#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
❤️ፌናን
===
‹‹ምነው የስራ መልቀቂያ ልታስገቢ ነው እንዴ የመጣሽው……?››አለኝ
‹‹አይ አይደለም››
‹‹እና ታዲያ እኔ እንደሆነ አልጠራውሽም …ልጠራሽ የምችልበት ምክንያትም የለኝም .. መልክ መልካምነት ከልዩ ስነምግባር ጋር አሞልቶ የሰጣት ፀሀፊዬ መጥታ ገላግላኛለች….››አለኝ የአሹሙር ለዛ ባለው ንግግር
‹‹በጣም ደስ ይላል…እወነትህን ነው ትሁትና ምርጥ ልጅ ነች..በነገራችን ላይ ከባሏ ጋር አብረን ነው የተማርነው …እሱን ብታየው ደግሞ ዋው.. የሚያሰኝ ውበት ያለው አፍ አስከፋች ሸበላ ልጅ ነው፡፡››አልኩት
የተኮስኩት የነገር ጥይት በትክክል አዕምሮውን መቶታል …በግርምትም በንዴትም አይኖቹን በልጥጦ ‹‹ስለስራ እኮ ነው እያወራሁሽ ያለሁት..ፀሀፊዬ ጎበዝ ሰራተኛ ነች ተስማማታኛለች ነው ያልኩሽ..ስለባሏ ውበት በዚህ አይነት ግነት ለእኔ መንገሩ ለምን አስፈለገ……?››
‹‹አይ እንዲሁ ለጠቅላላ ዕውቀት ያህል ነው…በዛውም እኔም የእሷ አድናቂ መሆኔን እንድታውቅ ፈልጌ ነው››
‹‹የእሷ ወይስ የባሏ…?››መልሶ ተኮሰብኝ
‹‹የሁለቱም››
‹‹እሺ አሁን ለምን መጣሽ…?ስራ እየተዉ በየቢሮው መዞር የስነምግባር ብልሹነት መሆኑን አታውቂም? ››
‹‹አውቃልው ግን አመጣጤ ስታዛጋ ሰምቼ ነው …አስር ደቂቃ ካለህ እዚህ ፊት ለፊታችን ካለ ካፌ አሪፍ የጀበና ቡና ስላለ ልጋብዝህ ስለፈለኩ ነው››
‹‹ምን…?››አደነጋገጡ አብረን እንደር ያልኩት ነው ያስመሰለው…
‹‹ምነው..…?አስር ደቂቃ እኮ ነው›››
‹‹አይ ይቅርብኝ ቡና አልጠጣም…››
‹‹ማኪያቶ ግን ትጠጣለህ…››
….ምንም ሳይለኝ ከመቀመጫው ተነሳና ጃኬቱን ከማንጠልጠያ ላይ በማንሳት እየለበሰ በተቀመጥኩበት ጥሎኝ ቢሮውን ትቶ ወጣ…. ከኃላ ተከተልኩት…እርምጃዬን ከእሱ ማስተካከል አልቻልኩት…. ሊፍት ውስጥ ቀድሞ ገባ ተከትዬው ገባው…ልክ ከረሜላ ከአፉ የነጠቁት ህፃን ይመስል ለንቦጩን ጥሏል….በውስጤ የታፈነውን ሳቅ እንዳያመልጠኝ የተጨነቅኩትን ጭንቀት ልገልጽላችሁ አልችልም፡፡
ከህንፃው ወጥተን መንገዱን እንደያዝን እርምጃዬን ከእርምጃው አስተካከልኩ…ስጠመዘዝ ተጠመዘዘና ተከትሎኝ ካፌ ገባ…
‹‹ምን ይምጣልህ ……?››ወንበር ይዘን እንደተቀመጥን ጠየቅኩት
‹‹ምን አገባሽ›› አለና አስተናጋጇን ጠርቶ ማኪያቶ አዘዘ እኔ የጀበና ቡና አዘዝኩ
‹‹አሁን በትክክል ወስኜያለው››
‹‹ምኑን…? ›››አልኩት
እዚህ ካምፓኒ እግሬ እንደረገጠ አንቺን ለማባረር መወሰኔ ቀድሞውንም ትክክለኛ ውሳኔ ነበር….አሁንም ቢሆን ስራዬን በትክክል ለመሳራት ቅድሚያ ማድረግ ያለብኝ አንቺን ማሰናበት ነው…ደግሞ በመከርሺኝ መሰረት የአሰሪና ሰራተኛ ህጉን አንብቤዋለው..እናም በውል ስምምነታችን መሰረት አሁን እንደገባን የ30 ቀን ማስጠንቀቂያ እንዲደርስሽ አደርጋለው…ከዛ ደግሞ የወር እረፍት ትሞያለሽ…ከዛ ከፊቴ ገላል አደረግኩሽ ማለት ነው..ከዛ ጊዜሽ ሲያልቅ ደሞዝሽም ሆነ ሌሎች የሚገባሽን ጥቅማ ጥቅሞች ባለሽበት ይላክልሻል… አይዞሽ አትጨነቂ እኔ እንዳአንቺ አይደለውም የስራ ልምድሽ ላይ የማቃቸውን ስርዓት አልበኝነትሽን እና ታዛዤ አለመሆንሽን አልፅፍብሽም…››አለኝ…. አገኘውሽ የሚል የአሸናፊነት ኩራት ባለው ንግግር…
‹‹በነገራን ላይ የሥራ ልምድ ስትል በዚህች ሀገር ለአንድ ሰራተኛ የሚሠጥ የስራ ልምድ ማስረጃ ከሰውዬው ብቃት ጋር ሃማሳ ፐርሰንት እንኳን ተመሳሳይነት ካለው በጣም ጥሩ ነው….አንድ ሰው ስራ ለመቀጠር አምስት የስራ ልምዶች ይዞ ከመጣ በእርግጠኝነት ሶስቱ ፎርጂድ ይሆናል..የቀረው ደግሞ የሶሻሊስት ፓርቲ መፈክር ይመስል በብቃታቸው የተመሰከረላቸው…በችሎታቸው ወደርአልባ..በፀባያቸው ምስጉን የሚሉ ግነቶች የታጨቁበት በቃ ምን ልበልህ እንደውም በብዙ መስሪያ ቤቶች ደብዳው አንዴ ይፃፍል ሰራተኛው የስራ ልምድ ሲጠይቅ ስም እና የደሞዝ መጠን የሚገልፀው ቁጥር ብቻ እየተቀየረ ነው ፕሪንት በማድረግ የሚሰጠው…...እና ይሄ የስራ ልምድን ዓላማ ማርከስና ሀገርንም መግደል …ሰውዬው ገብቶ በለቀቀባቸው መስሪያ ቤቶች ሁሉ በተመሳሰሳይ ሁኔታ ስለጀግንነቱ ብቻ የሚያትት ልብ ወለዳዊ ምስክርነት የሚሠጠው ከሆነ ለምን ብሎ እራሱን ያሻሸላል……?እና ለማለት የፈለኩት አንተ ምርጥ ሀለቃ ስለሆንክ ያልከውን አታደርግም… ስለእኔ በትክክል የሆንኩትን እና ያልሆንኩትን..የምችለውንና የሚጎድለኝን በትክክል በመዘርዘር ነው የምትሸኘኝ…ጉድለቴን መፃፍህ እኮ የሚቀጥረኝ መስሪያ ቤት በመጀመሪያውኑ ስለእኔ እውነቱን አውቆት እንዲቀጥረኝና እና ጉድለቴንም እንዳሻሽል ስልጣና በማመቻቸት እንዲያግዘኝ ቅድሚያ መረጃ ይሰጠዋል፡፡
‹‹እሺ እንዳልሺን አደርጋለው…ስርዓት አልበኝነትሽን እና ወደ ላይ ያለአቅምሽ በመንጠራራት ሚስተካከልሽ እንደሌላ ቦልድ ተደርጎ እንዲፀፍልኝ አደርጋለው››አለኝ…. በዚህ ጊዜ ያዘዝነው ቡናና ማኪያቶ መጥቶልን ነበር….
‹‹አመሰግናው..ግን ከመባረሬ በፊት አንድ ነገር እንድታደርግልኘ እፈልጋለው››
‹‹ጠይቂኝ..››
‹‹ይሄንን ፈርምና ለመጨረሻ ጊዜ ዘና ብዬ ሁላችሁንም ተሰናብቼ ልልቀቅ..››ወረቀቱን አቀበልኩት…ገልጦ አየውና እስከዛሬ ካፈጠጠብኝ በላይ አፈጠጠብኝ…
‹‹ደግሞ ከአቶ ሰይፉ ሰርቄ ነው ያመጣሁት ..ለእሳቸወ ከነገርክብኝ አለቀልኝ››
‹‹ስንቴ ነው የሚያልቅልሽ……?ከእዚህ ካማፓኒ እህል ውሀሽ እኮ ተበጥሶል….ምንም የቀረሽ ነገር የለም››
‹‹ቢሆንም ..››
‹‹በይ ከሰረቅሽበት ቦታ መልሺ››ብሎ ወረቀቱን መልሶ አስታቀፈኝ
‹‹ይሄውልህ ..ይሄንን መፈረም ከማንም በላይ ላንተ ነው የሚጠቅምህ..››
‹‹እንዴት ብሎ ነው ሁለት ቀን ስራ መፍታት እና 3 መቶ ሺ ብር ማውጣት ሊጠቅመኝ የሚችለው……?››
‹‹አንደኛ ይሄ ለአስር አመት በካምፓኒው የቆየ ልምድ ነው፤ለዛውም ውጤታማ ልምድ፡፡ የካምፓኒውን የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ግባና ተመልከት …ምንጊዜም ከዚህ ዝግጅትና መዝናናት ቡኃላ ባሉ ሶስትና አራት ተከታታይ ወራቶች የእያንደንዱ ሰራተኛ የስራ አፈፃፀም ውጤት በሚገርም መጠን ነው የሚያድገው..የሄንን ያወጣሀውን 3 መቶ ሺ ብር በአንድ ወር ውስጥ እጥፍ ሆኖ ይመለሳልሀል፡፡ በአመታዊ ክብረ በዓሉ ካምፓኒው ከደሞዛቸው ውጭ በሆነ ብር የሆነ ነገር ስላደረጋቸው.የእኔነት ስሜት እንዲያድርባቸው ያደርጋል…፡፡፡ሁለተኛ ሰው በስራ በጣም ውጤታማ የሚሆነው በጣም ዘና ባለበት ጊዜ ነው…ለቀናትም ቢሆን ወደ ሆነ ሀገር ሄደው አየር መቀየራቸው ፤ ያላዩትን ነገር ማየታቸው መንፈሳቸው እንዲታደስ የስራ መነሳሳታቸው እዲጨምር እና ለህይወት ያላቸውም ጉጉት እንዲያንሰራራ ያደርጋል…፡፡ሌላው ያው ሰው ሆኖ መቼስ አንድ ላይ ሲሳራ በተለያየ ምክንያት የተጋጨ የተኮረፈ ይኖራል.. ልክ እደእኔና አንተ ማለት ነው..አንድ ላይ እየሰሩ ደግሞ ቅሬታ ውስጥ መግባት የስራ ጥራትንና ውጤትን በጣም እደሚቀንስ የታወቀ ነው፣እና እንዚህ አይነት ሰዎች ከስራ መንፈስ ውጭ ሆነው እንዲህ አይነት ቦታ ሲሄዱ መንፈሳቸው ከውጥረት የራቀና ዘና ለማለትም ዝግጁ ስለሚሆን ሁሉም ከገባበት ቅሬታ በቀላሉ ይወጣና እርስበርስ ይቅር ይባባላል፡፡ ሌላው በስራ ብቻ የሚተዋወቅ እና ግንኙነቱ በአየር ላይ የሆነ ሰው ግንኑነቱን በአንድ እስቴፕ ያሳድጋል…የተሸለ መግባባት እና አንዱ የአንደን ድክመት እና ጥንካሬ በተወሰነ መልኩ ለመረዳት እድል ያመቻችለታል… አንዳችን ያንዳችንን ፀባይ ፤ ድክመትና ጥንካሬ ማወቃችን እርስ በርስ ለመረዳዳት ተከባብረን እና ተደማምጠን ውጤታማ ለመሆን ያግዘናል...
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
❤️ፌናን
===
‹‹ምነው የስራ መልቀቂያ ልታስገቢ ነው እንዴ የመጣሽው……?››አለኝ
‹‹አይ አይደለም››
‹‹እና ታዲያ እኔ እንደሆነ አልጠራውሽም …ልጠራሽ የምችልበት ምክንያትም የለኝም .. መልክ መልካምነት ከልዩ ስነምግባር ጋር አሞልቶ የሰጣት ፀሀፊዬ መጥታ ገላግላኛለች….››አለኝ የአሹሙር ለዛ ባለው ንግግር
‹‹በጣም ደስ ይላል…እወነትህን ነው ትሁትና ምርጥ ልጅ ነች..በነገራችን ላይ ከባሏ ጋር አብረን ነው የተማርነው …እሱን ብታየው ደግሞ ዋው.. የሚያሰኝ ውበት ያለው አፍ አስከፋች ሸበላ ልጅ ነው፡፡››አልኩት
የተኮስኩት የነገር ጥይት በትክክል አዕምሮውን መቶታል …በግርምትም በንዴትም አይኖቹን በልጥጦ ‹‹ስለስራ እኮ ነው እያወራሁሽ ያለሁት..ፀሀፊዬ ጎበዝ ሰራተኛ ነች ተስማማታኛለች ነው ያልኩሽ..ስለባሏ ውበት በዚህ አይነት ግነት ለእኔ መንገሩ ለምን አስፈለገ……?››
‹‹አይ እንዲሁ ለጠቅላላ ዕውቀት ያህል ነው…በዛውም እኔም የእሷ አድናቂ መሆኔን እንድታውቅ ፈልጌ ነው››
‹‹የእሷ ወይስ የባሏ…?››መልሶ ተኮሰብኝ
‹‹የሁለቱም››
‹‹እሺ አሁን ለምን መጣሽ…?ስራ እየተዉ በየቢሮው መዞር የስነምግባር ብልሹነት መሆኑን አታውቂም? ››
‹‹አውቃልው ግን አመጣጤ ስታዛጋ ሰምቼ ነው …አስር ደቂቃ ካለህ እዚህ ፊት ለፊታችን ካለ ካፌ አሪፍ የጀበና ቡና ስላለ ልጋብዝህ ስለፈለኩ ነው››
‹‹ምን…?››አደነጋገጡ አብረን እንደር ያልኩት ነው ያስመሰለው…
‹‹ምነው..…?አስር ደቂቃ እኮ ነው›››
‹‹አይ ይቅርብኝ ቡና አልጠጣም…››
‹‹ማኪያቶ ግን ትጠጣለህ…››
….ምንም ሳይለኝ ከመቀመጫው ተነሳና ጃኬቱን ከማንጠልጠያ ላይ በማንሳት እየለበሰ በተቀመጥኩበት ጥሎኝ ቢሮውን ትቶ ወጣ…. ከኃላ ተከተልኩት…እርምጃዬን ከእሱ ማስተካከል አልቻልኩት…. ሊፍት ውስጥ ቀድሞ ገባ ተከትዬው ገባው…ልክ ከረሜላ ከአፉ የነጠቁት ህፃን ይመስል ለንቦጩን ጥሏል….በውስጤ የታፈነውን ሳቅ እንዳያመልጠኝ የተጨነቅኩትን ጭንቀት ልገልጽላችሁ አልችልም፡፡
ከህንፃው ወጥተን መንገዱን እንደያዝን እርምጃዬን ከእርምጃው አስተካከልኩ…ስጠመዘዝ ተጠመዘዘና ተከትሎኝ ካፌ ገባ…
‹‹ምን ይምጣልህ ……?››ወንበር ይዘን እንደተቀመጥን ጠየቅኩት
‹‹ምን አገባሽ›› አለና አስተናጋጇን ጠርቶ ማኪያቶ አዘዘ እኔ የጀበና ቡና አዘዝኩ
‹‹አሁን በትክክል ወስኜያለው››
‹‹ምኑን…? ›››አልኩት
እዚህ ካምፓኒ እግሬ እንደረገጠ አንቺን ለማባረር መወሰኔ ቀድሞውንም ትክክለኛ ውሳኔ ነበር….አሁንም ቢሆን ስራዬን በትክክል ለመሳራት ቅድሚያ ማድረግ ያለብኝ አንቺን ማሰናበት ነው…ደግሞ በመከርሺኝ መሰረት የአሰሪና ሰራተኛ ህጉን አንብቤዋለው..እናም በውል ስምምነታችን መሰረት አሁን እንደገባን የ30 ቀን ማስጠንቀቂያ እንዲደርስሽ አደርጋለው…ከዛ ደግሞ የወር እረፍት ትሞያለሽ…ከዛ ከፊቴ ገላል አደረግኩሽ ማለት ነው..ከዛ ጊዜሽ ሲያልቅ ደሞዝሽም ሆነ ሌሎች የሚገባሽን ጥቅማ ጥቅሞች ባለሽበት ይላክልሻል… አይዞሽ አትጨነቂ እኔ እንዳአንቺ አይደለውም የስራ ልምድሽ ላይ የማቃቸውን ስርዓት አልበኝነትሽን እና ታዛዤ አለመሆንሽን አልፅፍብሽም…››አለኝ…. አገኘውሽ የሚል የአሸናፊነት ኩራት ባለው ንግግር…
‹‹በነገራን ላይ የሥራ ልምድ ስትል በዚህች ሀገር ለአንድ ሰራተኛ የሚሠጥ የስራ ልምድ ማስረጃ ከሰውዬው ብቃት ጋር ሃማሳ ፐርሰንት እንኳን ተመሳሳይነት ካለው በጣም ጥሩ ነው….አንድ ሰው ስራ ለመቀጠር አምስት የስራ ልምዶች ይዞ ከመጣ በእርግጠኝነት ሶስቱ ፎርጂድ ይሆናል..የቀረው ደግሞ የሶሻሊስት ፓርቲ መፈክር ይመስል በብቃታቸው የተመሰከረላቸው…በችሎታቸው ወደርአልባ..በፀባያቸው ምስጉን የሚሉ ግነቶች የታጨቁበት በቃ ምን ልበልህ እንደውም በብዙ መስሪያ ቤቶች ደብዳው አንዴ ይፃፍል ሰራተኛው የስራ ልምድ ሲጠይቅ ስም እና የደሞዝ መጠን የሚገልፀው ቁጥር ብቻ እየተቀየረ ነው ፕሪንት በማድረግ የሚሰጠው…...እና ይሄ የስራ ልምድን ዓላማ ማርከስና ሀገርንም መግደል …ሰውዬው ገብቶ በለቀቀባቸው መስሪያ ቤቶች ሁሉ በተመሳሰሳይ ሁኔታ ስለጀግንነቱ ብቻ የሚያትት ልብ ወለዳዊ ምስክርነት የሚሠጠው ከሆነ ለምን ብሎ እራሱን ያሻሸላል……?እና ለማለት የፈለኩት አንተ ምርጥ ሀለቃ ስለሆንክ ያልከውን አታደርግም… ስለእኔ በትክክል የሆንኩትን እና ያልሆንኩትን..የምችለውንና የሚጎድለኝን በትክክል በመዘርዘር ነው የምትሸኘኝ…ጉድለቴን መፃፍህ እኮ የሚቀጥረኝ መስሪያ ቤት በመጀመሪያውኑ ስለእኔ እውነቱን አውቆት እንዲቀጥረኝና እና ጉድለቴንም እንዳሻሽል ስልጣና በማመቻቸት እንዲያግዘኝ ቅድሚያ መረጃ ይሰጠዋል፡፡
‹‹እሺ እንዳልሺን አደርጋለው…ስርዓት አልበኝነትሽን እና ወደ ላይ ያለአቅምሽ በመንጠራራት ሚስተካከልሽ እንደሌላ ቦልድ ተደርጎ እንዲፀፍልኝ አደርጋለው››አለኝ…. በዚህ ጊዜ ያዘዝነው ቡናና ማኪያቶ መጥቶልን ነበር….
‹‹አመሰግናው..ግን ከመባረሬ በፊት አንድ ነገር እንድታደርግልኘ እፈልጋለው››
‹‹ጠይቂኝ..››
‹‹ይሄንን ፈርምና ለመጨረሻ ጊዜ ዘና ብዬ ሁላችሁንም ተሰናብቼ ልልቀቅ..››ወረቀቱን አቀበልኩት…ገልጦ አየውና እስከዛሬ ካፈጠጠብኝ በላይ አፈጠጠብኝ…
‹‹ደግሞ ከአቶ ሰይፉ ሰርቄ ነው ያመጣሁት ..ለእሳቸወ ከነገርክብኝ አለቀልኝ››
‹‹ስንቴ ነው የሚያልቅልሽ……?ከእዚህ ካማፓኒ እህል ውሀሽ እኮ ተበጥሶል….ምንም የቀረሽ ነገር የለም››
‹‹ቢሆንም ..››
‹‹በይ ከሰረቅሽበት ቦታ መልሺ››ብሎ ወረቀቱን መልሶ አስታቀፈኝ
‹‹ይሄውልህ ..ይሄንን መፈረም ከማንም በላይ ላንተ ነው የሚጠቅምህ..››
‹‹እንዴት ብሎ ነው ሁለት ቀን ስራ መፍታት እና 3 መቶ ሺ ብር ማውጣት ሊጠቅመኝ የሚችለው……?››
‹‹አንደኛ ይሄ ለአስር አመት በካምፓኒው የቆየ ልምድ ነው፤ለዛውም ውጤታማ ልምድ፡፡ የካምፓኒውን የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ግባና ተመልከት …ምንጊዜም ከዚህ ዝግጅትና መዝናናት ቡኃላ ባሉ ሶስትና አራት ተከታታይ ወራቶች የእያንደንዱ ሰራተኛ የስራ አፈፃፀም ውጤት በሚገርም መጠን ነው የሚያድገው..የሄንን ያወጣሀውን 3 መቶ ሺ ብር በአንድ ወር ውስጥ እጥፍ ሆኖ ይመለሳልሀል፡፡ በአመታዊ ክብረ በዓሉ ካምፓኒው ከደሞዛቸው ውጭ በሆነ ብር የሆነ ነገር ስላደረጋቸው.የእኔነት ስሜት እንዲያድርባቸው ያደርጋል…፡፡፡ሁለተኛ ሰው በስራ በጣም ውጤታማ የሚሆነው በጣም ዘና ባለበት ጊዜ ነው…ለቀናትም ቢሆን ወደ ሆነ ሀገር ሄደው አየር መቀየራቸው ፤ ያላዩትን ነገር ማየታቸው መንፈሳቸው እንዲታደስ የስራ መነሳሳታቸው እዲጨምር እና ለህይወት ያላቸውም ጉጉት እንዲያንሰራራ ያደርጋል…፡፡ሌላው ያው ሰው ሆኖ መቼስ አንድ ላይ ሲሳራ በተለያየ ምክንያት የተጋጨ የተኮረፈ ይኖራል.. ልክ እደእኔና አንተ ማለት ነው..አንድ ላይ እየሰሩ ደግሞ ቅሬታ ውስጥ መግባት የስራ ጥራትንና ውጤትን በጣም እደሚቀንስ የታወቀ ነው፣እና እንዚህ አይነት ሰዎች ከስራ መንፈስ ውጭ ሆነው እንዲህ አይነት ቦታ ሲሄዱ መንፈሳቸው ከውጥረት የራቀና ዘና ለማለትም ዝግጁ ስለሚሆን ሁሉም ከገባበት ቅሬታ በቀላሉ ይወጣና እርስበርስ ይቅር ይባባላል፡፡ ሌላው በስራ ብቻ የሚተዋወቅ እና ግንኙነቱ በአየር ላይ የሆነ ሰው ግንኑነቱን በአንድ እስቴፕ ያሳድጋል…የተሸለ መግባባት እና አንዱ የአንደን ድክመት እና ጥንካሬ በተወሰነ መልኩ ለመረዳት እድል ያመቻችለታል… አንዳችን ያንዳችንን ፀባይ ፤ ድክመትና ጥንካሬ ማወቃችን እርስ በርስ ለመረዳዳት ተከባብረን እና ተደማምጠን ውጤታማ ለመሆን ያግዘናል...
👍7
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
...ቀኑ እሁድ እንደመሆኑ ከእንቅልፌ የተነሳውት አረፋፍጄ ነው….አባቴ ክንዱን ከአንገቴ ዙሪያ እንዴት አድርጎ አውጥቶ፤ከደረቱ ላይ እንዴት አንሸራቶ ከስሬ እንደተነሳ አለውቅም…ከሰራተኞቻችን አንዷ ነች የቀሰቀሰቺኝ፡
‹‹ምነው ትንሽ ልተኛ››ተነጫነጭኩባት
‹‹ጋሼ ለቁርስ እየጠበቁሽ ነው..ቀስቅሺያት ብለውኝ ነው…ካለበለዚያ ጥዬሽ መውጣቴ ነው ብለውሻል››
‹‹እንዳታደርገው… መጣው ጠብቀኝ በይው…››አልኩና ተስፈንጥሬ አልጋዬን ለቅቄ ወረድኩ…..የለበስኩትን ቢጃማ እያወለቅኩና ወለል ላይ እየጣልኩ ወደሻወር ቤት ገባው.፡፡ ሰውነቴን ታጥቤ ለእርፍት ቀን የሚሆን ቀለል ያለ ልብስ ለብሼ ቁርስ ቦታ ለመድረስ ከ15 ደቂቃ በላይ ፈጀቶብኛል…አባቴ ፊት ለፊት በረንዳ ላይ ተቀምጦ መጽሀፍ እያነበበ ነበር…..
ከሶስት ቀን በፊት እንደተለየኝ በሚያስመስል ጥልቅ ስሜት ጉንጬን ሙጭሙጭ አድርጌ ሳምኩትና ከጎኑ ካለው ባዶ ወንበር ላይ ተቀመጥኩ….
‹‹በለሊት ምነው ተነሳህ…?››
‹‹በለሊት እንደምነሳ ሁሌ ታውቂያለሽ…እኔ እያየዋት ያልወጣችን ፀሀይ ቀኑን ሙሉ ምቾት ስትነሳኝ ነው የምትውለው…እንኳን በሰላም ወጣሽ ብዬ በደስታ መቀበል እና ማታ ደግሞ በሰላም ወደማደሪያሽ ግቢ ብዬ መሸኘት ለመኖር ያለኝ ጉጉቴን ይጨምርልኛል..ፀሀይ ለእኔ ያንቺ ተምሳሌት ነች፤እኩል ነው የምወዳችሁ……››
‹‹እንዴ አባ..እኔን ከፀሀይ እኩል ብቻ…እኔ እኮ ከራስህ እኩል የምትወደኝ ይመስለኝ ነበር….…?››
‹‹ለማለት የፈለኩት በትክክል ገብቶሻል…አንቺን ከእኔ እኩል መውደድ አንቺን ማሳነስ ነው…አንቺ ማለት በጣም የተስተካከለው እኔ ማለት ነሽ..አንቺ የእኔ በጣም ጥሩ ጎን ከእናትሽ ጥሩ ጎን ጋር አንድ ላይ ተቀይጦ ሲዋሀድ ማለት ነሽ…..የሁለታችንም ስህተት ሲታረም ንጥር ያለ ንጽህ እውነት ይወጣዋል… ያ እውነት ማለት ደግሞ አንቺ ነሽ…እና አንቺን ከእኔ እኩል ሳይሆን ከእኔ በላይ ነው የምወድሽ….››
ሳይቸግረኝ ቆስቁሼው በጥዋት በጣፍጭና አቅላጭ ንግግሩ እንባዬን አስመጣው…‹‹የእኔ ልዩ አባት››ብዬ ተንጠራርቼ ሳምኩት
ቁርሱ ቀረበልን እና በ10 ደቂቃ ውስጥ እያወራን በልተን ጨረስን……
‹‹አሁን መሄድ እንችላለን…?፡፡››አለኝ
‹‹አዎ ….››ብዬ ከመቀመጫዬ ተነሳውና ወደገራዥ በመሄድ የአባዬን መኪና በማውጣት እሱን ከጎኔ አስቀምጬ ከግቢው ወጣን…እኔና አባቴ እሁድን ተአምር የሚመስል አጋጣሚ ካልተፈጠረ እና አንዳችን የግድ ለብቻችን የምንሄድበት ቦታ ካልገጠመን በስተቀር አንለያይም…ለምሳሌ የእሱ ጓደኛ ጋር ለቅሶ ቢኖርና መሄድ የግድ ቢሆንበት አወቅኳቸውም አላወቅኳቸውም አብረን ነው የምንሄደው…ሰርግ እና ድግስ ተውት ከነባለቤቱ በሚለው ቦታ ባለቤቱን ወክዬ ሁሌ የምሄደው እኔ ነኝ
ከአራት ሰዓት እስከ ስምንት ሰዓት ያለው ፕሮግራማችን ከሞላ ጎደል ሁሌ ተመሳሳይ ነው….በመጀመሪያ ሆስፒታል ነው የምንሄደው…ሆስፒታሉ እንደየሁኔታው ሊለያይ ይችልላ…ግን የትኛውም ሆስፒታል ይሁን ብቻ አንዱ ጋር እንሄዳለን…..ከዛ በተቻለን መጠን የታመሙትን በየክፍሉ እየገባን መጠየቅ እንጀምራለን..ከዛ ቡኃላ በጥየቃችን ወቅት ምንም አስታማሚ የሌላቸውን አዛውንት..ወይም እናቷን የምታስታምም የዘጠኝ ዓመት ልጅ…መድሀኒት መግዣ ብር ያጣ ስንት ወንዘ አቋርጦ ከክፍለሀገር የመጣ ገበሬ …ብቻ ብዙ ብዙ ታሪክ ያላቸው ሰዎች ያጋጥሙናል….ከዛ አባቴ ይዞ የመጣውን ብር እንደየ ችግራቸው ከባድነትና እንደሚያስፈልጋቸው የብር መጠን ያከፋፍላቸዋል…
አንዳንዴ በሁኔታው ስደመም‹‹አባ ልዩ ሰው እኮ ነህ…ሰው ጤናውን ለማስመለስ በሚያደርገው ጥረት ገንዘብ ሲቸግረው…. ህክምናውን አግኝቶ መድሀኒት መግዣ ሲያጣ የሚሰማው ሀዘንና መሸማቀቅ .. በዛ ሰዓት ደግሞ አንተ ደርሰህ አይዞችሁ ስትላቸው የሚሰማቸው ደስታና እፎይታ …››ብዬ ላደንቀውም ላመሰግነውም ሞክራለው….
‹‹እኔ እኮ ምንም አላደረኩላቸውም..ደላላ በይኝ››ይለኛል
‹‹አልገባኝም››
‹‹ደላላ ማለት የሆነ ገዢን ከሻጭ አገናኝቶ ኮሚሽን የሚቀበል እና ባገኘው ኮሚሽን ደስተኛ የሚሆን ሰው አይደል…?እኔም ችግር ላይ ባሉ ሰዎች እና በእናትሽ መካከል አገናኝ ድልድይ በይኝ..ዋናዋ ተመስጋኝ ባለብሯ እናትሽ ነች፡፡ እኔ ከእሷ ብሩን እቀበላለው መጥቼ ልቤ በፈቀደው መንገድ እየመደብኩ አከፋፍላለው… የድለላዬን ዋጋ ሰዎቹ የማይገባኝን አይነት ሙገሳና ፤ መንግሰተ ሰማያት መሬት ለመግዛት የሚያስችለኝን አይነት ምርቃት ያሸክሙኛል..››ይለኛል
‹‹አይ አባ..እናቴ እኮ ብሩን ለሰዎቹ ብላ ሳይሆን አንተን ለማስደሰት ስትል ነው የምትሰጥህ…ለምሳሌ ይሄንን ብር ከጓደኞችህ ጋር ውስኪ ለመራጨት ብትጠቀምበትም እሷ ደንታዋ አይደለም…አረ ውሽማ ኖሮህ ለእሷም ብትሰጣት እንኳን ምንም የሚመስላት አይመስለኝም ….ደግሞ ማላውቅ እንዳይመስልህ››
‹‹ምኑን…? ››
‹‹ይሄንን ባህሪህን ከእናቴም ከመገናኘትህ በፊት ፤ ምንም ብር ባልነበረህም ጊዜ በዝርዝር ሳንቲሞች ደረቅ ዳቦ እየገዛህ በሽተኞችን እንደምትጠይቅ አዎቃለው..››
‹‹እሱስ ትክክል ነሽ›› ብሎ ትክዝ ይላል፡፡››
===
አባቴ ዝም ብሎ አይደለም የዚህ ባህሪ ባለቤት የሆነው…ታሪኩን እሱ ለእናቴ ነግሯት እሷ ደግሞ ለእኔ ነግራኛላች… እኔ ደግሞ አሁን አጠር አድርጌ ለእናንተ ልንገራችሁ…
አባቴ የአጄ ልጅ ነው፡፡አጄ በሻሸመኔ እና በአላባ መካከል የምትገኝ መለስተኛ ከተማ ነች ፡፡ለእናትና አባቱ አንድ ብቸኛ ልጅ ነበር.፡፡አባትዬው ህፃን ሳለ ነበር የሞቱት፡፡እናትዬው ግን አባት አልባ መሆኑን እንዳይሰማው ፊታቸው በማድያት እስኪሸፈን፤ ወገባቸው ያለእድሜያቸው እስኪጎብጥ እንደወንድ እያረሱ..እንደሴት እየፈተሉ ፤እንደገበሬ እያመረቱ ፤እደ ነጋዴ እየቸረቸሩ ምንም ሳይጎድልበት እስተማሩት ..እሱም ልፋታቸውን መሬት እንዲበተን አላደረገም… ጥሩ ውጤት አምጥቶ ዩኒቨርሲቲ ገባ፡፡ሁሉም ነገር መልካም ሆኖ ከቀጠለ ቡኃላ የመጨረሻ የመመረቂያው አመት ላይ ያልተጠበቀ ጨለማ ነገር ተፈጠረ….
ለእናቴ ደረስኩላት ብሎ ፈንጠዝያ ላይ ባለበት ጊዜ…..የአለምን ሁሉ ጥሩ ነገር በሚገባት መጠን ለአናቴ አደርግላታለው ብሎ በጉጉት በሚናጥበት ጊዜ ፡፤ እናቴን ስንድ እመቤት አድርጌ በምቾትና በድሎት እንድትኖር አደርጋታለው ብሎ ዝግጅት ላይ ባለበት ጊዜ በአስቸኳይ ድረስ ተብሎ ከዩኒቨርሲቲ ተጠራ…ሲደርስ እናቱ በሞትና በህይወት መካከል ስታጣጥር ነበር የደረሰው….ከዛ ያደረገው የአካባቢው ሰዎች ባዋጡት እና እናትዬውም እጅ ላይ በነበረች ጥቂት ገንዘብ ለተሻለ ህክምን ወደሻሸመኔ ሆስፒታል ይዞቸው መሄድ ነበር…በምርመራው የበሽታቸው አይነት ተለይቶ መድሀኒት ይታዘዝላቸዋል …ሶስት መድሀኒት 950 ብር…ያ ብር ከየት ይምጣ..…?አቅም ያላቸው የአባቱም ሆኑ የእናቱ ዘመዶች ጋር እየደወለም እራሱም በአካል እየሄደ እደጅ ቢጠና ከአስርና ከሃያ ብር በላይ ሊሰጠው የሚችል አዛኝ ልብ ያለው ሰው ማግኘት አልቻለም..ከዛ የመጨረሻ አማራጭ በሽተኛ እናቱን አስፓልት ዳር አስተኝቶ እናቴን አድኑልኝ እያለ ምድሀኒት መግዣ መለመን ነበር…ግን የተፈላገው ዘጠኝ መቶ ሃምሳ ብር ከማግኘቱ በፊት እዛው አስፓልት ላይ እናቱ ትሞትበታላች…ያ አባቴ ሙሉ በሙሉ የተቀየረበት ወቅት ነበር..ለገንዘብም ለህይወትም የነበረው ምልከታ ከስር መሰረቱ የተደረማመሰበት …ያ ወቅት አባቴ ዘመድ አልባ ብቸኛ ሰው እንደሆነ የተቀበለበት ጊዜ ነበር…
ትምህርቱን አጠናቆ ወደሀገሩ አልተመለሰም ….ዝም ብሎ ወደማያውቀው አዲስ አበባ ዲግሪውን
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
...ቀኑ እሁድ እንደመሆኑ ከእንቅልፌ የተነሳውት አረፋፍጄ ነው….አባቴ ክንዱን ከአንገቴ ዙሪያ እንዴት አድርጎ አውጥቶ፤ከደረቱ ላይ እንዴት አንሸራቶ ከስሬ እንደተነሳ አለውቅም…ከሰራተኞቻችን አንዷ ነች የቀሰቀሰቺኝ፡
‹‹ምነው ትንሽ ልተኛ››ተነጫነጭኩባት
‹‹ጋሼ ለቁርስ እየጠበቁሽ ነው..ቀስቅሺያት ብለውኝ ነው…ካለበለዚያ ጥዬሽ መውጣቴ ነው ብለውሻል››
‹‹እንዳታደርገው… መጣው ጠብቀኝ በይው…››አልኩና ተስፈንጥሬ አልጋዬን ለቅቄ ወረድኩ…..የለበስኩትን ቢጃማ እያወለቅኩና ወለል ላይ እየጣልኩ ወደሻወር ቤት ገባው.፡፡ ሰውነቴን ታጥቤ ለእርፍት ቀን የሚሆን ቀለል ያለ ልብስ ለብሼ ቁርስ ቦታ ለመድረስ ከ15 ደቂቃ በላይ ፈጀቶብኛል…አባቴ ፊት ለፊት በረንዳ ላይ ተቀምጦ መጽሀፍ እያነበበ ነበር…..
ከሶስት ቀን በፊት እንደተለየኝ በሚያስመስል ጥልቅ ስሜት ጉንጬን ሙጭሙጭ አድርጌ ሳምኩትና ከጎኑ ካለው ባዶ ወንበር ላይ ተቀመጥኩ….
‹‹በለሊት ምነው ተነሳህ…?››
‹‹በለሊት እንደምነሳ ሁሌ ታውቂያለሽ…እኔ እያየዋት ያልወጣችን ፀሀይ ቀኑን ሙሉ ምቾት ስትነሳኝ ነው የምትውለው…እንኳን በሰላም ወጣሽ ብዬ በደስታ መቀበል እና ማታ ደግሞ በሰላም ወደማደሪያሽ ግቢ ብዬ መሸኘት ለመኖር ያለኝ ጉጉቴን ይጨምርልኛል..ፀሀይ ለእኔ ያንቺ ተምሳሌት ነች፤እኩል ነው የምወዳችሁ……››
‹‹እንዴ አባ..እኔን ከፀሀይ እኩል ብቻ…እኔ እኮ ከራስህ እኩል የምትወደኝ ይመስለኝ ነበር….…?››
‹‹ለማለት የፈለኩት በትክክል ገብቶሻል…አንቺን ከእኔ እኩል መውደድ አንቺን ማሳነስ ነው…አንቺ ማለት በጣም የተስተካከለው እኔ ማለት ነሽ..አንቺ የእኔ በጣም ጥሩ ጎን ከእናትሽ ጥሩ ጎን ጋር አንድ ላይ ተቀይጦ ሲዋሀድ ማለት ነሽ…..የሁለታችንም ስህተት ሲታረም ንጥር ያለ ንጽህ እውነት ይወጣዋል… ያ እውነት ማለት ደግሞ አንቺ ነሽ…እና አንቺን ከእኔ እኩል ሳይሆን ከእኔ በላይ ነው የምወድሽ….››
ሳይቸግረኝ ቆስቁሼው በጥዋት በጣፍጭና አቅላጭ ንግግሩ እንባዬን አስመጣው…‹‹የእኔ ልዩ አባት››ብዬ ተንጠራርቼ ሳምኩት
ቁርሱ ቀረበልን እና በ10 ደቂቃ ውስጥ እያወራን በልተን ጨረስን……
‹‹አሁን መሄድ እንችላለን…?፡፡››አለኝ
‹‹አዎ ….››ብዬ ከመቀመጫዬ ተነሳውና ወደገራዥ በመሄድ የአባዬን መኪና በማውጣት እሱን ከጎኔ አስቀምጬ ከግቢው ወጣን…እኔና አባቴ እሁድን ተአምር የሚመስል አጋጣሚ ካልተፈጠረ እና አንዳችን የግድ ለብቻችን የምንሄድበት ቦታ ካልገጠመን በስተቀር አንለያይም…ለምሳሌ የእሱ ጓደኛ ጋር ለቅሶ ቢኖርና መሄድ የግድ ቢሆንበት አወቅኳቸውም አላወቅኳቸውም አብረን ነው የምንሄደው…ሰርግ እና ድግስ ተውት ከነባለቤቱ በሚለው ቦታ ባለቤቱን ወክዬ ሁሌ የምሄደው እኔ ነኝ
ከአራት ሰዓት እስከ ስምንት ሰዓት ያለው ፕሮግራማችን ከሞላ ጎደል ሁሌ ተመሳሳይ ነው….በመጀመሪያ ሆስፒታል ነው የምንሄደው…ሆስፒታሉ እንደየሁኔታው ሊለያይ ይችልላ…ግን የትኛውም ሆስፒታል ይሁን ብቻ አንዱ ጋር እንሄዳለን…..ከዛ በተቻለን መጠን የታመሙትን በየክፍሉ እየገባን መጠየቅ እንጀምራለን..ከዛ ቡኃላ በጥየቃችን ወቅት ምንም አስታማሚ የሌላቸውን አዛውንት..ወይም እናቷን የምታስታምም የዘጠኝ ዓመት ልጅ…መድሀኒት መግዣ ብር ያጣ ስንት ወንዘ አቋርጦ ከክፍለሀገር የመጣ ገበሬ …ብቻ ብዙ ብዙ ታሪክ ያላቸው ሰዎች ያጋጥሙናል….ከዛ አባቴ ይዞ የመጣውን ብር እንደየ ችግራቸው ከባድነትና እንደሚያስፈልጋቸው የብር መጠን ያከፋፍላቸዋል…
አንዳንዴ በሁኔታው ስደመም‹‹አባ ልዩ ሰው እኮ ነህ…ሰው ጤናውን ለማስመለስ በሚያደርገው ጥረት ገንዘብ ሲቸግረው…. ህክምናውን አግኝቶ መድሀኒት መግዣ ሲያጣ የሚሰማው ሀዘንና መሸማቀቅ .. በዛ ሰዓት ደግሞ አንተ ደርሰህ አይዞችሁ ስትላቸው የሚሰማቸው ደስታና እፎይታ …››ብዬ ላደንቀውም ላመሰግነውም ሞክራለው….
‹‹እኔ እኮ ምንም አላደረኩላቸውም..ደላላ በይኝ››ይለኛል
‹‹አልገባኝም››
‹‹ደላላ ማለት የሆነ ገዢን ከሻጭ አገናኝቶ ኮሚሽን የሚቀበል እና ባገኘው ኮሚሽን ደስተኛ የሚሆን ሰው አይደል…?እኔም ችግር ላይ ባሉ ሰዎች እና በእናትሽ መካከል አገናኝ ድልድይ በይኝ..ዋናዋ ተመስጋኝ ባለብሯ እናትሽ ነች፡፡ እኔ ከእሷ ብሩን እቀበላለው መጥቼ ልቤ በፈቀደው መንገድ እየመደብኩ አከፋፍላለው… የድለላዬን ዋጋ ሰዎቹ የማይገባኝን አይነት ሙገሳና ፤ መንግሰተ ሰማያት መሬት ለመግዛት የሚያስችለኝን አይነት ምርቃት ያሸክሙኛል..››ይለኛል
‹‹አይ አባ..እናቴ እኮ ብሩን ለሰዎቹ ብላ ሳይሆን አንተን ለማስደሰት ስትል ነው የምትሰጥህ…ለምሳሌ ይሄንን ብር ከጓደኞችህ ጋር ውስኪ ለመራጨት ብትጠቀምበትም እሷ ደንታዋ አይደለም…አረ ውሽማ ኖሮህ ለእሷም ብትሰጣት እንኳን ምንም የሚመስላት አይመስለኝም ….ደግሞ ማላውቅ እንዳይመስልህ››
‹‹ምኑን…? ››
‹‹ይሄንን ባህሪህን ከእናቴም ከመገናኘትህ በፊት ፤ ምንም ብር ባልነበረህም ጊዜ በዝርዝር ሳንቲሞች ደረቅ ዳቦ እየገዛህ በሽተኞችን እንደምትጠይቅ አዎቃለው..››
‹‹እሱስ ትክክል ነሽ›› ብሎ ትክዝ ይላል፡፡››
===
አባቴ ዝም ብሎ አይደለም የዚህ ባህሪ ባለቤት የሆነው…ታሪኩን እሱ ለእናቴ ነግሯት እሷ ደግሞ ለእኔ ነግራኛላች… እኔ ደግሞ አሁን አጠር አድርጌ ለእናንተ ልንገራችሁ…
አባቴ የአጄ ልጅ ነው፡፡አጄ በሻሸመኔ እና በአላባ መካከል የምትገኝ መለስተኛ ከተማ ነች ፡፡ለእናትና አባቱ አንድ ብቸኛ ልጅ ነበር.፡፡አባትዬው ህፃን ሳለ ነበር የሞቱት፡፡እናትዬው ግን አባት አልባ መሆኑን እንዳይሰማው ፊታቸው በማድያት እስኪሸፈን፤ ወገባቸው ያለእድሜያቸው እስኪጎብጥ እንደወንድ እያረሱ..እንደሴት እየፈተሉ ፤እንደገበሬ እያመረቱ ፤እደ ነጋዴ እየቸረቸሩ ምንም ሳይጎድልበት እስተማሩት ..እሱም ልፋታቸውን መሬት እንዲበተን አላደረገም… ጥሩ ውጤት አምጥቶ ዩኒቨርሲቲ ገባ፡፡ሁሉም ነገር መልካም ሆኖ ከቀጠለ ቡኃላ የመጨረሻ የመመረቂያው አመት ላይ ያልተጠበቀ ጨለማ ነገር ተፈጠረ….
ለእናቴ ደረስኩላት ብሎ ፈንጠዝያ ላይ ባለበት ጊዜ…..የአለምን ሁሉ ጥሩ ነገር በሚገባት መጠን ለአናቴ አደርግላታለው ብሎ በጉጉት በሚናጥበት ጊዜ ፡፤ እናቴን ስንድ እመቤት አድርጌ በምቾትና በድሎት እንድትኖር አደርጋታለው ብሎ ዝግጅት ላይ ባለበት ጊዜ በአስቸኳይ ድረስ ተብሎ ከዩኒቨርሲቲ ተጠራ…ሲደርስ እናቱ በሞትና በህይወት መካከል ስታጣጥር ነበር የደረሰው….ከዛ ያደረገው የአካባቢው ሰዎች ባዋጡት እና እናትዬውም እጅ ላይ በነበረች ጥቂት ገንዘብ ለተሻለ ህክምን ወደሻሸመኔ ሆስፒታል ይዞቸው መሄድ ነበር…በምርመራው የበሽታቸው አይነት ተለይቶ መድሀኒት ይታዘዝላቸዋል …ሶስት መድሀኒት 950 ብር…ያ ብር ከየት ይምጣ..…?አቅም ያላቸው የአባቱም ሆኑ የእናቱ ዘመዶች ጋር እየደወለም እራሱም በአካል እየሄደ እደጅ ቢጠና ከአስርና ከሃያ ብር በላይ ሊሰጠው የሚችል አዛኝ ልብ ያለው ሰው ማግኘት አልቻለም..ከዛ የመጨረሻ አማራጭ በሽተኛ እናቱን አስፓልት ዳር አስተኝቶ እናቴን አድኑልኝ እያለ ምድሀኒት መግዣ መለመን ነበር…ግን የተፈላገው ዘጠኝ መቶ ሃምሳ ብር ከማግኘቱ በፊት እዛው አስፓልት ላይ እናቱ ትሞትበታላች…ያ አባቴ ሙሉ በሙሉ የተቀየረበት ወቅት ነበር..ለገንዘብም ለህይወትም የነበረው ምልከታ ከስር መሰረቱ የተደረማመሰበት …ያ ወቅት አባቴ ዘመድ አልባ ብቸኛ ሰው እንደሆነ የተቀበለበት ጊዜ ነበር…
ትምህርቱን አጠናቆ ወደሀገሩ አልተመለሰም ….ዝም ብሎ ወደማያውቀው አዲስ አበባ ዲግሪውን
👍1
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_አስር
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
...‹‹ዛሬ የት እንሂድ…?›› አልኩት አባቴን ስምንት ሰዓት ከሩብ አካባቢ….
መኪና ውስጥ ገብተን እኔ እየነዳው ነው እያወራን ያለነው….
‹‹እኔ ምንም በውስጤ የለም…አረጀው መሰለኝ የመዝናኛ አይነቶች እየጠፉብኝ ነው፡፡››
‹‹የእኔ አባትማ እንዲህ በቀላሉ አያረጅም …ገና እኔና እናቴ ድል አድርገን ደግሰን ልጃገረድ ነው የምንድርህ››
‹‹አይ እብድ የሆንሽ ልጅ…በሚስት ላይ ሚስት ወንጀል እንደሆነ አታውቂም…››
‹‹አይ እናቴንማ ሚስቴ ብለህ መጥራቱን አቁም …አሁን መጨረሻ ውሳኔ ላይ ደርሼያለው…››
‹‹ምን አይነት ውሳኔ…?››
‹‹አሁን የጤናዋ ጉዳይ መስመር እስኪይዝ ነው እንጂ ወይ እንደገና ታግባህ ወይ ደግሞ በፍቃዷ ትልቀቅህና ልዳርህ››
ፈገግ አለና‹‹…አሁን ይሄን ምን አሳሰበሽ…?›
‹‹ለምን አላስብም አባ……? ደግሞ አሁን አይደለም …ሁሌ እኮ ነው ሚያንገበግበኝ…በዚህ ጉዳይ ላይ የሆነ ነገር ብትለኝ ደስ ይለኛል….››
‹‹ምን እንድልሽ ነው የምትፈልጊው……?››
‹‹እኔ እንጃ…እናቴን ለምን አልተውካትም……?መቼስ ለብሯ ስትል አብረሀት እንዳልቆየህ አውቃለሁ…አንተ በቁስ ፍቅር ልትሸነፍ ምትችል ሰው አይደለህም …››
‹‹ለምን ጥያቄውን ገልብጠሸ አልጠየቅሺኝም…?››
‹‹እንዴት ብዬ……?››
‹‹ለምን እናቴ አንተን ጥላህ አልሄደችም..…?ለምን እንደዛ ማድረግ ተሳናት……? ሀብታም ነች፤ቆንጆ ነች፤የተማረች እና ብልህ ነች ከንተ ጋር ለምን ኑሮዋን መቀጠል ፈለገች……?ለምን ከቤቷ አንተን አስወጥታ ሌላ የሚመጥናትን ባል አላገባችም ብለሽ አልጠየቅሺም….…?ለምን….…?››
‹‹ሚመጥናትን!! …?ጭራሽ አንተ ለእሷ መመጠን አቅቶህ…? አረ አታስቀኝ ....አንተ እኮ ሁሌ ባል ለመሆን ዝግጁ ነህ…አንተ እንከን አልባ ሰው ነህ…እሷ ነች ሀብት አሳዳጇ..እሷ ነች ቤቱን እርግፍ አድርጋ የአደባባይ ሴት የሆነችው…እሷ ነች…››
‹‹በይ ይብቃሽ ልጄ…ሁል ግዜ ስለምንወዳቸው ሰዎች ያለን ምልከታ ስለእነሱ እወነቱን እንዳናይ እያየንም እንኳን አምነን እንዳንቀበል ጥቁር መጋረጃ ይሆንብናል…ላንቺ አባትሽ ምንም ጉድፍ የለበትም…ያንቺን አባት የሚመስል ሰው በዚህ ምድር ላይ አልተፈጠረም…የዚህ ዓለም ቆነጃጅቶች ሁሉ አባትሽን ለማግኘት ቢደባደብና ቢቦጫጨቁ ተገቢ ነው…..አይደል..…?እንደዛ አይደል የምታስቢው..…?››
‹‹ምነው ባስብ ታዲያ ተሳሳትኩ……?.››
‹‹አዎ ተሳስተሸል..፡፡ባልና ሚስት በሆነ ነገር አልተስማሙም ማለት ጎጆቸውን ማፍረስ አለባቸው ማለት አይደለም…ደግሞ ልጄ አንድ ነገር ልነግርሽ እፈልጋለው.. ትዳርና ሀገር ውስብስብ ናቸው፡፡ትዳር ይዘሽ ልጆች ወልደሽ እና ንብረት አፍርተሸ ረጅም አመት ኖርሽ ማለት ሁሉ ነገር ገነታዊ ነው ማለት አይደለም…የሆነ ነገር ለማግኘት ሁሌ መክፈል ያለብሽ የሆነ መስዋዕትነት አለ…ባልሽ በምንም አይነት ሁኔታ መቶ ፐርሰንት አንቺ ወደምትወጂው ወይም አንቺ ወደምትጓዢበት የህይወት መንገድ ሊጓዝ አይችልም…እንደዛ እንዲያደርግ አደረግሽ ማለት ማነቱን አጠፋሺው ማለት ነው…ማንም ሰው ደግሞ የራሱን ማንነት እስከወዲያኛው ማጣት ስለማይፈልግ የሆነ ቀን ማንነቱን ለማስመለስ መንፈራገጡ አይቀርም ..ያ ደግሞ እቤት ወደመሰነጣጠቅ እና ወደማፍረሰ ያመራል…፡፡
አየሽ ባልና ሚስት ቃልኪዳናቸውን አክብረው እስከወዲያኛው ለመኖር አንድ ነገር ላይ ብቻ ነው እኩል መስማማት ሚገባቸው ‹‹ጎጆችን የጋራችን ነው… የጓጇችንን ህልውና ሁለታችንም እኩል እንፈልገዋለን… ለዛም ስንል ሁል ጊዜ በጋራ ሆነ በየግላችን የተቻለንን እንጥራለን..…››ይሄ ነው ወሳኙ ጉዳይ… ቃላቸውን ለማክበር ሲሉ ይከባበራሉ..ይሄንን ቃል ለማክበር ሲሉ ይደማመጣሉ፣ይሄንን እውን ለማድረግ ሲሉ ሁሌ ሳይሰለቻቸው ይቅር ይባባላሉ….ለጎጇቸው ህልውና ሲሉ ሰጥቶ በመቀበል ፤ተሸንፎም ጭምር በማሸነፍ እኩል ይጥራሉ….
እና ትዳር ቀላል ነገር አይደለም…ባልና ሚስት ተባብሎ እጅ ለእጅ በመያያዝ በየድግስ ቤቱ ከመሄድ በላይ ነው፣ባልና ሚስት መሆን አንድ መሶብ ከመብላት እና አንድ አልጋ ከመጋራትም በላይ ነው…
ይሄን ጌዜ ከተማውን ለቀን ቃሊቲ ኬላ ጋር ደርሰናል..…እየነዳው ያለውት ወደ ዱከም ነው..አባቴ ጥሬ ስጋ ይወዳል..ዱከም ደግሞ በጥሬ ስጋ የምታውቁት ነው…አባቴ ንግግሩን ቀጥሏል፡፡
ትዳር የሚባለው ተቋም ሀገር ከሚባለው የጋራ ቤት ጋር ይመሳሰላል…አንድ ሀገር ውስጥም በጋራ ለመኖር ሀገሬን እወዳለው ብቻ ማለት በቂ አይደለም..ለሀገሬ ስል ሌላው ወገኔ የማይፈልገውን ግማሽ ፍላጎቴን በውስጤ ማክሰምን ይጠይቃል…፡፡በሀገርሽ መጮኸ ሲያምርሽ መጮኸ ትችያለሽ….ጩኸትሽ ግን ህፃናቶች አስደንግጦ ችግር ላይ አለመጣሉን እርግጠኛ መሆንና ለሌላውም መጠንቀቅን ይጠይቃል…፡፡የጋራ በሆነ ሀገር ውስጥ ሙሉ ነፃነት ሚባል ነገር የለም…ያንቺ ነፃነት የእኔ ደህንነትን አደጋ ላይ የሚጥል ከሆነ ገደብ ይበጅለታል … ህግ የሚባል ገደብ…፡፡ስለዚህ በጋራ ሀገር ውስጥ የጋራ የሆነ ህግ ማክበር ስንችል ነው የጋራ የሆነች ሀገራችንን ህልውና ማስጠበቅ የምንችለው…ሀገራችን እንወዳለን ምንለው በትክክል የሚሰራው በዚህ መንገድ ብቻ ስንጓዝ ነው…ካለበለዚያ እንደፈለኩ ካልተንፈራገጥኩ ምል ከሆነ ስንፈራገጥ የሌላውን ሰው አፍንጫ ላጣምም ስለምችል ችግር መፍጠሬ አይቀርም ፤እራሴ አብኩቼ እራሴ ካልጋገርኩ አይጣፍጥም የምል ከሆነ አይደለም በጋራ ሀገር በጋራ ቤት ውስጥም ከቤተሰቦቼ ጋር መኖር አልችልም… …ሀገሩን የሚወድ ዲሞክራት ሰው እቤቱ ለተደገሰ ሰርግ የሚከፍተውን የሰርግ ዘፈን የጎራቤቱን የሀዘን ሙሾ አለመረበሹን ማረጋገጥ እና መጠንቀቅ እንዳለበት በደንብ ማወቅ አለበት….
ከየትኛው ሀሳብ ተነስተን ምን ውስጥ ገባን….አባቴ ሁሌ እንዴህ ነው….አንድ ነጠላ ስለቤተሰብ የተነሳችን ሀሳብ ለጥጦ ለጥጦ ሀገራዊና አለማቀፋዊ ጉዳይ ማድረግ የተካነበት ነው…...
አሁን ገላን ደርሰናል … የመኪናዋ ነዳጅ አስተማማኝ ስላልሆነ መኪናዬን ወደቀኝ ጠመዘዝኩና ወደ ነዳጅ ማደያ ገባው …. አስተካክዬ በማቆም ሞተሩን አጣፋውና ጋቢናውን ከፍቼ ከመኪናው ወረድኩ ..ነዳጁን እስኪሞላ ውሀ ስለጠማኝ ለመግዛት ወደሱፐር ማርኬት ነው ሄድኩት ….ምፈልገውን ገዝቼ ወደመኪናዬ ስመለስ ግማሽ መንገድ ላይ ከፊቴ ማን ገጭ ቢል ጥሩ መሰላችሁ ….?እስኪ ገምቱ …?አለቃዬ…አቤት የደነገጥኩት ድንጋጤ…በትምህርት ሰዓት ፎርፋ ሆቴል ቁጭ ብላ ስትዝናና አባቷ እይታ ውስጥ የገባች ልጃገረድ ነው የመሰልኩት…
‹‹ደግሞ እዚህ ምን ትሰሪያለሽ..…?››እጁን ለሰላምታ እየዘረጋልኝ
የዘረጋልኝን ከሶፍት የለሰለሰ የሴት የመሰለ እጁን እየጨበጥኩ..በዛውም ይሄ እጅ ገላዬ ላይ አርፎ ቢዳብሰኝ ምን ሊሰማኝ እደሚችል እየገመትኩ ‹‹ወደዱከም እየሄድን ..ነዳጅ እየሞላው ነው…›› ብዬ መለስኩለት ..በእጄ ወደመኪናችን እየጠቆምኩ
ግራ እንደማጋባትም እያለ‹‹ማለት…? ከማን ጋር……?››እንዴ!! እንደቦይ ፍሬንዴ እኮ ነው ኮስተር ብሎ እየጠየቀኝ ያለው
‹‹የትርፍ ጊዜ ስራ ከሚያሰሩኝ ከአለቃዬ ጋር …በእረፍት ቀናቸው መኪና ስላማይነዱ እኔነኝ ምሾፍርላቸው… ››ውሸቱን ከየት እንደመጣልኝ አላውቅም… ቀባጠርኩ…
‹‹አንቺ የእረፍት ቀንሽ አይደለ እንዴ……?ደግሞ መኪና መንዳት እደምትቺይ አልነገርሺኝም››
‹‹አልጠየቅከኝም እንጂ ብትጠይቀኝ እንገርህ ነበር……የእረፍት ቀንሽ ላልከው ደግሞ ደሀ እረፍት ቀን አያስፈልገውም..በዛ ላይ እንደምታየው ሰውዬዬ ጮማ ናቸው…አንተ ልታባርረኝ አይደል እሷቸው ናቸው
፡
፡
#ክፍል_አስር
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
...‹‹ዛሬ የት እንሂድ…?›› አልኩት አባቴን ስምንት ሰዓት ከሩብ አካባቢ….
መኪና ውስጥ ገብተን እኔ እየነዳው ነው እያወራን ያለነው….
‹‹እኔ ምንም በውስጤ የለም…አረጀው መሰለኝ የመዝናኛ አይነቶች እየጠፉብኝ ነው፡፡››
‹‹የእኔ አባትማ እንዲህ በቀላሉ አያረጅም …ገና እኔና እናቴ ድል አድርገን ደግሰን ልጃገረድ ነው የምንድርህ››
‹‹አይ እብድ የሆንሽ ልጅ…በሚስት ላይ ሚስት ወንጀል እንደሆነ አታውቂም…››
‹‹አይ እናቴንማ ሚስቴ ብለህ መጥራቱን አቁም …አሁን መጨረሻ ውሳኔ ላይ ደርሼያለው…››
‹‹ምን አይነት ውሳኔ…?››
‹‹አሁን የጤናዋ ጉዳይ መስመር እስኪይዝ ነው እንጂ ወይ እንደገና ታግባህ ወይ ደግሞ በፍቃዷ ትልቀቅህና ልዳርህ››
ፈገግ አለና‹‹…አሁን ይሄን ምን አሳሰበሽ…?›
‹‹ለምን አላስብም አባ……? ደግሞ አሁን አይደለም …ሁሌ እኮ ነው ሚያንገበግበኝ…በዚህ ጉዳይ ላይ የሆነ ነገር ብትለኝ ደስ ይለኛል….››
‹‹ምን እንድልሽ ነው የምትፈልጊው……?››
‹‹እኔ እንጃ…እናቴን ለምን አልተውካትም……?መቼስ ለብሯ ስትል አብረሀት እንዳልቆየህ አውቃለሁ…አንተ በቁስ ፍቅር ልትሸነፍ ምትችል ሰው አይደለህም …››
‹‹ለምን ጥያቄውን ገልብጠሸ አልጠየቅሺኝም…?››
‹‹እንዴት ብዬ……?››
‹‹ለምን እናቴ አንተን ጥላህ አልሄደችም..…?ለምን እንደዛ ማድረግ ተሳናት……? ሀብታም ነች፤ቆንጆ ነች፤የተማረች እና ብልህ ነች ከንተ ጋር ለምን ኑሮዋን መቀጠል ፈለገች……?ለምን ከቤቷ አንተን አስወጥታ ሌላ የሚመጥናትን ባል አላገባችም ብለሽ አልጠየቅሺም….…?ለምን….…?››
‹‹ሚመጥናትን!! …?ጭራሽ አንተ ለእሷ መመጠን አቅቶህ…? አረ አታስቀኝ ....አንተ እኮ ሁሌ ባል ለመሆን ዝግጁ ነህ…አንተ እንከን አልባ ሰው ነህ…እሷ ነች ሀብት አሳዳጇ..እሷ ነች ቤቱን እርግፍ አድርጋ የአደባባይ ሴት የሆነችው…እሷ ነች…››
‹‹በይ ይብቃሽ ልጄ…ሁል ግዜ ስለምንወዳቸው ሰዎች ያለን ምልከታ ስለእነሱ እወነቱን እንዳናይ እያየንም እንኳን አምነን እንዳንቀበል ጥቁር መጋረጃ ይሆንብናል…ላንቺ አባትሽ ምንም ጉድፍ የለበትም…ያንቺን አባት የሚመስል ሰው በዚህ ምድር ላይ አልተፈጠረም…የዚህ ዓለም ቆነጃጅቶች ሁሉ አባትሽን ለማግኘት ቢደባደብና ቢቦጫጨቁ ተገቢ ነው…..አይደል..…?እንደዛ አይደል የምታስቢው..…?››
‹‹ምነው ባስብ ታዲያ ተሳሳትኩ……?.››
‹‹አዎ ተሳስተሸል..፡፡ባልና ሚስት በሆነ ነገር አልተስማሙም ማለት ጎጆቸውን ማፍረስ አለባቸው ማለት አይደለም…ደግሞ ልጄ አንድ ነገር ልነግርሽ እፈልጋለው.. ትዳርና ሀገር ውስብስብ ናቸው፡፡ትዳር ይዘሽ ልጆች ወልደሽ እና ንብረት አፍርተሸ ረጅም አመት ኖርሽ ማለት ሁሉ ነገር ገነታዊ ነው ማለት አይደለም…የሆነ ነገር ለማግኘት ሁሌ መክፈል ያለብሽ የሆነ መስዋዕትነት አለ…ባልሽ በምንም አይነት ሁኔታ መቶ ፐርሰንት አንቺ ወደምትወጂው ወይም አንቺ ወደምትጓዢበት የህይወት መንገድ ሊጓዝ አይችልም…እንደዛ እንዲያደርግ አደረግሽ ማለት ማነቱን አጠፋሺው ማለት ነው…ማንም ሰው ደግሞ የራሱን ማንነት እስከወዲያኛው ማጣት ስለማይፈልግ የሆነ ቀን ማንነቱን ለማስመለስ መንፈራገጡ አይቀርም ..ያ ደግሞ እቤት ወደመሰነጣጠቅ እና ወደማፍረሰ ያመራል…፡፡
አየሽ ባልና ሚስት ቃልኪዳናቸውን አክብረው እስከወዲያኛው ለመኖር አንድ ነገር ላይ ብቻ ነው እኩል መስማማት ሚገባቸው ‹‹ጎጆችን የጋራችን ነው… የጓጇችንን ህልውና ሁለታችንም እኩል እንፈልገዋለን… ለዛም ስንል ሁል ጊዜ በጋራ ሆነ በየግላችን የተቻለንን እንጥራለን..…››ይሄ ነው ወሳኙ ጉዳይ… ቃላቸውን ለማክበር ሲሉ ይከባበራሉ..ይሄንን ቃል ለማክበር ሲሉ ይደማመጣሉ፣ይሄንን እውን ለማድረግ ሲሉ ሁሌ ሳይሰለቻቸው ይቅር ይባባላሉ….ለጎጇቸው ህልውና ሲሉ ሰጥቶ በመቀበል ፤ተሸንፎም ጭምር በማሸነፍ እኩል ይጥራሉ….
እና ትዳር ቀላል ነገር አይደለም…ባልና ሚስት ተባብሎ እጅ ለእጅ በመያያዝ በየድግስ ቤቱ ከመሄድ በላይ ነው፣ባልና ሚስት መሆን አንድ መሶብ ከመብላት እና አንድ አልጋ ከመጋራትም በላይ ነው…
ይሄን ጌዜ ከተማውን ለቀን ቃሊቲ ኬላ ጋር ደርሰናል..…እየነዳው ያለውት ወደ ዱከም ነው..አባቴ ጥሬ ስጋ ይወዳል..ዱከም ደግሞ በጥሬ ስጋ የምታውቁት ነው…አባቴ ንግግሩን ቀጥሏል፡፡
ትዳር የሚባለው ተቋም ሀገር ከሚባለው የጋራ ቤት ጋር ይመሳሰላል…አንድ ሀገር ውስጥም በጋራ ለመኖር ሀገሬን እወዳለው ብቻ ማለት በቂ አይደለም..ለሀገሬ ስል ሌላው ወገኔ የማይፈልገውን ግማሽ ፍላጎቴን በውስጤ ማክሰምን ይጠይቃል…፡፡በሀገርሽ መጮኸ ሲያምርሽ መጮኸ ትችያለሽ….ጩኸትሽ ግን ህፃናቶች አስደንግጦ ችግር ላይ አለመጣሉን እርግጠኛ መሆንና ለሌላውም መጠንቀቅን ይጠይቃል…፡፡የጋራ በሆነ ሀገር ውስጥ ሙሉ ነፃነት ሚባል ነገር የለም…ያንቺ ነፃነት የእኔ ደህንነትን አደጋ ላይ የሚጥል ከሆነ ገደብ ይበጅለታል … ህግ የሚባል ገደብ…፡፡ስለዚህ በጋራ ሀገር ውስጥ የጋራ የሆነ ህግ ማክበር ስንችል ነው የጋራ የሆነች ሀገራችንን ህልውና ማስጠበቅ የምንችለው…ሀገራችን እንወዳለን ምንለው በትክክል የሚሰራው በዚህ መንገድ ብቻ ስንጓዝ ነው…ካለበለዚያ እንደፈለኩ ካልተንፈራገጥኩ ምል ከሆነ ስንፈራገጥ የሌላውን ሰው አፍንጫ ላጣምም ስለምችል ችግር መፍጠሬ አይቀርም ፤እራሴ አብኩቼ እራሴ ካልጋገርኩ አይጣፍጥም የምል ከሆነ አይደለም በጋራ ሀገር በጋራ ቤት ውስጥም ከቤተሰቦቼ ጋር መኖር አልችልም… …ሀገሩን የሚወድ ዲሞክራት ሰው እቤቱ ለተደገሰ ሰርግ የሚከፍተውን የሰርግ ዘፈን የጎራቤቱን የሀዘን ሙሾ አለመረበሹን ማረጋገጥ እና መጠንቀቅ እንዳለበት በደንብ ማወቅ አለበት….
ከየትኛው ሀሳብ ተነስተን ምን ውስጥ ገባን….አባቴ ሁሌ እንዴህ ነው….አንድ ነጠላ ስለቤተሰብ የተነሳችን ሀሳብ ለጥጦ ለጥጦ ሀገራዊና አለማቀፋዊ ጉዳይ ማድረግ የተካነበት ነው…...
አሁን ገላን ደርሰናል … የመኪናዋ ነዳጅ አስተማማኝ ስላልሆነ መኪናዬን ወደቀኝ ጠመዘዝኩና ወደ ነዳጅ ማደያ ገባው …. አስተካክዬ በማቆም ሞተሩን አጣፋውና ጋቢናውን ከፍቼ ከመኪናው ወረድኩ ..ነዳጁን እስኪሞላ ውሀ ስለጠማኝ ለመግዛት ወደሱፐር ማርኬት ነው ሄድኩት ….ምፈልገውን ገዝቼ ወደመኪናዬ ስመለስ ግማሽ መንገድ ላይ ከፊቴ ማን ገጭ ቢል ጥሩ መሰላችሁ ….?እስኪ ገምቱ …?አለቃዬ…አቤት የደነገጥኩት ድንጋጤ…በትምህርት ሰዓት ፎርፋ ሆቴል ቁጭ ብላ ስትዝናና አባቷ እይታ ውስጥ የገባች ልጃገረድ ነው የመሰልኩት…
‹‹ደግሞ እዚህ ምን ትሰሪያለሽ..…?››እጁን ለሰላምታ እየዘረጋልኝ
የዘረጋልኝን ከሶፍት የለሰለሰ የሴት የመሰለ እጁን እየጨበጥኩ..በዛውም ይሄ እጅ ገላዬ ላይ አርፎ ቢዳብሰኝ ምን ሊሰማኝ እደሚችል እየገመትኩ ‹‹ወደዱከም እየሄድን ..ነዳጅ እየሞላው ነው…›› ብዬ መለስኩለት ..በእጄ ወደመኪናችን እየጠቆምኩ
ግራ እንደማጋባትም እያለ‹‹ማለት…? ከማን ጋር……?››እንዴ!! እንደቦይ ፍሬንዴ እኮ ነው ኮስተር ብሎ እየጠየቀኝ ያለው
‹‹የትርፍ ጊዜ ስራ ከሚያሰሩኝ ከአለቃዬ ጋር …በእረፍት ቀናቸው መኪና ስላማይነዱ እኔነኝ ምሾፍርላቸው… ››ውሸቱን ከየት እንደመጣልኝ አላውቅም… ቀባጠርኩ…
‹‹አንቺ የእረፍት ቀንሽ አይደለ እንዴ……?ደግሞ መኪና መንዳት እደምትቺይ አልነገርሺኝም››
‹‹አልጠየቅከኝም እንጂ ብትጠይቀኝ እንገርህ ነበር……የእረፍት ቀንሽ ላልከው ደግሞ ደሀ እረፍት ቀን አያስፈልገውም..በዛ ላይ እንደምታየው ሰውዬዬ ጮማ ናቸው…አንተ ልታባርረኝ አይደል እሷቸው ናቸው
👍1
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍስሀ
ምን ነካኝ..? የዓመታት ፍቅረኛዬን
ከወንድ ጋር ስትዳራ እጅ ከፍንጅ የያዝኳት አይነት ስሜት ነው የተሰማኝ…የሆነ ውስጥ አንጀትን የሚያላውስ አይነት የመረበሽ ስሜት…የሆነ ልብን ድክም የሚያደርግ አይነት የፍርሀት ስሜት…የሆነ ያሳደጋችኃት ለማዳ ወፍ ከእጃችሁ አምልጣ ሰማዩ ተንሳፋ አድማሱን ሰንጥቃ ስትበርባችሁ በዛው ትቀር ይሆን.? ብላችሁ ስትሰጉ የሚሰማችሁ አይነት የእጦት ስሜት …
ሱፐር ማርኬት ልገዛ የመጣውትን ዕቃ ስለጠፋኝ እንደፈዘዝኩ ዝም ብዬ ባዶዬን ነው ወደመኪናዬ የተመለስኩ…... መኪናዬ ውስጥ ገባውና ሞተሩን አስነስቼ የመኪናዋን አፍንጫ ወደ አዲስአባ መለስኩት……
‹‹እንዴ ምን እየሆንክ ነው.?››
‹‹ይቅርታ ለስራ ጉዳይ ስለተደወለልኝ መመለስ አለብን››
‹‹እርግጠኛ ነህ.?››አለቺኝ….
‹‹ማነች እንደዛ ያለችህ.?›› እንዳትሉኝ…ፍቅረኛዬ ነች…ሳሮን ተስፋሁን ትባላለች፡፡አብረን ከሆን አንድ አመት አስቆጥረናል…የዛሬ አመት ለቫኬሽን ከውጭ የመጣው ጊዜ ነበር የተዋወቅነው…አንድ ወር እዚህ ስቆይ አብራኝ ነበረች..ከዛ ለትምህርቴ ወደውጭ ከተመለስኩ ቡኃላም በስልኩም በስካይፒውም ፍቅራችንን እንዲቀጥል ማድረግ ችለናል….አሁን ጨርሼ ከመጣው ቡኃላም እንደዛው…ዛሬ ወደ ደብረዘይት ለአዳር እየሄድን ነበር…. ዘና ብለን ለነገ ስራ በማለዳ ለመመለስ አቅደን ….ግን ይሄው ከቁጥጥር ውጭ በሆነ አደፍራሽ ስሜት ወደ አዲስአባ እየተመለስኩ ነው…..
‹‹እርግጠኛ ነህ ስትይ ….ምን ለማለት ነው.?››ጅራፍ ራሱ ገርፎ እራሱ ይጮኸል ይባላል ..ተቆጣሇት
‹‹የተደወለልህን ስልክ ታሰየኛለህ….?››
‹‹ማለት.? ››
‹‹ስከታተልህ ነበር …ምንም አይነት ስልክ ስታናግር አላየውም..ልጅቷ ማነች...?››
‹‹የቷ ልጅ.?››የምትለው ያልገባኘኝ መስዬ ጠየቅኳት
‹‹እንደዛ ያፈዘዘችህ ነቻ…ለዘመናት የጠፋችብህን ፍቅረኛህን በአጋጣሚ ያገኘህ ነው እኮ የምትመስለው….››
‹‹አትቀባጥሪ….››
‹‹አልተሳሳትኩም ማለት ነው….እንደው ወንዶች ሰትባሉ..››
‹‹በናትሽ አሁን ዝም ልትይልኝ ትቺያለሽ ..ምንም ነገር የመናገር ሙድ ላይ አይደለውም…››
‹‹እንግዲያውም አውርደኝ….››
‹‹የትነው ማወርድሽ.?››ገርሞኝ
‹‹እዚሁ አውርደኝ… ብቻዬን በትራንስፖርት ሄጄ አድሬ መጣለሁ…በስንት ዘዴ እና ውትወታ ቤተሰቤን አሳምኜ ያገኘውትን ከቤት ውጭ የማደር ዕድል ላባክነው አልፈልግም….››
‹‹እወነትሽን ባልሆነ.?››
‹‹እወነቴን ነው ..አውርደኝ አልኩህ እኮ…››አንቧረቀችብኝ
‹‹ሆድ ለባሰው ማጭድ አታውሰው ››ይላል የሀገሬ ሰው….ዳር ይዤ ፍሬኑን ጠርቅሜ ያዝኩና አቆምኩላት… ኮስሞቲኮቾን እና ቅያሬ ልብሶቾን ያጨቀችበትን ቦርሳዋን አንጠልጥላ ወረደች…ኪሴ ገባውና ለመዝናናት ይዥው የነበረ ከእሽጉ ያልተፈታ አምስት ሺ ብር እግሯ ስር ወረወርኩላትና መኪናዬን አስፈንጥሬ ተፈተለኩ……
ከዛ አዳሬን አትጠይቁኝ…ጥዋት አንድ ሰዓት ተኩል ቢሮ ነበርኩ..ስደርስ ፅዳቶች እንኳን ስራቸውን አላጠናቀቁም ነበር… አግኝቼ እስካናግራት ቸኩያለው አይገልፀውም…ደግሞ ሳይቸግረኝ ቅዳሜ ለት ከስራ መሰናበቷን የሚገልፅ የ30 ቀን ማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ፈርሜ ነበር….እርግጥ ከሰዓት ሰራተኞች ከወጡ ቡኃላ ስለፈረምኩ ዛሬ ነው የሚደርሳት…ግን እንዴት አድርጌ ማስተካከል እችላለው.. .?መዝገብ ቤት የሚሰሩት አስተዳዳሪውም ጭምር ደብዳቤውን አይተውታል… በውሳኔው የሚዋልል አሐቃ ደግሞ ማንም አያከብረውም….እንደዛ እንዲያስቡኝ ፈፅሞ አልፈልግም….፡፡ ግን ደግሞ የሆነ ነገር ማድረግ አለብኝ…፡፡ብትከሰኝ ጥሩ ነው.. ግን እንዴት ጥሩ ሊሆን ይችላል...?አውቄ ልሸነፍላት ማለት ነው.? ….እሱም ሌላ ጣጣ አለው..‹ በክስ አሸንፍው ተመለሰች› መባሉ ሌላ ውድቀት ነው….አዳሜ ትንሽ በነካዋት ቁጥር ወደክስ እንድትበር መንገድ ማሳየት ነው….፡፡ይልቅ ይቅርታ እዲደረግላት ደብዳቤ ብታስገባ ጥሩ ነው…፡፡አዎ እንደዛ እድታደርግ በዘዴ አግባባታለው…ግን ሳስበው እሷ እንደዛ አታርግም …በፍጽም አንገቷን እንዲህ በቀላሉ የምትደፋ አይነት ልጅ አይደለችም ….
የባጥ የቆጡን ሳስብ 3 ሰዓት ሆነ ..ፀሀፊዬን ጠራዋትና ፌናንን እንድትጠራልኝ ነገርኳት…. ደወለችና….እንዳልገባች ነገረችኝ››
‹‹ምን ማለት ነው … 3 ሰዓት ድረስ አለመግባት….?››ፀሀፊዬ ላይ ነው የጮህኩት
‹‹እኔ እንጃ...?በሞባይሏ ልደውልላት››አለቺኝ እየተሸቆጠቆጠች…፡፡
‹‹አይ ተያት ..እሷን በተመለከተ የተፃፈ ደብዳቤ ከመዝገብ ቤት ታስመጪልኛለሽ.?››
‹‹ቆይ እኔ እራሴ ላምጣ ››ብላ ሄደች
ከሶስት ደቂቃ ቡኃላ ተመልሳ መጣችና ደብዳቤውን እየሰጠቺኝ ‹‹…ያመጣውት ቀሪው ነው ..ዋናውን ፈርማ ወስዳዋለች››አለቺኝ
‹‹ማን ነች የወሰደችው.?››..ሳላስበው ከመቀመጫዬ ተነሳው
‹‹ፌናን ነቻ››
‹‹ምን ጊዜ ወሰደች….? ቅዳሜ ከሰዓት ነበር እኮ የፈረምኩት …ለማንኛው አመሰግናለው..››ብዬ ፀሀፊዋን ሸኘዋትና አስተዳዳሪው ጋር ደወልኩ
‹ደህና አደርክ አቶ ፍሰሀ››
‹‹ሰላም ነኝ..ፌናንን ፈልጌያት ነበር››ቀጥታ ወደ ጉዳዬ ገባው….
‹‹አልገባችም ››
‹‹አልገባኝም ማለት.?››
‹‹ምትገባ አይመስለኝም …..ያው የተሰናበተችበትን ደብዳቤ ወስዳለች..››
‹‹ትውሰዳ..ዝም ብላ ደብዳቤ ተቀብላ መቅረት ትችላለች እንዴ...?ፎርማሊቲ ምናምን ሚባል ነገር የለም….?››
‹‹አይ ፍቃድ ሞልታለች..እንደዛ እንዲሆን መሰለኝ የተነጋገርነው››
‹‹ከምኔው እንዲህ ተዋክባ ሞላችው.?››
‹‹እኔም አልገባኝ አቶ ፍሰሀ …ደብዳቤውን ጥዋት ስገባ ጠረጳዛዬ ላይ ነው ያገኘውት››አሉኝ እየታዘብኝ መሆኑን በሚያሳብቅባቸው ቃና….
ስልኩን በንዴት ጆሮቸው ላይ ጠረቀምኩት ..እስቲ እሳቸው ምን አደረጉኝ…..
…..መልሼ የጠረጳዛውን መጥሪያ ተጫንኩ…ፀሀፊዬ መጣች…‹‹አቤት ፈለከኝ››
===
‹‹ደውይላት… ሞባይሏ ላይ ደውይላት …››ተመልሳ ሄደችና ሞባይሏን ይዛ መጥታ እያየዋት መሞከር ጀመረች… ትግስቴን በሚፈታተን ሁኔታ ደግማ ደጋግማ ሞከረች…‹‹ጥሪ አይቀበልም ነው ሚለው..ሁለቱም ሲሞ አይሰራም››
‹‹የቤት ወይም የጓደኛ ስልክ የላትም.?››
‹‹እኔ አላውቅም ..ወይ የሚያውቅ ሰው ካለ ልጠይቅልህ….?››ግራ ግብትብት ያላት ፀሀፊዬ መፍትሔ ያለችወን ሀሳብ አመጣች…››
‹‹አይ ተይው..አመሰግናለው…››ሸኘዋት
‹‹ምን እሆንኩ ነው ….?እዚህ ቢሮ ስራ ከጀማርኩ ሁለት ሳምንቴ ነው…፡፡በሁለት ሳምንት ብቻ የማውቃት ሴት እንዴት እንዲህ ውስጤን የማተረማመስ አቅም ኖራት….?ነው ወይስ ከእኔ ዕውቅና ውጭ ለዘማናት በውስጤ በስውር የኖረችበት የተፈጥሮ ምትሀታዊ ሚስጥር ይኖር ይሆን...?አይ እንደዛም አይሆንም አሁን እሷን መፈለግ ነው ወይስ በድያታለው ብዬ ስላሰብኩ መፀፀት የወለደው የጥፋተኝነት ስሜት ነው እንዲህ የሚያደርገኝ….?.በቃ አንዴ ላግኛትና አዋርቻት ይቅርታ ከጠየቅኳት ቡኃላ ይሄ ስሜት ይተወኛል…፡፡አዎ እርግጠኛ ነኝ ይተወኛል…››እራሴን ለማፅናናት ብዙ ጣርኩ…መልሼ የጠረጳዛዬን መጥሬያ አንጫረርኩ..የፈረደባት ፀሀፊዬ በፍጥነት መጣች
‹‹ፋይሎን ታመጪልኝ.?››››
‹‹የማንን.?››
‹‹ሌላ የማን ይሆናል .. .?የፌናንን ነዋ››
…‹‹እሺ›› ብላ ሹክክ ብላ ወጥታ ሄደች
‹‹ሰውዬው አረ ተረጋጋ….አሁን ይህቺ ምስኪን ምን አደረገችህ ….?›› እራሴን ለመገሰጽ ሞከርኩ…ይዛልኝ መጣችና አስረክባኝ ወደ ቦታዋ ተመለሰች …
‹‹ፋይሏን ገልጬ ማየት ጀመርኩ…ዝም ብሎ ስሜቴ ስለገፋፋኝ ወይንም ግራ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍስሀ
ምን ነካኝ..? የዓመታት ፍቅረኛዬን
ከወንድ ጋር ስትዳራ እጅ ከፍንጅ የያዝኳት አይነት ስሜት ነው የተሰማኝ…የሆነ ውስጥ አንጀትን የሚያላውስ አይነት የመረበሽ ስሜት…የሆነ ልብን ድክም የሚያደርግ አይነት የፍርሀት ስሜት…የሆነ ያሳደጋችኃት ለማዳ ወፍ ከእጃችሁ አምልጣ ሰማዩ ተንሳፋ አድማሱን ሰንጥቃ ስትበርባችሁ በዛው ትቀር ይሆን.? ብላችሁ ስትሰጉ የሚሰማችሁ አይነት የእጦት ስሜት …
ሱፐር ማርኬት ልገዛ የመጣውትን ዕቃ ስለጠፋኝ እንደፈዘዝኩ ዝም ብዬ ባዶዬን ነው ወደመኪናዬ የተመለስኩ…... መኪናዬ ውስጥ ገባውና ሞተሩን አስነስቼ የመኪናዋን አፍንጫ ወደ አዲስአባ መለስኩት……
‹‹እንዴ ምን እየሆንክ ነው.?››
‹‹ይቅርታ ለስራ ጉዳይ ስለተደወለልኝ መመለስ አለብን››
‹‹እርግጠኛ ነህ.?››አለቺኝ….
‹‹ማነች እንደዛ ያለችህ.?›› እንዳትሉኝ…ፍቅረኛዬ ነች…ሳሮን ተስፋሁን ትባላለች፡፡አብረን ከሆን አንድ አመት አስቆጥረናል…የዛሬ አመት ለቫኬሽን ከውጭ የመጣው ጊዜ ነበር የተዋወቅነው…አንድ ወር እዚህ ስቆይ አብራኝ ነበረች..ከዛ ለትምህርቴ ወደውጭ ከተመለስኩ ቡኃላም በስልኩም በስካይፒውም ፍቅራችንን እንዲቀጥል ማድረግ ችለናል….አሁን ጨርሼ ከመጣው ቡኃላም እንደዛው…ዛሬ ወደ ደብረዘይት ለአዳር እየሄድን ነበር…. ዘና ብለን ለነገ ስራ በማለዳ ለመመለስ አቅደን ….ግን ይሄው ከቁጥጥር ውጭ በሆነ አደፍራሽ ስሜት ወደ አዲስአባ እየተመለስኩ ነው…..
‹‹እርግጠኛ ነህ ስትይ ….ምን ለማለት ነው.?››ጅራፍ ራሱ ገርፎ እራሱ ይጮኸል ይባላል ..ተቆጣሇት
‹‹የተደወለልህን ስልክ ታሰየኛለህ….?››
‹‹ማለት.? ››
‹‹ስከታተልህ ነበር …ምንም አይነት ስልክ ስታናግር አላየውም..ልጅቷ ማነች...?››
‹‹የቷ ልጅ.?››የምትለው ያልገባኘኝ መስዬ ጠየቅኳት
‹‹እንደዛ ያፈዘዘችህ ነቻ…ለዘመናት የጠፋችብህን ፍቅረኛህን በአጋጣሚ ያገኘህ ነው እኮ የምትመስለው….››
‹‹አትቀባጥሪ….››
‹‹አልተሳሳትኩም ማለት ነው….እንደው ወንዶች ሰትባሉ..››
‹‹በናትሽ አሁን ዝም ልትይልኝ ትቺያለሽ ..ምንም ነገር የመናገር ሙድ ላይ አይደለውም…››
‹‹እንግዲያውም አውርደኝ….››
‹‹የትነው ማወርድሽ.?››ገርሞኝ
‹‹እዚሁ አውርደኝ… ብቻዬን በትራንስፖርት ሄጄ አድሬ መጣለሁ…በስንት ዘዴ እና ውትወታ ቤተሰቤን አሳምኜ ያገኘውትን ከቤት ውጭ የማደር ዕድል ላባክነው አልፈልግም….››
‹‹እወነትሽን ባልሆነ.?››
‹‹እወነቴን ነው ..አውርደኝ አልኩህ እኮ…››አንቧረቀችብኝ
‹‹ሆድ ለባሰው ማጭድ አታውሰው ››ይላል የሀገሬ ሰው….ዳር ይዤ ፍሬኑን ጠርቅሜ ያዝኩና አቆምኩላት… ኮስሞቲኮቾን እና ቅያሬ ልብሶቾን ያጨቀችበትን ቦርሳዋን አንጠልጥላ ወረደች…ኪሴ ገባውና ለመዝናናት ይዥው የነበረ ከእሽጉ ያልተፈታ አምስት ሺ ብር እግሯ ስር ወረወርኩላትና መኪናዬን አስፈንጥሬ ተፈተለኩ……
ከዛ አዳሬን አትጠይቁኝ…ጥዋት አንድ ሰዓት ተኩል ቢሮ ነበርኩ..ስደርስ ፅዳቶች እንኳን ስራቸውን አላጠናቀቁም ነበር… አግኝቼ እስካናግራት ቸኩያለው አይገልፀውም…ደግሞ ሳይቸግረኝ ቅዳሜ ለት ከስራ መሰናበቷን የሚገልፅ የ30 ቀን ማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ፈርሜ ነበር….እርግጥ ከሰዓት ሰራተኞች ከወጡ ቡኃላ ስለፈረምኩ ዛሬ ነው የሚደርሳት…ግን እንዴት አድርጌ ማስተካከል እችላለው.. .?መዝገብ ቤት የሚሰሩት አስተዳዳሪውም ጭምር ደብዳቤውን አይተውታል… በውሳኔው የሚዋልል አሐቃ ደግሞ ማንም አያከብረውም….እንደዛ እንዲያስቡኝ ፈፅሞ አልፈልግም….፡፡ ግን ደግሞ የሆነ ነገር ማድረግ አለብኝ…፡፡ብትከሰኝ ጥሩ ነው.. ግን እንዴት ጥሩ ሊሆን ይችላል...?አውቄ ልሸነፍላት ማለት ነው.? ….እሱም ሌላ ጣጣ አለው..‹ በክስ አሸንፍው ተመለሰች› መባሉ ሌላ ውድቀት ነው….አዳሜ ትንሽ በነካዋት ቁጥር ወደክስ እንድትበር መንገድ ማሳየት ነው….፡፡ይልቅ ይቅርታ እዲደረግላት ደብዳቤ ብታስገባ ጥሩ ነው…፡፡አዎ እንደዛ እድታደርግ በዘዴ አግባባታለው…ግን ሳስበው እሷ እንደዛ አታርግም …በፍጽም አንገቷን እንዲህ በቀላሉ የምትደፋ አይነት ልጅ አይደለችም ….
የባጥ የቆጡን ሳስብ 3 ሰዓት ሆነ ..ፀሀፊዬን ጠራዋትና ፌናንን እንድትጠራልኝ ነገርኳት…. ደወለችና….እንዳልገባች ነገረችኝ››
‹‹ምን ማለት ነው … 3 ሰዓት ድረስ አለመግባት….?››ፀሀፊዬ ላይ ነው የጮህኩት
‹‹እኔ እንጃ...?በሞባይሏ ልደውልላት››አለቺኝ እየተሸቆጠቆጠች…፡፡
‹‹አይ ተያት ..እሷን በተመለከተ የተፃፈ ደብዳቤ ከመዝገብ ቤት ታስመጪልኛለሽ.?››
‹‹ቆይ እኔ እራሴ ላምጣ ››ብላ ሄደች
ከሶስት ደቂቃ ቡኃላ ተመልሳ መጣችና ደብዳቤውን እየሰጠቺኝ ‹‹…ያመጣውት ቀሪው ነው ..ዋናውን ፈርማ ወስዳዋለች››አለቺኝ
‹‹ማን ነች የወሰደችው.?››..ሳላስበው ከመቀመጫዬ ተነሳው
‹‹ፌናን ነቻ››
‹‹ምን ጊዜ ወሰደች….? ቅዳሜ ከሰዓት ነበር እኮ የፈረምኩት …ለማንኛው አመሰግናለው..››ብዬ ፀሀፊዋን ሸኘዋትና አስተዳዳሪው ጋር ደወልኩ
‹ደህና አደርክ አቶ ፍሰሀ››
‹‹ሰላም ነኝ..ፌናንን ፈልጌያት ነበር››ቀጥታ ወደ ጉዳዬ ገባው….
‹‹አልገባችም ››
‹‹አልገባኝም ማለት.?››
‹‹ምትገባ አይመስለኝም …..ያው የተሰናበተችበትን ደብዳቤ ወስዳለች..››
‹‹ትውሰዳ..ዝም ብላ ደብዳቤ ተቀብላ መቅረት ትችላለች እንዴ...?ፎርማሊቲ ምናምን ሚባል ነገር የለም….?››
‹‹አይ ፍቃድ ሞልታለች..እንደዛ እንዲሆን መሰለኝ የተነጋገርነው››
‹‹ከምኔው እንዲህ ተዋክባ ሞላችው.?››
‹‹እኔም አልገባኝ አቶ ፍሰሀ …ደብዳቤውን ጥዋት ስገባ ጠረጳዛዬ ላይ ነው ያገኘውት››አሉኝ እየታዘብኝ መሆኑን በሚያሳብቅባቸው ቃና….
ስልኩን በንዴት ጆሮቸው ላይ ጠረቀምኩት ..እስቲ እሳቸው ምን አደረጉኝ…..
…..መልሼ የጠረጳዛውን መጥሪያ ተጫንኩ…ፀሀፊዬ መጣች…‹‹አቤት ፈለከኝ››
===
‹‹ደውይላት… ሞባይሏ ላይ ደውይላት …››ተመልሳ ሄደችና ሞባይሏን ይዛ መጥታ እያየዋት መሞከር ጀመረች… ትግስቴን በሚፈታተን ሁኔታ ደግማ ደጋግማ ሞከረች…‹‹ጥሪ አይቀበልም ነው ሚለው..ሁለቱም ሲሞ አይሰራም››
‹‹የቤት ወይም የጓደኛ ስልክ የላትም.?››
‹‹እኔ አላውቅም ..ወይ የሚያውቅ ሰው ካለ ልጠይቅልህ….?››ግራ ግብትብት ያላት ፀሀፊዬ መፍትሔ ያለችወን ሀሳብ አመጣች…››
‹‹አይ ተይው..አመሰግናለው…››ሸኘዋት
‹‹ምን እሆንኩ ነው ….?እዚህ ቢሮ ስራ ከጀማርኩ ሁለት ሳምንቴ ነው…፡፡በሁለት ሳምንት ብቻ የማውቃት ሴት እንዴት እንዲህ ውስጤን የማተረማመስ አቅም ኖራት….?ነው ወይስ ከእኔ ዕውቅና ውጭ ለዘማናት በውስጤ በስውር የኖረችበት የተፈጥሮ ምትሀታዊ ሚስጥር ይኖር ይሆን...?አይ እንደዛም አይሆንም አሁን እሷን መፈለግ ነው ወይስ በድያታለው ብዬ ስላሰብኩ መፀፀት የወለደው የጥፋተኝነት ስሜት ነው እንዲህ የሚያደርገኝ….?.በቃ አንዴ ላግኛትና አዋርቻት ይቅርታ ከጠየቅኳት ቡኃላ ይሄ ስሜት ይተወኛል…፡፡አዎ እርግጠኛ ነኝ ይተወኛል…››እራሴን ለማፅናናት ብዙ ጣርኩ…መልሼ የጠረጳዛዬን መጥሬያ አንጫረርኩ..የፈረደባት ፀሀፊዬ በፍጥነት መጣች
‹‹ፋይሎን ታመጪልኝ.?››››
‹‹የማንን.?››
‹‹ሌላ የማን ይሆናል .. .?የፌናንን ነዋ››
…‹‹እሺ›› ብላ ሹክክ ብላ ወጥታ ሄደች
‹‹ሰውዬው አረ ተረጋጋ….አሁን ይህቺ ምስኪን ምን አደረገችህ ….?›› እራሴን ለመገሰጽ ሞከርኩ…ይዛልኝ መጣችና አስረክባኝ ወደ ቦታዋ ተመለሰች …
‹‹ፋይሏን ገልጬ ማየት ጀመርኩ…ዝም ብሎ ስሜቴ ስለገፋፋኝ ወይንም ግራ
😁2👍1👏1
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍስሀ
መፅሃፍ መደብሩ ቆሜያለሁ ነገረ ስራዋን በአትኩሮት እየተከታተልኩ ነው፡፡
ገዢው የሆነ መፃፍ ርዕስ ነገሯት
‹‹እንደዚህ የሚባል መጽሀፍ አለሽ.?››ጠየቃት
‹‹አለኝ ግን ለምን ፈለግከው?››
‹‹አልገባኝም?ልገዛሽ ነዋ.?››
‹‹እሱማ ልትገዛኝ ነው ?ለምን መጽሀፉን ልትገዛው ፈለክ ነው ጥያቄዬ?››
‹‹ለምንስ ብፈልገው አንቺ ምን ይመለከትሻል ?ካለሽ ሽጪልኝ ከሌለሽ የለኝም በይ››
‹‹ስኳር ወይ ሳሙና አይደለም የምትገዛው፤ መጽሀፍ ነው..፡፡መጽሀፍቶች ደግሞ ሳያነቡ የሚያነቡ ለመምሰል ታቅፈዋቸው የሚዞሩ ከንቱዎች እጅ እንዲገቡ አልፈልግም በተለይ እንደጠየቅከው ያለ መጽሀፍ……..፡፡ይሄውልህ እዛ አካባቢ በመደዳ መጽሀፍት ቤቶች አሉ ካላቸው ምክንያት ሳይጠይቁ ይሸጡልኸል….ደህና ሁን››ብላ አሰናበተችው፡፡
ሰውዬው በመገረም እያጉረመረመ ጥሏት ሄደ ..ዞር ስትል እኔን አየቺኝ
‹‹እንዴ አለቃ ምን እግር ጣለህ...?መፅሀፍ ልገዛሽ ነው እንዳትለኝ…?››አለች በመጠኑ ፈገግ ብላ
‹‹ለመሆኑ የትኛው የዋህ ነጋዴ ነው ለመክሰር አንቺን እዚህ ያቆመሽ….?››የእወነቴን ነበር የተናገርኩት
‹‹የሚተማመንብኝ››
‹‹እንዲ ደንበኛ እያበሳጨሽ እያባረርሽበት ነው የሚተማመንብሽ…››
ልትመልስልኝ አፎን ስታስተካክል አንድ ሽበት የወረራቸው ደስ የሚል ግርማ ሞገስ ያላቸው ግን ደግሞ ጎስቆል ያሉ አዛውንት ድምጽ በመሀከላችን ገባ ?››
‹‹ደህና ነሽ የእኔ አለም….?››
‹‹ደህና አደሩ..እንዴት ኖት? ጤናዎትስ?››እኔን ከማውቃት ተቃራኒ በሆነ እርብትብት ትህትና እየተፍለቀለቀች እና እየፈገገች በጋለ ሰላምታ ተቀበለቻቸው፡፡ሰው እንዴት እንዲህ ሁለት ገፃ ይኖረዋል?
‹‹….ሰላም ነኝ ልጄ…፡፡ይመስገነው፡፡››
‹‹አኔ እኮ ሲጠፉብኝ ያመሞት መስሎኝ ሰግቼ ነበር››
‹‹አይ ደህና ነኝ.ባለፈው ያስቀመጥሺልኝን መጽሀፍ ልጆቹ ሰጥተውኝ ወስጄ ነበር..እና መጻሀፎ ስለመሰጠቺኝ ከቤት መውጣት አልቻልኩም ለዛ ነው የጠፋሁብሽ››
‹‹ጨረሱት?››
‹‹ጨረሱት..ሁለት ጊዜ ነው ደግሜ ያነበብኩት…አሁንም አንዴ የምደግመው ይመስለኛል..››
‹‹ስለወደዱት ደስ ብሎኛል..አሁንም ያዘጋጀውሏት መጽሀፍ አለች›› ብላ ከተቆለሉት መጽሀፎቶች ጀርባ እጆን ሰደደችና አንድ ልባሱ አርጀት ያለ መጽሀፍት አውጥታ ሰጣቻቸው ፡፡በመንሰፍሰፍ ተቀበሏት እና ርዕሱን አገላብጠው ካነበብ ቡሃላ እሷን ወደ ራሳቸው ጎትተው ግንባሯን ከሳሟት ቡኃላ ‹‹ ስንትነው የእኔ ልጅ .?››ጠየቋት
‹‹ሁለት መቶ ሀምሳ ብር ነው የገዛውሎት››
ቀኝ የካፖርት ኪሳቸው ገቡ…የሆነ ባለአስር ብር ዝርዝር ብሮች አወጡ..የካፖርታቸውን ኪስ ከፈቱና ደረት ኪሳቸው ገቡ ሳንቲም ሳይቀር ያለቸውን ብር ከየኪሳቸው እያወጡ ባንኮኒው ላይ ዘረገፍት.በትኩረተ ስከታተላቸው ነበር…ቢቆጠር ከመቶ ምናንም ብር አይበልጥም ቢያንስ የጠየቀቻቸውን ግማሹን አይሸፍንም
‹‹ልጄ በዚህ ላይ አንቺ ሙይልኝ…››አሏት…የልመና ሳይሆን የትዕዛዝ ቃና ባለው የመተማመን ስሜት
‹‹.አይ ይሄ ልጅ የእርሶ አድናቂ ነው… ገና ሲመጡ አይቶት የሚወስዱትን መፃሀፍን እኔ ነኝ የምከፈለው.. አደራሽን እንዳተቀበያቸው ሲለኝ ነበር..አይደል ፍሰሀ?››አለቺኝ ወደእኔ ቀና ብላ አፍጥጣ እያየቺኝ
‹‹አዎ…እባኮት እልኩና ወደኪሴ ገብቼ ዋሌቴን በማውጣት በግምት አንድ ሺ ምናምን ብር ይመስለኛል አወጣውና ይሄው ብሩ የሚችለውን አይነት የሚፈልጉትን መጽሀፍ ስጭልኝ….››
<<አላልኮትም ››አለችና የእሳቸውን ብር ከባንኮኒው ሰብስባ ኪሳቸው መልሳ ጨመረችላቸውና…
‹‹ሌላ ምን ምን መፃሀፍ ነው የሚፈልጉት….?››
‹‹ያው የመጽሀፍ ምርጫዎቼን ታውቂ የለ.››
…ስድስት ወይም ሰባት የሚሆኑ መጻሀፎችን መረጠችና በፔስታል አድርጋ ሰጠቻቸው
ሰውዬው ከመሄዳቸው በፊት ወደእኔ ጠጋ አሉ..ብዙ ምርቃት እንደሚያዘንቡብኝ እየጠበቅኩ ነው…‹‹እነዚህን መፃሀፎች አንብቦ ለመጨረስ ሁለት ወር ያህል ይፈጅብኛል…ለቀጣዬቹ ሁለት ወራት እንድኖር የሚያስችል ምክንያት ሰጠተኸኛል ማለት ነው..ምክንያቱም እኔ በምንም አይነት ሁኔታ እጄ ላይ ያሉ መጽሀፎቸን አንብቤ ሳልጨርስ አልሞትምና.››አሉኝ ..ምን ለማለት እንደፈለጉ አልገባኝም..ይህቺ ልጅ ግራ አጋቢ የሆነችው ከእንደዚህ አይነት ግራ አጋቢ ብኩኖች ጋር እየኖረች ነው ስል በውስጤ አሰብኩ.. ሽማግሌው ወደፌናን ዞረው ‹‹የእኔ ትንሽ መላአክ ደህና ሰንብቺልኝ..››ብለው ፊታቸውን አዙረው የመጽሀፍ መደብሩን ለቀው ወጡ
‹‹ምትገርሚ እብድ ነሽ.ለማላውቃቸው ሰው መጽሀፍ ታስገዥኛለሽ…ደግሞ ባዋርድሽስ.?››
‹‹ምን ብለህ ነው የምታዋርደኝ.?››
<<መች አልኩሽ .?››ብልሽስ
‹‹አትልማ ..ለራስህ ያለህን ግምት በደንብ አውቃለው..››
<<እንዴት ነው ምታውቂው ….?በጣም ጉረኛ ነሽ…?ዘመድሽ መስለውኝ ነው..ደግሞ ደስ የሚሉ አዛውንት ናቸው.የሚያነብ ሰው እወዳለው ለዛ ነው…›› አልኩ ቀጥሎ በመሀከላችን ለሚፈጠረው ነገር ጥሩ ስሜት እንዲፈጠር ና ንግግራችን እንዳይከር እየፈራው
‹‹ ማን መሆናቸውን ታውቃለህ?››
‹‹እኔ እንጃ .በምን አውቃለው ፡፡ካለዛሬም አይቻቸው አላውቅም..እዚህ ቦታም ስገኝ የመጀመሪያ ቀኔ ነው››
እንግዲህ እንደዛ እንድታደርግ እድሉን ስላመቻቸውልህ አመስግነኝ…ምክንያቱም ለእሷቸው መፅሀፍ መግዛት ብዙ ሰዎች ቢፈልጉም እድሉን አያገኙምና›› ብላ ማንነታቸውን ነገረቺኝ… ነዘረኝ ከሰማዩ የሚከብድ ስም ያላቸው..ለኢትዬጵያ ብዙ የሰሩ ፤ ብዙ መጽሀፍ የጻፉ ታላቅ ደራሲ ናቸው..አፍሬ አፌን ያዝኩ.ማንነታቸውን ቀድሜ ባውቅ ኖሮ መፅሀፍ ልግዛሎት ብዬ ገንዘብ ከኪሴ ለማውጣት ድፍረት ሚኖረኝ አይመስለኝም
‹‹ስማቸው እና ኪሳቸው ምነው እንዲህ ተራራቀ.››ብዬ የገረመኝን ጥያቄ ጠየቅኳት
‹‹ስማቸውን እኮ በአዕምሮቸው እንጂ በኪሳቸው አይደለም ያገኙት…እሳቸው ለቁሳዊ ሀብት ብዙም ግድ የላቸውም ..ከሚጠቀሙት በላይ ገንዘብ ኪሳቸው እዲከርም አይፈልጉም..ግን አንዳንዴ እንደዛሬ ቀን የሚፈልጉት መፃሀፍ የሚገዙበት ብር ሲጎድላቸው ይበሳጫሉ..››ብላ ልታስረዳኝ ሞከረች፡፡
‹‹ሚገርም ፅናት ነው››አልኩኝ
‹‹ አዎ ነው..አንተ ግን ምን ፈልገህ እዚህ ድረስ መጣህ .?ነው እግረመንገድህን ስታልፍ ድንገት አይተኸኝ ነው?››አለችኝ ኮስተር ብላ..ሞባይሌን ከፈትኩና ሰዓቱን አየው..አምስት ሰዓት ከሩብ ይላል
‹‹ምሳ ልጋብዝሽ ነው አመጣጤ…ምሳ ስንት ሰዓት ነው መውጣት የሚፈቀድልሽ….?››
‹‹ምሳ ምሳ...?››
‹‹አዎ ምሳ..››
ስልኳን አወጣችና ደወለች…‹‹ቶሎ ና ልወጣ ነው…››ብላ መልሳ ዘጋችው…
‹‹የሚቀበለኝ ልጅ እስኪመጣ መኪና ውስጥ ጠብቀኝ ከአስር ደቂቃ ቡኃላ መጣለው››እንዲህ በቀላሉ እሺ ትለኛች ብዬ እልጠበቅኩም ነበር…ሀሳቧን እንዳትቀይር ‹‹እሺ አመሰግናለው›› ብዬ እንደህጻን በውስጤ እየቧረቅኩ በፍጥነት ወደ መኪናዬ ተመለስኩና መሪውን ከሹፌሬ ተቀብዬ እሱ በታክሲ ወደቢሮ እንዲመለስ ልኬው እሷን መጠበቅ ጀመርኩ…ስለእሷ እያሰብኩ…ስንት ሰው እንደሆነች እያሰላው...ከሳምንት በፊት እኛ ካምፓኒ ነበር የምትሰራው…ከዛ ሹፌር ሆና ስትሰራ አገኛዋት አሁን ደግሞ የመፃሀፍት መደብር ሻጭ..ህይወቷን እንዴት እዴት ነው ጢቢ ጢቢ እየተጫወተችበት ያለው.?መስመር የሚያሲዛት ቤተሰብ የላትም ማለት ነው….?እስቲ ትምጣና ለዚህ ሁሉ ጥያቄዎቼ መልስ ትሰጠኛለች….
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍስሀ
መፅሃፍ መደብሩ ቆሜያለሁ ነገረ ስራዋን በአትኩሮት እየተከታተልኩ ነው፡፡
ገዢው የሆነ መፃፍ ርዕስ ነገሯት
‹‹እንደዚህ የሚባል መጽሀፍ አለሽ.?››ጠየቃት
‹‹አለኝ ግን ለምን ፈለግከው?››
‹‹አልገባኝም?ልገዛሽ ነዋ.?››
‹‹እሱማ ልትገዛኝ ነው ?ለምን መጽሀፉን ልትገዛው ፈለክ ነው ጥያቄዬ?››
‹‹ለምንስ ብፈልገው አንቺ ምን ይመለከትሻል ?ካለሽ ሽጪልኝ ከሌለሽ የለኝም በይ››
‹‹ስኳር ወይ ሳሙና አይደለም የምትገዛው፤ መጽሀፍ ነው..፡፡መጽሀፍቶች ደግሞ ሳያነቡ የሚያነቡ ለመምሰል ታቅፈዋቸው የሚዞሩ ከንቱዎች እጅ እንዲገቡ አልፈልግም በተለይ እንደጠየቅከው ያለ መጽሀፍ……..፡፡ይሄውልህ እዛ አካባቢ በመደዳ መጽሀፍት ቤቶች አሉ ካላቸው ምክንያት ሳይጠይቁ ይሸጡልኸል….ደህና ሁን››ብላ አሰናበተችው፡፡
ሰውዬው በመገረም እያጉረመረመ ጥሏት ሄደ ..ዞር ስትል እኔን አየቺኝ
‹‹እንዴ አለቃ ምን እግር ጣለህ...?መፅሀፍ ልገዛሽ ነው እንዳትለኝ…?››አለች በመጠኑ ፈገግ ብላ
‹‹ለመሆኑ የትኛው የዋህ ነጋዴ ነው ለመክሰር አንቺን እዚህ ያቆመሽ….?››የእወነቴን ነበር የተናገርኩት
‹‹የሚተማመንብኝ››
‹‹እንዲ ደንበኛ እያበሳጨሽ እያባረርሽበት ነው የሚተማመንብሽ…››
ልትመልስልኝ አፎን ስታስተካክል አንድ ሽበት የወረራቸው ደስ የሚል ግርማ ሞገስ ያላቸው ግን ደግሞ ጎስቆል ያሉ አዛውንት ድምጽ በመሀከላችን ገባ ?››
‹‹ደህና ነሽ የእኔ አለም….?››
‹‹ደህና አደሩ..እንዴት ኖት? ጤናዎትስ?››እኔን ከማውቃት ተቃራኒ በሆነ እርብትብት ትህትና እየተፍለቀለቀች እና እየፈገገች በጋለ ሰላምታ ተቀበለቻቸው፡፡ሰው እንዴት እንዲህ ሁለት ገፃ ይኖረዋል?
‹‹….ሰላም ነኝ ልጄ…፡፡ይመስገነው፡፡››
‹‹አኔ እኮ ሲጠፉብኝ ያመሞት መስሎኝ ሰግቼ ነበር››
‹‹አይ ደህና ነኝ.ባለፈው ያስቀመጥሺልኝን መጽሀፍ ልጆቹ ሰጥተውኝ ወስጄ ነበር..እና መጻሀፎ ስለመሰጠቺኝ ከቤት መውጣት አልቻልኩም ለዛ ነው የጠፋሁብሽ››
‹‹ጨረሱት?››
‹‹ጨረሱት..ሁለት ጊዜ ነው ደግሜ ያነበብኩት…አሁንም አንዴ የምደግመው ይመስለኛል..››
‹‹ስለወደዱት ደስ ብሎኛል..አሁንም ያዘጋጀውሏት መጽሀፍ አለች›› ብላ ከተቆለሉት መጽሀፎቶች ጀርባ እጆን ሰደደችና አንድ ልባሱ አርጀት ያለ መጽሀፍት አውጥታ ሰጣቻቸው ፡፡በመንሰፍሰፍ ተቀበሏት እና ርዕሱን አገላብጠው ካነበብ ቡሃላ እሷን ወደ ራሳቸው ጎትተው ግንባሯን ከሳሟት ቡኃላ ‹‹ ስንትነው የእኔ ልጅ .?››ጠየቋት
‹‹ሁለት መቶ ሀምሳ ብር ነው የገዛውሎት››
ቀኝ የካፖርት ኪሳቸው ገቡ…የሆነ ባለአስር ብር ዝርዝር ብሮች አወጡ..የካፖርታቸውን ኪስ ከፈቱና ደረት ኪሳቸው ገቡ ሳንቲም ሳይቀር ያለቸውን ብር ከየኪሳቸው እያወጡ ባንኮኒው ላይ ዘረገፍት.በትኩረተ ስከታተላቸው ነበር…ቢቆጠር ከመቶ ምናንም ብር አይበልጥም ቢያንስ የጠየቀቻቸውን ግማሹን አይሸፍንም
‹‹ልጄ በዚህ ላይ አንቺ ሙይልኝ…››አሏት…የልመና ሳይሆን የትዕዛዝ ቃና ባለው የመተማመን ስሜት
‹‹.አይ ይሄ ልጅ የእርሶ አድናቂ ነው… ገና ሲመጡ አይቶት የሚወስዱትን መፃሀፍን እኔ ነኝ የምከፈለው.. አደራሽን እንዳተቀበያቸው ሲለኝ ነበር..አይደል ፍሰሀ?››አለቺኝ ወደእኔ ቀና ብላ አፍጥጣ እያየቺኝ
‹‹አዎ…እባኮት እልኩና ወደኪሴ ገብቼ ዋሌቴን በማውጣት በግምት አንድ ሺ ምናምን ብር ይመስለኛል አወጣውና ይሄው ብሩ የሚችለውን አይነት የሚፈልጉትን መጽሀፍ ስጭልኝ….››
<<አላልኮትም ››አለችና የእሳቸውን ብር ከባንኮኒው ሰብስባ ኪሳቸው መልሳ ጨመረችላቸውና…
‹‹ሌላ ምን ምን መፃሀፍ ነው የሚፈልጉት….?››
‹‹ያው የመጽሀፍ ምርጫዎቼን ታውቂ የለ.››
…ስድስት ወይም ሰባት የሚሆኑ መጻሀፎችን መረጠችና በፔስታል አድርጋ ሰጠቻቸው
ሰውዬው ከመሄዳቸው በፊት ወደእኔ ጠጋ አሉ..ብዙ ምርቃት እንደሚያዘንቡብኝ እየጠበቅኩ ነው…‹‹እነዚህን መፃሀፎች አንብቦ ለመጨረስ ሁለት ወር ያህል ይፈጅብኛል…ለቀጣዬቹ ሁለት ወራት እንድኖር የሚያስችል ምክንያት ሰጠተኸኛል ማለት ነው..ምክንያቱም እኔ በምንም አይነት ሁኔታ እጄ ላይ ያሉ መጽሀፎቸን አንብቤ ሳልጨርስ አልሞትምና.››አሉኝ ..ምን ለማለት እንደፈለጉ አልገባኝም..ይህቺ ልጅ ግራ አጋቢ የሆነችው ከእንደዚህ አይነት ግራ አጋቢ ብኩኖች ጋር እየኖረች ነው ስል በውስጤ አሰብኩ.. ሽማግሌው ወደፌናን ዞረው ‹‹የእኔ ትንሽ መላአክ ደህና ሰንብቺልኝ..››ብለው ፊታቸውን አዙረው የመጽሀፍ መደብሩን ለቀው ወጡ
‹‹ምትገርሚ እብድ ነሽ.ለማላውቃቸው ሰው መጽሀፍ ታስገዥኛለሽ…ደግሞ ባዋርድሽስ.?››
‹‹ምን ብለህ ነው የምታዋርደኝ.?››
<<መች አልኩሽ .?››ብልሽስ
‹‹አትልማ ..ለራስህ ያለህን ግምት በደንብ አውቃለው..››
<<እንዴት ነው ምታውቂው ….?በጣም ጉረኛ ነሽ…?ዘመድሽ መስለውኝ ነው..ደግሞ ደስ የሚሉ አዛውንት ናቸው.የሚያነብ ሰው እወዳለው ለዛ ነው…›› አልኩ ቀጥሎ በመሀከላችን ለሚፈጠረው ነገር ጥሩ ስሜት እንዲፈጠር ና ንግግራችን እንዳይከር እየፈራው
‹‹ ማን መሆናቸውን ታውቃለህ?››
‹‹እኔ እንጃ .በምን አውቃለው ፡፡ካለዛሬም አይቻቸው አላውቅም..እዚህ ቦታም ስገኝ የመጀመሪያ ቀኔ ነው››
እንግዲህ እንደዛ እንድታደርግ እድሉን ስላመቻቸውልህ አመስግነኝ…ምክንያቱም ለእሷቸው መፅሀፍ መግዛት ብዙ ሰዎች ቢፈልጉም እድሉን አያገኙምና›› ብላ ማንነታቸውን ነገረቺኝ… ነዘረኝ ከሰማዩ የሚከብድ ስም ያላቸው..ለኢትዬጵያ ብዙ የሰሩ ፤ ብዙ መጽሀፍ የጻፉ ታላቅ ደራሲ ናቸው..አፍሬ አፌን ያዝኩ.ማንነታቸውን ቀድሜ ባውቅ ኖሮ መፅሀፍ ልግዛሎት ብዬ ገንዘብ ከኪሴ ለማውጣት ድፍረት ሚኖረኝ አይመስለኝም
‹‹ስማቸው እና ኪሳቸው ምነው እንዲህ ተራራቀ.››ብዬ የገረመኝን ጥያቄ ጠየቅኳት
‹‹ስማቸውን እኮ በአዕምሮቸው እንጂ በኪሳቸው አይደለም ያገኙት…እሳቸው ለቁሳዊ ሀብት ብዙም ግድ የላቸውም ..ከሚጠቀሙት በላይ ገንዘብ ኪሳቸው እዲከርም አይፈልጉም..ግን አንዳንዴ እንደዛሬ ቀን የሚፈልጉት መፃሀፍ የሚገዙበት ብር ሲጎድላቸው ይበሳጫሉ..››ብላ ልታስረዳኝ ሞከረች፡፡
‹‹ሚገርም ፅናት ነው››አልኩኝ
‹‹ አዎ ነው..አንተ ግን ምን ፈልገህ እዚህ ድረስ መጣህ .?ነው እግረመንገድህን ስታልፍ ድንገት አይተኸኝ ነው?››አለችኝ ኮስተር ብላ..ሞባይሌን ከፈትኩና ሰዓቱን አየው..አምስት ሰዓት ከሩብ ይላል
‹‹ምሳ ልጋብዝሽ ነው አመጣጤ…ምሳ ስንት ሰዓት ነው መውጣት የሚፈቀድልሽ….?››
‹‹ምሳ ምሳ...?››
‹‹አዎ ምሳ..››
ስልኳን አወጣችና ደወለች…‹‹ቶሎ ና ልወጣ ነው…››ብላ መልሳ ዘጋችው…
‹‹የሚቀበለኝ ልጅ እስኪመጣ መኪና ውስጥ ጠብቀኝ ከአስር ደቂቃ ቡኃላ መጣለው››እንዲህ በቀላሉ እሺ ትለኛች ብዬ እልጠበቅኩም ነበር…ሀሳቧን እንዳትቀይር ‹‹እሺ አመሰግናለው›› ብዬ እንደህጻን በውስጤ እየቧረቅኩ በፍጥነት ወደ መኪናዬ ተመለስኩና መሪውን ከሹፌሬ ተቀብዬ እሱ በታክሲ ወደቢሮ እንዲመለስ ልኬው እሷን መጠበቅ ጀመርኩ…ስለእሷ እያሰብኩ…ስንት ሰው እንደሆነች እያሰላው...ከሳምንት በፊት እኛ ካምፓኒ ነበር የምትሰራው…ከዛ ሹፌር ሆና ስትሰራ አገኛዋት አሁን ደግሞ የመፃሀፍት መደብር ሻጭ..ህይወቷን እንዴት እዴት ነው ጢቢ ጢቢ እየተጫወተችበት ያለው.?መስመር የሚያሲዛት ቤተሰብ የላትም ማለት ነው….?እስቲ ትምጣና ለዚህ ሁሉ ጥያቄዎቼ መልስ ትሰጠኛለች….
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍2
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሦስት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
...ሆቴል ፍለጋ ብዙም አራቅንም ..እዛው ዞር ብለን ዋቤ ሸበሌ ነበር የገባነው…እንደተቀመጥን ነው የምንበላውን በማዘዝ ወደጭቅጭቃችን የገባነው…እኔን ፍለጋ ይሄን ያህል መንገድ ይጓዛል ብዬ አልገመትኩም ነበር…እርግጥ ነገሮችን በፍጥነት እንዲህ እንዲሆኑ አድርጌ ስልኬንም፤ አድራሻዬንም አጠፋፍቼ ከመስሪያ ቤቴ የጠፋውት አውቄ ነው …ለእሱ የማሰቢያ እና የመረጋጊያ ጊዜ እንዲያገኝ በማሰብ ….እንጂማ ስራዬን እሱ ስላለ መልቀቄ አይደለም..እንደዛማ አይታሰብም…ሰው በገዛ ግዛቱ ውስጥ በታነፀ ቤተመንግስት ሊነግስበት ያሰበውን ወንበር ሌላ ተቀናቃኝ ልቀቅ ስላለው በቀላሉ ይለቃል…አይ በፍፁም ይሄ የነገስታት ባህሪ አይደለም..እሱ በንግስናው ኃይል ተማምኖ ወግጂልኝ ቢለኝ እኔ በቀላሉ ምኞቱን ላሳካለት አልችልም..ምክንያቱም እኔም ከእሱ እኩል ኃይል ያለኝ ንግስት ስለሆንኩ…
‹‹እኔን ፍለጋ እንዲህ መባከንህ አስደስቶኛል››አልኩት
‹‹ጉረኛ አትሁኚ… ስለአንቺ አንዳንድ ነገር ሳጣራ ከበፊትም ጀመሮ በካምፓኒው አንቺን በተመለከተ ያለው ነገር ትክክል ስላልመሰለኝ ያንን ለማስተካከል ነው..የአንድ አዲስ መሪ ስራ የወደፊት የካምፓኒውን አካሄድ ማስተካከል ብቻ ሳይሆን ወደኃላም ተመልሶ በባለፍት መሪዎች አላግባብ የተሰሩ ስራዎች ካሉ ለእነዛ እርማት እንዲደረግ ማሰድረግም ጭምር ነው…
‹‹ስለመሪነት ጥሩ ግንዛቤ እያገኘህ ነው››
‹‹አዎ…አስተዳደግሽ፤ የቤተሰቦችሽ ሁኔታ እና የህይወት ገጠመኞችሽ የፈጠሩብሽ ተፅዕኖ እንዳለ ሆኖ ካምፓኒያችንም ላንቺ የሰጠው ቦታ ለህይወትሽ መበላሸት አንድ አስዋፅኦ እንዳበረከተ ተሰምቶኛል..እኔም ነገሩን በደነብ ሳላጣራ በእሳቱ ላይ ቤንዚል ጨመርኩበት››አለኝ እጆቹን እያፍተለተለ…አይገርማችሁም አንዳንድ ሰው ወደ ህይታችሁ ድንገት ከመንገድ ጎራ ብሎ ይገባና ገና በሁለት እግሩ እንኳን ተስተካክሎ ሳይቆም አፍርሼ ልስራችሁ ይላል፡፡
‹‹ያው ቸኩሎ መፍረድ የአንተ ብቻ ሳይሆን…የእኛ ኢትዬጵያውያን ዋና ችግር ነው.. ለወሬ ያለን ፍቅር ለራሳችን ካለን ፍቅር በብዙ እጥፍ ይበልጣል፡፡እንደህዝብ ብቻ ሳይሆን በከፍተኛ ደረጃ ተምረዋል በሚባሉት የህብረተሰብ ደረጃ ጨምር የ<critical thinking >ልምምድ የለንም… የሆነ ውሳኔ ላይ ከመድረሳችን በፊት የሰማነውን ወሬ ‹‹ለምን?›› ‹‹እንዴት?›› ‹‹የት?›› ‹‹ መቼ?›› ብለን በመጠየቅ የነገሩን ብልት በታትነን የማየት የምናደርገው ጥረት ለዜሮ የቀረበ ነው፡፡የሰማነውን ወሬ ወይም መረጃ በዚህ መጠን መመርመር ደግሞ የመረጃዎችን ጥራት ለመጨመር..እርግጠኝነቱን አስተማማኝ ለማድረግ እና እወነተኝነቱን በአስተማማኝ መንገድ ለማረጋገጥ ወሳኝ መንገዶች ናቸው፡፡ እኛ ግን እንደዛ አናደርግም…በዛም ምክንያት ውሳኔያችን ቡዙ ግዜ የጥድፊያና በስህተት የተሞላ ነው››አልኩት… ከገባው ብዬ
‹‹አዎ ትክክል ነሽ››አለኝ ኮራና ጀነን ብሎ
‹‹አየህ አሁንም ተሳሳትክ..ትክክል መሆኔን እንዴት በዚህ ቅፅበት ልታረጋግጥ ቻልክ….?››
ግራ ገባውና ‹‹ማለቴ….››ብሎ ሊያብራራልኝ ሲሞክር መልሼ ጣልቃ ገባውና
‹‹ግዴለም ብታስረዳኝም አታሳምነኝም..ይልቅ ህይወቴ እንደተበላሸ ስትናገር ነበር…እስቲ እንዴት እንዲያ ልታስብ እንደቻልክ አስረዳኝ..….?››
‹‹ይሄ ምን ማስረዳት ያስፈልገዋል…በዛ ነጥብ ዲግሪ ተመርቀሽ በትንሽ ደሞዝ በፀሀፊነት እየሰራሽ ነው..በቀደም አያትሽ ከሚሆን ሰው ጋር አግኝቼሻለው…ዛሬ ደግሞ ተራ የሽያጭ ሰራተኛ ሆነሽ መጽሀፍ ስትቸረችሪ ነው ያገኘውሽ…ህይወትሽ እርጋታ የሌለው ምስቅልቅሉ የወጣ ነው….ከዚህ በላይ የህይወት መበለሻሸት ከየት ይመጣል››በቃ በእሱ ቤት የእኔን ህይወት ብጥርጥር አድርጎ አጥንቶ ጨርሶል..
‹‹እውነት ግን ምንድነው ….?››ጠየቅኩት
ግራ ተጋባ‹‹….ምን አልሺኝ….?››
‹‹እውነት ምንድነው..….?››ፍጥጥ ብዬ ጥያቄዬን ደገምኩለት
‹‹ምን አይነት ጥያቄ ነው….….?እውነት ሀቅ ነው…በትክክል የተተገበረ ወይም የተነገረ ክንውን ነው..በቃ ይሄው ነው፡፡››
‹‹እሱ ብቻማ አይደለም…እውነት እረቂቅ ነው..እውነት ጥልቅ ነው…የሰማህው ነገር ሁሉ እውነት ሊሆን አይችልም..ለምን ይመስልሀል እኔ እና አንተ አንድ አይነት ነገር ከአንድ ሰው በእኩል ሰዓት ብንሰማ የምንረዳበት መንገድ አንድ አይነት ሊሆን አይችልም…ምክንያም ሁለታችንም በየራሳችን አዕምሮ ተጠቅመን ነው ተርጉመን ነገሩን ለመገንዘብ የምንጥረው…..ስንተረጉም ደግሞ የበፊት የህይወት ልምዳችን..የምንከተለው የሀይማኖት አይዲኦሎጂ፤ ከተወለድንበት አካባቢ ማህበረሰብ የቀሰምነው ባህል፤ የራሳችን ፍላጎት…..እነዚህና ሌሎችም በአተረጋጎማችን ላይ የየራሳቸውን ስውር ተፅዕኖ ያሳድራብናል…… የሰማነው እውነት በግማሽ ይበረዛል ማለት ነው…ያየነውም እንደዛ..፡፡ሌላ ምሳሌ ልስጥህ የአንድ ወጣት ልጃገረድ ፎቶን ሶስት ወጣት ወንዶች ቢያዩት እና ከሳዕታት ቡኃላ ምን እንዳዩ ቢጠየቁ..አንድ የተቀሰረ አስጎሚዥ ጡቶች ያላት ወጣት ይልሀል…ሌላው የሚያምረ መቀመጫ ያላት ሞዴል መሆን የምትችል ወጣት ይልሀል…ሌላው ደግሞ የሚያምር ቁንጅና ያላት ግን ልቧ በሀዘን የተሰበረ፤የእኔ ያለችውን ነገር በመጠበቅ በናፍቆ እየተሰቃየች መሆኖን አይኖቾ ውስጥ ያጋቱት እናባዋ የሚመሰክሩ ፤ ግን ደግሞ ያልሸነፍ ባይነት እና የራስን ስሜት የመቆጣጠር ጥረት በፊቷ ላይ የሚነበብባት፤ከዕድሜዋ በላይ የምታውቅ ወጣት ነች ይላል፡፡አየህ ሶስቱንም አስተያየት ሰጪዎች አንድ አይነት ስዕል ከአንድ አይነት እርቀት ላይ አይተው የተረዱት ነገር የተለያየ ነው፡፡እውነቱ የማናኛቸው ነው…….?አየህ እውነት እንደሽንኩርት ነው ሚባለው ለዛ ነው…በላጥከው ቁጥር ሌላ አዲስ ነገር..አሁንም ስትልጠው ሌላ ሚስጥር…..አንዳንዴማ ማብቂያ ሁሉ ላይኖረው ይችላል….ጲላጦስ እኮ እኔ ማውቀው አለማወቄን ነው ያለውም አንድም ለዛ ነው….ያወቀ የመሰለው ሁሉ እሱ ገና ጀማሪ ተማሪ ነው….
‹‹ወይ አንቺ ልጅ…እያወራን የነበረውን ቁም ነገር እኮ አወሳስበሽ ድራሹን አጠፋሽው….››
‹‹አይ አሁን ያወራውት ነው ትክክለኛው ቁም ነገር….አየህ የእኔ ህይወት ብልሽትሽት ማለቱን ለመወሰን በአንድ ሰምንት ውስጥ ያየሀቸው ወይም የሰማሀቸው ቅንጭብጫቢ ታሪኮች ላንተ በቂዎች መሆናቸው አስገራሚ ነው››
‹‹እኛ ካምፓኒ በፀሀፊነት እንደምትሰሪ ማንም ተናገረው ማንም እውነት ነው…..በቢዝነስ ማነጅመንት ዲግሪ እንዳለሽም አንቺ እራስሽ አትክጂም…ሹገር ዳዲሽንም በአይኔ ነው ያየውት››
በዚህ ጊዜ ምግቡ ቀርቦልን እየበላን ነበር እያወራን ያለነው..ሁሉን ነገር ጨርሶ ሳያውቅ እንደአወቀ የሚያወራው ነገር ብሽቅ አደረገኝ ‹‹ሌላውን ተወው ….ሹገር ዳዲዬ መሆኑን በምን አረጋገጥክ…….?››
‹‹አይቼሻለው አልኩሽ እኮ..አንቺም አረጋግጠሽልኛል…››
‹‹ዋሽቼህ ቢሆንስ…….?››
‹‹በምን ምክንያት ትወሺኛለሽ ….?››
‹‹ላስቀናህ ፈልጌ››
ሳቁን ለቀቀው…
‹‹ምን ያስቅሀል….?››
‹‹ለምን ብዬ ቀናለው…አፈቅሬሽ ነበር እንዴ….?››
‹‹እኔ እንጃ… ሰው አንድ ሰውን ላይ ካለምክንያት ትኩረት ካደረገና ምክንያት እየፈለገ ጥዋትና ቀን የሚነጫነጭበት ከሆነ ያው በእኔ ግምት ፍቅር ነው ብዬ ነው የማስበው፡፡››
‹‹እንደ ህይወትሽ ለራስሽ ያለሽ ግምት የተዘበራረቀ ነው…አንዳዴ መሬት የሚወረድ ሌላ ጊዜ ደግሞ ሰማይ ላይ ልንጠልጠል የሚል…›› አለኝ …በመበሳጨትና ስሜቱን ለመቆጣጠር በሚጥር የስሜት መደበላለቅ
‹‹እሺ ተሳስቼ ይሆናል..ለምን
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሦስት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
...ሆቴል ፍለጋ ብዙም አራቅንም ..እዛው ዞር ብለን ዋቤ ሸበሌ ነበር የገባነው…እንደተቀመጥን ነው የምንበላውን በማዘዝ ወደጭቅጭቃችን የገባነው…እኔን ፍለጋ ይሄን ያህል መንገድ ይጓዛል ብዬ አልገመትኩም ነበር…እርግጥ ነገሮችን በፍጥነት እንዲህ እንዲሆኑ አድርጌ ስልኬንም፤ አድራሻዬንም አጠፋፍቼ ከመስሪያ ቤቴ የጠፋውት አውቄ ነው …ለእሱ የማሰቢያ እና የመረጋጊያ ጊዜ እንዲያገኝ በማሰብ ….እንጂማ ስራዬን እሱ ስላለ መልቀቄ አይደለም..እንደዛማ አይታሰብም…ሰው በገዛ ግዛቱ ውስጥ በታነፀ ቤተመንግስት ሊነግስበት ያሰበውን ወንበር ሌላ ተቀናቃኝ ልቀቅ ስላለው በቀላሉ ይለቃል…አይ በፍፁም ይሄ የነገስታት ባህሪ አይደለም..እሱ በንግስናው ኃይል ተማምኖ ወግጂልኝ ቢለኝ እኔ በቀላሉ ምኞቱን ላሳካለት አልችልም..ምክንያቱም እኔም ከእሱ እኩል ኃይል ያለኝ ንግስት ስለሆንኩ…
‹‹እኔን ፍለጋ እንዲህ መባከንህ አስደስቶኛል››አልኩት
‹‹ጉረኛ አትሁኚ… ስለአንቺ አንዳንድ ነገር ሳጣራ ከበፊትም ጀመሮ በካምፓኒው አንቺን በተመለከተ ያለው ነገር ትክክል ስላልመሰለኝ ያንን ለማስተካከል ነው..የአንድ አዲስ መሪ ስራ የወደፊት የካምፓኒውን አካሄድ ማስተካከል ብቻ ሳይሆን ወደኃላም ተመልሶ በባለፍት መሪዎች አላግባብ የተሰሩ ስራዎች ካሉ ለእነዛ እርማት እንዲደረግ ማሰድረግም ጭምር ነው…
‹‹ስለመሪነት ጥሩ ግንዛቤ እያገኘህ ነው››
‹‹አዎ…አስተዳደግሽ፤ የቤተሰቦችሽ ሁኔታ እና የህይወት ገጠመኞችሽ የፈጠሩብሽ ተፅዕኖ እንዳለ ሆኖ ካምፓኒያችንም ላንቺ የሰጠው ቦታ ለህይወትሽ መበላሸት አንድ አስዋፅኦ እንዳበረከተ ተሰምቶኛል..እኔም ነገሩን በደነብ ሳላጣራ በእሳቱ ላይ ቤንዚል ጨመርኩበት››አለኝ እጆቹን እያፍተለተለ…አይገርማችሁም አንዳንድ ሰው ወደ ህይታችሁ ድንገት ከመንገድ ጎራ ብሎ ይገባና ገና በሁለት እግሩ እንኳን ተስተካክሎ ሳይቆም አፍርሼ ልስራችሁ ይላል፡፡
‹‹ያው ቸኩሎ መፍረድ የአንተ ብቻ ሳይሆን…የእኛ ኢትዬጵያውያን ዋና ችግር ነው.. ለወሬ ያለን ፍቅር ለራሳችን ካለን ፍቅር በብዙ እጥፍ ይበልጣል፡፡እንደህዝብ ብቻ ሳይሆን በከፍተኛ ደረጃ ተምረዋል በሚባሉት የህብረተሰብ ደረጃ ጨምር የ<critical thinking >ልምምድ የለንም… የሆነ ውሳኔ ላይ ከመድረሳችን በፊት የሰማነውን ወሬ ‹‹ለምን?›› ‹‹እንዴት?›› ‹‹የት?›› ‹‹ መቼ?›› ብለን በመጠየቅ የነገሩን ብልት በታትነን የማየት የምናደርገው ጥረት ለዜሮ የቀረበ ነው፡፡የሰማነውን ወሬ ወይም መረጃ በዚህ መጠን መመርመር ደግሞ የመረጃዎችን ጥራት ለመጨመር..እርግጠኝነቱን አስተማማኝ ለማድረግ እና እወነተኝነቱን በአስተማማኝ መንገድ ለማረጋገጥ ወሳኝ መንገዶች ናቸው፡፡ እኛ ግን እንደዛ አናደርግም…በዛም ምክንያት ውሳኔያችን ቡዙ ግዜ የጥድፊያና በስህተት የተሞላ ነው››አልኩት… ከገባው ብዬ
‹‹አዎ ትክክል ነሽ››አለኝ ኮራና ጀነን ብሎ
‹‹አየህ አሁንም ተሳሳትክ..ትክክል መሆኔን እንዴት በዚህ ቅፅበት ልታረጋግጥ ቻልክ….?››
ግራ ገባውና ‹‹ማለቴ….››ብሎ ሊያብራራልኝ ሲሞክር መልሼ ጣልቃ ገባውና
‹‹ግዴለም ብታስረዳኝም አታሳምነኝም..ይልቅ ህይወቴ እንደተበላሸ ስትናገር ነበር…እስቲ እንዴት እንዲያ ልታስብ እንደቻልክ አስረዳኝ..….?››
‹‹ይሄ ምን ማስረዳት ያስፈልገዋል…በዛ ነጥብ ዲግሪ ተመርቀሽ በትንሽ ደሞዝ በፀሀፊነት እየሰራሽ ነው..በቀደም አያትሽ ከሚሆን ሰው ጋር አግኝቼሻለው…ዛሬ ደግሞ ተራ የሽያጭ ሰራተኛ ሆነሽ መጽሀፍ ስትቸረችሪ ነው ያገኘውሽ…ህይወትሽ እርጋታ የሌለው ምስቅልቅሉ የወጣ ነው….ከዚህ በላይ የህይወት መበለሻሸት ከየት ይመጣል››በቃ በእሱ ቤት የእኔን ህይወት ብጥርጥር አድርጎ አጥንቶ ጨርሶል..
‹‹እውነት ግን ምንድነው ….?››ጠየቅኩት
ግራ ተጋባ‹‹….ምን አልሺኝ….?››
‹‹እውነት ምንድነው..….?››ፍጥጥ ብዬ ጥያቄዬን ደገምኩለት
‹‹ምን አይነት ጥያቄ ነው….….?እውነት ሀቅ ነው…በትክክል የተተገበረ ወይም የተነገረ ክንውን ነው..በቃ ይሄው ነው፡፡››
‹‹እሱ ብቻማ አይደለም…እውነት እረቂቅ ነው..እውነት ጥልቅ ነው…የሰማህው ነገር ሁሉ እውነት ሊሆን አይችልም..ለምን ይመስልሀል እኔ እና አንተ አንድ አይነት ነገር ከአንድ ሰው በእኩል ሰዓት ብንሰማ የምንረዳበት መንገድ አንድ አይነት ሊሆን አይችልም…ምክንያም ሁለታችንም በየራሳችን አዕምሮ ተጠቅመን ነው ተርጉመን ነገሩን ለመገንዘብ የምንጥረው…..ስንተረጉም ደግሞ የበፊት የህይወት ልምዳችን..የምንከተለው የሀይማኖት አይዲኦሎጂ፤ ከተወለድንበት አካባቢ ማህበረሰብ የቀሰምነው ባህል፤ የራሳችን ፍላጎት…..እነዚህና ሌሎችም በአተረጋጎማችን ላይ የየራሳቸውን ስውር ተፅዕኖ ያሳድራብናል…… የሰማነው እውነት በግማሽ ይበረዛል ማለት ነው…ያየነውም እንደዛ..፡፡ሌላ ምሳሌ ልስጥህ የአንድ ወጣት ልጃገረድ ፎቶን ሶስት ወጣት ወንዶች ቢያዩት እና ከሳዕታት ቡኃላ ምን እንዳዩ ቢጠየቁ..አንድ የተቀሰረ አስጎሚዥ ጡቶች ያላት ወጣት ይልሀል…ሌላው የሚያምረ መቀመጫ ያላት ሞዴል መሆን የምትችል ወጣት ይልሀል…ሌላው ደግሞ የሚያምር ቁንጅና ያላት ግን ልቧ በሀዘን የተሰበረ፤የእኔ ያለችውን ነገር በመጠበቅ በናፍቆ እየተሰቃየች መሆኖን አይኖቾ ውስጥ ያጋቱት እናባዋ የሚመሰክሩ ፤ ግን ደግሞ ያልሸነፍ ባይነት እና የራስን ስሜት የመቆጣጠር ጥረት በፊቷ ላይ የሚነበብባት፤ከዕድሜዋ በላይ የምታውቅ ወጣት ነች ይላል፡፡አየህ ሶስቱንም አስተያየት ሰጪዎች አንድ አይነት ስዕል ከአንድ አይነት እርቀት ላይ አይተው የተረዱት ነገር የተለያየ ነው፡፡እውነቱ የማናኛቸው ነው…….?አየህ እውነት እንደሽንኩርት ነው ሚባለው ለዛ ነው…በላጥከው ቁጥር ሌላ አዲስ ነገር..አሁንም ስትልጠው ሌላ ሚስጥር…..አንዳንዴማ ማብቂያ ሁሉ ላይኖረው ይችላል….ጲላጦስ እኮ እኔ ማውቀው አለማወቄን ነው ያለውም አንድም ለዛ ነው….ያወቀ የመሰለው ሁሉ እሱ ገና ጀማሪ ተማሪ ነው….
‹‹ወይ አንቺ ልጅ…እያወራን የነበረውን ቁም ነገር እኮ አወሳስበሽ ድራሹን አጠፋሽው….››
‹‹አይ አሁን ያወራውት ነው ትክክለኛው ቁም ነገር….አየህ የእኔ ህይወት ብልሽትሽት ማለቱን ለመወሰን በአንድ ሰምንት ውስጥ ያየሀቸው ወይም የሰማሀቸው ቅንጭብጫቢ ታሪኮች ላንተ በቂዎች መሆናቸው አስገራሚ ነው››
‹‹እኛ ካምፓኒ በፀሀፊነት እንደምትሰሪ ማንም ተናገረው ማንም እውነት ነው…..በቢዝነስ ማነጅመንት ዲግሪ እንዳለሽም አንቺ እራስሽ አትክጂም…ሹገር ዳዲሽንም በአይኔ ነው ያየውት››
በዚህ ጊዜ ምግቡ ቀርቦልን እየበላን ነበር እያወራን ያለነው..ሁሉን ነገር ጨርሶ ሳያውቅ እንደአወቀ የሚያወራው ነገር ብሽቅ አደረገኝ ‹‹ሌላውን ተወው ….ሹገር ዳዲዬ መሆኑን በምን አረጋገጥክ…….?››
‹‹አይቼሻለው አልኩሽ እኮ..አንቺም አረጋግጠሽልኛል…››
‹‹ዋሽቼህ ቢሆንስ…….?››
‹‹በምን ምክንያት ትወሺኛለሽ ….?››
‹‹ላስቀናህ ፈልጌ››
ሳቁን ለቀቀው…
‹‹ምን ያስቅሀል….?››
‹‹ለምን ብዬ ቀናለው…አፈቅሬሽ ነበር እንዴ….?››
‹‹እኔ እንጃ… ሰው አንድ ሰውን ላይ ካለምክንያት ትኩረት ካደረገና ምክንያት እየፈለገ ጥዋትና ቀን የሚነጫነጭበት ከሆነ ያው በእኔ ግምት ፍቅር ነው ብዬ ነው የማስበው፡፡››
‹‹እንደ ህይወትሽ ለራስሽ ያለሽ ግምት የተዘበራረቀ ነው…አንዳዴ መሬት የሚወረድ ሌላ ጊዜ ደግሞ ሰማይ ላይ ልንጠልጠል የሚል…›› አለኝ …በመበሳጨትና ስሜቱን ለመቆጣጠር በሚጥር የስሜት መደበላለቅ
‹‹እሺ ተሳስቼ ይሆናል..ለምን
👍1
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
‹‹ሁለተኛው ቢሮ በሰራተኛ አስተዳደር አንድ ኤክስፐርት ለመቅጠር ይፈልጋሉ…እዛ ቦታ እንድታመለክቺ ልመክርሽ ነው…››
‹‹እንዴ!!! በስነምግባር ጉድላት ከስራው የተባረረ ሰው እኮ መልሶ መዋዳደር እንደማይችል ይታወቃል..ለዛውም ከበፊቱ ከፋ ባለ የስራ መደብ….?››
‹‹ግድ የለሽም በማነጅመንት እናየዋለን…ያ ውሰኔ የእኔ የግሌ ነበር..እንደውም ባንቺ መባረር ማናጅመንቱ ብዙም ምቾት አልተሰማቸውም..ስለዚህ አንቺን ለመመለስ ብዙም አያንገራንግሩም..››
‹‹አንተስ.?››አልኩት በብልጣ ብልጥነቱ ተደምሜ..
‹‹እኔ ድምፀ-ተአቅቦ አደርጋለው….በእነሱ ድምጽ መልሰሽ በሚገባሽ ቦታ ትቀጠሪያለሽ..ህይወትሽ ይስተካከላል….ግን ቅድመ ሁኔታ አለው››
‹‹ምን ?የፍቅር ጥያቄ እንዳይሆን››
‹‹ቢሆንስ?››አለኝ ፊቱን ጨምድዶ
‹‹አይ እንቢ ስለማልልህ ይቅርብህ ልልህ ነው››
በግርምት አፍጥጦ ለደቂቃዎች አየኝና ‹‹እያስፈራራሺኝ ነው…….?››
ማስፈራራት አይደለም.. ለእኔ ፍቅር ማለት መላላስ እና መወሳሰብ አይደለም…ሁሌ አድቬንቸር ነው…ሁሌ ሚተረመመስ ነገር ፈልጋለው…››
‹‹ግን .ጤነኛ አዕምሮ ነው ያለሽ...?እንዴት ሰው የሚተረማመስ ነገር ያስደስተዋል.?››
‹‹አየህ የተረማመሰውን ነገር በጥበብ ሳስተካክል የሚሰማኝ የአሸናፊነት እና የውጤታማነት ደስታ ነው የፍቅር እርካታዬ…ሁል ጊዜ በፍቅር ውስጥ ጌም እንዲኖር እፈልጋለው…ላሸንፍም ልሸነፍም እችላለው..ዋናው ሁል ጊዜ ምጫወተውን ማጣት የለብኝም …ጥሩ ቁማርተኛ ካልሆንክ ከአኔ ጋር በፍቅር መዝለቅ አትችልም እና ይቅርብህ ብዬ ልመክርህ ነው፡፡››
‹‹ምን ጉድ ነሽ በፈጣሪ…እኔ ቅድመ ሁኔታ ያልኩት አንድ ከዛ ከሹገር ዳዲሽ ጋር ያለሽን ፍቅርም ሆነ የስራ ግንኙነት ታቆሚያለሽ ልልሽ ነው..ሌላው እዚህ መፃሀፍት መደብርም ያለሽን ስራ እንደዛው….
‹‹ያስቃል..››አልኩት..እውነትም ገርሞኝ
‹‹ምኑ ገረመሽ?››
‹‹በዚህ ምድር ላይ ሶስት አይነት ሰዎች አሉ .. givers , takers , matcher ይባላሉ፡፡ < givers > ምንም ነገር ሲሰጡህ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ነው…ሲያፈቅሩህ የእነሱን ማፍቀር ብቻ እንጂ የእነሱን መፈቀር አለመፈቅር አያስጨንቃቸውም..ሲለግሱህም ከአንተ በመልሱ ምንም የሚጠብቁት ነገር የለም…እንደዚህ አይነት ሰዎች የአለም በጣም ደሀ ሰዎች ሊሆኑ ይችላሉ ግን ሰማያዊ ስብዕና ያላቸው ናቸው… በተቃራኒውም የአለም በጣም ሀብታሞቹና ባለትልቅ ገቢ ባለቢቶችም እንዚሁ < givers > የሚባሉ ሰዎች ናቸው..ምክንያቱም ለአበባ ያደረጉት በእጥፍ ከሰለሞን ይደረግላቸዋል…ይሄ የተፈጥሮ ህግ ነዋ፡፡‹‹ለማታውቀው ወገንህ አንድ ስትሰጥ ከማታቀው ዘጠኝ ተጭምሮ አስር ሆኖ ይመለሰልሀል…›› የሚለው ዋና መመሪያቸው ነው..እነእየሱስ ፤ ነብዩ ሙሀመድ፤እነማዘር ትሬዛ..እነአበበች ጎበና እነሲስተር ዘቢደር፤ማህተመጋንዲ፤ማንዴላ ወዘተ …እነዚህ ዝም ብለው በነፃ ሲሰጡ በመኖራቸው ሀብታምነትን ብቻ ሳይሆን በታሪክ ማህደር ዘላለማዊነትንም የተጎናፀፈ ናቸው….
ሌላው‹‹ takers› የሚባሉት ናቸው …ከሌላው መቀበልን ብቻ ነው ዓላማ አድርገው የሚንቀሳቀሱት..ሁሌ ማትረፍን ብቻ ነው የሚያስቡት…ለእነሱ ዋናው ውጤት ነው …ምን ያህል አተርፋለው እንጂ በእኔ ማትረፍ ውስጥ እነማን ይጎዳሉ… ?የማን ቤት ይፈርሳል..?የማን ነፍስ ይነጠቃል ?አያስጨንቃቸውም..፡፡የአለም ሙሰኞች፤ ኮንትሮባንዲስቶች፤ቅጥረኛ ነፍስ ገዳዬች… ሀሺሽ ነጋዴዎች እዚህ ግሩፕ ውስጥ ይጠቃለላሉ..
ሶስተኛዎቹ ‹matcher› የሚባሉት ናቸው፡፡በሰጡት ልክ መቀበልን ይፈልጋሉ….ሁል ጊዜ በህይወት ሚዛን እየጠበቁ መጓዝ ዓላማቸው ነው…ዲፕሎማቶች ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ናቸው…‹በሰጥቶ መቀበል መርህ› የሚጓዙ ናቸው… በዚህ ህግ ስትሰጥ በተሻለ መጠን እንደምትቀበል እርግጠኛ መሆን አለብህ››.እከክልኝ ልከክልህ…መመሪያቸው ነው፡፡
‹‹እና እኔ ከሶስቱ የትኛው ነኝ.?››አለኝ
‹‹እራስህን ፈልገዋ….አሁን ይብቃን እንሂድ….››
‹‹ስላልኩሽ ነገር እኮ ምንም አላልሺኝም...?››
‹‹እየሄድን መኪና ውስጥ ነገርሀለው….››
‹‹እሺ ››ብሎ ሂሳብ ሊከፍል አስተናጋጁን ደረሰኝ ሲጠይቀው..እንደተከፈለ ነገረው…
‹‹ማን ነው የከፈለው...?››አይን አይኔን እያየ ባለማመን ጠየቀኝ..የእኔም ጥያቄ ስለነበረ ልመልስለት አልቻልኩም
‹‹እዛ ጥግ ተቀምጦ የነበረው ሰውዬ ጥቁር ሱፍ ለብሶ የነበረው ..›› አስተናጋጁ አብራራልን
‹‹ማነው አውቀሺዋል….?››
‹‹አዎ፡፡ ተነስ እንሄድ በቃ…የእኔ ሰው ነው››አልኩት…
የአይኖቹ ቀለማት ሲቀየሩ ታወቀኝ
‹‹ምንድነው እንዲህ አይነት ነገር… ሰው በሰው ነገር እንዲህ ጥልቅ ሲል ሲያበሳጨኝ ..ከፈለገ ሌላ ቀን አይጋብዝሽም.?…››ይሄንን እጃችንን ታጥበን ከሆቴሉ እየወጣን በነበረበት ጊዜ ነው የሚነጫነጭብኝ..
‹‹ ምንድነው የደበረህ ….?ይክፈል…እንደውም ጥሩ ነው››
‹‹ለምን ይከፍላል .?አሁን አራት መቶ የማትሞላ ብር ከፈለ አልከፈለ ለእኔ ምኑ ነው ጥሩ…ጉረኛ በይው…››
ሁሉን ነገር ከማሸነፍና ከመሸነፍ ጋር የሚያገናኝ ምን አይነት ሰው ነው… .?አሁን አበሳጨኝ ‹‹እውነትህን ነው….እንደውም ብሩን ስጠኝ ልመልስለት…››አልኩት
ፈገግ አለ..‹‹የት ታገኚዋለሽ ወጥቷል እኮ››
‹‹አይ ያ ፊት ለፊት ያለው ብቲክ የእሱ ነው.. ስጠኝና አፍንጫው ላይ ወርውሬለት ልምጣ..ነገ ይሄንን እንደውለታ ቆጥሮ ሊለፋደድብኝ ይችላል››
ጥርስ በጥርስ ሆነ‹‹ ..በደስታ ብሩን አውጥቶ ሰጠኝ..‹‹ጠብቀኝ ››አልኩና አስፓልት ጠርዝ ላይ አቁሜው በዝብራ ተሸገርኩና ሁለት ልጆች ታቅፋ ለምትለምን ለማኝ እጆ ላይ አስጨበጥኮት ሴትዬዋ መብረቅ እንደመታት አይነት በድንጋጤ ፈዛ ለመጮህም ዳድቶት ስትርበተበት ፊቴን አዞርኩና መልሼ አስፓልቱን ተሸግሬ ወደእሱ ስሄድ እያጨበጨበ ጠበቀኝ …ሁኔታው የብሽቀት ነው…‹‹ጀግና ነሽ… ሸወድሽኝ ማለት ነው››አለኝ ለንቦጩን ጥሎ
‹‹አይ አልሸወድኩህም..አሁን ጋብዘኸኛል ማለት ነው….ስለዚህ ዘና ማለት ትችላለህ›› አልኩት
‹‹ግን ታውቂያለሽ አይደል …በጣም እብድ ልጅ ነሽ…የምትገርሚ እብድ…ነይ በይ ላድርስሽ..››
‹‹አይ.. አንተ በዚሁ ሄድ እኔ በዚች ጋ አቋራጬ መንገድ አለች …በዛ ሄዳለው.››
‹‹አረ ችግር የለም አደርስሻለው..››
‹‹ለራሴው ነው..በዚህ አቋራጭ አምስት ደቂቃ ነው የሚፈጅብኝ..አንተ ግን ገና መብራት ጠብቀህ አደባባይ ዞረህ 30 ደቂቃም አይበቃ..››
‹‹ይሁን ግን መልሱን አልነገርሺኝም እኮ...?››
‹‹እ እረሳውት ነገ 12 ሰዓት አይደል መነሻው ..እመጣለው..አንተም ባትለኝ ያ ፕሮግራም እንዲያመልጠኝ አልፈልግም››
‹‹ጥሩ ነው ስራውን ደግሞ ካዛ ስንመለስ ሰኞ ታመለክቺያለሽ..››
‹‹አይ አላመለክትም ቅዳሜ ወይም እሁድ እዛ ዝግጅቱ ላይ ሁሉም ሰራተኞች ባሉበት እኔን በተመለከተ በተሳሳተ መረጃ በማባረርህ ስህተት መስራትህን ተናግረህ ይቅርታ ትጠይቀኛለህ..ከዛ ሞራሌን በመንካትህ ለመካስ ይሄ ያልከኸውን አዲስ ቦታ በእድገት እንደሰጠኸኝ ለሁሉም ታበስራለህ….አንተ ራስህ እንደዛ ታደርጋለህ…እንደዛ ሲሆን ነው ሁሉ ነገር ተፈታ የሚባለው ከዛ እንዳልከው ስለሹገር ዳዲዬ እና ሰለ መፃሀፍ መደብሩ እናወራለን በል ቻው ››እልኩና ምንም እንዲናገር ዕድሉን ሳልሰጠው ፈዞ በደነዘዘበት ጥዬው ሄድኩ
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
‹‹ሁለተኛው ቢሮ በሰራተኛ አስተዳደር አንድ ኤክስፐርት ለመቅጠር ይፈልጋሉ…እዛ ቦታ እንድታመለክቺ ልመክርሽ ነው…››
‹‹እንዴ!!! በስነምግባር ጉድላት ከስራው የተባረረ ሰው እኮ መልሶ መዋዳደር እንደማይችል ይታወቃል..ለዛውም ከበፊቱ ከፋ ባለ የስራ መደብ….?››
‹‹ግድ የለሽም በማነጅመንት እናየዋለን…ያ ውሰኔ የእኔ የግሌ ነበር..እንደውም ባንቺ መባረር ማናጅመንቱ ብዙም ምቾት አልተሰማቸውም..ስለዚህ አንቺን ለመመለስ ብዙም አያንገራንግሩም..››
‹‹አንተስ.?››አልኩት በብልጣ ብልጥነቱ ተደምሜ..
‹‹እኔ ድምፀ-ተአቅቦ አደርጋለው….በእነሱ ድምጽ መልሰሽ በሚገባሽ ቦታ ትቀጠሪያለሽ..ህይወትሽ ይስተካከላል….ግን ቅድመ ሁኔታ አለው››
‹‹ምን ?የፍቅር ጥያቄ እንዳይሆን››
‹‹ቢሆንስ?››አለኝ ፊቱን ጨምድዶ
‹‹አይ እንቢ ስለማልልህ ይቅርብህ ልልህ ነው››
በግርምት አፍጥጦ ለደቂቃዎች አየኝና ‹‹እያስፈራራሺኝ ነው…….?››
ማስፈራራት አይደለም.. ለእኔ ፍቅር ማለት መላላስ እና መወሳሰብ አይደለም…ሁሌ አድቬንቸር ነው…ሁሌ ሚተረመመስ ነገር ፈልጋለው…››
‹‹ግን .ጤነኛ አዕምሮ ነው ያለሽ...?እንዴት ሰው የሚተረማመስ ነገር ያስደስተዋል.?››
‹‹አየህ የተረማመሰውን ነገር በጥበብ ሳስተካክል የሚሰማኝ የአሸናፊነት እና የውጤታማነት ደስታ ነው የፍቅር እርካታዬ…ሁል ጊዜ በፍቅር ውስጥ ጌም እንዲኖር እፈልጋለው…ላሸንፍም ልሸነፍም እችላለው..ዋናው ሁል ጊዜ ምጫወተውን ማጣት የለብኝም …ጥሩ ቁማርተኛ ካልሆንክ ከአኔ ጋር በፍቅር መዝለቅ አትችልም እና ይቅርብህ ብዬ ልመክርህ ነው፡፡››
‹‹ምን ጉድ ነሽ በፈጣሪ…እኔ ቅድመ ሁኔታ ያልኩት አንድ ከዛ ከሹገር ዳዲሽ ጋር ያለሽን ፍቅርም ሆነ የስራ ግንኙነት ታቆሚያለሽ ልልሽ ነው..ሌላው እዚህ መፃሀፍት መደብርም ያለሽን ስራ እንደዛው….
‹‹ያስቃል..››አልኩት..እውነትም ገርሞኝ
‹‹ምኑ ገረመሽ?››
‹‹በዚህ ምድር ላይ ሶስት አይነት ሰዎች አሉ .. givers , takers , matcher ይባላሉ፡፡ < givers > ምንም ነገር ሲሰጡህ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ነው…ሲያፈቅሩህ የእነሱን ማፍቀር ብቻ እንጂ የእነሱን መፈቀር አለመፈቅር አያስጨንቃቸውም..ሲለግሱህም ከአንተ በመልሱ ምንም የሚጠብቁት ነገር የለም…እንደዚህ አይነት ሰዎች የአለም በጣም ደሀ ሰዎች ሊሆኑ ይችላሉ ግን ሰማያዊ ስብዕና ያላቸው ናቸው… በተቃራኒውም የአለም በጣም ሀብታሞቹና ባለትልቅ ገቢ ባለቢቶችም እንዚሁ < givers > የሚባሉ ሰዎች ናቸው..ምክንያቱም ለአበባ ያደረጉት በእጥፍ ከሰለሞን ይደረግላቸዋል…ይሄ የተፈጥሮ ህግ ነዋ፡፡‹‹ለማታውቀው ወገንህ አንድ ስትሰጥ ከማታቀው ዘጠኝ ተጭምሮ አስር ሆኖ ይመለሰልሀል…›› የሚለው ዋና መመሪያቸው ነው..እነእየሱስ ፤ ነብዩ ሙሀመድ፤እነማዘር ትሬዛ..እነአበበች ጎበና እነሲስተር ዘቢደር፤ማህተመጋንዲ፤ማንዴላ ወዘተ …እነዚህ ዝም ብለው በነፃ ሲሰጡ በመኖራቸው ሀብታምነትን ብቻ ሳይሆን በታሪክ ማህደር ዘላለማዊነትንም የተጎናፀፈ ናቸው….
ሌላው‹‹ takers› የሚባሉት ናቸው …ከሌላው መቀበልን ብቻ ነው ዓላማ አድርገው የሚንቀሳቀሱት..ሁሌ ማትረፍን ብቻ ነው የሚያስቡት…ለእነሱ ዋናው ውጤት ነው …ምን ያህል አተርፋለው እንጂ በእኔ ማትረፍ ውስጥ እነማን ይጎዳሉ… ?የማን ቤት ይፈርሳል..?የማን ነፍስ ይነጠቃል ?አያስጨንቃቸውም..፡፡የአለም ሙሰኞች፤ ኮንትሮባንዲስቶች፤ቅጥረኛ ነፍስ ገዳዬች… ሀሺሽ ነጋዴዎች እዚህ ግሩፕ ውስጥ ይጠቃለላሉ..
ሶስተኛዎቹ ‹matcher› የሚባሉት ናቸው፡፡በሰጡት ልክ መቀበልን ይፈልጋሉ….ሁል ጊዜ በህይወት ሚዛን እየጠበቁ መጓዝ ዓላማቸው ነው…ዲፕሎማቶች ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ናቸው…‹በሰጥቶ መቀበል መርህ› የሚጓዙ ናቸው… በዚህ ህግ ስትሰጥ በተሻለ መጠን እንደምትቀበል እርግጠኛ መሆን አለብህ››.እከክልኝ ልከክልህ…መመሪያቸው ነው፡፡
‹‹እና እኔ ከሶስቱ የትኛው ነኝ.?››አለኝ
‹‹እራስህን ፈልገዋ….አሁን ይብቃን እንሂድ….››
‹‹ስላልኩሽ ነገር እኮ ምንም አላልሺኝም...?››
‹‹እየሄድን መኪና ውስጥ ነገርሀለው….››
‹‹እሺ ››ብሎ ሂሳብ ሊከፍል አስተናጋጁን ደረሰኝ ሲጠይቀው..እንደተከፈለ ነገረው…
‹‹ማን ነው የከፈለው...?››አይን አይኔን እያየ ባለማመን ጠየቀኝ..የእኔም ጥያቄ ስለነበረ ልመልስለት አልቻልኩም
‹‹እዛ ጥግ ተቀምጦ የነበረው ሰውዬ ጥቁር ሱፍ ለብሶ የነበረው ..›› አስተናጋጁ አብራራልን
‹‹ማነው አውቀሺዋል….?››
‹‹አዎ፡፡ ተነስ እንሄድ በቃ…የእኔ ሰው ነው››አልኩት…
የአይኖቹ ቀለማት ሲቀየሩ ታወቀኝ
‹‹ምንድነው እንዲህ አይነት ነገር… ሰው በሰው ነገር እንዲህ ጥልቅ ሲል ሲያበሳጨኝ ..ከፈለገ ሌላ ቀን አይጋብዝሽም.?…››ይሄንን እጃችንን ታጥበን ከሆቴሉ እየወጣን በነበረበት ጊዜ ነው የሚነጫነጭብኝ..
‹‹ ምንድነው የደበረህ ….?ይክፈል…እንደውም ጥሩ ነው››
‹‹ለምን ይከፍላል .?አሁን አራት መቶ የማትሞላ ብር ከፈለ አልከፈለ ለእኔ ምኑ ነው ጥሩ…ጉረኛ በይው…››
ሁሉን ነገር ከማሸነፍና ከመሸነፍ ጋር የሚያገናኝ ምን አይነት ሰው ነው… .?አሁን አበሳጨኝ ‹‹እውነትህን ነው….እንደውም ብሩን ስጠኝ ልመልስለት…››አልኩት
ፈገግ አለ..‹‹የት ታገኚዋለሽ ወጥቷል እኮ››
‹‹አይ ያ ፊት ለፊት ያለው ብቲክ የእሱ ነው.. ስጠኝና አፍንጫው ላይ ወርውሬለት ልምጣ..ነገ ይሄንን እንደውለታ ቆጥሮ ሊለፋደድብኝ ይችላል››
ጥርስ በጥርስ ሆነ‹‹ ..በደስታ ብሩን አውጥቶ ሰጠኝ..‹‹ጠብቀኝ ››አልኩና አስፓልት ጠርዝ ላይ አቁሜው በዝብራ ተሸገርኩና ሁለት ልጆች ታቅፋ ለምትለምን ለማኝ እጆ ላይ አስጨበጥኮት ሴትዬዋ መብረቅ እንደመታት አይነት በድንጋጤ ፈዛ ለመጮህም ዳድቶት ስትርበተበት ፊቴን አዞርኩና መልሼ አስፓልቱን ተሸግሬ ወደእሱ ስሄድ እያጨበጨበ ጠበቀኝ …ሁኔታው የብሽቀት ነው…‹‹ጀግና ነሽ… ሸወድሽኝ ማለት ነው››አለኝ ለንቦጩን ጥሎ
‹‹አይ አልሸወድኩህም..አሁን ጋብዘኸኛል ማለት ነው….ስለዚህ ዘና ማለት ትችላለህ›› አልኩት
‹‹ግን ታውቂያለሽ አይደል …በጣም እብድ ልጅ ነሽ…የምትገርሚ እብድ…ነይ በይ ላድርስሽ..››
‹‹አይ.. አንተ በዚሁ ሄድ እኔ በዚች ጋ አቋራጬ መንገድ አለች …በዛ ሄዳለው.››
‹‹አረ ችግር የለም አደርስሻለው..››
‹‹ለራሴው ነው..በዚህ አቋራጭ አምስት ደቂቃ ነው የሚፈጅብኝ..አንተ ግን ገና መብራት ጠብቀህ አደባባይ ዞረህ 30 ደቂቃም አይበቃ..››
‹‹ይሁን ግን መልሱን አልነገርሺኝም እኮ...?››
‹‹እ እረሳውት ነገ 12 ሰዓት አይደል መነሻው ..እመጣለው..አንተም ባትለኝ ያ ፕሮግራም እንዲያመልጠኝ አልፈልግም››
‹‹ጥሩ ነው ስራውን ደግሞ ካዛ ስንመለስ ሰኞ ታመለክቺያለሽ..››
‹‹አይ አላመለክትም ቅዳሜ ወይም እሁድ እዛ ዝግጅቱ ላይ ሁሉም ሰራተኞች ባሉበት እኔን በተመለከተ በተሳሳተ መረጃ በማባረርህ ስህተት መስራትህን ተናግረህ ይቅርታ ትጠይቀኛለህ..ከዛ ሞራሌን በመንካትህ ለመካስ ይሄ ያልከኸውን አዲስ ቦታ በእድገት እንደሰጠኸኝ ለሁሉም ታበስራለህ….አንተ ራስህ እንደዛ ታደርጋለህ…እንደዛ ሲሆን ነው ሁሉ ነገር ተፈታ የሚባለው ከዛ እንዳልከው ስለሹገር ዳዲዬ እና ሰለ መፃሀፍ መደብሩ እናወራለን በል ቻው ››እልኩና ምንም እንዲናገር ዕድሉን ሳልሰጠው ፈዞ በደነዘዘበት ጥዬው ሄድኩ
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍2
.:
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
እንዲህማ የእሷ መቀለጃ አልሆንም….እንዴ!!! ከሚገባት በላይ እኮ ፊት ሰጠዋት..አረ ፊት መስጠትም ብቻ አይደለም..ልቤንም ገልብጬ ነው የውስጥ ገበሩን ያሳየዋት….ካልጠፋ ሰው እሷን ምሳ ለመጋበዝ ጊዜዬን ማባከኔ ነው የሚቆጨኝ… መኪናዬን አስነስቼ ወደ ቢሮ እየተጎዝኩ ነው ፡፡ምን ማድረግ እንዳለብኝ እያሰብኩ ያለውት..አሁን በቃ ይህቺን ልጅ እበቀላታለው…፡፡እንዲህ ፊጥ እንዳለችብኝ ልኳን እንድታውቅ እና ጥሩ ትምህርት እንድታገኝ አደርጋለው…፡፡አዎ የእሷን አንገት ለማስደፋት ያስችለኝ ዘንድ ዘዴዬን መቀየር አለብኝ…፡፡አዎ ምርጥ ሀሳብ መጣልኝ… ስልኬን አወጣውና ደወልኩ፡፡ ለሳምንት ስልኳን ማንሳት አሻፈረኝ ብዬ ሳበሳጫት ወደከረምኳት ፍቅረኛዬ ጋር……..
‹‹አንተ በህይወት አለህ……..?ይደብርሀል ብዬ ነው እንጂ ግራ ከመጋባቴ የተነሳ ቢሮ ሁሉ ልመጣ አስቤ ነበር…ምነው ይሄን ያለህ……..?.››ተንጣጣችብኝ
‹‹ ሳሮን…ትንሽ ስልክ የማነሳበት ሁኔታ ላይ አልነበርኩ››
‹‹እንዴ ቢያንስ ሚሴጄን አትመልስም…..?››
‹‹ይቅርታ አጥፍቼያለው..››
‹‹እንዲህ ይቅርታ በማለት ብቻማ አንላቀቅም…..››
‹‹እኮ ልክስሽ ነው…ነገ እና ተነገ ወዲያ ካምፓኒያችን የዓመታዊ በዓሉን በቢሾፍቱ ያከብራል…››
‹‹እና …..?››
‹‹እና እኔ ያው ሀለቃ እንደመሆኔ መጠን ከፍቅረኛዬ ጋር እንድገኝ እድሉ ተሰጥቶኛል..››
‹‹ከፍቅረኛህ ነው ወይስ ከባለቤትህ…..?››
‹‹ያው ሁለቱንም ቢሉ አንቺው ነሽ ሌላ ማን አለ…..?››
‹‹አስደሰትከኝ….እና ምን አድርጊ እያልከኝ ነው…..?››
‹‹እናማ ተዘጋጂ ..ነገ 1 ሰኣት መኪናዬ በራፍሽ ላይ ቆማ ትጠብቅሻለች …››
‹‹እውነትህን ነው…..?››
‹‹እውነቴን ነው..ደግሞ አሁን ትንሽ ብር በባንክ አስገባልሻለው ፤የመጨረሻ የምትይውን መዘነጥ ዘንጠሸ እንድትመጪ ነው የምፈልገው… ካልሆነ ብዙ ቆንጆዎች ሳላሉ ትነጠቂያለሽ…››
‹‹አረ እኔ ልጅት……በመዘነጥ ማን ጫፌ ደርሶ…›
ለነገሩ ጨቅጫቃ ባትሆኚ በመልክና በመዘነጥ እንኳን ማንም ስርሽ አይደርስም…በተለይ በመዘነጥ›› በውስጤ ነው ያጉረመረምኩት …ስልኩን ከመዝጋቴ በፊት ግን..ትራፊክ ያዘኝ…ስልኩን ዘግቼ አንሸራትቼ ብለቀውም ትራፊኩ አልተሸወደልኝም..ምን ነካኝ አንዲህ አይነት ቀሺም ባህሪ እኮ አልነበረኝም….
ጥዋት ሳሮን ጋር ስደርስ አንድ ሰዓት ከሩብ ነበር፡፡እውነትም በዝነጣ ማን ጫፍሽ ይደርሳል….…..?ነው ያልኩት ገና እንዳየዋት …ዓይኖች ሁሉ ዛሬ የእኔዋ ንግስት ላይ ሲንከባለሉ መዋላቸው ነው…..በተለይ ያቺ ትዕቢተኛ …እሷ እንደሆነ ለጥሩ ምላስ እንጂ ለጥሩ አለባበስ ደንታ የላትም…. በደስታ እየተፍለቀለቅኩ እሷን ይዥ ቢሮ ስደርስ አንድ ሰዓት ተኩል ሆኖ ነበር፡፡
እሷን እዛው መኪና ውስጥ እንድትጠብቀኝ አድርጌ ወረድኩና ወደቢሮ ግቢ ሄድኩ ….. አንድ ባስና፤ አንድ ሚኒባስ ቆሟል …ሰው ይተራማመሳል…አቶ ሰይፉ እንዳዩኝ በደስታ እየተፍለቀለቁ ወደእኔ መጡ..‹‹እንዴት ናችሁ… ሰው ሁሉ መጣ …..?›ለሰላምታ የዘረጉልኝን እጃቸውን እየጨበጥኩ ጠየቅኳቸው…
‹‹የመጡ ይመስለኛል …….አሁን ወደ መኪና እየገቡ ነው ..ለማጣራት እንዲመቸን መኪና ውስጥ ከገቡ ቡኃላ ይሻላል..ሁሉም መጥተው ከሆነ ….ከአስር ደቂቃ ቡኃላ እንነሳለን……..››
…በአምስት ደቂቃ ውስጥ ሁሉም ወደየመኪኖቹ ገብተው ቦታ ቦታ እንዲይዙ ተደረገ ..የእኔ አይን አንድ ሰው እየፈለገ ነው…. እስከአሁን አላየዋትም…ቆይ ወደባስ ውስጥ ገብታ ይሆናል …ብዬ ባስ ውስጥ ገባውና ሰራተኞችን ሰላምታ ለመስጠት በሚመስል ሁኔታ ፊት ለፊት ቆሜ እጄን ለሰላምታ እያውለበለብኩ አይኖቼን ከጥግ እስከጥግ አንከባለልኩ…. ባሱ ባዶ ነው..ማለቴ እሱማ ሙሉ ነው እሷ የለችም እንጂ …‹‹መልካም ጉዞ ››ብዬ ከባሱ ወረድኩና ወደ ሚኒባሶ ሄድኩ…ገብቼ ተመለከትኩ .. እዛም የለችም…
አቶ ሰይፉን አስጠራዋቸው…እያለከለኩ መጡ
‹‹እሺ ጨረሳችሁ…..?››
‹‹አዎ ሁሉም ተሞልተው መጥተዋል..ልንቀሳቀስ ነው››
‹‹እርግጠኛ ናችሁ…››
‹‹አዎ መዝገቡን ዘርገግተው በየስሙ ፊት ለፊት ረይት የተደረገበትን እያሰዩኝ… እይ አመስት ሰዎች ናቸው የቀሩት እነሱ ደግሞ በተለያየ ምክንያ መሄድ እንደማይችሉ ቀድመው አሳውቀዋል…››
ዙሪያ ጥምዝ መሄድን አቁሜ ‹‹ፊናንስ››
‹‹ፊናን እ..ረስቼት ነበር››
‹‹እንዴት ይረሷታል…..?››አልኳቸው …እስቲ ምን ማለቴ ነው…..?፡፡እሷ የእኔ ችግር እንጂ የእሳቸው ችግር አይደለችም፡፡
‹‹አይ ያው ስራ ለቃለች ብዬ ነዋ…. ትናንት ግን ደውዬላት ልመጣ እችላለው ብላኝ ነበር… ቆይ እስኪ ልደውልላት ›› አሉና ስልካቸውን አውጥተው ደወልሉላት…..ስልኳ አይሰራም
‹‹ታዲያ ምን ይሻላል…..?››ጠየቅኳቸው…ልክ ዝግጅቱ ሰርግ ሆኖ እሷ ደግሞ የሰርጉ ሙሽራ ሆና እንደዘገየች ነገር አንገቴን በሀዘን ሰብሬ
‹‹ረፍዶባትም ከሆነ በትራንስፖር መምጣት ትችላለች ..ስልኳን ስትከፍት እንድታየው መልዕክት ልክላታለው››ብለውኝ ወደስራቸው ሄዱ…
‹‹እኔም እያግረመረምኩ በራፉ አካባቢ በጥበቃ ስራ ላይ ወደነበረው ዘበኛ ሄድኩና የምፈልገውን ነገር ነገርኩት ..ከዛ ወደመኪናዬ አመራው፡፡እንደደረስኩ ‹‹ፍቅር ውጪ››አልኳት
‹‹ምነው..አንሄድም እንዴ…..?››
‹‹አይ ምን አንቀዠቀዠን…እነሱ ይቅደሙን… ቁርስ በልተን ቀስ ብለን እንከተላቸዋለን..››ብዬ ፊት ለፊት መንገድ ተሸግሮ ወደሚገኝ ካፌ ይዤት ገባውና ለእይታ የሚመች ቦታ መርጠን ተቀመጥን….ባሱም ሆነ ሚኒባሱ ተከታትለው ሲወጡና ሲሄዱ እያየው ነው…ቁርሱን አዘን ቢመጣም ለአመል ያህል ከመነካካት ውጭ የመብላት ፍላጎት አልነበረኝም …አይኔ ቢሮችን በራፍ አካባቢ እደተሰካ ነው…..አሁን ፌናንን እየጠበቅኩ ነው ብላችሁ መቼም አትታዘቡኝም….ምን አልባት አርፍዳ ብትመጣ ወደዝግጅቱ ቦታ የምትመጣበት መኪና አጥታ እንዳትቀር ስለሰጋው….ካልመጣች እኮ እቅዴ ሁሉ በዜሮ ተባዛ ማለት ነው፡፡ ዘበኛው በነገርኩት መሰረት ከወዲህ ወዲያ እየተንጎራደደ እየጠበቃት ነው..እንደመጣች እንዲደውልልኝ ተነጋግረናል.. ቢሆንም በእሱ ላይ ብቻ እምነቴን ጥዬ ቁጭ ማለት እቻልኩም…አይኖቼ እዛው እንደተሰኩ ናቸው…
‹‹ከደቂቃዎች በፊት ፍልቅልቅ ነበርክ አሁን ደግሞ… ››አለቺኝ ሳሮን
‹‹አሁን ምን ሆንኩ…..?››
‹‹እኔ እንጃ…. ገባያ የሄደች እናቱን የሚጠብቅ ህጻን ልጅ ነው የምትመስለው..››
‹‹ትንሽ የፕሮግራሙ ቅንጅት ጥሩ ስላልመሰለኝ ነው እንጂ የምትይውን ያህል ምንም አልሆንኩም...››
‹‹ታዲዬ ምን አስጨነቀህ…..? ››
‹‹እንዴ ምን ለማለት ፈልገሽ ነው……..?አሁን ምኔ ነው የተበሳጨ የሚመስለው…››ሰዓቴን ተመለከትኩ ሁለት ከሩብ ሆኖል …አንድ ሰዓት ድረሺ የተባለች ሴት ሁለት ከሩብ ድረስ ዘግይታ ትመጣለች ብሎ ማሰብ የዋህነት መሆኑ ስለገባኝ
‹‹በይ ከጨረሽ ተነሺ እንሂድ ››አልኳት
‹‹እሺ ››አለችና ተነሳች….ተያይዘን ካፌውን ለቀቅንና ቢሮ በራፍ ላይ ወደ ቆመችው መኪናችን አመራን….. ልክ እንደደረስን ዘበኛው እየተንቀዠቀዥ ወደ እኔ ሮጦ መጣና ‹‹ጌታዬ አልመጣችም››አለኝ ….‹‹እሺ›› አልኩትና ተጨማሪ ነገር እንዳይናገር ፊትን ከስክሼበት ፈጠን ብዬ መኪና ውስጥ ገባው እና እሷም እስክትገባ ጠብቄ መኪናውን አስነሳውት …ወደቢሾፍቱ ጉዞ ጀመርን….
‹‹ማነች…..?››አመዴን ቡን አደረገችው ..
‹‹ምኗ…..?››
‹‹ስትጠብቃት የነበረችው ሴት…አሁን ዘበኛው እንዳልመጣች የነገረህ ልጅ››አቤት የሴት ደመ ነፍስ
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
እንዲህማ የእሷ መቀለጃ አልሆንም….እንዴ!!! ከሚገባት በላይ እኮ ፊት ሰጠዋት..አረ ፊት መስጠትም ብቻ አይደለም..ልቤንም ገልብጬ ነው የውስጥ ገበሩን ያሳየዋት….ካልጠፋ ሰው እሷን ምሳ ለመጋበዝ ጊዜዬን ማባከኔ ነው የሚቆጨኝ… መኪናዬን አስነስቼ ወደ ቢሮ እየተጎዝኩ ነው ፡፡ምን ማድረግ እንዳለብኝ እያሰብኩ ያለውት..አሁን በቃ ይህቺን ልጅ እበቀላታለው…፡፡እንዲህ ፊጥ እንዳለችብኝ ልኳን እንድታውቅ እና ጥሩ ትምህርት እንድታገኝ አደርጋለው…፡፡አዎ የእሷን አንገት ለማስደፋት ያስችለኝ ዘንድ ዘዴዬን መቀየር አለብኝ…፡፡አዎ ምርጥ ሀሳብ መጣልኝ… ስልኬን አወጣውና ደወልኩ፡፡ ለሳምንት ስልኳን ማንሳት አሻፈረኝ ብዬ ሳበሳጫት ወደከረምኳት ፍቅረኛዬ ጋር……..
‹‹አንተ በህይወት አለህ……..?ይደብርሀል ብዬ ነው እንጂ ግራ ከመጋባቴ የተነሳ ቢሮ ሁሉ ልመጣ አስቤ ነበር…ምነው ይሄን ያለህ……..?.››ተንጣጣችብኝ
‹‹ ሳሮን…ትንሽ ስልክ የማነሳበት ሁኔታ ላይ አልነበርኩ››
‹‹እንዴ ቢያንስ ሚሴጄን አትመልስም…..?››
‹‹ይቅርታ አጥፍቼያለው..››
‹‹እንዲህ ይቅርታ በማለት ብቻማ አንላቀቅም…..››
‹‹እኮ ልክስሽ ነው…ነገ እና ተነገ ወዲያ ካምፓኒያችን የዓመታዊ በዓሉን በቢሾፍቱ ያከብራል…››
‹‹እና …..?››
‹‹እና እኔ ያው ሀለቃ እንደመሆኔ መጠን ከፍቅረኛዬ ጋር እንድገኝ እድሉ ተሰጥቶኛል..››
‹‹ከፍቅረኛህ ነው ወይስ ከባለቤትህ…..?››
‹‹ያው ሁለቱንም ቢሉ አንቺው ነሽ ሌላ ማን አለ…..?››
‹‹አስደሰትከኝ….እና ምን አድርጊ እያልከኝ ነው…..?››
‹‹እናማ ተዘጋጂ ..ነገ 1 ሰኣት መኪናዬ በራፍሽ ላይ ቆማ ትጠብቅሻለች …››
‹‹እውነትህን ነው…..?››
‹‹እውነቴን ነው..ደግሞ አሁን ትንሽ ብር በባንክ አስገባልሻለው ፤የመጨረሻ የምትይውን መዘነጥ ዘንጠሸ እንድትመጪ ነው የምፈልገው… ካልሆነ ብዙ ቆንጆዎች ሳላሉ ትነጠቂያለሽ…››
‹‹አረ እኔ ልጅት……በመዘነጥ ማን ጫፌ ደርሶ…›
ለነገሩ ጨቅጫቃ ባትሆኚ በመልክና በመዘነጥ እንኳን ማንም ስርሽ አይደርስም…በተለይ በመዘነጥ›› በውስጤ ነው ያጉረመረምኩት …ስልኩን ከመዝጋቴ በፊት ግን..ትራፊክ ያዘኝ…ስልኩን ዘግቼ አንሸራትቼ ብለቀውም ትራፊኩ አልተሸወደልኝም..ምን ነካኝ አንዲህ አይነት ቀሺም ባህሪ እኮ አልነበረኝም….
ጥዋት ሳሮን ጋር ስደርስ አንድ ሰዓት ከሩብ ነበር፡፡እውነትም በዝነጣ ማን ጫፍሽ ይደርሳል….…..?ነው ያልኩት ገና እንዳየዋት …ዓይኖች ሁሉ ዛሬ የእኔዋ ንግስት ላይ ሲንከባለሉ መዋላቸው ነው…..በተለይ ያቺ ትዕቢተኛ …እሷ እንደሆነ ለጥሩ ምላስ እንጂ ለጥሩ አለባበስ ደንታ የላትም…. በደስታ እየተፍለቀለቅኩ እሷን ይዥ ቢሮ ስደርስ አንድ ሰዓት ተኩል ሆኖ ነበር፡፡
እሷን እዛው መኪና ውስጥ እንድትጠብቀኝ አድርጌ ወረድኩና ወደቢሮ ግቢ ሄድኩ ….. አንድ ባስና፤ አንድ ሚኒባስ ቆሟል …ሰው ይተራማመሳል…አቶ ሰይፉ እንዳዩኝ በደስታ እየተፍለቀለቁ ወደእኔ መጡ..‹‹እንዴት ናችሁ… ሰው ሁሉ መጣ …..?›ለሰላምታ የዘረጉልኝን እጃቸውን እየጨበጥኩ ጠየቅኳቸው…
‹‹የመጡ ይመስለኛል …….አሁን ወደ መኪና እየገቡ ነው ..ለማጣራት እንዲመቸን መኪና ውስጥ ከገቡ ቡኃላ ይሻላል..ሁሉም መጥተው ከሆነ ….ከአስር ደቂቃ ቡኃላ እንነሳለን……..››
…በአምስት ደቂቃ ውስጥ ሁሉም ወደየመኪኖቹ ገብተው ቦታ ቦታ እንዲይዙ ተደረገ ..የእኔ አይን አንድ ሰው እየፈለገ ነው…. እስከአሁን አላየዋትም…ቆይ ወደባስ ውስጥ ገብታ ይሆናል …ብዬ ባስ ውስጥ ገባውና ሰራተኞችን ሰላምታ ለመስጠት በሚመስል ሁኔታ ፊት ለፊት ቆሜ እጄን ለሰላምታ እያውለበለብኩ አይኖቼን ከጥግ እስከጥግ አንከባለልኩ…. ባሱ ባዶ ነው..ማለቴ እሱማ ሙሉ ነው እሷ የለችም እንጂ …‹‹መልካም ጉዞ ››ብዬ ከባሱ ወረድኩና ወደ ሚኒባሶ ሄድኩ…ገብቼ ተመለከትኩ .. እዛም የለችም…
አቶ ሰይፉን አስጠራዋቸው…እያለከለኩ መጡ
‹‹እሺ ጨረሳችሁ…..?››
‹‹አዎ ሁሉም ተሞልተው መጥተዋል..ልንቀሳቀስ ነው››
‹‹እርግጠኛ ናችሁ…››
‹‹አዎ መዝገቡን ዘርገግተው በየስሙ ፊት ለፊት ረይት የተደረገበትን እያሰዩኝ… እይ አመስት ሰዎች ናቸው የቀሩት እነሱ ደግሞ በተለያየ ምክንያ መሄድ እንደማይችሉ ቀድመው አሳውቀዋል…››
ዙሪያ ጥምዝ መሄድን አቁሜ ‹‹ፊናንስ››
‹‹ፊናን እ..ረስቼት ነበር››
‹‹እንዴት ይረሷታል…..?››አልኳቸው …እስቲ ምን ማለቴ ነው…..?፡፡እሷ የእኔ ችግር እንጂ የእሳቸው ችግር አይደለችም፡፡
‹‹አይ ያው ስራ ለቃለች ብዬ ነዋ…. ትናንት ግን ደውዬላት ልመጣ እችላለው ብላኝ ነበር… ቆይ እስኪ ልደውልላት ›› አሉና ስልካቸውን አውጥተው ደወልሉላት…..ስልኳ አይሰራም
‹‹ታዲያ ምን ይሻላል…..?››ጠየቅኳቸው…ልክ ዝግጅቱ ሰርግ ሆኖ እሷ ደግሞ የሰርጉ ሙሽራ ሆና እንደዘገየች ነገር አንገቴን በሀዘን ሰብሬ
‹‹ረፍዶባትም ከሆነ በትራንስፖር መምጣት ትችላለች ..ስልኳን ስትከፍት እንድታየው መልዕክት ልክላታለው››ብለውኝ ወደስራቸው ሄዱ…
‹‹እኔም እያግረመረምኩ በራፉ አካባቢ በጥበቃ ስራ ላይ ወደነበረው ዘበኛ ሄድኩና የምፈልገውን ነገር ነገርኩት ..ከዛ ወደመኪናዬ አመራው፡፡እንደደረስኩ ‹‹ፍቅር ውጪ››አልኳት
‹‹ምነው..አንሄድም እንዴ…..?››
‹‹አይ ምን አንቀዠቀዠን…እነሱ ይቅደሙን… ቁርስ በልተን ቀስ ብለን እንከተላቸዋለን..››ብዬ ፊት ለፊት መንገድ ተሸግሮ ወደሚገኝ ካፌ ይዤት ገባውና ለእይታ የሚመች ቦታ መርጠን ተቀመጥን….ባሱም ሆነ ሚኒባሱ ተከታትለው ሲወጡና ሲሄዱ እያየው ነው…ቁርሱን አዘን ቢመጣም ለአመል ያህል ከመነካካት ውጭ የመብላት ፍላጎት አልነበረኝም …አይኔ ቢሮችን በራፍ አካባቢ እደተሰካ ነው…..አሁን ፌናንን እየጠበቅኩ ነው ብላችሁ መቼም አትታዘቡኝም….ምን አልባት አርፍዳ ብትመጣ ወደዝግጅቱ ቦታ የምትመጣበት መኪና አጥታ እንዳትቀር ስለሰጋው….ካልመጣች እኮ እቅዴ ሁሉ በዜሮ ተባዛ ማለት ነው፡፡ ዘበኛው በነገርኩት መሰረት ከወዲህ ወዲያ እየተንጎራደደ እየጠበቃት ነው..እንደመጣች እንዲደውልልኝ ተነጋግረናል.. ቢሆንም በእሱ ላይ ብቻ እምነቴን ጥዬ ቁጭ ማለት እቻልኩም…አይኖቼ እዛው እንደተሰኩ ናቸው…
‹‹ከደቂቃዎች በፊት ፍልቅልቅ ነበርክ አሁን ደግሞ… ››አለቺኝ ሳሮን
‹‹አሁን ምን ሆንኩ…..?››
‹‹እኔ እንጃ…. ገባያ የሄደች እናቱን የሚጠብቅ ህጻን ልጅ ነው የምትመስለው..››
‹‹ትንሽ የፕሮግራሙ ቅንጅት ጥሩ ስላልመሰለኝ ነው እንጂ የምትይውን ያህል ምንም አልሆንኩም...››
‹‹ታዲዬ ምን አስጨነቀህ…..? ››
‹‹እንዴ ምን ለማለት ፈልገሽ ነው……..?አሁን ምኔ ነው የተበሳጨ የሚመስለው…››ሰዓቴን ተመለከትኩ ሁለት ከሩብ ሆኖል …አንድ ሰዓት ድረሺ የተባለች ሴት ሁለት ከሩብ ድረስ ዘግይታ ትመጣለች ብሎ ማሰብ የዋህነት መሆኑ ስለገባኝ
‹‹በይ ከጨረሽ ተነሺ እንሂድ ››አልኳት
‹‹እሺ ››አለችና ተነሳች….ተያይዘን ካፌውን ለቀቅንና ቢሮ በራፍ ላይ ወደ ቆመችው መኪናችን አመራን….. ልክ እንደደረስን ዘበኛው እየተንቀዠቀዥ ወደ እኔ ሮጦ መጣና ‹‹ጌታዬ አልመጣችም››አለኝ ….‹‹እሺ›› አልኩትና ተጨማሪ ነገር እንዳይናገር ፊትን ከስክሼበት ፈጠን ብዬ መኪና ውስጥ ገባው እና እሷም እስክትገባ ጠብቄ መኪናውን አስነሳውት …ወደቢሾፍቱ ጉዞ ጀመርን….
‹‹ማነች…..?››አመዴን ቡን አደረገችው ..
‹‹ምኗ…..?››
‹‹ስትጠብቃት የነበረችው ሴት…አሁን ዘበኛው እንዳልመጣች የነገረህ ልጅ››አቤት የሴት ደመ ነፍስ
👍2
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስድስት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
...ወደ ደብረዘይት በራሴ መኪና ለመሄድ የወሰንኩት ከነጋ ቡኃላ ነው፡፡አባቴ ሀሳቤን ተቃውሞኝ ነበር…
‹‹ህብረት የመፍጠሪያ እና ወዳጅነትን ለማጎልበት ታስቦ በተዘጋጀ ዝግጅት ላይ ለብቻ ተገንጥሎ መሄድ ጥሩ ስሜት አይፈጥርም ››አለኝ.
‹‹እንዴ ምን ችግር አለው..?››
‹‹ችግርማ አለው… አንዳንዴ ማድረግ ስላቻልሽ ብቻ ሁሉን ነገር የግድ ማድረግ አይኖርብሽም…አንቺ በግል መኪናሽ ስትሄጅ ሌሎች የስራ ባለደረቦችሽ ላይ ምን አይነት ስሜት ነው ሊፈጥር የሚችለው….በተለይ እኔ እና አንቺ ለእንዲህ አይነት ጉራ ስንል ያለንን ነገር መጠቀም አያምርብንም››አለኝ
‹‹እንዴት አባ..? ለምን …...?ማን ይከለክለናል..?››ጥያቄዬን ደረደርኩለት
‹‹የእኛ አይደለማ ..ሰርተን የገዛነው መኪና አይደለም..የእናትሽ ላብ ነው››
‹‹እንዴ…. !!!እናቴ ታዲያ የእኔ አይደለች..?››
‹‹…እናትሽ ያንቺ ነች ማለት ንብረቷ ሁሉ ያንቺ ነው ማለት አይደለም…››
‹‹አባ አንተ ደግሞ..ደግነቱ እናቴ እንደአንተ አታስብም…›› ሀሳቡ ውስጤ ገብቶ ቢቧጥጠኝም ምክሩን ሰምቼ ግን መኪናውን ጥዬ ለመሄድ አልፈለኩም…..መኪና መያዜ ከሰውዬው ጋር ላለኝ ወሳኝ ፊልሚያ ያግዘኛል የሚል ግምት አሳድሮብኛል፡፡እና ቀድሜ ደብረዘይት በመድረስ የተቀበልኳቸው እኔ ነኝ፡፡ቡድኑ ያረፈው ቢን ኢንተርናሺናል ሆቴል ነው፡፡ለአለቅዬ ብቻ ሆቴሉ አይመጥነውም ተብሎ አሻም አፍሪካ ሆቴል ነው የተያዘለት…ሰው ሁሉ እንደ አመዳደቡ ሁለት ሁለት እየሆነ በየክፍሉ እየገባ ባለበት ሰዓት እኔ ሆቴሉ በረንዳ ላይ አረፍ ብዬ ማኪያቶ ነገር በመጠጣት ላይ ሳለው አቶ ሰይፉ ወደእኔ መጡ…..
‹‹ፌናን ላስቸግርሽ ነው..?››
‹‹ምነው ምን ቸገሮት..?››
‹‹ባክሽ ሰውዬችን መኪናዬ ተበላሽታብኝ አጉል ቦታ ቆሚያለው ብሎ ደወለልኝ ..…ሚኒባሶ መካኒክ ፍልጋ እስክትሄድ እዛ እንዳይቸገር ባንቺ መኪና ሄደሽ ብታመጪው…..መኪናውን ልጆቹ አሰርተው ያመጡለታል››
‹‹ችግር የለውም እርሶ አዘውኝ እንዴት እምቢ እላለው ››ብዬ ከመቀመጫዬ ተነሳውና መኪናዬን ወደአቆምኩበት ሄድኩ….አጋጣሚው ደስ ብሎኛል…ገቢና ከጎኔ አስቀምጬ እየነቆርኩት ይዤው መጣለው…ሀሳቤ እንደዛ ነበር..
ስደርስ ያላሰብኩት ነገር ነው የገጠመኝ… ከሰው ጋር ነው…ደስ አላለኝም..ለምን ደስ አላለኝም…..?አይ እንዲሁ ይመስለኛል..በቃ አለ አይደለ ብቻውን ነው ብዬ ሰለገመትኩ መደናገር ተፈጥሮብኝም ይሆናል…፡፡
መኪናዬ አቁሜ ወደ እነሱ እየሄድኩ ነው ያሰብኩት…ከእነሚስቱማ አልጭነውም….ይዣቸው ከመሄዴ ለመገላገል የመኪናዋን ብልሽት ቀላል ከሆነ እስኪ ልየው…እድሜ ለአባቴ የመኪና የአካል ክፍል ብትንትን አድርጌ እንዳውቅ አድረርጎኛል…ጫን ያለ ብልሽት ካልሆነ በስተቀር የእኔንም ሆነ የአባዬን መኪና ቱታዬን ለብሼ መሬት ላይ እየተንከባለልኩና በዘይት እየተጨመላለቅኩ የምጠግነው እና ሰርቢስ የማደርገው እራሴው ነኝ….
እሱ ባለበት አቅጣጫ ወደመስኮቱ ተጠጋው..እኔን በማየቱ እጅግ ደንግጦል…እንደህጻን ልጅ ነው የተረብተበተው..እንደዛ ሲርበተበት ደግሞ እኔ ውስጤ እንዲቁነጠነጥና ..መቁነጥነጤን ተከትሎ እንድሾርበት አስገደደኝ..፡፡ያው እንደከዚህ ቀደሙ.. ከዛም ትንሽ ከፍ ባለ ደረጃ ተሸቀርቅሯል…፡፡መቼስ የካምፓኒ ማናጀር ለመሆን ከመዳከር ይልቅ ፕሮፌሽናል ሞዴል ለመሆን ትንሽ ቢጥር አመት ሳይሞላ የሀገሪቱ አይኖች ሁሉ ማረፊያ ይሆን ነበር….፡፡እሷም ቆንጅዬ ነች …አዘናነጧ ግን ጭንቀት የወለደው አይነት ይመስላል…እሱን ላለማሳጣት እየጣረች በሚመስል ሁኔታ....፡፡ግን ምን ማለቴ ነው....?እየተናገርኩ ያለውት እኮ ትርጉም የሚሰጥ አይነት አይደለም..፡፡ጭንቀት ያለበት አዘናነጥ ማለት ምን ማለት ነው…..?እንደውም እኔ ስለእሷ የሰጠውት አስተያየት ይመስለኛል ከጭንቀት የተወለደው…፡፡ለማንኛውም የመኪናውን ኮፈን አስከፍቼ ስመረምረው ብልሽቱ አስቂኝ ነበር…ለማስተካከል ግማሽ ደቂቃ አልፈጀብኝም…እንደዛ በመሆኑ ደግሞ የተሰማኝ ስሜት ልነግራችሁ አልችልም…
…. አሁን ከኃላ እየተከተልኳቸው ነው…..በእስፖኪዬ ወደኃላ እያየኝ መሆኑን በደንብ አውቃለው…ከተማ ውስጥ ገብተን ጌትሼት ጋር ስደርስ ነበር ሚኒባሶ መካኒክ ይዛ ስትመጣ አግኝተን የመለስነው…..
የመጀመሪያው ፕሮግራም ከምሳ ግብዣ ነበር የሚጀምረው...እዛው ብዙሀኑ ያረፈበት ሆቴል እየተጫወትን ከበላን ቡኃላ በወጣው ፕሮግራም መሰረት በከተማዋ መታየት ያለባቸውን ቦታዎች ወደማየት ነው ያመራነው …ስምንት ሰዓት ሲሆን ተንቀሳቀስን፡፡
መቼስ ቢሾፍቱን ስትጎበኝ በዋናነት በሁሉም አዕምሮ ሚመጣው ሀይቆቾ ናቸው..ቢሾፍቱ ፤ሆራ ፤ባቦጋያ ፤ኩሪፍቱ፤ጨለቅለቃ.. መቼስ መታደል ነው…አንድ መለስተኛ ከተማ ይሄ ሁሉ ሀይቆች ባለቤት መሆን በራሱ ትልቅ ድልብ ሀብት ነው፡፡ለከተማዋ ብቻ አይደለም ለሀገሪቱም ጭምር..፡፡በዛ ለይ ከመዲናዋ 50 ኪሎ ሜትር ብቻ እርቃ መገኘቷ….ለአንድ ቀን እንኳን ለስራ ወደሀገሪቱ የመጣ ሰው ጎራ ብሎ አንድ ሁለት ሰዓት ዘና ብሎ ሊመለስባት በሚችልበት ቦታ ላይ መገኘቷ ሌላ እድል ነው…ግን ከተማዋም ሆነች ሀገሪቱ 5 ፐርሰንቱን እንኳን አልተጠቀመችበትም…አለም አቀፍ ቱሪስቶችን በልዩ ሁኔታ እንዲስብ ተደርጎ ፕሮሞሽን አልተሰራለትም… ፡፡ሌሎች ሀገሮች መሰል የተፈጥሮ ፀጋ ባለመታደላቸው አርቴፊሻል ወንዝ እና ሀይቅ በመስራት የቱሪስት ገቢያቸውን በሚያጧጡፈበት በዚህ ቴክኖሎጂ በመጠቀበት ዘመን እኛ ግን ተፈጥሮ በቸርነቷ የለገሰችንን የነፃ ችሮታ እንዲሁ ባልባሌ ሁኔታ ለዘመናት በማባከነ ስንዴ እንለምናለን…ያሳዝናል፤የእኔ ነገር ሳላስበው ወደንጭንጬ ገባው…ለዛውም በዚህ ዘና በማያ ቀኔ… ..ቅድሚያ ሆራ ሀይቅ ነው የሄድነው…ሆራ በከተማዋ ካሉት ሀይቆች በስፋት ትልቁ ነው..ዙሪያውን በተራራ የተከበበ ሲሆን ተራራው ላይ ደግሞ ዘመናዊ የሚባሉ ሎጆችና ሆቴሎች አልፎ አልፎም ቢሆንም ታንፀው ወደአካባቢው ለመዛናናት የሚመጡትን ቱሪስቶች ሆነ ሀገርኛ ቱሪስቶችን ለማስተናገድ እየሞከሩ ነው ፡፡አሪፍ ጊዜ ነበር ያሳለፍነው ..አብዛኛው በጀልባ ባህሩን ሰንጥቆ በመጓዝ ተዝናንቷል....12 ሰዓት ወደየአረፍንበት ሆቴል ነው የተመለስነው..ለማታ እራት ፕሮግራም ለመዘጋጀት….የእራቱ ፕሮግራም ፕራሚድ ሆቴል ነው የሚከናወነው፡፡አንድ ሰዓት ሁሉም እዛ ተሰባስቦ መገኘት አለበት፡፡
አንድ ሰዓት ከሩብ ሲል ፕራሚድ በሚገኝ የስብሰባ አዳራሽ ሁሉም ስታፎቻችን ቦታቸውን ይዘው ለፕሮግራሙ ዝግጁ ሆነው ነበር…ልክ እንደባለፈው አመት ዘንድሮም የፕሮግራሙ መሪ እኔ ስለሆንኩ ወደ መድረኩ ወጥቼ ሁሉንም አንዴ ቃኘው…የካምፓኒው ከፍተኛ ሀላፊዎች አለቃዬንና ሚስቱን በግራና ቀኝ አጅበው የፊተኛውን ረድፋ ላይ ተደርደረረዋል፡፡
ጉሮሮዬን አፀዳዳውና ማይኩን ፈታትሼ ንግግሬን ጀመርኩ…
‹‹››የተከበሩ የድርጅታችን ስራ አስኪያጅ ፤ እኛን አክብረው በመሀከላችን የተገኙት የዕለቱ የክብር እንግዳ የተከበሩት የስራ-አስኪያጃችን እጮኛ….የተከበራችሁ የስራ መሪዎችና ድንቅና ምርጥ የካማፓኒያችን ሰራተኞች እንኳን ለዚህ አመት የካማፓኒያችን ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ …አደረሰን፡፡…››
አደራሹ በጭብጨባ ተናጋ…
ፋታ ወስጄ ንግግሬን ቀጠልኩ፡፡
…የዚህ ዓመት በዓላችን ከዚህ በፊቱ የተለየ ይሆናል ፡፡አንደኛ በዓላችን ነው..ሁለተኛ ወጣቱንና እና ካምፓኒያችንንም ሆነ የእያንዳንዱን ሰራተኛ የግል ህይወት ላይ ተጨባጭ ለውጥ እንዲመጣ ያደርጋሉ ብለን ሁለችንም ተስፋ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስድስት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
...ወደ ደብረዘይት በራሴ መኪና ለመሄድ የወሰንኩት ከነጋ ቡኃላ ነው፡፡አባቴ ሀሳቤን ተቃውሞኝ ነበር…
‹‹ህብረት የመፍጠሪያ እና ወዳጅነትን ለማጎልበት ታስቦ በተዘጋጀ ዝግጅት ላይ ለብቻ ተገንጥሎ መሄድ ጥሩ ስሜት አይፈጥርም ››አለኝ.
‹‹እንዴ ምን ችግር አለው..?››
‹‹ችግርማ አለው… አንዳንዴ ማድረግ ስላቻልሽ ብቻ ሁሉን ነገር የግድ ማድረግ አይኖርብሽም…አንቺ በግል መኪናሽ ስትሄጅ ሌሎች የስራ ባለደረቦችሽ ላይ ምን አይነት ስሜት ነው ሊፈጥር የሚችለው….በተለይ እኔ እና አንቺ ለእንዲህ አይነት ጉራ ስንል ያለንን ነገር መጠቀም አያምርብንም››አለኝ
‹‹እንዴት አባ..? ለምን …...?ማን ይከለክለናል..?››ጥያቄዬን ደረደርኩለት
‹‹የእኛ አይደለማ ..ሰርተን የገዛነው መኪና አይደለም..የእናትሽ ላብ ነው››
‹‹እንዴ…. !!!እናቴ ታዲያ የእኔ አይደለች..?››
‹‹…እናትሽ ያንቺ ነች ማለት ንብረቷ ሁሉ ያንቺ ነው ማለት አይደለም…››
‹‹አባ አንተ ደግሞ..ደግነቱ እናቴ እንደአንተ አታስብም…›› ሀሳቡ ውስጤ ገብቶ ቢቧጥጠኝም ምክሩን ሰምቼ ግን መኪናውን ጥዬ ለመሄድ አልፈለኩም…..መኪና መያዜ ከሰውዬው ጋር ላለኝ ወሳኝ ፊልሚያ ያግዘኛል የሚል ግምት አሳድሮብኛል፡፡እና ቀድሜ ደብረዘይት በመድረስ የተቀበልኳቸው እኔ ነኝ፡፡ቡድኑ ያረፈው ቢን ኢንተርናሺናል ሆቴል ነው፡፡ለአለቅዬ ብቻ ሆቴሉ አይመጥነውም ተብሎ አሻም አፍሪካ ሆቴል ነው የተያዘለት…ሰው ሁሉ እንደ አመዳደቡ ሁለት ሁለት እየሆነ በየክፍሉ እየገባ ባለበት ሰዓት እኔ ሆቴሉ በረንዳ ላይ አረፍ ብዬ ማኪያቶ ነገር በመጠጣት ላይ ሳለው አቶ ሰይፉ ወደእኔ መጡ…..
‹‹ፌናን ላስቸግርሽ ነው..?››
‹‹ምነው ምን ቸገሮት..?››
‹‹ባክሽ ሰውዬችን መኪናዬ ተበላሽታብኝ አጉል ቦታ ቆሚያለው ብሎ ደወለልኝ ..…ሚኒባሶ መካኒክ ፍልጋ እስክትሄድ እዛ እንዳይቸገር ባንቺ መኪና ሄደሽ ብታመጪው…..መኪናውን ልጆቹ አሰርተው ያመጡለታል››
‹‹ችግር የለውም እርሶ አዘውኝ እንዴት እምቢ እላለው ››ብዬ ከመቀመጫዬ ተነሳውና መኪናዬን ወደአቆምኩበት ሄድኩ….አጋጣሚው ደስ ብሎኛል…ገቢና ከጎኔ አስቀምጬ እየነቆርኩት ይዤው መጣለው…ሀሳቤ እንደዛ ነበር..
ስደርስ ያላሰብኩት ነገር ነው የገጠመኝ… ከሰው ጋር ነው…ደስ አላለኝም..ለምን ደስ አላለኝም…..?አይ እንዲሁ ይመስለኛል..በቃ አለ አይደለ ብቻውን ነው ብዬ ሰለገመትኩ መደናገር ተፈጥሮብኝም ይሆናል…፡፡
መኪናዬ አቁሜ ወደ እነሱ እየሄድኩ ነው ያሰብኩት…ከእነሚስቱማ አልጭነውም….ይዣቸው ከመሄዴ ለመገላገል የመኪናዋን ብልሽት ቀላል ከሆነ እስኪ ልየው…እድሜ ለአባቴ የመኪና የአካል ክፍል ብትንትን አድርጌ እንዳውቅ አድረርጎኛል…ጫን ያለ ብልሽት ካልሆነ በስተቀር የእኔንም ሆነ የአባዬን መኪና ቱታዬን ለብሼ መሬት ላይ እየተንከባለልኩና በዘይት እየተጨመላለቅኩ የምጠግነው እና ሰርቢስ የማደርገው እራሴው ነኝ….
እሱ ባለበት አቅጣጫ ወደመስኮቱ ተጠጋው..እኔን በማየቱ እጅግ ደንግጦል…እንደህጻን ልጅ ነው የተረብተበተው..እንደዛ ሲርበተበት ደግሞ እኔ ውስጤ እንዲቁነጠነጥና ..መቁነጥነጤን ተከትሎ እንድሾርበት አስገደደኝ..፡፡ያው እንደከዚህ ቀደሙ.. ከዛም ትንሽ ከፍ ባለ ደረጃ ተሸቀርቅሯል…፡፡መቼስ የካምፓኒ ማናጀር ለመሆን ከመዳከር ይልቅ ፕሮፌሽናል ሞዴል ለመሆን ትንሽ ቢጥር አመት ሳይሞላ የሀገሪቱ አይኖች ሁሉ ማረፊያ ይሆን ነበር….፡፡እሷም ቆንጅዬ ነች …አዘናነጧ ግን ጭንቀት የወለደው አይነት ይመስላል…እሱን ላለማሳጣት እየጣረች በሚመስል ሁኔታ....፡፡ግን ምን ማለቴ ነው....?እየተናገርኩ ያለውት እኮ ትርጉም የሚሰጥ አይነት አይደለም..፡፡ጭንቀት ያለበት አዘናነጥ ማለት ምን ማለት ነው…..?እንደውም እኔ ስለእሷ የሰጠውት አስተያየት ይመስለኛል ከጭንቀት የተወለደው…፡፡ለማንኛውም የመኪናውን ኮፈን አስከፍቼ ስመረምረው ብልሽቱ አስቂኝ ነበር…ለማስተካከል ግማሽ ደቂቃ አልፈጀብኝም…እንደዛ በመሆኑ ደግሞ የተሰማኝ ስሜት ልነግራችሁ አልችልም…
…. አሁን ከኃላ እየተከተልኳቸው ነው…..በእስፖኪዬ ወደኃላ እያየኝ መሆኑን በደንብ አውቃለው…ከተማ ውስጥ ገብተን ጌትሼት ጋር ስደርስ ነበር ሚኒባሶ መካኒክ ይዛ ስትመጣ አግኝተን የመለስነው…..
የመጀመሪያው ፕሮግራም ከምሳ ግብዣ ነበር የሚጀምረው...እዛው ብዙሀኑ ያረፈበት ሆቴል እየተጫወትን ከበላን ቡኃላ በወጣው ፕሮግራም መሰረት በከተማዋ መታየት ያለባቸውን ቦታዎች ወደማየት ነው ያመራነው …ስምንት ሰዓት ሲሆን ተንቀሳቀስን፡፡
መቼስ ቢሾፍቱን ስትጎበኝ በዋናነት በሁሉም አዕምሮ ሚመጣው ሀይቆቾ ናቸው..ቢሾፍቱ ፤ሆራ ፤ባቦጋያ ፤ኩሪፍቱ፤ጨለቅለቃ.. መቼስ መታደል ነው…አንድ መለስተኛ ከተማ ይሄ ሁሉ ሀይቆች ባለቤት መሆን በራሱ ትልቅ ድልብ ሀብት ነው፡፡ለከተማዋ ብቻ አይደለም ለሀገሪቱም ጭምር..፡፡በዛ ለይ ከመዲናዋ 50 ኪሎ ሜትር ብቻ እርቃ መገኘቷ….ለአንድ ቀን እንኳን ለስራ ወደሀገሪቱ የመጣ ሰው ጎራ ብሎ አንድ ሁለት ሰዓት ዘና ብሎ ሊመለስባት በሚችልበት ቦታ ላይ መገኘቷ ሌላ እድል ነው…ግን ከተማዋም ሆነች ሀገሪቱ 5 ፐርሰንቱን እንኳን አልተጠቀመችበትም…አለም አቀፍ ቱሪስቶችን በልዩ ሁኔታ እንዲስብ ተደርጎ ፕሮሞሽን አልተሰራለትም… ፡፡ሌሎች ሀገሮች መሰል የተፈጥሮ ፀጋ ባለመታደላቸው አርቴፊሻል ወንዝ እና ሀይቅ በመስራት የቱሪስት ገቢያቸውን በሚያጧጡፈበት በዚህ ቴክኖሎጂ በመጠቀበት ዘመን እኛ ግን ተፈጥሮ በቸርነቷ የለገሰችንን የነፃ ችሮታ እንዲሁ ባልባሌ ሁኔታ ለዘመናት በማባከነ ስንዴ እንለምናለን…ያሳዝናል፤የእኔ ነገር ሳላስበው ወደንጭንጬ ገባው…ለዛውም በዚህ ዘና በማያ ቀኔ… ..ቅድሚያ ሆራ ሀይቅ ነው የሄድነው…ሆራ በከተማዋ ካሉት ሀይቆች በስፋት ትልቁ ነው..ዙሪያውን በተራራ የተከበበ ሲሆን ተራራው ላይ ደግሞ ዘመናዊ የሚባሉ ሎጆችና ሆቴሎች አልፎ አልፎም ቢሆንም ታንፀው ወደአካባቢው ለመዛናናት የሚመጡትን ቱሪስቶች ሆነ ሀገርኛ ቱሪስቶችን ለማስተናገድ እየሞከሩ ነው ፡፡አሪፍ ጊዜ ነበር ያሳለፍነው ..አብዛኛው በጀልባ ባህሩን ሰንጥቆ በመጓዝ ተዝናንቷል....12 ሰዓት ወደየአረፍንበት ሆቴል ነው የተመለስነው..ለማታ እራት ፕሮግራም ለመዘጋጀት….የእራቱ ፕሮግራም ፕራሚድ ሆቴል ነው የሚከናወነው፡፡አንድ ሰዓት ሁሉም እዛ ተሰባስቦ መገኘት አለበት፡፡
አንድ ሰዓት ከሩብ ሲል ፕራሚድ በሚገኝ የስብሰባ አዳራሽ ሁሉም ስታፎቻችን ቦታቸውን ይዘው ለፕሮግራሙ ዝግጁ ሆነው ነበር…ልክ እንደባለፈው አመት ዘንድሮም የፕሮግራሙ መሪ እኔ ስለሆንኩ ወደ መድረኩ ወጥቼ ሁሉንም አንዴ ቃኘው…የካምፓኒው ከፍተኛ ሀላፊዎች አለቃዬንና ሚስቱን በግራና ቀኝ አጅበው የፊተኛውን ረድፋ ላይ ተደርደረረዋል፡፡
ጉሮሮዬን አፀዳዳውና ማይኩን ፈታትሼ ንግግሬን ጀመርኩ…
‹‹››የተከበሩ የድርጅታችን ስራ አስኪያጅ ፤ እኛን አክብረው በመሀከላችን የተገኙት የዕለቱ የክብር እንግዳ የተከበሩት የስራ-አስኪያጃችን እጮኛ….የተከበራችሁ የስራ መሪዎችና ድንቅና ምርጥ የካማፓኒያችን ሰራተኞች እንኳን ለዚህ አመት የካማፓኒያችን ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ …አደረሰን፡፡…››
አደራሹ በጭብጨባ ተናጋ…
ፋታ ወስጄ ንግግሬን ቀጠልኩ፡፡
…የዚህ ዓመት በዓላችን ከዚህ በፊቱ የተለየ ይሆናል ፡፡አንደኛ በዓላችን ነው..ሁለተኛ ወጣቱንና እና ካምፓኒያችንንም ሆነ የእያንዳንዱን ሰራተኛ የግል ህይወት ላይ ተጨባጭ ለውጥ እንዲመጣ ያደርጋሉ ብለን ሁለችንም ተስፋ
👍1
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍሰሀ
...ከአዳራሹ ሳይሆን ትንሽ ወደኃላ ተመልሼ ልጀምርላችሁ፡፡ እስከ አሁን አዋዋላችን በጣም ግሩም የተባለ ነበር..ከተለያዩ ሰራተኞችም ጋር በየምክንያቱ የመነጋገር ስሜታቸን ማዳመጥ፤ የመቀላለድ እና እስከዛሬ ከነበረው በተሸለ የመግባባት አጋጣሚውን ስንጠቀምበት ነበር የዋልኩት…ከፌናን ጋር ግን ከሩቁ ከመተያየት በስተቀር ፊት ለፊት የመገናኘቱ አጋጣሚ አልነበረም….ምን አልባት ሰላም ያዋልኩትም እንደዛ ስለሆነ ይሆናል..የማታውን ፕሮግራም ለመጀመር አዳራሽ ከገባን ቡኃላ ከቀኑ ከነበረው አለባበሷ በተቃራኒ በጣም ረጅም ግን ደግሞ በተመሳሳይ ውብ ያደረጋትን ደማቅ ቀይ ቀሚስ ለብሳ ወደመድረኩ ስትወጣ ነበር ያየሆት…
ምትፈልገው የሆነ ዕቃ ኖሮ እሱን ለመውሰድ ወደ መድረክ የወጣች ነበር የመሰለኝ ግን ተሳስቼ ነበር… ፊት ለፊት ቆማ …ልክ ለአመታት የመድረክ ልምድ አንዳለው ፓለቲካኛ በሙሉ በራስ መተማመን ንግግሯን ጀመረች….እኔ እራሱ ምን አይነት እንከፍ ነኝ..እስኪ ቀደም ብዬ ፕሮግራማቸውን ባየው..እርግጠኛ ነኝ ከአስር ደቂቃ ባፊት እንኳን አውቄ ቢሆን እዚህች መድረክ ላይ እንድትወጣ ፈጽሞ አልፈቅድላትም ነበር…. ከመጀመሪያው ንግግሯ ነው የነገር ጦሮን በስውር የወረወረይብኝ..እስኪ እዚህ ሁሉ ሰው መካከል አቶ ፍሰሀና እጮኛቸው ማለት ምን ማለት ነው……..?እጮኛዬ ትሁን አትሁን አልነገርኮት ከየት አባቷ አወቀች…..?አቤት ወስጤ እንደተቃጠለላችሁ ..ሰውነቴ ሁሉ ሲንቀጠቀት ይታወቀኛል…ደግሞ ይህቼ ከጎኔ የተቀመጠችው መፍለቅለቅ ምን የሚሉት ነው…?የማንም ስርዓት አልባ መድረክ ላይ ወጥታ በዘጠና ምናምን ሰዎች ፊት‹‹.. የፍሰሀ እጮኛ… ››ብላ ስለተናገረችላት የእውነት እጮኛዬ የሆነች መሰላት እንዴ..?አናደደቺኝ……..
ከዛ አስተዳዳሪው ወጣ..የካማፓኒውን ሪፖርት እያቀረበ ቢሆንም ምን እንደለ አንዱንም አልሰማው…እያብሰለሰልኩ ያለውት ስለእዛች የተረገመች ልጅ ነው…እንዴት አድርጌ ነው አንገቷን ላስደፋ የምችለው….…እግዜር ይስጠው ሽማግሌው ሪፖርቱን አላንዛዛውም…ጨርሶ አመስግኖ መድረኩን ለዛች እብድ ለቀቀላት….እሷ ማለት ያቺ የተረገመች ወጥታ ስትናገር ብዙም ቁብ አልሰጣዋትም ነበር ..ግን ሽማግሌው ያቀረበውን ሪፖርት እያብራራች እየበታተነች ሳልወድ በግድ እየመረረኝ እንድሰማውና አደረገች…
ከፍተኛ ጥቃት ነው የተፈፀመብኝ ..በእኔ ብቻ አይደለም በካማፓኒውም…..ሰራተኞቹን ጠቃሚ ከሆኑት በላይ ጠቃሚ እንደሆኑ እዲሰማቸው…በትዕቢት ልባቸው እንዲወጣጠርና ነገሮች ለእኔ ከባድ እንዲሆኑብኝ ያሴረችው ሴራ ነው በእያንዳንዱ የዋህ ሰራተኛ አዕምሮ በጥበብ የበተነችው ..አዎ ንግግሯን ሰምተው ያጨበጨብላት ሰራተኞቹ የተናገረችው ሁሉ ለእነሱ አስባ ይመስላቸዋል…የእሷን ሴራ እኔ ብቻ ነኝ የማውቀው…እንደውም እሷን ማባረሬ በጣም ትክክለኛ ውሳኔ ነው..እና ይቅር ብያት እንድትመለስ የማስበውን ነገር ትቼዋለው..ለዚህችማ አይገባትም…ይህቼ ወጥ ረጋጭ ካቅሟ በላይ የምትንጠራራ… መኪና ተከራይታ ወይም ደግሞ ከሹገር ዳዲዋ ተውሳ እዚህ ይዛ በመምጣት ለመጎረር የምትጥር ከአቅም በላይ ለመኖር ስቃዬን ለምታይ ሴት ማዘን…
ወደመድረክ ስትጋብዘኝ የውስጥ ስሜቴ እየተተረማምሰ ነበር…የተዘጋጀውበትን ንግግር ሁሉ ቃላቶች ብትንትን ብለው ከአዕምሮዬ ተሰደዋል…ብቻ በደመነፍስ ወጣውና ወደጆሮዋ ጠጋ ብዬ‹‹በጣም በጣም ባለጌና መሰሪ ልጅ ነሽ ››አልኳት…ቆሽቴን እንዳሳረረቺኝ ቆሽቷን ላሳርርረው ብዬ..እሷ እቴ ምን በወጣት የመረቅኳት ይመስል ፈገግ ብላና ድምጽን ለሁሉም እንዲሰማ አድርጋ ‹‹አመሰግናለው አቶ ፍሰሀ …በእውነት ለካምፓኒዬ እና ለምወዳቸው የስራ ባለደረቦቼ ከዚህ በላይ መናገር ችዬ ብናገርና ባገለግል ደስ ይለኛል››ብላ ጭራሽ ያረረው ቆሽቴ እንዲከስል አድርገ መድረኩን ለእኔ በመልቀቅ ከኃላዬ ቆመች….
❤️ፌናን
የማታውን ፕሮግራም አትጠይቁኝ…ብዙሀኑ የተደሰቱበት እኔና ሰውዬው በየምክንያቱ በተገናኘን ቁጥር ስንጠዛጠዝና ስንነቋቆር ያሳለፍንበት ገራሚ ምሽት ነበር…በተለይ ፍቀረኛው የእኛኑ እንቅስቃሴ በጥንቃቄ ስትከታተልና ስትጠብቀን ነው ያመሸችው…አራት ሰዓት ሲሆን ይዛው ትሂድ ወይም ይዟት ይሂድ አላውቅም ብቻ ተያይዘው ወጡ….ወደ ማደሪያቸው…
እኔም ከ30 ደቂቃ ቡኃላ ቡድኑን ተለይቼ ወደማደሪያዬ ሄድኩ…..ገብቼ አልጋዬ ላይ እንደተዘርርኩ ነበር እንቅልፍ ይዞኝ ጭልጥ ያለው....ትንሽ መጠጥ የቀማመስኩ ጊዜ እንዲሁ ነው የሚያደርገኝ…ክፋቱ እንቅልፌ ቶሎ ያልቅብኛል…ዘጠኝ ሰዓት ተኩል ላይ ሙለ በሙሉ እንቅልፌን ጨርሼ ፈጠጥኩ…እዛው እየተገላበጥኩ በውስጤ የሚተረማመሰውን ሀሳብ ማመንዠግ ቀጠልኩ… በዚህ ውድቅት ለሊትም ሀሳቤ ስለእሱው ነው….ምን እየሰራው ነው…….?ከልጁ ጋር ምን እንደዚህ አይነት ጫወታው ውስጥ አሰጋባኝ..….? እሱ አልሸነፍ ባይ ስለሆነ ነው..ወይስ እኔ የማሸነፍ ሱስ ስላለብኝ….….?ነው ወይስ ቀጥታ ከአላማዬ ጋር የሚገናኝ ትግል ነው…….?እንዴት እንደዛማ አይሆንም የእኔ ዓላማ በእሱ መሸነፍ ላይ እንደማይመሰረት እርግጠኛ ነኝ..እና ምንድነው ችገሬ…….?ይሄንን ሳስብ የለበስኩትን አንሶላና ብርድልብስ ከላዬ ገፍፌ ከአልጋዬ ወረደኩ….አፍቅሬው ብቻ እንዳይሆን…….?ፍቅር እንዲህ ነው እንዴ…….?ቆይ እስኪ ፍቅር እንዴት ነበር..….? አውቃለው እንዴ…….?
በሀያ አመቴ አካባቢ አንድ ሁለት የትምህርት ቤት ጓደኞቼ ጋር ፍቅር ፍቅር መጫወት ጀምሬ ነበር..ግን እኩዬቼ ቢሆንም እኔ በማስበው ልክ ሊያስቡልኝ ስላልቻሉ..እኔ ፍቅርን በምተረጉምበት ልክ ሊተረጉሙልኝ ሳላልቻሉ ከአንዱ ጋር አንድ ወር ከሌለኛው ለሶስት ወራት ብቻ ነበር አብረን መዝለቅ የቻልነው…፡፡ያው ወንዶች ከሴት በእኩል ዕድሜ ሊበስሉ እንደማይችሉ ዘግይቼ ነው የተረዳውት…ማለት ያው የ18 ዓመት ሴት አንድ ቤትን እማወራት ሆና በደንብ ማስተዳደር ትችላለች አንድ የ18 ዓመት ወንድ ግን እራሱንም የማስተዳደር ብቃት ላይ አይደርስም…የድሮ አባቶቻችን እንዲሁ በዘፈቀደ አይደለም ወጣቶችን ሲያጋቡ ቢያንስ ወንዱ ከሴቷ በ5 ዓመት ቢበልጣት ጥሩ እንደሆነ የሚመክሩት እና እንደዛም እንዲሆን በተቻላቸው መጠን የሚጠነቀቁት…
የእሳትነቱን ዘመን ካለፍኩ ቡኃላ ደግሞ ፍቅርን በተመለከተ አንድ ቅድመ ሁኔታ ለራሴ አስቀመጥኩ… የማፈቅረው ሰው እኔ እንደምወደው እሱ ግን እንክትክት እስኪል ድረስ እንደሚያፈቅረኝ እርግጠኛ ስሆን ብቻ ነው እጄን ዘርግቼ ልቀበለው የምችለው፡፡ይሄን ለምን እንዳልኩ ማስረዳት አለብኝ መሰለኝ..ወንድ ልጅ በደንብ እንዳፈቀራት እርግጠኛ ሳትሆን እጇን የሰጠችና ወደጋብቻ የገባች ሴት ብዙ ጊዜ ከሳሪ ነች፡፡ምክንያቱም አብዛኛቹ ወንዶች የፍቅር ጫፍ ላይ የሚደርሱት በመጀመሪያዎቹ የፍቅር ጊዜያቶች ነው…ከዛ ወደግንኙነት ሲገቡ ፤ ከዛም አልፎ ወደ ትዳር ሲሸጋገሩ የማፍቀር መጠናቸው እየወረደ ነው የሚመጣው..ቢያንስ በግንኙነት ፍቅር ላይ የነበረ ስሜቱ ወደ ትዳር ሲገባ መውደድ ላይ አርፎ እንዲረጋጋ ከፍቅር መጀመር አለበት....ለሴት ልጅ ግን ተቃራኒው ነው ፡፡በግንኙነት እና በመላመድ ስሜቷ እያደገና እየጎለበተ ነው የሚመጣው.. ፡፡ በግንኙነት ወቅት መውደድ ከቻለች፤በትዳር ውስጥና በመላመድ ወደላይ ነው የምታሳድገው ወደፍቅር …አብዛኛዋ ሴት እንደዚህ ነች…እና እኔም የምወደውን እና እሱ ደግሞ የሚያፈቅረኝን እንዳገኘው እርግጠኛ እስክሆን ድረስ ለማንም ልቤን ከፍቼ አልሰጥም፡፡ለዚህ ፍሰሀ ለሚባለውም ቢሆን
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍሰሀ
...ከአዳራሹ ሳይሆን ትንሽ ወደኃላ ተመልሼ ልጀምርላችሁ፡፡ እስከ አሁን አዋዋላችን በጣም ግሩም የተባለ ነበር..ከተለያዩ ሰራተኞችም ጋር በየምክንያቱ የመነጋገር ስሜታቸን ማዳመጥ፤ የመቀላለድ እና እስከዛሬ ከነበረው በተሸለ የመግባባት አጋጣሚውን ስንጠቀምበት ነበር የዋልኩት…ከፌናን ጋር ግን ከሩቁ ከመተያየት በስተቀር ፊት ለፊት የመገናኘቱ አጋጣሚ አልነበረም….ምን አልባት ሰላም ያዋልኩትም እንደዛ ስለሆነ ይሆናል..የማታውን ፕሮግራም ለመጀመር አዳራሽ ከገባን ቡኃላ ከቀኑ ከነበረው አለባበሷ በተቃራኒ በጣም ረጅም ግን ደግሞ በተመሳሳይ ውብ ያደረጋትን ደማቅ ቀይ ቀሚስ ለብሳ ወደመድረኩ ስትወጣ ነበር ያየሆት…
ምትፈልገው የሆነ ዕቃ ኖሮ እሱን ለመውሰድ ወደ መድረክ የወጣች ነበር የመሰለኝ ግን ተሳስቼ ነበር… ፊት ለፊት ቆማ …ልክ ለአመታት የመድረክ ልምድ አንዳለው ፓለቲካኛ በሙሉ በራስ መተማመን ንግግሯን ጀመረች….እኔ እራሱ ምን አይነት እንከፍ ነኝ..እስኪ ቀደም ብዬ ፕሮግራማቸውን ባየው..እርግጠኛ ነኝ ከአስር ደቂቃ ባፊት እንኳን አውቄ ቢሆን እዚህች መድረክ ላይ እንድትወጣ ፈጽሞ አልፈቅድላትም ነበር…. ከመጀመሪያው ንግግሯ ነው የነገር ጦሮን በስውር የወረወረይብኝ..እስኪ እዚህ ሁሉ ሰው መካከል አቶ ፍሰሀና እጮኛቸው ማለት ምን ማለት ነው……..?እጮኛዬ ትሁን አትሁን አልነገርኮት ከየት አባቷ አወቀች…..?አቤት ወስጤ እንደተቃጠለላችሁ ..ሰውነቴ ሁሉ ሲንቀጠቀት ይታወቀኛል…ደግሞ ይህቼ ከጎኔ የተቀመጠችው መፍለቅለቅ ምን የሚሉት ነው…?የማንም ስርዓት አልባ መድረክ ላይ ወጥታ በዘጠና ምናምን ሰዎች ፊት‹‹.. የፍሰሀ እጮኛ… ››ብላ ስለተናገረችላት የእውነት እጮኛዬ የሆነች መሰላት እንዴ..?አናደደቺኝ……..
ከዛ አስተዳዳሪው ወጣ..የካማፓኒውን ሪፖርት እያቀረበ ቢሆንም ምን እንደለ አንዱንም አልሰማው…እያብሰለሰልኩ ያለውት ስለእዛች የተረገመች ልጅ ነው…እንዴት አድርጌ ነው አንገቷን ላስደፋ የምችለው….…እግዜር ይስጠው ሽማግሌው ሪፖርቱን አላንዛዛውም…ጨርሶ አመስግኖ መድረኩን ለዛች እብድ ለቀቀላት….እሷ ማለት ያቺ የተረገመች ወጥታ ስትናገር ብዙም ቁብ አልሰጣዋትም ነበር ..ግን ሽማግሌው ያቀረበውን ሪፖርት እያብራራች እየበታተነች ሳልወድ በግድ እየመረረኝ እንድሰማውና አደረገች…
ከፍተኛ ጥቃት ነው የተፈፀመብኝ ..በእኔ ብቻ አይደለም በካማፓኒውም…..ሰራተኞቹን ጠቃሚ ከሆኑት በላይ ጠቃሚ እንደሆኑ እዲሰማቸው…በትዕቢት ልባቸው እንዲወጣጠርና ነገሮች ለእኔ ከባድ እንዲሆኑብኝ ያሴረችው ሴራ ነው በእያንዳንዱ የዋህ ሰራተኛ አዕምሮ በጥበብ የበተነችው ..አዎ ንግግሯን ሰምተው ያጨበጨብላት ሰራተኞቹ የተናገረችው ሁሉ ለእነሱ አስባ ይመስላቸዋል…የእሷን ሴራ እኔ ብቻ ነኝ የማውቀው…እንደውም እሷን ማባረሬ በጣም ትክክለኛ ውሳኔ ነው..እና ይቅር ብያት እንድትመለስ የማስበውን ነገር ትቼዋለው..ለዚህችማ አይገባትም…ይህቼ ወጥ ረጋጭ ካቅሟ በላይ የምትንጠራራ… መኪና ተከራይታ ወይም ደግሞ ከሹገር ዳዲዋ ተውሳ እዚህ ይዛ በመምጣት ለመጎረር የምትጥር ከአቅም በላይ ለመኖር ስቃዬን ለምታይ ሴት ማዘን…
ወደመድረክ ስትጋብዘኝ የውስጥ ስሜቴ እየተተረማምሰ ነበር…የተዘጋጀውበትን ንግግር ሁሉ ቃላቶች ብትንትን ብለው ከአዕምሮዬ ተሰደዋል…ብቻ በደመነፍስ ወጣውና ወደጆሮዋ ጠጋ ብዬ‹‹በጣም በጣም ባለጌና መሰሪ ልጅ ነሽ ››አልኳት…ቆሽቴን እንዳሳረረቺኝ ቆሽቷን ላሳርርረው ብዬ..እሷ እቴ ምን በወጣት የመረቅኳት ይመስል ፈገግ ብላና ድምጽን ለሁሉም እንዲሰማ አድርጋ ‹‹አመሰግናለው አቶ ፍሰሀ …በእውነት ለካምፓኒዬ እና ለምወዳቸው የስራ ባለደረቦቼ ከዚህ በላይ መናገር ችዬ ብናገርና ባገለግል ደስ ይለኛል››ብላ ጭራሽ ያረረው ቆሽቴ እንዲከስል አድርገ መድረኩን ለእኔ በመልቀቅ ከኃላዬ ቆመች….
❤️ፌናን
የማታውን ፕሮግራም አትጠይቁኝ…ብዙሀኑ የተደሰቱበት እኔና ሰውዬው በየምክንያቱ በተገናኘን ቁጥር ስንጠዛጠዝና ስንነቋቆር ያሳለፍንበት ገራሚ ምሽት ነበር…በተለይ ፍቀረኛው የእኛኑ እንቅስቃሴ በጥንቃቄ ስትከታተልና ስትጠብቀን ነው ያመሸችው…አራት ሰዓት ሲሆን ይዛው ትሂድ ወይም ይዟት ይሂድ አላውቅም ብቻ ተያይዘው ወጡ….ወደ ማደሪያቸው…
እኔም ከ30 ደቂቃ ቡኃላ ቡድኑን ተለይቼ ወደማደሪያዬ ሄድኩ…..ገብቼ አልጋዬ ላይ እንደተዘርርኩ ነበር እንቅልፍ ይዞኝ ጭልጥ ያለው....ትንሽ መጠጥ የቀማመስኩ ጊዜ እንዲሁ ነው የሚያደርገኝ…ክፋቱ እንቅልፌ ቶሎ ያልቅብኛል…ዘጠኝ ሰዓት ተኩል ላይ ሙለ በሙሉ እንቅልፌን ጨርሼ ፈጠጥኩ…እዛው እየተገላበጥኩ በውስጤ የሚተረማመሰውን ሀሳብ ማመንዠግ ቀጠልኩ… በዚህ ውድቅት ለሊትም ሀሳቤ ስለእሱው ነው….ምን እየሰራው ነው…….?ከልጁ ጋር ምን እንደዚህ አይነት ጫወታው ውስጥ አሰጋባኝ..….? እሱ አልሸነፍ ባይ ስለሆነ ነው..ወይስ እኔ የማሸነፍ ሱስ ስላለብኝ….….?ነው ወይስ ቀጥታ ከአላማዬ ጋር የሚገናኝ ትግል ነው…….?እንዴት እንደዛማ አይሆንም የእኔ ዓላማ በእሱ መሸነፍ ላይ እንደማይመሰረት እርግጠኛ ነኝ..እና ምንድነው ችገሬ…….?ይሄንን ሳስብ የለበስኩትን አንሶላና ብርድልብስ ከላዬ ገፍፌ ከአልጋዬ ወረደኩ….አፍቅሬው ብቻ እንዳይሆን…….?ፍቅር እንዲህ ነው እንዴ…….?ቆይ እስኪ ፍቅር እንዴት ነበር..….? አውቃለው እንዴ…….?
በሀያ አመቴ አካባቢ አንድ ሁለት የትምህርት ቤት ጓደኞቼ ጋር ፍቅር ፍቅር መጫወት ጀምሬ ነበር..ግን እኩዬቼ ቢሆንም እኔ በማስበው ልክ ሊያስቡልኝ ስላልቻሉ..እኔ ፍቅርን በምተረጉምበት ልክ ሊተረጉሙልኝ ሳላልቻሉ ከአንዱ ጋር አንድ ወር ከሌለኛው ለሶስት ወራት ብቻ ነበር አብረን መዝለቅ የቻልነው…፡፡ያው ወንዶች ከሴት በእኩል ዕድሜ ሊበስሉ እንደማይችሉ ዘግይቼ ነው የተረዳውት…ማለት ያው የ18 ዓመት ሴት አንድ ቤትን እማወራት ሆና በደንብ ማስተዳደር ትችላለች አንድ የ18 ዓመት ወንድ ግን እራሱንም የማስተዳደር ብቃት ላይ አይደርስም…የድሮ አባቶቻችን እንዲሁ በዘፈቀደ አይደለም ወጣቶችን ሲያጋቡ ቢያንስ ወንዱ ከሴቷ በ5 ዓመት ቢበልጣት ጥሩ እንደሆነ የሚመክሩት እና እንደዛም እንዲሆን በተቻላቸው መጠን የሚጠነቀቁት…
የእሳትነቱን ዘመን ካለፍኩ ቡኃላ ደግሞ ፍቅርን በተመለከተ አንድ ቅድመ ሁኔታ ለራሴ አስቀመጥኩ… የማፈቅረው ሰው እኔ እንደምወደው እሱ ግን እንክትክት እስኪል ድረስ እንደሚያፈቅረኝ እርግጠኛ ስሆን ብቻ ነው እጄን ዘርግቼ ልቀበለው የምችለው፡፡ይሄን ለምን እንዳልኩ ማስረዳት አለብኝ መሰለኝ..ወንድ ልጅ በደንብ እንዳፈቀራት እርግጠኛ ሳትሆን እጇን የሰጠችና ወደጋብቻ የገባች ሴት ብዙ ጊዜ ከሳሪ ነች፡፡ምክንያቱም አብዛኛቹ ወንዶች የፍቅር ጫፍ ላይ የሚደርሱት በመጀመሪያዎቹ የፍቅር ጊዜያቶች ነው…ከዛ ወደግንኙነት ሲገቡ ፤ ከዛም አልፎ ወደ ትዳር ሲሸጋገሩ የማፍቀር መጠናቸው እየወረደ ነው የሚመጣው..ቢያንስ በግንኙነት ፍቅር ላይ የነበረ ስሜቱ ወደ ትዳር ሲገባ መውደድ ላይ አርፎ እንዲረጋጋ ከፍቅር መጀመር አለበት....ለሴት ልጅ ግን ተቃራኒው ነው ፡፡በግንኙነት እና በመላመድ ስሜቷ እያደገና እየጎለበተ ነው የሚመጣው.. ፡፡ በግንኙነት ወቅት መውደድ ከቻለች፤በትዳር ውስጥና በመላመድ ወደላይ ነው የምታሳድገው ወደፍቅር …አብዛኛዋ ሴት እንደዚህ ነች…እና እኔም የምወደውን እና እሱ ደግሞ የሚያፈቅረኝን እንዳገኘው እርግጠኛ እስክሆን ድረስ ለማንም ልቤን ከፍቼ አልሰጥም፡፡ለዚህ ፍሰሀ ለሚባለውም ቢሆን
👍3
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍሰሀ
===
እየጎተትኳት መኪናው ጋር ስንደርስ ቀጥ አልኩ…ለካ የመኪናዬን ቁልፍ አልያዝኩም ‹‹ሶሪ ፊናን ሁለት ደቂቃ››
‹‹ምነው››ግራ ገብቷት
‹‹የመኪና ቁልፍ ይዤ መጣሁ…››በማለት እዛው ጥያት በሶምሶማ ወደ መኝታ ቤቴ ሄድኩ…እመቤቲቱን እዳልቀሰቅሳ በቀስታ ከፍቼ ገባውና ወደ ኮመዲኖ ሄጄ የመኪናዬን ቁልፍና ሞባይሌን በቀስታ አንስቼ በዝግታ እየተራመድኩ ልወጣ በራፍ አካባቢ ስደርስ ‹‹ማሬ ››የሚል ድምጽ ወደ ኃላዬ እንድዞር አስገደደኝ..
‹‹ተነሳሽ እንዴ? ››
የተጨናበሰ አይኗን በእጆቾ እያሻሻች ‹‹አዎ ..ወዴት ነው…?››አለቺኝ
እየተንደረደርኩ ወደውስጥ ተመለስኩና ግንባሯን ስሜ ‹‹መጣው ተኝተሸ ጠብቂኝ..ወይንም እታች ወርደሽ ቁርስ መብላትም ትቺያለሽ››
‹‹እንዴ ምን ማለትህ ነው..? ምትሄድበት ቦታ አብሬህ እሄዳለው..አምስት ደቂቃ ጠብቀኝ……››
‹‹አይ ምን አስቻኮለሽ ..ዘና ብለሽ ተነሽ…ብዙም አልቆይም መጣው….››እልኳትና መልሷን ሳልሰማ ተንደርድሬ ወጣሁና በራፍን መልሼ በላይዋ ላይ ዘግቼባት እየተንደረደርኩ የሆቴሉን ደረጃ በመውረድ ወደምትጠብቀኝ አስደማሚዎ ፊናን ተመልሼ ሄድኩ….
ስደርስ‹‹እኔስ ሚስትህ አፍና አስቀረችህ ብዬ ወደ ክፍሌ ልመለስ ነበር››በሚል ሽርደዳ ተቀበለቺኝ
‹‹አይ ተርፌያለው›› አልኩና መኪናዋን ከፍቼ እሷን አስቀድሜ በማስገባት ዞሬ መሪውን በመጨበጥ ግቢውን ለቀን ወጣን… አስፓልቱን እንደያዝን ….‹‹ወዴት እንደምትወስደኝ ለማወቅ ጓጉቼለው››አለቺኝ
‹‹ይገርምሻል በጫወታሽ በመማረክ ከአንቺ ጋር ተጫማሪ የብቻችን ጊዜ ለማሳለፍ ስለፈሉኩ እንጂ ወደየት እንደምወስድሽ ምኑንም አላውቅም…››አልኳት…እውነትም በዚህ ጥዋት ለዛውም በለሊት ልብሷ ያለች ሴት ወዴት ይዣት ልሄድ እንደምችል ምኑንም አላውቅም…ሳቋን ለቀቀችው..ስትስቅ በጣም ታምራለች…ኪሊዬፓትራም ስትስቅ እንዲህ ታምር ነበር እንዴ ..?እሷም ስትስቅ የጁሊዬስ ቄሳር እና የማርክ አንቶኒዬን ልብ አሁን የእኔ ልብ ቀጥ እንዳለው ቀጥ ይልባቸው ነበር እንዴ…‹‹አንተ ይሄ ጥሩ ስነ-ምግባር ነው…?››አለቺኝ በትዝብት
‹‹እንዴት ምን አጠፋው?››ግራ ገብቶኝ ጠየቅኳት
‹‹ አንተን ብላ ኪሎ ሜትር አቋርጣ አምናህ የመጣችውን ፍቅረኛህን መኝታ ቤት ውስጥ ዘግተህባት ከሌላ ሴት ጋር ለብቻችን ሆነን ማውራት አማረኝ በሚል ተቀባይነት በሌለው ምክንያት እንዲህ ማድረግህ?››
‹‹በነገርሺኝ ታሪክ ነው የተማርኩት…ኪሊዬፓትራ ያፈቀሩት ሁለቱም ጀግኖች ባለትዳር ነበሩ..በእሷ ፍቅር ሲሸነፍ ትዳር ስላለን ይቅርብን አላሉም፡፡››
‹‹ጥሩ ተማሪ ነህ..ክፍ ክፉውን ብቻ መርጠህ አዕምሮ ውስጥ አስቀረህ….ደግሞ ፍቅር ያዘህ እንዴ?››
መኪናውን ዝም ብዬ በሰርክል አድርጌ ወደ ሆራ መስመር እየነዳውት ነው…
‹‹ማ እኔ ካንቺ ፍቅር…?››
‹‹አይ ድንገት እንደው ተሳስተህ አፍቅረኸኝ እንደሆነ ብዬ ነው?››
‹‹አይ እንደዚህ አይነት ስህተትማ አልሳሰትም……››አልኳት.
.እውነት አልተሳሳትኩም እንዴ..ካልተሳሳትኩ ታዲያ ምን እንደዚህ ያደርገኛል …?አንዴት ስለእሷ በየሰዓቱ የተዘበራረቀ አይነት ስሜት ሊሰማኝ ቻለ…?. ስታበሳጨኝ ምበሳጭላት ሳታስቀኝ ምስቅላት ምኔ ስለሆነች ነው ..?እራሴን የጠየቅኩትና በርግጠኝነት መልስ ላገኝላት ያልቻልኩት ጥያቄ ነው፡፡ምክንያቱም ከራስ ልብ ውስጥ እውነተኛ መልስ ማግኘት ከአንደበት ቃላት አውጥቶ ለሌላ ሰው ድንገተኛ መልስ እንደመመለስ ቀላል አይደለም፡፡
መከላከያ ኮሌጅ አካባቢ ስንደርስ ስልኬ ተንጫረረ…ሳየው የአባቴ ነው….‹‹ወይ ዳድ ነው የደወለው ማንሳት አለብኝ››አልኩን መኪናዬን ዳር ላይ አቆምኩ...ከምንቆም ቀይሪኝና አንቺ ንጂ ››አልኳትና ስልኩን አንስቼ እያዋራው ከገቢናው ወጥቼ ዞርኩ እሷም ዞረችና መሪውን በመጨበጥ በዝግታ ትነዳ ጀመር …እኔም አዕምሮዬን ሰብስቤ የናፈቀኝን አባቴን ማዋራት ቀጠልኩ….
‹‹እንዴ ዳድ አበዛሀው እኮ…በጣም ነው የናፈቅከኝ››ተነጫነጭኩበት….
‹‹ልጄ እኔም …..በጣም ነው የናፈቅከኝ››
‹‹አይ አይመስለኝም… ብናፍቅህማ ይሄን ያህል እትቆይም….››
‹‹አሁን መምጫዬ ደርሷል..ለመሆኑ ስራው እንዴት እየሄደልህ ነው፡፡››
‹‹አሪፍ ነው አባዬ…. በጣም አስደሳች እየሆነ ነው….አሁን ሰራተኛችንም ሆነ ስራውን በደንብ ለምጄዋለው… አንዳንድ ውጤታማ ለውጦችንም ለማድረግ እያሰብኩ ነው››
‹‹አይ አሪፍ ነው…ለመሆኑ ሰራተኞቹ በአንተ ላይ እምነት ያሳደሩ ይመስልሀል….መቼም ታውቃለህ ልጄ የምትመራቸውን ሰራተኞች ቀልብ ማሸነፍ ሳትችል ውጤት ማምጣት አትችልም››
‹‹አዎ ትክክል ነህ ዳድ..ሀላፊዎቹም ሆኑ ተራ ሰራተኞች በጣም ታዛዥና ተግባቢ ናቸው..እርግጥ አልደብቅህም አልፎ አልፎ አልታዘዝ ባዬችና ስርአት የሌላቸው ሰራተኞች አሉ ..እነሱንም የሚገባቸውን ትምህርት የሚሰጥ ቅጣት እየቀጣው ሁሉንም ነገር መቆጣጠር ችያለው››ይሄንን ስናገር በቆረጣ ፊናንን እያየዋት ነው….ምን ያህል ትበሳጫለች የሚለውን ለማየት..በተቃራኒው የሹፈት ሳቅ እየሳቀች እንደሆነ ነው መታዘብ የቻልኩት ፡
‹‹ልጄ ሰራተኞችን በጥበብ ያዝ …ዝም ብለህ ቀጥታ አትላተም…››አባታ ምክሩን ቀጠለ
‹‹አይ አባ …ሁሉን የምታገስ ከሆነም እንዴት ብዬ ነው በሶስት ወር የምትፈልገውን ውጤት ማግኘት የምችለው..በዛ ላይ አንደኛው ወር እያለቀ ነው..››
‹‹ልጄ አሁን የደወልኩልህ ስለዛ ላወራህ ነው…ለዛ የሚሆን ጊዜ የለንም …ስብሰባው ከአንድ ወር ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ እንዲደረግ ተወስኗል..››
‹‹ብዥ ነው ያለብኝ….እንኳንም እኔ እየነዳው አልሆነ ….መኪናዋን መንገድን ስቼ ከሆነ ግንብ ጋር እላተም ነበር..
‹‹እንዴ አባ ..በአንድ ወር ምን አይነት ተአምር ልሰራ ነው…እሰከአሁን እኳን ሙሉ በሙሉ የካማፓኒውን አሰራር እና የእያንዳዱን ሰራተኛ ብቃትና ጉድለት አጥንቼ አልጨረስኩም…እነዚህን ነገሮች በጥልቀት ሳላውቅ ደግሞ የካምፓኒው ጥሩ ጎኑንና ለውጥ የሚያስፈልገውን ቦታ ለይቷ ማወቅ ያስቸግረኛል…..በሶስት ወር ምን አይነት የተለየ ነገር ማድረግ እችላለው ብዬ ስጨነቅ ጭራሽ አንድ ወር?፡፡..አልችልም አባ … የእውነት የመጣው ይምጣ እንጄ በአንድ ወር ውስጥ የምትፈልገው ነገር ላሳካው አልችልም ››
‹‹አውቃለው ልጄ..እኔም ያማትችለውን ነገር አድርግ ብዬ ላስጨንቅህ አልፈልግም››
‹‹እና ታዲያ እንሸነፍ…ዕድሜ ልክህን የለፋህበትን ካምፓኒ እጅ ሰጥተን ለሴትዬዋ እናስረክባት…እሷ ለሴት ልጄ ሰጥታ ድርጅታችንን ድምጥማጡን እንድታጠፋው እንፍቀድላት…እንዴ አባዬ አንዴት እንዲህ በቀላሉ ተሸናፊ ሆንክ…?. ህልሜንማ እነዲህ ፍቺ አልባ አታድርገው…››
‹‹ልጄ አሁን መስፈርቱ ተቀይሯል ..አንተም ሆንክ የሴትዬዋ ልጅ የምትወዳደሩት በምታቀርብት ፕሮፕዛል ጥራት እንዲሆን ተወስኗል….ክምፓኒውን በጥልቀት ምን ያህል አውቃችሁታል …ወደፊትስ የት እንዲደርስ ለማድረግ ትችላላችሁ… …በዛ ነው የእያንዳንዳችንን ድምጽ በተለይ ልዩነት የሚያመጣውን የሰውዬውን ድምጽ ማግኘት የምትችሉት››
‹‹እንደዛ ከሆነማ ቀላል ነው…››
‹‹እንዴት ቀላል ነው ልትል ቻልክ.?.››
‹‹እንዴ አባ አንደኛ አሁን በካምፓኒው እንድሰራ እድል በማግኘቴ ምክንያት ብዙ ዕውቀቶችን አግኝቼያለው….ይሄ ደግሞ ለፕሮፖዛሉ በቂ ግብአት እንዳገኝ ያግዘኛል..ሁለተኛ የካምፓኒውን ሀላፊዎች ሆነ ኤክስፐርቶችን ሁሉ ቀኑ እስኪደርስ ድረስ መጠቀም እችላለው፤ ከእነሱ የማገኘው እገዛም ሆነ ግብአት ቀላል አይደለም…ሌላው አስፈላጊወም ከሆን ረዳት
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍሰሀ
===
እየጎተትኳት መኪናው ጋር ስንደርስ ቀጥ አልኩ…ለካ የመኪናዬን ቁልፍ አልያዝኩም ‹‹ሶሪ ፊናን ሁለት ደቂቃ››
‹‹ምነው››ግራ ገብቷት
‹‹የመኪና ቁልፍ ይዤ መጣሁ…››በማለት እዛው ጥያት በሶምሶማ ወደ መኝታ ቤቴ ሄድኩ…እመቤቲቱን እዳልቀሰቅሳ በቀስታ ከፍቼ ገባውና ወደ ኮመዲኖ ሄጄ የመኪናዬን ቁልፍና ሞባይሌን በቀስታ አንስቼ በዝግታ እየተራመድኩ ልወጣ በራፍ አካባቢ ስደርስ ‹‹ማሬ ››የሚል ድምጽ ወደ ኃላዬ እንድዞር አስገደደኝ..
‹‹ተነሳሽ እንዴ? ››
የተጨናበሰ አይኗን በእጆቾ እያሻሻች ‹‹አዎ ..ወዴት ነው…?››አለቺኝ
እየተንደረደርኩ ወደውስጥ ተመለስኩና ግንባሯን ስሜ ‹‹መጣው ተኝተሸ ጠብቂኝ..ወይንም እታች ወርደሽ ቁርስ መብላትም ትቺያለሽ››
‹‹እንዴ ምን ማለትህ ነው..? ምትሄድበት ቦታ አብሬህ እሄዳለው..አምስት ደቂቃ ጠብቀኝ……››
‹‹አይ ምን አስቻኮለሽ ..ዘና ብለሽ ተነሽ…ብዙም አልቆይም መጣው….››እልኳትና መልሷን ሳልሰማ ተንደርድሬ ወጣሁና በራፍን መልሼ በላይዋ ላይ ዘግቼባት እየተንደረደርኩ የሆቴሉን ደረጃ በመውረድ ወደምትጠብቀኝ አስደማሚዎ ፊናን ተመልሼ ሄድኩ….
ስደርስ‹‹እኔስ ሚስትህ አፍና አስቀረችህ ብዬ ወደ ክፍሌ ልመለስ ነበር››በሚል ሽርደዳ ተቀበለቺኝ
‹‹አይ ተርፌያለው›› አልኩና መኪናዋን ከፍቼ እሷን አስቀድሜ በማስገባት ዞሬ መሪውን በመጨበጥ ግቢውን ለቀን ወጣን… አስፓልቱን እንደያዝን ….‹‹ወዴት እንደምትወስደኝ ለማወቅ ጓጉቼለው››አለቺኝ
‹‹ይገርምሻል በጫወታሽ በመማረክ ከአንቺ ጋር ተጫማሪ የብቻችን ጊዜ ለማሳለፍ ስለፈሉኩ እንጂ ወደየት እንደምወስድሽ ምኑንም አላውቅም…››አልኳት…እውነትም በዚህ ጥዋት ለዛውም በለሊት ልብሷ ያለች ሴት ወዴት ይዣት ልሄድ እንደምችል ምኑንም አላውቅም…ሳቋን ለቀቀችው..ስትስቅ በጣም ታምራለች…ኪሊዬፓትራም ስትስቅ እንዲህ ታምር ነበር እንዴ ..?እሷም ስትስቅ የጁሊዬስ ቄሳር እና የማርክ አንቶኒዬን ልብ አሁን የእኔ ልብ ቀጥ እንዳለው ቀጥ ይልባቸው ነበር እንዴ…‹‹አንተ ይሄ ጥሩ ስነ-ምግባር ነው…?››አለቺኝ በትዝብት
‹‹እንዴት ምን አጠፋው?››ግራ ገብቶኝ ጠየቅኳት
‹‹ አንተን ብላ ኪሎ ሜትር አቋርጣ አምናህ የመጣችውን ፍቅረኛህን መኝታ ቤት ውስጥ ዘግተህባት ከሌላ ሴት ጋር ለብቻችን ሆነን ማውራት አማረኝ በሚል ተቀባይነት በሌለው ምክንያት እንዲህ ማድረግህ?››
‹‹በነገርሺኝ ታሪክ ነው የተማርኩት…ኪሊዬፓትራ ያፈቀሩት ሁለቱም ጀግኖች ባለትዳር ነበሩ..በእሷ ፍቅር ሲሸነፍ ትዳር ስላለን ይቅርብን አላሉም፡፡››
‹‹ጥሩ ተማሪ ነህ..ክፍ ክፉውን ብቻ መርጠህ አዕምሮ ውስጥ አስቀረህ….ደግሞ ፍቅር ያዘህ እንዴ?››
መኪናውን ዝም ብዬ በሰርክል አድርጌ ወደ ሆራ መስመር እየነዳውት ነው…
‹‹ማ እኔ ካንቺ ፍቅር…?››
‹‹አይ ድንገት እንደው ተሳስተህ አፍቅረኸኝ እንደሆነ ብዬ ነው?››
‹‹አይ እንደዚህ አይነት ስህተትማ አልሳሰትም……››አልኳት.
.እውነት አልተሳሳትኩም እንዴ..ካልተሳሳትኩ ታዲያ ምን እንደዚህ ያደርገኛል …?አንዴት ስለእሷ በየሰዓቱ የተዘበራረቀ አይነት ስሜት ሊሰማኝ ቻለ…?. ስታበሳጨኝ ምበሳጭላት ሳታስቀኝ ምስቅላት ምኔ ስለሆነች ነው ..?እራሴን የጠየቅኩትና በርግጠኝነት መልስ ላገኝላት ያልቻልኩት ጥያቄ ነው፡፡ምክንያቱም ከራስ ልብ ውስጥ እውነተኛ መልስ ማግኘት ከአንደበት ቃላት አውጥቶ ለሌላ ሰው ድንገተኛ መልስ እንደመመለስ ቀላል አይደለም፡፡
መከላከያ ኮሌጅ አካባቢ ስንደርስ ስልኬ ተንጫረረ…ሳየው የአባቴ ነው….‹‹ወይ ዳድ ነው የደወለው ማንሳት አለብኝ››አልኩን መኪናዬን ዳር ላይ አቆምኩ...ከምንቆም ቀይሪኝና አንቺ ንጂ ››አልኳትና ስልኩን አንስቼ እያዋራው ከገቢናው ወጥቼ ዞርኩ እሷም ዞረችና መሪውን በመጨበጥ በዝግታ ትነዳ ጀመር …እኔም አዕምሮዬን ሰብስቤ የናፈቀኝን አባቴን ማዋራት ቀጠልኩ….
‹‹እንዴ ዳድ አበዛሀው እኮ…በጣም ነው የናፈቅከኝ››ተነጫነጭኩበት….
‹‹ልጄ እኔም …..በጣም ነው የናፈቅከኝ››
‹‹አይ አይመስለኝም… ብናፍቅህማ ይሄን ያህል እትቆይም….››
‹‹አሁን መምጫዬ ደርሷል..ለመሆኑ ስራው እንዴት እየሄደልህ ነው፡፡››
‹‹አሪፍ ነው አባዬ…. በጣም አስደሳች እየሆነ ነው….አሁን ሰራተኛችንም ሆነ ስራውን በደንብ ለምጄዋለው… አንዳንድ ውጤታማ ለውጦችንም ለማድረግ እያሰብኩ ነው››
‹‹አይ አሪፍ ነው…ለመሆኑ ሰራተኞቹ በአንተ ላይ እምነት ያሳደሩ ይመስልሀል….መቼም ታውቃለህ ልጄ የምትመራቸውን ሰራተኞች ቀልብ ማሸነፍ ሳትችል ውጤት ማምጣት አትችልም››
‹‹አዎ ትክክል ነህ ዳድ..ሀላፊዎቹም ሆኑ ተራ ሰራተኞች በጣም ታዛዥና ተግባቢ ናቸው..እርግጥ አልደብቅህም አልፎ አልፎ አልታዘዝ ባዬችና ስርአት የሌላቸው ሰራተኞች አሉ ..እነሱንም የሚገባቸውን ትምህርት የሚሰጥ ቅጣት እየቀጣው ሁሉንም ነገር መቆጣጠር ችያለው››ይሄንን ስናገር በቆረጣ ፊናንን እያየዋት ነው….ምን ያህል ትበሳጫለች የሚለውን ለማየት..በተቃራኒው የሹፈት ሳቅ እየሳቀች እንደሆነ ነው መታዘብ የቻልኩት ፡
‹‹ልጄ ሰራተኞችን በጥበብ ያዝ …ዝም ብለህ ቀጥታ አትላተም…››አባታ ምክሩን ቀጠለ
‹‹አይ አባ …ሁሉን የምታገስ ከሆነም እንዴት ብዬ ነው በሶስት ወር የምትፈልገውን ውጤት ማግኘት የምችለው..በዛ ላይ አንደኛው ወር እያለቀ ነው..››
‹‹ልጄ አሁን የደወልኩልህ ስለዛ ላወራህ ነው…ለዛ የሚሆን ጊዜ የለንም …ስብሰባው ከአንድ ወር ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ እንዲደረግ ተወስኗል..››
‹‹ብዥ ነው ያለብኝ….እንኳንም እኔ እየነዳው አልሆነ ….መኪናዋን መንገድን ስቼ ከሆነ ግንብ ጋር እላተም ነበር..
‹‹እንዴ አባ ..በአንድ ወር ምን አይነት ተአምር ልሰራ ነው…እሰከአሁን እኳን ሙሉ በሙሉ የካማፓኒውን አሰራር እና የእያንዳዱን ሰራተኛ ብቃትና ጉድለት አጥንቼ አልጨረስኩም…እነዚህን ነገሮች በጥልቀት ሳላውቅ ደግሞ የካምፓኒው ጥሩ ጎኑንና ለውጥ የሚያስፈልገውን ቦታ ለይቷ ማወቅ ያስቸግረኛል…..በሶስት ወር ምን አይነት የተለየ ነገር ማድረግ እችላለው ብዬ ስጨነቅ ጭራሽ አንድ ወር?፡፡..አልችልም አባ … የእውነት የመጣው ይምጣ እንጄ በአንድ ወር ውስጥ የምትፈልገው ነገር ላሳካው አልችልም ››
‹‹አውቃለው ልጄ..እኔም ያማትችለውን ነገር አድርግ ብዬ ላስጨንቅህ አልፈልግም››
‹‹እና ታዲያ እንሸነፍ…ዕድሜ ልክህን የለፋህበትን ካምፓኒ እጅ ሰጥተን ለሴትዬዋ እናስረክባት…እሷ ለሴት ልጄ ሰጥታ ድርጅታችንን ድምጥማጡን እንድታጠፋው እንፍቀድላት…እንዴ አባዬ አንዴት እንዲህ በቀላሉ ተሸናፊ ሆንክ…?. ህልሜንማ እነዲህ ፍቺ አልባ አታድርገው…››
‹‹ልጄ አሁን መስፈርቱ ተቀይሯል ..አንተም ሆንክ የሴትዬዋ ልጅ የምትወዳደሩት በምታቀርብት ፕሮፕዛል ጥራት እንዲሆን ተወስኗል….ክምፓኒውን በጥልቀት ምን ያህል አውቃችሁታል …ወደፊትስ የት እንዲደርስ ለማድረግ ትችላላችሁ… …በዛ ነው የእያንዳንዳችንን ድምጽ በተለይ ልዩነት የሚያመጣውን የሰውዬውን ድምጽ ማግኘት የምትችሉት››
‹‹እንደዛ ከሆነማ ቀላል ነው…››
‹‹እንዴት ቀላል ነው ልትል ቻልክ.?.››
‹‹እንዴ አባ አንደኛ አሁን በካምፓኒው እንድሰራ እድል በማግኘቴ ምክንያት ብዙ ዕውቀቶችን አግኝቼያለው….ይሄ ደግሞ ለፕሮፖዛሉ በቂ ግብአት እንዳገኝ ያግዘኛል..ሁለተኛ የካምፓኒውን ሀላፊዎች ሆነ ኤክስፐርቶችን ሁሉ ቀኑ እስኪደርስ ድረስ መጠቀም እችላለው፤ ከእነሱ የማገኘው እገዛም ሆነ ግብአት ቀላል አይደለም…ሌላው አስፈላጊወም ከሆን ረዳት
👍7
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
❤️ፌናን
ህይወትን እንደፈለገው ያሽከረከራት ጀግና ማን ነው….….?ለሆነ የተገደበ ጊዜ አይደለም…ለሆነ ዓመታትም ብቻ ማለቴ አይደለም..የእድሜ ልክ የህይወት ዘመኑን በሙሉ ህይወትን በቁጥጥሩ ስር አድርጎ እያሾራት ያለው ወይንም ከታሪክ ማህደር ውስጥም ቢሆን እደዛ አድርጎ በፈለገው አይነትና ሁኔታ እስከወዲያኛው በመኖር የተሳካለት ማነው…….?አይ ሕይወትማ እንዲህ ልፍስፍስ አትመስለኝም… ፡፡በቃ እንዲህ እንደዋዛ በቀየስንላት መንገድ የምትጓዝ ወይም በቀደድንላት ቦይ የምትፈስ አይደለችም ..::እኛ በእሷ ላይ ባለን ፍላጎት ልክ እሷም ራሷ በእኛ ህይወት ላይ የሆነ መርምረን ልንደርስበት የማንችለው ስውር ሚስጥራዊ ፍላጎት አላትና …እኛ በህይወት ላይ ያለን ፍላጎትና ህይወት በእኛ ላይ ያላት ፍላጎት አንድ አይነት በሚሆንበት ጊዜ መንገዳችንም አንድ አይነት መነሻ እና ተመሳሳይ መዳረሻ ይኖረዋል ….እናም የኑሮ መስመራችን አልጋ በአልጋ የሚባል አይነት ስያሜ ይሰጠዋል..፡፡ይህ ግን ብዙ ጊዜ ተደጋግሞ የሚከሰት አይደለም ፤የእኛ ፍላጎት እና ህይወት እየፈሰሰችበት ያለበት መስመር ብዙ ጊዜ ተቃራኒ መስመርም ስለሚይዝ ብዙዎቻችን ሁለት ምርጫ እንመራጣለን፡፡ አንድም የራሳችን የውስጥ ፍላጎትና ብቻ በማዳመጥ ሕይወት በተቃራኒው እየተጓዘች እደሆነ ብናውቅም ትግላችንን መቀጠል..ብንቆስልና ብንላላጥም ከዛም እልፎ እስከሞት የሚያደርስ መከራ ቢገጥመንም እስከመጨረሻዋ እስትንፋስ መፋለም …ሌሎቻችን ደግሞ ፍላጎታችንና ከህይወት ተቃራኒ መሆኑን በተረዳን ጊዜ ቆም ብለን በማሳብ እንዴት ነው የእኛ ፍላጎት ውጤታማ የሚሆንበት መንገዱ በዚህ ቢሆንም ህይወት ግን እየወሰደችን ያለው በዚህ ነው…እና ህይወት መንገዷን በእኛ ፍላጎት እስክታስተካክል ድረስ ፍሰታችንን ከእሷ ፍሰት ጋር አስተካክለን እንዴት መጓዝ እንችላለን..….?የእኛ ቀን እስኪመጣ ከእነ አቋማችን መቆየት ስለሚገባን ሳንቆስል ፤ ሳንላላጥና ስንሰባበር ለመቆየት ህይወት እስከ አስገደደችን ድረስ በማፈንፈልገውም መንገድ ቢሆን መጓዝ ብልህነት ነው በማለት ሁለተኛው መንገድ ይመርጣሉ….እና የትኛው ነው የተሸለ ዘዴ ….?የሚለው አጠያያቂ መልስ ነው ያለው….
ህይወትን እንደ ወንዝ ቁጠሩት ..እዛ ወንዝ ከመግባታችሁ በፊት ወንዙ በስክነት የሚፈስ የረጋ መሆኑን ስላያችሁ በቁጥጥራችሁ ውስጥ እደሚሆን ገምታችሁ ለመዋኘት ወደ ውስጥ ትገባላችሁ…ከዛም እንደ እናንተ ፍላጎት ስትፋልጉ ከወንዙ ፍሰት በተመሳሳይ አቅጣጫ በቀላል ጉልበት ወይንም ትንሽ ተጨማሪ ጉልበት በማውጣት ከወንዙ ፍሰት በተቃራኒ ወደላይ እየዋኛችሁ እያላችሁ ድንገት ሳታስቡት ደራሽ ወንዝ እየተስገመገመ ስራችሁ ቢደርስ ምንድነው ምታደርጉት..?ጥያቄው ያ ነው፡፡ በጀመራሁት መንገድ ከፍሰቱ በተቃራኒ መዋኘታችሁን ትቀጥላላችሁ ወይስ አቅጣጫ ትቀይራላችሁ…..?ውሳኔያችሁ በጽናት ወደፊት ለመሄድ ከሆነ ያንን የሚያስገመግም እየተገለባበጠ የሚመጣ ማዕበል እየሰነጣጠቃችሀ ወደፊት የምትቀጥሉበት በቂ ኃይል አላችሁ..? ማዕበሉ ይዞ እያገላበጠ የሚመጣቸውን ግንድና መሰል ባዕድ ነገር ጋር የሚፈጠረውን መጋጨትና መላተም ተቋቁማችሁ ለመዝለቅ ጉዞችሁን ትቀጥላላችሁ ..? ወይስ የትም ይወሰደኝ የትም ቢያንስ ድንገተኛው ደራሽ እስኪቀንስ ድረስ በህይወት መቆየት የምችለው ከፍሰቱ ጋር አብሬ በአንድ አይነት አቅጣጫ ስፈስ ነው፤ለዛም እንዲያግዘኝ አንድ ግንድ ጉማጅ ላይ ተጠምጥሜ የወሰደኝ ድረስ መሄድ አለብኝ ማዕበሉ እስኪቀንስ ወይም ወደ ዳር እስኪተፋኝ መታገስ ነው የሚጠቅመኝ ብላችሁ ያንን ታደርጋላችሁ …...?እንግዲህ በደራሽ ውሃ በሚናጠው ወንዝ መሀከል ሆኖ ከፍሰቱ በተቃራኒ አቅጣጫ መጓዝ መሞከር መጋጋጥን፤ በግንድ መገጨትን ፤ብሎም ሞትንም ጭምር የሚያስከትል ቢሆንም የወንዙ ፍሰትን ተከትሎ መጓዝም የት ድረስ ..?ለምን ያህል ጊዜ..? ይዞን እንደሚጓዝ ስለማናውቅ የማናውቀውና ዓለም፤ የማናውቀው ሀገር ድረስ መጓዝና፤ በማናውቀው ኑሮ ውስጥ ተጠምዶ መጣልን ሊያስከትልብን ይችላል……
ይሄ ሁሉ ምቀበጣጥረው ቸግሮኝ ነው…የቸገረኝ ከዚህ ፍሰሀ ከሚባለው ልጅ ጋር ሳላስበው ቀስ በቀስ እየሰመጥኩበት ያለው ውስብስ ጉዳይ ነው…እርግጥ እኔ እና እሱን ያገናኘችን ህይወት ነች..ምን ማለቴ ነው..? ሁሉንስ ሰው የምታገኛኘውም የምታለያየው ያቺው የህይወት አጋጣሚ አይደለች....?..ለማን
ኛው ከቢሾፍቱ የካማፓኒውን ዓመታዊ በዓል ከተመለስን አስር ቀን አልፎናል…በአስር ቀን ውስጥ ብዙ ነገሮች ሆነዋል…..ያው መቼስ ወደ ስራዬ እንደምመለስ ትገምታላችሁ..አዎ ተመልሼያለው ፡፡ለዛው በተለየ የስራ ዘርፍ…፡፡.አሁን በዋናነት እየሰራው ያለውት ግን እሱ ለረጂም ዓመታት የዚህ ካማፓኒ ስራ አስኪያጅ ለመሆን የሚያስችለውን ድምጽ ለማግኘት እያዘጋጀው ያለውን ፕሮፕዛል በረዳትነት ማገዝ ነው..በረዳትነት ያልኳችሁ እዲሁ ለእሱ ሞራል ነው እንጂ አብዛኛውን ስራ እየሠራው ያለውት እኔው ነኝ..እርግጥ ሙሉ ቀኑን አንዳንዴም ከምሽቱ ሶስት ሰዓት እና አራት ሰዓት ድረስ ፊት ለፊት ተፋጠን ስንጨቃጨቅ ፤በሀሳብ ስንከራከተር ፤አንዱን ሀሳብ ስናፈርስ ደግሞም ሌላውን ስንገነባ ነው ውለን የምናመሸው……
በዚህ አስር ቀናት ውስጥ ከምነግራችሁ በላይ ተቀራርበናል…ከመቀራረብም አልፈን ተለማምደናል… ተለማምደናል ማለት ግን ምን ማለት ነው…?መለማመድ በጥልቀት ስሜትን መጋራትን የሚያመለክት ቃል ይመስለኛል…የግንባሩን ቋጠር ፈታ አይቼ ምን እየተሰማው እንዳሆነ ማወቅ ችላለው…..ሲፈግግ እንዴት ነው የፈገገው… ..?የሚለውን በማየት የደስታ መፍገግ ነው…....?የሽሙጥ ነው…...?የቅሬታ ነው…...? መተንተን ጀምሬያለው…እሱም እንደዛው ይመስለኛል፡፡ግን ችግሩ የዚህ ነገር ማብቂያው የት ነው የሚለውን መገመት አለመቻሌ ነው…?ለመሆኑ መጨረሻ አለው ወይ..? የሚለውም እርግጠኛ ሆኖ መናገር አይቻልም ….ሁኔታዎች ወደ ወሰዱን ዝም ብለን እንሄዳለን ወይስ ከሁኔታዎች ጋር በመቃረን የየግላችን መዳረሻ በማሰብ እርስ በርስ ጦርነት ውስጥ እንገባለን….
ይገርማችሆል !!አሁን ከምሽቱ ሁለት ሰዓት አልፎል… ግን ቢሮ ነኝ ያለውት …እርግጥ አጠገቤ የለም ምንአልባት ወደ መጽዳጃ ቤት መሰለኝ የሄደው…. ወጣ ባለበት ሰዓት ነው እያወራዋችሁ ያለውት… ቆይ ምን እንኳን ለስራ ቢሆንም እስከዚህን ሰዓት ድረስ ስትቆዩ አንቺስ እሺ ይሁን አባትሽን አስረድተሸ ካሳመንሺው ሌላ ችግር የለብሽም… እሱ ግን ፍቅረኛው እንዴት ነው ይሄን ያህል ክፍተት ልትሰጣችሁ የቻለችው..? ካላችሁኝ ስለእሷ ልነግራችሁ የሚገባኝ ነገር አለ….የዛን ቀን ትዝ ይላችሆል አይደል....?ከእሱ ጋር ስንቀዠቀዥ በለሊት ልብሴ ተያይዘን የወጣን ቀን…ተመልሰን ሆቴላችን ስደርስ ሶስት ሰዓት ሆኖ ነበር…መኪናውን በስርዓት አቁመን ወርደን ጎን ለጎን ወደመኝታ ቤታችን እየሄድን ሳለ ፍቅረኛ የሆቴል በረንዳ ላይ ሆና ስጠብቀን ነበር ላካ..ተንደርድራ ፊታችን ገጭ…. ገና ወደ እኛ እየተንደረደረች ስትመጣ ሳያት ሁኔታዋ ጥሩ እንዳልሆነ ስለተረዳውና ስለከበደኝ ቶሎ ብዬ በፍቅራኛዋና በእኔ መካከል ያለውን ክፍተት ፈንጠር ብዬ በማስፈት እርምጃዬን ሽሽት በሚመስል መልኩ ሳራዝም …..አጅሪት እሱን ጥላ ወደእኔ በመንደርደር ፊቴ ገጭ ብላ አስቆመችኝ…
‹‹ምነው የወንድ ችግር አለብሽ እንዴ..?››ቀጥታ እንዲሁ ነው ያለቺኝ
‹‹ምን እያልሽ ነው..?››
‹‹በውድቅት ለሊት ፍቅረኛዬን ከጉያዬ ሰርቀሽ በመውሰድ ለምነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
❤️ፌናን
ህይወትን እንደፈለገው ያሽከረከራት ጀግና ማን ነው….….?ለሆነ የተገደበ ጊዜ አይደለም…ለሆነ ዓመታትም ብቻ ማለቴ አይደለም..የእድሜ ልክ የህይወት ዘመኑን በሙሉ ህይወትን በቁጥጥሩ ስር አድርጎ እያሾራት ያለው ወይንም ከታሪክ ማህደር ውስጥም ቢሆን እደዛ አድርጎ በፈለገው አይነትና ሁኔታ እስከወዲያኛው በመኖር የተሳካለት ማነው…….?አይ ሕይወትማ እንዲህ ልፍስፍስ አትመስለኝም… ፡፡በቃ እንዲህ እንደዋዛ በቀየስንላት መንገድ የምትጓዝ ወይም በቀደድንላት ቦይ የምትፈስ አይደለችም ..::እኛ በእሷ ላይ ባለን ፍላጎት ልክ እሷም ራሷ በእኛ ህይወት ላይ የሆነ መርምረን ልንደርስበት የማንችለው ስውር ሚስጥራዊ ፍላጎት አላትና …እኛ በህይወት ላይ ያለን ፍላጎትና ህይወት በእኛ ላይ ያላት ፍላጎት አንድ አይነት በሚሆንበት ጊዜ መንገዳችንም አንድ አይነት መነሻ እና ተመሳሳይ መዳረሻ ይኖረዋል ….እናም የኑሮ መስመራችን አልጋ በአልጋ የሚባል አይነት ስያሜ ይሰጠዋል..፡፡ይህ ግን ብዙ ጊዜ ተደጋግሞ የሚከሰት አይደለም ፤የእኛ ፍላጎት እና ህይወት እየፈሰሰችበት ያለበት መስመር ብዙ ጊዜ ተቃራኒ መስመርም ስለሚይዝ ብዙዎቻችን ሁለት ምርጫ እንመራጣለን፡፡ አንድም የራሳችን የውስጥ ፍላጎትና ብቻ በማዳመጥ ሕይወት በተቃራኒው እየተጓዘች እደሆነ ብናውቅም ትግላችንን መቀጠል..ብንቆስልና ብንላላጥም ከዛም እልፎ እስከሞት የሚያደርስ መከራ ቢገጥመንም እስከመጨረሻዋ እስትንፋስ መፋለም …ሌሎቻችን ደግሞ ፍላጎታችንና ከህይወት ተቃራኒ መሆኑን በተረዳን ጊዜ ቆም ብለን በማሳብ እንዴት ነው የእኛ ፍላጎት ውጤታማ የሚሆንበት መንገዱ በዚህ ቢሆንም ህይወት ግን እየወሰደችን ያለው በዚህ ነው…እና ህይወት መንገዷን በእኛ ፍላጎት እስክታስተካክል ድረስ ፍሰታችንን ከእሷ ፍሰት ጋር አስተካክለን እንዴት መጓዝ እንችላለን..….?የእኛ ቀን እስኪመጣ ከእነ አቋማችን መቆየት ስለሚገባን ሳንቆስል ፤ ሳንላላጥና ስንሰባበር ለመቆየት ህይወት እስከ አስገደደችን ድረስ በማፈንፈልገውም መንገድ ቢሆን መጓዝ ብልህነት ነው በማለት ሁለተኛው መንገድ ይመርጣሉ….እና የትኛው ነው የተሸለ ዘዴ ….?የሚለው አጠያያቂ መልስ ነው ያለው….
ህይወትን እንደ ወንዝ ቁጠሩት ..እዛ ወንዝ ከመግባታችሁ በፊት ወንዙ በስክነት የሚፈስ የረጋ መሆኑን ስላያችሁ በቁጥጥራችሁ ውስጥ እደሚሆን ገምታችሁ ለመዋኘት ወደ ውስጥ ትገባላችሁ…ከዛም እንደ እናንተ ፍላጎት ስትፋልጉ ከወንዙ ፍሰት በተመሳሳይ አቅጣጫ በቀላል ጉልበት ወይንም ትንሽ ተጨማሪ ጉልበት በማውጣት ከወንዙ ፍሰት በተቃራኒ ወደላይ እየዋኛችሁ እያላችሁ ድንገት ሳታስቡት ደራሽ ወንዝ እየተስገመገመ ስራችሁ ቢደርስ ምንድነው ምታደርጉት..?ጥያቄው ያ ነው፡፡ በጀመራሁት መንገድ ከፍሰቱ በተቃራኒ መዋኘታችሁን ትቀጥላላችሁ ወይስ አቅጣጫ ትቀይራላችሁ…..?ውሳኔያችሁ በጽናት ወደፊት ለመሄድ ከሆነ ያንን የሚያስገመግም እየተገለባበጠ የሚመጣ ማዕበል እየሰነጣጠቃችሀ ወደፊት የምትቀጥሉበት በቂ ኃይል አላችሁ..? ማዕበሉ ይዞ እያገላበጠ የሚመጣቸውን ግንድና መሰል ባዕድ ነገር ጋር የሚፈጠረውን መጋጨትና መላተም ተቋቁማችሁ ለመዝለቅ ጉዞችሁን ትቀጥላላችሁ ..? ወይስ የትም ይወሰደኝ የትም ቢያንስ ድንገተኛው ደራሽ እስኪቀንስ ድረስ በህይወት መቆየት የምችለው ከፍሰቱ ጋር አብሬ በአንድ አይነት አቅጣጫ ስፈስ ነው፤ለዛም እንዲያግዘኝ አንድ ግንድ ጉማጅ ላይ ተጠምጥሜ የወሰደኝ ድረስ መሄድ አለብኝ ማዕበሉ እስኪቀንስ ወይም ወደ ዳር እስኪተፋኝ መታገስ ነው የሚጠቅመኝ ብላችሁ ያንን ታደርጋላችሁ …...?እንግዲህ በደራሽ ውሃ በሚናጠው ወንዝ መሀከል ሆኖ ከፍሰቱ በተቃራኒ አቅጣጫ መጓዝ መሞከር መጋጋጥን፤ በግንድ መገጨትን ፤ብሎም ሞትንም ጭምር የሚያስከትል ቢሆንም የወንዙ ፍሰትን ተከትሎ መጓዝም የት ድረስ ..?ለምን ያህል ጊዜ..? ይዞን እንደሚጓዝ ስለማናውቅ የማናውቀውና ዓለም፤ የማናውቀው ሀገር ድረስ መጓዝና፤ በማናውቀው ኑሮ ውስጥ ተጠምዶ መጣልን ሊያስከትልብን ይችላል……
ይሄ ሁሉ ምቀበጣጥረው ቸግሮኝ ነው…የቸገረኝ ከዚህ ፍሰሀ ከሚባለው ልጅ ጋር ሳላስበው ቀስ በቀስ እየሰመጥኩበት ያለው ውስብስ ጉዳይ ነው…እርግጥ እኔ እና እሱን ያገናኘችን ህይወት ነች..ምን ማለቴ ነው..? ሁሉንስ ሰው የምታገኛኘውም የምታለያየው ያቺው የህይወት አጋጣሚ አይደለች....?..ለማን
ኛው ከቢሾፍቱ የካማፓኒውን ዓመታዊ በዓል ከተመለስን አስር ቀን አልፎናል…በአስር ቀን ውስጥ ብዙ ነገሮች ሆነዋል…..ያው መቼስ ወደ ስራዬ እንደምመለስ ትገምታላችሁ..አዎ ተመልሼያለው ፡፡ለዛው በተለየ የስራ ዘርፍ…፡፡.አሁን በዋናነት እየሰራው ያለውት ግን እሱ ለረጂም ዓመታት የዚህ ካማፓኒ ስራ አስኪያጅ ለመሆን የሚያስችለውን ድምጽ ለማግኘት እያዘጋጀው ያለውን ፕሮፕዛል በረዳትነት ማገዝ ነው..በረዳትነት ያልኳችሁ እዲሁ ለእሱ ሞራል ነው እንጂ አብዛኛውን ስራ እየሠራው ያለውት እኔው ነኝ..እርግጥ ሙሉ ቀኑን አንዳንዴም ከምሽቱ ሶስት ሰዓት እና አራት ሰዓት ድረስ ፊት ለፊት ተፋጠን ስንጨቃጨቅ ፤በሀሳብ ስንከራከተር ፤አንዱን ሀሳብ ስናፈርስ ደግሞም ሌላውን ስንገነባ ነው ውለን የምናመሸው……
በዚህ አስር ቀናት ውስጥ ከምነግራችሁ በላይ ተቀራርበናል…ከመቀራረብም አልፈን ተለማምደናል… ተለማምደናል ማለት ግን ምን ማለት ነው…?መለማመድ በጥልቀት ስሜትን መጋራትን የሚያመለክት ቃል ይመስለኛል…የግንባሩን ቋጠር ፈታ አይቼ ምን እየተሰማው እንዳሆነ ማወቅ ችላለው…..ሲፈግግ እንዴት ነው የፈገገው… ..?የሚለውን በማየት የደስታ መፍገግ ነው…....?የሽሙጥ ነው…...?የቅሬታ ነው…...? መተንተን ጀምሬያለው…እሱም እንደዛው ይመስለኛል፡፡ግን ችግሩ የዚህ ነገር ማብቂያው የት ነው የሚለውን መገመት አለመቻሌ ነው…?ለመሆኑ መጨረሻ አለው ወይ..? የሚለውም እርግጠኛ ሆኖ መናገር አይቻልም ….ሁኔታዎች ወደ ወሰዱን ዝም ብለን እንሄዳለን ወይስ ከሁኔታዎች ጋር በመቃረን የየግላችን መዳረሻ በማሰብ እርስ በርስ ጦርነት ውስጥ እንገባለን….
ይገርማችሆል !!አሁን ከምሽቱ ሁለት ሰዓት አልፎል… ግን ቢሮ ነኝ ያለውት …እርግጥ አጠገቤ የለም ምንአልባት ወደ መጽዳጃ ቤት መሰለኝ የሄደው…. ወጣ ባለበት ሰዓት ነው እያወራዋችሁ ያለውት… ቆይ ምን እንኳን ለስራ ቢሆንም እስከዚህን ሰዓት ድረስ ስትቆዩ አንቺስ እሺ ይሁን አባትሽን አስረድተሸ ካሳመንሺው ሌላ ችግር የለብሽም… እሱ ግን ፍቅረኛው እንዴት ነው ይሄን ያህል ክፍተት ልትሰጣችሁ የቻለችው..? ካላችሁኝ ስለእሷ ልነግራችሁ የሚገባኝ ነገር አለ….የዛን ቀን ትዝ ይላችሆል አይደል....?ከእሱ ጋር ስንቀዠቀዥ በለሊት ልብሴ ተያይዘን የወጣን ቀን…ተመልሰን ሆቴላችን ስደርስ ሶስት ሰዓት ሆኖ ነበር…መኪናውን በስርዓት አቁመን ወርደን ጎን ለጎን ወደመኝታ ቤታችን እየሄድን ሳለ ፍቅረኛ የሆቴል በረንዳ ላይ ሆና ስጠብቀን ነበር ላካ..ተንደርድራ ፊታችን ገጭ…. ገና ወደ እኛ እየተንደረደረች ስትመጣ ሳያት ሁኔታዋ ጥሩ እንዳልሆነ ስለተረዳውና ስለከበደኝ ቶሎ ብዬ በፍቅራኛዋና በእኔ መካከል ያለውን ክፍተት ፈንጠር ብዬ በማስፈት እርምጃዬን ሽሽት በሚመስል መልኩ ሳራዝም …..አጅሪት እሱን ጥላ ወደእኔ በመንደርደር ፊቴ ገጭ ብላ አስቆመችኝ…
‹‹ምነው የወንድ ችግር አለብሽ እንዴ..?››ቀጥታ እንዲሁ ነው ያለቺኝ
‹‹ምን እያልሽ ነው..?››
‹‹በውድቅት ለሊት ፍቅረኛዬን ከጉያዬ ሰርቀሽ በመውሰድ ለምነሽ
👍1
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍሰሀ
===
መቼስ ያለውበትን ሁኔታ በጥቂቱም ቢሆን ግንዛቤው ይኖራችሆል ብዬ አስባለው፡፡ለዚህ ለዓላማዬ መሳካት ቁልፍ ለሆነው የፕሮፖዛል ዝግጅት ሙሉ ጊዜዬን ሰጥቼ ጠብ እርግፍ እያልኩ ነው….በሌላ ጎን ደግሞ ይህቺ ፌናን የምትባል ልጅ እራሷን የቻለች የቤት ስራ ሆናብኛለች፡፡በቃ የሆነ ነገር ሳታውቁት ከቁጥጥራችሁ ውጭ በሆነ ስሜት ስተት ብሎ ከደምስራችሁ ጋር በመስረግ በመላ ሰውነታችሁ ጋር ተዋህዶባችሁ ያውቃል…በቃ ልቤ ላይም ፤ አዕምሮዬ ውስጥም፤ እታች የእግሯቼ ጥፍሮች ላይም በእኩል መጠን ያለች ነው የሚመስለኝ..፡፡እንደእዚህ እንዴት ሆነ ……?አላውቅም….፡፡በቃ አፍቅሬያታለው፡፡ማፍቀሬን ደግሞ በውስጤ ስላፈንኩት እየተጎዳው ነው...ህመሙ ልቤ ስር እስኪሰማኝ ድረስ የተጎዳውበት ነው….
ስራውን በተመለከተ ረዳቴ ሆና በጣም እያገዘቺኝ ነው..እርዳታዋ በጣም ጠቃሚና ወሳኝ ከመሆኑ የተነሳ እራሴን እስክታዘብ ድረስ ነበር ስደመምባት የነበረው፡፡ ….አሁን ተሰርቶ በመጠናቀቅ ላይ ያለው ፕሮፖዛል እሷ ባታግዠኝ ኖሮ በራሴ እሰራው ከነበረው ጋር በሀሳቤ ሳመዛዝነው ደነግጣለው..፡፡ልጅን እንደ ቁጥር አንድ ጀግና በሚያስበው አባቴ ፊት ተዋርጄ ነበር…፡፡አሁን ግን እድሜ ለፌናን አይደለም ከአንዲት ልምድ አልባ ወጣት ሴት ጋረ ይቅርና ከማንም በስራው እድሜ ጠገብ ልምድ ያለው ሰው ጋር ተወዳድሬ ቦታውን በእጄ ማስገባት እችላለው፡፡፡የዛን ያህል በራሴ እንድተማመን አድርጋኛለች ፡፡አሁን በዛ እርግጠኛ ሆኜያለው ፤ ይገርማችሆል ፌናን ጭቅጭቆ እራሱ ሱስ ይሆንባችኃል…….አሁንም ቢሮ ጭቅጭቅ ላይ ነን፡፡ ስለዚሁ የፕሮፖዛል አንዱ ክፍል የሆነ የሰራተኛ ደሞዝን በተመለከተ እየተነጋገርን ነው…
‹‹አሁን ለሰራተኟች እየተከፈለ ያለው ደሞዝ መስተካከል አለበት ..››የሚል ሀሳብ አቀረበች
ወዲያው ነው የተቃወምኳት‹‹ትቀልጂያለሽ እንዴ……?በተመሳሳይ የስራ መደብ በመንግስት ቤት ከሚከፈላቸው ሰራተኞች ጋር ሲነፃፀር ቢያንስ አርባና ሀምሳ ፐርሰንት የእኛ ጭማሪ አለው..እና በዚህ ላይ አሁን በምናደርገው ማሻሻያ ላይ የ5 ፐርሰንት ጭማሪ ማድረጋችን በጣም ምክንያታዊና በቂ ነው ብዬ አስባለው፡፡››
‹‹አልስማማም..››አለቺኝና ንግግሯን ማብራራት ቀጠለች‹‹ይሄውልህ በመጀመሪያ ደሞዝን በተመለከተ የመንግስትን እስኬል ማነፃፀሪያ ማድረግ ትክክል አይመስለኝም፡፡››
‹‹ለምን ………..?መንግስት እንደዛ ለምን እንደሚከፍል ታውቂያለሽ ፡፡ሀገሪቱ ደሀ ስለሆነች ነው፡፡እኛም ደግሞ መክፈል ሰለቻልን ብቻ ዝም ብለን መክፈል የለብንም ….ገበያውን ማበላሸት ነው የሚሆነው››
‹‹ላስቁምህ..ይህቺ ገበያውን ማበላሸት ነው የምትለው ቀሺም ምክንያት ነች ..እዚህ ሀገር ላይ የሰው ጉልበት ዋጋን በተመለከተ በጣም የተዛባ አመለካከት አለ…መንግስት ሀገሪቱ ደሀ ስለሆነች ከዚህ በላይ የተሻለ ደሞዝ መክፈል አልችልም ይላል..ግን እውነቱ ያ ብቻ ይመስልሀል…?፡፡እንደእኔ ግንዛቤ ዋናው ችግሩ ያመለካከት ነው……በየመስሪያ ቤት በቋሚ እና አላቂ ንብረቶች ላይ የሚከሰትን ብክነትና ብልሽትን የተወሰነ ግንዛቤ በመፍጠር እና የተወሰነ የጥንቃቄ እርምጃ በማድረግ ለዓመታዊ ዕቃ ግዢ የሚወጣውን ወጪ በ50 ፐርሰን መቀነስ ብንችል ከዛ በተገኘ ገንዘብ ቢያንስ የእያንዳንዱ የመንግስት ሰራተኛ ላይ የ25 ፐርሰንት የደሞዝ ጭማሪ ማድረግ አይቻልም ብለህ ታስባለህ…?.ባለስልጣኗች በሙስና የሚቀራመቱትን ገንዘብ የተወሰኑ ክፍተት ያላቸውን አሰራሮች በማሻሻል እና የተወሰነ ቁጥጥር በማድረግ ቢያንስ 50 ፐርሰንቱን ማስጣል ቢቻል የሰራተኛውን ደሞዝ 200 ፐርሰንት ማሳደግ አይቻልም ትላለህ…?የተቀላጠፈ የስራ ቢሮክራሲ ተፈጥሮ የእያንዳንዱን ሰራተኛ የስራ ውጤታማነትን በተወሰነ ስልተና እና ማነቃቃት በአንድ እጥፍ ማሰደግ ቢቻልና አጠቃላይ የሀገሪቱን ዓመታዊ ምርታማነትን የእውነት 11 ፐርሰንት ማሳደግ ማይቻል ይመስልሀል? እንደዛ ከሆነ ድግሞ በየአመቱ ስንት ፐርሰንት ለሰራተኛ ደሞዝ መጨመር ይቻላል…?አየህ የሀገሪቱን የድህነት ችግር ለመቅረፍ እየሞከርን ያለነው በተሳሳተ የድህነት አመለካከት ነው….
‹‹እኔ እንጃ የምትያቸውን ነገሮች በቀላሉ ማድረግ ይቻላል የሚለውን መቀበል ይከብደኛል››አለኳት…
ተቃውሞዬን ችላ ብላ ቀጠለች‹‹አንዳንዴ ይገርመኛል አንድ የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ ስንት እና ስንት ለሀገር ደህነንነት ወሳኝ የሆኑ ጉዳዩችን ሲዳኝ ውሎ፤ የሚሊዬን እና ቢሊዬን ሙስና ወንጀሎችን ሲመረምር ቆይቶ ወደቤቱ የሚወስደው አንድ ቪትስ መኪና እንኳን አጥቶ በታክሲ ሰልፍ ይዞ እየተጋፋ ወይም በባስ ታጭቆ እየተንገላታ ወደቤቱ ሲሄድ የሚፈጥርበት ስሜት ይታይህ…ይሄ ሰው የሚከፈለውስ ደሞዝ ስንት ነው…?ልጁ ቢታመምበት የግለሰብ ሆስፒታል ወስዶ ማሳካም አቅም ይኖረዋል ወይ ….?እና ሄዶ ሄዶ ሙስና ውስጥ ሳይገባ ምን የህል ጊዜ በጽናት መቆየት ይችላል …?በእሱ ላይ የሚመጣውን የድህንት ችግር መታገስ አለበት ብለን እንፍረድበት በልጁ ላይስ ሲሆን …?ክፋቱ ደግሞ ማንም ሰው ለወቅቱ የሚያስፈልገውን ለችግሩ ሚበቃውን ያህል ብቻ ዘርፎ አያቆምም..፡፡አንዴ መዝረፍ ከተጀመራ ሱስ ነው የሚሆነው…ለዛውም አደገኛ የሀሽሽ ሱስ አይነት …፡፡ለመኖር መሰረታዊ ፍላጎቶቹን ማሟላት ያቃተው ዳኛ ዘራፋ ሲጀምር…ለመኖር መሰረታዊ ፍላጎቶቹን ማሟላት ያቃተው መሀንዲስ መዝርፈ ሲጀምር…. ለመኖር መሰረታዊ ፍላጎቶቹን ማሟላት ያቃተው የባንክ ማናጀር መዝረፍ ሲጀምር ..ሀገር ሁሉ በዘራፊዎች መነኸሪያ ሆና ታርፈዋለች….. በጣም የሚያስጠላው ደግሞ መዝረፍ ውስጥ የገባ ሰው በዘረፋው ብቻ አይደለም ሀገሪቱን የሚጎዳው የስራ ሞራሉም ቀን በቀን አየወረደ ስለሚመጣ ነው…ተጫሪ ገንዘብ በቀጥታ ለኪሱ የሚያስገባለት ገንዘብ የማያገኝበትን ስራ ዞር ብሎ ለማየት ፍላጎቱ ወደ ዜሮ እየተንደረደረ ይሄዳል …
አሁን እኮ ለሙሰኞችና ቀማኞች ይቅራታ እንዲባሉ ምክንያት እየሰጠሽላቸው ነው››
በፍጽም እንደዛ አይደለም ..ምንም ሳይቸግረው በስነምግባር ጉድለትና በስግብግብነት በሽታ ብቻ በመጠቃታቸው በሙስና የሚጨማለቁ ቡዙ ዜጎች እንዳሉ አውቃለው…ግን ሳይፈልጉ ችግርና እጦት አንደርድሮ እዛ አዝቅጠት ውስጥ የጨመራቸው የመንግስት ሰራተኞች ቀላል ቁጥር የላቸውም እያልኩህ ነው…እንደዚህ አይነት ሰዎች ደግሞ አንድ ንጽህ ህሊናቸው በሆነ ምክያት ከጨቆየ ይሰባራሉ… በራሳቸውም ስለሚያፍሩ ብኩን ዜጎች እንደሆኑ ይቀራሉ..እያወራውልህ ያለውት ስለእነዛ ሰዎች ነው..በነዛ ጠቃሚ ሰዎች ውድቀት መንግስት የደሞዝ ክፍያ ስርዓትና አሰስተሳሰብ ትልቅ አስተዋፅኦ አለው ፡፡እያልኩህ ነው…
‹‹ቆይ…. እንደምታውቂው የሰው ልጅ ፍላጎት ማብቂያ የለውም፡፡የሆነ ነገር በሰጠሸው ቁጥር ሌላ ተጨማሪ ነገር ይጠይቅሻል..ታዲያ ምን ያህል ቢከፈል ነው በቂ ሚባለው?፡፡››
‹‹ለችሎታውና ለአገልግሎቱ የሚመጥነውን ቢያንስ ዝቅተኛውን ክፍያ ማግኘት አለበት….አንድ ምሳሌ ልስጥህ በመዘጋጃ ቤት የሚሰራ መሀንዲስ 5 ሺብር ደሞዝ እየተከፈለው የሀምሳ ሚሊዬን ብር ባጀት ያለው ሰማይ ጠቀስ ህንፃ እንዲቆጣጠር ይመደባል…. እና መንግስን ወክሎ ባለሀብቱ በተሰጠው ቦታና በፀደቀለት ዲዛይን መሰረት ህንጻውን እየገነባ መሆኑን ለማረጋገጥ በሚሰማራበት ጊዜ ያገኘውን ስህተት ለባለቤቱ ተናግሮ የማሳገጃ ትዕዛዝ ሊፅፍ ሲል ባለሀብቱ 20 ሺብር ማለት የአራት ወር ደሞዙን በአንድ ቀን ቢሰጠው አልፈልግም ለማለት የሚያስችል ስብዕና ጽናት ከመቶ ሰው
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍሰሀ
===
መቼስ ያለውበትን ሁኔታ በጥቂቱም ቢሆን ግንዛቤው ይኖራችሆል ብዬ አስባለው፡፡ለዚህ ለዓላማዬ መሳካት ቁልፍ ለሆነው የፕሮፖዛል ዝግጅት ሙሉ ጊዜዬን ሰጥቼ ጠብ እርግፍ እያልኩ ነው….በሌላ ጎን ደግሞ ይህቺ ፌናን የምትባል ልጅ እራሷን የቻለች የቤት ስራ ሆናብኛለች፡፡በቃ የሆነ ነገር ሳታውቁት ከቁጥጥራችሁ ውጭ በሆነ ስሜት ስተት ብሎ ከደምስራችሁ ጋር በመስረግ በመላ ሰውነታችሁ ጋር ተዋህዶባችሁ ያውቃል…በቃ ልቤ ላይም ፤ አዕምሮዬ ውስጥም፤ እታች የእግሯቼ ጥፍሮች ላይም በእኩል መጠን ያለች ነው የሚመስለኝ..፡፡እንደእዚህ እንዴት ሆነ ……?አላውቅም….፡፡በቃ አፍቅሬያታለው፡፡ማፍቀሬን ደግሞ በውስጤ ስላፈንኩት እየተጎዳው ነው...ህመሙ ልቤ ስር እስኪሰማኝ ድረስ የተጎዳውበት ነው….
ስራውን በተመለከተ ረዳቴ ሆና በጣም እያገዘቺኝ ነው..እርዳታዋ በጣም ጠቃሚና ወሳኝ ከመሆኑ የተነሳ እራሴን እስክታዘብ ድረስ ነበር ስደመምባት የነበረው፡፡ ….አሁን ተሰርቶ በመጠናቀቅ ላይ ያለው ፕሮፖዛል እሷ ባታግዠኝ ኖሮ በራሴ እሰራው ከነበረው ጋር በሀሳቤ ሳመዛዝነው ደነግጣለው..፡፡ልጅን እንደ ቁጥር አንድ ጀግና በሚያስበው አባቴ ፊት ተዋርጄ ነበር…፡፡አሁን ግን እድሜ ለፌናን አይደለም ከአንዲት ልምድ አልባ ወጣት ሴት ጋረ ይቅርና ከማንም በስራው እድሜ ጠገብ ልምድ ያለው ሰው ጋር ተወዳድሬ ቦታውን በእጄ ማስገባት እችላለው፡፡፡የዛን ያህል በራሴ እንድተማመን አድርጋኛለች ፡፡አሁን በዛ እርግጠኛ ሆኜያለው ፤ ይገርማችሆል ፌናን ጭቅጭቆ እራሱ ሱስ ይሆንባችኃል…….አሁንም ቢሮ ጭቅጭቅ ላይ ነን፡፡ ስለዚሁ የፕሮፖዛል አንዱ ክፍል የሆነ የሰራተኛ ደሞዝን በተመለከተ እየተነጋገርን ነው…
‹‹አሁን ለሰራተኟች እየተከፈለ ያለው ደሞዝ መስተካከል አለበት ..››የሚል ሀሳብ አቀረበች
ወዲያው ነው የተቃወምኳት‹‹ትቀልጂያለሽ እንዴ……?በተመሳሳይ የስራ መደብ በመንግስት ቤት ከሚከፈላቸው ሰራተኞች ጋር ሲነፃፀር ቢያንስ አርባና ሀምሳ ፐርሰንት የእኛ ጭማሪ አለው..እና በዚህ ላይ አሁን በምናደርገው ማሻሻያ ላይ የ5 ፐርሰንት ጭማሪ ማድረጋችን በጣም ምክንያታዊና በቂ ነው ብዬ አስባለው፡፡››
‹‹አልስማማም..››አለቺኝና ንግግሯን ማብራራት ቀጠለች‹‹ይሄውልህ በመጀመሪያ ደሞዝን በተመለከተ የመንግስትን እስኬል ማነፃፀሪያ ማድረግ ትክክል አይመስለኝም፡፡››
‹‹ለምን ………..?መንግስት እንደዛ ለምን እንደሚከፍል ታውቂያለሽ ፡፡ሀገሪቱ ደሀ ስለሆነች ነው፡፡እኛም ደግሞ መክፈል ሰለቻልን ብቻ ዝም ብለን መክፈል የለብንም ….ገበያውን ማበላሸት ነው የሚሆነው››
‹‹ላስቁምህ..ይህቺ ገበያውን ማበላሸት ነው የምትለው ቀሺም ምክንያት ነች ..እዚህ ሀገር ላይ የሰው ጉልበት ዋጋን በተመለከተ በጣም የተዛባ አመለካከት አለ…መንግስት ሀገሪቱ ደሀ ስለሆነች ከዚህ በላይ የተሻለ ደሞዝ መክፈል አልችልም ይላል..ግን እውነቱ ያ ብቻ ይመስልሀል…?፡፡እንደእኔ ግንዛቤ ዋናው ችግሩ ያመለካከት ነው……በየመስሪያ ቤት በቋሚ እና አላቂ ንብረቶች ላይ የሚከሰትን ብክነትና ብልሽትን የተወሰነ ግንዛቤ በመፍጠር እና የተወሰነ የጥንቃቄ እርምጃ በማድረግ ለዓመታዊ ዕቃ ግዢ የሚወጣውን ወጪ በ50 ፐርሰን መቀነስ ብንችል ከዛ በተገኘ ገንዘብ ቢያንስ የእያንዳንዱ የመንግስት ሰራተኛ ላይ የ25 ፐርሰንት የደሞዝ ጭማሪ ማድረግ አይቻልም ብለህ ታስባለህ…?.ባለስልጣኗች በሙስና የሚቀራመቱትን ገንዘብ የተወሰኑ ክፍተት ያላቸውን አሰራሮች በማሻሻል እና የተወሰነ ቁጥጥር በማድረግ ቢያንስ 50 ፐርሰንቱን ማስጣል ቢቻል የሰራተኛውን ደሞዝ 200 ፐርሰንት ማሳደግ አይቻልም ትላለህ…?የተቀላጠፈ የስራ ቢሮክራሲ ተፈጥሮ የእያንዳንዱን ሰራተኛ የስራ ውጤታማነትን በተወሰነ ስልተና እና ማነቃቃት በአንድ እጥፍ ማሰደግ ቢቻልና አጠቃላይ የሀገሪቱን ዓመታዊ ምርታማነትን የእውነት 11 ፐርሰንት ማሳደግ ማይቻል ይመስልሀል? እንደዛ ከሆነ ድግሞ በየአመቱ ስንት ፐርሰንት ለሰራተኛ ደሞዝ መጨመር ይቻላል…?አየህ የሀገሪቱን የድህነት ችግር ለመቅረፍ እየሞከርን ያለነው በተሳሳተ የድህነት አመለካከት ነው….
‹‹እኔ እንጃ የምትያቸውን ነገሮች በቀላሉ ማድረግ ይቻላል የሚለውን መቀበል ይከብደኛል››አለኳት…
ተቃውሞዬን ችላ ብላ ቀጠለች‹‹አንዳንዴ ይገርመኛል አንድ የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ ስንት እና ስንት ለሀገር ደህነንነት ወሳኝ የሆኑ ጉዳዩችን ሲዳኝ ውሎ፤ የሚሊዬን እና ቢሊዬን ሙስና ወንጀሎችን ሲመረምር ቆይቶ ወደቤቱ የሚወስደው አንድ ቪትስ መኪና እንኳን አጥቶ በታክሲ ሰልፍ ይዞ እየተጋፋ ወይም በባስ ታጭቆ እየተንገላታ ወደቤቱ ሲሄድ የሚፈጥርበት ስሜት ይታይህ…ይሄ ሰው የሚከፈለውስ ደሞዝ ስንት ነው…?ልጁ ቢታመምበት የግለሰብ ሆስፒታል ወስዶ ማሳካም አቅም ይኖረዋል ወይ ….?እና ሄዶ ሄዶ ሙስና ውስጥ ሳይገባ ምን የህል ጊዜ በጽናት መቆየት ይችላል …?በእሱ ላይ የሚመጣውን የድህንት ችግር መታገስ አለበት ብለን እንፍረድበት በልጁ ላይስ ሲሆን …?ክፋቱ ደግሞ ማንም ሰው ለወቅቱ የሚያስፈልገውን ለችግሩ ሚበቃውን ያህል ብቻ ዘርፎ አያቆምም..፡፡አንዴ መዝረፍ ከተጀመራ ሱስ ነው የሚሆነው…ለዛውም አደገኛ የሀሽሽ ሱስ አይነት …፡፡ለመኖር መሰረታዊ ፍላጎቶቹን ማሟላት ያቃተው ዳኛ ዘራፋ ሲጀምር…ለመኖር መሰረታዊ ፍላጎቶቹን ማሟላት ያቃተው መሀንዲስ መዝርፈ ሲጀምር…. ለመኖር መሰረታዊ ፍላጎቶቹን ማሟላት ያቃተው የባንክ ማናጀር መዝረፍ ሲጀምር ..ሀገር ሁሉ በዘራፊዎች መነኸሪያ ሆና ታርፈዋለች….. በጣም የሚያስጠላው ደግሞ መዝረፍ ውስጥ የገባ ሰው በዘረፋው ብቻ አይደለም ሀገሪቱን የሚጎዳው የስራ ሞራሉም ቀን በቀን አየወረደ ስለሚመጣ ነው…ተጫሪ ገንዘብ በቀጥታ ለኪሱ የሚያስገባለት ገንዘብ የማያገኝበትን ስራ ዞር ብሎ ለማየት ፍላጎቱ ወደ ዜሮ እየተንደረደረ ይሄዳል …
አሁን እኮ ለሙሰኞችና ቀማኞች ይቅራታ እንዲባሉ ምክንያት እየሰጠሽላቸው ነው››
በፍጽም እንደዛ አይደለም ..ምንም ሳይቸግረው በስነምግባር ጉድለትና በስግብግብነት በሽታ ብቻ በመጠቃታቸው በሙስና የሚጨማለቁ ቡዙ ዜጎች እንዳሉ አውቃለው…ግን ሳይፈልጉ ችግርና እጦት አንደርድሮ እዛ አዝቅጠት ውስጥ የጨመራቸው የመንግስት ሰራተኞች ቀላል ቁጥር የላቸውም እያልኩህ ነው…እንደዚህ አይነት ሰዎች ደግሞ አንድ ንጽህ ህሊናቸው በሆነ ምክያት ከጨቆየ ይሰባራሉ… በራሳቸውም ስለሚያፍሩ ብኩን ዜጎች እንደሆኑ ይቀራሉ..እያወራውልህ ያለውት ስለእነዛ ሰዎች ነው..በነዛ ጠቃሚ ሰዎች ውድቀት መንግስት የደሞዝ ክፍያ ስርዓትና አሰስተሳሰብ ትልቅ አስተዋፅኦ አለው ፡፡እያልኩህ ነው…
‹‹ቆይ…. እንደምታውቂው የሰው ልጅ ፍላጎት ማብቂያ የለውም፡፡የሆነ ነገር በሰጠሸው ቁጥር ሌላ ተጨማሪ ነገር ይጠይቅሻል..ታዲያ ምን ያህል ቢከፈል ነው በቂ ሚባለው?፡፡››
‹‹ለችሎታውና ለአገልግሎቱ የሚመጥነውን ቢያንስ ዝቅተኛውን ክፍያ ማግኘት አለበት….አንድ ምሳሌ ልስጥህ በመዘጋጃ ቤት የሚሰራ መሀንዲስ 5 ሺብር ደሞዝ እየተከፈለው የሀምሳ ሚሊዬን ብር ባጀት ያለው ሰማይ ጠቀስ ህንፃ እንዲቆጣጠር ይመደባል…. እና መንግስን ወክሎ ባለሀብቱ በተሰጠው ቦታና በፀደቀለት ዲዛይን መሰረት ህንጻውን እየገነባ መሆኑን ለማረጋገጥ በሚሰማራበት ጊዜ ያገኘውን ስህተት ለባለቤቱ ተናግሮ የማሳገጃ ትዕዛዝ ሊፅፍ ሲል ባለሀብቱ 20 ሺብር ማለት የአራት ወር ደሞዙን በአንድ ቀን ቢሰጠው አልፈልግም ለማለት የሚያስችል ስብዕና ጽናት ከመቶ ሰው
👍1
ውድ አንባብያን ያለፈው ክፍል ላይ በስተት ክፍል 21 22 የተባለው በስተት ነው ምንም የታሪክ መቆራረጥ የለም መልካም ንባብ
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሦስት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍሰሀ
‹‹አሁን ተስማምቼለው››
‹‹አመስግናለው››
‹‹አንድ ነገር ልጠይቅሽ ነበር?››
‹‹አለቃ እኮ ለመጠየቅ ፍቃድ አይጠይቅም››
‹‹አሁን እኮ የስራ ሰዓት አይደለም …ስለዚህ አለቃ ምናምን ብሎ ነገር የለም..››አልኳት
‹‹እሺ ጠይቀኝ››አለቺኝ አቀማጧን እያስተካከለች
‹‹የዛን ቀን እሷን ለማናደድ ብለሽ ያደረግሺውን እንደሆነ ባውቅም ግን በምንም አይነት ከአዕምሮዬ ላወጣው አልቻልኩም….ከአዕመሮዬም ብቻ አይደለም ከህልሜም ማስወገድ አልቻልኩም….ሙሉ አዕምሮዬ በአንቺ ከንፈር ተሞልቷል…ምነው አሁንም አንድ ሰው አበሳጭቷት በሳመቺኝ እያልኩ በየቀኑ ነው የምፀልየው…
‹‹እየቀለድክ ነው አይደል?››አለቺኝ በፈገግታ እና በመኮሳተር መካከል በሚዋልል ስሜት
‹‹አይደለም…››አልኩና እንደምንም እራሴን አደፋፍሬ እጇን በመዶፎቼ መካከል አስገባውና እያሻሸው ንግግሬን ቀጠልኩ..አልተቃወመችኝም፡፡
‹‹አይደለም..እውነቴን ነው…ከህይወቴ አንድ አመት ተቀንሶ ያንን አይነት መሳም አንድ ጊዜ ደግማ ትሳምህ ብባል እስማማለው …እና እባክሽ..››
‹‹እንዲህ አይጠየቅም እኮ …አንድን ሴት እንዴት ልሳምሽ ብለህ ትጠይቃታለህ…ነውር እኮ ነው፡፡ነው ወይስ ውጭ ስለኖርክ ነውር የሚባል ነገር እረስተሀል?››
‹‹እንደዛ ማለቴ አይደለም..ፍቅረኛዬ እንድትሆኚ እየጠየቅኩሽ ነው››
በጥያቄዬ ምንም የመገረም ስሜት አልታየባትም ‹‹ከዛም በፊት ፍቅረኛ አለሽ ወይ ተብሎ ይጠየቃል…በዛ ላይ አንተም ፍቅረኛ አንዳለችህ አውቃለው..ታዲያ ፍቅረኛ ያለችውን ሰው መጥበስ የምፈልግ ይመስልሀል…?››
‹‹የእኔን እርሺው አብቅቶለታል..አንቺን ፍቅረኛ አለሽ ወይ ብዬ ያልጠየቅኩሽ ግን መልሱን ስለፈራው ነው..አለኝ ካልሺኝ ምን እንደምሆን አላውቅም…››
‹‹የእውነት ልንገርህ አለኝ ብልህም ምንም አትሆንም ..ሁሉም ወንዶች አንዱን ሴት ለማሰመን እንዲህ ነው የሚሉት..››
‹‹እወነቴን ነው …ትክክለኛ የሚሰማኝን ነው እየነገርኩሽ ያለውት..እኔ እስከዛሬ የነበሩት የፍቅር ገጠመኞቼ በአጋጣሚ የተከሰቱ ስለነበሩ እንዲህ አይነት ውስብስብ ነገሮችን አላውቃቸውም…››
‹‹ይሁን ግን የእሳትእራትን የፍቅር ታሪክ ታውቃለህ
አላውቅም እስኪ ንገሪኝ…
የአሳት እራት ፍቅረኛው እየመሰለችው ነው አንፖል በበራ ቁጥር ሲሽከረከር እምታየው ….ሴቷ ለፍቅር ዝግጁ ስትሆን የራሷን ብርሀን ከሰውነቷ አመንጭታ በመርጨት ነው ምልክት የምትሰጠው.. በዛ ብርሀን ተስቦ ወደ እሷ ይሄድና ፍቅሩን ያጣጥማል…እና ይሄ የዋህ አፍቃሪ የሚያምር እና የሚንበለበል ብርሀን ባየበት ሁሉ አፍቃሪ ያገኘ እየመሰላው ተንደርድሮ ምስግ ነው…የሚንበለበል እወነተኛ እሷት ውስጥም ቢሆን ከመግባት ስሜቱን መግታት አይችልም…ከገባና ደግሞ ታውቃለህ እርር ክስም ማለቱ አይቀርም …
‹‹እና ምን ለማለት ነው..››አልኳት ምሳሌዋ ግራ አጋብቶኝ
‹‹ከእኔ ጋር የሚጠብቅህ ፍቅር መንደድ እና መክሰምንም ሊያስከትልብህ ይችላል ብዬ እያመከርኩህ ነው››
‹‹ሰምቼሻለው..እሺ በይኝ እንጄ መንደዱም መክሰሉም አያስጨንቀኝም››
‹‹ወደ እኔ ተሳበች እና ወደ ከንፈሬ ተጠጋች…ከበቀደም ለታው መሳም በላይ የጠለቀ..ከዛ በላይ የሚያደነዝነዝና ረጅም ትንፋሸ አስቋራጭ ነበር… ከተቀመጥኩበት ሶፋ ተንሸራትቼ ወለል ላይ በጉልበቴ እስከምንበረከክ ድረስ አቅል የሚያሳጣ አይነት መሳም ነበር የሳመቺኝ….ቆይ የአሳሳም ጥበብን በዩኒቨርሲቲ ደረጃ የሚያሰለጥን ተቋም አለ እንዴ…?.እንደዛ ካልሆነማ እንዲህ አይነትን አደንዛዣ አሳሳም ጥበብ ልትጎናፀፍ ትችላለች፡፡
እንደምንም ገፍታ ነበር ከንፈሯን ከከንፈሬ ያለቀቀችው….
ትንፋሽ ወስጄ እራሴን ካረጋጋው ቡኃላ‹‹እና እሺ አልሺኝ ማለት ነው..ፍቅረኛሞች ሆነናል ማለት ነው››ስል በመንሰፍሰፍ አይነት ስሜት ጠየቅኮት
‹‹በፍጽም አልሆንም….ስብሰባው ተካሄዶ የዚህን የፕሮፖዛል ውጤት ካወቅክ ቡኃላ መልሰህ ምትጠይቀኝ ከሆነ የዛን ጊዜ መልሱን ነግርሀለው››
ምን ማለቷ እንደሆነ ግልጽ ሊሆንልኝ አልቻለም‹‹ፕሮፖዛሉ ውጤትና የእኔ እና አንቺ ጉዳይን ምን አገናኘው…?.››
ተገናኘም አልተገናኘውም ያልኩህን ከማድረግ ውጭ ምንም ምርጫ የለህም…ከፈለክ ወይም ከዛ ቡኃላም ፍቅርህ የሚኖር ከሆነ እዚሁ አጠገብህ ጋር ስለምገኝ ጠይቀኝ….አንድ ሰምንት አይደል የሚቀረው..?ሳምንት መታገስ ያቅትሀል?
ይብላኝ ላንቺ እንጂ እኔስ ጠብቃለው….ስሜቴ በሳምንት የሚጠፋ መስሎሽ ነው…?ከአመታት ቡኃላም ብትይኝም ተመሳሳይ ጥያቄ ነው የምጠይቂኝ….የፍቅር ጓደኛዬ ሁኚ ብዬ…..
‹‹እናያለን…››አለቺኝ
‹‹እናያለን ››አባባሏ አስፈራኝ..የሆነ እሳት በውስጤ እንዲጫር አደረገብኝ….
❤️ፌናን
===
እለቱ እሁድ ነው…ያው ይሄ ዓረፍተ ነገር ብቻ የሚገልፀው ሀሳብ አለ አይደል…….?እለቱ ዕሁድ ከሆነ ብዙ ነገሮች የሚረጋጉበት ቀን ነው ማለት ነው..፡፡ወከባና መተረማማስ በጣም የሚቀንስበት ቀን…የስራ ስልክ ሲያወሩ ከመዋል ተገላግለው ቤተሰብን ወይም ወዳጅ ዘመድን በመደወል እንዴት ናችሁ….? የሚባልበት ቀን …የታመመ የሚጠየቅበት ፤ያዘነን የሚያፅናኑበት ለመንፈስ የቀረበ ስራ የሚሰራበት ቀን፡፡
በቤታችን ውስጥ ነው ምንገኘው..እኔ አባቴና እናቴ ብቻ ..ወይ ሳልነጋራችሁ እናቴ ከውጭ ተመልሳ ከመጣች ዛሬ ሶስተኛ ቀኗ ነው…ደግሞ በዚህ ዘመን ከውጭ ተመልሶ መምጣት ብርቅ ነው እንዴ….? እንደማትሉኝ ተስፋ አደርጋለው…
ለማኛውም የዛሬዋ ቀን ልዩ ቀን እንድትሆን ስለፈለኩ ለሁሉም የቤቱ ሰራተኞች ፍቃድ ሰጥቼያቸዋለው…ግን ከመሄዳቸው በፊት ቀኑን ሙሉ ሲያግዙኝ እና ለእለቱ የሚያስፈልገውን ነገር ሁሉ ሲሰሩልኝ ነው የዋሉት ..ልክ እንደምፈልገው፡፡አሁን ሰዓቱ ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ነው፡፡እናቴ የገዛ መኝታ ቤቷ እንደተኛች ነው..አባቴ ደግሞ ያው እንደልማዱ ላይብረሪው ውስጥ እራሱን ዘግቶ ወይ እያነበበ ነው ወይ ደግሞ እየጻፈ ነው..ብቻ እዛ ነው ያለው፡፡
እኔ ደግሞ የምግብ ጠረጵዛው በምግብ እየሞላው ነው….ልክ እንደጨረስኩና ነገሮች በፈለኮቸው መሰረት እንደተማቻቹና ቀልብ ሳቢ እንደሆኑ ካረጋገጥኩ ቡኃላ ወደእናቴ መኝታ ቤት አመራው
===
..በዝግታ ሳንኳኳ ‹‹ግቡ››የሚል የደከመ ድምጽ ፍቃድ ሰጠኝ… በራፉን ገፋ አድርጌ ገባው…እናቴ አልጋዋን በወረቀት ሞልታ አፍንጫዋ ላይ የሰካችው መነጻር ከፍ ዝቅ አያደረገች አንገቷን አቀርቅራ ወረቀቷቹ ላይ አፍጥጣለች፡፡
‹‹እንዴ እማ የተኛሽ መስሎኝ ነበር እኮ….?››
‹‹በዚህ ሰዓት…….?አረ አልተኛውም››
‹‹ይሄ ሁሉ ወረቀት ምንድ ነው….?››
‹‹የካምፓኒውን የስድስት ወር ሪፖርት ልከውልኝ ነው..እስኑ እያየውት ነው››
‹‹ምነው ተዲያ ተኮሳተርሽ ….….?የጠፋ ነገር አለ እንዴ…….?››
‹‹አይ የለም…..አንድ ብቻ ደስ ያላለኝ ነገር አለ…››
‹‹ልትነግሪኝ ትቺያለሽ….?››
‹‹የሰውዬው ልጅ ስር-አስኪያጅ ከሆነ ምን ያህል ጊዜ ሆነው….?››
‹‹ወር ከሀያ ቀን …››
‹‹እና ምን አድርጎ ነው በዚህ አጭር ጊዜ በጣም የተለየ ትርፍ ሊገኝ የቻለው…….?››
‹‹ጎበዝ ነው ብዬ ነግሬሻለው እኮ….›››አልኳት በፈገግታ ተሞልቼ
‹‹አይ ይሄንን ስራ ጥርሴን የነቀልኩበት ነው..የፈለገ ጎበዝ ቢሆን ሁለት ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ሊታይ የሚችል ልዩነት ማምጣት የሚችል ሰው አይኖርም… ምን አልባት ስራውን በደንብ የሚያውቅና ካምፓኒውን ቀድሞ
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሦስት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍሰሀ
‹‹አሁን ተስማምቼለው››
‹‹አመስግናለው››
‹‹አንድ ነገር ልጠይቅሽ ነበር?››
‹‹አለቃ እኮ ለመጠየቅ ፍቃድ አይጠይቅም››
‹‹አሁን እኮ የስራ ሰዓት አይደለም …ስለዚህ አለቃ ምናምን ብሎ ነገር የለም..››አልኳት
‹‹እሺ ጠይቀኝ››አለቺኝ አቀማጧን እያስተካከለች
‹‹የዛን ቀን እሷን ለማናደድ ብለሽ ያደረግሺውን እንደሆነ ባውቅም ግን በምንም አይነት ከአዕምሮዬ ላወጣው አልቻልኩም….ከአዕመሮዬም ብቻ አይደለም ከህልሜም ማስወገድ አልቻልኩም….ሙሉ አዕምሮዬ በአንቺ ከንፈር ተሞልቷል…ምነው አሁንም አንድ ሰው አበሳጭቷት በሳመቺኝ እያልኩ በየቀኑ ነው የምፀልየው…
‹‹እየቀለድክ ነው አይደል?››አለቺኝ በፈገግታ እና በመኮሳተር መካከል በሚዋልል ስሜት
‹‹አይደለም…››አልኩና እንደምንም እራሴን አደፋፍሬ እጇን በመዶፎቼ መካከል አስገባውና እያሻሸው ንግግሬን ቀጠልኩ..አልተቃወመችኝም፡፡
‹‹አይደለም..እውነቴን ነው…ከህይወቴ አንድ አመት ተቀንሶ ያንን አይነት መሳም አንድ ጊዜ ደግማ ትሳምህ ብባል እስማማለው …እና እባክሽ..››
‹‹እንዲህ አይጠየቅም እኮ …አንድን ሴት እንዴት ልሳምሽ ብለህ ትጠይቃታለህ…ነውር እኮ ነው፡፡ነው ወይስ ውጭ ስለኖርክ ነውር የሚባል ነገር እረስተሀል?››
‹‹እንደዛ ማለቴ አይደለም..ፍቅረኛዬ እንድትሆኚ እየጠየቅኩሽ ነው››
በጥያቄዬ ምንም የመገረም ስሜት አልታየባትም ‹‹ከዛም በፊት ፍቅረኛ አለሽ ወይ ተብሎ ይጠየቃል…በዛ ላይ አንተም ፍቅረኛ አንዳለችህ አውቃለው..ታዲያ ፍቅረኛ ያለችውን ሰው መጥበስ የምፈልግ ይመስልሀል…?››
‹‹የእኔን እርሺው አብቅቶለታል..አንቺን ፍቅረኛ አለሽ ወይ ብዬ ያልጠየቅኩሽ ግን መልሱን ስለፈራው ነው..አለኝ ካልሺኝ ምን እንደምሆን አላውቅም…››
‹‹የእውነት ልንገርህ አለኝ ብልህም ምንም አትሆንም ..ሁሉም ወንዶች አንዱን ሴት ለማሰመን እንዲህ ነው የሚሉት..››
‹‹እወነቴን ነው …ትክክለኛ የሚሰማኝን ነው እየነገርኩሽ ያለውት..እኔ እስከዛሬ የነበሩት የፍቅር ገጠመኞቼ በአጋጣሚ የተከሰቱ ስለነበሩ እንዲህ አይነት ውስብስብ ነገሮችን አላውቃቸውም…››
‹‹ይሁን ግን የእሳትእራትን የፍቅር ታሪክ ታውቃለህ
አላውቅም እስኪ ንገሪኝ…
የአሳት እራት ፍቅረኛው እየመሰለችው ነው አንፖል በበራ ቁጥር ሲሽከረከር እምታየው ….ሴቷ ለፍቅር ዝግጁ ስትሆን የራሷን ብርሀን ከሰውነቷ አመንጭታ በመርጨት ነው ምልክት የምትሰጠው.. በዛ ብርሀን ተስቦ ወደ እሷ ይሄድና ፍቅሩን ያጣጥማል…እና ይሄ የዋህ አፍቃሪ የሚያምር እና የሚንበለበል ብርሀን ባየበት ሁሉ አፍቃሪ ያገኘ እየመሰላው ተንደርድሮ ምስግ ነው…የሚንበለበል እወነተኛ እሷት ውስጥም ቢሆን ከመግባት ስሜቱን መግታት አይችልም…ከገባና ደግሞ ታውቃለህ እርር ክስም ማለቱ አይቀርም …
‹‹እና ምን ለማለት ነው..››አልኳት ምሳሌዋ ግራ አጋብቶኝ
‹‹ከእኔ ጋር የሚጠብቅህ ፍቅር መንደድ እና መክሰምንም ሊያስከትልብህ ይችላል ብዬ እያመከርኩህ ነው››
‹‹ሰምቼሻለው..እሺ በይኝ እንጄ መንደዱም መክሰሉም አያስጨንቀኝም››
‹‹ወደ እኔ ተሳበች እና ወደ ከንፈሬ ተጠጋች…ከበቀደም ለታው መሳም በላይ የጠለቀ..ከዛ በላይ የሚያደነዝነዝና ረጅም ትንፋሸ አስቋራጭ ነበር… ከተቀመጥኩበት ሶፋ ተንሸራትቼ ወለል ላይ በጉልበቴ እስከምንበረከክ ድረስ አቅል የሚያሳጣ አይነት መሳም ነበር የሳመቺኝ….ቆይ የአሳሳም ጥበብን በዩኒቨርሲቲ ደረጃ የሚያሰለጥን ተቋም አለ እንዴ…?.እንደዛ ካልሆነማ እንዲህ አይነትን አደንዛዣ አሳሳም ጥበብ ልትጎናፀፍ ትችላለች፡፡
እንደምንም ገፍታ ነበር ከንፈሯን ከከንፈሬ ያለቀቀችው….
ትንፋሽ ወስጄ እራሴን ካረጋጋው ቡኃላ‹‹እና እሺ አልሺኝ ማለት ነው..ፍቅረኛሞች ሆነናል ማለት ነው››ስል በመንሰፍሰፍ አይነት ስሜት ጠየቅኮት
‹‹በፍጽም አልሆንም….ስብሰባው ተካሄዶ የዚህን የፕሮፖዛል ውጤት ካወቅክ ቡኃላ መልሰህ ምትጠይቀኝ ከሆነ የዛን ጊዜ መልሱን ነግርሀለው››
ምን ማለቷ እንደሆነ ግልጽ ሊሆንልኝ አልቻለም‹‹ፕሮፖዛሉ ውጤትና የእኔ እና አንቺ ጉዳይን ምን አገናኘው…?.››
ተገናኘም አልተገናኘውም ያልኩህን ከማድረግ ውጭ ምንም ምርጫ የለህም…ከፈለክ ወይም ከዛ ቡኃላም ፍቅርህ የሚኖር ከሆነ እዚሁ አጠገብህ ጋር ስለምገኝ ጠይቀኝ….አንድ ሰምንት አይደል የሚቀረው..?ሳምንት መታገስ ያቅትሀል?
ይብላኝ ላንቺ እንጂ እኔስ ጠብቃለው….ስሜቴ በሳምንት የሚጠፋ መስሎሽ ነው…?ከአመታት ቡኃላም ብትይኝም ተመሳሳይ ጥያቄ ነው የምጠይቂኝ….የፍቅር ጓደኛዬ ሁኚ ብዬ…..
‹‹እናያለን…››አለቺኝ
‹‹እናያለን ››አባባሏ አስፈራኝ..የሆነ እሳት በውስጤ እንዲጫር አደረገብኝ….
❤️ፌናን
===
እለቱ እሁድ ነው…ያው ይሄ ዓረፍተ ነገር ብቻ የሚገልፀው ሀሳብ አለ አይደል…….?እለቱ ዕሁድ ከሆነ ብዙ ነገሮች የሚረጋጉበት ቀን ነው ማለት ነው..፡፡ወከባና መተረማማስ በጣም የሚቀንስበት ቀን…የስራ ስልክ ሲያወሩ ከመዋል ተገላግለው ቤተሰብን ወይም ወዳጅ ዘመድን በመደወል እንዴት ናችሁ….? የሚባልበት ቀን …የታመመ የሚጠየቅበት ፤ያዘነን የሚያፅናኑበት ለመንፈስ የቀረበ ስራ የሚሰራበት ቀን፡፡
በቤታችን ውስጥ ነው ምንገኘው..እኔ አባቴና እናቴ ብቻ ..ወይ ሳልነጋራችሁ እናቴ ከውጭ ተመልሳ ከመጣች ዛሬ ሶስተኛ ቀኗ ነው…ደግሞ በዚህ ዘመን ከውጭ ተመልሶ መምጣት ብርቅ ነው እንዴ….? እንደማትሉኝ ተስፋ አደርጋለው…
ለማኛውም የዛሬዋ ቀን ልዩ ቀን እንድትሆን ስለፈለኩ ለሁሉም የቤቱ ሰራተኞች ፍቃድ ሰጥቼያቸዋለው…ግን ከመሄዳቸው በፊት ቀኑን ሙሉ ሲያግዙኝ እና ለእለቱ የሚያስፈልገውን ነገር ሁሉ ሲሰሩልኝ ነው የዋሉት ..ልክ እንደምፈልገው፡፡አሁን ሰዓቱ ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ነው፡፡እናቴ የገዛ መኝታ ቤቷ እንደተኛች ነው..አባቴ ደግሞ ያው እንደልማዱ ላይብረሪው ውስጥ እራሱን ዘግቶ ወይ እያነበበ ነው ወይ ደግሞ እየጻፈ ነው..ብቻ እዛ ነው ያለው፡፡
እኔ ደግሞ የምግብ ጠረጵዛው በምግብ እየሞላው ነው….ልክ እንደጨረስኩና ነገሮች በፈለኮቸው መሰረት እንደተማቻቹና ቀልብ ሳቢ እንደሆኑ ካረጋገጥኩ ቡኃላ ወደእናቴ መኝታ ቤት አመራው
===
..በዝግታ ሳንኳኳ ‹‹ግቡ››የሚል የደከመ ድምጽ ፍቃድ ሰጠኝ… በራፉን ገፋ አድርጌ ገባው…እናቴ አልጋዋን በወረቀት ሞልታ አፍንጫዋ ላይ የሰካችው መነጻር ከፍ ዝቅ አያደረገች አንገቷን አቀርቅራ ወረቀቷቹ ላይ አፍጥጣለች፡፡
‹‹እንዴ እማ የተኛሽ መስሎኝ ነበር እኮ….?››
‹‹በዚህ ሰዓት…….?አረ አልተኛውም››
‹‹ይሄ ሁሉ ወረቀት ምንድ ነው….?››
‹‹የካምፓኒውን የስድስት ወር ሪፖርት ልከውልኝ ነው..እስኑ እያየውት ነው››
‹‹ምነው ተዲያ ተኮሳተርሽ ….….?የጠፋ ነገር አለ እንዴ…….?››
‹‹አይ የለም…..አንድ ብቻ ደስ ያላለኝ ነገር አለ…››
‹‹ልትነግሪኝ ትቺያለሽ….?››
‹‹የሰውዬው ልጅ ስር-አስኪያጅ ከሆነ ምን ያህል ጊዜ ሆነው….?››
‹‹ወር ከሀያ ቀን …››
‹‹እና ምን አድርጎ ነው በዚህ አጭር ጊዜ በጣም የተለየ ትርፍ ሊገኝ የቻለው…….?››
‹‹ጎበዝ ነው ብዬ ነግሬሻለው እኮ….›››አልኳት በፈገግታ ተሞልቼ
‹‹አይ ይሄንን ስራ ጥርሴን የነቀልኩበት ነው..የፈለገ ጎበዝ ቢሆን ሁለት ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ሊታይ የሚችል ልዩነት ማምጣት የሚችል ሰው አይኖርም… ምን አልባት ስራውን በደንብ የሚያውቅና ካምፓኒውን ቀድሞ
👍3
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አራት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
‹‹የዛሬዋን ቀን ለዓመታት ሳስባትና ስዘጋጅባት የነበረች ቀን ነች::በምን አይነት ሁኔታ ላድርገው?እንዴት ቢሆን ይሻላል?ለብዙ ለብዙ ቀናት ሳብሰለስለው ነው የኖርኩት….እና ይቺ ቀን ዛሬ ነች ደቂቃዋም አሁን…..››
‹‹ይሄን ያህል ያሰጨነቀሽ ነገር ምን ቢሆን ነው?››እናቴ ነች
‹‹እዚህ ቤት ያለው ሚስጥር..በእናንተ ሁለታችሁ መካከል ያለው ሚስጥር……የማትጨቃጨቁበት፤ የማትለያበት ሚስጥር….?››
<<እንዴ ልጄ ምን እያልሽ ነው…….?እንዲህ ይባላል እንዴ..….? ሰው እኮ አባትና እናቴ እየተጨቃጨቁና እየተጣሉ እረበሹኝ እያለ ነው ሚሰቃየው..ለምን አልተጣላችሁም ብሎ መጨነቅ ምን የሚሉት ነው….?››አለች እናቴ
አባቴ እንዳቀረቀረ ነው..ምን ለማለት እንደፈለኩ ለእሱ በደንብ እደሚገባው አውቃለው…በጥልቀትም ባይሆን ብዙ ጌዜ እያነሳሳውበት ስጨቀጭቀው ስለነበር ከእናቴ በተሸለ ምን ለማለት እንደፈለኩ ማወቁ ብዙም አይግርምም….
‹‹በመሀከላችሁ የታፈነው ነገር ነዋ የሚያስጨንቀኝ…መቼ ይሆን የሚፈነዳው ….?እያልኩ ሁሌ እንቅልፍ እስካጣ ድረስ አስባለው…ሲፈነዳስ?የፍንዳታው ፍንጥርጣሪ እያዳንዳችንን ምን ያህል ይጎዳናል? ከፍንዳታው ቡኃላም እንዲህ አንድ ላይ በአንድ ቤት ጣሪያ ውስጥ መኖር እንቀጥላለን?ወይስ ብትንትናችን ይወጣል?ሁሌ ያስጨንቀኛል››
‹‹የምን መአት ነው የምታወሪው?እኔና አባትሽን እንዴት ይለያያሉ ብለሽ አሰብሽ….ወደ አባቴ ዞረችና በጥርጣሬና ግራ በመጋባት እየመረመረችው‹‹ምን አልካት…….?››ብላ ጠየቀችውና ወዲያው እራሷ መልሱን መመለስ ጀመረች ‹‹ይቅርታ አንተ ምንም ልትላት እንደማትችል አውቃለው››ብላ መልሳ እኔው ላይ አፈጠጠችብኝ
‹‹ቆይ እናንተ ምንድን ናቹሁ.?››
‹‹ምን ማለት ነው.?ሰዎች ነና››
‹‹አይደለም… የሁለታችሁ ግንኙነት ምን ስያሜ ነው የምትሰጡት?የውጭ ሰዎች እንደሚሉት ባልና ሚስት ናችሁ?.እኔ እንደማውቀው አንድ የጋራ ቤት ተጋርተው የሚኖሩ ደባል ናችሁ…..….የትኛውን ናችሁ….?››
‹‹ተረጋጊ….አባትሽ ለእኔ ምኔ እንደሆነ ታውቂያለሽ .. ….?ባሌ ብቻ እንድልሽ ትፈልጊያለሽ.?ባልማ ማንም ወንድ ባል ሊሆን ይችላል ..እሱ ህይወቴ ነው…፡፡ህይወቴን ለማቆየት በየሰው ሀገር እየተንከራተትኩ ሰውነቴን በየጊዜው እያስተለተልኩ መከራዬን እደማይ ታውቂያለሽ…ለምን ይመስልሻል?ለሀብቴ አይደለም..አሁን ለእኔ ገንዘብ ምን ያደርግልኝ ይመስልሻል?ያማረኝን የማልበላና ያሰኘኝን የማልጠጣ ሰው ነኝ…፡፡እና ለተጨማሪ ጊዜያቶች አብሬው ለመኖር ፍላጎት ባይኖረኝ ኖሮ ምን እንደማደርግ ታውቂያለሽ?አንድ ወርም ሆነ ሁለት ወር ያሰኘኝን በልቼ ያማረኝን ጠጥቼ ይህቺን ህይወት እሰናበት ነበር..ግን ከእሱ ላለመለየት ስለምፈልግ ነው እያዳንዳን የሀኪም ቃል ከፈጣሪዬ ቃል በላይ በየቀኑ እየደገምኩ በዛ መሰረት ለመጓዝ ምጥረው….እና ደግሞ ከእሱ በተጨማሪ አንቺም አለሽ››ንግግሯ ፀጥ አሰኘኝ…ሀሳቤን በታተነቺብኝ….እሷ እንደዛ በስሜት እየተንቀጠቀጠች ስትናገር አባቴ ደግሞ እንባውን በጉንጮቹ እያረገፈ ነበር…እኔ ደግሞ አባቴ ጉንጮች ላይ እንባ ሲወርድ ከማይ አለም አብቅቶላት ምጽአት ቢታወጅ ይቀለኛል….ግን ይገርማችሆል በዚህ የስሜት መጨፍገግ ላይም ሆኜ ምን እንደተዛብኩ ታውቃላችሁ?እማዬ ስለአባቴ የሚሳማትን ተንትና በስተመጨረሻ ደግሞም አንቺም አለሽ ስትል…ለእሷ እኔ የሆን እንጎቻ ነገር እንደሆንኩ ነው የተሰማኝ….ልጣፊ ነገር፡፡
ጥያቄዬን ቀጠልኩ ‹‹እና እንድምትይው አባቴን የምታፈቅሪው ከሆነ እንዴት እንዲህ ትጨክኚበታልሽ? ሀያ አምስት አመት ሙሉ ልጅን አቅፎ ሲተኛ ትንሽ ህሊናሽን አይቆረቁርሽም?ነው ወይስ የአንድ ሚስትን ግዴታና ኃላፊነት አታውቂም.?››
አባቴ ንግግሬ አስጨንቆት ይንቋራጠጣል….
‹‹ስለማታውቂው ነገር አትዘባርቂ…››
‹‹እኮ አሳውቂኝ… የሆነው ነገር ሁሉ እንዴት እንደዛ ሲሆን እንደኖረ የማወቅ መብት አለኝ…ንገሪኝና ልረዳው….ከለበለዛ…!!!››
‹‹ካለበለዛ ምን ….?››አይኗን አጉረጥርጣ ጠየቀቺኝ..ዛሬ ምንም ብትቆጣ …ምንም ያህል ብትኮሳተር ልፈራትና ልሸነፍላት አልችልም ….አባቴ ለመጀመሪያ ጊዜ በመካከላችን ገባ
‹‹ወዴ በቃሽ….ይሄንን ነገር እንዳለ ተይው ››
‹‹አልተወውም አባ::ለአንተ ስል አልተወውም››
‹‹ለእኔ አስበሽ ከሆነ ብትተይው ነው በጣም የምትጠቅሚኝ…እናትሽ እንዳለቺው እስከዛሬም የኖርነው የፈለግነውን አይነት ኑሮ ነው …ሁለታችንም እየሆነ ባለው ነገር ደስተኞች ነን::ስለዚህ አንዳንድ ነገሮችን ባሉበት መተው መልካም ነው..››
‹‹አልተውም አልኩ እኮ..አባ ዛሬ እውነቷን ሳላውቅ አላድርም››
‹‹ተውሽም አልተውሽም እኛ ምንም የምንነግርሽም የምንልሽም ነገር የለም…እና ምን ልታደርጊ ነው?››እናቴ ነች…ምንም ልታመጪ አትቺይም በሚል ስሜት የተናገረቺው
‹‹አፋታችሁለው….አባቴ ካንቺ እንዲፋታና ይሄንን ቤት ለቆልሽ እንዲወጣ አደርጋለው::ከዛ በቅርብ ሌላ ሚስት እድረዋለው::እና ደግሞ ያንን ካምፓኒሽን አልፈልገውም::አንቺንም ጭምር አልፈልግሽም.››
ዝም አለች… ዝም ብሎ ማፈጠጥ ብቻ….የሆነ 5 ደቂቃ ያህል መሰለኝ ዝም ያለችው …ግን የ5 ዓመት ያህል ርዝመት ነበረው..አስፈሪ ምንጩ ከወደሲኦል ሚመስል ዝምታ….እና ከዝምታዋ ወደ መዳካምና አንገቷን ዘንበል አድርጋ ወደጎን ልትወቀድቅ ስትል አባቴ ፈጠን ብሎ ያዘት ..ከዛ ቡኃላ የነበረውን መሯሯጥና መተረማመስ አትጠይቁኝ..በስንት ማናፈስ …መዳሀኒቷ ከመኝታ ቤት አምጥተን አውጠናት በመከራ ነው አይኖቾን የገለጠችው….እና እንደገለጠች…
.‹‹ወደመኝታ ቤቴ ውሰደኝ …ደከመኝ ልተኛ >>አለችው አባቴን ስልምልም ባለ ድምጽ
‹‹እሺ›› አለና ከተቀመጠበት ተነስቶ ሰቅስቆ አቀፋትና የፎቁን ደረጃ ማውጣት ጀመረ….እኔም ቀደምኩና ከፊት ለፊቱ መኝታ ቤቷን ከፈትኩለት …ወደውስጥ ገባውና ብርድልብሱን ገለጥኩለት…. ቀስ ብሎ አስተኛት…
ወደእሷ ተጠጋውና ‹‹እማ ይቅርታ››እጆን አናሳችና ፊቴ ላይ እሰቀምጣ በመዳበስ‹‹‹..በጣም ነው የምወድሽ…የእኔ ልጅ በመሆንሽ ሁል ጊዜ እንደኮራውብሽ ነው…ግን እንድታውቂ የምፈልገው አባትሽን ደግሞ ካቺም በላይ ነው የምወደው››አለቺኝ …ከሳለፉነው ሁኔታ ጋር የማይገናኝና በተቃራኒ የሆነ ልስልስ ያለና ወደልብ የሚሰርግ የፍቅር ንግግር ነው ያሰማቺኝ…በመጠኑ ተንፈስ አልኩ
‹‹በቃ አሁን ሂዱ…ልተኛ ››
‹‹እኔ አብሬሽ ልቆይ››አባቴ ነው ተናጋሪው
‹‹አይሆንም… ካመመኝ መጥሪያውን እጫናለው…››
ባለችው ተስማምተን ለቀንላት ተያይይዘን ወጣን..ወደሳሎን ነበር የተመለስነው….‹‹አባ ውስኪውን መጠጣት ነው የምፈልገው›› አልኩት
ባዶ ብርጭቆ አናሳና ቀዳልኝ …የራሱንም ጎዶሎ ሞላ …..በዝምታ መጠጣት ጀመርን…እኩለ ለሊት ሊቃረብ ሲል ነበር አባቴ ማውራት የጀመረው….
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አራት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
‹‹የዛሬዋን ቀን ለዓመታት ሳስባትና ስዘጋጅባት የነበረች ቀን ነች::በምን አይነት ሁኔታ ላድርገው?እንዴት ቢሆን ይሻላል?ለብዙ ለብዙ ቀናት ሳብሰለስለው ነው የኖርኩት….እና ይቺ ቀን ዛሬ ነች ደቂቃዋም አሁን…..››
‹‹ይሄን ያህል ያሰጨነቀሽ ነገር ምን ቢሆን ነው?››እናቴ ነች
‹‹እዚህ ቤት ያለው ሚስጥር..በእናንተ ሁለታችሁ መካከል ያለው ሚስጥር……የማትጨቃጨቁበት፤ የማትለያበት ሚስጥር….?››
<<እንዴ ልጄ ምን እያልሽ ነው…….?እንዲህ ይባላል እንዴ..….? ሰው እኮ አባትና እናቴ እየተጨቃጨቁና እየተጣሉ እረበሹኝ እያለ ነው ሚሰቃየው..ለምን አልተጣላችሁም ብሎ መጨነቅ ምን የሚሉት ነው….?››አለች እናቴ
አባቴ እንዳቀረቀረ ነው..ምን ለማለት እንደፈለኩ ለእሱ በደንብ እደሚገባው አውቃለው…በጥልቀትም ባይሆን ብዙ ጌዜ እያነሳሳውበት ስጨቀጭቀው ስለነበር ከእናቴ በተሸለ ምን ለማለት እንደፈለኩ ማወቁ ብዙም አይግርምም….
‹‹በመሀከላችሁ የታፈነው ነገር ነዋ የሚያስጨንቀኝ…መቼ ይሆን የሚፈነዳው ….?እያልኩ ሁሌ እንቅልፍ እስካጣ ድረስ አስባለው…ሲፈነዳስ?የፍንዳታው ፍንጥርጣሪ እያዳንዳችንን ምን ያህል ይጎዳናል? ከፍንዳታው ቡኃላም እንዲህ አንድ ላይ በአንድ ቤት ጣሪያ ውስጥ መኖር እንቀጥላለን?ወይስ ብትንትናችን ይወጣል?ሁሌ ያስጨንቀኛል››
‹‹የምን መአት ነው የምታወሪው?እኔና አባትሽን እንዴት ይለያያሉ ብለሽ አሰብሽ….ወደ አባቴ ዞረችና በጥርጣሬና ግራ በመጋባት እየመረመረችው‹‹ምን አልካት…….?››ብላ ጠየቀችውና ወዲያው እራሷ መልሱን መመለስ ጀመረች ‹‹ይቅርታ አንተ ምንም ልትላት እንደማትችል አውቃለው››ብላ መልሳ እኔው ላይ አፈጠጠችብኝ
‹‹ቆይ እናንተ ምንድን ናቹሁ.?››
‹‹ምን ማለት ነው.?ሰዎች ነና››
‹‹አይደለም… የሁለታችሁ ግንኙነት ምን ስያሜ ነው የምትሰጡት?የውጭ ሰዎች እንደሚሉት ባልና ሚስት ናችሁ?.እኔ እንደማውቀው አንድ የጋራ ቤት ተጋርተው የሚኖሩ ደባል ናችሁ…..….የትኛውን ናችሁ….?››
‹‹ተረጋጊ….አባትሽ ለእኔ ምኔ እንደሆነ ታውቂያለሽ .. ….?ባሌ ብቻ እንድልሽ ትፈልጊያለሽ.?ባልማ ማንም ወንድ ባል ሊሆን ይችላል ..እሱ ህይወቴ ነው…፡፡ህይወቴን ለማቆየት በየሰው ሀገር እየተንከራተትኩ ሰውነቴን በየጊዜው እያስተለተልኩ መከራዬን እደማይ ታውቂያለሽ…ለምን ይመስልሻል?ለሀብቴ አይደለም..አሁን ለእኔ ገንዘብ ምን ያደርግልኝ ይመስልሻል?ያማረኝን የማልበላና ያሰኘኝን የማልጠጣ ሰው ነኝ…፡፡እና ለተጨማሪ ጊዜያቶች አብሬው ለመኖር ፍላጎት ባይኖረኝ ኖሮ ምን እንደማደርግ ታውቂያለሽ?አንድ ወርም ሆነ ሁለት ወር ያሰኘኝን በልቼ ያማረኝን ጠጥቼ ይህቺን ህይወት እሰናበት ነበር..ግን ከእሱ ላለመለየት ስለምፈልግ ነው እያዳንዳን የሀኪም ቃል ከፈጣሪዬ ቃል በላይ በየቀኑ እየደገምኩ በዛ መሰረት ለመጓዝ ምጥረው….እና ደግሞ ከእሱ በተጨማሪ አንቺም አለሽ››ንግግሯ ፀጥ አሰኘኝ…ሀሳቤን በታተነቺብኝ….እሷ እንደዛ በስሜት እየተንቀጠቀጠች ስትናገር አባቴ ደግሞ እንባውን በጉንጮቹ እያረገፈ ነበር…እኔ ደግሞ አባቴ ጉንጮች ላይ እንባ ሲወርድ ከማይ አለም አብቅቶላት ምጽአት ቢታወጅ ይቀለኛል….ግን ይገርማችሆል በዚህ የስሜት መጨፍገግ ላይም ሆኜ ምን እንደተዛብኩ ታውቃላችሁ?እማዬ ስለአባቴ የሚሳማትን ተንትና በስተመጨረሻ ደግሞም አንቺም አለሽ ስትል…ለእሷ እኔ የሆን እንጎቻ ነገር እንደሆንኩ ነው የተሰማኝ….ልጣፊ ነገር፡፡
ጥያቄዬን ቀጠልኩ ‹‹እና እንድምትይው አባቴን የምታፈቅሪው ከሆነ እንዴት እንዲህ ትጨክኚበታልሽ? ሀያ አምስት አመት ሙሉ ልጅን አቅፎ ሲተኛ ትንሽ ህሊናሽን አይቆረቁርሽም?ነው ወይስ የአንድ ሚስትን ግዴታና ኃላፊነት አታውቂም.?››
አባቴ ንግግሬ አስጨንቆት ይንቋራጠጣል….
‹‹ስለማታውቂው ነገር አትዘባርቂ…››
‹‹እኮ አሳውቂኝ… የሆነው ነገር ሁሉ እንዴት እንደዛ ሲሆን እንደኖረ የማወቅ መብት አለኝ…ንገሪኝና ልረዳው….ከለበለዛ…!!!››
‹‹ካለበለዛ ምን ….?››አይኗን አጉረጥርጣ ጠየቀቺኝ..ዛሬ ምንም ብትቆጣ …ምንም ያህል ብትኮሳተር ልፈራትና ልሸነፍላት አልችልም ….አባቴ ለመጀመሪያ ጊዜ በመካከላችን ገባ
‹‹ወዴ በቃሽ….ይሄንን ነገር እንዳለ ተይው ››
‹‹አልተወውም አባ::ለአንተ ስል አልተወውም››
‹‹ለእኔ አስበሽ ከሆነ ብትተይው ነው በጣም የምትጠቅሚኝ…እናትሽ እንዳለቺው እስከዛሬም የኖርነው የፈለግነውን አይነት ኑሮ ነው …ሁለታችንም እየሆነ ባለው ነገር ደስተኞች ነን::ስለዚህ አንዳንድ ነገሮችን ባሉበት መተው መልካም ነው..››
‹‹አልተውም አልኩ እኮ..አባ ዛሬ እውነቷን ሳላውቅ አላድርም››
‹‹ተውሽም አልተውሽም እኛ ምንም የምንነግርሽም የምንልሽም ነገር የለም…እና ምን ልታደርጊ ነው?››እናቴ ነች…ምንም ልታመጪ አትቺይም በሚል ስሜት የተናገረቺው
‹‹አፋታችሁለው….አባቴ ካንቺ እንዲፋታና ይሄንን ቤት ለቆልሽ እንዲወጣ አደርጋለው::ከዛ በቅርብ ሌላ ሚስት እድረዋለው::እና ደግሞ ያንን ካምፓኒሽን አልፈልገውም::አንቺንም ጭምር አልፈልግሽም.››
ዝም አለች… ዝም ብሎ ማፈጠጥ ብቻ….የሆነ 5 ደቂቃ ያህል መሰለኝ ዝም ያለችው …ግን የ5 ዓመት ያህል ርዝመት ነበረው..አስፈሪ ምንጩ ከወደሲኦል ሚመስል ዝምታ….እና ከዝምታዋ ወደ መዳካምና አንገቷን ዘንበል አድርጋ ወደጎን ልትወቀድቅ ስትል አባቴ ፈጠን ብሎ ያዘት ..ከዛ ቡኃላ የነበረውን መሯሯጥና መተረማመስ አትጠይቁኝ..በስንት ማናፈስ …መዳሀኒቷ ከመኝታ ቤት አምጥተን አውጠናት በመከራ ነው አይኖቾን የገለጠችው….እና እንደገለጠች…
.‹‹ወደመኝታ ቤቴ ውሰደኝ …ደከመኝ ልተኛ >>አለችው አባቴን ስልምልም ባለ ድምጽ
‹‹እሺ›› አለና ከተቀመጠበት ተነስቶ ሰቅስቆ አቀፋትና የፎቁን ደረጃ ማውጣት ጀመረ….እኔም ቀደምኩና ከፊት ለፊቱ መኝታ ቤቷን ከፈትኩለት …ወደውስጥ ገባውና ብርድልብሱን ገለጥኩለት…. ቀስ ብሎ አስተኛት…
ወደእሷ ተጠጋውና ‹‹እማ ይቅርታ››እጆን አናሳችና ፊቴ ላይ እሰቀምጣ በመዳበስ‹‹‹..በጣም ነው የምወድሽ…የእኔ ልጅ በመሆንሽ ሁል ጊዜ እንደኮራውብሽ ነው…ግን እንድታውቂ የምፈልገው አባትሽን ደግሞ ካቺም በላይ ነው የምወደው››አለቺኝ …ከሳለፉነው ሁኔታ ጋር የማይገናኝና በተቃራኒ የሆነ ልስልስ ያለና ወደልብ የሚሰርግ የፍቅር ንግግር ነው ያሰማቺኝ…በመጠኑ ተንፈስ አልኩ
‹‹በቃ አሁን ሂዱ…ልተኛ ››
‹‹እኔ አብሬሽ ልቆይ››አባቴ ነው ተናጋሪው
‹‹አይሆንም… ካመመኝ መጥሪያውን እጫናለው…››
ባለችው ተስማምተን ለቀንላት ተያይይዘን ወጣን..ወደሳሎን ነበር የተመለስነው….‹‹አባ ውስኪውን መጠጣት ነው የምፈልገው›› አልኩት
ባዶ ብርጭቆ አናሳና ቀዳልኝ …የራሱንም ጎዶሎ ሞላ …..በዝምታ መጠጣት ጀመርን…እኩለ ለሊት ሊቃረብ ሲል ነበር አባቴ ማውራት የጀመረው….
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍3
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አምስት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
❤️ፌናን
===
‹‹….ምን አልባት ትክክል ነሽ››አለኝ
‹‹ምኑን አባ…?››
‹‹እውነቱን የማወቅ መብት አለሽ …እናም ነገርሻለው››
አቀማመጤን አስተካከልኩ..በስካርና በድካም እየታጠፉ የነበሩ ጆሮዎቼን ሲነቃቁና ሲዘረጋጉ ይታወቀኛል…
‹‹በዚህ የታፈነ በምትይው የእኔ እና የእናትሽ ኑሮ ውስጥ ባጣም ተጎጂው እኔ ሳልሆን እናትሽ ነች››
‹‹ማለት…?››
‹‹የመፋታቱን ሀሳብ አንቺ ከመወለደሽም በፊት ሆነ ከተወለድሽ በኃላ ደጋግሜ አቅርቤላት ነበር::ግን ከተለየዋት እራሷን እንድምታጠፋ ደጋግማ ስላስጠነቀቀቺኝ ነው ጥያቄዬን አቁሜ ሀሳቤንም ቀይሬ ዝም ብዬ እንደምታይው መኖር የጀምርኩት..››
‹‹መኖራችሁ ካልቀረ ታዲያ እንደ ሰዎቹ በስርዓት አትኖሩም..…?እንደባልና ሚስት››
‹‹እንደዛ መኖር አንችልም..ታሪኩን ከመጀመሪያ ላስረዳሽ…እናትሽ የአዲስአባ ልጅ ብትሆንም የእናቷ ቤተሰቦች የአንቦ ኦሮሞዎች እንደሆኑ ታውቂያለሽ››የሚናገርውን ነገር ማስረዳት ስለከበደው ዙሪያ ጥምዝ እንደሚሽከረከር ገባኝ ..አሁን እያለኝ ያለው እኮ ያንቺ ሰም መቼስ ፌናን እንደሆነ ታውቂያለሽ አይደል …?ቢጤ ነው፡፡
‹‹…..እና ልክ እኔ እና እናትሽ እንደተጋባን ሰሞን የእናቷ ታናሽ ወንድም ስሙ ቶሌራ ይባላል ..በውድቅት ለሊት በራፋችንን አንኳክቶ ይመጣል….ሲመጣ ሰው አይመስልም…ልብሱ በጭቃና በከሰል ብናኝ በክቷ፤በደረቀ ደም ተለውሶ ነበር…ማንነቱን በመልኩ ሳይሆን በድምጹ ነበር እናትሽ የለየችው…ከዛ አፋፍሰን ወደቤት አስገብተን ሰውነቱን እንዲታጠብ አድርገን ልብሱን ቀይረን የቆሰለውን የተቻለንን ያህል የመጀመሪያ እርዳታ እንዲያገኝ አድርገን አስተኛነው…
‹‹ምን ሆኖ ነበር…?››
ይሄ ልጅ ብሩህ ጭንቅት ያለው ድንቅ ልጅ ነበር…ግን ያው እንደማንኛውም የዘመኑ ወጣት ፓለቲካ ውስጥ እስከአንገቱ ነበር የገባበት::እኔም ሆንኩ እናትሽ እንደው ባጋጣሚ ወይ እኛ ሄደን ወይ ደግሞ እሱ ሊጠይቃና በመጣ ቁጥር ነገሮችን በእርጋታ እንዲይዛቸው ልንመክረው ሞክረን ነበር::አዎ ያቅማችንን ጥረን ነበር:: ግን ያው ታውቂያለሽ አንዳንዴ ፓለቲካ ልክ እንደልክፍት ነው::ሰው ተይ ባለሽ ቁጥር ይበለጥ ይብስብሻል..እና ይሄ የማታውቂው አጎትሽ ሚስጥራዊ የኦነግ አባል ሆኖ በአንቦ ከታማ ይንቀሳቀስ ነበር::.እና ህዝቡን ያነሳሱና መንግስትን በመቃወም ከተማዋን ያምሶታል ::በዛም ምክንያት ብዙ የመንግስትና የግል ንብረት ይወድማል::ከወታደሩም ከኑዋሪውም ከ12 ሰዋች በላይ ይሞታሉ…እና የዚህ ጉዳይ መሪ ይሄ አጎትሽ እንደሆነ በከተማዋ የሚንቀሳቀሱ ደህነነቶች መረጃ ይደርሳቸውና ለሊቱን አድፍጠው ሊይዙት ወደቤት ሄደው ሲከቡት አንዱን ገድሎ ሁለቱን አቁስሎ አጥር ዘሎ ያመልጣል፡፡እድል ከእሱ ጋር ነበረችና ከሰል በጫነ መኪና መሀል በድብቅ ተወሽቆ በለሊት አዲስአበባ ይገባና እንደነገርኩሽ በውድቅት ለሊት ወደእኛ ቤት ይመጣል፡፡
‹‹ታዲያ እንዲት አደረጋችሁ…?››ጥያቄዬን ቀጠልኩ..እኔ መስማት ከምፈልገው የወላጆቼ የጋብቻ ታሪክ ውጭ የሆነ ሀገራዊ እና ፓለቲካዊ ታሪክ ለምን እንደሚነግረኝ ፍንጩን እንኳን ማወቅ አቅቶኝ ፡፡
‹‹ለጊዜው ምን አልባት የእኛ ቤት አስታማማኝ ላይሆን ስለሚችል እና በጥቆማ መጥተው ቢፈትሹ ሊያገኙት ስለሚችሉ ብለን ሊነጋጋ ሲል አቃቂ የሚኖር አንድ ጎደኛዬ ቤት ወስደን አስተኛነውና እዛው ህክምና እንዲያገኝ አድርገን በዘላቂነት ምን ማድረግ እንዳለብን ማሰብ ጀመርን::እናትሽ ለእሱ ያላት ፍቅር ይሄን ያህል ነው ተብሎ ከሚለካው በላይ ነበር…‹አይኔ እያየ አይገሉብኝም ወይም አስርቤት አይጥሉብኝም ብላ በድብቅ ከሀገር ይዛው ልትስወጣው ተነሳች…ቢያንስ እስከድንበር ልትሸኘው::ስሰማ ተቃወምኩ….የተቃወምኩት ለማድረግ ያሰበቸው ነገር አግባብ አይደለም ብዬ አይደለም..ለእሱ ያላትን ፍቅር ስለማውቅ ከዛ በላይም ላድርግለት ብትል የምቃወምበት ምክንያት አይኖረኝም ነበር::ችግሩ ግን በዛን ጊዜ አንቺን እርጉዝ ነበረች::የአራት ወር አርጉዝ ነበረች….‹‹ልጄን ይዘሽ ይሄንን የመሰለ አደጋ ልጋፈጥ ስትይኝ ቁጭ ብዬ አላይሽም ››አልኳት
‹‹ታዲያ ምን ይሁን? ግደሉት ብዬ ብቻውን ልልቀቀው ወይ…?››ብላ ህሊና የሚሞግት ጥያቄ አቀረበችልኝ
‹‹እኔ እስከፈለግሺው ቦታ ይዤው እሄዳለው::ይሄን አደጋ ለመጋፈጥ ካንቺ ይልቅ እኔ እሻላለው››የሚል ሀሳብ አቀረብኩላት
በወቅቱ አሻፈረኝ አይሆንም አለች….‹‹ለምን…?››ያቀረብኩላት ጥያቄ ነበር
‹‹የሆነ ነገር ከሆንክ ምን ብዬ አወራለው ነው ያለቺኝ…‹‹በእኔ ቤተሰብ ይሄንን ያህል መከራ እንድትጋፈጥ አልፈቅድም›› አለቺኝ ….በዚህ ጉዳይ ከሁለት ቀን በላይ ተጨቃጨቅን… ቡኃላ ሽማግሌም መሀላችን ገብቶ በእኔ መሄድ ተስማማን…
ከዛ እኔና አጎትሽ ጨላማን ተገን አድርገን ከአዲስ አበባ በእግር ወጣን .. ግማሽ መንገድ በግር ሲመቻችልን ደግሞ መኪና በመጠቀም ሞያሌ ድረስ ሸኘውት..እዛ ለመድረስ 8 ቀን ነበር የፈጀብን…ከዛ ደላሎች ወደኬንያ እንዲያሸጋግሩት አመቻችቼ…ድንበር ማቋረጡንም ካረጋገጥኩ ቡኃላ በስኬት ተመለስኩ….
‹‹ከዛስ…?››
‹‹ከዛማ…ከከተማ ይዤው ወጥቼ እንዳስመለጥኩት ደህነቶች መረጃ ደርሶቸው ነበረና እቤቴ ሳልገባ ከመንገድ ነው የጠለፉኝ…››
‹‹ወይ አባ አንተን..…?ታዲያ ምን አደረጉህ…?››
‹‹ከዛም አሁን ሙዚዬም ይሁን ተብሎ የተዘጋው ማዕከላዊ አስገቡኝ::በፊልም ላይ አይቼው ማለውቀውን..በመፃፍም ላይ እንኳን ማንበቤን ትዝ የማይለኝን አይነት ስቃይ አሰቃዩኝ::መፈጠሬን እስክጠላ…ሰው ምን አይነት ፍጡር ነው? ብዬ እስክጠይቅ ድረስ……?እግዜር እንዴት እንደዚህ አይነት ፍጡር ይፈጥራል…? ብዬ ሙግት ውስጥ እስክገባ ድረስ….‹‹እግዜር ሰውን በመፍጠሩ ተፀፀተ› የሚትለው መፃፍ ቅዱስ ላይ ከአመታት በፊት ያነበብኩት ጥቅስ ትርጉም በደንብ እስኪገባኝ ድረስ አሰቃዩኝ››
‹‹አንተን..?ስለአስመለጥከው ብቻ…?››
‹‹አዎ …የት ነው ያደረስከው..…?በድርጅቱ ውስጥ አንተስ የነበረህ ኃላፊነት ምንድነው?ውጭ ካሉት ጋር መመሪያ እየተቀበልክ ክፍለሀገር ላሉት አባሎቻችሁ ሽብር እዲፈፅሙ ምታሰማራቸው አንተ ነህ ወይ?ቀጣዩ የድርጅቱ እቅድ ምንድነው?ሌሎችስ እዚህ ከተማ ውስጥ ሆነ በሌሎች የኦሮሚያ ከተሞች ያሉ አባሎቻችሁን ዝርዝር ?›› የማይጠይቁኝ ጥያቄ የለም..እያንዳንዶ ነጠላ ጥያቄ ከብዙ ማሰቃየትና ገሀነማዊ ቶርቸር ቡኃላ ነበር የምትከተለው፡፡እንዴት አንድ ሰው በገዛ ወንድሙ ላይ በዚህ መጠን ሊጨክን ይችላል?ምን ለማግኘት …?ስንት ዓመት በዚህ ምድር ላይ ለመኖር?በፓለቲካ ልዩነት ብቻ የገዛ ወገንን በየምክንያቱ ከዚህም ከዛም እየሰበሰብ በጭለማ ቤት አጉሮ ጥፍር እየነቀሉ እና ብልት ላይ ሀይላንድ እያንጠለጠሉ በማሰቃየት የሚያስገኘው ውጤት ስልጣን ብቻ አይደለም ዘላለማዊነትስ ቢሆን ያዋጣል እንዴ?በእኔ ሚዛን አያዋጣም፡፡ያንን መከራ በራሴ ላይ ደርሶ ከማያቴ በፊት በሰው ልጅ ላይ የሚሰራ የመጨረሻው አሰቃቂ ወንጀል ወይም ግፍ ግድያ ይመስለኝ ነበር…አንድን ሰው ግንባሩን በጥይት አፍርሶ መግደል፡፡ለካ አሱ ቸር እና አዛኝ የሆኑ ወንጀለኞች የሚፈጽሙት ቀላል ከሚባሉ ቅጣቶች ውስጥ የሚካተት ነው?ብዙም ሊጨክኑበት የማይፈልጉትን ሰው በእንክብካቤ የሚያስወግዱበት ዘዴ…ይህንነ አሁን እየተነጋርኩ ያለውትን ንግግር ሴሜቱ በትክክል የሚሰማው ተመሳሳዩ ነገር የደረሰበት ሰው ብቻ ነው፡ግን ከሰው ውጭ ሌላ ፍጡር በራሱ ፍጡር ላይ ይሄንን ያህል ይጨክናል?ለምሳሌ አንበሳ በአንበሳ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አምስት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
❤️ፌናን
===
‹‹….ምን አልባት ትክክል ነሽ››አለኝ
‹‹ምኑን አባ…?››
‹‹እውነቱን የማወቅ መብት አለሽ …እናም ነገርሻለው››
አቀማመጤን አስተካከልኩ..በስካርና በድካም እየታጠፉ የነበሩ ጆሮዎቼን ሲነቃቁና ሲዘረጋጉ ይታወቀኛል…
‹‹በዚህ የታፈነ በምትይው የእኔ እና የእናትሽ ኑሮ ውስጥ ባጣም ተጎጂው እኔ ሳልሆን እናትሽ ነች››
‹‹ማለት…?››
‹‹የመፋታቱን ሀሳብ አንቺ ከመወለደሽም በፊት ሆነ ከተወለድሽ በኃላ ደጋግሜ አቅርቤላት ነበር::ግን ከተለየዋት እራሷን እንድምታጠፋ ደጋግማ ስላስጠነቀቀቺኝ ነው ጥያቄዬን አቁሜ ሀሳቤንም ቀይሬ ዝም ብዬ እንደምታይው መኖር የጀምርኩት..››
‹‹መኖራችሁ ካልቀረ ታዲያ እንደ ሰዎቹ በስርዓት አትኖሩም..…?እንደባልና ሚስት››
‹‹እንደዛ መኖር አንችልም..ታሪኩን ከመጀመሪያ ላስረዳሽ…እናትሽ የአዲስአባ ልጅ ብትሆንም የእናቷ ቤተሰቦች የአንቦ ኦሮሞዎች እንደሆኑ ታውቂያለሽ››የሚናገርውን ነገር ማስረዳት ስለከበደው ዙሪያ ጥምዝ እንደሚሽከረከር ገባኝ ..አሁን እያለኝ ያለው እኮ ያንቺ ሰም መቼስ ፌናን እንደሆነ ታውቂያለሽ አይደል …?ቢጤ ነው፡፡
‹‹…..እና ልክ እኔ እና እናትሽ እንደተጋባን ሰሞን የእናቷ ታናሽ ወንድም ስሙ ቶሌራ ይባላል ..በውድቅት ለሊት በራፋችንን አንኳክቶ ይመጣል….ሲመጣ ሰው አይመስልም…ልብሱ በጭቃና በከሰል ብናኝ በክቷ፤በደረቀ ደም ተለውሶ ነበር…ማንነቱን በመልኩ ሳይሆን በድምጹ ነበር እናትሽ የለየችው…ከዛ አፋፍሰን ወደቤት አስገብተን ሰውነቱን እንዲታጠብ አድርገን ልብሱን ቀይረን የቆሰለውን የተቻለንን ያህል የመጀመሪያ እርዳታ እንዲያገኝ አድርገን አስተኛነው…
‹‹ምን ሆኖ ነበር…?››
ይሄ ልጅ ብሩህ ጭንቅት ያለው ድንቅ ልጅ ነበር…ግን ያው እንደማንኛውም የዘመኑ ወጣት ፓለቲካ ውስጥ እስከአንገቱ ነበር የገባበት::እኔም ሆንኩ እናትሽ እንደው ባጋጣሚ ወይ እኛ ሄደን ወይ ደግሞ እሱ ሊጠይቃና በመጣ ቁጥር ነገሮችን በእርጋታ እንዲይዛቸው ልንመክረው ሞክረን ነበር::አዎ ያቅማችንን ጥረን ነበር:: ግን ያው ታውቂያለሽ አንዳንዴ ፓለቲካ ልክ እንደልክፍት ነው::ሰው ተይ ባለሽ ቁጥር ይበለጥ ይብስብሻል..እና ይሄ የማታውቂው አጎትሽ ሚስጥራዊ የኦነግ አባል ሆኖ በአንቦ ከታማ ይንቀሳቀስ ነበር::.እና ህዝቡን ያነሳሱና መንግስትን በመቃወም ከተማዋን ያምሶታል ::በዛም ምክንያት ብዙ የመንግስትና የግል ንብረት ይወድማል::ከወታደሩም ከኑዋሪውም ከ12 ሰዋች በላይ ይሞታሉ…እና የዚህ ጉዳይ መሪ ይሄ አጎትሽ እንደሆነ በከተማዋ የሚንቀሳቀሱ ደህነነቶች መረጃ ይደርሳቸውና ለሊቱን አድፍጠው ሊይዙት ወደቤት ሄደው ሲከቡት አንዱን ገድሎ ሁለቱን አቁስሎ አጥር ዘሎ ያመልጣል፡፡እድል ከእሱ ጋር ነበረችና ከሰል በጫነ መኪና መሀል በድብቅ ተወሽቆ በለሊት አዲስአበባ ይገባና እንደነገርኩሽ በውድቅት ለሊት ወደእኛ ቤት ይመጣል፡፡
‹‹ታዲያ እንዲት አደረጋችሁ…?››ጥያቄዬን ቀጠልኩ..እኔ መስማት ከምፈልገው የወላጆቼ የጋብቻ ታሪክ ውጭ የሆነ ሀገራዊ እና ፓለቲካዊ ታሪክ ለምን እንደሚነግረኝ ፍንጩን እንኳን ማወቅ አቅቶኝ ፡፡
‹‹ለጊዜው ምን አልባት የእኛ ቤት አስታማማኝ ላይሆን ስለሚችል እና በጥቆማ መጥተው ቢፈትሹ ሊያገኙት ስለሚችሉ ብለን ሊነጋጋ ሲል አቃቂ የሚኖር አንድ ጎደኛዬ ቤት ወስደን አስተኛነውና እዛው ህክምና እንዲያገኝ አድርገን በዘላቂነት ምን ማድረግ እንዳለብን ማሰብ ጀመርን::እናትሽ ለእሱ ያላት ፍቅር ይሄን ያህል ነው ተብሎ ከሚለካው በላይ ነበር…‹አይኔ እያየ አይገሉብኝም ወይም አስርቤት አይጥሉብኝም ብላ በድብቅ ከሀገር ይዛው ልትስወጣው ተነሳች…ቢያንስ እስከድንበር ልትሸኘው::ስሰማ ተቃወምኩ….የተቃወምኩት ለማድረግ ያሰበቸው ነገር አግባብ አይደለም ብዬ አይደለም..ለእሱ ያላትን ፍቅር ስለማውቅ ከዛ በላይም ላድርግለት ብትል የምቃወምበት ምክንያት አይኖረኝም ነበር::ችግሩ ግን በዛን ጊዜ አንቺን እርጉዝ ነበረች::የአራት ወር አርጉዝ ነበረች….‹‹ልጄን ይዘሽ ይሄንን የመሰለ አደጋ ልጋፈጥ ስትይኝ ቁጭ ብዬ አላይሽም ››አልኳት
‹‹ታዲያ ምን ይሁን? ግደሉት ብዬ ብቻውን ልልቀቀው ወይ…?››ብላ ህሊና የሚሞግት ጥያቄ አቀረበችልኝ
‹‹እኔ እስከፈለግሺው ቦታ ይዤው እሄዳለው::ይሄን አደጋ ለመጋፈጥ ካንቺ ይልቅ እኔ እሻላለው››የሚል ሀሳብ አቀረብኩላት
በወቅቱ አሻፈረኝ አይሆንም አለች….‹‹ለምን…?››ያቀረብኩላት ጥያቄ ነበር
‹‹የሆነ ነገር ከሆንክ ምን ብዬ አወራለው ነው ያለቺኝ…‹‹በእኔ ቤተሰብ ይሄንን ያህል መከራ እንድትጋፈጥ አልፈቅድም›› አለቺኝ ….በዚህ ጉዳይ ከሁለት ቀን በላይ ተጨቃጨቅን… ቡኃላ ሽማግሌም መሀላችን ገብቶ በእኔ መሄድ ተስማማን…
ከዛ እኔና አጎትሽ ጨላማን ተገን አድርገን ከአዲስ አበባ በእግር ወጣን .. ግማሽ መንገድ በግር ሲመቻችልን ደግሞ መኪና በመጠቀም ሞያሌ ድረስ ሸኘውት..እዛ ለመድረስ 8 ቀን ነበር የፈጀብን…ከዛ ደላሎች ወደኬንያ እንዲያሸጋግሩት አመቻችቼ…ድንበር ማቋረጡንም ካረጋገጥኩ ቡኃላ በስኬት ተመለስኩ….
‹‹ከዛስ…?››
‹‹ከዛማ…ከከተማ ይዤው ወጥቼ እንዳስመለጥኩት ደህነቶች መረጃ ደርሶቸው ነበረና እቤቴ ሳልገባ ከመንገድ ነው የጠለፉኝ…››
‹‹ወይ አባ አንተን..…?ታዲያ ምን አደረጉህ…?››
‹‹ከዛም አሁን ሙዚዬም ይሁን ተብሎ የተዘጋው ማዕከላዊ አስገቡኝ::በፊልም ላይ አይቼው ማለውቀውን..በመፃፍም ላይ እንኳን ማንበቤን ትዝ የማይለኝን አይነት ስቃይ አሰቃዩኝ::መፈጠሬን እስክጠላ…ሰው ምን አይነት ፍጡር ነው? ብዬ እስክጠይቅ ድረስ……?እግዜር እንዴት እንደዚህ አይነት ፍጡር ይፈጥራል…? ብዬ ሙግት ውስጥ እስክገባ ድረስ….‹‹እግዜር ሰውን በመፍጠሩ ተፀፀተ› የሚትለው መፃፍ ቅዱስ ላይ ከአመታት በፊት ያነበብኩት ጥቅስ ትርጉም በደንብ እስኪገባኝ ድረስ አሰቃዩኝ››
‹‹አንተን..?ስለአስመለጥከው ብቻ…?››
‹‹አዎ …የት ነው ያደረስከው..…?በድርጅቱ ውስጥ አንተስ የነበረህ ኃላፊነት ምንድነው?ውጭ ካሉት ጋር መመሪያ እየተቀበልክ ክፍለሀገር ላሉት አባሎቻችሁ ሽብር እዲፈፅሙ ምታሰማራቸው አንተ ነህ ወይ?ቀጣዩ የድርጅቱ እቅድ ምንድነው?ሌሎችስ እዚህ ከተማ ውስጥ ሆነ በሌሎች የኦሮሚያ ከተሞች ያሉ አባሎቻችሁን ዝርዝር ?›› የማይጠይቁኝ ጥያቄ የለም..እያንዳንዶ ነጠላ ጥያቄ ከብዙ ማሰቃየትና ገሀነማዊ ቶርቸር ቡኃላ ነበር የምትከተለው፡፡እንዴት አንድ ሰው በገዛ ወንድሙ ላይ በዚህ መጠን ሊጨክን ይችላል?ምን ለማግኘት …?ስንት ዓመት በዚህ ምድር ላይ ለመኖር?በፓለቲካ ልዩነት ብቻ የገዛ ወገንን በየምክንያቱ ከዚህም ከዛም እየሰበሰብ በጭለማ ቤት አጉሮ ጥፍር እየነቀሉ እና ብልት ላይ ሀይላንድ እያንጠለጠሉ በማሰቃየት የሚያስገኘው ውጤት ስልጣን ብቻ አይደለም ዘላለማዊነትስ ቢሆን ያዋጣል እንዴ?በእኔ ሚዛን አያዋጣም፡፡ያንን መከራ በራሴ ላይ ደርሶ ከማያቴ በፊት በሰው ልጅ ላይ የሚሰራ የመጨረሻው አሰቃቂ ወንጀል ወይም ግፍ ግድያ ይመስለኝ ነበር…አንድን ሰው ግንባሩን በጥይት አፍርሶ መግደል፡፡ለካ አሱ ቸር እና አዛኝ የሆኑ ወንጀለኞች የሚፈጽሙት ቀላል ከሚባሉ ቅጣቶች ውስጥ የሚካተት ነው?ብዙም ሊጨክኑበት የማይፈልጉትን ሰው በእንክብካቤ የሚያስወግዱበት ዘዴ…ይህንነ አሁን እየተነጋርኩ ያለውትን ንግግር ሴሜቱ በትክክል የሚሰማው ተመሳሳዩ ነገር የደረሰበት ሰው ብቻ ነው፡ግን ከሰው ውጭ ሌላ ፍጡር በራሱ ፍጡር ላይ ይሄንን ያህል ይጨክናል?ለምሳሌ አንበሳ በአንበሳ
👍5
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስድስት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍሰሀ
===
በህይወቴ በጣም የተፈተንኩበት አንድ ሳምንት ነው እያሳለፍኩ ያለውት…በጣም አስጨናቂና ትንፋሽ የሚያሳጣ አይነት ሳምንት…. ደግነቱ ስራዎቼን ቀድሜ ማጠናቀቄ በጀኝ እንጂ በዚህ አይነት የጨፈገገ ስሜት እንዴት እሰራው እንደነበር ማሰቡ እራሱ ይከብደኛል ፡፡
ምክንያቱ አለመኖሯ ነው……ይሄው አይኖቼ አይኖቾን ካዩ አንድ ድፍን ሳምንት ተቆጠረ…የቤተሰብ ጉዳይ ስላጋጠመኝ ድሬደዋ ሄጃለው ነበር ያለቺኝ…እኔማ ደርሶ መልስም ቢሆን ልምጠና አንዴ አይቼሽ ልመለስ ብያት ነበር..ብትመጣም አታጋኘኝምና አትልፋ.. ይልቅ ዝግጅትህ ላይ አተኩር ፤ፍልሚያውን በድል ከተወጣህ ቡኃላ ደውልልኝ..እስከዛ እኔም እዚህ ያለውን ነገር ጨርስና እመለሳለው ካልሆነም ያለውበትን አድራሻ እነግርህና ትመጣለህ›› ስላለቺኝ… ምርጫ አጥቼ በናፍቆቷ እየተሰቃየሁ ባለቺው ተስማምቼ እጄን አጣጥፌ ቁጭ አላልኩም፡፡ምናልባት ድሬደዋ የሄደችበትን አድራሻዋን ባገኝ ብዬ ከሶስት ቀን በፊት በፊት ትሰራበት ወደነበረ ከዚህ በፊትም እንዲህ በጠፋችበት ጊዜ ወደአገኘዋት ሜክሲኮ መጽሀፍት ቤት ሄጄ ነበር ……መኪናዬን ቦታ አስይዤ በማቆም ወደ መጻሀፍ መደብሩ አመራው::ሁለት በአስራዎቹ መጨረሻ ዕድሜ ላይ የሚገኙ ወጣቶች ናቸው ያሉት…አንደኛው ደንበኛ እያስተናገደ ስለነበረ ነፃ ወደሆነው ተጠጋሁ…
‹‹ምን መፃሀፍ ልስጥህ…..? ››አለኝ… እዚህ ቤት መፃሀፍ እንጂ ሴት ፍለጋ የሚመጣ ሰው ይኖራል ብሎ ስላልገመተ መሰለኝ ቀጥታ ስለመፃፍ የጠየቀኝ ፡፡
‹‹ፌናንን ፈልጌ ነበር..ሰሞኑን መጥታ ነበር?››
‹‹አይ ቆየች.. አስራ አምስት ቀን ሆኗታል››
‹‹ጓደኛዋ ነኝ …ማለቴ የመስሪያ ቤት ጎደኛዋ..ስልኳ አልሰራ ብሎኝ ነው ..ቢሮ ደግሞ እሷ ብቻ የምትሰራው አፋጣኝ ስራ ነበር..እና እቤቷን ልትጠቁመኝ ትችላለህ፡፡››
‹‹እቤታቸው ቤቴል አካባቢ እንደሆነ ነው እንጂ ትክክለኛውን ቦታ አላውቅም…ግን ትንሽ ብትጠብቅ እኮ ጋሼ ስለሚመጡ ትጠይቃቸዋለህ››
‹‹ጋሼ ማነው…..?››
‹‹አባቷ ናቸዋ››
‹‹እርግጠኛ ነህ ይመጣሉ?››
‹‹አዎ እንደሚመጡ ደውለው ነግረውኛል፡፡››
‹‹አይ እንደዛ ከሆነማ አሪፍ ነው.. እጠብቃቸዋለው ››አልኩ…ግን ደግሞ ወዲያው ሌላ ጥያቄ በውስጤ ተፈጠረ…‹‹ከአባቷ በጣም ትግባባላችሁ ማለት ነው?››ጠየቅኩት
‹‹እንዴ አሰሪዬ አይደሉ ለምን አንግባባም?››ሲለኝ እየገባኝ የመሰለኝ ጉዳይ መልሶ ድንግርግር አለብኝ
‹‹አሰሪዬ ስትል..…..?››
‹‹ይሄ የመፅሀፍ መደብር እኮ የእሷቸው ነው …ሌላም ቦታዎችም አላቸው››ሊያብራራልኝ ሞከረ…
‹‹ይሄ መጻሀፍ ቤት የፌናን አባት ነው?››
‹‹አዎ ››አለኝ ይሄን ሁሉ ሳታውቅ ነው እንዴ ጓደኛዋ ነኝ የምትለው በሚል ስሜት ..
ገረመኝ..ከዚህ በፊት እዚህ ባገኘዋት ጊዜ በትርፍ ጊዜዋ ተቀጥራ እንደምትሰራ ነበር የነገረቺኝ ፡፡ይሄ ሁሉ መዋሸት ለምን አስፈለገ?
በውስጤ የተፈጠረ የመደነቅ ጥያቄ ነበር…
‹‹አባቷ ጎበዝ ናቸው ማለት ነው?››አልኩት ልጁን….ስለእዚህች ሚስጥር ስለሆነች ልጅ ሌላ ተጨማሪ ሚስጥር እንዲነግረኝ በመፈለግ ለመጎትጎት ፈልጌ
‹‹እንዴ…!!!››አለና ዝም አለ
‹‹ምነው…..?››
‹‹ጋሼን አታውቃቸውም እንዴ?››
ነገሮች እንዳይበላሹ ዋሸውት‹‹አውቃቸዋለው››
‹‹አይ ጎበዝ ናቸው ስትል ገርሞኝ ነው››
‹‹ለምን ይገርምሀል…..?››
‹‹ጎበዝ ናቸው ማለት ነው ስትል በጉብዝናቸው ጥርጣሬ ያለብህ ይመስላል..እሷቸው እኮ ይሄንን የከፈቱት እኛንም ለመርዳት ነው እንጂ ጎበዝ ለመሆን አይደለም…አስተማሪነታቸው እና ደራሲነታቸው ብቻ ለጉብዝናቸው በቂ ነው››
‹‹እሱስ እወነትህን ነው››አልኩት ልክ አስተማሪም ሆነ ደራሲ መሆናቸውን እንደማውቅ ሆኜ…‹‹ አሀ የአስተማሪና የደራሲ ልጅ ነሻ?.ለዛ ነው ነገሮችን መበታተን እና መልሶ መሰብሰብ ሚያስደስታት….አሁን ገባኝ››ብዬ በወስጤ አብሰለሰልኩ…አሁን በዘዴ ብዙ ነገር እያወቅኩ ነው…ይበልጥ ለማወቅ ሌላ ዘዴ መጣልኝ፡፡
‹‹እስቲ የእሳቸው መፃሀፍ ይኖራል..…..?››
‹‹የቱን ልስጥህ……..?››
‹‹ሁሉንም የለኝም… አሪፍ ያልከውን …››
በፈገግታ ከዚህም ከዛም አየመዘዘ አምስት መፃሀፍ እጄ ላይ ዘረገፈ…
‹‹እንዴ…? ይሄን ሁሉ እንደፃፍ አላውቅም ነበር››መደነቄን መደበቅ አልቻልኩም
‹‹11 መፃሀፍ እኮ ነው ያላቸው..ይበዛብሀል ብዬ ነው የቅርቦቹን ብቻ መርጬ የሰጠውህ…. ልጁን እያዳመጥኩ ግን ደግሞ መፃሀፎቹን እያገላበጥኩ በማየት ላይ ሳለው አይኖቼ የመፃፍ ጀርባ ላይ የታተመ የደራሲው ፎቶ ላይ አረፈ ..ደነገጥኩ…. እባብ ሱሬው ውስጥ እንደገባበት ሰው አይነት ነው አደነጋገጤ ..ሰውዬውን አውቃቸዋለው፡፡ሌላውን መፃሀፍ ጀርባ ገለበጥኩ ፎቶ የለውም……ሌላውን ገለጥኩ አዎ እራሳቸው ናቸው…ከመቀመጫዬ ተነሳው….
‹‹ሂሳቡ ስንት ነው…..?››
‹‹የየትኛው…..? ››
‹‹የሁሉም››
መፃሀፎቹን ከእጆቼ ወሰደና ጀርባቸው ላይ ያለውን ዋጋ ደምሮ ነገረኝ..ከፍዬ መልስም ሳልጠይቅ ወጣሁ…
‹‹እንዴ አትጠብቃቸውም……..?››ልጁ ግራ ተጋብቶ ጠየቀኝ
‹‹ተመልሼ መጣለው ››ቻው..ተንደርድሬ መኪናዬ ውስጥ ገባውና አሁንም ድጋሜ የመጽሀፉን ጀርባ ላይ ያለውን ፎቶ አየሁት…ንዴትም ደስታም የተቀላቀለበት ስሜት ነው ተሰማኝ፡፡እኚን እኮ ነው ሹገር ዳዲዋ እንደሆኑ የነገረቺኝ ፡፡ለካ አባቷ ናቸው…?ሲያስደስት..ግን እንዴት ነው የምታስበኝ ?ይሄን ሁሉ ውሸት እንዴት ስትዋሸኝ ትከርማለች……? ስለእሷ የማላውቀው ሌላስ ምን አለ……?ይህቺ ልጅ እስከመቼ ነው እየራቀቀችብኝና እየጠለቀችብኝ የምትሄደው…?ለማንኛውም በእሷ በመታለሌ ከተበሳጨውት ይበልጥ ሹገር ዳዲዋ ናቸው ብዬ ለቀናት በንዴት ስንጨረጨር እና እንቅልፍ ሳጣበት የነበረው ጉዳይ ውሸት ሆኖ አባቷ በመሆናቸው የተደሰትኩት በእጥፍ ይበልጣል…
ከዛን ቡኃላም ስልኳ አይሰራም…ካላጋነንኩት ለመቶ የቀረብ መልዕክቶችን ልኬላታለሁ…ምንአልባት ከከፈተችው ወዲያው እድትደውልልኝ በማለት..ግን አንደዛ አልሆነም…ይገርማችሆል አንዳንዴ በውድቅት ለሊት ስምንትና ዘጠኝ ሰዓት ከእንቅልፌ ድንገት በርግጌ እነሳና ስልኬን አንስቼ እሞክርላታለው….ግን የተለወጠ ነገር አልነበረም፡፡ዛሬ ግን በተቻለኝ መጠን ስለእሷ ከማሰብ እራሴን መግታትና እና ትኩረቴን ሰብሰብ አድርጌ ስለፍፃሜው ጦርነት ብቻ ማሰብ ነው የምፈልገው፡፡ቀኗ ዛሬ ነች…ማንነቴን ለአባቴም ለሌላውም ሰው የማሳይበት ቀን፡፡ይህቺን ቀን አብራኝ ለወራት የለፋችው ፊናን ከጎኔ ብትሆን ኖሮ የበለጠ ጠንካራ የበለጠ ልበሙሉ እሆን ነበር…አይ የኔ ነገር አሁንም መልሼ ወደእሷ ወሰድኮችሁ አይደል፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስድስት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍሰሀ
===
በህይወቴ በጣም የተፈተንኩበት አንድ ሳምንት ነው እያሳለፍኩ ያለውት…በጣም አስጨናቂና ትንፋሽ የሚያሳጣ አይነት ሳምንት…. ደግነቱ ስራዎቼን ቀድሜ ማጠናቀቄ በጀኝ እንጂ በዚህ አይነት የጨፈገገ ስሜት እንዴት እሰራው እንደነበር ማሰቡ እራሱ ይከብደኛል ፡፡
ምክንያቱ አለመኖሯ ነው……ይሄው አይኖቼ አይኖቾን ካዩ አንድ ድፍን ሳምንት ተቆጠረ…የቤተሰብ ጉዳይ ስላጋጠመኝ ድሬደዋ ሄጃለው ነበር ያለቺኝ…እኔማ ደርሶ መልስም ቢሆን ልምጠና አንዴ አይቼሽ ልመለስ ብያት ነበር..ብትመጣም አታጋኘኝምና አትልፋ.. ይልቅ ዝግጅትህ ላይ አተኩር ፤ፍልሚያውን በድል ከተወጣህ ቡኃላ ደውልልኝ..እስከዛ እኔም እዚህ ያለውን ነገር ጨርስና እመለሳለው ካልሆነም ያለውበትን አድራሻ እነግርህና ትመጣለህ›› ስላለቺኝ… ምርጫ አጥቼ በናፍቆቷ እየተሰቃየሁ ባለቺው ተስማምቼ እጄን አጣጥፌ ቁጭ አላልኩም፡፡ምናልባት ድሬደዋ የሄደችበትን አድራሻዋን ባገኝ ብዬ ከሶስት ቀን በፊት በፊት ትሰራበት ወደነበረ ከዚህ በፊትም እንዲህ በጠፋችበት ጊዜ ወደአገኘዋት ሜክሲኮ መጽሀፍት ቤት ሄጄ ነበር ……መኪናዬን ቦታ አስይዤ በማቆም ወደ መጻሀፍ መደብሩ አመራው::ሁለት በአስራዎቹ መጨረሻ ዕድሜ ላይ የሚገኙ ወጣቶች ናቸው ያሉት…አንደኛው ደንበኛ እያስተናገደ ስለነበረ ነፃ ወደሆነው ተጠጋሁ…
‹‹ምን መፃሀፍ ልስጥህ…..? ››አለኝ… እዚህ ቤት መፃሀፍ እንጂ ሴት ፍለጋ የሚመጣ ሰው ይኖራል ብሎ ስላልገመተ መሰለኝ ቀጥታ ስለመፃፍ የጠየቀኝ ፡፡
‹‹ፌናንን ፈልጌ ነበር..ሰሞኑን መጥታ ነበር?››
‹‹አይ ቆየች.. አስራ አምስት ቀን ሆኗታል››
‹‹ጓደኛዋ ነኝ …ማለቴ የመስሪያ ቤት ጎደኛዋ..ስልኳ አልሰራ ብሎኝ ነው ..ቢሮ ደግሞ እሷ ብቻ የምትሰራው አፋጣኝ ስራ ነበር..እና እቤቷን ልትጠቁመኝ ትችላለህ፡፡››
‹‹እቤታቸው ቤቴል አካባቢ እንደሆነ ነው እንጂ ትክክለኛውን ቦታ አላውቅም…ግን ትንሽ ብትጠብቅ እኮ ጋሼ ስለሚመጡ ትጠይቃቸዋለህ››
‹‹ጋሼ ማነው…..?››
‹‹አባቷ ናቸዋ››
‹‹እርግጠኛ ነህ ይመጣሉ?››
‹‹አዎ እንደሚመጡ ደውለው ነግረውኛል፡፡››
‹‹አይ እንደዛ ከሆነማ አሪፍ ነው.. እጠብቃቸዋለው ››አልኩ…ግን ደግሞ ወዲያው ሌላ ጥያቄ በውስጤ ተፈጠረ…‹‹ከአባቷ በጣም ትግባባላችሁ ማለት ነው?››ጠየቅኩት
‹‹እንዴ አሰሪዬ አይደሉ ለምን አንግባባም?››ሲለኝ እየገባኝ የመሰለኝ ጉዳይ መልሶ ድንግርግር አለብኝ
‹‹አሰሪዬ ስትል..…..?››
‹‹ይሄ የመፅሀፍ መደብር እኮ የእሷቸው ነው …ሌላም ቦታዎችም አላቸው››ሊያብራራልኝ ሞከረ…
‹‹ይሄ መጻሀፍ ቤት የፌናን አባት ነው?››
‹‹አዎ ››አለኝ ይሄን ሁሉ ሳታውቅ ነው እንዴ ጓደኛዋ ነኝ የምትለው በሚል ስሜት ..
ገረመኝ..ከዚህ በፊት እዚህ ባገኘዋት ጊዜ በትርፍ ጊዜዋ ተቀጥራ እንደምትሰራ ነበር የነገረቺኝ ፡፡ይሄ ሁሉ መዋሸት ለምን አስፈለገ?
በውስጤ የተፈጠረ የመደነቅ ጥያቄ ነበር…
‹‹አባቷ ጎበዝ ናቸው ማለት ነው?››አልኩት ልጁን….ስለእዚህች ሚስጥር ስለሆነች ልጅ ሌላ ተጨማሪ ሚስጥር እንዲነግረኝ በመፈለግ ለመጎትጎት ፈልጌ
‹‹እንዴ…!!!››አለና ዝም አለ
‹‹ምነው…..?››
‹‹ጋሼን አታውቃቸውም እንዴ?››
ነገሮች እንዳይበላሹ ዋሸውት‹‹አውቃቸዋለው››
‹‹አይ ጎበዝ ናቸው ስትል ገርሞኝ ነው››
‹‹ለምን ይገርምሀል…..?››
‹‹ጎበዝ ናቸው ማለት ነው ስትል በጉብዝናቸው ጥርጣሬ ያለብህ ይመስላል..እሷቸው እኮ ይሄንን የከፈቱት እኛንም ለመርዳት ነው እንጂ ጎበዝ ለመሆን አይደለም…አስተማሪነታቸው እና ደራሲነታቸው ብቻ ለጉብዝናቸው በቂ ነው››
‹‹እሱስ እወነትህን ነው››አልኩት ልክ አስተማሪም ሆነ ደራሲ መሆናቸውን እንደማውቅ ሆኜ…‹‹ አሀ የአስተማሪና የደራሲ ልጅ ነሻ?.ለዛ ነው ነገሮችን መበታተን እና መልሶ መሰብሰብ ሚያስደስታት….አሁን ገባኝ››ብዬ በወስጤ አብሰለሰልኩ…አሁን በዘዴ ብዙ ነገር እያወቅኩ ነው…ይበልጥ ለማወቅ ሌላ ዘዴ መጣልኝ፡፡
‹‹እስቲ የእሳቸው መፃሀፍ ይኖራል..…..?››
‹‹የቱን ልስጥህ……..?››
‹‹ሁሉንም የለኝም… አሪፍ ያልከውን …››
በፈገግታ ከዚህም ከዛም አየመዘዘ አምስት መፃሀፍ እጄ ላይ ዘረገፈ…
‹‹እንዴ…? ይሄን ሁሉ እንደፃፍ አላውቅም ነበር››መደነቄን መደበቅ አልቻልኩም
‹‹11 መፃሀፍ እኮ ነው ያላቸው..ይበዛብሀል ብዬ ነው የቅርቦቹን ብቻ መርጬ የሰጠውህ…. ልጁን እያዳመጥኩ ግን ደግሞ መፃሀፎቹን እያገላበጥኩ በማየት ላይ ሳለው አይኖቼ የመፃፍ ጀርባ ላይ የታተመ የደራሲው ፎቶ ላይ አረፈ ..ደነገጥኩ…. እባብ ሱሬው ውስጥ እንደገባበት ሰው አይነት ነው አደነጋገጤ ..ሰውዬውን አውቃቸዋለው፡፡ሌላውን መፃሀፍ ጀርባ ገለበጥኩ ፎቶ የለውም……ሌላውን ገለጥኩ አዎ እራሳቸው ናቸው…ከመቀመጫዬ ተነሳው….
‹‹ሂሳቡ ስንት ነው…..?››
‹‹የየትኛው…..? ››
‹‹የሁሉም››
መፃሀፎቹን ከእጆቼ ወሰደና ጀርባቸው ላይ ያለውን ዋጋ ደምሮ ነገረኝ..ከፍዬ መልስም ሳልጠይቅ ወጣሁ…
‹‹እንዴ አትጠብቃቸውም……..?››ልጁ ግራ ተጋብቶ ጠየቀኝ
‹‹ተመልሼ መጣለው ››ቻው..ተንደርድሬ መኪናዬ ውስጥ ገባውና አሁንም ድጋሜ የመጽሀፉን ጀርባ ላይ ያለውን ፎቶ አየሁት…ንዴትም ደስታም የተቀላቀለበት ስሜት ነው ተሰማኝ፡፡እኚን እኮ ነው ሹገር ዳዲዋ እንደሆኑ የነገረቺኝ ፡፡ለካ አባቷ ናቸው…?ሲያስደስት..ግን እንዴት ነው የምታስበኝ ?ይሄን ሁሉ ውሸት እንዴት ስትዋሸኝ ትከርማለች……? ስለእሷ የማላውቀው ሌላስ ምን አለ……?ይህቺ ልጅ እስከመቼ ነው እየራቀቀችብኝና እየጠለቀችብኝ የምትሄደው…?ለማንኛውም በእሷ በመታለሌ ከተበሳጨውት ይበልጥ ሹገር ዳዲዋ ናቸው ብዬ ለቀናት በንዴት ስንጨረጨር እና እንቅልፍ ሳጣበት የነበረው ጉዳይ ውሸት ሆኖ አባቷ በመሆናቸው የተደሰትኩት በእጥፍ ይበልጣል…
ከዛን ቡኃላም ስልኳ አይሰራም…ካላጋነንኩት ለመቶ የቀረብ መልዕክቶችን ልኬላታለሁ…ምንአልባት ከከፈተችው ወዲያው እድትደውልልኝ በማለት..ግን አንደዛ አልሆነም…ይገርማችሆል አንዳንዴ በውድቅት ለሊት ስምንትና ዘጠኝ ሰዓት ከእንቅልፌ ድንገት በርግጌ እነሳና ስልኬን አንስቼ እሞክርላታለው….ግን የተለወጠ ነገር አልነበረም፡፡ዛሬ ግን በተቻለኝ መጠን ስለእሷ ከማሰብ እራሴን መግታትና እና ትኩረቴን ሰብሰብ አድርጌ ስለፍፃሜው ጦርነት ብቻ ማሰብ ነው የምፈልገው፡፡ቀኗ ዛሬ ነች…ማንነቴን ለአባቴም ለሌላውም ሰው የማሳይበት ቀን፡፡ይህቺን ቀን አብራኝ ለወራት የለፋችው ፊናን ከጎኔ ብትሆን ኖሮ የበለጠ ጠንካራ የበለጠ ልበሙሉ እሆን ነበር…አይ የኔ ነገር አሁንም መልሼ ወደእሷ ወሰድኮችሁ አይደል፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍5
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍሰሀ
፡
፡
ብቻ አሁን ከንጋቱ 12 ሰዓት ነው…መኝታዬን ለቅቄ ቢጃማዬን እያወላለቅኩ ወደሻወር ቤት አመራው…የሻወሩን ውሀ ለብ እንዲል አደረግኩና ገባውበት…አዎ ንጹህና ቀለል ብሎኝ መዋል ነው የምፈልገው፡፡
ዛሬ የምለብሰውን ልብስ ከአስር ቀን በፊት ነበር የተዘጋጀው…ሙሉበሙሉ በፌናን ምርጫ በጥንቃቄ ተመርጠው የተገዙ አዳዲስ ናቸው፡፡ከሻወር ወጥቼ እራሴን ካደራረቅኩ ቡኃላ ከቁም ሳጥኔ ውስጥ እያወጣው ሙሉ ቁመናዬን በጥራት የሚያሳየ መስታወት ፊት ቆሜ በጥንቃቄ ለበስኩ፡፡ፀጉሬን አስፈላጊውን ቅባት በተገቢው መጠን በመቀባት አስተካከልኩ፡፡ካሉኝ ሽቶዎች ምርጥ የተባለውን ሽቶ ሳይበዛም ሳያንስም ከተጠቀምኩ ቡኃላ ለመጨረሻ ጊዜ መስታወቱ ፊት አየተሸከረከርኩ..እየቀረብኩ ..እየራቅኩ የጎደለ ወይም የተዛነፈ ነገር ካለ አረጋገጥኩና ስልኬንና የመኪና ቁልፌን ይዤ ከመኝታ ቤቴ ወጣው
በዚህን ጊዜ ለአንድ አስር ጉዳይ ሆኖ ነበር፡፡ፕሮግራሙ የሚጀመረው ሶስት ሰዓት ስለሆነ ገና ቡዙ ጊዜ አለኝ፡፡አባቴ እየተዘጋጀ መሆኑን ለማረጋገጥ ወደእሱ መኝታ ቤት አመራው…፡፡አዎ ተንስቷል… ምክንያቱም መኝታ ቤቱ ገርበብ እንዳለ ነው፡፡እየተቃረብኩ ስመጣ ድምጹን ሰማው …ያወራል፡፡ስልክ ላይ እንደሆነ ገባኝና ልመለስ ስል ከአንደበቱ ወጥተው ጆሮዬ የደረሱ ዓ/ነገር ጭራሽ ተጠግቼ እንዳዳምጥ ገፋፋኝ፡፡የኮቴዬን ድምጽ እንዳይሰማ ተጠንቅቄ ወደ በራፉ ቀረብኩና አጨንቁሬ ወደውስጥ እያየው ጆሮዬን ለጠፍኩ፡፡አባቴ ፊቱን ከበሩ በተቃራኒው አዙሮ የአልጋው ጠርዝ ላይ ተቀምጦ እያወራ ነው፡፡
‹‹ስሚኝ ክብረወርቅ …ዛሬም ድረስ እንደማፈቅርሽ አትዘንጊ››ይሄንን መስማቴ ነው በፈገግታ ቀሪውን የስልክ ልውውጥ እንዳዳምጥ የገፋፋኝ..‹‹አባዬ ውሽማ አለችው እንዴ..?..የሚገርም ነው….››
ከዛኛው ወገን የሚነገረው ከርቀቱ አንጻር አይሰማኝም…
‹‹ይሄውልሽ…አንቺ ለልጅሽ እንደምታዳይ ሁሉ እኔም ልጄ የፈለገውን እንዲያገኝ የማልፈነቅለው ድንጋይ አይኖርም››
‹‹አይደለም..ፈፅሞ አንቺን ለመበቀል እየሰራው ያለውት ስራ የለም፡፡እርግጥ ለዓመታት እንድታገቢኝ ስማፀንሽ አሻፈረኝ ስላልሺኝ ሁሌ እንደተበሳጨውብሽ ነው፡፡አሁንም ከንዴቴ ጋር ነው ያለሁት…፡፡ቢሆንም ግን ላንቺ ያለኝ ፍቅር እዛው ድሮ ያለበት ቦታ እንደሆነ ልደብቅሽ የሚያስችል ጥንካሬ አይኖረኝም…
‹‹አዎ ባል እንዳለሽ አንድ ሺ ጊዜ ነግረሺኛል..አውቃለውም…፡፡ግን አንቺ ለእኔ የተፈጠርሽ ሴት ነበርሽ፡፡ባልሽ እኮ ምኑም ካንቺ ጋር አይሄድም፡፡አንቺን የምታህል ሚኒዬነር ነጋዴ አንድ ተራ የሀይ-እስኩል አስተማሪ አግብታ እድሜ ልኳን ከእሱ ጋር……….››
‹‹ይቅርታ ..ሁል ጊዜ ስለእሱ ሳወራ እንደምትበሳጪ አውቃለው፡፡ግን እይውእስቲ…እኔ እና አንቺ በጋራ ይሄን የመሰለ ካምፓኒ መመስረት ችለናል፡፡ለአመታት በጣም ውጤታማ ነን፡፡ይሄንን የቢዝነስ ስኬታችንን ለልጆቻችን አስተላልፈን እኔና አንቺ ወደ ፍቅር ውህደት ማለቴ ወደ ትዳር ብንገባና ቀሪ ዘመናችንን የተረጋጋ እና የሰከነ ኑሮ ብንኖር ደስ ይለኛል፡፡ምንኖረው ሀገር ውስጥም ላይሆን ይችላል ፡፡አንቺ ተስማሚ እንጂ የፈለግሽው የሀገር ጫፍ ብትይ ይመቸኛል፡፡ሰው ማይኖርበት አንታርቲካም ቢሆን ..››
‹‹የምሰማው ንግግር ከአባቴ አንደበት እየወጣ መሆኑን ማመን ተሳነኝ ‹‹…ወይ ጉድ!! ለካ ሼባው አደገኛ የፍቅር አክተር ነበረና…እኔ እንኳን እሱ በሚያወራው መጠን የማወራትና የምጀነጅናት ሴት ኖራኝ አታውቅም….. ደግሞ ተፈቃሪዋ እኮ የካምፓኒው አንዷ ባለድርሻ ነች …ለካ ይህ ጉዳይ ለእሱ ወሳኝ እንደሆነ ለመቶ ምናምነኛ ጊዜ ደጋግሞ ሲነግረኝና ሲያስጠነቅቀኝ የነበረው ሌላ ምክንያት ስላለው ነበር… አዎ አሁን ገባኝ … በመካከላቸው ያለው ጦርነት ቢዝነሳዊ ብቻ ሳይሆን ፃታዊም ነበር ማለት ነው…፡፡
‹‹ቀጥሏል አባቴ››
‹‹…በቃ እንግዲህ ….የልጅሽና የልጄ ፊልሚያ ላይ እንገናኝ፡፡እና የመጨረሻው ደስታ የእኔ ስለሚሆን ፅዋችንን በእኔ ወጪ ነው የምናነሳው…››
‹‹አታስቢ.. የልጄን ዕወቀትና ብቃት ስለማታውቂ ነው…እኔን ስለምታውቂኝ እሱንም ያወቅሽ እንዳይመስልሽ፡፡እኔን ቁጭ አድርጎ ሊያስተምረኝ ሚችል ጀግና ነው››
ከአባቴ አንደበት በዚህ አይነት ሁኔታ የራስን ልጅ ግነታዊ በሆነ ደረጃ ከፍ ከፍ እያደረገ ሲናገር መስማቱን አልወደድኩትም …ከዚህ የባሰ ነገር ተናግሮ ለወራት የገነባውትን ማንነቴን እና በራስ መተማመን እንዲሸረሽርብኝ ስለማልፈልግ ቀስ እያልኩ ወደኃላ አፈገፈግኩና ወደሳሎን ወረድኩ….
ሰራተኛዋ በምግብ ጠረጵዛው ላይ ቁርስ ደርድራ እንደጨረሰች አባቴም መጣ…
‹‹ፐፐፐፐ…ጠቅላይ ሚኒስቴር መስለሀል.››ብሎ ወደኔ ቀረበና ግንባሬን ሳመኝ..ደስ አለኝ…
ሌላውም ሰው እንደእሱ ከተሰማው አሪፍ ነው ስል አሰብኩ…በፌናን ምክር መሰረት አንዱ ነገር ተሳክቷል ማለት ነው…በዝግጅቱ ቀን የገምጋሚዎቹን ቀልብ ሰብስቦ የሚይዝ ፤በራስ መተማመንኔን በራሱ የሚያስረዳ አይነት አለባበስ መልበስ የመጀመሪያ መመሪያዋ ነበር…ሌላው ፕሮፖዛሉ ሙሉ ሰነድ እንደመሆኑ መጠን ከዛ ዋና ዋናውን ሀሳብ በአንድ ሰዓት ውስጥ ለሶስቱ ወሳኝ ሰዎች ለማቅረብ መከተል የሚገባኝን አካሄድ …
*
To make sticky idea you should be focuse on the following criteria
1/simplicity
2/un expected
3/Cridibel
4/concerete
5/Emotional
6/Story ……ትለኛለች
**
ሶስት ቀን ሙሉ ነው ስለእያንዳንዱ ነጥብ ምሳሌ በመስጠት ያስጠናቺኝ…፡፡እናም ጥናቱን ፍሬ ነገር ጨምቄ ቀላልና ግልጽ በሆነ አገላለጽ በገምጋሚዎች ላይ ያልጠበቁትን መደመም በመፍጠር ሚዛን ሚደፍ ሀሳቦችንና በሚያስምን አቀራረብ ሙሉ የጥናቱን ታሪክ በሚያስረዳ መልኩ የተጨመቀውን ሀሳብ በተሰጠኝ አንድ ሰዓት ውስጥ ማቅረብ እንድችል የተቻላትን ያህል አዘጋጅታኛለች… እኔም ብዙ ጊዜ እያፈረስኩ እየገነባው ሳምንቱን ሙሉ ተለማምጄዋለው፡፡እና አሁን ከአንድ ሰዓት ቡኃላ ይሄን የወራት ልፋቴን ውጤት የእኔም ብቻ ሳይሆን በዚህ መጠን እንድዘጋጅና ተፎካካሪዬን በብቃት እንድረታ በሚስችለኝ መጠን እንድዘጋጅ ለረዳችኝ ፊናን ልፋትም ፍሬው የሚለቀምበት ሰዓት ደርሷል፡፡ዝግጅቱን የማቀርብበት ሰዓት ….
በነገራችን ላይ ፕሮግራሙን ሳልነግራችሁ፡፡ከሶስት እስከአራት ሰዓት ባለው ጊዜ እኔ ሙሉ ሰነዱን አስረክቤ የተዘጋጀውበትን ሀሳብ በተሠጠኝ አንድ ሰዓት ውስጥ አቀርባለው…፡፡ከዛ ከአራት ሰዓት እስከ ተኩል ድረስ የምጠየቀውን ጥያቄ የምመልስበት ሰዓት ይሆናል፡፡. ከዛ የሻይ እርፍት ይኖርና፡፡ ከ5 እስከ ስድስት ሰዓት ደግሞ የሴትዬዋ ልጅ ትገባና በተመሳሳይ እንደ እኔ ያዘጋጀችውን ሰንድ አስረክባ በአንድ ሰዓት ውስጥ አቅርባ ስድስት ሰዓት ትጨርሳለች፡፡ከስድስት እስከ ስድስት ተኩል ልክ እንደእኔ በተመሳሳይ የጠየቋትን ጥያቄ የምትመልስበት ወቅት ይሆናል…፡፡
ከዛ አምስታችንም ወደምሳ ፕሮግራም እንሄዳለን፡፡ከ 6:30 እስከ 8 ሰዓት የምሳ ሰዓታችን ነው፡፡ከ8 እስከ 10 ሰዓት ሶስቱ የካምፓኒው ባለቤቶች ለብቻቸው ሰብሰባ ያደርጋሉ፡፡ በሰነዱና በቀረበላቸው ሀሳብ ላይ ይወያያሉ፡፡ለተኩል ሰዓት ሻይ ይወጣና ተፎካካሪዎቹም ባሉበት የመጨረሻ ድምጽ ይሰጣል፡፡የተሰጠው ድምጽ በግልጽ ሁሉም እያየ ይከፈታል አሸናፊው ይለይና ሙሉ ፕሮግራሙ ይጠናቀቃል፡፡
አሁን ከጥዋቱ 2፡40 ሆኗል እኔና አባቴ ቢሮ ደርሰናል፡፡ጋሼ ከበደ ከእኛ አምስት ደቂቃ ዘግይተው
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍሰሀ
፡
፡
ብቻ አሁን ከንጋቱ 12 ሰዓት ነው…መኝታዬን ለቅቄ ቢጃማዬን እያወላለቅኩ ወደሻወር ቤት አመራው…የሻወሩን ውሀ ለብ እንዲል አደረግኩና ገባውበት…አዎ ንጹህና ቀለል ብሎኝ መዋል ነው የምፈልገው፡፡
ዛሬ የምለብሰውን ልብስ ከአስር ቀን በፊት ነበር የተዘጋጀው…ሙሉበሙሉ በፌናን ምርጫ በጥንቃቄ ተመርጠው የተገዙ አዳዲስ ናቸው፡፡ከሻወር ወጥቼ እራሴን ካደራረቅኩ ቡኃላ ከቁም ሳጥኔ ውስጥ እያወጣው ሙሉ ቁመናዬን በጥራት የሚያሳየ መስታወት ፊት ቆሜ በጥንቃቄ ለበስኩ፡፡ፀጉሬን አስፈላጊውን ቅባት በተገቢው መጠን በመቀባት አስተካከልኩ፡፡ካሉኝ ሽቶዎች ምርጥ የተባለውን ሽቶ ሳይበዛም ሳያንስም ከተጠቀምኩ ቡኃላ ለመጨረሻ ጊዜ መስታወቱ ፊት አየተሸከረከርኩ..እየቀረብኩ ..እየራቅኩ የጎደለ ወይም የተዛነፈ ነገር ካለ አረጋገጥኩና ስልኬንና የመኪና ቁልፌን ይዤ ከመኝታ ቤቴ ወጣው
በዚህን ጊዜ ለአንድ አስር ጉዳይ ሆኖ ነበር፡፡ፕሮግራሙ የሚጀመረው ሶስት ሰዓት ስለሆነ ገና ቡዙ ጊዜ አለኝ፡፡አባቴ እየተዘጋጀ መሆኑን ለማረጋገጥ ወደእሱ መኝታ ቤት አመራው…፡፡አዎ ተንስቷል… ምክንያቱም መኝታ ቤቱ ገርበብ እንዳለ ነው፡፡እየተቃረብኩ ስመጣ ድምጹን ሰማው …ያወራል፡፡ስልክ ላይ እንደሆነ ገባኝና ልመለስ ስል ከአንደበቱ ወጥተው ጆሮዬ የደረሱ ዓ/ነገር ጭራሽ ተጠግቼ እንዳዳምጥ ገፋፋኝ፡፡የኮቴዬን ድምጽ እንዳይሰማ ተጠንቅቄ ወደ በራፉ ቀረብኩና አጨንቁሬ ወደውስጥ እያየው ጆሮዬን ለጠፍኩ፡፡አባቴ ፊቱን ከበሩ በተቃራኒው አዙሮ የአልጋው ጠርዝ ላይ ተቀምጦ እያወራ ነው፡፡
‹‹ስሚኝ ክብረወርቅ …ዛሬም ድረስ እንደማፈቅርሽ አትዘንጊ››ይሄንን መስማቴ ነው በፈገግታ ቀሪውን የስልክ ልውውጥ እንዳዳምጥ የገፋፋኝ..‹‹አባዬ ውሽማ አለችው እንዴ..?..የሚገርም ነው….››
ከዛኛው ወገን የሚነገረው ከርቀቱ አንጻር አይሰማኝም…
‹‹ይሄውልሽ…አንቺ ለልጅሽ እንደምታዳይ ሁሉ እኔም ልጄ የፈለገውን እንዲያገኝ የማልፈነቅለው ድንጋይ አይኖርም››
‹‹አይደለም..ፈፅሞ አንቺን ለመበቀል እየሰራው ያለውት ስራ የለም፡፡እርግጥ ለዓመታት እንድታገቢኝ ስማፀንሽ አሻፈረኝ ስላልሺኝ ሁሌ እንደተበሳጨውብሽ ነው፡፡አሁንም ከንዴቴ ጋር ነው ያለሁት…፡፡ቢሆንም ግን ላንቺ ያለኝ ፍቅር እዛው ድሮ ያለበት ቦታ እንደሆነ ልደብቅሽ የሚያስችል ጥንካሬ አይኖረኝም…
‹‹አዎ ባል እንዳለሽ አንድ ሺ ጊዜ ነግረሺኛል..አውቃለውም…፡፡ግን አንቺ ለእኔ የተፈጠርሽ ሴት ነበርሽ፡፡ባልሽ እኮ ምኑም ካንቺ ጋር አይሄድም፡፡አንቺን የምታህል ሚኒዬነር ነጋዴ አንድ ተራ የሀይ-እስኩል አስተማሪ አግብታ እድሜ ልኳን ከእሱ ጋር……….››
‹‹ይቅርታ ..ሁል ጊዜ ስለእሱ ሳወራ እንደምትበሳጪ አውቃለው፡፡ግን እይውእስቲ…እኔ እና አንቺ በጋራ ይሄን የመሰለ ካምፓኒ መመስረት ችለናል፡፡ለአመታት በጣም ውጤታማ ነን፡፡ይሄንን የቢዝነስ ስኬታችንን ለልጆቻችን አስተላልፈን እኔና አንቺ ወደ ፍቅር ውህደት ማለቴ ወደ ትዳር ብንገባና ቀሪ ዘመናችንን የተረጋጋ እና የሰከነ ኑሮ ብንኖር ደስ ይለኛል፡፡ምንኖረው ሀገር ውስጥም ላይሆን ይችላል ፡፡አንቺ ተስማሚ እንጂ የፈለግሽው የሀገር ጫፍ ብትይ ይመቸኛል፡፡ሰው ማይኖርበት አንታርቲካም ቢሆን ..››
‹‹የምሰማው ንግግር ከአባቴ አንደበት እየወጣ መሆኑን ማመን ተሳነኝ ‹‹…ወይ ጉድ!! ለካ ሼባው አደገኛ የፍቅር አክተር ነበረና…እኔ እንኳን እሱ በሚያወራው መጠን የማወራትና የምጀነጅናት ሴት ኖራኝ አታውቅም….. ደግሞ ተፈቃሪዋ እኮ የካምፓኒው አንዷ ባለድርሻ ነች …ለካ ይህ ጉዳይ ለእሱ ወሳኝ እንደሆነ ለመቶ ምናምነኛ ጊዜ ደጋግሞ ሲነግረኝና ሲያስጠነቅቀኝ የነበረው ሌላ ምክንያት ስላለው ነበር… አዎ አሁን ገባኝ … በመካከላቸው ያለው ጦርነት ቢዝነሳዊ ብቻ ሳይሆን ፃታዊም ነበር ማለት ነው…፡፡
‹‹ቀጥሏል አባቴ››
‹‹…በቃ እንግዲህ ….የልጅሽና የልጄ ፊልሚያ ላይ እንገናኝ፡፡እና የመጨረሻው ደስታ የእኔ ስለሚሆን ፅዋችንን በእኔ ወጪ ነው የምናነሳው…››
‹‹አታስቢ.. የልጄን ዕወቀትና ብቃት ስለማታውቂ ነው…እኔን ስለምታውቂኝ እሱንም ያወቅሽ እንዳይመስልሽ፡፡እኔን ቁጭ አድርጎ ሊያስተምረኝ ሚችል ጀግና ነው››
ከአባቴ አንደበት በዚህ አይነት ሁኔታ የራስን ልጅ ግነታዊ በሆነ ደረጃ ከፍ ከፍ እያደረገ ሲናገር መስማቱን አልወደድኩትም …ከዚህ የባሰ ነገር ተናግሮ ለወራት የገነባውትን ማንነቴን እና በራስ መተማመን እንዲሸረሽርብኝ ስለማልፈልግ ቀስ እያልኩ ወደኃላ አፈገፈግኩና ወደሳሎን ወረድኩ….
ሰራተኛዋ በምግብ ጠረጵዛው ላይ ቁርስ ደርድራ እንደጨረሰች አባቴም መጣ…
‹‹ፐፐፐፐ…ጠቅላይ ሚኒስቴር መስለሀል.››ብሎ ወደኔ ቀረበና ግንባሬን ሳመኝ..ደስ አለኝ…
ሌላውም ሰው እንደእሱ ከተሰማው አሪፍ ነው ስል አሰብኩ…በፌናን ምክር መሰረት አንዱ ነገር ተሳክቷል ማለት ነው…በዝግጅቱ ቀን የገምጋሚዎቹን ቀልብ ሰብስቦ የሚይዝ ፤በራስ መተማመንኔን በራሱ የሚያስረዳ አይነት አለባበስ መልበስ የመጀመሪያ መመሪያዋ ነበር…ሌላው ፕሮፖዛሉ ሙሉ ሰነድ እንደመሆኑ መጠን ከዛ ዋና ዋናውን ሀሳብ በአንድ ሰዓት ውስጥ ለሶስቱ ወሳኝ ሰዎች ለማቅረብ መከተል የሚገባኝን አካሄድ …
*
To make sticky idea you should be focuse on the following criteria
1/simplicity
2/un expected
3/Cridibel
4/concerete
5/Emotional
6/Story ……ትለኛለች
**
ሶስት ቀን ሙሉ ነው ስለእያንዳንዱ ነጥብ ምሳሌ በመስጠት ያስጠናቺኝ…፡፡እናም ጥናቱን ፍሬ ነገር ጨምቄ ቀላልና ግልጽ በሆነ አገላለጽ በገምጋሚዎች ላይ ያልጠበቁትን መደመም በመፍጠር ሚዛን ሚደፍ ሀሳቦችንና በሚያስምን አቀራረብ ሙሉ የጥናቱን ታሪክ በሚያስረዳ መልኩ የተጨመቀውን ሀሳብ በተሰጠኝ አንድ ሰዓት ውስጥ ማቅረብ እንድችል የተቻላትን ያህል አዘጋጅታኛለች… እኔም ብዙ ጊዜ እያፈረስኩ እየገነባው ሳምንቱን ሙሉ ተለማምጄዋለው፡፡እና አሁን ከአንድ ሰዓት ቡኃላ ይሄን የወራት ልፋቴን ውጤት የእኔም ብቻ ሳይሆን በዚህ መጠን እንድዘጋጅና ተፎካካሪዬን በብቃት እንድረታ በሚስችለኝ መጠን እንድዘጋጅ ለረዳችኝ ፊናን ልፋትም ፍሬው የሚለቀምበት ሰዓት ደርሷል፡፡ዝግጅቱን የማቀርብበት ሰዓት ….
በነገራችን ላይ ፕሮግራሙን ሳልነግራችሁ፡፡ከሶስት እስከአራት ሰዓት ባለው ጊዜ እኔ ሙሉ ሰነዱን አስረክቤ የተዘጋጀውበትን ሀሳብ በተሠጠኝ አንድ ሰዓት ውስጥ አቀርባለው…፡፡ከዛ ከአራት ሰዓት እስከ ተኩል ድረስ የምጠየቀውን ጥያቄ የምመልስበት ሰዓት ይሆናል፡፡. ከዛ የሻይ እርፍት ይኖርና፡፡ ከ5 እስከ ስድስት ሰዓት ደግሞ የሴትዬዋ ልጅ ትገባና በተመሳሳይ እንደ እኔ ያዘጋጀችውን ሰንድ አስረክባ በአንድ ሰዓት ውስጥ አቅርባ ስድስት ሰዓት ትጨርሳለች፡፡ከስድስት እስከ ስድስት ተኩል ልክ እንደእኔ በተመሳሳይ የጠየቋትን ጥያቄ የምትመልስበት ወቅት ይሆናል…፡፡
ከዛ አምስታችንም ወደምሳ ፕሮግራም እንሄዳለን፡፡ከ 6:30 እስከ 8 ሰዓት የምሳ ሰዓታችን ነው፡፡ከ8 እስከ 10 ሰዓት ሶስቱ የካምፓኒው ባለቤቶች ለብቻቸው ሰብሰባ ያደርጋሉ፡፡ በሰነዱና በቀረበላቸው ሀሳብ ላይ ይወያያሉ፡፡ለተኩል ሰዓት ሻይ ይወጣና ተፎካካሪዎቹም ባሉበት የመጨረሻ ድምጽ ይሰጣል፡፡የተሰጠው ድምጽ በግልጽ ሁሉም እያየ ይከፈታል አሸናፊው ይለይና ሙሉ ፕሮግራሙ ይጠናቀቃል፡፡
አሁን ከጥዋቱ 2፡40 ሆኗል እኔና አባቴ ቢሮ ደርሰናል፡፡ጋሼ ከበደ ከእኛ አምስት ደቂቃ ዘግይተው
👍4
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍሰሀ
===
ልዩ የሆነ ቆይታ ነበር፡፡ሶስቱንም ፈታኞቼን እንዳስደመምኮቸው እርግጠኛ ነኝ፡፡መድረኩን በስነስርዓት፤ ባጠናውት እና በተዘጋጀውት መጠን ነበር የተወጣሁት፡፡በመጨረሻ ሁሉም ወ/ሮ ክብረወርቅም ጭምር ቆመው ነበር ያጨበጨብልኝ፡፡እኔም በደስታ ሰክሬ ከወገቤ ሽብርክ ብዬ አመሰገንኳቸው፡፡
ለመውጣት ቸኩያለው ቀልቤ ያለው ፌናን ጋር ነው፡፡እስከአሁን ከቤቷ መጥታ ውጭ በረንዳ ላይ ወይም ቢሮዬ ቁጭ ብላ እደምትጠብቀኝ እርግጠኛ ነኝ፡፡አዎ አይኖቼ መላ እሷነቷን ተርበዋል፡፡ከራሴ በላይ እወደዋለው፡፡ ብዬ የማስበው አባቴ እንኳን ከስድስት ወር ባላይ ተለይቶኝ ሲኖር በዚህ መጠን ናፍቆኝና ተርቤው አላውቅም…
ናፍቆቴ የቱንም ያህል ቢሆን ግን እነሱን ቀድሜ መውጣት በአይን አውጣነት የሚያስፈርጀኝ መስሎ ስለተሰማኝ እንደምንም ስሜቴን ተቆጣጥሬ እየታገስኩ ነው፡፡እነሱ በእርጋታ የሚንቀሳቀሱትን ሽማጊሌውን አስቀድመው እየተጎተቱ ክፍሉን እስኪለቁልኝ መጠበቅ ግድ ሆነብኝ፡፡ይባስ ብሎ አባቴ ወደእኔ መጣ፡፡ተጠመጠመብኝ ፡፡ምን ላድርግ …?መልሼ በተመሳሳይ አቀፍኩት፡፡ለዚህች ቀን አይደል ስንት ወር ሙሉ ሲወተውተኝ የነበረው?እሱ ያልተደሰተ ማን ይደሰታል……?ግን እሱ ያላወቀው እንዲህ መታቀፍ ያለብኝ እኔ ሳልሆን ፌናን መሆኗን ነው፡፡ግድ የለም ..እሱ እኔን ባቀፈኝ መጠን እኔ ደግሞ ከደቂቃ ቡኃላ እሷን አቅፋታለው፡፡.ጭምቅ አድርጌ አቅፋትና ምስጋናዬን አቀርብላታለው፡፡ምስጋናዬን ብቻ ሳይሆን ዛሬ ማታ አፕል አበረክትላታለው፡፡አዎ ጥንት ግሪካዊያን ለሚያፈቅሩት ሰው አፕል ነበር የሚልኩት አንተም የምታፈቅረኝ ከሆነ ከዝግጅቱ ቡኃላ አፕል ላክልኝ የዛን ጊዜ መልሱን ነግርሀለው አይደለ ያለቺኝ?ዋው..ማታ እራት ጋብዛታለው::ከዛ አፕል እሰጣታለው::አፕሉ ውስጥ ደግሞ ቀለበት ይኖርታል::አብረቅራቂ የአልማዝ ቀለበት::ይህንን በማሰቤ ውስጤ ዘላለማዊ በሚመስል ደስታ ተጥለቀለቀ
‹‹በጣም ነው ያኳራኸኝ…እጅግ በጣም ከጠበቅኩት በላይ ጀግና ሆነህልኛል ለካ?አሁን እርግጠኛ ሆነህ ካማፓኒውን በቋሚነት ለመረከብ ተዘጋጅ..››አለኝ አባቴ ሌሎቹ ሊሰሙት በማይችሉት ዝቅተኛ ድምጽ
‹‹እሺ አባዬ አመሰግናለው፡፡››
‹‹ና እንውጣ›› አለኝና ትከሻዬን በኩራት አቅፎ ወደውጭ ይዞኝ ወጣ::በራፍ ላይ እንደደረስን በሃያ ሜትር ርቀት ፌናን ቀድመውን ከወጡት ጋሽ ከበደ እና ከወ/ሮ ክብረወርቅ ጋር ሲያወሩ ለዛውም እየተሳሳቁ ተመለከትኩ
እኔም አባቴም ሳንነጋገር እርምጃችንን እዛው በራፍ ላይ ገታነው::እንዴት አምሮባታል ?ይህ ሁሉ ውበት እንዲህ ጎልቶ እና ፈክቶ የወጣው ከእራሷ ከአፈጣጠር ነው ወይስ ከአለባበሷ…?ልቤ እንደለመደችው ቅልጥልጥ አለች…ግን ከሰዎቹ ጋር የት ተዋውቃ ነው እንዲህ በመፈንጠዝያና በፈገግታ የምታወራቸው……?
‹‹አንተ ተፋላሚህ መታልሀለች::ደግሞ እንዴት ታምራለች……?ልክ እንደእናቷ ››አባቴ ነው በአድናቆትና በስጋት መሀከል በሚዋልል ስሜት የተናገረው…
‹‹አባ እሷ አይደለችም::ይህቺ እኮ የእኔ ረዳት ነች››አረምኩት
‹‹እርግጠኛ ነህ…?ፎቶዋና እኮ እናትዬው ያሳየቺኝ መሰለኝ..ለማንኛውም ና ወደ እነሱ እንሂድ..››አለኝና ተያዘን ስራቸው ደረስን …ፌናን ዞር ብላ እንዳየችኝ ተሸከርክራ ተጠመጠመችብኝ….በጣም እንደናፈቀቺኝ ያወቅኩት ሁሉም እያዩኝ ያለይሉኝታ ልክ እንደ ህጋዊ እጮኛዬ አቅፌ በአየር ላይ ሳንጠለጥላት ነው….
አባቴ ‹‹ክብረወርቅ ልጅሽ ነች እንዴ…?››ብሎ ሲጠይቅ በጆሮዬ ገባ..
‹‹አዎ ልጄ ነች::ፌናን ሰላም በይው…››የሰማውትን መልስ ማመን አቃተኝ….. ምንድነው እየተካሄደ ያለው..?.ከእሷ ሸሸት እልኩና እናትዬው ላይ አፈጠጠኩባት
<<…ምን ተፈጠረ …?በሚል ግራ በተጋባ አሰተያየት ንግግሯን ቀጠለች‹‹እንዲህ ምትግባቡ አይመስለኝም ነበር››ለእኔ ነው የምትለኝ ፡፡
‹‹ፌናን ያንቺ ልጅ ነች…?››አንቱነታውንን እረስቼ የአባቴን ጥያቄ መልሼ ደገምኩ
‹‹አዎ ..ፌናን ልጄ ነች..ምነው …?አልነገረችህም እንዴ……?››
ወደ እሷ ተንደረደርኩና ሁለት ትከሻዋን ጨምድጄ ያዝኳት …ሶስትም ደነገጡ‹‹በጣም ባለጌ ነሽ..በጣም አታለሺኛል..መቼም ይቅር አልልሽም….››
ይሄን ሁሉ ስላት እሷ ምንም እንዳልተፈጠረ በግማሽ ፈገግታ እያደማጠቺኝ ነው…ገፍትሬ አባቴ ትከሻ ላይ ወረወርኳትና ወደቢሮዬ ተንደረደርኩ…
‹‹ምንድነው ነገሩ?ልጄን ምን አደረጋችሁት…?››የአባቴ ድምጽ እየተሰማኝ ነው…ቤሮዬን ገባውና ከውስጥ ቀረቀርኩ.. ቢያንኳኩም ልከፍትላቸው አልፈለኩም..ትንሽ ይብረድለት ብለው መሰለኝ ትተውኝ ዞር አሉ….እኔም ምፈልገው ያንን ነበር፡፡
…….ታንቄበት የዋልኩትን ከረባት ከአንገቴ ፈትቼ ጥዬ ኮቴን አውልቄ በመወርወር ወንበሬ ላይ ቁጭ ብዬ አንገቴን ጠረጳዛ ላይ ደፍቼ አነባው ጀመር::እንዲህ አይነት ለቅሶ ካለቀስኩ ስንት ዓመት እንዳለፈኝ ትዝ አይለኝም::ንፍጤ እስኪዝረከረክ ድረስ ነው ያለቀስኩት፡፡በህይወቴ አንድ ሰው በዚህ መጠን ተጫውቶብኝና አታሎኝ አያውቅም::እንዴ አምኜያት ነበርኮ..?በአድናቆት ፈዝዤያለት አፍቅሬያትና ብዙ ብዙ ህልም አልሜላት ነበር…?እንዴት አንዲህ ትሰብረኛለች?ይህችን ካምፓኒ ለማስተዳደር ብላ……?እኔ እኮ ከካምፓኒው ስራ በላይ ነበር ያፈቀርኳት…
…እያንዳንዷን የሰራዋትን ጥናት ቃል በቃል ታውቀዋለች፤ ምክንያቱም አብረን ነው የሰራነው.፡፡ስለዚህ የእሷ ዝግጅት የእኔን ጥናት አይታና ከእዛ በበለጠና ያንን በሚያጠቃ መልኩ ለማዘጋጀት እድሉን አግኝታለች… .በዛ ላይ ችሎታዋን አውቃዋለው..እና እንዴት ነው ከእሷ በልጬ ይሄን ቦታ የማገኘው…?ተዋረድኩ….፡፡በቃ ሁሉ ነገር አስጠላኝ ::ስራው አስጠላኝ ..ካምፓኒውም አስጠላኝ ..ያፈቀርኮት ልጅ አስጠላቺኝ…ሀገሬም አስጠላቺኝ …፡፡መመለስ አለብኝ…አዎ ወደመጣውበት ሀገር እመለሰላው..ስደት ይሻለኛል..ስራዬን እየሰራው ሶስትኛ ዲግሪዬን ብማር ይሻለኛል..::እንደውም በተጨማለቀ ሀገር የተጨማለቀ ኑሮ ለመኖር ምንድነው እንደዚህ አፈር የሚያስግጠኝ..…?ወሰንኩ…እንባዬን ከጉንጬ ላይ ጠራረግኩ…ኮምፒተሬን ከፈትኩና መጻፍ ጀመርኩ…ለቦርድ አባላቱ ነው::የካምፓኒውን ስራ ስለማልፈልገው ውድድሩ እንዲቀርና ስራውንም በገዛ ፍቃዴ መልቀቄን የሚገልጽ ደብዳቤ …ፕሪንት አድርጌ ፈረምኩበትና ኮቴን መልሼ በመልበስ ወጣው…ሰራተኞቹ ሁሉ ለምሳ የወጡ ቢሆንም ጸሀፊዬ ግን ስጠብቀኝ ነበር….
‹‹አሁን የቦርድ አባሎቹ ሲመጡ ይሄንን ማመልከቻ አስገቢልኝ›› አልኩና በካኪ ፓስታ የታሸገውን ማመልከቻ ሰጠዋት
‹‹አባትህ ደጋግመው ሲደውሉ ነበር…ምሳ እየጠበቅንህ ነው ፤ደውልኝ ብለውሀል…››
‹‹ዝም በይው::ስልኬን ዘግቼዋለው …ከደወለ ወጥቼ እንደሄድኩና እንደማልመለሰም ንገሪው……››
‹‹አንተ ግን ሰላም ነህ…?›ሁኔታዬ ስላላማራት መሰለኝ የጠየቀቺኝ
‹‹ሰላም ነኝ ….አመሰግናለው…››ጥያት ወጣው…..
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
፡
#ፍሰሀ
===
ልዩ የሆነ ቆይታ ነበር፡፡ሶስቱንም ፈታኞቼን እንዳስደመምኮቸው እርግጠኛ ነኝ፡፡መድረኩን በስነስርዓት፤ ባጠናውት እና በተዘጋጀውት መጠን ነበር የተወጣሁት፡፡በመጨረሻ ሁሉም ወ/ሮ ክብረወርቅም ጭምር ቆመው ነበር ያጨበጨብልኝ፡፡እኔም በደስታ ሰክሬ ከወገቤ ሽብርክ ብዬ አመሰገንኳቸው፡፡
ለመውጣት ቸኩያለው ቀልቤ ያለው ፌናን ጋር ነው፡፡እስከአሁን ከቤቷ መጥታ ውጭ በረንዳ ላይ ወይም ቢሮዬ ቁጭ ብላ እደምትጠብቀኝ እርግጠኛ ነኝ፡፡አዎ አይኖቼ መላ እሷነቷን ተርበዋል፡፡ከራሴ በላይ እወደዋለው፡፡ ብዬ የማስበው አባቴ እንኳን ከስድስት ወር ባላይ ተለይቶኝ ሲኖር በዚህ መጠን ናፍቆኝና ተርቤው አላውቅም…
ናፍቆቴ የቱንም ያህል ቢሆን ግን እነሱን ቀድሜ መውጣት በአይን አውጣነት የሚያስፈርጀኝ መስሎ ስለተሰማኝ እንደምንም ስሜቴን ተቆጣጥሬ እየታገስኩ ነው፡፡እነሱ በእርጋታ የሚንቀሳቀሱትን ሽማጊሌውን አስቀድመው እየተጎተቱ ክፍሉን እስኪለቁልኝ መጠበቅ ግድ ሆነብኝ፡፡ይባስ ብሎ አባቴ ወደእኔ መጣ፡፡ተጠመጠመብኝ ፡፡ምን ላድርግ …?መልሼ በተመሳሳይ አቀፍኩት፡፡ለዚህች ቀን አይደል ስንት ወር ሙሉ ሲወተውተኝ የነበረው?እሱ ያልተደሰተ ማን ይደሰታል……?ግን እሱ ያላወቀው እንዲህ መታቀፍ ያለብኝ እኔ ሳልሆን ፌናን መሆኗን ነው፡፡ግድ የለም ..እሱ እኔን ባቀፈኝ መጠን እኔ ደግሞ ከደቂቃ ቡኃላ እሷን አቅፋታለው፡፡.ጭምቅ አድርጌ አቅፋትና ምስጋናዬን አቀርብላታለው፡፡ምስጋናዬን ብቻ ሳይሆን ዛሬ ማታ አፕል አበረክትላታለው፡፡አዎ ጥንት ግሪካዊያን ለሚያፈቅሩት ሰው አፕል ነበር የሚልኩት አንተም የምታፈቅረኝ ከሆነ ከዝግጅቱ ቡኃላ አፕል ላክልኝ የዛን ጊዜ መልሱን ነግርሀለው አይደለ ያለቺኝ?ዋው..ማታ እራት ጋብዛታለው::ከዛ አፕል እሰጣታለው::አፕሉ ውስጥ ደግሞ ቀለበት ይኖርታል::አብረቅራቂ የአልማዝ ቀለበት::ይህንን በማሰቤ ውስጤ ዘላለማዊ በሚመስል ደስታ ተጥለቀለቀ
‹‹በጣም ነው ያኳራኸኝ…እጅግ በጣም ከጠበቅኩት በላይ ጀግና ሆነህልኛል ለካ?አሁን እርግጠኛ ሆነህ ካማፓኒውን በቋሚነት ለመረከብ ተዘጋጅ..››አለኝ አባቴ ሌሎቹ ሊሰሙት በማይችሉት ዝቅተኛ ድምጽ
‹‹እሺ አባዬ አመሰግናለው፡፡››
‹‹ና እንውጣ›› አለኝና ትከሻዬን በኩራት አቅፎ ወደውጭ ይዞኝ ወጣ::በራፍ ላይ እንደደረስን በሃያ ሜትር ርቀት ፌናን ቀድመውን ከወጡት ጋሽ ከበደ እና ከወ/ሮ ክብረወርቅ ጋር ሲያወሩ ለዛውም እየተሳሳቁ ተመለከትኩ
እኔም አባቴም ሳንነጋገር እርምጃችንን እዛው በራፍ ላይ ገታነው::እንዴት አምሮባታል ?ይህ ሁሉ ውበት እንዲህ ጎልቶ እና ፈክቶ የወጣው ከእራሷ ከአፈጣጠር ነው ወይስ ከአለባበሷ…?ልቤ እንደለመደችው ቅልጥልጥ አለች…ግን ከሰዎቹ ጋር የት ተዋውቃ ነው እንዲህ በመፈንጠዝያና በፈገግታ የምታወራቸው……?
‹‹አንተ ተፋላሚህ መታልሀለች::ደግሞ እንዴት ታምራለች……?ልክ እንደእናቷ ››አባቴ ነው በአድናቆትና በስጋት መሀከል በሚዋልል ስሜት የተናገረው…
‹‹አባ እሷ አይደለችም::ይህቺ እኮ የእኔ ረዳት ነች››አረምኩት
‹‹እርግጠኛ ነህ…?ፎቶዋና እኮ እናትዬው ያሳየቺኝ መሰለኝ..ለማንኛውም ና ወደ እነሱ እንሂድ..››አለኝና ተያዘን ስራቸው ደረስን …ፌናን ዞር ብላ እንዳየችኝ ተሸከርክራ ተጠመጠመችብኝ….በጣም እንደናፈቀቺኝ ያወቅኩት ሁሉም እያዩኝ ያለይሉኝታ ልክ እንደ ህጋዊ እጮኛዬ አቅፌ በአየር ላይ ሳንጠለጥላት ነው….
አባቴ ‹‹ክብረወርቅ ልጅሽ ነች እንዴ…?››ብሎ ሲጠይቅ በጆሮዬ ገባ..
‹‹አዎ ልጄ ነች::ፌናን ሰላም በይው…››የሰማውትን መልስ ማመን አቃተኝ….. ምንድነው እየተካሄደ ያለው..?.ከእሷ ሸሸት እልኩና እናትዬው ላይ አፈጠጠኩባት
<<…ምን ተፈጠረ …?በሚል ግራ በተጋባ አሰተያየት ንግግሯን ቀጠለች‹‹እንዲህ ምትግባቡ አይመስለኝም ነበር››ለእኔ ነው የምትለኝ ፡፡
‹‹ፌናን ያንቺ ልጅ ነች…?››አንቱነታውንን እረስቼ የአባቴን ጥያቄ መልሼ ደገምኩ
‹‹አዎ ..ፌናን ልጄ ነች..ምነው …?አልነገረችህም እንዴ……?››
ወደ እሷ ተንደረደርኩና ሁለት ትከሻዋን ጨምድጄ ያዝኳት …ሶስትም ደነገጡ‹‹በጣም ባለጌ ነሽ..በጣም አታለሺኛል..መቼም ይቅር አልልሽም….››
ይሄን ሁሉ ስላት እሷ ምንም እንዳልተፈጠረ በግማሽ ፈገግታ እያደማጠቺኝ ነው…ገፍትሬ አባቴ ትከሻ ላይ ወረወርኳትና ወደቢሮዬ ተንደረደርኩ…
‹‹ምንድነው ነገሩ?ልጄን ምን አደረጋችሁት…?››የአባቴ ድምጽ እየተሰማኝ ነው…ቤሮዬን ገባውና ከውስጥ ቀረቀርኩ.. ቢያንኳኩም ልከፍትላቸው አልፈለኩም..ትንሽ ይብረድለት ብለው መሰለኝ ትተውኝ ዞር አሉ….እኔም ምፈልገው ያንን ነበር፡፡
…….ታንቄበት የዋልኩትን ከረባት ከአንገቴ ፈትቼ ጥዬ ኮቴን አውልቄ በመወርወር ወንበሬ ላይ ቁጭ ብዬ አንገቴን ጠረጳዛ ላይ ደፍቼ አነባው ጀመር::እንዲህ አይነት ለቅሶ ካለቀስኩ ስንት ዓመት እንዳለፈኝ ትዝ አይለኝም::ንፍጤ እስኪዝረከረክ ድረስ ነው ያለቀስኩት፡፡በህይወቴ አንድ ሰው በዚህ መጠን ተጫውቶብኝና አታሎኝ አያውቅም::እንዴ አምኜያት ነበርኮ..?በአድናቆት ፈዝዤያለት አፍቅሬያትና ብዙ ብዙ ህልም አልሜላት ነበር…?እንዴት አንዲህ ትሰብረኛለች?ይህችን ካምፓኒ ለማስተዳደር ብላ……?እኔ እኮ ከካምፓኒው ስራ በላይ ነበር ያፈቀርኳት…
…እያንዳንዷን የሰራዋትን ጥናት ቃል በቃል ታውቀዋለች፤ ምክንያቱም አብረን ነው የሰራነው.፡፡ስለዚህ የእሷ ዝግጅት የእኔን ጥናት አይታና ከእዛ በበለጠና ያንን በሚያጠቃ መልኩ ለማዘጋጀት እድሉን አግኝታለች… .በዛ ላይ ችሎታዋን አውቃዋለው..እና እንዴት ነው ከእሷ በልጬ ይሄን ቦታ የማገኘው…?ተዋረድኩ….፡፡በቃ ሁሉ ነገር አስጠላኝ ::ስራው አስጠላኝ ..ካምፓኒውም አስጠላኝ ..ያፈቀርኮት ልጅ አስጠላቺኝ…ሀገሬም አስጠላቺኝ …፡፡መመለስ አለብኝ…አዎ ወደመጣውበት ሀገር እመለሰላው..ስደት ይሻለኛል..ስራዬን እየሰራው ሶስትኛ ዲግሪዬን ብማር ይሻለኛል..::እንደውም በተጨማለቀ ሀገር የተጨማለቀ ኑሮ ለመኖር ምንድነው እንደዚህ አፈር የሚያስግጠኝ..…?ወሰንኩ…እንባዬን ከጉንጬ ላይ ጠራረግኩ…ኮምፒተሬን ከፈትኩና መጻፍ ጀመርኩ…ለቦርድ አባላቱ ነው::የካምፓኒውን ስራ ስለማልፈልገው ውድድሩ እንዲቀርና ስራውንም በገዛ ፍቃዴ መልቀቄን የሚገልጽ ደብዳቤ …ፕሪንት አድርጌ ፈረምኩበትና ኮቴን መልሼ በመልበስ ወጣው…ሰራተኞቹ ሁሉ ለምሳ የወጡ ቢሆንም ጸሀፊዬ ግን ስጠብቀኝ ነበር….
‹‹አሁን የቦርድ አባሎቹ ሲመጡ ይሄንን ማመልከቻ አስገቢልኝ›› አልኩና በካኪ ፓስታ የታሸገውን ማመልከቻ ሰጠዋት
‹‹አባትህ ደጋግመው ሲደውሉ ነበር…ምሳ እየጠበቅንህ ነው ፤ደውልኝ ብለውሀል…››
‹‹ዝም በይው::ስልኬን ዘግቼዋለው …ከደወለ ወጥቼ እንደሄድኩና እንደማልመለሰም ንገሪው……››
‹‹አንተ ግን ሰላም ነህ…?›ሁኔታዬ ስላላማራት መሰለኝ የጠየቀቺኝ
‹‹ሰላም ነኝ ….አመሰግናለው…››ጥያት ወጣው…..
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
.:
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ (የመጨረሻ ክፍል)
፡
❤️ፌናን
===
ይሄ እንደሚፈጠር ቀድሞውኑም ጠብቄያለው::ቀድሜ መናገር
ነበረብኝ …ግን ልረብሸው ስላልፈለኩ ነበር እንደዚህ ያደረኩት
::.ሁኔታውን እንዳወቀ አባቱ ትከሻ ላይ ገፍትሮኝ እየተመናጨቀ
ቢሮው ገብቶ ከዘጋ ቡኃላ ሶስቱም ነበር ያፈጠጡብኝ….
‹‹ምንድነው ልጄን ያደረጋችሁት…? ››አሉ አባቱ…..ያው
ያደረግሽው ለማለት ፈልጎ ነው፡፡
‹‹ምንም ያደረኩት ነገር የለም::ግን ተወዳዳሪው እኔ ትሆናለች
ብሎ ስላልጠበቀ ነው የተበሳጨው››መለስኩ
‹‹በዛማ አይበሳጭም::ጥናቱን ሲሰራ ምትረጂው አንቺ ነበርሽ
አይደል…?››
‹‹አዎ …በሙያዬ ፕሮፌሽናል በሆነ ደረጃ
ረድቼዋለው::የማውቀውን ምንም ወደኃላ አላልኩም::ምነው
ጥናቱ አሪፍ አልነበረም እንዴ…?››
‹‹ጥናቱማ ሁላችንንም ያስደመመ እንከን አልባ ነበር…››መለሱ
አባቱ ግራ በተጋባ ስሜት
‹‹ስለዚህ ምንም ያጠፋውት ነገር የለም ማለት ነው››መለስኩ
‹‹ልጄን አባሳጭተሸዋል…የክብረወርቅ ልጅ መሆንሽን አለመናገርሽ
አግባብ ስራ አልነበረም..››በጋለና በሞቀ የንዴት ስሜት
‹‹በቃ ልጄ ላይ አትጩሁባት ..ካልፈለገች አለመናገር መብቷ
ነው::የበደለችው ነገር ከለ ወይም ጥናቱ ላይ ያሳሳተችው ነገር
ካለ ለቦርዱ አቤቱታውን ማቅረብ ይችላል…››እናቴ ተንዘረዘረች
‹‹በቃ አቀዝቅዙት..አሁን እሱ ትንሽ ይረጋጋ እኛ ወደ ምሳው
እንሂድ››አቶ ከበደ ናቸው የተናገሩት
‹‹ሂዱ እኔ ከልጄ ጋር ነው የምበላው ..ጠብቀዋለው››
‹‹ተው አንተ ደግሞ ሰው ሚልህን ስማ ..ትደውልላታለህ ፡፡ቀለል
ብሎት በወጣ ሰዓት ይቀላቀለናል..››ብለው አሳመኑትና የቢሮውን
ህንፃ ለቀን ወጣን..እኔ ግን አብሬያቸው ወደ ሆቴል አልሄድም
አልኩ::ቢቆጡኝም አለሰማዋቸውም::ብቻዬን መሆን ነው
የፈለኩት::የሰራውትን ነገረ ሁሉ አምኜበትና አስቤበት ቢሆንም
ፍሰሀን የመከፋት መጠን ባየው ጊዜ ከፋኝ::ይሄን የመከፋት
ስሜት ደግሞ ብቻዬን ነው ማጣጣም የምፈልገው….
እንግዲህ ለአምስት ሆነን ልንቋደስ የነበረው የምሳ ፕሮግራም
ወደ ሶስት ሰው ዝቅ አለ ማለት ነው፡፡
ሰዓቱ ከቀኑ 8፡10 ሆኖል ፡፡አሁን እራሴን አረጋግቼ ቅድመ
ዝግጅቴን ጨርሼ ሶስቱ የቦርድ አባላት ፊት ለፊት
ቆሜያለው::የጥናት ወረቀቴን ከቦርሳዬ አወጣውና ለሶስቱም
አደልኩ::ሶስቱም ላይ ግራ መጋባት አየው::ሽማግሌው አቶ ከበደ
ግራ ገብቷቸዋል::የፍሰሀ አባት ፈገግ አሉ ::እናቴ ፊቷን
ጨመደደች እና እንደውም ይባስ ብላ በንቀት መልክ ከ10 ገጽ
የማይበልጠውን የጥናት ወረቀቴን በሁለት ጣቷ አንጠልጥላ
እያወዛወዘች‹‹በቃ››አለቺኝ
‹‹ምኑ…?››
‹‹ለወራት ውስጥ ያዘጋጀሽው የመወዳደሪያ የጥናት ወረቀትሽ
ይሄው ብቻ ነው…?››ምን ታርግ መቶ ገፅ ሊሞላ ትንሽ ገጽች
ከሚጎድሉት የፍሰሀ የጥናት ወረቀት ጋር ስታነፃፅረው ከወዲሁ
ሀሞቷ ፈሶ ነው፡፡
‹‹አንዴ የቀረበው ቀርቦል…. እንስማው››አለ የፍሰሀ አባት
ጨፍግጎት የነበረው ስሜት ለቆትና ኩርፊያውንም ረስቶት..
‹‹እሺ ቀጥለላው.. ››ስል..በራፉ ተንኳኳ::ፍሰሀ ሊበጠብጥን
መጣ ይሆን እንዴ……?ወዲያው በሀሳቤ የተሰነቀረ ክፉ ሀሳብ
ነበር
‹‹ይቅርታ… ››አልኩን ሄጄ ስከፍት የፍሰሀ ፀሀፊ ነች
‹‹ይቅርታ ይሄን ለእነሱ ልሰጥ ነበር››አለቺኝ የሆነ ካኪ ፖስታ
አንከርፍፋ
‹‹አንጪ እኔ ልስጥልሽ››
እንደማቅማማት እያለች ሰጠቺኝ..በራፉን ዘጋውና ሂጄ ለጋሽ ከበደ
ሰጠዋቸው..
‹‹ምንድነው…?››
‹‹እኔ እንጃ የፍሰሀ ፀሀፊ ነች ያመጣችው››
<<.አባትዬው ከጋሽ ከበደ እጅ ፓስታውን መንጭቀው ተቀበሉትና
ሸረከቱት …ከዛ ለብቻቸው ያነቡት ጀመር…ምን ይፈጠር ይሆን…?
ብለን ሌሎቻችን በንቃት እየጠበቅን ነው ‹‹ያው ደስ ይበልሽ
ያለውድድር አሸንፈሻል››አሉኝ አንብበው እንደጨረሱ እኔ ላይ
አፍጥጠው
‹‹ምንድነው እሱ…?›› ጋሽ ከበደ ናቸው ጠያቂው
‹‹ያው ስራውን አልፈልግም የሚል ማመልከቻ ነው ያስገባው…
መቼስ ይሄንን አይነት ስውር ብልሀት ከእናትሽ ነው
የወረሺው::ሳትፋለሚ በብልጠት ማሸነፍን ››
‹‹ሰውዬ ምን እያወራህ ነው…?››እናቴ ነች በእሱ ልክ ግላና
እየተንዘረዘረች ዘራፍ ተደፈርኩ በሚል ሰሜት የተናገራቸው
‹‹በቃችሁ…››እኔ ነኝ መሀከል የገባውት..‹‹ይሄ የልጆች ጫወታ
አይደለም::እናንተ በመሀከላችሁ ያለውን የግል ንትርክ በአኔ
አሳባችሁ ማወራረድ አትችሉም::እኔ የተዘጋጀውበትን ሳለቀርብ
ከዚህ አልወጣም::ሳልወዳደርም ማሸነፍ የምፈልግ ሰው
አይደለውም::ምክንያቱም የፍሰሀ አባት አንድ የማያውቁት ነገር
ያለ ይመስለኛል… እኔ የእናቴ ልጅ ብቻ ሳልሆን የአባቴም ልጅ
ነኝ::አባቴ ደግሞ ገነትም ቢሆን በአቋራጭ እንድገባ አድርጎ
አላሳደገኝም…. ››
ጋሽ ከበደ በዛ እርገታቸው መሀከል ገቡ‹‹እወነቷን ነው…የፍሰሀን
ጉዳይ ቡኃላ እንዴት ማድረግ እንዳለብን እንመክራለን::ፕሮግራሙ
ግን በዕቅዱ መሰረት መቀጠል አለብን::ትልልቅ ሰዎች አይደለን
እንዴ…? ስሜታዊ መሆን አሁን ምን ይረባል……?››
‹‹መልስ እንዲመልሱ እድል ሳልሰጣቸው ቀጠልኩ
‹‹አመሰግናለው::ምን አልባት ያቀረብኩት የጥናት ወረቀት መጠን
አነስ ያለች በመሆኗ ከተመደበልኝ ጊዜ ውስጥም ስልሳ ፐርሰንቱን
ብቻ ተጠቅሜ ሙሉውን ዝግጅት ለማጠናቀቅ
እሞክራለው::ስለዚህ ሁላችሁም ምናባችውን ሰብሰብ አድርጋችሁ
በትኩረት እንድትከታተሉኝ እየጠየቅኩ ቀጥታ ወደ ገለፃዬ
እገባለው፡፡››
ካምፓኒው የተቋቋመበት ዓላማ ምንድነው…?ለካምፓኒው
ባለቤቶች ደለብ ያለ ትርፍ በየዓመቱ ማስገኘት?መቶና ሁለት መቶ
ለሆኑ ዜጎች ቋሚ ስራ መፍጠር .. …?ከ5መቶ እስከ 1 ሺ
ለሚሆን ጊዜያዊ ሰራተኞች የስራ እድል መፍጠር..…?ለመንግስት
ግብር በማስጋባት የዜግነት ግዴታን መወጣት…? በቃ ይሄ ነው
…..…?
እርግጥ ሶስት ሰዎች ያቋቋሙት ካምፓኒ እንዲህ ውጤታማ ሆኖ
በዚህ መጠን ለሌሎችም ሆነ ለሀገር ጥቅም ከሰጠ አስደሳች
ነው…ስኬታማ የሚያሰኝ ነው…ግን በእኔ አስተያየት ተራ ስኬትና
ተራ አላማ ነው፡፡….እኔ ይሄ ካምፓኒ ልዩ እና የማይቻለውን ነገር
አስችሎ ለመላ ሀገሪቱ እንዲያሳይ ነው የምፈልገው…
ኢትዬጵያ 20 ሚሊዬን ዜጎቾ ከድህነት ወለል በታች የሚኖሩባት
ሀገር መሆን ነበረባት…?ዘወትር በስደት በየባህሩ የምናልቅ
ህዝቦች መሆን አለብን…? ፡፡ይሄ ቁጭት በውስጤ አለ ፡፡ከዚህም
ቁጭት የተመዘዙ የራሴ የሆኑ ሁለት እቅዶች አሉኝ፡፡አንደኛ
በሚቀጥሉት አስር አመት ውስጥ ውጤታማ የቢዝነስ ሰው
በመሆን ሀገሬንና ህዝቤን መርዳት …ሁለተኛ ከአስርአመት ቡኃላ
በቢዝነስ ያገኘውትን እውቅና እና ጥበብ ይዤ ወደፓለቲካ
መግባት እና የዛሬ ሀያ አመት ከተራዘመም ሀያ አምስት አመት
ድረስ ይህቺን ሀገር መምራት …
‹‹ማለት…?››አለች እናቴ በአግራሞት..
‹‹ጠቅላይ ሚኒስቴር መሆን…እና ይህን የሀብት ምንጫችሁ ብቻ
ሳይሆን የስማችሁ መጠሪያ የሆነውን ካማፓኒያችሁን የምፈልገው
መጀመሪያ ለራሴ አላማ ነው…፡፡ካፓኒውን በተለየ መልኩ
ውጤታማ አድርጌ ለዚህች ሀገር የቢዝነስ ሞዴል እንዲሆን
በማድረግ የራሴን ስም መገንባት::ያንን ማድረግ ከቻልኩ
የእናንተን ፍላጎት ብቻ ሳይሆን የራሴንም ህልም ነው
የማጨልመው…
እና እንዴት አድርገሽ ነው የተለየ ካምፓኒ የምታደርጊው……?.በእኔ
እምነት በአሁኑ የካማፓኒ አካሄድ ለሀገሪቱ እድገት እየተጋለ እና
የራሱን አስተዋፅኦ እያበረከተ ነው? አዎ ትክክል ነው…
በተቃራኒውን ለሀገሪቱ ውድቀትም በተመሳሳይ አስተዋጽኦ ቀላል
አይደለም…
ንግግሬን ገታ አድርጌ የሶስቱንም ፊት ሳይ ልጅቷ አብዳለች እንዴ
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
፡
✍
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ (የመጨረሻ ክፍል)
፡
❤️ፌናን
===
ይሄ እንደሚፈጠር ቀድሞውኑም ጠብቄያለው::ቀድሜ መናገር
ነበረብኝ …ግን ልረብሸው ስላልፈለኩ ነበር እንደዚህ ያደረኩት
::.ሁኔታውን እንዳወቀ አባቱ ትከሻ ላይ ገፍትሮኝ እየተመናጨቀ
ቢሮው ገብቶ ከዘጋ ቡኃላ ሶስቱም ነበር ያፈጠጡብኝ….
‹‹ምንድነው ልጄን ያደረጋችሁት…? ››አሉ አባቱ…..ያው
ያደረግሽው ለማለት ፈልጎ ነው፡፡
‹‹ምንም ያደረኩት ነገር የለም::ግን ተወዳዳሪው እኔ ትሆናለች
ብሎ ስላልጠበቀ ነው የተበሳጨው››መለስኩ
‹‹በዛማ አይበሳጭም::ጥናቱን ሲሰራ ምትረጂው አንቺ ነበርሽ
አይደል…?››
‹‹አዎ …በሙያዬ ፕሮፌሽናል በሆነ ደረጃ
ረድቼዋለው::የማውቀውን ምንም ወደኃላ አላልኩም::ምነው
ጥናቱ አሪፍ አልነበረም እንዴ…?››
‹‹ጥናቱማ ሁላችንንም ያስደመመ እንከን አልባ ነበር…››መለሱ
አባቱ ግራ በተጋባ ስሜት
‹‹ስለዚህ ምንም ያጠፋውት ነገር የለም ማለት ነው››መለስኩ
‹‹ልጄን አባሳጭተሸዋል…የክብረወርቅ ልጅ መሆንሽን አለመናገርሽ
አግባብ ስራ አልነበረም..››በጋለና በሞቀ የንዴት ስሜት
‹‹በቃ ልጄ ላይ አትጩሁባት ..ካልፈለገች አለመናገር መብቷ
ነው::የበደለችው ነገር ከለ ወይም ጥናቱ ላይ ያሳሳተችው ነገር
ካለ ለቦርዱ አቤቱታውን ማቅረብ ይችላል…››እናቴ ተንዘረዘረች
‹‹በቃ አቀዝቅዙት..አሁን እሱ ትንሽ ይረጋጋ እኛ ወደ ምሳው
እንሂድ››አቶ ከበደ ናቸው የተናገሩት
‹‹ሂዱ እኔ ከልጄ ጋር ነው የምበላው ..ጠብቀዋለው››
‹‹ተው አንተ ደግሞ ሰው ሚልህን ስማ ..ትደውልላታለህ ፡፡ቀለል
ብሎት በወጣ ሰዓት ይቀላቀለናል..››ብለው አሳመኑትና የቢሮውን
ህንፃ ለቀን ወጣን..እኔ ግን አብሬያቸው ወደ ሆቴል አልሄድም
አልኩ::ቢቆጡኝም አለሰማዋቸውም::ብቻዬን መሆን ነው
የፈለኩት::የሰራውትን ነገረ ሁሉ አምኜበትና አስቤበት ቢሆንም
ፍሰሀን የመከፋት መጠን ባየው ጊዜ ከፋኝ::ይሄን የመከፋት
ስሜት ደግሞ ብቻዬን ነው ማጣጣም የምፈልገው….
እንግዲህ ለአምስት ሆነን ልንቋደስ የነበረው የምሳ ፕሮግራም
ወደ ሶስት ሰው ዝቅ አለ ማለት ነው፡፡
ሰዓቱ ከቀኑ 8፡10 ሆኖል ፡፡አሁን እራሴን አረጋግቼ ቅድመ
ዝግጅቴን ጨርሼ ሶስቱ የቦርድ አባላት ፊት ለፊት
ቆሜያለው::የጥናት ወረቀቴን ከቦርሳዬ አወጣውና ለሶስቱም
አደልኩ::ሶስቱም ላይ ግራ መጋባት አየው::ሽማግሌው አቶ ከበደ
ግራ ገብቷቸዋል::የፍሰሀ አባት ፈገግ አሉ ::እናቴ ፊቷን
ጨመደደች እና እንደውም ይባስ ብላ በንቀት መልክ ከ10 ገጽ
የማይበልጠውን የጥናት ወረቀቴን በሁለት ጣቷ አንጠልጥላ
እያወዛወዘች‹‹በቃ››አለቺኝ
‹‹ምኑ…?››
‹‹ለወራት ውስጥ ያዘጋጀሽው የመወዳደሪያ የጥናት ወረቀትሽ
ይሄው ብቻ ነው…?››ምን ታርግ መቶ ገፅ ሊሞላ ትንሽ ገጽች
ከሚጎድሉት የፍሰሀ የጥናት ወረቀት ጋር ስታነፃፅረው ከወዲሁ
ሀሞቷ ፈሶ ነው፡፡
‹‹አንዴ የቀረበው ቀርቦል…. እንስማው››አለ የፍሰሀ አባት
ጨፍግጎት የነበረው ስሜት ለቆትና ኩርፊያውንም ረስቶት..
‹‹እሺ ቀጥለላው.. ››ስል..በራፉ ተንኳኳ::ፍሰሀ ሊበጠብጥን
መጣ ይሆን እንዴ……?ወዲያው በሀሳቤ የተሰነቀረ ክፉ ሀሳብ
ነበር
‹‹ይቅርታ… ››አልኩን ሄጄ ስከፍት የፍሰሀ ፀሀፊ ነች
‹‹ይቅርታ ይሄን ለእነሱ ልሰጥ ነበር››አለቺኝ የሆነ ካኪ ፖስታ
አንከርፍፋ
‹‹አንጪ እኔ ልስጥልሽ››
እንደማቅማማት እያለች ሰጠቺኝ..በራፉን ዘጋውና ሂጄ ለጋሽ ከበደ
ሰጠዋቸው..
‹‹ምንድነው…?››
‹‹እኔ እንጃ የፍሰሀ ፀሀፊ ነች ያመጣችው››
<<.አባትዬው ከጋሽ ከበደ እጅ ፓስታውን መንጭቀው ተቀበሉትና
ሸረከቱት …ከዛ ለብቻቸው ያነቡት ጀመር…ምን ይፈጠር ይሆን…?
ብለን ሌሎቻችን በንቃት እየጠበቅን ነው ‹‹ያው ደስ ይበልሽ
ያለውድድር አሸንፈሻል››አሉኝ አንብበው እንደጨረሱ እኔ ላይ
አፍጥጠው
‹‹ምንድነው እሱ…?›› ጋሽ ከበደ ናቸው ጠያቂው
‹‹ያው ስራውን አልፈልግም የሚል ማመልከቻ ነው ያስገባው…
መቼስ ይሄንን አይነት ስውር ብልሀት ከእናትሽ ነው
የወረሺው::ሳትፋለሚ በብልጠት ማሸነፍን ››
‹‹ሰውዬ ምን እያወራህ ነው…?››እናቴ ነች በእሱ ልክ ግላና
እየተንዘረዘረች ዘራፍ ተደፈርኩ በሚል ሰሜት የተናገራቸው
‹‹በቃችሁ…››እኔ ነኝ መሀከል የገባውት..‹‹ይሄ የልጆች ጫወታ
አይደለም::እናንተ በመሀከላችሁ ያለውን የግል ንትርክ በአኔ
አሳባችሁ ማወራረድ አትችሉም::እኔ የተዘጋጀውበትን ሳለቀርብ
ከዚህ አልወጣም::ሳልወዳደርም ማሸነፍ የምፈልግ ሰው
አይደለውም::ምክንያቱም የፍሰሀ አባት አንድ የማያውቁት ነገር
ያለ ይመስለኛል… እኔ የእናቴ ልጅ ብቻ ሳልሆን የአባቴም ልጅ
ነኝ::አባቴ ደግሞ ገነትም ቢሆን በአቋራጭ እንድገባ አድርጎ
አላሳደገኝም…. ››
ጋሽ ከበደ በዛ እርገታቸው መሀከል ገቡ‹‹እወነቷን ነው…የፍሰሀን
ጉዳይ ቡኃላ እንዴት ማድረግ እንዳለብን እንመክራለን::ፕሮግራሙ
ግን በዕቅዱ መሰረት መቀጠል አለብን::ትልልቅ ሰዎች አይደለን
እንዴ…? ስሜታዊ መሆን አሁን ምን ይረባል……?››
‹‹መልስ እንዲመልሱ እድል ሳልሰጣቸው ቀጠልኩ
‹‹አመሰግናለው::ምን አልባት ያቀረብኩት የጥናት ወረቀት መጠን
አነስ ያለች በመሆኗ ከተመደበልኝ ጊዜ ውስጥም ስልሳ ፐርሰንቱን
ብቻ ተጠቅሜ ሙሉውን ዝግጅት ለማጠናቀቅ
እሞክራለው::ስለዚህ ሁላችሁም ምናባችውን ሰብሰብ አድርጋችሁ
በትኩረት እንድትከታተሉኝ እየጠየቅኩ ቀጥታ ወደ ገለፃዬ
እገባለው፡፡››
ካምፓኒው የተቋቋመበት ዓላማ ምንድነው…?ለካምፓኒው
ባለቤቶች ደለብ ያለ ትርፍ በየዓመቱ ማስገኘት?መቶና ሁለት መቶ
ለሆኑ ዜጎች ቋሚ ስራ መፍጠር .. …?ከ5መቶ እስከ 1 ሺ
ለሚሆን ጊዜያዊ ሰራተኞች የስራ እድል መፍጠር..…?ለመንግስት
ግብር በማስጋባት የዜግነት ግዴታን መወጣት…? በቃ ይሄ ነው
…..…?
እርግጥ ሶስት ሰዎች ያቋቋሙት ካምፓኒ እንዲህ ውጤታማ ሆኖ
በዚህ መጠን ለሌሎችም ሆነ ለሀገር ጥቅም ከሰጠ አስደሳች
ነው…ስኬታማ የሚያሰኝ ነው…ግን በእኔ አስተያየት ተራ ስኬትና
ተራ አላማ ነው፡፡….እኔ ይሄ ካምፓኒ ልዩ እና የማይቻለውን ነገር
አስችሎ ለመላ ሀገሪቱ እንዲያሳይ ነው የምፈልገው…
ኢትዬጵያ 20 ሚሊዬን ዜጎቾ ከድህነት ወለል በታች የሚኖሩባት
ሀገር መሆን ነበረባት…?ዘወትር በስደት በየባህሩ የምናልቅ
ህዝቦች መሆን አለብን…? ፡፡ይሄ ቁጭት በውስጤ አለ ፡፡ከዚህም
ቁጭት የተመዘዙ የራሴ የሆኑ ሁለት እቅዶች አሉኝ፡፡አንደኛ
በሚቀጥሉት አስር አመት ውስጥ ውጤታማ የቢዝነስ ሰው
በመሆን ሀገሬንና ህዝቤን መርዳት …ሁለተኛ ከአስርአመት ቡኃላ
በቢዝነስ ያገኘውትን እውቅና እና ጥበብ ይዤ ወደፓለቲካ
መግባት እና የዛሬ ሀያ አመት ከተራዘመም ሀያ አምስት አመት
ድረስ ይህቺን ሀገር መምራት …
‹‹ማለት…?››አለች እናቴ በአግራሞት..
‹‹ጠቅላይ ሚኒስቴር መሆን…እና ይህን የሀብት ምንጫችሁ ብቻ
ሳይሆን የስማችሁ መጠሪያ የሆነውን ካማፓኒያችሁን የምፈልገው
መጀመሪያ ለራሴ አላማ ነው…፡፡ካፓኒውን በተለየ መልኩ
ውጤታማ አድርጌ ለዚህች ሀገር የቢዝነስ ሞዴል እንዲሆን
በማድረግ የራሴን ስም መገንባት::ያንን ማድረግ ከቻልኩ
የእናንተን ፍላጎት ብቻ ሳይሆን የራሴንም ህልም ነው
የማጨልመው…
እና እንዴት አድርገሽ ነው የተለየ ካምፓኒ የምታደርጊው……?.በእኔ
እምነት በአሁኑ የካማፓኒ አካሄድ ለሀገሪቱ እድገት እየተጋለ እና
የራሱን አስተዋፅኦ እያበረከተ ነው? አዎ ትክክል ነው…
በተቃራኒውን ለሀገሪቱ ውድቀትም በተመሳሳይ አስተዋጽኦ ቀላል
አይደለም…
ንግግሬን ገታ አድርጌ የሶስቱንም ፊት ሳይ ልጅቷ አብዳለች እንዴ
👍8