ቃል ከአፋቸው ሳይወጣ
ፍቅር ተሰናብቶ መለያየት መጣ
ቻው እንኳን ሳይሉኝ
ሁሉም አገለሉኝ
እኔ ብቻ ሆነ እኔን የወደደው
እሱስ ተራው ደርሶ መች ይሆን ሚሄደው
By @Absari_seven
@getem
@getem
ፍቅር ተሰናብቶ መለያየት መጣ
ቻው እንኳን ሳይሉኝ
ሁሉም አገለሉኝ
እኔ ብቻ ሆነ እኔን የወደደው
እሱስ ተራው ደርሶ መች ይሆን ሚሄደው
By @Absari_seven
@getem
@getem
❤37🤩9🔥5
ራሱ’ንደማይጠጣ - የውሃ ማሰሮ፣
መሆን ላልተቻለው - ክው ያለ ጉሮሮ፤
አስመሳይ ደጋጎች - ውሃ ሰጡት’ና፣
የሞት ሞቱን ሲኖር - ችግሩ እንደጠና፤
ጉሮሮ ማሰሮ - ተመሳስሎባቸው፣
ያጠጡትን ቀድተው - መውሰድ ላቃታቸው፤
ረሃብ አንጎራጉሮ - ለለመደው ውሃ፣
ሰጥቶ ተቀባዮች አስቀየመልሃ!
(የሞገሴ ልጅ)
@eyadermoges
@getem
@getem
@getem
መሆን ላልተቻለው - ክው ያለ ጉሮሮ፤
አስመሳይ ደጋጎች - ውሃ ሰጡት’ና፣
የሞት ሞቱን ሲኖር - ችግሩ እንደጠና፤
ጉሮሮ ማሰሮ - ተመሳስሎባቸው፣
ያጠጡትን ቀድተው - መውሰድ ላቃታቸው፤
ረሃብ አንጎራጉሮ - ለለመደው ውሃ፣
ሰጥቶ ተቀባዮች አስቀየመልሃ!
(የሞገሴ ልጅ)
@eyadermoges
@getem
@getem
@getem
❤19👍14🔥1
ዛሬ ሌላ ሰው ነኝ።
ያኔ ትንሽ ሆኜ-
በእድሜዬ ለጋ - በበሓሪ ችኩል፣
አፍንጫ አሽትቻለሁ፣
ቀድሞኝ ከበሰለው - ለመታየት እኩል።
ልጅነትን ሳልፈው-
ሌላን ማየት ትቼ - ራሴን ዐየሁ እና፣
ገደብ ሰራሁለት፣
ጉጉቴ ልክ አልፎ -ስጎድል እንዳይቀና።
ልልሽ የፈለግሁት-
አንቺ ላታስቢኝ አትበይ “ረስተኸኛል”፣
የሰርግሽን ፎቶ-
ከልቤ ሳደንቀው እራሴም ገርሞኛል።
ምክንያት፣...
ያኔ ወጣትነት - ኩራት የኮፈሰኝ፣
ትእቢት ላንዳፍታ - ወስዶ የመለሰኝ፤
እልህ እየጋተ - ምላጭ የሚያስውጠኝ፣
“ዛሬ ብቻ” ባይ ኅዝብ - አስሶ እሚመርጠኝ፤
ዛሬ...
አንቺ የኖርሽውን - ዘመን የኖርኩ እኔ፣
እራሴን ያስተማርኩ - በሕይወት ጠመኔ፤
አንቺ “ፈልጉኝ” ባይ - እኔ ራሴን መሪ፣
አንቺ ላይሽ ፋኖስ - እኔ ውስጤ በሪ፤
ከመንገድሽ እሩቅ - መንገዴ ወስዶኛል፣
ሺህ ግዜ አግብተሽ - ሺህ ግዜ ብትፈቺ ምን ያናድደኛል?
በርቺ 😐
@eyadermoges
@getem
@getem
@getem
ያኔ ትንሽ ሆኜ-
በእድሜዬ ለጋ - በበሓሪ ችኩል፣
አፍንጫ አሽትቻለሁ፣
ቀድሞኝ ከበሰለው - ለመታየት እኩል።
ልጅነትን ሳልፈው-
ሌላን ማየት ትቼ - ራሴን ዐየሁ እና፣
ገደብ ሰራሁለት፣
ጉጉቴ ልክ አልፎ -ስጎድል እንዳይቀና።
ልልሽ የፈለግሁት-
አንቺ ላታስቢኝ አትበይ “ረስተኸኛል”፣
የሰርግሽን ፎቶ-
ከልቤ ሳደንቀው እራሴም ገርሞኛል።
ምክንያት፣...
ያኔ ወጣትነት - ኩራት የኮፈሰኝ፣
ትእቢት ላንዳፍታ - ወስዶ የመለሰኝ፤
እልህ እየጋተ - ምላጭ የሚያስውጠኝ፣
“ዛሬ ብቻ” ባይ ኅዝብ - አስሶ እሚመርጠኝ፤
ዛሬ...
አንቺ የኖርሽውን - ዘመን የኖርኩ እኔ፣
እራሴን ያስተማርኩ - በሕይወት ጠመኔ፤
አንቺ “ፈልጉኝ” ባይ - እኔ ራሴን መሪ፣
አንቺ ላይሽ ፋኖስ - እኔ ውስጤ በሪ፤
ከመንገድሽ እሩቅ - መንገዴ ወስዶኛል፣
ሺህ ግዜ አግብተሽ - ሺህ ግዜ ብትፈቺ ምን ያናድደኛል?
በርቺ 😐
@eyadermoges
@getem
@getem
@getem
❤26👍20🔥1😁1
የማመንታት ፍቅር
ልሂድ ወይስ ልቅር
(ያለበት)
ጓዝሽን ጠቅልለሽ በስንብትሽ እለት
ደግሞ ተመልሶ
ከበቃኸኝ በኃላ ካልበላሁ ማለት
(ምን ይሉታል አሁን)
ተፍተሺኝ አንቅረሽ
ጥላቻን አፍቅረሽ
ባፍንጫሽ ወጥቼ
ለፍቺያችን ድግስ የወይን ጠጅ ጠጥቼ
(ችርስ ተባብለን)
ወይ መተሽ አትመጪ ወይ ቀርተሽ አትቀሪ
ድንገት ትገኛለሽ ለፍቅር ከፊቴ ስትደነቀሪ
By @Absari_seven
@getem
@getem
ልሂድ ወይስ ልቅር
(ያለበት)
ጓዝሽን ጠቅልለሽ በስንብትሽ እለት
ደግሞ ተመልሶ
ከበቃኸኝ በኃላ ካልበላሁ ማለት
(ምን ይሉታል አሁን)
ተፍተሺኝ አንቅረሽ
ጥላቻን አፍቅረሽ
ባፍንጫሽ ወጥቼ
ለፍቺያችን ድግስ የወይን ጠጅ ጠጥቼ
(ችርስ ተባብለን)
ወይ መተሽ አትመጪ ወይ ቀርተሽ አትቀሪ
ድንገት ትገኛለሽ ለፍቅር ከፊቴ ስትደነቀሪ
By @Absari_seven
@getem
@getem
❤32👍11🔥4
ቆርጦልኝ ነበረ ነግሬሽ የልቤን ወድሻለሁ ብዬ
የምትወጂኝ መስሎኝ ስጠብቅሽ ቀረሁ ካደርኩበት ውዬ
ነካክተሽ ነካክሽ ልቤን አደረግሽው የፍቅርሽ ምርኮኛ
የማትወጂኝ ከሆን ለምን ቀሰቀስሽው ይቅር እንደተኛ
አይቀርም አንድ ቀን ያፈቀረሽ ልቤ የጎኑን ማግኘቱ
ህይወት ይቀጥላል ምን ልቤ ቢደክም አንቺን በማጣቱ
አገኘሽኝ እንጂ ሆኜ ያንቺ ወዳጅ
ከፍቅርሽ አለም ውስጥ
ሳላውቀው ገብቼ እንደ ባህር ሰርጓጅ
ግን ...
ያሳሰበኝ ፍቅር
ካንቺ ስር ያዋለኝ እንዲህ እንደከረረ
ሌላ ሲያይሽ ጊዜ ቀንቼ ነበረ
አፈቀርኩሽ ያልኩት
የኔ ያልኩትን ሰው በሌላ ሲታቀፍ
እንዴት ብዬ ልለፍ
የመነጠቅ መንፈስ
ውስጤን እንገብግቦት አላመጣሁሽም
እውነቱን ስነግርሽ
ቀንቼ ነው እንጂ አላፈቀርኩሽም
አልልሽም ይህን ቃሌን ድፍረት የለኝ የምልበት
ያጠፋዋልና የወንድነት ልኩን ይህን ያልኩሽ እለት
እንደገባኝ ቢሆን ከዚህ ሁሉ ነገር
ቅናት መንፈስ እንጂ አልነበረም ማፍቀር
ዮርዳኖስ @JorDanos7
@getem
@getem
@getem
የምትወጂኝ መስሎኝ ስጠብቅሽ ቀረሁ ካደርኩበት ውዬ
ነካክተሽ ነካክሽ ልቤን አደረግሽው የፍቅርሽ ምርኮኛ
የማትወጂኝ ከሆን ለምን ቀሰቀስሽው ይቅር እንደተኛ
አይቀርም አንድ ቀን ያፈቀረሽ ልቤ የጎኑን ማግኘቱ
ህይወት ይቀጥላል ምን ልቤ ቢደክም አንቺን በማጣቱ
አገኘሽኝ እንጂ ሆኜ ያንቺ ወዳጅ
ከፍቅርሽ አለም ውስጥ
ሳላውቀው ገብቼ እንደ ባህር ሰርጓጅ
ግን ...
ያሳሰበኝ ፍቅር
ካንቺ ስር ያዋለኝ እንዲህ እንደከረረ
ሌላ ሲያይሽ ጊዜ ቀንቼ ነበረ
አፈቀርኩሽ ያልኩት
የኔ ያልኩትን ሰው በሌላ ሲታቀፍ
እንዴት ብዬ ልለፍ
የመነጠቅ መንፈስ
ውስጤን እንገብግቦት አላመጣሁሽም
እውነቱን ስነግርሽ
ቀንቼ ነው እንጂ አላፈቀርኩሽም
አልልሽም ይህን ቃሌን ድፍረት የለኝ የምልበት
ያጠፋዋልና የወንድነት ልኩን ይህን ያልኩሽ እለት
እንደገባኝ ቢሆን ከዚህ ሁሉ ነገር
ቅናት መንፈስ እንጂ አልነበረም ማፍቀር
ዮርዳኖስ @JorDanos7
@getem
@getem
@getem
👍35❤25🤩6🔥3
ግጥም ነው ምትመስዪው!
---------------------------------------
ከፊደል ማሳ ላይ ቃላት ለሚቃርም
ካገኘም ከትቦ እያደር ሚያርም÷
በአርኬው መባቻ በመድፋት አባዜ
ከሃሳብ ባህር ላይ ሰጥሞ በትካዜ÷
በብዕሩ እንባ ስንኞች ሲቋጥር
ቤቱን በመዘንጋት ቤት ለመምታት ሚጥር÷
እቴ አትሞኚ ከቁብ ለማይቆጥርሽ
በፍቅር አጊጠሽ አምሮብሽ ቢያይሽ÷
በቃላት ስደራ የተሽቀረቀረ
በታሪክ ፍሰቱ ጎልቶ የዳበረ÷
ግጥም ነው ምትመስዪው
መምቻና መድፊያው ፍፃሜው ያማረ::
By @Abuugida
@getem
@getem
@getem
---------------------------------------
ከፊደል ማሳ ላይ ቃላት ለሚቃርም
ካገኘም ከትቦ እያደር ሚያርም÷
በአርኬው መባቻ በመድፋት አባዜ
ከሃሳብ ባህር ላይ ሰጥሞ በትካዜ÷
በብዕሩ እንባ ስንኞች ሲቋጥር
ቤቱን በመዘንጋት ቤት ለመምታት ሚጥር÷
እቴ አትሞኚ ከቁብ ለማይቆጥርሽ
በፍቅር አጊጠሽ አምሮብሽ ቢያይሽ÷
በቃላት ስደራ የተሽቀረቀረ
በታሪክ ፍሰቱ ጎልቶ የዳበረ÷
ግጥም ነው ምትመስዪው
መምቻና መድፊያው ፍፃሜው ያማረ::
By @Abuugida
@getem
@getem
@getem
❤29👍4😁1
ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
--------------------------
አንቺ ስትስቂ
ከሰማይ ላይ ወፎች፣
እስከ ምድር ሰዎች፣
የገነት በር ደጆች፣
የቅዱሳን ፊቶች፣
አምረው ያበራሉ፤
ደስታን ያገኛሉ።
ትልቁ ጎልያድ
በሳቅሽ ተማሎ፣
ብላቴነው ዳዊት
ጠጠሮቹን ጥሎ፣
ያንቺን ሳቅ ነበረ
ተቃቅፈው ሚሰሙት፣
ፈገግታሽን ነበር
ሚያስቡት ሚያልሙት።
አንቺ ስትስቂ
ፀሃይ ከጨርቃ፣
ብርሃን ከጨለማ፣
ሰማይ ከምድር ጋ፣
ወፎች ከአረዊቶች፣
ክረምት ሳይቀር በጋ፣
አንድ አምሳል ነበሩ፣
በሳቅሽ ግዞት ውስጥ
አንድ ላይ ሚኖሩ።
ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
ጎልያድ አቅራራ
ዳዊት ላይ ደነፋ፣
አባቶች ተከፍተው
መቋሚያ አነሱ፣
እንድትስቂላቸዉ
ፆም ፀሎት ሊያደርሱ።
ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
ሰማይ አለቀሰ፣
ፀሃይ ተናደደች፣
ነፍሳትን አቃጥላ
ጨለማን ሰደደች።
እኔም ስጠባበቅ
በምኞት በተስፋ፣
ሳቅሽን ናፍቄ
ሳቅሽን ተርቤ
ግዜ ይዞኝ ጠፋ
ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
@getem
@getem
@paappii
--------------------------
አንቺ ስትስቂ
ከሰማይ ላይ ወፎች፣
እስከ ምድር ሰዎች፣
የገነት በር ደጆች፣
የቅዱሳን ፊቶች፣
አምረው ያበራሉ፤
ደስታን ያገኛሉ።
ትልቁ ጎልያድ
በሳቅሽ ተማሎ፣
ብላቴነው ዳዊት
ጠጠሮቹን ጥሎ፣
ያንቺን ሳቅ ነበረ
ተቃቅፈው ሚሰሙት፣
ፈገግታሽን ነበር
ሚያስቡት ሚያልሙት።
አንቺ ስትስቂ
ፀሃይ ከጨርቃ፣
ብርሃን ከጨለማ፣
ሰማይ ከምድር ጋ፣
ወፎች ከአረዊቶች፣
ክረምት ሳይቀር በጋ፣
አንድ አምሳል ነበሩ፣
በሳቅሽ ግዞት ውስጥ
አንድ ላይ ሚኖሩ።
ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
ጎልያድ አቅራራ
ዳዊት ላይ ደነፋ፣
አባቶች ተከፍተው
መቋሚያ አነሱ፣
እንድትስቂላቸዉ
ፆም ፀሎት ሊያደርሱ።
ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
ሰማይ አለቀሰ፣
ፀሃይ ተናደደች፣
ነፍሳትን አቃጥላ
ጨለማን ሰደደች።
እኔም ስጠባበቅ
በምኞት በተስፋ፣
ሳቅሽን ናፍቄ
ሳቅሽን ተርቤ
ግዜ ይዞኝ ጠፋ
ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
@getem
@getem
@paappii
❤84😁5🔥4👎1
ፍቅር አለኝ ለአንተ!
-----------------------------
አደመጥሁኝ ቅኔ መልሴ መልሼ፣
ሙዚቃውን ሰማሁ ዓለሙን አስሼ።
ዜማ ሰለለብኝ ሥዕል ደበዘዘ ግጥም አነከሰ፤
ባሳይህ... ብኖረው... የልቤ አልደረሰ።
(አንደ ምን ልግለጸው?)
ጥበብ ያሳነሰው .
ቋንቋ ያኮሰሰው .
ፍቅር አለኝ ለአንተ፣
በፍጥረት ዘመን ልክ እየተጎተተ
አስከ ዓለም ፍጻሜ ደግሞ 'ሚዘረጋ፣
ብኖርም ባንኖርም
ምጽአት የሚጠብቅ በነፍስም በሥጋ።
ፍቅር አለኝ ላንተ
ምድር የሚሞላ፣
ከእግዜር የሚያስታርቅ ከእግዜር የሚያጣላ።
By Meron Ghetnet
@getem
@getem
@getem
-----------------------------
አደመጥሁኝ ቅኔ መልሴ መልሼ፣
ሙዚቃውን ሰማሁ ዓለሙን አስሼ።
ዜማ ሰለለብኝ ሥዕል ደበዘዘ ግጥም አነከሰ፤
ባሳይህ... ብኖረው... የልቤ አልደረሰ።
(አንደ ምን ልግለጸው?)
ጥበብ ያሳነሰው .
ቋንቋ ያኮሰሰው .
ፍቅር አለኝ ለአንተ፣
በፍጥረት ዘመን ልክ እየተጎተተ
አስከ ዓለም ፍጻሜ ደግሞ 'ሚዘረጋ፣
ብኖርም ባንኖርም
ምጽአት የሚጠብቅ በነፍስም በሥጋ።
ፍቅር አለኝ ላንተ
ምድር የሚሞላ፣
ከእግዜር የሚያስታርቅ ከእግዜር የሚያጣላ።
By Meron Ghetnet
@getem
@getem
@getem
❤39
ልጅ እያለሁ –··· ጨረቃ....
(በሌሊቱ ሰማይ ደምቃ ...)
ቁልቁል ዓይኔን እያየችኝ ፤
(እያልኩ –··· “ተከተለችኝ ”)
መስሎኝ የወደደችኝ...
(ሽቅብ... ሽቅብ.... እያየኋት)
ስራመድ አቅንቼ አንገቴን ፤
መች አየሁት እንቅፋቴን ?!
(ሲነቅልብኝ አውራ ጣቴን...)
ሲጥለኝ ከመሬት ጠልፎ ፤
ሲከነብለኝ አደናቅፎ ....!
(“ወደደችኝ” ካልኩት ይብስ...)
እዛው መሬት ላይ ወድቄ ፤
(ጨረቃ ከሰማይ ወርዳ...)
እስክታነሳኝ መጠበቄ ፤
ትልቁ –··· አለማወቄ ።
💧
ያኔ ታዲያ....
“አይዞህ ልጄን !
እኔን!” እያለች ፤
አንስታኝ እያባበለች ....
(በክንዶቿ ደግፋ )
አቧራዬን አራግፋ ...
ቁስሌን በጨረቅ ያሰረች ፤
እናቴ “ግጥም” ነበረች ።
💧
“ግጥም” ነበረች እናቴ ....
(አባባይ ለልጅነቴ....)
ዘቢብ ጠብታ — ለመሪር ቀኔ
ክፍተቴን መዝጊያ — ክዳኔ ።
(ታዲያ ያኔ.....!)
ህመሜ ሲቀሰቅሰኝ...
(ጨረቃም ስትታወሰኝ....)
“እኔን ልጄን!” — መባል ሽቼ ፤
(“አመመኝ እናቴ” እያልኳት...)
እግሮቿ ላይ — ተደፍቼ....
ሲቃዬን በጨርቅ አፍኜ
(ፊቴን በቀሚሷ ሸፍኜ)
“ስቅስቅ” ያልኩት...
(“እሪ” ያልኩት...)
ልብሷ ላይ እስካሁን አለ...
እንደ ጥልፍ አምሮ –··· ተጥሎ ፤
(ዕምባዬ —··· “አበባ” መስሎ ።)
____
የካቲት 8 — 2016 ዓም
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
(በሌሊቱ ሰማይ ደምቃ ...)
ቁልቁል ዓይኔን እያየችኝ ፤
(እያልኩ –··· “ተከተለችኝ ”)
መስሎኝ የወደደችኝ...
(ሽቅብ... ሽቅብ.... እያየኋት)
ስራመድ አቅንቼ አንገቴን ፤
መች አየሁት እንቅፋቴን ?!
(ሲነቅልብኝ አውራ ጣቴን...)
ሲጥለኝ ከመሬት ጠልፎ ፤
ሲከነብለኝ አደናቅፎ ....!
(“ወደደችኝ” ካልኩት ይብስ...)
እዛው መሬት ላይ ወድቄ ፤
(ጨረቃ ከሰማይ ወርዳ...)
እስክታነሳኝ መጠበቄ ፤
ትልቁ –··· አለማወቄ ።
💧
ያኔ ታዲያ....
“አይዞህ ልጄን !
እኔን!” እያለች ፤
አንስታኝ እያባበለች ....
(በክንዶቿ ደግፋ )
አቧራዬን አራግፋ ...
ቁስሌን በጨረቅ ያሰረች ፤
እናቴ “ግጥም” ነበረች ።
💧
“ግጥም” ነበረች እናቴ ....
(አባባይ ለልጅነቴ....)
ዘቢብ ጠብታ — ለመሪር ቀኔ
ክፍተቴን መዝጊያ — ክዳኔ ።
(ታዲያ ያኔ.....!)
ህመሜ ሲቀሰቅሰኝ...
(ጨረቃም ስትታወሰኝ....)
“እኔን ልጄን!” — መባል ሽቼ ፤
(“አመመኝ እናቴ” እያልኳት...)
እግሮቿ ላይ — ተደፍቼ....
ሲቃዬን በጨርቅ አፍኜ
(ፊቴን በቀሚሷ ሸፍኜ)
“ስቅስቅ” ያልኩት...
(“እሪ” ያልኩት...)
ልብሷ ላይ እስካሁን አለ...
እንደ ጥልፍ አምሮ –··· ተጥሎ ፤
(ዕምባዬ —··· “አበባ” መስሎ ።)
____
የካቲት 8 — 2016 ዓም
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
❤52👍5
አይ አንቺ ጨረቃ
.
.
.
ስንቱን ሰዉ ታዘብሽዉ?
ስንቱን አደመጥሽዉ?
የከፋዉ እንደሆን
ላንቺ የሚያወጋዉ
በልቡ ያለዉን
ሚስጥራቱን ሁሉ.....
የሚዘረግፈዉ
እስቲ ልጠይቅሽ?
ምን ቢያይብሽ ነዉ?
✍️ዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
.
.
.
ስንቱን ሰዉ ታዘብሽዉ?
ስንቱን አደመጥሽዉ?
የከፋዉ እንደሆን
ላንቺ የሚያወጋዉ
በልቡ ያለዉን
ሚስጥራቱን ሁሉ.....
የሚዘረግፈዉ
እስቲ ልጠይቅሽ?
ምን ቢያይብሽ ነዉ?
✍️ዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
❤47🎉7👎2
ምስጋና
-------------------------
ባንቺ ተማምኜ እምነቴን ጥዬብሽ
አምኜሽ ቆይቼ ቃሌን ጠብቄልሽ፣
ዛሬ ትመጣለች ግድ የለም ወይ ነገ
ፀሃዩ ፍቅራችን ስል መች ገና አደገ፣
እልፍ አላፍ አመታት ጥሎኝ እያለፈ
መንፈቅ በመንፈቅ ላይ ሄዶ እየከነፈ፣
በዋሊት ትዝታ በሀሳብ እየኖርኩኝ
ስቀመጥ ስነሳ አንቺን እያሰብኩኝ፣
ያዘዙኝን ሳደርግ ያሉኝን ስሰራ
ስንቱን አለፍኳቸው ስንቱንስ መከራ፣
ቢሆንም
እንደው ብቅ ብለሽ ካጣሽኝ ከሌለዉ
ጆሮሽን አትስጪ ቸግሮታል ለሚለዉ
የመኖሬ ተስፉ አንቺ ነበርሽና፣
ዘግይተሽ ብትመጪም ይድረስሽ ምስጋና።
@getem
@getem
@paappii
-------------------------
ባንቺ ተማምኜ እምነቴን ጥዬብሽ
አምኜሽ ቆይቼ ቃሌን ጠብቄልሽ፣
ዛሬ ትመጣለች ግድ የለም ወይ ነገ
ፀሃዩ ፍቅራችን ስል መች ገና አደገ፣
እልፍ አላፍ አመታት ጥሎኝ እያለፈ
መንፈቅ በመንፈቅ ላይ ሄዶ እየከነፈ፣
በዋሊት ትዝታ በሀሳብ እየኖርኩኝ
ስቀመጥ ስነሳ አንቺን እያሰብኩኝ፣
ያዘዙኝን ሳደርግ ያሉኝን ስሰራ
ስንቱን አለፍኳቸው ስንቱንስ መከራ፣
ቢሆንም
እንደው ብቅ ብለሽ ካጣሽኝ ከሌለዉ
ጆሮሽን አትስጪ ቸግሮታል ለሚለዉ
የመኖሬ ተስፉ አንቺ ነበርሽና፣
ዘግይተሽ ብትመጪም ይድረስሽ ምስጋና።
@getem
@getem
@paappii
❤39👍9😢5🔥2
ተመስገን🙏🙏🙏
.
.
.
መስከረም ሲያከታትም አልፎ ሲተካ ጥቅምት፤
ፀደይ ብራ ሲሆን ሰማዩ በዛች መጀመሪያ ዕለት፤
በእልልታ ታጅቤ ወደዚች ዓለም መጣሁኝ፤
የለቅሶን ሸማ ደርቤ ዛሬን ነው የተወለድኩኝ፤
አዲስ እድሜን ለንስሐ ጨመረልኝ፤
መከራዬን አሳልፎ ለዚች እለት አደረሰኝ፤
አንዳች ፍሬ ቢታጣብኝ ምንም ምግባር ባይኖረኝም፤
ከአጠገቤ ሳይለየኝ ለሴኮንዳት አልተወኝም።
ትናትናም አልሸሸኝም ሳማርረዉ በአንደበቴ፤
ዛሬም አለ ተነሽ ብሎ እያነሳኝ ከዉድቀቴ፤
ወዳጅ ያልኩት ሰዉ ቢርቀኝ፤
ለአፍታም እንኳ ቸል አላለኝ፤
በምሕረቱ አስጠልሎ ሳይገባኝ ስላኖረኝ፤
ተመስገን ነዉ እንጂ ሌላ ምን ቃል አለኝ።
🎊🎊🎊🎊🎊🎊🎊🎊🎊🎊
🎂🎂01/02/2018🎂🎂
✍️ ዔደን ታደሰ
@ediwub
@getem
@getem
.
.
.
መስከረም ሲያከታትም አልፎ ሲተካ ጥቅምት፤
ፀደይ ብራ ሲሆን ሰማዩ በዛች መጀመሪያ ዕለት፤
በእልልታ ታጅቤ ወደዚች ዓለም መጣሁኝ፤
የለቅሶን ሸማ ደርቤ ዛሬን ነው የተወለድኩኝ፤
አዲስ እድሜን ለንስሐ ጨመረልኝ፤
መከራዬን አሳልፎ ለዚች እለት አደረሰኝ፤
አንዳች ፍሬ ቢታጣብኝ ምንም ምግባር ባይኖረኝም፤
ከአጠገቤ ሳይለየኝ ለሴኮንዳት አልተወኝም።
ትናትናም አልሸሸኝም ሳማርረዉ በአንደበቴ፤
ዛሬም አለ ተነሽ ብሎ እያነሳኝ ከዉድቀቴ፤
ወዳጅ ያልኩት ሰዉ ቢርቀኝ፤
ለአፍታም እንኳ ቸል አላለኝ፤
በምሕረቱ አስጠልሎ ሳይገባኝ ስላኖረኝ፤
ተመስገን ነዉ እንጂ ሌላ ምን ቃል አለኝ።
🎊🎊🎊🎊🎊🎊🎊🎊🎊🎊
🎂🎂01/02/2018🎂🎂
✍️ ዔደን ታደሰ
@ediwub
@getem
@getem
🎉29❤22
እኔም እንደ አዳም . . .
በገነት ገዳም
ሁሉ ተሟልቶ ፥ ኑሮ ሲመቻች
አድርጎኝ ታካች
ማለት ሲዳዳኝ "ከፀሐይ በታች..."
የዛኔ መጣች !
መጣች ...
"ንቃ" አለችኝ
ጎኔን እየወጋች ፥ ተፈታተነችኝ
ዝም አልኩኝ በግብሯ
ታገስኳት እንዴትም ፤
ለካ እንደመሳሳቅ ፥ ይጥማል ንዴትም ።
( ምቾት ብቻውን መች ያስደስታል ?
መስኩ ለምለም ነው
አፀዱ ሙሉ
ምግቡ ፥ መጠጡ በገነት ሞልቷል
ምስኪኑ አዳም ግን ትቶት ተኝቷል ።
ሳይጠፋበት ጥፋት ፥ ሳይጎበኘው ሐጥያት
ለካስ ይሰለቻል ፥ መንግስተ - ሰማያት ። )
እሷ ግን በቃ
እግዜር ያስተኛኝ በገነት አልጋ
እንዳልነቃበት ስለሚሰጋ
መሆኑን አውቃ
ህይወት ሰጠችኝ ፥ ምቾቴን ነጥቃ ።
By Habtamu Hadera
@getem
@getem
@paappii
በገነት ገዳም
ሁሉ ተሟልቶ ፥ ኑሮ ሲመቻች
አድርጎኝ ታካች
ማለት ሲዳዳኝ "ከፀሐይ በታች..."
የዛኔ መጣች !
መጣች ...
"ንቃ" አለችኝ
ጎኔን እየወጋች ፥ ተፈታተነችኝ
ዝም አልኩኝ በግብሯ
ታገስኳት እንዴትም ፤
ለካ እንደመሳሳቅ ፥ ይጥማል ንዴትም ።
( ምቾት ብቻውን መች ያስደስታል ?
መስኩ ለምለም ነው
አፀዱ ሙሉ
ምግቡ ፥ መጠጡ በገነት ሞልቷል
ምስኪኑ አዳም ግን ትቶት ተኝቷል ።
ሳይጠፋበት ጥፋት ፥ ሳይጎበኘው ሐጥያት
ለካስ ይሰለቻል ፥ መንግስተ - ሰማያት ። )
እሷ ግን በቃ
እግዜር ያስተኛኝ በገነት አልጋ
እንዳልነቃበት ስለሚሰጋ
መሆኑን አውቃ
ህይወት ሰጠችኝ ፥ ምቾቴን ነጥቃ ።
By Habtamu Hadera
@getem
@getem
@paappii
❤35🔥4
ገና ያኔ ድሮሮ
ከሩቅ ዘመን በፊት፣
አማኝ በሞላበት
ፈላስፎችም አሉ ብቻ ትንሽ ጥቂት፤
ታድያ በዛ ዘመን
መሬት ክብ ነበረች
ምጣድ ምትመስል፣
ለጥ ብላ ምትኖር
የማትዞር ማትዋልል፥
ያችኛዋ መሬት
አሁን ከነበረው በጣም ትለያለች፣
ምንም አድሎ የለም
ሁሉን ታበቅላለች፤
ታድያ እነዛ ጥቂት
የሚፈላሰፉ፣
ከንቱ ሀሰበቸውን
በሰው ውስጥ አስፋፉ፤
መሬት ክብ ሳትሆን
ሰማይ የምታክል፣
እንቁላል ነገር ነች
አሎሎ ምትመስል፤
ብለው ማይሆን ወሬ
ምድር ላይ በተኑ፣
ደበራት መሰለኝ
እንደዚ ሲሆኑ፤
አሁን በኛ ዘመን
ትንሽ መረጋጋት ያለ ከመሰላት፣
ለስሟ ነዉ መሰል
ድርቅና ቸነፈር
ጦርነት አይቀራት።
@getem
@getem
@paappii
ከሩቅ ዘመን በፊት፣
አማኝ በሞላበት
ፈላስፎችም አሉ ብቻ ትንሽ ጥቂት፤
ታድያ በዛ ዘመን
መሬት ክብ ነበረች
ምጣድ ምትመስል፣
ለጥ ብላ ምትኖር
የማትዞር ማትዋልል፥
ያችኛዋ መሬት
አሁን ከነበረው በጣም ትለያለች፣
ምንም አድሎ የለም
ሁሉን ታበቅላለች፤
ታድያ እነዛ ጥቂት
የሚፈላሰፉ፣
ከንቱ ሀሰበቸውን
በሰው ውስጥ አስፋፉ፤
መሬት ክብ ሳትሆን
ሰማይ የምታክል፣
እንቁላል ነገር ነች
አሎሎ ምትመስል፤
ብለው ማይሆን ወሬ
ምድር ላይ በተኑ፣
ደበራት መሰለኝ
እንደዚ ሲሆኑ፤
አሁን በኛ ዘመን
ትንሽ መረጋጋት ያለ ከመሰላት፣
ለስሟ ነዉ መሰል
ድርቅና ቸነፈር
ጦርነት አይቀራት።
@getem
@getem
@paappii
👍25❤14😁9🔥2
ቀኑ ሲረፍድ
ዱካክ አካሌ ላይ የሙጢኝ ሲሳፈር
ድርጊቴን አጢነው ሲመጡልኝ ከንፈር
ጥላው ሄደች ብለው እንደሳቀብኝ ሰው
ሀዘን ይሙላት ነፍስሽ ልብሽን ይውረሰው
ባፍሽ ምላስ ያነሳሽው የማልሽልኝ ጠቅሰሽ ኪዳን
መጨረሻሽ ይሁን የሄድሽበት ሁሉ እግርሽ ሄዶ አይደን
በቀል የሱ ሆኖ ምን ባለደርግ ላንቺ በቀል
ተራግሜሽ ይቁረጥልኝ
በሄድሽበት ዝግጅት ላይ ሂውማን ሄርሽ ከቶ ይነቀል
የወደደሽ ልቤን
እንደተውሽው ከመንገድ ላይ
ከወደቅሽበት ማቅ ስትነሺ እንዳላይ!
አይበቃኝም ሰርክ መስደብ
ገና ብዙ እረግማለሁ
ግን
እወድሻለሁ።
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
ዱካክ አካሌ ላይ የሙጢኝ ሲሳፈር
ድርጊቴን አጢነው ሲመጡልኝ ከንፈር
ጥላው ሄደች ብለው እንደሳቀብኝ ሰው
ሀዘን ይሙላት ነፍስሽ ልብሽን ይውረሰው
ባፍሽ ምላስ ያነሳሽው የማልሽልኝ ጠቅሰሽ ኪዳን
መጨረሻሽ ይሁን የሄድሽበት ሁሉ እግርሽ ሄዶ አይደን
በቀል የሱ ሆኖ ምን ባለደርግ ላንቺ በቀል
ተራግሜሽ ይቁረጥልኝ
በሄድሽበት ዝግጅት ላይ ሂውማን ሄርሽ ከቶ ይነቀል
የወደደሽ ልቤን
እንደተውሽው ከመንገድ ላይ
ከወደቅሽበት ማቅ ስትነሺ እንዳላይ!
አይበቃኝም ሰርክ መስደብ
ገና ብዙ እረግማለሁ
ግን
እወድሻለሁ።
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
❤7👍4