ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
929 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
#የገነት ወግ

ከምጽሐት በኃላ ገነት ውስጥ ነው። ቸርነቱ የበዛ መዐቱ የራቀ እግዚአብሔር አምላክ ከሦስት ወጣቶች ሦስት ነገሮች አግኝቶባቸው ገነት አስገባቸው። መቼም እግዚአብሔር አምላክ መንግሥተ ሰማያትን የምታክል ቦታ በጥርኝ ውኃ የሚሸጥ ሞኝ ነጋዴን ይመስላል። #ማቴ10÷41

#ከወጣቶቹ የተገኘባቸው መልካም ነገርም እነኸህ ነበሩ። በአንዱ እምነት በአንዱ ማስተዋል በአንዱ የዋሕነት ነው። ከዚህ የተረፈ የጠለቀ መንፈሳዊ ትጋት የላቸውም በሳምንት አንድ ቀን እሁድ ግጥሚያና ትሬሊንግ ከሌለባቸው ያስቀድሳሉ ከአጽዋማት ሦስቱን መርጠው እንነገሩ ይጦማሉ በቃ ለገነት ዜግነት ያሳጫቸው ይህው ጥቂቱ ጥረታቸው እእና ብዙሁ የእግዚአብሔር ቸርነት ነው።

#ከገነት በአንዱ ዕለት ታድያ አንደኛው ወጣት እንዲ ይላል " እንተ ገነት ገነት እያልን ስንናፍቃት የነበረችሁ ይችሁ ናትን? እንዴ ጠዋት ቅዳሴ ማታ ውዳሴ እረፍቱ ቆይ መቼ ነው ?
ሌላኛው ወጣት ቀበል አድርጎ ታገስ እስቲ በዚህኮ እረፍቱ ምስጋና ምስጋናው እረፍት ሆኖ ነው የሚኖረው ቢሆንም ግን ጥቂት ማረፋችን አይቀርም ሲል ለማጽናናት ሞከረ
ሦስተኛው ወጣት ግን የሱ ጭንቀት ሌላ እንደሆነ ነገራቸው እንዲህ ሲል እረፍት ብቻውን ምን ያደርጋል? በእረፍት ጊዜያችን ሻምፒዮን ስሊግና ላሊጋን የመሳሰሉት የእግር ኳስ ውድድሮችን መከታተል ካልቻልን

የመጀመሪያው ወጣት ጣልቃ ገብቶ አንተ ደሞ እሱንም ለማየትኮ ቅድሚያ የዕረፍት ጊዜ ሊኖረን ይገባል ማታ ውዳሴ ቀን ቅዳሴ ይህው ከገባን ጀምሮ ስንት ሰንበታት አለፉ በሰንበት እንኳ አናርፍም እኮ አለ ምርር ብሎ

#ለምን ካልሆነ እዚሁ ገነት ውስጥ wi fi እንዲገባ ና ለእያንዳንዳችን እስማርት ስልኮች እንዲታደሉን አናደርግም ከዛ በቃ ላሊጋ በል ሻምፒዮን ስሊግ በል በቃ ሁሉ በእጃችን ሆነ ማለት ነው በተጨማሪም ማኅበራዊ ድኅረ ገጾችን ከፍተን ምድር ካሉ ዘመዶቻችን ጋር ያለ ገደብ እንገናኝ ከናፍቆታቸውም እንገላገላለን አይመስላችሁም? ሲል ሀሳብ አቀረበ

ሁለተኛው ወጣት ድንገት ሳይታሰብ ገብቶ አይመስለንም ሲል አንቧረቀበት ጭራሽ ገነት ውስጥ ዋይ ፋይ ? ጭራሽ ገነት ውስጥ እስማርት ስልክ ? ገነትን ገነት ያሰኙት እኮ የነዚህ ነገር አለመኖር ነው አለዚያማ ከምድር በምን ተሻለ ሆሆሆሆ

#ሦስተኛው ወጣት ፈጠን ብሎ ምን ችግር አለው በምድር ሳለን ትዝ አይላችሁም ካህኑ በስማርት ስልክ ተደግፎ ተንስዑ ሲል ዲያቆኑት ቢሆን እያንዳንዱን የመቅደስ እንቅስቃሴ እየቀረጸ እዛው ማኅበራዊ ድኅረ ገጾች ላይ ሲለቅ አላያችሁም? ስለዚህ ብዙ ችግር ያለው አይመስለኝም አለ

እናንተ ሰዎች ያ በምድር ነው ሆኖም ትክክል ነው ማለት አይደለም።ምክንያቱም የምድሪቱ ቤተ ክርስቲያን የሰማያዊቱ ለዚህች ቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ናትና። (camera man) ቀራጭነትና ድቁና ፈሪሳዊነትና ክህነት አብረው አይሄዱም። ግማሽ መላጣ ግማሽ ጎፈሬ ብርሃንና ጽልመት እንዴት አንድ ይሆናሉ? ብንችል ለምድር ሰዎች እንጸልይላቸው እንዴት የነርሱን ስዕተት እዚህ እንደግማለን።

#አንዱ ወጣት የሆነ መላ ብልጭ ያለለት በሚመስል ሆናቴ ፍክት ብሎ ቆይ ከዚህ ሁሉ ጭንቅ ለምን ከገነት አንወጣም ?
ሌላኛው ወጣት ከዛስ ? ሲዖል ጥገኝነት እንጠይቅ?
አንተ ባክህ አቀልድ
በቃ ማለቴ ወደ ቀደመ ኑሯችን ወደ ምድር መልሱን ለምን አንላቸውም ???
ይቻላል እንዴ ? ገነትኮ ካገኙ ማጣት ከገቡ መውጣት የለም ማነው የሚያሶጣን?
ቀላልኮነው ለምን ገነት ውስጥ ያልተፈቀደ ነገር ለምን አናደርግም ከዛ በቃ በራሳቸው ጊዜ ያስወጡናል
አረ ባካችሁ ጓደኞቼ ምን ሆናችዋል? አዳምና ሔዋን በገነት ያልተፈቀደውን አድርገው ከገነት ሲባረሩ የምትገለባበጥ የኪሩቤል ሰይፍም ተመዞባቸው ነበር በኛ ደግሞ ይወድቅብን ይሆናል ማን ያውቃል ።
ማለት ገነት ሰይፍ አለ ? ታድያ ሰይፍ ካለ wifi ቢኖር ምን ችግር አለ? ቢያን አመስግነን ቀድሰን አወድሰን ስንጨርስ ትንሽ እንደበርበት ነበር እኮ ።

#ይህን ሲነጋገሩ ከቀደሙት ደጋግ አባቶች አንዱ በለወሳስ የምስጋና ውዳሴ እያቀረበ ወደ ወደ መንበረ መንግሥት ሲጓዝ አያቸው ከንግግራቸውም ያሉበት ቦታ እንዳልተመቻቸውና መውጣት እንደሚሹ ተረዳ መንገዱንም ገታ አድርጎ ወደ ወጣቶቹ ተጠግቶ ሰላምታ ሰጣቸው።
ከግርማ ሞገሱና ከንግግሩ ለዛ ተደመሙ የተነጋገሩትን አንዲቱንም ቃል ባልሰማን ብለውም ተመኙ። ያ ሰው ግን ያለ ዕውቀት እንደተናገሩ ያውቃልና እያለዛዘበ ጠየቃቸው ልጆች ምን ሆናችኋል የምረዳችሁ ነገር አለ አላቸው እነርሱ ግን ለማስቀየስ ተጠቃቀሱና አይ የለም አሉት በጋራ። መልካም ብሎ ጥሏቸው ጉዞዎን ሊቀጥል ሲል ግን አንደኛው ወጣት ግን አንተ ማነህ? ሲል የገነት ጠባቂ ጥጦስን የጠየቀውን ጥያቄ አቀረበለት አብርሃም ነህን አለው ያም ሰው ዝም አለ እሽ ሙሴ ነህን አለው ያ ሰው አለመለሰለትም በቃ ቅዱስ ጳውሎስ ነህን መሆን አለብህ አለው በጥያቄው ሳይሰለች ነኝም አይደለውምም ሳይለው እርሱ ይቆየኝ

ወጣትነት አስቸጋሪ ነው እኔም ወጣት ሳለው ብዙ ጠባያት እየተፈራረቁ አስቸግረውኝ ነበር ግን በእግዚአብሔር ቸርነት በእናቱ አማላጅነት ሁሉም አልፌያቸው እዚህ ደርሻለው ከፈለጋችሁ ከልምዴ በማካፈል ልረዳችሁ እችላለሁ አላቸው። ካልሆነ ግን በሉ በደህና ዋሉ ብሎ ፊቱን አዙሮ መንገዱን ቀጠለ በእውኑ ግን ጥሏቸው ሊሄድ ልቡ አልወደደም ነበር

#ቢያንስ ከልምዱና ከዕውቀቱ ሊያካፍለን ይችላል በገነት ብዙ ስለቆየ መግቢያ መውጫውንም ሊነግረን ይችላል ለምን ሀሳባችንን አንነግረውም ተባባሉ በለወሳስ ቀስ ብለው። ከዛም አንደኛው ፈጠን ብሎ አባት አባቴ አንዴ ቆይ ብሎ ከኋላ ከተል እያለ ተጣራ አንድ ጊዜ አባቴ ሁለት ደቂቃ ይኖሮታል እባካችሁ ለምስጋና ወደ መንበረ መንግሥት እየሄድኩ ነው ከፈለጋችሁ ግን አብራችሁኝ እየሄዳችሁ የፈለጋችሁትን ልትጠይቁኝ ትችላላችሁ አላቸው። እሺ ይሁን አብረኖት እንሄዳለን ብቻ እርሶ መፍትኤ ብቻ ይስጡን መፍትኤስ ከእግዚአብሔር ነው ግን ምን ገጠማችሁ ?

አንደኛው እጆቹን እያፍተለተለ በእግሮቹም ወደፊት አብሯቸው እየተራመደ ይህውሎት አባ እኛ የገነት ኑሮ ሰልችቶናል ወደ ቀደመ ቦታችን ወደ መሬት መመለስ እስፈልጋለን አለ ሁለቱ ሀሳቡን በመደገፍ በአውንታ ጭንቅላታቸውን አነቃነቁ ያ ባለ ግርማ ሞገስ ሰው ግን ፈገግ አለና ለአህያ ማር አይጥማት አሉ ሲል ተረተባቸው ቀጥሎም እርሷስ ሳያቀምሷት ነው አይጥማትም እያሉ የሚያሟት እናተ ቀምሳችሁ ሳለ እንዴት ሳይጥማችሁ ቀረ ለመሆኑ ገነት ምን ጎደለ?

#አንዱ ቀበል አድርጎ ሻምፒዮ ሲሊግ የለ ፤ ላሊጋ የለ ፤ facebook የለ ፤ instageram የለ ፤ ጠዋት ቅዳሴ ማታ ውዳሴ ይሰለቻልኮ አባ

አይ ልጆቼ ይህ ነው ጭንቀታችሁ ይህን እናንተ ያያችሁትን እኮ ብዙዎች ሊያዮት ወደው ሊያዮት አልቻሉም እስራኤል የሰማይ መና ሰለችን ሥጋ አማረን ቢሉ መና ("ና"ይላላ) ሆነው ቀሩ። የተመኙት ሥጋ ተሰጣቸው ከአፋቸው ከተው እንደቀመሱትም ሁሉም እረግፈው ሞቱ ቦታዋም እስከዛሬ ድረስ የምኞት መቃብር ተብላ እየተጠራች ነው። ምነው ከሕይወት ይልቅ የምኞት መቃብርን ሻታችሁ ከመና ይልቅ መና መሆንን ወደደዳችሁ?