አትሮኖስ
286K subscribers
117 photos
3 videos
41 files
566 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_አስር


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

///

አለም በረጅሙ ተነፈሰችና "እናቴ እዚህ አካበቢ ነው የተገደለችው አይደል?"

"ትክክል እዚህ ነው የሞተችው" ብሎ በቁጣ መለሰላ፡፡

"የት? የትኛው ጋጣ አካባቢ?"

ዝም አላት…
‹‹ኩማንደር ሬሳዋን የት እንዳገኘህ አሳየኝ” ስትል ተማፀነችው፡፡

በረድፍ ካሉት የፈረስ ጋጣዎች ሁለተኛ ጋጣ ላይ ወሰዳትና። "እዚህ ነው የሞተችው"ብሎ ነገራት፡፡
አለም ሙሉ በሙሉ ደንዝዛ ቆመች፣ ከዚያም ወደ ገመዶ እስክትቀርብ ድረስ በዝግታ ወደፊት ሄደች። ወደ ጋጣው ዞረች። በውስጡ ምንም ፈረስ ሆነ ድርቆሽ አልነበረም, ወለል የተሸፈነው በጎማ ብቻ ነው. በሩ ተወግዷል ..ክፍት ነበር"ያ አደጋ ከተፈጠረ ጀምሮ በዚህ ጋጣ ውስጥ ፈረስ ገብቶበት አያውቅም?።"ስትል ጠየቀችው፡፡

በንቀት፣ "ጋሽ ፍሰሀ ስሜታዊ ስለሆነ ይሄን ውሳኔ ወስኗል›› አላት።

አለም በደም የተጨማለቀ አስከሬን በጋጣው ውስጥ እንደተጋደመ በምናቧ አሰበችና ..ተንቀጠቀጠች፡፡ ጠያቂ አይኖቿን ወደ ገመዶ አነሳች።ቆዳው በጉንጩ አጥንቶቹ ላይ በደንብ የተለጠጠ ይመስላል፣ ፡፡
ወንጀሉን የተፈጸመበትን ቦታ መጎብኘት ያሰበችውን ያህል ቀላል አልነበረም።"ስለ ጉዳዩ በዝርዝር ንገረኝ እባክህ?››አለችው፡፡
እያመነታ፣

“በጎኗ ተኝታ ነበር፣ ጭንቅላቷ በዚያ ጥግ ላይ ነበር፣ እግሮቿ እዚህ ነበሩ” እያለ በዝርዝር አስረዳት፡፡ባደረገው ቦቲ ጫፍ አንድ ቦታ እየነካ፡፡" በደም ተሸፍና ነበር፤ፀጉሯ በደም ተነክሮ ነበር… በሁሉም ቦታ ላይ ደም ነበር."

"ስንት ሰአት ነበር?" ብላ ጠየቀች።

" ሳገኛት?"

‹‹አዎ››

"ንጋት ላይ ነበረ. 12 ሰዓት ከሰላሳ አካባቢ."

"በዚያ ቀን አንተ እዚህ ምን ታደርግ ነበር?"

"ብዙውን ጊዜ ወደቢሮ ከመሄዴ በፊት ወደእዚህ መጥቼ ፈረሶቼን አይቼና ምግብ እንደተሰጣቸው አረጋግጬ ነበር የምሄደው››

"ሌሊቱን ሙሉ ቤትህ ነበርክ ?"

"ተጨማሪ መልስ ከፈለግሽ ፣ ጉዳዩን ለፍርድ ቤት በኩል አቅርቢው።" "እንደዛ አቅጃለሁ."

ወደ ኃላዋ ዞረችና ወደፊት ተንቀሳቀሰች…ከኃላ ተጠጋት፣ ክንዷን ይዞ ወደ እሱ አስጠጋት። ከባድ እና ጠንካራ ወንድ ነው። "ወ.ሪት አለም" በብስጭት እና ትዕግስት በማጣት አጉረመረመ

"ብልህ ነሽ… ይህን ጉዳይ ተይው። ካላደረግሽው ግን አንድ አካል ሊጎዳ ይችላል።"

"ማለት?"

ሰውነቱን ወደ እሷ ይበልጥ አቀረበ።‹‹ ሴትን የመግደል አቅም ነበረው?›› ስትል እራሷን ጠየቀች…በአጠቃላይ ለሴቶች ዝቅተኛ አመለካከት ያለው ይመስላል፤ነገር ግን እንደ ጁኒየር ሁሉ እሱም ሰሎሜን ይወዳት ነበር. እሷም በአንድ ወቅት እሱን ማግባት ትፈልግ ነበር። ምናልባት ገመዶን ጨምሮ ሁሉም ሰው ሰሎሜ ጎበና የተባለ ሌላ ሰው አግብታ እሷን እስክትፀንስ ድረስ እንደሚጋቡ ያስብ ይሆናል።አለም ገመዶ በማንኛውም ሁኔታ ሰሎሜን ሊገድላት እንደሚችል ማመን አልፈለገችም፤ነገር ግን እሱ ጨካኝ፣ ትዕቢተኛ፣እንደሆነም መካድም አልቻለችም ። ገዳይ ግን?አይመስልም። ወይም እሷ ሁልጊዜም ለፈርጣማ ሰውነትና ጥቋቁር ሰርሳሪ አይኖቹ ላላቸው ወንዶች ደካማ ስሜት ስላላት ይሆናል።

‹‹እናቴን ማን እንደገደላት እና ለምን እንደገደላት እስካውቅ ድረስ ይህን ምርመራ የማቋረጥ ሀሳብ የለኝም። የእናቴን ገዳይ ለማወቅ ህይወቴን በሙሉ ጠብቄአለሁ። አሁን እዚህ ደርሼ ተስፋ አልቆርጥም"

አለም ከጋጣው በወጣችበት ደቂቃ ኩማንደሩ የእርግማን መአቱን አዥጎደጎደ ።ከቀናት በፊት በአቶ ፍሰሀ ከስራው የተባረረው ሙስጠፋ በአቅራቢያው በሚገኝ ጋጣ ውስጥ ተደብቆ የሚያወሩትን ሁሉ ሰምቷቸው ነበር። በቦታው የተገኘው በአጋጣሚ እንጂ ንግግራቸውን ለማዳመጥ አስቦ አልነበረም። ብቸኝነት ስለተሰማውና ግራ ስለተጋባ ነበር በጨለማ ውስጥ ጭብጥብጥ ብሎ ሲተክዝ የነበረው… ከስራ ስላባረረው የቀድሞ አሠሪው እያሰላሰለ እንዴት ቂሙን እንደሚወጣ ማሰብ ብቻ ነበር የሚፈልገው። አሁን ግን በአጋጣሚ ያላሰበውን የኩማንደሩን እና የአለምን ውይይት ቃል በቃል ሰምቷል፡፡ እና የሰማው ነገር ደግሞ ለእሱ ልክ ከሰማይ እንደወረደ መና ነው የቆጠረው ፣ እሷ በደንብ የሚያውቃት የሰሎሜ ሴት ልጅ መሆኗን አውቋል፣ እዚህ የተገኘችው የእናቷን ግድያ ለመመርመር እንደሆነ በመስማቱ ተደንቋል። አቶ ፍሰሀ ላይ በቀሉን ለመወጣት ወርቃማ እድል እንዳገኘ ተሰምቷታል እና ያ የማይረባ ልጁንም ደህና አድርጎ ያጠፋዋል። ወደ ሠላሳ ዓመታት ጉልበቱን አንጠፍጥፎ አገልግሎት ነበር።ደህና፣ በመጨረሻ እድል ለሙስጠፋ ፈገግ እንዳለችለት ገባው ፡፡እሱ በትክክል ካርዶቹን መጫወት ከቻለ በመጨረሻ የተወሰነ ገንዘብ ሊያገኝ እንደሚችል  አሰበ፡፡ የአሁኑ አዲሷ ሚስቱ ገንዘብ ስለሌለው እያመነጫጨቀችው ነው…እንደውም ከቤቷ ገፍትራ ወደበረንዳ ልትጥለው ቋፍ ላይ እንደሆነች ተረድቷል….ታዲያ በዚህ ሚስጥር የሆነ ገንዘብ ማግኘት ከቻለ ሀሳቧን እንደሚያስቀይራት እርግጠኛ ነው፡፡

ኩማንደሩ ስራውን ጨርሶ ጋጣውን ለቆ እስከወጣበት ጊዜ ድረስ በትዕግሥት ማጣት ባለበት ተወሽቆ ነበር ያሳለፈው።ሙስጠፋ ትኩስ ገለባ ውስጥ የተጠቀጠቀበት ጋጥ ከመውጣቱ በፊት በአካባቢው ሌላ ሰው እንደሌለ ለማረጋገጥ ብዙ ጊዜ ጠብቋል።ከዛ ቀጥታ በጥላ ከተሸፈነው ኮሪደር ወርዶ አካባቢውን ለቆ ወደከተማ ሔደና ሁለት መለኪያ አረቄ ጠጥቶ ራሱን ካበረታታ በኃላ ስልኳን ለማግኘት ምን ማድረግ እንዳለበት ማሰብ ጀመረ….ግን በከተማ ውስጥ እሷን የሚያውቁ ሰዎች በቁጥር ስለነበሩ ቀላል ስራ አልነበረም….እንምንም በሁለተኛው ቀን ማግኘት ቻለና በኤርገንዶ ስልኩ ደወለላት…፡፡ ከአምስት ጥሪ በኃላ ስልኩ ተነሳ፡፡

"ወ.ሪት አለም ነሽ?"

"አዎ ማን ልበል?"

"ማወቅ አያስፈልገሽም ..እኔ አውቅሻለሁ እና ያ በቂ ነው።"

ግራ መበጋባት‹‹አልገባኝም ?" አለችው፡፡
"ስለ እናትሽ ግድያ ሁሉንም አውቃለሁ።"

ሙስጠፋ በድንገት ዝምታ ውስጥ በመግባቷ እየተደሰተ ..እስክታገግም ጠበቃት፡፡ ለእሷ ሚያደነዝ አይነት ድብዳ ዜና ነው የሆነባት፡፡

‹‹እየሰማሁ ነው።››አለችው፡፡

‹‹አሁን ማውራት አልችልም.፡፡"

‹‹ለምን አይሆንም?"

‹‹ስለማልችል ነው ..ጉዳዩ አደገኛ መሆኑን የምታውቂ መሰለኝ።››

በስልክ ከእሷ ጋር ለመግባት አደገኛ እንደሆነ አስቦል… አንድ ሰው ሰምቷት ለአቶ ፍሰሀ ወይም ለኩማንደሩ ሹክ ሊላቸው ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት አለው፡፡

‹‹መልሼ እደውልልሻለሁ።"አላት፡፡

‹‹ግን "

‹‹መልሼ እደውልልሻለሁ አልኩሽ እኮ…ስልኬን ጠብቂ…ደህና ሁኚ።››

ሙስጠፋ እሷ በምትገደልበት ጊዜ በቦታው ነበር.. እርሱ ጣልቃ ሳይገባ በተደበቀበት ሆኖ ሲመለከት ነበር ።ያንን ምሽት እንደ ትላንትናው የሆነውን ሁሉ ያስታወሰ። ይህን ሁሉ ጊዜ በሚስጥር ነበር ያያዘው። አሁን ግን የሚያወራበት ጊዜ መድረሱን አውቋል ። እናም ስለ ጉዳዩ ሁሉ ለዐቃቤት ሕጓ ለመናገር እስከ ሞት ድረስ ክፍያ ሊያስከፍለው እንደሚችል ያምናል…ግን ደግሞ ጥሩ ገንዘብም ሊያገኝበት የሚችልበት እድልም ሰፊ ነው፡።
/////
44👍5
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_አስራ_አንድ


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ


///

ፀሀፊዋ አለምን አቁማ ወደዳኛው ቢሮ ተራማዳ በራፉን በጥንቃቄ አንኳኳች እና ወደውስጥ ገባች…ብዙ ሳተቆይ ተመልሳ ወጣችና ወደአለም ቀርባ …በአጭሩ

‹‹ሊያይሽ ተስማምቷል ››አለቻት፡፡

"አመሰግናለሁ።" አለችና እሷን አልፋ ወደ ክፍሉ ገባች።

"ወ.ሮ አለም …በዚህ ጊዜ ስለምንድነው የምታናግሪኝ?" ዳኛ ዋልልኝ ኮቱን ከመስቀያው ላይ እየጎተተ ነበር የሚያናግራት። "ያለ ቀጠሮ ሰው ቢሮ የመግባት መጥፎ ልማድ ያለሽ ይመስላል። እንደምታየው እኔ ልወጣ ነው። ልጄ ስርጉት ያለ እኔ እራት መብላት አትወድም እና እሷን ማስጠበቅ ለእኔ አሳፋሪ ነው።"

"ሁለታችሁንም ይቅርታ እጠይቃለሁ ክቡር ዳኛ… ለፀሀፊዎ እንደነገርኩት ጉዳዬ በጣም አስቸኳይ ስለሆነብኝ ነው ።"

"እሺ…ልስማው?"

"መቀመጥ እንችላለን?"

" ቆሜ መስማት እችላለሁ …ምን ልትነግሪኝ ፈልገሽ ነው?"

"የእናቴ አስከሬን ተቆፍሮ እንዲወጣ እና  ዳግም የፎረንስክ ምርመራ እንዲደረግበት የፍርድ ቤት ትዕዛዝ እንዲሰጡልኝ እፈልጋለሁ."

ዳኛው ቀስ ብሎ ወንበሩ ላይ ተቀመጠ። አለም ግልፅ የሆነ ጭንቀት ተመለከተችበት።

"ይቅርታ፣ ምን አልሺኝ?፧"

"ክቡር ዳኛ  ያልኩትን እንደሰሙኝ አምናለሁ፣ ግን ጥያቄዬን መድገም አስፈላጊ ከሆነ፣ አደርገዋለሁ።"

ዳኛው  እጁን አወዛወዘ። "አይ. ቸሩ ጌታ አይሆንም. አንድ ጊዜ መስማት በቂ ነው…ለምን እንዲህ አይነት አስቀያሚ ነገር ማድረግ ፈለግሽ?"

"የመፈለግ ጉዳይ ሳይሆን ግድ ሆኖብኝ ነው, በጣም  አስፈላጊ ነው ብዬ ባላምን ኖሮ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ አልጠይቅም ነበር."

"አስቲ ተቀመጪና…  ምክንያቶችሽን አስረጂኝ።››

"እናቴ ላይ ወንጀል ተፈጽሟል ፣ነገር ግን ትክክለኛው ፍርድ ተገኝቷል ብዬ አላምንም ።"

"እንደዛ ማድረግ አትችዬም " ብሎ ጮኸ።
"አልሰማሽም።ከአመታት በኃላ ድንገት ከመሀከላችን ተገኘሽ፣ ወዲያው መሠረተ ቢስ ውንጀላ ይዘሽ ትረብሺኝ ያዝሽ፣ ለበቀል ቆርጠሻል።"

"ይህ እውነት አይደለም" ስትል ለመከላከል ሞከረች ፡፡ " ለመሆኑ ሀለቃሽ ግርማ ስለዚህ ጉዳይ ምን ይላል?"

"አሱ ለጊዜው የለም ..ለጥቂት ቀናት እረፍት ወሰዶ ወደ አዲስአበባ የሄደ ይመስኛል።›› ዳኛው ተናደደ።

" ለማንኛውም ጥያቄሽ … ጥሩ ሀሳብ አይመስለኝም››

" ክቡር ዳኛ ማስረጃ እንድፈልግ ይፈቅዱልኛል?"

"ምንም ማስረጃ አታገኚም" ሲል አፅንዖት ተናገረ፡፡

"ከእናቴ አስከሬን የተወሰነ መነሻ ሚሆነን መረጃ ልናገኝ እንችላለን."

" የተገደለችውና ሬሳዋ የተገኘው እኮ ከዛሬ ከሃያ አምስት ዓመታት በፊት ነበር ።"
"በዚያን ጊዜ ለሬሳ ምርመራ ለማድረግ ቴክኖሎጂዎች አልነበሩም… ..በአሁኑ ጊዜ ግን ነገሮች የተለዩ ናቸው፡፡እኔ በግሌ ጎበዝ የተባለ የፎረንሲክ ስፔሻሊስት አውቃለሁ።አሁን ለሚከሰቱ የወንጀል ድርጊቶች በተደጋጋሚ ጊዜ ከእሱ ጋር የመስራት እድል ነበረኝ …እሱና ጎደኞቹ በጣም ውጤታማ ናቸው ..በዛን ወቅት ባለው ቴክኖሎጂ ሊገኝ ያልቻለ የሆነ ነገር ሊያገኝልን እንደሚችል ዋስትና እሰጥዎታለሁ።››

"ጥያቄሽን እንደጥያቄ እወስደዋለሁ።››

"መልሱ ለዛሬ ማታ ቢደርስልኝ ምስጋናዬ ከፍ ያለ ነው ።"

" ይቅርታ ወ/ሪት አለም ማድረግ የምችለው በአንድ ጀምበር አስብበት እና በጠዋት መልሱን እሰጥሻለው።እስከዛው ሀሳብሽን ለውጠሽ ጥያቄውን እንደምትሰርዢ ተስፋ አደርጋለሁ።"

"አላደርገውም።››

ዳኛው ከተቀመጠበት ተነሳ። "ደክሞኛል፣ በዛ ላይ ርቦኛል፣ እናም በዚህ የማይመች ቦታ ላይ ስላስቀመጥሺኝ ተበሳጫችቻለሁ።" የክስ አመልካች ጣት አነጣጥሮባት። "እኔ እንደህ አይነት የተጨመላለቀ ነገር አልወድም."አላት፡፡

" ይህ በጣም አስፈላጊ ባይሆን እኔም አላደርገውም ነበር."

"አስፈላጊ አይደለም."

"እኔ ደግሞ እንደሆነ አምናለሁ" ስትል በግትርነት መለሰች።

" አሁን፣ በቂ ጊዜዬን ወስደሻል። ይሄኔ ልጄ ስርጉት ተጨንቃለች።››

‹‹ ደህና ይሁኑ ብላ ።"ከክፍሉ ወጣች።
///
አለም ቀጥታ  ወደመኪናዋ አመራችና ወደቤቷ ነው የነዳችው… መንገድ በትራፊክ ስለተጨናነቀ ወደቤቷ ለመመለስ ረጅም ጊዜ ነበር የወሰደባት፡፡

ክፍሏ ገብታ አልጋዋ ላይ ተዘርራ ትንሽ እረፍት ለመውሰድ ሞከረች…ከዛ ተነሳች….ማስታወሻዎቿን እንደገና ለመገምገም ሞከረች….ወዲያው ሰለቻት፡፡ ቴሌቪዥኑን ለመክፈት ወሰነች። ሪሞቷን አነሳችና ከፈተች፡፡ፊልም ላይ አደረገችውና ሰውነቷን ለመለቃለቅ ልብሷን አወላልቃ ወደሻወር ቤት ሄደችና መታጠብ ጀመረች……ታጥባ ከመጨረሷ በፊት አንድ ሰው በሯን ሲያንኳኳ ሰማች… እርጥብ ፀጉሯን በፎጣ ጠቅልላለች። ረጅምና ነጭ ካባዋን አደረገችና እና ወገቧ ላይ ያለውን መቀነት ለማሰር እያስተካከለች ወደሳሎን ሄደችና በበራፉ ቀዳዳ በማጮለቅ ማንነቱን ለማረጋገጥ ሞከረች፡፡

የሰንሰለት መቆለፊያው እስከሚፈቅደው ድረስ በሩን ከፈተችው "እንኳን ደህና መጣህ ኩማንደር ምነው በሰላም?"

ኮስተር ብሎ"በሩን ክፈቺ" አላት

"ለምን?"

" ካንቺ ጋር መነጋገር አለብኝ።"

"ስለ ምን?"

‹‹ወደ ውስጥ ካስገባሺኝ እነግርሻለሁ።
አለም  አልተንቀሳቀሰችም."በሩን  ልክፈት  ወይስ  ምን?"እለች  ከራሷ  ጋር  ሙግት ገባች፡፡ግድግዳ ላይ የተንጠለጠለውን ሰዓት ተመለከተች….ለሶስት እሩብ ጉዳይ ይላል፡፡
"እዚያው ሆነህ ላናግርህ እችላለሁ።"

"በሩን ክፈቺ" ብሎ ጮኸ።

‹‹ሰውነቴን እየታጠብኩ ነበር."አለም ሰንሰለቱን አላቀቀችና በሩን ከፍታ ወደ ጎን ቆመች።

"አንድ ሰው እየጠበቅሽ ነበር?"

"አይደለም."

ኮፍያውን ከጭንቅላቱ አወለቀና ጠረጴዛው ላይ አስቀምጦ … ወደ ወንበር ሄዶ ተቀመጠ እና ወደ ቴሌቭዥን ስክሪን ተመለከተ፣ ልብስ ያልለበሱ ጥንዶች ተቆላልፈው ይሳሳማሉ ። ካሜራው የወንዱ ከንፈር ከሴቷ ጡት ጋር ሲጣበቅ እያሳየ ነው፡፡

"ስለአቋረጥኩሽ መናደድሽ አይገርምም።››አላት ሪሞቱን አነሳችና አጠፋችው "አያየሁት አልነበር."
"በራፍሽን ለሚያንኳኳ ሰው ሁል ጊዜ በርሽን ትከፍቺያለሽ?"

"በዚህ ከተማ ውስጥ ከፍተኛው የህግ አስከባሪ የፖሊስ መኮንን ነህ። አንተን ማመን ካልቻልኩ ማንን ማመን እችላለሁ?ይልቅ በዚህ ማታ ለምን መጣህ? እስከ ጠዋት ድረስ መጠበቅ አልቻልክም?"

"ዳኛ ዋልልኝ ደውሎልኝ ስለጠየቅሽው የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ነገረኝ.››

በንዴት ሲመታ የነበረው ልቧ በፍጥነት ቀዘቀዘ፣ "በዚህ ከተማ ውስጥ የግል የሚባል ነገር የለም ማለት ነው?"ብላ ጠየቀች፡፡

"ብዙ አይደለም"

"በከተማው ክልል ውስጥ ያለ ማንኛውም ሰው የእናንተ ቡድን ሳይፈቅድለት ማስነጠስ የሚችል አይመስለኝም።"

"እንደፈለግሽ ተርጉሚው …አንቺ ዙሪያችን እየተሸከረከርሽ ጉድጓዳችንን ስትቆፍሪ ምን እንድናደርግ ጠብቀሽ ነበር?"

"የእናቴን መቃብር እንዲከፈት ማድረግ ትክክለኛ የግድያዋን መንሴ ለማወቅ ወሳኝ እርምጃ ነው ብዬ ባላስብ ኖሮ የምረበሻት ይመስላችኋል?" ሞቅ ባለ ስሜት ጠየቀች ።

‹‹አንቺ ቋሚንም ሆን ሟችን ከመረበሽ ውጭ ምን ስራ አለሽ?››

"አምላኬ ሆይ ጥያቄውን ማቅረብ እንኳን ቀላል ብሎኝ ያደረኩት ይመስልሃል? እና ዳኛው ከ አንተ እና ከሰዎች ሁሉ ጋር መማከር ለምን አስፈለገው?"

‹‹ለምን ብለሽ ትጠይቂያለሽ እንዴ?… ተጠርጣሪ ስለሆንኩ ነዋ?"

"ዳኛው በዚህ ጉዳይ ከአንተ ጋር መወያየቱ ሞያዊ ሥነ ምግባር የጎደለው ሽማግሌ መሆኑን ነው የሚያሳየው "

"እኔ እኮ የከተማው ፖሊስ አዛዥ ነኝ፣ አስታውሺ?"
39👍4
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_አስራ_ሁለት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

////

ኩማደሩ በቤት ውስጥ ምርጥ የተባለ ውስኪ እያለው በአውራ ጎዳናው ላይ ወደሚገኝ ግርግር ወደሚበዛበት መጠጥ ቤት ገብቶ ለመጠጣት ለምን እንደመረጠ ማወቅ አልቻለም። ምናልባት አዕምሮው ስለተጨናነቀ የተጨናነቀ ቦታ ፈልጎ ሊሆን ይችላል…እሾህን በእሾህ ለማክሰም ።የቡና ቤት አስተናጋጅ መጠጥ እንዲያመጣለት በምልክት ነገረው።ውስኪውን ወደ ብርጭቆው ሲቀዳ እያየ"አመሰግናለሁ" አለ ብቻውን እየቆዘመ ውስኪውን መሳብ ጀመረ፡፡

የጠጣው ውስኪው ቀስ በቀስ በሆዱ ውስጥ እሳት እንዲንቀለቀል እያደረገ ነው። ሲጠጣ ጨጓራውን በጣም ያመዋል….በዛም ምክንያት እርግፍ አድርጎ ለማቆም ሁሌ ይወስናል
..ግን ደግሞ ምክንያት ፈልጎ መጠጣቱን አይተውም…ቢሆንም እስኪሰክር ጠጥቶ አያውቅም በፍጽም የአባቱን ስህተት መድገም አይፈልግም…።ይህ የሌሊቱ የመጨረሻ መጠጥ እንደሚሆን ወሰነ …አዘዘ ፡፡ገና ህጻን ሳለ ነው እንደአባቱ መሆን እንደሌለበት ወስኖ የነበር ።የወህኒ ቤት ወፍ ወይም መነኩሴ፣ የጠፈር ተመራማሪ ወይም የመቃብር ጉድጓድ ቆፋሪ፣ የእንስሳት ጠባቂ ወይም ትልቅ አዳኝ ሆኖ ሊያድግ ይችላል፣ ነገር ግን አንድ መሆን የማይፈልገው ነገር ሰካራም መሆን ብቻ ነበር። ቀድሞውኑ በቤተሰቡ ውስጥ አንዱ ፕሮፌሽናል ጠጪ ነበራቸው እና ያ ደግሞ በጣም በቂ እንደሆነ ያምናል፡፡

"ሂይ ኩማንደር " የሚል ንግግር ከሀሳቡ አናጠበው፡፡

አንገቱን ቀና ሲያደርግ የለበሰችው ጅንስ ሱሪ የጠበባት እና ፊቷን በሚካፕ ያደመቀች ውብ ሴት ፊት ለፊቱ ቆማለች፡፡ይህቺን ሴት ከረጅም ጊዜ በፊት ጀምሮ ያውቃታል….፡፡

‹‹ሰላም ሮዛ።››

"ቢራ ትጋዘኛለህ ብዬ በማመን ነው ከጓደኞቼ ተነጥዬ የመጣሁት?"አለችው በተቃራኒው ኮሪደር ጥግ ከላይ ተቀምጠው ቢራ እየጠጡ ወደ ሚሳሳቁ ሁለት ሴቶች እየጠቆመችው፡፡

"ይቻላል።" አለና እንድትቀመጥ ካደረጋት በኃላ ትዕዛዙን ወደ አስተናጋጁ አስተላለፈ። ትኩር ብላ እያየችው ነው…ብቻውን ከእሷ ጋር መቀመጡ ምቾት ስላልሰጠው..‹‹ከፈለግሽ ጓደኞችሽን ጥሪያቸው››አላት፣ ከአንድ ሴት ጋር ለብቻ ከመሆን ከሶስት ሴት ጋር መሆን የተሻለ መስሎ ስለተሰማው ነው ሶስት ሴቶችን ለመጋበዝ ፍቃደኛ የሆነው፡፡

"አይ እነሱ የሞቀ ጫወታ ይዘዋል …አታስቸግራቸው" አለችው በማሽኮርመም ፡፡

"እየተዝናናችሁ ነው?››

"አዎ..እኛ ሴቶችም አንዳንዴ ወጣ ማለት አያስፈልገንም ትላለህ ?"

"አይ ጥሩ ነው፡፡"

ያዘዘችው ቢራ መጣላትና እየተጎነጨች ማውራቷን ቀጠለች‹‹ከቤት ተያይዘን ስንወጣ ፊልም ቤት ለመግባት ነበር..ግን እንደአለመታደል ሆኖ ፊልሙ ያየነው ስለሆነ ሀሳባችንን ቀየርንና ወደእዚህ ጎራ አልን…እና ደግሞ ደስ የሚለው አንተን አገኘሁህ››

‹‹ጥሩ ነው››ብሎ በአጭሩ መለሰላት፡፡

ሮዛ በቀላሉ የምትተወው አይነት ሴት አልነበረችም። "አይ ኩማንደር ሁል ጊዜ በራስህ ዙሪያ የምትሽከረከር ብቸኛ ፍጡር ነህ።"የሚል አስተያየት ጣል አደረገችበት

" ብቸኝነት ምርጫዬ ነው."ሲል መለሰላት

"አውቃለሁ ግን አሁንም…" እጇን አንቀሳቀሰችና ታፋው አካባቢ አስቀመጠች…በድንጋጤ ግራና ቀኙን አየና..ቀስ ብሎ እጇን  አንሸራቶ ነፃ ወጣ፡፡

"ምናልባት አንተን ማስደሰት እችል ይሆናል፡፡ " አለችው ፡፡ " እስቲ እናያለን››አላት፡፡

"ሰባተኛ ክፍል እያለሁ ጀምሮ በጣም ወድጄህ ነበር። መቼስ ያንን አታውቅም አይደል?"

"አይ ያንን አላውቅም ነበር."

"እሺ አሁን ነገርኩህ ። በወቅቱ አብዬት ፍሬ ትምህርት ቤት እየተማርን እያለ አፈቅርህ ነበር…..ግን ያኔ ተነጠቅኩ። የዚያች ልጅ ስም ማን ነበር? በእነ ጁኒዬር የከብቶች በረት ውስጥ የተገደለችው?"

"ሰሎሜ."

"አዎ. በእሷ ላይ ተመስጠህ ነበር አይደል? ወደሀይስኩል ስንገባም በግልፅ ፍቅረኛማቾች መሆናችሁን በይፋ አሳወጃችሁ…ከዚያም እኔም ተስፋ ቆርጬ አግብቼ ልጆች ወለድኩ." ለንግግሯ ፍላጎት እንደሌለው አላስተዋለችም።

"'በእርግጥ አሁን ባሌ ሞቷል፣ እና ልጆቼም እራሳቸውን ችለው ከቤት ወጥተዋል….አንተ ግን በዚ ሁሉ ዘመን ትራስ ታቅፈህ ታድራለህ…ነው ወይስ ሳልሰማ አገባህ?››

"አይመስለኝም።"

‹‹እስካሁን ››ወደ ፊት ቀረበችው፣

"ምናልባት እኔን እየጠበቅከኝ ይሆናል፡፡››ብላ ወንበሯን አንሸራታ ወደእሱ አቀረበችውና እላዩ ላይ ተለጠፈች፣እሱም ቀኝ እጁን ሰነዘረና"ጡቶቿን በእጁ እያሻሸ ምላሽ ሰጣት፡፡ የጡት ጫፎቿ በቲሸርትዋ ላይ ጠንካራ እና የተለየ ስሜት ፈጠሩበት። የሆነ ሆኖ፣ ግልጽነቷ ልክ እንደ አለም ንፁህ እና ባዶ ጣቶች ከነጭ ጋወን ውስጥ አጮልቆ እንደሚወጣ የሚያማልሉ አልነበረም።
በአለም ነጭ ካባ ስር ምን አለ? ብሎ እንዲያስብ ስለተገደደ አላስደሰተውም። ለምን ብሎ አሰበ።አለም በጣም ቆንጆ ነበረች. ከንፈሮቿ ተከፍለው እርጥብ ነበሩ። ሳይፈልግ ከአለም ከሜካፕ ነፃ ከሆኑ ከንፈሮች ጋር አነጻጽሯቸዋል፣ ነገር ግን አሁንም ሞቃት እና እርጥብ፣ የሚሳም እና ሴሰኛ፣እንደሆኑም እርግጠኛ ቢሆንም ምንም አይነት ሙከራ ሳያደርግ የቢራዋን ዋጋ የሚሸፍን ብር ከጂንስ ኪሱ ውስጥ በማውጣት ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠና

‹‹መሄድ አለብኝ"በማለት ከተቀመጠበት ተነሳ፡፡

"ግን እኔ ያሰብኩት…."

"ወደ ጓደኞችሽ ብትመለሺ ይሻላል፣ አለበለዚያ ፓርቲው ያመልጥሻል ።"አላት፡፡ ከጓደኞቾ ጋር በፊት ያልነበሩ አራት የሚሆኑ ወንዶች ተቀላለቅለዋቸው ሞቅ ያለ ቡድን መስርተው ነበር….፡፡

‹‹ሮዛ ስለየሁሽ ደስ ብሎኛል›› አለና ኩማንደር ኮፍያውን ዝቅ አድርጎ ፊቱን በከፈል ሸፈነና ወጥቶ ሄደ፣ ፡፡

እና ስለአለም መብሰልሰሉን ቀጠለ..ትናንት ማታ የእናቷ አስከሬን እንደተቃጠለ ሲነግራት ፊቷ ላይ የተመለከተው ሀዘን አሁንም ትዝ ይለዋል፡፡

"ዳኛ ዋልልኝ ያውቅ ነበር?" ስትል ጠየቀችው፡፡

"እነሆ እኔ የማውቀው ነገር ቢኖር እሱ ጠርቶኝ የፈለጋችሁት ነገር የማይቻል ነው ማለቱን ነው፣ "

"የእናቴ አስከሬን መቃጠሉን የሚያውቅ ከሆነ ለምን እራሱ አልነገረኝም?"

"የእኔ ግምት አንቺ ለዜናው የምታሳይውን ትዕይንት ማየት ስለማይፈልግ ይመስለኛል "

"አዎ" ብላ ትኩረቷን ሳትከፋፍል አጉረመረመች፣

"ሁከትን አይወድም። ››

በዝምታ ተመለከተችው። "ቆሻሻ ስራውን እንድትሰራለት ነው አይደል የላከህ ?። ››ነበር ያለችው፡፡

ኩማንደሩ አስተያየት ለመስጠት ፈቃደኛ ባለመሆኑ ጓንቱን አንስቶ አጠለቀ…ኮፍያውንም መልሶ አደረገ ።

"አሁን ደንግጠሻል ..ግን አይዞሽ ደህና ትሆኚያለሽ?"

"ደህና ነኝ።"

"ጥሩ ››

ጥቋቁር አይኖቿ በእንባ ተሞሉ እና አፏ በትንሹ ተንቀጠቀጠ። ድንገት ወደእሱ ተንቀሳቀሰችና እጆቿን ከወገብዋ ጋር አጣበቀች..እና ተሸጎጠችበት። ያን አጥር እንደገና ከመገንባቷ በፊት፣ እጆቹን አንሸራትቶ ወደ እሱ ጎተታት። እሷ ሞቃት ትንፋሽ እና ጥሩ መዓዛ ነበራት በሀዘኗ ውስጥ ደካማ ሆናለች. እጆቿ ሳይጨነቁ ወደ ጎን ተንጠልጥለዋል።

"ኦ አምላኬ እባክህ በዚህ ፈተና ውስጥ እንዳልፍ አታድርገኝ" ስትል በሹክሹክታ ተናገረች እና ጡቶቿ ሲንቀጠቀጡ ተሰማት። እንባዋን ሲንጠባጠብ በልብሱ አልፎ እስኪሰማው ድረስ ጭንቅላቷን ወደ እሱ አስጠጋች። ፀጉሯን የጠቀለለችበት ፎጣ ተንሸራቶ መሬት ላይ ወደቀ። ፀጉሯ እርጥብ ነበር። በወቅቱ እሷን መሳም እንደሌለበት ለራሱ እየተናገረ ነው… ነገር ግን ከንፈሩ ፀጉሯን ከዚያም የአንገቷ ስር ሽታን ወደውስጡ እየማገ ስለሆነ እየደነዘዘ ነበር፡።በዚያን ጊዜ፣ ከባድ የፍትወት ስሜት አቅበጠበጠው፣ እናም በጣም
42👍6
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

////
አለም መተኛት አቅቷት እየተገለበጠች ባለችበት ጊዜ ነበር ስልኩ የጮኸው፡፡ሰዓቱ እኩለ ለሊት በመጠጋቱ የተነሳ ጥሪው በጣም ነበር ያስደነገጣት ። የራስጌ መብራቱን በማብራት የስልኩን እጄታ አነሳችና ጆረዋ ላይ ለጥፋ ጎላ ባለ ድምፅ "ጤና ይስጥልኝ" አለች፡፡ቀደም ብሎ ስታለቅስ ስለቆየች ድምጿ የሻከረ ነበር
"ሰላም ››መለሰላት፡፡

"አወቅሽኝ ወ.ሪት አለም "

ልቧ በደስታ ዘለለ፣"አንተ እንደገና? በዚህ ውድቅት ለሊት ከእንቅልፍ ያስነሳኸኝ ደህና ነገር ልትነግረኝ እንደሆነ ተስፋ አደርጋለሁ" አለችው።እምቢተኛ ምስክሮች ብዙ ጊዜ የሚናገሩትን ነገር አስፈላጊነት ሲጠቀስላቸው ለመናገር እንደሚበረታቱ ከልምድ ታዝባለች፡፡

"ከኔ ጋር ድብብቆሽ አትጫወቺ …. ማወቅ የምትፈልጊውን በጠቅላላ አውቃለሁ። "

"ለምሳሌ ምን?"

"ለምሳሌ እናትሽን ማን እንደገደላት››

አለም አተነፋፈስዋን በመቆጣጠር ላይ ትኩረት አደረገች።

" ይመስለኛል ዜናው አስደምሞሻል››

"ታዲያ ንገረኝ ማን ነበር?"

"እመቤት ደደብ እመስልሻለሁ እንዴ? ኩማንደሩ ቀደም ሲል ስልክሽን አለማስጠለፉን በምን አውቃለው ?"

"ይመስለኛል….በጣም ብዙ ፊልሞችን አይተሃል?››

‹‹ተረቡን አቁሚና ይልቅ በፅሞና አድምጪኝ ….ነገ ማታ አንድ ሰዓት ሸዋበር የሚገኘው ደንበል ሆቴል እንገናኝ" በማለት ሰዓቱንና ቦታውን ነገራት፡፡

"እንዴት ላውቅህ እችላለሁ?"

"እኔ አውቅሻለሁ"

ሌላ ነገር ከመናገሯ በፊት ስልኩን ዘጋው። አለም በአልጋው ጠርዝ ላይ ለጥቂት ጊዜ ተቀምጣ ጨለማውን እያየች ደርቃ ቀረች። ልትጎዳ እንደምትችል የነገራትን የኩማንደሩ ማስጠንቀቂያ አስታወሰች። የእርሷ ምናባዊ አእምሮ በሴት ላይ ብቻ ሊደርስ የሚችለውን አሰቃቂ ነገር ሁሉ አስተናገደ። በተኛችበት ሆና በላብ ተጠምቀው ነበር።
///
የከተማው የፖሊስ አዛዥ እንፋሎት የሚትገለግበትን ቡናውን አንስቶ ጠጣ። ምላሱን አቃጠለው። ግን ግድ አልነበረውም። በጣም በከፋ መንገድ የካፌይን ማነቃቂያ ያስፈልገዋል
‹‹ስለማን ነው የምናወራው?›› ሲል በግል ቢሮው ደጃፍ ላይ ቆሞ የነበረውን ምክትሉን ጠየቀ ..

" ስለአቃቢ ህግ ፅ/ቤት ነው››

"ስለ ወ.ሪት አለም እያወራህ ነው ?" ምክትሉ መለሰ " አዎ ጌታዬ ስለእሷ ነው።" "እሺ ምን አዲስ ነገር አለ?"

"  የእናቷን  የሬሳ  ምርመራ  መዝገብ  አስወጥታ  ዠለመመርመር  ወደ  ተክለሀይማኖት ቤ/ክርስቲያን ሄዳለች ››

"ምን?"

"አዎ ጌታዬ እንዲከታተሏት የመደብናቸው ፖሊሶች  ናቸው ደውለው የነገሩኝ፡፡››

‹‹በል አሁኑኑ ደውልላቸውና ወደእነሱ እየመጣሁ እንደሆነ ንገራቸው››

ገመዶ ኮቱን ከተሰቀለበት አንስቶ ቢሮውን ለቆ ወጣ…፡፡ ትምህርት ቤቶችን እና አብዛኛዎቹን የንግድ ድርጅቶች እንዲዘጉ ያደረጋቸውን የፀጥታ ችግር ቢኖርም ግድ አል ነበረውም። ሰልፈኛውን እየሰነጠቀ እና ወንበር እያሳበረ ወደሆስፒታል ነዳው፡፡

"የት ነው ያለችው?" እንደደረሰ ኩማንደሩ ጮኸ፣..አንድ አነስተኛ ቢሮ መሰል ክፍል ውስጥ ቁጭ ብላ ከአስተዳዳሪው ጋር ስታወራ ተመለከታ…ወደእዛው ተንደርድሮ ሄደ፡፡
ምንም ፍቃድ ሳይጠይቅ ሰተት ብሎ ገባና " ምን እየሰራሽ ነው ?"አንቧረቀባት፡፡ "እንደምን አደርክ ኩማንደር"አለችው ለስለስ ብላ፡፡

"ጥያቄዬን መልሺልኝ?"

‹‹ምን እያደረኩ እንደሆነማ በደንብ ታውቃለህ?››

"በአንቺ ምክንያት ሴትዮዬ ስራዬን መስራት አልቻልኩም….ከተማዋ በበጥባጭ ጎረምሶች ተረብሻ ያንን ማረጋጋት ሲጠበቅብኝ እኔ አንቺን በየመቃብር ቤቱ እከታተልሻል። ለማንኛውም እንዴት እዚህ ደረስሽ?"

" እየነዳሁ።"

በንዴት በጠረጴዛው ላይ የተበተኑትን ፋይሎች አያመለከተ"ይህ ሁሉ ምንድን ነው?"ሲል ጠየቃት፡፡

" መዛግብት ነዋ…..እናቴ ስትቀበር ለአገልግሎት የተከፈሉ ካርኒዎች እና መሰል መረጃዎች ሊኖሩ ስለሚችሉ ያንን እያዩልኝ ነው፣ ፡፡

"አስገድደሽው ነው?::"

‹‹እኔ እንደዚህ ያለ ነገር አላደረኩም..እንዴት ነው ምታስበኝ…?ደፍሬ አባቶቼን የማስገድድ ይመስልሀል?."

" ታዲያ የፍተሻ ማዘዣ ፍቃደሽን አልጠየቁሽም?"

ካህኑ‹‹ልጆቼ ይቅርታ እስኪ እናንተ አውሩ እኔ መጣሁ››ብለው ከመቀመጫቸው ተነሱና ክፍሉን ለቀውላቸው ወጡ … ገመዶ ወደሷ ቀረበና በንዴት ክንዷን ጨምድዷ ያዘ፡፡

‹‹ምን እያደረክ ነው?››

‹‹ቄሱን የሆነ ነገር ብዬ ከማስቀየሜ በፊት ቀጥ ብለሽ ቦታውን ለቀሽ ውጪ››

‹‹ለምንድነው እንደዛ የምታደርገው?››

‹‹ነገርኩሽ እኮ..አሁን ተከትለሺኝ ትሄጂያለሽ ወይስ…የማደርገውን ቆመሽ ትመለከቻለሽ?››

ትኩር ብላ አየችው … ፊቱ እንደ ተራራ ሰንሰለታማና ወጣ ገባ ነው፣በአጭሩ ቋጥኝ ይመስላል፣ ነገር ግን እስካሁን ካጋጠሟት በጣም ማራኪ ወንዶች ውስጥ አንዱ ነው።አብረው በሚሆኑበት ጊዜ ሁሉ፣ ስለ እሱ፣ ስለ ሰውነቱ ታስባለች፡፡ የእሷ ለእሱ ያላት መስህብ ሥነ ምግባር የጎደለው እና ከዛም አልፎ እንዝላልነት እንደሆነ ታውቃለች። መጀመሪያ የእናቷ ፍቅረኛ ነበረ።ያንን በደንብ ታውቃለች ..ሆኖም ብዙ ጊዜ እሱን ለመንካት ትፈልግ ነበር። ትናንት ማታ በምታለቅስበት ጊዜ እንዲያባብላት ትፈልግ ነበር። ወደመኝታ ቤቷ ተከትሏት እንዲገባም ፈልጋ ነበር…ደግነቱ እሱ በተሻለ ብቃት እራሱን የመቆጣጠር ችሎታ ነበረው እና ምንም ሳያደርግ ትቷት ሄደ።

‹‹የሰሎሜ ሬሳ እንደተቃጠለ ነግሬሻለሁ።››
"አንተ እና ዳኛው  ጭንቅላታችሁን አንድ ላይ አድርጋችሁ እያሻጠራችሁ መሆኑን ማወቄ የተመቸኝ ይመስልሀል?።››

"ነገሮችን መገመት ያስደስትሻል?."

"ጁኒየር እናቴ ሬሳ መቃጠሏን ለምን አልነገረኝም?እንደተቀበረች ነበር የነገረኝ ››

‹‹እኔ እየዋሸሁሽ ይምስልሻል….?ለምን ብዬ?" " አስከሬኑ እንዳይወጣ ስለምትፈልግ ነዋ።"

"ሬሳው እንዳይወጣ ለምንድነው የምፈልገው? በእኔ ላይ ምን ለውጥ ያመጣል?"

ፍርጥም ብላ "የእድሜ ልክ እስራት" በማለት መለሰችለት፡፡ "የፎረንሲክ ሪፖርቱ አንተን ነፍሰ ገዳይ መሆንህን የሚያመለክት ፍንጭ ከሰጠን ወደወህኒ መወርወርህ የማይቀር ነው።››

" “አህ...” አለ..ደም ስሯቹ ሲግተረተር እየታዘበች ነው፡፡ "አንቺ ጠበቃ አይደለሽም, ጠንቋይ አዳኝ ነሽ."

"ወንጀል ባይኖር ኖሮ ያ እውነት ሊሆን ይችላል….ግን አንድ ሰው ወደዚያ በረት ውስጥ ገብቶ እናቴን ወግቶ ገድሏታል..እና እስከአሁን ለጥፋቱ የሚመጥን ቅጣት አላገኘም።››

"በእስክሪፕት ደረጃ ትክክል ነሽ" አለ እየተሳለቀ።

"ጋሽ ፍሰሀ ፣ ጁኒየር ወይስ እኔ የቀዶ ጥገና መሳሪያ ይዘን እናትሽን እንደወጋናት ነው ግምትሽ? ለምን በባዶ እጃችን አንገቷን አንቀን አንገድላትም??"

"ሁላችሁም ጎበዝ ስለሆናችሁ።ከመካከላችሁ ወንጀሉን የፈፀመው ሰው እንደዛ ያደረገው ወንጀሉን የአእምሮ ሚዛናዊ የተዛባ ሰው ያደረገው እንዲመስል ፈልጎ ነው።››

‹‹አመንሽም አላመንሽም …እኔ አላደረግኩም

"በብስጭት መለሰላት፡፡

"ታዲያ ማን እንዳደረገው ማወቅ አትፈልግም? ወይስ ነፍሰ ገዳዩ የምትወደው ሌላ ሰው እንዳይሆን ትፈራለህ ?"ስትል ሞጋች ጥያቄ ጠየቀችው፡፡

‹‹አይ ማወቅ አልፈልግም" ሲል በአጽንኦት መለሰላት፡፡

"እኔ ግን ገዳዩን እስካገኝ ድረስ ምርመራዬን አላቋርጥም..››

ሊመልስላት አፉን ሲከፍት አንድ ግራ እግራቸው ሸንከል የሚል አዛውንት አንድ ያረጀች መዝገብ ይዘው ወደውስጥ ሲገቡ ሲመለከት አፉን መልሶ ከደነ፡፡
43👍1
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_አስራ_አራታ


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

///

ስርጉት ወደአባቷ የጥናት ክፍል ስትገባ ። አባቷ ጠረጴዛው ላይ አቀርቅሮ አንድ ፋይል እያነበበ ነበር ››

"ዛሬ እረፍት የሆንክ መስሎኝ ነበር››

" አዎ ነበርኩ ግን አንዱ ማየት የሚገባኝ ጉዳይ ስለነበረ ይሄው እንደምታይኝ ፋይል እያገላበጥኩ ነው፡፡››

"በቅርብ በጣም ጠንክረህ እየሰራህ ነው.. ግን ደግሞ በጣም መጨናነቅ ይታይብሀል…ምነው ችግር አለ እንዴ."

"ያቺ የሰሎሜ ልጅ ነች"

"የሰሎሜ ሴት ልጅ? አሁንም እያስቸገረችህ ነው?"

‹‹የእናቷ አስከሬኑ እንዲወጣ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ፈልጋ ትናንት ቢሮዬ መጥታ ነበር።››

"አምላኬ!"

ስርጉት ባለማመን በሹክሹክታ ተናገረች።
"እና ምን አልካት?."

"ጥያቄዋን ውድቅ አደረኩታ."

"መልካም አድርገሀል "

"ምንም አማራጭ አልነበረኝም። አስከሬኑ ተቃጥሎል …ብትከፍትም በትንሽ የእንጨት ሳጥን የተቀመጠ አመድ ነው የምታገኘው››

"እና የእናቷ ሬሳ እንደተቃጠለ ስትሰማ ምን አለች?"

"አላውቅም …ኩማንደሩ ነው የነገራት ።, ሙሉ በሙሉ እንዳላመነችበት እገምታለሁ."

"ጋሽ ፍሰሀ እና ጁኒዬር ስለዚህ ጉዳይ ያውቃሉ?"

"እስከአሁን ድረስ እንደሚያውቁ እርግጠኛ ነኝ። ኩማንደሩ ይነግራቸዋል።"

ስርጉት"ምናልባት" ስትል አጉረመረመች። ለአንድ አፍታ በፀጥታ ማሰላሰል ጀመረች. "ታዲያ ምን ላመጣልህ..ሻይ ወይስ ቡና ..ቁርስ በልተሀል??"

"ስርጉቴ ፣ አመሰግናለሁ ምንም አልፈልግም….አሁን ይሄንን ፋይል መመርመሬን መቀጠል አለብኝ..ብቻዬን ተይኝ።"

" ይቅርታ ስላስጨነቅኩህ..አባዬ…በቃ  ቻው " ብላ ግንባሩን ሳመችና ቢሮውን ለቃ ወጣች፡፡

ስርጉት የጥናት ክፍሉን በጸጥታ ዘጋችለትና ወደ መኝታ ቤቷ አመራች፡፡ ጥሩ ስሜት አልተሰማትም።ስርጉት ሆዷን እየቆረጣት ነው ፡፡ዛሬ ጥዋት ነበር የወር አበባዋን የጀመረው።ምንም እንኳን እነዚህን ወርሃዊ ፍሰቶች በየወሩ መቀበል እና መሸኘት የግድ ቢሆንም የአርባዎቹ አጋማሽ ዕድሜዋ ልክ እንደ ታዳጊ ልጅ የሚያሰቃያት ቁርጠት የሚያሰለች ብቻ ሳይሆን አስቂኝ ሆናባታል። ይሄ ግማሽ እድሜዋን ያስተናገደችው የወርአበባ ሴት መሆኗን ማሳሰቢያ ብቻ ነበር። አንድም ልጅ መውለድ አልቻለችም፡፡

በህይወቷ ውስጥ ለልጅ የሚከፈል መስዋዕትነትና  እና ከልጅ የሚገኝ ፍቅር ተቋዳሽ ባለመኗ በየቀኑ ታዝናለች። አንዳንድ ሰዎች አዘውትረው እንደሚጸልዩ ሁሉ፣ ስርጉትም ለፈጣሪዎ ስለት ሁሉ ተስላ ነበር…ለዛውም ደጋግማ ..ግን ምንም ለውጥ እልነበረውም፡፡በቤቱ ውስጥ የሚሯሯጡ የሕጻናት ትናፍቃለች። ባሏ በለሊት ወደመኝታ ክፍሏ ገብቶ ጡቶቿን እየነካካ እና እረፍት ያጣ ገላዋን ረሀብ እንዲያረካላት ትፈልጋለች።ሶስተኛውን መሳቢያ ከፈተች እና የፎቶ አልበሙን አወጣች።በአክብሮት ከፈተችው። አንድ በአንድ እየገለጠች ማየት ጀመረች፡፡ ውድ ትዝታዎችን - ቢጫ ቀለም ያለው ጋዜጣ ከፎቶዋ ስር አለ፣አወጣችና አየችው….ስለሰሎሜ ግድያ የሚያትት ነው፡፡ .. ጨው ጨው የሚል እንባ ከአይኖቿ ፈሰሰ። በማህፀኗ ውስጥ ያለውን የባዶነት ህመም ለማስታገስ የእጇን ጭኖቾ መካከል ጨመረችና ጭብጥብጥ ብላ ተኛች፡፡
…///
አለም ከስራ ቀደም ብላ ወጣችና ለጁኒዬር ደወለችለት…

‹‹እንዴት ነሽ አሌክስ?››

ለስላሳና ማራኪ ድምፅ ነው …በዛ ላይ አሌክስ ብሎ ሲጠራት የተለየ ስሜት ነው የተሰማት፡፡

‹‹ሰላም ነኝ..ላገኝህ ፈልጌ ነበር››

‹‹ምነው? መክሰስ ልትጋብዢኝ ነው?››

‹‹ብጋብዝህ  ደስ ይለኝ ነበር…ግን ደግሞ አጣዳፊ ጉዳይ ነበረኝ…አንተን እና አባትህን ማግኘት ፈልጌ ነበር››

‹‹ምነው በሰላም?››

‹‹አይ በሰላም ነው ማለት እንኳን አልችልም..ግን ላገኛችሁ እፈልጋለው፡፡››

‹‹እንግዲው ሁለታችንም ቢሮ ነው ያለነው…የሶሌ ኢንተርፕራይዝ ህንፃን የት እንደሆነ ታውቂያለሽ?፡፡››

‹‹አዎ ..ወደዛው ልምጣ?››

‹‹ጥሩ… ነይ.. እጠብቅሻለው››

ስልኳን ዘጋችና ቀጥታ ወደእዛው ነው የሄደችው፡፡ከህንፃው ውጭ ጠብቆ ተቀበላትና ቀጥታ ወደ አባትዬው ቢሮ ይዞት ሄደ፡፡ጠረጴዛውን ከበው ከተቀመጡ በኃላ የንግግሩን ቅድሚያ ወሰደች…ቀጥታ ወደመጣችበት ጉዳይ ነው የገባችው፡፡

"ትናንት ዳኛ ዋልልኝን በድጋሚ አናግሬቸው ነበር።" አለም ሁለቱም ሰዎች ንግግሯን ተከትሎ ውጥረት ውስጥ ሲገቡ ተመለከተች፡፡

"ለምን ጉዳይ… ?" አቶ ፍሰሀ ጠየቀ።

"የእናቴን አስከሬን ለማውጣት ፈልጌ ነበር.››

"አምላኬ ሆይ፣ ለምን እንደዚህ አይነት ነገር ማድረግ ፈለግሽ? ››አቶ ፍሰሀ ደነገጠ።

" ለማንኛውም የጠየቅኩት ነገር የማይቻል ነው።ያንን እንደምታውቁት ደግሞ እርግጠኛ ነኝ… የእናቴ አስክሬን ተቃጥሏል።"

"ልክ ነው" አለ አቶ ፍሰሀ።
ጁኒዬር በስቃይ አይኖቹን ጨፈነ…

"አቶ ፍሰሀ በዛን ወቅት ሁሉን ነገር የወሰንከው አንተ ነበርክ ? በየትኛው መብትህ? አያቴ በህይወት እያለች አንተ እንዴት? ››

" አስከሬኗ የተቃጠለው ማስረጃ ለማጥፋት መስሎሽ ነው እንዴ?"

"አላውቅም!" ጮኸች እና ከተቀመጠችበት ተነሳች። ወደ መስኮቱ ሄደች እና ባዶውን ሰማይ ትኩር ብላ ተመለከተች።ከዛ ተመልሳ ወደእነሱ መጣችና ወንበሯ ላይ ተቀመጠች እና"ያደረግከው ያልተለመደ ነገር ነው..ማብራሪያ እፈልጋለው።"አለችው

"እኔ የፈለኩት አያትሽን ከኃላፊነት ለማላቀቅ ብቻ ነበር። ልጇ በእኔ መሬት ላይ ስለተገደለች ቢያንስ ማድረግ የምችለውን ማድረግ አለብኝ ብዬ አሰብኩ።አያትሽ በሀዘን አእምሮዋ ስለተጎዳ ልንከባከባት ብቻ ነበር የፈለኩት። ያደረኩት ነገር አጠራጣሪ ከመሰለኝ፣ ያ በጣም መጥፎ ነው ፡፡ ወጣቷ ሴት ፣ ዛሬም እንደገና ተመሳሳይ ሁኔታ ቢያጋጥመኝ የማደርገው ተመሳሳዩን ነው ››

‹‹እርግጠኛ ነኝ አያቴ በወቅቱ ላደረከው ነገር አድንቃህና አመስግናህ ነበር..እንደውም ሳስበው ይሄንን ሀገር ላቃ ወደአዲስአበባ መግባት እንደምትፈልግ ስትነግርህ ገንዘብ ሰጥተሀታል፡፡››
‹‹እሷ ነች የነገረችሽ….?አዎ አምስት ሺ ብር ሰጥቼት ነበር…››

‹‹በዛን ጊዜ 5 ሺብር እኮ ማለት የዛሬ መቶ ሺብር ነው፡፡››

‹‹አዎ በትክክል..ለዚህ ነው መመስገን እንጂ መወቀስ አይገባኝም የምልሽ፡፡››

ጁኒዬር ምንም ጣልቃ ሳይገባ የሁለቱን ምልልስ በትግስትና በጭንቀት እያዳመጠ ነው፡፡አለም ንግግሯን ቀጥላለች‹‹ይገርማል ….ቆይ እናቴ ምን ያህል ብትበድላችሁ ነው ትዝታዋንም ሆነ እሷን የሚያስታውሳችሁን ነገሮች ሁሉ ከከተማዋ ለማስወገድ ያንን ሁሉ መስዋዕትነት መክፈል የፈለጋችሁት?››

‹‹ነገ የምታፍሪበትን ነገር አትናገሪ..አያትሽ በወቅቱ በጣም አመስጋኝ ነበረች…ብዙ ?‹‹ታዲያ አሁን ከአመታት በኃላ እናቴን እናንተ እንደገደላችኋት ለምን ነገረችኝ?››

‹‹እሱ እኛንም ግራ ያጋባን ጉዳይ ነው…ምን አልባት በእርጅናዋ የተነሳ አእምሮዋ ሚዛኑን አጥቶ ነገሮችን በትክክል ማሳታወስ ተስኗት ይሆናል..አዎ ከዛ ውጭ ሌላ ማብራሪያ ሊኖረው አይችልም፡፡››

‹‹ቆይ እኔ ያልገባኝ…እንደምትሉት የእናቴ ሬሳ ከተቃጠለ..አመዱን በሳጥን አድርጎ መቅበሩ ለምን አስፈለገ…..?ምን ሊረባ?››

"መቼስ ሰሎሜ ዘሞዶች አሏት …ከዛ በላይም ልጅ አለቻት…ልጅቷ አድጋ እናትሽ ሞታለች ስትባል..የት ነው የተቀበረችው…?መቃብሯን ማየት እፈልጋለው ብትል ለእሷ ለማሳየት ታስቦ ነው…ይሄው እንደፈራነውም የእናቴ መቃብር የት ነው ብለሽ መጠየቅሽ አልቀረም፡፡››

‹‹በእውነቱ አርቆ አሳቢነታችሁ በጣም እያስደነቀኝ ነው፡፡››ስትል በምፀት ተናገረች፡፡
33👍9🥰1
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_አስራ_አምስት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ


///
አለም ወደ አፓርታማዋ  እደገባች የእጅ ቦርሳዋን እና ካፖርትዋን ወንበር ላይ አስቀመጠች
ዛሬ ከሰአት በኋላ ለዋናው አቃቢ ህጉ ደውላለት ነበር። እስካሁን እጇ ላይ ባስገባችው ግኝት ደስተኛ ሆኖ አላገኘችውም፡፡ ስራውና እርግፍ አድርጋ ወደ አዲስ አበባዋ እንድትመለስ ወይም እራሷን ካለፈው ታሪኳ ጋር እንድታስታርቅ ምርጫ አቀረበላት።እስከአሁን በሚጠበቀው ልክ ተጨባጭ ውጤት ማግኘት ያለመቻሏ የሱ ቅሬታ አንዱ ምክንያት ነበር። ዛሬ ማታ ባላት ቀጠሮ መሰረት ለዋናው አቃቢ ህግጉ የአይን እማኙን አግኝታ ያገኘችውን መረጃ ስታቀርብለት ስሜቱ ሙሉ በሙሉ እንደሚቀየር እርግጠኛ ነች።
ወደ መጠጥ ቤቱ የመኪና ማቆሚያ ቦታ በገባችበትን ቅጽበት ብዙም ተስፋ እንደማይሰጥ ማወቅ ነበረባት። አምፖሎቹ ቦግ ብልጭ ድርግም ከሚለው የሸዋ በር መጠጥ ቤቶች መካከል በአንዱ ነው የቀጠራት ። ከደረሰች በላ ወደ ውስጥ አልፋ ለመግባት በጣም አመንትታ ነበር።ግን ይሄ የያዘችውን ምርመራ ከስኬት ለማድረስ መክፈል ከሚገባት መስዋዕትነት መካከል አንዱ እንደሆነ ራሷን በራሷ አሳመነችና እግሮቾን እየጎተተች ወደውስጥ ገባች፡፡በክፍሉ ውስጥ ያለው እያንዳንዱ ሰው ትኩስ ስጋ እንዳየ ጥንብ አንሳ ወደ እሷ ተመለከቷት፡። የተወሰኑ ሴቶች ቢኖርም የእነሱ እይታ እንደውም ከወንዶቹ በተቃራኒ ሻካራ መስሎ ነው የተሰማት ፡፡ወደኋላ ዞራ ሁሉን ነገር እርግፍ አድርጋ ትታ መሮጥ ፈለገች ..ግን ያደረገችው ወደግራዋ ታጥፋ ኮርነር አካባቢ ወንበር ስባ መቀመጥ ነበር፡፡

አስተናጋጆ መጥታ

‹‹ ምን ልታዘዝ ስትላት"

‹‹እባክሽ ነጭ ወይን "ስትል አዘዘች፡፡
በስልክ ያናገራት እና ድምፁን ብቻ የሰማችው ሰው የትኛው እንደሆነ ለማወቅ ዓይኗን ከአንዱ አቅጣጫ ወደሌላው በማወናጨፍ ለመገመት ሞከረች ።ግን ….አይኗ ሲንከራተት እየተካታተሉ የነበሩ አንዳንድ ወንዶች ሁኔታዋን በተለየ መንገድ ትርጉም ሰጥተውት አስፀያፊ ምልክት ሲሰጦት ነው ያወቀችው። ከዛ በኋላ አይኖቾን አደብ አስገዛችና መጠጧን እየተጎነጨች አቀርቅራ ማሰላሰሏን ቀጠለች፡፡ የምትፈልገው ሰው እዛ ሆቴል ውስጥ ካሉት ሰዎች መካከል አንዱ ከሆነ የምትወደው አይነት ሰው ሊሆን እንደማይችል አሰበችና ተረበሸች፡፡

እያጨሰች ባትሆንም በዙሪያዋ ብዙ ሰዎች የተለያየ አይነት ሲጋር እያጬሱ ስለሆነ በጭስ ደመና ታፍናለች። እና አሁንም ብቻዋን እንደተቀመጠች ነው።በመጨረሻ፣ እሷ ስትመጣ ባለጌ ወንበር ላይ ተቀምጦ የነበረ የተጎሳቆለ አይነት ሰው ከመቀመጫው ተነሳና ወደ እሷ አቅጣጫ መጣ። ከእሷ ጠረጴዛ ጋር ከመድረሱ በፊት ካለው ሌለኛው ጠረጴዛ ላይ ወንበር ስቦ ተቀመጠና ይዞ የመጣውን ቢራ ከፊት ለፊቱ አስቀመጠ…የሁለቱ ወንበር መደገፊያ የተደጋገፈ ስለሆነ ጅርባቸው ተጋጥሟል ማለት ይቻላል..በዛ ላይ ሰውዬው ጥቁር ኮፍያ አድርጎ ፊቱን በከፍል ስለሸፈነ ምን እንደሚመስል በትክክል ልትለየው አልቻለችም፡፡፡

አንገቱን ወደኋላ ለጥጦ"ሰው እየጠበቅሽ ነው?"ሲል ተናገረ…ድምፁ የተለየ ይመስላል፣
"እኔ መሆኔን በምን አወቅክ ?ደግሞስ ይህን ያህል ጊዜ የፈጀብህ ለምንድን ነው?"ብላ በቀዝቃዛ ድምጽ መለሰችለት።

"ድፍረቴን እያሰባሰብኩ ነበር" አለ ከቢራው እየተጎነጨለት።

‹‹ጥሩ….ከእኔ ጋር አንድ ጠረጴዛ ለመጋራት ይሄን ያህል ትፈራለህ እንዴ?››

‹‹ህይወት እኮ ነው የያዝኩት… ለምን አልፈራም?››

"ይሁን እሺ…የምትነግረኝ ነገር እንዳለህ ገምታለው…ምንድነው ?።"

"የምትፈልጊውን ሁሉ ማውራት እንችላለን " የቢራ ጠርሙስ ጠረጴዛው ላይ አስቀምጦ ከኪሱ ብር አወጣና አስቀምጦ ‹‹..ግን መጀመሪያ ከዚህ መውጣት አለብን›› አላት፡፡

‹‹ ጥሩ የእኔ መኪና ውጭ ነው …ነጭ ቪታራ ነች"
‹‹አውቃታለው››

‹‹ሂሳብ ከፍዬ መጣሁ.. እዛ ጠብቀኝ››
ቀድሞ መራመድ ጀመረ፡፡ሹክክ ብሎ ሆቴሉን ለቆ ተሰወረ….እሷም አስተናጋጁን ጠርታ ሂሳብን ዘጋችና ግማሽ የቀረውን የወይን ጠርሙስ ባለበት ጥላ ቦርሳዋን ይዛ ወደውጭ ወጣች ..ወደ መኪናዋ ቀረበች ….ምንም ሰው በአካባቢው አይታያትም…..ወደመኪናዋ ውስጥ ገባችና ..የውስጥ መብረቱን አብርታ መጠበቅ ጀመረች…….ምንም ብቅ የሚል ሰው አልነበረም፡፡ ግራ ተጋባች…ተበሳጨች…ሰሞኑን ይደውልላት በነበረው ስልክ ደወለችለት…እንደተለመደው ይጠራል አይነሳም፡፡ማልቀስ ሁሉ አማራት..እዛው መኪናዋ ውስጥ ኩርምት እንዳለች ከአንድ ሰዓት በላይ አሳለፈች..በመጨረሻ ተስፋ ቆረጠችና አዲስ ወደ ተከራየችው አፓርታማ ነዳችው፡፡ከሀሳቧ ያባነናት የስልክ ጥሪ ድምፅ ነው… ከብስጭቷ ሳትወጣ ከአልጋዋ ተፈናጥራ ተነሳችና አነሳችው።

"ሀሎ።"

"እብድ ነው እንዴ ብለሽ አስበሻል አይደል ?"
የምታውቀውና የምትጠብቀው ድምፅ ነው።

"አንተ የት ነበርክ? ከእኔ ጋር ምን አይነት ጫወታ ነው አየተጫወትክ ያለኸው?መኪናዬ ውስጥ ተጎልቼ አንድ ሰዓት ያህል ስጠብቅህ ነበር.."

"ካንቺ ጋር ድብብቆሽ መጫወት ብፈልግ ኖሮ መልኬን እንድታይው አልፈቅድልሽም ነበር….ኩማንደሩ እዛው ነበር?"

"ምንድን ነው የምታወራው? ገማዶ እዚያ አልነበረም"

"የእኔ እመቤት ነበረ፣ በትክክል ነው ያየሁት። በቀጠሯችን መሰረት በቦታው ተገኝቻለሁ ግን ኩማንደር ገመዶ ከጀርባሽ በቅርብ ርቀት ተቀምጦ እያየሁት በአካባቢው መቆየት እና ከአንቺ ጋር ማውራቱን መቀጠል አልችልም… ፡፡››

‹‹ኩማንደሩ እየተከተለህ ነበር እንዴ?"

"እንዴት እንደዛ ያደርጋል….እኔ ምንም አይነት ህግ እልጣስኩም,…በተለይም ከፍሰሀ ጋር ግንኙነት ያላቸው ሰዎች አንገቴ ስር ሲተነፍሱ. ደስ አይለኝም…ኩማንደሩ ደግሞ ከልጅነቱ ጀምሮ ከፍሰሀ ጋር ያበረ ወፍራም ሌባ ነው. የእሱ ዋነኛ ቀኝ እጁ ነው..ለማንኛውም አንቺን ተከትሎ የመጣ ይመስለኛል!!››

"ኩማንደሩ በአካባቢዬ እንዳለ አላውቅም ነበር. ሌላ ቦታ እንገናኛለን. በሚቀጥለው ጊዜ እሱ እንዳልተከተለኝ እርግጠኛ እሆናለሁ."ስትል ቃል ገባችለት፡፡

" እስቲ እናያለን።"

‹‹እናያለን ማለት ምንድነው…?ነው ወይስ የምትነግረኝ ነገር ያን ያህል አስፈላጊ አይደለም፡፡.››

"ወንጀሉን ማን እንደፈፀመው አይቻለሁ እመቤት"

ተፈላጊነቱን ስታሳንስበት ተበሳጨ፡፡

"ታዲያ የት ነው የምንገናኘው?

እና መቼ?"

‹‹አሁን ህዝብ የተሰበሰበበት ቦታ አይደለም መገናኘት ያለብን ….ከቶታል ማደያ በቀኝ በኩል በምታስገባው መንገድ አንድ ሰማያዊ ቀለም የተቀባ ህንጻ አለ…. ከእሱ ፊት ለፊት
አንድ አሮጌ ሰማያዊ ባጃጅ ውስጥ ቁጭ ብዬ እጠብቅሻለው። እኔ ከኃላ ውስጥ አለሁ..ዝም ብለሽ ትገቢያለሽ።"

‹‹ባጃጁ ያንተ ነው ማለት ነው››

‹‹ከየት አባቴ አምጥቼ…የጓደኛዬ ነው..ሰሞኑን ስለታመመ እኔ ደግሞ ስራ ፈት ስለሆንኩ እየሰራሁለት ነው፡፡››

"በቃ በሰዓቱ እገኛለሁ- ግን እስከዛው ቢያንስ ስምህን ልትነግረኝ አትችልም?"

"አይ አልችልም" ስልኩን ዘጋው። አለም ተሳደበች። ከአልጋው ወርዳ ወደ መስኮቱ ሄደች ፣ መጋረጃዎችን ገለጠችና ወደውጭ ተመለከተች…የጠቆረው እና ኮከቦች የተበተሉበት ሰማይን በትኩረት አየች፡፡መጋረጃዎቹን ዘጋች፣ ወደ ስልኩ ተመለሰች፣ እና በቁጣ ውስጥ እንዳለች ሌላ ቁጥር ላይ ደወለች። የዓይን እማኝን በማስፈራራቱ በኩማንደሩ ላይ በጣም ተናደደች፣ እየተንቀጠቀጠች ነበር።ቀጥታ እሱ ላይ ነበር መደወል የፈለገችው…ግን ደግሞ ቁጥሩን አታውቅም…..የሰዓቱ መምሸት ግድ አልሰጣትም ፡፡ስልኩ ተነሳ፡፡
49👍2🥰2
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_አስራ_ስድስት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

////

‹‹ለፈረሶች የምታሳየውን ፍቅር ግማሹ ለሰው ብታሳይ እንዴት ጥሩ ነበር….ፈረሶችህን በትህትና ስታናግር ከቆየህ በኋላ ከሰው ጋር ማውራት ስትጀምር ቶንህ ወዲያው ይቀየርና ተናዳፊ ትሆናልህ››

የምፀት ፈገግታ ፈገግ አለና‹‹ለፈረሶችም ሆነ ለሰዎች የሚገባቸውን ነው ማደርገው….››አለና አጥሩ ላይ የተንጠለጠለውን ኮርቻ በማንሳት ፈረሱ ጀርባ ላይ አድርጎ አሳሰረውና የፈረሱን ሉጋም ይዞ ወደመውጫው መሄድ ጀመረ፡፡
ግራ ተጋብታ

"ወዴት ትሄዳለህ?"ስትል ጠየቀችው

" ትንሽ መጋለብ ፈልጋለው"

ከንዴቷ አንፃር ማልቀስ አማራት ‹‹ላናግርህ እፈልጋለሁ..ለምን እንደመጣሁ እያወቅክ ጥለኸኝ ልትሄድ ነው..?›› አለችው

ፈረሱ ላይ ወጣና ወደእሷ ቀረበ…እጁን ዘረጋላት….ግራ ተጋብትና በቆመችበት አይኖቾን አቁለጨለጨች….

‹‹እጅሽን ስጪኝ››አላት…..ዝምብላ ቀኝ እጇን ወደላይ ሰቀለችለት.. አጥብቆ ያዛትና ወደላይ ጎተታት…ጥንካሬው አስገረማት….እርካብ ላይ እግሯና አኖረችና እንጣጥ ብላ በመውጣት ከጀርባው ፈረሱ ላይ ተፈናጠጠች፡፡ከዛ ለፈረሱ ሉጋሙን ለቀቅ ሲያደርግለት ፈረሱ እየሰገረ ወደፊት ተስፈነጠረ ፡፡በፍራቻ ወገቡን አጥብቃ አቀፈችው….የኮረኮንች መንገዱን ይዞ ወደ ከተማዋ መውጫ ሽምጥ መጋለብ ጀመሩ….፡፡
"ትላንትና ማታ በቡና ቤት ውስጥ ከማን ጋር ነበር የተገናኘሽው?"

"ይሄ የኔ ጉዳይ ነው ኩማንደር …ለምን ተከተልከኝ?"ልትጠይቀው የምትፈልገው ብዙ ጥያቄዎች ነበራት፣ ነገር ግን በእያንዳንዱ የፈረስ እንቅስቃሴ ከተቀመጠችበት እንጣጥ ብላ ጀርባው ላይ ስትለጠፍበት ስለነበር አእምሮዋን በጀመረው ሀሳብ ላይ ፀንቶ እንዲቆይ ማድረግ ከባድ ሆነባት። እንደምንም ወደ አእምሯዋ የመጣውን የመጀመሪያ ጥያቄ ጠየቀችው።

"አንተ እና እናቴ እንዴት የቅርብ ጓደኛሞች ሆናችሁ?"

"አብረን ነው ያደግነው" አለ በንቀት። ተንፋሽ ወሰደና ቀጠለ"ት/ቤት መጫወቻ ሜዳ ላይ ተጀምሮ በእድሜ እየገፋን ስንሄድ ተሻሻለ"

"አስቸጋሪ ሆኖ አያውቅም?"

"አይ አንዳችን ከሌላችን የምደብቀው ምንም ምስጢር አልነበረንም. እንዲያውም ያንቺን ካሳየሺኝ የእኔንም አሳይሻለው እያልን እንጫወት ነበር."አለና ፈገግ አለ።‹‹በአጠቃላይ በእኔ እና እሷ መካከል አይነኬ የተባለ የውይይት ርዕስ አልነበረም ።››ሲል አከለበት፡፡

"ያ አንድ ሴት ልጅ ከሌላ ሴት ጋር የሚኖራት አይነት ግንኙነት አይደለምን?"

‹‹ብዙውን ጊዜ ግን ሰሎሜ ብዙ የሴት ጓደኞች አልነበራትም, አብዛኛዎቹ ልጃገረዶች በእሷ ይቀኑ ነበር."

"ለምን፧"

አለም መልሱን ቀድሞውንም ብታውቅም ከእሱ አንደበት መስማት ፈለገች፡፡ "በአንተ ምክንያት ነበር አይደል? ካንተ ጋር የነበራት ወዳጅነት?"
"ምናልባት ሊሆን ይችላል, ዋናው ጉዳይ ግን እሷ በጣም ቆንጆ ነበረች…በዙሪያዋ ያሉ አብዛኞቹ ልጃገረዶች እንደ አጋር ሳይሆን እንደ ተቀናቃኝ ነበር የሚቆጥሯት፡፡….ቆይ አንዴ።›› ፈረሱን አቅጣጫ ከመቀየሩ በፊት አስጠነቀቃት እና ፈረሱ ጓድጓዳ አካባቢ ሲረግጥ ወደ ፊት ገፋት፣ እሱ ላይ ተለጠፈች። በደመ ነፍስ ወገቡን አጥብቃ አቀፈችው።

"ፈረስ ቁልቁል ሲወርድ ወደፊት መንሸራተቱ የሚጠበቅ ነው….››
ስትረጋጋ“እናቴ ሁሉንም ሚስጥሮቾን እያመጣች ለአንተ ትዘረግፍ እንደነበረ እየነገርከኝ ነው?›› ብላ ጠየቀችው፡፡

‹‹አዎ, እንደዛ ነበር የምታደርገው…እሷ እንደአንቺ አይነት ውስብስብ ሴት አልበረችም…ለምሳሌ አንድ ቀን ምንም ሳትነግረኝ ከትምህር ቤት ቀረች እና የሆነ ችግር እንዳለ አውቄ ነበር...ተጨንቄ ስለነበር በእረፍት ወደ ቤቷ ሄድኩ. አያትሽ በሥራ ላይ ስለነበሩ ሰሎሜን ብቻዋን እያለቀሰች ነበር ያገኘዋት…ፈርቼ ምን እንደሆነች እስክትነግረኝ ድረስ ጨቀጨቅኳት።"

‹‹ጉዳዩ ምን ነበር?"

‹‹ የወር አበባዋን ለመጀመሪያ ጊዜ መቶባት ነበር….አያትሽ የወር አበባን በተመለከተ የሀጥያት ፍሬ እና እርግማን እንደሆነ የሚተርኩ አስፈሪ ታሪኮች ነግረዋት ስለነበር በጣም አዝና ነበር ያገኘኋት ፡፡ እንዴት ነው አያትሽ ለአንቺም እንደዛ አይነት አስፈሪ ታሪኮችን ይነግሩሽ ነበር?››
አለም ወገቡን ሳትለቅ አንገቷን እንደምንም ቀና አደረገችና‹‹ያን ያህል የሚረብሹ አይነት ታሪኮችን ነግራኝ አታውቀኝም… ምናልባት አያቴ እኔን ማሳደግ በጀመረችበት ጊዜ ተሻሽላ ሊሆን ይችላል።ለአቅመ አዳም በደረስኩበት ጊዜ በቀላሉ ነው የተቀበልኩት።››

ፈረሱ ግልቢያውን እስኪያቆም ድረስ አለም ያሉበትን ቦታ አላስተዋለችም ነበር፡፡መኖሪያ ቤቱ ደርሶ ነበር ያቆመው፡፡

" ከዛስ እንዴት ሆነ?"

‹‹አፅናናኋት እና የወርአበባ ማለት ሴትነቷ በይፋ የታወጀበት ድንቅ ቀን እንደሆነ እና መደስት እንጂ ማልቀስ እንደማይገባት ነገርኳት።››

"ሰራ ታዲያ?"

"እንደምገምተው አዎ። ማልቀሷን አቆመች"
'እና...?'' አለም የታሪኩን በጣም አስፈላጊ ክፍል እንዳልነገራ ስላወቀች  እንዲቀጥል አነሳሳችው።
"ከዛማ.. በቃ ።››አለና ቀድሞ ከፈረሱ ላይ በቀላሉ በመውረድ ‹‹ እግርሽን አንሺው።" አለና እሷን ለማውረድ እጁን ዘርግቶ በጠንካራ እጁ ወገቡ ላይ አቀፋትና ወደ መሬት አወረዳት።

ከእናቷ ጋር ሲሳሳም ሚያሳየውን ፎቶ መመልከቷን አስታወሰች ። "ለቅሶዋን ካቆመች በኃላ ሳምካት አይደል?"

በትከሻው የማይመች እንቅስቃሴ አደረገ። "ከዚያን ቀን በፊትም ስሜያት ነበር።" "ግን ያ የመጀመሪያው እውነተኛ መሳም ነበር አይደል?"
እሷን በጥልቀት ተመለከታትና ወደ ቤቱ  በረንዳ ወጥቶ በሩን ገፋው ። ወደኃላ ዞር አለና

‹‹መግባትም ሆነ አለመግባት የአንቺ ጉዳይ ነው።››አለና ክፍት አድርጎ ተወው… ወደ ውስጥ ገብቶ ጠፋ, ተስፋ የቆረጠች ቢሆንም ግን ደግሞ ተጫማሪ የማወቅ ጉጉት ስላላት ተከተለችው።
መየፊት ለፊት በር በቀጥታ ወደ ሳሎን ተከፈተ። በግራዋ በኩል ባለው በር በኩል የመመገቢያ ቦታ እና ኩሽና ማየት ችላለች። በተቃራኒው በኩል ያለው የመተላለፊያ መንገድ ወደ መኝታ ክፍል ይወስዳል፣ እሱም ሲያወራ ትሰማለች። የሳሎኑን በር ዘጋች፣ መነጽርዋን አውልቃ ዙሪያዋን ተመለከተች።ቤቱ የወንደላጤነት ወዝ ነበረው …ፈሪኒቸሮቹ መጠነኛና ቅልብጭ ያሉ ናቸው፡፡በግራ ግድግዳ ያለው መደርደሪያ ላይ ያሉት መጻሕፍቶች የተዘበራረቁ ነበሩ፣ ፡፡

"ቡና ትፈልጊያለሽ?"

"ባገኝ ደስ ይለኛል።››

ወደ ኩሽና ገባ። የቀዘቀዙ እግሮቿ የደም ዝውውር እንዲስተካከል እያፍታታች በክፍሉ ውስጥ መዞሯን ቀጠለች። ከመጽሐፍ መደርደሪያው በላይ ወደተቀመጠው አንድ ረጅም ዋንጫ ቀልቧ ተሳበ። በላዩ ላይ የኩማንዱሩ ስም እና ቀኑ በግልፅ ፊደላት ተቀርጾበታል።
"ይህ ትክክለኛው ቀለም ነው?" ዘወር ስትል አንድ ኩባያ ቡና ይዞላት ወደ እሷ እየቀረበ ነበር።

"አመሰግናለሁ።" ብላ ተቀበለችውና …ጭንቅላቷን ወደ ዋንጫው በማዘንበል "ይሄ ያንተ ምርጡ አመት አይደል?"ስትል ጠየቀችው፡፡

"ምን አልባት"

"ምነው ?እርግጠኛ አይደለህም?"

ወደ ወንበሩ ሄደና ተቀመጠ ፡፡ "ያኔ እንደዛ ተሰምቶኝ ነበር እና አሁንም ድረስ በወቅቱ የሚደግፈኝ ጥሩ ቡድን እንደነበረኝ ይሰማኛል።ሌሎች በእጩነት የቀረቡት ተጫዋቾችም እንደኔ ዋጋ ያላቸው ነበሩ።"

"ለምሳሌ ጁኒየር?"

"አዎ እሱም ከነሱ አንዱ ነበር " ሲል መለሰ፣

‹‹ሽልማቱን ያሸነፍከው አንተ እንጂ ጁኒየር አይደለም።››ዓይኖቹ ወደሷ አፍጠጠ፡፡
"ውድ አቃቢህግ ከእኔ ጋር የጀመርሽውን ጫወታ አቁሚ እና በአእምሮሽ ያለውን ነገር ቀጥታ ተናገሪ።"
40👍4🔥1
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_አስራ_ሰባት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

////
ነጋ አልነጋ ብላ ጥዋት ወደቢሮዋ ከመግባቷ በፊት ቀጥታ ወደኩማንደሩ ቢሮ ነው የሄደችው፡፡እንዳጋጣሚ እሱም በማለዳ እንደገባ ነገሯት፡፡ቀጥታ ወደቢሮ መራመድ ጀመረች፡፡
ኩማንደር ወደቢሮ በጥዋት ቢገባም ከጥቂት ሰኮንዶች በላይ በአንድ ሀሳቡ ላይ ትኩረት አድርጎ ማሰብ አልቻለም። የአለም ምስል በምናቡ ብልጭ ድርግም እያለ እየረበሸው ነው፡፡ወንበሩን ትቶ ወደ መስኮቱ ሄደ። መጋረጃውን ገልጦ ወደ ውጭ መመልከት ጀመረ፣የጥዋቷ ፀሐይ ደማቅና ብሩህ ነች። ትላንትን ከአለም ጋር ያሳለፈውን ጊዜ አስታወሰ
.. እሷን ጎትቶ ፈረስ ላይ ሲያወጣት እና ተፈናጥራ በእጇቾ ወገቡን ጨምድዳ ስትይዝ… ጀርባዋ ላይ ስትለጠፍበት …አናዳጅና አብሻቂ ጥያቄዎቾን ስታዥጎደጉድበት በወቅቱ ያየባት ብልሀትና ብልጠት አስገርሞታል….በተቃራኒው ደግሞ ማታ የሙስጠፋ ሬሳ ጋር በዛ በጭለማ ቦታ ሲያገኛት በጣም የፈራች ፤የምትንቀጠቀጥና ፈሪ ሴት ሆና ነው ያገኛት፡፡

‹‹ምናልባት የሙስጠፋ አሰቃቂ ግድያ ስለእናቷ ግድያ የምታደርገውን ምርመራ ፈርታ እንድታቆም ያስገድዳት ይሆናል። ምናልባት ሻሸመኔን ትታ ወደ ኋላ ላትመለስ ወደ አዲስአባዋ ትመለስ ይሆናል።››ሲል አሰበ፡፡ይህ አጋጣሚ ሊያስደስተው በተገባ ነበር። ግን አላስደሰተውም። በእሷ እና በራሱ ላይ የበለጠ ተናደደ።ትላንትን ከእሷ ጋር መሳሳሙ የደደብ ሰው ተግባር እንደፈፀመ ነው የተሰማው፡፡በወቅቱ ራሱን መቆጣጠር ፈልጎ ነበር። ግን ለስሜቱ ተገዢ ሆኖ ማድረግ የሌለበትን ነገር አድርጎል፡፡በህይወቱ እንዲህ እንዲያደርግ ያስቸለው አንድ ሌላ ሴት ብቻ ነበረች እሷም ሰሎሜ ነች። ገረመው። ለዓመታት አላሰበውም ነበር ፣ ግን አሁን በአእምሮው ውስጥ ግልፅ ሆኖ እየታየው ነው።

ሰሎሜ ትወደው ነበር።እሱም ወዷት ነበር። አንድ ቀን ሊጋቡ ተስማምተው ነበር….ፍቅራቸውን የሚያጨነግፍ ምንም አይነት እንቅፋት በመሀከላቸው እንደማይፈጠር እርግጠኞች ነበሩ….ገመዶ አይኑን በድካም እያሻሸ ወደ ጠረጴዛው ተመለሰ እና ወንበር ላይ
ተቀመጠ ። አለም ለዓመታት ውስጡ የቀበረውን  ትዝታ እየቆሰቆሰች እንዲያስታውስ እየደረገችው ስለሆነ ተበሳጨባት ፡፡ትናንት እሷን ሲስማት  ሊቀጣት እና ሊያበሳጫት ነበር አላማው ። ነገር ግን ውጤቱ ተገላቢጦሽ ነበር የሆነበት… ።ከንፈሯ ልክ እንደእናቷ በዛ መጠን  ይጣፍጣል ብሎ አልጠበቀም ነበር። ያ ጣፋጭነት አሁንም በምላሱ ላይ ቀርቷል. ድድር ጡቶቿ በዛ ልክ ስሜት ቀስቃሽ እና ለስላሳ እንደሚሆኑ እንዴት ሊገምት ይችላል? ለወደፊቱ ሁሉንም እቅዶቹን ማበላሸቷ እንደማይቀር ገመተ። ህልሙን እውን ለማድረግ በጣም ቅርቦ ነበር። ሊደርስ  ጥቂት ነበር የቀረው….።ህይወቱን በሙሉ በትጋት የሰራበት ቦታ ለመሆን አንድ የመጨረሻ እርምጃ ነበር የቀረው።በዚህ መጥፎ ጊዜ ነው እንቅፋት ሆና ከፊቱ የተገተረችው፡፡‹እና ምን ያድርግ አንቆ ይግደላት ?›ስለማነቅ ሲያስብ ዘገነነው፡፡ ሀሳቡን ሳያገባድድ የበራፍ መቆርቆር ሰማ….

‹‹ይግቡ››

በራፉን  ከፈተችና  ገባች  እና  "  እንደገባህ  ነግረውኝ  ነው  ቀጥታ  ወደእዚህ የመጣሁት››አለችው፡፡

እሷን በማያቱ እንዳልተደሰተ በሚያሳብ የድምፅ ቃና‹‹እ …ዛሬ ደግሞ ምንድነው?››ሲል ጠየቃት ፡፡አለም በሩን ዘጋችና ወደውስጥ ዘልቃ በመግባት ወንበር ይዛ ተቀመጠች፡፡

"ከደቂቃዎች በኋላ ወደ ፍርድ ቤት እንደምሄድ አልነገሩሽም? ››

‹‹አይ…አልነገሩኝም››አለችው ፈገግ ብላ…ከትናንት ማታው ሁኔታ ያገገመች ትመስላለች፡፡ " እሺ ምንድነው ጉዳይሽ?"በመሰላቸት ጠየቃት፡፡

"ስለተገደለው  ሰው  ልትጠይቁኝ  ትፈልጋላችሁ  ብዬ  ስላሰብኩ  ነው…ቃል  ልሰጥ የመጣሁት››

"በእርግጥ ተጠርጣሪ አይደለሽም። የተሳሳተ ጊዜ ላይ በተሳሳተ ቦታ ተገኝተሸ ነው ፡፡ይሄ ድግሞ ያንቺ መጥፎ ልማድ ነው።"አላት፡፡

"በእኔ እና በእሱ ግድያ መካከል ግንኙነት ያለ አይመስላችሁም?" "አይ አይመስለንም ››አላት ፍርጥም ብሎ፡፡

‹‹እኔ ደግሞ ይመስለኛል››

"ከሆነ እንስማው" አለ።

"አስቀድመህ የምታውቀው ይመስለኛል። ሙስጠፋ የሰሎሜን ግድያን አይቷል…የአይን እማኝ ምስክር ነበር።"

በበደነ እና በቀዘቀዘ ስሜት "እንዴት አወቅሽ?"ሲል ጠየቃት፡፡

"በስልክ ደውሎ ነገረኝ።"

"እሱ እኮ  ውሸታም ሰው እንደሆነ ማንም ያውቃል….ስለባህሪው የሚያውቁትን ሰዎች መጠየቅ ትችያለሽ "

"እኔ አምኜዋለሁ። በጣም የተደናገጠ እና በጣም የፈራ ይመስላል ነበር። በመጨረሻ ለመገናኘት ቀጠሮ ይዘን ነበር፣ አንተ ስትከተለኝ እንደነበረ የነገረኝ እሱ ነው…በዛን ቀን እዛ ሆቴል ባትገኝ ኖሮ የእናቴን ገዳይ በዝርዝር ይነግረኝ ነበር።"

"ታዲያ ይሄ ዝርዝር.. የሰሎሜ ገዳይ ያደርገኛል?"

"ገዳይ ባትሆን አንኳን ለገደለው ሰው እየሸፈንክለት ሊሆን ይችላል ››

"በንድፈ ሀሳብሽ ላይ ምን ችግር እንዳለ ልንገርሽ?አቶ ፍሰሀ ከስራ ካባረረው ቀን አንስቶ እሱ የበቀል ጉዞ ላይ ነበር፣ ድንገት አንቺ የእናትሽን ገዳይ እያነፈነፍሽ እንዳለ ሲሰማ በዛ ተንኮለኛ ጭንቅላቱ ነገሮችን አገጣጠመና ጥሩ ድረሰት በአእምሮ ቀምሞ ሊያጃጅልሽ ሞከረ…››

" ያ እውነት አይደለም..ሰውዬው የተገደለው. ስለእናቴ አሟሟት ለእኔ እንዳይነግረኝ አፉን ለማዘጋት ነው ፡፡ይህ ሰውዬ የእናቴን መገደል ለማየት የሚችልበት አጋጣሚ ከፍተኛ ነው…እንደሚታወቀው እናቴ የሞተችው በእርባታ ድርጅት ውስጥ በከብቶቹ በረት አካባቢ ነው..እሱ ደግሞ የከብቶቹ ተንከባካቢ ስለሆነ አብዛኛውን ጊዜ ከአካባቢው አይጠፋም፣››

‹‹የፈለግሽውን ማመን ትችያለሽ…ለማንኛውም የእሱን መገደል የተመለከተ የአይን እማኝ እንዳገኘን ነግሬሽ ነበር..እድሜ ለእሱ አሁን የሰውዬውን ገዳይ ይዘነዋል…››

ደነገጠች‹‹ይዘነዋል…..እና አመነ?››

‹‹ትንሽ ቢያቅማማም አምኗል››

‹ለምን ገደልኩት አለ?››

‹‹ሚስቴን አማግጦብኛል ..የሚል ምክንያት ነው የሰጠው…የሰውዬውን ሚስትም አግኝተን አናግረናታል…ከሟቹ ጋር የድብቅ የፍቅር ግንኙነት እንዳላት አልካደችም…..››

‹‹ይገርማል…ለሊቱን ሙሉ አልተኛህም አይደል….?በእውነት በአንድ ለሊት ይሄን ሁሉ አቀናብራችሁና አደራጅታችሁ ማደር በመቻላችሁ በራሳችሁ ልትኮሩ ይገባል….››

‹‹ምን ለማለት ፈልገሽ ነው?››የደፈረሱ አይኖቹን አጉረጠረጠባት፡፡

‹‹አንዲት ሴት የደፈረ ወንጀለኛ ለመያዝ ስድስት ወር የማይበቃችሁ በ12 ሰዓት ውስጥ ለዛውም በለሊት ገዳዩን ይዛችሁ …ምስክር አጠናቅራችሁ እንዲህ ጥንቅቅ ብላችሁ ሳያችሁ ባልደነቅ ነው የሚገርመው…..እርግጠኛ ነኝ በጥዋት መጥቼ እንደማፋጥጥህ እርግጠኛ ስለሆንክ መደረግ ያለበትን ነገር ሁሉ አድርገሀል…አድናቂህ ነኝ፡፡››

ሚመልስላት ስላልነበረው ዝም አላት..

"ሁሉንም ፕሮፌሽናል ሴቶች ትጠላለህ ወይስ በተለይ እኔ ነው የምትጠላው?"ስትል ሌላ ያልጠበቀውን ጥያቄ ጠየቀችው፡፡

‹‹በተለይ አንቺ ነው የምጠላው።"አላት ፡፡ድፍረቱ አስነዋሪ ነበር። የትናንት መሳሳማቸውን እንዳልወደደው የሚያሳይ ነገር አላነበበችበትም ፡፡በመሀከላቸው ምንም እንዳልተፈጠረ ለማስመሰል ሞከረች፡፡ ግን መርሳት አልቻለችም። ንግግሩ በጣም ጎድቷታል።

"ለምንድነው ማትወደኝ?"ስትል ጠየቀችው

"ምክንያቱም አንቺ ጣልቃ ገብ ነሽ። በሌሎች ሰዎች ህይወት ውስጥ ጣልቃ የሚገቡ ሰዎችን አልወድም።"

"ይህ ጣልቃ መግባት አይደለም… የእኔ ጉዳይ የእናቴን ገዳይ መፈለግ  ነው."
31👍5
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_አስራ_ስምንት


#ድርሰት__በዘሪሁን_ገመቹ
……

ከባለፈው ክፍል ተቆርጦ የቀረ

///
ዝግጅቱ በተዘጋጀበት የከተማዋ ግዙፉ ሆቴል የጁኒዬርን እጅ ይዛ ስትገባ ደስ የሚል ስሜት ነው የተሰማት፡፡ ለስለስ ያለ ምርጥ ሙዚቃ እና እዚህማ እዛም በፈገግታ የታጀበ ሳቅ ይሰማ ነበር፡ከበርካታ ሰዎች ጋር አስተዋወቃት…ከብዙ ሰዎች ጋር የማውራት እድል አገኘች፡፡ አንዳቸውም ውይይቶች በእናቷ ግድያ ዙሪያ ያተኮሩ አልነበሩም። ያ በራሱ መንፈስን የሚያድስ ለውጥ ነበር። እረፍት ላይ እንዳለች መስሎ ተሰማት። ጁኒየር በመጠጥ ተፅዕኖ ውስጥ ገብቶ ሚስጥሩን ለእሷ አሳልፎ እንደሚሰጣት ቀድሞውንም አላመነችም። እሷ ምንም አስገራሚ ኑዛዜዎችን የመስማት ዕድል እንደሌለት ገምታ ነበር።ቢሆን ከምሽቱ አንድ ጠቃሚ ነገር ሊወጣ ይችላል የሚል ተስፋ መሰነቋ ግን አልቀረም. ፡፡
ከሁሉም በላይ፣ ከአካባቢው ነዋሪዎች፣ ከአቶ ፍሰሀ እና ከኩማደሩ ጋር በደንብ ከሚተዋወቁ እና ባህሪያቸውንና ድብቅ ተግባራቸው ከሚያውቁ ሰዎች ጋር የመቀላቀል እድል አላት፡፡
እንደተለመደው "ነጭ ወይን"ይዛ እየጠጣች ነው ጁኒዬር ከጎኗ አለ፡፡

"ሙዚቃው የእኔ ጣዕም አይደለም ነገር ግን መደነስ ከፈለግሽ እኔ ታዛዥ ነኝ.››አላት

ጭንቅላቷን በአሉታ ነቀነቀች። "አመሰግናለሁ …እኔ ከመደነስ ይልቅ ማየት እመርጣለሁ።››

ከጥቂት ዘፈኖች በኋላ ጁኒየር ጠጋ ብሎ በሹክሹክታ፣"እናትና አባቴ እዛ ጋር ናቸው….ሰላም እንበላቸው›› አለና..እየጎተተ ይዟት ሄደ፡፡
አለም በዳንስ ወለል ዙሪያ ለመመገቢያ ወደተዘጋጁት የጠረጴዛዎች ስብስብ አብሮት ሄደ። ሳራ ጆ እና አቶ ፍሰሀ በአንድ ላይ ተቀምጠዋል። ደረሱና

"ጤና ይስጥልኝ ወይዘሮ ሳራ ዛሬ ማታ ቆንጆ ሆነሻል።››አለቻት አለም

‹‹አንቺም እንደዛው ….እንኳን በሰላም መጣሽ››ስትል መለሰችላት፡፡

ሰላምታ  ተለዋውጠው  አንድ  ጠረጴዛ  ከበው  የየግላቸውን  መጠጥ  በመጠጣት ጫወታቸውን ጀመሩ፡፡

‹‹የሙስጠፋን የሞተ  አካል ለመጀመሪያ ጊዜ ያገኘሽው አንቺ  እንደሆንሽ  ሰማሁ››።ሲል ኮስተር ባለ ነገር ጫወታውን የጀመረው አቶ ፍሰሀ ነበር፡፡

"አባዬ  ይህ  ፓርቲ  ነው…አለም  ስለ  እንደዚህ  አይነት  መጥፎ  ነገር  ማውራት አትይፈልግም."አለ ጁኒየር።

"አይ፣ ምንም አይደለም፣ ጁኒየር፣ ይዋል ይደር እንጂ እኔ ራሴ አነሳው ነበር።››

"ጥሩ ..ከሱ ጋር የተገናኘሽው በአጋጣሚ ነው ብዬ አላስብም።ያንን ደደብ ሽማግሌ ለምን ነበር ልታገኚ የፈለግሽው?"

"አይ….።››በማለት ከሙስጠፋ ጋር የነበራትን የስልክ ውይይት በዝርዝር ነገረቻቸው፡፡

‹‹ያ ውሸታም ሽማግሌ ሊያታልልሽና አንቺን አጓጉቶ ገንዘብ ሊቀበልሽና ..እግረ መንገዱንም እኔን ለመበቀል ሲያደባ ነበር…ግን ፈጣሪ የልቡን ተንኮል አይቶ ለሌላ ወንጀለኛ አሳልፎ ሰጠው፡፡››
"ኦህ፣ እንዴት በእርግጠኝነት እንደዛ ደመደምክ..?››

‹‹ ሙስጠፋ ከሰሎሜ ጋር ወደዚያ በረት ውስጥ የገባው ማን እንደሆነ አይቶ ሊሆን ይችላል፣ ግን የእውነት እንደሚለው ሰው አይቶ ከሆነ ሊያይ የሚችለው ሊቁን ነው።››ሲል ጁኒዬር አከለበት፡፡
አለም ..ለመናገር የፈለገውን ከተናገረ በኋላ …እንዲከራከር እድል አልሰጠችውም ፣ የሙስጠፋ ርዕስ ለጊዜው ባለበት እንዲቆም አደረገች ።መጠጣቸውን እንደጨረሱ፣ አቶ ፍሰሀ እና ጁኒየር ሴቶቹን ባሉበት ጥለው ሌሎች የቢዝነስ ሰዎችና ለማነጋገር ተያይዘው ሄዱ፡፡
ከሳራ ጆ ጋር ለረጅም ደቂቃዎች መቆየት ከባድ ነው ..ከእሷ ጋር ማውራትም ቀላል እንደማይሆን አሰበች፣ቢሆንም እንደምንም እራሷን አጀግና "ለረጅም ጊዜ የዚህ ማህበር አባል ናችሁ?"የሚል ጥያቄ ሰነዘረችላት፡፡

"ፍሰሀ ከመስራች አባላት አንዱ ነበር" ስትል ሳራ ግድ በሌለው ሁኔታ መለሰችላት ።
በመድረኩ ላይ በርካንታ ጥንዶች እየደነሱ እና እየተጎነታተሉ ይታያሉ፡፡አለም"አቶ ፍሰሀ በእያንዳንዱ የከተማዋ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ እጁ ያለበት ይመስላል " ስትል አስተያየት ሰጠች.
"ትክክል ነሽ…የከተማዋ ጠባቂ እንደሆነ ነው የሚያስበው… እየሆነ ያለውን ሁሉ ማወቅ ይፈልጋል….በዛ ምክንያት ..ሁሉንም ነገር ለመቆጣጠር ሲል ሁሉም ነገር ውስጥ ይገባል››ሳራ በረጅሙ ተነፈሰች እና ንግግሯን ካቆመችበት ቀጠለች "አየሽ ፍሰሀ በእያንዳዱ የከተማው ኑዋሪ …በባለስልጣናቱም ዘንድ ሆነ በነጋዴዎች ክበብ የመወደድ ፍላጎት አለው
፤ እሱ ሁል ጊዜ ፖለቲከኛ ነው ፣ ››
አለም እጆቿን ከአገጯ በታች አጣጥፋ በክርኖቿ ጠረጴዛው ላይ ተደግፋ። "አንቺ ያ.. አስፈላጊ ነው ብለሽ ታምኚያለሽ?"

"አይ አላንም።" አለችና ለመጀመሪያ ጊዜ አለምን በትኩረት  ተመለከተች።

"ጁኒየር ለአንቺ የሚያሳይሽን እንክብካቤ ብዙም ትርጉም አትስጪው››በማለት አዲስ ርዕስ ከፈተች፡፡

"አቤት…ምን ማለት ነው?"

"ልጄ የሚያገኛት ሴት ሁሉ የማሽኮርመም ልክፍት አለበት እያልኩሽ ነው ››

አለም ቀስ ብላ እጆቿን ወደ ታች አወረደች። ንዴቷ ወደ ውስጥ ገባ፣ ነገር ግን ድምጿን ዝቅ አድርጋና እራሷን እንደምንም ተቆጣጥራ “ወ/ሮ ሳራ አንድምታይው ተናድጃለሁ።››

ሳራ ጆ በግዴለሽነት አንድ ትከሻ ከፍ ዝቅ አደረገች‹‹ግድ የለኝም ››የሚለውን መልዕክት ለማስተላለፍ ፈልጋ እንደሆነ አለም በግልፅ ገብቷታል፡፡

"ሁለቱም ወንዶቼ ቆንጆዎች ናቸው እና እነሱም ያንን ስለሚያውቁ አላግባብ ይጠቀሙበታል..አብዛኛዎቹ ሴቶች ደግሞ የእነሱ ማሽኮርመም ትርጉም የለሽ እንደሆነ አይገባቸውም."

" እርግጠኛ ነኝ ፍሰሀን በተመለከተ ያልሽው እውነት ነው፣ ስለ ጁኒየር ግን አይመስለኝም።
ሶስት የቀድሞ ሚስቶች ስለ እሱ ማሽኮርመም ከአንቺ ጋር ላይስማሙ ይችላሉ።››

"ሁሉም እሱን በተመለከተ ተሳስተው ነበር።"

"እናቴስ? እሷም እሱን በተመለከተ ታሳስታ  ነበር?"ሳራ ባዶ አይኗን አሌክስ ላይ በድጋሚ ተከለች።

"አዎ ተሳስታለች ፤አንቺም እንደሷ  ነሽ ….ታውቂያለሽ አይደል?።"

"እኔ?"

" አዎ!!አለመግባባት መፍጠር ያስደስትሻል። እናትሽ አስጨናቂ ነገሮችን በመፍጠር እርካታ አልነበራትም። ልዩነቱ አንቺ ከሷ በላይ ችግር እና መጥፎ ስሜትን በመፍጠር የተሻልሽ መሆንሽ ብቻ ነው። ብዙውን ጊዜ ብልሀት የሚጎድልሽ ቀጥተኛ ሴት ነሽ።››ዓይኖቿን ከአለም ጀርባ አሻግራ አንድ ሰው ትመለከት ጀመረ፡፡

"ደህና አመሻሽ ሳራ "

"ዳኛ ዋልልኝ" ጣፋጭ ፈገግታ በሳራ ጆ ፊት ላይ ታየ።በዛ ቅፅበት የሚመለከታት አንድ ሰው ከሴኮንዶች ቀደም ብሎ ከፍተኛ ንዴት ላይ እንደነበረች በጭራሽ መገመት አይችልም

‹‹… ሰላም ስርጉት።››አለም በሳራ ያልተጠበቀ ትችት የተናደደ ፊቷን ወደኋላ አዞረች። ዳኛው የእሷን እዛ መገኘት እንደትልቅ ጥፋት የቆጠረ እንደሆነ በሚያሳብቅ ስሜት ትኩር ብሎ ያያት ጀመር።

" ክብርት አቃቢት ህግ "

"ጤና ይስጥልኝ ክቡር ዳኛ " ከሳቸው ጎን የቆመችው ሴት አለምን ከሱ ጋር የሚዛመድ ተግሳፅ ተመለከተች ፣ ዳኛው የሴትየዋን ክንድ ነካ አድርገው ወደ ሌላ ጠረጴዛ ሄዱ

"ሚስቱ ናት?" አለም ለሳራ ጥያቄ አቀረበች ፡፡

ሳራ በመደነቅ "በእግዚያብሄር ስም….አረ አይደለችም..የሱ ሴት ልጅ ነች ስርጉት…የመጀመሪያ እና ብቸኛ  ሴት ልጁ ነች፡››

ከላይ የለጠፍነው ከባለፈው ክፍል ተቆርጦ የቀረ ነው።

#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

///

"ሰሎሜና ስትሞት ደስ ብሎኝ ነበር."

የጥርጣሬ ብልጭታ በአለም አይኖች ውስጥ ዘለለ፣ ‹‹አልዋሽሽም…የሆነ ተራራ ከጭንቅላቴ እንደወረደ እፎይታ ነው የተሰማኝ ››
55👍3👎1
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

////

አለም የቢሮውን በራፍ አንኳኳች… የኩማንደሩን ‹ይግቡ› የሚል ሻካራ ቃል እስክትሰማ ድረስ ጠበቀች እና ወደውስጥ ገባች፡፡

"እንደምን አደርክ። ልታገኘኝ ስለፈቀድክ  አመሰግናለሁ።››በማለት ከጠረጴዛው ፊት ለፊት ባለው ወንበር ላይ ተቀመጠች ፡፡
ሳይጠይቃት አንድ ኩባያ ቡና ቀዳላትና ከፊት ለፊቷ አስቀመጠ።ስለቡናው አመሰገነችው። ተሸከርካሪ ወንበሩ ላይ ተቀመጦ፡

"ስለ አያትሽ አዝናለሁ ..አለም" አላት፡፡

"አመሰግናለሁ።"አለች፡፡

አለም የአያቷን የቀብር ሥነ ሥርዓት መፈፅምና ተያያዝ ጉዳዬችን መስመር ለማስያዝ ለአንድ ሳምንት አዲስአበባ ቆይታ ከመጣች ገና ሁለተኛ ቀኗ ነው ። በቀብሩ ላይ ጥቂት የድሮ ጓደኞቾ እና ከመቅዶኒያ የመጡ አያቷን በቅርበት የሚያውቁ ጥቂት ሰዎች ነበር የተገኙት፡፡… ከቀብር ሥነ ሥርዓቱ በኋላ አለም ወደአረጋዊ ማእከሉ ሄዳ የአያቷን እቃዎች መሰብሰብ ነበረባት…አብዛኛውን እቃዎች እዛው ለሚስፈልጋቸው ሰዎች በመስጠት ነበር ያስወገደችው፡፡
ከዛ ጥልቅ የሆነ ትካዜ ውስጥ ገባችው፡፡ ዳግመኛ ወደ ሻሸመኔ ከተማ መሄድ ይኑርባት ወይም እዛው አዲስአባ ትቅር ግራ ገብቷት ነበር፡፡አሁን አያቷ ሞተዋል….‹‹የእናትሽ ጋዳይ ነሽ››ብሎ እጣቱን የሚጠቁምባት ሰው የለም….ታዲያ ምን አሰቃያታል?፡፡በኋላ ግን ስታስበው እንደዛ ብታደርግ ፈፅሞ የመንፈስ እረፍት እንደማታገኝ ገባት …እንደውም ከበፊቱ በበለጠ እራሷን አጠንክራ ወደሻሸመኔ መመለስ እንዳለባት ወሰነች፡፡ ከህግ አንፃር፣ አሁንም ጉዳዩ በጣም ደካማ ነው…በዛም ምክንያት ፍርድ ቤት መቆም አልቻለችም። ከመካከላቸው የትኛው ለእናቷ ግድያ ተጠያቂ መሆን አለመሆኗቸውን ማወቅ አለባት። በዚህም ምክንያት ወደሻሸመኔ ተመልሳ መጣች።

ከደቂቃዎች ዝምታ በኃላ"እንደምትመለሺ እርግጠኛ አልነበርኩም" ብሎ በግልፅ ነገራት።

‹‹ተስፋ አልቆርጥም አልኩህ እኮ።››

‹‹ አዎ አስታውሳለሁ" አለ በብስጭት፡

"አዲስአበባ ከመሄድሽ በፊት የነጋዴዎች ማህበር አመታዊ ክብረ በአል ላይ ያሳለፍሽው ምሽት እንዴት ነበር?"በማለት ያልጠበቀችውን ጥያቄ ጠየቃት፡

በመገረም "እዛ ዝግጅት ላይ መሄዴን እንዴት አወቅክ?" ስትል ጠየቀችው፡፡ ዝም አላት፡፡

" ጁኒየር ነው የነገረህ?"

‹‹አይ።"

‹‹እና››

‹‹ምክትሌ በዛን ቀን ማታ …በአውራ ጎዳናው ላይ ከሱ ጋር በመኪናው ውስጥ አይቶሻል።ከፍጥነት በላይ ይነዳ ስለነበረ ቀልቡን ስቦት ነበር››

‹‹አዎ ነበርኩ…. ጁኒዬር ጋብዞኝ ሄጄ ነበር››

‹‹እንዴት ነው ጥሩ ጊዜ አሳለፍሽ?››

"ቆይ ስርጉት የጁኒየር ሚስት እንደነበረች ማንም ያልነገረኝ ለምንድን ነው?"

" አልጠየቅሽም።ደግሞስ ስላልተሳካ የድሮ ትዳር ማወቅ ለአንቺ ምን ይፈይድልሻል ?"

‹‹ሙሽራይቱ የዳኛው ልጅ ሆና መገኘቷ እንግዳ ነገር አይመስልህም? ።" "ይህ በፍፁም እንግዳ ነገር አይደለም."
"የአጋጣሚ ጉዳይ ነው እያልከኝ ነው?."

"አይ አይደለም:: ስርጉት ለመጀመሪያ ጊዜ ጂኒዬርን ካየችበት ቀን ጀምሮ በፍቅር ወይም በፍትወት ውስጥ ነበረች። ሁሉም ያንን ያውቅ ነበር። እሷም ምንም አይነት በደል በማንም ላይ አልፈፀመችም። ሰሎሜ ስትሞት. እድሏን ተጠቀመችበት።››

‹‹እንደዛ ነው የምታስበው››
"በግልፅ…ጁኒየር እንዲወዳት ማድረግ አልቻለችም።ምክንያቱም በየሄደበት እየተንሸራተተ የሚከፈተውን የሱን የሱሪ ዚፕ መዝጋት ለማንም ሴት ቢሆን የሚከብድ ፈታኝ ስራ ነበር።››

"ገመዶ፣ ጥድፊያው ምን ነበር? ጁኒየር ከስርጉት ጋር ፍቅር አልያዘውም ነበር። ታዲያ ለምን ተጋቡ?ነው ወይስ የቤተሰብ ግፊት ነበረባቸው?"

‹‹እነሱኑ ብትጠይቂያቸው አይሻልም?›› ከተቀመጠችበት ተነሳችና ወደ መስኮቱ አመራች፡፡

‹‹ያው አንተም ቤተሰብ ነህ ብዬ እኮ ነው ››

‹‹አዎ…ቤተሰቦቼ ናቸው..ሁል ጊዜ አብረውኝ ነበሩ …››

ወደ እሱ ዞር አለች፣ እሱ ግን ምንም እያያት አልነበረም። ‹‹አባቴ ሲሞት ከመላው የሻሸመኔ ኑዋሪ ለቀብር ሥነ ሥርዓቱ የመጡት አቶ ፍሰሀ እና ጁኒየር ብቻ ነበሩ ። ከቀብር በኃላ አቶ ፍሰሀ  ወደ ሥራ ተመለሰ። ጁኒየር ደግሞ ወደ ትምህርት ቤት ኄደ። እኔ ወደ ቤት ሄድኩ።ብዙም ሳይቆይ ሰሎሜ ወደ ቤቴ መጣች። ትምህርቷን አቋርጣ ነበር የመጣችው። አባቴን በህይወት እያለ ብጠላውም በመሞቱ ግን ብቸኝነት እንደሚሰማኝ ታውቅ ነበር። አልጋዬ ላይ አብረን ተኛን እና እስኪመሽ ድረስ እዚያ ቆየን። ወደ ቤቷ የሄደችው እናቷ እንደምትጨነቅ ስለሰጋች ነበር። ››
ንግግሩን ሲያቆም በክፍሉ ውስጥ ስሜታዊ ፀጥታ ሰፈነ። አለም ምንም እንቅስቃሴ ሳታደርግ በታሪኩ ተመስጣ .. በመስኮቱ አጠገብ ቆማ ነበር። በብቸኝነት የነበረውን ያንን ሚስኪን ወጣት አሰበችና ደረቷ ላይ ህመም ተሰማት።

"ከእናቴ ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ ፍቅር የያዘህ በዛን ቀን ነበር?"ስትል ጠየቀችው፡፡

በቀጥታ ወደእሷ ተመለከተ… እና ከወንበሩን ለቆ ወደ እሷ ቀረበ። "የፍቅር ጉዳይ ካነሳሽ… ያንቺ እንዴት ነው?"

‹‹የእኔ ምን?››በንዴት ጠየቀችው

"ከጂኒዬር ጋር…..?ማለቴ….››ሆነ ብሎ ንግግሩን አንጠልጥሎ ተወው

"አንተ ባለጌ ነህ"አለችው

"እንደሞከረ እርግጠኛ ነኝ። እሱ ሁልጊዜም ይሞክራል።››ሲል አከለበት፡፡

"ገሃነም ግባ።"

በእሷን በጁኒዬር መሀከል ስላለው ሁኔታ ለማወቅ ለምን አጥብቆ ፈለገ ?‹‹… አሁን ፊቱ ላይ የሚነበብበት ስሜት ምንድነው ?ምናልባትም ንቀት፣ ወይስ ቅናት….››አሰላሰለች፡፡

"ለምንድነው  ክረምት እናቴ ወደኮፈሌ ስትሄድ የፈቀድክላት…ወደዛ ባትሄድ ኖሮ ከአባቴ ጋር አትገናኝም ነበር….ከአንተ ጋር የነበራችሁ ፍቅርም እክል አያጋጥመውም ነበር››
"ምናልባት  የመልክአ  ምድር  ለውጥ  አስፈልጎት  ይሆናል….ወይንም  ደግሞ  ዘመዶቾ ስለናፈቋት…" ሲል በቁጭት ተናግሯል።

‹‹የቅርብ ጓደኛህ ምን ያህል ይወዳት እንደነበረ ታውቃለህ አይደል?።››
"በትምህርት ቤት ያሉ ሁሉም ወንዶች እናትሽን ያፈቅሯት እንደነበረ አውቃለው እና ደግሞ የከበርቴው ልጅ ከሆነው ጁኒዬር ጋር ስለ ፍቅር ጉዳይ አላወራም ነበር››.

"ጁኒየር እሷ ላይ ባለው ፍቅር ምን እንደተሰማው ታውቃለህ?"

‹‹ነገርኩሽ እኩ…ስለፍቅር ከእሱ ጋር አውርተን አናውቅም››

"እሷን ለማግኘት ምንም ነገር ቢሞክር ትገድለው እንደነበረ ነው የነገረኝ:: የእውነት ሁለቱም ቢከዱህ ትገድላቸው ነበር ?"

"እርግጠኛ ነኝ እንደዛ ያለሽ ንግግሩን ለማሳመር ፈልጎ ነው."አላት፡፡

"ጁኒየርም መልሼ ስጠይቀው የተናገረው ይህንኑ ነው፣ ግን አይመስለኝም" አለች
"ብዙ የሚቀሰቅሱ ስሜቶች ነበሩ። እርስ በርስ ያላችሁ ግንኙነት ተደራራቢ እና ውስብስብ ነው።"

"የምን ግንኙነቶች?"

"አንተ እና እናቴ ትዋደዳላችሁ፣ነገር ግን ሁለታችሁም ጁኒየርን ትወዱታላችሁ።››

"ምንድን ነው የምታወሪው? ከጁኒየር ጋር ፣አልወዳደርም."

"ምናልባት እያወቅክ ላይሆን ይችላል፣ ነገር ግን ሌሎች ሰዎች እርስ በእርሳችሁ ያወዳድራችኋል። እና ከመካከላችሁ የትኛው ነው ሁልጊዜ ወደላይ የሚወጣው? አንተ። ያ ያስጨንቅሀል?። ››
"ይሄ የአንቺ የስነ ልቦናህ ጫወታ ነው"

"የእኔ አስተያየት ብቻ አይደለም። ስርጉት በቀደም ይሄንኑ ነገር ነግራኛለች፡፡። ሰዎች ሁል ጊዜ ሁለታችሁን እንደሚያነፃፅሩና ጁኒየር ሁል ጊዜ በሁለተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ነግራኛለች።"
42👍6
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ_አንድ


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

///

ገመዶ እኩለ ለሊት ላይ ስልኩ ጮኸ….

"ምንድን ነው ነገሩ" በማለት እየተነጫነጨ በተኛበት እጁን ዘረጋና ስልኩን ከኮመዲኖ ላይ አንስቶ ጆሮው ላይ ለጠፈና ‹‹ሄሎ››አለ፡፡

‹‹ኮማንደር መስማት አለብህ ብዬ ነው…ድንገተኛ ነገር ተከስቷል."ምክትሉ ነበር፡፡ ከመኝታው ተነሳና አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጠ፡፡

"…ምንድነው የተፈጠረው?"

"ከእርባታ. ቦታው …ማለቴ የቤተሰቦችህ እርባታ ቦታ፣ከዛ ነው የተደወለልን"አለው…

ከአልጋው ወርዶ ጂንስ ሱሪውን መልበስ ጀምሮ ነበር፡፡ጭንቅላቱ የፍርሀት ቅዝቃዜ ሲፈስ ታወቀው፡፡

"ምን አይነት ድንገተኛ አደጋ ነው?"
‹‹ገና አልተረጋገጠም..ኃይል ወደእዛው ልከናል፡፡›› ያልተቆለፈ ሸሚዙን ከቆለፈ በኋላ ቆሞ ጫማውን አደረገ፡፡

‹‹በቃ ቶሎ አጣርተህ ደውልልኝ…ወደእዛው እሄዳለው፣ይሄው እየወጣሁ ነው… ››ስልኩን ዘጋና ኮቱንና ኮፍያውን አድርጎ ወደ ኮሪደሩ ሮጠ።
/////

አለም በከባድ እንቅልፍ ውስጥ ነበረች፣ ለዚህም ነው የበሯን መንኳኳት በህልሟ መስሎ የተሰማት…።ህልም ውስጥ ነበረች….በመጨረሻ ተከታታይ የሆነው የጥሪ ድምፅ ከእንቅልፏ ቀስቅሷት።

"ተነሺ እና በሩን ክፈቺ."በቁጣ እየጮኸባት ነው፣ ቁጭ አለችና አልጋው ዳር ያለውን መብራት አበራችው… መብራቱ ሲበራ …. ብርሃኑ ዓይኗን አጭበረበራት።

"ገመዶ ነኝ… ክፈቺ?" ጮኸ ። ዝም አለችው፡፡

"በአስር ሰከንድ ውስጥ ካልተነሳህሽ በሩን ሰብረዋለው››

የግድግዳውን ሰዓት ተመለከተች። ከምሽቱ ስምንት ሰዓት ገደማ ነበር።

‹‹ኩማንደሩ ወይ ሰክሯል ወይም አብዷል።››ስትል አሰበች፡፡ ያም ሆነ ይህ አሁን ባለበት ሁኔታ በሯን ልትከፍትለት አልፈለገችም።

"ምን ፈለክ?"

ከእሱ መልስ ስትጠብቅ በራፉ ላይ ፈንጅ የተጣለበት ይመስል ጎጎጎጎ አለና ተከፈተ….ተንደረደረና መኝታ ቤቷ ገባ፡፡በድንጋጤ እየተንቀጠቀጠች አልጋዋ ላይ ቆመች "ምን እየሰራህ ነው?"ብላ ጮኸችበት በቆመችበት አልጋ ልብሱን እየሰበሰበች እርቃኗን ለመሸፈን እየጣረች ነው››

"አንቺን ለማግኘት ነው የመጣሁ ‹‹
ከአልጋው ላይ ጎተተና ወለሉ ላይ አቆማት፣የተጠቀለለችበትን አልጋ ልብስ ከላዬ ላይ ገፎ ወረወረው፣እርቃኗን በፓንት ብቻ ፊት ለፊቱ ቆመች፣ምን ሊያደርጋት እንደሆነ መገመት ሁሉ አልቻለችም፡፡

"ኩማንደር በሬን ገንጥለህ መኝታ ቤቴ ለመግባትህ በቂ ምክንያት እንዳለህ ተስፋ አደርጋለሁ።"

"ማብራሪያ አለኝ።" አለና መሳቢያውን ከፈተ እና ውስጡ ያሉትን ልብሶች ማተረማመስ ጀመረ።

"ንገረኝ ምን እየፈለክ ነው?."አለችና እርቃኗን ወደእሱ ሄዳ ሚያተራምሰውን  የቁምሳጥን በራፍ በዳሌዋ ገፋችና ዘጋችበት ፡፡

"ምን ፈልገህ ነው?"ዳግመኛ ጠየቀችው፡፡
"ልብስ። እንደዚህ እርቃንሽን  መውጣት ካልመረጥሽ በስተቀር  ምትለብሺው ልብስ ያስፈልግሻል››

‹‹ወደየትም አልሄድም››

" ጂንስሽ የት ነው ያለው?›› በ ወፍራም ድምፁ ጠየቀ ። "የትም አልሄድም። ስንት ሰዓት እንደሆነ ታውቃለህ?››

ድንገት ቀና ሲል ከአልጋው አጠገብ ባለው ግድግዳ ልብሷ ተሰቅሎ አየው፡፡ ጂንሱን ከተሰቀለበት ላይ አወረደና ወረወረላት፣ መያዝ ስላልቻለች ወደ ወለሉ ወደቀ።
ከጫማዋቾ ውስጥ አንዱን መረጠና ወደእግሯቾ አቀረበላት፡፡ ዝም ብላ ፈዛ ታየው ጀመር፡፡ "እሺ.. እንዳለብስሽ ትፈልጊያለሽ?"

እሱን ለማስቆጣት ምን እንዳደረገች መገመት አልቻለችም። እርቃኗን እሱ ፊት ቆማ መከራከሩ ስለደከማት ጆንሱን አነሳችና አጠለቀች ፡፡ከላይ ሹራብ ለበሰች….ከኮመዲኖ መሳቢያ ውስጥ አንድ ካልሲ አወጣችና አራግፋ አጠለቀችና ጫማዋን አደረገች፡፡ በመጨረሻም ዞር ብላ አየችው።

"እሺ ይሄው ልብስ ለብሻለሁ …አሁን ምን እየተካሄደ እንደሆነ ንገረኝ ?"

"እየሄድን  እነግርሻለው  ››አለና  እጆቿን  በመያዝ  እየጎተተ  ይዞት  ወጣ  ፡፡በንዴት እየተንቀጠቀጠች ነበር።

‹‹እንዲህ እንድታደርገኝ ማን ነው የፈቀደልህ?››

"አንገትሽን መስበር አለብኝ…..አላደረገውም››በማለት ወደእሷ ተጠጋና ከንፈሯን ሳማት።ያለተቃውሞ ተሳመችለት፡፡ምላሱን ወደ አፏ ውስጥ አስገባ። በዚህ ጊዜ በቁጣ ስሜት መነጨቀችውና እራሷን አላቀቀች፡፡

ኮትዋን ከሳሎን በራፍ አካባቢ ካለው ማንጠልጠያ አነሳችና ያዘች፡፡ ከቤት ይዞት ወጣ " በሩስ?"ብላ ጠየቀችው ።
"የሚጠግን ሰው እልካለሁ።"

"በዚህ ለሊት?"

"በፈጣሪ … በሩን እርሺው..በአካባቢው ቤትሽን በንቃት የሚጠብቁ ፖሊሶች አሉ" ብሎ ጮኸ።

‹‹የሚጠብቁ ነው ሚሰልሉኝ?››

እጇን ጨምድዶ እንደያዛት ስትጠብቀው ወደነበረ ታክሲ ውስጥ ይዞት ገባ፡፡

"በፈጣሪ ገመዶ…ምን እየተፈጠረ ነው……?ነው ወይስ እያሰርከኝ ነው?››

‹‹እያሰርከኝ ..አንቺን……?ምነው ወንጀል ሰርተሸል እንዴ?›› ፡፡

‹‹እና ምንድነው ንገረኛ….?ወደየት እንደምሄድና ለምን እንደምሄድ የማወቅ መብት አለኝ›› ።

"የእርባታ ቦታው እየተቃጠለ ነው."

‹‹የእርባታ ቦታው.?.የነጁኒዬር?››

‹‹አዎ››

‹‹ወይ..ፈረሶችህ ተረፉ?››

ፈረሶቹን ምን ያህል ይወዳቸውና በምን ያህል መጠን ይንከባከባቸው እንደነበረ ስለምታውቅ ነው ቀድማ ስለፈረሶቹ የጠየቀችው፡፡

‹‹አላውቅም…የወደመውንና የተረፈውን ስንደርስ ነው የምናውቀው፡፡››
////
ሲደርሱ እሳቱ ከፈረሶቹ ጋጣ አካባቢ እየተንቀለቀለ ነው…በአንድ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ሚገኘው የእንጨት ፋብሪካው ከአደጋ ውጭ ነው፡፡ቢሆንም በንፋስ ታግዞ ወይም በሆነ ምክንያት እሳቱ እዛ ቢደርስ ከፍተኛ ውድመት እንደሚያስከትል የታወቀ ነው፡፡

እንደደረሱ መኪናዋ ስትቆም ኩማንደሩ ከመኪናው ወረደና ወደእሳቱ አቅጣጫ ተንቀሳቀሰ…አለም ከኋላው ተከተለችው፡፡ከአንዱ የፈረስ ጋጣ ጭስ ሲትጎለጎል ይታያል…አለም ሆዷ ተገለባበጠባት። የእሳት አደጋ መከላከያ ሰራተኞች፣ የደንብ ልብሳቸውን ለብሰው እሳቱን ለመቆጣጠር እየሞከሩ ነበር።ብዛት ያላቸው የእርባታው ሰራተኞችና የአካባቢው ኑዋሪዎች ቅጠለም አፈርም እየተጠቀሙ እሳቱ እንዳይዛመት ለመቆጣጠር እየተረባረቡ ነው፡፡
አንድ ሰው ወደኩማንደሩ ቀርቦ"በጣም ብዙ ጉዳት ከማድረሱ በፊት ደርሰውበታል" ሲል ነገረው፡፡

‹‹ሰውስ አልተጎዳም?››

‹‹አንድ የተጎዳ ሰው አለ…››የሚል ድምፅ ሰማ፡፡

"ማንው የተጎድቷል?"

‹‹በጣም አሰቃቂ ትዕይንት ነበር።ከፈረስ ተንከባካቢዎች አንዱ ነው… በቂ አየር ወደ ሳምባዋ መሳብ አልቻለችም። ፈረሶችን ለማዳን ሲሯሯት አንድ እግሩም ተሰብሯል››

በዛ ቅፅበት አንድ ፈረስ እየጮኸ ነበር፣ በግልጽ ህመም ላይ እንዳለ ያስታውቃል። አለም እስካሁን ሰምታ የማያውቀው እጅግ አሳቃቂ ድምፅ ነበር የሰማችው። ገመዶ በፍጥነት ወደእዛው አመራ…ከኃላው ተከተለችው….የአቶ ፍሰሀ ቤተሰቦች በጠቅላላ በለሊት ቢጃማቸው በአካባቢው ነበሩ ፡፡መኖሪያ ቤታቸው ከእርባታው ድርጅት ብዙም ሰላማይርቅ እንደሰሙ በእግራቸው ነው ሮጠው ወዲያው ነው የደረሱት፡፡ ሳራ እያለቀሰች ነበር። ፍሰሀ

እራሱን ተቆጣጥሮ በፅናት ቆሞ ይታያል…ጁኒዬር እናቱን አቅፎ ያፅናናል፡፡ ገመዶ ወደ ጎን ገፋቸው እና እሳቱ ጠፍቶ ጭሱ ብቻ ከሚታይበት ጋጣ ውስጥ ገባ ፡፡
47👍4🔥1
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ_ሁለት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

////

ከኪሊንኩ ጀርባ ያለው የዶ/ር ኤሊያስ  ቢሮ ምናልባት አለም ከዚህ በፊት ካየቻቸው ቢሮዎች ሁሉ የተዝረከረከ ሆኖ ነው ያገኘችው፡፡

"ዶክተር ኤሊያስ እኔን ለማየት ስለተስማማህ አመሰግናለሁ።"

"ችግር የለም …ዛሬ ብዙም ስራ አልነበረኝም " ከቀጥታ ከጠረጴዛው አጠገብ ያለውን የእንጨት ወንበር ላይ ያሉትን መጽሔቶችን አስነሳና ጠረጴዛ ላይ በማድረግ ለአለም እንድትቀመጥበት አመቻቸላት፡፡

"አንቺን ሳይሽ ብዙም አልተገረምኩም

"አላት በቅንነት ።

"ለምን?"

"ዋና አቃቢ ህጉ ደውሎ አንዳንድ ጥያቄዎችን ልትጠይቂኝ እንደምትፈልጊ ነግሮኝ ነበር።"

"ዛሬ ከከተማ ውጭ ያለ መስሎኝ ነበር."

"አይ ከቀናት በፊት ነበር ሰሞኑን ትመጣለች ቡሎ የነገረኝ ።"

"ገባኝ…ለሊት የእሳት ቃጠሎ ቦታው እንስሳቶችን ለመርዳት ስትሯሯጥ ስለነበርክ…ዛሬ እንዲህ ንቁ ሆነህ ቢሮህ አገኝሀለው ብዬ አላሰብኩም ነበር።"

በመደነቅ‹‹እንዴ እዛ እንደነበርኩ በምን አወቅሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡

‹‹እኔም እንዳጋጣሚ እዛ ነበርኩ…አሁን ጊዜህን ሳልሻማብህ ቀጥታ ወደጉዳዬ ልግባ …የእናቴ የሰሎሜን ግድያን በተመለከተ መረጃዎችን እየሰበሰብኩ ነው….እባክህ አንተ በአቶ ፍሰሀ የእንስሳት እርባታ ድርጅት ውስጥ የእንስሳት ሀኪም ሆነህ እንደመስራትህ የምታውቀው ነገር ይኖር ይሆን ?" ስትል አሳዛኝ በሆነ የድምፅ ቅላፄ ጠየቀችው፡፡

"በእርግጥ እናትሽን አውቃታለው . እሷ በጣም አስደማሚ ሴት ነበረች. በእሷ ሞት ያላዘነ ሰው የለም ››

"አመሰግናለሁ፣ በዛን ወቅት በአቶ ፍሰሀ የእርባታ ድርጅት ውስጥ የእንስሳቱን ጤንነት ሚከታተሉት አባትህ እንደነበሩ ማወቅ ችያለው፡፡ "

" ልክ ነው …በዛን ወቅት አባቴ ነበር….እሱ ከሞተ በኋላ ግን ስራውን እኔ ተረክቤያለሁ." "አባትህ ስለ ሰሎሜ ግድያ ሁኔታ የሆነ ነገር ነግሮህ ይሆን?››

"በቀዶ ጥገና ቢላዋ መገደሏን በሰማ ጊዜ እንደ ሕፃን ነበር ተንሰቅስቆ ያለቀሰው››

"አባትህ እናቴ የተገደለለችበት መሳሪያ ከየት እንደመጣ አውቋል›?›

"አዎ …ያ አባቴ እንስሳቱን ለማከም የሚጠቀምበት መሳሪያ ነበር፣እናቴ ነበረች የሸለመችው የስሙ የመጀመሪያ ፊደል ተቀርፆበት ነበር ፡፡እንዴት አድርጎ ከቦርሳው እንደወደቀበት ነው ግራ የገባው፡፡››

"እንደዛ አይነት ግድ የለሽነት ከእሱ ባህሪ ጋር አይሄድም አይደል?"

"ትክክል ነሽ….አባዬ ለህክምና እቃዎቹ ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያደርግ አይነት ሰው ነው
…በቆዳ በተለበጠ የእንጨት ሣጥን ውስጥ ነበር የሚያስቀምጣቸው…ያ ስለት ከሳጥኑ እንዴት እንደወደቀ ፈጽሞ ማወቅ አልቻለም ነበር, ››

"እናቴ በሞተችበት ቀን አንተ እዚያ ነበርክ?"

"ይህን ቀድመሽ ታውቂያለሽ ብዬ አስባለሁ። አባዬን ለመርዳት ትምህርት ከሌለኝ በስተቀር እዛ እገኝ ነበር …በዛም ቀን  አብሬው ሄጄ ነበር።››

"ገመዶ እዚያ ነበር?"

"በእርግጥ ኩማንደር እዚያም ነበረ።››

"ለሊቱን ሙሉ."

‹‹እሱን እርግጠኛ አይደለሁም…በመሀል አቋርጦ የሄደ ይመስለኛል››

"አባትህ የህክምና ቁሳቁስ የሚይዝበትን ሳጥን የሆነ ቦታ አስቀምጦ ዞር ብሎ ያውቃል?" ኤሊያስ ማሰላሰል ጀመረ … መልስ መስጠት እንደማይፈልግ ነገራት፡፡

‹‹ በዚያ ቀን በዛ አካባቢ ሌላ ማን ነበር?"ስትል ሌላ ጥያቄ ጠየቀችው፡፡

ለማስታወስ ሲጥር ተመለከተች‹‹‹ጁኒየር፣ ገመዶ፣ ጋሽ ፍሰሀ….እናትሽ….ስርጉት."

‹‹ ማን… ስርጉት ነበረች? ››

‹‹አዎ ነበረች …ከዛ ወደ ቤት መሄድ እንዳለባት ተናገረች እና አካባቢውን ለቃ ሄደች፡፡

‹‹ከግቢው ወጥታ ስትሄድ አይተሃታል….››

‹‹አይ መሄድ አለብኝ ብላ ስታወራ እንጂ ወጥታ ስትሄድ አላየኋትም….›› " ስለ ሊቁ ምን ማለት ይቻላል? እሱ በአካባቢው ነበር?"

‹‹እሱ ሁሌ  በሁሉም ቦታ የሚዞር..በሄድሽበት ቦታ የማታጪው አይነት ንክ ነበር ፣እውነቱን ንገረኝ ካልሺን ግን በዛን ቀን እሱን እዛ ቦታ እንዳየሁት አላስታውስም››

"እርሱን ካላየኸው በሰሎሜ ደም በተሸፈነ ልብሱ በቁጥጥ ስር ሲውል አልተገረምክም?"

‹‹በእርግጥ አልተገረምኩም…. ምን አልባት እኔ ሳላየው ጊቢ ውስጥ ሲዞዞር ከአባዬ ቦርሳ የወደቀውን ቢላዋ እንዳገኘው ገምታለው፣ ከዛ እናትሽን ገድሏታል ብዬ አስባለው.››

‹‹ነገር ግን ከዛ ሁሉ የአባትህ የህክምና መሳሪያዎች መካከል አንድ ቢላዋ ብቻ ሾልኮ መውደቁ ግራ መጋባት ውስጥ አይከትም… ?››

ዝም አላት…..፡፡

ይህ ዶ.ር የሶስቱም ተጠርጣሪዎች ጓደኛ ነው። በዛ ላይ በቋሚነት ለአቶ ፍሰሀ ተቀጥሮ የሚሰራ ሰው ነው፡፡የሚያውቀው ነገር እንኳን ቢኖር በምንም አይነት ተአምር አሳልፎ ሊሰጣቸው እንደማይፈቅድ አወቀች፡፡ከዚህ በላይ ጊዜዋን ማባከን ፋይዳ እንደሌለው ስላመነች ከመቀመጫዋ ተነሳችና አመስግናው ወደ ሁለተኛ ጉዳዮ አመራች፡፡
///
የእርባታ ድርጅት የእንቅስቃሴ አልባ ሆኗል ። የጽዳት ሠራተኞች ከቃጠሎ የተረፈውን ፍርስራሹን እና አመዱን እየሰበሰቡ እና እየጠረጉ በአካባቢው የቆመው መኪና ላይ እየጫኑ ነው። ኩማንደሩ በአካባቢው ወዲህ ወዲያ እየለ የሚሰራውን እየተመለከተ ነው፡፡ አለም ከመኪናዋ ስትወርድ አይቶታል፣ ነገር ግን እሷን ለማናገር ሲሞክር በአካባቢው የነበረው የእሳት አደጋ ተቆጣጣሪ ሰለጠራው ወደእዛ ለመሄድ ከተንቀሳቀሰ በኋላ ሀሳቡን ቀይሮ ቆሞ ጠበቃት፡፡ ደረሰችበት…ሰላም ይለኛል ብላ ስትጠብቅ

"እዚህ ምን እየሰራሽ ነው?"ብሎ ጠየቃት፡፡

‹ከሳራ ጋር ሻይ ልጠጣ ነው የመጣሁት።››

በመደነቅ አፍጥጦ ተመለከታ‹‹ከእሷ ጋር ደግሞ ከመቼ ወዲህ ነው ጓደኛ የሆናችሁት?››

“ሃሳብ የእኔ ሳይሆን የእሷ ነበር” አለችው።

"እሺ ተዝናኑ" አለና ፊቱን አዙሮ ሲጠራው ወደ ነበረው ሰውዬ ሄደ፡፡

እሷም ወደማረፊያ ቤቱ ተራመደች..አቶ ፍሰሀ  በቤቱ በረንዳ ላይ ቆሞ ነበር፣ ስትጠጋ ፍርሃቷ እንዳይታይ ለማድረግ ሞክራለች።

"እንዴት ነህ … ጋሽ ፍሰሀ?"

"  ሰዓት  አክባሪነትሽ  የሚደነቅ  ነው…እናትሽም  ልክ  እንደዚህ  ነበረች››አላት፡፡ለምን እንደመጣች እንደሚያውቅ ተረዳች

‹‹አመሰግናለው››አለችው፡፡

‹‹ምንም አይደል››

"ኩማንደሩ እሳቱን ያስነሳውን ሰው  በቁጥጥር ስር እንደሚያውለው  ተስፋ አደርጋለሁ። እኔም ተገቢን ፍትህ እንድታገኙ አስፈላጊውን ሁሉ አደርጋለሁ።"ስትል ቃሏን ሰጠችው፡፡

"አዎ፣ እኔም ተስፋ አደርጋለው… ሁሉንም ነገር ችላ ማለት እችላለሁ። ነገር ግን ያን የመሰለ ተወዳጁን የገመዶን ፈረስ እንዲሞት ያደረገውን ሰው ግን ይቅር አልለውም።ያን ፈረስ በማሳደግና በመንከባከቡ ይሰማው የነበረውን ኩራት እኔ ነበርኩ የማውቀው።"

በዚህ ጊዜ ጁኒዬር ከውስጥ ወጣ…በውብ ፈገግታ ተሞልቶ የሞቀ ሰላምታ ሰጣት፡፡ አለም"ወደ ውስጥ ብገባ ይሻለኛል… እናትህን ብዙ አላስጠብቃት" አለቸው ።
ጁኒየር እጁን ትከሻዋ ላይ ጫነና "እናቴ የትላንት ማታውን ጥፋቷን ማረም ትፈልጋለች። ግብዣዋን ስለተቀበልሽ በጣም ተደስታ ነበር። አንቺን ለማየት በጉጉት እየጠበቀችሽ ነው።››አላት

‹‹ጥሩ››ብላ ወደ ውስጥ ገባች፡፡
አገልጋይዋ በራፉ ድረስ መጥታ ተቀበለቻት።‹‹ግቢ።››ብላ ወደ ውስጠኛው ክፍል እየመራች ወሰደቻትና ከሳራ ጋር አገናኘቻት፡፡

ከሳራ ጋር ተጨባበጡና ጉንጭ ለጉንጭ ተሳሳሙ፡፡
አለም የክፍሉን ዙሪያ ገባ እየተመለከተች"እንዴት የሚያምር ክፍል ነው?!"

"ወደድሽው?።"

‹‹በጣም እንጂ…››
42👍7👏2
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ_ሶስት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///

"ምንድነው የነገረችሽ?"

"እኔ ዲቃላ መሆኔን ."

የጁኒየር ፊት በድንጋጤ ባዶ ሆነ።

"እውነት ነው አይደል?"
ጁኒየር እጆቹን ዘረጋና እቅፉ ውስጥ አስገባት… እንባዋ በመጨረሻ የዐይን ሽፋኖቿን ሞልተው ያለከልካይ ፈሰሰ።

"ሰሎሜ ከኮፈሌ ተመልሳ መጣች። ከገመዶ ጋር ለመታረቅ ተዘጋጅታ ነበር።ፍቅራቸውን ለማደስ ተስማምተው ነበር …የመጋባት እድል ሁሉ ነበራቸው…በመሀል ግን ለማንኛችንም ሳትነግረን መልሳ ጠፋች….በኋላ ነው አንቺን ማረገዟን ስላወቀች እንደጠፋች ያወቅነው፡፡››ሲል አስረዳት፡፡

በእፍረት ፊቷን በእጆቿ ሸፈነች።
" ኦ አምላኬ በጣም ቢጠላኝ አይገርምም።››

ጁኒየር እጆቿን ከፊቷ ላይ አንስቶ በቅን ልቦና የሚወዳቸውን ጥቆቁር አይኖችን እየተመለከተ።

"ገመዶ አንቺን አይጠላሽም አሌክስ። ማናችንም ብንሆን አንጠላሽም…ያ ከአመታት በፊት ተጋፍጠን በይቅርታ ያለፍነው ጉዳይ ነው››

በንግግሩ በምሬት ሳቀች።‹‹ለምን አያቴ ሁሌ እኔ ላይ ጥብቅ እንደምትሆን እያሰብኩ እበሳጭ ነበር …በስንት ሰዓት ከቤት እንደወጣው? በስንት ሰዓት እንደተመለስኩ..?ከማን ጋር እንደነበርኩ ከአግባቡ ያለፈ ቁጥጥር ታደርግብኝ ነበር…ምክንያቷ አሁን ነው የገባኝ
…ለካ እናቴን ያጋጠማት ነገር እንዳያጋጥመኝ ፈርታ ነው፡፡አሁን ነው የገባኝ፡››

"ይሄ ከሃያ አምስት አመታት በፊት የሆነ ድርጊት ነው ፣ አሌክስ አሁን ስለዛ ማሰብ አቁሚ "

"አያቴ በእውነት እኔን ለምን እንደማትወደኝ የሚያብራራልኝ ታሪክ ነው… የሰሎሜን ህይወት አበላሽቻዋለሁ…እና ለዛ ፈጽሞ ይቅር ሳትለኝ ነው የሞተችው…. ሰሎሜ ገመዶን አጥታለች …ፍቅራቸው እንዳይሆን ሆኖ ተሰባብሯል … እና ሁሉም የሆነው በእኔ ምክንያት ነው››.

‹‹ኦህ፣በእግዚአብሔር !ተረጋጊ እንጂ!"
አለም ከእቅፉ ወጣችና ወደ መኪናዋ ሮጠች…መኪና ውስጥ በመግባት አስነሳችና አካባቢውን ለቀቀች።

."ምንድነው ነገሩ?" አለም ወደ መኪናዋ አቅጣጫ ስትሮጥ ያያት አቶ ፍሰሀ ጠየቀው።

"ሁለታችሁም እሷን ተዋት" ሳራ ከውስጥ እየወጣች ለባሏ መለሰች፡፡

ጁኒየር ወደ እናቱ ዞረና።

"እማዬ እንዴት እንዲህ ታደርጊያለሽ? እንዴት ልጅቷን እንዲህ ትጎጂያታለሽ?"

"ልጎዳት አስቤ አይደለም የነገርኳት፡፡››

"ምን ነግራት ነው?" አቶ ፍሰሀ ጠየቀ ፡፡

ጁኒየር “በእርግጥ ጎድተሻታል። ደግሞ አቅደሽበት ነው ያደረግሽው… ለምን ነገርሻት?"

‹‹ምክንያቱም እሷ ማወቅ ስላለባት። አለምን የምትጎዳት እራሱ አለም ብቻ ነች። ሸቅዠቷን እያሳደደች ነው። የምትፈልጋት አይነት ቅድስት የሆነች እናት በሰሎሜ ውስጥ አልነበረችም። ሰሎሜ ምትባል ድንቅ እናት እንደነበረቻት በማይረባ ጭንቅላቷ ደምድማለች። እናቷ ምን ያህል ተንኮለኛ እና ሀጥያተኛ እንደሆነች ልጅቷ ማወቅ አለባት.. እናቷ ስትማግጥ እሷን ዲቃላ እንዳረገዘቻት የማወቅ መብት አላት››

" አንቺ እኮ ጤነኛ አይደለሽም!" አቶ ፍሰሀ ተበሳጨባት፡፡

አቶ ፍሰሀ በጸጥታ ወደ መኝታ ቤት ገባና ከኋላው በሩን ዘጋው፡፡ሳራ በአልጋዋ ላይ ያሉትን ትራስ ደራርባ ተደግፋ መፅሃፏን እያነበበች ነበር…እሱን ስታይ መፅሀፉን ከደነችና አጠገቧ ያለው ኮመዲኖ ላይ አስቀመጠች ።

ወደአልጋው ቀረበና " ላናግርሸ እፈልጋለሁ።"አላት፡፡

"ስለ ምን?"

‹‹ዛሬ ከሰአት በኋላ ስለተፈጠረው ነገር።››
"ራስ ምታት እየፈለጠኝ ነው…ለእራት ወደታች ያልመጣሁትም ለዛ ነው"

‹‹የሆነ መድሀኒት አልወሰድሺበትም?"

"አዎ ወስጄለሁ…አሁን በመጠኑ እየተሻለኝ ነው ።"የሳራ የራስ ምታት በትዳራቸው ልክ አብሯት የቆየ ህመም ስለሆነ የተለመደ ነው፡፡

በአልጋው ጫፍ ላይ ተቀመጠ እና አቀርቅሮ ሀሳብ ውስጥ ገባ፡፡

" ምንድነው ፍሰሀ ?አሁንም የሚያሰጋን ችግር አለ እንዴ?››ጠየቀች፡፡

"አይ..ሁሉም ነገር ሰላም ነው።"

"ታዲያ ለምን ታስባለህ…?እግዚአብሔር ይመስገን ብቸኛው የሞተው ፈረስ የገመዶ ነው
።››
አቶ ፍሰሀ ምንም አስተያየት መስጠት አልፈለገም ። ሳራ ጆ ለገመዶ ያላት ስሜት ፈጽሞ አይለወጥም፤በዚህ ጉዳይ ከእሷ ጋር መነጋገር ጥቅም አልባ እንደሆነ እርግጠኛ ነው፡፡ከእሷ ጋር ሊወያይ የመጣው ስስ ስለሆነ ጉዳይ ነው። ቃላቱን በጥንቃቄ ለመምረጥ ትንሽ ጊዜ ወሰደበት.

"ሳራ ዛሬ ከሰአት በኋላ -……" "በጣም ተበሳጭቼ ነበር" አለችው፣ ፡፡

" ተበሳጭተሽ ነበር?" ፍሰሀ ትዕግሥተኛ ሆኖ ጠየቃት፡፡ወደ ድምዳሜው ከመዝለሉ በፊት ከእሷ ወገን ያለውን የታሪኩን ገጽታ መስማት ፍልጓል።

"የአለምን ስሜትስ የጎዳሽ አይመስልሽም…?"

"ዲቃላ መሆኗን ስላወቀች ብቻ አይደለም የተናደደችው….እሷ በተፈጥሮዋም ብስጩ ነች:: "

"እኔ በእሷ ቦታ ብሆን አይገርመኝም… ወላጆቼ የጋብቻ ሰርተፊኬት እንዳላቸው በጭራሽ አጣርቼ አላውቅም.., እና ባይኖራቸውም ምንም አይመስለኝም ነበር.››

" ሁሉም ሰው ለነገሮች ያለው ምላሽ የተለያየ ነው››

‹‹ አለም ግን ስሜታዊነት የሚያጠቃት ወጣት ሴት ነች።"

"እሷ ይሄን ታሪክ ለመቀበል የሚያስችል ጥንካሬ እንዳላት አምናለው."ስትል መለሰችለት

"በእርግጥ የምትይውን ያህል ጥንካሬ እንዳላት እርግጠኛ አይደለሁም።በረንዳ ላይ ቆሜ እያየችኝ እኔን እንኳን ሀሳትሰናበተኝ ነው ገፍትራኝ ሮጣ የሄደችው፡፡››

የሳራ ፈገግታ ተሰበረ። "ስለነገርኳት ትወቅሰኛለህ? ስህተት የሰራው  ይመስልሃል?"ስትል ጠየቀችው፡፡

በዛ ልብን በሚሰረስር የግሏ የሆነ ልዩ እይታ ስታየው፣ ልቡ ቀለጠ። ሁል ጊዜም የዚህ አይነት አስተያየት ስታየው የሚሆነው እንደዚሁ ነው። ፍሰሀ በስሱ ይዳብሳት ጀመር፡፡

‹‹ውዴ ስለነገርሻት አልወቅስሽም። ግን የነገርሽበት መንገድ እንደዚህ ባይሆን ጥሩ ነበር፡፡ እንደዛ ከማድረግሽ በፊት ከጁኒዬር እና ከእኔ ጋር መመካከር ነበረብሽ…በህይወቷ ሙሉ ባታውቀው የሚሻል ታሪክ ነበር፡፡››

"አልስማማም" ስትል ሳራ ተከራከረች።
አቶ ፍሰሀም "እናቷ እና አባቷ አብረው ከተኙ በኃላ አለመጋባታቸው ወይ መጋባታቸው በእሷ ልጅነት ላይ አሁን ምን ለውጥ ያመጣል? ይህ በቡዙ ወጣት ሴቶች ህይወት ላይ የሚያጋጥም በጣም የተለመደ ነገር ነው..››አላት፡፡

"ልጅቷ ስለ ሰሎሜ ያላት አመለካከት ላይ ግን ለውጥ ያመጣል። ››

‹‹እንዴት?››

‹‹ሰሎሜ ልጅቷ የምታስባትን አይነት ቅድስት ሴት አይደለችም…ይሄን ማወቋ የእሷን የግድያ ጉዳይ ለማወቅ የምታደርገውን ልፋትና ጥረት ቆም ብላ እንድታይ ያግዛት ይሆናል….ይልቅ ከአሁን በኃላ ሁላችሁም ከአለም ጋር መገናኘቱን እና መወያየቱን ማቆም አለባችሁ፡፡››

"ለምን?"ግራ ገብቶት ጠየቀው፡፡

"ለምን? ምክንያቱም እሷ እኛን ለማጥፋት እየሞከረች ነው…ለዚህ ነው. እሷን ለመፋለም የወሰንኩ…. ያለኝን ጥይት ነው የተጠቀምኩት….አንተን እና ጁኒየርን ለመጠበቅ እየሞከርኩ ነበር."

በእውነቱ፣ ፍሰሀ እንደ አለም ያለ በራስ መተማመን የነበራትን ሴትን ለመጋፈጥ ለሣራ ትልቅ ድፍረት እንደሆነ አሰበ። ያደረገችው ስህተት ቢሆንም ሳራ ያደረገችውን ነገር ያደረገችው ቤተሰቧን ልትጠብቅ እንደሆነ ተረድቷታል። የጀግንነት ጥረቷ ከትችት የተሻለ ነገር ይገባዋል ብሎ አሰበ እና ጎንበስ ብሎ ግንባሯን ሳመ።

ለስለስ ባለ ንግግር" የትግል መንፈስሽን አደንቃለሁ… ግን ማናችንም ያንቺን ጥበቃ አንፈልግም ።"አላት፡፡
46👍3
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ_አራት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

///
ስርጉት እኩለ ለሊት ቢያልፍም ኪችን ውስጥ ስራ እየሰራች ስለነበር አልተኛችም..ድንገት ግን የውጭ በራፍ ሲንጎጎ ስትሰማ እጇ ላይ የነበረውን የሸክላ ሰሀን ለቀቀችውን ወለል ላይ አርፎ ፍርክስክስ ብሎ ተሰበረባት፡፡የበሩ መንኳኳት እንደቀጠለ ነው..ቶሎ ብላ ኪችኑን ለቃ ወጣችና ወደሳሎን ሄደች ...

" በፈጣሪ ማን ነው ?" ጠየቀች፡፡

"ስርጉት… እኔ ነኝ ..ክፈቺ."

የሰማችውን ድምፅ ልታምን አልቻለችም  ….ለማሰብ ጥቂት ሰከንድ እንኳን ሳታቅማማ
ተንደርድራ ወደበሩ ሄደችና ከፈተችው፡፡

በረንዳው ላይ ተገትሯል…ለደቂቃዎች በራፉን አንደያዘች በትኩረት ተመለከተች፣

‹‹በሰላም ነው ጁኒዬር?››

‹‹ሰላም ነው››መለሰላት፡፡

‹‹ግባ …››አለችና ከበራፉ ዞር አለችለት..ሰተት ብሎ ገባ፡፡

"እዚህ ምን እየሰራህ ነው?"

"አንቺ ጋር መጥቼ ነዋ…ክብር ዳኛ ተኝቶ እንደሚሆን እገምታለው››

"አዎ አባዬ በጊዜ ነው የተኛው።››

የቀድሞ ባለቤቷ በዚህ እኩለ ለሊት እሷን ብሎ የሚመጣበት አንድም አሳማኝ ምክንያት ሊመጣላት አልቻለም፡፡ ቢሆንም ግን….ግድ አልነበራትም። እዚህ መገኘቱ በቂ ነበር። አባቷ ካገመሰው ቦድካ በብርጭቆ ቀዳችና ሰጠችው፡፡ተቀበላትና በቆመበት አንዴ ተጎነጨለት፡፡

"ይህ የሌሊቱ የመጀመሪያ መጠጥህ አይደለም አይደል?"

"አይ..አይደለም." ድምፁን ዝቅ አድርጎ መለሰላት ፡፡

"ወደእኔ እንድትመጣ ለወራት ስጠብቅ ነበር ። ከዚህ ሁሉ ጊዜ በኋላ አሁን ወደእኔ ስትመጣ ደግሞ ለምን የሚል ጥያቄ በአእምሮዬ እየተመላለሰ ነው፡፡››አለችው፡፡

" ፈልጌ ነበር." አላት፡፡

ለጁኒየር አእምሮ ያ በቂ ምክንያት እንደሆነ ታውቃለች። ሶፋው ላይ ተቀመጠና ጎትቶ ከጎኑ አስቀመጣት።ከበርካታ ደቂቃ ፀጥታ በኋላ " በእርባታ ድርጅቱ ውስጥ ስለተፈጠረው ችግር ሰምቻለሁ" አለችው.

"አሁን ሁሉ ነገር ሰላም ሆኗል….እሳቱ በጊዜው ነው የተደረሰበት…በጣም የከፋ ሊሆን ይችል ነበር."

እያመነታች እጇን እጁ ላይ አሳረፈች፡፡
‹‹አንተ ግን ራስህን ጠብቅ…ንብረታችሁን ለማቃጠል የደፈረ ጠላት በእናንተም ላይ ቀጥታ ጥቃት ከመፈፀም ወደኃላ ላይል ይችላል፡፡››

"አሁንም ለደህንነቴ ትጨነቂያለሽ?"

"ሁልጊዜ።"አለችው፡፡

‹‹ሰሎሜ እንዳንቺ ጣፋጭ ሆኖልኝ አታውቅም። ››

"የደከመህ እና የተቸገርክ ትመስላለህ?።"

"አዎ ደክሞኛል!!።"

ሶፋው ላይ ሙሉ በሙሉ ወጣና ትራሱን ተንተርሶ አረፈ። "በሰሎሜ ግድያ ላይ ያለው ውዥንብር እየበጠበጠን ነው።ሁሉም ነገር እንደ ገሃነም ተስፋ አስቆራጭ ነው።››አላት፡፡ከትራሱ ቀና አለና እሷ ትከሻ ላይ ተንተራሰ"እህ…ጥሩ መዓዛ አለሽ…ይህ ሽታ ናፍቆኝ ነበር. በጣም ንጹህ. ነው፡፡

"ስለዚህ ምርመራ በጣም የሚያስጨንቅህ ምንድን ነው?"

"ምንም የተለየ ነገር የለም። አለም ነች ። እሷ እና እናቴ ዛሬ ተፋጠው ነበር። እናቴ ስለሰሎሜ አንዳንድ መጥፎ ነገሮችን ነገረቻትና በጣም እንድታዝን አደረገቻት… ያ ጥሩ ትእይንት አልነበረም።››

ክንዱ በወገቧ ዙሪያ ላከውና አቀፋት ..እጇን አነሳች እና ጭንቅላቱ ላይ አሳርፋ እንደህፃን ልጅ ታሻሸው ጀመር፡፡

"ዋሻተኋታል እንዴ?"

"የማጣት ፍርሀት የወለደው ውሸት"ጁኒየር ፍላጎት በማጣት አጉተመተመ።

"እናቷ በተገደለችበት ቀን በረንዳ ላይ እንደነበርኩ አልነገርኳትም።ለምን እንደዛ አደረክ ?"

" በተከታታይ ጥያቄዎች እንድታጣድፈኝ አልፈለኩም።አንዳንድ መመለስ የማልችላቸውን ጥያቄዎች ብትጠይቀኝ እንዴት አደርጋለው?›››

‹‹ ጁኒየር ዳግመኛ ችግር ስለፈጠረችብህ ጠላኋት።"

"አለም ሁኔታውን ልትረዳ አትችልም….ያም የእሷ ጥፋት አይደለም.››

ጁኒየር ስለ ሶለሜ ብዙ ጊዜ ተመሳሳይ ነገር ተናግሮ ነበር። የቱንም ያህል ብታበሳጨውም ስለእሷ ጠንከር ያለ ቃል ተናግሮ አያውቅም።ስርጉት በሹክሹክታ

‹‹ይህችን የሰሎሜን ልጅ ልክ እንደእናቷ በጣም እጠላታለሁ››ስትል አንሾካሾከች፡፡

"አሁን ስለዛ አታስቢ። ይህ ጥሩ ስሜት እንዲሰማኝ አያደርግም" አላት፡

እጁን አነሳና እርጥበታማ ከንፈሯ ላይ አሳርፉ ዳበሳት …ከለበሰችው ጋወን ያፈነገጡ ጡቶቾን ተመለከተ።እጁን ከከንፈሯ አነሳና ጡቷ ላይ አስቀመጠ…

‹‹እንደዚህ ሳደርግ ሁል ጊዜ ደስ ይልሽ ነበር ።››

"አሁንም አድርገው።››

‹‹እውነት? ››

"ጡቷን ወደ አፉ አቀረበችለት…ጎረሰው…. እጁን በጭኖቿ መካከል ሰነቀረው፡፡እርጥበት ያለውን ፀጉር እየዳበሰ ወደውስጥ መጓዙን ቀጠለ … ስሙን እየጠራች አቃሰተች።

‹‹ካልፈለግሽ ይገባኛል››አላት

"አይ" አለች በፍጥነት "እፈልጋለው እባክህ።›››ተማፀነችው፡፡፡

"ስርጉቴ ያንቺ በርህራሄ የበለጸገ ፍቅራዊ እንክብካቤ ዛሬ ማታ ያስፈልገኛል። ጥሩ ስሜት እንዲሰማኝ ሁልጊዜም በአንቺ ልተማመንብሽ እችላለሁ።››ሲል ተናዘዘላት፡፡

ጎንበስ አለችና ከንፈሩን ሳመችው፡፡

"ሁልጊዜ ጥሩ ስሜት እንዴሰማኝ እንደጣርሽ ነው…አይደል እንዴ?" ብሎ ጠየቃት፡፡

"አዎ ።"አለችና አጎንብሳ ተመለከተችው። ልክ እንደ መልአክ ፈገግ አለላት ። እንደዚያ ሲያያት ምንም ልትከለክለው አቅም አይኖራትም በጭራሽ።
///
"ወ/ሪት አለም…ወ.ሪት አለም?አለሽ እንዴ?››

አለም ድክምክም ብላ ተኝታ ነበር። ጥገና የተደረገላት በሯን በተደጋጋሚ ሲንኳኳ ነው ከእንቅልፎ የነቃችው፡፡ ስትነቃ… ደንዛዛ እና ቀዝቃዛ ነበር።ከመተኟቷ በፊት ለረጅም ሰዓት ከማልቀሷ የተነሳ ዓይኖቿ አብጠው ነበር።

"ምን ፈለክ?" ድምጿ ለጩኸት የቀረበ ነበር።

" ክፈቺልኝ እትዬ…መልዕክት አለሽ?።"
እንደምንም ከአልጋው ወረደችና ጋወኗን ለብሳ ወደሳሎን በመሄድ በራፉን ከፈተች፡፡የተከራየችበት አፓርታማ ዘበኛ ነው

"እትዬ ስልክሽ ከአገልግሎት መስጫ ውጭ ነው ይላል?"

"አዎ…ዝግ ነው….ለምን ፈለከኝ?" ግራ በመጋባት ጠየቀችው፡፡

‹‹እኔ አይደለውም…አቶ ግርማ የሚባሉ ሰውዬ መጥተው ነበር›› ደነገጠች‹‹የት ነው..?አሁን አለ?››

‹‹አይ ሄደዋል …መልዕክት ንገርልኝ ብለዋል….ነገ ጥቃት ዝዋይ ስብሰባ ስላለ እንድትገኚ ብለዋል››

‹‹ዝዋይ..?የምን ስብሰባ?››

‹‹አላውቅም እትዬ …ሰውዬው ናቸው ያሉት››

‹‹ማለት ተሳስተህ እንዳይሆን?››

‹‹አይ  ይሄው  ማስታወሻ  ላይ  አስፍሬዋለው…››ብሎ  በተወለጋገደ  ፅሁፍ  የተፃፈውን ማስታወሻ አሳያት፡፡

‹‹እሺ በቃ አመሰግናው››ብላ ሸኘችውና ወደ መኝታ ቤቷ ተመለሰች፡፡ከዛ ስልኳን ፈለግችና አበራችው…ዋናው አቃቢ ህጉ ጋር ደወለች….ስልኩ አይሰራም፡፡፡ስልኳን አስቀመጠችና ጋወኗን አውልቃ ቢጃማ መልበስ ጀመረች፡፡እንደጨረሰች ከእንደገና ስልኳን አነሳችና ደወለች፡፡

"ፖሊስ መምሪያ ነው…ምን እንርዳዎት?."

"እባክህ ኩማንደር ገመዶን ፈልጌ ነበር፡፡"

"እሱ የለም። ሌላ የሚረዳሽ ሰው ጋር እናገናኝሽ?"

"አይ፣ አመሰግናለሁ፣ በቀጥታ ከእሱ ጋር መነጋገር አለብኝ…ምክትል አቃቢ ህግ አለም ጎበና ነኝ።"

‹‹ክብርት አቃቢ ህግ እንዴት ነሽ….አሁን የት ነሽ?፧"

"እቤቴ ነኝ …ለምን ጠየቅከኝ?"

"ኩማንደር ወደአንቺ እየመጣ ነው….እስከአሁን ይደርሳል››

‹‹ምነው በሰላም…..?››መልሱን ሳይመልስላት በራፏ ሲንኳኳ ሰማች‹‹ እሺ …በል ደህና ሁን…ደርሶል መሰለኝ ››አለችና ስልኩን በመዝጋት ወደሳሎን ሄዳ በራፉን ከፈተችለት፡፡

‹‹እሺ ኩማንደር ?››

‹‹ዞር በይልኝ እንጂ ልግባ።››

‹‹መግባትህ አስፈላጊ ነው?››እያለች በራፉን ለቀቀችለት፡፡
82👍15
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ከሰፍል_ሀያ_አምስት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

///
የዝዋዩን ስብሰባ ተሳትፈው በተመለሱ በማግስት ዋና አቃቢ ህጉና አለም በቢሮቸው ፊት ለፊት ተፋጠው ተቀምጠዋል፡፡

እሱ እጁ ላይ አንድ ደብዳቤ በትኩረት እየተመለከተ ትካዜ ውስጥ ገብቷል …

‹‹ክብሩ አቃቢ ህግ…ምነው ችግር አለ እንዴ?››ስትል ጠየቀችው፡፡

‹‹ወደስራ ስትመጪ ከተማው ውስጥ የታዘብሽው ነገር የለም?››

‹‹ምንን በተመለከተ…?››

‹‹የምታሳድጃቸውን ሰዎች በተመለከተ፡፡››
‹‹እ..የጁኒዬር ፍሰሀ ምስል የያዘ የምርጫ ቅስቀሳ ፖስተር ከተማውን ሞልቶታል፡፡ገዢውን ፓርቲ ወክሎ ለተወካዬች ምክር ቤት መወዳደሩ እርግጥ ሆኗል….ያንን ነው የታዘብኩት›››

‹‹አዎ…የዚህ ትርጉም ገብቶሻል ብዬ አስባለው….ጠላቶችሽ ከቀን ወደቀን የማይነኩ አይነት ኃያል እየሆኑ ነው፡፡››

"ምንም ሆነ ምንም …እኔ የጀመርኩትን ወደፊት ከመቀጠል አያስቆመኝም››
‹‹አይ የግድ ለማቆም ትገደጂያለሽ…..››

‹‹ለምን ተብሎ››

እጁ ላይ ያለውን ደብዳቤ ወረወረላት፤ግራ ከመጋባት ውስጥ ሳትወጣ ተቀበችውና አነበበች..ማመን ነው ያቃታት….ከመቀመጫዋ ተነሳች…ተወራጨች…

‹‹ምንድነው ይሄ…››

‹‹ታላቅ እድል ነው….እንደኦሮሚያ ይህንን እድል ካገኙ ሁለት የህግ ባለሞያዎች መከካል አንዷ አንቺ ነሽ…ቀጣዩን ስድስት ወር ቻይና ሄደሽ ይህንን ስልጠና ትወስጂያለሽ…ከዛ ስትመለሺ እርግጠኛ ነኝ….ወይ እዛው ክልል ዋናው ቢሮ ካለበለዚያም ሌላ ዞን በዋና አቃቢ ህግነት ትመደቢያለሽ››

‹‹እኔ መች ፈለኩና…?በምን መስፈርት ነው እኔ የተመረጥኩት….?››

‹‹እሱን እኔ አላውቅም..››

‹‹አወቅክም አላወቅክም ..ይህ እኔን ከእዚህ ገለል ለማድረግ የተሸረበ ሴራ ነው..ለስድስት ወር ከሀገር ወጣሁ ማለት… እስከዛ ጁኒዬር ምርጫውን አሸንፎ ምክርቤት ይገባል…ስመለስም ወደእዚህ ከተማ ስለማይልኩኝ የእናቴ ገዳይ ነፃ እንደሆነ ይቀጥላል ማለት ነው…ይህን መቀበል አልችልም፡፡››

‹‹መቀበልማ የግድ ነው….በዚህ ስራ ላይ ለመቆየት ያለሽ እድል ከ15ቀን አይበልጥም……እሱም ምን አልባት ነው፡፡ደብዳቤውን አንብበሻል አይደል?ይሄ ደብዳቤ ከደረሰት ቀን አንስቶ እጇት ላይ ያለውን ስራና የመንግስት ንብረት ለተተኪው ሰው አስረክበው ለጉዞው ይዘጋጁ ነው የሚለው፡፡››

በንዴት ተንዘረዘረች‹‹አየህ የሰዎቹን ተንኮል….ይህንን ያቀናጁት አቶ ፍሰሀ እና ገመዶ እናም ዳኛው እንደሆኑ እርግጠኛ ነኝ…በዘዴ እኔን ለማስወገድ የሄዱበትን ርቀት የማይታመን ነው››

‹‹አይ የእነሱ እጅ የለበትም ብዬ ልከራከርሽ አልፈልግም….እንደውም ሁኔታውን በደንብ አንድትረጂ ነው የምፈልገው…የሰዎች አቅምና ኃይል ክልል እና ፌዴራል ድረስ ምን ያህል የተዘረጋ እና ስር የሰደደ እንደሆነ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው፡፡አንቺ በማትጎጂበት መንገድ ከጀመርሽው መንገድ ዞር ለማድረግ የቀየሱት ጥበብ የተሞላበት ዘዴ ነው፡፡ያ ማለት እኔ እፈራው እንደነበር ቀጥታ አንቺ ላይ ምንም አይነት አካላዊ ጉዳት ሊያደርሱብሽ ፍላጎቱም ሆነ እቅዱ የላቸውም ማለት ነው….ይሄንን በማወቄ አፎይታ ተሰምቶኛል፡፡››

"አንተም እንድሄድ ነው የምትፈልገው?"

"አዎ፣ ሳስበው ለአንቺም የሚበጅሽ እንደዛ ማድረጉ ነው።" በለሆሳስ መለሰላት፡፡
ዋና አቃቢ ህጉ ለእሷ ከአለቃ ይልቅ እንደ ጓደኛ ነው። ስለዚህ እሷ ደህነንት ያሳስበዋል፡፡ " እንደምንም አንድ ወር በስራዬ ላይ እንድቆይ አድርግ"ተማፀነችው፡፡

" እንደዛማድረግ አልችልም.. አልፈልግም."
‹‹እባክህ››

"አንድ ሳምንት አለሽ…ልክ የዛሬ ሳምንት የቢሮሽን ቁልፍ አስረክበሽ ወደ አዲስ አበባሽ ጉዞ ትጀምሪያለሽ።"

" አታስበው…የመጣሁበትን ከግብ ሳላደርስ ከዚህች ከተማ ንቅንቅ አልልም››

‹‹እንዳዛ ከሆነ ስራሽን ታጪያለሽ››

‹‹ስራውን በስራነቱ እንደማልፈልገው ታውቃለህ….የእናቴን ገዳይ እንዳገኝ ካረዳኝ ስራው ምን ያደርግልኛል?››

‹‹የውጭ እድሉም ይቃጥልብሻል››

‹‹አልፈልገውም …ለሌላ ሰው ስጡት፡፡››

‹‹ይሄንን ስራ ከለቀቅሽ…በራስሽ ብቻሽን ነው የምትቆሚው…የቢሮው እገዛና ጥበቃ አይኖርሽም::እንደአንድ ተራ ግለሰብ እነሱን መጋፈጥ እትችይም….››

‹‹ያንን ስሞክር ነው የማውቀው››

"በእግዚያብሄር ስም …ምን አይነት ግትር ሴት ነሽ?"

‹‹ይህ ግትርነት አይደለም…እዚ ከተማ ስመጣ አሁን እናቴን ገድለዋት ይሆናሉ ብዬ የምጠረጥራቸው ሶስት ሰዎች ነበሩ ..ወደዚህ መጥቼ ምርመራዬን ከጀመርኩ በኃላ ተጠርጣሪዎች ወደአምስት አድገዋል፡፡››

‹‹ጭራሽ ተጠርጣሪዎችሽን ቁጥር እያጠበብሽ መሄድ ሲገባሽ እያንዛዛሽው መጣሽ ማለት ነው…ለመሆኑ እነማን ናቸው የተካተቱበት?››

‹‹የአቶ ፍሰሀ ባለቤት ሳራ እና የጁኒዬር የቀድሞ ባለቤት ስርጉት››

ሲጋራውን ከፓኮው አወጣና ለኮሰ ፣ አንዴ ማገና ጭሱን በአየሩ ላይ በተነው ‹‹እንሱ ደግሞ ለምን ብለው ነው እናትሽን የሚገድሏት?››ሲል ከመገረም ውስጥ ሳይወጣ ጠየቃት፡፡

እንደውም ከወንዶቹ በተሻለ እናቴን ለመግደል በቂ ምክንያት እና ጥላቻ ያላቸው ሴቶቹ ናቸው፡፡ወ.ሮ ሳራ ልጇ ጁኒዬር እናቴን እዳያገባ ስትጥር ነበር ቆየችው....በዚህ ጉዳይ ከአያቴ ጋር ሁሉ እንተጨቃጨቁ በገዛ አንደበቷ ነው የነገረቺኝ፡፡በእሷ እምነት እናቴ በሁሉም መስፈርት ለአንድዬና ብቸኛ ልጇ ሚስት ለመሆን እንደማትመጥን ነው የምታስበው፡፡እና ልጇም ተመሳሳዪን እንዲያስብ ብዙ ጊዜ ሞክራ እንዳልተሳካላት ነግራኛለች..ይታይህ ታዲያ ድንገት እኔን ወልዳ አራስ የሆነችውን እናቴን ሊያገባ እየተዘጋጀ ነው ብለው ሲነግሯት እሷን አስወግዳ ልጇን ነፃ ለማውጣት ብትሞክር ምን ይገርማል…?በሌላ በኩል የዳኛው ልጅ የሆነችው ስርጉት ደግሞ ጁኒዬርን ለአመታት ስታፈቅረው እና የራሷ እንዲሆን ስትመኘው የነበረ ሰው ነው….እሱን የራሷ እንዳታደርገው እንቅፋት የሆነቻት እናቴ ነች..ይባስ ብሎ ከአንድ ዲቃላ ልጇ ጋር ሊያገባት እንደሆነ ስትሰማ ምንድነው የሚሰማት….?ደግሞ እናቴን እንዴት አምርራ ትጠላት እንደነበረና መሞቷን እንደግልግል እንደወሰደችው እዛ ድግስ ላይ
የተገናኘን ቀን ምንም ሳትደብቅ ነግራኛለች፡፡እና በአጠቃላይ ከእናቴ ሞት ይበልጥ ተጠቃሚ የሆነው ማን ነው? ብለን ሰንጠይቅ ለጊዜው ሁለቱ ሴቶች የሚል መልስ ነው ምናገኘው…ሳራም ልጇ የማትፈልጋትን ሴት ከማግባት ተገላገለ..ስርጉትም እናቴ ሞታ ብዙም ሳይቆይ ለአመታት ስታፈቅረው የነበረውን ሰው አሳምና ማግባት ቻለች….ምንም እንኳን ጋብቻው ረጅም እድሜ መቆየት ባይችልም ለጊዜው ግን ተጠቃሚ ነበረች፡፡››
በጥሞና ሲያዳምጣት የቆየው አቃቢ ህግ ጭንቅላቱን እየነቀነቀ‹‹ጥሩ መላ ምት ነው››አላት
፡፡
"በዚህ ጉዳይ እኔን የገረመኝን አንድ ነገር ታውቃለህ? ዳኛው። የእናቴን ግድያ በተመለከተ ተጠርጣሪዎች በጠቅላላ በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ ከእሱ ጋር ትስስር ያላቸው ናቸው..ታዲያ እንዴት አድርጎ ነው ትክክለኛውን ፍርድ ሊፈርድ የሚችለው?።"

በማግስቱ የአለም የመጀመሪ ስራ የዋና አቃቢ ህጉን ቢሮ ማንኳኳት ነበር፡፡ ባልተሟሸ የጥዋት ሻካራ ድምፅ፡፡‹‹ይግቡ››አላት፡፡
በራፉን ገፋ አድርጋ ገባች

‹‹የመጀመሪያ ባለጉዳይ አንቺ ትሆኜያለሽ ብዬ አልጠበቅኩም ነበር››
ለቀልዱ ምንም መልስ ለመስጠት ፍላጎት አልነበራትም…ጠረጴዛውን ተጠጋች እና ከቦርሰዋ ውስጥ አንድ ወረቀት አውጥታ ፊቱ አስቀመጠችለት፡፡ጠቅላላ አቃቢ ህጉ በሁኔታዋ ግራ ተጋብቶ‹‹ምንድነው?›› ሲል ጠየቃት፡፡

‹‹ስራ መልቀቂያ ነው››

‹‹ማለት ?አልገባኝም››
44👍6👎1👏1
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ


///
እሱ በራፉን ለመክፈት ሲሄድ አለም ቶሎ ብላ ቦርሳዋ ውስጥ ገባች እና በጣም የሚያምር ውድና ጌጠኛ ብእር አወጣችና ወደቤቱ በራፉ ፊት ለፊት በመወርወር ወደፊት ራመድ ብላ እስኪመለሱ መጠበቅ ጀመረች፡፡

‹‹እ..ሰላም ነው..?ስልክህ አይነሳም፡፡››አቶ ፍሰሀ ነው ተናጋሪው፡፡

‹‹ውስጥ ቻርጅ ላይ እርጌው አላየሁትም…ግባ››ኩማንደሩ መለሰለት፡፡ ወደውስጥ ሲገባ አለምን ስላያት ነገሩ ገባው፡፡

‹‹እንዴት ነህ አቶ ፍሰሀ?››

‹‹ሰላም ነኝ…አንቺስ?››

‹‹አለሁ..››አላችና ‹‹በሉ እንግዲህ መሄዴ ነው››ስትል አከለችበት፡፡

‹‹ምነው ..እኔ ስመጣ ነው እንዴ ምትሄጂው?››

‹‹አይ መጀመሪያውኑም ለመሄድ ስል ነው የመጣሀው…ጉዳዬን ጨርሼለው..ተራውን ለአንተ ልልቀቅ፡፡››አለችና ሁለቱንም ተሰናብታ ወጣች፡፡

ገመዶ እና አቶ ፍሰሀን አስከትሎ ወደውስጥ ለመግባት ሲራመድ በራፉ ጋር ሲደርሱ አቶ ፍሰሀ ጎንበስ አለና አይኑ የገባውን ብዕር አነሳ፡፡

‹‹ይሄን የመሰለ ብዕር ትጥላልህ እንዴ?››ብሎ ወደ ኩማንደሩ ዘረጋለት፡፡ኩማንደሩ ተቀብሎ አገላብጦ ተመለከተውና‹‹ወይ የእኔ አይደለም…የአለም መሰለኝ›››አለና ስልኩን አውጥቶ ደወለላት፡፡

‹‹ሄሎ››

‹‹ ምነው ከአሁኑ ናፈቅኩህ እንዴ?››
‹‹ባክሽ ሌላ ቦታ ጥዬዋለው ብለሽ እንዳትፈልጊ ነው…አንድ ብዕር ጥለሽ ሄደሻል..ካልራቅሽ ተመለሺና ውሰጂው››

‹‹ወይ  እንዴት  ጣልኩት…?ለማንኛውም  በጣም  ከምወደው  ሰው  የተሰጠኝ  ስጦታ ነው…ከኪስህ እንዳይወጣ …ስንናኝ ትሰጠኛለህ››አለቸው፡፡

‹‹እሺ ቻው››አለና ስልኩን በመዝጋት ብእሩን ደረት ኪሱ ውስጥ ሻጠውና ከአቶ ፍሰሀ ጋር ተያይዘው ወደውስጥ ገቡ….

‹‹ቢራ ልክፈትልህ››

‹‹በጣም ደስ ይለኛል››

ለሁለቱም ቢራ ከፈተና ፊት ለፊት ተቀመጠ፡፡

‹‹መጥፎ ሰዓት ነው እንዴ የመጣሁት?››አቶ ፍሰሐ ጠየቀ፡፡

‹‹አይ እንደውም በተቃራኒው ጥሩ ሰዓት ላይ ነው የመጣሀው..በጣም አደጋ ላይ ነን››

‹‹ማለት››

‹‹ይህቺ ልጅ ከጠበቅኳት በላይ አደገኛ ነች…ሳታጠፋን አርፋ አትቀመጥም….››

‹‹ማለት….አንተ እንዲህ ካልክ ነገሮች ከባድ ናቸው ማለት ነው››

‹‹አዎ…ስለእያንንድ  የሶሌ  ኢንተርፕራይዝ  የአክሲዬን  ድርሻ…ማን  ስንት  ፐርሰንት እንዳለው…አክሲዬኑ መቼ እንዳገኘነው….ዝርዝር መረጀ አላት፡፡››
አቶ ፍሰሀ ልብ ምቱ በደቂቃ ውስጥ ሲጨምር ታወቀው….

‹‹ምን እያልከኝ ነው?››

‹‹አዎ….የእናቴን ሞት ተከትሎ የአንዳችሁ አክሲዬን ተቀንሶ ለሌሎቻችሁ የተጨመረው ለምንድነው ብላ ጠየቀችኝ…?፡፡››

‹‹ይሄ እኮ ወደእውነት እየቀረበች መሆኑን የሚያመለክት ነው፡፡››

‹‹አዎ…አንድ ውሳኔ መወሰን አለብን፡፡››
አቶ ፍሰሀ ወዲያው ስልኩን አወጣ…መጀመሪያ ዳኛ ዋልልኝ ጋር ደወል…አሁኑኑ ወደቤት እንዲመጣ ነገረውና ስልኩን ዘግቶ መልሶ ልጁ ጁኒዬር ጋር ደወለ..ቤት እንደሆነ ነገረው…ሳይወጣ እንዲጠብቀው ነግሮ ዘጋውና‹‹በል ተነስ እንሂድ….አሁኑኑ ተነጋግረን አንድ ነገር ማድረግ አለብን፡፡››
///
ከምሽቱ አራት ሰዓት አራቱ ሰዎች ምድር ቤት በሚገኘው የአቶ ፍሰሀ ቢሮ ውስጥ ተቀምጠው ፊት ለፊት ተፋጠዋል…በጠረጴዛው መሀከል ሙሉ የውስኪ ጠርሙስ ሲኖር በመሀከላቸው ግማሽ ድረስ የተሞላ ብርጭቆ አለ….

‹‹እኔ  ከመጀመሪያውም  ነግሬችሁ  ነበር..ይህቺን  ሴት  አንድ  ነገር  አድርጓት  ስላችሁ ነበር››ዳኛው በንዴት ደነፉ፡፡

‹‹አሁን ያለፈውን ገር እያነሳን ልንወቃቀስ አይደለም የተገናኘው…አሁን እንዴት አድርገን እናሳቁማት የሚለው ነው ወሳኙ ነገር፡፡››

‹‹ለምን ሁችንም ባለንበት አግኝተናት ይሄንን ጉዳይ እንድታቆም ለመጨረሻ ጊዜ አናሳጠነቅቃትም››አለ ጁኒዬር፡፡

‹‹ትቀልዳለህ እንዴ….መቼስ ልጅቷን ግትርነት ከአንተ በላይ የሚያውቅ ያለ አይመስለኝም፡፡ እኔ በበክሌ እዚህ እግሯ ከረገጠበት ቀን አንስቶ በሰላምም በማስፈራራትም ይህንን ጉዳይ እንዳታቆም ያልጠየቅኳት ቀን የለም…አንድም ቀን ሽብርክ ስትል አልሰማዋትም…ዛሬም የነገረችኝ ጉዳዩን ከማቆም መሞትን እንደምትመርጥ ነው፡፡››ሲል አስተያየቱን ያቀረበው ኩማንደሩ ነበር፡፡

‹‹እሱማ ትክክል ነህ …እኔም ያልሞከርኩበት ቀን የለም…›አለ ጁኒዬር፡፡

‹‹አዎ…ይሄ ጉዳይ አይሰራም፡፡››
ዳኛው ትእግስት አልባ በሆነ ንግግራቸው‹‹በቃ በንግግር ማስቆሙ ካልሰራ …አስወግዷታ

…መቼስ ይሄንን ስታደርጉ የመጀመሪያችሁ አይደለም››አለ ፡፡

በገመዶና በጂኒዬር ላይ የተከሰተው ድንጋጤ የተለየ ነበር…..እርስ በእርስ ተያዩ….ከዛ ሁለቱም በእኩል ጊዜ ወደአቶ ፍሰሀ ዞሩ….አቶ ፍሰሀ አይናቸው ተጉረጥርጧል…ለመናገር እየፈለጉ እየተናነቃቸው ነው፡፡ከአንደበታቸው ቃል ማውጣት የከበዳቸው መሆኑን ያስታውቃል…ከዛ እንደምንም አሉና መናገር ጀመሩ፡፡

‹‹ይሄንን ለሁላችሁም ነው የምናገረው…ለሁላችሁም….እዚህች ልጅ ላይ የመግደል ሀሳብ አይደለም አንዲት ፀጉሯን ለመንቀል ብታስቡ ቀጥታ ፀባችሁ ከእኔ ጋር ነው፡፡ማንም እጣቱን በእሷ ላይ ሊያነሳ አይችልም፡፡››

ዳኛው አይናቸውን አጉረጠረጡ‹‹ለምን ተብሎ..ለአንድ ዲቃላ ልጅ ሲባል የእኛ ህይወት መመሰቃቀል አለበት፡፡.እናንተ ማድረግ ካልፈለጋችሁ እኔ አደርገዋለው፡፡››

አቶ ፍሰሀ ልክ እንደጎረምሳ ከተቀመጡበት ተስፈንጥረው ተነሳና ከወገቡ ያለውን ሽጉጥ መዞ ሽማግሌው ዳኛ መላጣ ጭንቅላት ላይ ደቀነው፡፡

ገመዶና ጁኒዬር በርግገው ከተቀመጡበት ተነሱ‹‹እንዴ አባዬ ….!ምን እያደረክ ነው?››

‹‹አንተ ፈርሳም ሽማግሌ….ከዛሬ ጀምሮ እንደውም ለልጅቷ ጠባቂ ቀጥረህ እንቅፋት እንኳን እንዳይነካት ብታስጠብቃት ይሻልሀል….በማንም ሆነ በማን አንድ ነገር ገጠማት ሲባል ብሰማ ይሄንን ምላጭ በአንተ ጭንቅላት ላይ ለመሳብ ለሰከንድ እንኳን አላቅማማም፡፡››

‹‹ጋሼ በቃ…..ወደመቀመጫህ ተመለስ..ተረጋጋ…››አለ ገመዶ፡፡

አቶ ፍሰሀ የደቀነውን ሽጉጥ መልሶ ወደ ወገብ ሻጠው እና መደመቀመጫው ተመለሰ

…..ሁሉም በፀጥታ ማሰላሰል ውስጥ ገባ…ገመዶ ከተቀመጠበት ተነሳና ወደመስኮቱ ተጠግቶ ሲጋራውን ለኮሰና እያጬሰ ማሰብ ጀመረ፡፡ሲጋራውን እንደጨረሰ ወደመቀመጫው ተመለሰና ከውስኪው አንዴ ጠቀም አድርጎ ከተጎነጨ በኃላ ‹‹እኔ አንድ ሀሳብ አለኝ››ሲል የሁሉንም ቀልብ ሳበ፡፡

‹‹ምንድነው እንስማው››ሁሉም ተነቃቁና ኩማንደሩ የሚለውን ለመስማት ዝግጁ ሆነ፡፡

‹‹የሚቀጥሉት ስድስት ወራት ወሳኝ ጊዜዎች ናቸው..ማለቴ ከጂኒዬር የምርጫ ጉዳይ ጋር ተያይዞ ይሄ የክስ ጉዳይ ወደፊት ከገፋና እንዲህ አይነት ወሬዎች ህዝቡና ሚዲያው ጆሮ መግባት ከጀመሩ ነገሮች ድብልቅልቃቸው ነው ሚወጣው፡፡እንደእኔ ለተወሰነ ጊዜ ወደሆነ ቦት ዞር አድርገን ብናስቀምጣት፡፡››

‹‹ዞር አድርገን ስትል….?ግልፅ አድርገው?፡፡››

‹‹በቃ ከሰው እያታ ውጭ የሆነ ቤት ወሰድን እዛ ሁሉ ነገር እንዲሞላላት እድርገን ግን ደግሞ ከማንም የማትገናኝበትን ሁኔታ ብናመቻች ጥሩ ይመስለኛል፡፡››

‹‹ጥሩ…እኔም እስከዛ ጡረታ ወጣና ከዚህ ከተማ ዞር እላለሁ››በማለት ዳኛው ቅድሚያ ተስማማ፡፡

አቶ ፍሰሀ ‹‹ጥሩ ሀሳብ ይመስላል….እንደውም ይርጋ ጨፌ የቡና እርሻችን ያለበት ቦታ ብንወስዳት ማንም ሊያገኛት አይችልም……እዛ ሁሉን ነገር እናሟላላታለን…እኛም በየተራ እየሄድን እንጠይቃታለን..መጥፎ ሰዎች እንዳልሆን እንድታምን እናደርጋለን፡፡
51👍8😱2
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ



///
‹‹በተሰቀለው…አሁን ምንድነው የምናደርገው?››

‹‹አላውቅም…ለአባትህ  ደውልለትና  በአስቸኳይ  ይምጣ…እዛ  ይርጋጨፌ  ምንም አያደርግም››

‹‹ደውዬለታለው… እየመጣነው››ሲል መለሰ ጁኑየር

‹‹ዳኛውም እየደወለልኝ ነበር››

‹‹እሱን ተወው ባክህ..ከአሁኑ በልብ ድካም እስከወዲያኛው ማንቀላፋቱ አይቀርም..ለማንኛውም እዚህ ምንም አንሰራም ..ወደቤት እንሄድ›› ተባባሉና ሁለቱም ወደ መኪናቸው በመግባት ተከታትለው ወደእነ ጁኒዬር ቤት መጓዝ ጀመሩ፡፡

በማግስቱ ጥዋት  አንድ ሰዓት በሶሌ ኢንተርፕራይዝ ህንፃ የአቶ ፍሰሀ ቢሮ ውስጥ ቁጭ ብለው እየተወያዩ ነው፡፡

‹‹ያሰማራናቸውን ሰዎች ምንም ፍንጭ አላገኙም››አቶ ፍሰሀ ናቸው ጠያቂው፡፡

‹‹እዚህ  ከተማ  ውስጥ  ያለች  አይመስለኝም….እያንዳንዱን  ሆቴል  እና  ፔንሲዬን አሳስሼለው….የለችም፡፡››ገመዶ መለሰ፡፡

‹‹ወደ አዲስአበባ ተመልሳ ሊሆን ይችላል?››

‹‹ወደዛም ሰው ልኬለው…..እንግዲህ የሚሆነውን እናያለን፡፡››

‹‹ጥሩ …ዩቲዬብ ባለቤትስ ማግኘት ችለናል…..?››አቶ ፍሰሀ ናቸው ሌላ ጥያቄ የጠየቁት፡፡

‹‹አዎ አናግሬው ነበር…የፈለገውን ያህል ብር እንደምንከፍለውና ቀጣዩን ስራ እንዳይለቅ ጠይቄው ነበር…››

‹‹እና?››

‹‹እናማ…ቀጣዩን አልሰጠችኝም…እራሷ ቀርፃ ነው የምትልክልኝ ….››የሚል መልስ ነው የሰጠኝ፡፡

እንደዛ ከሆነ እኮ አሪፍ ነው…ለልጁ ደህና ብር ስጡትና ቀጣዩን ታሪክ ልታስረክበው ስትቀጥረው ይደውልልን እና እናገኛታለን ማለት ነው››ዳኛው በአዲስ ተስፋ ተሞልተው ተናገሩት፡፡

ኩማንደር ፈገግ አለና‹‹ክቡር ዳኛ….ይሄንን ማሰብ የሚያቅተኝ ይመስልሀል?››

‹‹አይ በፍጹም እንደዛ አላልኩም….ውይይት ላይ ስለሆን የተሰማኝን በግልፅ ነው የተናገርኩት››

‹‹ጥሩ…ለልጁ ይሄንን ሀሳብ አቅርቤለት ነበር….ወዲያው ይሄንን መልእክት አሳየኝ፡፡››

‹‹ምንድነው?››

በዩቲዬብ የተለቀቀውን የወንጀል ታሪካችሁን መንደርደሪያ ስትሰሙ መጀመሪያ ምታደርጉት ወደእዚህ ዩቲዩበሩ ልጅ ጋር ሄዳችሁ በገንዘብም በማስፈራራትም ቀጣዩን እንዳይለቀውና በእሱ አማካይነት እኔን ለመያዝ እንደምትሞክሩ አውቃለው….ለዛም ነው ቀድሜ ይሄንን መልዕክት ልጁ ጋር የተውኩት፡፡አንደኛ ከአሁን በኃላ ቀጥታ ልጁን አላገኘውም .. የተቀረፀውን በሌላ መንገድ ነው ምልክለት፡፡ሁለተኛ ልጅን የምታቆሙት ከሆነ እየተቆራረጠ በአምስት ክፍል ይለቀቅ የነበረውን ለሌላ ዩቲዬበር አንዴ ሰጥቼው በአንዴ እንዲለቀቅና ነገሮች ፍርጥርጥ እንዲሉ አደርጋለው ….ያ ማለት ደግሞ ለማሰቢያ እና የተሻለውን መንገድ መምረጫ ጊዜ ያሳጣችኋላ..እንግዲህ ምርጫው የእናንተ ነው፡፡››ይላል፡፡

‹‹ምን አይነት ጉድ ልጅ ነች?››አቶ ፍሰሀ ነው የተናገረው፡፡

‹‹ብዬችሁ  ነበር..አልሰማ  ብላችሁ  ሁላችንንም  መቀመቅ  ውስጥ  ከተታችሁኝ….በጊዜ ትወገድ ብያችሁ ነበር፡፡››ዳኛው ተወራጩ፡፡

‹‹አንተ  ቀበተት  ሽማግሌ…በዚህ  እድሜህ  አንድ  ፍሬ  ልጅ  ትገደል  ስትል  ትንሽ አይቀፍህም?››አቶ ፍሰሀ በንዴት መለሰ፡፡

‹‹አሁንማ እንድትገደል ብንስማማስ የት እናገኛታለን?በዚህ ሁሉ እድሜዬ አንተንና ኩማንደሩን በእንደዚህ አይነት ጫወታ የበለጠች ብቸኛዋ ሴት እሷ ብቻ ነች፡፡በጣም ብጠላትም በጣም የምትደነቅ ጀግና የሆነች ልጅ ነች››ሲል ዳኛው ተናገረ፡፡

በዚህ ሰዓት ድንገት የኩማንደሩ ስልክ ጠራ ..ከኪሱ አወጣና አየው…..የማያውቀው ቁጥር ነው፡፡አነሳው‹‹ውዴ በጣም ናፍቀኸኛል››
በስልኩ በእግር በፈረስ የሚፈልጋትን የአለም ድምፅ እየሰማ መሆኑን ማመን አልቻለም

‹‹አንቺ…የትነሽ ያለሽው?››

‹‹ቅርብህ ነኝ….ጁኒዬርም አብሮህ ነው አይደል?››

‹‹ምን እያወራሽ ነው?››

‹‹ሁለችሁም ናፍቃችሁኛል?››

‹‹ቀለድሽብን ማለት ነው?››

‹‹አይደለም…መቼስ ሁለታችሁንም እንደምወዳችሁ አትጠራጠሩም አይደል..?ልክ እንደእናቴ… እኔም አፈቅራኋላው፡፡››
ሁሉም አፍጥጠው ይመለከቱት ነበር‹‹እና ምንድነው የምትፈልጊው?፡፡››

‹‹ምፈልገውንማ መጀመሪያ ከተገናኘንበት ቀን አንስቶ መች ደብቄችሁ አውቃለው››

‹‹እና አሁን ምን ይሁን ነው የምትይው?››

‹‹ምንም ….እኔ አሁን እየፈለኩት ስላላው ፍትህ ወይም በቀል ላወራችሁ አይደለም የደወልኩት ..ድምፃችሁን ልሰማ ነው..እባክህ ስልኩን ለጁኒዬር ትሰጠዋለህ፣በጣም ነፍቆኛል…››

‹‹ገደል ግቢ››አለና ስልኩን ጠረቀመው፡፡
‹‹ምንድነው ..ስልኩን ለምን ዘጋህባት?››ጁኒዬር በንዴት ጠየቀው፡፡

‹‹እሷ  ኮመዲ  እየሰራችብን  ነው..እንደናፈቅካት  ተናግራ  ካንተ  እንዳገናኛት  ነው የምትፈልገው››

‹‹ታዲያ ለምን ሳታገኛኘን?››

‹‹ምነው ?አንተም ናፍቃሀለች እንዴ?››

‹‹ተረጋጉ…ሁላችም ወደመቀመጫችሁ ተመለሱ››አቶ ፍሰሀ በመሀከል ጣልቃ ገብተው ሁሉም ወደቀልባቸው እንዲመለሱ አደረጉ፡፡

‹‹ልጆች አይታያችሁም እንዴ..?ይሄ እኮ የበቀሏአንዱ አካል ነው፡፡››

‹‹ማለት..?››ገመዶም ሆነ ጁኒዬር በአንድነት አቶ ፍሰሀ ላይ አፈጠጡ፡፡

‹‹በሁለታችሁ መካከል ቅሬታ በመፍጠር ኃይላችንን ለመበታተን እየጣረች ነው….›› ጁኒዬር ባለማመን ‹‹እንደዛ አስባ ይመስልሀል?፡፡››ሲል በጥርጣሬ ጠየቀ፡፡
‹‹ታዲያ ያንተን ስልክ እያወቀች ለምን ብላ ነው ለገመዶ ደውላ ከጁኒዬር ጋር አገናኘኝ ናፍቆኝ ነው የምትለው?››
‹‹አባዬ እውነትህን ነው….››
///
በተሰጣቸው ሶስት ቀን ውስጥ እሷን አድነው መያዝ አልቻሉም…እሷንም ቀጣዩን ክፍል በተመሳሳይ በዩቲዩብ ገፅ እንዳትለቅ ማድረግ አልቻሉም…ይሄ ሁለተኛው ግን ከመጀመሪያው በበለጠ ጫና ውስጥ ከተታቸው፡፡የከተማው የገዢው ፓርቲ ፅህፈት ቤትም ጁኒዬርን አስጠርቶ በሶሻል ሚዲያው ስለሚዘዋወረው ነገር ማብራሪያ እንዲያቀርብና በአፋጣኝ እየተሰነዘረበት ካለው ክስ ራሱ ነፃ እንዲያደርግ ማስጠንቀቂያ ተሰጠው፡፡

‹‹አባዬ..ይህ ምርጫ ለምን አይቀርብኝም?››

‹‹ለምን እንደዛ አልክ?››

‹‹የፓርቲው ሰዎች እኮ ቁም ስቅሌን እያሳዩኝ ነው፡፡በአንድ ሳምንት ውስጥ በእኔና በቤተሰቦቼ ላይ እየተነዛ ያለውን ሀሚት ማጥራት ካልቻልኩ በእኔ ጉዳይ ላይ አቋም እንደሚወስዱ ነግረውኛል››

‹‹ምን አይነት አቋም››

‹‹ይመስለኛል..እጩ መቀየር የሚችሉት እስከዚህ ወር መጨረሻ ድረስ ነው፡፡እዚህ ከተማ ላይ በተቃዋሚዎች መሸነፍ አይፈልጉም ..ስለዚህ በሌላ እጩ ሊተኩኝ እያሰቡ ይመስለኛል፡፡››

‹‹ወይ ነዶ..ያን ሁሉ ብር ከስክሰን እንደዚህ ጉድ እንሁን…የክልል ወዳጆቻችንም ለእኔ ደጋግመው እየደወሉልኝ ነው፡፡ልጅቷን መያዝ ካልቻላችሁ እኛ እናግዛችሁ እያሉ ነው፡፡››

‹‹እንዴት አድርገው ነው የሚያግዙን››ጁኒዬር ጠየቀ፡፡

‹‹በአካባቢው ያሉትን የከተማ የፀጥታ አካላት በማነጋገር ፍላጋው ላይ እንዲሰማሩ በማድረግ ነዋ››

‹‹ታዲያ አሪፍ እድል አይደል?››

‹‹አሪፍ እድል ነው..ግን ደግሞ እገዛቸውን አልተቀበልኩም››

‹‹ለምን?››

‹‹ምክንያቱም እሷን በማደኑ ላይ የመንግስት የፀጥታ አካላት ከገቡበት ድንገት ባልታሰበ ሁኔታ ልትጎዳ ትችላለች…ያንን ሪስክ መውሰድ አልችልም››

‹‹አባዬ..እዚህች ልጅ ላይ የምታሳየው የርህራሄ ስሜት ከእለት ወደእለት እያስደመመኝ ነው፡፡የተለየ ምክንያት አለህ እንዴ?››
51👍7😁1
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ_ሰባት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

///
እሷ እንደጠረጠረችው…ልክ ግቢዋን ከፍታ እንደገባች በተጠንቀቅ ሲጠብቃት የነበረው ኩማንደር ያስቀመጠው ሰው ወዲያው ነበር ያያት…ስልኩን አንስቶ ኩማንደሩ ጋር ለመደወል ያባከነው ደቂቃ አልነበረም….

ኩማንደሩ ስልኩ ሲደወልለት ዳኛው ቤት ቁጭ ብሎ ማድረግ ስለሚገባቸው አንዳንድ ነገሮች እየተወያዩ ነበር….

‹‹በቃ ታክሲ ያዝና ተከታተላት..ከእይታህ እንዳትሰወር…ያለህበት ድረስ እመጣለው››የሚል ትዕዛዝ ነገረውና ስልኩን ዘግቶ ለዳኛው አለም እንደተገኘች ሲነግራቸው ዳግመኛ እንደተወለዱ አይነት እፎይታ ነው የተሰማቸው…

‹‹.እንዲከተሏት አድርጌያለው…አሁን መሄድ አለብኝ….. ››አለና ከተቀመጠበት ተነሳ፡፡

‹‹ለምን ሪስክ ትወስዳለህ..?ወዲያው እንዲይዞት ማድረግ ነበረብህ››ሲሉ አካሄዱ ላይ ያላቸውን ተቃውሟ አሰሙ፡፡

‹‹ይዘናትስ….?ምንም የሰራችው ወንጀል የለም እኮ…ዝም ብለን አንጠልጥለን ልናስራት አንችልም››

‹‹እስከዛሬ የምታስሯቸውን ሰዎች ሁሉ ወንጀል ሰርተው ነው?››ዳኛው ስትሰሩ የኖራችሁትን ማላውቅ መሰላችሁ የሚል ቃና ባለው ንግግር ታቃወሙ፡፡
‹‹ልጅቷ እኮ የዞኑ ምክትል አቃቢ ህግ የነበረች የህግ ባለሞያ ነች….ሌላ ሰው ላይ የምናደርገውን ሁሉ እሷ ላይ በቀላሉ ማድረግ አንችልም…በዛ ላይ መከተላችን…የትነው የምትሄደው…?አጋዥ አላት ወይስ ብቻዋን ነች?››የሚለውን ለማጥናት ይረዳናል….ምን
አልባት ከሌሎች ጠላቶቻችን ጋር ህብረት ፈጥራ የምትንቀሳቀስ ከሆነም እሷን ብቻ ነጥለን መያዝ ከምንም አያተርፈንም…..››

‹‹ጥሩ አስበሀል ..እንግዲያው እኔም አብሬህ መሆን ፈልጋለው….››

‹‹አረ በዚህ ምሽት ይቅርብህ…ባይሆን ሁኔታውን በየጊዜው እየደወልኩ አሳውቅሀለው…››

‹‹አረ እኔም ከእናንት ጋር እሄዳለው››

ፎቅ ላይ ሆና ንግግሯቸውን ስታዳምጥ የነበረችው ስርጉት የአለምን መገኘት ዜና ስትሰማ በደስታ ጃኬቷን ደርባ አምርራ የምትጠላትን ሴት መያዝ በቀጥታ በአይኗ ለመከታተል ዝግጁ ሆና ወደእነሱ ስትመጣ ተመለከተ…ብዙ ቢከራከራቸውም ሁለቱም ለመቅረት ፍላጎት ስላላሳዩ ምን አገባኝ በሚል መንፈስ አብረውት እንዲሄዱ ፈቀደላቸው፡፡በኩማንደሩ ሹፌርነት አባትና ልጅ ከኋላ ሆነው አለምን ለመከታል ወጡ ..አለምን የሚከታተላትን ታክሲ አዲሱ መነኸሪያ ካለፈ በኃላ ነበር የደረሱበት…ከዛ የአለምን መኪና ካሳያቸው በኃላ እሱ እንዲመለስ ነገረውና አነሱ የአለምን መኪና መከታተሉን ቀጠሉ..እሷ ቀጥታ ለዛ ምሽት ፈጣን በሚባል አነዳድ የቦሌን የአስፓልት መንገድ ይዛ እየነዳችው ነው፡፡

‹‹ልጅቷ ወደየት እየሄደች ነው?፡፡››ስርጉት ግራ በመጋባት ውስጥ ሆና ጠየቀች፡፡
‹‹ይመስለኛል…ግብረ አበሮቾ ጋር የምትገናኘው ከከተማው ውጭ ነው፡፡››አባቷ የመሰላቸውን ተናገሩ፡፡

‹‹አይመስለኝም››ኩማንደር ነው ተናጋሪው፡፡

‹‹ማለት…ምን አሰብክ?››

‹‹ትዝ ይላችኃላ እናቷ ኮፈሌ ዘመዶች ነበሯት…የአባቷም ዘመዶች እዛው ናቸው..እኛ በማናውቅበት መንገድ ከዘመዶቾ ጋር መገናኘት ጀምራ ነበር ማለት ነው..እና አሁን እነሱን ለማግኘት እየሄደች ያለ ይመስለኛል..››ሲል መላምቱን አስቀመጠ፡፡

‹‹እና ኮፈሌ ድረስ ልንከተላት ነው ማለት ነው?፡፡››

‹‹እንግዲህ ቀድሞውንም አትከተሉኝ ያልኩት ለዚህ ነው…እኔ እንኳን እዚህች ኮፈሌ ድረስ ይቅርና ሱማሌም ድረስ ከነዳችው ከመከተል ወደኃላ አልልም››ሲል ፍርጥም ያለ ውሳኔውን ነገራቸው፡፡
//

አለም መኪናዋን በፍጥነት እያበረረች እንኳን ደጋግማ አቶ ፍሰሀ ስልክ ላይ ከመደወል አልታቀበችም…ግን አሁንም ስልኩ ይጠራል እንጂ አይነሳም…‹‹ይሄ ማለት ሰውዬው ከባድ አደጋ ደርሶበታል ማለት ነው..?››ስትል አሰበችና ዝግንን አላት….በእሱ ላይ በሚደርስ አደጋ እንደዚህ አይነት ሽብር ውስጥ እገባለሁ ብላ አስባ አታውቅም ነበር….እርግጥ እንዲህ በድሎኛል ብላ አንድም ቀን አካላዊ ጉዳቱን ወይም ሞቱን ተመኝታለት አታውቅም
…ቢሆንም ደህንነቱ በዚህ መጠን እንዲህ ያሳስበኛል ብላም ግምቱ አልነበራትም፡፡እና የራሷ ሁኔታ በጣም ነው ያስገረማት፡፡

‹‹ፈጣሪ ሆይ እባክህ..ህይወቱን ጠብቃት››ከልቧ ፀለየች፡፡ለቤተሰቦቹ መሳወቅ እንዳለባት ትዝ ያላት ወደባሌ የሚያመራውን የአስፓልት መንገድ ለቃ ወደቀኝ በመታጠፋ ወደ  ሶሌ ደን የሚወስደውን ጥርጊያ መንገድ ከያዘች በኃላ ነበር፡፡የጂኒዬርን ቁጥር ፈለገችና ደወችለት፡፡

‹‹ሄሎ ጁኒዬር…. አለም ነኝ››

‹‹አለም ..ደህና ነሽ…?የት ነሽ….?እንዴት ነሽ?››የእሷን ድምፅ ሲሰማ የሚይዘው የሚጨብጠው ጠፋበት፡፡ስልኩ ሲደወልለት ቤት ከእናቱ ጋር ሳሎን ቁጭ ብሎ እየተጫወተ ነበር፡፡እሷ ለእሱ መርበትበት ቁብም ሳትሰጥ ንግግሯን ቀጠለች‹‹ጂኒዬር ልብ ብለህ አድምጠኝ…ከ30 ደቂቃ በፊት ከአባትህ ጋር በስልክ እያወራሁ ነበር…መኪና እየነዳ ሳያስበው ከከተማ እንደወጣ እና ወደሶሌ ደን እየተቃረበ መሆኑንና ከአሁን በኃላ ስለመሸ ወደከተማ እንደማይመለስና ማረፊያ ጎጆ ስላለው እዛው እንደሚያድር እየነገረኝ ነበር፡፡›

‹‹አዎ እዛ አልፎ አልፎ የምናርፍበት ጎጆ አለን….››

‹‹እና..ምን መሰለህ?››

‹‹እያስደነገጥሺኝ ነው..ስለምን ነበር እያወራችሁ የነበረው?››

‹‹እሱ ምን ይሰራልሀል…ለማንኛውም ንግግራችንን ሳንጨርስ አውሬ ገባብኝ የሚል ድምፅ እና ከፈተኛ ፍንዳታ የመሰለ ነገር ሰማው..እና ስልኩ ተቋረጠ.. መልሼ ደጋግሜ ብደውል ስልኩ ይጠራል… አይነሳም..፡፡››

‹‹ወይኔ ፈጣሪ…ምን እያልሺኝ ነው?››አጠገቡ የነበረችው እናቱ ሳራ የልጇ ጭንቀት በእሷም ላይ ተጋብቶባት…ስሩ ቆማ ትንቆራጠጥ ጀመር፡፡.

‹‹ለምንኛውም አሁን ቦታው ላይ እየደረስኩ ነው.. እንዳገኘሁትና ሁኔታውን እንዳየው እደውልልሀለው…ምን አልባት አንብላንስ ያስፈልግ ይሆናል››ስልኩ ተቋረጠ
‹‹ምንድ ነው ልጄ..?ፍሰሀ ምን ሆነ?››ሳራ ጠየቀች፡፡

‹‹አባዬ አደጋ ደርሶበታል መሰለኝ..ሶሌ ያለው ደን ውስጥ ነው…መሄዴ ነው››

‹‹እኔም አብሬህ እሔዳለው››

‹‹እማዬ አንቺ እዚሁ ሆነሽ ጠብቂ….››

‹‹እሔደለው..አልኩህ እሔዳው›› አጉረጠረጠችበት፡፡ምንም አላለም…በክርክር ጊዜ ማባከን ስላልፈለገ ቀጥታ ወደሳሎኑ መውጫ መራመድ ጀመረ… እናቱም ከኃላው ተከተለችው… መኪና ውስጥ ገቡ ..ወደባሌ ጎባ የሚወስደውን የአስፓልት መንገድ ይዘው ወደ ሶሌ ጉዞ ጀመሩ
///
አቶ ፍሰሀ አውሬውን አድናለው ብሎ መሪውን ሲጠመዝ ሙሉ በሙሉ ከመንገዱ ወጥቶ በግራ በኩል ባለው ገደል መሰል ጉድጓድ ውስጥ ነበር ጎማው ተንሸራቷ የገባው…ከዛ ፍሬኑን ለመያዝ ቢሞክርም የመኪናዋን ፍጥነትም ሆነ ባላንስ መቆጣጠር አቅቶት አንድ ዙር ተገለበጠና አንድ የብሳና ዛፍ ተደግፎ ቆመ….ለአምስት ደቂቃ ራሱን አያውቅም ነበር፡፡ከገባበት መደንዘዝ ሲወጣ ወንበሩ ስር ተወሽቆ ነው ራሱን ያገኘው…እንደምንም ታግሎ ቀበቶውን ከአንገቱ አወጣና በራፍን በእግሮቹ ገፍቶ ለመክፈት ሞከር..ቀላል ስራ እልሆነለትም፡፡እግሮቹ  ምን  እንደነካቸው  ባያውቅም  የሚያሰበውን  ያህል  ጥንካሬ
37👍4
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ_ስምንት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

///
‹‹ጋሽ ፍሰሀ..አንተ ነህ…?››

‹‹አዎ አለም…እዚህ ምን ትሰሪያለሽ?››አውሬው ካስደነገጠው በላይ የእሷ በዚህ ሰዓት እዚህ አካባቢ መገኘት አስደነገጠው፡፡

‹‹እንዴ ስልክ እያወራን ነበር እኮ የተቆረጠው….መኪናህ እንደተገለበጠች እርግጠኛ ስለነበርኩ ወዲያውኑ ወደእዚህ የመጣሁት…መኪናህን ቀድሜ ባገኛትም ውስጡ የለህም..ግን የሚንጠባጠበውን ደም እየተከተልኩ ደረስኩብህ››

‹‹ስሩ ደርሳ ደገፈችው››

‹‹አብሮሽ ማን አለ?››

‹‹አረ ማንም የለ….መንገድ ላይ ሆኜ ለጁኒዬር ደውዬለታለው..ይሄኔ እየመጡ ይሆናል፡››

‹‹ይገርማል..የሆነ ነገር ቢያጋጥምሽስ?››

‹‹ሀሳቤ ሁሉ ያንተን ደህንነት ማረጋገጥ ላይ ስለነበር እሱን አላሳብኩትም ነበር…እውነቱን ንገሪኝ ካልከኝ ግን አሁን በፍራቻ እየተንቀጠቀጥኩ ነው፡፡››

‹‹በጣም ነው ያስገረምሺኝ..አይዞሽ አሁን አምስት ደቂቃ ነው ደርሰናል….እንደውም እዛ መብራት ጭልጭል የሚልበት ቦታ ይታይሻል …?እዛ ነው ጎጆው…በአቅራቢያው የእኔ ሰራተኞች ቤትም አለ…››

‹‹ በአንድ እጇ ደግፋው በሌላ እጇ ደግሞ የስልኳን ባትሪ ከፊት ለፊት እያበራች ወደፊት በዝግታ መራመዳቸውን ቀጠሉ፡፡
አቶ ፍሰሀ ከአውሬው ጋር የነበረው መፋጠጥ አሁንም ከምናብ ሊደበዝዝ አልቻለም… ልቡ ለምን እንዲህ ከመጠን በላይ መታ? ጉዳዩ ምን ነበር? የዱር አውሬው በጣም አስፈርቶት ነው? አይደለም፡፡ እሱ ስለእነሱ አላሰበም። በህይወቱ የበለጠ አስፈሪ ነገሮችን አሳልፎ ያውቃል። ወዲያው ከኃላቸው እየተንሾካሾኩ የሚመጣ የእግር ኮቴ ሰሙ…መንገዱን ለቀቁና ጢሻውን ተከልለው ቆሙ..ሲጠጎቸው ማንነታቸውን በድምፅ ለዩ…‹‹ገመዶ››
ባትሪውን ሲያበራባት ፈጽሞ እዚህ አገኘዋለሁ ብሎ ያላሰበውን አቶ ፍሰሀን በአለም ተደግፋፎ ልክ እንደተወዳጅ ልጁ ስሩ ተሸጉጣ ሲያይ አይኑን ማመን አልቻለም፡፡

ሁሉም ተንደርድረው ከበቧቸው‹‹ጋሼ ምን እየተካሄደ ነው?››

‹‹አይዞችሁ አትደንግጡ… ተርፌለው››

‹‹ተርፌለው ማለት?››ኩማንደሩ በመገረም ጠየቀ፡፡

‹‹የመኪና አደጋ እንደደረሰብኝ ሰምታችሁ አይደለም እንዴ የመጣችሁት?››

‹‹አረ በፈጣሪ..ተርፍክ ታዲያ…?እኛ አልሰማንም..እሷን ከከተማ ስትወጣ አይተን ተከትለናት ነው የመጣናው…ከጠላቶቻችን ጋር ልትገናኝ መስሎን ነበር››

‹‹አይ እሷ እኔን ለማትረፍ ነው የመጣችው››

‹‹እንዴት ከእኛ ቀድማ ልትሰማ ቻለች?..ነው ወይስ በአደጋው ላይ የእሷ እጅ አለበት?››

‹‹እሱን ጎጆው ጋር  ደርሰን ትንሽ ካረፈ በኃላ ብትጠይቀው አይሻልም?››አለችው አለም በንዴት፡፡

‹‹ለምን ወደጎጆ እንሄዳለን? መኪናችንን እኮ በቅርብ ርቀት ላይ ነው ያቆምናት..እዚሁ ጠብቁኝና ይዣት ልምጣ..ቀጥታ ወደከተማ ሄደህ ህክምና ማግኘት አለብህ››

‹‹አይ ደህና ነኝ..አሁን ማረፍ ነው የምፈለገው..ወደጎጆ ውሰዱኝ››

‹‹ተው  እንጂ  ፍሰሀ  ..ሀኪም  ሊያይህ  ይገባል››ዳኛው  ጣልቃ  ገብተው  ለኩማንደሩ ድጋፋቸውን ሰጡ፡፡

‹‹የበለጠ  እያደከማችሁኝ  መሆኑን  ልብ  አላላችሁም  እንዴ..?ወደጎጆ  መሄድ  ነው የምፈልገው›› በማለት የማይቀየር አቋማቸውን አሰሙ፡፡

‹‹ይቅርታ ጋሼ..አንተ ካልክ እሺ ወደጎጆ እንወስድሀለን….እነ ጁኒዬርም አሁን ደውለውልኝ ነበር …መገንጠያው ጋር ደርሰዋል….ከደቂቃዎች በኃላ ይደርሳሉ..››አለና ሄዶ በሌላ ጎኑ አቶ ፍሰሀን ደገፈ….ከ5 ደቂቃ በኃላ ጎጆዋ ደረሱ፡፡ፋኖስ አበሩ፣ መኝታው ተስተካክሎ እንዲተኛ ተደረገና በቅርብ ርቀት ያሉ ሌላ የሳር ቤት ውስጥ ወደሚኖሩት የእነሱ ሰራተኞች ተቀስቅሰው መጡ..እሳት እንዲቃጣጠል ተደረገ…ጁኒዬርና ሳራ የመጀመሪያ ለእረዳታ መስጫ የሚያለግሉ ቁሳቁሶች ይዘው እያለከለኩ ደረሱ…ለተወሰነ ጊዜ ለቅሶና ግርግር በጠባቧ ጎጆ ነገሰ..ከዛ ቀስ በቀስ ወደመረጋጋት ቢመጣም በሰው ብዛት በታፈነችው ጎጆ ውጥረትና ጭንቀት ነግሶ ነበር፡፡

‹‹ቆይ እኔ ያልገባኝ…ምንድነው የሚያስጠብቀን..?ለምንድነው ወደከተማ ይዘነው ሔደን ሀኪማ የማያየው?››ሳራ ነች ግራ በመጋባት ተመሳሳይ አይነት ጥያቄ ለሶስተኛ ጊዜ ያነሳችው፡፡

‹‹ጋሼ አልፈልግም ስላለ እኮ ነው…ጋሼ አሁን ትንሽ አርፈሀል፣ብንሄድ ምን ይመስልሀል?››ኩማንደር ነው ተናጋሪው፡፡

‹‹አይ ዛሬ ማንም ከዚህ አይሄድም…አሁን ሰዎቹን ሸኞቸውና የምንነጋገረው ነገር አለ››ሲል ሁሉም በቀጣይ ምን ሊፈጠር ነው በሚል እርስ በርስ ተያዩ፡፡

ጁኒዬር ከጎረቤት ጎጆ የመጡትን ባልና ሚስቶች ከነልጆቻቸው አመስግኖ ወደቤታቸው እንዲሄዱ ካደረገ በኃላ የጎጆዋ ቤት ተዘጋ፡፡አሁን ስድስት ሰዎች ፊት ለፊት ተፋጠጡ …ሁለቱ ሴቶች እና አዛውንቱ ዳኛ አቶ ፍሰሀ ጎን የተቀመጠችውን አለምን በከፍተኛ ጥላቻን መጠየፍ ነበር የሚመለከቷት፡፡

አቶ ፍሰሀ ከትራሱ ቀና አደረገና አስተካክሎ በመደገፍ መናገር ጀመረ‹‹ዛሬ እየሆነ ያለው ሁሉ ነገር ተአምር ነው…እኔ እቅዴ እንደማንኛውም ቀን ስራ ውዬ ወደቤቴ መግባት ነበር….ነገር ግን የሰሞኑን ውጣ ውረድ እያሰላሰልኩ ሳላስበው ከከተማ ወጣሁና እራሴን እዚህ ሶሌ ደን አካባቢ አገኘሁት..እንዴት እዚህ ልደርስ ቻልኩ? ብዬ እየተገረምኩ ሳለ ያልጠበቅኳት አለም ደወለችልኝ..ከእሷ ጋር እያወራው ሳለ ድንገት ሳላስበው አውሬ ገባብኝና እሱን አድናለው ስል መኪናዬ መንገድ ስታ ተገለበጥኩ…እንደአደጋው መሞት ነበረብኝ..ግን ከተወሰነ ጭረት በስተቀር ምንም አልሆንኩም…እግዜር አሳይቶ ከሞት ደጃፍ መለሰኝ..ከመኪናው ወጥቼ በጫካው እያሳበርኩ ወደእዚህ እየመጣው ሳለ ከጅብ ጋር ፊት ለፊት ተፋጠጥኩ…እሱንም ወደሰማይ ተኩሼ አስበረገግኩትና ሁለተኛውን ፈተና አለፍኩ..ከዛ ወዲያው አለምን ከፊት ለፊቴ አገኘኃት..ወዲያው እነ ገመዶና መጡ…ጎጆው እንደደረስን ደግሞ ልጄና ባለቤቴ መጡ …እኔ ለማናችሁም አደጋ ደረሰብኝ ብዬ አልደወልኩም..በአደጋው ጊዜ ስልኬ ወደየት እንደጠፋም አላውቅም..ግን ሁላችሁም እዚህ ተገኝታችኃላ..ሁላችንን እዚህ ያለነው ለምክንያት ነው፡፡ከአለም ጋር የጀመርነው ድብብቆሽ እዚህ ጋ ማብቃት መቻል አለበት፡፡

‹‹አዎ ማብቃት አለበት …ይህቼ ሴት ከዚህ በፊት ንብረቴ እንዲቃጠል አደረገች… ዛሬ ባለቤቴን ገድላብኝ ነበር….››ሳራ ተንዘረዘረች…ዳኛውና ስርጉት አይናቸውን በማጉረጥረጥ እና በመገላመጥ ለሳራ ያላቸውን እገዛ አሳዩ ፡፡

‹‹ሳራ ተይ ..ዛሬ የምንበሳጭበትና ራሳችንን ሀጥያት ለመሸፈን ሌላ ስው በሀሰት የምንወቅስበት ቀን አይደለም..እኔ አንድ ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከሁለት ሞት ነው የዳንኩት…ይሄ ያለምክንያት አይደለም..ይህቺን ልጅ ሁላችንም በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ በድለናታል…ሁላችንም ለእሷ መናዘዝ መቻል አለብን..እውነቱን ልንነግራት ይገባል..ከዛ አመዛዝና ከፈለገች ትበቀለን… ከፈለገች ደግሞ ወደፍትህ አደባባይ ወስዳ ታሰቅለን፡፡

የአቶ ፍሰሀን ንግግር የሰሙት ዳኛው ጫንቃቸውን አላባቸው፡፡ይሄ ሰውዬ በተገበጠበት ወቅት ጭንቅላቱን ተመቶ ማሰቢያው ላልቶ ይሆን እንዴ?››ሲል አሰበና አይኑን ገመዶና ጁኒዬር ላይ አንከራተተ…የሆነ ነገር ብለው የጀመረውን ቅዠት የመሰል ድርጊት እንዲያስቆሙት ነው ፍላጎቱ.
45👍4
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ


///
‹‹ልጄ አንተ እንዲሁ ሰበብ ሆናብህ እንጂ ሰሎሜን የገደልካት አንተ አይደለህም››

‹‹እማዬ አሁን በቃሽ …ባበቃለት ጉዳይ ላይ ምንም ለውጥ ላታመጪ አትድከሚ››

‹‹አይደለም..ሰሎሜን የገደልናለት እኔና ስርጉት ተባብረን ነው.››ስርጉት በተቀመጠችበት ሆና አቃሰተች….ዳኛው መተንፈስ ከበዳቸው፡፡ሳራ ግን ለማናቸውም ግድ አልነበራትም..የእሷ ዋናው ትኩረት ልጇን ከእስር ማዳን ብቻ ነው..እና ንግግሯን ቀጠለች፡፡

‹‹.የዛን ቀን አንተ እኛን ወደቤታችን ከመሸኘትህ በፊት መጠጧ ውስጥ መድሀኒት ጨምረንባት ነበር..ከ30 ደቂቃ በኃላ እንደማሳበድ አድርጓት በአንድ ሰአት ውስጥ ሙሉ በሙሉ የሚገድላት መድሀኒት ነበር፡፡እሷ  የተቀየረችብህና ከመስታወት ላይ ግንባሮሯን የከሰከሰችው በመድሀኒቱ ተጽዕኖ ነው…መስታወቱ ሆዷ ውስጥ ቢሻጥ እንኳን  አልሞተችም ነበር…አባትህ መጥቶ ሀኪም ቤት ሊወስዳት መኪናው ውስጥ አስገብቶ መንገድ ከጀመረች በኃላ ነው እስትንፋሷ የተቋረጠው…ያም የሆነው በተወጋችው ውግ ወይም በፈሰሳት ደም ሳይሆን በጠጣችው መርዝ ምክንያት ነው፡፡

‹‹እማዬ ይሄን እንዴት እሰከዛሬ ሳላውቅ…?አባዬ አንተ እንዲህ መሆኑን ታውቃለህ?››ሲል አባቱ ላይ አፈጠጠበት፡፡
አቀርቅሮ የነበረው አቶ ፍሰሀ በከፊል ቀና አለና ‹‹ከአንተ እና ከአለም በስተቀር ይሄንን ጉዳይ እዚህ ቤት ያለው ሁሉም ሰው ያውቃል፡፡››ሲል እውነቱን ፍርጥም ብሎ መለሰለት፡፡

‹‹ምን አረገቻችሁ ቆይ …?ምናችሁ ላይ ደረሰች?››አለም በእንባ ታጥባ እየነፈረቀች ሳራ ላይ አፈጠጠችባት፡፡

ሳራ እሷን ችላ ብላ ወደልጇ እየተመለከተች‹‹አንተን እንዳታገባህ እና ከስርህ እንድትርቅ ለአመታት ለመናት.. አስጠነቀቅናት፤ እሷ ግን ሌላ ሰው አግብታ ወልዳ እንኳን ልትተውህ አልቻለችም…የልጄ ህይወት በእንደዛ አይነት ሁኔታ ሲበላሽ ቆሜ ማየት አልቻልኩም፡፡እኔ ስርጉትን እንድታገባ ነበር ምፈልገው፣ከልቧ በጣም የሚታፈቅርህ ሰሎሜ ሳትሆን ስርጉት እንደሆነች በደምብ አውቃለው..››
ወዲያው ሳራ ንግግሯን እንዳገባደደች ኩማንደር ተቀበላት‹‹ያው እንግዲህ መጠኑ ይለያይ እንጂ በእናትሽ ግድያ ሁላችንን የየድርሻችንን ተወጥተናል…እኔ በእለቱ እስከእራት ሰዓት ድረስ ብቻ ነበር አብሬቸው የቆየሁት…ከለሊቱ ዘጠንኝ ሰዓት ጋሽ ፍሰሀ ደወለልኝ.. ስመጣ
…እናትሽ ጋሼ መኪናው ውስጥ እጥፍጥፍ ብላና በደም ተበክላ ነበር…ጋሼ የሆነውን በአጭሩ አስረዳኝና የሚሆነውን እንዳደርግ ሀላፊነቱን ለእኔ ሰጠኝ ….ነገሩ ወደህግ ከሄደ ጁኒዬር፤ሳራም ሆነች ስርጉት ዘብጥያ መውረዳቸው አይቀርም …ምን ማድረግ እንዳለብኝ ሳስብ ያ ሊቁ የተባለው እብድ በዛ ውድቅት ለሊት እየለፈለፍ በእርባታ ድርጅቱ ፊት ለፊት ባለው መንገድ ሲያልፍ አየሁት..ወዲያው ሀሳብ ብልጭ አለልኝ..ሮጥኩና ይዤው ወደውስጥ ገባው..ከማታ እራት የተረፈ ምግብና መጠጥ ስለነበረ እሱን ሰጠሁትና ስለማደርገው ነገር መዘጋጀት ጀመርኩ..የምጠቀምበት እቃ ስፈልግ የእንስሳት ዶክተሩ የህክምና ቁሳቁስ የሚይዝበትን ሳጥን በረንዳ ላይ ተቀምጦ ነበር፤አይኔ ውስጥ ገባ፣ ቶሎ አልኩና ከፈትኩት ፡፡ የቀዶ ህክምን ሚገለገሉበትን ቢላዋ አገኘሁና .. በወቅቱ በጣም ተደናግጬ ስለነበረ የማደርገውን ሁሉ የማደርገው በደመነፍስ ነበር….እና ያው ልጅ እንደገደላት እንዲመስል አደረኩና ጥዋት ለፖሊስ ተደወለ.. በኃላ ነገሮች በጥሩ ሁኔታ እየተጓዙ ሳለ አያትሽ ልጄን የገደላት እብዱ ሳይሆን እነሱ ናቸው… የሚል ወሬ መንዛት እና
አቤቱታ ማሰማት ጀመሩ…ከዛ ጉዳዩ በሚመለከታቸው ሰዎች ዘንድ አንዳንድ ጥርጣሬዎች ብልጭ ማለት ጀመሩ..ሬሳው በደንብ ይመርመር የሚል ግሩፕ ተነሳ…ከዛ ከጋሼ ጋር ተማከርንና የሆስፒታሉ የሬሳ ማስቀመጫ ክፍል እሳት እንዲነሳና እሬሳውም እንዲቃጠል አደረግን..በስተመጨረሻም አያትሽን ይሄንን ሀገር ለቀው ካልሄዱ አንቺን ነጥቀን እስከወዲያኛው እንዳያገኙሽ እንደምናደርግ አስፈራርተናቸው ዝም እንዲሉና ከተማውንም ለቀው እንዲሄዱ አደረግን…እናም በተጨማሪ ስለእናትሽ አሟሟት ሊነግርሽ ነበረውን ሙስጠፋንም የገደልኩት እኔ ነኝ!!የዛን ቀን እኛ ሳናየው እዛ ተደብቆ እያንዳንዱን ነገር ሲያይ ነበር….ይሄን ሁሉ ነገር ግን ፍርድ ቤት ቀርቦ ያምንልኛል ብለሽ እንዳትጠብቂ…››ሲል ንግግሩን አገባደደ፡፡

አለም ደም በለበሱ አስፈሪ አይኖቾን ኩማንደሩ ላይ አፍጥጣ‹‹ቆይ ቆይ እስኪ…ልጁ የገደላት ለማስመሰል ከሞተች በኃላ በዛ የቀዶ ጥገና ቢላዋ ደጋግመህ ወጋሀት አይደል?
…?ከዛ ደሟ ሲንፎለፎል በእጅህ እየዘቅክ እዛ ሚስኪን ልጅ ልብስ ላይ አዳረስከው …እንዳዛ አይደል ያደረከው?በቁሟ እያለች በፍቅር ልብህን ስለሰበራች ልትበቀላት ታስብ ነበር፣ግን ለማድረግ ወኔ አልነበረህም..በዛን ወቅት ግን አጋጣሚው ተመቻቸልህ..ነፍሷ ውስጧ ባይኖርም ደጋግመህ ሰጋዋን በመበሳሳት ንዴትህን ተወጣህባት….ከዛ ሬሳዋ ለምርመራ ሆስፒታል ገባ ..አንዳንድ ጥርጣሬ የሚያስነሱ ነገሮች መፈጠር ሲጀምሩ እራሳችሁን ከማንኛውም አደጋ ጥርጣሬ ለመጠበቅ አስፈላጊ ስለነበረ ጋሼ ፍሰሀ ደግሞ የሆስፒታሉ የሆነ ክፍል በእሳት እንዲያያዝ እና ሬሳዋም እንዲቃጠል እና አመድ እንዲሆነ አደረገ..ከዛ አቶ ዳኛ በዚህ ወንጀል ውስጥ ልጁ ስላለችበት ይህንን ወንጀል እንዳይጋለጥ ባለህ ስልጣን ሁሉ ተጠቅመህ ፋይሉ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እንዲዘጋ አደረክ…፡፡በትክክል ተረድቼችኋለው አይደል..?እንዲህ ነው ያደረጋችሁት?
‹‹ሁሉም በመሸማቀቅ አንገታቸውን አቀርቅረው ነበር የሚሰሟት‹‹እስከአሁን እንደሰማሁት ከሆነ እኮ ጁኒዬር ብቻ አይደለም ራሱን ለህግ አሳልፎ መስጠት ያለበት …ሁላችሁም ናችሁ..እና እኔ ዳኛ ብሆን በጣም ትንሹን ፍርድ የምፈርደው በእሱ ላይ ነው….እሱ ሳያስበው…በድንገተኛ አደጋ የፈጠረው ወንጀል ነው…ሌለቻችሁ ግን አስባችሁ እና አቅድ አውጥታችሁ ደግማችሁ ደጋግማችሁ እናቴን በነፍስም በስጋም አጥፍታችኃታል….እና ነገ ወደከተማ ስንመለስ ምን እንደምታደርጉ ለማየት በጣም ጎጉቼለው….፡፡››

‹‹መቼስ ሁላችንም ሳታጠፊን እንቅልፍ አይወስድሽም አይደል…?ደስ ይበልሽ ይሄው ተሳካልሽ››አሉ ዳኛው ቅስማቸው ስብርብር ብሎ፡፡

‹‹ደስ ይበልሽ !!….ጭራሽ ደስ ይበልሽ…?.ፍርድን በአደባባይ ሲሸጦት ያዛን ጊዜ ማሰብ ነበረቦት››

‹‹አይ መሬት ያለ ሰው….በእኔ ላይ የደረሰውን ወላጅ ስትሆኚ ነው የምታውቂው….ልጄን ከእስርና ከእንግልት ለማዳን ስል ነው እዚህ ውጥንቅጥ ውስጥ የገባሁት››

‹‹አይ ልጆትን ከእስር ለማትረፍ ብቻ አይደለም….ከሶሌ ኢንተርፕራይዝም የ10 ፐርሰንት የአክሲዬን ድርሻ በልጆት ስም ማግኘት ችለዋል፡፡››

‹‹ይህ ፍፁም እውነት አይደለም…ያንን አክሲዬን የገዛሁት በራሴ ብር ነው….ከወላጆቼ በውርስ ያገኘሁትን ንብረት በጠቅላላ ሸጬ ነው የገዛሁት…ያንንም ፈልጌው ሳይሆን ኩማንደሩ እና ፍሰሀ አስገድደውኝ ነው፡፡በልጄ አስፈራርተውኝ ነው››

ዳኛው የሚናገሩትን ባለማመን ቀና አለችና ኩማንደሩ ላይ አፈጠጠችበት፡፡
‹‹አዎ..እውነቱን ነው፡፡ይሄንን ወንጀል ዛላለም በመሀከላችን እንደተቀበረ እንዲቆይ እርስ በርስ የበለጠ መተሳሰር አለብን ብለን አሰብን…ከዛ ከጁኒዬር እና ከሳራ ድርሻ ላይ ተቀንሶ በስርጉት ስም አክሲዬን እንዲገዙ አደረግን….ባይሆን እኔ ቀጥታ ጠይቄ ባይሆንም ከእናትሽ ሞት በኃላ የአክሲዬን ድርሻዬ ወደ30 ፐርሰንት እንዲያድግ ሆኗል….››
46👍5😱2