ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.83K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
391 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
▶️ ከላይ እንዳየነው አንዳንዶች #የስሙን ሙሉ #ሐረግ ተከትለው ሌሎች ለሁለት ከፍለው #ለመተርጎም ከሞከሩት #ውጪ ሌሎች ደግሞ ከዚህ በተለየ መንገድ #ማርያም የሚለውን ስም #ለማብለጥ ወይም #ከፍ #ለማረግ ሲሉ #ማርያም ስለሚለው #ስም #ትርጉም #የአማርኛውን ወይም #የግእዙን ሆህያት ብቻ ተከትለው #ፊደል #በፊደል እየከፋፈሉ #በግእዝ ቋንቋ #በግጥም መልክ ይተረጉማሉ።👇👇 ✳️👉 ማኅደረ መለኮት…
▶️ 'አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫና አፄ ዘርዓ ያዕቆብ' በመጽሐፋቸው <ማርያም> የሚለውን #ስም ባለመቀበል <ማሪሃም> በሚለው አስተካክለው <<በዕብራይስጥ እመቤታችን ስሟ "ማሪሃም" ነው>> ብለዋል[5]።

▶️ ትርጓሜው ግን በግልጽ ባይቀመጥም "ነገረ ማርያም" #በመጽሐፉ ሲተረጉመው <የሁሉ እናት ማለት ነው> ይላል[6]።

▶️ አጼው ሆነ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ #በአርጋኖን መጽሐፋቸው ስሟ <ማሪሃም> ነው ማለታቸው 'አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ' በመዝገበ ቃላታቸው መጽሐፍ <ማርያም> የሚለውን <ማሪሃም> ማለትም #ስህተትና #አላዋቂነት ነው ብለዋል[7]።

▶️ እንግዲህ ከላይ ያየናቸው ትርጉሞች ሁሉ #ቅድስት #ድንግል #ማርያምን #ማእከል ያደረገና ስለእሷ ከሰበኩ #አጼዎች ጋር #ለማስማማት #የተፈጠረ #ተራ #መላ #ምት እንደሆነና #ከስሟ #ትርጉም ጀምሮ #ከቃለ #እግዚአብሄር ውጪ እንደሆነ አይተናል።

▶️ አንድ ሰው ደግሞ #ስሙን ሌላ #ማንም ሰው ቢይዘው ወይም አንድ #አይነት ቢሆን ሊኖር የሚችለው #ትርጉም ግን አንድ ብቻ ነው። #አንድ #ስም #ከአንድ በላይ #ትርጉም ሊኖረው አይችልም።
[ለምሳሌ ያክል #በመጽሀፍቅዱስ ውስጥ " #ዩሐንስ" የሚለውን ስም ብዙዎች #መጠሪያቸው አድርገው ከተጠቀሙት መካከል

✳️ ሐዋሪያው ዩሀንስ {ማቲ 1፤1-4}
✳️ ማርቆስ የሚሉት ዩሐንስ {ሐዋ 12፥12}
✳️ መጥምቁ ዩሐንስ {ማር 1፥1-4} የሚጠቀሱ ናቸው። ይሁን እንጂ #ዩሐንስ የሚለው #የስሙ ትርጉም <<እግዚአብሔር ጸጋ ነው>> ማለት ነው[8]። ስለዚህ #በአንድ #አይነት #ቋንቋ ለተነገረ ለማንኛውም #ስም የተለያየ #የስም #ትርጉም ሊኖረው ፈጽሞ አይችልም። #አንድ #ስም ከአንድ #ትርጉም በላይ ሊወክል አይችልምና።

▶️ በመሆኑም 'በአለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ' #መዝገበ #ቃላት #ትርጉም መሰረት #ማርያም ማለት <መራራ ዘመን> ማለት ሲሆን ለመጀመሪያ ጊዜ #ስሙን የተጠቀመችው #የሙሴ #እህት #ማርያም ሆና #የስሙ #መነሻነት 'ዮሴፍ' ያደረገውን ውለታ ያላወቀ 'ፈርኦን' የሚሉት #አዲስ #ንጉስ #በግብጽ ተሹሞ #በሃገሪቱ ውስጥ #እስራኤላውያን #እንደበረቱና #እንደበዙ አይቶ #ከጠላቶቻችን ጋር #አብረው ሆነው #ሊዋጉን ይችላሉ በሚል #ስጋት በከባድ ጭቆና #ሲገዛቸውና የሚወለዱ #ወንዶችን ሁሉ #እንዲገድሉ #ትዕዛዝ በመስጠቱ #የወንድሟ #የሙሴ መወለድ #ቤተሰቧን #በማሳሰቡ #ለ3 ወራት እንዳይሞት #በጭንቅ #ደብቀው #ለማሳደግ ቢሞክሩም #ወሬም እየተሰማ ስለመጣባቸው #በሳጥን አርገው የተወለደውን ልጃቸውን ተገደው #በባህር ላይ #ሰለጣሉት #የወቅቱ #የአገዛዝ ስርአት #ቤተሰቦቻቸው ላይና #ዘመዶቻቸው ላይ #መራራ #ዘመን ስለሆነባቸው #የሙሴ #እናት የሴት ልጇን ስም <ማርያም> ወይም #መራራ #ዘመን ብለው ሰይመዋታል[9]።

️ሙሴንም ቢሆን #የንጉስ #ፈርኦን #ሴት ልጅ #ከባሕር አግኝታ ስላሳደገችው <ሙሴ> ትርጉሙም < #ከባህር #የተገኘ> ብላዋለች።
በተጨማሪም ከዚህ <ከአለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ> መዝገበ ቃላት #ትርጉም ጋር በተመሳሳይ <የአለቃ ደስታ ተክለወልድ መዝገበ ቃላት> #መጽሀፍም #የማርያምን #ስም #ትርጉም ያብራራል[10]።

▶️ በመሆኑም #በመጽሀፍ #ቅዱስ ውስጥ #በማርያም #ስም የተጠሩ #ሴቶች ሁሉ በዘመናቸው #የፖለቲካ ወይም #የማህበራዊ ችግር ሲደርስባቸው የነበሩ መሆናቸውና #የስማቸው መጠሪያም <<መራራ ዘመን፣ Bitterness>> ወይም <ማርያም> ይሉት እንደነበር መረዳት አያዳግትም።
<<ሁሉም ወደ #አምላኩ ወደ #እግዚአብሔር አንጋጦ #ሲለምን በአየን ጊዜ #መንፈሳዊ #ቅንዓትን ቀንቶ #ገሰጻቸው። በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ወደ ጸናች #አምላክን ወደ ወለደች ወደ ክብርት #እመቤታችን #ማርያም ለምን #እርዳታ አትሹም እርሱዋ #ከቅዱሳን ሁሉ #ድንቅ ድንቅ #ተአምራትን የምታደርግ፣ #ፈጥና #የምታደርስ #ልመናን የምትሰማ ናትና አላቸው። በዚያችም ጊዜ #ተአምራትን ወደ ምታደርግ #በድንጋሌ #ስጋ #በድንጋሌ #ነፍስ ወደ ጸናች ወደ ክብርት እመቤታችን #ማርያም ለመኑ .... የሃገሩም ሰዎች #እመቤታችንን አመሰገኑ[1]።>>

<<እግዚአብሔር #ሲመሰገን #ግሣጼ መጣ #ስለማርያም ግን #ምስጋና ሽልማት ይሆናል #ቀሲስ #እንድርያስም #የማርያምን #ቅዳሴ #ዘወትር ይቀድሳል #ከእርሷም #በቀር ሌላ #ቅዳሴ አያውቅም ነበር ... #ኤጲስቆጶሱ ጠርቶ ሁልጊዜ #ከአንድ #ቅዳሴ በቀር ለምን #ለእግዚአብሄር #አትቀድስም ብሎ ተቆጥቶ #እንዳይቀድስ ቢከለክለው #ማርያም ተገልጣ #የእኔን #ቅዳሴ ሲቀደስ አገልጋዩን #ያወገዝከው ለምንድን ነው? ... #በክፉ #አሟሟት እንድትሞት #በእውነት እነግርሃለው አለችው #ኤጲስቆጶሱም ከዛሬ ጀምሮ #ከእመቤታችን #ቅዳሴ በቀር ሌላ #ቅዳሴ #አትቀድስ አለው[2]።>>

▶️ ከላይ ያየነው ሁሉ #ስለማርያም የሚናገሩት #አዋልድ #መጽሀፍት #ከእግዚአብሄር ይልቅ #ማርያምን የሚያስበልጡና እርሷን #ስለማምለክ የሚያሳዩ የጠቀስናቸው #ጥቂት #አጸያፊ #ክፍሎች ሲሆኑ ከዚህ በታች ደግሞ #ከእግዚአብሄር ጋር ባልተናነሰ መልኩ #ስትመለክና #ስትመሰገን የሚያሳዩ #ጥቂት #ክፍሎችን ደግሞ #በመገረም እንመልከት፦

<< #ለአብ #ምስጋና ይገባል፣ #ለወልድ #ምስጋና ይገባል፣ #ለመንፈስ ቅዱስም #ምስጋና ይገባል፣ #አምላክን #ለወለደች #ለእመቤታችን #ድንግል #ማርያም #ምስጋና ይገባል[3]>>

ይህም ማለት #ከአብ #ከወልድና #ከመንፈስቅዱስ ጋር #እኩል #ምስጋና የምትቀበል #የስላሴ 4ተኛ #አካል ሆነች ማለት ነው። በሌላ መጽሐፍም
<<ወላዲተ አምላክ ማርያም ሆይ፥ ጧት ስነሳ #እግዚአብሔርንና #አንቺን እመቤቴን #በጸሎት #እንዳመሰግን የሚያነቃቃ መንፈስ ኅሊና አሳድሪብኝ፤[4]>> ይላል።

▶️ ከዚህም የከፋ #ማርያም እንደ #አምላክ #እግዚአብሔር ደግሞ ከእርሷ #ዝቅ ብሎ #እንደመማለጃዋ ሆኖም የቀረበበትን #መጽሀፍ ደግሞ እስኪ እንታዘብ ፦

<< #ዘጠኝ ወር #የተሸከምሽው ከሃሊ በሚሆን #ከጡትሽ #ወተቱን ባጠባሽውም #ልጅሽም #በሰው ልጅ ላይ #ቸርነቱና #ይቅርታው በበዛ #በአባቱ... #በእግዚአብሄርም #እማጸንሻለው #እማልድሻለሁ #እለምንሻለሁ[5]>> ይላል።

▶️ ስለዚህ እነዚህን የመሳሰሉ #ኢ-መጽሀፍ ቅዱሳዊና #አጸያፊ የሆኑ #አዋልድ መጽሀፍት ይዞ እግዚአብሔርን #አመልካለሁ ማለት ራስን #ማታለል ነው። እግዚአብሔር ግን <<እተካከለው ዘንድ በማን መሰላችሁኝ ይላል ቅዱሱ>> |ኢሳ 40፥25] ደግሞም <<እንደ እኔ ያለ ማን ነው ይነሳና ይጣራ ይናገርም>> ይላል እግዚአብሔር [ኢሳ 44፥7]።

✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆

"ማጣቀሻዎች - References"
___________
[1] 📚፤ የኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክ "መጽሀፈ ግብረ ህማማት፤ ዘረቡዕ በ1 ሰአት በነግህ የሚነበብ፤ ገጽ 394፤ ቁጥር 1-13፤ ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፥ አ.አ፥ 1996 ዓ.ም።

[2] 📚፤ የኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክ "መጽሀፈ ግብረ ሕማማት" ዘሐሙስ በመዓልት በ11 ሠዐት የሚነበብ፤ ገጽ 587 - 588 ቁጥር 1፤ 10 ፤ 1996 ዓ.ም።

[3] 📚፤ ተስፋ ገብረስላሴ፤ "ውዳሴ ማርያም ምስለ መልክዓ ማርያም በአማርኛ"፤ የዘውትር ጸሎት፤ ገጽ 6 ፥1986 ዓ.ም።

[4] እስመ ክብርት፥ የኅሊና ጸሎት አርኬ 15።

[5] 📚፤ ተአምረ ማርያም ግእዝና አማርኛ 3ተኛ ዕትም፥ ምዕ 102፥7፤ ገጽ 170፤ ትንሳዔ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፤ አ.አ፥ 1989 ዓ.ም።