ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.83K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
391 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
▶️ ሰው #በእግዚአብሄር #መልክና #አምሳል ስለተፈጠረ #ከእግዚአብሄር ጋር ለመገናኘት ሲፈልግ #መገናኛ መንገዱ #ጸሎት ነው። #ጸሎት #ከእግዚአብሄር ጋር ያለን የመገናኛ #ምልክትና የግንኙነታችን #ማጽኛ ነው። #ጸሎት #ህብረትን#ምስጋናን#ስግደትን#ንስሀን#ልመናን#ምልጃን ሁሉ ያጠቃልላል። ይህንንም #ሰዎች በራሳቸው #ቋንቋ#ቦታና #ጊዜ ሊያከናውኑት ይችላሉ። ዋናው ነገር #የልብ #መሰበር ነው [ዩሀ 4፤ 20-24]።

▶️ የሁሉም ሰዎች #ጸሎት አድራሻው ሁሉን #ለእርሱ #በራሱ #ለራሱ ወደ ፈጠረው ወደ #እግዚአብሔር #ብቻ እንደሆነና ወደ እሱ #ብቻ ሊሆን እንደሚገባው #መጽሀፍ ቅዱስ ይመሰክራል [ኢዮ 38፥41 ፣ ሉቃ 12፥24]። ለዛ ነው ዳዊት <<ሥጋ ለባሽ ሁሉ ጸሎትን ወደ ምትሰማ ወደ አንተ ይመጣል>> በማለት የተናገረው። [መዝ 65፥2 ]። ሌላ #ጸሎትን #መስማት የሚችል አካል የለም ማለት ነው[1]።

▶️ ጸሎት #ለክርስቲያኖች ሁሉ የተሰጠ #መለኮታዊ #ትእዛዝ ነው [1ተሰ 5፥17 ፣ ማር 14፥38]። አንዳንድ ጊዜ #እግዚአብሔር የሁሉም #አባት እንደመሆኑ መጠን ምንም እንኳን #መብታቸው ባይሆንም #መጋቤ #ዓለማት የሆነው ጌታ #በቸርነቱ #ለማያምኑና #ላልጸለዩም ሰዎችና ፍጥረታት ሁሉ #ይመግባቸዋል [ሐዋ 10፤ 1-6፣ ማቴ 6፥8]። ይሁን እንጂ አንድ #ሰው #ለመጸለይ ሲያስብ ግን መጀመሪያ #እግዚአብሔር እንዳለ ለሚፈልጉትም #ዋጋ #እንደሚሰጥ በእርግጠኝነት #ማመን ያስፈልገዋል [ዕብ 11፥6]። ከዚህ #አንጻር በቀጥታ ወደ #እግዚአብሔር ያልሆኑ ነገር ግን ወደ #ማርያም የሆኑ #ጸሎቶችን #ክርስቲያን ሊቀበላቸው የማያስፈልጉበት #ዋና #ዋና #ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው፦

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆

"ማጣቀሻዎች - References"
____________
[1] ወደፊት <ጸሎት> በሚል ርእስ በሰፊው የምናየው ይሆናል።
▶️ የሰው ልጅ #ሃሳቡን ከሚገልጽባቸው አያሌ ነገሮች አንዱ #ሥዕል ነው። #ሥዕላት #የሰውን ልጅና #የተፈጥሮን #የኑሮ #መልክና #ጸባይ በማንጸባረቅ መልሰው ለሰው ልጅ #የሚያስተምሩ#ታሪክን #መዝግበው የመያዝ #አቅማቸው ብርቱ የሆነና #በስልጣኔውም መስክ የበኩላቸውን #መረጃ ዘግበው በመያዝ ከፍተኛ #አስተዋጽኦ ያደረጉ ናቸው። #ሥዕላት ወደ #ቤተክርስቲያን ከመግባታቸው በፊት #በአህዛብና #በአይሁድ ዘንድ #ከአምልኮት ጋር በተያያዘ መልኩ በስፋት #ይገለገሉባቸው ነበር።

በተለይ #እስራኤላውያንና ቀደምት #የሀይማኖት #አባቶች #ሥዕላትን #ለቤተክርስቲያን አገልግሎት ሲያውሉ ማንኛውም #ጽሁፍን ማንበብ ለማይችል #ሰው #የክርስቶስን #ህማማቱን#መሰቀሉን#መሞቱን#መቀበሩን#መነሳቱንና #ማረጉን ደግሞም ተመልሶ እንደሚመጣ #ለመስበክ እንዲጠቅሙ በማድረግ ነበር።

▶️ ሥዕሎቹን #በተራራ ገመገም፣ #በሰሌዳ ላይ፣ #ድንጋይ #በመጥረብና #በመፈልፈል#በዛፍ #ቅጠልና #ቅርፊት ላይ፤ ቡኋላ ቡኋላም እየቆየ ሲሄድ #ከፍየልና #ከበግ ቆዳ ላይ ሁሉ #እጽዋትን #በቀለምነት በመጠቀም ለማስተማሪያነት ይጠቀሙበት ነበር። እንደውም አስተምረው ከጨረሱ ቡሀላ አንዳንዶቹን #ስዕሎች በቋሚነት #የማስተማሪያ #መሳሪያቸው አርገው እስከ ረጅም #የህይወት #ዘመናቸው በመጠቀም #ለተማሪዎቻቸው ከሚያወርሷቸው #ሃይማኖታዊ ንብረቶች ውስጥ ዋነኛውን #ስፍራ የያዙት #ሥዕላት ነበሩ።

▶️ ቀስ በቀስ #ሥዕሎችና #ቅርጻቅርጾች (ምስሎች) እየበዙ በመምጣታቸው በተለይም #በቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ #በግድግዳ ላይ በብዛት #በመንጠልጠላቸውና ልዩ #ትኩረት እየሳቡ በመምጣታቸው ምክንያት #በ8ኛው መቶ ክፈለ ዘመን #በክርስቲያኖች መካከል <<አምልኮ ባእድ እየሆኑ መተዋል>> በማለት #ከፍተኛ #ክፍፍልና #ጭቅጭቅን ፈጥሩ።

▶️ በ726 ዓ.ም #የቢዛንታይን መሪ የነበረው " #አጼ #ሊያ #ሳልሳዊ[1]" ምስሎችን #ማመን አጥብቆ #ተቃወመ። በዚህ ምክንያት #ፀረ ምስል ተናጋሪዎችና #ምስል ደጋፊዎች ወደ #ከረረ #ግጭት ውስጥ ገቡ። ይሄው ንጉስ #በ730 ዓ.ም ውሳኔውን #አጽንቶ #በግዛቱ #ምስሎችን ጥቅም ላይ መዋላቸውን #አገደ#በምስል #አፍቃሪያን ላይም ከፍትኛ #ስደትን አስከተለ።

▶️ ከዚህም የተነሳ በተለይ #ሊዎንን ተክቶ የነገሰው " #አፄ #ቆስጠንጢኖስ 5ኛ[2]" <<ክርስትናውን ለማጽዳት>> በሚል በርካታ #ምስል #አፍቃሪያን የነበሩትን #የሃይማኖት #መሪዎች እንዲገደሉ አደረገ። ብዙም ሳይቆይ #አፄ #ቆስጠንጢኖስ 5ኛ በመሞቱ ምክንያት ብዙ #መንፈሳዊ #እውቀት ያልነበራት የነገሩን #አሳሳቢነት የተመለከተች #የንጉስ አፄ #ቆስጠንጢኖስ #ባለቤት (ሚስት) የሆነችው #ኢፌኔ ከሁሉም #ክርስቲያን ሃገሮች የተዉጣጡ #የሃይማኖት #አባቶችን #በ784 ዓ.ም #በኒቂያ ጉባዔ ጠራች። ጉባዔውም #ሁለተኛው #የኒቂያ #ጉባኤ በመባል ተሰየመ[3]።

▶️ በዚህ #ጉባዔ በርካታ #አጀንዳዎች ቢኖሩም በተለይ #የሰንበት ቀን [እሁድ] ልዩ #ከበሬታ እንዲኖረው ፣ #ምስሎች ደግሞ #በአስተማሪነታቸውና ምስሉ የሚወክለውን #አካል #ማክበር ስለሆነ #በቤተክርስቲያን #ግድግዳ ላይ #በክብር #እንዲሰቀሉና ልዩ #ክብር እንዲሰጣቸው ብሎም #እንዲሰገድላቸው ጉባዔው ወስኗል።

▶️ ይህን ውሳኔ #ኦርቶዶክስ #ቤተክርስቲያን {ምስራቃውያን} እና #ካቶሊካውያን {ምዕራባውያን} ተቀብለው #ምስሎችን #ማክበር ጀመሩ። በተለይ #የግሪክ #ኦርቶዶክስና #የሊባኖስ #ማሮናይት #ቤተክርስቲያን የማርያምንና #የክርስቶስን #ስቅለት የሚያሳይ #ስዕል በመሳል በአጥቢያዎቻቸው #ግድግዳ ላይ ሲሰቅሉ በጊዜው #በምዕመኖቻቸው ዘንድ ከፍተኛ #ተቃውሞ ስለገጠማቸው <<ይህችን ስዕል የሳለው ወንጌላዊው ሉቃስ ነው ፤ የጌታችንንም ስቅለት የሳለው ዩሀንስ ነው ሲወርድ ሲዋረድ የመጣልን መመሪያ ነው>> በማለት #እንግዳ #ትምህርት ማስተማር ጀመሩ[4]።