አትሮኖስ
273K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
436 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
A:
#የወድያነሽ


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል


....እሑድ ከሰዓት በኋላ.….ስለ ለጎ ሐይቅ ከተማና አካባቢዋ ኣንድ ባንድ ካወራችልኝ በኋላ የሕሊናዋን ትዝታ ወደ ደሲ መልሳ ስለ በርበሬ ገንዳ ሙጋድ፣ ዳውዶ ገራዶ፣ ሆጤ፤ ሶሳ፣ አዘዋ ገደል ሰኞ ገበያ…. ነገረችኝ፡፡ «ቆየኝ ደግሞ ሥራዬን ጨርሼ ልምጣና አወራልሃለሁ» ብላ ካልጋው ጫፍ ላይ ሸርተት ብላ ሔደች፡፡ ከግማሽ ሰዓት በኋላ ሥራዋን አጠናቃ ከተፍ አለች::ነጣ ያለ ቦላሌና ሰማያዊ ሸሚዝ ለብሼ አልጋው ላይ በጀርባዬ ተንጋልዬ
የጋሻዬነህን ሥዕል አንጋጥጬ ስመለከት ደረሰች፡፡ ሲሠውረኝ አላየችብኝም፡፡
ትከሻዬ ሥር ጣል አድርጌ ተኛሁበት፡፡ አልጋው ጫፍ ላይ ተቀምጣ በሆዴ
ላይ እጂን አሻግራ በመመርኮዝ ከደረቷ ዘንበል አለች፡፡ ትከሻዋ ላይ የነበረችው ባለ አረንጓዴ ጥለት ያንገት ልብስ ተንሸራተተችና የተዘረጋችውን እጅዋን ሸፈነቻት፡፡ ከደረቴ በታች የሆዴ አካባቢ በድንኳን ውስጥ ያላ ነጭ አግዳሚ መቀጫ መሰለ፡፡

ያን በሆዴ ላይ ዐልፎ አልጋው ላይ እንደ ካስማ የተተከለውን እጅዋን በቀኝ እጄ እያሻሽሁ ምናልባት ቅር ይላት ይሆን? በማለት ስፈራ ስቸር ከቆየሁ በኋላ የወዲያ፣ አንድ ነገር ብጠይቅሽ ቅር ይልሻል?» አልኳት፡፡ አሽቆልቁላ ዐይን ዐይኔን ትክ ብላ እያየች ምንስ ነገር ብትጠይቀኝ ምን ብዬ እቀየማለሁ? ስል ጠይቀኝ ልንገርህ? ብላ አቀማመጡዋን አመቻቸች።

ለሁለት ደቂቃ ያህል ውስጥ ውስጡን ሐሳቢን አንቀረቀብኩ፡፡ እንግዲህ
ያለችውን ትበል አልኩና «የወዲያ! ለምን አስታወስከኝ ኣትበይና፣ እናትና
አባትሽ ሲሞቱ የስንት ዓመት ልጅ ነበርሽ?» አልኳት። ፈገግታዋን የቅሬታ
ደም ስለ በረዘው ፊቷ ፈዞ የክረምት ዋዜማ መሰለ፡ ውስጥ ውስጡን ራሴን
«ጌታነህ! የተዳፈነ የኅዘን ረመጥ ጫርክ፣ ያንቀላፋ ኀዘን ቀሰቀስክ» ብዩ ወቀስኩ፡፡ ደቂቃዎች ሠገሩ። ትንሽ ፈነከነክ ብላ «ምነው ምን ነካሀና ኖረሀ ኖረህ ጠየቅኸኝ?» ብላ ፊቷን የትካዜ ዐመድ ነሰነሰችበት፡፡ ካኣሁን አሁን ትጀምራለች በማለት አሰፍስፌ ጠበቅሁ፡፡ ያን እንደ አተር እምቡጥ እበጥ ብሎ የቆየ የታች ከንፈሯን በላይኛው ውብ ጥርሷ ረመጠጠችው። አንድ ጊዜ
አፈትልኮ የተነገረን ሐሳብ መልሶ መዋጥ የማይቻል በመሆኑ ችሎታዩ ከዝምታ ሊያልፍ አልቻለም። እየር ስትስብና ስታስወጣ ከፍና ዝቅ የሚለውን
ደረቷን በመመልከት ላይ እንዳለ «አባቴ ሲሞት አንዲት ፍሬ ልጅ ነበርኩ
አሉ፡፡ ትንሽ ትንሽ እንደ ሕልም ትዝ ይለኛል፡፡ እናቴም አባትሽ ከልጆቹ
ሁሉ አንቺን ይወድሽ ነበር፡፡ ሳይንት እሚባል አገር ካሉት ዘመዶቹ መኻል
የሚወዳትን አክስቱን ስለምትመስዪ የእርሷ ነገር ሆነበትና 'የወዲያነሽ የወዲያ
ሰው ብሎ ስም አወጣልሽና የወዲያዬ የወዲያነሽ አልንሽ ብላ ነገረችኝ። ልጅ
ስለ ነበርኩ ሁሉንም ኣላስታውስም እንጂ አባቴ ብዙ ጊዜ ታሞና ማቆ ማቆ
ነው የሞተው። የሞተ ዕለት ሰዎች ሁሉ ሲያለቅሱ አይቼ እኔም ትንሽ
አልቅሻለሁ፡፡ ሞት ምን እንደሆነ ስለማላውቅ ሄዶ የሚመለስ እንጂ በዚያው የሚቀር አይመስለኝም ነበር፡፡ ሬሳውን በአልጋ ይዘው ከቤት ሲወጡ ምንም ስላልመሰለኝ ጉድሮዬን እያዘናፈልኩ ከመንደሩ ልጆች ጋር እቦርቅ ነበር፡፡
ታናሽ እኅቴ እማዋይሽ ክርስትና የተነሣች ዕለት መጥተው የነበሩት ቄሶች ራሱ የቀብሩም ዕለት መጥተው ስለነበር ለደስታ የመጡ እንጂ ለሌላ ነገር
የመጡ አልመሰለኝም። እያደር ግን ዋል አደር ስል ዕንጨት ለቀማም ይሁን
ዋርማ ይዤ ጅረት ስወርድ ጓደኛቼ እንደ ቀልድ 'አንቺዬ ማሳዘኗ' አንድ ቀን እኮ የሞቱት የዚች አባት ናቸው” እያሉ ሲያንሾካሽኩ እየሰማሁ ግራ ግብት ይለኝ ነበር። አባቴ ከሞተ በኋላ እዚያው አገር ቤት ከእናቴና ከእኅት ወንድሞቼ ጋር ቆየሁ፡፡ ከዚያ በኋላ ግን የእናቴ ታላቅ እኅት ከአገር ቤት ወደ ከተማ ይዛኝ መጥታ ትምህርት ቤት አስገባችኝ ብላ ዝም ስላለች ያ በኀዘን ጉም ተሸፍኖ የቆየው ዐይኔ ቦግ ብሎ ወደ የወዲያነሽ ዐይኖች ተወረወረ፡፡እንባዋ እንደ አሸንዳ ጠፈጠፍ እየተንከባለለ በጉንጯ ላይ ተንኳለለ፡፡ ልብሴ ላይ የተንጠባጠበውን ዕንባዋን ደረቁ ሸሚዜ እንደ ግንቦት አፈር ጠጣው፡ የደቀነችውን ወሬ ለመጨረስ እንባዋን ካባበሰች በኋላ «አሁንም ቢሆን እነዚያ የትምህርት ቤት ጓደኞቼ ትዝ ይሉኛል። እነ የሻረግ፣ ዘነበች፡ አሚናት፡
ይመር፣ አያሌው፣ ገበያነሽ፣ ሰኢድ ኧረ ስንቱ ስንቱ... እክስቴ ከልጆቹ ሁሉ እኔን መርጣ የወሰደችኝ የረጋች ልጅ ነች፣ ደስ ትለኛለች» ብላ ነበር። ሁለት ሦስት ጊዜ ላግባ ባይ መጥቶ ሲጠይቅ ቆይ እስኪ ጥቂት ተምራ ነው ነፍስ ትወቅ» ብላ እምቢ አለቻቸው፡፡

እኔና እርሷ ብቻችንን ተቀምጠን በምናወራበት ጊዜ ግን፡ ያም የሸማኔ ልጅ ነው፣ ያኛው መናጢ ዘረ ድሃ ነው፣ የዚያኛውም እናት ዘር ማንዘሯ ሸክላ ሠሪ ነው የጠዳ የጨዋ ልጅ እስኪመጣ ሰጥ ብለሽ ትምርትሽን ተማሪ» ትለኝ ነበር፡፡ አክስቴ ከምላሷና ከንዝንኳ በስተቀር ሆዷ ባዶ ነው::ባልዋ አይዋ ዘለቀ አንድ ሲናገሩ ሁለትና ሦስት ነበር የምትመልስላቸው:: ችለው ችለው አንድ ቀን የተነሡ ለታ ግን ቀሽልደው ቀሽልደው ሲለቋት ውሃ ውስጥ የገባች አይጥ ትሆናለች። እሷ ታዲያ የሳቸውን እልክ በኔ ላይ ነበር የምትወጣው::

«አንቺ መድረሻ ቢስ ግንባረ ነጭ» ብላ ከጀመረች በርበሬ ሳታጥነኝና በጥርሷ ሳትበተብተኝ እንገላገልም፡፡ «አፈር ብይ! አፈር ያስበላሽ! ያባትሽን ቀን ይስጥሽ» ስትለኝ ግን አይመኙ ነገር ያስመኘኝ ነበር። ለጎ-ሐይቅ በሔድኩ በአራተኛው ዓመት አገር ቤት ወረርሽኝ ገባ ተባለና እናቴ በጠና ታመመች።ያኔውኑ ትምህርት ቤት በመዘጋቱ ካልሔድኩ ብዬ አገር አመስኩ፡፡ ቢሉኝ ቢፈጥሩኝ እዚያቹ ከናቴ
ጋር እሞታታለሁ እንጂ እይደረግም ብዬ
አስቸገርኩ፡፡ በማይረባው ነገር ሁሉ ካክስቴ ጋር መነታረኩ መሮኝ ስለ ነበር
ለጥቂት ጊዜም ቢሆን ከፊቷ ገለል ብዬ እፎይ ማለት ፈልጌ ነበር። ወሬ
አበዛሁብህ መሰል? ላሳጥርልህ፣ እናቴ ቡሄ በዋላ ልክ በሳምንቱ ሞተች። ያን
እለት የሆንኩትን አኳኋን ግን ባትሰማው ይሻላል። እናቴ ፀሐይነሽ አማረ ትባል ነበር። ከዘመዶቻችን ጋር ዕርባዋን አውጥቼ ትምህርት ቤት የተከፈተ
በሳምንቱ ከዚያቹ ከአክስቴ ጋር ወደ ከተማ ተመለስኩ፡፡ ከዚያ በኋላ ግን ወደ
አገር ቤት አልተመለስኩም» ብላ ጋደም አለች፡፡ ያ የቀድሞ ውበታዋም ርዝማኔውን ሊይዝ ጥቂት የቀረው የሴትነቷ ግርማ የሆነው ዞማ ጸጉሯ በአንገቷ ዙሪያ በተንተን ብሎ ተነሰነሰ። ድንገት
ቀና ብላ እግሯን ኮርምታ ተቀመጠች፡፡ «አልጨረስኩልህም እኮ» ብላ
ቀጠለች። በበኩሌ የሕይወቷ ምሬት አንገፍግፎኝ ነበር፡፡» ያክስቴ ባል ዘኃ
ነጋዴ ነበሩ። ከደሴ ዘኃ ያመጡና፣ ከሐይቅ ደግሞ አንጋሬና ቆዳ ይዘው
ይመለሳሉ። የኋላ ኋላ ግን ደሴ መሬት ገዝተው ቤት ስለሠሩና ንብረት ስላበጁ ሁላችንም ወደዚያው ሄድን። ደሴ ወይዘሮ ስሒን ትምህርት ቤት አምስተኛ ክፍል ገባሁ፡፡ ያነዩ ገና ዐሥራ አራት ዓመቴ ነበር፡፡ አክስቴ ውሃ ቀጠነ፣ ጪስ በነነ፣ እያለች ስለምትነዛነዝ ይብስ እሳትና ጭድ ሆንን። እልህ ማብረጃ አረገችኝ፡፡ ስወጣም ስገባም ስድብና ዱላ ሆነ፡፡
ለጊዜውም ቢሆን ሌላ የሚያስጠጋኝና የምገባበት ዘመድ ስላልነበረኝ ያለችውን ብትል ታግሼ ዝም አልኩ፡፡ እንደ ምንም ብዬ ተፍጨርጭሬ ሰባተኛ ክፍል እንደ ገባሁ ከነከተቴው ሒጂልኝ! ውጪልኝ! ዐይንሽን ላፈር! ማለት አመጣች። ንግግሯ ሁሉ አንገሸገሸኝ፡፡ የዓመቱ ትምህርት ባሳር በመከራ ካለቀልኝ በኋላ ብሞትም ልሙት ብዩ ቆርጬ ተነሣሁ አንድ ቀን
ጎረቤታችን የነበሩ አንድ የጦር
#የተወጋ_ልብ


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#ድርሰት_በትክክል_ገና

....በዝናሙ ምትክ ፀሃይዋ ክርር ያለ የሚያቃጥል ጨረሯን መፈንጠቅ
ጀምራለች። ዶሮዎች በየስራስሩ፣ በየበረቱ አጥር ስር እየተሹለከለኩ ይለቃቅማሉ.. አልፎ አልፎ ከቤት ወስጥ የታሰሩ ጥጆች ድምጽ ይሰማል።
ከብቶች በየዛፉ ጥላ ስር ቆመዋል፡፡ ከዚህ ሌላ ግን ምንም አይነት ድምፅ አይሰማም፡፡ ጭር... ያለ ጭውው…. ያለ ፀጥታ!! የጌትነት መንደር በሬሳ! ሰሞኑን ጤናዋ በይበልጥ የተቃወሰውና ሃሳብ ያመነመናት አስካለ ልብሷን እንደለባበሰች ከአልጋዋ ላይ ጋደም ብላለች። ዘይኑ ከቤት አልነበረችም፡፡ ከወዲያኛው መንደር ተልካ ሄዳለች፡፡

"ካ ካ.!ካ ኩ!ኩ.ኩ!.ካ!.ካክ! ኩ! ኩክ! " ዶሮዎቹ ተንጫጩ።
“ድመት!ድመት! ሸለምጥማጥ! ሽለምጥማጥ ወስዳት ይዟት ሮጠ" የወይዘሮ አስካለ ጎረቤት የወይዘሮ ተዋበች ትንሿ ሴት ልጅ ጮኽች።
የአስካለ ዶሮ ናትኮ! ጠልፏት ሄደ? እነሱ ቤት የሉም እንዴ? እዚህ ቤቶች! ዘይኑ ኽረ ዘይኑ!.ማንም ሰው የለምንዴ?" ወደ በሩ ተጠጉ፡፡

"ማነው? ይግቡ አለሁ ይክፈቱት በሩን..." አለች በደከመ ድምፅ፡፡
“ምነው? ባሰብሽ እንዴ? አይይ.. በጣም አሞሻል ለካ?! ደምሽ ሁሉ ከፊትሽ ላይ ምጥጥ ብሎ የለምንዴ?! ዘይኑ የለችምንዴ? እኔ ኮ አሁን ልጅቷ ዶሮዋን ወስዳት ብላ ስትጮህ ነው የወጣሁት። እሳት ላይ ምናምን ጥጃለሁ"
"ምን ወስዳት?” አለች በቀሰስተኛ ድምጽ።
"ሽለምጥማጥ ነዋ! ድመት! ድመት! ስትለኝ ሮጬ ብወጣ ይዟት ቁልቁል
ሲሮጥ አየሁት። ለትንሽ አመለጠኝንጂ ቀድሜ ብወጣ ኖሮ አስጥለው ነበር። ደግሞ መርጦ ያንን ወስራውንኮ ነው የጠለፈው"
"ይልቀማቸው ጥርግ ያድርጋቸው!.." አለች በታከተ አነጋገር፡፡
"አንቺ ሴት ራስሽ ነሽኮ ይሄንን ሁሉ ችግር በራስሽ ላይ የምታመጪው። ከበሽታው የበለጠ የጎዳሽ ሀሳቡ ነውኮ! ለመሆኑ ከዚያ ወዲህ ስለ ጤንነቱ የሰማሽው ነገር አለ?"
“ምን እስማለሁ እትዬ ተዋቡ?ጋሼ አለሙም ይኸውና ብቅ አላሉም፡፡
ምን አባቴ እንደማደርግ ግራ ግብት ብሎኝኮ ነው። አገሩን አያውቅ ሰው
አያውቅ አንድ ቶሎሳን ብሎ ነው እኮ እንደ ወፍ ብርር ብሎ የወጣው።
እኔን ብርር ያድርገኝ፡፡ እኔ ልንከራተት። የአባቱ ሀዘን ከአንጀቱ ሳይወጣለት ከአገሩ ወጥቶ ሄዶ በማያውቀው አገር ቶሎሳ ደጅ አውጥቶ ከጣለው ምን ይውጠዋል እትዬ ተዋቡ? ምን አልኩት ፈጣሪዬን? አይይ”በትኩስ እንባ ምክንያት ማዲያት በጀማመረው ፊቷ ላይ እምባዋ ክንብል አል።
ተይንጂ የጌትነት እናት ምን እያደረግሽ ነው? በደህና ውለሽ እኔ ስመጣ ነውንዴ የሚብስብሽ? እስቲ ምን ሰማሁ ብለሽ ነው እንዲህ የምትሆኚው? ለትንሽዋም ቢሆን እዘኝላት እንጂ! ባንቺ ለቅሶ ትጨነቅ? በወንድሟ ናፍቆት ትጨነቅ? ወይስ በአባቷ ሀዘን? ተይ የኔ እህት እንደዚህም አይደል ጠና ጠና እያልሽ የሆድሽን በሆድሽ ይዘሽ ሀዘንሽን ደብቀሽ
ደስተኛ መስለሽ እሷንም አጽናኛትንጂ!. ዘይኑ ዕድሜዋ ትንሽ ሆነንጂ
አስተሳሰቧ ትልቅ ነው። ወይኔ አባቴ ወይኔ እናቴ እንድትል አታድርጊያት፡፡ አመዛዝኝ

“አይ እትዬ ተዋቡ መቼ እሱን ሳላስበው ቀረሁ ብለው ነው? ሆዴ እያረረ ጥርሴ ለመሳቅ እየታገለ አቃተኝንጂ፡፡ እንቅልፍ በዓይኔ አልዞር እያላ እህል አልዋጥልሽ እያለ አስቸገረኝንጂ ጉልበቱ ጥናቱ ከዳኝንጂ ለዘይንዬ መቼ ሳላስብ ቀረሁ? እህህህ.."

“በይ ነግሬሻለሁ ለቅሶሽን አቁሚ! ፈጣሪሽን እየለመንሽ አንተ ርዳው
እያልሽ በፀሎትሽ መበርታት ነው የሚያስፈልገው፡፡ ደስ ደስ ሲልሽ ደስ
የሚል ዜና ትሰሚያለሽ፡፡ በበሽታሽ ላይ ሌላ በሽታ መጨመሩ ላኔ አይታየኝም፡፡ እስቲ በወጉ ጋደም በይና የሚቀመስ እህል ይዤልሽ ልምጣ ነጠላውን አለባበሷትና ወጡ። ወዲያውኑ ዘይኑ ከተላከችበት ተመለሰች::

“እማምዬ ምን ሆነሽ ነው ዐይንሽ ያበጠው? አልቅሰሻል አይደለም?” አኮረፈች።
አይደለም! አላለቀስኩም! ዶሯችንን ሸለመጥማጥ ይዟት ሲሮጥ እሷን
ለማስጣል ስወጣ ጨረር ዐይኔን ወጋኝ መሰለኝ" ልትዋሻት ሞከረች::
"አላውቅም ውሽትሽን ነው፣ ውሸትሽን ነው እያለቀስሽ ነው ፊትሽ እንደዚህ የተበላሸው።አንቺ እያለቀስሽ ለመሞት ነው የምትፈልጊው" ከንፈሯን የበለጠ ጣለች፡፡
“ዘይንዬ አላለቀስኩም ስልሽ? ለምን አለቅሳለሁ? ደስ ይለኛልንጂ! አሁን
ጋሼ አለሙ ሲመጡ ጌትዬ የጻፈልንን ደብዳቤ ይዘውልን ይመጣሉ።
ከቶሎሳ ጋር ታርቀናል ሥራም ይዣለሁ ብሎ የጻፈውን ደብዳቤ ይዘውልን እንደሚመጡ አትጠራጠሪ! ከዚያም ጌትዬ አንቺን አዲስ አበባ ወስዶ
ሲያተምርሽ ይታየኛል” እንደ ልማዷ እቅፍ አድርጋ ስታረሳሳት የእናቷ ጉያ ሞቃት። ፀጉሯን እያከከችላት እቅፍ ስታደርጋት በዚያው ልጥፍ እንዳለችባት እንቅልፍ ያባብላት ጀመር፡፡
“እማምዬ ወንድም ጋሻ ሥራ ሲይዝ ሁለታችንም እሱ ጋ አዲስ አበባ
ሄደን አብረን እንኖራለን አይደል?" የሟች ባለቤቷን የአደራ ቃል አስታወስቻት አስካልዬ ባለተራ ሆነሽ ወደኔ ስትመጪ ከጎኔ እንዳትርቂ አደራ! " ከባሏ ጋር ብዙ ትዝታ ያሳለፈችባትን ጎጆ ጥላ የትም እንደማትኖር ታውቀዋለች፡፡ ሬሳዋ ከዚያው ባለቤቷ ካረፈበት አልጋ ላይ እንደሚነሳ በልቧ ቢታወቃትም ዘይኑን ልታስደስታት ፈለገች።

“ታዲያስ ምን ጥርጥር አለው? ጌትዬ ሥራ ይዞ እኔንም አንቺንም አዲስ አበባ ወስዶን ደስ ብሎን አብረን እንኖራለን ምን ይጠየቃል?”
ስትላት ዘይኑ በደስታ ተፍነከነከች። በዚሁ መሀል.. "ሴቶች" አሉና ገቡ።
ወይዘሮ ተዋቡ ነበሩ።
“ዘይኑ መጣሽ እንዴ? በይ እስቲ ቀና በይ የጌትዬ እናት ይህችን ቅመሽ በሽሮ ፈትፈት አድርገው ያመጡትን እንጀራ በግድ ያጎርሷት ጀመር መቼም ከሩቅ ዘመድ የቅርብ ጎረቤት መድሀኒት ነው የሚባለው እውነት ነው። የምግብ ፍላጎቷ ጠፍቶ ባዶ ሆዷን ነበረች፡፡
አይ እትዬ ተዋቡ ምን አሳሰበሁ? አልበላ አለኝንጂ ዘይንዬ የሰራችው ሽሮ ነበርኮ አይ የርስዎ ነገር?” የምግብ ፍላጎቱ ባይኖራትም የሚያስቡላት ጎረቤቷን ላለማስቀየም ስትል ጎራረስች፡፡ እናቷ በጤናዋ ምክንያት እንደ ልቧ ወዲህ ወዲያ ማለት ባለመቻሏ ከትምህርት ቤት ሰዓት ውጭ ዘይኑ ወደ ገበያ ትሄድና ሽንኩርቱን፣ ድንቹን፣ ቃሪያውን፣ ጎመኑን እየሽጠች በምታገኛት ሳንቲም እናቷን ታስታምማለች። ካሉት ሁለት ላሞች
መካከል አንዷ የምትታለብ ስለሆነች ወተቷን ያጠራቅሙና ከተናጠ በኋላ
ለአናት የሚሆን ቅቤ በኩባያ እያደረጉ ወደ ገበያ ይወጣሉ፡፡ አሬራው ይቀ
ቀልና አይቡ ይሽጣል። አጓቷን እነሱ ይጠጣሉ፡፡
“እማማ ይህቺ እማዬን ለምንድነው የማይመክሯት? ሁልጊዜ እያለቀስች ፊቷን አበላሸችውኮ የምሰራላትን ደግሞ አልበላም እያለች ታስቸግረኛለች፡፡ ሁል ጊዜ ቡና ብቻ ነው የምትጠጣው" እንደ ልማዷ ከንፈሯን ጣል አድርጋ ወቀሳዋን ሰነዘረች። ወይዘሮ ተዋቡ የልጅቷ ነገር አንጀታቸውን በላው። ዘይኑ በአስተሳሰቧና በአነጋገሯ የአስራ ሁለት ዓመት ልጅ
አትመስልም፡፡ ነገረ ስራዋ እንደ አዋቂ ነው።

"የውልሽ የጌትነት እናት እንኳን እኛ አሮጊቶቹ ትንሽዋ ልጅሽ የምትልሽን ትሰሚያለሽ? እሷኮ እየበለጠችሽ ነው። መኩሪያንም ቢሆን መከራሽን አይተሽ አስታመሽው የግዜር ፈቃዱ ሆኖ ነው ወደ እውነቱ ቦታ የሄደው፡፡ መቼም ሰው ጊዜው ከደረስ ምን ይደረጋል? በሀዘን ብዛት
በለቅሶ ብዛትም ከአፈር የሚነሳ የለም፡፡ ጌትነትንም ቢሆን የልቡ እንዲሳካለት መርቀን የሸኘነው ራሱን ችሎ ላንችም አለኝታ እንዲሆንሽ ነው።
ባለበት ጤና ይሁን እንጂ ምን እንዳይሆን ብለሽ ነው? ሰው ሆኖ ችግርን
የማይቀምስ የለም ችግርን አሽንፎ ደካማ እናቱን መጦር እህቱን ማስተማር እንዲችል በፀሎትሽ ያለመርሳትንጂ
#የተወጋ_ልብ


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#ድርሰት_በትክክል_ገና


ለተከታታይ ቀናት ድርሰቶቹን ባለመልቀቄ
ይቅርታ እጠይቃለው የ Telegram app Update መደረግ እንዳለበት text ይመጣልኝ ነበር ባለማድረጌ አንድ ሁለት ቀን እስከሚስተካከል አስቸግሮኝ ነበር አሁን ግን የተስተካከለ ይመስለኛል እንቀጥላለን መልካም ንባብ።👇


.....“ጎንቻ! ቂጥህን ጠርጌ አሳድጌህ አንተም ሰው ሆንክና ለዚህ አበቃኸኝ?!” አለው በሚርበተበት ድምፅ፡፡ ጎንቻ ብልጭ! አለበት። “አንተም ሰው ሆንክና?” የሚለው የንቀት አነጋገር የንዴት ክብሪቱን በላዩ ላይ ጫረበት። መታገስ አቃተው፡፡ ከመቅፅበት እጁ በወገቡ ላይ ከዚያም
ከቶላ አንገት ጋር ተዋህዶ ጭንቅላቱ እያሽካካ ከበሩ ላይ ሲወድቅ የነበረው ፍጥነት እግዚኦ! የሚያሰኝ ነበር፡፡ ይህንን ትዕይንት ለሚያዩ እናትና ልጅ ጥናቱን ይስጣቸው እንጂ ጎንቻ ዶሮ ያረደ እንኳ አልመሰለውም፡፡
አወራረደውና እንጣጥ እንጣጥ….እያለ የወደቀውን አንገት ተራምዶት ሄደ ...
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ከማህፀኗ በወጣው ጉድ እንደ እሳት እየተለበለበች ነጋ ጠባ እንደተሸበረች የከረመችው ወልአርጊ ለጥቂት ጊዜ ሰላም ሰፍኖባት ነበር። ዛሬ ግን የተፈጠረው ትርዒት ከወትሮው ለየት ያለ በመሆኑ መከራዋና ሀዘኗ ሁሉ መሪር ሆኗል፡፡ እናትና ልጅ ከአልጋ ጋር ተጠፍረው ታስረው አኖቻቸው እየተቁለጨለጩ የቶላ አንገት ሲቀላ ተመለከቱ..ጩኸቱ ከአንደኛው ጎጆ ወደ ሌላው ከዚህኛው መንደር ወደዚያኛው መንደር አስተጋባ።ብራቅ...ከወልአርጊ ዘወትር ፊቷ ወደማይፈታው በጭጋግ ወደ
ተሸፈነችው ወደ ሞዬ መንደር ደረሰ፡፡ ከዚያም ወደ አኖሌ...ከዚያም ወደ ዩያ...መቼም በዘረፋው በኩል በትንሹ ፍየል ያልተሰረቀበት ጥቂቱ በመሆኑ ሁሉም ንብረቱን በዐይነ ቁራኛ በመጠባበቅ ብርቱ ጥንቃቄ በማድረግ ላይ ነው፡፡ ዛሬ የተከሰተው በአይነቱ ለየት ያለ ከተራ ሌብነት የዘለለና ለመንደሪቱ ነዋሪዎች እጅግ አስደንጋጭ የሆነ ግድያ የታከለበት የከብቶች ዝርፊያ ወንጀል ነበር። ወልአርጊ አሰቃቂውን መርዶ ለማርዳት እኩለሌሊት ለሊቱን ስታምጥ አንግታ ከጠዋቱ አሥራ ሁለት ሰዓት አካባቢ ጭንቀቷን በእሪታ ተነፈሰችው...ከአጋም የተጠጋ ቁልቋል ዘላለም ሲያለቅስ ይኖራል ሆነና የሐጂ ቦሩ ጎረቤት ቶላና ቤተሰቦቹ በጎንቻ ምክንያት በተደጋጋሚ ከማንባት ባለፈ የቶላን የህይወት ዋጋ እስከማስከፈል
የደረስ ጥቃት ሰለባዎች ሆኑ፡፡ በቶላ ቤተሰቦች ጩኽት ምክንያት የተቀሰቀሰው ህዝብ ለመስቀል በዓል እንደሚጎርፍ ምእመን ተመመና የቶላን ግቢ አጨናነቃት። የጎንቻ ወላጆች ምጥ በምጥ ሆኑ፡፡ እህ! እህ! ጭንቀት
በጭንቀት። ቀስ በቀስ ቤታቸውን አራቁቶ ከብቶቹን ሸጦ ከጨረሰ በኋላ
በአብዛኛው የሚተዳደሩት በትላልቅ ልጆቻቸው ድጎማ ነበር፡፡ ሽብር የተቀላቀለበት ዘረፋ መፈፀም የጀመረው ልጃቸው እያጎረሰ፣ ጭንቅላቱን እየደባበስ፣ ንፍጡን እየጠራረገ እንደ ወላጅ ያሳደገው ቶላን በአሰቃቂ ሁኔታ
አንገቱን እንደ ጎመን ቀንጥሶት ሄደ መቼም የእናቱ የወይዘሮ ዋሪቴ ሁኔታ አይነሳ፡፡እግራቸው መሬቱን ቆንጥጦ መያዝ አቃተውና ተብረከረኩ፡፡ የህዝቡ ዋይታና ለቅሶ በነሱ ላይ መዓቱን ያውርድባችሁ በሚል የእርግማን ጩኸት የተሞላ ነበር፡፡
“ጎንቻ! ጎንቻ! በላን! ፈጀን!የአውሬ የጅብ እናት! የአውሬ አባት! እግዚአብሔር ይይላችሁ! አይዞህ እያላችሁ በሌብነት አሳድጋችሁ አስፈጃችሁን! የዚህ ሁሉ ቁጣ የዚህ ሁሉ ግፍ ተጠያቂዎች እናንተ ናችሁ! ጥፉ ያጥፋችሁ!” የማይል የአልቃሽ አንደበት አልነበረም።

ሐጂ ቦሩ በባለቤታቸው ምክር መስረት ዘመድ አዝማዱን እየተማፀኑ
ወደ ቤቱ እንዲመለስ ሽማግሌ ልከው የሚያስለምኑበትን ቀን በተስፋ
ሲጠባበቁ፣ ገበየሁን ገድሎ መሸፈቱ ተሰማ፡፡ በዚህም ምክንያት ተስፋ
ቆርጠው ዕለተ ሞቱ እንዲቃረብ፣ የጅብ ራት ሆኖ እንዲቀርና በመቃብሩ ላይ አልቃሽ እንዳይቆምለት ፈጣሪያቸውን ሲለምኑ እሱ ግን በአቋራጭ መጣና ልክ እንደ ትንሽ ወንድማቸው የሚወዱት የክፉ ቀን ወዳጃቸው ቶላን እንደ በግ አርዶ ሄደ፡፡ ማን ያውቃል? ነገ ተነገወዲያ ደግሞ ተራው የእናትና የአባቱ ሳይሆን ይቀራል? “ያዳቆነ ሰይጣን ሳያቀስስ አይቀርም”
ነውና ጎንቻ በውስጡ ያበቀለው ቀንዳም ጋኔን ቀጥሎ የሚጠማው የዘመዶቹን ደም አለመሆኑን ማን በእርግጠኝነት መናገር ይችላል? የሰው ልጅ የማስተዋልና የማመዛዘን ችሎታው ሲዛባ፣ ከስነ ምግባር ማንነቱ ሲወጣ፣ በክፉና በመልካም ድርጊት መካከል ያለውን ልዩነት ከሚገነዘብበት የአእምሮ ብቃት ሊሸሽ፣ ራሱን ከመጠን በላይ በመውደድ መስገብገብ ሲጀምር ወደ አውሬነት መለወጡ የማይቀር ነውና ጎንቻ ከሰውነት ባህሪው ወጥቶ የክፉ ስግብግብ አውሬ ባህሪን ተላበሰ፡፡ በዚህ አካሄዱ ለሳቸውም ቢሆን እንደማይመለስላቸው የጠረጠሩት ሐጂ ቦሩ የጎንቻ ጩቤ በአንገታቸው ላይ እስከሚስካ፣ የተስበቀ ጦሩ በደረታቸው ላይ እስከሚቀረቀር ድረስ ለመጠበቅ ትዕግስት አጡ፡፡ የህዝቡን እርግማንና ጥላቻ በመቋቋም የከፈሉት ዋጋ ሳያንሳቸው የክፉም ሆነ የበጎ ጊዜ ወዳጃቸው የሚስጥረኛቸው የቶላ አሰቃቂ ግድያ በልጃቸው በጎንቻ እጅ ተፈፅሞ ማየት ግን ፍፁም ሊቋቋሙት የማይችሉት ጥቃት ሆነባቸውና በራሳቸው
እርምጃ ለመውሰድ ቆረጡ። አሮጊቷ እናትም ማህፀናቸው ጭራቕ በማፍራቱ መፈጠራቸውን ጠሉት፡፡ እግዚአብሔርን ወቀሱት። በስተመጨረሻ የተገኘው ጉድ ሰይጣን ጎብኝቷቸው እንደሆነ እንጂ እውነትም ከሐጂቦሩ የተገኘ ፍሬ መሆኑን ተጠራጠሩ፡፡ ለሁሉም ነገር አቅም አጡ፡፡ ለዋይታና ለእሪታው ልሳናቸው ተዘጋ፡፡ እምባቸው ደረቀ።

“እህህ..ጎንቻ ፈጣሪ የስራህን ይስጥህ!ከልጆቼ ሁሉ አስበልጬ አቀማጥዬ አሳድጌህ እንደሆነ ውለታውን ከሱ አትጣው! በስተርጅና በመውደቂያ ዘመኔ እናቴ ምን ልርዳሽ? ብለህ ጎኔን ልትደግፍ ተስፋ ልትሆነኝ በሚገባህ ሰዓት ከሰው እንዳልቀርብ የአውሬ እናት እየተባልኩ
ሰው እንዲሽሽኝ በመቃብሬ ላይ አልቃሽ እንዳይቆም ላደረግህልኝ ውለታ
ሼህ ሀና ሁሴን ብድሩን ይክፈሉህ! የእጅህን አትጣው።ወንድ ነኝ ብለህ
እንደፎከርክ ወንድ ይዘዝብህ...!” ብለው አለቀሱ። ከወዳጅ ዘመዶቻቸው አቆራርጦ ስማቸውን የቡና መጠጫ ባደረገው ልጃቸው የተሰማቸውን ምሬት ለፈጣሪያቸው በእምባ ገለፁ።እህቶቹና ወንድሞቹ የሚኖሩት ሩቅ ቦታ ቢሆንም ጎንቻ በየጊዜው ስለሚፈፅመው አሰቃቂ የውንብድና ተግባር እየሰሙ ተበጥብጠዋል።እነሱ ብቻ ሳይሆኑ የአካባቢው ባለስልጣን ባላባት ጉደታም ውንብድናው ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገና የጥቃት አድማሱን እያሰፋ በመጣው በጎንቻ አስከፊ ወንጀል ምክንያት ከህዝቡ በሚቀርብለት እሮሮ አእምሮው እረፍት እስከሚያጣ ድረስ ተበጥብጧል። ባልታሰበ ጊዜ ከተፍ ይልና ያምሳል፣ ያስለቅሳል፣ ያንጫጫል። አንዴ ከተሰወረ ደግሞ መኖሩ እስከሚያጠራጥር ድረስ ደብዛውን ያጠፋል። ደግሞ ሳይታሰብ ከተፍ ይልና የተለመደውን ጫጫታና ዋይታ ያስቀጥላል፡፡

የቶላ የቀብር ሥነ ሥርዓት በተካሄደ ዕለት ባላባት ጉደታ ህዝቡን በአንድ ትልቅ ዋርካ ጥላ ስር ስብስቦ የሚከተለውን ንግግር አሰማ፡፡
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ


...«አስቻለው!» አለችው ሔዋን፤ የዘመቻ ጥሪ ደብዳቤ በደረሰው አምስተኛ ቀን ላይ በዕለተ አርብ ከጠዋቱ ሦስት ሰአት አካባቢ ከቤቱ በመገኘት።

«ወይ!» አላት አስቻለው አልጋው ላይ ጋለል ብሎ ተኝቶ ከጎኑ ቁጭ
ያለችውን ሔዋንን ቀና ብሎ እየተመለከታት።
«ሰሞኑን የምሰማው ወሬ ምንድነው?» ስትል ዓይን ዓይኑን እያየች ጠየቀችው።
«ምን ሰማሽ?»
«ጥሩ ያልሆነ ወሬ::»
«ንገሪኛ!» አላት አስቻለው ፈገግ ብሎ እያያት፡፡
«ሳታውቀው ቀርተህ ነው?»
«ብዙ ይወራ የለ! የትኛውን ማለቴ ነው፡፡»
«በመሥሪያ ቤትህ በኩል ለስድስት ወር ያህል ዘመቻ ሂድ ተብለህ እምቢ ማለትህን ሰማሁ፡፡» አለችው በፍርሀት አስተያየት እያየችው።
«አዎ! አልሄድም ብያለሁ፡፡ አሁንም አልሄድም፡፡»
«ግን ለምን?»
«እንደማልሄድ የነገሩሽ ሰዎች
ምክንያቴንም ሳይነግሩሽ የቀሩ
አልመሰለኝም፡፡ አንቺም አትደብቂኝ፡፡» አላት የሔዋንን ግራ እጅ ይዞ እየደባበሳት፡፡
«ነግረውኛል። ግን ሆዴ በጣም ፈራ»
«ለምን ብለሽ?»
«ግዳጅ ላለመቀበልህ ምክንያቷ እኔ የምሆን ስለመሰለኝ፡» አለችና ሔዋን ዓይኖቿ ላይ ያቀረረ እንባዋን በለበሰችው ስከርፍ ጥርግ አደረገች።
«አይዞሽ ሔዩ፣ አትፍሪ! ምንም አይመጣም፡፡»
«ተው እስቹ ምንም አይመጣም አትበል። ኑሮህ ሁሎ ይበላሻል፡፡ ለአንተ ኑሮ መበላሽት እኔ ምክንያት መሆን የለብኝም፡፡ የአንተ ከተበላሸ የኔም ይበላሻል»
አለችና እንባዋን አሁንም በጉንጯ ላይ ታወርደው ጀመር።
“አታልቅሺ የኔ ፍቅር። የኔ ሕያወት የሚበላሸው አንቺን ከአጣው ብቻ
ነው:: ዘመቻ ከሄድኩ ደግሞ አንቺን ላጣሽ እችላለሁ። ስለዚህ አልሄድም»
«አንተ ዘመቻ ብትሄድ እኔ የት እሄድብሃለሁ?»
«እህትሽ እና ባርናባስ እየሰሩልሽ ያለውን መንገድ እጣሽውና ነው ወይስ አልገባሽ ይሆን?»
አውቃለሁ። ገብቶኛል::»
“ታዲያ የኔ ዘመቻ መሄድ እንዴት አንቺን አያሳጣኝም ብላሽ ትገምቻለሽ»
«ፈጽሞ አስቻለው ፈጽሞ አያለያየንም።
«እንዴት?»
«እኔም ላጣህ አልፈልግምና!»
«ወደሽ ሳይሆን ያስገድዱሻል»
«አንድ ነገር አትርሺ ሒዩ! ያለሽው በእህትሽ ቤት፤ የምትበይው
የምትጠጪው የእሷን፡ በዚያ ላይ ባርናባስን የሚያህል የፖለቲካ ስልጣን ያለው ወዳጅ አላት።
በዚሁ ላይ ያቀረቡልሽ ወዳጀ በከተማው ውስጥ አለ የተባለ ሀብታም 'በድሉ አሽናፊ' የባርናባስ ስልጣንና የበድሉ ገንዘብ ከተባበሩ እንዴት እኔና አንቺን
መለያየት ያቅታቸዋል?» አለ አስቻለው ከተንጋለለበት ቀና ብሎ ሔዋንን ፊትለፊት እያያት፡፡
«ይህን ሁሉ ግን የታመነ ልብ ያሸንፈዋል::» አለችው ሔዋን የአስቻለውን ደረት እየደባበሰች።
«ፈጽሞ፡ በበኩሌ ማመን ያስቸግረኛል።»
«ስማ አስቻለው!»
«ወይ የኔ ፍቅር»
«እኔንም አንተንም ለአደጋ የሚያጋልጥ አጋጣሚ የሚፈጠረው አንተ ዘመቻ አልሄድም ብለህ የቀረህ እንደሆነ ነው::»
«እንዴት?»
«ዘመቻ ካልሄድክ ከሥራ ያስወጡሃል! ወይም ያስሩሃል። ምናልባት ሊገድሉህ ወይም ሊያስገድሉህ ይችላሉ። አየህ አስቹ! ሥራ ከሌለህ ገንዘብ
አይኖርህም። ገንዘብ ከሌለህ ደግሞ ችግር ያበሳጭህና ለችግርህ ምክንያት በሆኑ
ሰዎች ላይ አደጋ አድርስህ በሌላ የከፋ ችግር ወስጥ ልትገባ ትችላለህ:: ያኔ ልብህ ለጭካኔ እንጂ ለፍቅር ቦታ አይኖረውም፡፡ ዞሮ ዞሮ ለኔ አልሆንከኝም። ታስረህ ማየቱም ለአዕምር'ዩ አይመቸውም፡፡ ብትሞትም ሀዘኔ መራርና የዕድሜ ልክ ነው፡፡
ግን ይህ ሁሉ ይወገድ ዘንድ ግዳጁን ተቀብለህ መሄድ ስትችል ለምን ሁለታችንም እንቸገራለን?» አለችው በትካዜ ውስጥ ሆና ዓይን ዓይኑን እያየች።
«ሔዩ የኔ ችግር አልገባሽም፡፡»
«ገብቶኛል። ግን እሱም ቢሆን መላ አለው::»
«ምን ታየሽ?»
«በቃ እኔ ከእት አበባ ቤት እወጣና አንተ በምትቆርጥልኝ ገንዘብ ከትርፍዬ ጋር በአንተ ቤት ውስጥ እኖራለሁ፡፡ ግዳጅህን ፈጽመህ ስትመለስ እኔና አንተ ራሳችን በምንደግሰው ሰርግ ተጋብተን አብረን መኖር እንችላለን:: ለኔና
ለአንተ ፍቅር የሚበጀው ይሄ ብቻ ነው።
ከዚህ በኋላ ሁሉቱም ትካዜ ወስጥ ገቡ። ሁለቱም በየበኩላቸው ያስቡ ጀመር
በየልባቸው ያለውን ነገር በማስታወስ።

እሷ አላወቀችም እንጂ ዛሬ ሔዋን ያቀረበችው ሀሳብ አስቻለው ራሱ
በተካፈለበት ጉባዔ ላይ የተቀየስ አቅጣጫ ነበር፡፡ እርግጥ ነው የአስቻለው የዘመፍቻውን ግዳጅ ያለመቀበል ውሳኔው እጅግ ጠንካራ ነበር፡፡ ነገር ግን ታፈሡና
በልሁ መርእድን ጨምሮ ሀሳቡን እንዲቀይር ብዙ ታግለውታል የስድስት ወር ጊዜ አጭር
መሆኗን ዘመቻውን ባለ መቀበሉ
ከሥራ መባረር ምናልባት እስር፣ ከዚያም ያለፈ ክፉ ነገር ሊመጣ እንደሚችል እየጠቀሱ ሊያግባቡት ሞክረዋል በዚያው በራሱ ቤት መርዕድና በልሁ ጫት እየቃሙ ታፈሡ ራሷ እስከ ውድቀት ሌሊት ድረስ አብራቸው በመቆየት በዚሁ ጉዳይ ላይ ከአስቻለው ጋር የተፋጩት ገና ደብዳቤው በደረሰው ማግስት
በአስቻለው ግዳጅ የመቀበልና
ያላመቀበል ውይይት ወቅት ጉልህ ሥፍራ ተሰጥቶት የነበረው የአስቻ ለውና የሔዋን ፍቅር ጉዳይ ነበር።

ለአስቻለው ለግዳጅ መመልመል የባርናባስ ሚና ወሳኝ ሊሆን እንደሚችል ሁሉም አምነውበታል እሱ ደግሞ ከራሱ ፍላጎት በተጨማሪ ሸዋዬ የምትጥልበትን
አደራ ለመወጣት ጭምር አስቦና ተገፋፍቶ የፈጸመው ስለመሆኑ አይጠራጠሩም።ሁለቱ ሰዎች የአስቻለውን አለመኖር ተጠቅመው ሊፈፅሙት ያቀዱት ነገር በሁሉም አእምሮ ውስጥ አለ። ሔዋንን ከበድሉ አሸናፊ ጋር ሊያላምዱ ነው። ይህ ደግሞ በአስቻለውና በሔዋን ፍቅር ላይ ጥላውን ሊያጠላ ነው።
ይህን አደጋ ለመከላከል ይቻል ዘንድ መላ መልምለዋል። በአንድ ወይም በሌላ መንገድ ሔዋንን ከሸዋዬና ከባርናባስ መዳፍ ውስጥ ፈልቅቀው ማወጣት፣
ዋሽቶም ለምኖም ሔዋንን የችግሩ ፈቺ አንድ አካል ማድረግ፡፡ በዚህ ጉዳይ አስቻለውን ጨምሮ ሁሉም ተስማምተዋል። ሔዋንን የማሳመን ጉዳይ ለታፈሡ እንግዳሰው ተሰቷት እሷም የተጣለባትን ሃላፊነት ለመወጣት አልዘገየችም፡፡ለአስቻለው የዘመቻ ትእዛዝ በደረሰው አራተኛ ቀን ላይ ነበር ሔዋንን ከመሰረተ ትምህርት ሥራዋ ስትመለስ ወደ ቤቷ ጎራ እንድትል የጠየቀቻት፡፡ሔዋንም
ጥያቄውን ተቀብላ ከታፈሡ ቤት ተገኘች።
«ሔዩ ተቸግረናል» ነበር ያለቻት ታፈሡ ሔዋንን ሶፋ ላይ አስቀምጣ እሷም ከፊትለፊቷ በመቀመጥ፡፡
«ምን ሆናችሁ?»
«አስቻለው በመሥሪያ ቤቱ በኩል ዘመቻ ታዝዞ ነገር ግን አልሄድም
በማለቱ እኔም በልሁና መርዕድም ተጨንቀናል፡፡»
«ዘመቻ?»
«አዎ»ለስድስት ወር ብቻ ለሚቆይ የሙያ ዘመቻ ወደ ኤርትራ እንዲሄድ በደብዳቤ ታዟል።እሱ ግን ሔዋንን በሸዋዬ ቤት ውስጥ ትቼ አልሄድም እያለ አስቸግሮናል»
«ኤርትራ ማለት የጦርነቱ አገር አይደል?»
«አዎ፣ እሱ ግን የሚሄደው ሊዋጋ አይደለም በጦርነቱ ለሚጎዱ ቁስለኞች የህክምና አገልግሎት ሊሰጥ ነው።»
«ታዴያ አንዴት ይሻላል?»
«ችግሩ ያለ አንቺ አይፈታም»
«ምን አድርጌ እፈታዋለሁ?»
«አስቹ የሚለው ወደዚህ ዘመቻ እንድሄድ ያደረጉኝ ሸዋዬና በርናባስ ናቸው። ዓላማቸውም ሔዋንን ለበድሉ አሸናፊ ሊድሩ አስበው ነው።ስለዚህ ፍቅሬን ከማጣት እነሱ ላይ አደጋ አድርሼ እስር ቤት ብገባ ይሻለኛል እያለ ድርቅ አለብን»
#ምንትዋብ


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ

....ምንትዋብ ከተንሴ ማሞ ጋር በተደረገው ውጊያ በእሱ ሆነ በእሷ በኩል ያለቀው ሰው ብዛት በአእምሮዋ እየተመላለሰ እያደር ሰላም ነሳት። ሰላም በሰው ልጅ ሕይወት ውስጥ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ይበልጥ እንድትገነዘብ አደረጋት። ሰላምን በሃገሯ ውስጥ ለማረጋገጥ
የበለጠ ጠንክራ መስራትና የልጇን መንግሥት ማደላደል እንዳለባት
የበለጠ ተገነዘበች፤ የበለጠ ተጋች።

የልጇን መንግሥት ለማጠናከር ወልደልዑልን፣ ተንሴ ማሞን ባሸነፉ በዓመቱ ራስ ቢትወደድ ብላ ሾመችው። አፄ ፋሲለደስ ያሰሩት የራሶች መኖሪያ ራስ ግንብ ውስጥ እንዲገባ አደረገች።
ያሰበችውን ሁሉ ለማሳካት፣
ዘወትር ጠዋት አስራ ሁለት ሰዐት ላይ ዳዊቷን ደግማ የጸሎት መጽሐፏን አንብባ እንደጨረሰች ወይዛዝርት ልብሷን ያለብሷታል
ያስጌጧታል። ብሎም ቁርስ ታደርጋለች። አፈ ንጉሡ መጥቶ ፍትሕ ፈላጊ እንዳለ ካስታወቃት፣ ሦስት ሰዐት ላይ ዙፋን ችሎት ከኢያሱ ጋር ተሰይማ አቤቱታ ትሰማለች። ፍትሐ ነገሥት
ጠንቅቀው ከሚያውቁ መሃል የተመረጡት ዐራት አዛዦች ፍትሓ
ነገሥት እየጠቀሱ ፍርድ ሲያሰሙና ፍርዳቸውን ሲሰጡ ትሰማለች።መኳንንቱ አንድ በአንድ የሚሰጡትን የብይን ሐሳብ ታዳምጣለች።በመጨረሻም የተለየ የተለየ ፍርድ ካላት ትሰጣለች።

ሽንጎ እንደተነሳ እልፍኟ ትመለሳለች። ከልጇ ጋር ሆና መሣፍንት መኳንንትና ሌሎችም እጅ ይነሳሉ። እነሱን እንዳሰናበተች ዘወትር ለራሷ የምታቀርበው ጥያቄ እንዴት ላስተዳድር?” በመሆኑ ጉባኤ ጠርታ የልጇን መንግሥት ለማጽናት፣ ዘላቂ ሰላም ለማምጣትና ለሃገሯ
ያሰበችውን ለመሥራት፣ ያንገራገረ መኰንን ካለ ከጥል ይልቅ ዕርቅ
እየመረጠች ለዕርቅ ትደራደራለች።
ጥምረት መፍጠር ካለባት ጋር ጥምረት ትፈጥራለች፣ በጋብቻ
ማስተሳሰር ያለባትን ታስተሳስራለች፤ ማን ከማን ጋር መጋባት እንዳለበት ትወጥናለች። ብሎም የመሣፍንቱንና የመኳንንቱን ቀልብ መሳብ ብቻ ሳይሆን ድጋፋቸውንም አገኘች። ሊቃውንት አድናቂያቸው
ካህናት ደግሞ አክባሪያቸው በመሆኗ ሊፃረሯት ምክንያት አጡ።ደከመኝ፣ ታከተኝ ሳትል ያለ ዕረፍት ራሷን በሥራ ጠመደች።

ሙሉ ለሙሉ ለሃገሯ ሰላምና ደሕንነት ማሰቧ፣ ለልጇ ሕይወት መጨነቋ፣ ከተንሴ ማሞ ጋር የተደረገው ውጊያ ያሳደረባት ድካም፣ ተጽዕኖና ያለ ዕረፍት መሥራቷ፣ ስለ ራሷ የምታስብበት ጊዜ እንዳይኖራት አደረጋት።

በሏ ከሞቱ ሦስት ዓመታቸው ነው
አፍላ እድሜዋ ላይ
በመሞታቸው የልጅነት ጊዜዋ እንደዚሁ መጥፋቱ ክፉኛ አሳሰባት።ሕይወቷ ጨው ጎደለው፤ ድግስ ላይ እንደሚቀርበው አዋዜ፣ ድቁስና
የተሰነገ ቃርያ ማጣፈጫ አጣ። ቋራን ለቃ ቤተመንግሥት የገባች ቀን ሕይወት የፈነጠቀችላትን ብርሃን መልሳ እንደ ክረምት ሰማይ ግራጫ ያለበሰችባት መስሎ ተሰማት።

ሙሉ ፀጋዋንም ሰስታ የያዘችባት መሰላት።

ዳግማዊ ኢያሱ በትምህርቱ ጎበዝ፣ በቅኔ ትምህርቱም ብስል
አእምሮውን እያሳየ ቢመጣም፣ ከቤተመንግሥት ውጭ ወጥቶ መዘዋወርዐእና እንደማንኛውም ልጅ መጫወት በመፈለጉ ወደ ውጭ በወጣ ቁጥር
ምንትዋብ ነፍስና ስጋዋ ይላቀቃሉ። ጠባቂዎች ቢኖሩትም፣ ምንትዋብ
ክፉ ያሰበ ይገድልብኛል ብላ ስለምትሰጋ ከእሷው ጋር ካልሆነ ባይወጣ ትመርጣለች። የኢያሱ የተፋጠነ ዕድገት የደስታ ምንጭ ቢሆንላትም፣ ደጅ ደጁን ማለቱ ግን ተጨማሪ የጭንቀት መነሻ ሆኖባታል።

በዕረፍት ጊዜዋ ከተወሰኑ መኳንንትና የኣፄ በካፋ እህት
የወለተእስራኤል ልጅ ከሆነው ከኢያሱና ከካህናት ጋር ጨዋታ
ባትይዝ ኖሮ ሕይወት የበለጠ እየከበደችባት በመጣች። በተለይም ልዑል ኢያሱ ዘወትር ጠያቂዋ በመሆኑ የቅርብ ወዳጅ እየሆነ መጣ።
ዙርያዋን ከከበባትና ዘወትር ለሥልጣንና ለሹመት ከሚቁነጠነጠውና ከሚወዳደረው፣ ካባውን እያወናጨፈ ከሚከራከረው ባላባት ጎን እሱን ረጋ ብሎ ማየቷ አረጋጋት። ጨዋታው ደስ እያላት መጣ። ለስለስ ማለቱና ቁጥብነቱ ማረካት።

እቴጌ መሆን ታላቅ ነገር ነው። በአደባባይና በሸንጎ የምትታየው
ደርባባዋ፣ ጠንካራዋና ደስተኛዋ ምንትዋብ ግን መኝታ ቤቷ ስትገባ
ብቸኛ ነች። ልጇ ኢያሱ ስላደገ፣ ከእሱ ጋር አንድ መኝታ ቤት
መተኛቱን አቁመዋል ። መኝታ ቤቷ ስትገባ ክፍሉ ባዶ፣ አልጋዋ
ቀዝቃዛ ሆነው ይጠብቋታል። በተለይም ደግሞ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሐሳቡ፣ ጭንቀቱና መጠበቡ በርትቶባታል።

አንድ ማታ ነው። ሁለተኛ ደርብ ላይ ባለው መኝታ ቤቷ መስኮት
ውጭውን ትመለከታለች አንዳንዴ ከራሷ ጋር ለመሆን ስትፈልግ
እንደምታደርገው። መንፈሷ ከመቼውም ጊዜ የበለጠ መረጋጋት አቅቶታል። ድፍን ጨለማው ላይ አፍጣ ቆየች። ለወራት ሲያስጨንቃት
የነበረው ሐሳብ ቀስ በቀስ ጭንቅላቷ ውስጥ ተንሸራቶ ገባ። እስተመቸ ብቻየን እቀመጣለሁ? የሚሉት ቃላት ከአፏ አፈትልከው ወጡ።ደነገጠች። የሰማት ሰው እንዳለም ለማወቅ በመስኮቱ ወደ ታች አየች።በአካባቢው ማንም ያለ አይመስልም።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ስታወጣ ስታወርደው የነበረ ነገር ቢሆንም፣
እንደዚህ ከአፌ ይወጣል ብላ አልገመተችም። ነገሩን ዳግም ላታነሳ ከራሷ ጋር ቃል ተገባብታና አፍና የያዘችው ነገር ከአፏ አምልጠ ሲወጣ ተገረመች። መልሳ ስውር ወደ ሆነውና ምሥጢር ደብቆ ወደ እሚያስቀምጠው የሰውነቷ ክፍል ሰግስጋ ልታስገባው ሞከረች።
አዳምጭኝ እያለ የሚወተውተውን ድምፅ ግን ማስቆም አቃታት።
አወጣች፤ አወረደች። መፍትሔ እንደሌለው ተገነዘበችና በትካዜ ሄዳ አልጋዋ ላይ ጋደም አለች።

ጸሎት ልታደርስ ፈልጋ የጸሎት መጽሐፉን ከዕንጨት የተሠራውና
ከፊት ለፊቱ የመስቀል ቅርጽ ያለው ረጅሙ #አትሮኖሷ ላይ አጋድማ፣ ከአንዱ ጸሎት ወደ ሌላው ብታልፍ መንፈሷ አልረጋጋ አለ። ዛሬስ እዝጊሃር ይቅር ይበለኝ ጠሎቱም እምቢየው ብሎኛል። ገና ግዝየ ነው ዛዲያ ምን ልሥራ? ብላ ጋደም እንዳለች አካሏ በሥራ፣ ስሜቷ በሐሳብ ደክመው ነበርና እንቅልፍ ጣላት።

በጣሙን ያስደነቃትን ሕልም አየች።

እጅም፣ እግርም፣ ፊትም ሆነ ጭንቅላት የሌለው፣ ግን ባያሌው
ደስ የሚል፣ ብርሃን የተሞላው፣ ቀይ አበባ መሳይ ነገር የሚያናግራት ይመስላታል ።
“ምንትዋብ!”
“አቤት! አንተ ማነህ?”
“እኔ ፍቅር ነኝ። ፍቅር ታቂያለሽ?”
“አዎን፣ በልዥነቴ ጥላዬ ሚባል ልዥ ኋላም ባሌን አፈቅር ነበር።”
“ጥላዬ ኻይንሽ ስለራቀ ኸልብሽ ርቋል። ባልሽን ትወጂ ነበር።
ለፍቅር ገና ነበርሽ።”
“ፍቅር ምንድርነው?”
“እኔ አልገለጥም። ሕይወታችሁ ውስጥ ኻሉ ምሥጢሮች አንዱ ነኝ።እናንት ሰዎች እኔን ሙሉ ለሙሉ ማወቅ ስለተሳናችሁ እኔን ሊገልጹ ሚችሉ በቂ ቃላት አላደራጃችሁም። እኔን ትመኛላችሁ፣ ግና ነፍሳችሁ
ምትላችሁን አታዳምጡም። ጠቢቡ እንዳለው የመውደድ ቦታው ነፍስ ነው። ዛዲያ እኔን ለመሸከም ነፍሳችሁን ማዳመጥ ይጠይቃል።”

“እንዴ አሁን እኔ ኸልዤና ካገሬ የበለጠ ማፈቅረው አለ?”

“አየሸ ምንትዋብ እኔ አንድ ነኝ። እናንተ ግና የፍቅር ዓይነት
እያላችሁ አስር ቦታ ትከፋፍሉኛላችሁ። ፍቅር ማለት ሕይወት ማለት ነው፤ ሞትንም ስንኳ በፍቅር ማሸነፍ ይቻላል። ግና ፍቅር ለናንተ ሲያልቅ ያልቃል... ሲያረጅ ያረጃል። ኻንዱ ቀንሳችሁ ለሌላው ታበዛላችሁ። ለምሳሌ አሁን አንቺ ለልዥሽና ላገርሽ ያለሽ ፍቅር ልብሽን በሙሉ ስለገዛ ራስሽን ችላ ብለሻል። ስለዝኸ ሕይወት ሙሉ ትርጉሟን ልትለግስሽ አልቻላት አለ። ጭንቀት ሲፈታተንሽ ውሎ
#ትኩሳት


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር

....ካንድ አመት ተኩል በፊት፣ በክረምት፣ ቤቱ ማሞቂያ
ስላልነበረውና የክረምቱ ብርድ ስለበረታበት፣ ካፌ «ሴንትራ» ያድር
ነበር፡፡ አሁን ደሞ የኒኮል እምባ እያባረረው ካፈ «ሴንትራ»
ያድራል። ሲጋራ እያጨሰ ሲተክዝ ያድራል፡፡ ስለ ኢራን ሲያሰላስል
ያድራል። ከንቱ ሀሳብ ሲያወጣ ከንቱ ሀሳብ ሲያወርድ ከንቱ
ሌሊቶችን ያነጋል

ያን ሰሞን የሲልቪ መፅህፍ ለሶስተኛ ጊዜ እምቢ አለ።
ለሶስተኛ ጊዜ አባረረችኝ። እኔም መፃፍ አቃተኝ፡፡ እንዴትስ ላያቅተኝ ይችላል? ሲልቪ በጉልህ ሰማያዊ አይኖቿ ብርሀን ካላየችኝ፡
በውብ ሰፊ አፏ ሙቀት ካልሳመችኝ፣ ሰለስላሳ ገላዋ ካላቀፈችኝ እንዴት ልስራ እችላለሁ? መስራቱን ተውኩት
ዩኒቨርሲቲው አጠገብ ያለው መናፈሻ ውስጥ የኤክስ አዛውንት
በስጋው አቧራ ውስጥ “boule” ሲጫወቱ፡ በኮሚክ የደቡብ
ፈረንሳይኛቸው እየፎከሩ አንዷን የብረት ኳስ በሌላ እያነጣጠሩ
ወርውረው እየገጩ እየተሳደቡ ወይም እየተሳሳቁ ሲንጫጩ አያለሁ
ከዚያ ወደ ኩር ሚራቦ ሄጄ Monoprix የተባለው ትልቅ ሱቅ
ፊት ለፊት ከአንዱ ሽማግሌ ወይም ከአንዷ አሮጊት አጠገብ
አግድም ወምበር ላይ እቀመጥና፣ የኤክስ ሚስቶችና እናቶች
ከመንገዱ ወደ ሱቁ እየገቡ፣ ከውስጥ “Monoprix የሚል
የታተመባቸው የሞሉ ቡኒ የወረቀት ከረጢቶች ይዘው ወደ መንገዱ ሲጎርፉ አያለሁ፡፡ አስተያየታቸውም ሆነ አለባበሳቸው ወይም
አረማመዳቸው የጎረምሳ አይን አይስብም፡፡ ድሮ የጎረምሳ አይን
ስበው፣ ፍቅረኛ ይዘው፣ አግብተው ወልደው በቅቷቸዋል። አሁን
ወይም አርጅተዋል፣ ወይም ወፍረዋል ወይም ተዝረክርከዋል
ኮረዳዎቹ ጡታቸውን አሹለው! ዳሌያቸውን አሳብጠው፤
አይናቸውን ተኩለው፣ ፀጉራቸውን ተሰርተው ሽቶ አርከፍክፈው
እጅጌ የሌለው የበጋ ልብስ እየለበሱ፣ የብብታቸውን የተለያየ ከለር ፀጉር እያሳዩ፣ በጎረምሳ ታጅበው እየሳቁ እያወሩ በኩር ሚራቦ ይመላለሳሉ፡፡ ወይም ካፌዎቹ በር አጠገብ መንገዱ ላይ ጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጠው ግማሽ ጭናቸውን እያሳዩ ልዩ ልዩ ቀዝቃዛ
እየጠጡ ያወራሉ

አሮጊቶቹና ሽማግሌዎቹ አግድም ወምበር ላይ ፈዘው ቁጭ
ብለው ፀሀይ ይሞቃሉ። እኔም ቁጭ ብዬ ስለሲልቪ ስለባህራም፣ስለኒኮል፣ ስለሉልሰገድ፣ ስለአማንዳ እያሰብኩ አላፊ አግዳሚውን
እመለከታለህ
ሲልቪ መቼ መጥታ ወደ እቅፏ ትጠራኝ ይሆን? ጊዜው አላልፍልህ ይለኛል። ወደ ዘጠኝ ሰአት ላይ ሲኒማ " እገባለሁ።
ከሲኒማ ወጥቼ አንዱ ካፌ እሄድና ኣንድ ቢራ ጠጣለሁ

አንድ ቀን ወደ አስራ ሁለት ሰአት ላይ ነበር። ሰማዩ ቀልቶ፣
ፀሀይዋ እንደ ቀይ ብርቱካን ከምእራባዊው አድማስ በላይ
ተንጠልጥላለች፡ ግን ገና አትጠልቅም፡ እስከ ሁለት ሰአት ተንጠልጥላ ኤክስን ታስውባታለች
አየሩ የሚለሰልስበት ጊዜ፣ ብቸኝነት የሚፈለግበት ሰአት ነው፡
የትዝታ የትካዜ ሰአት
ካፈ ኒኮል ሄድኩና በረንዳው ላይ ፊቴን ወደ ፀሀይዋ አድርጌ ቁጭ ብዬ ቡና አይነቱን ቢራ አዘዝኩ፡፡ አሮጊቷ ቢራውን እያቀረቡልኝ
"Ça fait longtemps qu'on vous a pas vu monsieur" አሉኝ ብዙ ጊዜ ሆነን ካየኖዎት)
Oui, madame." አልኳቸው
ጓደኛዎትስ ደህና ናቸው?»
ደህና ነው። አገሩ ገብቷል
ትምህርታቸውን ጨረሱ?»
"Il était tres gentil, votre ami“ (በጣም ጥሩ ሰው ነበር ጓደኞት")
"Oui, madame"
አሮጊቷ ሄዱ፡፡ ብቻየን ቀረሁ፡፡ ከቀይዋ ፀሀይ ጋር፣ ከቡናማው
ቢራ ጋር። ከሉልሰገድ ትዝታ ጋር መንግስተ ሰማያት ማለት
ሴት በየዛፉ ስር፣ በየግድግዳው ጥግ የሚበቅልበት ማለት ነው
አየህ፣ የኒኮል ጡት እንደ ነጭ ውብ ሰማይ ነው፡፡ ሰማዩ መሀል ላይ በሮዝ ቀለም የተከበበች ወይን ጠጅ ጨረቃ አለች እኔ 'ምልህ! ከኒኮል ጋር አልጋ ላይ የወጣህ ጊዜ' በቅዱስ ብልግናዋ ትባርክሀለች
አይ አንተ ባላገር መባዳት ቁላን እምስ ውስጥ መክተት ይመስልሀል። ስንት ሳይንስና ስንት አርት እንዳለው ባወቅክ! ኒኮልን
በቀመስክ!.....
ፀሀይዋን ከለለኝ፡ ከሉልሰገድ ነጠለኝ፡፡ ቀና ብዬ አየሁት፡፡
ባህራም። አጠገቡ አንድ ቀጭን ባለመነፅር ሰውዬ ቆሟል። ቁመቱ
ከባህራም ትንሽ ይበልጣል። ያገሩ ልጅ ይመስላል ብድግ አልኩ፡፡ ሰውዬው ፈገግ አለ። ፈገግታው ደስ ይላል። የልጅ ፈገግታ ይመስላል። እጁን እየዘረጋ፣ በጣም ወፍራም በሆነ
ድምፅ በእንግሊዝኛ ከለንደን መምጣቴ ነው አለኝ
ጨበጥኩት፡፡ አጨባበጡ ልዩ ሆኖ ተሰማኝ። እጁ አይመችም።
በኋላ ሳየው መሀል ጣቱ ወደ አንድ በኩል ተጣሟል አይታጠፍም።ሌሎቹ ጣቶቼ ረዣዥም ቀጭን ቆንጆ ናቸው
እንኳን ደህና መጣህ!» አልኩት። ቁጭ አልን፡፡ባህራም ግን አልተቀመጠም። እኔን «ይሄ ማኑ ነው።የፈለግከውን ልትነግረው ትችላለህ» አለኝና ወደ ካፌው ውስጥ ገባ የማኑ ግምባር በጣም ጠባብ ነው: ወደኋላ የተበጠረው ፀጉሩ ከቅንድቦቹ ጋር ሊገናኝ ምን ያህል አይቀረው
ሳቅ አለ፡፡ የላይኛ የፊት ጥርሱ ሁለቱ የራሱ አለመሆኑን አስተዋልኩ ሰው ሰራሽ የአጥንት ጥርስ ነው። ጥያቄው አመለጠኝና

ጥርሶችህ የት ሄዱ?» አልኩት። የልጅ ሳቁን እየሳቀ ሰባራ
መሀል ጣቱን በግራ እጁ እያሻሸ
“አገሬ ትቻቸው መጣሁ:: እስር ቤት ውስጥ ኣለኝ፡፡ ወፍራም
ድምፁ ውስጥ መመረር አያሰማም፡፡ ሲስቅ ከመነፅሩ ኋላ አይኖቹ ጥፍት ይላሉ

«አህ! » አልኩት፡፡ ምን ማለቴ እንደሆነ እንጃ

«አሁን ጥርሶቼን ፍለጋ አገሬ መመለስ አለብኝ፡፡ ባህራም
ቢያፋልገኝ ቶሉ አገኛቸው ነበር። እሱ ግን ኣላግዝህም አለኝ»

«የጥርስ ኣዳኝ መሆን አልፈልግም አለ? »

“እህስ! ያውም የኔን የጓደኛውን ጥርሶች! አይገርምህም?»
በጣም እንጂ» ይሄ ምን አይነት ንግግር ነው? የሚል ሀሳብ
ጨረፈኝ

“ካንተ ጋር ብተዋወቅና በሰፊው ባወራ ደስ ይለኝ ነበር። ግን
እቸገራለሁ። ጥርሶቼ ናፍቀውኛል» አለ። ይስቃል
«ይገባኛል» አልኩት እየሳቅኩ
ባሀራም እንደሚያስፈልገኝስ ይገባሀል?»
“አዎን"
ሳቁ ከፊቱ ጠፋ፡፡ ጉንጮቹ ወደ ውስጥ የጎደጎዱ ናቸው፡፡ በብዙ
የሚመገብ አይመስልም። ቆንጆ ጣቶቹን አየሁዋቸው፤ ንፁህ ናቸው፤ የሲጋራ ልማድ አልተለጠፈባቸውም

አሮጊቷ ሲመጡ ማኑ ቀዝቃዛ ወተት አዘዘ፡፡ አንዲት ኮረዳ
ባጠገባችን ስታልፍ ሽቶዋ አንድ ጊዜ አወደን፡፡ ነጭ ሸሚዝና
ሰማያዊ ቁምጣ የለበሰው ቅርፅዋ አይን ይማርካል፡ የሚወዛወዝ ዳሌዋ ያስጎመጃል፡፡ ማኑ አይኑን ጣል አረገባት፡ ያኔውኑ ረሳት፡ ወደ
ካፌው ውስጥ እስክትገባ በአይኑ አልተከተላትም። ለምግብም፤
ለሲጋራም፣ ለመጠጥም፡ ለሴትም ጊዜ ያለው አይመስልም። ጊዜውን
በሙሉ ለሬቮሉሽኑ መድቧል? ስራውም፤ ጨዋታውም፣ እረፍቱም
ያው ሬቮሉሽን ይሆን?
እንዲህ አይነቶቹ ታጥቀው ሲነሱ፤ በሁለት አመት ውስጥ ሞስኮ፤ ፒኪንግ፣ ቡዳፔስት ወዘተርፈ እየዞሩ ሶስት ሚልዮን
ፓውንድና አስራ አምስት ሺ መትረየስ የሚያከማቹ ጎልማሶች
ታጥቀው ሲነሱ፡ እስር ቤት ውስጥ ጣታቸው ተሰብሮ ጥርሳቸው
የተሽረፈ ሰዎች ታጥቀው ሲነሱ፣ ለሴትም ለመጠጥም ጊዜ የሌላቸው ጎረምሶች ታጥቀው ሲነሱ፡ የኢራን ሻህ ለምን ያህል ጊዜ ዙፋኑ ላይ ሊቆይ ይችል ይሆን?

ማኑ እንዲህ አለኝ
#ምንዱባን


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ


ማሪየስ

ጋርቡለስ

ዣን ቫልዣና ኮዜት ገዳም ከገቡ ከስምንት ወይም ከዘጠኝ ዓመት
በኋላ አንድ ያልተጠበቀ ነገር ይሆናል፡፡ የአሥራ አንድ ወይም የአሥራ ሁለት ዓመት ልጅ የተቀዳደደ የትልቅ ሰው ጫማና ልብስ አድርጎ ዋና ጎዳና ላይ ይንቀዋለላል፡፡ ይህ ልጅ ልብሱን ያገኘው ከአባቱ ወይም ከእናቱ
ሳይሆን ለነፍሴ ብሎ ካደረ መንገደኛ ነው፡፡ እናትና አባቱ ግን በሕይወት አሉ፡፡ አባቱ ስለልጁ ደንታ የለውም ፤ እናቱም ብትሆን እስከዚህም አትወደውም:: ይህ ልጅ እናትና አባት እያላቸው ቤተሰቦቻቸው የትም
እንደሚጥልዋቸው እንደማናቸውም ልጆች የሚታዘንለት ልጅ ነበር::

ልጁ መንገድ ለመንገድ በሚዞርበት ጊዜ በጣም ደስ ይለዋል።መንገድ ላይ የተነጠፈው ድንጋይ እንደ እናቱ ልብ ደንድኖና ጠጥሮ አይቆረቁረውም:: እናትና አባቱ ከቤት አስወጥተው የትም ጥለውታል።

ልጁ በጣም ንቁ፤ ቀልጣፋና ጮካ ልጅ ቢሆንም ታሞ የዳነ ይመስል ሰውነቱ ከመገርጣት አልፎ ክስት ብሏል፡፡ ይሮጣል፤ ይዘላል፤ ይጫወታል፧ ይዘፍናል ፧ የማያደርገው ነገር የለም:: ሲያመቸው ይሠርቃል፧ ሳያመቸው
ይለምናል:: አለዚያም ይቆምራል፡፡ ከጮሌነቱ ብዛት «ልጅ» እያሉ ሲጠሩት ከመቅጽበት ከተፍ ይላል፡፡ የሚለብሰው ልብስ፤ የሚበላው ምግብና
የሚጠለልበት ማደሪያ ወይም ደግሞ የሚወደውና የሚያፈቅረው ሰው የለውም:: ነገር ግን ነፃ ሆኖ በመኖሩ ደስተኛ ነው::

ከእንደነዚህ ያሉ ሰዎች ላይ ኅብረተሰቡ ይጨክናል፡፡ ከጭካኔው ብዛት አድቅቆ ይፈጫቸዋል፡፡ ግን ልጆች ከዚህ አይነቱ ጭካኔ አልፎ አልፎ
ያመልጣሉ:: ትንንሽ ልጆች በመሆናቸው በመጠኑም ቢሆን ህብረተሰቡ ስለሚያዝንላቸው ያልፋቸዋል:: ልጆቹም ማምለጫ ቀዳዳ አያጡም፡፡

ሆነም ቀረም፤ ይህ ብቸኛ ልጅ በየሁለት ወይም ሦስት ወር «አሁንስ እናቴ ጋ እሄዳለሁ» እያለ በየጊዜው ለራሱ ቃል ይገባል:: ወደዚያው ለመሄድ መንገድ ጀምሮ ከተወሰነ ሥፍራ ሲደርስ ‹‹
አሁንስ ወዴት ነው የምሄደው?» በማለት ራሱን በመጠየቅ ይቆማል፡፡ ቆም ብሎ ራሱን የጠየቀው ከአሁን ቀደም ከጠቀስነው ቁጥሩ 50-52 ከሆነ ቤት በራፍ ነበር፡፡

በተጠቀሰው ጊዜ ቤቱ ላይ «የሚከራዩ ክፍሎች» የሚል ጽሑፍ ከበሩ ላይ ተንጠልጥሎአል፡፡ ዣን ቫልዣ ከዚያ ሥፍራ ክፍል በተከራየበት
ጊዜ የነበረችው የቤቱ ጠባቂ ሞታለች:: ልክ እርስዋን የምትመስል ሴት ተተክታ ትሠራለች:: ስምዋ ማዳም ቡርዧ ይባላል::

ከዚያ ቤት ውስጥ ክፍል ከተከራዩት ሰዎች መካከል አንዱ አራት ቤተሰብ ያለው መናጢ ድሃ ይገኝበታል:: እነዚህ እናት፣ አባትና ለአቅመ ሔዋን የደረሱ ሁለት ሴቶች ልጆች የሚኖሩት ከአንድ ክፍል ውስጥ ነው::መንገድ ለመንገድ የሚንከራተተውም ልጅ የዚህ ቤተሰብ ልጅ ነበር፡፡ ልጁ
ከዚያ ቤት ሲደርስ የቆመው ልግባ ወይስ አልግባ በሚል የሕሊና ሙግት ምክንያት ነበር።

ቢገባ ያው ኩርፊያና ዱላ ነው የሚጠብቀው፡፡ የመጀመሪያው ጥያቄ ደግሞ «ከየት መጣህ?» የሚል ይሆናል፡፡ መልሱም ‹‹ከበረንዳ» ይሆናል፡፡ተመልሶ ሲወጣ ደግሞ «የት ነው የምትሄደው?» ብለው ይጠይቁታል፡፡መልሱም «ወደ በረንዳ» ነው የሚሆነው፡፡ እናቱ፡ ይህን ጊዜ «ታዲያ አሁን
ለምን መጣህ?» ብላ ትጠይቀዋለች::

እውነተኛ የአባት ወይም የእናት ፍቅር ለምን እንደሆነ ስለማያውቅ ልጁ በዚ ቅር አይሰኝም። እናቱ የልጁን እህቶች በጣም ትወዳቸዋለች::ልጁ የሚጠራው በእውነተኛው አባቱ ስም ሳይሆን በሌላ ነው:: ምነው ቢሉ የዚህ ዓይነት የተበላሸና የተመሰቃቀለ ኑሮ የሚኖሩ ሰዎች ዘራቸውን መቁጠር አይፈልጉምና ነው::

እነዚህ ቤተሰቦች የሚኖሩበት ክፍል የሚገኘው ከአንድ ጥግ ሲሆን በሌላ አቅጣጫ ከጥግ ያለውን ክፍል የተከራየው ሰው ደግሞ ማሪየስ የሚባል ወጣት ነበር፡፡

ይህ ማሪየስ የተባለው ወጣት ማነው?

የታወቁ ቡርዥዋ

ፓሪስ ከተማ ውስጥ ለብዙ ዓመታት ከኖሩ ሰዎች መካከል አንዱ መሴይ ጊልኖርማንድ የሚባሉ አንድ ሽማግሌ ነበሩ:: በ183 1 ዓ ም «ለረጅም
ዘመን ኖረዋል» ተብለው ከሚጠቀሱት ሰዎች መካከል አንዱ እኚህ ሰው ናቸው፡፡ ሰውዬው እድሜያቸው በጣም በመግፋቱ «ትውልድ የተላለፈበት»የሚል የቅጽል ስም ይታወቃሉ፡፡ እኚህ ሰው በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን
ጥሩ የእውነተኛ ቡርዣዎች ርዝራዥ በመሆናቸው ብዙ ሀብት አላቸው::
ድሜያቸው ወደ ዘጠና ዓመት ይሆናል፡፡ ብዙ ጊዜ ቶሎ የመቆጣት ስሜት ይጠናወታቸዋል
ሲናገሩ ይጮሃሉ፡፡ በዚህ እድሜያቸው ብዙ ይጠጣሉ፤ ቀጥ ብለው ይራመዳሉ፡፡ ከሰላሳ ሁለት ጥርሶቻቸው መካከል አንዱ እንኳን ኣልወለቀም:: ዓይኖቻቸው አልደከሙም፧ ሲያነቡ ብቻ ነው መነጽር የሚያደርጉት:: ገቢያቸው ከፍተኛ ቢሆንም ድሃ እንጂ
ሀብታም ነኝ አይሉም:: አሽከሮቻቸውን መደብደብና ማንቋሸሽ ይወዳሉ::
ሃምሣ ዓመት ያለፋት ያላገባች ሴት ልጅ አለቻቸው፡፡ ሲከፋቸው ሴትዮዋን ከመቆጣት አልፈው ይገርፏታል፡፡ በእርሳቸው ዓይን ልጅቱ የሃምሣ ሳይሆን
የስምንት ዓመት ልጅ ናት::

ሰውዬው የሚኖሩት በራሳቸው ቤት ሲሆን ቤታቸው ባለ ብዙ ፎቅ
ነው:: ግቢው እጅግ በጣም ሰፊ ሲሆን በአሸበረቁ አበቦችና ዛፎች ተሸፍኖአል።ሽማግሌው በወጣትነት ዘመናቸው ብዙ ሴቶች አታልለዋቸዋል፡፡ ሆኖም
አሁንም ቢሆን በዘጠና ዓመታቸው ራሳቸውን ወጣት አድርገው ነው
የሚገምቱት:: አለባበሳቸውም እንደወጣት ነው፡፡ ነገር ግን በወጣቶች የሚመራውን የፈረንሳይ አብዮትን እጅግ በጣም ይነቅፋሉ:: እርሳቸው እየሰሙ አንድ ሰው የነገሥታትን አገዛዝ ነቅፎ ሪፐብሊክ የሚመሠረትበትን
ሁኔታ ቢናገር ፊታቸው ከመቅጽበት ደም ይለብሳል:: ይህን ሲሰሙ በጣም ስለሚቆጡ ራሳቸውን እስከ መሳት የሚደርሱበት ጊዜ ነበር፡፡

የወንድና የሴት አሽከሮች በብዛት አሉዋቸው:: ሠራተኞቹን በጎሣቸው
እንጂ በራሳቸው ስም አይጠሯቸውም:: ለምሳሌ አንድ ቀን አዲስ የወጥ ቤት ሠራተኛ ለመቅጠር ፈልገው ሰዎችን ያነጋግራሉ፡፡

«ደመወዝ ስንት ትጠይቂአለሽ?»
«ሰላሣ ፍራንክ›
«ስምሽ ማነው?»
«ኦሎምፒ»
«ሃምሣ ፍራንክ እንከፍልሻለን፤ ስምሽ ግን ኒኮሌት ይሆናል፡፡» (ኒኮሌት የአንድ ጎሣ ስም መሆኑ ነው፡፡)

ሁለት ሚስቶች ነበሩዋቸው:: ከሁለቱም አንዳንድ ሴት ልጅ ሲወለዱ አንደኛዋ ልጅ በሰላሣ ዓመትዋ ነው የሞተችው:: ባል አግብታ ነበር ባልዋን ያገባችው አፍቅራና ተፈቅራ ወይም በአጋጣሚ ይሁን አይታወቅም
ወታደር ነበር፡፡ በትልቅ እህትዋና በእርስዋ መካከል የአሥር ዐመት የዕድሜ ልዩነት ነበር:: ትንሽዋ ስታገባ ትልቅዋ ቆማ ትቀራለች:: ምናልባት በዚህ ምክንያት ሳይሆን አይቀርም፧ ትልቅዋ ልጅ ዘወትር ትተክዛለች፡፡የምትተክዝበትን ትክክለኛ ምክንያት ግን ከራስዋ በስተቀር የሚያውቀው የለም:: ሕይወትዋ በድን ለመሆኑ ፊትዋ ይመሰክራል፡፡

ከአባትዋ ጋር ነው የምትኖረው:: በታሪኩ መጀመሪያ ያየናቸው!
ጳጳስ ከእህታቸው ጋር እንዲኖሩ ሁሉ እኚህ ከበርቴ ደግሞ ከልጃቸው ጋር ነው የሚኖሩት፡፡ አንደኛው የሌላው ደጋፊ ነው::

ከቤቱ ውስጥ ከአባትና ልጅ ሌላ አንድ ልጅ ነበር፡፡ ይህ ልጅ
ተሽቆጥቁጦና ተንቀጥቅጦ ነው ያደገው፡፡ ሚስተር ጊልኖርማንድ ልጁን በቁጣ እንጂ በለዘበ አንደበት አናግረውት አያውቁም፡፡
«ና በል! ወሮበላ፤ ጥፋ፧ ሰማህ፤ ዱርዬ፤ መልስ እንጂ፤ አህያ»
( በእንደነዚህ ዓይነት ስሞች በቁጣ ሲጠሩት በእጃቸው ሰበቅ ይዘው ነው፡፡
#ገረገራ


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#በታደለ_አያሌው


“እንዴት? ተለዉጫለሁ ማለት ነዉ በቃ?” እያልሁ፣ ከራሴ ጋር
ስተዛዘብ ቆየሁ።

እንዲያዉ ራሴንም ጭምር ስዋሸዉ የናፈቀኝ የለም አልሁ እንጂ፣ እንዴት ነዉ የማይኖረዉ? የጎዳናዉን ሰዉ ሁሉ የልቤ ሰዉ ማድረግ ይሆንልኝ የነበርሁት እኔ ዉብርስት፣የእናቴን ልጆች ከልቤ ችዬ ላስወጣ? አይሆንም፡ የናፈቀኝ የለም ያለ አፌን ይዤ እንኳንስ በባልቻ ፊት፣ በራሴ ኅሊናም ሚዛን ላይ ለመቆም ተሸማቀቅሁ።

አፈርሁ።

“ወዴት ነዉ ታዲያ?” አለኝ ባልቻ፣ ቱናት ያለችበትን አልጋ እየሳብሁ
ወደ መዉጫዉ ስራመድ አይቶኝ፡

“ወደ በረሃ”

“ወዴት?”

“ገዳሜን ወደ ገደምሁበት ወደ በረሃዬ። ወደ እመዋ ቤት!”

“ቅድም ምን ተባብለ'? ተይ እንጂ በማርያም: ይልቅ ቱናትን ይዘሽ
የማኅበራችን መዋእለ ሕጻናት እየጎበኛችሁት፣ ቅድም ያልሁሽን
አታስቢበትም?”

“እኔ የፈለገዉን ያህል ባስበዉ፣ የሚሆን የሚሆን መስሎ አልታኝም”

“ግድ የለሽም፣ እስከማታ ጊዜ አለሽ: ደጋግመሽ አስቢበት”

“እስኪ ይሁን። እሺ። መኪናህን አታዉሰኝም ታዲያ? ለማሰቡም ቢሆን እኮ የከረምሁባት በረሃዬ ትሻለኛለች: ወደ እመዋ ቤት መሄድ አለብኝ ትክ ብሎ ሲያየኝ ቆየና አንገቱን በይሁንታ ነቅንቆ፣ ቀድሞኝ ወደ በሩ አመራ፡ ዝም ብዬ ኖሯል እንጂ ቀደም ቀደም ያልሁት፣ ቀድሞ የነበሩኝ
የትለፍ ፈቃዶች ሁሉ መልሰዉ ካልታደሱልኝ በቀር ያለ'ሱ ወደ ሲራክ ፯ መግባትም ሆነ ከማዕከሉ መውጣት
አልችልም:: ስለሆነም
ጠመዝማዛዉን እና ባለ ብዙ በሩን ሲራክ ፯ አሳልፎኝ መኪናዉ
እስከቆመበት ድረስ ቱናትን ከነአልጋዋ አቅፎ አደረሰልኝ፡፡
“በይ እንግዲህ። ማታ፣ ልክ አንድ ሰዓት ሲሆን እደዉልልሻለሁ” አለኝ፣ የጠየቅሁትን የመኪናዉን ቁልፍና ያልጠየቅሁትን አንድ የእጅ ስልክ ጭምር አዉጥቶ እያቀበለኝ፡፡ እሺም፣ እምቢም፣ ቻዉም ሳልለዉ፣ ቱናትን ጭኜ የመኪናዉን ሞተር አስነሳሁ፡ እንደ ድሮዉ በችኮላ ሳይሆን፣ የመኪና መሪ ከነካሁ ቢያንስ መንፈቅ እንዳለፈኝ እና ከአጠገቤ
የጫንኋትም ሰዉ ገዳሜ ቱናት መሆኗን በማሰብ ወደ እመዋ ቤት
የሚወስደኝን ጎዳና በዝግታ አሽከረከርሁበት እንደ ደረስሁ፣ የግቢዉን በር ራሴዉ ለመክፈት ቀልጠፍ ብዬ ወረድሁ።
ስሞክረዉ ግን አልከፈትልሽ አለኝ፡፡ ለወትሮዉ ማናችንም የቤተሰቡ አባላት አድርሶን በመጣን ጊዜ እንዳንቸገር በሚል፣ ግቢያችን ተቆልፎብን
አያዉቅም: እንዲሁ በዉስጥ በኩል ይሸነጎርና፣ መሸንጎሪያዋን
የምንስብባት ደግሞ እኛ ብቻ የምናዉቃት አልባሌ ገመድ አለችልን፡አሁን ግን ይቺ ገመድ በሩን ልትከፍትልኝ አልቻለችም፡፡ እንዲያዉም እጄ ላይ ስለቀለለችብኝ፣ ሳብ ሳደርጋት ጭራሽ ምዝዝ ብላ ወጣች ገመዷ
ተበጥሳለች::

ቆይ፣ ገመዳችንን የበጠሰብን ማነዉ? ምንድነዉ?

“ኤጭ!” አልሁኝ፣ ንድድ ብሎኝ፡ በዚያ ላይ ልጄ ቱናት ምግብ
ከቀመሰች ቆይታለች፡፡ እንዲያዉም ለመንገድ ብዬ ይዤላት የነበረዉ
ምግብ ስለ ቀዘቀዘባት፣ እዚህ ደርሼ ትኩስ ምግብ እስከማጎርሳት ነበር
ችኮላዬ::
“ቆይ፤ ገመዳችንን ማነዉ የበጠሰብን?” አልሁኝ፣ እጄ ላይ ያለዉን የገመድ ቁራጭ ጨብጬ ምን ማድረግ እንዳለብኝ ግራ ቢገባኝ፡

“እኔ” አለኝ፣ ከዉስጥ በኩል።

“አሃ፣አላችሁ እንዴ? በሉ ክፈቱልኝ' አልሁኝ በደፈናዉ፣ ማን
እንዳናገረኝ ስላላወቅሁት

“ምን ልትሆኚ?” አለኝ አሁን በድምፁ ለየሁት፡ ጃሪም ነዉ፡

“ክፈትልኝ”

“እንዳታስቢዉ!”

“ኧረ ባክህ አትቀልድብኝ። ለራሴ ልጄን ርቦብኛል። በል ክፈተዉ ይልቅ”

“አይ እግዲህ! በቋንቋሽ መሰለኝ ያናገርሁሽ!''

“ምን መሆንህ ነዉ፣ ክፈትልኝ እኮ ነዉ የምልህ”

“ሴትዮ! ምናለበት ባትፈታተኚኝ? ነገርሁሽ፤ ከዛሬ በኋላ እዚህ ግቢ ላይሽ አልፈልግም”

“እኔ ተናግሪያለሁ ጃሪም! ክፈተዉ ልጄን ርቧታል። አላበዛኸዉም እንዴ ?
ብለህ ብለህ ደግሞ ወደ እናቴ ቤት እንዳልገባ ልትከለክለኝም ያምርሃል ጭራሽ?” እልህ እየመጣ ጉሮሮዬን ተናነቀኝ፡፡

“ዉነት የእናትሽ ቤት እንግዲያዉስ እርምሽን አዉጪ። ሰማይ ዝቅ
ቢል ይቺን ግቢ ደግመሽ አትረግጫትም: በጭራሽ! ለአንቺም ሆነ ለእናትሽ፣ በቂ ጊዜ ሰጥቻችሁ ነበር: የማያልቅ መስሏችሁ ስትቀልዱበት
ያለቀባችሁ እንደሆነ፣ እኔ ጃሪም ምን እዳዬ? ከዚህ በቀር ምን
ላድርጋችሁ? የራሳችሁ ችግር ነዉ፣ ሥራችሁ ያዉጣችሁ: ከደጄ ግን ፈቀቅ! ያቺ ቆዳ እናትሽ መቼም ልብ የላትም፣ ያልኋትን ረስታ ድርሽ እንዳትልብኝ ብቻ!"
ይኼን ሁሉ ስንባባል፣ ጎረቤት እና አላፊ አግዳሚዉ ሁሉ በግላጭ
እየሰማና እያየኝ ነዉ አንዳንዱ ለእኔ አዛኝ መስሎ ጠጋ ይልና፣ ‹እንዲህ በይዉ› ብሎ ይመክረኛል የተረፈዉ ደግሞ ድምፁን ከፍ አድርጎ እንደ'ሱ ልክ ልኳን ንገራት ጃሪምን
ይመክረዋል አንዳንዱ እንዳትከፍትላት፣ ደግ አደረግህ!» ይለዋል እሱን፣ ሌላዉ ደግሞ ምን አለማመነሽ? ፈሪ ነሽ እንዴ? መኪና ይዘሽ የለ? ዝም ብለሽ ደርምሰሽዉ የማትገቢ! ይለኛል እኔን፡ አልደነቀኝም ምክራቸዉን ሰምቼ የእናቴን
አጥር ብደረምሰዉ እና ቢፈርስ፣ እኛ እንጂ እነሱ አይጎዱም፡

መካሪ እና ግርግሩ መብዛቱን ሳይ፣ ለመሸሽ መረጥሁ: ምስስ ብዬ ወደ መኪናዉ ገባሁና፣ ቆይቼ ብመለስ
አልፎለት እንደሚጠብቀኝ
በመተማመን፣ እሱን ትቼ እመዋን ፍለጋ ወደ ኋላ መንዳት ጀመርሁ።

እሺ ጎረቤት እና አልፎ ሂያጅስ የእኛን ነገር ያባብስብን ግድየለም፣ የቀሩት
እህትና ወንድሞቼን ድምፅ አለመስማቴ ግን ደነቀኝ፡፡ መቼም በግቢዉ
ዉስጥ ያለዉ ጃሪም ብቻዉን አይመስለኝም: ያም ብቻ ሳይሆን፣ እኔን
ከብቦ እኔንም ግፊ፣ እሱንም ግፋ ይል ከነበረዉ ሰዉ መሀል አንደኛዋ
እህቴ ጭጭ ብላ፣ ልክ እንደሌላዉ ሰዉ ስትታዘበን አይቻታለሁ የሆነዉ ሆኖ በቅቶኛል፡ እየተንገሸገሽሁ ከመንደራችን ራቅ እንዳልሁ፣ መኪናዉን ዳር አስይዤ
አቆምሁትና፣ አብሮ በሚዞረዉ አልጋዋ ላይ ከኋላዬ ያስተኛኋትን ልጄን
ዳበስኋት፡ ቱናትን፡ ትራፊ ምግብ አላበላትም ብዬ የመብያ ሰዓቷን
በጣም አሳልፌባታለሁ፡ አሁን ግን አማራጭ ስለ ሌለኝ፣ ቅድም
ቀማምሳለት የተረፈዉን ቀዝቃዛ ፍትፍትም ቢሆን ማብላት አለብኝ በተጨማሪም እንደ ልማዴ ዓይኔን ጨፍኜ እየተንሰፈሰፍሁ፣ ትንሿን ጣቴን በፊንጢጣዋ በኩል ሰድጄ ካካ ማስባል አለብኝ፡ ይኼንንም በየሦስት
ሰዓቱ ማድረግ ሲጠበቅብኝ፣ ዛሬ ግን አሳልፌባታለሁ በዚያም ላይ
ከጠዋት ጀምሬ ወዲያ ወዲህ ስላልኋት ነዉ መሰለኝ፣ እነዚያ ቁልቁል
የሰረጉ ዓይኖቿ ይበልጡኑ ቡዝዝ ብለዉ ታዩኝ፡

ቱናትን እንደ ነገሩ አቀማመስኋትና፣ ሌላ ሌላዋንም እንደሚሆን እንደሚሆን አድርጌላት ስጨርስ፣ ወደ ነበረችበት መልሼ አስተኛኋት። ከዚያ፣ እመዋን ፍለጋ ወደ ታዕካ ነገሥት ገዳም ማሽከርhር ጀመርሁ።
ምን እየተደረገ እንደሆነ እመዋን መጠየቅ አለብኝ፡፡ መቼም እሷ መልስ
አታጣልንም አሁኑኑ አግኝቻት እስከዛሬ እየናቅሁ ያለፍሁትን ጥያቄ
ሁሉ መጠየቅ አለብኝ፡ ምን እስኪፈጠር ነዉ ከዚህ በላይ? አይበቃም? ኧረ በቃ በቃኝ...

“እመዋን አይተዋታል አባ?” አልኋቸዉ ቄሰ ገበዙን፣ በሥዕል ቤት ኪዳነምሕረ እና ታዕካ ነገሥት በዓታ መካከል ባለዉ ሰፊ አደባባይ አግኝቻቸዉ፡

“እግዚአብሔር ይመስገን: ደህና ዉለዋል?” አሉኝ፣ መንገዳቸዉን ገታ አድርገዉ አቤት ትሕትና! እኔን እኮ ነዉ አንቱ ያሉኝ፡ መቼም ትሕትና ከገዳም ሌላ መኖሪያም የላት! ያልኋቸዉን ባይሰሙኝም፣ ሰላምታ እንዳቀረብሁላቸዉ ገምተዋል።

“እመዋን አይተዋት ይሆን?” ስል አቻኮልኋቸዉ አሁንም፣ ሰላምታቸዉ ጊዜ የሚወስድብኝ ስለመለሰኝ፡፡
#ሳቤላ


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ


ሕፃኗ በሕይወት መኖሯን ቀጥላለች " እንግዲህም ቢሆን የሚያሠጋት ነገር የሚኖር አይመስለኝም " የሚቀጥለው ሐሳብ ደሞ ሞግዚት መፈለግ ነው ሳቤላ አልጠነከረችም ትኩሳትና ድካም እየተጋገዙ ያጠቋታል " አንድ ቀን ለባብሳ ከምቹ ወንበር ላይ እንደ ተቀመጠች ሚስ ካርላይል ገባ።

«ባካባቢው ካሉት የቤት ሠራተኞች ሁሉ ለሞግዚትነት ትበቃለች የምትባል ታስቢያለሽ ?» አለቻት

« ኧረ እኔ እገሊት ለማለት አልችልም »

« እንዴ ዊልሰን አለች ሚስዝ ሔር ዘንድ የነበረች ከነሱ ጋር ሦስት ዓመት ካምስት ወር ተቀምጣለች አሁን ከባርባራ ጋር ስለ ተጣላች ነው የምትወጣው ትምጣና ታያት ? »

« የምትሆን ትመስላለች ? ጥሩ ሠራተኛ ናት ? »

« በሠራተኛነቷ እንኳን አትከፋም " ሥራዋን አክባሪ ቁም ነገረኛ ናት "
ነገር ግን ከዚሀ እስከ ሊምበራ ' የሚደርስ ምላስ አላት»

« ምላሷ ሕፃኗን አይጐዳትም ግን በደንገጡርነት ስለኖረች የልጅ አያያዝ ልምድ ያጥራት እንዶሆነ ነው እንጂ " »

« ልምዱስ አላት ከሚስዝ ሔር ቤት ሳትገባ ስኳየር ስፒነር ቤት ዋና ሞግዚት ሆና አምስት ዓመት ተቀምጣ ነበር " »

« እንግዲያው ትምጣና ልያት »

« በይ እልክልሻለው ግን ካነጋገርሻት በኋላ ለመልሱ ቀጠሮ ስጫት።

እኔ ከሚስዝ ሔር ዘንድ ሔጀ ስለሷ አጥንቸ ከመጣሁ በኋላ መልሱን ትነግሪያታለሽ”»

አባባሏ ትክክል ነበር ። ሳቤላም ተስማማችና ሠራተኛይቱ ስትመጣ ተነገረላት " የደስ ደስ ያላት ዐይነ ጥቋቁር ረጅም ሴት ገባች ሳቤላ ከሚስዝ ሔር ቤት
ለምን እንደ ወጣች ጠየቀቻት "

« የባርባራን ጠባይ አልችለው ብዬ ነው የወጣሁት ... እመቤቴ " በተለይማ ከዓመት ወዲህ ያመጣችው ዐመል አንዱም ነገር አያስደስታትም " ከዚህ በላይም
ዕብሪቷ ልክ እንዳባቷ ነው " ብዙ ጊዜ ለመውጣት እያሰብኩ መልሸ ስተወው ኑሬ ትናንት ደግሞ ተጣላን " ዛሬ ጠዋት ጨርሸ ወጣሁ " ስለዚህ እርስዎ ሊቀጥሩኝ ከፈቀዱ በደስታ እቀበላለሁ » አለች ዊልሰን "

« ግን እንደ ተረዳሁት አንቺ ከሚስዝ ሔር ቤት የገረዶች አለቃ ነበርሽ እኛ ዘንድ ደሞ አለቃይቱ ጆይስ ናት ምናልባት እኔ ወጣ ብል ወይም ብታመም አዛዧ እሷ ስለሆነች አንቺን የከፋሽ እንደሆነስ ? »

«እኔ ለዚህ ግድ የለኝም ጆይስን ሁላችንም እንወዳታለን ሳቤላ ጥቂት ከጠያየቀቻት በኋላ ለመልሱ ወደ ማታ እንድትመጣ ነግራ ሰደደቻት ኮርነሊያ ወደ ዐጸዱ ሔዳ ስለ ዊልሰን ጠባይ ሚስዝ ሔርን አንድ ባንድ ጠየቀቻት ሚስዝ ሔርም
ዊልሰን በባርባራ አመካኝታ ቸኰላ ከመልቀቋ በቀር ይህ ነው የምትለው ጥፋት እንደሌላት በግልጽ ነግረቻት " ስለዚህ ዊልሰን ተቀጠረች " አዲሱን ሥራዋን በበነጋው ጧት መጥታ እንድትጀምር ተደረገ።
ሳቤላ ከመኝታ ቤቷ ውስጥ የእንቅልፍ ሰመመን ተጫጭኗት ሶፋ ላይ ተጋድማለች።

አዲሲቱ ሞግዚት ጧቱን መጥታ ሥራ ጀመረች በዚሁ ዕለት ከሰዓት በኋላ ሳቤላ ከመኝታ ቤቷ ውስጥ የእንቅልፍ ሰመመን ተጫጭኗት ሶፋ ላይ ተጋድማለች
የዚህ ዐይነቱ መስለምለም እንዴት እንደሚያደርግ በትክክል የሚያውቁት አንደ ሳቤላ በሰውነት ድካምና ትኩሳት የሚሠቃዩት ብቻ ናቸው ። ከሷ መኝታ ቤት ቀጥሎ ካለው ክፍል ዊልሰን የተኛ ሕፃን ከጉልበቷ ላይ ይዛ ጆይስ ልብስ ስትሰፋ ተቀምጠው ያወጋሉ " በሩ ጎርበብ ብሏል " ሳቤላ በእንቅልፍና በንቃት መካከል ሆኖ ስትስለመለም ስሟ ሲጠራ ድንገት ትሰማና ትነቃለች።

« እንዴት ተደይነዋል ! በጣም የታመሙ ይመስላሉ » አለች ዊልሰን "

« ማን ? » አለቻት ጆይስ "

« እሜቴ » እስከ መቼም በጐ የሚሆኑ አይመስሉም»

« አሁን እኮ በጣም እየተሻላቸው ነው " ባለፈው ሳምንት አይተሻቸው ቢሆን ኖሮና ካሁኑ ሁኔታቸው ጋር ብታነጻጽሪው ገመምተኛ ይመስላሉ አትይም ነበር"

« አሁን አይበለውና እሳቸው አንድ ነገር ቢሆኑ የአንድ ሰው ተስፋ አያንሰራራም ብለሽ ነው ? »

« ወጊጅ ወድያ !ሌላ ወሬ አምጨ»
« አንቺ ያልሺውን ብትይ አይቀርም» ቀጠለች ዊልሰን ።

« ለሁለተኛ ጊዜ እንዲያመልጧት አትፈልግም " በአንድ ጊዜ ነው የምትነጥቃቸው እሷ እንደሆነች ዛሬም ልክ እንደ ድሮዋ ስቅቅ ብላ ነው የምትወዳቸው»

« ይህ ሁሉ የዌስት ሊን ሰው ሥራ ሲፈታ የሚያናፍሰው ወሬ ነው ሚስተር ካርላይል እንደሆኑ ስለሷ ቅንጣት ደንታ የላቸውም»

« ጆይስ አንቺ አታውቂም እኔ ያየሁት ነገር አለኝ " ሲስሟት በዐይኔ አይቻለሁ»

« መንጋ ወሬኛ ! » አለች ጆይስ " « ይኸ እሳቸው እሷን ለማግባት መፈለ?ቸውን አያስረዳም»

« እኔ ያስረዳል አልወጣኝም " ብቻ አሁን የምታስረውን ባለሙዳይ ያንገት ሐብል የሰጧት እሳቸው ናቸው»
« ማናት የምታስረው ? እኔ ስለዚህ ነገር መስማት አልፈልግልም » አለች

« ሚስ ባርባራ እንጂ ደግሞ ማን ! ካንገቷ አውልቃው አታውቅም እኔስ ስትተኛም የምታስቀምጠው አይመስለኝም »

« እሷ አትረባም» አለች ጆይስ "

« እመቤት ሳቤላን ለማግባት ከዌስት ሊን ማለዳ ሊነሡ ማታውን ሚስ ባርባራ
ከሚስ ካርላይል ቤት አምሽታ ስለነበር ሚስተር ካርይል ወደ ቤቷ ይዘዋት መጡ"ገና በመንገድ እያሉ እንዴት እንደሆነ አላውቅም ጃንጥላዋን ሰበሩት ከዋናው
በር ሲዶርሱ የፍቅር ትርዒት ታየ»

« አንቺ ሦስተኛ ሆነሽ አብረሽ ከቦታው ነበሮሽ ? »

« አዎን ሳላስበው እዚያው ተገኘሁ " ያ ገብጋባ አሮጌ ዳኛ አንድም ሰው አስከትለን እንድንገባ አይፈቅድም ካበባ ጐመን የረዘመ አትክልት በሌለው በገላጣው
የማድ ቤት አታክልት ቦታ ውስጥ ማንንም በምስጢር ማነጋገር አይቻልም " ስለዚህ ጠያቂ ወዳጅ ሲመጣ የነበረው ዕድል ወደ ዐጸዱ ገባ ብሎ ለግማሽ ሰዓት ተጫውቶ መመለስ ነው " ያን ዕለት ማታ የምጠብቀው ሰው ስለነበረኝ ወደ ዐጸዱ ወጣሁ።
ወዲያው ሚስተር ካርላይል ሚስ ባርባራ መጡ " እንዲገቡ ብጠይቃቸውም አልፈለጉም ስለዚህ ሁለቱም እዛው ቆሙ ። ስለ መታሰቢያ መያዣው ያንገት
ሙዳይ ጸጉሩን ለማስታወሻ ስለ መስጠታቸው አንዳንድ ነገር ይነጋገሩ ነበር እንዳይሰሙኝ ስለፈራሁ hቆምኩበት አልተነቃነቅሁም የጦፈ የፍቅር ጭውውት ቀጠለ ጠቅላላ አነጋሯ ሁሉ ልክ እንደ ሚስት ነበር ።

« እንቺ ወሬኛ ሊያገቡ ከመሔዳቸው በፊት ማታውን አላልሺም ? »

« እና ቢሆንስ ? እሷ መቸም ዕብድ ሆነች ተሰናብተዋት ከሔዱ በኋላ እጆቿን ወደ ሰማይ ዘረጋች አግብተው እስኪያዩዋት ድረስ ምን ያህል እንደምትወዳቸው ሊገባቸው እንደማይችል ብቻዋን ታወራ ጀመር » አየሽ ጆይስ « በሁለቱ መኻል ብዙ የፍቅር ገድል መፈጸሙን አትጠራጠሪ በመጨረሻ ሚስተር ካርላይል እሜቴን ሲያገኙ ጊዜ በቁንጅናቸውና በትውልዳቸው ማረኳቸው የፊቱ ፍቅር ተረሳ ወንዶች ሲባሉ በተለይ እንደ ሚስተር ካርላይል በመልካቸው የሚመኩ ከሆነ ወረተኝነት ባሕሪያቸው ነው ። »

« ሚስተር ካርይል ወረተኛ አይደሉም ... አንቺ ! »

« አሁንም ሌላ ልንገርሽ » አለችና ጆይስ ማብራራቷን በመቀጠል ሚስተር ካርላይል ማግባቱን ለእኅቱ በጻፌላት ጊዜ ' ኮርነሊያ ለባርባራ ስትነግራት ከመኝታ
ቤቷ ገብታ ያለቀሰችውን ሁሎ እያሳመረችና እየኳኳለች ነገረቻት

« በምንም ለማይወዳት ሰው ይሀን ያህል መጨነቋ ምን ያህል ደንቆሮ ብትሆን ነው ? » አለች ጆይስ
#የጣሪያ_ስር_አበቦች


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ


የመንግስተ ሰማያት ጣዕም

ክሪስ በቀስታና በጥንቃቄ እጁን ከእጁ ስር፣ እግሩን ከእግሩ ስር እያደረገ ወደ መሬት ወረደ እኔ ደግሞ ጣሪያው ጠርዝ ላይ በደረቴ ተኝቼ ወደታች ሲወርድ እያየሁ ነው እጁን አንስቶ ሲያውለበልብልኝ ጨረቃዋ ወጥታ ብሩህ ሆና እያበራች ነበር፡ እንድወርድ ምልክት እየሰጠኝ ነበር። ክሪስ
እንዴት እንደወረደ አይቻለሁ: ዥዋዥዌ ከመጫወት የተለየ አይደለም ብዬ
ለራሴ ነገርኩት። ቋጠሮዎቹ ትልልቅና ጠንካሮች ናቸው: በዚያ ላይ በበቂ ሁኔታ አራርቀን ነው የሰራናቸው አንድ ጊዜ ጣሪያውን ከለቀቅኩ በኋላ ወደ
ታች እንዳልመለከት አስጠንቅቆኛል መጀመሪያ አንደኛውን እግር ካሳረፍኩ
በኋላ በሌላኛው እግሬ የታችኛውን ቋጠሮ መፈለግ ላይ እንዳተኩር ነገረኝ።
እንዳለኝ እያደረግኩ ከአስር ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ውስጥ መሬት ላይ ከክሪስ አጠገብ ቆምኩ።

“ዋው!” አለ ወደሱ አስጠግቶ እያቀፈኝ ከእኔ በተሻለ አደረግሽው”

የፎክስወርዝ አዳራሽ የጓሮ አትክልት ቦታ ውስጥ ነን፡ ክፍሎቹ በሙሉ ጨለማ ውጧቸዋል። የሠራተኞቹ መኖሪያ መስኮቶች ሁሉ ደማቅ ቢጫ ናቸው፡ ዝቅ ባለ ድምፅ “በል መንገዱን ካወቅከው ወደ መዋኛው ምራኝ አልኩት:

በእርግጥም መንገዱን ያውቀዋል እናታችን እሷና ወንድሞቿ ከጓደኞቻቸው
ጋር እንዴት ተደብቀው ወደ ዋና እንደሚሄዱ ነግራናለች:
እጄን ይዞ በጣቶቻችን እየተራመድን ከትልቁ ቤት ወጣን በሞቃታማው
የበጋ ምሽት ውጪ መሬት ላይ መሆን ለየት ያለ ስሜት አለው መንትዮቹን ብቻቸውን የተቆለፈ ክፍል ውስጥ ትተናቸዋል፡ ትንሽዬዋን ድልድይ ስናቋርጥ አሁን ከፎክስወርዝ ግዛት ውጪ መሆናችንን ስላወቅን ደስታ ተሰማን:: ነፃ የሆንን መሰለን፡ ቢሆንም ማንም እንዳያየን ጥንቃቄ ማድረግ አለብን። ወደ ሜዳውና እናታችን ወደ ነገረችን ሀይቅ ሮጥን።

ጣሪያው ላይ ስንወጣ አራት ሰዓት ነበር: በዛፎች የተከበበውን ትንሽ የውሀ
አካል ስናገኝ አራት ሰዓት ተኩል ሆኖ ነበር። ሌሎች ሰዎች እዚያ ኖረው ምሽታችን ይበላሽብናል ብለን ፈርተን ነበር። ነገር ግን የሀይቁ ውሀ ፀጥ ያለና
በንፋስ እንኳን የማይንቀሳቀስና የሚዋኙም ሆኑ በጀልባ የሚቀዝፉ ሰዎች የሌሉበት ነበር።

በጨረቃ ብርሃን በኮከቦች በደመቀ ሰማይ ስር ሆኜ ሀይቁን እየተመለከትኩ እንደዚህ አይነት የሚያምር ውሀ አይቼ እንደማላውቅና እንደዚህ በሀሴት
የሞላኝ ምሽት ኖሮ እንደማያውቅ አሰብኩ።

“እርቃናችንን እንዋኛለን?” ሲል ክሪስ ለየት ባለ ሁኔታ እያየኝ ጠየቀኝ፡

“አይ የውስጥ ሱሪያችንን ለብሰን ነው የምንዋኘው” አልኩት።

ችግሩ አንድም የጡት መያዣ የሌለኝ መሆኑ ነበር። አሁን ግን እዚህ ደርሰናል: አጉል የሆነው የጨዋነት ጥያቄ በዚህ በጨረቃ ብርሀን በደመቀ ውሀ ከመደሰት አያስቆመኝም። ልብሴን አውልቄ የመርከብ ማቆሚያ ወደ
ሆነው ጥልቀት የሌለው ጥግ ጋ ሮጥኩ። ስደርስ ግን ውሀው እንደ በረዶ ይቀዘቅዝ ይሆናል ብዬ ስላሰብኩ በመጀመሪያ እግሬን ነከር አድርጌ አረጋገጥኩ እውነትም በጣም ቀዝቃዛ ነው! ክሪስን ሳየው ሰዓቱን ከእጁ ላይ ፈትቶ ወደጎን
በማስቀመጥ ወደ እኔ እየሮጠ መጣና ደፍሬ ወደ ውሀው ከመግባቴ በፊት ጀርባዬ ጋ ደርሶ ገፈተረኝ: ውሀው ውስጥ በደረቴ ወደቅኩና ሙሉ በሙሉ
ውሀ ውስጥ ጠለቅኩ።

ከውሀው ስወጣ እየተንቀጠቀጥኩ ነበር። ወደ ክሪስ ተመለከትኩ ከፍ ያለ ድንጋይ ላይ ቆሟል ክንዶቹን ወደ ላይ አነሳና ወደ ሀይቁ ተወርውሮ ገባ፡ በድንጋጤ አቃተትኩ። ውሀው በቂ ጥልቀት ያለው ባይሆንስ? መሬቱ
መትቶት አንገቱ ወይም ጀርባው ቢሰበርስ?

ክሪስ ወደ ላይ አልተንሳፈፈም: አምላኬ! ሞቷል ሰምጧል!

“ክሪስ!” እየጠራሁትና እያለቀስኩ ገብቶ ወደተሰወረበት ቦታ መዋኘት ጀመርኩ።

ድንገት የሆነ ነገር እግሬን ያዘኝ! ጮህኩና ወደ ውስጥ ገባሁ የጎተተኝ ክሪስ ነበር፡ በጥንካሬ እግሮቹን እያወራጨ ወደምንስቅበትና ውሀ ወደምንረጫጭበት ወጣን

“እዚያ የተረገመ የሚሞቅ ቤት ውስጥ ከመዘጋት ቅዝቃዜው አይሻልም? ሲል ጠየቀኝ፡ ልክ እንደ እብድ ዙሪያውን እየዞረ ሲጮህ ላየው ይህች ትንሽ ነፃነት እንደ ጠንካራ የወይን ጠጅ አናቱ ላይ ወጥታ ያሰከረችው ይመስል
ነበር። ዙሪያዬን እየዞረ ዋኘና እግሬን ይዞ ወደታች ሊጎትተኝ ሞከረ: አሁን
ግን አልቻለም:

ውሀ እየተረጫጨንና እየዘፈንን፣ ከዚያ ደግሞ አቅፎኝ ስንስቅና ስንጮ ነበር። ልክ እንደገና ልጆች የሆንን ይመስል ታገልን… አበድን ውሀ ውስጥ በጣም ጎበዝ ነው ልክ እንደ ዳንሰኛ: እየዋኘን እያለ በድንገት ደከመኝ::በጣም ከመድከሜ የተነሳ እንደ እርጥብ ፎጣ ሆኜ ነበር። ክሪስ በክንዱ ደግፎ ወደ ዳር እንድወጣ አገዘኝ።

ሁለታችንም ሀይቁ ዳር ላይ ያለው ሳር ላይ በጀርባችን ተጋድመን ማውራት ጀመርን።

“አንድ ጊዜ እንዋኝና ወደ መንትዮቹ እንመለስ” አለ ሁለታችንም
የሚያብረቀርቁና የሚጣቀሱ የሚመስሉት ኮከቦች ላይ አተኩረናል። ደስ የምትል ግማሽ ጨረቃ ደመናው ውስጥ ብቅ ጥልቅ እያለች ድብብቆሽ
የምትጫወት ትመስላለች፡ “ምናልባት ወደ ጣሪያው መውጣት ባንችልስ?” አልኩ

“እንችላለን፡ ምክንያቱም ማድረግ አለብን” ክሪስቶፈር ሁልጊዜ እንደሚቻል የሚያምን ልጅ ነው: ሰውነቱ በውሀ ረጥቦ፣ ፀጉሩ ግንባሩ ላይ ተጣብቆ አጠገቤ ተጋድሟል። አፍንጫው እንደ አባታችን አፍንጫ ቀጥ ያለ ነው: ከንፈሮቹ የሚያምር ቅርፅ አላቸው:: አገጩ አራት ማዕዘን ሲሆን ደረቱ መስፋት ጀምሯል። እያደገ ያለው ወንድነቱ በጠንካራ ጭኖቹ መሀል ማበጥ ጀምሯል። ስለ ወንዶች ሳስብ አንድ ነገር ይማርከኛል
ያም ጥሩ ቅርፅ ያላቸው ጭኖች ናቸው፡ ጥፋተኝነት ሳይሰማኝና ሳላፍር ቁንጅናውን በአይኖቼ ለመመገብ ባለመቻሌ አዝኜ ጭንቅላቴን አዞርኩ።

ፊቱን አዙሮ አይኖቼን ተመለከተ: እኔም አየሁት። ሌላ ቦታ መመልከት
የማንችል እስኪመስል ድረስ እይታዎቻችን ተቆላለፉ ለስላሳ የደቡብ ነፋስ ፀጉሬ ውስጥ እየተጫወተና ፊቴ ላይ ያለውን ውሀ
እያደረቀው ነው፡ ምሽቱ በጣም ጣፋጭና በጣም ደስ የሚል ቢሆንም ፍቅርን የመራብ ከፍተኛ ስሜት ውስጥ ባለ ዕድሜ ላይ ያለሁ በመሆኔ ብቻ ምንም
ምክንያት ሳይኖረኝ ማልቀስ ፈለግኩ: ከዚህ በፊት እዚህ የነበርኩ አይነት ስሜት ተሰማኝ፡ ከሀይቁ አጠገብ ሳሩ ላይ እንደተጋደምኩ እንግዳ የሆነ
ሀሳብ በመጀመሪያ እንደ ተሳዳጅ ወደዚህ ወደመጣንበትና ከማይፈልገን አለም ወደተሸሸግንበት ወደዚያ ምሽት መለሰኝ።

ክሪስ፣ አሁን አስራሰባት አመት ሊሆንህ ነው፣ አባቴ እናቴን በመጀመሪያ ሲያገኛት የነበረበት እድሜ ማለት ነው”

አንቺ ደግሞ አስራ አራት፤ ልክ በእሷ እድሜ” ድምፁ ጎርነን ብሎ ነበር።

መጀመሪያ እይታ በሚፈጠር ፍቅር ታምናለህ?”

“በዚህ ርዕስ ላይ ጠቢብ አይደለሁም ትምህርት ቤት እያለሁ፣ አመነታ አንዲት የምታምር ልጅ አይቼ ወዲያው ፍቅር ይዞኝ ነበር ስናወራ ግን የሆነች ደነዝ ነገር ሆና ሳገኛት ለሷ የነበረኝ ስሜት ጠፋ፡ ግን ውበቷ በሌሎች
ነገሮች ከተደገፈ በመጀመሪያ እይታም ፍቅር ሊይዘኝ ይችላል ብዬ አስባለሁ ነገር ግን እንደዚያ አይነት ፍቅር አካላዊ መሳሳብ ብቻ እንደሆነ አንብቤያለሁ።

“እኔስ ደነዝ እመስልሀለሁ?”

“በጭራሽ! እንደሆንሽ እንደማታስቢ ተስፋ አለኝ፡፡ ምክንያቱም አይደለሽም።ፈገግ ብሎ ፀጉሬን ሊነካ እጁን እየዘረጋ ችግሩ ካቲ፣ ብዙ ተሰጥኦዎች ስላሉሽ ሁሉንም መሆን ትፈልጊያለሽ ያ ደግሞ የማይቻል ነው:"

“ዘፋኝም ተዋናይም መሆን እንደምፈልግ እንዴት አወቅክ?”
#ጠላፊዎቹ


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#በኬንፎሌት


#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ


...አሁን ሰዓቱ አስር ሰዓት ከሃያ ሆኗል፡ የመሳፈሪያው ሰዓት ደርሷል። ከስልክ መደወያው ኪዮስክ ወጣችና መርቪን ስልክ ወደሚነጋገርበት ክፍል ሄደች።ስታልፍ እንድትቆም የእጅ ምልክት ሰጣት በመስታወት አሻግራ
ስታይ ተሳፋሪዎች ወደ አይሮፕላኑ የሚወስዳቸው ጀልባ ላይ ሲወጡ አየች፡፡
ሆኖም መርቪን ቁሚ ስላላት ቆመች፡ መርቪን በስልክ አሁን በዚህ ነገር
አታስቸግረኝ፡፡ ሰራተኞቹ የጠየቁህን ክፈልና ስራው እንዲቀጥል አድርግ›› ሲል አዘዘ፡፡

በመርቪን ፋብሪካ ውስጥ ሰሞኑን የአሰሪና ሰራተኛ ውዝግብ እንደነበር
ነግሯታል፡ ከእሱ ባህሪ በተቃራኒ ሲታይ አሁን ለሰራተኞቹ ጥያቄ እጁን
የሰጠ ይመስላል፡

ስልኩን የደወለው ሰው በመርቪን አነጋገር ሳይደነቅ አይቀርም፡፡
‹‹አዎ እንዳልኩህ አድርግ፤ የምሬን ነው፡፡ ከማንም ቀጥቃጭ ጋር
ለመጨቃጨቅ ጊዜ የለኝም፡ ደህና ሁን›› አለና ስልኩን ዘጋ፡፡ ከዚያም
‹‹ስፈልግሽ ነበር?›› አላት ናንሲን፡፡

‹‹ተሳካልህ? ባለቤትህ አብሬህ እመጣለሁ አለች?›› ስትል ጠየቀችው፡
‹‹ገና በቀጥታ እንሂድ አላልኳትም››
‹‹አሁን የት ነው ያለችው?››
በመስኮት አየና ‹‹ያቻትልሽ ቀይ ኮት የለበሰችው››
ናንሲ በእድሜ በሰላሳዎቹ መጀመሪያ ላይ የምትገኝ ቃጫ የመሰለ ጸጉር
ያላት ሴት አየች፡ ‹‹መርቪን ባለቤትህ በጣም ቆንጆ ናት!›› አለች፡ ናንሲ
በመርቪን ሚስት ቁንጅና ተደንቃለች፡፡ እሷ የገመተቻት እንዲህ አልነበረም፡
‹‹ይህቺ ሴት ከእጅህ እንዳትወጣ ለምን እንደፈለግህ አሁን ገባኝ›› አለች፡ዳያና አንድ ሰማያዊ ሱሪ የለበሰ ሰው ሶቶ ይዛለች፡፡ ማርክ እንደ መርቪን አያምርም፡ ቁመቱ አጠር ያለ ሲሆን ፀጉሩ ከግንባሩ እየሸሸ ነው፡፡ ነገር ግን ፎልፎላ እና ተጫዋች ይመስላል ሲያዩት፡፡ ናንሲ የመርቪን ሚስት የባሏን
ተቃራኒ የሆነ ሰው መያዟን አስተዋለች፡፡ ለመርቪን አዘነችለት።
‹‹እግዚአብሔር ጽናቱን ይስጥህ›› አለችው፡፡

‹‹ገና እጅ አልሰጠሁም›› አለ፡፡ ‹‹ኒውዮርክ ድረስ ተከትያት እሄዳለሁ››
ናንሲ የመርቪን አባባል አሳቃት፡ ‹‹ደግ አደረግክ! ባለቤትህ ማንም ወንድ ልጅ አትላንቲክን አቋርጦ የሚከተላት አይነት ሴት ናት፡››

‹‹የችግሩ መፍትሄ አንቺ እጅ ውስጥ ነው ያለው›› አላት ‹‹አይሮፕላኑ ሞልቷል ቦታ የለም››

‹‹እውነት ነው ታዲያ ኒውዮርክ ድረስ በምን ትሄዳለህ? ደግሞ
ምንድን ነው በእኔ እጅ ውስጥ ያለው መፍትሄ?››
‹‹አንቺ ነሽ ቀሪውን ትርፍ ወንበር የያዝሽው፡፡ የሙሽሮችን ክፍል
መያዝሽን ሰምቻለሁ፡ ትርፏን ወንበር ለኔ ሽጭልኝ››

ናንሲ ከት ብላ ሳቀችና ‹‹የሙሽሮችን ክፍል ከወንድ ጋር መጋራት
አልችልም፡፡ እኔ የተከበርኩ ሴት ነኝ እንጂ የሆነች ዳንሰኛ አይደለሁም››
‹‹እኔ ግን ማንም ያላደረገልሽን ውለታ አድርጌልሻለሁ›› አላት ፍርጥም ብሎ።
‹‹ውለታህ ሊኖርብኝ ይችላል ክብሬን መሸጥ ግን አልችልም ናንሲ ያለችውን እንዳልተቀበለ ይመሰክራል ‹‹በአይሪሽ ባህር ላይ ከኔ ጋ
ስትበሪ ስለክብርሽ አልተጨነቅሽም››

‹‹እዚያ ላይ እኮ አብረን አላደርንም›› አለች፡፡ ብትረዳው በወደደች
ውቧን ሚስቱን ለማስመለስ ቁርጠኛ መሆኑ ልቧን ነክቷታል፡

‹‹ይቅርታ አድርግልኝ በዚህ እድሜዬ ካንተ ጋር አንድ ክፍል አድሬ የሰው መሳቅያ
መሆን አልፈልግም

‹‹ስለሙሽሮች ክፍል ጠይቄያለሁ። ከሌሎች ክፍሎች የሚለየው ነገር
የለም፡ ባለሁለት አልጋ ነው፡፡ ማታ ማታ በሩን ብንከፍተው ሁለት የማይተዋወቁ ሰዎች ፊት ለፊት የያዟቸው ትይዩ ወንበሮች መሆናቸው ይታያል፡››

‹‹ሰው ምን እንደሚል አስብ መርቪን››

‹‹ለማን ነው የምትጨነቂው? ባል የለሽ? ቤተሰቦችሽ ሞተዋል እዚህ
ለምታደርጊው ነገር ማን ግድ አለው?››

መርቪን አንድ ነገር ከፈለገ ፊት ለፊት ነው የሚናገረው፡
ይቀየመኛል ብሎ አያስብም፡፡

‹‹ሁለት ትልልቅ ወንድ ልጆች አሉኝ›› ስትል አነጋገሩን ተቃወመች።
‹‹ልጆችሽ ይህን ሲሰሙ ቀልድ ነው የሚመስላቸው››
ሊመስላቸው ይችላል አለች በሆዷ ሃዘን እየተሰማት፡ ‹‹እኔን የጨነቀኝ የድፍን ቦስተን ከተማ ሰው ምን እንደሚል ነው፡፡ እኔ ታዋቂ ሴት በመሆኔ ወሬው እንደ ቋያ እሳት በአንዴ ነው የሚዳረሰው››

‹‹ተመልከች! እንግሊዝ አገር እዚያ አይሮፕላን ጣቢያ ላይ ሆነሽ ምን ያህል ተቸግረሽ እንደነበር እንድወስድሽ ምን ያህል ፈልገሽ እንደነበር
አስታውሺ፡፡ ያኔ ከጉድ ነው ያወጣሁሽ፡፡ አሁን በተራዬ እኔ የማልወጣው ችግር ላይ ወድቄያለሁ፡ የኔ ጭንቀት አልገባሽም ማለት ነው?›› አላት

‹‹ይገባኛል››

‹‹ስለዚህ ችግር ላይ ስላለሁ ከጉድ አውጪኝ፡፡ ትዳሬን ለማዳን ያለኝ
የመጨረሻ እድል ይሄ ብቻ ነው፡፡ ይህን ማድረግ ደግሞ ትችያለሽ፡፡ እኔ በችግርሽ ጊዜ ደርሼልሻለሁ፡ አሁን ብድር የምትመልሽበት ጊዜ መጥቷል።ሰው እንደሆነ አምቶ አምቶ ሲደክመው ይተዋል፡፡ የአንድ ሰሞን ሀሜት ደግሞ ሰውን አይገድልም፡፡››

የአንድ ሰሞን ሀሜቱን አሰበች፡፡ አንዲት የአርባ አመት እድሜ ላይ የምትገኝ ባሏ የሞተባት ሴት በግድ የለሽነት እንዲህ አይነት ነገር ብታደርግ ምን ችግር አለው፡፡ ይህን በማድረጓ አትሞት! መርቪን እንዳለው ክብሯንም አይቀንሰውም፡፡ አሮጊቶች ምነው ቀበጠች› እንደሚሏት ጥርጥር የለውም:፡
የእድሜ እኩዮቼ ግን ድፍረቴን ያደንቃሉ አለች በሃሳቧ የመርቪን የተጎዳና አቋመ ፅኑ ፊት ስታይ ልቧ ከእሱ ጋርሄደ የቦስተን ህዝብ ገደል ይግባ፡፡ ይህ ሰው ችግር ላይ ወድቋል፡ እኔ ተቸግሬ በነበረበት ሰዓት ለችግሬ ደርሷል፡ እኔ ባላመጣሽ ኖሮ ዛሬ እዚህ አትገኝም ነበር› ያለው እውነት ነው።

‹‹ናንሲ የያዝሽው ክፍል ውስጥ ታስገቢኛለሽ? የመጨረሻ ተስፋዬ አንቺ ነሽ"

‹‹አዎ አስገባሀለሁ›› አለች፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የሄሪ ማርክስ የመጨረሻ አውሮፓ ትውስታ ለመርከበኞች ምልክት የሚሰጠውን የፓውዛ ማማ የአትላንቲክ ውቅያኖስ ሞገድ እየመጣ
ሲለትመው ያየው ብቻ ነው፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ የሚታይ መሬት
አልነበረም፧ ዳርቻ ከሌለው ባህር በስተቀር፡፡

አሜሪካ ስገባ ሀብታም እሆናለሁ› ሲል አሰበ፡፡

በሌዲ ኦክሰንፎርድ ሻንጣ ውስጥ የተሸጎጠው ጌጥ የወሲብ ያህል የሚያጓጓ ነው፡፡ ይህ እንቁ በዚህ አይሮፕላን ውስጥ አንድ ቦታ ይገኛል ዕንቁውን በእጁ ለማስገባት ቋምጧል፡

ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ እንቁ ከሌባ እጅ በመቶ ሺህ ብር ይገኛል።በዚህ ገንዘብ ጥሩ መኪና ምናልባትም የቴኒስ መጫወቻ ያለው ቤት እገዛለሁ ወይም ገንዘቡን ኢንቨስት አደርግና በወለዱ ብቻ እኖራለሁ፡ ስራ
ባልሰራ ደልቀቅ ብዬ እኖራለሁ› ሲል ተመኘ፡፡
በመጀመሪያ ግን እንቁውን በእጁ ማድረግ ይኖርበታል፡ ጌጡ በሌዲ ኦክሰንፎርድ አንገት ላይ አይታይም፡ ስለዚህ ሊኖር የሚችለው በእጅ ቦርሳቸው ውስጥ ወይም እዚህ አጠገባቸው ባለው ማስቀመጫ ወይም ደግሞ ሻንጣ የሚቀመጥበት ቦታ እኔ ብሆን ካጠገቤ አለየውም ነበር ከአይኔ ከራቀ እንቅልፍም አይዘኝም› ሲል አሰበ ሄሪ፡

መጀመሪያ የእጅ ቦርሳቸውን ይበረብራል፡ እንዴት እንደሚበረብር ግን
አልመጣለትም፡፡ ምናልባትም የሚሻለው ማታ ሰው ሁሉ ከተኛ በኋላ ነው።
#ኢቫንጋዲ


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ

ብላንክ ፓሎማ' ይሉታል ስፔኖች! ነጭ እርግብ ማለት ነው፡ የዚህ የስፔኑ ተወላጅ እውቁ ሰዓሊ ፓውሉ ፒካሶ ደግሞ ነጭ
እርግብን የሰላም ምልክት አድርጎ ለአለም ህዝብ አበርከቷል፡

ብላንካ ፓሎማ ሮሲ በተባለ ቦታ በዓመት አንዴ የሚከበር ከኢትዮጵያውያን ጥምቀት ጋር የሚመሳሰል በዓል ነው፡፡ ስፔናውያን
እየደነሱና እየጨፈሩ የአለፈውን ዘመን አመስግነው መጭውን
ደግሞ ሰላም የሰፈነበት የሥራ ዘመን እንዲሆንላቸው አምላክን የሚያመሰግኑበትና የሚለምኑበት ክብረ በዓል ነው ብላንካ ፓሎማ።

በዓሉን ለማክበር ከተለያየ ቦታ ለጥምቀት ያልሆነ ቀሚስ  እንዲሉ ሴቶቹ ከወገባቸው ጠቡብ ብሎ  ከታች ቦለል በማለት መሬት
የሚነካውን ቀሚሳቸውን ወደ ላይ በጣታቸው ሰብሰብ ያርጉና
አንቧለሌ እየዘሩ ጣቶቻቸውን እንደ ኮብራ አንገት እያሟለሉ ወንዶች ደግሞ የተተፈተፈ የቆዳ ሱሪና ሰደርያ ነጭ ሸሚዝ ሰፊ ባርኔጣ ይለብሱና ብብቱ ውስጥ ዝንብ እንደገባበት ፈረስ ባለ በሌለ ኃይላቸው መሬቱን እየደለቁ እጆቸውን እየሰበቁ እንደ አውራ ዶሮ በሴቷ ክብ ሲዞሩ ጭብጨባው ዝማሬው ፉጨቱና ጨኸቱ
ይቀልጣል፡፡ አሸነፈችው! አሸንፏታል! እየተባለ አቧራው ይጤሳል።

በብላንክ ፓሎማ በዓል
ዘመናዊ ተሽከርካሪ አይኬድም ዘመናዊ ነገር ፈጽሞ እንዲታይም አይፈለግም ወደ በዓሉ ቦታ
የሚጓዘው ሰው በፈረስና በቅሎ  በሚሳቡ ባህላዊ ጋሪዎች የሚበላ የሚጠጣው  ይጫንና ህፃናትና አዋቂን በባህል ልብሳቸው አሸብርቀው አልፎ አልፎ ወንዶቹ በሚገባ በተቀለበ ጠብደል ፈረሰና በቅሎ ሆነው ሶምሶማ እየረገጡ እንደ አባቶቻቸው ወግና ባህል በዓሉ ወደ ሚከበርበት ሮሲ ሲጓዙ በየከተማው ህዝቡ እየወጣ እያጨበጨበና
አብሮ እየጨፈረ ይሽኛቸዋል፡፡

በግብርና ምርቷ በመላው አውሮፖ በይበልጥ የምትታወቀው
ስፔን ህዝቧ በደስታ ፍንድቅድቅ እያለ የአለፈ  ወግና  ልማዱን በዓመት በዓመት እየተከተሉ አምላኩን ሲያመሰግን ሮሲ ሲሰባሰብ ደስታውን ለመክፈል ፈገግተኛና ደስተኛውን የበዓል አክባሪ አይቶ ለመርካት በብዙ ሺ የሚቆጠር ህዝብ ከፈረንሳይ ከፖርቹጋል ከሌሎችም የአውሮፓ አገሮች ወደ ሮሲ ይጎርፋል፡፡

ብላንክ ፓሉማን ለማክበር የሚሰባሰበው ሁሉ ዓላማው በሰላም  መዝናናት ነው፡፡ በቡድን በቡድን ጨዋታና ጭፈራው
ይቀልጣል ፍቅር እየታጨደ ይወቃል ደስታ እንደ ብርቱካን እየተላጠ ይበላል.. በብላንካ ፓሉማ
ኮንችትና ሶራን ወደ ኢትዮጵያ ከመሄዳቸው በፊት እዚህ ባህላዊ በዓል ላይ እንዲካፈል ጋበዘችው፡፡ ሶራ ሆራ ብላንካ ፓሎማን
ለማክበር የተሰባስበው ህዝብ  ለበዓሉ የሚሰጠው ግምት ሲያይ የባህል የማንነት መለያነት ጥቅሙ የመገናኛ ድልድይ መሆኑ
የፍቅር ማጠናከሪያነቱ… ወለል ብhሎ ታየው።
ስዉ ይጨፍራል ይተቃቀፋል በአንድ ጠርሙስ እየተቀባበለ ይጎነጫል እየተሸማ ይበላል... ደስ አለው ሶራን፡፡
እሱንም እየነካኩ  እያጨዋወቱ የስፓኛን ወይን እያቀማመሱ… በህዝቡ መስመር አሰለፉት፡፡ የችሎታውን አጨበጨበ ጨፈረ “ኢትዮጵያዬ' እያለም ጮኸ፡፡ የጥቁሩም የነጩም ፈጣሪ ወደ ሆነው
አምላኩም ምስጋናውን በማህሌተ ዜማው አሰማ፡፡ ቅዱስ ያሬድ ከጎኑ ጽናጽሉን እያንሿሿ ያዜም ቀሳውስት ሲወርቡ የአማራው የጉራጌው የወላይታው. የሲዳማው የኦሮሞው
የኤርቦሬ..ባጠቃላይ የኢትዮጵያ ህዝብ ባህላዊ ጭፈራ ታየው፡፡ እና ዘለለ!
ብቻውን ሳይሆን ምናቡ ከአመጣቸው ወገኖች ጋር ከዚያ ውብ አፍሪካዊ ጋር ከብላንካ ፓሎማ በዓል አክባሪ ጋር ዘለለ ነጭ
እርግቦች ሰማዩን ሞልተውታል፡

“ብረሩ ሂዱ አፍሪካንም ሙሏት..." ጠራቸው ነጫጭ
እርግቦችን፡፡ እርግቦቹ ይስሙት አይስሙት ግን አያውቅም፡፡

ኮንችት አረንጋዴ ሆኖ ዳር ዳሩ በቀይ ሪባን የተከፈፈ
ቀሚሷን ለብሳ ዞማ ፀጉሯን ጎንጉና አናቷ ላይ በቀይ ሮዝ የፀጉር ማስያዣ አስይዛ የሙቀት ማራገቢያዋን በቄንጥ በመያዝ እንደ አበባ
ፈክታ ወንዶች እንደ ንብ ዙሪያዋን እየበረሩ፤ መሬቱን እየደለቁ ጣታቸውን እየሰበቁ… በዚያ እንደማግኔት በሚስበው ፈገግታቸው እያሽኮረመሟት ሲያይ ኮንችት ልዩ ፍጥረት ሆነችበት፡፡ ጠይሟ
ለግላጋዋ... ኮንችት ደሙን ተክታ በውስጡ ተሰራጨች፡

ብላንካ ፓሎማ… ብላንካ ፓሎማ… ሶራ በሺ የሚቆጠረው ህዝብ ተረሳው፡፡ ሌሎችን ዘነጋቸው. ኮንችት ብቻ ታየችው ኢትዮጵያዊዋ ውብ የጠይም ቆንጆዋ የቁንጅና ልዕልቷ…

“በብላንካ ፓሎማ ስጦታ አበረክትልሀለሁ" ብላዋለች፡፡

“ምን ይሆን ስጦታዋ! ጎመዠ፡፡ እስካሁን ልትሰጠው ስላሰበችው ስጦታዋ አለማሰቡ  አስገረመው፡ አያት ከርቀት
ትደንሳለች፡፡ ቼኮሌቷ ጠይም እንቁዋ! በአይኑ ነካት  በአይኑ ቀመሳት  ጣፈጠችው።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እኩለ ለሊት አካባቢ ሰዉ ተዳከመ፡፡ ሁሉም ወደ
የማደሪያው ተበታተነ… ኮንችት ገላዋን ታጥባ ስስ የሌሊት ገዋኗን ለብሳ ስትወጣ ከድንኳኑ ትይዩ ሶራ ያቀጣጠለውን እሳት አየች፡፡
ከሐር የተሰራ ሰፊ  ስጋጃ ተነጥፏል አንድ ጠርሙስ ወይንና   ሁለት ብርጭቆ ይዛለች

እሳቱ አስቸግሮህ ነደደ" አለችው ስጋጃው ላይ
ቁጭ እያለች።

የት ያመልጣል ብሎ ሲያያት የሆነ ነገር ተመለከተ ነጭ ፓንት ተምታታበት፡ አንዳች ሀይል ከውስጡ አንገጫገጨው

"ብላንካ ፓሉማን ወደድከው?"

ቆንጆ በዓል ነው፡ ስሙ ራሱ ነጭ…" እንደገና ወደ እሷ
ተመለከተ ነጩንም ...አየው

ኮንችት ከላይ ገዋኗን ከታች ነጭ ፓንቷን ትልበስ እንጂ
እንደ ሎሚ ሁለት ቦታ ጉች ጉች ያሉት ጡቶችዋ ሰርጓዳ ወገቧ ለስላሳው ጭኗ ካለመከላከያ ይታየዋል፡

ሶራ ጫን ጫን ተነፈሰ ልቡ ፈራ ስሜቱ ተረበሸ ይባስ ብሎ ተንጫጫ።

ኮንችት በሁለቱ
ብርጭቆዎች ለብላንካ ፓሎማ የሚዘጋጀውን ምርጥ ወይን ቀዳችና  የዚህ ዓይነት ወይን ከዚህ
በፊት እርግጠኛ ነኝ የቀመስህ አይመስልኝም፡፡ ውድ ነው! እኔ ግን
የምወደው በውድነቱ ወይንም በቃናው ሳይሆን በመልኩ ነው፡፡
ፀሐይ ላይ ወይን ጠጀ በጨረቃ ብርሃን ደግሞ ወርቃማ ይሇናል ና አዚህ ጋ ቁጭ በልና ተጎንጨው" አለችው፡፡

ሄዶ ከሷ ፈንጠር ብሎ ቁጭ አለ መዓዛዋ ግን
አልራቀውም ለጤናችን ለስጦታዬ" ብላ አየችው፡ ተጎነጫጨለት፡፡

ለስጦታዬ አሰበ ሶራ
እንዳንጋጠጠ ወይኑ መሆኑ
ነው ስጦታዋ .. ውዱ በጨረቃና በፀሐይ ብርሃን እንደ እስስት ቀለሙን የሚቀያይረው

ጣምናውን  ለማወቅ እንደገና ጎንጭ አድርጎ አጣጣመው ወደ አፍንጫው ጠጋ አድርጎ አሽተተው ቀና አድርጎ በጨረቃ ብርሃን ተመለከተው… ወርቃማ ነው!

“ወደድከው አይደል?" የኮንችት አነጋገር እንደ ከላሲካል ሙዚቃ የጆሮውን ታንቡር እየዳሰሰው በሰራ አካላቱ ሰረገ፡፡

“አዎ ጥሩ ነው" ዝም ተባባሉ እሳቱ ይነዳል፡፡ የእሳቱ ብርሃን እነሱ ላይም ተንፀባርቆ ከርቀት ለሚያያቸው እነሱም የሳት
ላንቃ መስለዋል፡፡ ሶራ በጀርባው ስጋጃው ላይ ተኛ እሷ ደግሞ ወደ እሱ ዙራ በጎኗ ተኛች፡፡ የሆነ ነገር እየወዛወዘ እያት እያት አሰኘው ግን ፈራ፡፡

ዛሬስ ገና ስሜቷን እያዳመጠችው ይሆን? ጠየቀ ራሱን ዞር ብሎ ሊያያት አሰበ፡፡ የሆነው ነገር ወዘወዘው እንደገና ቀስ ብሎ ዞር ብሎ አያት  አይኗ ነው የወዘወዘው ፍዝዝ ብሏል አይኗ ከንፈሯ እንደ እንቡጥ ፅጌሬዳ አሞጥሙጧል አይኑን ፈጠጥ አድርጎ አያት፡፡ አየችው እሷም  በፈዘዙ አይኖችዋ፤ የእሳቱ ብርሃን
ግን በመካከላቸው አለ፡፡ ጡቷ ወገቧ ነጩ ፓንት. ታዩት የገዛ ምራቁ ሊያንቀው
ተቃረበ፡፡ ዘወዲያው ልቡ አይኑን ስልብ ስልምልም… አደረገበት፡፡
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ


#ክፍል_ሀያ_ስድስት

#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///

እኔ ይቅርታዬን ሳልጨርስ ምስርም ካለችበት ተንደርድራ መጥታ ልክ እኔ እንዳደረኩት እቴቴ እግር ስር ድፍት አለች።አንዳንድ እግር ተከፍፋልን ።እቤቱ ለቅሶ በለቅሶ ተደበላለቀ።ተረባርበው ሁለታችንንም ከተደፋንበት አነሱን ..እንደተነሳን በግራና ቀኝ ትከሻዋን ተከፋፍለን ተጠመጠምንባት፡፡ ተአምርን ጨምሮ ሌሎቹም እየመጡ ተቀላቀሉን። መላቀሱና መሳሳሙ አልቆ ስርአት ይዘን ለመቀመጥ ምን አልባት ከ20 ደቂቃ በላይ ሳይፈጅ አልቀረም።የዛ ሁሉ አመት ስቃይ….የዛ ሁሉ ጊዜ ቁጭትና ፀፀት ….የዛ ሁሉ ለሊትና ቀን የልብ ድማትና የጨጓራ ቁስለት እንዲህ በአስር ደቂቃ የይቅርታ ቃላቶች እና መላቀሶች መሻሩእና መጠገኑ የሚገርም ነው፡፡ይቅርታ የሚባል ነገር ባይኖር የሰው ልጅ ጠቅላላ ህይወቱ ምን መልከ ይኖረው ነበር ?ብዬ አሰበብኩና ዝግንን አለኝ ፡፡ብቻ ቀስ በቀስ መረጋጋቱ ሲመጣ ወደ ጫወታና መሳሳቅ ገባን።

"አያቴ ግን እንዴት..?"እኔ ነኝ ለመጀመሪያ ጊዜ አያቴን ፊት ለፊት በአካል ከእነአዛውንት ውበቱና ግርማ ሞገሱ በማየቴ እየተደመምኩ የጠየቅኩት፡፡

"እንዴት ምን..?"

"ዛሬ እንዴት ወጡ..አታስበው አልመጣም ብለውኝ ነበርኮ"

‹ሀሳቤን ቀየርኮ…ይሄ ተአምራዊ ቀን እንዲያመልጠኝ ፈፅሞ አልፈለኩም..ስለልጅህ ስለአክስትህ በአጠቃላይ ስለመላው ቤተሠብ ለሁለት አመት በእየለቱ ስታወራልኝ ስለከረምክ ለእኔም ልክ እንደቤተሠቤ ነበር የሚናፍቁኝ.ጄኔራል ሁኔታውንና የተቀደሰ ሀሳቧን አብራርታ ስትነግረኝ በእንቢታዬ መግፋት አልቻለልኩም።"

‹‹እሱሰ እውነቷትን ነው አያቴ. ግን ይሄ በጣም የሚገደርም ውሳኔ ነው ?መቼስ ጋሼ ይሄንን ቢያይ ተገርሞም አያባራም…››

ከዛ ብዙ ብዙ ጫወታ ተጫወትን..ምሳ ቀረበ የሚጣጡ መጠጦች እንደየምራጫችን ታደሉን …በሳቅና ጫወታ ያወራረድን በደስታ ተመገብን፡፡
እስከ10 ሰዓት ስንጫወት ቆየንና ከሳምንት በኃላ ወይ እኔ ሄጄ ልጠይቃቸው ወይ ደግሞ ሁሉም ተሰብስበው እኔ ቤት ሊመጡ ተነጋገርንና እንዳመጣጣቸው ሸኘናቸው….በመጨረሻ እኔና ጄኔራሎ ብቻ ቀረን፡፡ከዛ የተደመምኩባቸውን ጥያቄዎች ተራ በተራ አቀርብላት ጀመር፡፡

"ግን እንዴት?"
"እንዴት ማለት?"
"እነ አክስቴን እንዴት አገኘሽ ?እንዴት አሳመንሻቸው?"

"ቀላል ነበር..የአንተን ማንነት ካወቅኩ በኃላ የወላጆችህን ቤት የተከራዪት ሰዎች ጋር ሄድኩና ያክስትህን ስልክ ተቀበልኩ …ከዛ ወደ ደብረብርሀን ሄድኩ።"
"ደብረ ብርሀን ድረስ?"
"ደብረብርሀን እኮ እዚሁ አዲስ አበባ አፍንጫ ስር ነች።"
"እሺ ይሁን .ከዛስ..?"
"ከዛማ ደረስኩና ደወልኩላት… የሞች እህቷ የድሮ ወዳጅ እንደሆንኩ ነግሬ የቤቷን አድራሻ ጠየቅኩ ።በቀላሉ ነገረችኝ፡፡ቀጥታ እቤት ሄጄ አዋዝቼ ስላንተ ነገርኳት።"

"በፈጣሪ ምን አለች ..?አልተበሳጨችም?"በከፍተኛ ጉጉት ጠየቅኳት

"ወይ መበሳጨት ..እዬብ በህይወት አለ ስላት እህተሽ ከመቃብር ወጣች ያልኳት ነው የመሠላት ..ለአንድ ሰዓት ስታለቅስ፤ ስትስመኘ፤ስትመርቀኝ ምኑን ልንገርህ..እውነት መሆኑን አላመነችም እህትቶችህ..በተለይ በተለይ እማ!!ያው ይገባሀል..አሁንም የፍቅር ስቃይ ፊቷ ላይ አለ…አሁንም በናፍቆት እየቃተተች ነው..አሁንም በማይድነው አጉል በሽታ ተለክፋ ትንፍሽ እንዳጠራት መሆኑን ሁኔታዎን ለደቂቃ አይቶ መረዳት ይቻላል።››

"ልጅህ ደግሞ።"
"ልጄ ምን?"
"አደገኛ አክተር ይወጣታል ..ልክ ስለአንተ ለመጀመሪያ ቀን እንደሰማ ሰው አብራ ስታዳንቅ ሳይ እኔ እራሴ ይሄ ልጅ ዋሽቶኛል እንዴ?በእርግጥስ የእውነት አግኝቶት ያውቃል? ብዬ እራሴን ለመጠየቅ ተገደድኩ"
"አዎ ቆቅ የሆነች ልጅ ነች ያለቺኝ"
"እስማማለሁ"
"እሺ አያቴንስ እንዴት አሳምነሽ አመጣሻቸው?"
ቀላል አልነበረም፣የጥሪ ካርዱን ባንተ በኩል ል እንዳልተስማሙ ከነገርከኝ ቡኃላ ያንተን አለመኖር እየጠበቅኩ ከሶስት ቀን በላይ መመላለስ ነበረብኝ..ቢያለፋኝም ተሳክቶልኛል።በዚህ አጋጣሚ ልንገርህ ..መቼም መቼም አያትህን እንዳታስቀይማቸው።የእውነትም እንደልጃቸው ነው የሚያዪህ።በጣም ነው የሚወድህ"
"አውቃለሁ..እኔም አያቴ ስላቸው ለማስመሰል አይደለም...የእውነት ከልቤ እንደዛ ስለሚሰማኝ ነው።
"ታድለህ"
እንዴት ታድለህ ልትይ ቻልሽ?"
"ብዙ ሰዎች ብዙ ደክመው ብዙ ጥረው የማይሳካላቸውን የሠው መውደድ አንተ በቀላሉ አለህ..አክስትህ..እህቶችህ.ልጅህ..አያትህ ..እኔ..ሁላችንም አምርረን እንወድሀለን "
"የእውነት ..?አንቺም አምርረሽ ትወጂኛለሽ?"
"ከዝርዝሩ ውስጥ የእኔ ነው አጠራጣሪው?"
"አይ እንደዛ ማለቴ አይደለም ..እንዲሁ አለ አይደል ..ለማረጋገጥ ነው የጠየቅኩት"
‹‹አይዞህ አትጠራጠር ..አንተ በጣም ውድድድ የማደርግህ ፤ታናሽ ወንድሜ ነህ?"
"በለው....አየሽ እድሌን?"
"እንዴት?"
"አሁን እኔ እህት የናፈቀኝ ይመስልሻል..?"
"አሁን እኳ ምርጫ የለህም ..የልጅህ እናት አሁንም እንደተራበችህ ነው..እርግጠኛ ነኝ አንተን ሳትይዝ ወደአሜሪካዋ አትመለስም።"
"ይዛኝ ሄዳስ?"
"እሱን እንግዲህ ጊዜ የሚመልሰው አስቸጋሪ ጥያቄ ይሆናል።››

"እሺ እንዳልሽ አሁን ትንሽ ጉዳይ ስላለችብኝ ልሂድ… ነገ እመጣና እዚሁ አድሬ እሸኝሻለሁ..ይቻላል አይደል?"
"በጣም ደስ ይለኛል።ጉንጯን ስሜ ተሠናብቼ ወጣሁ።››

ይቀጥላል
#ባል_አስይዞ_ቁማር››


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///

‹‹ምነው…ፒያሳ ይሻላል እንዴ?››ልዩ ነች የጠየቀችው፡፡

‹‹አይ የሆነች ጉዳይ ሳላለችብኝ ነው… ደረስ እንልና እንደውም እዛው ኢሊሊ ራት በልተን ከዛ ወደምትፈልጉበት ጭፈራ ቤት እንሄዳለን..››

ጊፍቲ ፈገግ አለች….ቀጥታ ፒያሳ ወደሚገኙ መደዳ ወርቅ ቤቶች ነበር ይዟቸው የሄደው..ልዩ እራሱ ያልጠበቀችው ነገር ስለሆነ ግራ ተጋባች…እሱ ራሱ ቀድሞ ያሰበበት ጉዳይ አልነበረም..ሰጥሀለው የምትለዋ ቃል ከአንደበቷ ተስፈንጥራ ስትወጣ በውስጡ በተፈጠረ ፍንጠዛና በምርቃና ድንገት ብልጭ ያለለት ሀሳብ ነው፡፡

‹‹ምነው ምን መጣ..?››ጠየቀችው፡፡

‹‹ቀለበታችን ሳንመርጥ የቀለበቱ ቀን ደረሰ እኮ?››

‹‹እንዴ ገና ሁለት ወር ይቀረናል እኮ››

‹‹ሁለት ወር ምን አላት….አይደል ጊፍቲ፡፡›› አለ ወደ እሷ ዞሮ ድጋፍ እድትሰጠው በሚፈልግ ንግግር…

እሷ የሰማችው አይመስልም ቅዝዝ ብላ ጭልጥ ያለ ሀሳብ ውስጥ ገብታለች

‹‹ጊፍቲ፡፡››

‹‹እ..ታድላችሁ…አዎ ትክክል ነው..ሁለት ወር በጣም አጭር ጊዜ ነው…››አለችና ተያይዘው ወደ ውስጥ ገቡ…ተገቢውን ቀለበት አማርጦ ለመግዛት ከሰላሳ ደቂቃ በላይ ነው የፈጀባቸው….በመጨረሻ እንደውም ጊፍቲ አሪፍ ነው ብላ ያሳየቻቸውን የዳይመንድ ፈርጥ ያለበት ቀለበትን ነው ሁለቱም በአንድ ድምፅ ተስማምተው የተገዛው..የሁለቱንም ቀለበት ሰጣትና ቦርሳዋ ውስጥ በመክተት እየተሳሳቁ ተያይዘው ወጡ…

እንዳአለውም ኢልሌ ሆቴል ጎራ አሉና እራታቸውን በልተው ሲወጡ ሶስት ሰዐት አልፎል…

‹‹አሁን ጭፈራ ቤት ለመሄደ ትክክለኛው ሰዓት ነው››አለ መድሀኔ…ፍንድቅድቅ ባለ ድምፅ፡፡
‹‹አዎ ግን እናንተ ብትሄዱ ይሻላል ..ከዚህ በላይ ካመሸው አከራዬቼ የውጭ በራፍ አይከፍቱልኝም…››አለች ጊፍቲ
‹‹እኛም አይከፍቱልንም››ሲል መለሰላት መድህኔ

‹‹አይ ቢሆንም እናንተ የራሳችሁ ማለቴ የወላጆቻችሁ ቤት ነው..ጨክነው አይጨክኑባችሁም እኔ ግን ኪራይ ቤት..››
ክንዷን ያዘችና ‹‹ነይ ባክሽ እስከአራት እስከ ከአምስት ሰዓት ዘና እንልና አዲሱ ቤታችን ሄደን ነው የምናድረው…አይደል መድህኔ?››

‹‹እ አዎ..ጥሩ ሀሳብ ነው….››አለ…..እሱም ያላሰበው አዲስ ሀሳብ ነው ያመጣችው፡፡
መኪና ውስጥ ገብተው መድሀኒ መንዳት ከጀመረ በኃላ…‹‹እንዴ አዲስ ቤት ተከራያችሁ እንዴ ?›› ስትል ጠየቀች

‹‹ አይ የእኔ ፍቅር አሪፍ ቤት ገዝቶ ሰርፕራይዝ አደረገኝ፣››አለችና መልስ ሰጠቻት፡፡ ለቤት ያላትን ፍቅር እሷም ሆነች ቃል ደጋግመው ነግረዋታል፡፡ለዛም ነው አይን አይኗን እያየች አድምቃ እያወራች ያለችው፡፡

‹‹ለእናንተ እኔ ደስ ብሎኛል አለች››የንግግሯ መዝረክረክ ግን ደስ እንዳላላት ያስታውቅባታል፡፡
‹‹ሰዎች የተለየ ሀሳብ አለኝ››ልዩ ነች ተናጋሪዋ፡፡

‹‹ምንድነው?››

‹‹ለምን የሚስፈልገውን መጠጥ ገዝተን ቀጥታ ወደቤታችን አንሄድም…..ግርግሩ ብቻ ነው የሚቀርብን …ሙዚቃው እንደሆነ እቤት አለ …እንቀውጠዋለን…››
መድህኔ ሁለቱንም እያፈራረቀ አያቸው…

‹‹ወይ በቃ ለካ ጊፍትዬ ጭፈራ ቤት ትወዳለች…››አለች ልዩ..አውቃነው እሷን ይሉኝታ ውስጥ ለመጨመር አስባ ይህቺን አረፍተ ነገር የሰነዘረችው፡፡

‹‹አረ በፍፅም.. አሪፍ እና የተለየ ሀሳብ ነው ያመጣሽው..እንደውም ጭፈራ ቤት አድሬ ነገ ጥዋት ተነስቼ ቢሮ መግባት ይከብደኛል.. እያልኩ እያሰብኩ ነው…››

መድህኔ ‹‹እንግዲያው ወደቤት ነዳሁት…››አለና አቅጣጫውን አስተካከለ…

ከሀያት ሪል እስቴት ወደተገዛው ግዙፍ ቪላ ነው የነዳው..መንገድ ላይ ቆሞ ሴቶቹን መኪና ውስጥ አስቀምጦ መአት አይነት መጠጦችንና የተወሰኑ የሚበሉ ነሮችን ገዝቶ ተመለሰ….እቤት ሲደርሱ አራት ሰዓት ተቃርቦ ነበር..የመኪናውን ጡሩንባ ቢያንጣጣም በቀላሉ ሊከፈት አልቻለም..ወርዶ በእጁ ጭምር መቀጥቀጥ የግድ ሆኖበት ነበር..ከዛ ዘበኛው በድንጋጤና በማለክለክ መጥቶ ከፈተና በተደናገጠ ደምፅ..‹‹ጋሺዬ ይመጣሉ ብዬ ስላላሰብኩ እንቅልፊቱ ጣለችኝ፣እንደው ይቅርታ››ተሽቆጠቆጠ፡፡

‹‹…ችግር የለውም…››ብሎ አረጋጋው…ኮፈኑን ከፈተና
‹‹ይህቺን እቃ ወደሳሎን ውሰድልኝ›› አለው…ዘበኛው በታዛዥነት አንከብክቦ ወደሳሎኑ ከነፈ…ጊፍቲ በግቢው ውበት ፈዛ ከግራ ወደቀኝ አይኗን እያስወነጨፈች ታያለች…የምታደርገውን እየተካታተለ እንዳልሆነ ሰው ችላ ብላ ክንዷን ያዘችና ወደቤት ይዛት ገባች…ከሳሎኑ ጀምራ እያንዳንዱን መኝታ ቤት…መታጠቢያ ቤቶችን… ኪችኑን አስጎበኘቻት….

‹‹እንግዲህ ልጅ እስኪመጣ ድረስ ለእኛ ይበቃናል?››አለቻት
‹‹ትቀልጂያለሽ አይደል?››
‹‹ምን እቀልዳለው..እኔና እናቴ ከሰራተኞቻችን ጋር የምንኖርበት ቤት እኮ የዚህን ሶስት እጥፍ ይሆናል…ከዛ ወጥቶ እዚህ መኖር..ብቻ ይሁን አሪፍ ነው››
‹‹እና ከሁለት ወር በኃላ ልትጋቡ ነዋ››ጠየቀቻት፡፡

‹‹አይ ከሁለት ወር በኃላ ምርቃቴ ስለሆነ ቀለበቴ ነው በደባልነት የሚደረገው ሰርጋችን ከሶስት ወር ነው….ምን ይታወቃል… አብረን አንሞሸር ይሆናል?››

‹‹አይ!! ብለሽ ነው?››አለቻት… ትክዝና ቅዝዝ ብላ….፡፡አዎ የፈለገችውም እንዲህ ውስጧን መበጣጠስና ተስፋ ማስቆረጥ ….ወይንም ማስጎምዠት ነበረ…‹.እርግጠኛ ነኝ ይሄኔ ስንቴ ምን አለ ይሄ ቤት የግሌ በሆነ ብላ ተመኝታለች..እንግዲህ ይሄን ቤት ከፈለገች..የቃልዬን እጅ ለቃ የመድህኔን እጅ መያዝ አለባት ማለት ነው…ያንን እንደምታደርግ ደግሞ ከዛሬ ጀምሮ ምልክት ልትሰጠኝ ይገባል….ጊዜ የለንም፡፡››ስትል እሷን ከጎኗ አቁማ በውስጧ አብሰለሰለች፡፡

ጉብኝታቸውን ጨርሰው ወደሳሎን ሲመለስ መድህኔ ጠረጳዛውን በመጠጥና በሚበሉ ቀለል ባሉ ምግቦች ሞልቶት ግዙፍ እስፒከር ያለውን ቴፕ አዘጋጅቶ ጠበቃቸው…
‹‹የእኔ ፍቅር ምርጥ እኮ ነህ›› ብላ ተንጠልጥላበት ጉንጩን ሳመችው፡፡ ‹‹መቼስ ዛሬ ከወትሮ በተለየ ሁኔታ ቁልትልት ብዬበታለሁ……››ስትል እራሷን ታዘበች
ጊፍቲ ሶፋ ላይ ቁጭ አለች……

‹‹ምን ልቅዳለችሁ?›› መድሀኔ ጠየቀ፡፡

‹‹ወይን ቢሆን ደስ ይለኛል…››መረጠች ጊፍቲ፡፡…
‹‹አዎ ከቀላል እንጀምር ለእኔም ወይን››ልዩም ከጊፍቲ ምርጫ ጋር ምርጫዋን አስማማች፡፡
እንግዲያው ቆንጆ የፈረንሳይ ወይን አለኝ….አለና ከተኮለኮሉት ጠርሙሶች መካከል አንዱን መዞ በእያንዳንዳቸው ብርጭቆ ቀዳላቸው …እና የራሱንም ይዞ ከፊት ለፊታቸው ቁጭ አለ፡፡
መጠጡ በወይን ቢጀመርም..ወደውስኪ ሲሸጋገር አንድ ሰዓት አልፈጀበትም። ስድስት ሰዓት ላይ ተኪላ ነበር ሻት እየተደረገ የነበረው ...ዳንስ ..ጭፈራው ቅውጥ ያለ ነበር፡፡ ልዩም ዛሬ እንደው የእነሱን ያህል ችሎታው እንደሌላት ብታወቅም ቁብ ሳይሰጠት ከእነሱ እኩል ስትቀውጠው አመሸች...ልዪነቱ መጠጡ ላይ እየጠጣች በማስመሰል ስትደፍው ..አንዳንዴ ወደእነሱ ስትገለብጥ በተቻለኝ መጠን የሰከረች በመምሰል ግን ሳትሰክር እራሷን ለማቆየት የተቻላትን ጣረች..እናም ተሳክቶላት ሰባት ሰዓት ሲሆን ሁለቱም በዳንስ ብዛት ውልቅልቅ ብለው በላብ ወርዝተው ከላይ የለበሱትን እያወለቁ ጥለው እሱ በነጭ ፓክ አውት እሷ ደግሞ በጥቁር ጡት ማስያዣ ነበሩ...ልዩም ያው እነሱን ለማበረታት በጡት መያዠ ብቻ ቀርታለች...በዳንሱ ሞቅታ መካከል ሁለቱንም አቅፍቸውና አንድላይ አጣብቃ ወዳራሷ ትጨምቃቸዋለች…እንደዛ ሲሆን እርስ በርስ አንዲፍተጉ እያደረገች ቅርበታቸውን እያጠናከረች ነው፡፡..አንዳንዴ ሞቅ ብሏቸው የጋለ የእርስ በርስ
#ተአምራተ_ኬድሮን


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///

ከሶስት አመት በኃላ..
እናትዬውን አሳምና ከደሎ ለቃ ስትወጣ  አንድ ሻንጣ ልብሷን ይዛ በትራንስፖርት ሳይሆን በንስሯ አማካይነት እየበረረች ነበር የተጓዘችው..በእጇ እናቷ ያስጨበጠቻትን 2000 ሺ ብር እና አጎቷ የሰጣትን 5 ሺ ብር .. በቃ ይሄንን ነው የያዘችው፡፡ግን ሻንጣዋ ውስጥ ከአመታት በፊት ኪኒማጀሮን ለመጓብኘት በሄደች ጊዜ ንስሯ ከባህር ወንበዴዎች ነጥቆ የሰጣት ዳይመንድ እንደቀልድ እንዳስቀመጠችው ስለነበረ ይዛው ነበር.። አዲስ አበባ እንደገቡ በደላላ 45 ሚሊዬን ብር ተሸጠ.
በ25 ሚሊዬን ብር  ለገጣፎ ከተማ አካባቢ ምታርፍበት የራሷ የሆነ  2ሺ ካ.ሬ ሜትር  ግቢ ላይ ጥጉን ይዞ የታነፀ ባለአምስት ክፍል   ቢላ ቤት  ገዝታ ከንስሯ ጋር የብቸኝነት ኑሮ መኖር ጀመረች፡፡
እንደመጣች ሰሞን ብቸኝነቱ በጣም ከብዷት ነበር.. የምታውቀው ሰው በዙያዋ ካለመኖሩም በተጨማሪ ከደንና ጫካ ውስጥ ወጥቶ በፎቅና በመኪና የታጠረ አካባቢ መኖር በጣም ሚረብሽ ሆኖባት ነበር…ቆይቶ ግን እየለመደችው መጣች፡የገዛችውንም ጊቢ እንደምትፈልገው አደረገችው….እነሆ አሁን ከሶስት አመት በኃላ ከቤቱ ይልቅ በግቢ ውስጥ ያሉ ዛፎች ዕጻዋቶች እና ፍራፍሬዎች ይበልጥ ያስደምማሉ፡፡ በግቢዋ ውስጥ ከ1140 በላይ የዕፅዋት አይነቶች ይገኛሉ፡፡ከነዚህ ውስጥ 83ቱን ከተለያዩ አህጉራት በዞረችባቸው ወቅት ቀልቧን ስበውት ወይም አስደምመዋት አምጥታ የተከለቻቸው ናቸው፡፡እርግጥ  አምጥታ የተከለቻቸው ከዚህ አሁን ከተጠቀሰው ቁጥር በሶስት እጥፍ ከፍ ያለ ነበር..ከአዲስ አበባ የአየር ፀባይ ጋር ተላምደው  መጽደቅ የቻሉት ግን እነዚህ ብቻ ናቸው፡፡
ግቢዋ ውስጥ ያሉ ዕጽዋቶች ሁሉ አስደማሚነታቸው ለአይን መስብ ከመሆናቸው እና ንጽህ አየር ሚያመርቱ መንፈሳዊ ማሽኖች ስለሆኑ ብቻ አይደለም እዚህ ግቢ የመትከል ተተክሎም የመብቀል እድል ያገኙት…እያንዳንዱ የተለየ ሚስጥር እና ጥበብ የሚገለጽባቸው የእግዚያብሄርን  ሚስጥራዊ ሹክሹክታ በቅጠሎቻቸው እና በስሮቻቸው ነስለሚተነፍሱ ነው…::መድሀኒት ናቸው… ታአምራትን የሚሰራባቸው ናቸው..ብዙ ብዙ ነገር…በየዛፎች ቅርንጫፍች ላይ ቁጥራቸውን የማይታወቅ የወፍ ጎጆዎች ሞልተውባቸዋል፤ሶስት ጉሬዛ እና አራት ዝንጀሮዎችም አሏት ..ሁሉንም ያመጣቻው ከሀገሯ ጫካ ነው… ከደሎ መና፡፡እንደዛ ያደረገችው..ልጅነቷን ስለሚያስታውሷት ነው.እንደዛ ያደረገችው..አብራቸው እነሱን እያየች ከእነሱ እየተጫወተች ስላደገች ዘመዷቾ ስለሚመስሏት ነው… ስለምትወዳቸውና ከእነሱ ውጭ ህይወት ስለማይታያት ነው.. ስለምትወዳቸውና የሚወዷትም ስለሚመስላት ነው፡፡
አብረዋት የሚኖሩ አንድ የስልሳ ሁለት አመት አዛውንት ሰውዬ አሉ፡፡ጋሽ ተክለወልድ ይማም ይባላሉ፡፡ይሄንን ጊቢ እንዲህ ያሳመረችውም የምታስተዳድረውም ከእሳቸው ጋር ነው፡፡

እሷ ያው አብዝታ ከአንድ የምድር ጫፍ ወደሌላው መስፈንጠር የዘወትር ድርጊቷ ስለሆነ በሌለችበት ጊዜ እሳቸው ናቸው ሙሉ ሀላፊነቱን የሚወስዱላት፡፡ ዘበኛ  ወይም አትክልተኛ አይደሉም፡፡ከዕጽዋቶች ጋር በፍቅር የወደቁ ከሀለማያ ዩኒቨርሲቲ ለ32 ዓመት ያስተማሩና በቅርቡ ጡረታ የወጡ የዕጽዋት ሳይንስ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ናቸው፡፡

ሌላው  በዋናነት ለብቸኝነቷ መድሀኒት የሆናት  ንስሯ ነው ፡፡ የንስሯ እና የእሷ ግንኙነት ለሌላ ሰው ለማስረዳት ቀላል መንገድ የለም፡፡ እያንዳንዱ የሰው ልጅ እንዲጠብቀው እንዲንከባከበው እና ከክፉ ነገር እንዲከልለው ከፈጣሪው የተመደበለት ጠባቂ መልዐክ አለው ተብሎ በአብዛኛው ሰው ይታመናል፡፡ግን እነዚህ ጠባቂ መላዕክቶች አካል አልባ መንፈስ ናቸው ፡፡አይታዩም፤መታየት ብቻ ሳይሆን አብዛኛው ሰውም ጠባቂ መልአኩን በትከሻው ላይ ተሸክሞ እንደሚዞር አያውቅም… አያምንምም፡፡ስለዚህ አይገለገልባቸውም …አያዳምጣቸውም፡፡ሰው በጨለማ ውስጥ ሲጓዝ ማጅራት መቺ ከኃላው ካለ ምንም አይነት እንቅስቃሴ ሳይሰማ ትከሻዬን ከበደኝ ይላል፤ያ ምን  ማለት ነው? ለሚያምንበት ሰው ጠባቂ መላዕክ የማስጠንቂያ ደውል ነው…. እሱ ያልተመለከተውን በጭለማ ውስጥ የተሸሸገውን  አጥቂውን ጠባቂ መልአኩ አይቶት ሹክ ብሎታል ማለት ነው፡፡እንግዲህ ያ ሰው ብልህ ከሆነ ማድረግ ያለበት መልዕክቱን አምኖ ተፈትልኮ በመሮጥ ማምለጥ ወይም ጥቃቱን ለመመከት እራሱን ማዘጋጀት ነው፡፡አይ ዝም ብሎ ተራ ፍራቻ ነው ብሎ የደረሰውን መልዕክት ችላ ብሎ በእንዝላልነቱ ከገፋበት ግን ማጃራቱን  ተመቶ  ይዘረራልም..ይዘረፋልም ማለት ሊሆን ይችላል፡፡

እና ለእሷ ይሄ ንስር አሞራ ጠባቂ መላዕኳ በሉት፡፡በአካል አብሯት የሚንቀሳቀስ የሚያወራት የምታወራው ጠባቂ መልአክ ስላለት፡፡የፈለገችበት የአለም ጥግ አንጠልጥሎ የሚወስዳት...ከሚንቀለቀል እቶን እሳት ውስጥ ብትገባ እንኳን አንጠልጥሎ በማውጣት ሀይቅ ውስጥ ጨምሮ የሚያቀዘቅዘት፡፡ካለሀሪ በረሀ ላይ ወስዶ በጥም ጉሮሮዋ ከደረቀ  ከመንቁሩ ወይን አመንጭቶ የሚያጠጣት…..ከፈለገች የሲ.አይ .ኤን የስለላ መረብ በጣጥሶ የዋይት ሀውስ ራት ግብዝ ላይ አስገብቶ የሚጥላት፡፡ሱፐር ሂዩማን እንድትሆን ሱፐር ሆኖ ሱፐር የሚያደርጋት መልዐኳ ነው፡፡የማታውቀው አባቷ ስጦታ፡ከሀገሯ አብሮት የተሰደ የደስታዋም ሆነ የሀዘኗ ጊዜ ተጋሪዋ፡፡

በንስራ አካል ውስጥ ባለው የነቃና የበቃ  ነፍስ እገዛ እሱ  ያየውን አንደምታይ እና ያሰበውን እንዳምታስብ ታውቃለች፡፡ልክ በአንድ ዲኮደር እንደሚሰራ ሁለት ቴሌቪዝን በሉን….እሷ ቤቷ ቁጭ ብላ እሱ አየሩን ሰንጥቆ  በሚበርበት የምድር ጥግ ሁሉ እያየ ያለውን ነገር ጥርት ባለ ምስል በአዕምሮዋ ታያለች…የንስርን አይን ደግሞ የሚታውቅ ነው..እያንዳንዱ ንስር  ቅንጣት በቀላሉ በአይኑ ሌንስ ይቀልባታል፡፡ይሄ ገለጻ ለብዙዎችን ግራ ሊያጋባ ይችላል፡፡
ይሄ መልአክ ነው ሰይጣን የሚል ጥያቄ ሊያስነሳ ይችላል፡፡መልአክ ከሆነ ለምን በእርግብ አካል ውስጥ አላደረም ወይንም እንደተለመደው  ለምን የበግ ስጋና ቆዳ አለበሰም፡፡እሱን የሚያውቀው ይሄ እንዲሆን ያደረገው የማታውቀውና የሌላ አለም ፍጡር የሆነው አባቷ ነው፡፡ለእሷ ግን  ምንም ግድም አይሰጣትም፡፡ዋናው በእርግጠኝነት የምታውቀው ነገር የእሷ እኔነት እና የንስሩ ነፍስ የተሳሰረ መሆኑን ነው፡፡ የኖረውን ያህል ኖራ በሚሞትበት ቀን የምትሞት እንደሆነም ይሰማታል፡፡ወይንም የእሱ ነፍስ ከንስር አካሉ ውስጥ ተንጠፍጥበፎ በሚወጣበት ቅጽበት የእሷም ነፍስ ከዚህ የሰው ሰውነት ወይም አካል ውስጥ ተንጠፍጥፎ በመውጣት ከእሱ ነፍስ ጋር በመተቃቀፍ ወደሚሄድበት ሚስጥራዊ ቦታ አብሮት እንደሚነጉድ ታውቃለች… የመዳረሻቸው ፍጻሜም  የአምላክ እቅፍ ይሆን የሉሲፈር ጓዲያ  ምንም የምታውቀው ነገር የለም ፡፡
አሁን ባሉበት ቦታ ሁለቱምን  ደስተኞች ናቸው ፡፡በዚህች ምድር ሚስጥር እየተደመሙበት ነው፡፡

ይቀጥላል
#ትንግርት


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


ሁሴን ወደ ሲዊዘርላንድ ሊበር ከ3ዐ ሰዓት ያነሰ ጊዜ ቢቀረውም ከመሄዱ በፊት የውብዳርን እና ልጆቹን መሰናበት ስለፈለገ ወደ እነሱ እየሄደ ነው፡፡ ትናንትና የሽኝት ዝግጅቱ ላይ ልጆቹን ይዛ እንድትገኝ በስልክ ደውሎ ነግሯት ነበር፤እሷም እንደምትገኝ ቃሏን ስጥታው ነበር፤ነገር ግን አልተገኘችም፡፡ ያው ከድሮ ባሏ እና ከጣውንቷ ጋር ፊት ለፊት ተገናኝቶ መፍጠጥ ደብሯት እንደሆነ ስለገባው ባለመምጣቷ ብዙም ቅር አላለውም፡፡

እንደውም በተቀራኒው ከስልክ ግንኙነት ውጭ በአካል ሳያገኛት አራት ወራቶች በማሳለፉ ፀፀት ነገር ሽው ብሎበታል፡፡
ዛሬም እንደሚመጣ ሲደውልላት ቀዝቀዝ ባለ ስሜት ነበር ‹‹..በቃ ና... ቤት ነኝ፡፡››ያለችው፡፡

ደርሶ የመኪናውን ክላክስ ሲያስጮህ ዘበኛው የውጪን በራፍ ከፈተለት፡፡ መኪናውን ወደ ግቢ ውስጥ አስገባና ምቹ ቦታ ፈልጐ በማቆም ሞተሩን አጥፍቶ ወደ ውስጥ ገባ፡፡የውብዳር ሳሎን ብቻዋን ቁጭ ብላ ነበር፡፡

ሲያያት ደነገጠ.፡፡ጉስቁልቁል ብላለች፡፡የሆነ ጭምድድ ያለ ቢጃማ ቀሚስ ለብሳለች፣የፀጉሯ መንጨፍረር በየጫካው በመሽሎክሎክ ለዓመታት የተንከራተተ ያልተሳካለት አርበኛ አስመስሏታል፡፡ወደ ውበት ሳሎን ጎራ ካለች ወራቶች እንዳለፏት ለሰከንድ ብቻ ሁኔታዋን በማየት ማወቅ ይቻላል ፤ በሜካፕ ያሸበርቅ የነበረው ፊቷ ወይቧል፡፡

በአንድ እጁ አቅፎ ጉንጮቾን እየሳመ‹‹ሃይ.. የውብ ሰላም ነሽ?››አላት ::

‹‹አለው..ይመስገነው…ተቀመጥ፡፡››

ከጎኗ ተቀመጠ::

‹‹እሺ...ትንግርት ሰላም ነች?››

‹‹ሰላም ነች::››

‹‹ስራዎቿን አልፎ አልፎ ጋዜጣችሁ ላይ አነባለሁ፤እንዴት ነው አላረገዘችም እንዴ?››

‹‹አላረገዘችም፡፡››

‹‹አይ ይደርሳል፤ውጭ ትቆያለህ እንዴ?››

‹‹አዎ ትንሽ ስለምቆይ እኮ ነው ሳልሰናበትሽ መሄድ ያልፈለኩት::››

‹‹አይ ጥሩ አደረግክ ፡፡››አለችው በበረደ ስሜት::

ሁኔታዎን ሲያይ ምኗም አላማረው‹‹የውብ .ጤናሽን ሰላም ነሽ ግን?››

‹‹እኔ እንጃ ባክህ..አዎ ሰላም ነኝ መሰለኝ፡፡››ያለችበት ሁኔታ ለራሷም የተምታታባት እንደሆነ በቀላሉ ተረዳ::

‹‹እንዴት እንዴት ነው...?ችግር ካለ ንገሪኝ?››

‹‹ችግር ካለ አልክ..!!!ምን ብነግርህ ምን ይገባሀል?የቱንስ ነግሬህ የቱን እተወዋለው?

እቤቱ በሙሉ ችግር በችግር ሆኗል፡፡ ሲያመጣው ደራርቦ አይደል..?››

ሁሴን ገና እንደገባ ነበር የውብዳር ጥሩ ሁኔታ ላይ እንዳልሆነች ያወቀው <<የውብ ግዴለሽም በቅደም ተከተል ዋና ዋናውን ንገሪኝ::››

‹‹እሱማ ውሎ ያሳድረናል፤ያ ደግሞ ከመንገድህ ቀረህ ማለት ነው፡፡››

‹‹አትቀልጂ ..መስማት እፈልጋለው፡፡ ንገሪኝ፡፡››

‹‹አይ ጓደኛዬ... እኔና ቀልድ ከተቆራረጥን እኮ ሰነባበትን፡፡››እንባዋ ከቁጥጥሯ ውጭ በሆነ ኃይል እስገዳጅነት ዝርግፍ አለ፡፡ሁሴን ተረበሸ፡፡የውብ ዳር እንዲህ ስትሆን አይቶ አያውቅም፡፡

እንደምንም ተረጋጋችና መናገር ጀመረች‹‹በቃ ኑሮ ሁሉ ዝብርቅርቅ ብሎብኛል፡፡ሰው ያልሰራውን ምን አይነት ክፉ ሀጥያት እንደሰራው አላውቅም?››

‹‹የምን ሀጥያት ነው፡፡እንደማንኛውም ሰው የሆነ ስህተት ሰራሽ አከተመ ፡፡እራስሽንማ በትናንት ስህተት ላይ አጣብቀሽ አትጨናነቂ፡፡ ህይወት ትቀጥላለች፡፡ ሁሉን ነገር እንደ አዲስ ጀምሪ፡፡››

‹‹እንደምትለው ቀላል አይደለም፡፡ጓደኛህ ከወንድ ጋር ስትቀብጥ አየኋት ብሎ ቤቱን ጥሎ ከወጣ በኃላ ሁሉ ነገር ብልሽትሽት
ብሎብኛል፡፡ይገርምሀል ከልጁ ጋር ፍቅር ስጀምር ተሳስቼ አልነበረም፤አውቄና አቅጄበት ነበር፡፡እሱ እኔን አሰልሎ መረጃ ከማግኘቱ
በፊት እኔ ቢያንስ ከአምስት ሴቶች በላይ ጋር ሲማግጥ በተለያየ ጊዜ ማረጋገጥ ችዬ ነበር፡፡

በወቅቱ እሱ እንዳደረገው
አላደረግኩም፡፡.ፍቅራችን ቢያበቃለትም ትዳራችን እንዲፈረካከስ ስላልፈለኩ ዝም ነበር ያልኩት፡፡እንዲህ አድርገሀል እንኳን ብዬ
ጠይቄው አላውቅም ፣ምክንያቱም እንዲበረግግ ስልፈለኩም፡፡ግን ደግሞ ሰው ነኝ ፤በምግብ ብቻ አልኖርም፡፡ስለዚህ እሱ
ሚያደርገውን በጥቂቱ ለማድረግ ተንቀሳቀስኩ፡፡ቀልቤ ያረፈበትን አንድ ሰው አፈቀርኩ፡፡ያንን ፍቅር እሱ ሲደርስበት ሁለት ወር እንኳን አላጣጠምኩትም ነበር፡፡በቃ ይሄው ነው የእኔ ሀጥያት፡፡››

‹‹በግልፅ ልጠይቅሽ፡፡ቆይ እንዳልሽው መሆን የሌለበት ሆኖ ከሰሎሞን ጋር ከተፋታችሁ በኃላ ከዛ ከልጁ ጋር እንደቀጠልሽ እርግጠኛ ነኝ፡፡››

አቋረጠችው <<አንድ ሳምንት እንኳን አብሮኝ ሊዘልቅ አልደፈረም፡፡ባልሽ ሀብታም ስለሆነ ገዳይ የሚገዛበት በቂ ብር አለው፤ቢያስገድለኝስ›› ብሎ ጥሎኝ ጠፋ፡፡

‹‹ይገርማል››አለ ሁሴን የሚለው ጠፍቶት‹‹... ግን ሰሎሞን አስፈራርቶት ነበር እንዴ?››

‹‹አይመስለኝም ..ግን አንድ ሁለት ቀን መንገድ ላይ ሲገናኙ ገለማምጦታል መሰለኝ፤ለማንኛውም ትዳሬንም ፍቅሬንም ተነጠቅኩ፡፡ይሄስ ይሁን
እቋቋመዋለው፤የልጆቼን ጥያቄ እና ጭቅጭቅ ግን እንዴት ልቻለው?››

<<ማለት?>>

ለጠየቃት ጥያቄ መልስ ከመስጠቷ በፊት ሰራተኛዋ ከልጆቹ መኝታ ቤት ወጥታ ወደ እነሱ ቀረበችና‹‹ እትዬ ተነስተዋል፡፡››አለቻት፡፡

‹‹ተነሱ?›› አለችና ከመቀመጫዋ በርግጋ ተነሳች፡፡

‹‹ምነው..?ችግር አለ እንዴ?

‹‹ልጆቹ ትንሽ አሟቸዋል›› ብላ ወደ መኝታ ቤቱ በፍጥነት መራመድ ጀመረች፡፡ ተከተላት፡፡

መኝታ ቤት እንደገቡ ሁለቱም መንታዎች አንድ አልጋ ላይ ጎን ለጎን ተኝተዋል..‹‹ምን ሆነው ነው?››በድጋሚ ጠየቀ ሁሴን ፡፡

‹‹ባክህ ማታ ነው የጀመራቸው፡፡በጣም ያተኩሳሉ፡፡ጥዋት ሀኪም ቤት ወስጄያቸው
ነበር ፤መድሀኒት ተሰጥቶቸዋል፡፡እኔ እኮ ግራ ገባኝ..… እሱ ከዚህ ቤት ከወጣ በኃላ ቢያንስ በሳምንት ሶስት ቀን ይታመማሉ››ዳግመኛ እንባዎን ዘረገፈች ፡፡ሁሴን ወደ ልጆቹ ተጠጋና እጆቹን ጭንቅላታቸው ላይ ጭኖ ሙቀታቸውን ተመለከተ፡፡ያተኩሳሉ፡፡ጠይም ፊታቸው ቸፍ ብሎ በላብ ተጠምቋል፡፡

አንደኛዋን‹‹ዕፀ‐ህይወት ምንሽን ነው የሚያምሽ ?›› ብሎ ጠየቃት፡፡

እጇን ወደ ጭንቅላቷ በመጠቆም አሳየችው፡፡

‹‹አንቺስ ምንሽን ነው የሚያምሽ?››ሌለኛውን ጠየቃት፡፡

ግራ ገባው‹‹የሚያምሽን ቦታ እኮ ነው የጠየቅኩሽ ?እንደ ዕፀ‐ህይወት እራስሽን ነው ያመመሽ?››ጥያቄው ያልገባት መስሎት አብራራላት፡፡

‹‹አይደለም፡፡አባቴን ነው የሚያመኝ፡፡አባቴን እፈልጋለሁ››አለችው፡፡ በድንጋጤ ልቡ ቀጥ ልትል ትንሽ ነበር የቀራት ፡፡አይኖቹን ወደ የውብዳር አሽከረከረ፡፡በፀጥታ እያለቀሰች ነው፡፡

‹‹ዕፀ-ህይወትም መናገር ጀመረች‹‹እኔም አባቴን ነው የሚያመኝ›› በማለት የቀድሞ መልሷን አስተካከለች፡፡

‹‹የውብ አንዴ ላናግርሽ?›› ብሎ ይዞት ወጣ፡፡

<<ምነው?>>

‹‹እንቢ እንዳትይኝ...ይዤያቸው ልውጣና ትንሽ ላዝናናቸው፡፡እርግጠኛ ነኝ ይሻላቸዋል፡፡›› አላት፡፡

እንደማሰብ አለችና ‹‹እንዳልክ፤ልብስ ልቀይርላቸው ፡፡››ብላ ተመለሰች፡፡

ከአስር ደቂቃ በኋላ ሰባት አመት ዕድሜ ያላቸውን መንትዬቹን ይዟቸው ከግቢ ወጣ፡፡

ወደ ኤድናሞል ጉዞ ጀመረ፡፡

መንገድ ላይ ሞባይሉን አወጣና ሰሎሞን ጋር ደወለ‹‹እሺ ሰላም ነህ?››

‹‹ምንም ሰላም አይደለሁ..በአስቸኳይ ኤድናሞል ና፡፡››

‹‹ምነው? ችግር አለ እንዴ?››

‹‹ስትመጣ ነግርሀለው…ከአስራ አምስት ደቂቃ
በኃላ እዛ እንገናኝ፡፡››ብሎት ስልኩን ዘጋና መኪናውን በትኩረት ማሽከርከር ጀመረ፡፡
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


በማግስቱ ከእንቅልፏ ተነሳችና ቁርሷን በልታ አራት ሰዓት አካባቢ ከቤቷ ወጣች፡፡ የመፅሀፍን ረቂቅ ለማተሚያ ቤት አስረክባ..ቀብድ ሰጥታ ወደስራ ቦታ ሄደች፡፡ እረፍቷ ያለቀው ትናንት ነበር፡፡ዛሬ ስራ መጀመር ነበረባት፡፡ግን ፈፅሞ  ስራ የመጀመር ሞራልም ፍላጎትም የላትም፡፡
ቀጥታ ‹‹ቤርሙዳ ማሳጅ ቤት››ሄደች፡፡ትብለጥ እቤቷ  ሰለነበረች  አገኘቻት… ሳላምታ ተቀያየሩና ሳሎን ሶፋ ላይ ጎን ለጎን ተቀመጡ..

ሳባ በፊት መፅሀፉ ታትሞ አልቆ  ስራ  ቦታውንም  ሆነ  አሁን  ከጎኗ የተቀመጠችውን ሀለቃዋን እስከወዲያኛው አውድማ እስክትገላገል ድረስ እንደምንም ጨክና ለመቀጠል እቅድ  ነበራት፡፡ቢያንስ  ለሚቀጥለው  አንድ ወር…ግን አልቻለችም፡፡አስር አመት ያለማቋረጥና ያለመታከት የሰራችውን ስራ ከመናጢ ድህነት ተነስታ ሚሊዬነር የሆነችበትን ስራ፤  ለቀጣዩ  አንድ  ወር ለመስራት ገና ስታስበው ዘገነናት..
‹‹ሳቢ ግን ሰላም ነሽ?››
‹‹አዎ… ምንም  አልል…››
‹‹ህክምናው እንዴት ነው?››
‹‹ጥሩ ሀኪም አግኝቼያለሁ .መዳሀኒትም እየወሰድኩ ነው…ግን ለውጡ አዝጋሚ ነው፡፡››
‹‹ይሁን ዋናው ለውጥ መኖሩ ነው፡፡››አለቻት ትብለጥ፡፡
‹‹አዎ ግን ስራ መቀጠል የምችል መስሎ አልተሰማኝም..እንደው ስራውን ከምጎዳ ብለቅ ብዬ አስቤ ነበር› ›
‹‹ብለቅ ስተይ.?ሙሉ በሙሉ ለማለት ነው?››ከጠበቀችው በላይ ደነገጠች፡፡
ሳባ ደግሞ የትብለጥ በተጋነነ ስሜት መደንገጧን ስትመለከት በውስጧ የነበረውን ንዴት ይበልጥ እንዲቀሰቀስባት አደረጋት…
ይህቺ ሴትዬ በእሷ ትከሻ ላይ ተንጠላጥላ ብዙ  መቶ  ሚሊዬን  ብሮችን  ወደ ካዝናዋ አጭቃለች…ስራዋ ሁሉ የማፍያ ነው፡፡ብር የምታገኝበት መንገድ በጣም ይገርማታል…ለምሳሌ ማሳጅ አገልግሎት በማግኘት አንድ የመዘጋጃ ቤት ወሳኝ ባስልጣን እሷ ጋር ይመጣል…እሷ ያንን ደንበኛ አሳልፋ ለሳባ ትሰጣታለች….ሳባ
ከማሳጅ ጀምራ ነፍሱ ሩሆን እስክትስት ድረስ ፍላጎቱንና አመሉን  መሰረት በማድረግ ፈንጠዝያ ወስጥ እንዲገባና እንዲደሰት ታደርገዋለች.፡፡ከዛ ያ ባለስልጣን ላገኘው አገልግሎት ለሳባ ሀያ ወይ  ሰላሳ  ሺ  ብር  ይሰጣጥና  ለትብለጥ የአገልግሎት አራት ወይም አምስት ሺብር ከፍሎ አመስግኖ ይሄዳል…ወይዘሪት ትብለጥ ታዲያ ደንበኛዋን አሳዳ ፕሮፖዛሏን በእጇ ይዛ ሀገር አማን ነው ብሎ በተቀመጠበት ቢሮ ተከስታ ታስደምመዋለች..ከዛ በሁለት በሶስት ወር 5መቶ ካሬ መሬት ተቀብላ ካርታውን በስሟ ታሰራና መሬቷን በእጇ ካርታውን በካዝናዋ በማስቀመጥ ወጥመዷን አስተካክላ  ሌላ ታዳኝ ትጠብቃለች…ከሆነ ወር ቆይታ በኃላ ደግሞ አንድ የግሙሩክ ወሳኝ ባለስልጣን  የወሬ  ወሬ  ሰምቶ ይመጣል…ከእሱ ምን መጠቀም እንደምትችል ታጠናለች …ከዛ ተመሳሳዩን ታደርጋለች..
እና ባለፉት አስር አመት ውስጥ በእዚህች ሴትዬ ማሳጅ ቤት ወስጥ ብዙ ብዙ ስራ ሰርታ ከ30 ሚሊዬን በላይ ንብረት ብታፈራም..ሴትየዋ  ግን  በእሷ  ትከሻ ከ200 ሚሊዬን ብር በላይ ዘርፋለች….ይህንን ሳባ በደንብ ታውቃለች.ሳባ ማወቆን ግን ትብለጥ አታውቅም..
‹‹ሳቢ ከጤናሽ ሚበልጥ ነገር የለም….ታውቂያለሽ በጣም ብዙ ማሳጅ ሰራተኛች ነበሩኝ ..አሁንም አሉኝ…ባንቺ ልክ ግን የተሳካለትም እኔም የወድኩት ሰው የለም፡፡አንቺ ለእኔ ልክ እንደልጄ  ነሽ..ያለፉትን  አንድ  ወር  ከስራ  በመቅረትሽ እንኳን የደንበኞችሽን ጭቅጭቅ እረፍት ነው የነሳኝ…››

ሳባ የሆዷን በሆዶ ይዛ ቅጥል እያለች‹‹አውቃለሁ…ግን ጤና ከሌለ ሁሉም ነገር የለም…ምን ማድረግ እችላለሁ?›ስትል መለሰችላት፡፡ስራ በጀመረች በሶስተኛው አመት ማለትም የዛሬ ሰባት አመት ከዚህች ሀለቃዋ ጋር ክፉኛ ተደማምተዋል
….የጥላቸው ምክንያት አንድ ደንበኛቸው ነው፡፡ደንበኛው በወቅቱ ሳባ ጋር ከአንድ አመት በላይ የተመላለሰ በጣም ጨዋና ደግ፤ ግን ደግሞ የናጠጠ ሀብታም ሰው ነበር…. ታዲያ ያንን ሰው በቆይታ ከሳባ ጋር በጣም  እየተቀራረብ  ሲመጡ ሚስጥሩን ሁሉ ይዘረጋፍላት ነበር፡፡ከዛ እነትብለጥ ያንን መረጃ በሚስጥር ከተደበቀው ካሜራ የተቀረፀ ፊልም በማየት የሰውዬውን በአንድ ወቅት በስህተት የሰው ነፍስ በእጁ እንዳለፈ የተናዘዘላትን ወንጀል አብራቸው በምትሰራቸው ማፍያዎቾ  በኩል  በጥልቀት  ታስጠናና  መረጃዎችን  በመሰብሰብ  የደረሱበትን ሁሉ በአድራሻው እንዲደርሰው አድርገው ይደራደሩታል….ከዛ ሰውዬውም ምርጫ አጥቶ እስከ 50 ሚሊዬን የሚደርስ ብር ሊቀባበሉት ሁሉን ነገር ከጨረሱ በኃላ ይሄንን ስራ ከጀርባ ሆኖ ማን እንደሚያስኬደው   ሰገን  ከተባለች ረዳቷ ጋር ሲማከሩ ትሰማለች.. ከዛ  ደግማ  እንኳን  አላሰበችበትም….ሚስጥሩን ለሰውዬው ደውላ ትነግረዋለች ….ሰውዬውም ቀጥታ ትብለጥ ጋር ይደውላል››
‹‹50 ሚሊዬኑን ቀጥታ ለውሾችሽ ልስጣቸው ወይስ  ለአንቺ ላምጣልሽ››
‹‹የምን 50 ሚሊዬን?››
‹‹መደባበቁ ምንም አይረባንም….እጅሽ ላይ ያለውን መረጃ አሁኑኑ ሰብስበሽ ብታቃጥዬው ይሻልሻል…ስለእኔ አንድ  ነጠላ  መረጃ  ፖሊስ  እጅ  ከገባ  እኔም ያንቺን ቢዝነስ ሙሉ በሙሉ አወድመዋለው….ማሳጅ ቤትሽ የሽርሙጥና ቤት እንደሆነ…ሀሺስ እንደምትነግጂ…ግብረሰዶም ሳይቀር በቤትሽ  እንዲከወን እያደረግሽ ከፍተኛ ቢዝነስ እንደምትሰሪ…በቂ መረጃ እና  ምስክር  አለኝ፡፡››ብሎ ኩም  ያደርጋትና  ፅፎ  የፈረመውን  ቼክ  ቀዳዶ  ይልክላታል…ከዛ  ተረጋግቶ ስራውን ይቀጥላል፡፡…ለዚህ ውለታዋ ለሳባ  አንድ  ሚሊዬን  ብር  ባንክ  ደብተሯ ላይ አስገብቶ ያመሰግናታል ..ቋሚ ወዳጀዋም ይሆናል…እነ ትብለጥ ግን ለወራት የደከሙለት ስራ ካለቀ እና ፍሬ ለማፍራት ጫፍ ላይ ከደረሰ በኃላ በመጨረሻው ደቂቃ እንዴት እንደከሸፈ ምርመራ ያካሂዳሉ፣ ከብዙ ልፋት በኃላ እንደዛ የሰራችው ታማኞና ተወዳጇ ሳባ መሆኖን ይደርሱበታል፡፡ከዛ ትብልጥ ግራ ይገባታል…እንዳወቀች ልታስገድላት ነበር ያሰበችው…፡፡ግን የራሷን ገቢ እንዲነጥፍ ማድረግ መሆኑ ትዝ ሲላት ተረጋጋት ለማሰብ ሞከረች…ዝም  ብላ  አውቆ እንዳላወቀ በማስመሰል በምህረት ልታልፋት..በቀጣይ ግን እሷን በተመለከተ ጥንቃቄ ለማድረግ ወሰነች…ይሄም አላሳቻላትም ወዲያው ሰረዘችው…ውስጧ የነበረው ንዴት ያለቅጣት እንድትታለፍ ማድረግ  አላስቻላትም...ከዛ  ሙሉ ስልጣኑን ለሰገን ሰጠቻት…‹‹ሳትገድያት፤በእሷ ላይም ቀጥተኛ የአካል ጥቃት ሳታሳርፊባት..ግን ደግሞ  ለጥፋቷ ተመጣጣኝ ቅጣት እንድታገኝ አድርጊ›› የሚል ስልጣን ሰጠቻት…፡፡ሰገንም በዛን ወቅት ሳባን በተመለከተ የነበራት ቀና አመለካከት የተቀየረበት..…እንደዋና ተቀናቃኞና ጠላቶ  ማየት  የጀመረችበት  ስለነበረ የተሰጣትን እድል እስከመጨረሻው እንጥፍጣፊ አስባ፤እንደውም ከድንበሩ አልፋ ተጠቀመችበት..
እንግዲህ ያ ትብለጥ ለሰገን የሰጠችው ትዕዛዝና ትዕዙን ተከትሎ ወደተግባር የተሸጋገረው ድርጊት ለአባቷ ሞት ቀጥተኛ  ምክንያት  እንደሆነ  ሰባ በሙሉ  ልቧ ነው የምታምነው…ለዛም ነው የባለፉት ሰባት አመታት ዋና እቅዷና የህይወት አለማዋ እነዚህን ሁለት ሰዎች  ማጥፋት  ሆኖ  የኖረው፡፡››ሳባ  ከሀሳቧ  ባና ትኩረቷን ወደ ትብለጥ መለሰች፡፡
#ኢትዬጵያዊቷ_ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)

#የመጨረሻ_ክፍል


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


‹‹በል አስወጣቸው››ዳግላስ አንቦረቀ፡፡
‹‹ምን እየሆነ ነው ምን አጠፋን?››ኑሀሚ በተመሳሳይ የድምፅ ቃና  ጠየቀችው፡፡
‹‹ጠላቶቼ ይሄንን ቦታ እንዴት ሊያውቁት ቻሉ?››
‹‹እኛ ታዲያ ምን እናውቃለን? የራስህን ሰዎች አትመረምርም››
‹‹መሳሪያውን ወደ ግንባሯ ደቀነና‹‹እንደንዴቴ ሶስታችሁንም እዚህ ግንባር ግንባረችሁን ደፍቼያችሁ እሄድ ነበር፡፡ግን እንዳደረሳችሁብኝ ኪሳራ በሰላም እና በቀላሉ መሞት አይገባችሁም…ሶስታችሁም እባክህ ግደለን እያላችው በየቀኑ እንድትለምኑኝ ነው የማደርገው…በተለይ አንቺን…በሉ ያዟቸው..››

እሱን ከበው የነበሩ ጋንግስተሮች ወደቤት ውስጥ ገቡን ሶስቱንም እየገፈተሩ ወደውጭ አስወጣቸው…..በኮሪደሩ አልፈው ሳሎን ገቡ …ከዛ በደረጃው ወደግራውንድ ይዘዋቸው ሄዱ…ሰው ሁሉ ይተረማመሳል….መሳሪያዎች ከመጋዘን እየወጡ ይታደላሉ..ሀገር ወራሪ መጥቶ ለፊልሚያ እየተሰናዱ ነው የሚመስለው….ወደምድር ቤት ይዘዋቸው ወረዱ….ምድር ቤት ያለው  ትርምስ ከግራውንዱም ይብሳል….የተመረቱትን ኮኬይን አሰተካክለው ካርቶን ውስጥ በማስገባት ያሽጋሉ… ሌሎች ደግሞ የታሸገውን ወደጥግ እየወሰዱ ይደረድራሉ….ዳግላስ  እነኑሀሚን ለጠባቂዎቹ ተዋቸውና እያንቧረቀ ትእዛዝ በመስጠት ወደሰራተኞቹ ሄደ፡፡
‹‹እንዴ ይሄን ሁሉ ኮኬይን የሚደረድሩት እንዴት ሊየደርጉት ነው?››ምስራቅ ነች በሹክሹክታ የጠየቀችው፡፡
ኑሀሚን‹‹አልገባኝም ….ምን አልባት…..››ብላ ግምቷን መናገር ስትጀምር ያልጠበቁት ነገር ከፊት ለፊታቸው ተመለከቱ፡፡ የምድር ቤቱ ጥግ ላይ ያለ ወለል እንዴት አድርገውት እንደሆነ አይታወቅም ሲከፈት አዩ…
‹‹እንዴ!! ከዚህ በታች እቤት አለ እንዴ?››ናኦል ነው በገረሜታ የተናገረው፡፡
‹‹አይ እቤት አይመስለኝም….ከዚህ አካባቢ                                   ማምለጫ የውስጥ ለውስጥ መንገድ ነው፡፡
‹‹አንቺ እውነትሽን ሳይሆን አይቀርም…››
ስትል ሰዎች በካርቶን የታሸገውን ካርቶን እየተሸከሙ በተከፈተው ወለል በመሄድ እንደመሰላል  ባለ ብረት እየተንጠለጠሉ ወደታች መውረድ ጀመሩ፡፡፡
‹‹ሰዎች ትክክል ነኝ…ይሄ ከዚህ ስፍራ ማምለጫ የምድር ውስጥ መንገድ ነው….እናም እኛንም በዛ ውስጥ ይዘውን ሊሄዱ ነው››ኑሀሚ ነች ተናጋሪዋ፡፡
ምስራቅ‹‹የሆነ ነገር ማድረግ አለብን ..እዛ ውስጥ ይዘውን ገብተው ከዚህ ካስመለጡን እንዳለው ለወራት አስቃይቶ ነው የሚገድለን..መሞታችን ካልቀረ ደግሞ እዚሁ ለማምለጥ እየሞከርን ብንሞት ይሻላል››
‹‹ትክክል ነሽ ለማምለጥ መሞከሪያ ጊዜው አሁን ነው››ናኦልም በምስራቅ ሀሳብ ተስማማች፡፡
ምስራቅ ‹‹ናኦል››ስትል ተጣራች፡፡
‹‹በጣም ነው የምወድህ እሺ፣ማለቴ አፈቅርሀለው››አለችው፡፡
‹‹አውቃለው እኔም አፈቅርሻለው…ግን እያስፈራሺኝ ነው››
‹‹አትፍራ….ኑሀሚ አንቺንም ወድሻለው››
አቦ አንቺ ደግሞ አትረብሺኝ …ኑዛዜ አስመሰልሺው….ትኩረቴን እየበታተንሺው ነው…..ተመልከቱ እነዛ ሁለት ሰዎች ለእያንዳንዱ ሰው የእጅ ቦንብ እያደሉ ነው….ሲቀርብን በፍጥነት የተወሰነ ቦንብ በእጃችን ማስገባት አለብን…ከዛ…..››ኑሀሚ ንግግሯን ሳታገባድድ ምስራቅ ወደጎን ተስፈንጥራ  ጠረጴዛ ስር ሾልካ በመግባት ስትሰወር እነሱን ሲጠብቁ የነበሩ ጠባቂዎች የሚወስዱት እርምጃ ግራ ገብቷቸው ወዲህ ወዲያ ሲራወጡ ኑሀሚ የናኦልን ክን ድ ይዛ በግራ በኩል ስትሮጥ ከጠባቂዎቹ አንዱ ተወርውሮ የናኦል እግር ላይ ተጠምጥሞ አስቀረው….ኑሀሚ ወንድሟን ለቃ ሩጫዋን ቀጠለችና ከኮኬይኑ ካርቶን ጀርባ ተሰወረች….አንዱ መሳሪየውን ደቅኖ ተከተላት…በአየር ላይ ተንሳፈፈችን ጉሮሮውን ዘጋችለት…እጥፍጥፍ ብሎ ስሯ ወደቀ..መሳሪያውን ተቀበለችና ምላጩን ተጭና ዝም ብላ አንደቀደቀችው…እቅዷ ትርምስ መፍጠር ነው…ያሰበችው ተሳካላት፡፡ ሰው በፊትም ስጋትና ድንጋጤ ላይ የነበሩ ሰራተኞች የመሳሪያ መንደቅደቅ ሲሰሙ ሚይዙት የሚጨብጡት ጠፍቷቸው ከወዲህ ወዲያ መተረማመስ ጀመሩ ፡፡ይህ ደግሞ ለነኑሀሚ ጥሩ ሁኔታ ፈጠረላቸው፡፡
///
ወደቀኝ ታጥፋ ጠረጴዛ ተከልላ የተሰወረችው ምስራቅ ተንሸራታ ቦንብ የምታድለው እንስት ላይ ነው የተከመረችባት …ልጅቷ በድንጋጤ ቦንብ ያለበትን ካርቶን ለቀቀችው፡፡ መሬት ወድቆ ተዘረገፈ….ምስራቅ ልጅቷን በአንድ እጇ ይዛ በሌላ እጆሶስት ሚሆኑ ቦንቦችን ያዘች….ከግራ በኩል ይተኮስባት ጀመር..ምርጫ ስላልነበራት ልጅቶን ከፊት ለፊቷ  አቆመቻት…የሚተኮሰው ጥይት ሁሉ ልጅቷ ሰውነት ውስጥ ተሰገሰገ….ምስራቅ ወደኃላ አፈገፈገችና ቦታዋን ለቀቀች….ተኳሹ መሬት ላይ ከተዘረገፍት ቦንቦች አንድን አገኘው….አካባቢው ባልተጠበቀ ፍንዳታ ተናጋ…ዋና ዋና መብራቶቹ ጠፉና ጭላንጭል ድንግዝግዝ ብርሀን ብቻ ቀረ… ምድር ቤቱ በጥቁር ጭስ ተዋጠ…ምስራቅም ኑሀሚም በየፊናቸው  ናኦልን ሲፈልጉ ድንገት ተገናኙ….

‹‹ናኦልን አይተሸዋል…?››ኑሀሚ ነች ጠያቂዋ፡፡
‹‹አላየሁትም እየፈለኩት ነው፡፡ወደውጭ ይዘውት ወጥተው ሊሆን ይችላል›››ምስራቅ መለሰች፡
‹‹አይ በምድር ውስጥ ይዘውት ገብተው ከሆነስ..?እኔ ወደእዛ ልሂድ አንቺ ወደውጭ ውጪና ፈልጊው፡፡››
‹‹እርግጠኛ ነሽ….?››
‹‹አዎ ጊዜ አናጥፋ…››ተስማሙ……
ምስራቅ ወደውጭ መውጫው ከሚራኮቱት ሰዎች ጋር እየተጋፋች ስትሄድ ኑሀሚ ደግሞ ወደውስጠኛው የምድር ውስጥ መሹለኩያ ሮጠች…..፡፡
ኑሀሚ አስር ሜትር ርቀት ሲቀራት ወደእሷ ተተኮሰባት… ወደግራዋ ተስፈነጠረችና የሆነ የብረት ካዝና ስር ከለላ ይዛ እራሷን ለመከላከከል መተኮስ ጀመረች…

‹‹አንቺ ሸርሙጣ..ነይ ውጪ››የዳግላስ ድምፅ መሆኑን ለየች….እልክ ተናነቃት፡

‹‹እየተኮሰች ተሸለክልካ በመሀከላቸው ያለውን ርቀት ወደሳባት ሜትር አጠበበች…፡፡አሁን በግልፅ እየታያት ነው….አልማ ተኮሰች…ሆዱን ቦተረፈችው…አጎራና መሬት ተዘረረ…..፡፡ከግራና ከቀኝ ጠባቂዎች ወጡና ግማሹ ወደእሷ እየተኮሱ ለጓደኞቻቸው ሽፋን መስጠት ጀመሩ፡፡ ሁለቱ ደግሞ በደም የጨቀየውን ዳግላስን  እየጎተቱ ወደተከፈተው ጉድጎድ አስገቡት…ወደታች ይዘውት ወረዱ.፡፡ከዛ  እነሱ ተከተሉ…አንዱን ግንባሩን ብላ አስቀረችው፡፡ወደጉድጓዱ ተስፈነጠረች…ወንድሟን ይዘውት ሄደው ከሆነ መከተል አለባት…አንድ እርምጃ ሲቀራት እንዴት እንደሆነ በማታውቀው ዘዴ ወለሉ ተመልሶ ተዘጋ ፡፡ወደውስጥ የሚያሾልክ ምንም አይነት ቀዳዳ ሆነ ክፍተት በአካባቢው የለም፡፡መሳረያውን በወለሉ ላይ አርከፈከፈች…በንዴትና ተስፋ መቁረጥ በጉልበቷ ተናበረከከች…በዚህ ጊዜ ከኃላዋ አንድ በጣም ደስ የሚል ከገነት የመሰላ የጥሪ ድምፅ ሰማች‹‹…ኑሀም ኑሀሚ››
‹‹ዞር አለች››
‹‹ኑሀሚ ካርሎስ ነኝ››
ተንደርድራ ድምፅ ወደሰማችበት አካባቢ ተስፈነጠረች…..ኦ እራሱ ነው….በወገቡ ዙሪያ ቦንብ ደርድሮ  እንደዘንዶ የተጠመዘዘ ዝናር በጀርባው አንጠልጥሎ ዘመናዊ አውቶማቲክ መሳሪውን ደቅኖ አገኘችው…ተጠመጠመችበትና ከንፈሩ ላይ ተጣበቀች….
#ጉዞ_በፀሎት
(አቃቂ እና ቦሌ)


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧

የባልና ሚስቶቹ የምክር አገልግሎት እንደቀጠለ ነው…ዛሬ ወንጪ ከከተሙ አስራአራተኛው ቀን ላይ ሲሆኑ በዚህ የ14 ቀን ጉዞቸው ከፍተኛ ለውጥ ላይ ደርሰዋል…
አሁን በዚህ ሰአት ከሁለቱም ፊት ለፊት ተቀምጦ ተራ በተራ እያያቸው እያተናገረ ነው..
‹‹ሰው ምን ጊዜም ከስህተት ጋር ሚኖር ፍጡር ነው፡፡ከሰው ጋር ስንኖር ስህተት ፈላጊ ከሆን በማንኛውም ሰው ላይ ከመጠን ያለፈ ስህተቶችን በቀላሉ ማግኘት እንችላለን…..ያ ደግሞ ከሰው ጋር አያኖረንም…አንዳችን የሌላችንን ክፍተት ለመድፈን መፈጠራችንን እስካላሰብን

ድረስ ምንም ነገር ሰላም ሊሆን አይችልም፡፡ደግሞ አስቡት የጋብቻ ዋናው አስፈላጊነትም ይህ ነው ፡፡ወንድ ልጅ በራሱ ፍፅም ወንድ ብቻ አይደለም..75 ፐርሰንት የወንድነት ሆርሞን ሲኖረው 25 ፐርሰንት ግን የሴት ሆርሞን በውስጡ ይዞል..ሴቷም በተመሳሳይ 75 ፐርሰንት የሴት ሆርሞን ሲኖራት 25 ፐርሰንት የወንድ ሆርሞን ይዛለች…አያችሁ የተፈጥሮን ረቅቂነት ..ሁለቱ ሲጣመሩ ...አንድ ሙሉ ወንድና አንድ ሙሉ ሴት ይገኛል ማለት ነው፡፡ለመዋሀድ ደግሞ ፍቅር ዋናው አገኛኝ መሰላል ነው፡፡››
‹‹ግልፅ ነኝ አይደል?››
‹‹አዎ .. ቀጥል››ሲሉ የተናገሩት አቶ ኃይለ ልኡል ናቸው
ሰለሞን ንግሩን ቀጠለ‹‹በአንድ መንደር ውስጥ ትኖር የነበረች ሴት ሶስት ሽማግሌዎች ከቤቷ አካባቢ ከውጭ በፀጥታ ተቀምጠው ተመለከተች። ሴትዬዎም ከቤቷ ወጣችና ወደሽማግሌዎቹ ቀርባ" እናንተን ከዚህ በፊት አይቼያችሁ አላውቅም።ግን እዚህ በደጃፌ ለረጅም ጊዜ ተቀምጣችኋል። እርግጠኛ ነኝ እርቦችኋል። እባካችሁ ወደቤቴ ዘልቃችሁ ግብና ቤት ያፈራውን ቅመሱ››አለቻቸው።
ከመካከላቸው አንደኛው ሽማግሌ‹‹የቤቱ አባወራ በቤት አለ?››ሲሉ ጠየቋት። እሷም መለሰች‹‹አይ የለም››ስትል መለሰች።
ሽማግሌውም"ስለዚህ ወደቤት መግባት አንችልም።"ሲሉ መለሱላት።
ሴትዬዋም ወደውስጥ ተመልሳ ገባች ።መሸቶ ባሏ እንደመጣ ስለሰዎቹ ነገረችው። ባሏም
‹‹በይ አሁን ሂጂና ወደውስጥ እንዲገብ ጋብዢያቸው››አላት።
እሷም ወጣችና ወደውስጥ እንዲገብ በድጋሚ ጠየቀቻቸው‹‹ባለቤቴ ቤት ነው ያለው..ወደውስጥ እንድትገብም ጋብዛችኋል...እባካችሁ ወደ ውስጥ ዝለቁና የሆነ ነገር ቅመሱ››
‹‹እኛ በአንድ ላይ ወደውስጥ መግባት አንችልም››አሏት
‹‹ለምን ?››ግራ ገብቷት ጠየቀች።

ከሽማግሌዎቹ አንድ መመለስ ጀመረ "ይሄውልሽ ..."ወደአንደኛው ጓደኛው በጣቱ እየጠቆመ "..እሱ አቶ ሀብት ነው ወደቤትሽ ከገባ ቤትሽ በሀብት ለዘላለም እንደተሞላ ይዘልቃል።...ይሄኛው ደግሞ አቶ ስኬት ነው ከአንቺ ጋር ተከትሎ ወደውስጥ የሚገባው እሱ ከሆነ ቤትሽ በስኬት ይሞላል።እኔ ደግሞ አያ ፍቅር እባላለሁ። እኔ ከገባሁ ደግሞ በዘመንሽ ሁሉ በቤትሽ ፍቅር ሞልቶ ይፈሳል።ክፍቱ ግን አስቀድመን እንደነገርንሽ ሶስታችንም በአንድ ላይ ወደውስጥ መግባት አንችልም። ስለዚህ ወደቤትሽ ተመለሺና ከባልሽ ጋር በመማከር ከሶስታችን ማንኛችንን ወደውስጥ እንደምታስገብ ወስኑ "በማለት አብራሩላት።
እሷም እንደተባለችው ወደውስጥ ተመልሳ የሰማችውን ሁሉ ለባሏ አስረዳችው። ባሏ በሰማው ነገር ፈነጠዘ‹‹አቶ ሀብትን እንጋብዘው ፤ይግባና ቤታችን በሀብት ይሙላው፤ከእሱ የሚበልጥ ምን አለ?።››አላት።
ሚስትዬው ግን ውሳኔውን ተቃወመች"ለምን ስኬትን አንጋብዘውም፤ከሀብት ይልቅ ስኬት ነው የሚጠቅመን"አለች። እቤት ውስጥ የነበረች የልጃቸው ሚስት ወሬቸውን ስታዳምጥ ስለነበረ ወደእነሱ ቀረበችና‹‹ለምን ፍቅርን አንጋብዘውም..ከሁሉም በላይ በቤታችን ፍቅር ቢሞላ ይሻላል››የሚል ሀሳብ አቀረበች።
ጥቂት ካሠላሠሉ እና ከተከራከሩ በኃላ ባልና ሚስቶቹም በሀሳቧ ተስማሙ ፤ሚስትም ተመልሳ ወጣችና ወደእንግዶቹ ሄደች። ‹‹ከመካከላችው ፍቅርን ለመጋበዝ ወስነናል፤አያ ፍቅር እባክህ ተነስና ወደቤታችን ዘልቀህ ግባ...የተዘጋጀውን መአድም አብረኸን ተቋደስ..ሌሎቻችሁ ስላልመረጥናችሁ ይቅርታ "ስትል ተናገረች።
ፍቅር ተነሳና ወደቤት ለመግባት መንቀሳቀስ ሲጀምር ስኬትና ሀብትም ከተቀመጡበት ተነስተው ከኃላው ተከተሉት። ሴትዬዋ ግራ ገባት ‹‹አብረን መግባት አንችልም.. ከመሀላችን አንዳችንን ምረጪ አላላችሁኝም ነበር እንዴ?"ስትል ጠየቀች።
ከመሀከላቸው አንደኛው ማስረዳት ጀመረ‹‹ልጄ ስትመርጪ ስኬትን ወይም ሀብትን መርጠሽ ቢሆን ኖሮ አንዳችን ብቻ ነበር ወደቤትሽ የምንገባው።አሁን ግን የመረጥሽው ፍቅርን ነው። እኛ ደግሞ ፍቅር በገባበት ሁሉ ተከትለን መግባት ግዴታችን ነው።እኛም እራሳችን የፍቅር ምርኮኞች ነን።በዚህ ምክንያት ሶስታችንም የግድ ወደቤትሽ እንገባለን። ካዘጋጀሽውም መአድ እንቋደሳለን።ቤትሽንም ዘላለም በሚትረፈረፍ ሀብት ፤ስኬትና ፍቅር እንሞላዋለን።"አሏት። እሷም በደስታ እየፈነጠዘች ወደቤቷ ይዛቸው ገባች።

አያችሁ እናነት ሀብታም ናችሁ ስኬታማም ናችሁ…አሁን እየጣርን ያለነው ከመሀከሏችሁ ሾልኮ ተሰዶ ነበረውን ዋናውን ፍቅር ለመመለስ ነው..ፍቅር ከተመለሰ ሁሉ ነገር ሙሉ ይሆናል››
ዛሬ በዚህ በሰጠኋችሁ ምሳሌ በመሀከላችሁ፤በቤታችሁና በአካባቢያችሁ ፍቅር ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ እያሰላሰላችሁ እንድታድሩ እፈልጋለው…ነገ እዚህ የምናሳልፍበት የመጨረሻ ቀናችን ነው…ተነገ ወዲያ ወደአዲስ አበባ እንመለሳለን….አሁን ዋናውን ነገር አጠናቀናል…በቀጣይ ቤታችሁ ሆናችሁ ልጃችሁም ተመልሳ ስራችሁን እየሰራች የምናደርገው ይሆናል…››በማለት የእለቱን ፕሮግራም አገባደደ
ባልና ሚስቶቹ ክፍላቸው ተያይዘው ሲገቡ የጠበቃቸው የተለየ ነገር ነበር፡፡የመኝታ ክፍላቸውን ግራና ቀኝ ግድግዳ ታኮ የነበረው ሁለት አልጋ ሁለቱም ወደመሀል ተስቦና አንድ ላይ እንዲገጥም ተደርጎ አንድ አልጋ ሆኗል….ግዙፉ የተዋሀደው አልጋ በነጭ ውብ አልጋ ልብስ ተሸፍኗል.. አልጋ ልብሱ መሀል ላይ በልዩ ዲዛይን የተሰራ ባለቀይ ቀለም የልብ ቅርፅ ይታያል..ሙሉ ወለሉ በቀይ ፅጌረዳ አበባ ከመሞላቱም በተጫማሪ ባለቆርቆሮ ልዩ ሻማ በመሀከል መሀከል ጣልቃ በማስገባት የተለያ ቀለም ያው ብርሀን እየረጩ ነው፡፡አደኛውን ግድግዳ ተጠግቶ በሚታይ ጠረጴዛ ላይ ሻማፓኝ መጠጥ ከውብ ብርጭቆዎች ጋር ይታያል…በሚገፋ ተሸከርካሪ ጠረጴዛ ላይ አስጎምዢ ምግቦች ተደርድረዋል…
ሁለቱም ባልና ሚስት በመጀመሪያ የተሳሳተ ክፍል የገቡ ነበር የመሰላቸው….የገዛ ሻንጣቸውንና ሌሎች የግል እቃዎችን ሲያዩ ተረጋጉና ወደውስጥ ዘልቀው በራፉን ዘጉት፡፡
‹‹ስንድ ይሄ ጉደኛ ልጅ የ20 አመት ጎረምሳ አደረገን እኮ..››
ወ.ሮ ስንዱ እንባቸው እየረገፈ ተናገሩ‹‹ያበቃልኝ መስሎኝ ነበር….እድሜ ለልጄ ይሄው ዳግመኛ ልጃገረድ ሆንኩ››
‹‹እንዴ ስንድ ዛሬ ሳቅና ፈንጠዝያ ነው እንጂ የምን ለቅሶ?››አሉን እጃቸውን ወደባለቤታቸው ጉንጮች በመላክ እንባቸውን ጠረጉላቸውና አቅፈው ሳሞቸው….‹‹በይ ዛሬ ምሽቱ የእኛ መሰለኝ..እንቀመጥ››
‹‹መጀመሪያ ልብሴን ልቀይርና ቀለል ያለ ልብስ ልልበስ…እስከዛ እንተ ቁጭ በል››
#የድንግሊቷ_አፍቃሪዎች


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#ድርሰት_በዘሪሁን
===================

ቀለል ያሉ ሌሎች ጫወታዎችን  ሲጫወቱ  አመሹና  እቤቷ ድረስ ሸኝቷት በብዙ ነገር ተወስውሶ  ወደቤት ተመልሶ  ገባና የወንደላጤ ቤቱን ከፍቶ ባዶ ቤት ውስጥ ባዶ አልጋ ላይ ብቻውን ተኝቶ  ማሰላሰል ጀመረ፡፡

ሰሎሜ ደጋግማ እንደጠየቀችው..ከተማውንም ሆነ ሁሉንም ጓደኞቹን ድንገት ጣጥሎ ፖሊስ ማሰልጠኛ  የገባበት የራሱ የሆነ ምክንያት አለው..በቂና ጠንካራ ምክንያት ነበረው::
አለማየው  የፈራረሰና ጣሪያው የዛገ ባለአንድ ክፍል ቤት ውስጥ  ከእናትና አባቱ እና ከታናሽ ወንድሙ እና የሴት አያቱ ጋር የድህነት ግን ደግሞ ጣፋጭ ሳቅና ደስታ የሞላበት ኑሮ ይኖር ነበር፡፡ነበር እንዲህ ህልም ሆኖ አይን ጨፍኖ ሲገልጡ እንደሚበን ማሰብ ይከብደል፡፡ያ ሞቀትና የደመቀ… በፍቅር ሀውልት የተገናባ የቤተሰብ ትስስር በአንድ ወር ውስጥ ነው ድርምስምሱ ወጥቶ የፈረሰው፡፡በወቅቱ እሱ የ13 አመት ወጣት እና የ7 ክፍል ተማሪ ነበር፡፡ድንገት አባትዬው ታመምኩ አለና አልጋ ያዘ፡፡በሶስተኛው ቀን ሰፈር ያለ ጤና ጣቢያ ወሰዱት ፡፡አንድ ቀን አድሮ እስከወዲያኛው አሸለበ፡፡ ያልተጠበቀ ስለነበረ ሁኔታው ጠቅላላ ለቤተሰቡ እንደመቅሰፍት ነበር ፡፡በተለይ ለእናቱ…፡፡አባትዬው በሞተ በማግስቱ ተቀበረ፡፡ከቀብር መልስ እናትዬው ወደ ድንኳን ውስጥ ገብታ በተነጠፈላት የሀዘንተኛ ፍራሽ ላይ ተቀምጣ ሊያስተዛዝኗት የመጣውን የሩቅም ሆነ የቅርብ እንግዶችን በመቀበል ፋንታ ወደቤት ገብታ ከባሏ ጋር ትተኛበት የነበረበት አልጋዋ ላይ ገብታ ጥቅልል ብላ ተኛች፡፡.በሶስተኛው ቀን እስትንፋሷ በውስጧ አልነበረም…፡፡ጉድ ተባለ..፡፡ፍቅር እስከመቃብር….ማለት ይሄ ነው ተባለ…፡፡
የአለማየሁና የወንድሙ እጣ ፋንታ ግን በደካማና እድሜዋ በጋፋ ተጦሪ አያቱ እጅ ነበር የወደቀው፡፡፡ድሮም የድህነት  መቀመቅ ላይ የነበረ ቤተሰብ ውሉ የጠፋበት ሆነ፡፡ ምርጫ አልነበረም፡፡አለማየሁና ታናሹ ለመለያየት ተገደዱ፡፡አያትዬው ጎንደር ለሚኖር ሌለኛው ልጃቸው..‹‹ቢያንስ አንደኛውን ልጅ ውሰድልኝ ››ብለው ተማፀኑት..አጎትዬው ታናሹ ይሻለኛል ብለው መረጡና እሱን  ወሰዱት፡፡አለማየሁና አያትዬው ቀሩ..፡፡ይሄ ሁሉ ሲሆን ግድግዳ ሚጋሩት ቀጥሎ ካለው የቀበሌ ቤት የሚኖሩት ሰሎሜና እናትዬው ከጎናቸው ነበሩ፡፡በማፅናናቱም ካላቸው ላይ ቆረስ እያደረጉ በማጉረሱም አልተለዬቸውም ነበር፡፡ከዛ አያትዬው ሁለመናው ጭልምልም ሲልባቸው.የሰሎሜ እናት እቴቴን ፊት ለፊታቸው አስቀምጠው‹‹ …እኔ በቃኝ፡፡ ለራሴ ማልሆን ሰው የልጅ ልጄን ጠቅመዋለው ብዬ እዚህ  አልቀመጥም…፡፡ጭራሽ ሸክም ነው የምሆንበት፡፡አንቺ ለእናቱ ጎደኛዋ ነበርሽ…አለማየሁንም ልክ ከሰሎሜ እኩል አንቺም አሳድገሽዋል ፡፡..ልጅሽ ነው…፡፡አሁንም አንቺው ነሽ ምታጎርሺን.. ስለዚህ እኔ የልጅ ልጄን ላንቺ ጥዬ ወደ ገዳም መሄዴ ነው…ባይሆን እዛ ሄጄ ፀልይልሻለሁ››በማለት አለማየሁን  ለሰሎሜ እናት ጥለውት ጠቅልለው ገዳም ገቡ፡፡አለማየሁ ብቻውን ቀረ …፡፡
ከዛ ሁሉ ከሞላ ቤተሰብ አመት ባልሞላ ጊዜ ቀስ በቀስ እየበነኑ ጥለውት በመሄዳ ባዶውን አስቀሩት፡፡ በቃ ባዶውን…፡፡ግን ሰሎሜና እናትዬው ከመጠን በላይ እንዲሰበርና አልፈቀዱለትም፡፡ለሰሎሜም እህት ለእሳቸውም ሁለተኛ ልጅ ሆነ ፡፡በመሀከል የሚያዋስናቸውን ግድግዳ ቀደው የውስጥ ለውስጥ በር አበጁለትና አንደኛውን በር ዘጉት፡፡ሁለት የተለያ ክፍል የነበረው ቤት ሁለት  ክፍል ያለው አንድ ቤት ሆነ፡፡
እሱ ከትምህርት ቤት በተረፈው ጊዜ ሰፈር ውስጥ እየተሯሯጠና እየተላላከ በሚያገኘው ብር እራሱን መደጎም ቀጠለ፡፡የሰሎሜ እናት በመንግስት መስሪያ ቤት ውስጥ የመዝገብ ቤት ሰራተኛ ስለሆኑና ቆሚ ደሞዝ ስላላቸው..ምንም እንኳን የተትረፈረፈ ኑሮ ባይኖራቸውም ለሁለቱ ልጆችና ለእራሳቸው ለለት ጉርስ የሚቸግራቸው አይነት ሰው እልነበሩም…አለማየሁን ከልጃቸው እኩል ለማኖር የእለት ጉርስንና የአመት ልብሱን ለመሸፈን ቸግሯቸው አያውቅም፡፡በዛ ላይ አለማየሁን ከልጅነት ጀምሮ ሚወዱትና ከእናትዬው ጋር ካላቸው ቅርበት የተነሳ ብቸኛ ልጃቸውን ክርስትና የነሳቸው የእሱ እናት ስለሆነች ልጄ ወንድም ይሆናታል  በሚል አመለካከት ከልባቸው ነበር የተቀበሉት፡፡በዛ ላይ ከዚህ በፊት ልጃቸው በህይወትና በሞት መካከል ሆና ሆሲፒታል በገባች ጊዜ ከጓደኞቹ ጋር ሆኖ እሷን ለማትረፍ ያደረጉትን ታሪካዊ ድርጊት መቼም አይረሱትም…እናም ደግሞ ለሌላ ለማንም ሰው የማይነግሩት ተጨማሪ ዋና ምክንያትም ነበራቸው፡፡
.ከዛ ቀስ በቀን ከሰሎሜ ጋር ያለውን ግንኙነት እያላላ ከእናትዬውን ግን በወጉና በስርኣቱ በስልክ እየጠየቀ ስልጠናውን ጨርሶ በምክትል መቶ ሀለቅነት ተመረቀ..ከዛ አዲስ አበባ አካባቢ የመመደብ እድል ቢኖረውም በራሱ ምርጫ ድሬደዋ እንዲመድቡት አድርጎ እርቆ ሄደ፡፡ይሄንን ታሪክ ሰሎሜ ሆነች ሌሎች ጓደኞቹ አያውቁም..አይደለም በዛ ጊዜ ዛሬም እንዲህ ነበር ብሎ ሊነግራትና ሊያብራራላት አይችልም….ከባድ ነው፡፡በሀሳብ ሰውነቱ ስለዛለ ለመተኛት ወደ መኝታ ቤቱ ሄዶ …ድንገት ሳያስበው የአላዛር  ምስል በአእምሮ ተሰነቀረ፡፡

‹‹አሁን አላዛር ህክምናው ባይሳካለትስ…?ሰሎሜ ወደፍርድ ቤት ጉዳዩን ይዛ እንድትሄድ መክራታለው ወይስ ምን አደርጋለው….? ፍርድ ቤቱ እንዲፋቱ ከወሰነስ በኋላ ከእሷ ጋር ያለኝ ግንኙነት እንዴት ነው የሚሆነው…?አሁን ሳይቸግረኝ ሳፈቅራት እንደኖርኩና አሁንም እንደማፈቅራት ነገሬታለሁ…እና በቀጣይ ፡፡ ርቃታለሁ ወይስ የበለጠ ከእሷ ጋር ያለኝን ጓደኝነት አጠናክራለሁ….?እና ከዛስ…አሁን ተራው የእኔ ነው አግቢኝ እላታለሁ? ወይስ ?››..እራሱን አመመው፡፡

ስለምንም ነገር ማሰብ አቁሞ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ለመተኛት በመፈለግ የለበሰውን ልብስ አውልቆ ቢጃማ እየቀያየረ ሳለ ስልኩ  ድምጽ አሰማ..አነሳውና አየው… መልዕክት ነው፡፡ሰሎሜ ነች የላከችው፡፡

‹‹አሌክሶ ..በሰላም እቤት ገባህ..?››ይላል፡፡

‹‹አልጋው ጠርዝ ላይ ቁጭ አለና  መልስ ፅፎ ላከላት‹‹አዎ….ቢራ ቢሮዋ  ሰላም ገብቼለሁ?››

ከልጅቷ ጀምሮ በጣም ቀጭን እና በንፋስ ግፊት በአየር ላይ ተንሳፋ የምትበር ስለምትመስል ቢራቢሮ የሚል ቅፅል ስም አላት…ብዙውን ጊዜ እሱ በዚህ ስም ነው የሚጠራት፡፡

‹‹ጥሩ…ደስ የሚል ምሽት ነበር ያሳለፍነው…አመሰግናለሁ››

‹‹እኔም የልጅነት ጊዜዬን ወደኋላ ተመልሼ እንዳስታውስ ስላደረግሺኝ  ደስ ቢለኝም የተዳፈነ የልጅነት ፍቅሬን ስለቀሰቀሺብኝ ችግር ላይ ነኝ፡፡››ብሎ  ፃፍላና ላከላት፡፡

‹‹አንተ ባለትዳር እኮ ነኝ…ለምን ታሽኮረምመኛለህ?››

‹‹ይቅርታ ምን ላድረግ..?እንደምታውቂው ፍቅር  ይሉኝታ ቢስ ስሜት ነው፤ለማንኛውም አላዛርን ሰላም በይልኝ››

‹‹አይ …እራስ ደውለህ ሰላም በለው፤.ሌላ ነገር እንዲያስብ አልፈልግም…በመጀመሪያ ጉዳዩን ስለነገርኩህ እራሱ በጣም ቅር ብሎታል?፡፡››

‹‹አይ ታዲያ ምን ማድረግ ትችይ ነበር..?እስከመቼ ለብቻሽ በጉዳዩ መሰቃየት ትችያለሽ?››

‹‹አየህ አንተ ከልጅነቱ ጀምሮ የምታውቀው ጓደኛው ነህ.. ሁለታችሁም በጋራ የምታውቋቸው በርካታ ሰዎች አሉ ....ይሄንን ጉዳይ አንተ አወቅከው ማለት ሌሎች እሱንና አንተን የሚያውቁ ሰዎችም የማወቅ እድል ይኖራቸዋል ማለት ነው. .ይሄ ደግሞ ስነልቦናውን ይበልጥ ይጎዳል…..በዛ ላይ እንደምታውቀው የእናንተ የወንዶች ኢጎ ከፍተኛ ነው፡፡››