይህን ሰው በእጅሽ አድርጊ፡፡›

ሰውነቷ ላይ ሽቶ አርከፈከፈችና ወጣች፡

ስትወጣ ከመታጠቢያ ቤቱ አጠገብ የተቀመጡትን ናት ሪጅዌይና ወንድሟን ፒተርን አገኘቻቸው ናት ‹‹ደህና አደርሽ ናንሲ›› አላት::

ይህን ስትሰማ ከአምስት ዓመት በፊት በዚህ ሰው የነበራትን ስሜት
አስታወሳት፡፡ እኔ ከእሱ ፍቅር ይዞኝ ነበር፡፡ እሱ ግን ከእኔ ይልቅ የፈለገው
ብላክ ቡትስ ኩባንያን ነበር፡፡ አሁንም ኩባንያውን በእጁ ለማስገባት
የሚፈልገውን ያህል እኔን አይፈልገኝም፡፡ ለሰላምታው በራስ ንቅናቄ ብቻ
አፀፋዊ ሰላምታ ሰጥታው ወደ ክፍሏ ሄደች፡፡

አስተናጋጆቹ መኝታዎቹን ወደ ሶፋነት ለውጠዋቸዋል። መርቪን ጢሙን ተላጭቶና በነጭ ሽሚዝ ላይ ሱፍ ልብሱን ለብሶ ሶፋ ላይ ቁጭ ብሏል፡፡ ‹‹በመስኮት ተመልከች ደርሰናል›› አላት፡፡
👍19
#ባል_አስይዞ_ቁማር


#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

..ይገርማል እሱ በማንኛውም አእምሮዋ በሚያመርታቸው ሀሳቦች ውስጥ የሆነ ቦታ ፈልጎ ተሸንቅሮ ሲወጣ ነው የምታየው....ስለሰማይም ታስብ ስለምድር…ስለእግዚያብሄር ይሁን ስለሰይጣን እሱ አለበት….፡፡.ደግሞ በሀሳቧ ብቻ አይደለም በህልሟም ጭምር እንጂ…..ህልሟ እኮ ስለ ምንም ሊሆን ይችላል ብቻ እሱ አለበት…ለምሳሌ እሷ እናቷ  መኝታ ቤት አልጋዋ ላይ ወጥታ ፀጉሯን ስትዳብሳት በህልሟ ብታይ እሱም ወይ በመስኮት ተደብቆ ሲያያት..ወይ ደግሞ እራሱን ወደቢራቢሮ ቀይሮ ክንፉን እያማታ መጥቶ ግንባራ ላይ ሲያርፍ ታየዋለች፡፡ይሄ ሁሌ ለራሷም ሳታስበው ግርም ይላታል፡፡እንዴት የሆነ ቦታ ላይ አትረሳውም…እንዴት የሆነ ሀሳብ አሰናድታ አጣጥፋ ስትጨርስ ድንገት ከሆነ ቦታ ተስፈንጥሮ መጥቶ ከላይ በቀላሉ ይደረባል…?ይሄ እንግዲህ በዚህ ከተማ በዚህ ቤት ውስጥ ሲኖር ነበር..አሁንስ ሁሉን ነገር ጣጥሎ ከሄደ በኃላ…….ምንድነው የምትሆነው?የቀንም ሆነ የሌት ህልሟ እንደሆነ ይቀጥላል? ከቀጠለስ እንዴት ልትቋቋመው ትችላለች?
እጇን ዘረጋችና አጠገቧ የተኛችውን የጊፊቲ ሆድ ላይ በቀስታ አሳረፈች…ጊፍቲም ከትራሷ ገልበጥ አለችና ፊቷን ወደእሷ ዞራ በሀዘኔታ አየቻት፡፡
‹‹ምን አለ እኔም እንደአንቺ ለቃልዬ አርግዤ ቢሆን…ማለት ልጅ አስረግዞኝ  ጥሎልኝ ቢሄድ?››
‹‹እኔም አንድ ነገር ልንገርሽ…››
‹‹ምንድነው ንገሪኝ››
‹የቃልዬን እስከ ወዲያኛው ጥሎኝ መሄድን ስሰማ ወደውስጤ ከመጣው የፀፀት ሀሳብ አንዱ ምን አለ ይሄ የፀነስኩት ልጅ የቃልዬ በሆነ የሚል ነበር..እርግጥ መድህኔ በጣም ጥሩ ኃላፊነት የሚሰማው መልካም አባት እንደሚሆን አውቃለሁ…እሱን ስላገኘሁም እራሴን እንደእድለኛ ነው የምቆጥረው…የልጅነት ህልሜንና  የዘመናት ፍላጎቴን ሁሉ ሊያሞላልኝ የሚችል ሰው ነው…ግን መድህኔን የማፈቅርበት ጥልቀት የኩሬ ያህል ሲሆን የቃልዬ ግን ውቅያኖስ አይነት ነው..እና ለዛ ነው እንደዛ ልመኝ የቻልኩት››
ዝም ብዬ ፈዛ አየቻት..ይሄን የተናገረችው ከቀናቶች በፊት በሰላሙ ጊዜ ቢሆን ኖሮ በርግጠኝነት ልዩ አንገቷን ፈጥርቃት ልትገላት ሁሉ  ትችል ነበር..አሁን ግን ያንን ማድረጉም ብቻ ሳይሆን እንደዛ አይነት ስሜት ማስተናገዱም ጥቅም አልባ እንደሆነ ተረድታለች....በዛ ለይ በመንፈስም ሆነ በስጋዋ ደንዝዛለች…
‹‹ግን ከቃልዬ ይሄን ሁሉ አመት ሳታረግዤ እንዴት በዚህች በጥቂት ወራት ከመድህኔ ልታረግዢ ቻልሽ?፡፡››
‹‹ከቀል ጋር በትንፋሽ ነው ማረግዘው?…››
‹‹ማለት….?››
‹‹እኔና ቃል እኮ  ወሲብ ፈፅመን አናውቅም››
‹‹ማለት…ብዙ ቀን እኮ እሱ ጋር አድረሽ እንደወጣሽ… ሲያደክመኝ እንዳደረ ምናምን እያልሽ ስትጎሪርብኝ ነበር››
‹‹ፈርቼሽ ነዋ…..ቃልዬን እንዳትመኚውና እንዳትቀሚኝ ..ተስፋ ላስቆርጥሽ ብዬ ነው…ማለት ከአመታት በፊት  አብሬው ብዙ ጊዜ አድር ነበር..በኃላ ግን ዝም ብሎ ማደሩ ስቃይ ስለሆነብኝ ወስኜ አቆምኩ…..››
‹‹አረ የምን ጉድ ነው..ቆይ ለምን…..?››
‹‹ምነው ገረመሽ..አንቺስ ከመድህኔ ጋር ለምን;?››
‹‹እኔ እንጃ ብቻ የእናንተን በጣም ደጋግሜ ስላመነዠግኩት ነው መሰለኝ አልተዋጠልኝም…››
‹‹መድህኔን ስለወደድኩት..ወይም ቃልዬ ሀብታም ስላልሆነ ይመስልሻል ከቃልዬ ጋር አቋርጬ ከመድህኔ ጋር የሆንኩት ነው  ወይስ አንቺ ስላለስፈራራሺኝ…?››
‹‹እና ለምንድነው?››
‹‹ሳላውቅ ድንገት ከመድህኔ ጋር ተሳሳትኩና ወሲብ ፈፀምኩ..ድንግልናዬን አስረከብኩት ….ወደቃልዬ ጋር እንዴት ልመሰለስ .. ?ሌላ ሰው ቢሆን ችግር የለውም ቃልዬ ግን?
‹‹ቃል ምን ይልሻል..?ምንም አይልሽም እኮ ነበር አንደውም በግልፅ ነበር ይቅርታ የጠየቀሽ፡››
‹‹አውቃለሁ ..ችግሩም እሱ ነው….እኔ በአእምሮው ካለሁበት ቦታ ተንሸራትቼ ወርጄያለሁ.ቃልዬ...የወርቅ ካባ አድርጎ  በብር የተለበጠ  ጫማ ተጫምቶ ወደቤቴ ሲመጣ ውስጤ በሀሤት ትደንሳለች ...ድንግልናዬን በክብር ልሰጠው ለዘመናት ጎጉቼያለሁ ።.እሱ ፍጽም ድንግል እንደሆነ አውቃለሁ.....ማወራሽ ስለስጋዊ ድንግልና አይደለም….ለዛ ግድ የለኝም...ልብ ከቆሻሻ ሀሳብ ጋር ያልተዋሰበ ንፅህ ፤ከክደትና ከማጭበርበር ጋር ያልተጋደመ  ክብር  ነው ።ለዚህም ማረጋገጫው እስሬ ሆኖ ሲያወራኝ  ልቤ ውስጥ ብርሀን ሲፍለቀለቅ ይታወቅኛል….የሆነ አካሉ የሰውነቴን ጫፍ ሲነካው ነፍሴ ድረስ የሚዘልቅ ደስታ ይሰማኛል……ድንገት አግኝቼው  ሰላም ሊለኝ  ከንፈሩ ጉንጬን በስሱ ሲነካው እንኳን .....ከልቤ  የፍቅር ደም ሲንጠባጠብ ይሰማኛል ...
‹‹ከዚህ በፊት ስለእሱ ምን እንደሚሰማኝ ነግሬሽ ነበር …? የእኔን ስሜት እኮ ነው እየነገርሺኝ ያለሽው…››
‹‹አየሽልኝ..ቃልዬ ማለት እንዲህ ነው..ሁለት ሴቶችን ጫፋቸውን ሳይነካ በተመሳሳይ የእብደት በሚመስል ስሜት አንዲያፈቅሩት ማድረግ የሚችል የተለየ ሰው ነው፡፡እሱ ለእኔ መስታወቴ ነው.. ፊት ለፊቴ ተቀምጦ በተመስጦ  ሳየው በጥልቀት ርቄ ሄዳለሁ…. እያንዳንዷን የልጅነት ጊዜዬን በምልስት አስታውሳለሁ… ሀዘኔንና ደስታዬን መልሼ አጣጥማለሁ…. እንዴት እንደተሰራው…? የት ጋር  ማደግ እንደጀመርኩና? የት ጋር ደግሞ እንደተሰበርኩ? ሁሉ እንዳስታውስ ያደርገኛል…እናም በዛ ምክንያት ቃልዬን ሳገኝ  ነፍሴ ሀሴት ታርጋለች…ውስጤ ይፍነከነካል..፡፡ግን ይሄ ስሜት ሁሌ አይደለም የሚያስደስተኝ ..አንዳንዴ ትናንቴ ፈፅሞ የሚያስጠላኝ ጊዜ አለ..አንገቴን ወደኃላ አዙሬ አይኖቼን ትናንቴ ላይ ተክዬ ማሰላሰል የሚያስከትልብኝን ህመም መቋቋም አቅም በማጣበት ጊዜ እሱን ለማግኘት ከራሴ ጋር ትግል እገባለሁ  …ምክንያት ፈጥሬ እሸሸዋለሁ….
ግን የሰዓታ ክፍተት እንኳን መቆየት ተስኖኝ  ግራ ይሁን ቀኝ ልቤ ላይ ብቻ በማለውቀው ቦታ በሆነ የልቤ ክፍል ብቸኝነት  ይለበልበኛል…መለብለብ ብቻም ሳይሆን እብጠትና ጥዝጣዜም አለው…ግን ደግሞ መቻል እስከምችል ደረስ እችለዋለሁ…ለአንድ ወይም ለሁለት ቀን..ከዛ መተንፈስ ሲያቅተኝና ከአቅሜ በላይ ሲሆን ያለምን ማቅማማት ወደ አለበት በርሬ እሄዳለሁ ፡፡ፊቱ እገተራለሁ…የተጨማደደ ፊቱ በደስታ ፀደል ሲፈካ…ተከርችሞ የነበረ ጥርሶቹ ተፈልቅቀው  መሳቅ ሲጀምሩ አይና እደሰታለሁ....ተንደርድሬ ሄጄ እንጠለጠልበታለሁ….ያለምንም ቅሬታና ወቀሳ ወደላይ አንጠልጥሎ ልክ እንደእርግብ በአየር ላይ ያንሳፍፈኛል…..እና አሁን ያ የልጅነተ መስታወቴ ነው የተሰነጣጠቀዉ… የትዝታ ድልድዬ ነው ተንዶ የተሰበረው…..ወደትናንቴ ለመሻገር በጣም ይከብደኛል….ግማሽ  ሆኜያለሁ
‹እውነትሽን  ነው…..አሁን ሳስበው ቢነካንስ ኖሮ…ማለቴ ያው ነካክቶን ጥሎን ሂዶ ቢሆንስ..?››
‹‹እሰከ መጨረሻ ያበቃልን ነበራ…››ብላ መለሰችላት፡፡
‹‹እኔ እኮ አሁንም እስከመጨረሻው ነው ያበቃልኝ…›
‹‹ቆይ ግን ወደ ወሬሽ ልመልስሽና..ቃልዬንም እኮ ከዚህ በፊት ማለቴ አንቺ ከመድሀኔ ጋር ተገናኝተሸ ከመጀመርሽ በፊት ስለሁለታችሁ ግንኙነት ጠይቄው ነበር…››
👍8810😁1
​​#ተአምረተ_ኬድሮን


#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
//
ሰሚራ ለዚህ ሀሳብ ውል ሳታበጅለት ማደር አልፈለገችም….. ቦርሳዋን አንጠልጥላ ተመልሳ ወደስራዋ ቦታ ተመለሰች….መመለሷ ምን እንደሚጠቅማት ለራሷም አልገባትም ..ግን በቃ ተመለሰች..እንደደረሰች ቀጥታ መላኩ ወደተኛበት ክፍል ነበር የገባችው…በሽተኛው የተኛበት ክፍል ውስጥ የተኙ ሌሎች ሶስት ታካሚዎችና እነሱን የሚያስታሙም  አስታማሚወች  ነበሩ…
ቀጥታ ወደተኛበት አልጋ ተጠግታ አስተዋለችው…አይኖቹ እንደተጨፈኑ ናቸው… ጥቁር ፊቱ ላይ የሰላምና የመረጋጋት መንፈስ አርብቦበታል…በታዋቂ ቀራፂ በጥንቃቄ የተቀረፀ የሚመስለው አፍንጫው ለፊቱ ውበት አጎናጽፎት ትልቅ ግርማ ሞገስ ሆኖታል…የዓይኖቹ  ሽፋ ሽፍቶች ድምቅ ያሉና የተለየ ስሜት የሚያጭሩ ሆነው ነው ያገኘቻቸው..
‹‹እንዴ እስከዛሬ ለምን እንደዚህ እትኩሬ አላስተዋልኩትም…..?›› ስትል እራሷን ጠየቀች ….እስከዛሬ ባለ እይታዋማ ከማንኛውም በሽተኛ የተለየ  ምንም ነገር አልነበረውም….አሁን ግን ሁኔታዎች ተቀያይሩባት..አሁን ስሩ ቆማ የምታየው  ጥቁር ቆንጆ ወጣትን ለመግደል ግማሽ ሚሊዬን ብር ተቀብላለች…ስለዚህ አሁን ለእሷ ዝም ብሎ ሰው አይደለም….‹‹ደግሞ እንዴት አባቱ ነው የሚያምረው  ….…..?››አለችና ክፍሉን  ለቃ ወጣች …
ወደ ዶክተር እስክንድር ቢሮ …ዶ/ር እስክንድር በእሷ እድሜ ክልል የሚገኝ አስተዋይ ወጣትና ጓደኛዋ ነው ..ይሄንን ነገር በምትፈልገው መጠን ሊረዳት እንደሚችል  ያሰበችው  እና ሚስጥር ጠባቂ ነው ብላ ያመነችው እሱን ነው፡፡እሱን ብቻ፡፡

ቢሮው ብቻው ቁጭ ብሎ የበሽተኞችን ፋይል እየመረመረ ነበር ያገኘችው….

‹‹እንዴ ወደቤት የሄድሽ መስሎኝ?››

‹‹ሄጄ ነበር››

‹‹ታዲያ ምን ገጠመሽ እና ተመለሽ…?››

‹‹ታአምር ተፈጥሮ››

‹‹እስቲ ቁጭ በይ እና ተአምሩን ንገሪኝ .››

በድካም ስሜት ከፊት ለፊቱ ያለውመን ወንበር ስባ ቁጭ አለች….

‹‹እሺ አጫውቺ……..?ምን ተፈጠረ…..?››

‹‹እንድታግዘኝ ነው የመጣሁት… በጣም እርዳታህን እፈልጋለሁ…››

‹‹አልገባኝም ምንድነው የምረዳሽ…..?››

‹‹ልናግር አይደል››

‹‹እያዳመጥኩሽ ነው››አላት ትኩረቱን ሰብስቦ ተመቻችቶ እየተቀመጠ

ከሰዓታት በፊት ያጋጠማትን እና እያበረረ ወደእሱ ያስመጣትን ጉዳይ ከመጀመሪያው አንስታ በዝርዝር አስረዳችው…በገረሜታ አፉን ከፍቶ አዳመጣት…ስትጨርስ
‹‹ወይኔ ጉዳችን.!!!.እንዴት ቼኩን ትቀበያለሽ…..?››

‹‹አልቀበልም ብል ዝም ሚሉኝ  ይመስልሀል…ሚስጥራቸውን እንደማጋልጥባቸው ስለሚጠረጠሩ ሊያጠፍኝ ይችላሉ ብዬ ፈራኋ…››. 

‹‹እሱስ ትክክል ነሽ …ለገዛ ዘመዳቸው ያላዘኑ ላንቺ አይመለሱም…..እና ምን እናድርግ›መልሶ እሷኑ ጠየቃት፡፡

‹‹እርዳኛ››

‹‹እኮ እንዴት ልርዳሽ…?››

‹‹እኔ እንጃ›› 

ትኩር ብሎ በጥርጣሬ አይን አይኗን እየያያት ቆየና‹‹…ልጅን እንዲሞት ትፈልጊያለሽ እንዴ….?ማለቴ በመግደል እንዳግዝሽ ነው የምትፈልጊው…..?››ሲል ጠየቃት

‹‹አረ በአላህ…..!!እንዴት እንደዛ አሰብክ..…..?››

‹‹እኔ እንጃ… ምን አልባት ብሩ ብዙ ስለሆነ….››ንግግሩን አላስጨረሰችውም

‹‹የፈለገ ብዙ ብር ቢሆን ይህን ለግላጋ ጥንቅሽ  ወጣት ለመግደል ጭካኔውን ከየት አመጣለሁ…..?››

‹‹እንዴ ለግላጋ ወጣት ነው ያልሺኝ..…..? ቆንጆ ነው እንዴ..…..?››

ከንግግሩ ተነስታ የተናገረችውን ነገር በምልሰት ስታስታውስ  እፈረት ተሰምቷት ‹‹….አንተ ደግሞ በዚህ ሰዓት እንዲህ አይነት ቀልድ ይቀለዳል…..?››አለችው 

‹‹ቀልድ እኮ አይደለም ..አንቺው ስላልሽ ነው…ለግላጋ ባይሆን እንዲሞት ትፈቅጂ ነበር ማለት ነው.…..?ንግግርሽ እኮ እንደዛ የምትይ ነው የሚመስለው››

‹‹ይሁንልህ እስቲ አሁን እንዴት እናድርግ….…..?››

አምስት ለሚሆኑ ደቂቆዎች ሁለቱም በየፊናቸው አሰብ …ከዛ ደ/ር እስክንድር ከሀሳቡ ባኖ በፈገግታ መናገር ጀመረ‹‹…አሪፍ ሀሳብ መጣልኝ ››

‹‹ምን አይነት ሀሳብ ንገረኝ……..?.››
‹‹አሁን አልነግረሽም… መጀመሪያ እራት ጋብዢኝ››

‹‹ንገረኝና ጋብዝሀለሁ…..?››

‹‹እዚህ አልነግረሽም… በዘመናችን ምንም   በነፃ የሚሰጥ ነገር የለም….ሁሉም ነገር ያስከፍላል…ስለዚህ ጋብዢኝና ልንገርሽ ወይም ደግሞ ይቅርብሽ››

‹‹ይሁንልህ እሺ … አሪፍ ምክር ይሁን እንጂ  በደስታ ጋብዝሀለሁ››

‹‹አይ አንቺ ብዙ ቀን ጋብዢኝ ብዬሽ አሻፈረኝ ብለሽ ነበር..ዛሬ እጄ ገባሽ›››

‹‹ስለተሳካልህ እንኳን ደስ ያለህ››አለችውና ተያይዘው ወጡ
እራት በልተው እንዳጠናቀቁ ያሰበውን ይነግራት ጀመር

‹እንግደለው››

‹‹ምን አይነት ብሽቅ ሀሳብ ነው››
‹‹ማለቴ  ለተወሰኑ ደቂቃዎች የሞተ እንዲመስል እናደረግና መሞቱን አይተው እንዲያምኑ እናድርግ››
ከቁጣዋ መለስ ብላ‹‹ከዛስ?››ስትል በጉጉጉ ጠየቀች፡

‹‹‹ከዛማ በቃ ሳጥን አምጡ እንላቸውና የሆነ ነገር አሽገን እንሰጣቸዋለን….››

‹‹ከዛስ…?››

‹‹ከዛማ ሰውዬውን የሆነ ቦታ ወስደን እስኪድን እንጠብቅና ለምን ሊገድሉት እንደፈለጉ ከራሱ እናጣራለን…ከእሱ በምናገኘው መረጃ የሆነ ነገር እናደርጋለን…ወይም እራሱ ሲድን የሆነ ነገር ያደርጋል››

ተነስታ ተጠመጠመችበት ‹‹..እንዲት ይህ  ሀሳብ መጣልህ?››

‹‹እድሜ ለሆሊውድ ፊልም …ሊዚህ ለዚህ ካልተጠቀምንበት ለምን ይጠቅመናል?››

‹‹እና መቼ እናድርገው…››
ነገ ተነጋግረን የሚሆነውን እናደርጋለን››

ይቀጥላል
👍12917😁5😱2👎1
#ትንግርት


#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


ዶ/ር ሶፊያ የተኛችበት ሆስፒታል አልጋ ላይ ሆና በኤልያስ በኩል ከትንግርት የተላከላትን ዲያሪ ማንበብ ጀመረች፡፡

ጥቅምት 25 1999ዓ.ም

የሁለተኛ አመት የዩኒቨርሲቲ ትምህርት ከጀመርን አንድ ወር ሊሞላን ነው፡፡አምና ፍቅረኛ ነበረኝ፡፡ጌዲ ከኔ ጋር ነበር..አሁን ግን ብቻዬን ነኝ፡፡ቢሆንም ምርጥ የሴት ጓደኛ ማግኘት ችያለሁ፡፡ሶፊያ ትባላለች፡፡አንድ ዶርም ነው የምንጋራው፡፡እርግጥ ሌሎች አራት ልጆችም አብረውን ይኖራሉ..በአርባ ምንጭ ሙቀት አንድ ዶርም ውስጥ ስድስት ሰው ታጭቆ መኖር ይከብዳል..ቢሆንም እየኖርን ነው፡፡

ሶፊ የምትገርም ልጅ ነች…የተወለደችውም ያደገችውም አሜሪካ ነው፡፡ በዲሞሽን ወደ

ኢትዬጵያ ከተወረወረች ሶስተኛ አመቷ ነው፡፡ አንድ አመት ሃይስኩል የተቀሩትን ሁለት ዓመት እዚህ ዩኒቨርሲቲ እንዳሳለፈች አጫውታኛለች፡፡

ስለእሷ ሳስብ ሚገርመኝ የኢትዬጵያ ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ውጭ ለመላክ አፈር ድሜ ይግጣሉ..የእሷ ወላጆች እሷን ባህሏን እረሳች..ፀባዮ ተበላሸ ...መረን ለቀቀች በሚል ሰበብ ወደ ኢትዬጵያ ላኳት..ልክ እንደ ፀባይ ማረሚያ..አይ ሚስኪኗ ሶፊያ፡፡

ህዳር-5 1999 ዓም

ከሶፊ ጋር ዛሬ ወደ ከተማ ወጥተን ነበር..ሲቀላ ፡፡ ዋናው የሄድንበት ምክንያት አባቷ ከአሜሪካ ዶላር ልኮላት ስለነበር ያንን ለመቀበል ነው፡፡ አንድ ሺ ዶላር ነበር የላከላት፡፡ከዛ ምሳ ጋበዘችኝ..ወይን ጠጣን…ለእሷ አንድ ሱሪ ብቻ ስትገዛ ለእኔ ሁለት ሱሪና ሁለት ቀሚስ ገዛችልኝ፡፡ግርም ነው ያለኝ፡፡ ማነው ለጓደኛው እንዲህ የሚያደርገው…?በዛ ላይ የእሷን ያህል አይሁን እንጂ እኔም ከውጭ በሚላክ ዶላር የምማር ልጅ ነኝ፤ሌላው ደግሞ አንድ ደርዘን የሚያማምሩ ፓንቶች ገዛችና ስድስቱና ለእኔ ስድስቱን ለራሷ ወሰደች፡፡በእውነት የዋህ ነች እንዳልል ለሌሎች ጓደኞቿ እንደዛ ስታደርግ አይቼት አላውቅም፡፡ብቻ እኔ ወደድኳት፡፡ጥሩ ጓደኛዬም አድርጌ ከልብ ተቀብዬታለሁ፡፡

ህዳር 29 1999 ዓ ም

የሚቀርቡን የዩኒቨርቲ የወንድ ጓደኞቻችን ከተማ ካልወጣን አሉን፡፡አስር ሆነን ወጣን.... አራት ሴት ስድስት ወንድ፡፡ከግቢ ስንወጣ እራሱ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ሆኖ ነበር፡፡ከግቢ በታክሲ ሲቀላ... ከሲቀላ ደግሞ ሼቻ አመራን፡፡ በመጀመሪያ ወደ በቀለ ሞላ ሆቴል ነው ያመራነው፡፡፡

ሆቴሉን ጥለን ወደ ጓሮ አለፍንና ውጭ ወንበር ከበን በመቀመጥ እራት አዘዝን፡፡ከፍታ ቦታ ላይ ያለው የበቀለ ሞላ ሆቴል ወደ ታች የነጭ ሳርን የተንጣለለ ደን፤ በእግዜር ድልድይ የተከፈሉትን አባያና ጫሞ ሀይቅን፤ በግሩም

ሁኔታ ማየት የሚያስችል እስትራቴጂካዊ ቦታ ላይ ነው የታነፀው ..ከዛ ከዝቅታው የተፈጥሮ ሙዚዬም ወደ ላይ ሚነፍሰው ቀዝቃዛና ነፋሻማ አየርም ልብን ስውር ያደርጋል፡፡ እራታችንን በልትን ስናጠናቅቅ እና የበቀለ ሞላን ሆቴል ለቀን ስንወጣ 2፡45 ሆኖ ነበር፡፡ ቀጥሎ ሞቅ ወዳለው ጫሞ ሆቴል ነው የገባነው፡፡በተለያ አጋጣሚዋች ሶስት ቀን እዚህ ቤት መጥቼያለሁ....በተለይ ከጊዲዬን ጋር የመጣሁባቸው ሁለት ቀናት አይረሱኝም፡፡

መጠጥ መጠጣት በቢራ ነው የተጀመረው፡፡ ጨወታው፣ ተረቡ ደስ ይል ነበር፡፡ በተለይ የሶፊ ደስታ ልዩ ነበር፡፡በፊትም እኔ ስለማጣጥልባት እንጂ እንዲህ አይነት ቸበርቻቻ ነፍሷ ነው፡፡ ..አራት ሰዓት አካባቢ መቀመጫው ላይ ማንም አልነበረም፡፡ ሁሉም በሙዚቃ ምት በመታገዝ ጭፈራውን እየቀወጠው ነው፡፡አንዳንዱም መጠጡን ከቢራ ወደ አልኮል ቀይሮታል….. እየሰከረ ያለም አለ፡፡ወንዶቹ የመረጧትን እና ቀልባቸውን የተመኛት ሴት ዙሪያ ይሽከረከራሉ… ይጎነታትላሉ ...ይጀነጅናሉ፡፡

ሁለቱ ሴቶች ከሁለቱ ወንዶች ጋር ተግባብተው እየተላላሱ ነው፡ኃይሌ የሚባል የመቀሌ ልጅ እኔን እየጀነጀነኝ ነው..በጣም ያምራል..፡፡ለምን እንደሆነ አላውቅም ይሄን ልጅ ካወቅኩት ቀን ጀምሮ የሆነ ነገሩ ይመቸኛል፡፡እና እንዲሁ በሴትነቴ እግደረደራለሁ እንጂ ቀልቤ ፈቅዶታል..፡፡እሱም እየተግደረደርኩ መሆኔ ገብቶት መሰለኝ ጥረቱን አጠናከረ..ቀስ በቀስ እየደከምኩለት መጣሁ..<በቃ ዛሬ አብሬው ማደሬ ቁርጥ ነው› ስል አስቤ ነበር በውቅቱ ፡፡ ባዛ ላይ ከጌዲዬን ከተለያየው ስድስት ወር ሆኖኛል ...ስድስት ወር ሙሉ ምንም አላገኘሁም ..በጣም አምሮኛል፡፡

ሶፊያ ሶስት ወንዶች እየተሻሙባት ነው፡፡የሆነ ሙድ እየያዘችባቸው መሰለኝ፡፡እዚህኛው ላይ ትንጠለጠላለች.... ያኛውን ትጠቅሰዋለች.. ደግሞ ከዛኛው ጋር ትጎነታተላለች፡፡በመጨረሻ ጓደኛ የሆኑት ሶስቱ ወንዶች እርስ በርስ
መገለማመጥ ጀመሩ…..ስድስት ሰዓት ሲሆን

ሁላችንም በስካር ጥንብዝ ብለን ሆቴሉን ለቀን

ወደ ቤርጓችን ሄድን ፡፡አምስት ክፍል በመደዳ
ነበር የተያዘው፡፡እንዲህ እንዲሆን የወንዶቹ
ዕቅድ ነው ፡፡ዕድል የቀናቸው አራቱ ወንዶች
አንዳንድ ሴት ይዘው ይተኛሉ ምስኪኖቹ ሁለት ወንዶች የቀረችው አንድ አልጋ ላይ አብረው ያድራሉ.. በሚል ስሌት ነበር የተሰላው፡፡....
.......................


እዚህ ጋር ከደረሲው እውቅና ውጪ ቢሆንም ለአንባቢው የሚጎረብጡ ሐሳቦች የተነሱበት ክፍል ስለሆነ ቆርጬ አውጥቼዋለሁ  ለምን ተቆረጠ  የሚልም አይጠፋምና ከወዲሁ ይቅርታ እጠይቃለሁ



........"በየጓዲያችን ቀስ በቀስ እየገባ ያለ ነገር ሆኖ ሳለ ቃሉን አናንሳ ..ጭራሽ በጆሮችን አንስማ ማለት አግባብም አይደለም አያዋጣንምም ብዬ አምናለሁ ፡፡

ይልቅ ችግሩ በቤታችን አለ...? አዎ አለ ፡፡… አግባብ ያልሆነ እና መቅረት ያለበት አካሄድ ነው ወይ..? አዋ ነው፡፡..ስለዚህ ውስጡ ያሉትን እንዴት አግዘናቸው ከህይወቱ እንዲወጡ ማድረግ እንችላለን…?ሊገቡ ቋፍ ላይ ያሉትንስ ሳይቃጠል በቅጠል እንዴት ነው ከገደሉ አፋፍ ልንመልሳቸው የምንችለው…? መልሱ ችግሩ በመሀከላችን መኖሩን በግልፅ ስናምን..በችግሩ ላይ በግልፅ መነጋገር
መወያት እና መግባባት ስንችል ነው መፍትሄውን በእጃችን መጨበጥ የምንችለው፡፡ እራሳችንንም ከችግሩ የምናድንበት መድሀኒት ማግኘት የምንችለው ... መጪውን ትውልድንም መታደግ የምንችለው የዛን ጊዜ ነው፡፡››

ካለበለዚያ እንዲሁ በጭፍን ባህላችን አጎደፉት .... እርኩሶች ናቸው፤ ይጨፍጨፉ….ይመንጠሩ በማለት ቅንጣት ውጤት ማምጣት አንችልም፡፡እንደውም ስለዚህ ነገር ሳስብ

1980ዎቹ ቤት አካባቢ የነበረውን የኤች. አይ ቪ ጥፋት ያስታውሰኛል ፡፡የዛኔ ጊዜም ስለበሽታው በአደባባይ አውጥተን መወያየትና መፍትሔ መፈለግ ሲገባን በየጓዲያው በማንሾካሾክ ....አውሬ መጣላችሁ፣ጭራቅ መጣላችሁ እያልን ለተጠቂዎች ሲኦልን
ስንሸልማቸው..እኛም በፍርሀት ታፍነን በቁም
ስንንዘፈዘፍ ስንት እና ስንት ህይወት ረገፈ ….?

ስንቱ አፍላ ወጣት ለውይይትና ለምክክር ዝግ
በሆነው ባህላችን ምክንያት በየጓዳው ባክኖ ቀረ...?ቤት ይቁጠረው፡፡ዛሬም ከዛ ውድመት አልተማርንም፡፡መቼም እርግማን ሆኖብን አንድ ችግር የህዝባችንን እሩብ ካልጨረሰ በስተቀር መፍትሄው አይገለፅልንም፡፡

‹‹ትክክል ነህ .…እኔም ባንተ ሀሳብ እስማማለሁ፡፡›› አለችው ዶ/ር ሶፍያ፡፡

‹‹ጥሩ.. በይ አሁን ተነሺ እንውጣ፡፡››

‹‹ጨረስክ እንዴ ፕሮሰሱን?››
👍724👎1😁1