ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.83K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
391 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
▶️ በመጽሀፍ ቅዱስ #ሴቶች ሰፊ ስፍራ #ከወንዶች #እኩል ተሰጥቷአቸው #እግዚአብሔር ሲጠቀምባቸው እናነባለን። በተለይ #በአዲስ ኪዳን #የእግዚአብሄር ቃል በግልጽ <<አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም፥ ባሪያ ወይም ጨዋ ሰው የለም፥ ወንድም ሴትም የለም፤ ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ ሰው ናችሁና።>> {ገላ 3፥28} ይላል። እንዲሁም <<እግዚአብሔር ለሰው ፊት አያዳላምና።>> {ሮሜ 2፥11}፣ <<በአይሁዳዊና በግሪክ ሰው መካከል ልዩነት የለምና፤ አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና፥ ለሚጠሩትም ሁሉ ባለ ጠጋ ነው፤>> {ሮሜ 10፥12} ይላል።

▶️ በመጽሀፍ ቅዱስ ውስጥ #ከወንዶች ባልተናነሰ አንዳንዴም #በሚበልጥ ሁኔታ #እግዚአብሔር በተለያየ መልኩ የተጠቀመባቸው #ከ87 የሚበልጡ #ሴቶች #ከነታሪካቸው ተጽፏል። ከእነዚህም ውስጥ #ልጅ ባለመውለዳቸው #ሲነቀፉ የነበሩት #እንደነሳራና #ሐና የመሳሰሉ #እግዚአብሔር #ቃል ኪዳን ያለውን #ልጅ በመስጠት #አስደናቂና #ታዋቂ #እናቶች እንዲሆኑ አድርጓቸዋል።

▶️ የተጠቀሱት ሁሉም #ሴቶች #አንድ የሚያደርጋቸው ነገር ቢኖር #መሲሁን (ኢየሱስ ክርስቶስን) ማገልገላቸውና ለእርሱም #መንገድ ማዘጋጀታቸው ነው። ለምሳሌ፦


1፦ ሔዋን፦ #ከሴቲቱ #ዘር የሚመጣው (ኢየሱስ ክርስቶስ) #የእባቡን (የዲያብሎስንና የኃጢአትን) #ራስ #እንደሚቀጠቅጥ የተናገረላትና ይህንንም #ትንቢት በመጠበቅ ለዚህ #ዘር #ሐረግ በመጀመሪያ #አቤልን ከዚያም #ሴትን የወለደች።

2፦ ሩት፦ #ከሞዓባውያን ወገን የነበረች #በእምነት #ከወገኖቿ ተለይታ #ከእግዚአብሄር ህዝብ ጋር በመቀላቀል #እስራኤላዊውን #ቦኤዝን አግብታ #የእሴይን አባት #እዮቤድን በመውለድ ወደ #ክርስቶስ #የዘር #ግንድ ውስጥ ገብታለች።

3፦ አስቴር፦ #ዝርያው እንዲጠፋ የተፈረደበት #የአይሁድ #ህዝብ ወደ #ንጉሡ #በድፍረት በመግባት #ህዝቤን #በመሻቴ #ህይወቴም #በልመናየ ይሰጠኝ በማለት #በህዝቧ ላይ #የታወጀውን #የሞት #ፍርድ በመቀልበስ #ከአይሁድ ወገን ሊመጣ ያለውን #የኢየሱስ ክርስቶስን #ዘር በመጠበቅ የበኩሏን #አስተዋጽኦ አድርጋለች።

▶️ እነ #አቢግያ#ኢያኤል#ኤልሳቤጥ#ቤርሳቤህ#ራሔል#ሊዲያ#ፌበን#ሰሎሜ፣ . . .ወዘተ ሁሉም #እግዚአብሔር የሰጣቸውን #ተግባር ሁሉ #በድል ያከናወኑ አንቱ የሚባሉ #ሴቶች ናቸው።

▶️ ጌታ ኢየሱስ #በአገልግሎቱ #ወቅት #ከፍተኛ #እገዛ ሲያደርጉ የነበሩ በዚያ #አስፈሪ #ሰዓት በሆነው #በስቀለቱም ወቅት #ከመስቀሉ #ግርጌ ስር በስፋት #ሃዘናቸውን የገለጹ #በመቃብሩም ሄደው እንደተናገረው #መነሳቱን #ከቅዱሳን #መላእክት ሰምተው #ለህዝቡ ሁሉ በመጀመሪያ #ትንሳኤውን ያወጁና የእርሱን #መሞትና #መነሳት ... ወዘተ የሚያበስረውን #ወንጌል ይዘው ወጥተው #የግል #ቤታቸውን እንኳ #የወንጌል አደባባይና #ቤተክርስቲያን አድርገው #የእግዚአብሔርን ቃል ሲያስተምሩ የነበሩ #ሴቶች ነበሩ።

▶️ ይህን #ማንሳታችን ያለ ምክንያት ሳይሆን <<ማርያም #ከሴቶች ሁሉ እንዲያውም #ከፍጡራን ሁሉ የበላይ የሆነች #ፍጡር>> የሚል #የተዛባና #መጽሀፍቅዱሳዊ ያልሆነ አስተምህሮ ስላለ ነው። ለዚህም #ትምህርት መነሻው #በሉቃስ 1፥28 እና 1፥42 <<አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ>> ተብሎ የተገለጸው #ቃል ሲሆን <<ቅዱስ ገብርኤል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተልኮ ማርያምን ብሩክት አንቲ እምአንስት - አንቺ ከሴቶች ሁሉ የተለየሽ ሲል ከሴቶች ሁሉ የተለየች መሆኗን በምስጋና ቃል ገልጦ ተናግሯል፤ የዚህን መልአክ ቃል በመደገፍ በማጽናትም ኤልሳቤጥ አንቺ ከሴቶች የተባረክሽ ነሽ ብላ ጮሀና አሰምታ ተናግራለች። ይህም ቃል ቅድስት ማርያምን በነፍስ በሥጋ ቅድስት መሆኗን መትህተ ፈጣሪ መልዕልተ ፍጡራን (ከፈጣሪ በታች ከፍጡራን በላይ) መሆኗን ያጠቃልላል>> ብለው የተረጎሙት ስላሉ ነው[1]። በመሰረቱ ይህ #ትርጉም ሳይሆን #የመጻሐፉን ግልጽ #ቃል በመቀየርና ወደሚፈልጉት የማርያም #አምልኮ በማዞር የተቀመጠ #አስተምህሮ ነው።

▶️ ማርያምን <<ከፍጡራን በላይ ከፈጣሪ በታች>> የሚለውን ቃል #ለመጀመሪያ ጊዜ የገለጸው #በ15ኛው ክፍለ ዘመን ይኖር የነበረው #የደቡብ ወሎ ቦረናው #ሰው #አባ #ጊዮርጊስ #ዘጋስጫ ነው[2]።

▶️ ለዚህ ደግሞ ዋነኛው #ምክንያታቸው ከላይ የተገለጸው #የቅዱስ ገብርኤልና #የኤልሳቤጥ #ንግግር ሲሆን ሌላው እንደ #ምክንያት የሚጠቀሰው ደግሞ #ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን #መውለዷ ነው።

▶️ ከዚህ የተነሳ #ከእግዚአብሄር #ምስጋና #ቀጥሎና #አያይዞ #ማርያምን #ማመስገን እንደሚገባ #ከ15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ቡኋላ #የኢትዮጵያ #ኦርቶዶክስ #ተዋህዶ #ቤተክርስቲያን መጠቀም ጀምራለች። ለምሳሌ፦

〽️ 1፦ <አቡነ ዘበሰማያት(አባታችን ሆይ)> ከሚለው #ጸሎት ቀጥሎ <እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ.... ሰላም እንልሻለን> ማለትን

〽️ 2፦ <ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስቅዱስ (ምስጋና ይሁን ለአብ፣ ምስጋና ለወልድ፣ ምስጋና ለመንፈስቅዱስ ይገባል)" ከሚለው #ቀጥሎ <ስብሐት #ለእግዝትነ #ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ (አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ለድንግል ማርያም #ምስጋና ይሁን)> ማለትን

〽️ 3፦ <ለልዑል እግዚአብሔር ፍጹም #ምስጋና ይገባል> ይባልና ቀጥሎ <ለወለደችው ለድንግል ማርያም #ምስጋና ይገባል> ማለትን

〽️ 4፦ <የእግዚአብሄር ስሙ ፈጽሞ ይመሰገን ዘንድ ዘወትር በየጊዜያቱ በየሰአቱ #ምስጋና ይገባል> ካለ ቡሀላም <እናታችን ማርያም ሆይ ሰላምታ ለአንቺ ይሁን እያልን #እንሰግድልሻለን #እንማልድሻለን> ይላል[3]።
▶️ ምስልና ቅርጻ ቅርጽ በየወቅቱ #በክርስትናው_እምነት ውስጥ ሰርገው ገብተውና #እያደጉ መጥተው ዛሬ እንደሚታየው #ልዩ_አምልኮ እየተሰጣቸው ይገኛሉ። #ህዝበ_ክርስቲያኑ በተለይም #የማርያም_ስዕሎችን #እንዲቀበሏቸውና_እንዲሰግዱላቸው ከተደረገበት ዋና ዋና #ምክንያቶች መካከል፦

〽️ ሀ. ምስሎቿ #ይናገራሉ {ያወራሉ} በሚል ማስፈራራት፦

<<በዚያም ቤተክርስቲያን የእመቤታችን ስዕል ነበረችና ያ ብላቴና ስእሏን እጅግ ይወዳት ነበር። መምህሩ በሄደ ጊዜ ወደ ስዕሉ ቆሞ እጅ ይነሳትና ቅዳሴዋን ይደግም ነበር። ከዕለታት አንድ ቀን ስዕሉ ፊት ቆሞ ሳለ ስእሏ ተነጋገረችው። "ወዳጄ ሆይ አንተ ከምትወደኝ ይልቅ ፈጽሜ ወድጄሀለው! በአንተም ደስ ብሎኛልና በእኔ እመን! አለችው"። ያም ልጅ ከስእል ቃል በሰማ ጊዜ ፈጽሞ አደነቀ እጅግም ፈራ[1]>>

<<የኢትዮጽያ ሰዎች እነዚህን ትዕቢተኞች ራሳቸውን ተከናንበው እግራቸውን ተጫምተው ወደዚች ስዕል ሲገቡና ሲወጡ አይተው እንደ ግብጻውያን ክፉ ልማድ አደረጉ። ወደዚችም ስዕል ጫማ አድርገው ገቡ። . . . እመቤታችንም ወደ እኔ ስዕል ጫማ ተጫምታቹ የምትገቡ መራር ትምህርትና ክፉ ምግባር እንደምን አበቀላችሁ?! አለቻቸው ይህን ብላ የኢትዮጽያን ሰዎች ከስዕሏ በወጣ ቃል ገሰጸቻቸው[2]>>

〽️ ለ. ምስሎቿ ባለቡት #ይንቀሳቀሳሉ፣ የተለያየ #ድርጊትንም_ያደርጋሉ በሚል ማስፈራራት፦

<<በማርያም ስዕል ፊት ሲሰግዱ ስዕሏ ራስዋን ዘንበል አድርጋ ጸሎታቸውንና ስግደታቸውን ተቀበለች[3]>>

<<አባታችንም ከስእሏ ፊት ሲጸልይ እመቤታችን ከስእሉ አናገረችው። ጡቷንም አውጥታ እንካ ጥባ እንደ ልጄም አርጌ አሳድግሀለው አለችው። እርሱም ከጡቷ ጠባ[4]>>

<<አንዲት ሴት የወለደች ነበረች፧ ያቺንም ሴት ልጇን ጅብ ወሰደባት። ወደ ቤተክርስቲያንም ሄዳ በእመቤታችን ስዕል ፊት ቀይ ልጄን እስክምትመልሽልኝ ድረስ ልጅሽን እኔ ከእጅሽ ላይ እወስደዋለው አለች። ከዚያም ማርያም የታቀፈችው ልጇን {"ክርስቶስን ለማለት ነው"} ሰጠቻት፤ ሴትዮዋም ወደቤት ወሰደችው። ማርያምም ወደ ቤቷ መጥታ ጅብ ነጥቆ የወሰደብሽ ልጅሽን ውሰጂ ልጄን ስጪኝ ብላ ተቀበለቻት[5]>>

〽️ ሐ. ምስሎቿ #ሕይወት እንዳላቸው በማስመሰል ማስፈራራት፦

<<አፍርንጊያውም ስእሏን ይወስዳት ዘንድ እንዳልተቻለው ባወቀ ጊዜ ሾተል ይዞ እጁን በመስኮት አዝልቆ ከስእሉ የሥጋ ቁራጭ ያክል ቆረጠ። ያን ጊዜ ከስዕሉ ደም ወጣ። እርሱም የስጋ ቁራጭ ያክል ይዞ ወጥቶ ተሰወረ። ያን ጊዜም ሰዎች አውቀው ፈልገው በጭንቅ አግኝተው ያዙት ፤ይገድሉት ዘንድም ወደዱ። ያን ጊዜ እኔ ስለመውደዱ ክብር ሊሆነው ወስዷል እንጅ ይህን በክፋት አላደረገውምና ተውት አትግደሉት፤ የሚል ቃል ከስዕሉ ተነገረ ነገር ግን የተቆረጠውን ስጋ ከሱ ወስዳቹ ከተቆረጠበት ቦታ ግጠሙት። ያን ጊዜውን አኖሩትና ተጣብቆ ቀድሞ እንደነበረ ሆነ[6]>>

<<ያች ስዕል ስጋን የለበሰች ትመስላለች ከእርሷም እንባና ወዝ ይወጣ ነበር። ከወዙም የተቀቡት ከሚያስጨንቅ ደዌያቸው ይፈወሱ ነበር[7]>>

〽️ መ. በምስሎቿ ፊት #ያልሰገደ #የሞት_ቅጣት እንደሚያስከትል በማወጅ ማስፈራራት፦

<<በስፍሏም ፊት ስገዱ ለስዕሏ ያልሰገዱ ግን ከቆመበት ቦታ ይጥፋ ስም አጠራሩም አይታወቅ[8]>>

<<ለእመቤታችን ስዕል ስላልሰገደ ሞተ[9]>>

<<ወእሰግድ ካዕበ ለድንግልናኪ ክልኤ
ወእሰግድ ሰልሰ ለሥዕልኪ ቅድመ ጉባዔ
ዘኢሰገድ ለስዕልኪ አስሪጾ ምማኤ
በሥጋሁ ወበነፍሱ ኢይርከብ ትንሳኤ>>

ትርጉሙም፦

<<በሁለት በኩል ድንግል ነሽና እሰግድልሻለው
ለሥዕልሽም በጉባኤ ፊት ሶስት ጊዜ እሰግዳለሁ
ለሥዕልሽ ከመስገድ ወደ ኋላ ያለ
በነፍሱም በስጋውም ትንሳኤ አያግኝ[10]>>