ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.83K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
391 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
▶️ ቅዱስ ገብርኤል #ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር እንደሌለ #ለማርያም #ለማስረዳት የተጠቀመው #ምሳሌ #መካን የነበረችውና #ያረጀችው ዘመዷ #ኤልሳቤጥ #ወንድ ልጅ እንደጸነሰች በመግለጽ ነበር። #ልጅ አለመውለድ #የወላጆችን #የግል #ደስታ የሚያሳጣ ብቻ ሳይሆን #እግዚአብሔር እንደማይወዳቸውም የሚያመለክት ነው ተብሎ #በህብረተሰቡ ዘንድ ስለሚታመን {ዘፍ 16፥2 ፣ ዘፍ 25፥21 ፣ ዘፍ 30፥23 ፣ 1ኛሳሙ 1፤ 1-18 ፣ ዘሌ 20፤ 20-21 ፣ መዝ (128)፥3 ፣ ኤር 22፥30}። <<ነቀፌታዬን ከሰው መካከል ያስወግድልኝ ዘንድ ጌታ ተመለከተኝ>> ብላ #እግዚአብሔር #የመካንነትን #ህይወቷን ስለቀየረላት ምስጋና አቅርባለች {ሉቃ 1፥24}። #በደስታ#በጥሞና#በምስጋና... የነበረችውን #ኤልሳቤጥን ማርያም #ከገብርኤል መልእክት(ብስራት) ቡኋላ ወደ እሷ መጥታ #ሰላምታ ስታሰማት #ኤልሳቤጥ #በመንፈስ ቅዱስ ተሞልታ ከማርያም አፍ ሳትሰማው ማርያም #የጌታ #እናት እንደምትሆን አወቀች። በዚህ ጊዜ #ኤልሳቤጥ አፏን የሞላው #ቃል <<አንቺ ከሴቶች #መካከል የተባረክሽ ነሽ የማህጸንሽም ፍሬ የተባረከ ነው የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል?>> የሚል ነበር። አንዳንዶች እንደሚሉት ሳይሆን ኤልሳቤጥ ማርያምን <<ከሴቶች #በላይ የተባረክሽ>> እንዳላለቻትና ዳሩ ግን <<ከሴቶች #መካከል የተባረክሽ>> እንዳለቻት ልብ ማለት ያስፈልጋል። #ማርያም #በእግዚአብሄር #እቅድ ውስጥ ያላትን #ስፍራ ባናሳንስም(ልናሳንስም አንችልም) #እግዚአብሔር #ብቻ ሊቀበል የሚገባውን #የአምልኮት #ክብርና #ልእልና መስጠት ግን አይገባንም።

▶️ ስለማርያም ኤልሳቤጥ #ያገነነችው ነገር ቢኖር <<ያመነች ብጽኢት[1] ናት>> በሚል የማርያምን #እምነት ነበር {ሉቃ 1-45}። #ማርያም #የእግዚአብሔርን #ቃል ስላመነች የእግዚአብሔርን #ኃይልና #አንድያ #ልጅ ተቀበለች።

▶️ በኤልሳቤጥ #ጽንስ ውስጥ ያለው #ዩሀንስም በጊዜው #ደስ #ተሰኝቷል {ሉቃ 1፤ 41-44}። ዩሀንስ #በምድራዊ #አገልግሎቱ እንዳደረገው ሁሉ #ሳይወለድም በፊት #በኢየሱስ ክርስቶስ #ብቻ ደስ ተሰኝቷል {ዩሀ 3፤ 29-30}። #ካደገ ቡሀላም #መጥምቁ #ዩሀንስ ተብሎ ሲታወቅ #መሲሁን #ኢየሱስ ክርስቶስን ለአይሁድ ህዝብ የማስተዋወቅና የመግለጥ ታላቅ #እድል አግኝቷል። ነገሩ እንዲህ ሆኖ ሳለ <<ዩሀንስ በእናቱ ማህጸን ውስጥ የማርያምን ድምጽ በመስማቱ #ለማርያም #ሰገደላት>> የሚሉ #መናፍቃን አልታጡም። ይሁን እንጂ #የጽንስ #መዝለል #ሁኔታን #ጸንሰው የሚያቁ #እናቶች የሚረዱት ነገር ቢሆንም •ስግደት• ብሎ መቀየር ግን. . . •ለማርያም ሰገደ• ያሉትም #መጽሀፍ ቅዱስ ሳይሆን #ሲኖዶስ ተብለው የተጠሩ ተስብሳቢዎች እንደሆኑ #ራሱ #ኦርቶዶክስ ተዋህዶ #ቤተክርስቲያን ያሳተመችው #የሉቃስ ወንጌል አንድምታው ይገልጻል።

<<. . . ከዘካርያስ ቤት ገብታ ኤልሳቤጥን እንዴት ነሽ አለቻት፥ ወሶበ ስምዓት ኤልሳቤጥ ቃላ ለማርያም እንዝ ትትኣምኃ ኦንፈርዓፀ እጓል በውስተ ከርሣ እመቤታችን እንዴት ነሽ ስትላት ኤልሳቤጥ በሰማች ጊዜ በማኅፀኑዋ ያለ ብላቴና ሰገደ። ሐተታ፡ ሐዋርያት #በሲኖዶስ ሰገደ ብለውታል። #ያሬድም ሰገደ ብሎታል።[2]>>

▶️ ከዚሁ #ከማርያምና #ከኤልሳቤጥ #ውይይት በመነሳት <<ቅድስት ኤልሳቤጥ ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያምን መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ የሌለብሽ ነሽ በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስ እያማለድሽ የምትሰጪ መዝገበ በረከት ነሽ>> ብላ #አመስግናታለች #ዘምራላታለች የሚሉ አሉ[3]።

▶️ እንግዲህ እንዲህ አይነት #ቃል #በመጽሀፍ ቅዱስ ፈጽሞ ሳይኖር #ኤልሳቤጥ እንዲህ አይነት #ቃል ተጠቅማለች ብሎ #መጻፍና #ማስተማር #መጽሀፍ ቅዱስ እኛ ጋር #ብቻ ይገኛል ሌላው #ማንበብ አይችልም ብሎ ከማሰብና #የመጽሐፍ ቅዱስን #የበላይነት ካለመቀበል የሚመነጭ #ከንቱነት ነው። #ኤልሳቤጥ የተናገረችው <<አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ፥ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው። የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል? እነሆ፥ የሰላምታሽ ድምጽ በጆሮዬ በመጣ ጊዜ ፅንሱ በማኅፀኔ በደስታ ዘሎአልና። ከጌታ፤ የተነገረላት ቃል ይፈጸማልና ያመነች ብፅዕት ናት።>> {ሉቃ 1፥47} የሚል ብቻ ነው።

▶️ በአንጻሩ ደግሞ <<መርገመ ስጋ መርገመ ነፍስ የለብሽም>> ማለት በግልጽ #መጽሀፍ ቅዱስን መካድና #ማርያም የሰው ዘር መሆኗን #መዘንጋት ነው። እንዲያውም ማርያም ራሷ ክርስቶስን <<መድኃኒቴ>> ብላዋለች። #መድኃኒት ደግሞ #ለበሽተኞች (ለኃጢአተኞች) እንጂ #ለጤነኞች (ለጻድቃን) የሚያስፈልግ እንዳልሆነ #ቃሉ #በግልጽ ይናገራል{ማቴ 9፥12}።

▶️ በመሆኑም <<መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ የሌለብሽ. . . እያማለድሽ የምትሰጪ>> እያለ #የዘመረ #አካል #በመጽሀፍ ቅዱስ ባለመኖሩ የሌለ ነገር ላይ ተንተርሶ #ዶክትሪን ማስቀመጥ በቃሉ #መልእክት ላይ የተፈጸመ ተራ #አመጽ ነው።

✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆

"ማጣቀሻዎች - References"
_______________
[1] ብፁዕ፤፦
<<በቁሙ የታመነ፣ የተመሰገነ፣ ሥራውና ልቡ የቀና፣ ... ምስጉን፣ ብሩክ...>>
📚፤ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መጽሀፈ ሰዋሰው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ፤ *ገጽ 2081። አርቲስቲክ ማተሚያ ቤት፤ 1948 ዓ.ም።

<<የተባረከ፣ ደስተኛ>>
📚፤ የኢትዮጽያ መጽሀፍ ቅዱስ ማህበር፤ <የመጽሀፍቅዱስ መዝገበ ቃላት>፤ 6ኛ እትም፤ *ገጽ 112። ባናዊ ማተሚያ ቤት፥ አ.አ 1992 ዓ.ም።

[2] 📚፤ የኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክ፡ ወንጌል ቅዱስ፡ የሉቃስ ወንጌል ንባቡና አንድምታው 1፤ 36-40፤ ገጽ 268። ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፤ አ.አ 1997 ዓ.ም።

[3] 📚፤ የኢ.ኦ.ተ ቤ/ክ፤ <መርሐ ጽድቅ ባህለ ሃይማኖት>፡ ገጽ. 24-25፡ ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት። አ.አ፥ 1988 ዓ.ም።

📚፤ አንዱዓለም ዳግማዊ (መምህር) <ወላዲተ አምላክ በነገረ ድኅነት> ገጽ 290። ብራና ማተሚያ ድርጅት፥ ሚያዚያ፥ 1998 ዓ.ም።


(5.1▶️ጥያቄ) ይቀጥላል...
@gedlatnadersanat
▶️ በመጽሀፍ ቅዱስ #ሴቶች ሰፊ ስፍራ #ከወንዶች #እኩል ተሰጥቷአቸው #እግዚአብሔር ሲጠቀምባቸው እናነባለን። በተለይ #በአዲስ ኪዳን #የእግዚአብሄር ቃል በግልጽ <<አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም፥ ባሪያ ወይም ጨዋ ሰው የለም፥ ወንድም ሴትም የለም፤ ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ ሰው ናችሁና።>> {ገላ 3፥28} ይላል። እንዲሁም <<እግዚአብሔር ለሰው ፊት አያዳላምና።>> {ሮሜ 2፥11}፣ <<በአይሁዳዊና በግሪክ ሰው መካከል ልዩነት የለምና፤ አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና፥ ለሚጠሩትም ሁሉ ባለ ጠጋ ነው፤>> {ሮሜ 10፥12} ይላል።

▶️ በመጽሀፍ ቅዱስ ውስጥ #ከወንዶች ባልተናነሰ አንዳንዴም #በሚበልጥ ሁኔታ #እግዚአብሔር በተለያየ መልኩ የተጠቀመባቸው #ከ87 የሚበልጡ #ሴቶች #ከነታሪካቸው ተጽፏል። ከእነዚህም ውስጥ #ልጅ ባለመውለዳቸው #ሲነቀፉ የነበሩት #እንደነሳራና #ሐና የመሳሰሉ #እግዚአብሔር #ቃል ኪዳን ያለውን #ልጅ በመስጠት #አስደናቂና #ታዋቂ #እናቶች እንዲሆኑ አድርጓቸዋል።

▶️ የተጠቀሱት ሁሉም #ሴቶች #አንድ የሚያደርጋቸው ነገር ቢኖር #መሲሁን (ኢየሱስ ክርስቶስን) ማገልገላቸውና ለእርሱም #መንገድ ማዘጋጀታቸው ነው። ለምሳሌ፦


1፦ ሔዋን፦ #ከሴቲቱ #ዘር የሚመጣው (ኢየሱስ ክርስቶስ) #የእባቡን (የዲያብሎስንና የኃጢአትን) #ራስ #እንደሚቀጠቅጥ የተናገረላትና ይህንንም #ትንቢት በመጠበቅ ለዚህ #ዘር #ሐረግ በመጀመሪያ #አቤልን ከዚያም #ሴትን የወለደች።

2፦ ሩት፦ #ከሞዓባውያን ወገን የነበረች #በእምነት #ከወገኖቿ ተለይታ #ከእግዚአብሄር ህዝብ ጋር በመቀላቀል #እስራኤላዊውን #ቦኤዝን አግብታ #የእሴይን አባት #እዮቤድን በመውለድ ወደ #ክርስቶስ #የዘር #ግንድ ውስጥ ገብታለች።

3፦ አስቴር፦ #ዝርያው እንዲጠፋ የተፈረደበት #የአይሁድ #ህዝብ ወደ #ንጉሡ #በድፍረት በመግባት #ህዝቤን #በመሻቴ #ህይወቴም #በልመናየ ይሰጠኝ በማለት #በህዝቧ ላይ #የታወጀውን #የሞት #ፍርድ በመቀልበስ #ከአይሁድ ወገን ሊመጣ ያለውን #የኢየሱስ ክርስቶስን #ዘር በመጠበቅ የበኩሏን #አስተዋጽኦ አድርጋለች።

▶️ እነ #አቢግያ#ኢያኤል#ኤልሳቤጥ#ቤርሳቤህ#ራሔል#ሊዲያ#ፌበን#ሰሎሜ፣ . . .ወዘተ ሁሉም #እግዚአብሔር የሰጣቸውን #ተግባር ሁሉ #በድል ያከናወኑ አንቱ የሚባሉ #ሴቶች ናቸው።

▶️ ጌታ ኢየሱስ #በአገልግሎቱ #ወቅት #ከፍተኛ #እገዛ ሲያደርጉ የነበሩ በዚያ #አስፈሪ #ሰዓት በሆነው #በስቀለቱም ወቅት #ከመስቀሉ #ግርጌ ስር በስፋት #ሃዘናቸውን የገለጹ #በመቃብሩም ሄደው እንደተናገረው #መነሳቱን #ከቅዱሳን #መላእክት ሰምተው #ለህዝቡ ሁሉ በመጀመሪያ #ትንሳኤውን ያወጁና የእርሱን #መሞትና #መነሳት ... ወዘተ የሚያበስረውን #ወንጌል ይዘው ወጥተው #የግል #ቤታቸውን እንኳ #የወንጌል አደባባይና #ቤተክርስቲያን አድርገው #የእግዚአብሔርን ቃል ሲያስተምሩ የነበሩ #ሴቶች ነበሩ።

▶️ ይህን #ማንሳታችን ያለ ምክንያት ሳይሆን <<ማርያም #ከሴቶች ሁሉ እንዲያውም #ከፍጡራን ሁሉ የበላይ የሆነች #ፍጡር>> የሚል #የተዛባና #መጽሀፍቅዱሳዊ ያልሆነ አስተምህሮ ስላለ ነው። ለዚህም #ትምህርት መነሻው #በሉቃስ 1፥28 እና 1፥42 <<አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ>> ተብሎ የተገለጸው #ቃል ሲሆን <<ቅዱስ ገብርኤል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተልኮ ማርያምን ብሩክት አንቲ እምአንስት - አንቺ ከሴቶች ሁሉ የተለየሽ ሲል ከሴቶች ሁሉ የተለየች መሆኗን በምስጋና ቃል ገልጦ ተናግሯል፤ የዚህን መልአክ ቃል በመደገፍ በማጽናትም ኤልሳቤጥ አንቺ ከሴቶች የተባረክሽ ነሽ ብላ ጮሀና አሰምታ ተናግራለች። ይህም ቃል ቅድስት ማርያምን በነፍስ በሥጋ ቅድስት መሆኗን መትህተ ፈጣሪ መልዕልተ ፍጡራን (ከፈጣሪ በታች ከፍጡራን በላይ) መሆኗን ያጠቃልላል>> ብለው የተረጎሙት ስላሉ ነው[1]። በመሰረቱ ይህ #ትርጉም ሳይሆን #የመጻሐፉን ግልጽ #ቃል በመቀየርና ወደሚፈልጉት የማርያም #አምልኮ በማዞር የተቀመጠ #አስተምህሮ ነው።

▶️ ማርያምን <<ከፍጡራን በላይ ከፈጣሪ በታች>> የሚለውን ቃል #ለመጀመሪያ ጊዜ የገለጸው #በ15ኛው ክፍለ ዘመን ይኖር የነበረው #የደቡብ ወሎ ቦረናው #ሰው #አባ #ጊዮርጊስ #ዘጋስጫ ነው[2]።

▶️ ለዚህ ደግሞ ዋነኛው #ምክንያታቸው ከላይ የተገለጸው #የቅዱስ ገብርኤልና #የኤልሳቤጥ #ንግግር ሲሆን ሌላው እንደ #ምክንያት የሚጠቀሰው ደግሞ #ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን #መውለዷ ነው።

▶️ ከዚህ የተነሳ #ከእግዚአብሄር #ምስጋና #ቀጥሎና #አያይዞ #ማርያምን #ማመስገን እንደሚገባ #ከ15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ቡኋላ #የኢትዮጵያ #ኦርቶዶክስ #ተዋህዶ #ቤተክርስቲያን መጠቀም ጀምራለች። ለምሳሌ፦

〽️ 1፦ <አቡነ ዘበሰማያት(አባታችን ሆይ)> ከሚለው #ጸሎት ቀጥሎ <እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ.... ሰላም እንልሻለን> ማለትን

〽️ 2፦ <ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስቅዱስ (ምስጋና ይሁን ለአብ፣ ምስጋና ለወልድ፣ ምስጋና ለመንፈስቅዱስ ይገባል)" ከሚለው #ቀጥሎ <ስብሐት #ለእግዝትነ #ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ (አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ለድንግል ማርያም #ምስጋና ይሁን)> ማለትን

〽️ 3፦ <ለልዑል እግዚአብሔር ፍጹም #ምስጋና ይገባል> ይባልና ቀጥሎ <ለወለደችው ለድንግል ማርያም #ምስጋና ይገባል> ማለትን

〽️ 4፦ <የእግዚአብሄር ስሙ ፈጽሞ ይመሰገን ዘንድ ዘወትር በየጊዜያቱ በየሰአቱ #ምስጋና ይገባል> ካለ ቡሀላም <እናታችን ማርያም ሆይ ሰላምታ ለአንቺ ይሁን እያልን #እንሰግድልሻለን #እንማልድሻለን> ይላል[3]።
▶️ ይህም #ቤተመቅደስ #ማርያም በነበረችበት #ዘመን የነበረ ሲሆን ሁሉም #ሴቶች #በቁ.4 ላይ በተገለጸው ውስጥ በፍጹም #አይገቡም ነበር። ይሁን እንጂ #በውጭ (በተራ ቁ.7 ላይ) በተገለጸው #አደባባይ ላይ እንደ #የ91 ዓመቷ ዕድሜ #የፋኑኤል ልጅ #ሃና #ነብይት ዓይነቶች {ሉቃ 2፤ 36-38} #መቆም ይችሉ ነበር።

እስከዛሬም ድረስ የትኛዋም #ሴት ብትሆን #ቤተመቅደስ (ቅድስተ ቅዱሳን) ውስጥ #መግባት አልቻለችም። #ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን #ሴቶች ወደ #ቤተ መቅደስ እንዲገቡና #በመቅደስ ውስጥ #እንዲጸልዩ ለአፍታ እንኳ አለመፍቀዷ የራሷ #ስርዓት #ይደነግጋል[1]።
ታድያ #ማርያም በየትኛው #ቦታ በየትኛው #ቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ #መኖሪያዋ አድርጋ አደገች? አዎን #ማርያም #ቤተ መቅደስ ነበረች የሚለው #ሃሳብ ከየት መጣ ቢባል #ከቁርዓን ነው {ሱረቱ አልዒምራን 3፥37}። እርሱም #ስለቤተ መቅደሱ ሁኔታ #እውቀት የለውምና አይፈረድበትም።
▶️ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን #ደቀመዛሙርቶቹ ተሰብስበው #ስለጸሎት እንዲያስተምራቸው በጠየቁት ጊዜ እንግዲህ እናንተ እንዲህ #ጸልዩ፦ <<በሰማያት የምትኖር #አባታችን ሆይ፥ #ስምህ #ይቀደስ#መንግሥትህ #ትምጣ፤ ፈቃድህ #በሰማይ እንደ ሆነች እንዲሁ #በምድር ትሁን፤ የዕለት #እንጀራችንን ዛሬ ስጠን፤ እኛም ደግሞ የበደሉንን #ይቅር እንደምንል በደላችንን #ይቅር በለን፤ ከክፉም #አድነን እንጂ ወደ #ፈተና አታግባን፤ #መንግሥት ያንተ ናትና #ኃይልም #ክብርም #ለዘለዓለሙ፤ አሜን።>> በሉ በማለት አስተምሯል። [ማቴ 6፤ 9-13፣ ሉቃ 11፤ 1-4]።

▶️ ከዚህ ጌታ #ኢየሱስ ከሰጠው #የጸሎት #መመሪያ ላይ በመቀጠል #አድራሻው ወደ #ማርያም የሆነ፦ <<እመቤታችን ቅድስት #ድንግል #ማርያም ሆይ በገብርኤል ሰላምታ ሰላም እልሻለሁ....>> ምናምን የሚለው #ጸሎት ቢኖሮ ኖሮ ወይም መኖር ቢኖርበት ኖሮ ደቀመዛሙርቱ #ጸሎት #አስተምረን ባሉት ጊዜ ባገኘው ምርጥ #አጋጣሚ ወደ #ማርያም #መጸለይ #ትክክል ወይም #ተገቢ መሆኑን ባሳየ ነበር። #ዝንጋኤ የሌለበት በማስተዋልም #ተወዳዳሪ የማይገኝለት ጌታችን #ኢየሱስ ክርስቶስ <<መንግስት ያንተ ነውና ኃይልና ክብርም ለዘላለሙ አሜን>> ብሎ #የመዝጊያ #ቃል አስቀምጦ ባልደመደመውም ነበር።

▶️ መምህራችንና #ሊቃችን አንድ እርሱም #ክርስቶስ የሆነው #ጌታ [ማቴ 23፤ 8-11] ያላስተማረውን #ትምህርት ከእርሱ ይልቅ #ሊቅ ለመሆን #በመሞከርና #በመጨመር ሌላ ድርሰት ማምጣት #ከንቱ #ድካምና #ፍሬ #ቢስ ከመሆኑም በላይ የሚያመጣው #ፋይዳ (ጥቅም) አይኖርምና <<እንዳይዘልፍህ፥ ሐሰተኛም እንዳትሆን #በቃሉ አንዳች #አትጨምር።>> [ምሳ 30፥6]።

▶️ በመሰረቱ <<አባታችን ሆይ>> በሚለው #የማህበር #ጸሎት ላይ <<እመቤታችን ...ሆይ>> የሚለውን ብቻ ሳይሆን <<ሊቃውንቶች>> የጨማመሩት #ሠላም #ለኪን#ውዳሴ #ማርያምን#አንቀጸ #ብርሃንን#ይወድስዋ #መላዕክትን#መልክዓ #ማርያምን....ወ.ዘ.ተ ደራርበውበታል።

▶️ የካቶሊክ #ቤተክርስቲያንና ሌሎች #እህትማማች ተብለው የሚጠሩት #አብያተ #ክርስቲያናት በኢትዮጵያ ካለው የ<<እመቤታችን.... ሆይ>> ጸሎት #የቃላትና #የይዘት #ልዩነት አለው። የኢትዮጵያ #ኦርቶዶክስ #ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የምትለው፦ <<እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ በመልአኩ በቅዱስ ገብርኤል ሰላምታ ሰላም እንልሻለን በሃሳብሽ ድንግል ነሽ በስጋሽም ድንግል ነሽ የአሸናፊ የልዑል እግዚአብሔር እናት ሆይ ሰላምታ ይገባሻል እንዲሁም ከተወደደው ልጅሽ ከጌታችን ከመድሀኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ይቅርታውን ለምኝልን ኃጢታትችንን ያስተሰርይልን ዘንድ አሜን[1]።>> የሚል ሲሆን #የካቶሊክና#የእህትማማች #አብያተ ክርስቲያናት (የግሪክ፣ የህንድ፣ የአርመን የግብጽ. . .ኦርቶዶክስ) ደግሞ <<ድንግል ወላዲት ሆይ! ማርያም ሆይ፣ ጸጋ የሞላሽ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋራ ነው፤ ከሴቶች ሁሉ የተባረክሽ ነሽ የማህጸንሽም ፍሬ የተባረከ ነው የነፍሳችንን አዳኝ ተሸክመሻልና ደስ ይበልሽ[2]>> #ብቻ ነው የሚለው። ይህ ግን #መጽሀፍ ቅዱስ የማይቀበለውና #መጽሀፍ ቅዱሳዊ #ማስረጃ የሌለው ከንቱ #ፈጠራ ነው።

✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆

"ማጣቀሻዎች - References"
_____________
[1] 📚፤ ጌታቸው አየነው (መምህር)፤ "የዘውትር ጸሎት በአማርኛ"፥ ገጽ 5 ፥አ.አ፥ 1998 ዓ.ም።

[2] 📚፤ የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የጽ/ጠ/ጽ/ቤት ሐዋርያዊ ስራ መምሪያ ፤ "ሕያው እግዚአብሔር" ፤አማርኛ ትርጉም ገጽ 316፤ በገላውዲዎስ ተቋም በአባ ጳውሎስ ጻድዋ ካርዲናል ሊቀጳጳሳት ዘካቶሊካውያን እንዲታተም የተፈቀደ፤ ማስተር ማተሚያ ቤት፤ አ.አ፥ 1989 ዓ.ም።
▶️ የሰው ልጅ #ሃሳቡን ከሚገልጽባቸው አያሌ ነገሮች አንዱ #ሥዕል ነው። #ሥዕላት #የሰውን ልጅና #የተፈጥሮን #የኑሮ #መልክና #ጸባይ በማንጸባረቅ መልሰው ለሰው ልጅ #የሚያስተምሩ#ታሪክን #መዝግበው የመያዝ #አቅማቸው ብርቱ የሆነና #በስልጣኔውም መስክ የበኩላቸውን #መረጃ ዘግበው በመያዝ ከፍተኛ #አስተዋጽኦ ያደረጉ ናቸው። #ሥዕላት ወደ #ቤተክርስቲያን ከመግባታቸው በፊት #በአህዛብና #በአይሁድ ዘንድ #ከአምልኮት ጋር በተያያዘ መልኩ በስፋት #ይገለገሉባቸው ነበር።

በተለይ #እስራኤላውያንና ቀደምት #የሀይማኖት #አባቶች #ሥዕላትን #ለቤተክርስቲያን አገልግሎት ሲያውሉ ማንኛውም #ጽሁፍን ማንበብ ለማይችል #ሰው #የክርስቶስን #ህማማቱን#መሰቀሉን#መሞቱን#መቀበሩን#መነሳቱንና #ማረጉን ደግሞም ተመልሶ እንደሚመጣ #ለመስበክ እንዲጠቅሙ በማድረግ ነበር።

▶️ ሥዕሎቹን #በተራራ ገመገም፣ #በሰሌዳ ላይ፣ #ድንጋይ #በመጥረብና #በመፈልፈል#በዛፍ #ቅጠልና #ቅርፊት ላይ፤ ቡኋላ ቡኋላም እየቆየ ሲሄድ #ከፍየልና #ከበግ ቆዳ ላይ ሁሉ #እጽዋትን #በቀለምነት በመጠቀም ለማስተማሪያነት ይጠቀሙበት ነበር። እንደውም አስተምረው ከጨረሱ ቡሀላ አንዳንዶቹን #ስዕሎች በቋሚነት #የማስተማሪያ #መሳሪያቸው አርገው እስከ ረጅም #የህይወት #ዘመናቸው በመጠቀም #ለተማሪዎቻቸው ከሚያወርሷቸው #ሃይማኖታዊ ንብረቶች ውስጥ ዋነኛውን #ስፍራ የያዙት #ሥዕላት ነበሩ።

▶️ ቀስ በቀስ #ሥዕሎችና #ቅርጻቅርጾች (ምስሎች) እየበዙ በመምጣታቸው በተለይም #በቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ #በግድግዳ ላይ በብዛት #በመንጠልጠላቸውና ልዩ #ትኩረት እየሳቡ በመምጣታቸው ምክንያት #በ8ኛው መቶ ክፈለ ዘመን #በክርስቲያኖች መካከል <<አምልኮ ባእድ እየሆኑ መተዋል>> በማለት #ከፍተኛ #ክፍፍልና #ጭቅጭቅን ፈጥሩ።

▶️ በ726 ዓ.ም #የቢዛንታይን መሪ የነበረው " #አጼ #ሊያ #ሳልሳዊ[1]" ምስሎችን #ማመን አጥብቆ #ተቃወመ። በዚህ ምክንያት #ፀረ ምስል ተናጋሪዎችና #ምስል ደጋፊዎች ወደ #ከረረ #ግጭት ውስጥ ገቡ። ይሄው ንጉስ #በ730 ዓ.ም ውሳኔውን #አጽንቶ #በግዛቱ #ምስሎችን ጥቅም ላይ መዋላቸውን #አገደ#በምስል #አፍቃሪያን ላይም ከፍትኛ #ስደትን አስከተለ።

▶️ ከዚህም የተነሳ በተለይ #ሊዎንን ተክቶ የነገሰው " #አፄ #ቆስጠንጢኖስ 5ኛ[2]" <<ክርስትናውን ለማጽዳት>> በሚል በርካታ #ምስል #አፍቃሪያን የነበሩትን #የሃይማኖት #መሪዎች እንዲገደሉ አደረገ። ብዙም ሳይቆይ #አፄ #ቆስጠንጢኖስ 5ኛ በመሞቱ ምክንያት ብዙ #መንፈሳዊ #እውቀት ያልነበራት የነገሩን #አሳሳቢነት የተመለከተች #የንጉስ አፄ #ቆስጠንጢኖስ #ባለቤት (ሚስት) የሆነችው #ኢፌኔ ከሁሉም #ክርስቲያን ሃገሮች የተዉጣጡ #የሃይማኖት #አባቶችን #በ784 ዓ.ም #በኒቂያ ጉባዔ ጠራች። ጉባዔውም #ሁለተኛው #የኒቂያ #ጉባኤ በመባል ተሰየመ[3]።

▶️ በዚህ #ጉባዔ በርካታ #አጀንዳዎች ቢኖሩም በተለይ #የሰንበት ቀን [እሁድ] ልዩ #ከበሬታ እንዲኖረው ፣ #ምስሎች ደግሞ #በአስተማሪነታቸውና ምስሉ የሚወክለውን #አካል #ማክበር ስለሆነ #በቤተክርስቲያን #ግድግዳ ላይ #በክብር #እንዲሰቀሉና ልዩ #ክብር እንዲሰጣቸው ብሎም #እንዲሰገድላቸው ጉባዔው ወስኗል።

▶️ ይህን ውሳኔ #ኦርቶዶክስ #ቤተክርስቲያን {ምስራቃውያን} እና #ካቶሊካውያን {ምዕራባውያን} ተቀብለው #ምስሎችን #ማክበር ጀመሩ። በተለይ #የግሪክ #ኦርቶዶክስና #የሊባኖስ #ማሮናይት #ቤተክርስቲያን የማርያምንና #የክርስቶስን #ስቅለት የሚያሳይ #ስዕል በመሳል በአጥቢያዎቻቸው #ግድግዳ ላይ ሲሰቅሉ በጊዜው #በምዕመኖቻቸው ዘንድ ከፍተኛ #ተቃውሞ ስለገጠማቸው <<ይህችን ስዕል የሳለው ወንጌላዊው ሉቃስ ነው ፤ የጌታችንንም ስቅለት የሳለው ዩሀንስ ነው ሲወርድ ሲዋረድ የመጣልን መመሪያ ነው>> በማለት #እንግዳ #ትምህርት ማስተማር ጀመሩ[4]።
Forwarded from እውነት አርነት ያወጣል (ቴዎድሮስ)
ስንክሳር ጥቅምት 27

እንደሚታወቀው ዛሬ የዓመቱ መድኀኔዓለም ተብሎ ይጠራል፡፡ ስንክሳር ግን በዚህ ዕለት የማንን ስም ነው የሚያነሣው?

#ኦርቶዶክስ_በየዕለቱ_ኢየሱስን_ትሰብካለች_የምትሉ_ሰዎች_ከንባባችሁ_በዋላ_ከዚህ_ጽሑፍ_ኢየሱስን_አሳዩኝ፡፡

ስንክሳር በዛሬው ዕለት ሦስት ሰዎችን (አባ መቃርስን በዋሻ የሚኖር የሚለውን ጳውሎስንና ዮልያኖስን) እና ሰማዕታት የሚላቸውን ያነሣል፡፡ ከእነርሱ በተጨማሪ ጌታን ያነሣል፡፡

የሚገርመው ስለአባ መቃርስ ሁለት ገጽ ከግማሽ ሲያስነብብ ስለጌታችን የተጻፈው ግን የሚከተለው ብቻ ነው "በዚችም ቀን የመድኀኒታችን የስቅለቱ መታሰቢያ ነው"፡፡

ዕለተ ቀኑ ነው በሚባለው ቀን እንሰብከዋለን የሚሉትን ጌታ እንዲህ፡ጽፈውለት የሆነን ሰው ታሪክ በዝርዝር ማስፈራቸው ጸረ ኢየሱስነታቸውን ያሳያል፡፡

አሁን ስለ አባ መቃርስ የሰፈረውን አጠር አድርጌ ላስነብባችሁ፡፡

በእጆቹ የተደረጉ ተአምራት ስንቱን እንናገራለን? የተባለለት አባ መቃርስ ሕዝቡን ሲያስተምር ያለቅስ ነበር፡፡ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ ለምን ታለቅሳለህ? ሲለው የሕዝቡን ኀጢአት ጌታ ስላሰየው፡መሆኑን ይናገራል፡፡

ጌታ የሕዝቡን ኀጢአት እያየህ ለምን አታስተምርም? ብሎ ሲጠይቀው አባ መቃርስ "አይሰሙኝም" የሚል መልስ ሰጠ፡፡ ጌታም ካልሰሙህ ደማቸው፡በእጃቸው ነው ይለዋል፡፡

በመርቅያኖስ ምክንያት በተሰበሰበውና ሁለት ባሕርይ በሚለው ትምህርት የተነሣ አባ ዲዮስቆሮስና አባ መቃርስ ወደ ደሴተ ጋግራን ተወሰዱ፡፡

ከእስሩም በዋላ ወደ እስክንድርያ ተወስዶ የንጉሥ መርቅያንን ትምህርት በመቃወሙ ምክንያት "የንጉሡም መልእክተኛ አባ መቃርስ በንጉሥ ሃይማኖት እንደማያምን በአወቀ ጊዜ ተቆጥቶ ከኩላሊቱ ላይ ረገጠው፡፡ ያን ጊዜም ሙቶ የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ ሥጋውንም ምእመናን ወስደው ከነቢይ ኤልሳዕና ከመጥምቁ ዮሐንስ ሥጋ ጋር በአንድነት አኖሩት፡፡ ወደ ወደደው ክርስቶስም የመንግሥት ዘውድን ተቀዳጅቶ ሔደ"፡፡

የእኔ ጽሑፍ ዓላማ ኢየሱስን በየቀኑ ትሰብካለች የምትባለዋ ቤተ ክርስቲያን ኢየሱስን እንዴት ወደ ጎን እንዳደረገችው ማሳየት ነው፡፡ የለም ኢየሱስ ይሰበካል የምትሉ ሰዎች ስንክሳር በዛሬው፡ዕለት ከሚያስነብበው ከዚህ ጽሑፍ ኢየሱስን አሳዩኝ፡፡


https://tttttt.me/tewoderosdemelash/876