ግጥም ብቻ 📘
66.5K subscribers
1.54K photos
31 videos
61 files
175 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
ቃል ከአፋቸው ሳይወጣ
ፍቅር ተሰናብቶ መለያየት መጣ
ቻው እንኳን ሳይሉኝ
ሁሉም አገለሉኝ

እኔ ብቻ ሆነ እኔን የወደደው
እሱስ ተራው ደርሶ መች ይሆን ሚሄደው

By @Absari_seven

@getem
@getem
37🤩9🔥5
የአንተም ልብ ድንጋይ
የኔም ልብ ድንጋይ ...
(ለዚያ ነው መሰለኝ )
በተጋጨን ቁጥር በፍቅር የምንጋይ።

By meron ghetnet

@getem
@getem
@paappii
54🔥20🤩14👍7
ራሱ’ንደማይጠጣ - የውሃ ማሰሮ፣
መሆን ላልተቻለው - ክው ያለ ጉሮሮ፤
አስመሳይ ደጋጎች - ውሃ ሰጡት’ና፣
የሞት ሞቱን ሲኖር - ችግሩ እንደጠና፤
ጉሮሮ ማሰሮ - ተመሳስሎባቸው፣
ያጠጡትን ቀድተው - መውሰድ ላቃታቸው፤
ረሃብ አንጎራጉሮ - ለለመደው ውሃ፣
ሰጥቶ ተቀባዮች አስቀየመልሃ!

(የሞገሴ ልጅ)
@eyadermoges

@getem
@getem
@getem
19👍14🔥1
ላውሊያ ንጉስ ለጠቋሪት ደጋሽ
ዚያራ: ላይ ካድመሽ
ህልሜን ግራ አጋባሽ
የፅልመት እጆቼን ለኑሮሽ: ከነዳሽ
በኔ ጉሜ: ይዘሽ ተፋሽው ልብሽን
ካድመሽ: አገባሽው የልደት: ቀንሽን
ድቤው ስራ አልፈታ: ከህልሜ አለው ጋንታ
ላንቺ ኑሮ ሰቶ እኔን እሚያፋታ::
  
                                            by አለምሰገድ ወልዴ

@getem
@getem
@getem
23👍3
ዛሬ ሌላ ሰው ነኝ።

ያኔ ትንሽ ሆኜ-
በእድሜዬ ለጋ - በበሓሪ ችኩል፣
አፍንጫ አሽትቻለሁ፣
ቀድሞኝ ከበሰለው - ለመታየት እኩል።

ልጅነትን ሳልፈው-
ሌላን ማየት ትቼ - ራሴን ዐየሁ እና፣
ገደብ ሰራሁለት፣
ጉጉቴ ልክ አልፎ -ስጎድል እንዳይቀና።

ልልሽ የፈለግሁት-
አንቺ ላታስቢኝ አትበይ “ረስተኸኛል”፣
የሰርግሽን ፎቶ-
ከልቤ ሳደንቀው እራሴም ገርሞኛል።
ምክንያት፣...
ያኔ ወጣትነት - ኩራት የኮፈሰኝ፣
ትእቢት ላንዳፍታ - ወስዶ የመለሰኝ፤
እልህ እየጋተ - ምላጭ የሚያስውጠኝ፣
“ዛሬ ብቻ” ባይ ኅዝብ - አስሶ እሚመርጠኝ፤
ዛሬ...
አንቺ የኖርሽውን - ዘመን የኖርኩ እኔ፣
እራሴን ያስተማርኩ - በሕይወት ጠመኔ፤
አንቺ “ፈልጉኝ” ባይ - እኔ ራሴን መሪ፣
አንቺ ላይሽ ፋኖስ - እኔ ውስጤ በሪ፤
ከመንገድሽ እሩቅ - መንገዴ ወስዶኛል፣
ሺህ ግዜ አግብተሽ - ሺህ ግዜ ብትፈቺ ምን ያናድደኛል?

በርቺ 😐
@eyadermoges

@getem
@getem
@getem
26👍20🔥1😁1
የማመንታት ፍቅር
ልሂድ ወይስ ልቅር

(ያለበት)

ጓዝሽን ጠቅልለሽ በስንብትሽ እለት
ደግሞ ተመልሶ
ከበቃኸኝ በኃላ ካልበላሁ ማለት

(ምን ይሉታል አሁን)

ተፍተሺኝ አንቅረሽ
ጥላቻን አፍቅረሽ
ባፍንጫሽ ወጥቼ
ለፍቺያችን ድግስ የወይን ጠጅ ጠጥቼ

(ችርስ ተባብለን)

ወይ መተሽ አትመጪ ወይ ቀርተሽ አትቀሪ
ድንገት ትገኛለሽ ለፍቅር ከፊቴ ስትደነቀሪ

By @Absari_seven

@getem
@getem
32👍11🔥4
‎ቆርጦልኝ ነበረ ነግሬሽ የልቤን ወድሻለሁ ብዬ
‎የምትወጂኝ መስሎኝ ስጠብቅሽ ቀረሁ ካደርኩበት ውዬ
‎ነካክተሽ ነካክሽ ልቤን አደረግሽው የፍቅርሽ ምርኮኛ
‎የማትወጂኝ ከሆን ለምን ቀሰቀስሽው ይቅር እንደተኛ

‎አይቀርም አንድ ቀን ያፈቀረሽ ልቤ የጎኑን ማግኘቱ
‎ህይወት ይቀጥላል ምን ልቤ ቢደክም አንቺን በማጣቱ
‎አገኘሽኝ እንጂ ሆኜ ያንቺ ወዳጅ
‎ከፍቅርሽ አለም ውስጥ
‎ሳላውቀው ገብቼ እንደ ባህር ሰርጓጅ

‎ግን ...

‎ያሳሰበኝ ፍቅር
‎ካንቺ ስር ያዋለኝ እንዲህ እንደከረረ
‎ሌላ ሲያይሽ ጊዜ ቀንቼ ነበረ
‎አፈቀርኩሽ ያልኩት
‎የኔ ያልኩትን ሰው በሌላ ሲታቀፍ
‎እንዴት ብዬ ልለፍ

‎የመነጠቅ መንፈስ
‎ውስጤን እንገብግቦት አላመጣሁሽም
‎እውነቱን ስነግርሽ
‎ቀንቼ ነው እንጂ አላፈቀርኩሽም

‎አልልሽም ይህን ቃሌን ድፍረት የለኝ የምልበት
‎ያጠፋዋልና የወንድነት ልኩን ይህን ያልኩሽ እለት

‎እንደገባኝ ቢሆን ከዚህ ሁሉ ነገር
‎ቅናት መንፈስ እንጂ አልነበረም ማፍቀር



‎ ዮርዳኖስ @JorDanos7

@getem
@getem
@getem
👍3525🤩6🔥3
መተላለፍ
------------------------------

“ሰው ሀገር ነው" ቢሉኝ ሀገሬ ነህ ብዬ፣
አንተ ስር ተገኘሁ ነገሬን ጣጥዬ፡፡
ለወሬ 'ማይመች የቸገረ ነገር፣
አንተ እኔን ታቅፈህ ትመኛለህ ሀገር።

By ሜሮን ጌትነት

@getem
@getem
@paappii

''ሌላ አዉነት የለኝም'' ሚለዉን የሜሮን ጌትነት ግጥም ገዝታቹ እያነበባቹ
66😁7👍3
ምን ይሻለዋል
--------------------

ሂድልኝ ሂጂልኝ
ብለን ተለያይተን

ከማነቀው ህይወት
አንቺም እኔም ገብተን

ይሄንን ልቤን ግን
ቆይ ምን ይሻለዋል

አንቺን ሲያስብ ጊዜ
እንባ ይቀድመዋል

@getem
@getem
@paappii
60😢11🔥6
    ግጥም ነው ምትመስዪው!
  ---------------------------------------
            

ከፊደል ማሳ ላይ ቃላት ለሚቃርም
ካገኘም ከትቦ እያደር ሚያርም÷
በአርኬው መባቻ  በመድፋት አባዜ
ከሃሳብ ባህር ላይ ሰጥሞ በትካዜ÷
በብዕሩ እንባ ስንኞች ሲቋጥር
ቤቱን በመዘንጋት ቤት ለመምታት ሚጥር÷
እቴ አትሞኚ ከቁብ ለማይቆጥርሽ
በፍቅር አጊጠሽ አምሮብሽ ቢያይሽ÷
በቃላት ስደራ የተሽቀረቀረ
በታሪክ ፍሰቱ ጎልቶ የዳበረ÷
ግጥም ነው ምትመስዪው
መምቻና መድፊያው ፍፃሜው ያማረ::
                     

By @Abuugida

@getem
@getem
@getem
29👍4😁1
ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
--------------------------

አንቺ ስትስቂ
ከሰማይ ላይ ወፎች፣
እስከ ምድር ሰዎች፣
የገነት በር ደጆች፣
የቅዱሳን ፊቶች፣
አምረው ያበራሉ፤
ደስታን ያገኛሉ።

ትልቁ ጎልያድ
በሳቅሽ ተማሎ፣
ብላቴነው ዳዊት
ጠጠሮቹን ጥሎ፣
ያንቺን ሳቅ ነበረ
ተቃቅፈው ሚሰሙት፣
ፈገግታሽን ነበር
ሚያስቡት ሚያልሙት።

አንቺ ስትስቂ
ፀሃይ ከጨርቃ፣
ብርሃን ከጨለማ፣
ሰማይ ከምድር ጋ፣
ወፎች ከአረዊቶች፣
ክረምት ሳይቀር በጋ፣
አንድ አምሳል ነበሩ፣
በሳቅሽ ግዞት ውስጥ
አንድ ላይ ሚኖሩ።

ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
ጎልያድ አቅራራ
ዳዊት ላይ ደነፋ፣
አባቶች ተከፍተው
መቋሚያ አነሱ፣
እንድትስቂላቸዉ
ፆም ፀሎት ሊያደርሱ።

ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
ሰማይ አለቀሰ፣
ፀሃይ ተናደደች፣
ነፍሳትን አቃጥላ
ጨለማን ሰደደች።

እኔም ስጠባበቅ
በምኞት በተስፋ፣
ሳቅሽን ናፍቄ
ሳቅሽን ተርቤ
ግዜ ይዞኝ ጠፋ
ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
ያ ሳቅሽ ሲጠፋ


@getem
@getem
@paappii
84😁5🔥4👎1
ፍቅር አለኝ ለአንተ!
-----------------------------

አደመጥሁኝ ቅኔ መልሴ መልሼ፣
ሙዚቃውን ሰማሁ ዓለሙን አስሼ።
ዜማ ሰለለብኝ ሥዕል ደበዘዘ ግጥም አነከሰ፤
ባሳይህ... ብኖረው... የልቤ አልደረሰ።
(አንደ ምን ልግለጸው?)
ጥበብ ያሳነሰው .
ቋንቋ ያኮሰሰው .
ፍቅር አለኝ ለአንተ፣
በፍጥረት ዘመን ልክ እየተጎተተ
አስከ ዓለም ፍጻሜ ደግሞ 'ሚዘረጋ፣
ብኖርም ባንኖርም
ምጽአት የሚጠብቅ በነፍስም በሥጋ።
ፍቅር አለኝ ላንተ
ምድር የሚሞላ፣
ከእግዜር የሚያስታርቅ ከእግዜር የሚያጣላ።

By Meron Ghetnet

@getem
@getem
@getem
39
ልጅ እያለሁ –··· ጨረቃ....
(በሌሊቱ ሰማይ ደምቃ ...)
ቁልቁል ዓይኔን እያየችኝ ፤
(እያልኩ –··· “ተከተለችኝ ”)
መስሎኝ የወደደችኝ...
(ሽቅብ... ሽቅብ.... እያየኋት)
ስራመድ አቅንቼ አንገቴን ፤
መች አየሁት እንቅፋቴን ?!
(ሲነቅልብኝ አውራ ጣቴን...)
ሲጥለኝ ከመሬት ጠልፎ ፤
ሲከነብለኝ አደናቅፎ ....!
(“ወደደችኝ” ካልኩት ይብስ...)
እዛው መሬት ላይ ወድቄ ፤
(ጨረቃ ከሰማይ ወርዳ...)
እስክታነሳኝ መጠበቄ ፤
ትልቁ –··· አለማወቄ ።
💧
ያኔ ታዲያ....
“አይዞህ ልጄን !
እኔን!” እያለች ፤
አንስታኝ እያባበለች ....
(በክንዶቿ ደግፋ )
አቧራዬን አራግፋ ...
ቁስሌን በጨረቅ ያሰረች ፤
እናቴ “ግጥም” ነበረች ።
💧
“ግጥም” ነበረች እናቴ ....
(አባባይ ለልጅነቴ....)
ዘቢብ ጠብታ — ለመሪር ቀኔ
ክፍተቴን መዝጊያ —  ክዳኔ ።
(ታዲያ ያኔ.....!)
ህመሜ ሲቀሰቅሰኝ...
(ጨረቃም ስትታወሰኝ....)
“እኔን ልጄን!” — መባል ሽቼ ፤
(“አመመኝ እናቴ” እያልኳት...)
እግሮቿ ላይ — ተደፍቼ....
ሲቃዬን በጨርቅ አፍኜ
(ፊቴን በቀሚሷ ሸፍኜ)
“ስቅስቅ” ያልኩት...
(“እሪ” ያልኩት...)
ልብሷ ላይ እስካሁን አለ...
እንደ ጥልፍ አምሮ –··· ተጥሎ ፤
(ዕምባዬ —··· “አበባ”  መስሎ ።)
____

የካቲት 8 — 2016 ዓም
By @Bekalushumye


@getem
@getem
@getem
52👍5
አይ አንቺ ጨረቃ
.
.
.
ስንቱን ሰዉ ታዘብሽዉ?

ስንቱን አደመጥሽዉ?

የከፋዉ እንደሆን

ላንቺ የሚያወጋዉ

በልቡ ያለዉን

ሚስጥራቱን ሁሉ.....

የሚዘረግፈዉ

እስቲ ልጠይቅሽ?

ምን ቢያይብሽ ነዉ?

   ✍️ዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
47🎉7👎2
ምስጋና
-------------------------

ባንቺ ተማምኜ እምነቴን ጥዬብሽ
አምኜሽ ቆይቼ ቃሌን ጠብቄልሽ፣
ዛሬ ትመጣለች ግድ የለም ወይ ነገ
ፀሃዩ ፍቅራችን ስል መች ገና አደገ፣
እልፍ አላፍ አመታት ጥሎኝ እያለፈ
መንፈቅ በመንፈቅ ላይ ሄዶ እየከነፈ፣
በዋሊት ትዝታ በሀሳብ እየኖርኩኝ
ስቀመጥ ስነሳ አንቺን እያሰብኩኝ፣
ያዘዙኝን ሳደርግ ያሉኝን ስሰራ
ስንቱን አለፍኳቸው ስንቱንስ መከራ፣

ቢሆንም

እንደው ብቅ ብለሽ ካጣሽኝ ከሌለዉ
ጆሮሽን አትስጪ ቸግሮታል ለሚለዉ
የመኖሬ ተስፉ አንቺ ነበርሽና፣
ዘግይተሽ ብትመጪም ይድረስሽ ምስጋና።

@getem
@getem
@paappii
39👍9😢5🔥2
ተመስገን🙏🙏🙏
.
.
.
መስከረም ሲያከታትም አልፎ ሲተካ ጥቅምት፤
ፀደይ ብራ ሲሆን ሰማዩ በዛች መጀመሪያ ዕለት፤

በእልልታ ታጅቤ ወደዚች ዓለም መጣሁኝ፤
የለቅሶን ሸማ ደርቤ ዛሬን ነው የተወለድኩኝ፤


አዲስ እድሜን ለንስሐ ጨመረልኝ፤
መከራዬን አሳልፎ ለዚች እለት አደረሰኝ፤


አንዳች ፍሬ ቢታጣብኝ ምንም ምግባር ባይኖረኝም፤
ከአጠገቤ ሳይለየኝ ለሴኮንዳት አልተወኝም።



ትናትናም አልሸሸኝም ሳማርረዉ በአንደበቴ፤
ዛሬም አለ ተነሽ ብሎ እያነሳኝ ከዉድቀቴ፤

ወዳጅ ያልኩት ሰዉ ቢርቀኝ፤
ለአፍታም እንኳ ቸል አላለኝ፤

በምሕረቱ አስጠልሎ ሳይገባኝ ስላኖረኝ፤
ተመስገን ነዉ እንጂ ሌላ ምን ቃል አለኝ።
🎊🎊🎊🎊🎊🎊🎊🎊🎊🎊
🎂🎂01/02/2018🎂🎂
✍️ ዔደን ታደሰ
@ediwub
@getem
@getem
🎉2922
እኔም እንደ አዳም . . .
በገነት ገዳም
ሁሉ ተሟልቶ ፥ ኑሮ ሲመቻች
አድርጎኝ ታካች
ማለት ሲዳዳኝ "ከፀሐይ በታች..."
የዛኔ መጣች !

መጣች ...
"ንቃ" አለችኝ
ጎኔን እየወጋች ፥ ተፈታተነችኝ
ዝም አልኩኝ በግብሯ
ታገስኳት እንዴትም ፤
ለካ እንደመሳሳቅ ፥ ይጥማል ንዴትም ።

( ምቾት ብቻውን መች ያስደስታል ?
መስኩ ለምለም ነው
አፀዱ ሙሉ
ምግቡ ፥ መጠጡ በገነት ሞልቷል
ምስኪኑ አዳም ግን ትቶት ተኝቷል ።

ሳይጠፋበት ጥፋት ፥ ሳይጎበኘው ሐጥያት
ለካስ ይሰለቻል ፥ መንግስተ - ሰማያት ። )

እሷ ግን በቃ
እግዜር ያስተኛኝ በገነት አልጋ
እንዳልነቃበት ስለሚሰጋ
መሆኑን አውቃ
ህይወት ሰጠችኝ ፥ ምቾቴን ነጥቃ ።

By Habtamu Hadera

@getem
@getem
@paappii
35🔥4
ገና ያኔ ድሮሮ
ከሩቅ ዘመን በፊት፣
አማኝ በሞላበት
ፈላስፎችም አሉ ብቻ ትንሽ ጥቂት፤

ታድያ በዛ ዘመን
መሬት ክብ ነበረች
ምጣድ ምትመስል፣
ለጥ ብላ ምትኖር
የማትዞር ማትዋልል፥

ያችኛዋ መሬት
አሁን ከነበረው በጣም ትለያለች፣
ምንም አድሎ የለም
ሁሉን ታበቅላለች፤

ታድያ እነዛ ጥቂት
የሚፈላሰፉ፣
ከንቱ ሀሰበቸውን
በሰው ውስጥ አስፋፉ፤

መሬት ክብ ሳትሆን
ሰማይ የምታክል፣
እንቁላል ነገር ነች
አሎሎ ምትመስል፤

ብለው ማይሆን ወሬ
ምድር ላይ በተኑ፣
ደበራት መሰለኝ
እንደዚ ሲሆኑ፤

አሁን በኛ ዘመን
ትንሽ መረጋጋት ያለ ከመሰላት፣
ለስሟ ነዉ መሰል
ድርቅና ቸነፈር
ጦርነት አይቀራት።

@getem
@getem
@paappii
👍2514😁9🔥2
‎ቀኑ ሲረፍድ
‎ ዱካክ አካሌ ላይ የሙጢኝ ሲሳፈር
‎ ድርጊቴን አጢነው ሲመጡልኝ ከንፈር
‎ ጥላው ሄደች ብለው እንደሳቀብኝ ሰው
‎ሀዘን ይሙላት ነፍስሽ ልብሽን ይውረሰው

‎ ባፍሽ ምላስ ያነሳሽው የማልሽልኝ ጠቅሰሽ ኪዳን
‎ መጨረሻሽ ይሁን የሄድሽበት ሁሉ እግርሽ ሄዶ አይደን
‎ በቀል የሱ ሆኖ ምን ባለደርግ ላንቺ በቀል
‎ ተራግሜሽ ይቁረጥልኝ
‎ በሄድሽበት ዝግጅት ላይ ሂውማን ሄርሽ ከቶ ይነቀል

‎የወደደሽ ልቤን
‎እንደተውሽው ከመንገድ ላይ
‎ከወደቅሽበት ማቅ ስትነሺ እንዳላይ!

‎አይበቃኝም ሰርክ መስደብ
‎  ገና ብዙ እረግማለሁ

‎ ግን

‎ እወድሻለሁ።


‎ ዮኒ
‎     ኣታን @yonatoz

@getem
@getem
@getem
7👍4
Audio
ተጓዡ ተራማጅ ሀሳቤ ልጓሙን እስኪያገኝ……………

እድሜ ወረተኛ ገስግሶ ገስግሶ
ትምክተኛ መልኬ በሽብሽብ ተወርሶ

ርግበ እምነቴ ማረፊያዉን ሲያጣ
ጠባቂ እንደሌለዉ እንደስጥ ተስፋዬ በወፎች ሲበላ

ጠብቀኝ…………..

ባጣ ቀየኝ…………….
ዘመንህን - እድሜ መኖርህን በኔ እድሜ ለዉጠኝ።


ትዝታ ወልዴ✍️


@Tizita21
@getem
13👎3👍2🔥2