ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.82K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
393 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
ተሻሽሎ የቀረበ

መጽሀፈ ሰአታት
💠 "ኪሩቤል አፍራሰ ፌማ፣ ወሱራፌል ዘራማ፣ ክሉላነ ሞገስ ወግርማ፣ ይሴብሑኪ ማርያም በሐዋዝ ዜማ"
💠 " ግርማንና ሞገስን የተቀዳጁ የፌማ ፈረሶች ኪሩቤልና ራማዊው ሱራፌልም ባማረ ዜማ ማርያም ሆይ አንቺን ያመሰግኑሻል"
/ኲሎሙ ዘኪዳነ ምህረት -- ገጽ 109/


▶️ በዚህ ክፍል ላይ ደራሲው #ኪሩቤልና #ሱራፌል ባማረ ዜማ #ማርያምን #እንደሚያመሰግኗት ይናገራል። በእርግጥ እነዚህ #ቅዱሳን #ፍጥረታት #ተጨማሪ አድርገው ወይም #እግዚአብሔርን #ትተው #የሚያመሰግኑት #ሌላ ተመስጋኝ #ፍጡር #እንደተመደበላቸው የሚያሳይ #መፅሀፍቅዱሳዊ መረጃ የለንም። ደግሞም #በሰማይ #ፍጡር #አይመሰገንም፤ ወደዚያች #ከተማ #የገባ ሁሉ #የከተማዋን #ባለቤት #ያመሰግናል፤ <እኔ ልመስገን> የሚል #ፍጡርም የለም።
<ድንግል ማርያምም> በሰማይ #ከአእላፋት #መላእክትና #ከቅዱሳን ጋር ሆና ስለተደረገላት ነገር #ፈጣሪዎን ታመሰግናለች።
ከዚህ ውጪ ግን በዚያ #በሰማይ #ከኪሩቤልና #ከሱራፌል #ውዳሴን #ትቀበላለች ብሎ ማሰብ #በምድር እንኳን #የተወገዘውን #ፍጡራንን #ማምለክ ወደ #ሰማይ ለማውጣትና #በሰማይም #ተቀባይነት ያለው #ለማስመሰል የተደረገ ^ጥረት እንደሆነ #አስተዋዮች አያጡትም።
▶️ የሰማይ አምልኮ በተገለጠበት #በራእይ #መፅሀፍም #ቅዱሳን #መላእክት #በአንዱም አጋጣሚ #ፍጡራንን #ሲያመልኩ #አለመታየታቸው #ትምህርት ሊሆነን ይገባል።
<የጌታን እናት> የሕይወት #ታሪክ በሚገባ የሚያውቁ #ሐዋሪያት እንኳ ምንም #የጌታቸው #እናት ብትሆንም እርሷ #ምስጋናና፣ ውዳሴ #ልትቀበል #እንደሚገባት ለማመልከት #አንድ #ጥቅስ እንኳን አልፃፉልንም።
<< እነሆ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ #ብፅኢት ይሉኛል>>/ሉቃ 1-48/። ብላ ራሷ #ድንግል #ማርያም የተናገረችው #ቃልም ቢሆን እንደ #ኤልሳቤጥ <ከጌታ የተነገረላት ይፈጸማልና ያመነች ብጽኢት ናት>/ሉቃ 1-45/። ብሎ #ስለጌታ #እናት #በሦስተኛ መደብ #ምሥክርነት #መስጠት ማለት ነው እንጅ #እርሷ #ከሞተች ቡሀላ #በጸሎትና #በውዳሴ #በሁለተኛ #መደብ
<< #ማርያም ሆይ #ብጽኢት ነሽ>> ማለትን የሚያመለክት አይደለም።
( <ለድንግል ማርያም የሚጠቀሱ የተለመዱ መጽሀፍ ቅዱሳዊ ጥቅሶችና ማብራሪያቸው> በሚለው ስር ሰፊ ማብራሪያ ያገኙበታል።)

#ሐዋርያትም ለእርሷ የሚሆን #ውዳሴ አላቀረቡም፤ ይህንም አለማዳረጋቸው #በንቀት ሳይሆን #ማድረግ የሚገባቸውን #በውስጣቸው የሚኖር #መንፈስ #ቅዱስ ስለሚያሳያቸው ነው። #በሰማይ ያሉ #መላእክትም ባመሰገኑ ጊዜ ሁሉ #እሷን አለመጨመራቸው ይህን ማድረግ #ስህተት ስለሆነ ነው። በመሆኑም #የሰማይ #ቅዱሳን #ፍጥረታት #የሚያመሰግኑትንና#ምስጋና #የሚገባውን #ጠንቅቀው ስለሚያቁ #ሲያመሰግኑ እንዲህ ይላሉ፤ ፦

<<መጽሐፉን ትወስድ ዘንድ ማኅተሞቹንም ትፈታ ዘንድ #ይገባሃል#ታርደሃልና#በደምህም ለእግዚአብሔር #ከነገድ ሁሉ #ከቋንቋም ሁሉ #ከወገንም ሁሉ #ከሕዝብም ሁሉ #ሰዎችን #ዋጅተህ #ለአምላካችን #መንግሥትና #ካህናት ይሆኑ ዘንድ አደረግሃቸው፥ በምድርም ላይ #ይነግሣሉ እያሉ አዲስን ቅኔ ይዘምራሉ።>>
<<አየሁም፥ በዙፋኑም በእንስሶቹም በሽማግሌዎቹም ዙሪያ የብዙ መላእክትን ድምፅ ሰማሁ፤ ቍጥራቸውም አእላፋት ጊዜ አእላፋትና ሺህ ጊዜ ሺህ ነበር፥ በታላቅም ድምፅ። #የታረደው #በግ #ኃይልና #ባለ #ጠግነት #ጥበብም #ብርታትም #ክብርም #ምስጋናም #በረከትም #ሊቀበል #ይገባዋል አሉ።>> /ራእይ 5፤ 9-12/።
በዚህ ክፍል ላይ #ሲመሰገን የምናየው #ክርስቶስ ነው እንጅ #ድንግል ማርያም አይደለችም።
በአካባቢው መኖሯንም የሚገልጽ ምንም #የመጽሀፍ #ቅዱስ ክፍል የለም። በተጨማሪም እስቲ የሚከተሉትን ጥቅሶች እንመልከታቸው፤ ፦
ራእይ 4-8 , 7-9 , 11-15 , 12-10 , 15-3 , 19፥1።
በእነዚህም #ጥቅሶች #በሙሉ #ከጌታ #በስተቀር #በሰማይ #ማንም #አልተመሰገነም#በመንፈስ #ቅዱስ #ተመርተው #የጌታ #ሰዎች የጻፉት #መጽሀፍ #ቅዱስ በሰማይ #የሚመሰገነውንና ያለውን #የአምልኮ #ስርዓት በዚህ ዓይነት አስቀምጦልናል። ስለሆነም #ያላየነውንና #ያልሰማነውን #በመጽሀፍ #ቅዱስም የሌለውን በሚያስተምሩ #ሰዎች ላይ #በእውነትና #በመንፈስ የሚመለከው #አምላክ ይፈርድባቸዋል። #ከቅዱስ #መጽሐፍ #ሐሳብና #እውነታ በተለየ መንገድ <<በሰማይ ማርያም ትመሰገናለች፤ እነ ሱራፌል ያመሰግኗታል>> ማለቱ ራስን #ሀሰተኛ #ምስክር ማድረግ ነው። ይህም #በእግዚአብሄር ፊት ተጠያቂ ያደርጋል። ምክንያቱም #በእውነተኛው #ቅዱስ #መጽሀፍ #ባለመመዝገቡና #እውነት ባለመሆኑ ነው። ስለሆነም #ኪሩቤልና #ሱራፌል እንዲህ ያለውን #ስህተት ይፈጽማሉ ብሎ #መመስከሩ #የሀሰት #ምስክር #ያሰኛል እንጂ #ማርያምንም ሆነ #ኪሩቤልን ደስ ማሰኘት እንዳልሆነ #መገንዘብ ይገባል። ዩሐንስ #በራእይ ያን ሁሉ #ምስጋና ሲያይ አንዴ እንኳ <ድንግል ማርያም> #ስትመሰገን አልሰማም። በመሆኑም #ኪሩቤልና #ሱራፌል <<የታረደውን በግ>> ብቻ #እንደሚያመሰግኑ #መመስከሩ በቂ ነውና እንዲህ የሚያደርጉትን <<ከተጻፈው አትለፍ>> /1ቆሮ 4፥6/ የሚለውን #የተቀደሰ #መመሪያ ተማሩ እንላቸዋለን።


@gedlatnadersanat
▶️ እነዚህ #አለባበሶች ግን አሁን #በቤተ መቅደስ ውስጥ እንዲያገለግሉ አድርጋ #የኢትዮጵያ ኦ.ተ.ቤተ ክርስቲያን ከመደበቻቸው #የካህናት አለባበስ #በቁጥርም#በመልክም #በዲዛይንም እጅግ #የተራራቀ ነው። በብሉይ ኪዳን የነበሩት #የሊቀ ካህናት አለባበስ አንድ በአንድ መግለጽ አጀንዳችን ስላልሆነ እኛም እንደ #ጳውሎስ <<ስለእነዚህ እንዳንተርክ አሁን አንችልም>> {ዕብ 9፥5}። ይሁን እንጂ #በቤተ መቅደሱ (ቅድስተ ቅዱሳን) ውስጥ #ሴቶች ፈጽሞው የሚገቡበት ሁኔታ አልነበረም።

ይኸው #ካህን እንኳ በተገቢ ሁኔታ አለባበሱን አስተካክሎና ስለራሱ #ኃጢአት #መስዋዕትን በቅድሚያ አቅርቦ የህዝቡን #ኃጢአት የሚያስተሰርይበትን #መስዋዕት ይዞ በብዙ #ፍርሃት #መጋረጃውን ገልጦ ቢገባ #በታቦቱ #መክደኛ ላይ በወረደው #ደመና #ዓምድ መሰረት #እግዚአብሔር ያናግረዋል። ነገር ግን #ሊቀ ካህኑ #ባይቀደስና በተገቢው ሁኔታ #አለባበሱን #ሳያስተካክል ቢቀርና የመሳሰሉት ነገሮች ባያሟላ እዚያው #ይቀሰፍና #ይሞታል። በውጭ #በአደባባይ የተሰበሰበው #ምህረት ጠባቂ ህዝብ #ካህኑ ቢዘገይባቸውም #እንደተቀሰፈና #እንደሞተ ስለሚገባቸው #በወገቡ ላይ እስከውጨኛው ድረስ በታሰረው #ሰንሰለት ጎትተው ያወጡታል እንጂ እንኳንስ #ሴቶች #ወንዶች እንኳ ገብተው በፍጹም #ሬሳውን አያወጡም።
እንግዲህ ይኸው #ስርዓት በተሟላ መልኩ #ከድንኳንነት ወደ #ህንጻ ቤት ተቀይሮ #የዳዊት ልጅ #ሰለሞን #በኢየሩሳሌም እጅግ ውብ አድርጎ ሰራው። #የሰለሞን #ቤተመቅደስ #ሴቶች #ከአደባባዩ ውጭ ባለው #ዓምድ እንደ #ሃና #ይፀልያሉ እንጂ {1ኛ ሳሙ 1፥9} በጭራሽ #በቅድስተ ቅዱሳኑ (በቤተመቅደሱ) ውስጥ #ሴቶች አይገቡም ነበር።
▶️ ይህም #ቤተመቅደስ #ማርያም በነበረችበት #ዘመን የነበረ ሲሆን ሁሉም #ሴቶች #በቁ.4 ላይ በተገለጸው ውስጥ በፍጹም #አይገቡም ነበር። ይሁን እንጂ #በውጭ (በተራ ቁ.7 ላይ) በተገለጸው #አደባባይ ላይ እንደ #የ91 ዓመቷ ዕድሜ #የፋኑኤል ልጅ #ሃና #ነብይት ዓይነቶች {ሉቃ 2፤ 36-38} #መቆም ይችሉ ነበር።

እስከዛሬም ድረስ የትኛዋም #ሴት ብትሆን #ቤተመቅደስ (ቅድስተ ቅዱሳን) ውስጥ #መግባት አልቻለችም። #ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን #ሴቶች ወደ #ቤተ መቅደስ እንዲገቡና #በመቅደስ ውስጥ #እንዲጸልዩ ለአፍታ እንኳ አለመፍቀዷ የራሷ #ስርዓት #ይደነግጋል[1]።
ታድያ #ማርያም በየትኛው #ቦታ በየትኛው #ቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ #መኖሪያዋ አድርጋ አደገች? አዎን #ማርያም #ቤተ መቅደስ ነበረች የሚለው #ሃሳብ ከየት መጣ ቢባል #ከቁርዓን ነው {ሱረቱ አልዒምራን 3፥37}። እርሱም #ስለቤተ መቅደሱ ሁኔታ #እውቀት የለውምና አይፈረድበትም።
ይህ #ለከንፈርሽ#ለጉሮሮሽ#ለጡትሽ#ለሽንጥሽ#ለሆድሽ#ለኩላሊትሽ#ለአንጀትሽ#ለእንብርትሽ#ለማህፀንሽ#ለድንግልናሽ#ለተረከዝሽ#ለጫማዎችሽ#ለእግር ጥፍርሽ፣ #ለመቃብርሽ፣ የሚለው #መልክእ በየዕለቱ #በግልና #በጋራ በመከፋፈል #በቤተክርስቲያን ደረጃም፣ #በቃልም#በመጽሐፍም ይደገማል።

▶️ እንግዲህ ይህ #አይነቱ #ምስጋና እንኳንስ #ለማርያም #ለክርስቶስ እንኳ ብናረገው #መጽሀፍ ቅዱሳዊ አይደለም። ሁሉም ከዚህ #አለም ወደ እዛኛው #አለም #በነፍሳቸው የተሻገሩ #ሰዎች #በምድር በነበሩበት #በስጋዊ ዘመናቸው #ከልጅነት እድሜ #እውቀት ወደ #አዋቂ #ሲያድጉ#ሲበርዳቸው #ሲሞቃቸው#ሲያዝኑ#ሲደሰቱ#ጥፍራቸውና #ጸጉራቸው ሲያድግ፣ #ሲያጥር#ሰውነታቸው #ሲቆሽሽና ሲታጠብ.... ወዘተ እንደነበረው ሁሉ #በሰማይ እንደዛ አይታወቁም። #ሰማይ ሌላ #ስርዓት ነውና።

▶️ ስለዚህ #ድንግል ማርያም #በአጸደ ነፍስ ባለችበት #በሰማይ እንደ #ምድራዊ #ስጋ #አካል #ጥፍሯ በየቀኑ አያድግም፣ #ጡቶቿም ወተት #አያፈልቁም#አንጀቶቿም በሀዘን #አይቃጠሉም#ተረከዞቿም #ድጥ አያድጣቸውም፣ #እግሮቿም #ጫማ የላቸውም። <<ደግሞ ሰማያዊ አካል አለ፥ ምድራዊም አካል አለ፤ ነገር ግን የሰማያዊ አካል ክብር ልዩ ነው፥ የምድራዊም አካል ክብር ልዩ ነው።>> {1 ቆሮ 15፥40}። ስለሆነም #መልክዓ ማርያምና ተመሳሳይ #መጻሕፍት #ለአዕምሮ የማይመች #መጽሀፍ ቅዱሳዊ ያልሆነ #አጸያፊ #ስነ ጽሁፍ እንጂ #ጸሎት ሊሆን በፍጹም አይችልም።

✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆

"ማጣቀሻዎች - References"
____________
[1] 📚፤ አለቃ ኪዳነ ወልፍ ክፍሌ ፤መጽሐፈ ሰዋሰው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ፤ መልክእ፤ ገጽ 566፤ አርቲስቲክ ማተሚያ ቤት፥ አ.አ 1948።