ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.84K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
391 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
📖፤ / ሱረቱ መርየም 19፤ 27-28
(2ተኛ እትም 1998 ዓ.ም)
*ሱራህ 19, አያህ 27*
فَأَتَتْ بِهِۦ قَوْمَهَا تَحْمِلُهُۥ ۖ قَالُوا۟ يَٰمَرْيَمُ لَقَدْ جِئْتِ شَيْـًۭٔا فَرِيًّۭا
በእርሱም የተሸከመቺው ሆና ወደ ዘመዶቿ መጣች፡፡ «መርየም ሆይ! ከባድን ነገር በእርግጥ ሠራሽ» አሏት፡፡
*ሱራህ 19, አያህ 28*
يَٰٓأُخْتَ هَٰرُونَ مَا كَانَ أَبُوكِ ٱمْرَأَ سَوْءٍۢ وَمَا كَانَتْ أُمُّكِ بَغِيًّۭا
«የሃሩን እኅት ሆይ! አባትሽ መጥፎ ሰው አልነበረም፡፡ እናትሽም አመንዝራ አልነበረችም» አሏት፡፡

የክፍሉ የግርጌ ማብራሪያ ላይ ማሪያም #የሙሴ ወንድም #የአሮን #እህት እንደሆነች ይናገራል።
ይህ ደግሞ #ከክርስቶስ #ልደት በፊት 1500 #ዘመን ዘሎ #የአሮንን ዘመን #ከክርስቶስ እናት #ማርያም ጋር በምን #አይነት ሂሳብ እንዳጠጋጋው እንጃ??

▶️ "የኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን" ደግሞ #ሁለት #ተቃራኒ ሀሳቦችን ታስቀምጣለች፦

1ኛ👉 <"የዮሴፍ የወንድም ልጅ ናት">

<<የእስራኤል ሽማግሎችና መምህራንም አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች የክብርት እመቤታችን #የአባቷን #ወንድም #ዮሴፍን ወደ በአደባባይ . . . አደራ ያስጠበቅንህን #የወንድምህን #ልጅ #እጮኛህ #ማርያምን. . .[3]>>

በመሰረቱ "የዮሴፍ የወንድም ልጅ ናት" የሚለው #መጽሐፍ ቅዱስ ዮሴፍ #የማርያም #እጮኛ እንጅ አጎት(የአባት ወንድም) መሆኑን አይናገርም።
ምናልባት #ወንድሙ ቁጥር 2 ላይ የተጠቀሰው አባቷ #ኢያቄም ይሆን?? ብለን እንዳንገምት እንኳን። #ኢያቄም ወንድም እንዳልነበረውና #ለእናቱም #ለአባቱም አንድ እንደሆነ በሌሎች #መጽሀፍቶቻቸው ላይ ተጽፏል[4]። <የወንድምህን ልጅ እጮኛህን> ማለት በምን ዓይነት ቋንቋ እንደሆነ እንጃ!!

2ኛ👉 <"ማርያም የሃናና የኢያቄም ልጅ ስትሆን አያቷም #ቅስራ ነው"> ትላለች።

ማርያም " #የሃናና #የኢያቄም ልጅ" መሆኗን ለመጀመሪያ ጊዜ #ያለምንም #መረጃ የጠቀሰው " #በተአምረ #ማርያም" መጽሀፍ < #አጼ #ዘረያቆብ> ነው።/በ 1426-1460/ ዓ.ም።
በመቅድሙ ላይ "ስመ አቡሃ ኢያቄም ወስመ ወላዲታ ሐና -የአባቷም ስም ኢያቄም ነው የእናቷም ስም ሐና ነው" ብሏል[5]።

▶️ የ" #ዘውትር #ፀሎት" ድርሳኑም ውስጥ በተደጋጋሚ ተጠቅሷል።
ቡሀላ ግን ከእነዚህ #ኑፋቄ #ትምህርት ከገባባቸው #አዋልድ #መጽሀፍት በስተቀር
<•የሀናና የኢያቄም ልጅ•> ናት ብሎ ያመነ #የቤተክርስቲያን #አባት አንድም እንኳ እንዳልነበረ አንድ መጽሀፍ ሲገልጽ
<<እም ሐና ወኢያቄም ተወለድኪ - ከሐናና ከኢያቄም ተወለድሽ>> የሚለው #የሃገራችን #ደራሲያን የሚናገሩት #ቃል ነው እንጅ #ከአገር ውጪ ያሉ #አቢያተ #ክርስቲያናት ጠቅሰውት አያውቁም።
<ሐና ኢያቄም> የሚል ቃል #በሃይማኖተ #አበው መጽሀፍ ላይ ድርሰታቸው የተሰበሰበላቸው #ከ55 በላይ የሆኑ #ሊቃውንቶች ይህንን #ቃል አልጠቀሱም። ከእነዚህም በተለይ #እነቅዱስ #ኤፍሬም#እነዩሐንስ #አፈወርቅ አመሰገኗት የሚባሉት ላይ እንኳን እነዚህ ቃላቶች #አልተጠቀሱም ይላል[6]።
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
📖፤ / ሱረቱ መርየም 19፤ 27-28 (2ተኛ እትም 1998 ዓ.ም) *ሱራህ 19, አያህ 27* فَأَتَتْ بِهِۦ قَوْمَهَا تَحْمِلُهُۥ ۖ قَالُوا۟ يَٰمَرْيَمُ لَقَدْ جِئْتِ شَيْـًۭٔا فَرِيًّۭا በእርሱም የተሸከመቺው ሆና ወደ ዘመዶቿ መጣች፡፡ «መርየም ሆይ! ከባድን ነገር በእርግጥ ሠራሽ» አሏት፡፡ *ሱራህ 19, አያህ 28* يَٰٓأُخْتَ هَٰرُونَ…
▶️ ሌሎች #በኦርቶዶክስ ያሉ #መጽሀፍቶች ደግሞ የተለያዩ #የዘር ግንድ ቆጠራዎችን ይጠቅሳሉ።
" #ድርሳነ #ጽዮን" የተባለው መጽሀፍ #የማርያም የዘር ሃረግን ሲገልጽ👇
ሜሊኪ። "የሐና(የእናቷ)
/ \ |
ሴም ሌዊ። ኤሊ
| |
ሆናሲን። ሜሊኪን
| |
ቀለምዮስን። ማቴን
| |
ኢያቄምን። ሐና
\ /
ማ ር ያ ም ን
ወለዱ ይላል[7]።

▶️ የማቲዎስ ወንጌል እንድምታ ደግሞ ከዚህ የተለየ ይገልጻል።
አኪም
|
ኤልዩድ
|
አልዓዛር
|
ቅዕራ
|
ኢያቄም ይላል[8]።

እንግዲህ እነዚህ #መጽሀፍት ደግሞ #በማርያም #አባት ቢስማሙም #በአያቶቻቸው ግን ፈጽሞ #አይስማሙም

▶️ የአንዳንድ ካቶሊካውያን አመለካከትም። << #ማርያም #ሰማያዊ #ፍጡር>> እንደሆነች ሲገልጹ ይህንንም ሀሳብ #የሰዓታት ጸሐፊና #የተአምረ #ማርያም ጸሐፊም በከፊል የሚቀበሉት ቢሆንም #ሃይማኖተ #አበው ግን በግልጽ ይህን ሃሳብ ያወግዘዋል። << እመቤታችን ከሰው የተለየች #ፍጥረት #ምድራዊት ያልሆነች ቀድሞ #በሰማይ #የነበረች #ሃይል(ፍጡር) ናት የሚል ቢኖር #ውግዝ ይሁን። በቅድስት መጽሀፍት እንደተጻፈው #ቅድስት ድንግል ማርያም #ከዳዊት#ከይሁዳ #ከአብርሃም ዘር እንደሆነች #በእውነት የሚያምን ግን #ከግዝት የተፈታ ይሁን>> ይላል[9]።

▶️ ማርያም ዘመዷ #ኤልሳቤጥ፣ እጮኛዋም #ዮሴፍ የነበረ ሴት እንደሆነች ሃገሯም #ናዝሬት #ገሊላ ሆኖ #ከዳዊት #ዘር እንደነበረች #መጽሀፍቅዱስ እየተናገረ #ሰማያዊ #ፍጡር #ናት ማለት " ህዝቤ #እውቀት #ከማጣቱ የተነሳ ጠፍቷል/ሆሴ 4-6/። እንደሚለው #የእውቀት #ማጣት ይመስላል።
መጽሀፍቅዱስ የማርያም #አባት #ኢያቄም ሳይሆን < #ኤሊ> የተባለ #ሰው እንደነበር የሚገልጸው ፍንጭ አለ።
(በሉቃስ 3፥23)
ደግሞ #የማርያም #ገድሎች እንደሚሉት #ለእናት #ለአባቷ #አንዲት #ልጅ ሳትሆን #እህትም እንዳላት #መጽሀፍቅዱስ ይናገራል። 👇

<< ጭፍሮችም እንዲህ አደረጉ ነገር ግን በኢየሱስ መስቀል አጠገብ እናቱ፥ #የእናቱም #እኅት፥ የቀለዮጳም ሚስት ማርያም፥ መግደላዊትም ማርያም ቆመው ነበር።>> {ዮሐ19፥25}።

<<ለዮሴፍ አባቱም #የማታን ልጅ #የያዕቆብ ልጅ (የማታን የልጅ ልጅ) ነው ብሎ #ማቲዎስ (በማቲ 1-16) #የዘር #ሐረጉን ሲቆጥር ወንጌላዊው #ሉቃስ ደግሞ #የማርያምን #የዘር ሃረግ ተከትሎ #በመቁጠር #የማርያም #አባቷ < #ኤሊ> እንደሆነ አስቀምጧል {ሉቃ 3-23}።

🔆 የዮሴፍ የዘር ሀረግ 🔆

(የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 1)
----------
1፤ የዳዊት ልጅ የአብርሃም ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ትውልድ መጽሐፍ።

2፤ አብርሃም ይስሐቅን ወለደ፤ ይስሐቅም ያዕቆብን ወለደ፤ ያዕቆብም ይሁዳንና ወንድሞቹን ወለደ........
............................................

6፤ " እሴይም ንጉሥ ዳዊትን ወለደ።"...............................
............................................

15፤ ኤልዩድም አልዓዛርን ወለደ፤ አልዓዛርም #ማታንን ወለደ፤ ማታንም #ያዕቆብን ወለደ፤

16፤ ያዕቆብም ክርስቶስ የተባለውን ኢየሱስን የወለደች የማርያምን እጮኛ #ዮሴፍን ወለደ።
🔆 የማርያም የዘር ሃረግ 🔆

(የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ- 3:)
...............

23፤ " ኢየሱስም ሊያስተምር ሲጀምር ዕድሜው ሠላሳ ዓመት ያህል ሆኖት ነበር እንደመሰላቸው #የዮሴፍ ልጅ ሆኖ፥ #የኤሊ ልጅ፥".......
.........................................

32፤ " የዳዊት ልጅ፥ የእሴይ ልጅ፥ የኢዮቤድ ልጅ፥ የቦዔዝ ልጅ፥ የሰልሞን ልጅ፥"....................
...........................................

36፤ የቃይንም ልጅ፥ የአርፋክስድ ልጅ፥ የሴም ልጅ፥ የኖኅ ልጅ፥ የላሜህ ልጅ፥

37፤ የማቱሳላ ልጅ፥ የሄኖክ ልጅ፥ የያሬድ ልጅ፥

38፤ የመላልኤል ልጅ፥ የቃይናን ልጅ፥ የሄኖስ ልጅ፥ የሴት ልጅ፥ የአዳም ልጅ፥ የእግዚአብሔር ልጅ[10]።

▶️ የማቲዎስ የዘር ሃረግ ገለጻ
" #ከአብርሃም በመነሳት ወደ ፊት ወደ #ኢየሱስ ሲቀጥል " #የሉቃስ ግን #ከኢየሱስ ጀምሮ ወደ ኋላ ወደ #አዳም ይጓዛል።
#ማቲዎስ #የኢየሱስ ህጋዊ አሳዳጊ #አባት የነበረውን #የዮሴፍን #የዘር ሀረግ ሲሰጠን #ሉቃስ #የእናቱን #የማርያምን #የዘር #ሐረግ ይሰጠናል።

በሉቃስ 3-23
"ኢየሱስ አገልግሎቱን በጀመረበት ወቅት ዕድሜው 30 ዓመት ያክል ነበረ ይህም ኢየሱስ #የዮሴፍ ልጅ መሰላቸው እንጂ #የኤሊ...(የማርያም ዘር ማንዘር) ልጅ ነበር" ተብሎ ተገልጾአል።
ምንም እንኳ #ማቴዎስ 4 #ሴቶችን በዘር ሀረግ ዝርዝር ቢጠቅስም/ማቲ 1-3 ፣ 5 ፣ 16/ #ሴቶች #በህጋዊ #የዘር #ሐረግ ውስጥ ስለማይገቡ #ማርያም ራሷ ሳትጠቀስ #ከአባቷ #ከኤሊ ጀምሮ እስከ #ዘር #ማንዘሮቿ #አዳም ድረስ ተገልጾአል[11]።

ይህም #ኤሊ #የዮሴፍ #አባት መሆኑን እንደ ሉቃስ አጻጻፍ #ከተወሰደ ዮሴፍ #የያዕቆብ ልጅ እንደሆነ #ማቴዎስም በግልጽ #አስቀምጧልና #ዮሴፍ #የኤሊም #የያዕቆብም ልጅ ወይም #የሁለቱ #ውህድ ሊሆን አይችልም። ምክንያቱም 1 ሰው 2 #አባት የለውምና።
ይህ ከሆነ ደግሞ #በአዋልድ #መጽሀፍት
<< ጰጥሪቃና ቴክታ የማርያም ስምንተኛ ቅድመ አያት ዝርያዎች፤ ነጭ ጥጃ ከማህጸን ስትወጣ ያች ነጭ ጥጃ ስትወልድ እንዲህ እያለ እስከ 7ኛ ትውልድ ድረስ 7ኛይቱም ጨረቃን ስትወልድ ጨረቃም ፀሐይን ስትወልድ አይቻለሁ ብትል ቴክታ ህልም ፈችዎችን ጠርቶ ጨረቃይቱ ማርያም ናት ፅሐይ ግን አልተገለጠልኝም ቢላቸውና ቴክታ ሄኤሜን፤ ሄሜን ዴርዴም ፤ ዴርዴ ቶናን፤ ቶና ሲካርን፤ ሲካር ሄርሜላን፤ ሄርሜላ #ሃናን#ሃናም #ማርያምን ወለደች፡ #ሃና በባሏ #በኢያቄም እጅ በትር እንደተያዘች ያች በትር አብባና አፍርታ እንዳየቻት #ኢያቄምም #በሀና እጅ ከፍሬው ሁሉ የሚመስለው የሌላ የሚጣፍጥ መልካም ፍሬ ተይዛ እንዳየች እርሷም ልጃቸው #ማርያም እንደነበረች የሚገልጸው አፈ ታሪክ #ከቁርዓን ተኮርጆ #በነገረ #ማርያም የተጻፈ #ተረት ሆኖ #ይቀራል ማለት ነው[12]።>>

ስለዚህም እንዲህ የሚያደርጉትን #ከተጻፈው #አትለፍ የሚለውን #መመሪያ #እንዲያነቡና #እንዲተገብሩ እናሳስባለን።

✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆

"ማጣቀሻዎች - References"
____________
[1] 📚፤ ንቡር ዕድ ኤርምያስ ከበደ ወልደ ኢየሱስ፤ <ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት> (3ተኛ መጽሀፍ፥ ቼምበር ማተሚያ ቤት አ.አ፤ *ገጽ 264-267፤ 1998 ዓም።

📚፤ አማረ አፈለ ብሻው፤
<ኢትዮጽያ የሰው ዘር የተገኘባት የእምነትና የስልጣኔ ምንጭ ናት>
*ገጽ 116-122፥ አ.አ ጥር 1996 ዓ.ም

📚፤ አባ ተስፋ ሥላሴ ሞገስ <ቅዱስ ማርቆስ ኢትዮጵያዊ ነው የተዋህዶ አንበሣም መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው> (2ተኛ እትም ግንቦት 2001 ዓ.ም)

[2] 📚፤ በርሰ ሊቃነጳጳሳት ዩሐንስ ዳግማዊ ይፋ ካደረጉት ከዋናው የላቲን መጽሀፍ የተተረጎመ <የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ትምህርተ ክርስቶስ> *ገጽ 145፥ 1997 ዓ.ም።

[3] 📚፤ የኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክ ተአምረ ኢየሱስ፤ ምዕራፍ 3(፫)፤ 10(፲) ፤ *ገጽ 16(፲፮)፥ ትንሳኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፤ አ.አ 1994 ዓ.ም።

[4] 📚፤ ድርሳነ ኪዳን ለማርያም ሳልስ፤ *ገጽ 48 1978 ዓ.ም።

[5] 📚፤ ተአምረ ማርያም፤ የዘውትር መቅድም (*ገጽ 4(፬)፤ 16(፲፮) 1989 ዓ.ም።

[6] 📚፤ ደቀመዝሙር መልአኩ ዘድሜጥሮስ። <ስንዴውን ለመስዋት እንክርዳዱን ለእሳት> አ.አ. ሰኔ 1998፤ *ገጽ 21።

[7] 📚፤ <ድርሳነ ጽዮን ዘሐሙስ> 44-13 *ገጽ 158። አ.አ. ኅዳር 1998 ዓ.ም።

[8] 📚፤ ወንጌል ቅዱስ፤ ዘማቲዎስ ወንጌል፤ ንባቡና ትርጓሜው በግእዝና በአማርኛ፤ 1፡ 16። *ገጽ 52። 1997 ዓ.ም።
[9] 📚፤ ሃይማኖተ አበው፤ ቃል ግዝት ኤጲስቆጶስ፤ ክፍል 6 ፤ *ገጽ 577 1986 ዓ.ም።

[10] 📚፤ ዋረን ደብልዩ ዌርዝቢ፤ <ለጌታ የተገዛህ ሁን> ፧ የማቴዎስ ወንጌል; ትርጉም ግርማዌ፤ *ገጽ 9፤ S.A.M፥ ኤስ ኤይ ኤም ማተሚያ ቤት አ.አ፤ 1995 ዓ.ም

[11] 📚፤ ዋረን ደብልዩ ዌርዝቢ፤ <ሩህሩህ ሁን፥ የሉቃስ ወንጌል ትርጉም ፤ *ገጽ 31-32፤ S.A.M፥ ኤስ ኤይ ኤም ማተሚያ ቤት አ.አ፤ 1996 ዓ.ም

📚፤ ቄስ ኮሊን ማንሰል፤ <ትምህርተ እግዚአብሔር> ፩ኛ መጽሐፍ፤ *ገጽ 80፥ ንግድ ማተሚያ ድርጅት አ.አ፥ 1995።

[12] 📚፤ ተአምረ ማርያም 2፤ 8-9 3ተኛ እትም *ገጽ 17፥ ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት። አ.አ 1989 ዓ.ም

📚፤ ያዕቆብ ሰንደቁ <እናታችን ጽዮን> 3ተኛ እትም *ገጽ 7-12። አ.አ፥ 1997 ዓ.ም።

📚፤ ቅዳሴ ማርያም አንድምታ 5፥38። *ገጽ 111። ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፤ 1983 ዓ.ም።

📚፤ ቅዱስ ቁርአን ሱረቱ አል-ኢምራ 3፤ አርቲስቲክ ማተሚያ ቤት፤ አ.አ፥ 1998 ዓ.ም።

(1.2▶️ጥያቄ) ይቀጥላል...
@gedlatnadersanat
<<ሁሉም ወደ #አምላኩ ወደ #እግዚአብሔር አንጋጦ #ሲለምን በአየን ጊዜ #መንፈሳዊ #ቅንዓትን ቀንቶ #ገሰጻቸው። በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ወደ ጸናች #አምላክን ወደ ወለደች ወደ ክብርት #እመቤታችን #ማርያም ለምን #እርዳታ አትሹም እርሱዋ #ከቅዱሳን ሁሉ #ድንቅ ድንቅ #ተአምራትን የምታደርግ፣ #ፈጥና #የምታደርስ #ልመናን የምትሰማ ናትና አላቸው። በዚያችም ጊዜ #ተአምራትን ወደ ምታደርግ #በድንጋሌ #ስጋ #በድንጋሌ #ነፍስ ወደ ጸናች ወደ ክብርት እመቤታችን #ማርያም ለመኑ .... የሃገሩም ሰዎች #እመቤታችንን አመሰገኑ[1]።>>

<<እግዚአብሔር #ሲመሰገን #ግሣጼ መጣ #ስለማርያም ግን #ምስጋና ሽልማት ይሆናል #ቀሲስ #እንድርያስም #የማርያምን #ቅዳሴ #ዘወትር ይቀድሳል #ከእርሷም #በቀር ሌላ #ቅዳሴ አያውቅም ነበር ... #ኤጲስቆጶሱ ጠርቶ ሁልጊዜ #ከአንድ #ቅዳሴ በቀር ለምን #ለእግዚአብሄር #አትቀድስም ብሎ ተቆጥቶ #እንዳይቀድስ ቢከለክለው #ማርያም ተገልጣ #የእኔን #ቅዳሴ ሲቀደስ አገልጋዩን #ያወገዝከው ለምንድን ነው? ... #በክፉ #አሟሟት እንድትሞት #በእውነት እነግርሃለው አለችው #ኤጲስቆጶሱም ከዛሬ ጀምሮ #ከእመቤታችን #ቅዳሴ በቀር ሌላ #ቅዳሴ #አትቀድስ አለው[2]።>>

▶️ ከላይ ያየነው ሁሉ #ስለማርያም የሚናገሩት #አዋልድ #መጽሀፍት #ከእግዚአብሄር ይልቅ #ማርያምን የሚያስበልጡና እርሷን #ስለማምለክ የሚያሳዩ የጠቀስናቸው #ጥቂት #አጸያፊ #ክፍሎች ሲሆኑ ከዚህ በታች ደግሞ #ከእግዚአብሄር ጋር ባልተናነሰ መልኩ #ስትመለክና #ስትመሰገን የሚያሳዩ #ጥቂት #ክፍሎችን ደግሞ #በመገረም እንመልከት፦

<< #ለአብ #ምስጋና ይገባል፣ #ለወልድ #ምስጋና ይገባል፣ #ለመንፈስ ቅዱስም #ምስጋና ይገባል፣ #አምላክን #ለወለደች #ለእመቤታችን #ድንግል #ማርያም #ምስጋና ይገባል[3]>>

ይህም ማለት #ከአብ #ከወልድና #ከመንፈስቅዱስ ጋር #እኩል #ምስጋና የምትቀበል #የስላሴ 4ተኛ #አካል ሆነች ማለት ነው። በሌላ መጽሐፍም
<<ወላዲተ አምላክ ማርያም ሆይ፥ ጧት ስነሳ #እግዚአብሔርንና #አንቺን እመቤቴን #በጸሎት #እንዳመሰግን የሚያነቃቃ መንፈስ ኅሊና አሳድሪብኝ፤[4]>> ይላል።

▶️ ከዚህም የከፋ #ማርያም እንደ #አምላክ #እግዚአብሔር ደግሞ ከእርሷ #ዝቅ ብሎ #እንደመማለጃዋ ሆኖም የቀረበበትን #መጽሀፍ ደግሞ እስኪ እንታዘብ ፦

<< #ዘጠኝ ወር #የተሸከምሽው ከሃሊ በሚሆን #ከጡትሽ #ወተቱን ባጠባሽውም #ልጅሽም #በሰው ልጅ ላይ #ቸርነቱና #ይቅርታው በበዛ #በአባቱ... #በእግዚአብሄርም #እማጸንሻለው #እማልድሻለሁ #እለምንሻለሁ[5]>> ይላል።

▶️ ስለዚህ እነዚህን የመሳሰሉ #ኢ-መጽሀፍ ቅዱሳዊና #አጸያፊ የሆኑ #አዋልድ መጽሀፍት ይዞ እግዚአብሔርን #አመልካለሁ ማለት ራስን #ማታለል ነው። እግዚአብሔር ግን <<እተካከለው ዘንድ በማን መሰላችሁኝ ይላል ቅዱሱ>> |ኢሳ 40፥25] ደግሞም <<እንደ እኔ ያለ ማን ነው ይነሳና ይጣራ ይናገርም>> ይላል እግዚአብሔር [ኢሳ 44፥7]።

✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆

"ማጣቀሻዎች - References"
___________
[1] 📚፤ የኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክ "መጽሀፈ ግብረ ህማማት፤ ዘረቡዕ በ1 ሰአት በነግህ የሚነበብ፤ ገጽ 394፤ ቁጥር 1-13፤ ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፥ አ.አ፥ 1996 ዓ.ም።

[2] 📚፤ የኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክ "መጽሀፈ ግብረ ሕማማት" ዘሐሙስ በመዓልት በ11 ሠዐት የሚነበብ፤ ገጽ 587 - 588 ቁጥር 1፤ 10 ፤ 1996 ዓ.ም።

[3] 📚፤ ተስፋ ገብረስላሴ፤ "ውዳሴ ማርያም ምስለ መልክዓ ማርያም በአማርኛ"፤ የዘውትር ጸሎት፤ ገጽ 6 ፥1986 ዓ.ም።

[4] እስመ ክብርት፥ የኅሊና ጸሎት አርኬ 15።

[5] 📚፤ ተአምረ ማርያም ግእዝና አማርኛ 3ተኛ ዕትም፥ ምዕ 102፥7፤ ገጽ 170፤ ትንሳዔ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፤ አ.አ፥ 1989 ዓ.ም።