ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
930 photos
24 videos
271 files
193 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
Deleted Account
አንድ ሰው በተክሊል ማግባት የሚችል ወይም የምችል መቼ ነው? በምን ሁኔታስ ነው?
ተክሊል ማለት ከለለ አከበረ ከሚለው ግሥ የተገኘ ቃል ሲሆን ትርጓሜውም ክብር ማለት ነው። ተክሊል ምሥጢር ተብሎ መጠራቱ ሙሽራውና ሙሽሪት በግብር አምላካዊ አንድ የሚሆኑበት የጋብቻ ሥርዓት በመሆኑ ነው። ጋብቻ በቤተ ክርስቲያን ሲፈጸም ምሥጢርነት አለው። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም "... ይህ ምሥጢር ታላቅ ነው" ማለቱ ይህንኑ ያረጋግጥልናል።
#የተክሊል አፈጻጸም
እንደ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ /ሥርዓት/ ተክሊል ከሥርዓተ ቅዳሴና ከቅዱስ ቁርባን ጋር ተያይዞ የሚፈጸም ምሥጢር ነው። እንጂ ብቻውን አይፈጸምም። ጸሎተ ተክሊል ተደርሶ ቅዱስ ቁርባን መቀበል ከቀረ ግን ተክሊሉ ፍጹም አይደለምና ጋብቻው አይጸናም።
#ሥርዓተ ተክሊል ለማን ይፈጸማል?
ተክሊል የሚፈጸመው ንጽሕናዋን ጠብቃ ከወንድ እርቃ ለኖረች ጥብቅ ልጃገረድ ወይም በሥጋ ድንግልናዋን ለጠበቀች በተግባር ዝሙት ላልፈጸመች ኦርቶዶክሳዊ ሴት ነው። ሴትን በምንጣፍ ተገናኝቶ የማያውቅ ንጽሕናውን ጠብቆ ልኖር ኦርቶዶክሳዊ ወንድ ብቻ የሚፈጸም የጋብቻ መፈጸሚያ አይነት ነው። በአጠቃላይ ተክሊል ከሥጋዊ ድንግል ጋር አብሮ የሚሄድ ምሥጢር መሆኑን ቤተ ክርስቲያን የሥርዓት መጽሐፍቶች ሁሉ ተባብረው የሚመሰክሩት ጉዳይ ነው። ለምሳሌ ፍትሃ ነገስት እንዲህ ይላል ፦ "ይህ ተክሊል በጋብቻ ጊዜ ለድንግል ወንድና ለድንግል ሴት ይገባል።" ፍትሃ ነገስት 24:906 ከላይ ያነሳነው ሥርዓት ግን በደንብ ካልተብራራ ተክሊልን በተመለከተ የሚነሱትን ጥያቄዎች ከምንጫቸው ማድረግ የሚችል አይሆንም። ሰለዚህ በዚህ ምሥጢር ዙሪያ ለሚነሱት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት እንድንችል ድንግልና እንደቤቱ ክርስቲያናችን አስተምህሮ እንዴት ይታያላል /ይብራራል/ የሚለውን በደንብ መመልከት ይገባል።

#ድንግልና ምንድን ነው?
ድንግልና የሚለው ቃል ተደነገለ ተጠበቀ ከሚለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ትርጓሜውም መጠበቅ ማለት ነው። ድንግልና እንደ ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ንዑስ ሕዋስን /Hymen/ ለመግለጽ ብቻ ሳይሆን የንጽሕና አኗኗር ለማስረዳት አንድ ድርጊት መፈጸም ወይም አለመፈጸሙን ለማመልከት አገልግሎት ላይ የሚውል ቃል መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል።
ሰለዚህም አንዲት ኦርቶዶክሳዊት ሴት ሥጋዊ የሆነው የድንግል ማሕተም ስላልፈረሰባት ብቻ ሥርዓተ ተክሊል መፈጸም ትችላለች ሌላኛዋ ኦርቶዶክሳዊት ደግሞ ሥጋዊ የድንግልናዋ ማሕተም ሰለፈረሰ ብቻ ተክሊል አይገባትም ማለት አይደለም። በቅድሚያ እዚህ ላይ ያለውን ውዥንብር መደንብ ለማጥራት በሴቶች ተፈጥሮ ውስጥ የሚገኘውን የድንግልና አይነቶችን ማየት ይጠቅማል።
#የሴቶች ድንግልና ተፈጥሮ ዓይነቶች
ማኅተመ ድንግልና ሴት ከወንድ ጋር ሩካቤ አድርጋ አለማወቋን የሚያስረዳ የሥራዋ መገለጫ የአኗኗሯ መታወቂያ ልዩ የተፈጥሮ ምልክትና የድንግልናዊ ኑሮዋ ዘውድ ነው። ይህ ተፈጥሮዊ ማኅተም በሴቶች አፈ ማኅፀን ቀለበት በሚመስል ስስ ሥጋነት በጉልህ ይታወቃል። ይህ ማለት ግን ሩካቤና ሰስሎተ ድንግልና /የድንግልና መወገድ/ የተለያዩና
ራሳቸውን የቻሉ ተግባራት መሆናቸውን መገንዘብ ይኖርብናል። አንዲት ሴት ማኅተመ ድንግልና ስላላት ብቻ " ሩካቤ አድርጋ አታውቅም" " ወይም ሩካቤ ስላደረች ማኅተመ ድንግልና ሊኖራት አይችልም። ብሎ ድምዳሜ ላይ መድረስ አለመቻሉን እንረዳለን። በዚህም የተነሳ የድንግልና አይነቶችን ከተክሊል ጋር እያዛመዱ መመልከት ያስፈልጋል። ለምሳሌ ወንዶች እንደ ሴቶች ተጨባጭና ጉልህ የድንግልና ምልክት ስለሌላቸው ከሴት ጋር ሩካቤ ፈጽመው የማያውቁ ሆነው ሳለ ደናግል አይደሉም ማለት አይቻልም። እንደዚሁ ሁሉ ሩካቤን ፈጽመው የማያውቁ ሴቶች የድንግልና ማኅተም ስለሌላቸው ብቻ ደናግላን
ከመባል አይከለከሉም። በሌላ አቅጣጫ ስንመለከት ወንዶች ሩካቤ ፈጽመው ሳለ እንደ ሴቶች የሚገሠሥ ማኅተመ ድንግልና ስለሌላቸው ድንግልናቸውን አልፈረሰም እንደማይባል ሁሉ ሴቶች ሩካቤ ሥጋ እየፈጸሙ በልዩ ልዩ ምክንያት ማኅተመ ድንግልናቸውን ባይገሠሥም መደበኛ ሩካቤ እስከ ፈጽሙ ድረስ ደናግል ሊባሉ አይችሉም። ለዚህም ነው ሰለድንግልና አይነቶች ማውራት አስፈላጊ ሁኖ የተገኘው ፦
#የድንግልና ዓይነት
የድንግልና መለያ ወይም ስስ የክብር ንጽሕና ሽፋን /Hymen/ ዓይነታቸው አራት ሲሆኑ በሁሉም ሴቶች ላይ የሚኖረው ዓይነት ምንም እንኳን በተፈጥሮ ተወስኖ የተፈጠረ ቢሆንም ግን ከግብረ ሥጋ ግንኙነት ውጭ ድንግልና የሚጠፋባቸው በርካታ ምክንያቶች ይኖራሉ። ይህም ከሴቶች የድንግልና ተፈጥሮ አንጻር ነው።
#አንደኛ ደረጃ_የድንግልና ማኅተም /Hymen/ ምልክቶች ፦ ይህ ድንግልና አይነት ያላቸው ሴቶች ንዑስ ሕዋስ የድንግልና ማኅተም ምልክቱ የሌላቸው ሲሆኑ እነዚህ ምንም እንኳን ከአጠቃላዩ ሴቶች ሲታይ ቁጥራቸው አናሳና አንዳንድ መረጃዎች እንደ ሚጠቁሙት ከሦስት እስከ አምስት በመቶ የማይበልጡ ቢሆኑም የዚህ አይነት ተፈጥሮ ባለ ድርሻ የሆኑ እህቶች የሠርጋቸውን የመጀመሪያውን የግብረ ሥጋ ግንኙነት ሲዳርጉ ምናሴም እንኳን ሕመም ቢሰማቸውም እንደሌሎቹ የድንግልና አይነቶች ያለ መድማታቸው አይነቱን የተለየ ያደርገዋል። ይህ አይነቱ ድንግልና ያላቸው ወጣት ሴቶች ምንም እንኳን ከጋብቻ በፊት የግብረ ሥጋ ግንኙነት ፈጽመው የማያውቁ ራሳቸውን በቅድስናና በንጽሕና ጠብቀው የኖሩ ቢሆኑም ሆኖም ግን በጋብቻቸው ምሽት የመጀመሪያውን የግብረ ሥጋ ግንኙነት ሲፈጽሙ ደም ባለመታየቱ በባላቸው ዘንድ ተአማኒነት የሚያጡበት አሳዛኝ አጋጣሚ የሚከሰትበት አጋጣሚ አለ።
#ሁለተኛ ደረጃ የድንግልና ዓይነት፦ይህ የድንግልና አይነት በተፈጥሮ ያላቸው ሴቶች የድንግልና መለያቸው በጣም ስስነት ያለው ሲሆን እነዚህ አይነት ሴቶች በቁጥር ከአጠቃላዩ ሴቶች ከሃያ አምስት በመቶ ያላነሱ ናቸው። ይህ የድንግልና አይነት ከግብረ ሥጋ ግንኙነት ውጭ በተለያዩ የጥንቃቄ ጉድለቶች ሊወገድ የሚችልባቸውም አጋጣሚዎችም አሉ። በዚህ የድንግልና አይነት የሚኖሩ እህቶች ከባድ በሆነ አካላዊ እንቅስቃሴ ጥንቃቄ በጎደለው አለባበስ የተነሳ ሊወገድ ይችላል። እነዚህ እህቶች በሩካቤ ሥጋ ግንኙነት በዝሙት ተግባር ሳይገኙ ድንግልናቸውን ሊያጡት ይችላሉ።
#ሦስተኛው ደረጃ የድንግልና ዓይነት፦ ይህ የድንግልና ዓይነት መካከለኛ ደረጃ ውፍረት ያለው ሲሆን የድንግልና መለያ ምልክት በአብዛኛው ሴቶች ላይ ማለትም ከአጠቃላዩ ድንግልና ካላቸው ወጣት ሴቶች ከግማሽ በላይ በሚሆኑት ላይ የሚገኝ የድንግልና ማኅተም አይነት ነው። ይህ የድንግልና አይነት እስከ አሁን ካየናቸው የድንግልና ማኅተሞች በጥንካሬና በውፍረት የተሻለ ከመሆኑ በላይ ከግብረ ሥጋ ግንኙነት በስተቀር በሌሎች የጥንቃቄ ጉድለቶች ማለትም ጥንቃቄ በጎደለው ስፖርትና በመሳሰሉት የመወገድ ዕድሉ በጣም ዝቀተኛ ነው።
#አራተኛ ደረጃ የድንግልና ዓይነት ፦ ይህ የድንግልና አይነቶች ጽኑ የሚባል ነው። ከግብረ ሥጋ ግንኙነት ውጭ በሌላ በምንድን አይነት መንገድ የሚፈርስ የሚወገድ አይደለም። ተክሊል የሚገባት ሩካቤ ሥጋ ግንኙነት ፈጽማ ድንግልናዋ ላልፈረሰባት ሴት አይደለም። ይቺ ሴት ምንም እንኳን የሥጋ ድንግልናዋ ቢኖርም የዝሙት ተግባርን ፈጽማለችና ተክሊል አይገባትም። በተለይ አራተኛው የድንግልና አይነት ላይ የሚገኙ ጽን የድንግልና ማኅተም ያላቸው ሴቶች በመጀመሪያው የሩካቤ ሥጋ ግንኙነት የድንግልና ማኅተማቸው ላይወገድ ይችላል። ይህንን ሩካቤ ሥጋ ግንኙነት የፈጸሙት ከጋብቻ ውጭ ከሆነ ዝሙት ነውና የድንግልና ማኅተም አለኝ ተ
ተክሊል ማለት ከለለ አከበረ ከሚለው ግሥ የተገኘ ቃል ሲሆን ትርጓሜውም ክብር ማለት ነው። ተክሊል ምሥጢር ተብሎ መጠራቱ ሙሽራውና ሙሽሪት በግብር አምላካዊ አንድ የሚሆኑበት የጋብቻ ሥርዓት በመሆኑ ነው። ጋብቻ በቤተ ክርስቲያን ሲፈጸም ምሥጢርነት አለው። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም "... ይህ ምሥጢር ታላቅ ነው" ማለቱ ይህንኑ ያረጋግጥልናል።
#የተክሊል አፈጻጸም
እንደ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ /ሥርዓት/ ተክሊል ከሥርዓተ ቅዳሴና ከቅዱስ ቁርባን ጋር ተያይዞ የሚፈጸም ምሥጢር ነው። እንጂ ብቻውን አይፈጸምም። ጸሎተ ተክሊል ተደርሶ ቅዱስ ቁርባን መቀበል ከቀረ ግን ተክሊሉ ፍጹም አይደለምና ጋብቻው አይጸናም።
#ሥርዓተ ተክሊል ለማን ይፈጸማል?
ተክሊል የሚፈጸመው ንጽሕናዋን ጠብቃ ከወንድ እርቃ ለኖረች ጥብቅ ልጃገረድ ወይም በሥጋ ድንግልናዋን ለጠበቀች በተግባር ዝሙት ላልፈጸመች ኦርቶዶክሳዊ ሴት ነው። ሴትን በምንጣፍ ተገናኝቶ የማያውቅ ንጽሕናውን ጠብቆ ልኖር ኦርቶዶክሳዊ ወንድ ብቻ የሚፈጸም የጋብቻ መፈጸሚያ አይነት ነው። በአጠቃላይ ተክሊል ከሥጋዊ ድንግል ጋር አብሮ የሚሄድ ምሥጢር መሆኑን ቤተ ክርስቲያን የሥርዓት መጽሐፍቶች ሁሉ ተባብረው የሚመሰክሩት ጉዳይ ነው። ለምሳሌ ፍትሃ ነገስት እንዲህ ይላል ፦ "ይህ ተክሊል በጋብቻ ጊዜ ለድንግል ወንድና ለድንግል ሴት ይገባል።" ፍትሃ ነገስት 24:906 ከላይ ያነሳነው ሥርዓት ግን በደንብ ካልተብራራ ተክሊልን በተመለከተ የሚነሱትን ጥያቄዎች ከምንጫቸው ማድረግ የሚችል አይሆንም። ሰለዚህ በዚህ ምሥጢር ዙሪያ ለሚነሱት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት እንድንችል ድንግልና እንደቤቱ ክርስቲያናችን አስተምህሮ እንዴት ይታያላል /ይብራራል/ የሚለውን በደንብ መመልከት ይገባል።

#ድንግልና ምንድን ነው?
ድንግልና የሚለው ቃል ተደነገለ ተጠበቀ ከሚለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ትርጓሜውም መጠበቅ ማለት ነው። ድንግልና እንደ ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ንዑስ ሕዋስን /Hymen/ ለመግለጽ ብቻ ሳይሆን የንጽሕና አኗኗር ለማስረዳት አንድ ድርጊት መፈጸም ወይም አለመፈጸሙን ለማመልከት አገልግሎት ላይ የሚውል ቃል መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል።
ሰለዚህም አንዲት ኦርቶዶክሳዊት ሴት ሥጋዊ የሆነው የድንግል ማሕተም ስላልፈረሰባት ብቻ ሥርዓተ ተክሊል መፈጸም ትችላለች ሌላኛዋ ኦርቶዶክሳዊት ደግሞ ሥጋዊ የድንግልናዋ ማሕተም ሰለፈረሰ ብቻ ተክሊል አይገባትም ማለት አይደለም። በቅድሚያ እዚህ ላይ ያለውን ውዥንብር መደንብ ለማጥራት በሴቶች ተፈጥሮ ውስጥ የሚገኘውን የድንግልና አይነቶችን ማየት ይጠቅማል።
#የሴቶች ድንግልና ተፈጥሮ ዓይነቶች
ማኅተመ ድንግልና ሴት ከወንድ ጋር ሩካቤ አድርጋ አለማወቋን የሚያስረዳ የሥራዋ መገለጫ የአኗኗሯ መታወቂያ ልዩ የተፈጥሮ ምልክትና የድንግልናዊ ኑሮዋ ዘውድ ነው። ይህ ተፈጥሮዊ ማኅተም በሴቶች አፈ ማኅፀን ቀለበት በሚመስል ስስ ሥጋነት በጉልህ ይታወቃል። ይህ ማለት ግን ሩካቤና ሰስሎተ ድንግልና /የድንግልና መወገድ/ የተለያዩና
ራሳቸውን የቻሉ ተግባራት መሆናቸውን መገንዘብ ይኖርብናል። አንዲት ሴት ማኅተመ ድንግልና ስላላት ብቻ " ሩካቤ አድርጋ አታውቅም" " ወይም ሩካቤ ስላደረች ማኅተመ ድንግልና ሊኖራት አይችልም። ብሎ ድምዳሜ ላይ መድረስ አለመቻሉን እንረዳለን። በዚህም የተነሳ የድንግልና አይነቶችን ከተክሊል ጋር እያዛመዱ መመልከት ያስፈልጋል። ለምሳሌ ወንዶች እንደ ሴቶች ተጨባጭና ጉልህ የድንግልና ምልክት ስለሌላቸው ከሴት ጋር ሩካቤ ፈጽመው የማያውቁ ሆነው ሳለ ደናግል አይደሉም ማለት አይቻልም። እንደዚሁ ሁሉ ሩካቤን ፈጽመው የማያውቁ ሴቶች የድንግልና ማኅተም ስለሌላቸው ብቻ ደናግላን
ከመባል አይከለከሉም። በሌላ አቅጣጫ ስንመለከት ወንዶች ሩካቤ ፈጽመው ሳለ እንደ ሴቶች የሚገሠሥ ማኅተመ ድንግልና ስለሌላቸው ድንግልናቸውን አልፈረሰም እንደማይባል ሁሉ ሴቶች ሩካቤ ሥጋ እየፈጸሙ በልዩ ልዩ ምክንያት ማኅተመ ድንግልናቸውን ባይገሠሥም መደበኛ ሩካቤ እስከ ፈጽሙ ድረስ ደናግል ሊባሉ አይችሉም። ለዚህም ነው ሰለድንግልና አይነቶች ማውራት አስፈላጊ ሁኖ የተገኘው ፦
#የድንግልና ዓይነት
የድንግልና መለያ ወይም ስስ የክብር ንጽሕና ሽፋን /Hymen/ ዓይነታቸው አራት ሲሆኑ በሁሉም ሴቶች ላይ የሚኖረው ዓይነት ምንም እንኳን በተፈጥሮ ተወስኖ የተፈጠረ ቢሆንም ግን ከግብረ ሥጋ ግንኙነት ውጭ ድንግልና የሚጠፋባቸው በርካታ ምክንያቶች ይኖራሉ። ይህም ከሴቶች የድንግልና ተፈጥሮ አንጻር ነው።
#አንደኛ ደረጃ_የድንግልና ማኅተም /Hymen/ ምልክቶች ፦ ይህ ድንግልና አይነት ያላቸው ሴቶች ንዑስ ሕዋስ የድንግልና ማኅተም ምልክቱ የሌላቸው ሲሆኑ እነዚህ ምንም እንኳን ከአጠቃላዩ ሴቶች ሲታይ ቁጥራቸው አናሳና አንዳንድ መረጃዎች እንደ ሚጠቁሙት ከሦስት እስከ አምስት በመቶ የማይበልጡ ቢሆኑም የዚህ አይነት ተፈጥሮ ባለ ድርሻ የሆኑ እህቶች የሠርጋቸውን የመጀመሪያውን የግብረ ሥጋ ግንኙነት ሲዳርጉ ምናሴም እንኳን ሕመም ቢሰማቸውም እንደሌሎቹ የድንግልና አይነቶች ያለ መድማታቸው አይነቱን የተለየ ያደርገዋል። ይህ አይነቱ ድንግልና ያላቸው ወጣት ሴቶች ምንም እንኳን ከጋብቻ በፊት የግብረ ሥጋ ግንኙነት ፈጽመው የማያውቁ ራሳቸውን በቅድስናና በንጽሕና ጠብቀው የኖሩ ቢሆኑም ሆኖም ግን በጋብቻቸው ምሽት የመጀመሪያውን የግብረ ሥጋ ግንኙነት ሲፈጽሙ ደም ባለመታየቱ በባላቸው ዘንድ ተአማኒነት የሚያጡበት አሳዛኝ አጋጣሚ የሚከሰትበት አጋጣሚ አለ።
#ሁለተኛ ደረጃ የድንግልና ዓይነት፦ይህ የድንግልና አይነት በተፈጥሮ ያላቸው ሴቶች የድንግልና መለያቸው በጣም ስስነት ያለው ሲሆን እነዚህ አይነት ሴቶች በቁጥር ከአጠቃላዩ ሴቶች ከሃያ አምስት በመቶ ያላነሱ ናቸው። ይህ የድንግልና አይነት ከግብረ ሥጋ ግንኙነት ውጭ በተለያዩ የጥንቃቄ ጉድለቶች ሊወገድ የሚችልባቸውም አጋጣሚዎችም አሉ። በዚህ የድንግልና አይነት የሚኖሩ እህቶች ከባድ በሆነ አካላዊ እንቅስቃሴ ጥንቃቄ በጎደለው አለባበስ የተነሳ ሊወገድ ይችላል። እነዚህ እህቶች በሩካቤ ሥጋ ግንኙነት በዝሙት ተግባር ሳይገኙ ድንግልናቸውን ሊያጡት ይችላሉ።
#ሦስተኛው ደረጃ የድንግልና ዓይነት፦ ይህ የድንግልና ዓይነት መካከለኛ ደረጃ ውፍረት ያለው ሲሆን የድንግልና መለያ ምልክት በአብዛኛው ሴቶች ላይ ማለትም ከአጠቃላዩ ድንግልና ካላቸው ወጣት ሴቶች ከግማሽ በላይ በሚሆኑት ላይ የሚገኝ የድንግልና ማኅተም አይነት ነው። ይህ የድንግልና አይነት እስከ አሁን ካየናቸው የድንግልና ማኅተሞች በጥንካሬና በውፍረት የተሻለ ከመሆኑ በላይ ከግብረ ሥጋ ግንኙነት በስተቀር በሌሎች የጥንቃቄ ጉድለቶች ማለትም ጥንቃቄ በጎደለው ስፖርትና በመሳሰሉት የመወገድ ዕድሉ በጣም ዝቀተኛ ነው።
#አራተኛ ደረጃ የድንግልና ዓይነት ፦ ይህ የድንግልና አይነቶች ጽኑ የሚባል ነው። ከግብረ ሥጋ ግንኙነት ውጭ በሌላ በምንድን አይነት መንገድ የሚፈርስ የሚወገድ አይደለም። ተክሊል የሚገባት ሩካቤ ሥጋ ግንኙነት ፈጽማ ድንግልናዋ ላልፈረሰባት ሴት አይደለም። ይቺ ሴት ምንም እንኳን የሥጋ ድንግልናዋ ቢኖርም የዝሙት ተግባርን ፈጽማለችና ተክሊል አይገባትም። በተለይ አራተኛው የድንግልና አይነት ላይ የሚገኙ ጽን የድንግልና ማኅተም ያላቸው ሴቶች በመጀመሪያው የሩካቤ ሥጋ ግንኙነት የድንግልና ማኅተማቸው ላይወገድ ይችላል። ይህንን ሩካቤ ሥጋ ግንኙነት የፈጸሙት ከጋብቻ ውጭ ከሆነ ዝሙት ነውና የድንግልና ማኅተም አለኝ ተ
#የገነት ወግ

ከምጽሐት በኃላ ገነት ውስጥ ነው። ቸርነቱ የበዛ መዐቱ የራቀ እግዚአብሔር አምላክ ከሦስት ወጣቶች ሦስት ነገሮች አግኝቶባቸው ገነት አስገባቸው። መቼም እግዚአብሔር አምላክ መንግሥተ ሰማያትን የምታክል ቦታ በጥርኝ ውኃ የሚሸጥ ሞኝ ነጋዴን ይመስላል። #ማቴ10÷41

#ከወጣቶቹ የተገኘባቸው መልካም ነገርም እነኸህ ነበሩ። በአንዱ እምነት በአንዱ ማስተዋል በአንዱ የዋሕነት ነው። ከዚህ የተረፈ የጠለቀ መንፈሳዊ ትጋት የላቸውም በሳምንት አንድ ቀን እሁድ ግጥሚያና ትሬሊንግ ከሌለባቸው ያስቀድሳሉ ከአጽዋማት ሦስቱን መርጠው እንነገሩ ይጦማሉ በቃ ለገነት ዜግነት ያሳጫቸው ይህው ጥቂቱ ጥረታቸው እእና ብዙሁ የእግዚአብሔር ቸርነት ነው።

#ከገነት በአንዱ ዕለት ታድያ አንደኛው ወጣት እንዲ ይላል " እንተ ገነት ገነት እያልን ስንናፍቃት የነበረችሁ ይችሁ ናትን? እንዴ ጠዋት ቅዳሴ ማታ ውዳሴ እረፍቱ ቆይ መቼ ነው ?
ሌላኛው ወጣት ቀበል አድርጎ ታገስ እስቲ በዚህኮ እረፍቱ ምስጋና ምስጋናው እረፍት ሆኖ ነው የሚኖረው ቢሆንም ግን ጥቂት ማረፋችን አይቀርም ሲል ለማጽናናት ሞከረ
ሦስተኛው ወጣት ግን የሱ ጭንቀት ሌላ እንደሆነ ነገራቸው እንዲህ ሲል እረፍት ብቻውን ምን ያደርጋል? በእረፍት ጊዜያችን ሻምፒዮን ስሊግና ላሊጋን የመሳሰሉት የእግር ኳስ ውድድሮችን መከታተል ካልቻልን

የመጀመሪያው ወጣት ጣልቃ ገብቶ አንተ ደሞ እሱንም ለማየትኮ ቅድሚያ የዕረፍት ጊዜ ሊኖረን ይገባል ማታ ውዳሴ ቀን ቅዳሴ ይህው ከገባን ጀምሮ ስንት ሰንበታት አለፉ በሰንበት እንኳ አናርፍም እኮ አለ ምርር ብሎ

#ለምን ካልሆነ እዚሁ ገነት ውስጥ wi fi እንዲገባ ና ለእያንዳንዳችን እስማርት ስልኮች እንዲታደሉን አናደርግም ከዛ በቃ ላሊጋ በል ሻምፒዮን ስሊግ በል በቃ ሁሉ በእጃችን ሆነ ማለት ነው በተጨማሪም ማኅበራዊ ድኅረ ገጾችን ከፍተን ምድር ካሉ ዘመዶቻችን ጋር ያለ ገደብ እንገናኝ ከናፍቆታቸውም እንገላገላለን አይመስላችሁም? ሲል ሀሳብ አቀረበ

ሁለተኛው ወጣት ድንገት ሳይታሰብ ገብቶ አይመስለንም ሲል አንቧረቀበት ጭራሽ ገነት ውስጥ ዋይ ፋይ ? ጭራሽ ገነት ውስጥ እስማርት ስልክ ? ገነትን ገነት ያሰኙት እኮ የነዚህ ነገር አለመኖር ነው አለዚያማ ከምድር በምን ተሻለ ሆሆሆሆ

#ሦስተኛው ወጣት ፈጠን ብሎ ምን ችግር አለው በምድር ሳለን ትዝ አይላችሁም ካህኑ በስማርት ስልክ ተደግፎ ተንስዑ ሲል ዲያቆኑት ቢሆን እያንዳንዱን የመቅደስ እንቅስቃሴ እየቀረጸ እዛው ማኅበራዊ ድኅረ ገጾች ላይ ሲለቅ አላያችሁም? ስለዚህ ብዙ ችግር ያለው አይመስለኝም አለ

እናንተ ሰዎች ያ በምድር ነው ሆኖም ትክክል ነው ማለት አይደለም።ምክንያቱም የምድሪቱ ቤተ ክርስቲያን የሰማያዊቱ ለዚህች ቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ናትና። (camera man) ቀራጭነትና ድቁና ፈሪሳዊነትና ክህነት አብረው አይሄዱም። ግማሽ መላጣ ግማሽ ጎፈሬ ብርሃንና ጽልመት እንዴት አንድ ይሆናሉ? ብንችል ለምድር ሰዎች እንጸልይላቸው እንዴት የነርሱን ስዕተት እዚህ እንደግማለን።

#አንዱ ወጣት የሆነ መላ ብልጭ ያለለት በሚመስል ሆናቴ ፍክት ብሎ ቆይ ከዚህ ሁሉ ጭንቅ ለምን ከገነት አንወጣም ?
ሌላኛው ወጣት ከዛስ ? ሲዖል ጥገኝነት እንጠይቅ?
አንተ ባክህ አቀልድ
በቃ ማለቴ ወደ ቀደመ ኑሯችን ወደ ምድር መልሱን ለምን አንላቸውም ???
ይቻላል እንዴ ? ገነትኮ ካገኙ ማጣት ከገቡ መውጣት የለም ማነው የሚያሶጣን?
ቀላልኮነው ለምን ገነት ውስጥ ያልተፈቀደ ነገር ለምን አናደርግም ከዛ በቃ በራሳቸው ጊዜ ያስወጡናል
አረ ባካችሁ ጓደኞቼ ምን ሆናችዋል? አዳምና ሔዋን በገነት ያልተፈቀደውን አድርገው ከገነት ሲባረሩ የምትገለባበጥ የኪሩቤል ሰይፍም ተመዞባቸው ነበር በኛ ደግሞ ይወድቅብን ይሆናል ማን ያውቃል ።
ማለት ገነት ሰይፍ አለ ? ታድያ ሰይፍ ካለ wifi ቢኖር ምን ችግር አለ? ቢያን አመስግነን ቀድሰን አወድሰን ስንጨርስ ትንሽ እንደበርበት ነበር እኮ ።

#ይህን ሲነጋገሩ ከቀደሙት ደጋግ አባቶች አንዱ በለወሳስ የምስጋና ውዳሴ እያቀረበ ወደ ወደ መንበረ መንግሥት ሲጓዝ አያቸው ከንግግራቸውም ያሉበት ቦታ እንዳልተመቻቸውና መውጣት እንደሚሹ ተረዳ መንገዱንም ገታ አድርጎ ወደ ወጣቶቹ ተጠግቶ ሰላምታ ሰጣቸው።
ከግርማ ሞገሱና ከንግግሩ ለዛ ተደመሙ የተነጋገሩትን አንዲቱንም ቃል ባልሰማን ብለውም ተመኙ። ያ ሰው ግን ያለ ዕውቀት እንደተናገሩ ያውቃልና እያለዛዘበ ጠየቃቸው ልጆች ምን ሆናችኋል የምረዳችሁ ነገር አለ አላቸው እነርሱ ግን ለማስቀየስ ተጠቃቀሱና አይ የለም አሉት በጋራ። መልካም ብሎ ጥሏቸው ጉዞዎን ሊቀጥል ሲል ግን አንደኛው ወጣት ግን አንተ ማነህ? ሲል የገነት ጠባቂ ጥጦስን የጠየቀውን ጥያቄ አቀረበለት አብርሃም ነህን አለው ያም ሰው ዝም አለ እሽ ሙሴ ነህን አለው ያ ሰው አለመለሰለትም በቃ ቅዱስ ጳውሎስ ነህን መሆን አለብህ አለው በጥያቄው ሳይሰለች ነኝም አይደለውምም ሳይለው እርሱ ይቆየኝ

ወጣትነት አስቸጋሪ ነው እኔም ወጣት ሳለው ብዙ ጠባያት እየተፈራረቁ አስቸግረውኝ ነበር ግን በእግዚአብሔር ቸርነት በእናቱ አማላጅነት ሁሉም አልፌያቸው እዚህ ደርሻለው ከፈለጋችሁ ከልምዴ በማካፈል ልረዳችሁ እችላለሁ አላቸው። ካልሆነ ግን በሉ በደህና ዋሉ ብሎ ፊቱን አዙሮ መንገዱን ቀጠለ በእውኑ ግን ጥሏቸው ሊሄድ ልቡ አልወደደም ነበር

#ቢያንስ ከልምዱና ከዕውቀቱ ሊያካፍለን ይችላል በገነት ብዙ ስለቆየ መግቢያ መውጫውንም ሊነግረን ይችላል ለምን ሀሳባችንን አንነግረውም ተባባሉ በለወሳስ ቀስ ብለው። ከዛም አንደኛው ፈጠን ብሎ አባት አባቴ አንዴ ቆይ ብሎ ከኋላ ከተል እያለ ተጣራ አንድ ጊዜ አባቴ ሁለት ደቂቃ ይኖሮታል እባካችሁ ለምስጋና ወደ መንበረ መንግሥት እየሄድኩ ነው ከፈለጋችሁ ግን አብራችሁኝ እየሄዳችሁ የፈለጋችሁትን ልትጠይቁኝ ትችላላችሁ አላቸው። እሺ ይሁን አብረኖት እንሄዳለን ብቻ እርሶ መፍትኤ ብቻ ይስጡን መፍትኤስ ከእግዚአብሔር ነው ግን ምን ገጠማችሁ ?

አንደኛው እጆቹን እያፍተለተለ በእግሮቹም ወደፊት አብሯቸው እየተራመደ ይህውሎት አባ እኛ የገነት ኑሮ ሰልችቶናል ወደ ቀደመ ቦታችን ወደ መሬት መመለስ እስፈልጋለን አለ ሁለቱ ሀሳቡን በመደገፍ በአውንታ ጭንቅላታቸውን አነቃነቁ ያ ባለ ግርማ ሞገስ ሰው ግን ፈገግ አለና ለአህያ ማር አይጥማት አሉ ሲል ተረተባቸው ቀጥሎም እርሷስ ሳያቀምሷት ነው አይጥማትም እያሉ የሚያሟት እናተ ቀምሳችሁ ሳለ እንዴት ሳይጥማችሁ ቀረ ለመሆኑ ገነት ምን ጎደለ?

#አንዱ ቀበል አድርጎ ሻምፒዮ ሲሊግ የለ ፤ ላሊጋ የለ ፤ facebook የለ ፤ instageram የለ ፤ ጠዋት ቅዳሴ ማታ ውዳሴ ይሰለቻልኮ አባ

አይ ልጆቼ ይህ ነው ጭንቀታችሁ ይህን እናንተ ያያችሁትን እኮ ብዙዎች ሊያዮት ወደው ሊያዮት አልቻሉም እስራኤል የሰማይ መና ሰለችን ሥጋ አማረን ቢሉ መና ("ና"ይላላ) ሆነው ቀሩ። የተመኙት ሥጋ ተሰጣቸው ከአፋቸው ከተው እንደቀመሱትም ሁሉም እረግፈው ሞቱ ቦታዋም እስከዛሬ ድረስ የምኞት መቃብር ተብላ እየተጠራች ነው። ምነው ከሕይወት ይልቅ የምኞት መቃብርን ሻታችሁ ከመና ይልቅ መና መሆንን ወደደዳችሁ?