ዐውደ ምሕረት
3.68K subscribers
929 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
📢ዓውደ #ምህረት🎤
ሳምንታዊው #አሸላሚ ከኮርሱ #የተወጣጡ ጥያቄዎቻችን

1/ #ድኅነት በቅጽፈት ሳይሆን በሂደት የሚፈጸም መሆኑን የሚያስረዱ ጥቅሶችን ከትምህርቱ የሰማችሁትን ቢያንስ 3 ቱን ጥቀሱ?

2/#መፍቀሬ ጥበብ ቅዱስ ሰለሞን በመጽሐፈ መክብብ 4÷10 ላይ ያልሞተ ውሻ ከሞተ እንበሳ ይሸሻላል ብሎ በውሻና በአንበሳ የመሰላቸው ማንን ነው?

3/ #እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መቼ ተወለደች ?በየት ቦታ?

4/#የቅዱሳን መላእክት ከተማ ስንት ናቸው?ስማቸውስ?


እስከ ዛሬ ሳምንት መልሶቻችሁን በ @YeawedMeherte @YeawedMeherte ላይ መላክ የምችሉ መሆኑን እየገለጽን ለተሳታፊዎችና ለትክክለኛ መላሾቻችን ማበረታቻ ልዮ ልዮ መጻሕፍትን እንደመሸንሸልም በደስታ እንገልጻለን

መሳሳት አለ ማስተዋል እንጂ አለ ማወቅ አይደለም

ዓውደ ምህረት የእናንተ
🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤
📢 @AwediMeherit📢
📢 @AwediMeherit📢
📢📢📢📢📢📢📢📢
#እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም_መድኃኒታችን_ናት

የድኅነት ምክንያት በራሱ መድኃት ነው፡፡ የመድኃቱ መገኛ መሆን በራሱም መድኃኒት ያሰኘዋል፡፡ አዳኝ እግዚአብሔር መሆኑ እሙን ነው፡፡ እግዚአብሔር ደግሞ በምክኒያትም አለምክኒያትም ያድናል፡፡ ይህ ማለት ሌላ የማዳኛ መንገድ ተጠቅሞ ሊያድን ይችላል፡፡ ሳይጠቀምም ሊያድን ይችላል፡፡ ቅዱሳኑን ተጠቅሞ ሊያድን ይችላል፣ በጠበል ሊያድን ይችላል አልያም ሌላ መንገድ ተጠቅሞ ሊያድን ይችላል፡፡ በተቃራኒው ደግሞ ምንም አይነት የማዳኛ መንገድ ሳይጠቀም ሊያድን ይችላል፡፡ ለምሳሌ ዮሐ 5፡1-9 ላይ ስንመለከት በቤተ ሳይዳ 38 ዓመት ሙሉ አልጋው ላይ ተኝቶ የነበረውን ሰው ያዳነው ምንም ምክኒያት ሳይጠቀም ነው፡፡ ‹‹ልትድን ትወዳለህን›› አለው ከዛም ‹‹አልጋህን ተሸክመህ ሂድ፡፡›› አለው፡፡ በዮሐ 9፡1-7 በዚህ ክፍል ስንመለከት ደግሞ ጌታችን የእውሩን ዐይን ያበራለት በጠበል ሄዶ እንዲጠመቅ በማዘዝ ነበር፡፡ አዳኙ እግዚአብሔር ነው፡፡ ምክንያተ ድኅነቱ ደግሞ ጠበል፡፡ ጠበሉ ምክንያተ ድኂን በመሆኑ መድኃኒት ነው፡፡
መዝ 3፡8 ‹‹ማዳን የእግዚአብሔር ነው፡፡›› ይላል፡፡ በመሳ 3፡9 ላይ ደግሞ ‹‹የእስራኤል ልጆች ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፡፡ እግዚአብሔርም የሚያድናቸውን የቄኔዝን ልጅ ጎቶንያልን አዳኝ አድርጎ አስነሳላቸው፡፡›› እነዚህ ሁለት ቃላት እርስ በራሳቸው የሚገጩ ይመስላሉ፡፡ ነገር ግን በፍጹም አይጋጩም፡፡ ማዳን የእግዚአብሔር ቢሆንም እንዲሁም አዳኝ ተብሎ ሊጠራ የሚገባው አርሱ ሆኖ ሳለ ስለምን ጎቶንያል አዳኝ (መዳኒት) ተብሎ ተጠራ ቢሉ ምክንያቱም እስራኤልን እግዚአብሔር ያዳናቸው ጎቶንያልን ምክንያት አድርጎ ስለሆነ ነው፡፡ ስለዚህ ጎቶንያል ምክንያተ ድኂን ስለሆነ አዳኝ ተብሎ ተጠርቷል፡፡
ከላይ ባነሳናቸው ምሳሌዎች መሰረት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም የሰው ልጆች የድኅነት መፈጸሚያ ምክንያተ ድኂን በመሆኑዋ መድኃኒት ትባላለች፡፡ ለዚህ ነው በተዓምረ ማርያም መቅድም ላይ ‹‹መድኃኒታችሁ ናት›› ተብላ የተጠራችው፡፡ ለአዳም የተገባት ቃል ኪዳን ዘመኑ ሲፈጸም እግዚአብሔር ሰው ሆኖ እንደሚያድነው ነው፡፡ ገላ 4፡4 ይህ የመዳን ቃል ኪዳን እንዲፈጸም የግድ አምላክ ሰው መሆን አለበት፡፡ አምላክ ሰው እንዲሆን ደግሞ የግድ የሰውን ሥጋ መዋሐድ አለበት፡፡ ያንን ሥጋ ደግሞ ያገኘው ከንጽሕት ዘር ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ነው፡፡ በአጭሩ የአዳም መድኃኒት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት ማለት ይቻላል፡፡ አዳም ለመዳን የግድ የተገባለት ቃል ኪዳን መፈጸም አለበት፡፡ ያ ቃልኪዳን እንዲፈጸም የግድ እመቤታችን ቅደስት ድንግል ማርያም መኖር አለባት፡፡ ከእመቤታችን የተገኘው ሥጋ ነው በቀራንዮ የተሰቀለው፡፡ ከእመቤታችን የተገኘው ነፍስ ነው በአካለ ነፍስ ሲዖል ወርዶ አዳምና የልጅ ልጆቹን ከሲዖል ወደ ገነት ያስገባቸው፡፡ ከእመቤታችን የተገኘው ሥጋ ወደም ነው የዘላለም ሕይወትን ሥረይተ ኃጢአትን አሰጥቶ ድኅነት መንግሥተ ሰማይን የሚያስወርሰው፡፡ ዮሐ 6፡53-54 ለመዳናችን ምክኒያት የሆነው መድኃኒቱ የተገኘው ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም በመሆኑ ለአዳም የድኅነቱ ምክንያት መድኃኒቱ፣ የቃልኪዳኑ መፈጸሚያ የድኅነቱ ማረጋገጫ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት፡፡ በመሆኑም ዓለም ያለ እመቤታችን አልዳነም፡፡
ድኅነቱ ተፈጸመ ማለት ደግሞ ገነት ተከፈተ ማለት ነው፡፡ ጌታችን እስኪሞት በአካለ ነፍስ ሲዖል እስኪወርድ ድረስ የሞቱት አዳም እና የልጅ ልጆቹ ጌታችን እመቤታችንን ምክኒያት አድርጎ በፈጸመላቸው ድኅነት ተጠቅመው ገነትን አግኝተዋል፡፡ ጥያቄው ከዛ በኋላ ላሉ ሰዎችስ ድኅነቱ ምንድን ነው ቢሉ የገነት መከፈት ነው፡፡ ገነት ተከፍቷል ማለት ደግሞ ገነት ለመግባት የሚደረጉ ሥራዎች አሉ ማለት ነው፡፡ ከነዛም መካከል የሰዎች ልጆች እንዲድኑ ቅዱሳን በምልጃቸውና በተገባላቸው ቃልኪዳን መሰረት ወደ መዳን የሚያደርሱ መድኃኒቶች ይሆናሉ፡፡ ጌታችን አንድ ጊዜ ድኅነቱን ከፈጸመ በኋላ ሁሉንም አዲስ አደርጓቸው ነበር፡፡ ነገር ግን የሰው ልጅ በኃጢያት ምክንያት ስለሚያረጅ ድጋሚ የማዳን ስራውን ከሰማይ ወርዶ አይፈጽምልንም፡፡ ይልቁንም ቅዱሳኑን ምክንያት አድርጎ ያድነናል እንጂ፡፡ ዕብ 2፡14 ‹‹ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገዝ የሚላኩ የሚያገለግሉም መናፍስት አይደሉምን;›› እንዲል በሌላም ስፍራ 2ኛቆሮ 5:15-20 ‹‹በሕይወትም ያሉት ስለ እነርሱ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው እንዳይኖሩ ስለ ሁሉ ሞተ። ስለዚህ እኛ ከአሁን ጀምሮ ማንንም በሥጋ እንደሚሆን አናውቅም፤ ክርስቶስንም በሥጋ እንደ ሆነ ያወቅነው ብንሆን እንኳ፥ አሁን ግን ከእንግዲህ ወዲህ እንደዚህ አናውቀውም። ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል። ነገር ግን የሆነው ሁሉ፥ በክርስቶስ ከራሱ ጋር ካስታረቀን የማስታረቅም አገልግሎት ከሰጠን፥ ከእግዚአብሔር ነው፤ እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና፥ በደላቸውን አይቆጥርባቸውም ነበር፤ በእኛም የማስታረቅ ቃል አኖረ። እንግዲህ እግዚአብሔር በእኛ እንደሚማለድ ስለ ክርስቶስ መልክተኞች ነን፤ ከእግዚአብሔር ጋር ታረቁ ብለን ስለ ክርስቶስ እንለምናለን።›› ብለው ከአሁን ወዲያ ቅዱሳን የሰዎች የመዳኛ መንገድ እነርሱ መሆናቸውን ተናገሩ፡፡
ጌታችን በወንጌል ማቴ 10፡41 ‹‹ጻድቅን በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይቀበላል፡፡ ነቢይንም በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢዩን ዋጋ ይወስዳል፡፡ ማንም ከእነዚህ ለታናናሾች በደቀ መዝሙሬ ስም ጥቂት ውሃ ቢሰጥ እውነት እውነት እላችኋለው ዋጋው አይጠፋበትም፡፡›› ብሎ ለነድያን በቅዱሳን ስም ጥርኝ ውሃ መዘከር እንኳን ዋጋ መንግሥተ ሰማይን እንደሚያስወርስ እንዲሁም እንደሚያድን ተናግሯል፡፡

በወንድማችን #አቤኔዘር

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
#እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም_መድኃኒታችን_ናት

የድኅነት ምክንያት በራሱ መድኃት ነው፡፡ የመድኃቱ መገኛ መሆን በራሱም መድኃኒት ያሰኘዋል፡፡ አዳኝ እግዚአብሔር መሆኑ እሙን ነው፡፡ እግዚአብሔር ደግሞ በምክኒያትም አለምክኒያትም ያድናል፡፡ ይህ ማለት ሌላ የማዳኛ መንገድ ተጠቅሞ ሊያድን ይችላል፡፡ ሳይጠቀምም ሊያድን ይችላል፡፡ ቅዱሳኑን ተጠቅሞ ሊያድን ይችላል፣ በጠበል ሊያድን ይችላል አልያም ሌላ መንገድ ተጠቅሞ ሊያድን ይችላል፡፡ በተቃራኒው ደግሞ ምንም አይነት የማዳኛ መንገድ ሳይጠቀም ሊያድን ይችላል፡፡ ለምሳሌ ዮሐ 5፡1-9 ላይ ስንመለከት በቤተ ሳይዳ 38 ዓመት ሙሉ አልጋው ላይ ተኝቶ የነበረውን ሰው ያዳነው ምንም ምክኒያት ሳይጠቀም ነው፡፡ ‹‹ልትድን ትወዳለህን›› አለው ከዛም ‹‹አልጋህን ተሸክመህ ሂድ፡፡›› አለው፡፡ በዮሐ 9፡1-7 በዚህ ክፍል ስንመለከት ደግሞ ጌታችን የእውሩን ዐይን ያበራለት በጠበል ሄዶ እንዲጠመቅ በማዘዝ ነበር፡፡ አዳኙ እግዚአብሔር ነው፡፡ ምክንያተ ድኅነቱ ደግሞ ጠበል፡፡ ጠበሉ ምክንያተ ድኂን በመሆኑ መድኃኒት ነው፡፡
መዝ 3፡8 ‹‹ማዳን የእግዚአብሔር ነው፡፡›› ይላል፡፡ በመሳ 3፡9 ላይ ደግሞ ‹‹የእስራኤል ልጆች ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፡፡ እግዚአብሔርም የሚያድናቸውን የቄኔዝን ልጅ ጎቶንያልን አዳኝ አድርጎ አስነሳላቸው፡፡›› እነዚህ ሁለት ቃላት እርስ በራሳቸው የሚገጩ ይመስላሉ፡፡ ነገር ግን በፍጹም አይጋጩም፡፡ ማዳን የእግዚአብሔር ቢሆንም እንዲሁም አዳኝ ተብሎ ሊጠራ የሚገባው አርሱ ሆኖ ሳለ ስለምን ጎቶንያል አዳኝ (መዳኒት) ተብሎ ተጠራ ቢሉ ምክንያቱም እስራኤልን እግዚአብሔር ያዳናቸው ጎቶንያልን ምክንያት አድርጎ ስለሆነ ነው፡፡ ስለዚህ ጎቶንያል ምክንያተ ድኂን ስለሆነ አዳኝ ተብሎ ተጠርቷል፡፡
ከላይ ባነሳናቸው ምሳሌዎች መሰረት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም የሰው ልጆች የድኅነት መፈጸሚያ ምክንያተ ድኂን በመሆኑዋ መድኃኒት ትባላለች፡፡ ለዚህ ነው በተዓምረ ማርያም መቅድም ላይ ‹‹መድኃኒታችሁ ናት›› ተብላ የተጠራችው፡፡ ለአዳም የተገባት ቃል ኪዳን ዘመኑ ሲፈጸም እግዚአብሔር ሰው ሆኖ እንደሚያድነው ነው፡፡ ገላ 4፡4 ይህ የመዳን ቃል ኪዳን እንዲፈጸም የግድ አምላክ ሰው መሆን አለበት፡፡ አምላክ ሰው እንዲሆን ደግሞ የግድ የሰውን ሥጋ መዋሐድ አለበት፡፡ ያንን ሥጋ ደግሞ ያገኘው ከንጽሕት ዘር ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ነው፡፡ በአጭሩ የአዳም መድኃኒት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት ማለት ይቻላል፡፡ አዳም ለመዳን የግድ የተገባለት ቃል ኪዳን መፈጸም አለበት፡፡ ያ ቃልኪዳን እንዲፈጸም የግድ እመቤታችን ቅደስት ድንግል ማርያም መኖር አለባት፡፡ ከእመቤታችን የተገኘው ሥጋ ነው በቀራንዮ የተሰቀለው፡፡ ከእመቤታችን የተገኘው ነፍስ ነው በአካለ ነፍስ ሲዖል ወርዶ አዳምና የልጅ ልጆቹን ከሲዖል ወደ ገነት ያስገባቸው፡፡ ከእመቤታችን የተገኘው ሥጋ ወደም ነው የዘላለም ሕይወትን ሥረይተ ኃጢአትን አሰጥቶ ድኅነት መንግሥተ ሰማይን የሚያስወርሰው፡፡ ዮሐ 6፡53-54 ለመዳናችን ምክኒያት የሆነው መድኃኒቱ የተገኘው ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም በመሆኑ ለአዳም የድኅነቱ ምክንያት መድኃኒቱ፣ የቃልኪዳኑ መፈጸሚያ የድኅነቱ ማረጋገጫ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት፡፡ በመሆኑም ዓለም ያለ እመቤታችን አልዳነም፡፡
ድኅነቱ ተፈጸመ ማለት ደግሞ ገነት ተከፈተ ማለት ነው፡፡ ጌታችን እስኪሞት በአካለ ነፍስ ሲዖል እስኪወርድ ድረስ የሞቱት አዳም እና የልጅ ልጆቹ ጌታችን እመቤታችንን ምክኒያት አድርጎ በፈጸመላቸው ድኅነት ተጠቅመው ገነትን አግኝተዋል፡፡ ጥያቄው ከዛ በኋላ ላሉ ሰዎችስ ድኅነቱ ምንድን ነው ቢሉ የገነት መከፈት ነው፡፡ ገነት ተከፍቷል ማለት ደግሞ ገነት ለመግባት የሚደረጉ ሥራዎች አሉ ማለት ነው፡፡ ከነዛም መካከል የሰዎች ልጆች እንዲድኑ ቅዱሳን በምልጃቸውና በተገባላቸው ቃልኪዳን መሰረት ወደ መዳን የሚያደርሱ መድኃኒቶች ይሆናሉ፡፡ ጌታችን አንድ ጊዜ ድኅነቱን ከፈጸመ በኋላ ሁሉንም አዲስ አደርጓቸው ነበር፡፡ ነገር ግን የሰው ልጅ በኃጢያት ምክንያት ስለሚያረጅ ድጋሚ የማዳን ስራውን ከሰማይ ወርዶ አይፈጽምልንም፡፡ ይልቁንም ቅዱሳኑን ምክንያት አድርጎ ያድነናል እንጂ፡፡ ዕብ 2፡14 ‹‹ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገዝ የሚላኩ የሚያገለግሉም መናፍስት አይደሉምን;›› እንዲል በሌላም ስፍራ 2ኛቆሮ 5:15-20 ‹‹በሕይወትም ያሉት ስለ እነርሱ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው እንዳይኖሩ ስለ ሁሉ ሞተ። ስለዚህ እኛ ከአሁን ጀምሮ ማንንም በሥጋ እንደሚሆን አናውቅም፤ ክርስቶስንም በሥጋ እንደ ሆነ ያወቅነው ብንሆን እንኳ፥ አሁን ግን ከእንግዲህ ወዲህ እንደዚህ አናውቀውም። ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል። ነገር ግን የሆነው ሁሉ፥ በክርስቶስ ከራሱ ጋር ካስታረቀን የማስታረቅም አገልግሎት ከሰጠን፥ ከእግዚአብሔር ነው፤ እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና፥ በደላቸውን አይቆጥርባቸውም ነበር፤ በእኛም የማስታረቅ ቃል አኖረ። እንግዲህ እግዚአብሔር በእኛ እንደሚማለድ ስለ ክርስቶስ መልክተኞች ነን፤ ከእግዚአብሔር ጋር ታረቁ ብለን ስለ ክርስቶስ እንለምናለን።›› ብለው ከአሁን ወዲያ ቅዱሳን የሰዎች የመዳኛ መንገድ እነርሱ መሆናቸውን ተናገሩ፡፡
ጌታችን በወንጌል ማቴ 10፡41 ‹‹ጻድቅን በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይቀበላል፡፡ ነቢይንም በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢዩን ዋጋ ይወስዳል፡፡ ማንም ከእነዚህ ለታናናሾች በደቀ መዝሙሬ ስም ጥቂት ውሃ ቢሰጥ እውነት እውነት እላችኋለው ዋጋው አይጠፋበትም፡፡›› ብሎ ለነድያን በቅዱሳን ስም ጥርኝ ውሃ መዘከር እንኳን ዋጋ መንግሥተ ሰማይን እንደሚያስወርስ እንዲሁም እንደሚያድን ተናግሯል፡፡

በወንድማችን #አቤኔዘር

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
እሾህ #የሌለባት_ጽጌ_ሬዳ
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ጊዜው የአበባና የፍሬ ጊዜ ነው ቤተክርስቲያንም ዘመነ ጽጌ ወርሃ ጽጌ ብላ ስለ ጽጌያት ታስተምራለች:: #ከመስከረም 26 እስከ #ህዳር 6 ቀን ያሉት ተከታታይ 40 ቀናት ናቸው ስለ ጽጌ ወይም ስለ አበባ የምታስተምረው ትምህርት ይህ እኛ የምናውቀውን በአፈር፣ በውኃና በፀሐይ ብርሃን አማካኝነት የሚያድገውን የእጽዋት አይነት ብቻ የሚመለከት አይደለም። ከዛ ይልቅ አማናዊት አበባ ስለምትባል ስለ ድንግል ማርያም በዚህ ወቅት በምልዐት ታስተምራለች ትሰብካለች:: እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እውነተኛ አበባ ነች።
እንደ ሳይንሱ ገለጻ አንድ እጽዋት እጽዋት ለመሰኘት ሦስት መሠረታዊ ነገሮችን ሊያሞላ ይገባል ይላል። እነርሱም እውነተኛ ሥር እውነተኛ ግንድ እውነተኛ ቅርንጫፍ ናቸው ። እነዚህ እጽዋት በሥሮቻቸው አማካኝነት ከአፈር ውስጥ ውኃና ሚኒራልን በመውሰድ ከቅርንጫፍቻቸው ካሉ ቅጠሎች ደግሞ የፀሐይ ብርሃን በማምጣት በግንዶቻቸው አጓጓዠነት በመጠቀም ፖቶሰቴንስስ በተባለ ሂደት ምግቦቻቸውን ማዘጋጀት ይችላሉ ።እውነተኛ ሥር ግንድና ቅርንጫፍ የሌላቸውን አረንጓዴ ተክሎች ግን አልጋይ እና ፈንጋይ እየተባሉ ይጠራሉ እውነተኛ ሥር ግንድና ቅርንጫፍ የላቸውምና ምግባቸውን ማዘጋጀት አይችሉም ስለዚህ እጽዋት ተብለው አይጠሩም ::

#እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም ታዲያ ከእውነተኛም እውነተኛ የሆነች ( እጸ ሕይወት) እውነተኛ የሕይወት አበባ ነች መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች እውነተኛ የወይን ግንድ አብቃይ ቅርንጫፎቿም በሰማያተ የሚገኑ አረገ ወይን ነች:: (ሥር) መዝ 86÷1 (ግንድ)ኢሳ11÷1 (ቅርንጫፍ)ዮሐ 15÷5 ።

የሕይወት መብል መጠጥ የሆነ ክርስቶስን የወለደችልን ድንግል ማርያም እውነተኛ ሥር ግንድና ቅጠል ያላት እውነተኛ አበባ መሆኖን አሰረግጦ መናገር የተገባ ነው። ለምን ቢሉ
አንዳንድ ዲያቢሎስ ያደረባቸው ደፋር ሴቶች በዘመኑ ብኖር እኔም ክርስቶስን እወልደው ነበር ብለው የድንግልን ክብር ከእራሳቸው ክብር ጋር በትቢት ባልተገባ የሚያስተካክሉ ልካቸውን ማሳወቅ ስለሚገባ ነው በእስራኤል ያሉ ሴቶች ደግሞ ዛሬ ድረስ ክርስቶስ አልተወለደም ወደፊት ከአንዳችን ይወለዳል ብለው በድፍረት በከንቱ ይጠባበቃሉ በእውነት ግን እነዚህ ሴቶች እንኳን የሕይወት መብልና መጠጥ የሆነውን ክርስቶስን ሊወልዱ ቀርቶ ሊወልዱት የሚችሉትል ተራ ሰው እንኳ በአግባቡ ስለመመገባቸው እርግጠኞች አይደሉም ስለዚህም ምግባቸውን እንኳን ማዘጋጀት እንደ ማይችሉ አልጋይና ፋንጋይ ናቸው ማለት ይቻላል። እውነተኞች አይደሉምና ።

#እርሷ_እመቤታችን እንኳን ስለራሷ በትንቢት የተጻፈውን ባነበበች ጊዜ ከዚህች ቅድስት ሴት ከዘመኗ ደርሼ ውኃ ቀድቼ እንጨት ፈልጬ ገረዷ ሆኜ ባገለገልኳት ብላ በትህትና ገረድነትን ተመኘች እንጂ እኔ በሆኩ አላለችም ጊዜው ደርሶም መላእኩ ገብርኤል መጥቶ አምላክን ለመውለድ በተገባ ተገኝተሻል ብሎ የመውለዷን ዜና ሲያበሥራት እንኳ ይህ እንዴት ይሆንልኛል እኔ #የእግዚአብሔር ባሪያው ነኝ አለችሁ እንጂ ከወነማ ከመጣህማ ብላ በኩራት ሆና አልተናገረችሁም .....ይህ እንዴት ያለህ ትህትና ነው? የአምላክ እናቱ ነሽ እየተባሉ እራስን ገረድ ማለት! ሊቁም ይህ ትህትና ቢገርመው ልዕልናዋን ከትህትናዋ አስማምቶ " #በትህትና_የተናገርሽ ተራራ ሆይ " ብሎ ጠራት::
እውነተኛይቱ አበባ ግን አስቀድማ ዓለም ሳይፈጠር በተዘክሮተ ፈጣሪ ዋላም ዓለም ከተፈጠረ በኃላ በነቢያት ትንቢት በሐዋርያት ስብከት በደቂቀ አዳም ልብ የነበረች፣ ያለችና ፣የምትኖር የማደርቅና የማጠወልግ እንቡጥ አበባ ነች።
#አበባ የዓይን ማረፊያ የልብ ተስፋ የአፍንጫ መዐዛ ነው እመቤታችንም አስቀድማ ለእናት ለአባትዋ በኃላም ለደቂቀ አዳም ሁሉ የዓይን ማረፊያ የልብ ተስፋ የነፍስ መዐዛ ነች " #ከዕሴይ_ሥር የወጣሽ መዐዛሽ ያማረ አበባ አንቺ ነሽ " እንዳለ ሊቁ #ውዳሴ_ማርያም ዘእሁድ ኢሳ11÷1
#አበባ መድኃኒትን ያስገኛል እውነተኛይቱ አበባ እመቤታችንም መዳኒ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስን አስገኝታለች እስለዚህ " እሙ ለመዳኒት" የመዳኒት እናት ትባላለችና አባባ ነች ሉቃ 2÷10-11
አበባ ንብቦችን ይስባል ማርን ያሰራል እውነተኛይቱ አበባ እመቤታችንም ወልድ ክርስቶስን ስባለች ማር የሆነች የወንጌል ሕግን አሰርታለች። ማር ጥዑም ነው ክርስቶስና ወንጌልም ጥዑማን ናቸው አንድም ማር መድኃኒት ነው ክርስቶስ እና ወንጌልም መድኃኒት ናቸው::"ከያዕቆብ ድንኳኖች ይልቅ፥ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወድዳቸዋል" መዝ 86(87)÷2
"ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና" መዝ 44(45)÷10-11
አበባ ምግበ ሥጋን ያስገኛል (ለምሳሌ አበባ ጎመን የመሰሉ ተክሎች ወዘተ...) እውነተኛይቱ አባ እመቤታችንም ምግበ ሥጋወነፍስ የሆነ ክርቶስን አስገኝታለች ዮሐ 6÷56 ማቴ 26÷26
"በመኑ ወበ አምሳለ መኑ ናስተማስለኪ " እንዳሉ ሊቃውንት ድንግል ሆይ በምንና በማን እንመስልሻለን ክብርሽን የሚገልጥ ነገር አጣን ብለን በተደሞ ዝም እንበል እንጂ እመቤታችንንስ አበባ ብቻ የሚገልጣት ሆኖ አይደለም።
እንዴት? ቢሉ አበባ ከምድር ተገኝቶ በምድር ይቀራል አበባይቱ እመቤታች ግን ከምድር ብትገኝም ቅሉ የማትደርቅ የማትጠወልግ ምድራዊት ወ ሰማያዊት የሆነች ለምለም አበባ ነች።
አበባ ይልቁኑ ጽጌ ሬዳ በእህሾ የተከበበ ነው ። አበባይቱ እመቤታችን ግን የጥንተ አብሶ እሾህ ያልከበባት ንፁህ ጽጌ ሬዳ ናት። ወርቅ ከመሬት ከጭቃ ይገኛል ነገር ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችንም ከምድር የተገኘች ሆና ሳለ ግን ምድራዊ በደል ያላቆሸሻት እሾህ አልባ የወርቅ አበባ ነች ለይቶ ቀድሷታልና “ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ።” መዝ45(46)፥4
አበባ መድኃኒት ቢያስገኝ ከጊዜያዊ ሕመም የሚያድን ጊዜያዊ መድኃኒት ነው የሚያስገኘው አበባይቱ እመቤታችን ግን አንዴ ከተበላ አንዴ ከተጠጣ ዳግመኛ የማያስፈልገውን ዘላለማዊ ፍቱን መድኃኒትን ያስገኘች ሕያው አበባ ነች።
አንድ ንጥል አበባ ዘሩን የሚተካው ወንዴና ሴቴ የተባሉ ክፍሎቹን በመጠቀም ነው የወንዴው ብናኝ ጊዜውን ጠብቆ እራሱን ሲያበን ማጣበቅ የሚችለው የሴቴ ክፍል ብናኙን ይቀበልና ሌሎች አበቦችን ማፍራት ይጀምራል ። ይህ ሂደት ኢ ተሻጋሪ(እዛው በዛው) የማፍራት ሂደት ይባላል ። በሌላ በኩል ደግሞ የአንዱ ንጥል አበባ የወንዴ ብናኝ በንቦች ፣በወፎች፣ እንዲሁም በሰዎች ንኪኪ ወይም በንፋስ ሽውታ አማካኝነት በኖ ከራሱ የሴቴ ብናኝ ተቀባይ ውጪ ተሻግሮ በሌላ አበባ የሴቴ ክፍል ላይ በመጣበቅ የሚያፈራበትም መንገድ አለ ይህም ተሻጋሪ የአረባብ ዘዴ በመባል ይታወቃል ።

አበባ እንዲ ባለ መልክ ሲያብብ አማናዊቷ አበባ እመቤታችን ግን ያለ ዘርዐ ብዕሲ ያለ ወንድ ዘር ) በ ግብረ መንፈስ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ ሥራ ጸንሳ መውለድ ችላለች ስለዚህ በእጅጉ ከአበባዎች ሁሉ ትበልጣለች አልን።

"ሳይተክሏትና ውኃ ሳያጠጧት የለመለመች የአሮን በትር ነበረች #አንቺ_እንደ_እርሷ_ነሽ #ውዳሴ_ማርያም_ዘእሁድ
.......ይቆየን ............
ምልጃ ቃልኪዳኗ ከሁላችን ሕዝበ ክርስቲያኖች ጋር ለዘላለሙ ጸንቶ ይኑር ...አሜን!
ኃ/ ማርያም
ጥቅምት 1/2013 ዓ.ም
አ.አ ኢትዮጲያ
👇👇👇👇👇👇👇
#ዓውደ_ምህረት_የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
#ሞት_በጥር_ነሐሴ_መቃብር

መቼም ዞሮ ዞሮ ከቤት ኖሮ ኖሮ ከመሬት የሚቀር የለም :: ሞትን ሳይቀምሱ በሥጋ የተሰወሩ ቅዱሳን ሰዎች ቢኖሩም በመጨረሻ ግን የሞትን ጽዋ መጠጣታቸው ግድ ነው ሞት ወደ ክርስቶስ መሄጃ መንገድ መሸጋገሪያ ድልድይ ነውና:: ለዚህ ነው ሐዋርያው "፤ ልሄድ ከክርስቶስም ጋር ልኖር እናፍቃለሁ፥ " ያለው #ፊል ፩ ÷ ፳፫
#የዛሬን አያድርገውና ሞት እንዲ ተዋርዶ እና ዝቅ ብሎ መንገድ ተብሎ እንደ ተራ ከመጠራቱ በፊት እጅግ አስፈሪ ነበር :: ሰዎች መልካምም ይሁኑ እኩያት በሞት ተግዘው ሲዖል ወስዶ መማቀቃቸው አይቀርም ነበር "፤ ሁላችን እንደ ርኩስ ሰው ሆነናል፥ ጽድቃችንም ሁሉ እንደ መርገም ጨርቅ ነው፤ ሁላችንም እንደ ቅጠል ረግፈናል #ኢሳ ፷ ፬ ÷፮ እንዲል ነብዮ ::
በኋላ ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህች ምድር መምጣት ሞት የቀደመ መፈራቱን አጣ በትንሳኤ ተደመሰሰ በዚህም አስቀድመው እንኳንስ በደላችን ጽድቃችን እንኳ ሳይቀር እንደ
መርገም ጨርቅ ተቆጠረብን እንዳላሉ "፤ ሞት ሆይ፥ መውጊያህ የት አለ? ሲኦል ሆይ፥ ድል መንሣትህ የት አለ? " እያሉ የሞትን ኃይል አቃለሉት #፩ቆሮ ፲፭÷፶፭
#ሞት በራሱ ምንም ያልሆነ የልደት ተቃራኒ ነው ነገር ግን በግብሩ ሞት ተብሎ የሚጠራው ዲያቢሎስ ነው:: ሞት የሁሉ ገዥ ሆኖ ሰልጥኟል የክብር ባለቤት መድኃን ዓለም ክርስቶስ ሳይቀር በፈቃዱ ሞትን ቀምሷል :: ይህም ከመላእክት እንኳ በጥቂቱ አነሰ ተብሎ እንዲነገርለት አድርጓል ሞት ሁሉን እንዲገዛ ያሰለጠነው እርሱ እራሱ ነው። ቢሆንም ግን ቅሉ ክብር ይግባውና ከሞት ያንሳል አያሰኘውም::

#መጻሕፍትም ይህን ግልጽ ሲያደርጉልን እንዲ ብለዋል "፤ የኃለኛው ጠላት የሚሻረው ሞት ነው ሁሉን ከእግሩ በታች አስገዝቶአልና። ነገር ግን። ሁሉ
ተገዝቶአል ሲል፥ ሁሉን ካስገዛለት በቀር መሆኑ ግልጥ ነው። " #፩ቆሮ ፲፭ ÷፳፯ ሞት ለፈጣሪ ዓለማት ብቻም ሳይሆን ለእናቱ ለምክንያተ ድኅይን ለምትባል ለእመቤታችን ለማርያምም አልተመለሰም ::

#እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም በምድር ላይ ስልሳ አራት ዓመታትን ቆይታለች ማለትም ከእናት ከአባቷ ቤት ሦስት ዓመት ከሰባት ወር፣ በቤተመቅደስ ፲፪ ዓመት፣ በቤተ ዮሴፍ ፴፬ ዓመት ከሦስት ወር፣ ከጌታችን እርገት በኋላ ከወንጌላዊው ዮሐንስ ጋር ፲፬ ዓመት ኖራለች፡፡ ጥር ፳፩ በእሑድ ቀን ጌታ እልፍ አዕላፋት መላእክቱን
አስከትሎ መጥቶ እናቴ ሆይ ከዚህ ዓለም ድካም ላሳርፍሽ መጣሁ አላት።

ልጄ ሰማይና ምድር የማይወስኑህ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በማህጸኔ ተሸክሜ በድንግልና ወልጄህ እሞታለሁን? አለችው። እውነት ነው ሊቁ ቅዱስ ያሬድም ይህ ነገረ ሞቷን &ሞትሰ ለመዋቲ
ይደሉ ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኲሉ፤( ሞት ለማናቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው የማርያም
ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል ) ሲል አድንቋል ከዛም በሲዖል የሚሰቃዩ ነፍሳትን አሳይቶ እናቴ ሆይ ሞትሽ ለእነዚህ ቤዛ ይሆንላቸዋል አላት።

#እሊህን_ከማርክልኝስ ይሁን አንድ ጊዜ
አይደለም ሰባት ጊዜ ልሙት አለችው። ቅድስት ሥጋዋን ከቅዱስ ነፍሷ ለይቶ በዝማሬ መላእክት አሳረጋት። "ሞትኪሰ ማርያም ይመስል ከብካበ" የማርያምስ ሞት ሠርግን ይመስላል እንዲሉ አበው የእመቤታችን እረፍት እንባ መራጨት፣ ጠጉር መንጨት፣ ደረት መድቃት እንዳለበት የሰው ሞት አልነበረም፡፡ ይልቁንም አንደ ሠርግ ቤት መላዕክት
በውዳሴ፤ በማህሌት፣ በዝማሬ፣ በምስጋና ወደ ሰማይ ሸኟት እንጂ ቅዱስ ያሬድም "ተለዐለት እምድር ወበህየ ነበረት ዘምስለ ወልዳ በየማነ አብ ወመንፈስ ቅዱስ" እመቤታችን ድንግል ማርያም ከምድር ወደ ሰማይ ከፍ ከፍ አለች፡፡
በዚያም ከልጇ ጋር በአብና በመንፈስ ቅዱስ ቀኝ ተቀመጠች በማለትም ዘምሯል፡፡ "፤የቅዱሳኑ ሞት
በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።" መዝ ፻፲፮ (፻፲፯) ÷፲፭ አስቀድመው ሐዋርያት ሥጋዋን በአጎበር አድርገው ወደ ጌቴሰማኒ ይዘው ሲሄዱ ብዙ ተግዳሮት ገጥሞቸው ነበር:: አይሁድ ቀድሞ ልጇን ተነሳ ዐረገ እያሉ ሲያውኩን ይኖራሉ አሁን ደግሞ እሷን ተነሳች ዐረገች እያሉ ሊያውኩን አይደለምን? ኑ በእሳት እናቃጥላታለን ብለው ተነሱ።
#ታውፋንያ የሚባል አይሁዳዊ ተራምዶ አጎበሩን ጨበጠው። መልአክ መጥቶ በሰይፍ ሁለት እጁን ቀጣው ከአጎበሩ ተንጠልጥሎ ቀረ ። በድያለሁ ማሪኝ ብሎ ቢማጸናት እጁ ተመልሶለታል። ከዚህ በኋላ ዮሐንስን ጨምሮ በደመና ነጥቆ ከገነት አግብቶ ከዕፀ ሕይወት ሥር አኖራት። ቅዱስ ዮሐንስን እንደምን ሆነች አሉት ከገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር አለች አላቸው ቅዱስ ዮሐንስ አይቶ እኛ ሳናይ ብለው በነሐሴ መባቻ ጾም ጀመሩ ሁለት ሱባዔ ሲፈጸምም እሑድ አምጥቶ
ሰጥቷቸው ቀብረዋታል በሦስተኛው ቀን ማክሰኞ “ #ከመ_ትንሣኤ_ወልዳ ” እንደ ልጇ ባለ ትንሣኤ ተነሥታለች።
ቅዱስ ቶማስ አልነበረም ደመና ጠቅሶ ከሀገረ ስብከቱ ሲመጣ ስታርግ አገኛት ቀድሞ የልጅሽን ትንሳኤ ሳላይ ቀረሁ ዛሬም ደግሞ ያንችን ትንሳኤ ሳላይ ቀረሁን ብሎ “ወፈቀደ ይደቅ እምደመናሁ” ከሀዘኑ የተነሳ ሊወድቅ ወደደ እመቤታችንም አይዞህ
አትዘን እሊያ ትንሳኤየን ዕርገቴን አላዩም አንተ አይተሃል ተነሣች ዐረገች ብለህ ንገራቸው ብላ የያዘችውን ሰበን ሰጥታ ሰደደችው። ከዚህ በኋላ ሂዶ የእመቤታችን ነገር እንደምን ሆነ? አላቸው አግኝተን ቀበርናት አሉት #ሞት_በጥር_በነሐሴ_መቃብር ተው ይህ ነገርስ
አይመስለኝም አላቸው ። ቅዱስ ጴጥሮስ አንተ እንጅ ልማድህ ነው አንተ ብቻ ተጠራጥረህ አትቀርም ሰውን ሁሉ ስታጠራጥር ትኖራልህ ብሎ ተቆጥቶ ወደ መቃብሩ ሂዶ ቢከፍተው አጣት ደንግጦ ቆመ ሐዋርያው ቶማስም አታምኑኝም ብዬ እንጅ #እመቤታችንስ ተነሣች ዐረገች አላቸው የያዘውንም ሰበን ሰጣቸው ለበረከትም ተካፍለውታል።
#በዓመቱ ሐዋርያት ቅዱስ ቶማስ ትንሣኤሽን ዕርገትሽን አይቶ እኛ ሳናይ ብለው ጾም ጀመሩ በ፲፮ ኛው ቀን እመቤታችንን መንበር አድርጎ ቅዱስ ጴጥሮስን ካህን ዘይትራድኦ ቅዱስ እስጢፋኖስን ሠራዒ ዲያቆን አድርጎ በዚያው ላይ ቀድሶ አቁርቧቸዋል። ፍቅሯን በልቡናችን ጣዕሟን
በአንደበታችን ያትምልን
......... #ይቆየን .........
#የእመቤታችን_አማላጅነት_የልጇም_ይቅርታና_ቸርነት_አይለየን አሜን!

አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ጥር ፳፩ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም
እሾህ #የሌለባት_ጽጌ_ሬዳ
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ጊዜው የአበባና የፍሬ ጊዜ ነው ቤተክርስቲያንም ዘመነ ጽጌ ወርሃ ጽጌ ብላ ስለ ጽጌያት ታስተምራለች:: #ከመስከረም 26 እስከ #ህዳር 6 ቀን ያሉት ተከታታይ 40 ቀናት ናቸው ስለ ጽጌ ወይም ስለ አበባ የምታስተምረው ትምህርት ይህ እኛ የምናውቀውን በአፈር፣ በውኃና በፀሐይ ብርሃን አማካኝነት የሚያድገውን የእጽዋት አይነት ብቻ የሚመለከት አይደለም። ከዛ ይልቅ አማናዊት አበባ ስለምትባል ስለ ድንግል ማርያም በዚህ ወቅት በምልዐት ታስተምራለች ትሰብካለች:: እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እውነተኛ አበባ ነች።
እንደ ሳይንሱ ገለጻ አንድ እጽዋት እጽዋት ለመሰኘት ሦስት መሠረታዊ ነገሮችን ሊያሞላ ይገባል ይላል። እነርሱም እውነተኛ ሥር እውነተኛ ግንድ እውነተኛ ቅርንጫፍ ናቸው ። እነዚህ እጽዋት በሥሮቻቸው አማካኝነት ከአፈር ውስጥ ውኃና ሚኒራልን በመውሰድ ከቅርንጫፍቻቸው ካሉ ቅጠሎች ደግሞ የፀሐይ ብርሃን በማምጣት በግንዶቻቸው አጓጓዠነት በመጠቀም ፖቶሰቴንስስ በተባለ ሂደት ምግቦቻቸውን ማዘጋጀት ይችላሉ ።እውነተኛ ሥር ግንድና ቅርንጫፍ የሌላቸውን አረንጓዴ ተክሎች ግን አልጋይ እና ፈንጋይ እየተባሉ ይጠራሉ እውነተኛ ሥር ግንድና ቅርንጫፍ የላቸውምና ምግባቸውን ማዘጋጀት አይችሉም ስለዚህ እጽዋት ተብለው አይጠሩም ::

#እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም ታዲያ ከእውነተኛም እውነተኛ የሆነች ( እጸ ሕይወት) እውነተኛ የሕይወት አበባ ነች መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች እውነተኛ የወይን ግንድ አብቃይ ቅርንጫፎቿም በሰማያተ የሚገኑ አረገ ወይን ነች:: (ሥር) መዝ 86÷1 (ግንድ)ኢሳ11÷1 (ቅርንጫፍ)ዮሐ 15÷5 ።

የሕይወት መብል መጠጥ የሆነ ክርስቶስን የወለደችልን ድንግል ማርያም እውነተኛ ሥር ግንድና ቅጠል ያላት እውነተኛ አበባ መሆኖን አሰረግጦ መናገር የተገባ ነው። ለምን ቢሉ
አንዳንድ ዲያቢሎስ ያደረባቸው ደፋር ሴቶች በዘመኑ ብኖር እኔም ክርስቶስን እወልደው ነበር ብለው የድንግልን ክብር ከእራሳቸው ክብር ጋር በትቢት ባልተገባ የሚያስተካክሉ ልካቸውን ማሳወቅ ስለሚገባ ነው በእስራኤል ያሉ ሴቶች ደግሞ ዛሬ ድረስ ክርስቶስ አልተወለደም ወደፊት ከአንዳችን ይወለዳል ብለው በድፍረት በከንቱ ይጠባበቃሉ በእውነት ግን እነዚህ ሴቶች እንኳን የሕይወት መብልና መጠጥ የሆነውን ክርስቶስን ሊወልዱ ቀርቶ ሊወልዱት የሚችሉትል ተራ ሰው እንኳ በአግባቡ ስለመመገባቸው እርግጠኞች አይደሉም ስለዚህም ምግባቸውን እንኳን ማዘጋጀት እንደ ማይችሉ አልጋይና ፋንጋይ ናቸው ማለት ይቻላል። እውነተኞች አይደሉምና ።

#እርሷ_እመቤታችን እንኳን ስለራሷ በትንቢት የተጻፈውን ባነበበች ጊዜ ከዚህች ቅድስት ሴት ከዘመኗ ደርሼ ውኃ ቀድቼ እንጨት ፈልጬ ገረዷ ሆኜ ባገለገልኳት ብላ በትህትና ገረድነትን ተመኘች እንጂ እኔ በሆኩ አላለችም ጊዜው ደርሶም መላእኩ ገብርኤል መጥቶ አምላክን ለመውለድ በተገባ ተገኝተሻል ብሎ የመውለዷን ዜና ሲያበሥራት እንኳ ይህ እንዴት ይሆንልኛል እኔ #የእግዚአብሔር ባሪያው ነኝ አለችሁ እንጂ ከወነማ ከመጣህማ ብላ በኩራት ሆና አልተናገረችሁም .....ይህ እንዴት ያለህ ትህትና ነው? የአምላክ እናቱ ነሽ እየተባሉ እራስን ገረድ ማለት! ሊቁም ይህ ትህትና ቢገርመው ልዕልናዋን ከትህትናዋ አስማምቶ " #በትህትና_የተናገርሽ ተራራ ሆይ " ብሎ ጠራት::
እውነተኛይቱ አበባ ግን አስቀድማ ዓለም ሳይፈጠር በተዘክሮተ ፈጣሪ ዋላም ዓለም ከተፈጠረ በኃላ በነቢያት ትንቢት በሐዋርያት ስብከት በደቂቀ አዳም ልብ የነበረች፣ ያለችና ፣የምትኖር የማደርቅና የማጠወልግ እንቡጥ አበባ ነች።
#አበባ የዓይን ማረፊያ የልብ ተስፋ የአፍንጫ መዐዛ ነው እመቤታችንም አስቀድማ ለእናት ለአባትዋ በኃላም ለደቂቀ አዳም ሁሉ የዓይን ማረፊያ የልብ ተስፋ የነፍስ መዐዛ ነች " #ከዕሴይ_ሥር የወጣሽ መዐዛሽ ያማረ አበባ አንቺ ነሽ " እንዳለ ሊቁ #ውዳሴ_ማርያም ዘእሁድ ኢሳ11÷1
#አበባ መድኃኒትን ያስገኛል እውነተኛይቱ አበባ እመቤታችንም መዳኒ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስን አስገኝታለች እስለዚህ " እሙ ለመዳኒት" የመዳኒት እናት ትባላለችና አባባ ነች ሉቃ 2÷10-11
አበባ ንብቦችን ይስባል ማርን ያሰራል እውነተኛይቱ አበባ እመቤታችንም ወልድ ክርስቶስን ስባለች ማር የሆነች የወንጌል ሕግን አሰርታለች። ማር ጥዑም ነው ክርስቶስና ወንጌልም ጥዑማን ናቸው አንድም ማር መድኃኒት ነው ክርስቶስ እና ወንጌልም መድኃኒት ናቸው::"ከያዕቆብ ድንኳኖች ይልቅ፥ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወድዳቸዋል" መዝ 86(87)÷2
"ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና" መዝ 44(45)÷10-11
አበባ ምግበ ሥጋን ያስገኛል (ለምሳሌ አበባ ጎመን የመሰሉ ተክሎች ወዘተ...) እውነተኛይቱ አባ እመቤታችንም ምግበ ሥጋወነፍስ የሆነ ክርቶስን አስገኝታለች ዮሐ 6÷56 ማቴ 26÷26
"በመኑ ወበ አምሳለ መኑ ናስተማስለኪ " እንዳሉ ሊቃውንት ድንግል ሆይ በምንና በማን እንመስልሻለን ክብርሽን የሚገልጥ ነገር አጣን ብለን በተደሞ ዝም እንበል እንጂ እመቤታችንንስ አበባ ብቻ የሚገልጣት ሆኖ አይደለም።
እንዴት? ቢሉ አበባ ከምድር ተገኝቶ በምድር ይቀራል አበባይቱ እመቤታች ግን ከምድር ብትገኝም ቅሉ የማትደርቅ የማትጠወልግ ምድራዊት ወ ሰማያዊት የሆነች ለምለም አበባ ነች።
አበባ ይልቁኑ ጽጌ ሬዳ በእህሾ የተከበበ ነው ። አበባይቱ እመቤታችን ግን የጥንተ አብሶ እሾህ ያልከበባት ንፁህ ጽጌ ሬዳ ናት። ወርቅ ከመሬት ከጭቃ ይገኛል ነገር ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችንም ከምድር የተገኘች ሆና ሳለ ግን ምድራዊ በደል ያላቆሸሻት እሾህ አልባ የወርቅ አበባ ነች ለይቶ ቀድሷታልና “ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ።” መዝ45(46)፥4
አበባ መድኃኒት ቢያስገኝ ከጊዜያዊ ሕመም የሚያድን ጊዜያዊ መድኃኒት ነው የሚያስገኘው አበባይቱ እመቤታችን ግን አንዴ ከተበላ አንዴ ከተጠጣ ዳግመኛ የማያስፈልገውን ዘላለማዊ ፍቱን መድኃኒትን ያስገኘች ሕያው አበባ ነች።
አንድ ንጥል አበባ ዘሩን የሚተካው ወንዴና ሴቴ የተባሉ ክፍሎቹን በመጠቀም ነው የወንዴው ብናኝ ጊዜውን ጠብቆ እራሱን ሲያበን ማጣበቅ የሚችለው የሴቴ ክፍል ብናኙን ይቀበልና ሌሎች አበቦችን ማፍራት ይጀምራል ። ይህ ሂደት ኢ ተሻጋሪ(እዛው በዛው) የማፍራት ሂደት ይባላል ። በሌላ በኩል ደግሞ የአንዱ ንጥል አበባ የወንዴ ብናኝ በንቦች ፣በወፎች፣ እንዲሁም በሰዎች ንኪኪ ወይም በንፋስ ሽውታ አማካኝነት በኖ ከራሱ የሴቴ ብናኝ ተቀባይ ውጪ ተሻግሮ በሌላ አበባ የሴቴ ክፍል ላይ በመጣበቅ የሚያፈራበትም መንገድ አለ ይህም ተሻጋሪ የአረባብ ዘዴ በመባል ይታወቃል ።

አበባ እንዲ ባለ መልክ ሲያብብ አማናዊቷ አበባ እመቤታችን ግን ያለ ዘርዐ ብዕሲ ያለ ወንድ ዘር ) በ ግብረ መንፈስ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ ሥራ ጸንሳ መውለድ ችላለች ስለዚህ በእጅጉ ከአበባዎች ሁሉ ትበልጣለች አልን።

"ሳይተክሏትና ውኃ ሳያጠጧት የለመለመች የአሮን በትር ነበረች #አንቺ_እንደ_እርሷ_ነሽ #ውዳሴ_ማርያም_ዘእሁድ
.......ይቆየን ............
ምልጃ ቃልኪዳኗ ከሁላችን ሕዝበ ክርስቲያኖች ጋር ለዘላለሙ ጸንቶ ይኑር ...አሜን!
ኃ/ ማርያም
ጥቅምት 1/2013 ዓ.ም
አ.አ ኢትዮጲያ
👇👇👇👇👇👇👇
#ዓውደ_ምህረት_የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
እሾህ #የሌለባት_ጽጌ_ሬዳ
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ጊዜው የአበባና የፍሬ ጊዜ ነው ቤተክርስቲያንም ዘመነ ጽጌ ወርሃ ጽጌ ብላ ስለ ጽጌያት ታስተምራለች:: #ከመስከረም 26 እስከ #ህዳር 6 ቀን ያሉት ተከታታይ 40 ቀናት ናቸው ስለ ጽጌ ወይም ስለ አበባ የምታስተምረው ትምህርት ይህ እኛ የምናውቀውን በአፈር፣ በውኃና በፀሐይ ብርሃን አማካኝነት የሚያድገውን የእጽዋት አይነት ብቻ የሚመለከት አይደለም። ከዛ ይልቅ አማናዊት አበባ ስለምትባል ስለ ድንግል ማርያም በዚህ ወቅት በምልዐት ታስተምራለች ትሰብካለች:: እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እውነተኛ አበባ ነች።
እንደ ሳይንሱ ገለጻ አንድ እጽዋት እጽዋት ለመሰኘት ሦስት መሠረታዊ ነገሮችን ሊያሞላ ይገባል ይላል። እነርሱም እውነተኛ ሥር እውነተኛ ግንድ እውነተኛ ቅርንጫፍ ናቸው ። እነዚህ እጽዋት በሥሮቻቸው አማካኝነት ከአፈር ውስጥ ውኃና ሚኒራልን በመውሰድ ከቅርንጫፍቻቸው ካሉ ቅጠሎች ደግሞ የፀሐይ ብርሃን በማምጣት በግንዶቻቸው አጓጓዠነት በመጠቀም ፖቶሰቴንስስ በተባለ ሂደት ምግቦቻቸውን ማዘጋጀት ይችላሉ ።እውነተኛ ሥር ግንድና ቅርንጫፍ የሌላቸውን አረንጓዴ ተክሎች ግን አልጋይ እና ፈንጋይ እየተባሉ ይጠራሉ እውነተኛ ሥር ግንድና ቅርንጫፍ የላቸውምና ምግባቸውን ማዘጋጀት አይችሉም ስለዚህ እጽዋት ተብለው አይጠሩም ::

#እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም ታዲያ ከእውነተኛም እውነተኛ የሆነች ( እጸ ሕይወት) እውነተኛ የሕይወት አበባ ነች መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች እውነተኛ የወይን ግንድ አብቃይ ቅርንጫፎቿም በሰማያተ የሚገኑ አረገ ወይን ነች:: (ሥር) መዝ 86÷1 (ግንድ)ኢሳ11÷1 (ቅርንጫፍ)ዮሐ 15÷5 ።

የሕይወት መብል መጠጥ የሆነ ክርስቶስን የወለደችልን ድንግል ማርያም እውነተኛ ሥር ግንድና ቅጠል ያላት እውነተኛ አበባ መሆኖን አሰረግጦ መናገር የተገባ ነው። ለምን ቢሉ
አንዳንድ ዲያቢሎስ ያደረባቸው ደፋር ሴቶች በዘመኑ ብኖር እኔም ክርስቶስን እወልደው ነበር ብለው የድንግልን ክብር ከእራሳቸው ክብር ጋር በትቢት ባልተገባ የሚያስተካክሉ ልካቸውን ማሳወቅ ስለሚገባ ነው በእስራኤል ያሉ ሴቶች ደግሞ ዛሬ ድረስ ክርስቶስ አልተወለደም ወደፊት ከአንዳችን ይወለዳል ብለው በድፍረት በከንቱ ይጠባበቃሉ በእውነት ግን እነዚህ ሴቶች እንኳን የሕይወት መብልና መጠጥ የሆነውን ክርስቶስን ሊወልዱ ቀርቶ ሊወልዱት የሚችሉትል ተራ ሰው እንኳ በአግባቡ ስለመመገባቸው እርግጠኞች አይደሉም ስለዚህም ምግባቸውን እንኳን ማዘጋጀት እንደ ማይችሉ አልጋይና ፋንጋይ ናቸው ማለት ይቻላል። እውነተኞች አይደሉምና ።

#እርሷ_እመቤታችን እንኳን ስለራሷ በትንቢት የተጻፈውን ባነበበች ጊዜ ከዚህች ቅድስት ሴት ከዘመኗ ደርሼ ውኃ ቀድቼ እንጨት ፈልጬ ገረዷ ሆኜ ባገለገልኳት ብላ በትህትና ገረድነትን ተመኘች እንጂ እኔ በሆኩ አላለችም ጊዜው ደርሶም መላእኩ ገብርኤል መጥቶ አምላክን ለመውለድ በተገባ ተገኝተሻል ብሎ የመውለዷን ዜና ሲያበሥራት እንኳ ይህ እንዴት ይሆንልኛል እኔ #የእግዚአብሔር ባሪያው ነኝ አለችሁ እንጂ ከወነማ ከመጣህማ ብላ በኩራት ሆና አልተናገረችሁም .....ይህ እንዴት ያለህ ትህትና ነው? የአምላክ እናቱ ነሽ እየተባሉ እራስን ገረድ ማለት! ሊቁም ይህ ትህትና ቢገርመው ልዕልናዋን ከትህትናዋ አስማምቶ " #በትህትና_የተናገርሽ ተራራ ሆይ " ብሎ ጠራት::
እውነተኛይቱ አበባ ግን አስቀድማ ዓለም ሳይፈጠር በተዘክሮተ ፈጣሪ ዋላም ዓለም ከተፈጠረ በኃላ በነቢያት ትንቢት በሐዋርያት ስብከት በደቂቀ አዳም ልብ የነበረች፣ ያለችና ፣የምትኖር የማደርቅና የማጠወልግ እንቡጥ አበባ ነች።
#አበባ የዓይን ማረፊያ የልብ ተስፋ የአፍንጫ መዐዛ ነው እመቤታችንም አስቀድማ ለእናት ለአባትዋ በኃላም ለደቂቀ አዳም ሁሉ የዓይን ማረፊያ የልብ ተስፋ የነፍስ መዐዛ ነች " #ከዕሴይ_ሥር የወጣሽ መዐዛሽ ያማረ አበባ አንቺ ነሽ " እንዳለ ሊቁ #ውዳሴ_ማርያም ዘእሁድ ኢሳ11÷1
#አበባ መድኃኒትን ያስገኛል እውነተኛይቱ አበባ እመቤታችንም መዳኒ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስን አስገኝታለች እስለዚህ " እሙ ለመዳኒት" የመዳኒት እናት ትባላለችና አባባ ነች ሉቃ 2÷10-11
አበባ ንብቦችን ይስባል ማርን ያሰራል እውነተኛይቱ አበባ እመቤታችንም ወልድ ክርስቶስን ስባለች ማር የሆነች የወንጌል ሕግን አሰርታለች። ማር ጥዑም ነው ክርስቶስና ወንጌልም ጥዑማን ናቸው አንድም ማር መድኃኒት ነው ክርስቶስ እና ወንጌልም መድኃኒት ናቸው::"ከያዕቆብ ድንኳኖች ይልቅ፥ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወድዳቸዋል" መዝ 86(87)÷2
"ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና" መዝ 44(45)÷10-11
አበባ ምግበ ሥጋን ያስገኛል (ለምሳሌ አበባ ጎመን የመሰሉ ተክሎች ወዘተ...) እውነተኛይቱ አባ እመቤታችንም ምግበ ሥጋወነፍስ የሆነ ክርቶስን አስገኝታለች ዮሐ 6÷56 ማቴ 26÷26
"በመኑ ወበ አምሳለ መኑ ናስተማስለኪ " እንዳሉ ሊቃውንት ድንግል ሆይ በምንና በማን እንመስልሻለን ክብርሽን የሚገልጥ ነገር አጣን ብለን በተደሞ ዝም እንበል እንጂ እመቤታችንንስ አበባ ብቻ የሚገልጣት ሆኖ አይደለም።
እንዴት? ቢሉ አበባ ከምድር ተገኝቶ በምድር ይቀራል አበባይቱ እመቤታች ግን ከምድር ብትገኝም ቅሉ የማትደርቅ የማትጠወልግ ምድራዊት ወ ሰማያዊት የሆነች ለምለም አበባ ነች።
አበባ ይልቁኑ ጽጌ ሬዳ በእህሾ የተከበበ ነው ። አበባይቱ እመቤታችን ግን የጥንተ አብሶ እሾህ ያልከበባት ንፁህ ጽጌ ሬዳ ናት። ወርቅ ከመሬት ከጭቃ ይገኛል ነገር ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችንም ከምድር የተገኘች ሆና ሳለ ግን ምድራዊ በደል ያላቆሸሻት እሾህ አልባ የወርቅ አበባ ነች ለይቶ ቀድሷታልና “ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ።” መዝ45(46)፥4
አበባ መድኃኒት ቢያስገኝ ከጊዜያዊ ሕመም የሚያድን ጊዜያዊ መድኃኒት ነው የሚያስገኘው አበባይቱ እመቤታችን ግን አንዴ ከተበላ አንዴ ከተጠጣ ዳግመኛ የማያስፈልገውን ዘላለማዊ ፍቱን መድኃኒትን ያስገኘች ሕያው አበባ ነች።
አንድ ንጥል አበባ ዘሩን የሚተካው ወንዴና ሴቴ የተባሉ ክፍሎቹን በመጠቀም ነው የወንዴው ብናኝ ጊዜውን ጠብቆ እራሱን ሲያበን ማጣበቅ የሚችለው የሴቴ ክፍል ብናኙን ይቀበልና ሌሎች አበቦችን ማፍራት ይጀምራል ። ይህ ሂደት ኢ ተሻጋሪ(እዛው በዛው) የማፍራት ሂደት ይባላል ። በሌላ በኩል ደግሞ የአንዱ ንጥል አበባ የወንዴ ብናኝ በንቦች ፣በወፎች፣ እንዲሁም በሰዎች ንኪኪ ወይም በንፋስ ሽውታ አማካኝነት በኖ ከራሱ የሴቴ ብናኝ ተቀባይ ውጪ ተሻግሮ በሌላ አበባ የሴቴ ክፍል ላይ በመጣበቅ የሚያፈራበትም መንገድ አለ ይህም ተሻጋሪ የአረባብ ዘዴ በመባል ይታወቃል ።

አበባ እንዲ ባለ መልክ ሲያብብ አማናዊቷ አበባ እመቤታችን ግን ያለ ዘርዐ ብዕሲ ያለ ወንድ ዘር ) በ ግብረ መንፈስ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ ሥራ ጸንሳ መውለድ ችላለች ስለዚህ በእጅጉ ከአበባዎች ሁሉ ትበልጣለች አልን።

"ሳይተክሏትና ውኃ ሳያጠጧት የለመለመች የአሮን በትር ነበረች #አንቺ_እንደ_እርሷ_ነሽ #ውዳሴ_ማርያም_ዘእሁድ
.......ይቆየን ............
ምልጃ ቃልኪዳኗ ከሁላችን ሕዝበ ክርስቲያኖች ጋር ለዘላለሙ ጸንቶ ይኑር ...አሜን!
ኃ/ ማርያም
ጥቅምት 1/2013 ዓ.ም
አ.አ ኢትዮጲያ
👇👇👇👇👇👇👇
#ዓውደ_ምህረት_የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit