#ቸል እያሉ መጉደል!
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።።።።።።።።።።።።።
ለቅፅበት ህላዌ ፥ ተግተው 'ሚባትሉ
በህብር ታጅበው ፥ ጭረው የሚውሉ
ዶሮዎች!
ለቅመው አዳሪዎች...
ከእጀባው ወጥታ.. .. ከመንጋው ተጠቅታ
በታደነች ጫጩት.. .
ሀዘን ተሸብረው ፥ ለስጋት ተድረው ፥ ጮኸው ይንጫጫሉ
ከአፍታ በኋላ.. .
ዳግም ፍርሀት ሽረው ፥ በኗሪነት ተስፋ ፥ ጥሬ ይለቅማሉ ።
#እነዛ ዶሮዎች.. .
አንድም በፍርሀት
አንድም በቸልታ
አንድ ጊዜ በጩኸት
አንዴ በፀጥታ...
ጥሬ ሲናጠቁ ፥ መሬት እየጫሩ
ከቁጥር ተናንሰው ...
ከመንጋነት ጎድለው ፥ ምንም ሆነው ቀሩ።
#አሁን በዛ መሬት!
ለቅፅበት ህላዌ ፥ ተግተው 'ሚባትሉ
በህብር ታጅበው ፥ ጭረው የሚውሉ
አዳዲስ ዶሮዎች.. .
ጭሮ አዳሪዎች.. .
አንድም በፍርሀት
አንድም በቸልታ
አንድ ጊዜ በጩኸት
አንዴ በፀጥታ...
ኗሪ ነን እያሉ ... ጥሬ ይለቅማሉ ።
#እኔ
#ድመት ይታየኛል!
እንደ ሙት መልዓክ ፥ ጥፍሮቹን ያሾለ
ነፍስን ጌጥ አድርጎ ፥ አይኖቹን የኳለ
ጨለማውን ህልፈት ፥ ጀርባው ላይ ያዘለ
ቀስ እያለ ይቀርባል.. .
...........................፥ ቸልታቸው አለ ።
@getem
@getem
@getem
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።።።።።።።።።።።።።
ለቅፅበት ህላዌ ፥ ተግተው 'ሚባትሉ
በህብር ታጅበው ፥ ጭረው የሚውሉ
ዶሮዎች!
ለቅመው አዳሪዎች...
ከእጀባው ወጥታ.. .. ከመንጋው ተጠቅታ
በታደነች ጫጩት.. .
ሀዘን ተሸብረው ፥ ለስጋት ተድረው ፥ ጮኸው ይንጫጫሉ
ከአፍታ በኋላ.. .
ዳግም ፍርሀት ሽረው ፥ በኗሪነት ተስፋ ፥ ጥሬ ይለቅማሉ ።
#እነዛ ዶሮዎች.. .
አንድም በፍርሀት
አንድም በቸልታ
አንድ ጊዜ በጩኸት
አንዴ በፀጥታ...
ጥሬ ሲናጠቁ ፥ መሬት እየጫሩ
ከቁጥር ተናንሰው ...
ከመንጋነት ጎድለው ፥ ምንም ሆነው ቀሩ።
#አሁን በዛ መሬት!
ለቅፅበት ህላዌ ፥ ተግተው 'ሚባትሉ
በህብር ታጅበው ፥ ጭረው የሚውሉ
አዳዲስ ዶሮዎች.. .
ጭሮ አዳሪዎች.. .
አንድም በፍርሀት
አንድም በቸልታ
አንድ ጊዜ በጩኸት
አንዴ በፀጥታ...
ኗሪ ነን እያሉ ... ጥሬ ይለቅማሉ ።
#እኔ
#ድመት ይታየኛል!
እንደ ሙት መልዓክ ፥ ጥፍሮቹን ያሾለ
ነፍስን ጌጥ አድርጎ ፥ አይኖቹን የኳለ
ጨለማውን ህልፈት ፥ ጀርባው ላይ ያዘለ
ቀስ እያለ ይቀርባል.. .
...........................፥ ቸልታቸው አለ ።
@getem
@getem
@getem
ድርሳነ ፍቅር!
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።
#አንቺ የእኔ ጣዖት!
እኔ ያንቺ አማኝ
የምዕመኑ ጠሎት ቅዳሴና አዛኑ
በየት በኩል ይሰማኝ?
።።።
እሳት ያንቺ ገላ ~ መብረቅ ያንቺ መውደድ
በየት መንገድ ልጓዝ ~ እምን ላይ ልራመድ?
ዓይኖችሽ ጉልላት
ጥርሶችሽ በረዶ
ጣቶችሽ አለንጋ....
ሠንበር የወረሰው ~ ቁስል ልቤን ይዤ
እንደምን አልሰጋ?
።።።።
#እኔ
መድሀኒቴ አንቺ
በሽታዬም አንቺ
አንቺን እየዋጥሁኝ ~ አንቺን የምታመም
ባንቺ እየታመምሁኝ ~ ባንቺ የምታከም
.
ባለ አንድ ድዌያም ~ ባለ አንድ ክኒና
ወይ አልሞት ፥ ወይ አልድን
ወይ አልኖር በደህና!
@getem
@getem
@getem
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።
#አንቺ የእኔ ጣዖት!
እኔ ያንቺ አማኝ
የምዕመኑ ጠሎት ቅዳሴና አዛኑ
በየት በኩል ይሰማኝ?
።።።
እሳት ያንቺ ገላ ~ መብረቅ ያንቺ መውደድ
በየት መንገድ ልጓዝ ~ እምን ላይ ልራመድ?
ዓይኖችሽ ጉልላት
ጥርሶችሽ በረዶ
ጣቶችሽ አለንጋ....
ሠንበር የወረሰው ~ ቁስል ልቤን ይዤ
እንደምን አልሰጋ?
።።።።
#እኔ
መድሀኒቴ አንቺ
በሽታዬም አንቺ
አንቺን እየዋጥሁኝ ~ አንቺን የምታመም
ባንቺ እየታመምሁኝ ~ ባንቺ የምታከም
.
ባለ አንድ ድዌያም ~ ባለ አንድ ክኒና
ወይ አልሞት ፥ ወይ አልድን
ወይ አልኖር በደህና!
@getem
@getem
@getem
#የስሌት #ጋብቻ
#አንቺ
ሽማግሌ አዘጋጅ ብለሽ ተናግረሻል
ምን አለው ይሉኛል ብለሽ ተጨንቀሻል
#እኔ
ከቀየው መርጬ
በቂ ሽማግሌ አዘጋጅቻለሁ
የሌለኝ ነገር
ለራሴ አለኝ ብዬ በቃል ሸምድጃለሁ
#እነሱ
ቤተዘመድ መጥቶ
ምን አለው ለማለት ማልዶ ይሰለፋል
ሽማግሌ ከቦ
ምን አለው ለሚባል
የወላጅ ጥያቄ የሐሰት መልስ ይፅፋል
#ውዴ #አትጨነቂ
ያንቺ ብቻ አይደለም የሀገር ነው ችግሩ
እኛም ቤት ብትመጪ ይሔው ነው ነገሩ
#አምና
የታናሽ እህቴ
የልጅነት ፍቅሯ አመት በአል አስታኮ
በፍቅር መርቀን
ፈቅደን እንድንሰጠው ሽማግሌ ልኮ
#መልስ #ሲጠባበቅ
በዚህ ወገን ሆኜ እኔም ጠይቄያለሁ
ማይደርስብኝ መስሎኝ ምን አለው ብያለሁ
በሴት ወገን ስንሆን የወንዱን ባናውቅም
ምን አለው ተብሎ ሰው አይጠየቅም
ሀቅ ተዟዙሮ
ቦታ ተቀያይሮ
የትናንት ተቀባይ ከነገ ወዲያ ይልካል
በሴቷ ጠይቆ በወንድ ይጠየቃል
ሸፋፍነነው እንጂ
ደፍረን ከጠራነው ነገሩ ያሳስባል
በንግድ አጠያየቅ
ምን አለው አይደለም ስንት አለው ነው ሚባል
ባንክ ቤት ስንት አለው በጥሬው ያኖረው
ስንት መኪና አለው የሚያሽከረክረው
ስንት ካሬ መሬት ካርታ የወጣለት
ስንት ክፍል ቪላ የተንጣለለለት
በልጅ የደም ቀለም የሌለንን ስንስል
ልጅ የምንድር ሳይሆን ገዢ ነው ምንመስል
የመመኘት ቀመር
የማዟዟር ብዜት በዘመን ሲጣፋ
ምን አለው ነው እንጂ
ከዬት አመጣው የሚል ሽማግሌ ጠፋ
#እኔ #ምለው ?
የማካፈል ስሌት ዞሮ የመጣ ‘ለት
ምን ያህል ይዘናል ምን አለው ለማለት
#ይልቅ
እግዚአብሔር አድሎት
በጥላቻ ዘመን የሰው ልጅ ሲፋቀር
አፍቃሪ ልብና
ሁሉም ነገር አለው ከሀብት በስተቀር
ሀቁን እያወቅነው ውጠን ከማባበል
ምን አለውን ትተን ምን የለውም እንበል
=====||=====
✍ከሙሉቀን ሰ•
@getem
@getem
@beppa_19
#አንቺ
ሽማግሌ አዘጋጅ ብለሽ ተናግረሻል
ምን አለው ይሉኛል ብለሽ ተጨንቀሻል
#እኔ
ከቀየው መርጬ
በቂ ሽማግሌ አዘጋጅቻለሁ
የሌለኝ ነገር
ለራሴ አለኝ ብዬ በቃል ሸምድጃለሁ
#እነሱ
ቤተዘመድ መጥቶ
ምን አለው ለማለት ማልዶ ይሰለፋል
ሽማግሌ ከቦ
ምን አለው ለሚባል
የወላጅ ጥያቄ የሐሰት መልስ ይፅፋል
#ውዴ #አትጨነቂ
ያንቺ ብቻ አይደለም የሀገር ነው ችግሩ
እኛም ቤት ብትመጪ ይሔው ነው ነገሩ
#አምና
የታናሽ እህቴ
የልጅነት ፍቅሯ አመት በአል አስታኮ
በፍቅር መርቀን
ፈቅደን እንድንሰጠው ሽማግሌ ልኮ
#መልስ #ሲጠባበቅ
በዚህ ወገን ሆኜ እኔም ጠይቄያለሁ
ማይደርስብኝ መስሎኝ ምን አለው ብያለሁ
በሴት ወገን ስንሆን የወንዱን ባናውቅም
ምን አለው ተብሎ ሰው አይጠየቅም
ሀቅ ተዟዙሮ
ቦታ ተቀያይሮ
የትናንት ተቀባይ ከነገ ወዲያ ይልካል
በሴቷ ጠይቆ በወንድ ይጠየቃል
ሸፋፍነነው እንጂ
ደፍረን ከጠራነው ነገሩ ያሳስባል
በንግድ አጠያየቅ
ምን አለው አይደለም ስንት አለው ነው ሚባል
ባንክ ቤት ስንት አለው በጥሬው ያኖረው
ስንት መኪና አለው የሚያሽከረክረው
ስንት ካሬ መሬት ካርታ የወጣለት
ስንት ክፍል ቪላ የተንጣለለለት
በልጅ የደም ቀለም የሌለንን ስንስል
ልጅ የምንድር ሳይሆን ገዢ ነው ምንመስል
የመመኘት ቀመር
የማዟዟር ብዜት በዘመን ሲጣፋ
ምን አለው ነው እንጂ
ከዬት አመጣው የሚል ሽማግሌ ጠፋ
#እኔ #ምለው ?
የማካፈል ስሌት ዞሮ የመጣ ‘ለት
ምን ያህል ይዘናል ምን አለው ለማለት
#ይልቅ
እግዚአብሔር አድሎት
በጥላቻ ዘመን የሰው ልጅ ሲፋቀር
አፍቃሪ ልብና
ሁሉም ነገር አለው ከሀብት በስተቀር
ሀቁን እያወቅነው ውጠን ከማባበል
ምን አለውን ትተን ምን የለውም እንበል
=====||=====
✍ከሙሉቀን ሰ•
@getem
@getem
@beppa_19
#ሀሰሳ #አክቲቭ — ኢ — ዝም
በዚህ በኔ ትውልድ
በዚህ በኛ ዘመን
ከሰዎች ሞት ይልቅ ~ አሟሟት ቢታይም
ገዳዩ ነው እንጂ ~ ሞት አይለያይም
#እኔ #አክቲቪስት #ነኝ
ለሰዎች ምታገል ~ የህሊና ባለእዳ
ሰው በሰውነቱ ~ ደርሶ እንዳይጎዳ
ለሌሎች ልሞላ ~ ከራሴ ላይ ምዘርፍ
ርቀቴን ጠብቄ ~ ትውልዴን የማተርፍ
#እኔ #አክቲቪስት #ነኝ
በዛሬ ቀለሜ ~ የሰው ነገን ምስል
ሸፍኜ ማስነጥስ ~ አፌን ይዤ ምስል
ሠው ከመሆን ውጪ ~ ብዙ ማልጠበብ
ነብሶችን ለማዳን ~ እጆቼን ምታጠብ
#እኛ #አክቲቪስትቶች #ነን
የኛ ቢጤ ሰዎች
በፍፁም ነፃነት ~ በደህና እንዲሄዱ
ዛሬ በር ዘግተን
ቤት የተቀመጥን ~ ነገ እንዲራመዱ
———||———
ከሙሉቀን ሰ•
@getem
@getem
@peppac
በዚህ በኔ ትውልድ
በዚህ በኛ ዘመን
ከሰዎች ሞት ይልቅ ~ አሟሟት ቢታይም
ገዳዩ ነው እንጂ ~ ሞት አይለያይም
#እኔ #አክቲቪስት #ነኝ
ለሰዎች ምታገል ~ የህሊና ባለእዳ
ሰው በሰውነቱ ~ ደርሶ እንዳይጎዳ
ለሌሎች ልሞላ ~ ከራሴ ላይ ምዘርፍ
ርቀቴን ጠብቄ ~ ትውልዴን የማተርፍ
#እኔ #አክቲቪስት #ነኝ
በዛሬ ቀለሜ ~ የሰው ነገን ምስል
ሸፍኜ ማስነጥስ ~ አፌን ይዤ ምስል
ሠው ከመሆን ውጪ ~ ብዙ ማልጠበብ
ነብሶችን ለማዳን ~ እጆቼን ምታጠብ
#እኛ #አክቲቪስትቶች #ነን
የኛ ቢጤ ሰዎች
በፍፁም ነፃነት ~ በደህና እንዲሄዱ
ዛሬ በር ዘግተን
ቤት የተቀመጥን ~ ነገ እንዲራመዱ
———||———
ከሙሉቀን ሰ•
@getem
@getem
@peppac
#ድርሳነ ፍቅር!
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።
አንቺ የእኔ ጣዖት!
እኔ ያንቺ አማኝ
የምዕመኑ ጠሎት ቅዳሴና አዛኑ
በየት በኩል ይሰማኝ?
።።።
እሳት ያንቺ ትንፋሽ ~ መብረቅ ያንቺ መውደድ
በየት መንገድ ልጓዝ ~ እምን ላይ ልራመድ?
እቴ ያንቺ ገላ
እንደ ጥቅምት አዝዕርት ፥ በአይን የሚበላ
አወይ የዓይኖችሽ... ግርማቸው ጉልላት
አወይ የጥርሶችሽ ... የገፃቸው ንፃት
በመዳፍሽ ቅጠል .... በጣትሽ አለንጋ
ሠንበር የወረሰው ~ ቁስል ልቤን ይዤ
እንደምን አልሰጋ?
።።።።
#እኔ
መድሀኒቴ አንቺ
በሽታዬም አንቺ
አንቺን እየዋጥሁኝ ~ አንቺን የምታመም
ባንቺ እየታመምሁኝ ~ ባንቺ የምታከም
.
ባለ አንድ ድዌያም ~ ባለ አንድ ክኒና
ወይ አልሞት ፥ ወይ አልድን
ወይ አልኖር በደህና!
@getem
@getem
@paappii
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።
አንቺ የእኔ ጣዖት!
እኔ ያንቺ አማኝ
የምዕመኑ ጠሎት ቅዳሴና አዛኑ
በየት በኩል ይሰማኝ?
።።።
እሳት ያንቺ ትንፋሽ ~ መብረቅ ያንቺ መውደድ
በየት መንገድ ልጓዝ ~ እምን ላይ ልራመድ?
እቴ ያንቺ ገላ
እንደ ጥቅምት አዝዕርት ፥ በአይን የሚበላ
አወይ የዓይኖችሽ... ግርማቸው ጉልላት
አወይ የጥርሶችሽ ... የገፃቸው ንፃት
በመዳፍሽ ቅጠል .... በጣትሽ አለንጋ
ሠንበር የወረሰው ~ ቁስል ልቤን ይዤ
እንደምን አልሰጋ?
።።።።
#እኔ
መድሀኒቴ አንቺ
በሽታዬም አንቺ
አንቺን እየዋጥሁኝ ~ አንቺን የምታመም
ባንቺ እየታመምሁኝ ~ ባንቺ የምታከም
.
ባለ አንድ ድዌያም ~ ባለ አንድ ክኒና
ወይ አልሞት ፥ ወይ አልድን
ወይ አልኖር በደህና!
@getem
@getem
@paappii
#ዝም #ዝም
ሆድ ከሀገር ይሰፋል~ በሚሉባት ሀገር
አፍ ከአለም መስፋቱን ~ለማን እንናገር ?
ለማን እንናገር ~ እኮ ለማ እንማው
አፍ ባጋለው ሐገር~ምጣድ ነው
ሚሰማው
#ሰማ #ሰማ #ብለን
በቶሎ ተጋግረን ~ በጊዜ እንዳንወጣ
በሰማ ምጣድ ላይ ~ የሚያሰፋ መጣ
የሚያሰፋው መጣ ~ሊጡን አንጠልጥሎ
ማልዶ ሊማግድህ ~ ነፃ ላውጣህ ብሎ
ተናገር ይልሀል ~ አስከብር መብትህን
እንዳሻህ ተጠቀም ~ ሰብአዊነትህን
#እኔ ግን #እላለሁ
በንግግር ብቃት ~ እልፎች ቢጀግኑም
አንድ ሺህ ምላሶች ~አንድ ጆሮ አይሆኑም
በምላስ ተስቦ ~ ከሰነባበተ
ጆሮን ይከልላል ~ አፍ ከተከፈተ
#እኔ #ጠይቃለሁ
የወል ጥያቄህ ላይ
ያለ ሀሳብ ተኝተው ~ ሠው ለሚያንተርሱ
መናገር አይደል ወይ ~ ዝም ማለት ራሱ
#እኔ #ሞግታለሁ
ሐሳብን በመግለፅ ~ በመናገር አለም
ዝም የማለት መብቱን~የሚያስከብር የለም
#እኔ #እጠቁማለሁ
በነፃነት ጥላ ~ ግብሩ የተከለለ
በመናገር መብት ውስጥ~ዝም የማለት አለ
===||===
ከሙሉቀን ሰ•
@getem
@getem
@getem
ሆድ ከሀገር ይሰፋል~ በሚሉባት ሀገር
አፍ ከአለም መስፋቱን ~ለማን እንናገር ?
ለማን እንናገር ~ እኮ ለማ እንማው
አፍ ባጋለው ሐገር~ምጣድ ነው
ሚሰማው
#ሰማ #ሰማ #ብለን
በቶሎ ተጋግረን ~ በጊዜ እንዳንወጣ
በሰማ ምጣድ ላይ ~ የሚያሰፋ መጣ
የሚያሰፋው መጣ ~ሊጡን አንጠልጥሎ
ማልዶ ሊማግድህ ~ ነፃ ላውጣህ ብሎ
ተናገር ይልሀል ~ አስከብር መብትህን
እንዳሻህ ተጠቀም ~ ሰብአዊነትህን
#እኔ ግን #እላለሁ
በንግግር ብቃት ~ እልፎች ቢጀግኑም
አንድ ሺህ ምላሶች ~አንድ ጆሮ አይሆኑም
በምላስ ተስቦ ~ ከሰነባበተ
ጆሮን ይከልላል ~ አፍ ከተከፈተ
#እኔ #ጠይቃለሁ
የወል ጥያቄህ ላይ
ያለ ሀሳብ ተኝተው ~ ሠው ለሚያንተርሱ
መናገር አይደል ወይ ~ ዝም ማለት ራሱ
#እኔ #ሞግታለሁ
ሐሳብን በመግለፅ ~ በመናገር አለም
ዝም የማለት መብቱን~የሚያስከብር የለም
#እኔ #እጠቁማለሁ
በነፃነት ጥላ ~ ግብሩ የተከለለ
በመናገር መብት ውስጥ~ዝም የማለት አለ
===||===
ከሙሉቀን ሰ•
@getem
@getem
@getem
❤1
ግጥም ብቻ 📘
Audio
<< የምትወዱትን እስካልሰጣቹ ድረስ አላመናቹም>> (ነብዩ መሀመድ )
እኔ ደሞ ለምን ትንሽ ለወጥ ባደርገውስ የምትወዱት የወደዳችሁትን ነገር መስጠት እንኳን ባትችሉ ያ የወደዳችሁትን ነገር ሰዎች እንዲፈልጉት እንዲገዙት እንዲያነቡት እስካላደረጋችሁ ድረስ እናንተ ስስታም ናቹ። መስጠት ማለት ቁስን ብቻ ማካፈል መለገስ አይመስለኝ ...ፈገግታም መስጠት ነውና። መልካም ንግግርም መስጠት ነው።
#እኔ ዛሬ የወደድኩትን ውስጤን እያሞቀኝ ያለውን አንድ መፅሐፍ አለ። "ትዝታዬ ለኔ ትዝታዬ ለአንቺ ይሰኛል"
ለመጻፍ መቸክቸክ ብቻ በቂ አይደለም ። መጻፍ ለመጻፍ ሱስ ማውጫም ከሆነ ችግር ነው ። አንዳንዶች ደግሞ አሉ ። ሰከን ርግት ብለው ላገር ለወገን የሚበጅ ረብ ያለው ሃሳብ የሚጽፉ ። ሸጋውን መርጠው ለነፍስ የሚደርሱትን እንካቹ የሚሉን። እነርሱን ባነበብን ጊዜ እንጽናናለን ።ውስጣችን ሲረጥብ ይሰማናል። ከጥቂቶቹ መሃከል አንዱን እነሆ ላስተዋቅቃችሁ ።
#እሱባለው አበራ ንጉሤ ይባላል ። ሸግየ ጸሃፊ ነው ። ጸሃፊ ነው ስላችሁ ጸሃፊ ነው!!!! መፅሐፉ በቅርቡ ማለትም በሀምሌ ወር መጨረሻዎች ላይ ነው የወጣው...ብዙ ሰዎች ገዝተውት ወደውታል እናንተም ገዝታቹ ብታነቡት በእርግጠኝነት መናገር የምችለው ትወዱታላችሁ።
ዋጋው 120 ብር ነው ጃዕፈር ጋር ጎራ የምትሉ ከሆነ ግን 70 ብር ታገኙታላቹ...🙏
!!!!! መጣፍማ ሃቂቃው ነው! !!!
እንኪቶ ማሂቶ! !!! ይኸው ነው!!!!!!!!!!!!!
ተመኜሁላችሁ!!!!!
ሽብርቅርቅ፣
ድምቅምቅ፣
ፍልቅልቅ ያለ፣ በሳቅና በደስታ የተሞሸረ፣ ንባብ
ጀባ!!!!!!!
@getem
@getem
@Nagayta
እኔ ደሞ ለምን ትንሽ ለወጥ ባደርገውስ የምትወዱት የወደዳችሁትን ነገር መስጠት እንኳን ባትችሉ ያ የወደዳችሁትን ነገር ሰዎች እንዲፈልጉት እንዲገዙት እንዲያነቡት እስካላደረጋችሁ ድረስ እናንተ ስስታም ናቹ። መስጠት ማለት ቁስን ብቻ ማካፈል መለገስ አይመስለኝ ...ፈገግታም መስጠት ነውና። መልካም ንግግርም መስጠት ነው።
#እኔ ዛሬ የወደድኩትን ውስጤን እያሞቀኝ ያለውን አንድ መፅሐፍ አለ። "ትዝታዬ ለኔ ትዝታዬ ለአንቺ ይሰኛል"
ለመጻፍ መቸክቸክ ብቻ በቂ አይደለም ። መጻፍ ለመጻፍ ሱስ ማውጫም ከሆነ ችግር ነው ። አንዳንዶች ደግሞ አሉ ። ሰከን ርግት ብለው ላገር ለወገን የሚበጅ ረብ ያለው ሃሳብ የሚጽፉ ። ሸጋውን መርጠው ለነፍስ የሚደርሱትን እንካቹ የሚሉን። እነርሱን ባነበብን ጊዜ እንጽናናለን ።ውስጣችን ሲረጥብ ይሰማናል። ከጥቂቶቹ መሃከል አንዱን እነሆ ላስተዋቅቃችሁ ።
#እሱባለው አበራ ንጉሤ ይባላል ። ሸግየ ጸሃፊ ነው ። ጸሃፊ ነው ስላችሁ ጸሃፊ ነው!!!! መፅሐፉ በቅርቡ ማለትም በሀምሌ ወር መጨረሻዎች ላይ ነው የወጣው...ብዙ ሰዎች ገዝተውት ወደውታል እናንተም ገዝታቹ ብታነቡት በእርግጠኝነት መናገር የምችለው ትወዱታላችሁ።
ዋጋው 120 ብር ነው ጃዕፈር ጋር ጎራ የምትሉ ከሆነ ግን 70 ብር ታገኙታላቹ...🙏
!!!!! መጣፍማ ሃቂቃው ነው! !!!
እንኪቶ ማሂቶ! !!! ይኸው ነው!!!!!!!!!!!!!
ተመኜሁላችሁ!!!!!
ሽብርቅርቅ፣
ድምቅምቅ፣
ፍልቅልቅ ያለ፣ በሳቅና በደስታ የተሞሸረ፣ ንባብ
ጀባ!!!!!!!
@getem
@getem
@Nagayta
( መልካም አዲስ ዓመት )
#እኔ ና አዲስ ዓመት
:
:
አብረሺኝ እያለሽ በፍቅር በሰላም ባለፉት ዓመታት
ለኔ አዲስ ነበረ እያንዳንዱ ሰዓት።
:
:
እንዳዲስ መፋቀር እንዳዲስ መዋደድ
አዲስ ተስፋ ማርገዝ አዲስ ተስፋ መውለድ
:
:
ግና የኔ ፍቅር ...
ጥለሺኝ ስትሄጂ አዲስ አብሮሽ ሄዷል
ልክ አንቺ እንደተውሺኝ እሱም እኔን ክዷል።
:
:
አንቺ የለሽም ብለው ቀኖች አድማ መተው
ላንቺ ተደርበው ካንቺ ጋር አድብተው
በኔ ላይ ዘመቱ
አዲስ ዓመት ሚባል ላንተ አይኖርም ብለው ጭራሽ ተገዘቱ።
:
:
ምን ቀናቶች ብቻ ሁሉም ግራ ሰጠኝ
ሳር ቅጠሉ ሳይቀር ዞሮ ሰነበጠኝ።
:
:
አዲስ ዘመን ጠባ አውድ ዓመት መጣልን እያለ ሲያከብር ሀገሬው በሙሉ
አዲስ ሚባል ቀናት እኔ ጋር ግን የሉም ካንቺ ጋር አብረው ስለኮበለሉ።
:
:
ባ‘ገሬ ምድር ላይ ሜዳው ሸንተረሩ በ አደይ ተሞልቷል
አብረን ያበጀነው የኔና ያንቺ መስክ አንቺ የለሽም ብሎ አደይ ማብቀል ትቷል።
:
:
እንቁጣጣሽ ብለው ሚዘምሩ ልጆች ጎረቤት ተጫውተው
እንደሌለሽ ሲያውቁ አልፈውት ሄደዋል ቤታችንን ትተው።
:
:
የሰፈር እፃናት ወረቀት ላይ ስለው አበባ ሚያዞሩ
አንቺ የለሽም ብለው ለኔ ግን ሳይሰጡኝ አልፈዋል በበሩ።
:
:
የጎረቤት ጓሮ የጎረቤት ደጅ
ይላል ዶሮ ዶሮ ይላል ጠጅ ጠጅ
እኛ ደጅስ የታል እኛ ጓሮስ የታል
ያንቺ ጠረን እንጂ ሌላ መች ይሸታል።
:
:
መንደርተኛው ሁሉ አዲስ ዓመት ብሎ ጎመንን በገንፎ ተክቷል አውቃለው
እኔ አዲስ ርቆኝ የጎመን ድስት ይዤ ዛሬም በድጋሚ ጎመን ቀቅላለው።
:
:
እናልሽ ዓለሜ ያን ቀን ስንለያይ
እንደነበርኩኝ ነኝ ምንም አዲስ ሳላይ
ትመጪያለሽ ከሚል ጥቂት ተስፋ በቀር
በኔና በቤቴ የለም አዲስ ነገር።
:
:
ይሄ ነው እንግዲ ይሄ ነው እውነቴ
አንቺንና አዲስን አንድ ላይ ማጣቴ።
:
:
ስለዚም የኔ ሴት...
ካንቺ ጋር ያበሩት ቀኖቼ እስኪመጡ ወይ አንቺ እስክትመጪ
የለኝ አዲስ ነገር የለኝ አዲስ ዓመት ከመባተል ውጪ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@getem
@getem
@getem
#እኔ ና አዲስ ዓመት
:
:
አብረሺኝ እያለሽ በፍቅር በሰላም ባለፉት ዓመታት
ለኔ አዲስ ነበረ እያንዳንዱ ሰዓት።
:
:
እንዳዲስ መፋቀር እንዳዲስ መዋደድ
አዲስ ተስፋ ማርገዝ አዲስ ተስፋ መውለድ
:
:
ግና የኔ ፍቅር ...
ጥለሺኝ ስትሄጂ አዲስ አብሮሽ ሄዷል
ልክ አንቺ እንደተውሺኝ እሱም እኔን ክዷል።
:
:
አንቺ የለሽም ብለው ቀኖች አድማ መተው
ላንቺ ተደርበው ካንቺ ጋር አድብተው
በኔ ላይ ዘመቱ
አዲስ ዓመት ሚባል ላንተ አይኖርም ብለው ጭራሽ ተገዘቱ።
:
:
ምን ቀናቶች ብቻ ሁሉም ግራ ሰጠኝ
ሳር ቅጠሉ ሳይቀር ዞሮ ሰነበጠኝ።
:
:
አዲስ ዘመን ጠባ አውድ ዓመት መጣልን እያለ ሲያከብር ሀገሬው በሙሉ
አዲስ ሚባል ቀናት እኔ ጋር ግን የሉም ካንቺ ጋር አብረው ስለኮበለሉ።
:
:
ባ‘ገሬ ምድር ላይ ሜዳው ሸንተረሩ በ አደይ ተሞልቷል
አብረን ያበጀነው የኔና ያንቺ መስክ አንቺ የለሽም ብሎ አደይ ማብቀል ትቷል።
:
:
እንቁጣጣሽ ብለው ሚዘምሩ ልጆች ጎረቤት ተጫውተው
እንደሌለሽ ሲያውቁ አልፈውት ሄደዋል ቤታችንን ትተው።
:
:
የሰፈር እፃናት ወረቀት ላይ ስለው አበባ ሚያዞሩ
አንቺ የለሽም ብለው ለኔ ግን ሳይሰጡኝ አልፈዋል በበሩ።
:
:
የጎረቤት ጓሮ የጎረቤት ደጅ
ይላል ዶሮ ዶሮ ይላል ጠጅ ጠጅ
እኛ ደጅስ የታል እኛ ጓሮስ የታል
ያንቺ ጠረን እንጂ ሌላ መች ይሸታል።
:
:
መንደርተኛው ሁሉ አዲስ ዓመት ብሎ ጎመንን በገንፎ ተክቷል አውቃለው
እኔ አዲስ ርቆኝ የጎመን ድስት ይዤ ዛሬም በድጋሚ ጎመን ቀቅላለው።
:
:
እናልሽ ዓለሜ ያን ቀን ስንለያይ
እንደነበርኩኝ ነኝ ምንም አዲስ ሳላይ
ትመጪያለሽ ከሚል ጥቂት ተስፋ በቀር
በኔና በቤቴ የለም አዲስ ነገር።
:
:
ይሄ ነው እንግዲ ይሄ ነው እውነቴ
አንቺንና አዲስን አንድ ላይ ማጣቴ።
:
:
ስለዚም የኔ ሴት...
ካንቺ ጋር ያበሩት ቀኖቼ እስኪመጡ ወይ አንቺ እስክትመጪ
የለኝ አዲስ ነገር የለኝ አዲስ ዓመት ከመባተል ውጪ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@getem
@getem
@getem
#እኔ_እራሴን_የሆንኩኝ_ለት
፡
፡
፡
እኔ እራሴን አይደለሁም፣
እያለውኝ ግን የለሁም።
አጉል ጉራን ስቸረችር ማልበገር ሲመስላቸው፣
በሆዴ ውስጥ ብዬ አውቃለው ባረገልኝ እንደ አፋቸው።
ክንብንቤን ገፈው ጥለው ማንነቴን ቢያስተውሉ፣
የኔስ ሕይወት ድብብቆሽ ከራሴው ጋር አኩኩሉ።
፡
፡
አንደበቴም አንድ ብሎ ዋሾነትን ከለመደ፣
ፍቅር ልቤን ስልብ አድርጎት እሩቅ ትቶኝ ከነጎደ፣
እምጥ ሰዶ ተንሰራፍቶ ናፍቆት ሥሩን ከዘረጋ፣
ውሸት ጉራን እየነዛው ስንቴ መሽቶ ስንቴ ነጋ።
፡
፡
ለሰው እንጂ ማስመሰሌ ዳሩ ለኔ ምን ፋይዳ አለው፣
ባደባባይ የሚቃጣኝ ጀግና ኩሩ ልብ እንዳለው።
ድንቄም ኩሩ ድንቄም ጀግና፣
ለነገሩ ማን አውቆብኝ እኔ እራሴን መች ሆንኩና።
፡
፡
እውነቱማ
ቁርሾ ዘልቆ መሀላችን ስንራራቅ ስንለያይ፣
ካንጀት ፈልቆ የሚፈሰው ሳቄም ሆኑዋል ካንገት በላይ።
እህል ውሀው አራቀኝም ሆዴም ጠግቧል ልቤ እርቦት፣
በሞላ ሰው አንቺን ይላል ጀሌ ጅጊ አጀብ ከቦት።
ትከሻዬ ምን ቢሰፋ መንፈሴ ግን ተሰበረ፣
ትዝታሽም ከጫንቃዬ እንደ ቋጥኝ ተከመረ።
ለነገሩ ምን ፋይዳ አለው፣
መች ለማለው መች ሰማለው፣
እኔ እራሴን እኮ አይደለው።
፣
፣
ወደ ራሴው ተመልሼ፣
ማስመሰሌን ከቀበርኩት ላያዳግም መሬት ምሼ፣
እውነት እውነት ፣
እኔ ራሴን የሆንኩኝ ለት፣
እሺታሽም ታክሎበት፣
ድሪቶውን ወዲያ ጥዬ ሀቁን ላንቺው ብናገረው፣
የፍቅራችን ዳግም ውልደት ያኔ ነበር ሚከበረው።
፡
፡
ለነገሩ ምን ሊጠቅም፣
አልናገር አልጋገር እኔ እራሴን ሆኜ አላውቅም።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@henockb
@getem
@getem
@getem
፡
፡
፡
እኔ እራሴን አይደለሁም፣
እያለውኝ ግን የለሁም።
አጉል ጉራን ስቸረችር ማልበገር ሲመስላቸው፣
በሆዴ ውስጥ ብዬ አውቃለው ባረገልኝ እንደ አፋቸው።
ክንብንቤን ገፈው ጥለው ማንነቴን ቢያስተውሉ፣
የኔስ ሕይወት ድብብቆሽ ከራሴው ጋር አኩኩሉ።
፡
፡
አንደበቴም አንድ ብሎ ዋሾነትን ከለመደ፣
ፍቅር ልቤን ስልብ አድርጎት እሩቅ ትቶኝ ከነጎደ፣
እምጥ ሰዶ ተንሰራፍቶ ናፍቆት ሥሩን ከዘረጋ፣
ውሸት ጉራን እየነዛው ስንቴ መሽቶ ስንቴ ነጋ።
፡
፡
ለሰው እንጂ ማስመሰሌ ዳሩ ለኔ ምን ፋይዳ አለው፣
ባደባባይ የሚቃጣኝ ጀግና ኩሩ ልብ እንዳለው።
ድንቄም ኩሩ ድንቄም ጀግና፣
ለነገሩ ማን አውቆብኝ እኔ እራሴን መች ሆንኩና።
፡
፡
እውነቱማ
ቁርሾ ዘልቆ መሀላችን ስንራራቅ ስንለያይ፣
ካንጀት ፈልቆ የሚፈሰው ሳቄም ሆኑዋል ካንገት በላይ።
እህል ውሀው አራቀኝም ሆዴም ጠግቧል ልቤ እርቦት፣
በሞላ ሰው አንቺን ይላል ጀሌ ጅጊ አጀብ ከቦት።
ትከሻዬ ምን ቢሰፋ መንፈሴ ግን ተሰበረ፣
ትዝታሽም ከጫንቃዬ እንደ ቋጥኝ ተከመረ።
ለነገሩ ምን ፋይዳ አለው፣
መች ለማለው መች ሰማለው፣
እኔ እራሴን እኮ አይደለው።
፣
፣
ወደ ራሴው ተመልሼ፣
ማስመሰሌን ከቀበርኩት ላያዳግም መሬት ምሼ፣
እውነት እውነት ፣
እኔ ራሴን የሆንኩኝ ለት፣
እሺታሽም ታክሎበት፣
ድሪቶውን ወዲያ ጥዬ ሀቁን ላንቺው ብናገረው፣
የፍቅራችን ዳግም ውልደት ያኔ ነበር ሚከበረው።
፡
፡
ለነገሩ ምን ሊጠቅም፣
አልናገር አልጋገር እኔ እራሴን ሆኜ አላውቅም።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@henockb
@getem
@getem
@getem
👍5
#አንድ_አዝማሪ_ነበር.......
.
.
ማሲንቆውን 'ሚገርፍ ስንኝ እያጀበ
የከበበው ጠጪ ብሶት ገረበበ
ሚስቱ የፈታችው ተቀበል በሚል ቃል
ብሶቱን ሲያበርደው ቤቱ ግን ይሞቃል
ተቀበልልል
.
.
ሚስቴ የሰው ገፊ መሄድ ነው ሚደላት
እንደ ቀልድ ፈታችኝ አርግዢልኝ ብላት
ከጎኑ ሚገችም አንድ ቀለም ቀቢ
ደግሞ ያሽሟጥጣል ምን ጉድ ነው በረቢ
እሱም እንዲህ አለ
ክብር ጠለቀብን አዳም ደበዘዘ
ሄዋን በምትሰራው ወንዱ እያረገዘ
(ህመም አይደል ፅንሱ )
.
.
ስካር የጀመረው ሳይገባው ይስቃል
ከሆደ ከደረሰ ብቅል ያሳቅቃል
ከቀቢው ፊት ለፊት ስራ የፈታ ወጣት
ተበድሮ ይጠጣል ቀፋፊ ነው ማጣት
እሱም አቀበለ...
.
.
ሆዴን ይብሰኛል ብሶቴን ስደግመው
እኔን መሳይ የታል
ተመረኩኝ ቢልም ትምህርት የረገመው
.
.
ትካዜን ሲያጣጥም ከእንባው ተናንቆ
ችግር ያስተጋባል ቢቸገር ማሲንቆ
ያንሳል አትልቆ!
.
እኔ እንዳለሁ አለ
አንዴ ሰካራሙን ሲልም አዝማሪውን
ስገረም ስታዘብ መከራ ሲተውን
ወጣት ሽማግሌው ቃል እየተራጨ
ስንቱ ነው ያለፈው
ባ'ለም መቅጫ እድሜው ባ'ለም 'የተቀጨ
#እኔ_እንዳለሁ_አለሁ....
✍ናታን ኤርሚያስ
@UniqueDy
@getem
@getem
@getem
.
.
ማሲንቆውን 'ሚገርፍ ስንኝ እያጀበ
የከበበው ጠጪ ብሶት ገረበበ
ሚስቱ የፈታችው ተቀበል በሚል ቃል
ብሶቱን ሲያበርደው ቤቱ ግን ይሞቃል
ተቀበልልል
.
.
ሚስቴ የሰው ገፊ መሄድ ነው ሚደላት
እንደ ቀልድ ፈታችኝ አርግዢልኝ ብላት
ከጎኑ ሚገችም አንድ ቀለም ቀቢ
ደግሞ ያሽሟጥጣል ምን ጉድ ነው በረቢ
እሱም እንዲህ አለ
ክብር ጠለቀብን አዳም ደበዘዘ
ሄዋን በምትሰራው ወንዱ እያረገዘ
(ህመም አይደል ፅንሱ )
.
.
ስካር የጀመረው ሳይገባው ይስቃል
ከሆደ ከደረሰ ብቅል ያሳቅቃል
ከቀቢው ፊት ለፊት ስራ የፈታ ወጣት
ተበድሮ ይጠጣል ቀፋፊ ነው ማጣት
እሱም አቀበለ...
.
.
ሆዴን ይብሰኛል ብሶቴን ስደግመው
እኔን መሳይ የታል
ተመረኩኝ ቢልም ትምህርት የረገመው
.
.
ትካዜን ሲያጣጥም ከእንባው ተናንቆ
ችግር ያስተጋባል ቢቸገር ማሲንቆ
ያንሳል አትልቆ!
.
እኔ እንዳለሁ አለ
አንዴ ሰካራሙን ሲልም አዝማሪውን
ስገረም ስታዘብ መከራ ሲተውን
ወጣት ሽማግሌው ቃል እየተራጨ
ስንቱ ነው ያለፈው
ባ'ለም መቅጫ እድሜው ባ'ለም 'የተቀጨ
#እኔ_እንዳለሁ_አለሁ....
✍ናታን ኤርሚያስ
@UniqueDy
@getem
@getem
@getem
👍6
#እኔ_እንጃ
፡
፡
፡
«ፍቅር አይቀናም» ይላል፣
ከፈጣሪ የተሰጠን የማይሻረው ቅዱሱ ቃል፣
አንድ ልቤም ይህን ያውቃል።
እኔ ግን ...
ቆሽቴ ድብን እስኪል ድረስ ጨጓራዬም እስኪከስል፣
ፊቴም አመድ እስኪመስል፣
ሰርክ ባንቺ እቀናለሁ በማይረባ ተራ ነገር፣
ቢሆንም ግን አልታከትኩም አፈቀርኩሽ ብዬ ላንቺ ሁሌ እንዳዲስ ከመናገር።
፡
፡
«ፍቅር አይታበይም» ይላል፣
ፅኑ ወንጌል ቅዱሱ ቃል፣
እርግጥ ልቤም ይህን ያውቃል።
እኔ ግን ...
ባደባባይ አብረን ስንዞር እቅፌ ውስጥ አስገብቼሽ ቸርችሬያለሁ እልፍ ጉራ፣
አንቺን የኔ በማድረጌም ደረት እና ትከሻዬን ሰብቄአለሁ በየተራ፣
ሰው እንዲያየን ተመኝቼም ተጓደድኩኝ ተጎብሬ፣
አፈቅርሻለሁ ግን እላለሁ ተመልሼ ደግሞ ዞሬ።
፡
፡
«ፍቅር ቸርነት ያደርጋል»፣
ይላል የፈጣሪ ቅዱስ ቃል፣
ይህም እውነት ልቤ ዘልቋል።
እኔ ግን አንቺን ብቻ ስል ግራ ቀኜን ፊት ነስቼ፣
ሁሉን ላንቺ ለመስጠት ስል ወዳጅ ዘመድ ወዲያ ትቼ፣
ቸር ማድረግን እረስቼው ተቆራኝቶኝ ንፉግነት፣
ላፍታም ቢሆን አልቦዘንኩም አፈቅርሻለሁ ግን ከማለት።
፡
፡
«ፍቅር በ እውነት ደስ ይለዋል»፣
ቅዱሱ ቃል እንዲያ ይላል፣
ልቤም ይህን ያስተውላል።
እኔ ግን ላንቺ ደስታ ስል ያልሆንኩትን ሆኜ አውቃለሁ፣
እየከፋኝ እስቃለሁ፣
እንዳላጣሽ እየሰጋው እየዋሸው ስንቴ አለፈ፣
አፈቅርሻለሁ ግን ከማለት ልቤ ዛሬም አላረፈ።
፡
፡
«ፍቅር አመፅን ይጠላል» ይላል፣
የተሰጠን የ ሕይወት ቃል፣
በልቤም ውስጥ ተሰንቋል።
እኔ ግን ...
በክፉ ያዩሽ ሲመስለኝ ምኑንም ገና ሳልይዘው ጥላቻ ውስጤ እየሞላ፣
አስሼ ፀብ በደላላ፣
ባንቺም ላይ ዓይኔ እየቀላ፣
ተጋጨው ካላፊ አግዳሚ፣
ቢሆንም ነግቶ አይመሽም አፈቅርሻለሁ የሚል ቃል ከኔው አንደበት ሳትሰሚ።
፡
፡
ሲጋጭብኝ ብታዘበው ላንቺ ያለኝ ጥልቅ ስሜት፣
ከማይሻረው ቃለ ህይወት፣
ይጨንቀኛል ይጠበኛል ይጠፋኛል ምገባበት።
ማቅ ለብሼም ተክዛለሁ ላንቺ እስካሁን ባይታይሽም፣
ፍቅር ከቃል በላይ ነው እንዴ? ወይንስ አላፈቅርሽም?
እኔ እንጃ!
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@getem
@getem
@getem
፡
፡
፡
«ፍቅር አይቀናም» ይላል፣
ከፈጣሪ የተሰጠን የማይሻረው ቅዱሱ ቃል፣
አንድ ልቤም ይህን ያውቃል።
እኔ ግን ...
ቆሽቴ ድብን እስኪል ድረስ ጨጓራዬም እስኪከስል፣
ፊቴም አመድ እስኪመስል፣
ሰርክ ባንቺ እቀናለሁ በማይረባ ተራ ነገር፣
ቢሆንም ግን አልታከትኩም አፈቀርኩሽ ብዬ ላንቺ ሁሌ እንዳዲስ ከመናገር።
፡
፡
«ፍቅር አይታበይም» ይላል፣
ፅኑ ወንጌል ቅዱሱ ቃል፣
እርግጥ ልቤም ይህን ያውቃል።
እኔ ግን ...
ባደባባይ አብረን ስንዞር እቅፌ ውስጥ አስገብቼሽ ቸርችሬያለሁ እልፍ ጉራ፣
አንቺን የኔ በማድረጌም ደረት እና ትከሻዬን ሰብቄአለሁ በየተራ፣
ሰው እንዲያየን ተመኝቼም ተጓደድኩኝ ተጎብሬ፣
አፈቅርሻለሁ ግን እላለሁ ተመልሼ ደግሞ ዞሬ።
፡
፡
«ፍቅር ቸርነት ያደርጋል»፣
ይላል የፈጣሪ ቅዱስ ቃል፣
ይህም እውነት ልቤ ዘልቋል።
እኔ ግን አንቺን ብቻ ስል ግራ ቀኜን ፊት ነስቼ፣
ሁሉን ላንቺ ለመስጠት ስል ወዳጅ ዘመድ ወዲያ ትቼ፣
ቸር ማድረግን እረስቼው ተቆራኝቶኝ ንፉግነት፣
ላፍታም ቢሆን አልቦዘንኩም አፈቅርሻለሁ ግን ከማለት።
፡
፡
«ፍቅር በ እውነት ደስ ይለዋል»፣
ቅዱሱ ቃል እንዲያ ይላል፣
ልቤም ይህን ያስተውላል።
እኔ ግን ላንቺ ደስታ ስል ያልሆንኩትን ሆኜ አውቃለሁ፣
እየከፋኝ እስቃለሁ፣
እንዳላጣሽ እየሰጋው እየዋሸው ስንቴ አለፈ፣
አፈቅርሻለሁ ግን ከማለት ልቤ ዛሬም አላረፈ።
፡
፡
«ፍቅር አመፅን ይጠላል» ይላል፣
የተሰጠን የ ሕይወት ቃል፣
በልቤም ውስጥ ተሰንቋል።
እኔ ግን ...
በክፉ ያዩሽ ሲመስለኝ ምኑንም ገና ሳልይዘው ጥላቻ ውስጤ እየሞላ፣
አስሼ ፀብ በደላላ፣
ባንቺም ላይ ዓይኔ እየቀላ፣
ተጋጨው ካላፊ አግዳሚ፣
ቢሆንም ነግቶ አይመሽም አፈቅርሻለሁ የሚል ቃል ከኔው አንደበት ሳትሰሚ።
፡
፡
ሲጋጭብኝ ብታዘበው ላንቺ ያለኝ ጥልቅ ስሜት፣
ከማይሻረው ቃለ ህይወት፣
ይጨንቀኛል ይጠበኛል ይጠፋኛል ምገባበት።
ማቅ ለብሼም ተክዛለሁ ላንቺ እስካሁን ባይታይሽም፣
ፍቅር ከቃል በላይ ነው እንዴ? ወይንስ አላፈቅርሽም?
እኔ እንጃ!
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@getem
@getem
@getem
👍48❤40😱8🔥6
#እኔ ለወሎ ልጅ !
(ሚካኤል .አ)
ወለባ ወለባ ...
ደርቢና ግርማ በቁንጅናሽ ካባ
አረፍ በይ እስቲ ቁጭ በይ ሙሀባዬ
ይሙላልኝ ሀድራዬ...
ይጢስበት ቤቴን የትንሽ ገል እጣን
እንደዚህ ሲሆን ነው
ነፍሴን ደስ የሚላት እንደ ትንሽ ህፃን!
እቴ ደምዬዋ የበረሀ እንቧይ...
ያየሽ ሁሉ ፈዞ ይላል አሉ ዋይ ዋይ !
ዋይ ዋይ ስለ ጠጉርሽ
ዋይ ዋይ ስለ ጥርስሽ
እንደ ዝናር ጥይት ስለደቀደቅሽው
መቶ ወንድ በግራ መቶ ወንድ በስተቀኝ
ጥለሽ ተራመድሽው !
እንትፍ እንትፍ ይላል የመንደሩ ባልቴት
ከወዴት ታስቦ
እንዴት ተወጠነ ይሄ የውብ ስሌት?
በሚል ጉድ አግራሞት
ሁሉ ማየት ከብዶት
አጀብ አጀብ ይላል አሉ በመደመም
ይሄን ውበት ይዘሽ አረፍ በይ ከመደብ ።
አቦሉን ቅጂልኝ
የማሪቱን ዘፈን አብረሽ ተቀኚልኝ
የፍቅር ወስከንባ ጀምሬ ልሰፋ
ስንደዶው ተገኝቶ ደግሞ አክርማው ጠፋ
ሀውሳ ዝናብ አይጥል ያበቅላል በመስኖ
አካላቱ ታየኝ ጃምዮሽን መስሎ ...
ብላ እንዳለችው
ይሄን ስድር ዜማ በድምፅሽ ተወጭው
ወፎች ይከተሉሽ ... ይሙላልኝ ሀድራዬ
አዚሙን ሸኝቶ ... ይድመቅልኝ ቀዬ
እኔም ለዚህ ውበት ተጉዤ ባርምሞ
ስንኜን ልቋጥር ብዬሽ የደም ገንቦ።
እንደ ሼሁ ጅብሪል እንደ አያ ሙሌ
ዕፀ ሰመመኑን አቅምሼ ላካሌ
ሩቅ ላልም ልጓዝ በቅኔ ከንፌ
ሰነፍ ሆኜ አልዘምም በክርንሽ ታቅፌ።
ደግሞ ያንቺ እጣን
የነጭ ጭስ ጢያራ ...ቤቴን ሲሞላልኝ
የስንኝ ዛር መጥቶ ከኔ ባይሰፍርብኝ
ብሆን ቧልተኛ ብሽቅ
ተጫውቶ 'ማያስቅ
ቢናገር የማይጥም
አውሊያሽ ክፉ ነው ይነሳኛል ግጥም!
@getem
@getem
@paappii
(ሚካኤል .አ)
ወለባ ወለባ ...
ደርቢና ግርማ በቁንጅናሽ ካባ
አረፍ በይ እስቲ ቁጭ በይ ሙሀባዬ
ይሙላልኝ ሀድራዬ...
ይጢስበት ቤቴን የትንሽ ገል እጣን
እንደዚህ ሲሆን ነው
ነፍሴን ደስ የሚላት እንደ ትንሽ ህፃን!
እቴ ደምዬዋ የበረሀ እንቧይ...
ያየሽ ሁሉ ፈዞ ይላል አሉ ዋይ ዋይ !
ዋይ ዋይ ስለ ጠጉርሽ
ዋይ ዋይ ስለ ጥርስሽ
እንደ ዝናር ጥይት ስለደቀደቅሽው
መቶ ወንድ በግራ መቶ ወንድ በስተቀኝ
ጥለሽ ተራመድሽው !
እንትፍ እንትፍ ይላል የመንደሩ ባልቴት
ከወዴት ታስቦ
እንዴት ተወጠነ ይሄ የውብ ስሌት?
በሚል ጉድ አግራሞት
ሁሉ ማየት ከብዶት
አጀብ አጀብ ይላል አሉ በመደመም
ይሄን ውበት ይዘሽ አረፍ በይ ከመደብ ።
አቦሉን ቅጂልኝ
የማሪቱን ዘፈን አብረሽ ተቀኚልኝ
የፍቅር ወስከንባ ጀምሬ ልሰፋ
ስንደዶው ተገኝቶ ደግሞ አክርማው ጠፋ
ሀውሳ ዝናብ አይጥል ያበቅላል በመስኖ
አካላቱ ታየኝ ጃምዮሽን መስሎ ...
ብላ እንዳለችው
ይሄን ስድር ዜማ በድምፅሽ ተወጭው
ወፎች ይከተሉሽ ... ይሙላልኝ ሀድራዬ
አዚሙን ሸኝቶ ... ይድመቅልኝ ቀዬ
እኔም ለዚህ ውበት ተጉዤ ባርምሞ
ስንኜን ልቋጥር ብዬሽ የደም ገንቦ።
እንደ ሼሁ ጅብሪል እንደ አያ ሙሌ
ዕፀ ሰመመኑን አቅምሼ ላካሌ
ሩቅ ላልም ልጓዝ በቅኔ ከንፌ
ሰነፍ ሆኜ አልዘምም በክርንሽ ታቅፌ።
ደግሞ ያንቺ እጣን
የነጭ ጭስ ጢያራ ...ቤቴን ሲሞላልኝ
የስንኝ ዛር መጥቶ ከኔ ባይሰፍርብኝ
ብሆን ቧልተኛ ብሽቅ
ተጫውቶ 'ማያስቅ
ቢናገር የማይጥም
አውሊያሽ ክፉ ነው ይነሳኛል ግጥም!
@getem
@getem
@paappii
👍27😁16❤6🔥3
#እኔ የማስባት...
እንደ ሰማይ ንፁህ እንደ ወተት 'ርጉ
የሰው የሚገዳት ስስ አድርጌ ስጉ
የዋህ እንደ እርግብ ልባም እንደ እባብ
የፍቅር አበባ.. . እንደ ማር ባለ ጣ'ም ።
.
እኔ የማስባት...
በስጋ የወረደ የሰማይ ቤተኛ
የስክነት ማህደር ሀቂቅ እውነተኛ
እንደ ፀዓዳ ፍኩ.. .
የመንፈሴ በላጭ የስጋዬ ልኩ !
.
ሰው የሚያስባት...
በረሀ አርጎ ባዶ ችኩል እንደ ዥረት
የሰው የማይገዳት ከንዋይ ከንብረት
ክፉ እንደ እባብ... እስስት ተለዋዋጭ
ተዋጊ እንደ አጋም ... ጣዕም አልባ ልጣጭ።
.
ሰው የሚያስባት ...
በስጋ የመጣ የጋኔን ተወካይ
የክፋት ማህደር ሀቅ ሻሪ አባይ
እንደ እድፍ ቆሻሻ...
የስጋዬ እርግማን የመንፈሴ ልምሻ
ድኩም አርጎ ንቋት
ባዳ ጆሮ ይዤ ከኔ እንዴት ላስታርቃት ?
(ሚካኤል.አ)
@getem
@getem
@getem
እንደ ሰማይ ንፁህ እንደ ወተት 'ርጉ
የሰው የሚገዳት ስስ አድርጌ ስጉ
የዋህ እንደ እርግብ ልባም እንደ እባብ
የፍቅር አበባ.. . እንደ ማር ባለ ጣ'ም ።
.
እኔ የማስባት...
በስጋ የወረደ የሰማይ ቤተኛ
የስክነት ማህደር ሀቂቅ እውነተኛ
እንደ ፀዓዳ ፍኩ.. .
የመንፈሴ በላጭ የስጋዬ ልኩ !
.
ሰው የሚያስባት...
በረሀ አርጎ ባዶ ችኩል እንደ ዥረት
የሰው የማይገዳት ከንዋይ ከንብረት
ክፉ እንደ እባብ... እስስት ተለዋዋጭ
ተዋጊ እንደ አጋም ... ጣዕም አልባ ልጣጭ።
.
ሰው የሚያስባት ...
በስጋ የመጣ የጋኔን ተወካይ
የክፋት ማህደር ሀቅ ሻሪ አባይ
እንደ እድፍ ቆሻሻ...
የስጋዬ እርግማን የመንፈሴ ልምሻ
ድኩም አርጎ ንቋት
ባዳ ጆሮ ይዤ ከኔ እንዴት ላስታርቃት ?
(ሚካኤል.አ)
@getem
@getem
@getem
👍47❤7👎2😱1
#እኔ_እና_መስከረም🌼
አዎ አስታውሳለሁ
አመቱን በሙሉ ሳፈቅርሽ ስለኖርኩ
ጳጉሜንም ጨምሮ ሩፋኤል ተጠመቅኩ።
ሰው እንዴት ይሆናል አፍቅሮ ሀጢያተኛ
ክፉ ሳልናገር አብሬሽ ሳልተኛ።
ከመስከረም እስከ ጳጉሜ
ባንቺው ናፍቆት ላንቺው ቆሜ።
የማፍቀሬን ምላሽ በዋዜማው እለት መልስሽን ለመስማት
ፀሎት በያዝኩበት በዛ ረጅም ሌሊት
እሺ ትለኛለች...? ለአዲስ አመትማ አብረን እንዘልቃለን በሚል ደቂቅ ተስፋ
አምሮብኝ እንድታይ ኩታዬን ሳሰፋ
ምታዪኝ ይመስል ፀጉሬን አበጥሬ
ተስፋዬን አንግቤ ባንቺ ፍቅር ንሬ
አቤት የኔ ጉጉት አቤት የኔ እምነት
ከራሴ ስጣላ ከራሴ ስሟገት
ልንገራት? ይቅርብኝ?........
ፈራ ተባ እያልኩኝ ምታዪኝ ይመስል እንዲያ ስሽኮረመም
ፎቶሽን እያየው በሳቅሽ ስታከም
ምን ያልሆንኩት አለ ለሰው ማይወራ
በከርቤ የማይተው በወይራ ማይጠራ።
በላብ ከወጣልህ ባህርዛፍ ታጠነው የሚል የሰው ምክር
አመት በዓል ሲመጣ እንዲ ያረገኝ ነበር።
ትዝ ይለኛል ቀኑ ጳጉሜ ላይ ነበረ
በአንድ የፅሁፍ መልዕክት ልቤ ተሰበረ።
እንባ ተናነቀኝ የማደርገው ጠፋኝ
ከወትሮ የተለየ የእዉነት በጣም ከፋኝ
ህይወት ጣዕም አጣ ፈፅሞ ከረፋኝ።
እንቅልፍን ጠላሁት ውሎዬ እና አዳሬ ፀሎት ብቻ ሆነ
ይሄው እስከዛሬ ባንቺ የቃል ክህደት ልቤ እየባከነ።
በአል በመድረሱ ምኞቱን ለመግለፅ ሰላምታ ቢሰጥም
ቁጣ ቁጣ ይለኛል በባህሩ ጀልባ ወዳንቺ ሲያሰጥም
እናም እናቴዋ
እኔና መስከረም ትዝታ የለንም ለሰው የሚነገር
መስከረምም ይጥባ እኔም ልቤን ልዳር።
✍✍OB'☀️ (Jadon)
@jadmasse25
@getem
@getem
አዎ አስታውሳለሁ
አመቱን በሙሉ ሳፈቅርሽ ስለኖርኩ
ጳጉሜንም ጨምሮ ሩፋኤል ተጠመቅኩ።
ሰው እንዴት ይሆናል አፍቅሮ ሀጢያተኛ
ክፉ ሳልናገር አብሬሽ ሳልተኛ።
ከመስከረም እስከ ጳጉሜ
ባንቺው ናፍቆት ላንቺው ቆሜ።
የማፍቀሬን ምላሽ በዋዜማው እለት መልስሽን ለመስማት
ፀሎት በያዝኩበት በዛ ረጅም ሌሊት
እሺ ትለኛለች...? ለአዲስ አመትማ አብረን እንዘልቃለን በሚል ደቂቅ ተስፋ
አምሮብኝ እንድታይ ኩታዬን ሳሰፋ
ምታዪኝ ይመስል ፀጉሬን አበጥሬ
ተስፋዬን አንግቤ ባንቺ ፍቅር ንሬ
አቤት የኔ ጉጉት አቤት የኔ እምነት
ከራሴ ስጣላ ከራሴ ስሟገት
ልንገራት? ይቅርብኝ?........
ፈራ ተባ እያልኩኝ ምታዪኝ ይመስል እንዲያ ስሽኮረመም
ፎቶሽን እያየው በሳቅሽ ስታከም
ምን ያልሆንኩት አለ ለሰው ማይወራ
በከርቤ የማይተው በወይራ ማይጠራ።
በላብ ከወጣልህ ባህርዛፍ ታጠነው የሚል የሰው ምክር
አመት በዓል ሲመጣ እንዲ ያረገኝ ነበር።
ትዝ ይለኛል ቀኑ ጳጉሜ ላይ ነበረ
በአንድ የፅሁፍ መልዕክት ልቤ ተሰበረ።
እንባ ተናነቀኝ የማደርገው ጠፋኝ
ከወትሮ የተለየ የእዉነት በጣም ከፋኝ
ህይወት ጣዕም አጣ ፈፅሞ ከረፋኝ።
እንቅልፍን ጠላሁት ውሎዬ እና አዳሬ ፀሎት ብቻ ሆነ
ይሄው እስከዛሬ ባንቺ የቃል ክህደት ልቤ እየባከነ።
በአል በመድረሱ ምኞቱን ለመግለፅ ሰላምታ ቢሰጥም
ቁጣ ቁጣ ይለኛል በባህሩ ጀልባ ወዳንቺ ሲያሰጥም
እናም እናቴዋ
እኔና መስከረም ትዝታ የለንም ለሰው የሚነገር
መስከረምም ይጥባ እኔም ልቤን ልዳር።
✍✍OB'☀️ (Jadon)
@jadmasse25
@getem
@getem
👍47❤12😢8🔥3
#እኔ_እራሴን_የሆንኩኝ_ለት
፡
፡
፡
እኔ እራሴን አይደለሁም፣
እያለውኝ ግን የለሁም።
አጉል ጉራን ስቸረችር ማልበገር ሲመስላቸው፣
በሆዴ ውስጥ ብዬ አውቃለው ባረገልኝ እንደ አፋቸው።
ክንብንቤን ገፈው ጥለው ማንነቴን ቢያስተውሉ፣
የኔስ ሕይወት ድብብቆሽ ከራሴው ጋር አኩኩሉ።
፡
፡
አንደበቴም አንድ ብሎ ዋሾነትን ከለመደ፣
ፍቅር ልቤን ስልብ አድርጎት እሩቅ ትቶኝ ከነጎደ፣
እምጥ ሰዶ ተንሰራፍቶ ናፍቆት ሥሩን ከዘረጋ፣
ውሸት ጉራን እየነዛው ስንቴ መሽቶ ስንቴ ነጋ።
፡
፡
ለሰው እንጂ ማስመሰሌ ዳሩ ለኔ ምን ፋይዳ አለው፣
ባደባባይ የሚቃጣኝ ጀግና ኩሩ ልብ እንዳለው።
ድንቄም ኩሩ ድንቄም ጀግና፣
ለነገሩ ማን አውቆብኝ እኔ እራሴን መች ሆንኩና።
፡
፡
እውነቱማ
ቁርሾ ዘልቆ መሀላችን ስንራራቅ ስንለያይ፣
ካንጀት ፈልቆ የሚፈሰው ሳቄም ሆኑዋል ካንገት በላይ።
እህል ውሀው አራቀኝም ሆዴም ጠግቧል ልቤ እርቦት፣
በሞላ ሰው አንቺን ይላል ጀሌ ጅጊ አጀብ ከቦት።
ትከሻዬ ምን ቢሰፋ መንፈሴ ግን ተሰበረ፣
ትዝታሽም ከጫንቃዬ እንደ ቋጥኝ ተከመረ።
ለነገሩ ምን ፋይዳ አለው፣
መች ለማለው መች ሰማለው፣
እኔ እራሴን እኮ አይደለው።
፣
፣
ወደ ራሴው ተመልሼ፣
ማስመሰሌን ከቀበርኩት ላያዳግም መሬት ምሼ፣
እውነት እውነት ፣
እኔ ራሴን የሆንኩኝ ለት፣
እሺታሽም ታክሎበት፣
ድሪቶውን ወዲያ ጥዬ ሀቁን ላንቺው ብናገረው፣
የፍቅራችን ዳግም ውልደት ያኔ ነበር ሚከበረው።
፡
፡
ለነገሩ ምን ሊጠቅም፣
አልናገር አልጋገር እኔ እራሴን ሆኜ አላውቅም።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@getem
@getem
@getem
፡
፡
፡
እኔ እራሴን አይደለሁም፣
እያለውኝ ግን የለሁም።
አጉል ጉራን ስቸረችር ማልበገር ሲመስላቸው፣
በሆዴ ውስጥ ብዬ አውቃለው ባረገልኝ እንደ አፋቸው።
ክንብንቤን ገፈው ጥለው ማንነቴን ቢያስተውሉ፣
የኔስ ሕይወት ድብብቆሽ ከራሴው ጋር አኩኩሉ።
፡
፡
አንደበቴም አንድ ብሎ ዋሾነትን ከለመደ፣
ፍቅር ልቤን ስልብ አድርጎት እሩቅ ትቶኝ ከነጎደ፣
እምጥ ሰዶ ተንሰራፍቶ ናፍቆት ሥሩን ከዘረጋ፣
ውሸት ጉራን እየነዛው ስንቴ መሽቶ ስንቴ ነጋ።
፡
፡
ለሰው እንጂ ማስመሰሌ ዳሩ ለኔ ምን ፋይዳ አለው፣
ባደባባይ የሚቃጣኝ ጀግና ኩሩ ልብ እንዳለው።
ድንቄም ኩሩ ድንቄም ጀግና፣
ለነገሩ ማን አውቆብኝ እኔ እራሴን መች ሆንኩና።
፡
፡
እውነቱማ
ቁርሾ ዘልቆ መሀላችን ስንራራቅ ስንለያይ፣
ካንጀት ፈልቆ የሚፈሰው ሳቄም ሆኑዋል ካንገት በላይ።
እህል ውሀው አራቀኝም ሆዴም ጠግቧል ልቤ እርቦት፣
በሞላ ሰው አንቺን ይላል ጀሌ ጅጊ አጀብ ከቦት።
ትከሻዬ ምን ቢሰፋ መንፈሴ ግን ተሰበረ፣
ትዝታሽም ከጫንቃዬ እንደ ቋጥኝ ተከመረ።
ለነገሩ ምን ፋይዳ አለው፣
መች ለማለው መች ሰማለው፣
እኔ እራሴን እኮ አይደለው።
፣
፣
ወደ ራሴው ተመልሼ፣
ማስመሰሌን ከቀበርኩት ላያዳግም መሬት ምሼ፣
እውነት እውነት ፣
እኔ ራሴን የሆንኩኝ ለት፣
እሺታሽም ታክሎበት፣
ድሪቶውን ወዲያ ጥዬ ሀቁን ላንቺው ብናገረው፣
የፍቅራችን ዳግም ውልደት ያኔ ነበር ሚከበረው።
፡
፡
ለነገሩ ምን ሊጠቅም፣
አልናገር አልጋገር እኔ እራሴን ሆኜ አላውቅም።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@getem
@getem
@getem
👍37❤12😱2
#እኔ_ወይስ_ፍቅር
(ከአይነ-ስውሩ ፍቅር ጋር የተደረገ ምልልስ)
ሰላም በሰፈነ በዛች ለምለም ቦታ
ድምፁ ሚያስተጋባ የወፎች ጫጫታ
በለሙ ምድር ላይ አበቦች ተተክለው
መአዛው ግሩም ነው...
አንድ ሽታ ነበር ሰርፆ ከኔ የዋለ
ልቤም ጠረጠረ አይኔም ሸነገለ።
የሸተተኝ ነገር ምንጩን ልፈልገው
ፍቅርን ላገኘው ላየው ስለጓጓው
ሲሄድ ስከተለው ዞሮ እንኳን ሳያየኝ ከታጠረው ቦታ መርቶ አደረሰኝ
ስገምት ከፍቶታል......
በተፈጥሮ ጠረን እየተገረመ
ብሬሉን አንስቶ ግጥሙን ገጠመ
"አይኔ ጠፋ ብዬ አላማርርህም
መሪዬም ከጎኔ የለም አልልህም
ግና ግን አምላኬ...
#ንፁህ ልብ ላለው ፍቅር ለሚገባው
እኔን ለሱ ሰጥተህ ህይወቱን ላስውበው"
በፍቅር ግጥሞች እንዲህ ተገርሜ
አብሬው ገጠምኩኝ በብዕሬ ታክሜ
ጉሮሮዬን ጠራርጌ....
"እኔ ነኝ ፍቅር ሆይ ስከተልህ ነበር
ምን እንደምታደርግ ለማወቅ ስታትር
አንተን አገኘውህ ተቀምጠህ ካጥር"
"ስትገጥም ሰማሁኝ ለአምላክህ ስትለምን
ንፁህ ልብ ላለው ስጠኝ ያልከው ለምን?"
#የጎደፈ ልቡ ባንተ እንዲጠራ
ለሱ ነበር መሆን የሰጠህ አደራ
ግና ግን አንተ ራስ ወዳድ ነህና
ንፁህ ልብ ላለው ጠየክ በልመና"
እንዲ ስለው ድንገት እንደ ደነገጠ
ካለ'ውበት ጥሎኝ ሮጦ ፈረጠጠ
ማነው ቆይ ትክክል? ፍቅር ወይስ እኔ
በፅድቅ መንገድ ላይ የገባው ኩነኔ
✍OB'☀️(ja)
👇👇For your comments @jadmasse25
@getem
@getem
@getem
(ከአይነ-ስውሩ ፍቅር ጋር የተደረገ ምልልስ)
ሰላም በሰፈነ በዛች ለምለም ቦታ
ድምፁ ሚያስተጋባ የወፎች ጫጫታ
በለሙ ምድር ላይ አበቦች ተተክለው
መአዛው ግሩም ነው...
አንድ ሽታ ነበር ሰርፆ ከኔ የዋለ
ልቤም ጠረጠረ አይኔም ሸነገለ።
የሸተተኝ ነገር ምንጩን ልፈልገው
ፍቅርን ላገኘው ላየው ስለጓጓው
ሲሄድ ስከተለው ዞሮ እንኳን ሳያየኝ ከታጠረው ቦታ መርቶ አደረሰኝ
ስገምት ከፍቶታል......
በተፈጥሮ ጠረን እየተገረመ
ብሬሉን አንስቶ ግጥሙን ገጠመ
"አይኔ ጠፋ ብዬ አላማርርህም
መሪዬም ከጎኔ የለም አልልህም
ግና ግን አምላኬ...
#ንፁህ ልብ ላለው ፍቅር ለሚገባው
እኔን ለሱ ሰጥተህ ህይወቱን ላስውበው"
በፍቅር ግጥሞች እንዲህ ተገርሜ
አብሬው ገጠምኩኝ በብዕሬ ታክሜ
ጉሮሮዬን ጠራርጌ....
"እኔ ነኝ ፍቅር ሆይ ስከተልህ ነበር
ምን እንደምታደርግ ለማወቅ ስታትር
አንተን አገኘውህ ተቀምጠህ ካጥር"
"ስትገጥም ሰማሁኝ ለአምላክህ ስትለምን
ንፁህ ልብ ላለው ስጠኝ ያልከው ለምን?"
#የጎደፈ ልቡ ባንተ እንዲጠራ
ለሱ ነበር መሆን የሰጠህ አደራ
ግና ግን አንተ ራስ ወዳድ ነህና
ንፁህ ልብ ላለው ጠየክ በልመና"
እንዲ ስለው ድንገት እንደ ደነገጠ
ካለ'ውበት ጥሎኝ ሮጦ ፈረጠጠ
ማነው ቆይ ትክክል? ፍቅር ወይስ እኔ
በፅድቅ መንገድ ላይ የገባው ኩነኔ
✍OB'☀️(ja)
👇👇For your comments @jadmasse25
@getem
@getem
@getem
👍37❤18😢2😱1🎉1
#እኔ_እንደው
:
:
፡
በሀዘን ሌት ተቀን ብናኝ፤
በደስታ ውቅያኖስ ውስጥ ብዋኝ፤
በችግር ሰውነቴ ቢደቅ፤
በተድላ ምን ብንደላቀቅ፤
ቢበርደኝ ቁሩ በርትቶ፤
ቢሞቀኝ ኑሮ ተስማምቶ፤
ቢጥለኝ የዚህ ዓለም ፍዳ፤
ቢደላኝ ያለ አንዳች ዕዳ፤
ብታለቅስ ህይወቴ ታማ፤
ብትስቅ ደግሞ አገግማ፤
ብሸነፍ ካንዴም ሁለቴ፤
ቢበልጥ ከሰው ብርታቴ፤
ቢኖረኝ ብዙ ቀማኛ፤
አልያም ብሆን ዝነኛ፤
ቢነሳ ስሜ በክፉ፤
ቢስሙኝ እየደገፉ፤
ብከበር ባገር መንደሬ፤
ቢረሳም ከነ መኖሬ፤
፡
፡
እኔ እንደው እኔ እራሴው ነኝ፤
ሁኔታን ሁሉን ረግጬ፤
የምኖር አንቺን መርጬ።
፡
፡
እኔ እንደው እኔ እራሴው ነኝ፤
እንዳሻው ቢፈጠር ታምር፤
የምሞት አንቺን ሳፈቅር።
፡
፡
እኔ እንደው እኔ እራሴው ነኝ!
እኔ እንደው እኔ እራሴው ነኝ!
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@getem
@getem
@getem
:
:
፡
በሀዘን ሌት ተቀን ብናኝ፤
በደስታ ውቅያኖስ ውስጥ ብዋኝ፤
በችግር ሰውነቴ ቢደቅ፤
በተድላ ምን ብንደላቀቅ፤
ቢበርደኝ ቁሩ በርትቶ፤
ቢሞቀኝ ኑሮ ተስማምቶ፤
ቢጥለኝ የዚህ ዓለም ፍዳ፤
ቢደላኝ ያለ አንዳች ዕዳ፤
ብታለቅስ ህይወቴ ታማ፤
ብትስቅ ደግሞ አገግማ፤
ብሸነፍ ካንዴም ሁለቴ፤
ቢበልጥ ከሰው ብርታቴ፤
ቢኖረኝ ብዙ ቀማኛ፤
አልያም ብሆን ዝነኛ፤
ቢነሳ ስሜ በክፉ፤
ቢስሙኝ እየደገፉ፤
ብከበር ባገር መንደሬ፤
ቢረሳም ከነ መኖሬ፤
፡
፡
እኔ እንደው እኔ እራሴው ነኝ፤
ሁኔታን ሁሉን ረግጬ፤
የምኖር አንቺን መርጬ።
፡
፡
እኔ እንደው እኔ እራሴው ነኝ፤
እንዳሻው ቢፈጠር ታምር፤
የምሞት አንቺን ሳፈቅር።
፡
፡
እኔ እንደው እኔ እራሴው ነኝ!
እኔ እንደው እኔ እራሴው ነኝ!
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@getem
@getem
@getem
❤34👍17🔥2😱1
#እኔ_ነኝ
:
:
ትዝታ እና ተስፋን ድንበር ተከልሎ፤
በነገ እና ትናንት መሀል ድንኳን ተክሎ፤
ቀንበርን ሳይፈራ፤
ማቅ እና እጀ ጠባብ ለብሶ በየተራ፤
ለመላቅ ከቅድም፤
እራሱን ለመርታት እራሱን ሚቀድም።
እኔ ነኝ!
፡
፡
ተድላና ትካዜ ሚፈራረቁበት፤
ተንጋሎ የሚጓዝ ወደ ህልሙ አቀበት፤
ደጋን የማይወጥር ሾተልን የማይልስ፤
ፍላፃና ሎጋን በፍቅር ሚመልስ።
እኔ ነኝ!
:
:
አሜን ይሁን የሚል ክፉም ሆነ ደጉን፤
እኔ ነኝ ያ ምስጉን!
#ሄኖክ_ብርሃኑ (@yeneeyita)
@yeneeyita
@getem
@getem
:
:
ትዝታ እና ተስፋን ድንበር ተከልሎ፤
በነገ እና ትናንት መሀል ድንኳን ተክሎ፤
ቀንበርን ሳይፈራ፤
ማቅ እና እጀ ጠባብ ለብሶ በየተራ፤
ለመላቅ ከቅድም፤
እራሱን ለመርታት እራሱን ሚቀድም።
እኔ ነኝ!
፡
፡
ተድላና ትካዜ ሚፈራረቁበት፤
ተንጋሎ የሚጓዝ ወደ ህልሙ አቀበት፤
ደጋን የማይወጥር ሾተልን የማይልስ፤
ፍላፃና ሎጋን በፍቅር ሚመልስ።
እኔ ነኝ!
:
:
አሜን ይሁን የሚል ክፉም ሆነ ደጉን፤
እኔ ነኝ ያ ምስጉን!
#ሄኖክ_ብርሃኑ (@yeneeyita)
@yeneeyita
@getem
@getem
❤19👍11
#እኔ_እራሴን_የሆንኩኝ_ለት
፡
፡
፡
እኔ እራሴን አይደለሁም፣
እያለውኝ ግን የለሁም።
አጉል ጉራን ስቸረችር
ማልበገር ሲመስላቸው፣
በሆዴ ውስጥ ብዬ አውቃለው
ባረገልኝ እንደ አፋቸው።
ክንብንቤን ገፈው ጥለው
ማንነቴን ቢያስተውሉ፣
የኔስ ሕይወት ድብብቆሽ
ከራሴው ጋር አኩኩሉ።
፡
፡
አንደበቴም አንድ ብሎ
ዋሾነትን ከለመደ፣
ፍቅር ልቤን ስልብ አድርጎት
እሩቅ ትቶኝ ከነጎደ፣
እምጥ ሰዶ ተንሰራፍቶ
ናፍቆት ሥሩን ከዘረጋ፣
ውሸት ጉራን እየነዛው
ስንቴ መሽቶ ስንቴ ነጋ።
፡
፡
ለሰው እንጂ ማስመሰሌ
ዳሩ ለኔ ምን ፋይዳ አለው፣
ባደባባይ የሚቃጣኝ
ጀግና ኩሩ ልብ እንዳለው።
ድንቄም ኩሩ ድንቄም ጀግና፣
ለነገሩ ማን አውቆብኝ
እኔ እራሴን መች ሆንኩና።
፡
፡
እውነቱማ
ቁርሾ ዘልቆ መሀላችን
ስንራራቅ ስንለያይ፣
ካንጀት ፈልቆ የሚፈሰው
ሳቄም ሆኗል ካንገት በላይ።
እህል ውሀው አራቀኝም
ሆዴም ጠግቧል ልቤ እርቦት፣
በሞላ ሰው አንቺን ይላል
ጀሌ ጅጊ አጀብ ከቦት።
ትከሻዬ ምን ቢሰፋ
መንፈሴ ግን ተሰበረ፣
ትዝታሽም ከጫንቃዬ
እንደ ቋጥኝ ተከመረ።
ለነገሩ ምን ፋይዳ አለው፣
መች ለማለው መች ሰማለው፣
እኔ እራሴን እኮ አይደለው።
፣
፣
ወደ ራሴው ተመልሼ፣
ማስመሰሌን ከቀበርኩት
ላያዳግም መሬት ምሼ፣
እውነት እውነት፣
እኔ ራሴን የሆንኩኝ ለት፣
እሺታሽም ታክሎበት፣
ድሪቶውን ወዲያ ጥዬ
ሀቁን ላንቺው ብናገረው፣
የፍቅራችን ዳግም ውልደት
ያኔ ነበር ሚከበረው።
፡
፡
ለነገሩ ምን ሊጠቅም፣
አልናገር አልጋገር
እኔ እራሴን ሆኜ አላውቅም።
#ሄኖክ_ብርሃኑ (@yeneeyita)
@yeneeyita
@getem
@getem
@getem
፡
፡
፡
እኔ እራሴን አይደለሁም፣
እያለውኝ ግን የለሁም።
አጉል ጉራን ስቸረችር
ማልበገር ሲመስላቸው፣
በሆዴ ውስጥ ብዬ አውቃለው
ባረገልኝ እንደ አፋቸው።
ክንብንቤን ገፈው ጥለው
ማንነቴን ቢያስተውሉ፣
የኔስ ሕይወት ድብብቆሽ
ከራሴው ጋር አኩኩሉ።
፡
፡
አንደበቴም አንድ ብሎ
ዋሾነትን ከለመደ፣
ፍቅር ልቤን ስልብ አድርጎት
እሩቅ ትቶኝ ከነጎደ፣
እምጥ ሰዶ ተንሰራፍቶ
ናፍቆት ሥሩን ከዘረጋ፣
ውሸት ጉራን እየነዛው
ስንቴ መሽቶ ስንቴ ነጋ።
፡
፡
ለሰው እንጂ ማስመሰሌ
ዳሩ ለኔ ምን ፋይዳ አለው፣
ባደባባይ የሚቃጣኝ
ጀግና ኩሩ ልብ እንዳለው።
ድንቄም ኩሩ ድንቄም ጀግና፣
ለነገሩ ማን አውቆብኝ
እኔ እራሴን መች ሆንኩና።
፡
፡
እውነቱማ
ቁርሾ ዘልቆ መሀላችን
ስንራራቅ ስንለያይ፣
ካንጀት ፈልቆ የሚፈሰው
ሳቄም ሆኗል ካንገት በላይ።
እህል ውሀው አራቀኝም
ሆዴም ጠግቧል ልቤ እርቦት፣
በሞላ ሰው አንቺን ይላል
ጀሌ ጅጊ አጀብ ከቦት።
ትከሻዬ ምን ቢሰፋ
መንፈሴ ግን ተሰበረ፣
ትዝታሽም ከጫንቃዬ
እንደ ቋጥኝ ተከመረ።
ለነገሩ ምን ፋይዳ አለው፣
መች ለማለው መች ሰማለው፣
እኔ እራሴን እኮ አይደለው።
፣
፣
ወደ ራሴው ተመልሼ፣
ማስመሰሌን ከቀበርኩት
ላያዳግም መሬት ምሼ፣
እውነት እውነት፣
እኔ ራሴን የሆንኩኝ ለት፣
እሺታሽም ታክሎበት፣
ድሪቶውን ወዲያ ጥዬ
ሀቁን ላንቺው ብናገረው፣
የፍቅራችን ዳግም ውልደት
ያኔ ነበር ሚከበረው።
፡
፡
ለነገሩ ምን ሊጠቅም፣
አልናገር አልጋገር
እኔ እራሴን ሆኜ አላውቅም።
#ሄኖክ_ብርሃኑ (@yeneeyita)
@yeneeyita
@getem
@getem
@getem
👍58❤9😱8🔥1