ዐውደ ምሕረት
3.68K subscribers
930 photos
24 videos
271 files
193 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
#ውድ የትምህረተ ሃይማኖት እና የዓውደ ምህረት ታዳሚዎቻችን እንደምን ከረማችሁልን🙏

እንደሚታወቀው የዓውደ ምህረት እህት ቻናል የነበረው ትምህርተ ሃይማኖት የተባለው ቻናል ከሰኞ #06 -09-2010 ዓ.ም ጀምሮ #የኔታ የተባለ የአብነት ትምህርት ቤት ሆኗል:: በፊት ያስተላልፈው የተበረው መርሐ ግብራት #ማለትም

ሰኞ #ትምህርተ ሃይማኖት
ማክሰኞ #ክ .ሥነምግባር
ረቡዕ #የመ ጥናት
ሀሙስ #ነገረ ማርያም
አርብ #ሥነ ፍጥረት
እሁድ #ባሕረ ሐሳብ የተሰኙት ሲሆኑ ሁሉም መርሐ ግብራት ይዘታቸውን ሳይለቁ በፊት የዓውደ ምህረት የኮርስ መርሐ ግብራት በሚተላለፉበት ውል ጊዜ በሳምንቱ መጨረሻ በዕለተ አርብ በዓውደ ምህረት ከሚተላለፉት ኮርሶች ጋር በመሆን የሚቀጥሉ ይሆናሉ::በዚህም መሠረት #ከፊታችን አርብ ጀምሮ ዘወትር አርብ #አርብ ከምሽቱ 2:30 ጀምረን ኮረርሶቹን ካቆሙበት ክፍል የምንጀምራቸው ይሆናሉ:: በአንድ የመሆናቸው ታላቁ ሚስጢር በትምህርት ይዘታቸውና ዓላማቸው ተመሳሳይነት ስላላቸው ነው::

👉በዚሁ አገጋጣሚ ለቀደምት #የዓውደ ምህረትና #የትምህርተ ሃይማኖት ቻናል ታደዳሚወዎቻችን ሁሉንም ኮርሶች ከአንድ ቦታ የማግኘት ዕድል ስለገጠማችሁ #እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እንወዳለን🙏

#ዘወትር አርብ ከ#2:30 ጀምሮ

#1🎤 ነገረ ድኅነት
#2📢ነገረ ማርያም
#3🎤ነገረ ቅዱሳን
#4📢ሥነ ፍጥረት
#5🎤ትምህርተ ሃይማኖት
#6📢ሥነምግባር (አንድ ክፍል ብቻ ይቀራል)
#7🎤መ ጥናት (ሁለት ክፍል ብቻ ይቀራል )
#8📢ባሕረ ሐሳብ

❤️ ዘወትር ቅዳሜ

🧙‍♂እንደተለመደው #ምን እንጠይቅልዎ??? የተሰኘው መርሐ ግብራችን ከምሽቱ 2:00 ጀምሮ የሚቀጥል ይሆናል🙏

❤️ዘወትር እሁድ

በቀድሞ ፕሮግራም አርብ ከተላለፉት ኮርሶች እርሶን የምንጠይቅበትና ልዮ ልዮ የመጻሕፍት ሽልማቶችን የምንሸልምበት ነበር ነገር ግን አዳዲሶች ኮርሶች ስለተጨመሩ ያን ለማድረግ ይከብዳል ሆኖም ስለዚህ ለ ተከታታይ 3ሳምንታት ምንም ዓይነት ከኮርሱ የተወጣጡ ጥያቄዎችን አንጠይቅም ::ይህን አጋጣሚ በመጠቀምም አዳዲሶቹን ኮርሶ በሚገባ አድምጠው ከሦስት ሳምንት በኃላ በምናደርገው ወርሃዊ የጥያቄና መልስ ውድድር ላይ ተሳትፈው አሸንፈው" #ገድለ ተክለ #ሃይማኖት "እንዲሸለሙ ከወዲሁ ይዘጋጁ እንላለን እናመሰግናለን🙏

👉እስከዛሁ ግን በእሁድ መርሐ ግብረራችን ተጠይቀው ትከክክለኛ ምላሻቻው ያልተነገሩ ጠጥያቄዎች ስላሉ የእነርሱን ትክክለኛ መለሶች ይዘነን የምንቀርብበት ይሆናል::

ሽልማቱ በPDF format ሳይሆን በአካል ወይም በወኪሎቻችሁ አማካኝነት እንደሚሰጥ ለማሳወቅ እንወዳለን::

"መልካም የኮርስ ሳምንት"
ማንኛውንም ሀሳብ ጥቆማና አስተያየታችሁን በ @YeawedMeherte @YeawedMehert በኩል ያድርሱን


🍒ሌላውና #አስደሳቹ ነገር ከእንግዲ ወዲ በዓውደ ምህረው ምንም ዓይነት የሊንክ ጋጋታ እንደማይኖርና ከዕርዳታ ጥሪ ወይም ከቤተ ክረርስቲያናት ምረቃ ጋር የተገናኘ ማስታወቂያ ካልሆነ በቀር በሳምንት ከአንድ በላይ promotion የማንሰራ መሆኑን #በደስታ እንገልጻለን::

📢ዓውደ #ምህረት🎤
የእናንተ
🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤
📢 @AwediMeherit📢
📢 @AwediMeherit📢
📢📢📢📢📢📢📢📢
#የነገረ_ድኅነት ጥያቄ #መልሶች

#እውነት ወይም ሐሰት በሉ

#ኛ ሐሰት
#ምክንያቱም :-ሰው ለመዳን ከማመን ያለፈ የተግባር ሰው (ምግባራትን እና ምሥጢራትን የሚፈጽም) መሆን አለበት:: ምግባራት የሚባሉትም በዋናነት #ጾም #ጸሎት #ስግደት #ምጽዋት ሲሆኑ ምሥጢራቱም #ምሥጢረ_ሜሮን #ቅዱስ_ጥምቀት እና #ቅዱስ_ቁርባን ይጠቀሳሉ #ሃይማኖት ያለ #ምግባራት ጥቅም አልባ የሞተ ነው::
"፤ ከነፍስ የተለየ ሥጋ የሞተ እንደ ሆነ እንዲሁ ደግሞ #ከሥራ (ከምግባራት )የተለየ እምነት የሞተ ነው።" (የያዕቆብ መልእክት 2: 26)


#ኛ ሐሰት

#ምክንያቱም :-በተለየ አካሉ #ከእመቤታችን ከቅድስት #ድንግል_ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሶ ነፍስን ተስቶ በፍጽም ተዋህዶ #ተወልዶ ያዳነን ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ነውና:: #በምስጢረ ሥላሴ ትምህርታችን #አብ አባት #ወልድ ልጅ #መንፈስ ቅዱስ ሰራፂ ብለን ተምረናል እንዲህም እናምናለን:: ቅዱሳት መጻሕፍትም በተዋህዶ ተወልዶ ያዳነን ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን በስፋት ይነግሩናል:: ለምሳሌ "እግዚአብሔር አንድያ #ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶልና" ዮሐ3÷16

#ኛ ሐሰት

#ምክንያቱም :- ምንም እንኳን ድኅነት በዕለተ አርብ በቀራኒዮ አደባባይ አንድ ጊዜ ተፈጽሞ ለሰው ልጆች የተሰጠ ቢሆንም ከዚህ ከተሰጠው ድኅነት ግን ለመካፈል ሰው የራሱን ጥረት ማድረግ ይገባዋል። ድኅነት በእግዚአብሔር ዘንድ የተፈጸመ ስለሆነ ብቻ ሰው ሁሉ ያመነውም ያላመነውም በግዴታ ይድናል ማለት አይደለም:: ለመዳን የወደደ ብቻ ከተፈፀመለት የድኅነት ሥራ በምግባራት ተሳትፎ ድኅነትን ያገኛል:: ስለዚህ በድኅነት ውስጥ ሰውም ሊፈጽመው የሚገባ ሂደት ነው::
"፤ ስለዚህ፥ ወዳጆቼ ሆይ፥ ሁልጊዜ #እንደ_ታዘዛችሁ፥ በእናንተ ዘንድ በመኖሬ ብቻ ሳይሆን ይልቁን አሁን ስርቅ፥ በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ #የራሳችሁን_መዳን_ፈጽሙ፤"
(ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 2: 12)

ልናስተውለው የሚገባን #የታዘዛችሁትን_በመፈጸም የምትለዋ እና #የራሳችሁን_መዳን_ፈጽሙ የምትለዋን ነው

በመሆኑም የእራሳችንን መዳን መፈጸም የምንችለው እና ከተሰራልን የድኅነት ሥራ የምንካፈለው የታዘዝነውን በመፈፀም ነው:: #የታዘዝነውም 10ቱ ትዕዛዛት 6ቱ ቃላተ ወንጌል ናቸው እነዚህን ለመፈፀም ደግሞ ጊዜ ዘመን ያስፈልገናል:: ይህ ደግሞ ድኅነት በሂደት የሚፈፀም እንጂ በአንድ ቀን በአንድ ቦታ በሰዓት ጌታን በመቀበል ብቻ አለመሆኑን ያስገነዝበናል:: በጥቅሉ ለመዳን ሰው የራሱ ድርሻን መወጣት ይገባዋል።

#ኛ እውነት

#ኛ ሐሰት
ምክንያቱም:-ያልተመለሰለት ጸጋ የለምና::
ፀጋ:-
ልጅነትን:- ከእንግዲ ወዲ ባሮች አትባሉም
ወራሽነትን:-
ገዢነትን(ሥልጣንን):- ግዛ ንዳ የተባለሁ ዓለምና በዓለም ያሉትን ነገሮች ሁሉ ዛሬም ሰው ከትዕዛዙ ካልራቀ ሕጉን ከጠበቀ ከተፈጥሮ ሁሉ በላይ መግዛት መንዳት የሚችልና ሥልጣኑ ያለው መሆኑን በቅዱሳን ሕይወት መመልከት ይቻላል::


#በአጭሩ መልሱ

#ኛ #ስለ_ፍጽም_ፍቅሩ
#ለካሳ ለቤዛ
#የዲያብሎስ ጥበብ #በጥበቡ #ለመሻር
#ለምሳሌነት_ለአራያነት
#ድኅነት ሥርዓት ስላለው…

#ኛ #ማመን
#ሥራ (ምግባራት)
#ምሥጢራትን መፈጸም ማር 16:16 ዮሐ 6:54


#ኛ "፤ እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ #በእርሱም ቍስል #እኛ ተፈወስን።"

(ትንቢተ ኢሳይያስ 53: 5)
"፤ #እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ #ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም #የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ።"
(ትንቢተ ኢሳይያስ 53: 6)

ነብዩ ስለ እኔ ብቻ አላለም #እኛ ብሎ አብዝቶ ተናገረ እንጂ:: እኛ ብሎ አብዝቶ መናገሩ የዓለምን ኃጢያት የተሸከመ የዓለም መድኀን መሆኑን ሲገልጥ ነው::

"እነሆ #የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ #የእግዚአብሔር_በግ።"
(የዮሐንስ ወንጌል 1: 29)


#ኛ #መንግስቱን_ሲወርስ_ስሙን_ሲቀድስ


#ኛ ማዳን የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ነው ማለት እንጂ ቅዱሳን አያድኑም ወይም መድኀኒት አይባሉም ለማለት አይደለም:: በቅዱስ መጽሐፍ ሰዎች ሆነው አዳኝ ተብለው የተጠሩ አሉ #ለምሳሌ "፤ የእስራኤልም ልጆች ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፤ #እግዚአብሔርም_የሚያድናቸውን_አዳኝ የካሌብን የታናሽ ወንድሙን የቄኔዝን ልጅ #ጎቶንያልን_አስነሣላቸው።"
(መጽሐፈ መሳፍንት 3: 9) ይህ የሚያሳየው እግዚአብሔር ቅዱሳን ሰዎችን አዳኝ መድኀኒት አድርጎ እንደሚያስነሳ ነው:: መዳን በሌላ በማንም የለም ማለቱ የቅዱሳን አዳኝነት (መድኀኒትነት) ጠፍቶት አይደለም:: ቅዱሳን የጸጋ አዳኝ ናቸው:: ጸጋ ደግሞ ከእግዚአብሔር የተሰጠ ፣የተቸረ ፣የተለገሰ ስጦታ ማለት ነው:: ስለዚህ ቅዱሳን መድኀኒት ቢባሉ በስጦታ ያገኙት ነው። "#እድንበት ዘንድ ከሰማይ በታች የተሰጠን #ሌላ ስም የለም" ማለቱ ደግሞ ቅዱሳን ሲያድኑም በእራሳቸው ኃይል ሳይሆን ማዳንን በሰጣቸው በፈጣሪያቸው ስም ነው ማለቱ ነው:: ቅዱሳን መላእክት አዳኝ (መድኅኒት )ናቸው። ስማቸው ስመ እግዚአብሔር ተሸክሞልና:: ስለሆነም ቅዱስ ሚካኤል አዳነ ማለት እግዚአብሔር አደነ ማለት ነው ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ ጴጥሮስ (ቅዱሳን ሰዎችም) ቢያድኑ የፈጣሪን ስሙን ጠርተው ነው "፤ ጴጥሮስ ግን፦ ብርና ወርቅ የለኝም፤ ይህን ያለኝን ግን እሰጥሃለሁ፤ #በናዝሬቱ_በኢየሱስ_ክርስቶስ_ስም ተነሣና ተመላለስ አለው።"
(የሐዋርያት ሥራ 3: 6)
ከዚህም ባሻገር ቅዱሳን ወደ ቅድስና ሲጠሩ ስማቸው ይለወጣል ስመ እግዚአብሔርም ይሆናል:: በመሆኑ እነርሱም በስማቸው ማዳን ይቻላቸዋል "፤ እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ #በእኔ_የሚያምን_እኔ_የማደርገውን_ሥራ እርሱ ደግሞ ያደርጋል፤ #ከዚህም_የሚበልጥ_ያደርጋል፥" (የዮሐንስ ወንጌል 14: 12)
ከእርሱ አብልጦ የሚሰራ የለም ነገር ግን በስሙ ላመኑ እርሱ ያደረገውን ሁሉ የማድረግ ሥልጣን አላቸው ማለቱ ነው።

ይቆየን።

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
#ይህን ያለው ሻለቃ ኃይለ ገብረ ሥላሴ አይደለም ። እንዲ ያለው የደማስቆው ሯጭ ቅዱስ ጳውሎስ ነው ። “በእሽቅድምድም ስፍራ የሚሮጡት፥ ሁሉ እንዲሮጡ ነገር ግን አንዱ ብቻ ዋጋውን እንዲቀበል አታውቁምን? እንዲሁም ታገኙ ዘንድ ሩጡ።” #1ኛ ቆሮ 9፥24 ክርስቲያኖች የዚህች ዓለም ዙር እስኪያልቅ ድረስ በትጋት እና በውድድር መንፈስ መሮጥ አለባቸው ። ያሸነፉ ሁሉ እንጂ የሮጡ ሁሉ ጥሩ ዋጋን አይሸለሙም። “ እላችኋለሁና ጽድቃችሁ ከጻፎችና ከፈሪሳውያን ጽድቅ ካልበለጠ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም።” #ማቴ 5፥20 በእርግጥ የኑሮ ሩጫ ለየ ቅል ነው እግዚአብሔር ወንዱን ከሴቱ ሕጻኑን ከአዋቂው ደምሮ በአንድ መስፈርት አያወዳድርም ለሁሉም እንደስራው መደብ በጽድቅ ይፈርድለታል እንጂ። ጻድቁ ወደፊት ይጽደቅ ቅዱሱም ወደፊት ይቀደስ ጠማማውም ወደ ፊት ይጥመም "እነሆ በቶሎ እመጣለሁ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍለው ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ዘንድ አለ እንዳለ ራእይ .ዮሐ22÷12

#ቅዱስ_ጳውሎስ ምርጥ ዕቃዬ ከመባሉ በፊት ሳዉል ይባል ነበር። ሁል ጊዜ ለኦሪት ሕግ የሚቀና ስለነበር ክርስቶስን እንከተላለን የሚሉ ክርስቲያኖች ሲመጡ ከኦሪቷ ሕግ ያፈነገጡ ስለመሰለው እነርሱን ያጠፉ ዘንድ ሌሊትና ቀን ሳይታክት ተሯሩጧል ። #ሐዋ 8፥3

ክርስቲያኖችን ለማሰር ብዙ ጊዜ ሮጧል፤ ክርስቲያኖችን ለማስደብደብ ብዙ ጊዜ ጥሯል፤ ክርስቲያኖችን ለማሳደድ ብዙ ጊዜ ሽምጥ ጋልቧል፤ክርስቲያኖችም በድንጋይ ተወግረው ሲሞቱ የገዳዮችን ልብሶች በደስታ ጠብቆል። ሳውል በዚህ ነገር ሁሉ ሮጧል ግን በምድርም ሆነ በሰማይ ኒሻን የሚሸልመው አልነበረም።

#በመጨረሻ ግን ክርስቲያኖችን ጨርሶ ይፈጅ ዘንድም የፍቃድ ደብዳቤ ሊያጽፍ ወደ ደማስቆ ሽምጥ ጋለበ በአጥፊነት መንፈስም ሮጠ #ሐዋ 9÷15

ወደ ከተማዋ ሲገባ ግን በታላቅ ብርሃን ተመታ ከፈረሱም ወድቆ ከብርሃኑ ጸዳል የተነሳ ዐይኑ ታውሮ ማየት ተሳነው ወዲያውም ሳውል ሳውል ስለምን ታሳድደኛለህ የሚል ቃል ሰማ።

#የማሳድድህ_አንተ ማነህ ? ብሎ ጠየቀ የምታሳድደኝ የናዝሬቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነኝ የመውጊያውን ብረት ብትረግጥ ላንተ ይብስብሃል አለው ሳውልም ጌታ ሆይ ምን አደርግ ዘንድ ትወዳለህ አለው ወደ ደማስቆም ግባ ሐናንያ የሚባል የእግዚአብሔር ሰው ታገኛለህ እርሱ ይፈውስሃል አለው ።

ሳዉልም ከምድር ተነሳ ዐይኖቹም እንደታወሩ ነበሩ እየመሩም ወደ ከተማዋ አገቡት ለሐናንያም የጠርሴስ ሰው ሳውል ወደ እርሱ እንደሚመጣ በራዕይ ተነገረው ።

#ሐናንያ_ግን ስለ ሳውል ክፋት ብዙ ይሰማ ነበርና እንዴት እፈውሰው ዘንድ ይገባልን አለው ። ጌታም ይህ በአሕዛብም በነገሥታትም በእስራኤልም ልጆች ፊት ስሜን ይሸከም ዘንድ ለእኔ የተመረጠ ዕቃ ነውና ሂድ፤ ስለ ስሜ ስንት መከራ ሊቀበል እንዲያስፈልገው እኔ አመለክተዋለሁና አለው። #ሐዋ 9÷ 13-15

#እግዚአብሔር እንዲህ ነው እያሳደድከውም ይወድሃል እየገደልከው ያኖርሃል እያሰርከው ይፈታሃል እየሸሸህው በፍቅር ይከተልሃል ሰዎች እንደ ሸክም ሲቆጥሩህ ሁሉን ቻይ ትከሻህ ያለው ይሆናል ብሎ ይመሰክርልሃል ሰው ኃጢያተኛ እያለህ እርሱ ግን ምርጤ ይልሃል። #እግዚአብሔር እንዲህ ነው!
ሐናንያም ሄዶ ወደ ቤቱ ገባ፥ እጁንም ጭኖበት፦ ወንድሜ ሳውል ሆይ፥ ታይ ዘንድና መንፈስ ቅዱስ ይሞላብህ ዘንድ ላከኝ አለ። #ወዲያውም_እንደ_ቅርፊት_ያለ ከዓይኑ ወደቀ፥ ያን ጊዜም ደግሞ አየ፤ ተነሥቶም ተጠመቀ፥ በክፉት መንገድ ሮጦ ያተረፈው እውርነትን ተረዳ አሁን ግን በጽድቁም መንገድ መሮጥን መረጠ።“
#እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በመንገድ ላይ ቁሙ #ተመልከቱም፥ የቀደመችውንም መንገድ ጠይቁ፤ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደ ሆነች እወቁ፥ በእርስዋም ላይ ሂዱ፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤ እነርሱ ግን ” ያለ ዐይን መመልከት፣ መሄድ እንዲሁም መሮጥ አይቻልም።
በሥጋ ለመሮጥ ዓይነ ሥጋ በመንፈሳዊ ሕይወት ለመሮጥ ዐይነ ልቡና ሊኖረን ይገባል ያለ ዐይን እንኳን መሮጥ በደህንነትና በምቶት መራመድ አይቻልም። ዐይን ለሰውነት ሁሉ ወሳኝ አካል ናት በእርግጥ ዐይን አይሮጥም የሚሮጠው እግር ነው ሆኖም መነሻውን መገስገሻውንና መዳረሻውን ዐይን ካላመለከተችሁ እግር ወስዶ ወስዶ ገደል ይከታል ። “ዕውርም ዕውርን ቢመራው ሁለቱም ወደ ጉድጓድ ይወድቃሉ አለ።” #ማቴ 15፥14
ስለሆነም በእግረ ሥጋ ለመሮጥ ዐይነ ሥጋ በእግረ ልቡና ለመሮጥ ዐይነ ልቡና የግድ ያስፈልገናል። #ታገኙ_ዘንድ_ሩጡ " ብሎ ስለ መንፈሳዊ ሩጫ የመከረን ቅዱስ ጳውሎስ ከሥጋው ዐይንና ከልቦናው ዐይን ላይ ጋርዶት የነበረው ቅርፊት ከወደቀለት በኋላ ነው።
#አሁን የሚያሯሩጠው ሳውል ተብሎ አይጠራም ፤ አሁን የሚያሳድደው ሳውል መባሉ ቀርቷል፤አሁን ደብዳቢ መሆኑ አብቅቷል። አሁን ስለ ስሙ ከቦታ ቦታ የሚሯሯጥ ምርጥ ዕቃ ጳውሎስ ሆኗልና አሁን ስለስሙ ከሀገር ወደ ሀገር የሚንከራተት ስደተኛው ሆኗልና ። 2ቆሮ 11÷23-27
ዋጋ ለማግኘት መሮጥ እንዳናይ የጋረደንን ግርዶሽ ከመጣል ይጀምራል ። ከሳውል ዐይን ቅርፊት መሳይ ነገር ወደቀ ሲል ከአስተሳሰቡና ከልቦናውም ዐይን ጭምር ቅርፊቱ እንደወደቀለት ማስተዋል ያስፈልጋል። ክርስቶስን ወዶ እናቱን ማሳደድ ክርስቶስን ወዶ ክርስቲያኖችን መጥላት ይህ የልቡና ግርዶሽ ፣ ይህ የልቡና ሽፋን፣ ይህ የዕሊና ቅርፊትም ነውና። #እግዚአብሔር እንደ ሳውል ነቅሎ ይጣልላቸው አጥርተው ያዮ ዘንድም የተንሸዋረረ ዐይነ ልቦናቸውን ሐናንያ በመሰሉ የቅዱሳኑ ጸሎትና ምልጃ ያብራላቸው።

#ሃይማኖት የሌላችሁ ወደ ሃይማኖት ሩጡ
#ሃይማኖት ያላችሁ ወደ ምግባር ገስግሱ
#ምግባር ያላችሁ ወደ ትሩፉት ፍጠኑ ወደ ገነት በር ትደርሳላችሁ ተከፍቶም ታገኙታላችሁ ከየት ናችሁ የሚላችሁም አይኖርም። ያን ጊዜ የደማስቆውን ሯጭ ታኙታላችሁ አብራችሁትም “ መልካሙን ገድል ተጋድዬአለሁ፥ ሩጫውን ጨርሼአለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤” ትላላችሁ ። #2ኛ ጢሞ 4፥7


አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሐምሌ ፳፮/፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
#ይህን ያለው ሻለቃ ኃይለ ገብረ ሥላሴ አይደለም ። እንዲ ያለው የደማስቆው ሯጭ ቅዱስ ጳውሎስ ነው ። “በእሽቅድምድም ስፍራ የሚሮጡት፥ ሁሉ እንዲሮጡ ነገር ግን አንዱ ብቻ ዋጋውን እንዲቀበል አታውቁምን? እንዲሁም ታገኙ ዘንድ ሩጡ።” #1ኛ ቆሮ 9፥24 ክርስቲያኖች የዚህች ዓለም ዙር እስኪያልቅ ድረስ በትጋት እና በውድድር መንፈስ መሮጥ አለባቸው ። ያሸነፉ ሁሉ እንጂ የሮጡ ሁሉ ጥሩ ዋጋን አይሸለሙም። “ እላችኋለሁና ጽድቃችሁ ከጻፎችና ከፈሪሳውያን ጽድቅ ካልበለጠ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም።” #ማቴ 5፥20 በእርግጥ የኑሮ ሩጫ ለየ ቅል ነው እግዚአብሔር ወንዱን ከሴቱ ሕጻኑን ከአዋቂው ደምሮ በአንድ መስፈርት አያወዳድርም ለሁሉም እንደስራው መደብ በጽድቅ ይፈርድለታል እንጂ። ጻድቁ ወደፊት ይጽደቅ ቅዱሱም ወደፊት ይቀደስ ጠማማውም ወደ ፊት ይጥመም "እነሆ በቶሎ እመጣለሁ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍለው ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ዘንድ አለ እንዳለ ራእይ .ዮሐ22÷12

#ቅዱስ_ጳውሎስ ምርጥ ዕቃዬ ከመባሉ በፊት ሳዉል ይባል ነበር። ሁል ጊዜ ለኦሪት ሕግ የሚቀና ስለነበር ክርስቶስን እንከተላለን የሚሉ ክርስቲያኖች ሲመጡ ከኦሪቷ ሕግ ያፈነገጡ ስለመሰለው እነርሱን ያጠፉ ዘንድ ሌሊትና ቀን ሳይታክት ተሯሩጧል ። #ሐዋ 8፥3

ክርስቲያኖችን ለማሰር ብዙ ጊዜ ሮጧል፤ ክርስቲያኖችን ለማስደብደብ ብዙ ጊዜ ጥሯል፤ ክርስቲያኖችን ለማሳደድ ብዙ ጊዜ ሽምጥ ጋልቧል፤ክርስቲያኖችም በድንጋይ ተወግረው ሲሞቱ የገዳዮችን ልብሶች በደስታ ጠብቆል። ሳውል በዚህ ነገር ሁሉ ሮጧል ግን በምድርም ሆነ በሰማይ ኒሻን የሚሸልመው አልነበረም።

#በመጨረሻ ግን ክርስቲያኖችን ጨርሶ ይፈጅ ዘንድም የፍቃድ ደብዳቤ ሊያጽፍ ወደ ደማስቆ ሽምጥ ጋለበ በአጥፊነት መንፈስም ሮጠ #ሐዋ 9÷15

ወደ ከተማዋ ሲገባ ግን በታላቅ ብርሃን ተመታ ከፈረሱም ወድቆ ከብርሃኑ ጸዳል የተነሳ ዐይኑ ታውሮ ማየት ተሳነው ወዲያውም ሳውል ሳውል ስለምን ታሳድደኛለህ የሚል ቃል ሰማ።

#የማሳድድህ_አንተ ማነህ ? ብሎ ጠየቀ የምታሳድደኝ የናዝሬቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነኝ የመውጊያውን ብረት ብትረግጥ ላንተ ይብስብሃል አለው ሳውልም ጌታ ሆይ ምን አደርግ ዘንድ ትወዳለህ አለው ወደ ደማስቆም ግባ ሐናንያ የሚባል የእግዚአብሔር ሰው ታገኛለህ እርሱ ይፈውስሃል አለው ።

ሳዉልም ከምድር ተነሳ ዐይኖቹም እንደታወሩ ነበሩ እየመሩም ወደ ከተማዋ አገቡት ለሐናንያም የጠርሴስ ሰው ሳውል ወደ እርሱ እንደሚመጣ በራዕይ ተነገረው ።

#ሐናንያ_ግን ስለ ሳውል ክፋት ብዙ ይሰማ ነበርና እንዴት እፈውሰው ዘንድ ይገባልን አለው ። ጌታም ይህ በአሕዛብም በነገሥታትም በእስራኤልም ልጆች ፊት ስሜን ይሸከም ዘንድ ለእኔ የተመረጠ ዕቃ ነውና ሂድ፤ ስለ ስሜ ስንት መከራ ሊቀበል እንዲያስፈልገው እኔ አመለክተዋለሁና አለው። #ሐዋ 9÷ 13-15

#እግዚአብሔር እንዲህ ነው እያሳደድከውም ይወድሃል እየገደልከው ያኖርሃል እያሰርከው ይፈታሃል እየሸሸህው በፍቅር ይከተልሃል ሰዎች እንደ ሸክም ሲቆጥሩህ ሁሉን ቻይ ትከሻህ ያለው ይሆናል ብሎ ይመሰክርልሃል ሰው ኃጢያተኛ እያለህ እርሱ ግን ምርጤ ይልሃል። #እግዚአብሔር እንዲህ ነው!
ሐናንያም ሄዶ ወደ ቤቱ ገባ፥ እጁንም ጭኖበት፦ ወንድሜ ሳውል ሆይ፥ ታይ ዘንድና መንፈስ ቅዱስ ይሞላብህ ዘንድ ላከኝ አለ። #ወዲያውም_እንደ_ቅርፊት_ያለ ከዓይኑ ወደቀ፥ ያን ጊዜም ደግሞ አየ፤ ተነሥቶም ተጠመቀ፥ በክፉት መንገድ ሮጦ ያተረፈው እውርነትን ተረዳ አሁን ግን በጽድቁም መንገድ መሮጥን መረጠ።“
#እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በመንገድ ላይ ቁሙ #ተመልከቱም፥ የቀደመችውንም መንገድ ጠይቁ፤ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደ ሆነች እወቁ፥ በእርስዋም ላይ ሂዱ፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤ እነርሱ ግን ” ያለ ዐይን መመልከት፣ መሄድ እንዲሁም መሮጥ አይቻልም።
በሥጋ ለመሮጥ ዓይነ ሥጋ በመንፈሳዊ ሕይወት ለመሮጥ ዐይነ ልቡና ሊኖረን ይገባል ያለ ዐይን እንኳን መሮጥ በደህንነትና በምቶት መራመድ አይቻልም። ዐይን ለሰውነት ሁሉ ወሳኝ አካል ናት በእርግጥ ዐይን አይሮጥም የሚሮጠው እግር ነው ሆኖም መነሻውን መገስገሻውንና መዳረሻውን ዐይን ካላመለከተችሁ እግር ወስዶ ወስዶ ገደል ይከታል ። “ዕውርም ዕውርን ቢመራው ሁለቱም ወደ ጉድጓድ ይወድቃሉ አለ።” #ማቴ 15፥14
ስለሆነም በእግረ ሥጋ ለመሮጥ ዐይነ ሥጋ በእግረ ልቡና ለመሮጥ ዐይነ ልቡና የግድ ያስፈልገናል። #ታገኙ_ዘንድ_ሩጡ " ብሎ ስለ መንፈሳዊ ሩጫ የመከረን ቅዱስ ጳውሎስ ከሥጋው ዐይንና ከልቦናው ዐይን ላይ ጋርዶት የነበረው ቅርፊት ከወደቀለት በኋላ ነው።
#አሁን የሚያሯሩጠው ሳውል ተብሎ አይጠራም ፤ አሁን የሚያሳድደው ሳውል መባሉ ቀርቷል፤አሁን ደብዳቢ መሆኑ አብቅቷል። አሁን ስለ ስሙ ከቦታ ቦታ የሚሯሯጥ ምርጥ ዕቃ ጳውሎስ ሆኗልና አሁን ስለስሙ ከሀገር ወደ ሀገር የሚንከራተት ስደተኛው ሆኗልና ። 2ቆሮ 11÷23-27
ዋጋ ለማግኘት መሮጥ እንዳናይ የጋረደንን ግርዶሽ ከመጣል ይጀምራል ። ከሳውል ዐይን ቅርፊት መሳይ ነገር ወደቀ ሲል ከአስተሳሰቡና ከልቦናውም ዐይን ጭምር ቅርፊቱ እንደወደቀለት ማስተዋል ያስፈልጋል። ክርስቶስን ወዶ እናቱን ማሳደድ ክርስቶስን ወዶ ክርስቲያኖችን መጥላት ይህ የልቡና ግርዶሽ ፣ ይህ የልቡና ሽፋን፣ ይህ የዕሊና ቅርፊትም ነውና። #እግዚአብሔር እንደ ሳውል ነቅሎ ይጣልላቸው አጥርተው ያዮ ዘንድም የተንሸዋረረ ዐይነ ልቦናቸውን ሐናንያ በመሰሉ የቅዱሳኑ ጸሎትና ምልጃ ያብራላቸው።

#ሃይማኖት የሌላችሁ ወደ ሃይማኖት ሩጡ
#ሃይማኖት ያላችሁ ወደ ምግባር ገስግሱ
#ምግባር ያላችሁ ወደ ትሩፉት ፍጠኑ ወደ ገነት በር ትደርሳላችሁ ተከፍቶም ታገኙታላችሁ ከየት ናችሁ የሚላችሁም አይኖርም። ያን ጊዜ የደማስቆውን ሯጭ ታኙታላችሁ አብራችሁትም “ መልካሙን ገድል ተጋድዬአለሁ፥ ሩጫውን ጨርሼአለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤” ትላላችሁ ። #2ኛ ጢሞ 4፥7


አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሐምሌ ፳፮/፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
" #ኢትዮጵያዊው_ኤልሳዕ
#በአጽሙ_ሙት_ያስነሳ "
_
፪ኛ ነገሥት ፲ ፫÷፳ -፳ ፩
ገ/ተ #ሃይማኖት ም/፶ ፫

አጥንት በመጻሕፍ ቅዱስ ውስጥ በምሳሌነት ሲጠቀስ ሦስት ነገሮችን ያመለክታል።
፩ የሰው ኃይልን ያመላክታል መዝ ፶ ፫፥፭ ኢሳ፴ ፰፥፲ ፫
፪ የቅርብ ዝምድና መግለጫ ሆኖ ቀርቧል ዘፍ ፳ ፱÷፲ ፬ ሳሙ ፱÷፪
፫ የሞተ ሰውን ክብር ያስረዳል ዘፍ ፶÷፳ ፭ ዕብ ፲ ፩÷፳ ፪
#ይበልጡኑ_የቅዱሳን_ሰዎች ሞት /አጥንት (አጽም)/ እጅግ የከበረ ነው ። መዝ ፻ ፲ ፭ (፻ ፲ ፮) ÷፲ ፭ ለአብነትም ተቀብሮ የነበረው የኤልሳዕ አጥንት /አጽም/ ሌላ የሞተ ሰው ከሞት እንዳስነሳ መመልከት በቂ ነው። ከሞዓብም አደጋ ጣዮች በየዓመቱ ወደ አገሩ ይገቡ ነበር።ሰዎችም አንድ ሰው ሲቀብሩ አደጋ ጣዮችን አዩ፥ ሬሳውንም በኤልሳዕ መቃብር ጣሉት፤ የኤልሳዕንም አጥንት በነካ ጊዜ ሰውዮው ድኖ በእግሩ ቆመ። ፪ኛ ነገሥት ፲ ፫÷፳ -፳ ፩
በተመሳሳይ ኢትዮጵያዊው ኤልሳዕ ጻድቁ አባታችን ተክለ ሃይማኖትም የሥጋ ድካም ከትጋቱ እንዳያስታጉለው በስምንት ሰለታም ጦር እራሱን ከቦ ከደብረ አስቦ ዋሻ ከቆመ ሳይቀመጥ ከዘረጋ ሳያጥፍ ፳ ፪ ዓመት ሲጋደል ሳለ ከመቆም ብዛት አንዲቷ የእግሩ አገዳ ተሰበረችና ከሰውነቱ ተለይታ ወደቀች።
#ደቀ_መዛሙርቱም እንደ ማንም መስሏቸው ስባረ እግሩን ከመቃብር ሥፍራ ወረወሯት የኤልሳዕን አጽም ሲነካው ከሞት ድኖ እንደተነሳው ሰው የአባታችን የእግራቸው አጥንት የነካው በመቃብሩ ሥፍራ ተቀብሮ የነበረ አንድ ሰው አፈፍ ብሎ ድኖ በእግሩ ቆመ ። ገ/ተ ሃይማኖት ፶ ፫
የአባታችንንም ስባረ አጽም (ስባረ እግር) እያመሰገነ ሰላምታ ሰጠ " ይህን ያዮ ደቀ መዛሙርቶቻቸውም የጻድቁ ስባረ አጽም ገባሬ ተአምራት መሆኗን አውቀው ከመንበሩ እግር በታች አክብረው በሰበን ጠቅልለው ቀብረዋታል::
" #የጻድቃን መከራቸው ብዙ ነው፥ እግዚአብሔርም ከሁሉ ያድናቸዋል። እግዚአብሔር አጥንቶቻቸውን ሁሉ ይጠብቃል፥ ከእነርሱም አንድ አይሰበርም። " መዝ ፴ ፫{፴ ፬}÷፲ ፱-፳ ይህ የቅዱሳን አጥንት (አጽም) እግዚአብሔር የማይለየውና ሌት ተቀን የሚጠብቀው ነውና ቅዱሳን ጻድቃን ካረፉበት ሄዶ መሳለም በረከትን ያሰጣል ከሥጋም ከነፍስም ህመም አድኖ በጤና ያቆማልና የአጽማቸውን በዓል ማክበር እጅግ የሚገባ ነው ::
ቅዱስ ጳውሎስ በልብሱ ጨርቅ " (ሐዋ፲ ፱÷፲ ፩-፲ ፪) ቅዱስ ጴጥሮስ በሰውነቱ ጥላ ድውያንን ሁሉ ይፈውሳቸው ነበር ። ( ሐዋ ፭÷፲ ፭ ) ቅዱሳን የነፍሳቸው ቅድስና ለሥጋቸው፣ የሥጋቸው ቅድስና ለለበሱት ልብስና ለአካላቸው ጥላ ተርፎ ድንቅ ተአምራትን የሚሰራ ከሆነ እግዚአብሔር የሚጠብቀው አጽማቸውማ እንዴት አብልጦ ድንቆችን አይሰራ?!::
#አጥንት_ለሰዉ ልጅ ተክለ ሰውነት ወሳኝ ድርሻ አለው። ከሚሰጣቸው ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች መካከል የተወሰኑት ብንዳስስ፤ ለሰዉነታችን ቅርፅ ለመስጠት፣ የሰዉነት የውስጥ አካላት (Organs) ከአደጋ ለመከላከል #ለምሳሌ ደረት የሚያርፍበት ክፍለ አጥንት ለሳንባና ለልብ ከለላ(covering) ይሰጣል፤ የራስ ቅል አጥንት አንጎል ምንም አይነት ጉዳት እንዳይገጥመው ጠንካራ ልባስ ሆኖ ይከላከላል ፣ ሥጋና ጡነቻዎቻችንን አጣብቆ ለመያዝና የካልስየም ንጥረ ነገርን ለማጠራቀም ይረዳል፡፡
ክቡር የሆነ አባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖትም ለቀናች ሃይማኖቱ አጥንት ነው። አጥንት የሌለው አካል ጤፍ እንደሌለው ማዳበሪያ መቆም አይቻለሁም:: ሀገሪቱና ቤተክርስቲያኒቱ ዶግማ ቀኖናና ትውፊቷን ይዛ ቅርጻን ሳትለቅ ቀጥ ብላ እንድትቆም አድርጓታልና።
# ምዕመኗ ልዮ ልዮ በሆነ በእግዳ ትምህርት ከበረትቷ እንዳይኮበልሉ ኖላዊ ትጉሁ ሆኖ
በጾም በጸሎቱ የሀገር ዋልታ በመሆንም አካል ለምትባል ቅድስት ቤተክርስቲያን እንደ
አጥንት ጋሻ፣ መከታ፣ ጥላ ፣ከለላ ሆነላት።
የሃይማኖት ማነስ የምግባር ጉድለት እንዳያጋጥማትም በቃሉ ትምህር በእጁ ተአምራት
በበረከቱ ሞላት፤ በረድኤቱ ጋረዳት እንደ አጥንት የሃይማኖት መፍሰሻ ነቅ የወንጌል
መፍለቂያ ምንጭም አደረጋት።
#የምታበረታ_አጥንት_በረከቱ_ትደርብን ! #አሜን!!

ኃ/ማርያም አ.አ ኢትዮጵያ
ጥር ፳ ፬\፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም