#ሮሚዮና_ዡልየት ።
እስቲ #በትያትር ደግሞ ዘና በሉ
#ክፍል_አንድ
ካፑሌና ፡ ሞንታግ ፡ ሁለት ፡ ባላባቶች ፡
ሆነው ፡ የሚኖሩ፡ ሁል ፡ ጊዜ ፡ ጠላቶች ፡
የእነሱም ፡ ወገኖች ፡ ባገረ ፡ ቬሮና ፡
ድንገት ፡ ሲገናኙ ፡ ሲያልፉ ፡ በጐዳና ፡
ጠብ ፡ እያበቀሉ ፡ በተንኰል ፡ በዘዴ ፡
ይተላለቃሉ ፡ በሰይፍ ፡ በጐራዴ ።
ሮሜዎና ዡልዬት ፡ ሁለት ፡ ልጆቻቸው ፡
በጣም ፡ ተዋደዱ ፡ ፍቅር ፡ አድሮባቸው፡
ግን ፡ አባቶቻቸው ፡ በነሱ ፡ መካከል ፡
ብርቱ ፡ ስለ ፡ ሆነ ፡ የነበረው ፡ በቀል ፡
ዕርቅን ፡ እንቢ ፡ ብለው ፡ ከቂም ፡ ስላልወጡ ፡በእነሱ ፡ ኀጢአት ፡ ልጆቹ ፡ ተቀጡ ።
ሆኖ ፡ የተገኘ ፡ ባገረ ፡ ቬሮና፡
እጅግ ፡ የሚያሳዝን ፡ የሚያስለቅስ ፡ ዜና ፡
አንባቢ፡ ተመልከት ፥ እንግዲህ፡ አስተውለው፤የምናቀርብልህ ፡ ታሪኩ ፡ ይኸ ፡ ነው ።
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
#በቤሮና_ከተማ_አውራ_መንገድ_ላይ
#ሶምሶንና ፡ #ጎርጎርዮስ ፡
#ሶምሶን
ዛሬ ፡ ሣር ፡ ቅጠሉ ፡ ዐፈርና ፡ ሙጃ ፡
ደም ፡ ደም ፡ ይሸተኛል ፡ ምክንያቱን ፡ እንጃ ።
#ጎርጎርዮስ
የሞንታግ ፡ ወገኖች ፡ ሸተውህ ፡ ይሆናል
#ሶምሶን ።
የነሱማ ፡ ጠረን ፡ በሩቅ ፡ ይቀረናል ።
#ጎርጎርዮስ ።
ምን ፡ ታደርግ ፡ ኖሯል ፡ አሁን ፡ ብቅ ፡ ቢሉ ?
#ሶምሶን ።
ኣይዞህ ፥ በኔ ፡ በኩል ፡ አይነሣም ፡ ጥሉ ፡
ግን ፡ እኔ ፡ በሰላም ፡ ብሄድም ፡ ዐርፌ ፡
ሳይጣላ ፡ አይቀርም ፡ ዐመለኛው ፡ ሰይፌ
#ጎርጎርዮስ
አይጠረጠርም ፤ መቼም ፡ ካየናቸው ፤
እነሱም ፡ አይለቁን ፥ እኛም አንተዋቸው ።
#ሶምሶን ።
እኔማ ፡ እንኳንስ ፡ እነሱን ፡ አይቼ ፡
ውሻቸውን ፡ ሳየው ፡ በድንገት ፡ አግኝቼ ፡
ያንቀጠቅጠኛል ፡ ደሜ ፡ እየተቈጣ ።
#ጎርጎርዮስ ።
ከሞንታግ ፡ አሽከሮች ፡ ያው ፡ አንደኛው ፡ መጣ ፡አንዱም፡ተከተለ ፡ ብቅ፡አሉ፡ሁለቱ ።
#ሶምሶን ።
ይንቀሳቀስ ፡ ጀመር ፡ የሰይፌ፡ ስለቱ ።
#ጎርጎርዮስ ።
እንግዲህ ፡ ተጠንቀቅ ፡ ሶምሶን ፡ ተሰናዳ
#ሶምሶን ።
ብቻ ፡ እንዳያገኘን ፡ የዳኝነት ፡ ዕዳ ፡
አንድ፡ ዘዴ ፡ እናምጣ ፡ ጠቡን ፡ እንዲያነሡ ፡እዚህ ፡ ከኛ ፡ አጠገብ ፡ ጠብቄ ፡ ሲደርሱ ፡ ፊቴን ፡ ወደ ፡ እነሱ ፡ እንዲያዩኝ ፡ መልሼ ፡
አስቆጣቸዋለሁ ፡ ከንፈሬን ፡ ነክሼ ።
( #አብርሃምና #ቤልሻጥር #መጡ ) ።
👇👇
#አብርሃም ።
አንተ ፡ በኛ ፡ ነው ፡ ወይ ፡ ከንፈር ፡ የምትነክሰው ፤
#ሶምሶን ።
እኔን ፡ አይጠይቅም ፡ እንዳንተ ፡ ያለ ፡ ሰው ።
#አብርሃም ።
በኛ፡ ላይ ፡ እንደሆን ፡ ንገረኝ ፡ በፍጥነት ፡
#ሶምሶን ።
መጠየቅ ፡ አያሻም፡ ከኖረህ ፡ ወንድነት ።
#አብርሃም ።
ሁሉም ፡ በጃቸው ፡ ነው ፡ ሻምላ ፡ ሆነ ፡ ሰይፉም ፤
#የሞንታግ ፡ ወገኖች ፡ ተሰድበው ፡ አያልፉም ።
#ሶምሶን ።
የት ፡ አይተሃል ፡ ቀርተው ፡መዋጋት ፡ ሳያውቁ ፤
#የካፑሌ ፡ አሽከሮች ፡ በናንተ ፡ ሲጠቁ ?
#አብርሃም ።
ሊታይ ፡ ነው ፡ እኮ ፡ የናንተ ፡ ጕብዝና ፤
#ሶምሶን ።
መች፡ አጣህ ፡ መሆኑን ፡ የኛ ፡ ወገን ፡ ጀግና ።
( #ውግያ' #ይገጥማሉ )
#ቤንቮሊዎ ። (ይመጣል) ።
ያላንድ ፡ ምክንያት ፡ በከንቱ ፡ ሳይቸግር ፡
አሁን ፡ ምን ፡ ይባላል ፡ የናንተ ፡ ግርግር ።
ሁል ፡ ጊዜ ፡ ጧት ፡ ማታ ፡ ስታልፉ፡ በመንገድ ፡ልማድ ፡ ሆነባችሁ ፡ ደርሶ ፡ ማንገራበድ ።
ለማምጣት ፡ ነው ፡ እኮ ፡ በናንት ፡ የተነሣ
በጌቶቻችሁ ፡ ላይ ፡ የዳኛ ፡ ወቀሣ።
#ቲባልት ፡ (ሻምላውን መዞ እያወዛወዘ ' መጣ )
እየው ፡ ቤንቮሊዎ ፡ ጥላውን ፡ ዘርግቶ
ሞት ፡ የያዘ ፡ ሻሞላ ' በራስህ ፡ ላይ፡ መጥቶ ፡ ተመልከት ፡ ሲያንዣብብ ፡ እንደ ፡ ጆፌ አሞራ
#ቤንቮሊዎ ።
መንፋትህ ፡ ይቅርና ፡ የማይረባ ፡ ጉራ
እንገላግላቸው ፡ ይልቅ ፡ ተረዳድተን ።
#ቲባልት ።
ልገጥምህ ፡ ነውና ፡ የመጣሁት ፡ አንተን ፡
ይልቅ ፡ ተሰናዳ ፡ ሻምላህን ፡ ምዘዘው ፤
ሳትዋጋ ፡ እንዳትሞት ፡ ቶሎ ፡ በጅህ 'ያዘው "
ቲባልት ፡ ሻምላ ፡ መዞ ፡ እጁን ፡ ከዘረጋ ፡
ሊመለስ ፡ አይችልም ፡ ጠላቱን ፡ ሳይወጋ
ወይም ፡ ደግሞ ፡ ራሱ ፡ ቀድሞ ፡ ካልወደቀ ።
#ቤንቮሊዎ ።
ፉከራህ ፡ ከንቱ ፡ ነው፡ በጣም ፡ የተናቀ ።
(#ውጊያ #ይገጥማሉ) ።
#ሞንታግ ፡ (መጣ)
ወገኖቼ ፡ ሁሉ ፡ ድረሱ ፡ በፍጥነት ፤
እነሆ ፡ ሰዎቼን ፡ ፈጁዋቸው ፡ በድንገት ።
💫ይቀጥላል💫
እስቲ #በትያትር ደግሞ ዘና በሉ
#ክፍል_አንድ
ካፑሌና ፡ ሞንታግ ፡ ሁለት ፡ ባላባቶች ፡
ሆነው ፡ የሚኖሩ፡ ሁል ፡ ጊዜ ፡ ጠላቶች ፡
የእነሱም ፡ ወገኖች ፡ ባገረ ፡ ቬሮና ፡
ድንገት ፡ ሲገናኙ ፡ ሲያልፉ ፡ በጐዳና ፡
ጠብ ፡ እያበቀሉ ፡ በተንኰል ፡ በዘዴ ፡
ይተላለቃሉ ፡ በሰይፍ ፡ በጐራዴ ።
ሮሜዎና ዡልዬት ፡ ሁለት ፡ ልጆቻቸው ፡
በጣም ፡ ተዋደዱ ፡ ፍቅር ፡ አድሮባቸው፡
ግን ፡ አባቶቻቸው ፡ በነሱ ፡ መካከል ፡
ብርቱ ፡ ስለ ፡ ሆነ ፡ የነበረው ፡ በቀል ፡
ዕርቅን ፡ እንቢ ፡ ብለው ፡ ከቂም ፡ ስላልወጡ ፡በእነሱ ፡ ኀጢአት ፡ ልጆቹ ፡ ተቀጡ ።
ሆኖ ፡ የተገኘ ፡ ባገረ ፡ ቬሮና፡
እጅግ ፡ የሚያሳዝን ፡ የሚያስለቅስ ፡ ዜና ፡
አንባቢ፡ ተመልከት ፥ እንግዲህ፡ አስተውለው፤የምናቀርብልህ ፡ ታሪኩ ፡ ይኸ ፡ ነው ።
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
#በቤሮና_ከተማ_አውራ_መንገድ_ላይ
#ሶምሶንና ፡ #ጎርጎርዮስ ፡
#ሶምሶን
ዛሬ ፡ ሣር ፡ ቅጠሉ ፡ ዐፈርና ፡ ሙጃ ፡
ደም ፡ ደም ፡ ይሸተኛል ፡ ምክንያቱን ፡ እንጃ ።
#ጎርጎርዮስ
የሞንታግ ፡ ወገኖች ፡ ሸተውህ ፡ ይሆናል
#ሶምሶን ።
የነሱማ ፡ ጠረን ፡ በሩቅ ፡ ይቀረናል ።
#ጎርጎርዮስ ።
ምን ፡ ታደርግ ፡ ኖሯል ፡ አሁን ፡ ብቅ ፡ ቢሉ ?
#ሶምሶን ።
ኣይዞህ ፥ በኔ ፡ በኩል ፡ አይነሣም ፡ ጥሉ ፡
ግን ፡ እኔ ፡ በሰላም ፡ ብሄድም ፡ ዐርፌ ፡
ሳይጣላ ፡ አይቀርም ፡ ዐመለኛው ፡ ሰይፌ
#ጎርጎርዮስ
አይጠረጠርም ፤ መቼም ፡ ካየናቸው ፤
እነሱም ፡ አይለቁን ፥ እኛም አንተዋቸው ።
#ሶምሶን ።
እኔማ ፡ እንኳንስ ፡ እነሱን ፡ አይቼ ፡
ውሻቸውን ፡ ሳየው ፡ በድንገት ፡ አግኝቼ ፡
ያንቀጠቅጠኛል ፡ ደሜ ፡ እየተቈጣ ።
#ጎርጎርዮስ ።
ከሞንታግ ፡ አሽከሮች ፡ ያው ፡ አንደኛው ፡ መጣ ፡አንዱም፡ተከተለ ፡ ብቅ፡አሉ፡ሁለቱ ።
#ሶምሶን ።
ይንቀሳቀስ ፡ ጀመር ፡ የሰይፌ፡ ስለቱ ።
#ጎርጎርዮስ ።
እንግዲህ ፡ ተጠንቀቅ ፡ ሶምሶን ፡ ተሰናዳ
#ሶምሶን ።
ብቻ ፡ እንዳያገኘን ፡ የዳኝነት ፡ ዕዳ ፡
አንድ፡ ዘዴ ፡ እናምጣ ፡ ጠቡን ፡ እንዲያነሡ ፡እዚህ ፡ ከኛ ፡ አጠገብ ፡ ጠብቄ ፡ ሲደርሱ ፡ ፊቴን ፡ ወደ ፡ እነሱ ፡ እንዲያዩኝ ፡ መልሼ ፡
አስቆጣቸዋለሁ ፡ ከንፈሬን ፡ ነክሼ ።
( #አብርሃምና #ቤልሻጥር #መጡ ) ።
👇👇
#አብርሃም ።
አንተ ፡ በኛ ፡ ነው ፡ ወይ ፡ ከንፈር ፡ የምትነክሰው ፤
#ሶምሶን ።
እኔን ፡ አይጠይቅም ፡ እንዳንተ ፡ ያለ ፡ ሰው ።
#አብርሃም ።
በኛ፡ ላይ ፡ እንደሆን ፡ ንገረኝ ፡ በፍጥነት ፡
#ሶምሶን ።
መጠየቅ ፡ አያሻም፡ ከኖረህ ፡ ወንድነት ።
#አብርሃም ።
ሁሉም ፡ በጃቸው ፡ ነው ፡ ሻምላ ፡ ሆነ ፡ ሰይፉም ፤
#የሞንታግ ፡ ወገኖች ፡ ተሰድበው ፡ አያልፉም ።
#ሶምሶን ።
የት ፡ አይተሃል ፡ ቀርተው ፡መዋጋት ፡ ሳያውቁ ፤
#የካፑሌ ፡ አሽከሮች ፡ በናንተ ፡ ሲጠቁ ?
#አብርሃም ።
ሊታይ ፡ ነው ፡ እኮ ፡ የናንተ ፡ ጕብዝና ፤
#ሶምሶን ።
መች፡ አጣህ ፡ መሆኑን ፡ የኛ ፡ ወገን ፡ ጀግና ።
( #ውግያ' #ይገጥማሉ )
#ቤንቮሊዎ ። (ይመጣል) ።
ያላንድ ፡ ምክንያት ፡ በከንቱ ፡ ሳይቸግር ፡
አሁን ፡ ምን ፡ ይባላል ፡ የናንተ ፡ ግርግር ።
ሁል ፡ ጊዜ ፡ ጧት ፡ ማታ ፡ ስታልፉ፡ በመንገድ ፡ልማድ ፡ ሆነባችሁ ፡ ደርሶ ፡ ማንገራበድ ።
ለማምጣት ፡ ነው ፡ እኮ ፡ በናንት ፡ የተነሣ
በጌቶቻችሁ ፡ ላይ ፡ የዳኛ ፡ ወቀሣ።
#ቲባልት ፡ (ሻምላውን መዞ እያወዛወዘ ' መጣ )
እየው ፡ ቤንቮሊዎ ፡ ጥላውን ፡ ዘርግቶ
ሞት ፡ የያዘ ፡ ሻሞላ ' በራስህ ፡ ላይ፡ መጥቶ ፡ ተመልከት ፡ ሲያንዣብብ ፡ እንደ ፡ ጆፌ አሞራ
#ቤንቮሊዎ ።
መንፋትህ ፡ ይቅርና ፡ የማይረባ ፡ ጉራ
እንገላግላቸው ፡ ይልቅ ፡ ተረዳድተን ።
#ቲባልት ።
ልገጥምህ ፡ ነውና ፡ የመጣሁት ፡ አንተን ፡
ይልቅ ፡ ተሰናዳ ፡ ሻምላህን ፡ ምዘዘው ፤
ሳትዋጋ ፡ እንዳትሞት ፡ ቶሎ ፡ በጅህ 'ያዘው "
ቲባልት ፡ ሻምላ ፡ መዞ ፡ እጁን ፡ ከዘረጋ ፡
ሊመለስ ፡ አይችልም ፡ ጠላቱን ፡ ሳይወጋ
ወይም ፡ ደግሞ ፡ ራሱ ፡ ቀድሞ ፡ ካልወደቀ ።
#ቤንቮሊዎ ።
ፉከራህ ፡ ከንቱ ፡ ነው፡ በጣም ፡ የተናቀ ።
(#ውጊያ #ይገጥማሉ) ።
#ሞንታግ ፡ (መጣ)
ወገኖቼ ፡ ሁሉ ፡ ድረሱ ፡ በፍጥነት ፤
እነሆ ፡ ሰዎቼን ፡ ፈጁዋቸው ፡ በድንገት ።
💫ይቀጥላል💫
#ሮሜዎና_ዡልዬት
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
የካፑሌ ፡ ሚስት (የዡልዬት እናት)
ወዴት ፡ ነው ፡ ያለሽው ፡ ልጄ ፡ ተነሣሽ ፡ ወይ ?
#ዡልዬት።
ይኸው ፡ ተነሣሁኝ ፡ ምነው ፡ እናቴ ሆይ ?
(ለብቻዋ ፡ ቀስ ብላ)
ምን ፡ ነካት ፡ እናቴ ፡ እንዲህ ፡ ጧት ፡ ተነሥታ ፈልጋኝ አታውቅም በማለዳ መጥታ ።
(የካፑሌ ሚስት ' ወደልጅዋ፡ወደ፡ዡልዬት መኝታ' ቤት፡ገባች
#የካፑሌ_ሚስት ።
ዐፈር ፡ አስመሰለሽ ፡ የቲባልት ፡ ሐዘን ፡
ያስፈልጋል ፡ ልጄ ፡ ማሰብ ፡ ማመዛዘን '
እንባ ፡ ቢያፈሱለት ፡ ቢያለቅሱለት በጣም
ሰው ፡ አንዴ ከሞተ ተመልሶ ፡ አይመጣም
ሐዘን ፡ የሚያስረሳ ፡ ደስ ፡ የሚያሰኝ ፡ ወሬ
ይዤ ፡ ወዳንቺ ፡ ዘንድ ፡ መጥቻለሁ' ዛሬ "
#ዡልዬት ።
እናቴ ፡ ንገሪኝ ፡ እንደ ፡ ምን ፡ ያለ ፡ ነው ?
#የካፑሌ_ሚስት ።
በቲባልት ፡ መሞት ፡ በብዙ ፡ ያዘነው ፡
ልብሽ ፡ እንዲጽናና ፡ በጣም ፡ በማሰቡ ፡
መልካሙ ፡ አባትሽ ፡ አላረፈም ፡ ልቡ ፤
በዚሁ ፡ ምክንያት ፡ ሳይውልም ፡ ሳያድር ፡
ቈርጧል ለጥሩ ባል ኀሙስ አንቺን ሊድር
ባልሽ ፡ የሚሆነው ቆንዦ ነው ፡ ጌታ ሰው
በዘርም ፡ በገንዘብ ፡ ምንም ፡የማያንሰው !
እንዲያውም ፡ ገልጨ ፡ ልንገርሽ ፡ ካሁኑ ፤
መልካሙ ፡ፓሪስ ፡ ነው ፡ ወጣት ፡ መኰንኑ
#ዡልዬት ።
እናቴ ፡ ሆይ ፡ምነው ፡ በፊት ፡ ሳንማከር ፡
እንደ ፡ ምን ፡ ይሆናል ፡ እንዲህ ያለ ፡ ነገር
አስቀድመን ፡ እኛ ፡ ተጫጭተን ፡ በደንቡ፡
ሳላውቀው ሳያውቀኝ ፡በፍጥነት ፡ ተጋቡ !
እንዴት ፡ ትላላችሁ ፡ እንዲህ ፡ በችኰላ ?
አሁንም ፡ በቶሎ ፡ ፈልጉለት ፡ መላ'
እኔ ፡ አልችልምና ፡ ለማግባት ፡ በቶሎ ፤
አባቴን 'ንገሪው ፡ እንደ ፡ ምንም ፡ ብሎ
ቃል ቢኖር ምናልባት ለፓሪስ የሰጠው
አንድ' ዘዴ ፡ ፈጥሮ ፡ ቶሎ ፡እንዲለውጠው
#የካፑሌ_ሚስት ።
አፍሽን ፡ አታጥፊ ፡ ምክንያት ፡ አታምጪ '
ያለቀ ፡ ነገር ፡ ነው ፡ ዐርፈሽ ፡ ተቀመጪ ።
#ዡልዬት ።
አድምጪኝ ፡ እናቴ ፡ እንግዲያውስ ፡ ስሚ
አባቴም ፡ አይልፋ ፡ አንቺም ፡ ኣትድከሚ'
የመጣ ፡ ቢመጣ ፡ መቼም ፡ቢሆን ደግሞ
እኔ ፡ አላገባም ፡ ፓሪስን ፡ ፈጽሞ ።
#የካፑሌ_ሚስት ።
አልገባም ፡ ጨርሼ ፡ እኔ ፡ በዚህ ፡ ጣጣ ፤
ንገሪው ፡ ላባትሽ ፡ ይኸው ፡ወዲህ ፡ መጣ
#ካፑሌ ፡ (ገባ)
ምነው ፡ ምን ሆናችሁ ? በይ ልመለስ ሄጄ
ታዲያስ ፡ ነገርሻት ፡ ወይ ነገሩን ፡ ለልጄ ?
#የካፑሌ_ሚስት ።
እኔ ፡ ከሷ'ጋራ ፡ አልችልም ፡ ክርክር ፤
ትችል ፡ እንደ ፡ ሆነ ፡አስረዳት ፡ በምክር ።
#ካፑሌ ።
እስቲ ፡ እኮ ፡ ንገሪኝ ፡ ምንድነው ፡ ነገሩ ፡
አሁን ፡ ምን ፡ ይባላል ፡ ደርሶ ፡ ግርግሩ ።
#የካፑሌ_ሚስት
ትችል ፡ ትመስላለህ አንተ ፡ ደግሞ ፡ ደርሶ
የምሥራች ፡ « እንቢ» ፡ ብላለች ፡ ጨርሶ ፡
የመጣ ፡ ቢመጣ ፡ ይልቁንም ፡ ደግሞ ፡
አላገባም ፡ አለች ፡ ፓሪስን ፡ ፈጽሞ ።
#ካፑሌ ።
እግራችንን ፡ ስማ ፡ እኛን ፡ አመስግና ፡
በትልቅ ፡ ደስታ ፡ መቀበል 'ቀረና ፡
እንቢ ፡ አለች ፡ ብትይኝ ጆሮዬም ፡ አይሰማ
እስቲ ፡ ልስማው ፡ እኔ ፡ ትናገረው ፡ ደግማ
#ዡልዬት ።
ለክፋት ፡ አይደለም ፡ አትቈጣ ፡ አባቴ ።
#ካፑሌ ።
እረግ ፡ የኛ ፡ ሕፃን ፡ ትንሿ ፡ ማሚቴ ፡
የማነሽ ፡ ለዛ ፡ ቢስ ፡ የማነሽ ፡ ወልጋዳ ፤
የማነሽ ፡ አመዳም ፡ የማነሽ ፡ ገዳዳ'
ባለወግ ፡ አድርገን እኛ ፡ ነን ያጠፋን ፡
ብታውቂው ፡ ባታውቂው ኧረ ምን ፡ አለፋን
በግድ፡ ነው ፡ እንጂ፡ በኅይል ፡ የምንድር ፡
መች ፡ ያስፈልግና ፡ ይህ ፡ ሁሉ ፡ንግግር
ነገ ፡ በማለዳ ፡ ተዘጋጅተሽ ፡ ውጪ ፣
ከተክሊሉ ፡ ቦታ ፡ ዐውቀሽ ' እንድትመጪ,
ታዛዤ ፡ ነሽና ፡ የወለድኩሽ ፡ ልጄ ፣
እኔ ፡ እድርሻለሁ ፡ በኀይል' አስገድጄ ፤
ለወግ ፡ መጠየቄ ፡ ቅብጠት ፡ነው ፡ አብጄ
እስከዚያ ፡ ድረስ ፡ ግን ፡ በፊቴ ፡ አትለፊ ፤
ዐይንሽን ፡ አልየው ፡ ካጠገቤ ፡ ጥፊ ።
#ዡልዬት ።
ነገሩን ፡ ላስረዳህ ፡ አባቴ ፡ አድምጠኝ ፤
ጋብቻው ፡ ፈጠነ ፡ ጥቂት ፡ ጊዜ ፡ ስጠኝ
#ካፑሌ ።
ነገርሽ እሬት ነው ፡ መሪር ነው ፡ ኮምጣጣ
ካፍሽ ፡ ካንደበትሽ ፡ አንድ ፡ቃል፡ አይውጣ'
ሴት ልጅ እንቢ፡ብትል፡አለው አንድ አገባብ
መች ተሠርቶ ያውቃል እንዲህ፡ያለ ጥጋብ
ዘሩ ፡ የታወቀ ነዉ መልኩ ፡ የሚያኰራ ፡
ገንዘብ ፡ የተረፈው ፡ ስሙ ፡ የተጠራ፡
ደኅና ፡ ባል ፡ ፈልጎ ፡ በስንት ፡ መከራ፡
አባቷ ፡ ሲያመጣ ፡ ወዲያ ፡ ወዲህ ፡ ዞሮ '
ከቤት ፡ ተወዝፋ ፡ የኛ ፡ ሴት ፡ ወይዘሮ ፡
እኔ ፡ ባል ፡ አልሻም ፡ ትላለች ፡ ሞጋጌ ፤
መካን ፡ ሰው ፡ ይሻላል ከመውለድ ፡ ባለጌ
ጥኀጋብሽ ፡ ነው ፡ እኮ ደሜን ፡ የሚያፈላው ፤
ምኑ ፡ ነው ፡ እባክሽ ፡ፓሪስ ፡ የሚጠላው ?
ያለባል ፡ ለመኖር ፡ ከሆንሽ ፡
የምትወጂ ፡
ምን ፡ ቸገረኝ፡ እኔ ፡ ወደ ፡ ገዳም ፡ሂጂ ፡
ነገር ፡ ግን ፡ ከሆነ ፡ ማግባትሽ ፡ የማይቀር ፡
የመረጥኩልሽን ፡ ይገባሻል ፡ ማፍቀር ፡
ያላንድ ፡ ክርክር ፡ ያላንድ ፡ ቅሬታ ፡
ፈቃዴን ፡ መቀበል ፡ አለብሽ ፡ ግዴታ ።
የምትይ ፡ ከሆነ ፡ የኔን ፡ ፈቃድ ፡ እንቢ ፡
ከዛሬ ፡ ጀምረሽ ፡ ሂጂ ፡ ገደል ፡ ግቢ ፤
ዐይንሽን ፡ አልየው ፡ በዚህ ፡ በኔ ፡ ግቢ ።
የካፑሌ ፡ ሚስት ።
ቀስ ፡ ብሎ ፡ ነው ፡ እንጂ ፡ አባት ፡ ከመከረ ፡
አንተም ፡ አበዛኸው ፡ ነገርህ ፡ ከረረ ።
ካፑሌ ።
አትግቢ ፡ ፈጽሞ ፡ አንቺ ፡ በኔ ፡ ሥራ ፤
ሂጂ ፡ ወደ ፡ ጓዳ ፡ ከሴቶቹ ፡ ጋራ ፡
ቀኑን ፡ ሙሉ ፡ ባሳብ ፡ ሌሊቱን ፡ በሕልሜ ፡
ባል ፡ ስፈልግላት ፡ በመኖር ፡ ደክሜ ፡
በስንት 'ዐይነት ፡ ዘዴ ፡ እኔ ፡ ተጣጥሬ፡ .
እግዚአብሔር ረድቶኝ ፡ ይኸውና ፡ ዛሬ ፡
የሚሆን ፡ ሰው ፡ ባገኝ ፡ ጨዋ ፡ባለገንዘብ፡
እሜቴ ፡ ፈጠሩ ፡ ሠላሳ ፡ ሺሕ፡ ሰበብ ።
ስሚኝ፡ እኔ ፡ ደግሞ ፡ ልንገርሽ ፡ ካሁኑ፤
እሱን ፡ ካላገባሽ ፡ ታዘቢኝ ፡ በውኑ
የትም ፡ ትሄጃለሽ ፡ አብርሬሽ፡ ከቤቴ፤
እርሜን ፡ አወጣለሁ ፡ ቆርጬሽ ፡ ካንጀቴ
ልጅና ፡ አባት ፡ ሆነን ፡ መኖራችን ፡ ቀርቶ ፡
ክጄሽ ፡ ትሄጃለሽ ፡ አልምርሽም ፡ ከቶ ፡
ስለዚህ ፡ አስቢ፡ ከልብሽ ፡ ምከሪ፤
የሚከተለውን ፡ ተመልክተሽ ፡ ፍሪ'
ካሁኑ ፡ ጀምረሽ ፡ በነገሩ፡ ሥጊ፤
ቃሌ ፡ አይታጠፍም ፡ ኋላ ፡ ልብ ፡ አድርጊ
(ካፑሌ "ከቤት " ወጥቶ ሄደ)
#ዡልዬት ።
እባክሽ ፡ እናቴ ፡ ለልጅሽ ፡ እዘኚ፤
ባይሆን ፡እንኳን ፡ አንቺ ፡ ከኔ ፡ ወገን ፡ ሁኚ'
ቀኑ ፡ ረዘም ፡ ይበል ጥቂት ፡ ጊዜ ስጡኝ፤
አሳቤን ፡ ሳታውቁ ፡ በከንቱ ፡ አትቁጡኝ ።
ግዴታ፡ ካልሆነ' በጣም ' ካልቸረኝ፡
እንቢ ፡ አልልምና ፡ ምክንያት ፡ ካልኖረኝ ።
#የካፑሌ_ሚስት ።
ዕዳሽን ፡ በጨርቅሽ ፡ እንደምትፈልጊ '
አንቺ ፡ እንደ ፡ ፈቃድሽ 'እንዳሻሽ አድርጊ ።
(እናቷም' ወጥታ ሄደች)
#ዡልዬት ።
ርጂኝ ፡ አንቺ ፡ እባክሽ ፡ ምከሪኝ ፡
#ሞግዚቴ ፤
ምስጢር፡ ተካፋዬ፡አንቺ፡ነሽ ፡እናቴ '
የኛን ተክሊል ማንም አይችልም፡ሊያፈርሰው፡
ዳሩ ፡ ግን ፡ድብቅ ፡ ነው አያውቅም፡ማንም፡ሰው፡
እባክሽ ፡ ምከሪኝ ፡ ዘዴ ፡ አታጭምና ፤
ጨነቀኝ ፡ ጠበበኝ'አገኘኝ ፡ ፈተና ።
#ሞግዚት ።
ቃሌን ፡ ብትሰሚ ፡ ተራዬን ፡ ልናገር ፤
ሮሜዎ ፡ ሰው ፡ ገድሎ ፡ ተሰደደ ፡ ካገር፡
ልትኖሩ ፡ ከሆነ ፡ ለብቻ ፡ ለብቻ ፡
በዚሁ ፡ ይፈርሳል ፡ የናንተ ፡ ጋብቻ ፡
በዚሁ ፡ ላይ ፡ ደግሞ ፡ አባትሽ ፡ ላባቱ
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
የካፑሌ ፡ ሚስት (የዡልዬት እናት)
ወዴት ፡ ነው ፡ ያለሽው ፡ ልጄ ፡ ተነሣሽ ፡ ወይ ?
#ዡልዬት።
ይኸው ፡ ተነሣሁኝ ፡ ምነው ፡ እናቴ ሆይ ?
(ለብቻዋ ፡ ቀስ ብላ)
ምን ፡ ነካት ፡ እናቴ ፡ እንዲህ ፡ ጧት ፡ ተነሥታ ፈልጋኝ አታውቅም በማለዳ መጥታ ።
(የካፑሌ ሚስት ' ወደልጅዋ፡ወደ፡ዡልዬት መኝታ' ቤት፡ገባች
#የካፑሌ_ሚስት ።
ዐፈር ፡ አስመሰለሽ ፡ የቲባልት ፡ ሐዘን ፡
ያስፈልጋል ፡ ልጄ ፡ ማሰብ ፡ ማመዛዘን '
እንባ ፡ ቢያፈሱለት ፡ ቢያለቅሱለት በጣም
ሰው ፡ አንዴ ከሞተ ተመልሶ ፡ አይመጣም
ሐዘን ፡ የሚያስረሳ ፡ ደስ ፡ የሚያሰኝ ፡ ወሬ
ይዤ ፡ ወዳንቺ ፡ ዘንድ ፡ መጥቻለሁ' ዛሬ "
#ዡልዬት ።
እናቴ ፡ ንገሪኝ ፡ እንደ ፡ ምን ፡ ያለ ፡ ነው ?
#የካፑሌ_ሚስት ።
በቲባልት ፡ መሞት ፡ በብዙ ፡ ያዘነው ፡
ልብሽ ፡ እንዲጽናና ፡ በጣም ፡ በማሰቡ ፡
መልካሙ ፡ አባትሽ ፡ አላረፈም ፡ ልቡ ፤
በዚሁ ፡ ምክንያት ፡ ሳይውልም ፡ ሳያድር ፡
ቈርጧል ለጥሩ ባል ኀሙስ አንቺን ሊድር
ባልሽ ፡ የሚሆነው ቆንዦ ነው ፡ ጌታ ሰው
በዘርም ፡ በገንዘብ ፡ ምንም ፡የማያንሰው !
እንዲያውም ፡ ገልጨ ፡ ልንገርሽ ፡ ካሁኑ ፤
መልካሙ ፡ፓሪስ ፡ ነው ፡ ወጣት ፡ መኰንኑ
#ዡልዬት ።
እናቴ ፡ ሆይ ፡ምነው ፡ በፊት ፡ ሳንማከር ፡
እንደ ፡ ምን ፡ ይሆናል ፡ እንዲህ ያለ ፡ ነገር
አስቀድመን ፡ እኛ ፡ ተጫጭተን ፡ በደንቡ፡
ሳላውቀው ሳያውቀኝ ፡በፍጥነት ፡ ተጋቡ !
እንዴት ፡ ትላላችሁ ፡ እንዲህ ፡ በችኰላ ?
አሁንም ፡ በቶሎ ፡ ፈልጉለት ፡ መላ'
እኔ ፡ አልችልምና ፡ ለማግባት ፡ በቶሎ ፤
አባቴን 'ንገሪው ፡ እንደ ፡ ምንም ፡ ብሎ
ቃል ቢኖር ምናልባት ለፓሪስ የሰጠው
አንድ' ዘዴ ፡ ፈጥሮ ፡ ቶሎ ፡እንዲለውጠው
#የካፑሌ_ሚስት ።
አፍሽን ፡ አታጥፊ ፡ ምክንያት ፡ አታምጪ '
ያለቀ ፡ ነገር ፡ ነው ፡ ዐርፈሽ ፡ ተቀመጪ ።
#ዡልዬት ።
አድምጪኝ ፡ እናቴ ፡ እንግዲያውስ ፡ ስሚ
አባቴም ፡ አይልፋ ፡ አንቺም ፡ ኣትድከሚ'
የመጣ ፡ ቢመጣ ፡ መቼም ፡ቢሆን ደግሞ
እኔ ፡ አላገባም ፡ ፓሪስን ፡ ፈጽሞ ።
#የካፑሌ_ሚስት ።
አልገባም ፡ ጨርሼ ፡ እኔ ፡ በዚህ ፡ ጣጣ ፤
ንገሪው ፡ ላባትሽ ፡ ይኸው ፡ወዲህ ፡ መጣ
#ካፑሌ ፡ (ገባ)
ምነው ፡ ምን ሆናችሁ ? በይ ልመለስ ሄጄ
ታዲያስ ፡ ነገርሻት ፡ ወይ ነገሩን ፡ ለልጄ ?
#የካፑሌ_ሚስት ።
እኔ ፡ ከሷ'ጋራ ፡ አልችልም ፡ ክርክር ፤
ትችል ፡ እንደ ፡ ሆነ ፡አስረዳት ፡ በምክር ።
#ካፑሌ ።
እስቲ ፡ እኮ ፡ ንገሪኝ ፡ ምንድነው ፡ ነገሩ ፡
አሁን ፡ ምን ፡ ይባላል ፡ ደርሶ ፡ ግርግሩ ።
#የካፑሌ_ሚስት
ትችል ፡ ትመስላለህ አንተ ፡ ደግሞ ፡ ደርሶ
የምሥራች ፡ « እንቢ» ፡ ብላለች ፡ ጨርሶ ፡
የመጣ ፡ ቢመጣ ፡ ይልቁንም ፡ ደግሞ ፡
አላገባም ፡ አለች ፡ ፓሪስን ፡ ፈጽሞ ።
#ካፑሌ ።
እግራችንን ፡ ስማ ፡ እኛን ፡ አመስግና ፡
በትልቅ ፡ ደስታ ፡ መቀበል 'ቀረና ፡
እንቢ ፡ አለች ፡ ብትይኝ ጆሮዬም ፡ አይሰማ
እስቲ ፡ ልስማው ፡ እኔ ፡ ትናገረው ፡ ደግማ
#ዡልዬት ።
ለክፋት ፡ አይደለም ፡ አትቈጣ ፡ አባቴ ።
#ካፑሌ ።
እረግ ፡ የኛ ፡ ሕፃን ፡ ትንሿ ፡ ማሚቴ ፡
የማነሽ ፡ ለዛ ፡ ቢስ ፡ የማነሽ ፡ ወልጋዳ ፤
የማነሽ ፡ አመዳም ፡ የማነሽ ፡ ገዳዳ'
ባለወግ ፡ አድርገን እኛ ፡ ነን ያጠፋን ፡
ብታውቂው ፡ ባታውቂው ኧረ ምን ፡ አለፋን
በግድ፡ ነው ፡ እንጂ፡ በኅይል ፡ የምንድር ፡
መች ፡ ያስፈልግና ፡ ይህ ፡ ሁሉ ፡ንግግር
ነገ ፡ በማለዳ ፡ ተዘጋጅተሽ ፡ ውጪ ፣
ከተክሊሉ ፡ ቦታ ፡ ዐውቀሽ ' እንድትመጪ,
ታዛዤ ፡ ነሽና ፡ የወለድኩሽ ፡ ልጄ ፣
እኔ ፡ እድርሻለሁ ፡ በኀይል' አስገድጄ ፤
ለወግ ፡ መጠየቄ ፡ ቅብጠት ፡ነው ፡ አብጄ
እስከዚያ ፡ ድረስ ፡ ግን ፡ በፊቴ ፡ አትለፊ ፤
ዐይንሽን ፡ አልየው ፡ ካጠገቤ ፡ ጥፊ ።
#ዡልዬት ።
ነገሩን ፡ ላስረዳህ ፡ አባቴ ፡ አድምጠኝ ፤
ጋብቻው ፡ ፈጠነ ፡ ጥቂት ፡ ጊዜ ፡ ስጠኝ
#ካፑሌ ።
ነገርሽ እሬት ነው ፡ መሪር ነው ፡ ኮምጣጣ
ካፍሽ ፡ ካንደበትሽ ፡ አንድ ፡ቃል፡ አይውጣ'
ሴት ልጅ እንቢ፡ብትል፡አለው አንድ አገባብ
መች ተሠርቶ ያውቃል እንዲህ፡ያለ ጥጋብ
ዘሩ ፡ የታወቀ ነዉ መልኩ ፡ የሚያኰራ ፡
ገንዘብ ፡ የተረፈው ፡ ስሙ ፡ የተጠራ፡
ደኅና ፡ ባል ፡ ፈልጎ ፡ በስንት ፡ መከራ፡
አባቷ ፡ ሲያመጣ ፡ ወዲያ ፡ ወዲህ ፡ ዞሮ '
ከቤት ፡ ተወዝፋ ፡ የኛ ፡ ሴት ፡ ወይዘሮ ፡
እኔ ፡ ባል ፡ አልሻም ፡ ትላለች ፡ ሞጋጌ ፤
መካን ፡ ሰው ፡ ይሻላል ከመውለድ ፡ ባለጌ
ጥኀጋብሽ ፡ ነው ፡ እኮ ደሜን ፡ የሚያፈላው ፤
ምኑ ፡ ነው ፡ እባክሽ ፡ፓሪስ ፡ የሚጠላው ?
ያለባል ፡ ለመኖር ፡ ከሆንሽ ፡
የምትወጂ ፡
ምን ፡ ቸገረኝ፡ እኔ ፡ ወደ ፡ ገዳም ፡ሂጂ ፡
ነገር ፡ ግን ፡ ከሆነ ፡ ማግባትሽ ፡ የማይቀር ፡
የመረጥኩልሽን ፡ ይገባሻል ፡ ማፍቀር ፡
ያላንድ ፡ ክርክር ፡ ያላንድ ፡ ቅሬታ ፡
ፈቃዴን ፡ መቀበል ፡ አለብሽ ፡ ግዴታ ።
የምትይ ፡ ከሆነ ፡ የኔን ፡ ፈቃድ ፡ እንቢ ፡
ከዛሬ ፡ ጀምረሽ ፡ ሂጂ ፡ ገደል ፡ ግቢ ፤
ዐይንሽን ፡ አልየው ፡ በዚህ ፡ በኔ ፡ ግቢ ።
የካፑሌ ፡ ሚስት ።
ቀስ ፡ ብሎ ፡ ነው ፡ እንጂ ፡ አባት ፡ ከመከረ ፡
አንተም ፡ አበዛኸው ፡ ነገርህ ፡ ከረረ ።
ካፑሌ ።
አትግቢ ፡ ፈጽሞ ፡ አንቺ ፡ በኔ ፡ ሥራ ፤
ሂጂ ፡ ወደ ፡ ጓዳ ፡ ከሴቶቹ ፡ ጋራ ፡
ቀኑን ፡ ሙሉ ፡ ባሳብ ፡ ሌሊቱን ፡ በሕልሜ ፡
ባል ፡ ስፈልግላት ፡ በመኖር ፡ ደክሜ ፡
በስንት 'ዐይነት ፡ ዘዴ ፡ እኔ ፡ ተጣጥሬ፡ .
እግዚአብሔር ረድቶኝ ፡ ይኸውና ፡ ዛሬ ፡
የሚሆን ፡ ሰው ፡ ባገኝ ፡ ጨዋ ፡ባለገንዘብ፡
እሜቴ ፡ ፈጠሩ ፡ ሠላሳ ፡ ሺሕ፡ ሰበብ ።
ስሚኝ፡ እኔ ፡ ደግሞ ፡ ልንገርሽ ፡ ካሁኑ፤
እሱን ፡ ካላገባሽ ፡ ታዘቢኝ ፡ በውኑ
የትም ፡ ትሄጃለሽ ፡ አብርሬሽ፡ ከቤቴ፤
እርሜን ፡ አወጣለሁ ፡ ቆርጬሽ ፡ ካንጀቴ
ልጅና ፡ አባት ፡ ሆነን ፡ መኖራችን ፡ ቀርቶ ፡
ክጄሽ ፡ ትሄጃለሽ ፡ አልምርሽም ፡ ከቶ ፡
ስለዚህ ፡ አስቢ፡ ከልብሽ ፡ ምከሪ፤
የሚከተለውን ፡ ተመልክተሽ ፡ ፍሪ'
ካሁኑ ፡ ጀምረሽ ፡ በነገሩ፡ ሥጊ፤
ቃሌ ፡ አይታጠፍም ፡ ኋላ ፡ ልብ ፡ አድርጊ
(ካፑሌ "ከቤት " ወጥቶ ሄደ)
#ዡልዬት ።
እባክሽ ፡ እናቴ ፡ ለልጅሽ ፡ እዘኚ፤
ባይሆን ፡እንኳን ፡ አንቺ ፡ ከኔ ፡ ወገን ፡ ሁኚ'
ቀኑ ፡ ረዘም ፡ ይበል ጥቂት ፡ ጊዜ ስጡኝ፤
አሳቤን ፡ ሳታውቁ ፡ በከንቱ ፡ አትቁጡኝ ።
ግዴታ፡ ካልሆነ' በጣም ' ካልቸረኝ፡
እንቢ ፡ አልልምና ፡ ምክንያት ፡ ካልኖረኝ ።
#የካፑሌ_ሚስት ።
ዕዳሽን ፡ በጨርቅሽ ፡ እንደምትፈልጊ '
አንቺ ፡ እንደ ፡ ፈቃድሽ 'እንዳሻሽ አድርጊ ።
(እናቷም' ወጥታ ሄደች)
#ዡልዬት ።
ርጂኝ ፡ አንቺ ፡ እባክሽ ፡ ምከሪኝ ፡
#ሞግዚቴ ፤
ምስጢር፡ ተካፋዬ፡አንቺ፡ነሽ ፡እናቴ '
የኛን ተክሊል ማንም አይችልም፡ሊያፈርሰው፡
ዳሩ ፡ ግን ፡ድብቅ ፡ ነው አያውቅም፡ማንም፡ሰው፡
እባክሽ ፡ ምከሪኝ ፡ ዘዴ ፡ አታጭምና ፤
ጨነቀኝ ፡ ጠበበኝ'አገኘኝ ፡ ፈተና ።
#ሞግዚት ።
ቃሌን ፡ ብትሰሚ ፡ ተራዬን ፡ ልናገር ፤
ሮሜዎ ፡ ሰው ፡ ገድሎ ፡ ተሰደደ ፡ ካገር፡
ልትኖሩ ፡ ከሆነ ፡ ለብቻ ፡ ለብቻ ፡
በዚሁ ፡ ይፈርሳል ፡ የናንተ ፡ ጋብቻ ፡
በዚሁ ፡ ላይ ፡ ደግሞ ፡ አባትሽ ፡ ላባቱ
👍1
#ሮሜዎና_ዡልዬት
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
#አባ_ሎራና። #ዡልየት ።
#ዡልዬት ።
ይዘኑልኝ ፡ በጣም ፡ አባቴ ፡ አባ ፡ ሎራ ፤
በኔ ፡ ላይ ፡ ዘንድሮ ፡ የመጣው ፡ መከራ ፡
ፍጻሜ ፡ የለውም ፡ ቈርጫለሁ ፡ ተስፋ፤
ይርዱኝ ፡ እባክዎ ፡ ጨርሼ ፡ ሳልጠፋ ።
#አባ_ሎራ ።
አዝኛለሁ ፡ ልጄ ፡ ነገሩን ፡ ሰምቼው ፤
አሁን ፡ መጥቶ ፡ ነበር ፡ፓሪስን ፡ አግኝቼው
ተክሊሉን ፡ ለናንተ ፡ ኀሙስ ፡ እንድሞላ ፡
ለምኖኝ ፡ ነበረ ፡ እንዲህ ፡ በችኰላ ፡
እንደ ፡ ምን ፡ ይሆናል ፡ብዬ ፡ መለስኩለት፤
በነገሩ ፡ በጣም ፡ አዝኛለሁ ፡ በውነት ።
#ዡልዬት ።
እንግዲያው ፡ ከሰሙት ፡ እንሆ ፡ ችግሬ ፤
ሥቃዬ ፡ የጠና ፡ ብርቱ ፡ ነው ፡ አሳሬ
እሄድ ነበር በውነት ሴት፡ ባልሆን' ጠፍቼ
ለፓሪስ ፡ ሊድሩኝ፡ቈርጠው 'ዘመዶቼ
አስጨንቀው ያዙኝ'ይኸው ፡በግዴታ፤
አባትም እናትም የምድር'ሁሉ፡ ጌታ ፡
እግዜር ' የዳረውን ፡ አይችልም ሊያፋታ ።
እኔና 'ሮሜዎን ፡ ሁለቴ ' ሲድረን '
በፊት፡ በጥበቡ' ከልብ' አፋቀረን ፤
ቀጥሎ ፡ በርስዎ ፡ በካህኑ' ሥልጣን ፡
ባርኮ ፡አገናኘን' በተክሊል ፡ ቃል፡ ካዳን ።
አባቴና እናቴ ፡ ይህን ፡ አላወቁ ፤
ለፓሪስ ፡ ሊድሩኝ 'እንሆ 'ታጠቁ '
እንግዴህ ፡ አባቴ ፡ እርስዎ ፡ ከግዜር ፡ ጋራ
በርትተው ፡ ያድኑኝ ፡ ከዚህ ፡ ከመከራ ፡
የማይቻል ፡ ሆኖ ፡ ካልተገኘ ፡ ዘዴ !
ብልሃቱን ፡ መፈለግ ፡ አለብኝ ፡ በግዴ ፡
ይኸው ፡ በዚህ ፡ ጩቤ ፡ ሆዴን ፡ እቀድና ፡
እገላገላለሁ ፡ ከዚህ ፡ ከፈተና
#አባ_ሎራ ።
ኀጢአቱ ፡ትልቅ ነው ከነፍስ ፡ የሚያስቀጣ
በገዛ ፡ እጅሽ ፡ መሞት ባሳብሽ ፡ አይምጣ
ፓሪስን ለማግባት ልብሽ ፡ ካልፈቀደ
ይህን 'ያኽል፡ በውነት ፡ ሆድሽ ፡ ካልወደደ
ግልጥ ፡ አድርጊና ፡ ንገሪኝ አትፍሪ
#ዡልዬት ።
እግዚአብሔር ብቻ ነው መንፈስን መርማሪ
ፓሪስን ፡ ከማግባት ፡ በውነቱ ፡ አባቴ ፡
አሁን ባሁን ፡ ፈጥኖ፡ ይምጣ ጊዜ፡ ሞቴ ፡
ልገረፍ ልሰቀል ፥ በሥቃይ ፡ ልገደል ፤
ወስዳችሁ ፡ ወርውሩኝ ጣሉኝ ወደ ፡ ገደል
የትም ፡ ተረስቼ ፡ ልዋረድ ፡ ልጕላላ ፤
ብትፈልጉ ፡ ዳሩኝ ፡ ለዱር ፡ ወሮ ፡ በላ '
ከዥብ ፡ ጋራ ፡ እሰሩኝ ፡ ከነብር ፡ ካንበሳ ፤
ካፅም 'ጋራ ፡ ቅበሩኝ፣ ከትኵስ'ሬሳ፡
እሳት አንድዳችሁ፡ አሁን ፡ ከቶ ፡ ነፍሴ ፡
አቃጥሉኝ ፡ በቁሜ ፡ ከእግር እስከ ፡ ራሴ
ወደ ፡ አራዊት ፡ ጐሬ ጣሉኝ ፡ ወዶ ፡ ዋሻ ፣
ሮሜዎ ከቀረ ምንም ፡ ባል እልሻ
#አባ_ሎራ ።
እኔም ፡ ባንቺ፡ነገር፡እጅግ፡ተጠብቤ
ልጄ ፡ ሆይ ፡ሐዘንሽ ተሰማኝ፡ ለልቤ ፡
የሚቻልሽ ፡ ቢሆን ፡ ልብሽ ፡ የሚደፍር ፡
አድምጭኝ ልጄ ሆይ ልስጥሽ አንድ ምክር
አሁን ፡ ተመልሰሽ ፡ ስትገቢ ፡ ከቤትሽ ፡
እንደዚህ ፡ በዪና ፡ ንገሪው ፡ ላባትሽ ፡
« ፈቃድህን ፡ ልፈጽም ፡ ፓሪስን ፡ አግብቼ፡
« መጥቻለሁና ፡ ይኸው ፡ ተጸጽቼ ፡
« እንግዴህ ፡ ይደገስ ፡ ሰርጉ ፡ ይሰናዳ »
አባትሽ ፡ ይህነን ፡ ነግረሽው ፡ ሲረዳ '
ይታረቃል ፡ ካንቺ ፡ መንፈሱም ፡ ይረጋል ፤
ከንዴቱ ፡ በርዶ ፡ ይቅርታ ፡ ያደርጋል ።
እኔም ፡ የምሰጥሽ ፡እግዚአብሔር ፡ ቢረዳ
አንድ፡ መድኀኒት ነው ምንም ፡ የማይጎዳ ፡
ልብስሽን ፡ አውልቀሽ ፡ ስትተኝ ፡ ማታ ፡
ደብቀሽ ፡ ሰው ፡ ሳያይ ጠጪው ፡ በቀስታ
ሌሊቱን ፡ ሳትሰሚ ፡ መድኀኒቱ ፡ ሠርቶ ፡
ነገ ፡ ጧት ፡ ከእንቅልፍሽ መነሣትሽ ፡ ቀርቶ
ሞተሽ ፡ ትገኛለሽ ፡ ትንፋሽሽም ፡ ጠፍቶ ፡
ወስደው ፡ ይቀብሩሻል ፡ ሞታለች ፡ ተብሎ
ለቤተ ፡ ሰባችሁ ፡ በሰፊው ፡ ተንጣሎ ፡
አምሮ ፡ በተሠራው ፡በመቃብር ፡ ቤት ፡
ተኝተሽ ፡ ቈይተሽ ፡ ቀንና ፡ ሌሊት ፡
ታዝኖ ፡ ተለቅሶልሽ ፡ ካለቀ ፡ በኋላ ፡
ዐውቀሽ ፡ ትነሻለሽ ፡ አንድ ፡ ቀን ፡ ሲሞላ
እስከዚያ ፡ እሠራለሁ ፡ እኔ ፡ ግን ፡ ተግቼ ፤
ደብዳቤ ፡ እጽፍና ፡ ሮሜዎን ፡ ጠርቼ ፡
እሱም ፡ በቬሮና ፡ ተደብቆ ፡ ገብቶ ፡
ወዳንቺ ፡ መቃብር ፡ ከኔ ፡ ጋራ ፡ መጥቶ ፡
አንቺ ፡ ሳትነሺ 'አጠገብሽ 'ደርሰን ፡
በምስጢር ፡ በፍጥነት ፡ ልብስሽን ፡ አልብሰን አንቺና ፡ ሮሜዎ ከዚህ ፡ ከከተማ
ማንም ሳይጠረጥር ማንም ሰው ሳይሰማ
ወጥታችሁ ፡ሄዳችሁ የትም ፡ በሌላ ፡ አገር
ዕረፍት ፡ አግኝታችሁ ፡ ያለ ፡ ክፉ ፡ ነገር
ኑሩልኝ ፡ በሰላም ፡ በፍጹም ፡ ደስታ ፡
ከናንተ ጋር ይሁን የእግዚአብሔር እርዳታ
ትጠጭው ፡ እንዲሆን ፡ ዡልዬት ፡ ሳትፈሪ'
አስቢና ፡ ቶሎ ፡ ገልጠሽ ፡ ተናገሪ ፡
እኔም ፡ መድኒቱን ልስጥሽ አሁን ፡ ሳልቈይ
ከዚህ በቀር ፡ ዘዴ ፡ የለኝም ፡ ልጄ ፡ ሆይ ።
#ዡልዬት ።
መልካም ፡ ነው ፡ አባቴ ፡ ያላንድ' ቅሬታ' .
ሳልፈራ፡እጠጣለሁ፡ በትልቅ ፡ ደስታ "
እባ፡ ሎራ ፡ ገብተው ጓዳ መድኀኒቱን በብልቃጥ አመጡ
ዶግሞስ በገዛ እጁ ለመሞት ሲቃጣ ከዚህ የተሻለ ምን ዘዴ ሊመጣ ።
እንግዲያውስ፡እንቺ ፡ ይኸው ፡ መድኀኒቱ :
እግዚአብሔር ልብሽን ፡ ያድርግልሽ ብርቱ
#ዡልዬት።
አዝነው ፡ ስለ ፡ ረዱኝ ፡ ልብዎ ፡ ስለ ፡ ራራ
እግዚአብሔር ይስጥልኝ ፡ አባቴ አባ ሎራ
#አባ_ሎራ ።
ግድ ፡ የለሽም ፡ ልጄ ፡ ሳልዘገይ ፡ ፈጥኜ ፡
እንደ ፡ ምንም ፡ ብዬ ፡ አንድ ፡ ቄስ ፡ ለምኜ
ወደ ፡ ሮሜዎ ፡ ዘንድ ፡ጒዳዩን ፡ ሸሽጌ፥
ደብዳቤውን ፡ ጽፌ ፡ በምስጢር ፡ አድርጌ
እልክለታለሁ ፡ በቶሎ ፡ እንዲመጣ '
ዡልዬት ፡ በኔ ፡ ጣዪው ፤ የቀረውን ፡ ጣጣ
#ካፑሌ ፡ #የካፑሌ_ሚስት #ዡልዬት ።
(ዡልዬት ' ከውጭ መጣች)
#ካፑሌ ።
በጣም ያሳዝናል ባሕሪሽ ፡ ተበላሸ ፤
ወዴት ሄደሽ ኖሯል ደግሞ ፡ እንዲህ ፡ ከመሽ
💫ይቀጥላል💫
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
#አባ_ሎራና። #ዡልየት ።
#ዡልዬት ።
ይዘኑልኝ ፡ በጣም ፡ አባቴ ፡ አባ ፡ ሎራ ፤
በኔ ፡ ላይ ፡ ዘንድሮ ፡ የመጣው ፡ መከራ ፡
ፍጻሜ ፡ የለውም ፡ ቈርጫለሁ ፡ ተስፋ፤
ይርዱኝ ፡ እባክዎ ፡ ጨርሼ ፡ ሳልጠፋ ።
#አባ_ሎራ ።
አዝኛለሁ ፡ ልጄ ፡ ነገሩን ፡ ሰምቼው ፤
አሁን ፡ መጥቶ ፡ ነበር ፡ፓሪስን ፡ አግኝቼው
ተክሊሉን ፡ ለናንተ ፡ ኀሙስ ፡ እንድሞላ ፡
ለምኖኝ ፡ ነበረ ፡ እንዲህ ፡ በችኰላ ፡
እንደ ፡ ምን ፡ ይሆናል ፡ብዬ ፡ መለስኩለት፤
በነገሩ ፡ በጣም ፡ አዝኛለሁ ፡ በውነት ።
#ዡልዬት ።
እንግዲያው ፡ ከሰሙት ፡ እንሆ ፡ ችግሬ ፤
ሥቃዬ ፡ የጠና ፡ ብርቱ ፡ ነው ፡ አሳሬ
እሄድ ነበር በውነት ሴት፡ ባልሆን' ጠፍቼ
ለፓሪስ ፡ ሊድሩኝ፡ቈርጠው 'ዘመዶቼ
አስጨንቀው ያዙኝ'ይኸው ፡በግዴታ፤
አባትም እናትም የምድር'ሁሉ፡ ጌታ ፡
እግዜር ' የዳረውን ፡ አይችልም ሊያፋታ ።
እኔና 'ሮሜዎን ፡ ሁለቴ ' ሲድረን '
በፊት፡ በጥበቡ' ከልብ' አፋቀረን ፤
ቀጥሎ ፡ በርስዎ ፡ በካህኑ' ሥልጣን ፡
ባርኮ ፡አገናኘን' በተክሊል ፡ ቃል፡ ካዳን ።
አባቴና እናቴ ፡ ይህን ፡ አላወቁ ፤
ለፓሪስ ፡ ሊድሩኝ 'እንሆ 'ታጠቁ '
እንግዴህ ፡ አባቴ ፡ እርስዎ ፡ ከግዜር ፡ ጋራ
በርትተው ፡ ያድኑኝ ፡ ከዚህ ፡ ከመከራ ፡
የማይቻል ፡ ሆኖ ፡ ካልተገኘ ፡ ዘዴ !
ብልሃቱን ፡ መፈለግ ፡ አለብኝ ፡ በግዴ ፡
ይኸው ፡ በዚህ ፡ ጩቤ ፡ ሆዴን ፡ እቀድና ፡
እገላገላለሁ ፡ ከዚህ ፡ ከፈተና
#አባ_ሎራ ።
ኀጢአቱ ፡ትልቅ ነው ከነፍስ ፡ የሚያስቀጣ
በገዛ ፡ እጅሽ ፡ መሞት ባሳብሽ ፡ አይምጣ
ፓሪስን ለማግባት ልብሽ ፡ ካልፈቀደ
ይህን 'ያኽል፡ በውነት ፡ ሆድሽ ፡ ካልወደደ
ግልጥ ፡ አድርጊና ፡ ንገሪኝ አትፍሪ
#ዡልዬት ።
እግዚአብሔር ብቻ ነው መንፈስን መርማሪ
ፓሪስን ፡ ከማግባት ፡ በውነቱ ፡ አባቴ ፡
አሁን ባሁን ፡ ፈጥኖ፡ ይምጣ ጊዜ፡ ሞቴ ፡
ልገረፍ ልሰቀል ፥ በሥቃይ ፡ ልገደል ፤
ወስዳችሁ ፡ ወርውሩኝ ጣሉኝ ወደ ፡ ገደል
የትም ፡ ተረስቼ ፡ ልዋረድ ፡ ልጕላላ ፤
ብትፈልጉ ፡ ዳሩኝ ፡ ለዱር ፡ ወሮ ፡ በላ '
ከዥብ ፡ ጋራ ፡ እሰሩኝ ፡ ከነብር ፡ ካንበሳ ፤
ካፅም 'ጋራ ፡ ቅበሩኝ፣ ከትኵስ'ሬሳ፡
እሳት አንድዳችሁ፡ አሁን ፡ ከቶ ፡ ነፍሴ ፡
አቃጥሉኝ ፡ በቁሜ ፡ ከእግር እስከ ፡ ራሴ
ወደ ፡ አራዊት ፡ ጐሬ ጣሉኝ ፡ ወዶ ፡ ዋሻ ፣
ሮሜዎ ከቀረ ምንም ፡ ባል እልሻ
#አባ_ሎራ ።
እኔም ፡ ባንቺ፡ነገር፡እጅግ፡ተጠብቤ
ልጄ ፡ ሆይ ፡ሐዘንሽ ተሰማኝ፡ ለልቤ ፡
የሚቻልሽ ፡ ቢሆን ፡ ልብሽ ፡ የሚደፍር ፡
አድምጭኝ ልጄ ሆይ ልስጥሽ አንድ ምክር
አሁን ፡ ተመልሰሽ ፡ ስትገቢ ፡ ከቤትሽ ፡
እንደዚህ ፡ በዪና ፡ ንገሪው ፡ ላባትሽ ፡
« ፈቃድህን ፡ ልፈጽም ፡ ፓሪስን ፡ አግብቼ፡
« መጥቻለሁና ፡ ይኸው ፡ ተጸጽቼ ፡
« እንግዴህ ፡ ይደገስ ፡ ሰርጉ ፡ ይሰናዳ »
አባትሽ ፡ ይህነን ፡ ነግረሽው ፡ ሲረዳ '
ይታረቃል ፡ ካንቺ ፡ መንፈሱም ፡ ይረጋል ፤
ከንዴቱ ፡ በርዶ ፡ ይቅርታ ፡ ያደርጋል ።
እኔም ፡ የምሰጥሽ ፡እግዚአብሔር ፡ ቢረዳ
አንድ፡ መድኀኒት ነው ምንም ፡ የማይጎዳ ፡
ልብስሽን ፡ አውልቀሽ ፡ ስትተኝ ፡ ማታ ፡
ደብቀሽ ፡ ሰው ፡ ሳያይ ጠጪው ፡ በቀስታ
ሌሊቱን ፡ ሳትሰሚ ፡ መድኀኒቱ ፡ ሠርቶ ፡
ነገ ፡ ጧት ፡ ከእንቅልፍሽ መነሣትሽ ፡ ቀርቶ
ሞተሽ ፡ ትገኛለሽ ፡ ትንፋሽሽም ፡ ጠፍቶ ፡
ወስደው ፡ ይቀብሩሻል ፡ ሞታለች ፡ ተብሎ
ለቤተ ፡ ሰባችሁ ፡ በሰፊው ፡ ተንጣሎ ፡
አምሮ ፡ በተሠራው ፡በመቃብር ፡ ቤት ፡
ተኝተሽ ፡ ቈይተሽ ፡ ቀንና ፡ ሌሊት ፡
ታዝኖ ፡ ተለቅሶልሽ ፡ ካለቀ ፡ በኋላ ፡
ዐውቀሽ ፡ ትነሻለሽ ፡ አንድ ፡ ቀን ፡ ሲሞላ
እስከዚያ ፡ እሠራለሁ ፡ እኔ ፡ ግን ፡ ተግቼ ፤
ደብዳቤ ፡ እጽፍና ፡ ሮሜዎን ፡ ጠርቼ ፡
እሱም ፡ በቬሮና ፡ ተደብቆ ፡ ገብቶ ፡
ወዳንቺ ፡ መቃብር ፡ ከኔ ፡ ጋራ ፡ መጥቶ ፡
አንቺ ፡ ሳትነሺ 'አጠገብሽ 'ደርሰን ፡
በምስጢር ፡ በፍጥነት ፡ ልብስሽን ፡ አልብሰን አንቺና ፡ ሮሜዎ ከዚህ ፡ ከከተማ
ማንም ሳይጠረጥር ማንም ሰው ሳይሰማ
ወጥታችሁ ፡ሄዳችሁ የትም ፡ በሌላ ፡ አገር
ዕረፍት ፡ አግኝታችሁ ፡ ያለ ፡ ክፉ ፡ ነገር
ኑሩልኝ ፡ በሰላም ፡ በፍጹም ፡ ደስታ ፡
ከናንተ ጋር ይሁን የእግዚአብሔር እርዳታ
ትጠጭው ፡ እንዲሆን ፡ ዡልዬት ፡ ሳትፈሪ'
አስቢና ፡ ቶሎ ፡ ገልጠሽ ፡ ተናገሪ ፡
እኔም ፡ መድኒቱን ልስጥሽ አሁን ፡ ሳልቈይ
ከዚህ በቀር ፡ ዘዴ ፡ የለኝም ፡ ልጄ ፡ ሆይ ።
#ዡልዬት ።
መልካም ፡ ነው ፡ አባቴ ፡ ያላንድ' ቅሬታ' .
ሳልፈራ፡እጠጣለሁ፡ በትልቅ ፡ ደስታ "
እባ፡ ሎራ ፡ ገብተው ጓዳ መድኀኒቱን በብልቃጥ አመጡ
ዶግሞስ በገዛ እጁ ለመሞት ሲቃጣ ከዚህ የተሻለ ምን ዘዴ ሊመጣ ።
እንግዲያውስ፡እንቺ ፡ ይኸው ፡ መድኀኒቱ :
እግዚአብሔር ልብሽን ፡ ያድርግልሽ ብርቱ
#ዡልዬት።
አዝነው ፡ ስለ ፡ ረዱኝ ፡ ልብዎ ፡ ስለ ፡ ራራ
እግዚአብሔር ይስጥልኝ ፡ አባቴ አባ ሎራ
#አባ_ሎራ ።
ግድ ፡ የለሽም ፡ ልጄ ፡ ሳልዘገይ ፡ ፈጥኜ ፡
እንደ ፡ ምንም ፡ ብዬ ፡ አንድ ፡ ቄስ ፡ ለምኜ
ወደ ፡ ሮሜዎ ፡ ዘንድ ፡ጒዳዩን ፡ ሸሽጌ፥
ደብዳቤውን ፡ ጽፌ ፡ በምስጢር ፡ አድርጌ
እልክለታለሁ ፡ በቶሎ ፡ እንዲመጣ '
ዡልዬት ፡ በኔ ፡ ጣዪው ፤ የቀረውን ፡ ጣጣ
#ካፑሌ ፡ #የካፑሌ_ሚስት #ዡልዬት ።
(ዡልዬት ' ከውጭ መጣች)
#ካፑሌ ።
በጣም ያሳዝናል ባሕሪሽ ፡ ተበላሸ ፤
ወዴት ሄደሽ ኖሯል ደግሞ ፡ እንዲህ ፡ ከመሽ
💫ይቀጥላል💫
#ሮሜዎና_ዡልዬት
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
#ዡልየት
ወደ ፡ አባ " ሎራ ፡ ዘንድ ፡ ደርሼ ፡ ነበረ ፤
ምክራቸው ፡ ገሠጸኝ ልቢ ፡ ተሰበረ ፡
ያንተን ፡ ያባቴን ፡ ቃል ፡ ልፈጽም ፡ ፈቅጄ ፡
የምጠላውን ፡ ሰው ፡ ስላንተ ፡ መድጄ፡
ፓሪስን ፡ ላገባ ፡ ሆኛለሁ ፡ ዝግጁ
ሰርጌ ፡ ይሰናዳ ፡ ሁሉንም ፡ አብጁ
ደግሞም ብለውኛል አጥብቀው በብርቱ
« ምሕረቱን ፡ ለምኚ፡ ወድቀሽ ፡ ከጕልበቱ
(ተንበረከከች)
ንዴት ፡ አይግባችሁ ፡ በኔ ፡ የተነሣ ፤
ያለፈው ፡ ጥፋቴ ፡ እንግዴህ ፡ ይረሳ፡
የሰላም ፡ ቤት ፡ ይሁን ፡ ያለም ፡ የደስታ ፡
ለኔም ፡ ለልጃችሁ ፡ አድርጉ ፡ ይቅርታ ።
#ካፑሌ ።
እንዲህ ፡ ያለ ፡ ካህን ፡ እግዜር ፡ የባረከው
ምክሩ ፡ ንግግሩ ፡ ለሰው ፡ የሚሰብከው ፡
ከጻድቅ ፡ የመጣ ፡ ንጹሕ ፡ በመሆኑ ፡
ጠልቆ ፡ ልብ ፡ ይገባል ያጠግባል ፡ በውኑ
እስቲ ፡ አሁን ፡ ባሁን እንደ ፡ ምን ፡ አድርጎ
መልሶ ፡ ላከልኝ ፡ አንቺን ፡ ወደ ፡ በጎ ።
(ከተንበረከከችበት ቦታ'ያስነሣታል )
ተነሺ ፡ ከመሬት ፡ ይብቃ ፡ አትንበርከኪ ፡
ምክሩን ፡ መከተልሽ ፡ አንቺም ፡ ተባረኪ ።
(ወዴ ፡ ሚስቱ' መለስ ' ብሎ)
እንግዴህ ፡ ይፋጠን ፡ ይቀጥል ፡ ድግሡ፤
አሽከሮቹ ፡ ሁሉ ፡ በሌሊት ፡ ይነሡ ፡
ተክሊሉ ፡ እንዲፈጸም ፡ ነገ ፡ በማለዳ ፡
ማንኛውም ፡ ነገር ፡ ዛሬ ፡ ይሰናዳ ።
(በካፑሌ ፡ ቤት ጧት) ,
#ካፑሌ ።
ሰዎቼ ፡ ተኝተው ፡ ሳይነሡ ፡ ካልጋ ፡
ወፎቹ ፡ ተንጫጩ ፡ ይኸው ፡ ሌቱ ፡ ነጋ ፡
ተነሡ፡ረፈደ፡እሳቱን ፡ አንድዱ፤
መብሉን ፥ መጠጡን ፥ በቶሎ ፡ አሰናዱ ።
የዡልዬት ፡ ሞግዚት'
ርስዎ ፡ ዛሬ ፡ ሌሊት ፡ ጨርሰው ፡ ሳይትኙ
ቁጭ ፡ ብለው ፡ ነጋ ፡ ሥራውን ፡ ሲቃኙ፡
በጣም መልካም ነበር አሁን ጥቂት ቢያርፉ
#ካፑሌ ።
አታስቡ ፡ ለኔ ፡ ይልቅ ፡ አትስነፉ ፡
አያሸንፈኝም ፡ ዱሮም ፡ ቢሆን ፡ እንቅልፍ ፡
መብልና ፡ መጠጥ ፡ ደኅና ፡ የሚያሳልፍ ፡
ወዴት፡አገኝ፡ ይሆን ፡ የሠለጠነ ፡ ሰው ፤
ምንም ፡ ሳይዘጋጅ ፡ አንዱንም ፡ ሳንይዘው
ስትተራመሱ ፡ እንዲሁ ፡ በከንቱ ፡
የሙሽራው ፡ መምጫ ፡ ደረሰ ፡ ሰዓቱ ፡
ዕቃ ፡ ማነሱ፡ ነው ፡ አንዱም ፡ የሚያውከው ፡
(አሽከሮቹ'ገቡ' በያይነቱ፡ ዕቃ ፡ ይዘው)»
ምንድነው'ደግሞ አንተ ይህ የተሸከምከው ?
#አሽከር ።
የጠቦት፡ ሥጋ ነው፡ ለጥብስ ፡ የታረደ
#ካፑሌ ።
በል ፡ፍጠን ፡ ቶሎ ፡ በል ፡ ሰዓቱ ፡ ረፈደ ።
#የካፑሌ_ሚስት ።
ከምን ጊዜ ነጋ አለፈ ሌሊቱ ካፑሌ
አንቺን ፡ አይጠብቅም ፡ ጊዜና ፡ ሰዓቱ
ሙሽራው ይመጣል አንዱን ሳትጨብጨው።
የሚያስፈልገውን ፡ ለወጥ ፡ ቤቱ ፡ ስጪው
አለዚያ ፡ ሲቸኵል ፡ ይበላሻል ፡ ወጡ!
አንችም ፡ ቶሎ ፡ ልበሽ ፡ ሰርገኞች ፡ ሳይመጡ ።
#የካፑሌ_ሚስት ።
ዡልዬት ሳትነሣ እኔም ልብሴን ሳልለብስ ፡
በጣም ፡ ያስደንቃል ፡ የሰዓቱ ፡ መድረስ ፡
እመጣለሁ ፡ ብሏል ፡ ፓሪስ ፡ በሙዚቃ ፡
እንግዴህ ፡ ዡልዬትም ፡መተኛቷ ፡ ይብቃ።
(ሞግዚቷ ፡ ገባች)
እንዴት ፡ ረፈደ ፡ በጣም ፡ ያስገርማል ፤
ሰርገኞቹ ፡ መጡ ፡ ሙዚቃው ፡ ይሰማል !
እባክሽ ፡ ፍጠኚ ፡ ቶሎ ፡ በይ ፡ አስነሻት ፤
ገላዋን ፡ ትታጠብ ፡ ልብሷንም ፡ አልብሻት
ቶሎ ፡ እንደ ፡ ጨረሰች ፡ ለብሳና ፡ አጊጣ ፡
አብራችሁ ፡ ካንቺ ጋር ወደኛ እንድትመጣ
እኔም ፡ ሰርገኞቹን ፡ እስከዚያ ፡ ልቀበል ፤
አሽከር ፡ በሩን ፡ ክፈት እባክህ ፡ ቶሎ ፡ በል
በዡልዬት ፡ መኝታ ፡ ቤት ።
#ሞግዚት ፡ (ዡልዬትን፡ትቀሰቅሳለች) •
ተነሺ ፡ ረፈደ ፡ ዡልዬት ፡ እመቤቴ ፤
ተነሺ ፡ ይሉሻል ፡ እናትሽ ፡ እሜቴ ፡
ሰርገኞች ፡ ሲመጡ ፡ ሙዚቃ ፡ ሲሰማ
አትንቀሳቀስም ፡ እሷ ፡ ግን ፡ ፈጽማ ፤
ምነው ፡ ምን ሆንሽብኝ ተነሺ እንጂ ቶሎ
አንቺን ፡ ይጠብቃል ፡ ሰው ፡ ሁሉ ፡ ቸኩሎ
(ገልጣ' ታያታለች) •
እኔ ፡ ጠፋሁ ፡ ዛሬ ፡ ያለትንፋሽ ፡ ቀርታ ፡
ገላዋ ፡ ቀዝቅዟል ፡ እመቤቴ ፡ ሞታ፡
እረ ፡ ትልቅ ፡ጉድ፡ ነው ፡ ኑ፡ ቶሎ ፡ድረሱ !
#የካፑሌ_ሚስት ።
ማነው ይህን ያኽል የሚጮኸው እሱ ?
#ሞግዚት ።
አሁን ፡ በገደለኝ ፡ መሬት ፡ እኔን ፡ ውጦ ።
#የካፑሌ ፡ ሚስት ።
አትጩሂ ፡ እባክሽ ፡ እንግዳ ፡ ተቀምጦ ።
#ሞግዚት ።
ልጅዎን ፡ ያስተውሏት ፡ በመኝታ ፡ ቤቷ ፤
#የካፑሌ_ሚስት (ግባች) •
ስለምን፡ነው ፡ እስካሁን ፡ አለመነሣቷ ?
ልጄ ፡ ዡልዬት ፡ ተነሽ ፡ ዐይንሽን ፡ ግለጪ
አባቷን ጥሩልኝ ፡ በቶሎ ፡ ከውጪ
ልጄን ፡ ምን፡ አገኛት ፥ ሞታለች ፡ ጨርሶ ።
#ካፑሌ ፡ (ገባ) «
እንግዲህ ፡ መንጫጫት ይወዳሉ ፡ ደርሶ
ዡልዬት አትመጣም ወይ ሙሽራው ሲጠብቅ
💫ይቀጥላል💫
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
#ዡልየት
ወደ ፡ አባ " ሎራ ፡ ዘንድ ፡ ደርሼ ፡ ነበረ ፤
ምክራቸው ፡ ገሠጸኝ ልቢ ፡ ተሰበረ ፡
ያንተን ፡ ያባቴን ፡ ቃል ፡ ልፈጽም ፡ ፈቅጄ ፡
የምጠላውን ፡ ሰው ፡ ስላንተ ፡ መድጄ፡
ፓሪስን ፡ ላገባ ፡ ሆኛለሁ ፡ ዝግጁ
ሰርጌ ፡ ይሰናዳ ፡ ሁሉንም ፡ አብጁ
ደግሞም ብለውኛል አጥብቀው በብርቱ
« ምሕረቱን ፡ ለምኚ፡ ወድቀሽ ፡ ከጕልበቱ
(ተንበረከከች)
ንዴት ፡ አይግባችሁ ፡ በኔ ፡ የተነሣ ፤
ያለፈው ፡ ጥፋቴ ፡ እንግዴህ ፡ ይረሳ፡
የሰላም ፡ ቤት ፡ ይሁን ፡ ያለም ፡ የደስታ ፡
ለኔም ፡ ለልጃችሁ ፡ አድርጉ ፡ ይቅርታ ።
#ካፑሌ ።
እንዲህ ፡ ያለ ፡ ካህን ፡ እግዜር ፡ የባረከው
ምክሩ ፡ ንግግሩ ፡ ለሰው ፡ የሚሰብከው ፡
ከጻድቅ ፡ የመጣ ፡ ንጹሕ ፡ በመሆኑ ፡
ጠልቆ ፡ ልብ ፡ ይገባል ያጠግባል ፡ በውኑ
እስቲ ፡ አሁን ፡ ባሁን እንደ ፡ ምን ፡ አድርጎ
መልሶ ፡ ላከልኝ ፡ አንቺን ፡ ወደ ፡ በጎ ።
(ከተንበረከከችበት ቦታ'ያስነሣታል )
ተነሺ ፡ ከመሬት ፡ ይብቃ ፡ አትንበርከኪ ፡
ምክሩን ፡ መከተልሽ ፡ አንቺም ፡ ተባረኪ ።
(ወዴ ፡ ሚስቱ' መለስ ' ብሎ)
እንግዴህ ፡ ይፋጠን ፡ ይቀጥል ፡ ድግሡ፤
አሽከሮቹ ፡ ሁሉ ፡ በሌሊት ፡ ይነሡ ፡
ተክሊሉ ፡ እንዲፈጸም ፡ ነገ ፡ በማለዳ ፡
ማንኛውም ፡ ነገር ፡ ዛሬ ፡ ይሰናዳ ።
(በካፑሌ ፡ ቤት ጧት) ,
#ካፑሌ ።
ሰዎቼ ፡ ተኝተው ፡ ሳይነሡ ፡ ካልጋ ፡
ወፎቹ ፡ ተንጫጩ ፡ ይኸው ፡ ሌቱ ፡ ነጋ ፡
ተነሡ፡ረፈደ፡እሳቱን ፡ አንድዱ፤
መብሉን ፥ መጠጡን ፥ በቶሎ ፡ አሰናዱ ።
የዡልዬት ፡ ሞግዚት'
ርስዎ ፡ ዛሬ ፡ ሌሊት ፡ ጨርሰው ፡ ሳይትኙ
ቁጭ ፡ ብለው ፡ ነጋ ፡ ሥራውን ፡ ሲቃኙ፡
በጣም መልካም ነበር አሁን ጥቂት ቢያርፉ
#ካፑሌ ።
አታስቡ ፡ ለኔ ፡ ይልቅ ፡ አትስነፉ ፡
አያሸንፈኝም ፡ ዱሮም ፡ ቢሆን ፡ እንቅልፍ ፡
መብልና ፡ መጠጥ ፡ ደኅና ፡ የሚያሳልፍ ፡
ወዴት፡አገኝ፡ ይሆን ፡ የሠለጠነ ፡ ሰው ፤
ምንም ፡ ሳይዘጋጅ ፡ አንዱንም ፡ ሳንይዘው
ስትተራመሱ ፡ እንዲሁ ፡ በከንቱ ፡
የሙሽራው ፡ መምጫ ፡ ደረሰ ፡ ሰዓቱ ፡
ዕቃ ፡ ማነሱ፡ ነው ፡ አንዱም ፡ የሚያውከው ፡
(አሽከሮቹ'ገቡ' በያይነቱ፡ ዕቃ ፡ ይዘው)»
ምንድነው'ደግሞ አንተ ይህ የተሸከምከው ?
#አሽከር ።
የጠቦት፡ ሥጋ ነው፡ ለጥብስ ፡ የታረደ
#ካፑሌ ።
በል ፡ፍጠን ፡ ቶሎ ፡ በል ፡ ሰዓቱ ፡ ረፈደ ።
#የካፑሌ_ሚስት ።
ከምን ጊዜ ነጋ አለፈ ሌሊቱ ካፑሌ
አንቺን ፡ አይጠብቅም ፡ ጊዜና ፡ ሰዓቱ
ሙሽራው ይመጣል አንዱን ሳትጨብጨው።
የሚያስፈልገውን ፡ ለወጥ ፡ ቤቱ ፡ ስጪው
አለዚያ ፡ ሲቸኵል ፡ ይበላሻል ፡ ወጡ!
አንችም ፡ ቶሎ ፡ ልበሽ ፡ ሰርገኞች ፡ ሳይመጡ ።
#የካፑሌ_ሚስት ።
ዡልዬት ሳትነሣ እኔም ልብሴን ሳልለብስ ፡
በጣም ፡ ያስደንቃል ፡ የሰዓቱ ፡ መድረስ ፡
እመጣለሁ ፡ ብሏል ፡ ፓሪስ ፡ በሙዚቃ ፡
እንግዴህ ፡ ዡልዬትም ፡መተኛቷ ፡ ይብቃ።
(ሞግዚቷ ፡ ገባች)
እንዴት ፡ ረፈደ ፡ በጣም ፡ ያስገርማል ፤
ሰርገኞቹ ፡ መጡ ፡ ሙዚቃው ፡ ይሰማል !
እባክሽ ፡ ፍጠኚ ፡ ቶሎ ፡ በይ ፡ አስነሻት ፤
ገላዋን ፡ ትታጠብ ፡ ልብሷንም ፡ አልብሻት
ቶሎ ፡ እንደ ፡ ጨረሰች ፡ ለብሳና ፡ አጊጣ ፡
አብራችሁ ፡ ካንቺ ጋር ወደኛ እንድትመጣ
እኔም ፡ ሰርገኞቹን ፡ እስከዚያ ፡ ልቀበል ፤
አሽከር ፡ በሩን ፡ ክፈት እባክህ ፡ ቶሎ ፡ በል
በዡልዬት ፡ መኝታ ፡ ቤት ።
#ሞግዚት ፡ (ዡልዬትን፡ትቀሰቅሳለች) •
ተነሺ ፡ ረፈደ ፡ ዡልዬት ፡ እመቤቴ ፤
ተነሺ ፡ ይሉሻል ፡ እናትሽ ፡ እሜቴ ፡
ሰርገኞች ፡ ሲመጡ ፡ ሙዚቃ ፡ ሲሰማ
አትንቀሳቀስም ፡ እሷ ፡ ግን ፡ ፈጽማ ፤
ምነው ፡ ምን ሆንሽብኝ ተነሺ እንጂ ቶሎ
አንቺን ፡ ይጠብቃል ፡ ሰው ፡ ሁሉ ፡ ቸኩሎ
(ገልጣ' ታያታለች) •
እኔ ፡ ጠፋሁ ፡ ዛሬ ፡ ያለትንፋሽ ፡ ቀርታ ፡
ገላዋ ፡ ቀዝቅዟል ፡ እመቤቴ ፡ ሞታ፡
እረ ፡ ትልቅ ፡ጉድ፡ ነው ፡ ኑ፡ ቶሎ ፡ድረሱ !
#የካፑሌ_ሚስት ።
ማነው ይህን ያኽል የሚጮኸው እሱ ?
#ሞግዚት ።
አሁን ፡ በገደለኝ ፡ መሬት ፡ እኔን ፡ ውጦ ።
#የካፑሌ ፡ ሚስት ።
አትጩሂ ፡ እባክሽ ፡ እንግዳ ፡ ተቀምጦ ።
#ሞግዚት ።
ልጅዎን ፡ ያስተውሏት ፡ በመኝታ ፡ ቤቷ ፤
#የካፑሌ_ሚስት (ግባች) •
ስለምን፡ነው ፡ እስካሁን ፡ አለመነሣቷ ?
ልጄ ፡ ዡልዬት ፡ ተነሽ ፡ ዐይንሽን ፡ ግለጪ
አባቷን ጥሩልኝ ፡ በቶሎ ፡ ከውጪ
ልጄን ፡ ምን፡ አገኛት ፥ ሞታለች ፡ ጨርሶ ።
#ካፑሌ ፡ (ገባ) «
እንግዲህ ፡ መንጫጫት ይወዳሉ ፡ ደርሶ
ዡልዬት አትመጣም ወይ ሙሽራው ሲጠብቅ
💫ይቀጥላል💫
#ሮሜዎና_ዡልዬት
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
#ሞግዚት ።
ሞታለች ፡ ሞታለች ፡ ጕድ ፡ ነው ፡ የሚያስደንቅ ,
#የካፑሌ_ሚስት ።
ምን ፡መድኀኒት ላምጣ ወዴት ስፍራ ሄጄ
#ካፑሌ ።
ቆዩ፡እስቲ፡እኔ፡ልያት፡ የታለች፡ ቀዝቃዛ ፡ (እየዳበሳት).
ፈጽማ ፡ ሞታለች ፡ በምን ፡ ጕዴ በዛ
ሌሊት፡ በጨለማ ፡ ፀሓይዋ፡ ሳትወጣ ፡
ልጄ ፡ አበባዬ ፡ ወድቃለች ፡ ተቋርጣ ።
#ሞግዚት ።
የተረገመ ፡ ነው ፡ አወይ ፡ የዛሬው ቀን ፤
#የካፑሌ_ሚስት
ምነው ፡ ብንቀበር ፡ ሁላችንም ፡ አልቀን !
#ካፑሌ
ምንም ፡ አልናገር' ምላሴ 'ታሰረ
ልሳኔ ፡ በሐዘን 'ተቁልፎ ፡ ቀረ ።
(አባ ' ሎራና 'ፓሪስ ' በሙዚቃ ገቡ ።)
#አባ_ሎራ
ወደ ፡ ቤተ ፡ ክርስቲያን እንሂድ ፍጠኑ
ሙሽራዋን ጥሩ እናንተም ቶሎ'ኑ ።
#ካፑሌ
ጉድ ሆነናል ዛሬ ይተዉ አባቴ
ጕድ ፡ ለማየት ፡ ኖሯል ፡ የቈየች ፡ ሕይወቴ
እኔ ፡ ወዴት ፡ ልድረስ ፡ የት ፡ አባቴ ፡ ልግባ
ሞተች ፡ ተቀጠፈች ፡ ልጄ ፡ የኔ ፡ ኣበባ ።
እናቷ ፡ ሳታስብ ፡ ኣባቷ ፡ ሳይሰማ ፡
ሞት ፡ የሚባል ፡ ሌባ ፡ ሌሊት በለጨለማ
ለካ ፡ ከቤታችን ፡ ገብቶ ፡ ተደብቆ ፡
ይዟት ፡ ሄዶ ፡ ኖሯል ፡ ልጃችንን ፡ ሰርቆ ፤
እንዴት ፡ ጉድ፡ ሆነናል ፡ እንዲህ ፡ ተደግሶ
ሰርጓ ሐዘን ፡ ሆነ ደስታችን ለቅሶ ።
#ፓሪስ።
እኔ ፡ ዕድለ ፡ ቢሱ፡ እንዴት፡ ያለ ፡ መርዶ፡
እንዴት ፡ ያለ ፡ሐዘን ፡ ጠበቀኝ ፡ ተወልዶ
#የካፑሌ_ሚስት ።
የተረገመ ፡ ነው ፡ አወይ ፡ የዛሬ ፡ ቀን
ቀረን ፡ እኮ ፡ ሰዎች ፡ እንደዚህ ፡ ተሳቀን ፡
ያይኖቼ ፡ ማረፊያ ብትኖረኝ አንዲት ፡ ልጅ
ያንድ ፡ ቀን 'ደስታ' ለማየት'ስዘጋጅ፡
ለማን ኣቤት ልበል ፡ ሞት ፡ ይዞብኝ ፡ ሄደ
ሆዴ ተቃጠለ አንጀቴ ፡ ነደደ
#አባ_ሎራ "
ይብቃ ፡ ለሐዘኑ ፡ አድርጉለት ፡ መጠን ፤
አስቡ ፡ ይችን 'ልጅ' እግዜር ፡ ነው' የሰጠን
አሁንም ፡እግዚአብሔር ወሰዳት መልሶ :
ሐዘናችሁ ፡ አይሁን ፡ ያረመኔ ፡ ለቅሶ ፡
ቀረባት ፡ ብላችሁ ፡ የመሬት ፡ ደስታ ፡
ጸጸታችሁ ፡ አይሁን ፡ በጣም ፡ የበረታ ፡
የመሬት ፡ ደስታ ፡ ምንም ፡ የለው ፡ ዋጋ ፤
ይልቅ አይበልጥም ወይ የሰማይቤት ጸጋ፡
ከሚያልፍ ፡ዓለም ወጥታ፡ ከዘለዓለም ቤቷ
መተላለፍ፡ ነው ፡ በሰላም ፡ መግባቷ ፡
መሆኑ ፡ ቀረና፡ ሰርጓ በመሬት ላይ፤
ብርሃን ፡ ወዳለበት፡ሄደች፡ ወደ ፡ ሰማይ ፡
እናድርጋት ፡ ስንል ፡ ምድራዊት ፡ ሙሽራ ፡
አይሆናትም ፡ ብሎ ፡ የመሬት ፡ መከራ ፡
ሺሕ ፡ ጊዜ ፡ የላቀ ፡ ደስታ፡ አዘጋጅቶ ፡
እግዚአብሔር ፡ ወሰዳት ፡በፈቃዱ ፡ ጠርቶ
የሰርግ ልብሷን ለብሳ እንዳማረች በክብር
በሉ ፡ ያዟትና ፡ እንሂድ ፡ መቃብር ።
#ሮሜዎ ። (በተሰደደበት ፡ አገር 'ሆኖ)
መሠረት ፡ ቢኖረው ፡ የኔ ፡ ሕልም፡ ዛሬ ፡
አገኝ ፡ ይመስለኛል ፡ ደስ የሚያሰኝ ፡ ወሬ
ዡልዬት ፡ ስትመጣ ፡ ስታገኘኝ ፡ ሞቼ ፡
አልቅሳ ፡ ስትስመኝ ፡ እኔ ፡ ተዘርግቼ ።
ኋላም ፡ በሷ ፡ ትንፋሽ ፡ ሕይወቴን ፡ አድሼ
ከሞት ፡ ተነሥቼ ፡ አየሁኝ ፡ ነግሼ ።
በጣም ፡ ደስ ፡ ብሎኛል ፡ ዛሬ ጧት፡ጀምሮ
ሰላም ፡ ይሰማኛል ፡ የመንፈስ ፡ የአእምሮ
(ቤልሻጥር ቦት ጫማ አድርጎ፡ መጣ)
ቤልሻጥር ፡ጐበዙ፡ እንኳን ፡ ገባህ ፡ ደኅና'
ምን ወሬ ይዘህ መጣህ ዛሬ ከቤሮና ?
ዡልዬት ደኅናነች ወይ አባቴስ እንዴት ነው ?
እሷ ፡ ደኅና፡ ብትሆን ፡ግድ የለም የቀረው
ዡልዬት ፡እንደ ፡ምን ነች ? አሁንም አድሼ
ልጠይቅህ ፡ በጣም ሺሕ ፡ ጊዜ ፡ መልሼ
#ቤልሻጥር ።
ደኅና ፡ ነች ፡ ልበልህ ፡ አልነካትም ፡ ዐፈር
እንደሌላው ፡ ፍጥረት ፡ መሬት ፡ ሳትቀበር
ከመቃብሩ ፡ ቤት፡ ሠርተው ፡ አባቷ
ካዘጋጁት ፡ ገብታ ፡ እግሮቿም ፡ እጆቿ ፡
ታስረው ፡ ሳትገነዝ ፡ በማዕርግ ፡ ተንጋላ ፡
ተኝታ ፡ ኣየናት ፡ ያንቀላፋች ፡ መስላ ።
እንዲህ ፡ በጌትነት ፡ ዡልዬት ፡ ተቀበረች ፤
በቃ ፡ የሷ፡ ነገር ፡ እንደ ፡ ዘበት ፡ ቀረች ።
ነፍሷ ፡ ግን ወደ እግዜር ዐረገች ወደ ላይ
ዐርፋ ፡ ከዚህ ዓለም ወጣች ፡ ወደ ሰማይ
#ሮሜዎ ። (በድንጋጤ ፊቱ ተለወጠ)
ምን ፡ አገኛትና ? በምን ፡ የተነሣ ?
#ቤልሻጥር ።
ጧት፡ ባልጋዋ ፡ ላይ ፡ በድን ሆና ሬሳ፡
ተገኘች ፡ ከእንቅልፍ፡ ሳትነቃ ፡ ሞታ ፤
#ሮሜዎ ።
እንደዚህ ፡ ከሆነ 'የዡልዬት ፡ ሁኔታ ፡
ደግ ፡ ነው መልካም ፡ ነው ፤ ብዕር፡ቀለም፡ኣምጣ፡
ፈረሶች ፡ ተከራይ ፈጥነህ መንደር ፡ውጣ
ማንም ሰው ሳያየኝ ማንም ሰው ሳይሰማ
መሄዴ' ነውና ፡ ሌሊት ፡ በጨለማ ።
#ቤልሻጥር
እባክህ ፡ ጌታዬ ፡ ፊትህ ፡ ተለወጠ ፤
ደምህም ፡ ጠቈረ ፡ ልቤ ፡ ደነገጠ '
ቻለው ፡ ሐዘንህን ፡ ከትዕግሥት ፡ ጋራ
#ሮሜዎ ።
አትሥጋ ፡ ግድ የለም ፡ ቤልሻጥር አትፍራ
የማይሆን አይሆንም የሚሆን ፡ ይሆናል !
ይልቅ ፡ቶሎ ፡ ፍጠን ፡ ጊዜው ፡ ያልፍብናል
(ቤልሻጥር ሄደ፤ ሮሜዎ'ብቻውን) »
እንገናኛለን ፡ ዥልዬት ፡ ዛሬ ፡ ማታ ፤
ወዳንቺ ፡ ለመድረስ ፡ ቶሎ ፡ በደስታ ፡
መንገዱን ፡ መፈለግ ፡ አለብኝ ፡ ግዴታ ፡
መድኀኒት ፡ የሚሸጥ ፡ አንድ ፡ ጎረቤቴ ፡
መኖሩን ፡ ዐውቃለሁ ፥ እኔ ፡ በሕይወቴ ፡
አይቼ ፡ አላውቅም ፡ ችግረኛ ፡ እንደ ፡ እሱ
ሁል ፡ ጊዜ ፡ ያደፈ፡ ቀዳዳ ፡ ነው ፡ ልብሱ ፡
የተጐዳ ፡ ሰው ፡ ነው ፡ ድህነት ፡ ያጠቃው
ሰውነቱ ፡ ከስቷል ፡ የመደብር ፡ ዕቃው ፡
አሮጌ ፡ ብቻ ፡ ነው ፡ ቈሻሻ ፡ ሰባራ ፤
ተጠርጎ ፡ የማያውቅ ፡ የለበሰ ፡ ዐቧራ ።
ከሱቁ ፡ ስገባ ኔም አስተውዬ
እሱን ፡ባየሁ ቍጥር አሰብኩ እንዲህ ብዬ
በማንቱ ፡ ከተማ ፡ ለሰው ፡ መርዝ ፡ የሸጠ
በምንም ፡ አኳኋን ፡ አውጥቶ ፡ የሰጠ ፡
ምንም ፡ እንኳ፡ የሚያዝ ፡ በሞት ፡ እንዲቀጣ ፡
ኀይለኛ ፡ ዐዋጅ ፡ ቢኖር ፡ ተጽፎ ፡ የወጣ ፡
መርዝ ፡ የሚፈልግ ፡ ሰው ፡ ብዙ ፡ ገንዘብ ፡ ሰጥቶ ፡
ይህን ችግረኛ፡ ቢጠይቀው ፡ መጥቶ ፡
አይጠረጠርም : እንቢ ፡ እንደማይለው ፤
ስለዚህ ፡ ጠርቼ ፡ እስቲ ፡ ልሞክረው ፡
አንተ ፡ መድኀኒት ፡ ሽያጭ፡ እባክህ ፡ ወዲህ ፡ ና ።
#መድኀኒት_ሽያጭ ።
ምነው ፡ ሮሜዎ አይዶለም ወይ ፡ ደኅና ?
#ሮሜዎ ።
ሰው ፡ አንተን ይሻሃል ባጣ ፡ ጊዜ ፡ ጤና፡
አንድ ፡ ነገር ፡ አሁን ፡ ልንገርህ ፡አድምጠኝ
ቶሎ ፡ የሚገድል ፡ ብርቱ ፡ መርዝ ፡ ስጠኝ፡
አርባ ፡ ዱካ ፡ ልስጥህ ለመርዝህም ዋጋ
አንተም ፡ ትሆናለህ ፡ በዚህ ፡ ባለጸጋ ፡
አንተን ፡ ለመሰለ ፡ በጣም ፡ ለተጐዳ ፡
ይህ ፡ ብዙ ፡ ገንዘብ ነው በጣም የሚረዳ
#መድኅኒት ፡ ሽያጭ ።
ኀይለኛ ፡ መርዝ አለኝ በመደብሬ ውስጥ
ግን ፡ ባዋጅ ፡ ክልክል ነው፡ለማንም፡ እንዳልሸጥ ።
#ሮሜዎ ።
ሞኝ ፡ ነህ ፡ መሰለኝ ፡ ዐዋጅ ፡ብሎ ፡ ጣጣ
ራብ ፡ ለገደለህ ፡ ዐጥንትህ ' ለወጣ'
ላንተ ፡ ምን ' ጠቀመህ ይልቅ ስጠኝ' ቶሎ
ድኽነት ፡ ይታያል ፡ በመልክህ ፡ ተሥሎ'
ጒዳት ፡ አቈራምዶ፡ ችግር ፡ ያሸነፈህ
💫ይቀጥላል💫
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
#ሞግዚት ።
ሞታለች ፡ ሞታለች ፡ ጕድ ፡ ነው ፡ የሚያስደንቅ ,
#የካፑሌ_ሚስት ።
ምን ፡መድኀኒት ላምጣ ወዴት ስፍራ ሄጄ
#ካፑሌ ።
ቆዩ፡እስቲ፡እኔ፡ልያት፡ የታለች፡ ቀዝቃዛ ፡ (እየዳበሳት).
ፈጽማ ፡ ሞታለች ፡ በምን ፡ ጕዴ በዛ
ሌሊት፡ በጨለማ ፡ ፀሓይዋ፡ ሳትወጣ ፡
ልጄ ፡ አበባዬ ፡ ወድቃለች ፡ ተቋርጣ ።
#ሞግዚት ።
የተረገመ ፡ ነው ፡ አወይ ፡ የዛሬው ቀን ፤
#የካፑሌ_ሚስት
ምነው ፡ ብንቀበር ፡ ሁላችንም ፡ አልቀን !
#ካፑሌ
ምንም ፡ አልናገር' ምላሴ 'ታሰረ
ልሳኔ ፡ በሐዘን 'ተቁልፎ ፡ ቀረ ።
(አባ ' ሎራና 'ፓሪስ ' በሙዚቃ ገቡ ።)
#አባ_ሎራ
ወደ ፡ ቤተ ፡ ክርስቲያን እንሂድ ፍጠኑ
ሙሽራዋን ጥሩ እናንተም ቶሎ'ኑ ።
#ካፑሌ
ጉድ ሆነናል ዛሬ ይተዉ አባቴ
ጕድ ፡ ለማየት ፡ ኖሯል ፡ የቈየች ፡ ሕይወቴ
እኔ ፡ ወዴት ፡ ልድረስ ፡ የት ፡ አባቴ ፡ ልግባ
ሞተች ፡ ተቀጠፈች ፡ ልጄ ፡ የኔ ፡ ኣበባ ።
እናቷ ፡ ሳታስብ ፡ ኣባቷ ፡ ሳይሰማ ፡
ሞት ፡ የሚባል ፡ ሌባ ፡ ሌሊት በለጨለማ
ለካ ፡ ከቤታችን ፡ ገብቶ ፡ ተደብቆ ፡
ይዟት ፡ ሄዶ ፡ ኖሯል ፡ ልጃችንን ፡ ሰርቆ ፤
እንዴት ፡ ጉድ፡ ሆነናል ፡ እንዲህ ፡ ተደግሶ
ሰርጓ ሐዘን ፡ ሆነ ደስታችን ለቅሶ ።
#ፓሪስ።
እኔ ፡ ዕድለ ፡ ቢሱ፡ እንዴት፡ ያለ ፡ መርዶ፡
እንዴት ፡ ያለ ፡ሐዘን ፡ ጠበቀኝ ፡ ተወልዶ
#የካፑሌ_ሚስት ።
የተረገመ ፡ ነው ፡ አወይ ፡ የዛሬ ፡ ቀን
ቀረን ፡ እኮ ፡ ሰዎች ፡ እንደዚህ ፡ ተሳቀን ፡
ያይኖቼ ፡ ማረፊያ ብትኖረኝ አንዲት ፡ ልጅ
ያንድ ፡ ቀን 'ደስታ' ለማየት'ስዘጋጅ፡
ለማን ኣቤት ልበል ፡ ሞት ፡ ይዞብኝ ፡ ሄደ
ሆዴ ተቃጠለ አንጀቴ ፡ ነደደ
#አባ_ሎራ "
ይብቃ ፡ ለሐዘኑ ፡ አድርጉለት ፡ መጠን ፤
አስቡ ፡ ይችን 'ልጅ' እግዜር ፡ ነው' የሰጠን
አሁንም ፡እግዚአብሔር ወሰዳት መልሶ :
ሐዘናችሁ ፡ አይሁን ፡ ያረመኔ ፡ ለቅሶ ፡
ቀረባት ፡ ብላችሁ ፡ የመሬት ፡ ደስታ ፡
ጸጸታችሁ ፡ አይሁን ፡ በጣም ፡ የበረታ ፡
የመሬት ፡ ደስታ ፡ ምንም ፡ የለው ፡ ዋጋ ፤
ይልቅ አይበልጥም ወይ የሰማይቤት ጸጋ፡
ከሚያልፍ ፡ዓለም ወጥታ፡ ከዘለዓለም ቤቷ
መተላለፍ፡ ነው ፡ በሰላም ፡ መግባቷ ፡
መሆኑ ፡ ቀረና፡ ሰርጓ በመሬት ላይ፤
ብርሃን ፡ ወዳለበት፡ሄደች፡ ወደ ፡ ሰማይ ፡
እናድርጋት ፡ ስንል ፡ ምድራዊት ፡ ሙሽራ ፡
አይሆናትም ፡ ብሎ ፡ የመሬት ፡ መከራ ፡
ሺሕ ፡ ጊዜ ፡ የላቀ ፡ ደስታ፡ አዘጋጅቶ ፡
እግዚአብሔር ፡ ወሰዳት ፡በፈቃዱ ፡ ጠርቶ
የሰርግ ልብሷን ለብሳ እንዳማረች በክብር
በሉ ፡ ያዟትና ፡ እንሂድ ፡ መቃብር ።
#ሮሜዎ ። (በተሰደደበት ፡ አገር 'ሆኖ)
መሠረት ፡ ቢኖረው ፡ የኔ ፡ ሕልም፡ ዛሬ ፡
አገኝ ፡ ይመስለኛል ፡ ደስ የሚያሰኝ ፡ ወሬ
ዡልዬት ፡ ስትመጣ ፡ ስታገኘኝ ፡ ሞቼ ፡
አልቅሳ ፡ ስትስመኝ ፡ እኔ ፡ ተዘርግቼ ።
ኋላም ፡ በሷ ፡ ትንፋሽ ፡ ሕይወቴን ፡ አድሼ
ከሞት ፡ ተነሥቼ ፡ አየሁኝ ፡ ነግሼ ።
በጣም ፡ ደስ ፡ ብሎኛል ፡ ዛሬ ጧት፡ጀምሮ
ሰላም ፡ ይሰማኛል ፡ የመንፈስ ፡ የአእምሮ
(ቤልሻጥር ቦት ጫማ አድርጎ፡ መጣ)
ቤልሻጥር ፡ጐበዙ፡ እንኳን ፡ ገባህ ፡ ደኅና'
ምን ወሬ ይዘህ መጣህ ዛሬ ከቤሮና ?
ዡልዬት ደኅናነች ወይ አባቴስ እንዴት ነው ?
እሷ ፡ ደኅና፡ ብትሆን ፡ግድ የለም የቀረው
ዡልዬት ፡እንደ ፡ምን ነች ? አሁንም አድሼ
ልጠይቅህ ፡ በጣም ሺሕ ፡ ጊዜ ፡ መልሼ
#ቤልሻጥር ።
ደኅና ፡ ነች ፡ ልበልህ ፡ አልነካትም ፡ ዐፈር
እንደሌላው ፡ ፍጥረት ፡ መሬት ፡ ሳትቀበር
ከመቃብሩ ፡ ቤት፡ ሠርተው ፡ አባቷ
ካዘጋጁት ፡ ገብታ ፡ እግሮቿም ፡ እጆቿ ፡
ታስረው ፡ ሳትገነዝ ፡ በማዕርግ ፡ ተንጋላ ፡
ተኝታ ፡ ኣየናት ፡ ያንቀላፋች ፡ መስላ ።
እንዲህ ፡ በጌትነት ፡ ዡልዬት ፡ ተቀበረች ፤
በቃ ፡ የሷ፡ ነገር ፡ እንደ ፡ ዘበት ፡ ቀረች ።
ነፍሷ ፡ ግን ወደ እግዜር ዐረገች ወደ ላይ
ዐርፋ ፡ ከዚህ ዓለም ወጣች ፡ ወደ ሰማይ
#ሮሜዎ ። (በድንጋጤ ፊቱ ተለወጠ)
ምን ፡ አገኛትና ? በምን ፡ የተነሣ ?
#ቤልሻጥር ።
ጧት፡ ባልጋዋ ፡ ላይ ፡ በድን ሆና ሬሳ፡
ተገኘች ፡ ከእንቅልፍ፡ ሳትነቃ ፡ ሞታ ፤
#ሮሜዎ ።
እንደዚህ ፡ ከሆነ 'የዡልዬት ፡ ሁኔታ ፡
ደግ ፡ ነው መልካም ፡ ነው ፤ ብዕር፡ቀለም፡ኣምጣ፡
ፈረሶች ፡ ተከራይ ፈጥነህ መንደር ፡ውጣ
ማንም ሰው ሳያየኝ ማንም ሰው ሳይሰማ
መሄዴ' ነውና ፡ ሌሊት ፡ በጨለማ ።
#ቤልሻጥር
እባክህ ፡ ጌታዬ ፡ ፊትህ ፡ ተለወጠ ፤
ደምህም ፡ ጠቈረ ፡ ልቤ ፡ ደነገጠ '
ቻለው ፡ ሐዘንህን ፡ ከትዕግሥት ፡ ጋራ
#ሮሜዎ ።
አትሥጋ ፡ ግድ የለም ፡ ቤልሻጥር አትፍራ
የማይሆን አይሆንም የሚሆን ፡ ይሆናል !
ይልቅ ፡ቶሎ ፡ ፍጠን ፡ ጊዜው ፡ ያልፍብናል
(ቤልሻጥር ሄደ፤ ሮሜዎ'ብቻውን) »
እንገናኛለን ፡ ዥልዬት ፡ ዛሬ ፡ ማታ ፤
ወዳንቺ ፡ ለመድረስ ፡ ቶሎ ፡ በደስታ ፡
መንገዱን ፡ መፈለግ ፡ አለብኝ ፡ ግዴታ ፡
መድኀኒት ፡ የሚሸጥ ፡ አንድ ፡ ጎረቤቴ ፡
መኖሩን ፡ ዐውቃለሁ ፥ እኔ ፡ በሕይወቴ ፡
አይቼ ፡ አላውቅም ፡ ችግረኛ ፡ እንደ ፡ እሱ
ሁል ፡ ጊዜ ፡ ያደፈ፡ ቀዳዳ ፡ ነው ፡ ልብሱ ፡
የተጐዳ ፡ ሰው ፡ ነው ፡ ድህነት ፡ ያጠቃው
ሰውነቱ ፡ ከስቷል ፡ የመደብር ፡ ዕቃው ፡
አሮጌ ፡ ብቻ ፡ ነው ፡ ቈሻሻ ፡ ሰባራ ፤
ተጠርጎ ፡ የማያውቅ ፡ የለበሰ ፡ ዐቧራ ።
ከሱቁ ፡ ስገባ ኔም አስተውዬ
እሱን ፡ባየሁ ቍጥር አሰብኩ እንዲህ ብዬ
በማንቱ ፡ ከተማ ፡ ለሰው ፡ መርዝ ፡ የሸጠ
በምንም ፡ አኳኋን ፡ አውጥቶ ፡ የሰጠ ፡
ምንም ፡ እንኳ፡ የሚያዝ ፡ በሞት ፡ እንዲቀጣ ፡
ኀይለኛ ፡ ዐዋጅ ፡ ቢኖር ፡ ተጽፎ ፡ የወጣ ፡
መርዝ ፡ የሚፈልግ ፡ ሰው ፡ ብዙ ፡ ገንዘብ ፡ ሰጥቶ ፡
ይህን ችግረኛ፡ ቢጠይቀው ፡ መጥቶ ፡
አይጠረጠርም : እንቢ ፡ እንደማይለው ፤
ስለዚህ ፡ ጠርቼ ፡ እስቲ ፡ ልሞክረው ፡
አንተ ፡ መድኀኒት ፡ ሽያጭ፡ እባክህ ፡ ወዲህ ፡ ና ።
#መድኀኒት_ሽያጭ ።
ምነው ፡ ሮሜዎ አይዶለም ወይ ፡ ደኅና ?
#ሮሜዎ ።
ሰው ፡ አንተን ይሻሃል ባጣ ፡ ጊዜ ፡ ጤና፡
አንድ ፡ ነገር ፡ አሁን ፡ ልንገርህ ፡አድምጠኝ
ቶሎ ፡ የሚገድል ፡ ብርቱ ፡ መርዝ ፡ ስጠኝ፡
አርባ ፡ ዱካ ፡ ልስጥህ ለመርዝህም ዋጋ
አንተም ፡ ትሆናለህ ፡ በዚህ ፡ ባለጸጋ ፡
አንተን ፡ ለመሰለ ፡ በጣም ፡ ለተጐዳ ፡
ይህ ፡ ብዙ ፡ ገንዘብ ነው በጣም የሚረዳ
#መድኅኒት ፡ ሽያጭ ።
ኀይለኛ ፡ መርዝ አለኝ በመደብሬ ውስጥ
ግን ፡ ባዋጅ ፡ ክልክል ነው፡ለማንም፡ እንዳልሸጥ ።
#ሮሜዎ ።
ሞኝ ፡ ነህ ፡ መሰለኝ ፡ ዐዋጅ ፡ብሎ ፡ ጣጣ
ራብ ፡ ለገደለህ ፡ ዐጥንትህ ' ለወጣ'
ላንተ ፡ ምን ' ጠቀመህ ይልቅ ስጠኝ' ቶሎ
ድኽነት ፡ ይታያል ፡ በመልክህ ፡ ተሥሎ'
ጒዳት ፡ አቈራምዶ፡ ችግር ፡ ያሸነፈህ
💫ይቀጥላል💫
👍1
#ሮሜዎና_ዡልዬት
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት(የመጨረሻ
ክፍል)
#ሁለተኛ_ዘበኛ ።
ይኸው ፡ አገኘነው ፡ የሮሜዎን ፡ አሽከር ።
#የመጀመሪያ_ዘበኛ ።
መስፍኑ ፡ እስቲመጡ፡ እንዳይመረመር ።
(ሦስተኛ ፡ ዘበኛ ፡ ከአባ ' ሎራ፡ጋራ፡ መጣ)
#ሦስተኛ_ዘበኛ ።
እያንቀጠቀጠው ፡ ጥግ ፡ ይዞ ፡ ሲያለቅስ
ይኸውና ፡ ደግሞ ፡ አገኘሁ ፡ አንድ ፡ ቄስ ፡
ለምን ፡ እንደ ፡ ያዘው ፡ አልታወቀም፡ ከቶ ፡
ጕጠቱን ፡ ቀማነው ፡ በእጁ ፡ ላይ ፡ተገኝቶ
#የመጀመሪያ_ዘበኛ ።
መስፍኑ ፡ እስቲመጡ ፡ እሱን ፡ አትልቀቁ ፤
የሚጠረጠር ፡ ነው ፡ ይዛችሁ ፡ ጠብቁ ።
(መስፍኑ ፡ ታጅቦ ፡ መጣ) ።
#መስፍን ።
እኔን ፡ የሚያስጠራ ፡ ሳይነጋ ፡ ሌሊቱ ፤
ምንድነው ፡ንገሩኝ ፡ እስቲ ፡ ምክንያቱ ? ..
(ካፑሌ ' ፤ ሚስቱና ሌሎች ሰዎች መጡ)
#ካፑሌ ።
ምስጢሩ ፡ ምንድነው ፡ የሰዉ ጫጫታ ?
#የካፑሌ_ሚስት ።
እረ ፡ እንዲህ ፡ አይደለም ፡ የሕዝቡ ጋጋታ ፡
ግማሹ ፡ ሮሜዎ ፡ ግማሹ ፡ ዡልዬት ፡
ግማሾቹም ፡ ፓሪስ ፡ እያሉ ፡ በጩኸት ፡
ወደ ፡ እኛ ፡ መቃብር ፡ ገቡ ፡ እየተጋፉ ።
#መስፍን ።
ነገሩን ፡ ንገሩኝ፡ ደግም ፡ ሆነ፡ ክፉ ።
#የመጀመሪያ_ዘበኛ ።
ልዑል ፡ ሆይ ፡ ያስተውሉ'ፓሪስን ፡ተገድሎ
እዩት ፡ ሮሜዎ ፡ መሬት ፡ ላይ ፡ ተንጋሎ ፡
ቀድሞ ፡ የሞተችው ፡ ዡልዬት ፡ ተመልሳ፣
እይዋት ፡ እሷ ፡ ደግሞ ፡ በደም ተለውሳ ።
#መስፍን ።
ይህ ፡ ዐመፅ ፡ እንደ፡ምን ፡ ሆኖ ፡ እንደ ፡ ተሠራ ፍጠኑ ፡ በቶሎ ፡ይደረግ ፡ ምርመራ
#የመጀመሪያ_ዘበኛ ።
የሮሜዎ ፡ ሎሌ ፥ ካንድ ፡ ካህን ፡ ጋራ ፡
እነሆ ፡ ተገኝቷል ፡ አሁን ፡ በዚህ ፡ ስፍራ ።
#ካፑሌ ።
ሚስቴ ፡ ተመልከቺ ፡ ልጃችን ፡ ተኝታ ፥
እዪው ፡ ደሟ ፡ ሲፈስ ሆዷ ላይ ፡ ተወግታ
አስተውዪው ይህ ጩቤ ከመጣበት ፡ ቦታ
ከሞንታግ ልጅ ላይ ነው ተመልከች አፎቱ
ባዶውን ፡ ይታያል ፡ ይግባሽ ፡ ምክንያቱ ።
#የካፑሌ_ሚስት ።
እባክህን ፡ ተወኝ ፡ እኔ ፡ አልችልም ፡ ማየት
ወይ፡ልጄ ፡ ወይ ልጄ ፡ ወይ፡ ልጄ ፡ ዝልዬት
ሐዘን ፡ ጨፈለቀኝ ፡ ውሃ ፡ ሆንኩኝ ፡ እኔ ፤
ይህንን ፡ ትልቅ ፡ ጕድ ፡ ይህንን ፡ ጭካኔ፡
ኣይችልም ፡ አይችልም። ሊመለከት ዐይኔ
(ሞንታግና ፡ ሌሎች ፡ ሰዎች ፡ መጡ) "
#መስፍን ።
ሞንታግ ፡ ወዲህ ፡ ቅረብ ፡ ተመልከተው ፡ አንተ ፡ልጅህን ፡ አስተውለው ፥ እየው ፡ እንደ ፡ ሞተ ።
#ሞንታግ ።
የልጅዋ ፡ መሰደድ ፡ ሆኖባት ፡ በሽታ ፡
ሚስቴ ፡ ሌሊት ፡ ሞተች በሐዘን ተጐድታ
ያሁን ፡ ሐዘኔ ፡ ግን በጣም ፡ ትልቅ መዓት
የባሰ ፡ ጐዳት፡ ነው ፡ የመጣ ፡ ለቅጣት ።
#መስፍን ።
እንባህን ፡ አግደው ፡ አትቸኵል ፡ ለማልቀስ
በፊት ፡ ምርመራውን ፡ ይገባል ፡ መጨረስ
ያመፁን ፡ ምክንያት፡ ምንጩን ፡ እንወቀው
ምርመራው ይጀመር አብረን ፡ እንዝለቀው
የተያዙት ፡ ሰዎች ፡ በፍጥነት ፡ ይቅረቡ ።
#አባ_ሎራ ።
እዚህ ፡ ያላችሁት ፡ አሁን ፡ ስታስቡ ፡
እኔ ፡ መገኘቴ ፡ በዚህ ፡ ዐመፅ ፡ ቦታ ፡
ያስጠረጥረኛል ፡ ገፍቶ ፡ በግዴታ ፡
ዳሩ ፡ ግን ፡ ነገሩን ፡ ልናገረውና ፡
ተረዱት ፡ ዕወቁት ፡ የኔን ፡ ንጽሕና ።
#መስፍን ።
ታሪኩን ፡ እንስማ ፡ በሉ ፡ ይናገሩ ።
#አባ_ሎራ ።
ሐተታ ፡ አላበዛም ፡ ልናገር ፡ ባጭሩ ፤
ረዥም ፡ አይደለም ፡ቀላል፡ ነው ምስጢሩ
መልካሙ ፡ ሮሜዎ ፡ ይህ አሁን ፡ የሞተው ለዡልዬት ፡ባሏ ነው በተክሊል ተጋብተው
ቃል ኪዳን ሞልተዋል ቈርበው እንደ ሕጉ
በሃይማኖት ሥራት ቃል፡ ኪዳን ሲያደርጉ
የተክሊሉን ፡ ሥራት ፡ ባርኮ ፡ የቀደሰው ፡
እኔው ፡ ራሴ ፡ ነኝ፤ አይደለም ፡ ሌላ ፡ ሰው
በዚያው ቀን ቲባልትን ቢገድለው ፡ ተፈርዶ
ከዚህ ፡ አገር ፡ ወጣ ፡ ሮሜዎ ፡ ተሰዶ፡
ዡልዬት ፡ ዘመዶቿ ፡ ይህንን ፡ ሳያውቁ ፡
ለፓሪስ ፡ ሊድሯት ፡ እሷን ፡ ቢያስጨንቁ ፡
በሐዘን ፡ አልቅሳ ፡ ነገረችኝ ፡ መጥታ ፤
ዘዴ ፡ ካልተገኘ ፡ በገዛ ፡ እጅዋ ፡ ሞታ ፡
ልትድን ፡ አሰበች ፡ ካገኛት ፡ ፈተና ፤
እኔም ፡ በዚህ ፡ ነገር ፡ በጣም ፡ አዘንኩና ፡
መድኀኒት ፡ ሰጠኋት ሕይወት ፡ አጠውልጎ
እንቅልፍ ፡ የሚያስተኛ እንደ ሞት ፡ አድርጎ
ከዚያም ፡ ለሮሜዎ ፡ ወረቀት ፡ ጽፌለት ፡
እንዲመጣ ፡አዘዝኩት ገሥግሦ በፍጥነት
ከእንቅልፋ፡ ስትነቃ የመርዙ ኃይል ፡ አልቆ
እንዲወስዳት ፡ ነበረ ውጭ ፡ አገር ፡ ደብቆ
የኔንም ፡ ወረቀት ፡ የወሰደልኝ ፡ ሰው ፡
የኛ ፡ ካህን ፡ ነበር ፤ እሱም ፡ ሳያደርሰው ፡
እክል፡ ስላገኘው ፡ በሄደበት ፡ ቦታ ፡
መልሶ ፡ አመጣልኝ ፡ ትናንትና ፡ ማታ ።
የዡልየት ፡ መነሻ ፡ ሌሊት ፡ ስለ ፡ ነበር ፡
እኔም ፡ በጨለማ ፡ መጣሁ ፡ ስደናበር ፡
አሳቤ ፡ ነበረ ፡ ሮሜዎ ፡እስቲመጣ ፡
ደብቄ ፡ ላቆያት ፡ ከቤት ፡ ሳላስወጣ ፡
ዳሩ፡ግን ፡ ገሥግሼ ፡ እኔ ፡ ከዚህ ፡ ስደርስ
ወድቀው ፡ አየኋቸው ፡ ሮሜዎና፡ ፓሪስ ።
እሷም ፡ ነቃችና ፡ ወዲያው ፡ ስትነሣ ፡
እግዜር ፡ ያመጣውን ፡ ብትቀበል ፡ ታግሣ
የሚሻል ፡ መሆኑን ፡ ላስረዳት ፡ ሞክሬ ፡
ከደጅ ፡ ድምፅ ሰማሁ ሳጥናናት በምክሬ
ለመንኳት ፡ እንድትሄድ ፡ እኔን ፡ ተከትላ ፥
ምክሬን ፡ አልሰማችም ቀረች እንቢ ፡ ብላ
እኔም ፡ የመጣውን ፡ ለማየት ፡ በኋላ ፤
ወጥቼ ፡ መጣሁኝ ፡ ይኸው ፡ እዚህ ፡ ቦታ
ያስረዳ፡ ነበረ ፡ የዡልዬት ፡ ሁኔታ ፡
ሐዘኗ ፡ መሆኑን ፡ በጣም ፡ የበረታ ።
ከዚያ በኋላ ፡ ግን ፡ የሆነውን ፡ ነገር ፡
አላየሁምና ፡ አልችልም ፡ መናገር ፡
ዡልዬት ፡ ሮሜዎን በተክሊል ፡ ማግባቷን
ታውቀዋለችና ፡ ጠይቁ ፡ ሞግዚቷን ፡
እንግዴህ ፡ ልቀጣ ፡ ቃሌ ፡ ቢገኝበት ፡
በውስጡ ፡ የገባ ፡ ሐሰትና፡ ውሸት
#መስፍን ።
ጻድቅ ፡ሰው ኣድርገን ፡እርስዎን ከማክበር
አቋርጠን ፡ አናውቅም የሮሜዎን ፡ አሽከር
በፍጥነት ፡ አቅርቡት ፡ ያየውን ፡ ይናገር ።
#ቤልሻጥር ።
የዡልዬትን ፡ መሞት ፡ ጌታዬ ፡ ብነግረው ፡
መርዶውን ፡ ሲሰማ ፡ ሐዘን ፡ አሰከረው ፡
ወዲያው ፡ ተነሣና ፡ እየገሠገሠ ፡
ሌሊት ፡ እዚህ ፡ ቦታ ፡ ከኔ ፡ ጋር ፡ ደረሰ ።
ይህንን ፡ ደብዳቤ ፡ ላባቴ ፡ ስጥ ፡ ብሎ ፡
እኔን ፡ እንዳልገባ ፡ በብርቱ ፡ ከልክሎ ፡
ትእዛዙን ፡ ባልፈጽም ፡ በሞት ፡ አስፈራርቶ
አየሁት ፡ ሲገባ ፡ እኔን ፡ እዚህ ፡ ትቶ ።
#መስፍን ።
ደብዳቤውን ፡ ስጠኝ እስቲ ፡ ልመልከተው
የፓሪስም ፡ አሽከር ፡ ይጠራ ወዴት ፡ ነው ?
(የፓሪስ • አሽከር ፡ ቀረበ) ።
ሌሊት ፡ በጨለማ ፡ ደግሞ ፡ ያንተ ፡ ጌታ ፡
እዚህ ፡ ለምን ፡ መጣ ፡ እመቃብር ፡ ቦታ ?
#የፓሪስ_አሽከር ።
አበባ ፡ ሊያስቀምጥ ፡ እመቃብሯ ፡ ላይ ፡
መጣና ፡ እኔንም ፡ እዚሁ ፡ ሁኜ ፡ እንዳይ ፡
አዞኝ ፡ እንድጠብቅ ፡ እዚህ ፡ እንድቀመጥ
ሰው ፡የመጣ እንደሆን ምልክት እንድሰጥ
ስጠብቅ አንድ፡ ሰው፡ መብራት ይዞ መጣ
አፍጨሁ ፡ ጌታዬም ፡ ከመቃብር ፡ ወጣ ።
ሁለቱ ፡ ሲዋጉ ፡ ይኸው ፡ እዚህ ፡ ስፍራ ፡
ቶሎ ፡ ሮጬ ፡ ወጣሁ ፡ ዘበኛ ፡ ልጠራ ።
#መስፍን ።
አምነን ፡ ለመቀበል ፡ እኛ ፡ የቄሱን ፡ ቃል ፡
ተመልክቼዋለሁ ፥ ደብዳቤው ፡ ይበቃል ።
የፍቅራቸው ፡ ነገር ፡ የዡልዬትም ፡ መሞት
ይኸው ፡ ይነበባል ፡ በደብዳቤው ፡ ጽፎት
ሁሉንም ፡ ገልጦታል ፤ ከዡልዬትም ፡ ጋራ
ለመሞት መምጣቱን ይኸው እዚህ ስፍራ
መድኀኒት የሚሸጥ ድኻ ሰው ፡ አግኝቶ
መርዝ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት(የመጨረሻ
ክፍል)
#ሁለተኛ_ዘበኛ ።
ይኸው ፡ አገኘነው ፡ የሮሜዎን ፡ አሽከር ።
#የመጀመሪያ_ዘበኛ ።
መስፍኑ ፡ እስቲመጡ፡ እንዳይመረመር ።
(ሦስተኛ ፡ ዘበኛ ፡ ከአባ ' ሎራ፡ጋራ፡ መጣ)
#ሦስተኛ_ዘበኛ ።
እያንቀጠቀጠው ፡ ጥግ ፡ ይዞ ፡ ሲያለቅስ
ይኸውና ፡ ደግሞ ፡ አገኘሁ ፡ አንድ ፡ ቄስ ፡
ለምን ፡ እንደ ፡ ያዘው ፡ አልታወቀም፡ ከቶ ፡
ጕጠቱን ፡ ቀማነው ፡ በእጁ ፡ ላይ ፡ተገኝቶ
#የመጀመሪያ_ዘበኛ ።
መስፍኑ ፡ እስቲመጡ ፡ እሱን ፡ አትልቀቁ ፤
የሚጠረጠር ፡ ነው ፡ ይዛችሁ ፡ ጠብቁ ።
(መስፍኑ ፡ ታጅቦ ፡ መጣ) ።
#መስፍን ።
እኔን ፡ የሚያስጠራ ፡ ሳይነጋ ፡ ሌሊቱ ፤
ምንድነው ፡ንገሩኝ ፡ እስቲ ፡ ምክንያቱ ? ..
(ካፑሌ ' ፤ ሚስቱና ሌሎች ሰዎች መጡ)
#ካፑሌ ።
ምስጢሩ ፡ ምንድነው ፡ የሰዉ ጫጫታ ?
#የካፑሌ_ሚስት ።
እረ ፡ እንዲህ ፡ አይደለም ፡ የሕዝቡ ጋጋታ ፡
ግማሹ ፡ ሮሜዎ ፡ ግማሹ ፡ ዡልዬት ፡
ግማሾቹም ፡ ፓሪስ ፡ እያሉ ፡ በጩኸት ፡
ወደ ፡ እኛ ፡ መቃብር ፡ ገቡ ፡ እየተጋፉ ።
#መስፍን ።
ነገሩን ፡ ንገሩኝ፡ ደግም ፡ ሆነ፡ ክፉ ።
#የመጀመሪያ_ዘበኛ ።
ልዑል ፡ ሆይ ፡ ያስተውሉ'ፓሪስን ፡ተገድሎ
እዩት ፡ ሮሜዎ ፡ መሬት ፡ ላይ ፡ ተንጋሎ ፡
ቀድሞ ፡ የሞተችው ፡ ዡልዬት ፡ ተመልሳ፣
እይዋት ፡ እሷ ፡ ደግሞ ፡ በደም ተለውሳ ።
#መስፍን ።
ይህ ፡ ዐመፅ ፡ እንደ፡ምን ፡ ሆኖ ፡ እንደ ፡ ተሠራ ፍጠኑ ፡ በቶሎ ፡ይደረግ ፡ ምርመራ
#የመጀመሪያ_ዘበኛ ።
የሮሜዎ ፡ ሎሌ ፥ ካንድ ፡ ካህን ፡ ጋራ ፡
እነሆ ፡ ተገኝቷል ፡ አሁን ፡ በዚህ ፡ ስፍራ ።
#ካፑሌ ።
ሚስቴ ፡ ተመልከቺ ፡ ልጃችን ፡ ተኝታ ፥
እዪው ፡ ደሟ ፡ ሲፈስ ሆዷ ላይ ፡ ተወግታ
አስተውዪው ይህ ጩቤ ከመጣበት ፡ ቦታ
ከሞንታግ ልጅ ላይ ነው ተመልከች አፎቱ
ባዶውን ፡ ይታያል ፡ ይግባሽ ፡ ምክንያቱ ።
#የካፑሌ_ሚስት ።
እባክህን ፡ ተወኝ ፡ እኔ ፡ አልችልም ፡ ማየት
ወይ፡ልጄ ፡ ወይ ልጄ ፡ ወይ፡ ልጄ ፡ ዝልዬት
ሐዘን ፡ ጨፈለቀኝ ፡ ውሃ ፡ ሆንኩኝ ፡ እኔ ፤
ይህንን ፡ ትልቅ ፡ ጕድ ፡ ይህንን ፡ ጭካኔ፡
ኣይችልም ፡ አይችልም። ሊመለከት ዐይኔ
(ሞንታግና ፡ ሌሎች ፡ ሰዎች ፡ መጡ) "
#መስፍን ።
ሞንታግ ፡ ወዲህ ፡ ቅረብ ፡ ተመልከተው ፡ አንተ ፡ልጅህን ፡ አስተውለው ፥ እየው ፡ እንደ ፡ ሞተ ።
#ሞንታግ ።
የልጅዋ ፡ መሰደድ ፡ ሆኖባት ፡ በሽታ ፡
ሚስቴ ፡ ሌሊት ፡ ሞተች በሐዘን ተጐድታ
ያሁን ፡ ሐዘኔ ፡ ግን በጣም ፡ ትልቅ መዓት
የባሰ ፡ ጐዳት፡ ነው ፡ የመጣ ፡ ለቅጣት ።
#መስፍን ።
እንባህን ፡ አግደው ፡ አትቸኵል ፡ ለማልቀስ
በፊት ፡ ምርመራውን ፡ ይገባል ፡ መጨረስ
ያመፁን ፡ ምክንያት፡ ምንጩን ፡ እንወቀው
ምርመራው ይጀመር አብረን ፡ እንዝለቀው
የተያዙት ፡ ሰዎች ፡ በፍጥነት ፡ ይቅረቡ ።
#አባ_ሎራ ።
እዚህ ፡ ያላችሁት ፡ አሁን ፡ ስታስቡ ፡
እኔ ፡ መገኘቴ ፡ በዚህ ፡ ዐመፅ ፡ ቦታ ፡
ያስጠረጥረኛል ፡ ገፍቶ ፡ በግዴታ ፡
ዳሩ ፡ ግን ፡ ነገሩን ፡ ልናገረውና ፡
ተረዱት ፡ ዕወቁት ፡ የኔን ፡ ንጽሕና ።
#መስፍን ።
ታሪኩን ፡ እንስማ ፡ በሉ ፡ ይናገሩ ።
#አባ_ሎራ ።
ሐተታ ፡ አላበዛም ፡ ልናገር ፡ ባጭሩ ፤
ረዥም ፡ አይደለም ፡ቀላል፡ ነው ምስጢሩ
መልካሙ ፡ ሮሜዎ ፡ ይህ አሁን ፡ የሞተው ለዡልዬት ፡ባሏ ነው በተክሊል ተጋብተው
ቃል ኪዳን ሞልተዋል ቈርበው እንደ ሕጉ
በሃይማኖት ሥራት ቃል፡ ኪዳን ሲያደርጉ
የተክሊሉን ፡ ሥራት ፡ ባርኮ ፡ የቀደሰው ፡
እኔው ፡ ራሴ ፡ ነኝ፤ አይደለም ፡ ሌላ ፡ ሰው
በዚያው ቀን ቲባልትን ቢገድለው ፡ ተፈርዶ
ከዚህ ፡ አገር ፡ ወጣ ፡ ሮሜዎ ፡ ተሰዶ፡
ዡልዬት ፡ ዘመዶቿ ፡ ይህንን ፡ ሳያውቁ ፡
ለፓሪስ ፡ ሊድሯት ፡ እሷን ፡ ቢያስጨንቁ ፡
በሐዘን ፡ አልቅሳ ፡ ነገረችኝ ፡ መጥታ ፤
ዘዴ ፡ ካልተገኘ ፡ በገዛ ፡ እጅዋ ፡ ሞታ ፡
ልትድን ፡ አሰበች ፡ ካገኛት ፡ ፈተና ፤
እኔም ፡ በዚህ ፡ ነገር ፡ በጣም ፡ አዘንኩና ፡
መድኀኒት ፡ ሰጠኋት ሕይወት ፡ አጠውልጎ
እንቅልፍ ፡ የሚያስተኛ እንደ ሞት ፡ አድርጎ
ከዚያም ፡ ለሮሜዎ ፡ ወረቀት ፡ ጽፌለት ፡
እንዲመጣ ፡አዘዝኩት ገሥግሦ በፍጥነት
ከእንቅልፋ፡ ስትነቃ የመርዙ ኃይል ፡ አልቆ
እንዲወስዳት ፡ ነበረ ውጭ ፡ አገር ፡ ደብቆ
የኔንም ፡ ወረቀት ፡ የወሰደልኝ ፡ ሰው ፡
የኛ ፡ ካህን ፡ ነበር ፤ እሱም ፡ ሳያደርሰው ፡
እክል፡ ስላገኘው ፡ በሄደበት ፡ ቦታ ፡
መልሶ ፡ አመጣልኝ ፡ ትናንትና ፡ ማታ ።
የዡልየት ፡ መነሻ ፡ ሌሊት ፡ ስለ ፡ ነበር ፡
እኔም ፡ በጨለማ ፡ መጣሁ ፡ ስደናበር ፡
አሳቤ ፡ ነበረ ፡ ሮሜዎ ፡እስቲመጣ ፡
ደብቄ ፡ ላቆያት ፡ ከቤት ፡ ሳላስወጣ ፡
ዳሩ፡ግን ፡ ገሥግሼ ፡ እኔ ፡ ከዚህ ፡ ስደርስ
ወድቀው ፡ አየኋቸው ፡ ሮሜዎና፡ ፓሪስ ።
እሷም ፡ ነቃችና ፡ ወዲያው ፡ ስትነሣ ፡
እግዜር ፡ ያመጣውን ፡ ብትቀበል ፡ ታግሣ
የሚሻል ፡ መሆኑን ፡ ላስረዳት ፡ ሞክሬ ፡
ከደጅ ፡ ድምፅ ሰማሁ ሳጥናናት በምክሬ
ለመንኳት ፡ እንድትሄድ ፡ እኔን ፡ ተከትላ ፥
ምክሬን ፡ አልሰማችም ቀረች እንቢ ፡ ብላ
እኔም ፡ የመጣውን ፡ ለማየት ፡ በኋላ ፤
ወጥቼ ፡ መጣሁኝ ፡ ይኸው ፡ እዚህ ፡ ቦታ
ያስረዳ፡ ነበረ ፡ የዡልዬት ፡ ሁኔታ ፡
ሐዘኗ ፡ መሆኑን ፡ በጣም ፡ የበረታ ።
ከዚያ በኋላ ፡ ግን ፡ የሆነውን ፡ ነገር ፡
አላየሁምና ፡ አልችልም ፡ መናገር ፡
ዡልዬት ፡ ሮሜዎን በተክሊል ፡ ማግባቷን
ታውቀዋለችና ፡ ጠይቁ ፡ ሞግዚቷን ፡
እንግዴህ ፡ ልቀጣ ፡ ቃሌ ፡ ቢገኝበት ፡
በውስጡ ፡ የገባ ፡ ሐሰትና፡ ውሸት
#መስፍን ።
ጻድቅ ፡ሰው ኣድርገን ፡እርስዎን ከማክበር
አቋርጠን ፡ አናውቅም የሮሜዎን ፡ አሽከር
በፍጥነት ፡ አቅርቡት ፡ ያየውን ፡ ይናገር ።
#ቤልሻጥር ።
የዡልዬትን ፡ መሞት ፡ ጌታዬ ፡ ብነግረው ፡
መርዶውን ፡ ሲሰማ ፡ ሐዘን ፡ አሰከረው ፡
ወዲያው ፡ ተነሣና ፡ እየገሠገሠ ፡
ሌሊት ፡ እዚህ ፡ ቦታ ፡ ከኔ ፡ ጋር ፡ ደረሰ ።
ይህንን ፡ ደብዳቤ ፡ ላባቴ ፡ ስጥ ፡ ብሎ ፡
እኔን ፡ እንዳልገባ ፡ በብርቱ ፡ ከልክሎ ፡
ትእዛዙን ፡ ባልፈጽም ፡ በሞት ፡ አስፈራርቶ
አየሁት ፡ ሲገባ ፡ እኔን ፡ እዚህ ፡ ትቶ ።
#መስፍን ።
ደብዳቤውን ፡ ስጠኝ እስቲ ፡ ልመልከተው
የፓሪስም ፡ አሽከር ፡ ይጠራ ወዴት ፡ ነው ?
(የፓሪስ • አሽከር ፡ ቀረበ) ።
ሌሊት ፡ በጨለማ ፡ ደግሞ ፡ ያንተ ፡ ጌታ ፡
እዚህ ፡ ለምን ፡ መጣ ፡ እመቃብር ፡ ቦታ ?
#የፓሪስ_አሽከር ።
አበባ ፡ ሊያስቀምጥ ፡ እመቃብሯ ፡ ላይ ፡
መጣና ፡ እኔንም ፡ እዚሁ ፡ ሁኜ ፡ እንዳይ ፡
አዞኝ ፡ እንድጠብቅ ፡ እዚህ ፡ እንድቀመጥ
ሰው ፡የመጣ እንደሆን ምልክት እንድሰጥ
ስጠብቅ አንድ፡ ሰው፡ መብራት ይዞ መጣ
አፍጨሁ ፡ ጌታዬም ፡ ከመቃብር ፡ ወጣ ።
ሁለቱ ፡ ሲዋጉ ፡ ይኸው ፡ እዚህ ፡ ስፍራ ፡
ቶሎ ፡ ሮጬ ፡ ወጣሁ ፡ ዘበኛ ፡ ልጠራ ።
#መስፍን ።
አምነን ፡ ለመቀበል ፡ እኛ ፡ የቄሱን ፡ ቃል ፡
ተመልክቼዋለሁ ፥ ደብዳቤው ፡ ይበቃል ።
የፍቅራቸው ፡ ነገር ፡ የዡልዬትም ፡ መሞት
ይኸው ፡ ይነበባል ፡ በደብዳቤው ፡ ጽፎት
ሁሉንም ፡ ገልጦታል ፤ ከዡልዬትም ፡ ጋራ
ለመሞት መምጣቱን ይኸው እዚህ ስፍራ
መድኀኒት የሚሸጥ ድኻ ሰው ፡ አግኝቶ
መርዝ
👎1