ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.82K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
393 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
📖፤ / ሱረቱ መርየም 19፤ 27-28
(2ተኛ እትም 1998 ዓ.ም)
*ሱራህ 19, አያህ 27*
فَأَتَتْ بِهِۦ قَوْمَهَا تَحْمِلُهُۥ ۖ قَالُوا۟ يَٰمَرْيَمُ لَقَدْ جِئْتِ شَيْـًۭٔا فَرِيًّۭا
በእርሱም የተሸከመቺው ሆና ወደ ዘመዶቿ መጣች፡፡ «መርየም ሆይ! ከባድን ነገር በእርግጥ ሠራሽ» አሏት፡፡
*ሱራህ 19, አያህ 28*
يَٰٓأُخْتَ هَٰرُونَ مَا كَانَ أَبُوكِ ٱمْرَأَ سَوْءٍۢ وَمَا كَانَتْ أُمُّكِ بَغِيًّۭا
«የሃሩን እኅት ሆይ! አባትሽ መጥፎ ሰው አልነበረም፡፡ እናትሽም አመንዝራ አልነበረችም» አሏት፡፡

የክፍሉ የግርጌ ማብራሪያ ላይ ማሪያም #የሙሴ ወንድም #የአሮን #እህት እንደሆነች ይናገራል።
ይህ ደግሞ #ከክርስቶስ #ልደት በፊት 1500 #ዘመን ዘሎ #የአሮንን ዘመን #ከክርስቶስ እናት #ማርያም ጋር በምን #አይነት ሂሳብ እንዳጠጋጋው እንጃ??

▶️ "የኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን" ደግሞ #ሁለት #ተቃራኒ ሀሳቦችን ታስቀምጣለች፦

1ኛ👉 <"የዮሴፍ የወንድም ልጅ ናት">

<<የእስራኤል ሽማግሎችና መምህራንም አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች የክብርት እመቤታችን #የአባቷን #ወንድም #ዮሴፍን ወደ በአደባባይ . . . አደራ ያስጠበቅንህን #የወንድምህን #ልጅ #እጮኛህ #ማርያምን. . .[3]>>

በመሰረቱ "የዮሴፍ የወንድም ልጅ ናት" የሚለው #መጽሐፍ ቅዱስ ዮሴፍ #የማርያም #እጮኛ እንጅ አጎት(የአባት ወንድም) መሆኑን አይናገርም።
ምናልባት #ወንድሙ ቁጥር 2 ላይ የተጠቀሰው አባቷ #ኢያቄም ይሆን?? ብለን እንዳንገምት እንኳን። #ኢያቄም ወንድም እንዳልነበረውና #ለእናቱም #ለአባቱም አንድ እንደሆነ በሌሎች #መጽሀፍቶቻቸው ላይ ተጽፏል[4]። <የወንድምህን ልጅ እጮኛህን> ማለት በምን ዓይነት ቋንቋ እንደሆነ እንጃ!!

2ኛ👉 <"ማርያም የሃናና የኢያቄም ልጅ ስትሆን አያቷም #ቅስራ ነው"> ትላለች።

ማርያም " #የሃናና #የኢያቄም ልጅ" መሆኗን ለመጀመሪያ ጊዜ #ያለምንም #መረጃ የጠቀሰው " #በተአምረ #ማርያም" መጽሀፍ < #አጼ #ዘረያቆብ> ነው።/በ 1426-1460/ ዓ.ም።
በመቅድሙ ላይ "ስመ አቡሃ ኢያቄም ወስመ ወላዲታ ሐና -የአባቷም ስም ኢያቄም ነው የእናቷም ስም ሐና ነው" ብሏል[5]።

▶️ የ" #ዘውትር #ፀሎት" ድርሳኑም ውስጥ በተደጋጋሚ ተጠቅሷል።
ቡሀላ ግን ከእነዚህ #ኑፋቄ #ትምህርት ከገባባቸው #አዋልድ #መጽሀፍት በስተቀር
<•የሀናና የኢያቄም ልጅ•> ናት ብሎ ያመነ #የቤተክርስቲያን #አባት አንድም እንኳ እንዳልነበረ አንድ መጽሀፍ ሲገልጽ
<<እም ሐና ወኢያቄም ተወለድኪ - ከሐናና ከኢያቄም ተወለድሽ>> የሚለው #የሃገራችን #ደራሲያን የሚናገሩት #ቃል ነው እንጅ #ከአገር ውጪ ያሉ #አቢያተ #ክርስቲያናት ጠቅሰውት አያውቁም።
<ሐና ኢያቄም> የሚል ቃል #በሃይማኖተ #አበው መጽሀፍ ላይ ድርሰታቸው የተሰበሰበላቸው #ከ55 በላይ የሆኑ #ሊቃውንቶች ይህንን #ቃል አልጠቀሱም። ከእነዚህም በተለይ #እነቅዱስ #ኤፍሬም#እነዩሐንስ #አፈወርቅ አመሰገኗት የሚባሉት ላይ እንኳን እነዚህ ቃላቶች #አልተጠቀሱም ይላል[6]።
▶️ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን #ደቀመዛሙርቶቹ ተሰብስበው #ስለጸሎት እንዲያስተምራቸው በጠየቁት ጊዜ እንግዲህ እናንተ እንዲህ #ጸልዩ፦ <<በሰማያት የምትኖር #አባታችን ሆይ፥ #ስምህ #ይቀደስ#መንግሥትህ #ትምጣ፤ ፈቃድህ #በሰማይ እንደ ሆነች እንዲሁ #በምድር ትሁን፤ የዕለት #እንጀራችንን ዛሬ ስጠን፤ እኛም ደግሞ የበደሉንን #ይቅር እንደምንል በደላችንን #ይቅር በለን፤ ከክፉም #አድነን እንጂ ወደ #ፈተና አታግባን፤ #መንግሥት ያንተ ናትና #ኃይልም #ክብርም #ለዘለዓለሙ፤ አሜን።>> በሉ በማለት አስተምሯል። [ማቴ 6፤ 9-13፣ ሉቃ 11፤ 1-4]።

▶️ ከዚህ ጌታ #ኢየሱስ ከሰጠው #የጸሎት #መመሪያ ላይ በመቀጠል #አድራሻው ወደ #ማርያም የሆነ፦ <<እመቤታችን ቅድስት #ድንግል #ማርያም ሆይ በገብርኤል ሰላምታ ሰላም እልሻለሁ....>> ምናምን የሚለው #ጸሎት ቢኖሮ ኖሮ ወይም መኖር ቢኖርበት ኖሮ ደቀመዛሙርቱ #ጸሎት #አስተምረን ባሉት ጊዜ ባገኘው ምርጥ #አጋጣሚ ወደ #ማርያም #መጸለይ #ትክክል ወይም #ተገቢ መሆኑን ባሳየ ነበር። #ዝንጋኤ የሌለበት በማስተዋልም #ተወዳዳሪ የማይገኝለት ጌታችን #ኢየሱስ ክርስቶስ <<መንግስት ያንተ ነውና ኃይልና ክብርም ለዘላለሙ አሜን>> ብሎ #የመዝጊያ #ቃል አስቀምጦ ባልደመደመውም ነበር።

▶️ መምህራችንና #ሊቃችን አንድ እርሱም #ክርስቶስ የሆነው #ጌታ [ማቴ 23፤ 8-11] ያላስተማረውን #ትምህርት ከእርሱ ይልቅ #ሊቅ ለመሆን #በመሞከርና #በመጨመር ሌላ ድርሰት ማምጣት #ከንቱ #ድካምና #ፍሬ #ቢስ ከመሆኑም በላይ የሚያመጣው #ፋይዳ (ጥቅም) አይኖርምና <<እንዳይዘልፍህ፥ ሐሰተኛም እንዳትሆን #በቃሉ አንዳች #አትጨምር።>> [ምሳ 30፥6]።

▶️ በመሰረቱ <<አባታችን ሆይ>> በሚለው #የማህበር #ጸሎት ላይ <<እመቤታችን ...ሆይ>> የሚለውን ብቻ ሳይሆን <<ሊቃውንቶች>> የጨማመሩት #ሠላም #ለኪን#ውዳሴ #ማርያምን#አንቀጸ #ብርሃንን#ይወድስዋ #መላዕክትን#መልክዓ #ማርያምን....ወ.ዘ.ተ ደራርበውበታል።

▶️ የካቶሊክ #ቤተክርስቲያንና ሌሎች #እህትማማች ተብለው የሚጠሩት #አብያተ #ክርስቲያናት በኢትዮጵያ ካለው የ<<እመቤታችን.... ሆይ>> ጸሎት #የቃላትና #የይዘት #ልዩነት አለው። የኢትዮጵያ #ኦርቶዶክስ #ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የምትለው፦ <<እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ በመልአኩ በቅዱስ ገብርኤል ሰላምታ ሰላም እንልሻለን በሃሳብሽ ድንግል ነሽ በስጋሽም ድንግል ነሽ የአሸናፊ የልዑል እግዚአብሔር እናት ሆይ ሰላምታ ይገባሻል እንዲሁም ከተወደደው ልጅሽ ከጌታችን ከመድሀኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ይቅርታውን ለምኝልን ኃጢታትችንን ያስተሰርይልን ዘንድ አሜን[1]።>> የሚል ሲሆን #የካቶሊክና#የእህትማማች #አብያተ ክርስቲያናት (የግሪክ፣ የህንድ፣ የአርመን የግብጽ. . .ኦርቶዶክስ) ደግሞ <<ድንግል ወላዲት ሆይ! ማርያም ሆይ፣ ጸጋ የሞላሽ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋራ ነው፤ ከሴቶች ሁሉ የተባረክሽ ነሽ የማህጸንሽም ፍሬ የተባረከ ነው የነፍሳችንን አዳኝ ተሸክመሻልና ደስ ይበልሽ[2]>> #ብቻ ነው የሚለው። ይህ ግን #መጽሀፍ ቅዱስ የማይቀበለውና #መጽሀፍ ቅዱሳዊ #ማስረጃ የሌለው ከንቱ #ፈጠራ ነው።

✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆

"ማጣቀሻዎች - References"
_____________
[1] 📚፤ ጌታቸው አየነው (መምህር)፤ "የዘውትር ጸሎት በአማርኛ"፥ ገጽ 5 ፥አ.አ፥ 1998 ዓ.ም።

[2] 📚፤ የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የጽ/ጠ/ጽ/ቤት ሐዋርያዊ ስራ መምሪያ ፤ "ሕያው እግዚአብሔር" ፤አማርኛ ትርጉም ገጽ 316፤ በገላውዲዎስ ተቋም በአባ ጳውሎስ ጻድዋ ካርዲናል ሊቀጳጳሳት ዘካቶሊካውያን እንዲታተም የተፈቀደ፤ ማስተር ማተሚያ ቤት፤ አ.አ፥ 1989 ዓ.ም።