ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.83K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
391 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
ሀሳባቸውንም ሲያብራሩ፦
<<የድንግል ማርያም #ወላጆች#አያቶች#ቅድመ አያቶች .. አጽመ ርስታቸውን #አገራቸው ከሆነችው #ከኢትዮጽያ ተነስተው መስራችና አስተዳዳሪዋ በሆነው #በኢትዮጽያዊው #መልከ #ጼደቅ ምክንያት ምድረ - ርስት #ቅድስት #አገር #ከተማቸው ወደሆነችው ወደ #ኢየሩሳሌም ተጓዙ። በዚህ መልክ ከግንዶቹ #አዳምና #ሔዋን #የሰረጸው #የኢትዮጽያዊና #የኢትዮጽያዊነት #የትውልድ #ሀረግ #ከልጅ #ልጅ ተያይዞ እየወረደ #በመጨረሻው #በኢያቄምና #በሃና አማካኝነት #ከድንግል #ማርያም ደርሷል .... እርሷም #ኢትዮጽያዊ ተብላ እኛን #ኢትዮጽያዊ አሰኘችን። #እናታችን #ማርያም ሆይ.... ቀድሞ #በነብያት " #ኢትዮጽያ ታበጽሐ እደዊሃ ኅበ እግዚአብሔር - #ኢትዮጽያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች" የተባልሽ እኛም " #አምነ #ጽዮን - #እናታችን #ጽዮን" ስንልሽ የኖርን #በሰማይና #በምድር ንግስታችን ሆይ ደስ ይበልሽ[1]>> ብለዋል።.

▶️ አንዳንድ #ካቶሊኮችም #በመንፈስቅዱስ እንደተሰራችና #አዲስ ፍጡርም (ኃይል አርያማዊት) እንደሆነችና #እናትም #አባትም የሌላት #ከሰማይ ዱብ ያለች #እንደሆነችም የሚናገሩ አልጠፉም[2]።

▶️ ከእስልምናውም #ማርያም #የኢምራ ልጅ ናት ብሎም #የአሮን(የሙሴ ወንድም) #እህት ናት ይላል።
📖፤ / ሱረቱ መርየም 19፤ 27-28
(2ተኛ እትም 1998 ዓ.ም)
*ሱራህ 19, አያህ 27*
فَأَتَتْ بِهِۦ قَوْمَهَا تَحْمِلُهُۥ ۖ قَالُوا۟ يَٰمَرْيَمُ لَقَدْ جِئْتِ شَيْـًۭٔا فَرِيًّۭا
በእርሱም የተሸከመቺው ሆና ወደ ዘመዶቿ መጣች፡፡ «መርየም ሆይ! ከባድን ነገር በእርግጥ ሠራሽ» አሏት፡፡
*ሱራህ 19, አያህ 28*
يَٰٓأُخْتَ هَٰرُونَ مَا كَانَ أَبُوكِ ٱمْرَأَ سَوْءٍۢ وَمَا كَانَتْ أُمُّكِ بَغِيًّۭا
«የሃሩን እኅት ሆይ! አባትሽ መጥፎ ሰው አልነበረም፡፡ እናትሽም አመንዝራ አልነበረችም» አሏት፡፡

የክፍሉ የግርጌ ማብራሪያ ላይ ማሪያም #የሙሴ ወንድም #የአሮን #እህት እንደሆነች ይናገራል።
ይህ ደግሞ #ከክርስቶስ #ልደት በፊት 1500 #ዘመን ዘሎ #የአሮንን ዘመን #ከክርስቶስ እናት #ማርያም ጋር በምን #አይነት ሂሳብ እንዳጠጋጋው እንጃ??

▶️ "የኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን" ደግሞ #ሁለት #ተቃራኒ ሀሳቦችን ታስቀምጣለች፦

1ኛ👉 <"የዮሴፍ የወንድም ልጅ ናት">

<<የእስራኤል ሽማግሎችና መምህራንም አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች የክብርት እመቤታችን #የአባቷን #ወንድም #ዮሴፍን ወደ በአደባባይ . . . አደራ ያስጠበቅንህን #የወንድምህን #ልጅ #እጮኛህ #ማርያምን. . .[3]>>

በመሰረቱ "የዮሴፍ የወንድም ልጅ ናት" የሚለው #መጽሐፍ ቅዱስ ዮሴፍ #የማርያም #እጮኛ እንጅ አጎት(የአባት ወንድም) መሆኑን አይናገርም።
ምናልባት #ወንድሙ ቁጥር 2 ላይ የተጠቀሰው አባቷ #ኢያቄም ይሆን?? ብለን እንዳንገምት እንኳን። #ኢያቄም ወንድም እንዳልነበረውና #ለእናቱም #ለአባቱም አንድ እንደሆነ በሌሎች #መጽሀፍቶቻቸው ላይ ተጽፏል[4]። <የወንድምህን ልጅ እጮኛህን> ማለት በምን ዓይነት ቋንቋ እንደሆነ እንጃ!!

2ኛ👉 <"ማርያም የሃናና የኢያቄም ልጅ ስትሆን አያቷም #ቅስራ ነው"> ትላለች።

ማርያም " #የሃናና #የኢያቄም ልጅ" መሆኗን ለመጀመሪያ ጊዜ #ያለምንም #መረጃ የጠቀሰው " #በተአምረ #ማርያም" መጽሀፍ < #አጼ #ዘረያቆብ> ነው።/በ 1426-1460/ ዓ.ም።
በመቅድሙ ላይ "ስመ አቡሃ ኢያቄም ወስመ ወላዲታ ሐና -የአባቷም ስም ኢያቄም ነው የእናቷም ስም ሐና ነው" ብሏል[5]።

▶️ የ" #ዘውትር #ፀሎት" ድርሳኑም ውስጥ በተደጋጋሚ ተጠቅሷል።
ቡሀላ ግን ከእነዚህ #ኑፋቄ #ትምህርት ከገባባቸው #አዋልድ #መጽሀፍት በስተቀር
<•የሀናና የኢያቄም ልጅ•> ናት ብሎ ያመነ #የቤተክርስቲያን #አባት አንድም እንኳ እንዳልነበረ አንድ መጽሀፍ ሲገልጽ
<<እም ሐና ወኢያቄም ተወለድኪ - ከሐናና ከኢያቄም ተወለድሽ>> የሚለው #የሃገራችን #ደራሲያን የሚናገሩት #ቃል ነው እንጅ #ከአገር ውጪ ያሉ #አቢያተ #ክርስቲያናት ጠቅሰውት አያውቁም።
<ሐና ኢያቄም> የሚል ቃል #በሃይማኖተ #አበው መጽሀፍ ላይ ድርሰታቸው የተሰበሰበላቸው #ከ55 በላይ የሆኑ #ሊቃውንቶች ይህንን #ቃል አልጠቀሱም። ከእነዚህም በተለይ #እነቅዱስ #ኤፍሬም#እነዩሐንስ #አፈወርቅ አመሰገኗት የሚባሉት ላይ እንኳን እነዚህ ቃላቶች #አልተጠቀሱም ይላል[6]።
▶️ ስለቤተ #መቅደስ ሁኔታ #ሙሴ ከሰራው #ከማደሪያ #ድንኳን ጀምሮ #ማደሪያ ድንኳኑ 3 #ክፍሎች <ቅድስተ ቅዱሳን>፣ <ቅድስት>፣ እና <አደባባይ> ነበሩት {ዘጸ 26፥33} #በቅድስተ #ቅዱሳኑ ውስጥ #ታቦት ብቻ ነበር። #ታቦቱም #ሳጥን የሚመስል ሲሆን በውስጡ #አስርቱ ቃላት (ትእዛዛት) የተጻፈባቸውን 2 #ጽላት#መና ያለበት #የወርቅ #መሶብ #የአሮን #በትር ይዞ ነበር {ዕብ 9፤ 2-4}። #የታቦቱ ርዝመት 2 #ክንድ ተኩል ወይም 1 #ክንድ ተኩል ቁመቱ 1 ክንድ ተኩል ነበር። በውስጥና በውጭ በጥሩ #ወርቅ #የተለበጠ በእርሱም ዙሪያ #የወርቅ #አክሊል የተደረገለትና በጎንና #በጎኑ በግርጌ በኩል #የመሸከሚያ #መሎጊያ የሚገባባቸው 4 #ቀለበቶች ነበሩት {ዘጸ 25፤ 10-11}።

▶️ በማደሪያው #ድንኳኑ 2ኛ ክፍል በሆነው #በቅድስት ውስጥ ደግሞ #በስተግራ #ከወርቅ የተሰራ መቅረዝ {ዘጸ 25፥30፣ 40} #በስተቀኝ ለመገኘቱ #ህብስት {ህብስተ-ገጽ} የሚሆን #ገበታ {ዘጸ 25፤ 23-30} እንዲሁም ፊት ለፊት #በመጋረጃው ስር #የዕጣን #መሰዊያ (የወርቅ መሰዊያ) ነበር {ዘጸ 30፥1፣ 3-4}።

▶️ በ3ኛው ክፍል (በአደባባዩ) ደግሞ #የመታጠቢያ ሰን (ሳህን) እና #የናስ #መሰዊያ #ብቻ ነበር {ዘጸ 30፤ 17-18፣ ዘዳ 27፤ 1-8}።