#ያልተቋጨ
#ክፍል_አምስት (የመጨረሻ ክፍል)
#በክፍለማርያም
ህሊና
"አይይይይይይይ" እያለች ወረቀቱን አራገፈችዉ ትንሳኤ ጀርባዉን ሲያልበዉ ይታወቀዋል
ከአጠገቧ ገፋ አርጓት አይኑን በጨዉ አጥቦ ተቀመጠ
አንዳንዴ ተዋረድ ካለህ እንደዚህ ነዉ
አጠገቧ ተቀምጦ እጆቹን ወደ ሰደርያዋ ኪስ በቀስታ ሰዶ ከኪሷ ሶፍት አወጣ
አንደኛዋ ጉዋደኛዋ አይታዉ ሳቀች ህሊናም እንደወሰደባት ስታዉቅ ተናዳ አፈጠጠችበት
ትንሳኤም በሶፍቱ አፍንጫዉን እያበሰ በመዋረዱ በልቡ በጣም እያዘነ ሲወጣ በር ላይ ዮናስ ጠበቀዉ
"ባክህ ተዋረድኩልህ"
አለዉ ትንሳኤ በንዴት ከንፈሩን ነክሶ
"ምን ተፈጠረ"
ሲል ዮናስ አፋጠጠዉ
"ደረቅ መሆኑ ጠቅሞኛል ...."
እያለ ትንሳኤ የተፈጠረዉን ነገረዉ ከዛን ቀን ጀምሮ ነገሮች በህሊናና በእሱ መሀል ሴጣን እንዳለ ተገነዘበ እየወደዳት እያፈቀራትም ቢሆን ሌላ ሌላ ነገር ዉስጥ ገባ
የሆነ ቀን ሲያገረሽበት ለጉዋደኛዉ
"ጥራልኝ ላዋራት ናፈቀችኝ"
አለዉ
"ምን ጣጣ አለዉ"
ተከተለኝ አለዉና ወደ ህሊና ክፍል አምርተዉ ትንሳኤ በረንዳ ሲቆም ደፋሩ ጉዋደኛዉ ህሊናን አቀፍ አርጎ እያዋራት ይዧት ከወጣ በኋላ
"ተነጋገሩ "
ብሏቸዉ ትንሳኤን እና ህሊናን አገናኝቷቸዉ ሄደ።
"የመጀመርያ ቀን ቦርሳ በትከሻሽ ይዘሽ እየሳቅሽ ስትገቢ ነዉ ያየሁሽ
ደሞ በግራ እጅሽ ነዉ የምትፅፊዉ አደል"
ትንሳኤ ሊያዋራት የመጣዉ ሌላ ቢሆንም የልቡን በቻለዉ ቋንቋ መናገር ቀጠለ
ነገር ግን የህሊና መልስ
"ጉዋደኛ አለኝ አንደዉም አሁን እራሱ ሰዉ አይቶኝ ካንተ ጋር መቆሜን እንዳይነግሩት"
አለችዉ
ሀሳቡ ተበታተነ እኔ ነኝ እንጂ እስዋ አትወደኝም ሲል አስቦ በልቡ እሳት እየነደደ ዉስጡ በንዴት ግሎ
"እሺ ስታገኚኝ ግን አትዝጊኝ ሰላምታ እንኳን"
"እሺ"
ብላዉ ጥላዉ ገባች
ነገር ግን አንዴ ታክሲ ስትጠብቅ ከሩቅ አይቷት በደስታ ክንፍ ብሎ ሲጠጋት እየገላመጠች እራቀችዉ
ተከትሏት ጥቂት ለማዋራት እየሞከረ ተከተላት ነገር ግን እሷ ማዋራት አልፈለገችም
ትንሳኤ አመታት አልፈዉም አሁንም እንደ መጀመርያዉ ቦርሳ ይዛ እየሳቀች ስትገባ ያለዉ ምስል አይምሮዉ ዉስጥ አለ ፍቅሯ አመታት አልፎ እንደ ትላንት ይታወሰዋል መልኳ አይኗ ሰዉነቷ አወራሯ ሁሉ ነገሯ አይረሳዉም
ማፍቀር ማለት የማያገኙትን ሰዉ በተስፋ እንደመጠበቅ ነዉ ስሜቱ ያማል ያስከፋል መንገዱ ዉስጥ ግን አይረሴ ታሪኮች አሉ
አንድ ቀን አጊንቷት ያለ ፍርሀት ያለ ሰቀቀን እንደ ጉዋደኛ እንኳን ቢያዋራት ህልሙ ነዉ አንዳንዶች ለቀልድ ተዋዉቀዉ ይጋባሉ አንዳንዶች የእዉነት አፍቅረዉ ያጣሉ አለም ትገርማለች ፍቅርም ይገርማል ይሄ ታሪክ ለትንሳኤ የህይወቱ ክፍል ለህሊና ተራ ወሬ ሊሆን ይችላል
ትንሳኤ በልቡ የያዘዉ ታሪክ ነዉ ህሊና የናቀችዉ ተራ ነገር
ትንሳኤ በህሊና መፍረድ አቁሟል ምክንያቱም ሰዉ የፍላጎቱ ዉጤት ነዉ
የእሷ ምርጫና ፍላጎት የራሷ ዉሳኔ ነዉ
💫አለቀ💫
ነገ በተለመደው ሰዓት #ህመም_ያዘለ_ፍቅርን #ምእራፍ_ሁለት እንጀምራለን እሰከዛው መልካም ቆይታ🙏
#ክፍል_አምስት (የመጨረሻ ክፍል)
#በክፍለማርያም
ህሊና
"አይይይይይይይ" እያለች ወረቀቱን አራገፈችዉ ትንሳኤ ጀርባዉን ሲያልበዉ ይታወቀዋል
ከአጠገቧ ገፋ አርጓት አይኑን በጨዉ አጥቦ ተቀመጠ
አንዳንዴ ተዋረድ ካለህ እንደዚህ ነዉ
አጠገቧ ተቀምጦ እጆቹን ወደ ሰደርያዋ ኪስ በቀስታ ሰዶ ከኪሷ ሶፍት አወጣ
አንደኛዋ ጉዋደኛዋ አይታዉ ሳቀች ህሊናም እንደወሰደባት ስታዉቅ ተናዳ አፈጠጠችበት
ትንሳኤም በሶፍቱ አፍንጫዉን እያበሰ በመዋረዱ በልቡ በጣም እያዘነ ሲወጣ በር ላይ ዮናስ ጠበቀዉ
"ባክህ ተዋረድኩልህ"
አለዉ ትንሳኤ በንዴት ከንፈሩን ነክሶ
"ምን ተፈጠረ"
ሲል ዮናስ አፋጠጠዉ
"ደረቅ መሆኑ ጠቅሞኛል ...."
እያለ ትንሳኤ የተፈጠረዉን ነገረዉ ከዛን ቀን ጀምሮ ነገሮች በህሊናና በእሱ መሀል ሴጣን እንዳለ ተገነዘበ እየወደዳት እያፈቀራትም ቢሆን ሌላ ሌላ ነገር ዉስጥ ገባ
የሆነ ቀን ሲያገረሽበት ለጉዋደኛዉ
"ጥራልኝ ላዋራት ናፈቀችኝ"
አለዉ
"ምን ጣጣ አለዉ"
ተከተለኝ አለዉና ወደ ህሊና ክፍል አምርተዉ ትንሳኤ በረንዳ ሲቆም ደፋሩ ጉዋደኛዉ ህሊናን አቀፍ አርጎ እያዋራት ይዧት ከወጣ በኋላ
"ተነጋገሩ "
ብሏቸዉ ትንሳኤን እና ህሊናን አገናኝቷቸዉ ሄደ።
"የመጀመርያ ቀን ቦርሳ በትከሻሽ ይዘሽ እየሳቅሽ ስትገቢ ነዉ ያየሁሽ
ደሞ በግራ እጅሽ ነዉ የምትፅፊዉ አደል"
ትንሳኤ ሊያዋራት የመጣዉ ሌላ ቢሆንም የልቡን በቻለዉ ቋንቋ መናገር ቀጠለ
ነገር ግን የህሊና መልስ
"ጉዋደኛ አለኝ አንደዉም አሁን እራሱ ሰዉ አይቶኝ ካንተ ጋር መቆሜን እንዳይነግሩት"
አለችዉ
ሀሳቡ ተበታተነ እኔ ነኝ እንጂ እስዋ አትወደኝም ሲል አስቦ በልቡ እሳት እየነደደ ዉስጡ በንዴት ግሎ
"እሺ ስታገኚኝ ግን አትዝጊኝ ሰላምታ እንኳን"
"እሺ"
ብላዉ ጥላዉ ገባች
ነገር ግን አንዴ ታክሲ ስትጠብቅ ከሩቅ አይቷት በደስታ ክንፍ ብሎ ሲጠጋት እየገላመጠች እራቀችዉ
ተከትሏት ጥቂት ለማዋራት እየሞከረ ተከተላት ነገር ግን እሷ ማዋራት አልፈለገችም
ትንሳኤ አመታት አልፈዉም አሁንም እንደ መጀመርያዉ ቦርሳ ይዛ እየሳቀች ስትገባ ያለዉ ምስል አይምሮዉ ዉስጥ አለ ፍቅሯ አመታት አልፎ እንደ ትላንት ይታወሰዋል መልኳ አይኗ ሰዉነቷ አወራሯ ሁሉ ነገሯ አይረሳዉም
ማፍቀር ማለት የማያገኙትን ሰዉ በተስፋ እንደመጠበቅ ነዉ ስሜቱ ያማል ያስከፋል መንገዱ ዉስጥ ግን አይረሴ ታሪኮች አሉ
አንድ ቀን አጊንቷት ያለ ፍርሀት ያለ ሰቀቀን እንደ ጉዋደኛ እንኳን ቢያዋራት ህልሙ ነዉ አንዳንዶች ለቀልድ ተዋዉቀዉ ይጋባሉ አንዳንዶች የእዉነት አፍቅረዉ ያጣሉ አለም ትገርማለች ፍቅርም ይገርማል ይሄ ታሪክ ለትንሳኤ የህይወቱ ክፍል ለህሊና ተራ ወሬ ሊሆን ይችላል
ትንሳኤ በልቡ የያዘዉ ታሪክ ነዉ ህሊና የናቀችዉ ተራ ነገር
ትንሳኤ በህሊና መፍረድ አቁሟል ምክንያቱም ሰዉ የፍላጎቱ ዉጤት ነዉ
የእሷ ምርጫና ፍላጎት የራሷ ዉሳኔ ነዉ
💫አለቀ💫
ነገ በተለመደው ሰዓት #ህመም_ያዘለ_ፍቅርን #ምእራፍ_ሁለት እንጀምራለን እሰከዛው መልካም ቆይታ🙏
👍3
#ህመም_ያዘለ_ፍቅርን
፡
፡
#ምእራፍ_ሁለት
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
#በክፍለማርያም
ፀሀይዋ ለመጥለቅ ጥቂት ሰዐታት ይቀራታል እስዋን እየተመለከቱ ብዛት ያላቸዉ ወንዶች ግቢዉ ዉስጥ ከወዲህ ወድያ ይንጎማለላሉ።
ፍፁም በብቸኝነት ተቆራምቶ ከተቀመጠበት ጥግ ተነስቶ ቆመና ወደ ሰፊዉ ክፍል አምርቶ ወረቀት እና እስኪርቢቶ አንስቶ መፃፍ ጀመረ።
ለመጀመርያ ጊዜ ቤዛዊትን ያገኛት ቀን ሰአት ጠይቃዉ ስትሰድበዉ ታሪኩን እየፃፈ ከታሰረ ለመጀመርያ ጊዜ ፊቱ ላይ ፈገግታ ተነበበ መፃፉን አላቋረጠም የሚያስታዉሳቸዉን የእሱን እና የቤዛዊትን ታሪክ ወረቀቱ ላይ እየከተበዉ ነዉ።
ትምህርት ቤት ዉስጥ የጠቀሰችዉን ሲያስታዉስ ድምፅ አዉጥቶ መንከትከት ጀመረ ከጎኑ የነበሩት እስረኞች እየገላመጡት ከአጠገቡ ተነስተዉ እራቁት ማንም ሰዉ ያንተን ህመም እንዳንተ አያመዉም
ማንም ሰዉ አንተ ያሳለፍከዉ ከባድ ነገር ለእሱ ክብደቱ አይታወቀዉም
መሸከም ስትችል ተቋቁመሀዉ ስታልፍ ያበረታሀል እንጂ አቅቶህ ስትወድቅ የሚያነሳህ ውስን ነዉ።
መፃፉን እየቀጠለ ነዉ ቤዛዊት ፅፋ የምትሰጠዉን ወረቀቶች አሁንም ድረስ ያስታዉሳቸዋል
ህመሟን እብደቷን ሳያዉቅ ቀሚስሽ አጥሯል ሲላት ጠልፎ የሚጥል እረጅም ቀሚስ ለብሳ ቤቱ የመጣችዉንም አልረሳዉም አሁንም እንደታመመች አዉቆ ስላልተዋት ስላልራቃት በራሱ ደስተኛ ነዉ።
ቤዛዊትን ሲያስብ ፈገግታዋ የፊቷ እንቅስቃሴ አይኑ ላይ ይታየዋል ሳቋ በጆሮወቹ ዛሬም ያስተጋባሉ
ንዴትዋን ኩርፊያዋን ህመሟን ሲያስብ ብታናድደዉም ስለተላመዳቸዉ እንደ እንከኖቿም አይቆጥርባትም
የእሱን በድንገት በአጋጣሚ ፍቃዱ የሚባልን የተረገመን ፍጥረት በንዴት ተገፋፍቶ መግደሉን ሲያስብ ፀፀት መላ ሰዉነቱን እየወረረዉ የጀመረዉን ፅሁፍ አቁዋርጦ ማልቀስ ጀመረ።
ፍፁም እስር አልተመቸዉም ለነገሩ መታሰር ለማን ይመቻል ገና አሁን ወዳለበት የእስር ግቢ እንደገባ የሬሽን መዝገብ ዉስጥ ስሙ ስላልተካተተ ደረቅ ዳቦ ብቻ ቀምሶ ትራስ እያስፈለገዉ
ፍራሽ ላይ ጋደም አለ ለማሰብ ግዜ አላገኘም እራሱን ሀይለኛ ህመም እየተሰማዉ ነዉ።
ሰዉነቱ በትኩሳት ግሎ ነገር ግን ብርድብርድ እያለዉ እየተንቀጠቀጠ ለሊቱን እንቅልፍ በአይኑ ሳይዞር ነጋ
የመከራ ለሊት ይረዝማል ከታሰረ ሳምንት ወራት የቆየ ይመስለዋል ጠዋት ለህክምና የእስር ቤቱ ግቢ ካለዉ ክሊኒክ ለመሄድ ቢሞክርም ወረፋ ስላለ እንዲታገስ
ስለተነገረዉ መራመድ እያቃተዉ በልቡ
"መሞቴ ነዉ"
እያለ እንደምንም ፍራሹ ላይ ወድቆ ለመተኛት ሞከረ።
ቤዛዊት አይምሮዋ እየተረጋጋ ሲመጣ እማማ ስንቅነሽን ለፍፁም ምግብ እንዲቋጥሩለት አርጋ በተዘበራረቀ ስሜት ዉስጥ ሆና እንባ እየተናነቃት ወደ ፍፁም አመራች
እስካሁን ፍፁም ፍቃዱን መግደሉን አላመነችም
"የማይሆን የማይታሰብ ነገር"
ትላለች ከአፏ እያመለጣት ስትራመድ
የእስር ቤቱ ግቢ መግቢያ ስትደርስ የልብ ምቷ መፍጠን ጀመረ
ፍፁምን ካየችዉ ቆይታለች በፖሊሶች ታጅቦ ሲያልፍ ካየችዉ ወድያ ምንም የምታስታዉሰዉ ነገር አልነበረም እድሜ ለእማማ ስንቅነሽ እና ለልጃቸዉ ለጌታቸዉ ስታስቸግር ስትረብሽ ተንከባክበዉ ለዛሬ እንድትበቃ ላገዟት
ዉስጥ ገብታ የምትፈልገዉን ሰዉ ስም ተናግራ ቆማ መጠበቅ ጀመረች።
ፍፁም አይኖቹ ቀልተዉ ደም መስለዋል በተኛበት ፍራሽ እንደሰመመን "ፍፁም ደምሴ"
እየተባለ ሲጠራ ይሰማዋል መነሳት ግን አልቻለም
በሞት እና በህይወት መሀል ያለ እየመሰለዉ ሲያጣጥር ቆይቶ የቤዛዊት ምስል ፊቱ ላይ ድቅን ስላለበት አይኖቹ እንባ አዝለዉ እንደምንም ተነስቶ ለመቀመጥ ሞከረ
"ፍፁም ደምሴ ጠያቂ መጥቶሎታል"
የሚል ድምፅ ስለሰማ እያቃሰተ ወደ ዘመድ ጥየቃዉ ቦታዉ ለመሄድ መታገል ጀመረ።
ቤዛዊት እንደሆነች አስቀድሞ ልቡ አዉቆታል ጥቂት እንደተራመደ ግን የማጥወልወል ስሜት
ስለተሰማዉ ለመረጋጋት አስቦ ለመቆም ሲሞክር ወደቀ ጨለማ እየታየዉ የነበረ ቢሆንም ቀስበቀስ ጨለማዉም ጠፍቶ እራሱን ስቶ ወድቆ ቀረ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ምእራፍ_ሁለት
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
#በክፍለማርያም
ፀሀይዋ ለመጥለቅ ጥቂት ሰዐታት ይቀራታል እስዋን እየተመለከቱ ብዛት ያላቸዉ ወንዶች ግቢዉ ዉስጥ ከወዲህ ወድያ ይንጎማለላሉ።
ፍፁም በብቸኝነት ተቆራምቶ ከተቀመጠበት ጥግ ተነስቶ ቆመና ወደ ሰፊዉ ክፍል አምርቶ ወረቀት እና እስኪርቢቶ አንስቶ መፃፍ ጀመረ።
ለመጀመርያ ጊዜ ቤዛዊትን ያገኛት ቀን ሰአት ጠይቃዉ ስትሰድበዉ ታሪኩን እየፃፈ ከታሰረ ለመጀመርያ ጊዜ ፊቱ ላይ ፈገግታ ተነበበ መፃፉን አላቋረጠም የሚያስታዉሳቸዉን የእሱን እና የቤዛዊትን ታሪክ ወረቀቱ ላይ እየከተበዉ ነዉ።
ትምህርት ቤት ዉስጥ የጠቀሰችዉን ሲያስታዉስ ድምፅ አዉጥቶ መንከትከት ጀመረ ከጎኑ የነበሩት እስረኞች እየገላመጡት ከአጠገቡ ተነስተዉ እራቁት ማንም ሰዉ ያንተን ህመም እንዳንተ አያመዉም
ማንም ሰዉ አንተ ያሳለፍከዉ ከባድ ነገር ለእሱ ክብደቱ አይታወቀዉም
መሸከም ስትችል ተቋቁመሀዉ ስታልፍ ያበረታሀል እንጂ አቅቶህ ስትወድቅ የሚያነሳህ ውስን ነዉ።
መፃፉን እየቀጠለ ነዉ ቤዛዊት ፅፋ የምትሰጠዉን ወረቀቶች አሁንም ድረስ ያስታዉሳቸዋል
ህመሟን እብደቷን ሳያዉቅ ቀሚስሽ አጥሯል ሲላት ጠልፎ የሚጥል እረጅም ቀሚስ ለብሳ ቤቱ የመጣችዉንም አልረሳዉም አሁንም እንደታመመች አዉቆ ስላልተዋት ስላልራቃት በራሱ ደስተኛ ነዉ።
ቤዛዊትን ሲያስብ ፈገግታዋ የፊቷ እንቅስቃሴ አይኑ ላይ ይታየዋል ሳቋ በጆሮወቹ ዛሬም ያስተጋባሉ
ንዴትዋን ኩርፊያዋን ህመሟን ሲያስብ ብታናድደዉም ስለተላመዳቸዉ እንደ እንከኖቿም አይቆጥርባትም
የእሱን በድንገት በአጋጣሚ ፍቃዱ የሚባልን የተረገመን ፍጥረት በንዴት ተገፋፍቶ መግደሉን ሲያስብ ፀፀት መላ ሰዉነቱን እየወረረዉ የጀመረዉን ፅሁፍ አቁዋርጦ ማልቀስ ጀመረ።
ፍፁም እስር አልተመቸዉም ለነገሩ መታሰር ለማን ይመቻል ገና አሁን ወዳለበት የእስር ግቢ እንደገባ የሬሽን መዝገብ ዉስጥ ስሙ ስላልተካተተ ደረቅ ዳቦ ብቻ ቀምሶ ትራስ እያስፈለገዉ
ፍራሽ ላይ ጋደም አለ ለማሰብ ግዜ አላገኘም እራሱን ሀይለኛ ህመም እየተሰማዉ ነዉ።
ሰዉነቱ በትኩሳት ግሎ ነገር ግን ብርድብርድ እያለዉ እየተንቀጠቀጠ ለሊቱን እንቅልፍ በአይኑ ሳይዞር ነጋ
የመከራ ለሊት ይረዝማል ከታሰረ ሳምንት ወራት የቆየ ይመስለዋል ጠዋት ለህክምና የእስር ቤቱ ግቢ ካለዉ ክሊኒክ ለመሄድ ቢሞክርም ወረፋ ስላለ እንዲታገስ
ስለተነገረዉ መራመድ እያቃተዉ በልቡ
"መሞቴ ነዉ"
እያለ እንደምንም ፍራሹ ላይ ወድቆ ለመተኛት ሞከረ።
ቤዛዊት አይምሮዋ እየተረጋጋ ሲመጣ እማማ ስንቅነሽን ለፍፁም ምግብ እንዲቋጥሩለት አርጋ በተዘበራረቀ ስሜት ዉስጥ ሆና እንባ እየተናነቃት ወደ ፍፁም አመራች
እስካሁን ፍፁም ፍቃዱን መግደሉን አላመነችም
"የማይሆን የማይታሰብ ነገር"
ትላለች ከአፏ እያመለጣት ስትራመድ
የእስር ቤቱ ግቢ መግቢያ ስትደርስ የልብ ምቷ መፍጠን ጀመረ
ፍፁምን ካየችዉ ቆይታለች በፖሊሶች ታጅቦ ሲያልፍ ካየችዉ ወድያ ምንም የምታስታዉሰዉ ነገር አልነበረም እድሜ ለእማማ ስንቅነሽ እና ለልጃቸዉ ለጌታቸዉ ስታስቸግር ስትረብሽ ተንከባክበዉ ለዛሬ እንድትበቃ ላገዟት
ዉስጥ ገብታ የምትፈልገዉን ሰዉ ስም ተናግራ ቆማ መጠበቅ ጀመረች።
ፍፁም አይኖቹ ቀልተዉ ደም መስለዋል በተኛበት ፍራሽ እንደሰመመን "ፍፁም ደምሴ"
እየተባለ ሲጠራ ይሰማዋል መነሳት ግን አልቻለም
በሞት እና በህይወት መሀል ያለ እየመሰለዉ ሲያጣጥር ቆይቶ የቤዛዊት ምስል ፊቱ ላይ ድቅን ስላለበት አይኖቹ እንባ አዝለዉ እንደምንም ተነስቶ ለመቀመጥ ሞከረ
"ፍፁም ደምሴ ጠያቂ መጥቶሎታል"
የሚል ድምፅ ስለሰማ እያቃሰተ ወደ ዘመድ ጥየቃዉ ቦታዉ ለመሄድ መታገል ጀመረ።
ቤዛዊት እንደሆነች አስቀድሞ ልቡ አዉቆታል ጥቂት እንደተራመደ ግን የማጥወልወል ስሜት
ስለተሰማዉ ለመረጋጋት አስቦ ለመቆም ሲሞክር ወደቀ ጨለማ እየታየዉ የነበረ ቢሆንም ቀስበቀስ ጨለማዉም ጠፍቶ እራሱን ስቶ ወድቆ ቀረ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍3
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ምእራፍ_ሁለት (#ክፍል_ሁለት)
፡
፡
#በክፍለማርያም
...ወድቆ ቀረ
ቤዛዊት ከዘመድ መጠየቅያዉ ስፍራ ቆማ የፍፁምን መምጣት እየተጠባበቀች እንደ መለያ ከታጠረዉ ጥልፍልፍ የሽቦ አጥር መሀል ጥዉልግ ያለዉ ፍፁም እየተንቀራፈፈ ሲራመድ
እሱን እያየች ዉስጧ ስለተረበሸ በቆመችበት
"እኔን እኔን እኔን"
እያለች ለእሱ ያመጣችለትን ምግብ የያዘ ጎድጓዳ የምሳ እቃ መሬት ላይ እያስቀመጠች
በሁለቱም እጆቿ ደረቷን ለኮፍ ለኮፍ እያረገች መድቃት ጀመረች
"ምነው ለኔ ለበሽተኛዋ ባረገዉ እሱን ፈተዉ እኔን ባሰሩኝ"
ስትል ቆይታ ፍፁም መራመድ አቅቶት ሲቆም የእሷም ልብ በድንጋጤ ቆመ
መሬት ላይ ዝልፍልፍ እያለ ሲወድቅ እስዋም እንደሱ ወደ መሬት ተንበረከከች የለበሰችዉ ጥቁርበጥቁር ቀሚስ አዋራ ለበሰ ከአይኗ እንባ እንደ ዉሀ ትኩስ ሆኖ ጉንጮቿን አቁዋርጦ ይፈሳል
አጠገቧ የነበሩት እስረኛ ጠያቂዎች እና የማረምያ ቤቱ ፖሊሶች ሊያነሷት ቢጠጉም በጉልበቷ እንደተንበረከከች አንገቷን መሬቱ ላይ ደፍታ
"አስተማሪዬን አስተማሪዬን መልሱልኝ እኔ የሚያመኝን እሰሩኝና ፍፁሜን ፍቱልኝ"
ጩሀቷን የታመቀ ብሶቷን ማሰማት ጀመረች።
ፍፁምን እስረኞች በጥንቃቄ ደግፈዉ አቅፈዉ ወደ ክሊኒኩ ለመዉሰድ ሲሞክሩ ጠዋት የመለሰዉ ህክምና ወረፋ የሚያሲዘዉ ሰዉ እየተፀፀተ እና
"ምን አለ ጠዋቱኑ እንዲታከም በፈቀድኩለት"
በሚል ስሜት ዉስጥ ሆኖ ፍፁም ህክምናውን በፍጥነት እንዲያገኝ እረዳዉ
ፍፁም አይኑን ሲገልጥ ያስተዋለዉ አሁንም እስር ቤት ግቢ ዉስጥ መሆኑን ነዉ
አካባቢዉን እየቃኘ አንድ ወጣት ነጭ ገዋን የለበሰ ሀኪም መጥቶ
"ተከተለኝ"
አለዉ ፍፁምም ከተኛበት የክሊኒኩ አልጋ ቀስ እያለ ተነስቶ ተከተለዉ
ብዛት ያላቸዉ መድሀኒት ሰጥቶት ሰዐቱን ጠብቆ እንዲዉጥ ከመከረዉ በኋላ የደንብ ልብስ የለበሰ የማረምያ ቤቱ ፖሊት ወደ መታሰርያዉ ግቢ እየመለሰዉ።
መንገድ ላይ ለዘመድ ጥየቃ እንደተጠራ ሲያስታዉስ ከጎኑ ያለዉን ፖሊስ
"ዘመድ ፈልጎኝ ነበር እባክህ አንዴ ላናግራት"
አለ በተያያዘ አንደበት በህመም ቅላፄ ባለዉ አወራር
"ምንህ ናት"
ሲል ፖሊሱ ጥያቄዉን በጥያቄ መለሰለት
"ጉዋደኛዬ ፍቅረኛዬ "
እየተንተባተበ መለሰለት
"ትንሽ አስቸግራ ነበር አልወጣም ብላ ትንሽ ቆይተን ተሽሎታል ሌላ ግዜ ነይ ስንላት ተመልሳ ሄዳለች"
አለዉና ፍፁም የታሰረበት ግቢ ሲደርሱ ለሌላኛዉ ፖሊስ አስረክቦ
"ፈጣሪ ይማርህ"
ብሎ ተለየዉ።
(ከደቂቃወች በፊት)
ቤዛዊት በርቀት ፍፁምን በሽቦዉ አጮልቃ አፋፍሰዉ ሲወስዱት እየች
ሽቦዉን እየነቀነቀች መጮኋን አላቋረጠችም ነበር ፖሊሶች ሊያረጋጓት ቢሞክሩም የምትሰማበት ጆሮም ልብም አልነበራትም እናት አባት እንደተሞተበት ትኩስ ሀዘን ከልቧ አምርራ
"አረ ወገን አረ ፖሊስ አረ ወንድም አረ እህቴ"
እያለች ፊት ለፊቷ ያየችዉን ሰዉ ሁላ በለቅሶ እየለመነች
"አስፈቱልኝ አስለቅቁልኝ አስተማሪዬ እኮ ነዉ
ወደቀ እኮ ወ ደ ቀ አረ ላንሳዉ ኡኡኡኡ አረ የሰዉ ያለ..."
ልብሷ እንዳለ በአቧራ ተላዉሶ ፀጉሯን እያመነቃቀረች ደረቷን እየደቃች ስታስቸግር በሁኔታዋ ግራ የተጋቡት ፖሊሶች በስንት ልፋትና ትግል አረጋግተዋት ፍፁም ደህና እንደሆነና ህክምና እያገኘ እንደሆነ አስረድተዋት በፈለገችዉ ሌላ ቀን መጥታ ማየት እንደምትችል ነግረዋት እስከግቢዉ በር ደግፈው ሸኙዋት።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ምእራፍ_ሁለት (#ክፍል_ሁለት)
፡
፡
#በክፍለማርያም
...ወድቆ ቀረ
ቤዛዊት ከዘመድ መጠየቅያዉ ስፍራ ቆማ የፍፁምን መምጣት እየተጠባበቀች እንደ መለያ ከታጠረዉ ጥልፍልፍ የሽቦ አጥር መሀል ጥዉልግ ያለዉ ፍፁም እየተንቀራፈፈ ሲራመድ
እሱን እያየች ዉስጧ ስለተረበሸ በቆመችበት
"እኔን እኔን እኔን"
እያለች ለእሱ ያመጣችለትን ምግብ የያዘ ጎድጓዳ የምሳ እቃ መሬት ላይ እያስቀመጠች
በሁለቱም እጆቿ ደረቷን ለኮፍ ለኮፍ እያረገች መድቃት ጀመረች
"ምነው ለኔ ለበሽተኛዋ ባረገዉ እሱን ፈተዉ እኔን ባሰሩኝ"
ስትል ቆይታ ፍፁም መራመድ አቅቶት ሲቆም የእሷም ልብ በድንጋጤ ቆመ
መሬት ላይ ዝልፍልፍ እያለ ሲወድቅ እስዋም እንደሱ ወደ መሬት ተንበረከከች የለበሰችዉ ጥቁርበጥቁር ቀሚስ አዋራ ለበሰ ከአይኗ እንባ እንደ ዉሀ ትኩስ ሆኖ ጉንጮቿን አቁዋርጦ ይፈሳል
አጠገቧ የነበሩት እስረኛ ጠያቂዎች እና የማረምያ ቤቱ ፖሊሶች ሊያነሷት ቢጠጉም በጉልበቷ እንደተንበረከከች አንገቷን መሬቱ ላይ ደፍታ
"አስተማሪዬን አስተማሪዬን መልሱልኝ እኔ የሚያመኝን እሰሩኝና ፍፁሜን ፍቱልኝ"
ጩሀቷን የታመቀ ብሶቷን ማሰማት ጀመረች።
ፍፁምን እስረኞች በጥንቃቄ ደግፈዉ አቅፈዉ ወደ ክሊኒኩ ለመዉሰድ ሲሞክሩ ጠዋት የመለሰዉ ህክምና ወረፋ የሚያሲዘዉ ሰዉ እየተፀፀተ እና
"ምን አለ ጠዋቱኑ እንዲታከም በፈቀድኩለት"
በሚል ስሜት ዉስጥ ሆኖ ፍፁም ህክምናውን በፍጥነት እንዲያገኝ እረዳዉ
ፍፁም አይኑን ሲገልጥ ያስተዋለዉ አሁንም እስር ቤት ግቢ ዉስጥ መሆኑን ነዉ
አካባቢዉን እየቃኘ አንድ ወጣት ነጭ ገዋን የለበሰ ሀኪም መጥቶ
"ተከተለኝ"
አለዉ ፍፁምም ከተኛበት የክሊኒኩ አልጋ ቀስ እያለ ተነስቶ ተከተለዉ
ብዛት ያላቸዉ መድሀኒት ሰጥቶት ሰዐቱን ጠብቆ እንዲዉጥ ከመከረዉ በኋላ የደንብ ልብስ የለበሰ የማረምያ ቤቱ ፖሊት ወደ መታሰርያዉ ግቢ እየመለሰዉ።
መንገድ ላይ ለዘመድ ጥየቃ እንደተጠራ ሲያስታዉስ ከጎኑ ያለዉን ፖሊስ
"ዘመድ ፈልጎኝ ነበር እባክህ አንዴ ላናግራት"
አለ በተያያዘ አንደበት በህመም ቅላፄ ባለዉ አወራር
"ምንህ ናት"
ሲል ፖሊሱ ጥያቄዉን በጥያቄ መለሰለት
"ጉዋደኛዬ ፍቅረኛዬ "
እየተንተባተበ መለሰለት
"ትንሽ አስቸግራ ነበር አልወጣም ብላ ትንሽ ቆይተን ተሽሎታል ሌላ ግዜ ነይ ስንላት ተመልሳ ሄዳለች"
አለዉና ፍፁም የታሰረበት ግቢ ሲደርሱ ለሌላኛዉ ፖሊስ አስረክቦ
"ፈጣሪ ይማርህ"
ብሎ ተለየዉ።
(ከደቂቃወች በፊት)
ቤዛዊት በርቀት ፍፁምን በሽቦዉ አጮልቃ አፋፍሰዉ ሲወስዱት እየች
ሽቦዉን እየነቀነቀች መጮኋን አላቋረጠችም ነበር ፖሊሶች ሊያረጋጓት ቢሞክሩም የምትሰማበት ጆሮም ልብም አልነበራትም እናት አባት እንደተሞተበት ትኩስ ሀዘን ከልቧ አምርራ
"አረ ወገን አረ ፖሊስ አረ ወንድም አረ እህቴ"
እያለች ፊት ለፊቷ ያየችዉን ሰዉ ሁላ በለቅሶ እየለመነች
"አስፈቱልኝ አስለቅቁልኝ አስተማሪዬ እኮ ነዉ
ወደቀ እኮ ወ ደ ቀ አረ ላንሳዉ ኡኡኡኡ አረ የሰዉ ያለ..."
ልብሷ እንዳለ በአቧራ ተላዉሶ ፀጉሯን እያመነቃቀረች ደረቷን እየደቃች ስታስቸግር በሁኔታዋ ግራ የተጋቡት ፖሊሶች በስንት ልፋትና ትግል አረጋግተዋት ፍፁም ደህና እንደሆነና ህክምና እያገኘ እንደሆነ አስረድተዋት በፈለገችዉ ሌላ ቀን መጥታ ማየት እንደምትችል ነግረዋት እስከግቢዉ በር ደግፈው ሸኙዋት።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ምእራፍ_ሁለት (ክፍል ሶስት)
፡
፡
#በክፍለማርያም
ቤዛዊት ቤትዋን እነ እማማ ስንቅነሽ ቤት ካረገች ሰነባበተች ይሄ ሁሉ ምስቅልቅል ይፈጠራል ብላ አልነበረም ወደ እነ እማማ ቤት አመጣጧ ፍፁምንም የጋበዘችዉ በነፋሻዉ አየር ከሰዉ እራቅ ብለዉ የሰላም የፍቅር ጊዜ ለማሳለፍ ነበር
ነገር ግን አንዳንዴ ሀሳብ እንደ ንፋስ የማይታይ ሆኖ ይነፍከሳል ሀይል ካለዉም ነገሮችን ሳይጠበቅ እያንሳፈፈ እንደሚወስደዉ የታሰበዉ ሳይሆን ቀርቶ ያልተጠበቀ ነገር ይፈጠራል
ከእስር ቤቱ በር ጥቂት እንደወጣች ድንጋይ አጊንታ አረፍ አለች ጭንቅላቷ ዉስጥ ፍፁም ሲወድቅ ያለዉ ሁኔታ አሁንም ይታያታል አይኖቿ በለቅሶ ብዛት እንባ ማዉጣት ቢያቅታቸዉም ለአመል በቀስታ የሚፈሱ የእንባ ዘለላወች የአፍንጫዋን መስመር አቋርጠዉ አፍዋን እያራሱ በአገጯ አርገዉ ልብሷን እያረጠቡት ነዉ።
"ፍፁም ፍፁም ፍፁም"
በልቧ ይሄን ቃል ታነበንባለች እስካሁን መታሰሩ እዉነት አልመስልሽ እያላት እራሷን
"እንዴት እንዲህ ሊሆን ቻለ"
እያለች ትጠይቃለች መመለስ እና መፍታት የማትችለዉ ጥያቄ ሲሆን አይምሮዋ እየተቃወሰም ቢሆን ከተቀመጠችበት ተነስታ እንባዋን በእጆቿ እያበሰች ወደ እነ እማማ ስንቅነሽ ቤት አመራች።
ፍፁም ለመጀመሪያ ግዜ መድሀኒቱን ዉጦ የሰላም እንቅልፍ ወሰደዉ በህልሙ
ቤዛዊት ፊት ለፊቱ ተቀምጣ ስትስቅ እያያት ከጀርባዋ ጥቁር አሞራ እየበረረ ትከሻዋ ላይ ተቀምጦ የማያስፈራ ድምፅ እያወጣ ሲጮህ ባኖ ተነሳ
እየነጋጋ ነበር ከእስር ቤቱ ሚዲያ ክፍል መዝሙር ድምፁ ከፍተደርጎ ተከፍቷ ይሰማዋል እስረኞች ከእንቅልፋቸዉ እየተነሱ ወደ ዉጪ እየወጡ ነዉ ተነስቶ ለመቀመጥ ሞከረ ህመም አልተሰማዉም ተነስቶ ቆመ እራሱን ለቆታል
ፊቱ ላይ ጥልቅ ብሎ የጠፋ ፈገግታ ታይቶ እየተራመደ ወደ ዉጪ ወጣ አለ።
ቤዛዊት ከተኛችበት ስትነቃ የእማማ ስንቅነሽ ልጅ ጌታቸዉ በጥቂት ተገልጧ ወደ ሚታየዉ ባቷ ሲያፈጥ ያዘችዉ ቀሚሷን እያስተካከለች ተነሳች ጌታቸዉ ግን አሁንም በአይኑ እየተከታተላት ነዉ
"ቆንጆ እንደሆንሽ ታዉቂያለሽ"
አላት ማታ የጠጣዉ መጠጥ አሁንም አለቀቀዉም አፉን አሳስሮታል
ቤዛዊት ልብ ብላ አልሰማችዉም እማማ ስንቅነሽ ቤተክርስቲያን ለመሳለም በጠዋት ስለወጡ ሁለቱ ብቻ ናቸው ቤቱ ዉስጥ ያሉት።
(ከደቂቃ በፊት)
ቤዛዊት ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ዉስጥ ሆና እማማ ስንቅነሽ
"ልጄ ቤዛዊት ቤተስኪያን ደርሰን እንምጣ"
እያሉ ሊቀሰቅሷት ቢሞክሩም አልሰማም ስላለቻቸዉ እሳቸዉ ደጅ ወጥተዉ ልብሳቸዉን ቀያይረዉ ነጠላ ቢጤ ደርበዉ እንደወጡ በሩን ለመዝጋት ሲሞክሩ ልጃቸዉ ጌታቸዉ ከእንቅልፉ ይነቃል
ጥቂት አልጋዉ ላይ ሆኖ ስለ ቤዛዊት ቆንጅና ስለ ገላዋ ስለ ሰዉነቷ በህሊናዉ ሲስል ቆይቶ በቀስታ ከአልጋዉ ይነሳና ወደ እማማ እና ቤዛዊት ወደ ተኙበት ክፍል ያመራል
ቤዛዊት ብርድ ልብስ ተሸፋፍና ጥቅልል ብላ ተኝታለች ጌታቸዉ ፊት ለፊቷ እያያት ከቆመ በኋላ ብርድ ልብሱን ቀስ አርጎ ገለጠዉ ቤዛዊት አሁንም የእንቅልፍ ልብ ዉስጥ ናት
ቀስ ብሎ እረጅሙን ቀሚሷን እየገለጠዉ እና ታፋዋን እየተመለከተ ቤዛዊት ተገላብጣ ስትነቃ ፈንጠር ብሎ ቆሞ ማየቱን ቀጠለ።
(አሁን)
ጌታቸዉ ከቤዛዊት ጀርባ ቀስ ብሎ እየተጠጋ ሊያቅፋት ሲሞክር
"ምን መሆንህ ነዉ"
እያለች ገፍትራዉ አይኗን አጉረጠረጠችበት
እንደ መፍራት እያለ
"ምንም ምን አረኩ ደህና መሆንሽን ለማወቅ ነው "
እያለ ወደኋላ አፈገፈገ ነገር ግን በልቡ መጥፎ ሀሳብ ጠንስሶ ጠብቂ አገኝሻለሁ እያለ ነበር።
"ደህና ነኝ "
እያለችዉ ቤዛዊት ዛሬስ ፍፁምን አየዉ ይሆን እያለች እራሶን እየጠየቀች ለእራሷ
ዛሬማ አገኘዋለሁ አዋራዋለሁ እያለች ወጣች።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ምእራፍ_ሁለት (ክፍል ሶስት)
፡
፡
#በክፍለማርያም
ቤዛዊት ቤትዋን እነ እማማ ስንቅነሽ ቤት ካረገች ሰነባበተች ይሄ ሁሉ ምስቅልቅል ይፈጠራል ብላ አልነበረም ወደ እነ እማማ ቤት አመጣጧ ፍፁምንም የጋበዘችዉ በነፋሻዉ አየር ከሰዉ እራቅ ብለዉ የሰላም የፍቅር ጊዜ ለማሳለፍ ነበር
ነገር ግን አንዳንዴ ሀሳብ እንደ ንፋስ የማይታይ ሆኖ ይነፍከሳል ሀይል ካለዉም ነገሮችን ሳይጠበቅ እያንሳፈፈ እንደሚወስደዉ የታሰበዉ ሳይሆን ቀርቶ ያልተጠበቀ ነገር ይፈጠራል
ከእስር ቤቱ በር ጥቂት እንደወጣች ድንጋይ አጊንታ አረፍ አለች ጭንቅላቷ ዉስጥ ፍፁም ሲወድቅ ያለዉ ሁኔታ አሁንም ይታያታል አይኖቿ በለቅሶ ብዛት እንባ ማዉጣት ቢያቅታቸዉም ለአመል በቀስታ የሚፈሱ የእንባ ዘለላወች የአፍንጫዋን መስመር አቋርጠዉ አፍዋን እያራሱ በአገጯ አርገዉ ልብሷን እያረጠቡት ነዉ።
"ፍፁም ፍፁም ፍፁም"
በልቧ ይሄን ቃል ታነበንባለች እስካሁን መታሰሩ እዉነት አልመስልሽ እያላት እራሷን
"እንዴት እንዲህ ሊሆን ቻለ"
እያለች ትጠይቃለች መመለስ እና መፍታት የማትችለዉ ጥያቄ ሲሆን አይምሮዋ እየተቃወሰም ቢሆን ከተቀመጠችበት ተነስታ እንባዋን በእጆቿ እያበሰች ወደ እነ እማማ ስንቅነሽ ቤት አመራች።
ፍፁም ለመጀመሪያ ግዜ መድሀኒቱን ዉጦ የሰላም እንቅልፍ ወሰደዉ በህልሙ
ቤዛዊት ፊት ለፊቱ ተቀምጣ ስትስቅ እያያት ከጀርባዋ ጥቁር አሞራ እየበረረ ትከሻዋ ላይ ተቀምጦ የማያስፈራ ድምፅ እያወጣ ሲጮህ ባኖ ተነሳ
እየነጋጋ ነበር ከእስር ቤቱ ሚዲያ ክፍል መዝሙር ድምፁ ከፍተደርጎ ተከፍቷ ይሰማዋል እስረኞች ከእንቅልፋቸዉ እየተነሱ ወደ ዉጪ እየወጡ ነዉ ተነስቶ ለመቀመጥ ሞከረ ህመም አልተሰማዉም ተነስቶ ቆመ እራሱን ለቆታል
ፊቱ ላይ ጥልቅ ብሎ የጠፋ ፈገግታ ታይቶ እየተራመደ ወደ ዉጪ ወጣ አለ።
ቤዛዊት ከተኛችበት ስትነቃ የእማማ ስንቅነሽ ልጅ ጌታቸዉ በጥቂት ተገልጧ ወደ ሚታየዉ ባቷ ሲያፈጥ ያዘችዉ ቀሚሷን እያስተካከለች ተነሳች ጌታቸዉ ግን አሁንም በአይኑ እየተከታተላት ነዉ
"ቆንጆ እንደሆንሽ ታዉቂያለሽ"
አላት ማታ የጠጣዉ መጠጥ አሁንም አለቀቀዉም አፉን አሳስሮታል
ቤዛዊት ልብ ብላ አልሰማችዉም እማማ ስንቅነሽ ቤተክርስቲያን ለመሳለም በጠዋት ስለወጡ ሁለቱ ብቻ ናቸው ቤቱ ዉስጥ ያሉት።
(ከደቂቃ በፊት)
ቤዛዊት ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ዉስጥ ሆና እማማ ስንቅነሽ
"ልጄ ቤዛዊት ቤተስኪያን ደርሰን እንምጣ"
እያሉ ሊቀሰቅሷት ቢሞክሩም አልሰማም ስላለቻቸዉ እሳቸዉ ደጅ ወጥተዉ ልብሳቸዉን ቀያይረዉ ነጠላ ቢጤ ደርበዉ እንደወጡ በሩን ለመዝጋት ሲሞክሩ ልጃቸዉ ጌታቸዉ ከእንቅልፉ ይነቃል
ጥቂት አልጋዉ ላይ ሆኖ ስለ ቤዛዊት ቆንጅና ስለ ገላዋ ስለ ሰዉነቷ በህሊናዉ ሲስል ቆይቶ በቀስታ ከአልጋዉ ይነሳና ወደ እማማ እና ቤዛዊት ወደ ተኙበት ክፍል ያመራል
ቤዛዊት ብርድ ልብስ ተሸፋፍና ጥቅልል ብላ ተኝታለች ጌታቸዉ ፊት ለፊቷ እያያት ከቆመ በኋላ ብርድ ልብሱን ቀስ አርጎ ገለጠዉ ቤዛዊት አሁንም የእንቅልፍ ልብ ዉስጥ ናት
ቀስ ብሎ እረጅሙን ቀሚሷን እየገለጠዉ እና ታፋዋን እየተመለከተ ቤዛዊት ተገላብጣ ስትነቃ ፈንጠር ብሎ ቆሞ ማየቱን ቀጠለ።
(አሁን)
ጌታቸዉ ከቤዛዊት ጀርባ ቀስ ብሎ እየተጠጋ ሊያቅፋት ሲሞክር
"ምን መሆንህ ነዉ"
እያለች ገፍትራዉ አይኗን አጉረጠረጠችበት
እንደ መፍራት እያለ
"ምንም ምን አረኩ ደህና መሆንሽን ለማወቅ ነው "
እያለ ወደኋላ አፈገፈገ ነገር ግን በልቡ መጥፎ ሀሳብ ጠንስሶ ጠብቂ አገኝሻለሁ እያለ ነበር።
"ደህና ነኝ "
እያለችዉ ቤዛዊት ዛሬስ ፍፁምን አየዉ ይሆን እያለች እራሶን እየጠየቀች ለእራሷ
ዛሬማ አገኘዋለሁ አዋራዋለሁ እያለች ወጣች።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ምእራፍ_ሁለት ( #ክፍል_አራት)
፡
፡
#በክፍለማርያም
..ፍፁም ወረቀቱን ገልጦ ስለቤዛዊት እና ስለሱ መከራ የበዛበት የፍቅር ታሪክ መፃፉን ተያይዞታል
ህመሙ እየተሻለዉ ስለሆነ ጥሩ ስሜት ዉስጥ ነዉ ስላለፈዉ ታሪክ እያሰበ ይፅፋል አስደሳች ጊዜወቹ ታዉሰዉት ፊቱ ላይ ደማቅ ፈገግታ እየተነበበ አእምሮዉ ላይ ያለዉን ከወረቀቱ ጋር እያዋሀደዉ ነዉ።
እንደምትወደዉ የነገረችዉን ቀን አስታወሰ ፅፋ የሰጠችዉ ወረቀት ዉል አለበት የተጣሉበትን ቀን መሀል ላይ ፍቃዱ መሀላቸዉ ገብቶ የእህቱን ፎቶ ሚስቱ ናት ብሎ ያወራ ቀን የተፈጠረዉን ሲያስታዉስ የሚፅፉት እጆቹ መንቀጥቀጥ ጀመሩ
ለቤዛዊት ሊያስረዳት ዉሸት መሆኑን ሊያብራራላት ሲጣደፍ መኪና የገጨዉን ሲያስታዉስ መፃፍ ስላልቻለ እስኪቢርቶዉን ወረቀቱላይ ጥሎ በዝምታ ተቀመጠ
ከጎኑ አብሮት የታሰረዉ ማስረሻ የተባለ ታሪሚ የፍፁምን ሁኔታ በአይኖቹ ሲከታተል ስለነበረ
"ምን እየፃፍክ ነዉ ወዳጄ?"
ሲል ለዉቀት መከላከያ ብሎ ዉሀ ዉስጥ ነክሮ አናቱ ላይ ያስቀመጠዉን ፎጣ እያወረደ
ፍፁም የጠየቀዉን ልጅ ትኩር ብሎ ተመለከተዉ ማስረሻ ቀጠን ብሎ ቀዉላላ የሚባል ወጣት ነዉ አይኖቹን ሲያስተዉላቸዉ ከተረገመዉ ፍቃዱ ጋር ተመሳሰሉበት
ለመጀመርያ ግዜ ከተቀመጠበት ተነስቶ ጮሀ
"ምን አገባት ምን አገባህ"
ደም ስሮቹ ተገታትረዉ ንዴት እያንቀጠቀጠዉ መናገሩን ተያያዘዉ
"ለምን አተወኝም ተዉኝ ተዉኝ"
እጆቹን እያወራጨ ወደ ማስረሻ ተጠጋዉ
ማስረሻ በፍፁም ሁኔታ እየተገረመ እና ጥሎት እንደመሄድ እያለ
"እብድ ድሮስ ነብሰ በላ መጨረሻዉ ማበድ ነዉ"
ብሎት ወደ ዉጪ ፍፁምን ትቶት ወጣ።
ፍፁም ግን ማስረሻ የተናገረዉ ንግግር አይምሮዉ ላይ እያቃጨለበት ነበር
"ነብሰበላ ነብሰ በላ ማበድ ማበድ"
እዉነት ነዉ የሰዉ ደም ወደ ሰማይ ይጮሀል ገዳይም የሰላም እንቅልፍ አያገኝም ማንም መጥፎ ሰው ቢሆን እንኳን የፈጠረዉ ፈጣሪ በሞት ካልወሰደዉ በቀር በሰዉ ቢገደል
ገዳዩ ሀጥያቱን ይሸከማል
ቤዛዊት መንገድ ላይ ወደ እስር ቤቱ አቅራቢያ ስትደርስ ካገኘችዉ ጥሩ ምግብ ይሰራሉ ብላ ካሰበችበት ምግብ ቤት ገብታ ለፍፁም በገዛችዉ ሰፊ የምግብ መያዣ ምግብ አስቋጠረችለት
ደስ እያላት ነው በልቧ ፍፁምን ዛሬ እንደምታገኘዉ እንደምታዋራዉ እርግጠኛ ሆናለች።
ዘመድ መጠየቅያዉ ቦታ ላይ ቆማ የፍፁምን ሙሉ ስም ተናግራ መጠበቅ ጀመረች
ፍፁም ከላይ የተጣበቀ ቲሸርት ከስር ያረጀ ቁምጣ በሲሊፐር ለብሶ ሲመጣ በርቀት ተመለከተችዉ ልቧ እየተረበሸ ነዉ አሳዘናት የሴትነት አንጀቷ ባሀሪዋም እሩሩ ስለሆነች ሆድ ብሷት እንባ ማንባት ጀምራ ሲያየኝ እሱም ይጨነቃል ብላ አስባ እንባዋን ወድያዉ ጠራረገች።
የያዘችዉን ምግብ ፖሊሶቹ ፊት ለፊታቸዉ እንድትጎርስ አዘዟት እየጎረሰች ፍፁምን በከርታታ አይኗ እያየችዉ ነዉ ፍፁም አንገቱን ደፍቶ መሬት መሬቱን እያየ ምግቡን በግዴለሽነት ተቀብሏት
መሬት ላይ አስቀምጦ በጨረፍታ እያያት
"ለምን ተቸገርሽ ለኔ ብለሽ መልፋት የለብሽም እኔ የብዙ አመት ፍርደኛ ነኝ..."
የጀመረላትን ሳታስጨርሰዉ
"ሁሌም ቢሆን እጠብቅካለሁ ሁሌም"
ቅድም ያስቆመቻቸዉ እንባወቿ መፍሰስ ጀመሩ።
"አስራ ምናምን አመት..."
አለና የፌዝ ሳቅ ሳቀ
ፍፁም እራሱ ማስረሻ ካዋራዉ ጀምሮ ፀባዩ እየተቀያየረ ነበር ዉስጡ ሰላም እየተሰማዉ አደለም
እሱ በእስር እየበሰበሰ የወጣቷን የቤዛዊትን ህይወትም የቁም እስር ዉስጥ አትክተተዉ የሚል እርኩስ መንፈስ ልቡ ዉስጥ ማደግ እየጀመረ ነበር መንፈሱ ህፃን ስለሆነም እያነጫነጨዉ ነዉ።
"እንዋደድ የለ አትወደኝም ስትል ጠየቀችው ?"
ቤዛዊት አይን አይኑን እያየች
"እወድሻለሁ"
አላትና ጥቂት አስቦ
"ነብሰ ገዳይ ሰው ግን ላንቺ አይጠቅምሽም ሌላ አዲስ ህይወት መጀመር ትችያለሽ አልቀየምሽም ባንቺ ደስተኛ ነኝ ሁለተኛ ግን እኔ ጋር እንዳትመጪ"
አላትና አይኗን ላለማየት እየተጣደፈ ሳይሰናበታት ወደ እስር ቤቱ አመራ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ምእራፍ_ሁለት ( #ክፍል_አራት)
፡
፡
#በክፍለማርያም
..ፍፁም ወረቀቱን ገልጦ ስለቤዛዊት እና ስለሱ መከራ የበዛበት የፍቅር ታሪክ መፃፉን ተያይዞታል
ህመሙ እየተሻለዉ ስለሆነ ጥሩ ስሜት ዉስጥ ነዉ ስላለፈዉ ታሪክ እያሰበ ይፅፋል አስደሳች ጊዜወቹ ታዉሰዉት ፊቱ ላይ ደማቅ ፈገግታ እየተነበበ አእምሮዉ ላይ ያለዉን ከወረቀቱ ጋር እያዋሀደዉ ነዉ።
እንደምትወደዉ የነገረችዉን ቀን አስታወሰ ፅፋ የሰጠችዉ ወረቀት ዉል አለበት የተጣሉበትን ቀን መሀል ላይ ፍቃዱ መሀላቸዉ ገብቶ የእህቱን ፎቶ ሚስቱ ናት ብሎ ያወራ ቀን የተፈጠረዉን ሲያስታዉስ የሚፅፉት እጆቹ መንቀጥቀጥ ጀመሩ
ለቤዛዊት ሊያስረዳት ዉሸት መሆኑን ሊያብራራላት ሲጣደፍ መኪና የገጨዉን ሲያስታዉስ መፃፍ ስላልቻለ እስኪቢርቶዉን ወረቀቱላይ ጥሎ በዝምታ ተቀመጠ
ከጎኑ አብሮት የታሰረዉ ማስረሻ የተባለ ታሪሚ የፍፁምን ሁኔታ በአይኖቹ ሲከታተል ስለነበረ
"ምን እየፃፍክ ነዉ ወዳጄ?"
ሲል ለዉቀት መከላከያ ብሎ ዉሀ ዉስጥ ነክሮ አናቱ ላይ ያስቀመጠዉን ፎጣ እያወረደ
ፍፁም የጠየቀዉን ልጅ ትኩር ብሎ ተመለከተዉ ማስረሻ ቀጠን ብሎ ቀዉላላ የሚባል ወጣት ነዉ አይኖቹን ሲያስተዉላቸዉ ከተረገመዉ ፍቃዱ ጋር ተመሳሰሉበት
ለመጀመርያ ግዜ ከተቀመጠበት ተነስቶ ጮሀ
"ምን አገባት ምን አገባህ"
ደም ስሮቹ ተገታትረዉ ንዴት እያንቀጠቀጠዉ መናገሩን ተያያዘዉ
"ለምን አተወኝም ተዉኝ ተዉኝ"
እጆቹን እያወራጨ ወደ ማስረሻ ተጠጋዉ
ማስረሻ በፍፁም ሁኔታ እየተገረመ እና ጥሎት እንደመሄድ እያለ
"እብድ ድሮስ ነብሰ በላ መጨረሻዉ ማበድ ነዉ"
ብሎት ወደ ዉጪ ፍፁምን ትቶት ወጣ።
ፍፁም ግን ማስረሻ የተናገረዉ ንግግር አይምሮዉ ላይ እያቃጨለበት ነበር
"ነብሰበላ ነብሰ በላ ማበድ ማበድ"
እዉነት ነዉ የሰዉ ደም ወደ ሰማይ ይጮሀል ገዳይም የሰላም እንቅልፍ አያገኝም ማንም መጥፎ ሰው ቢሆን እንኳን የፈጠረዉ ፈጣሪ በሞት ካልወሰደዉ በቀር በሰዉ ቢገደል
ገዳዩ ሀጥያቱን ይሸከማል
ቤዛዊት መንገድ ላይ ወደ እስር ቤቱ አቅራቢያ ስትደርስ ካገኘችዉ ጥሩ ምግብ ይሰራሉ ብላ ካሰበችበት ምግብ ቤት ገብታ ለፍፁም በገዛችዉ ሰፊ የምግብ መያዣ ምግብ አስቋጠረችለት
ደስ እያላት ነው በልቧ ፍፁምን ዛሬ እንደምታገኘዉ እንደምታዋራዉ እርግጠኛ ሆናለች።
ዘመድ መጠየቅያዉ ቦታ ላይ ቆማ የፍፁምን ሙሉ ስም ተናግራ መጠበቅ ጀመረች
ፍፁም ከላይ የተጣበቀ ቲሸርት ከስር ያረጀ ቁምጣ በሲሊፐር ለብሶ ሲመጣ በርቀት ተመለከተችዉ ልቧ እየተረበሸ ነዉ አሳዘናት የሴትነት አንጀቷ ባሀሪዋም እሩሩ ስለሆነች ሆድ ብሷት እንባ ማንባት ጀምራ ሲያየኝ እሱም ይጨነቃል ብላ አስባ እንባዋን ወድያዉ ጠራረገች።
የያዘችዉን ምግብ ፖሊሶቹ ፊት ለፊታቸዉ እንድትጎርስ አዘዟት እየጎረሰች ፍፁምን በከርታታ አይኗ እያየችዉ ነዉ ፍፁም አንገቱን ደፍቶ መሬት መሬቱን እያየ ምግቡን በግዴለሽነት ተቀብሏት
መሬት ላይ አስቀምጦ በጨረፍታ እያያት
"ለምን ተቸገርሽ ለኔ ብለሽ መልፋት የለብሽም እኔ የብዙ አመት ፍርደኛ ነኝ..."
የጀመረላትን ሳታስጨርሰዉ
"ሁሌም ቢሆን እጠብቅካለሁ ሁሌም"
ቅድም ያስቆመቻቸዉ እንባወቿ መፍሰስ ጀመሩ።
"አስራ ምናምን አመት..."
አለና የፌዝ ሳቅ ሳቀ
ፍፁም እራሱ ማስረሻ ካዋራዉ ጀምሮ ፀባዩ እየተቀያየረ ነበር ዉስጡ ሰላም እየተሰማዉ አደለም
እሱ በእስር እየበሰበሰ የወጣቷን የቤዛዊትን ህይወትም የቁም እስር ዉስጥ አትክተተዉ የሚል እርኩስ መንፈስ ልቡ ዉስጥ ማደግ እየጀመረ ነበር መንፈሱ ህፃን ስለሆነም እያነጫነጨዉ ነዉ።
"እንዋደድ የለ አትወደኝም ስትል ጠየቀችው ?"
ቤዛዊት አይን አይኑን እያየች
"እወድሻለሁ"
አላትና ጥቂት አስቦ
"ነብሰ ገዳይ ሰው ግን ላንቺ አይጠቅምሽም ሌላ አዲስ ህይወት መጀመር ትችያለሽ አልቀየምሽም ባንቺ ደስተኛ ነኝ ሁለተኛ ግን እኔ ጋር እንዳትመጪ"
አላትና አይኗን ላለማየት እየተጣደፈ ሳይሰናበታት ወደ እስር ቤቱ አመራ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏