ወንድ አይደለሁ?
ታውቂም አይደል?
ወንድነቱ የሰጠኝን - ክብር ኩራት እንዴት ልጣል?
ላንድ ላንቺ ተንበርክኬ፣
ላንድ ላንቺ በመሸነፍ፣
ጠመንጃዬን ዝቅ አድርጌ ባንቺ ፍቅር - ራሴን ስፅፍ፤
ወንድነቴ ጠፍቶ አይደለም - ላንቺ ሲሆን ዝም ያለው፣
ከናት እቅፍ ሙቀት በላይ - ያንቺ መሳም ቢደላው ነው።
ግን ፀባይሽ ተለዋውጦ - እሹሩሩ እስካልዳኘው፣
ትንሽ ግዜ ቢቆይ እንጂ - ወንድነቴን እንዳሞኘው፤
ጠብ እርግፍ እያልኩልሽ ከቆጠርሽው እንደምንም፣
ረስተሽ እንጂ የማረክሽው - ሓይል ያጣ ልብ አልነበረም።
ግን ያው ተውኩት!
ዳግም ራራሁ!
አንከባክበኝ ስትይ እማ - መቼ ድሮስ አመነታሁ!
ነይ ተጠጊ ወደጎኔ - ፍርጥም ክንዴን ተንተራሽው፣
አትተወኝ ባልተለየው ሄዳለሁ ቃል - እንደልብሽ ግፊው እሺው፤
ብስጭቴን - አባሪልኝ - በከንፈርሽ ውድ መና፣
ከእጆችሽ መድሓኒቴን - አቀብይኝ ዳብሽኝ እና፤
እስትንፋስሽ እንፋሎቱ - ብርዴን ይዞት ገደል ይግባ፣
ቀለበቴን አጥልቄልሽ ዛሬም ዳግም እንጋባ!
By @eyadermoges
@getem
@getem
@getem
ታውቂም አይደል?
ወንድነቱ የሰጠኝን - ክብር ኩራት እንዴት ልጣል?
ላንድ ላንቺ ተንበርክኬ፣
ላንድ ላንቺ በመሸነፍ፣
ጠመንጃዬን ዝቅ አድርጌ ባንቺ ፍቅር - ራሴን ስፅፍ፤
ወንድነቴ ጠፍቶ አይደለም - ላንቺ ሲሆን ዝም ያለው፣
ከናት እቅፍ ሙቀት በላይ - ያንቺ መሳም ቢደላው ነው።
ግን ፀባይሽ ተለዋውጦ - እሹሩሩ እስካልዳኘው፣
ትንሽ ግዜ ቢቆይ እንጂ - ወንድነቴን እንዳሞኘው፤
ጠብ እርግፍ እያልኩልሽ ከቆጠርሽው እንደምንም፣
ረስተሽ እንጂ የማረክሽው - ሓይል ያጣ ልብ አልነበረም።
ግን ያው ተውኩት!
ዳግም ራራሁ!
አንከባክበኝ ስትይ እማ - መቼ ድሮስ አመነታሁ!
ነይ ተጠጊ ወደጎኔ - ፍርጥም ክንዴን ተንተራሽው፣
አትተወኝ ባልተለየው ሄዳለሁ ቃል - እንደልብሽ ግፊው እሺው፤
ብስጭቴን - አባሪልኝ - በከንፈርሽ ውድ መና፣
ከእጆችሽ መድሓኒቴን - አቀብይኝ ዳብሽኝ እና፤
እስትንፋስሽ እንፋሎቱ - ብርዴን ይዞት ገደል ይግባ፣
ቀለበቴን አጥልቄልሽ ዛሬም ዳግም እንጋባ!
By @eyadermoges
@getem
@getem
@getem
❤52🔥3👎2🎉2🤩2
ፍትህ ለቃላት
ቤት ለመድፋት በሚል ሰበብ አሳብቤ
እንቅልፌን ሰውቼ ቃላትን ሰብስቤ
ከቶ አልማግጥም ቃል በቃል ደርቤ፡፡
ማንስ ሆኜና ነው ቃላትን ምመርጠው
አንደኛው ከሌላው የማበላልጠው?
ላንዲት ተራ ግጥም
ወይ ሊጥም ወይ ላይጥም
የአንዱን ክብር ጥዬ ሌላ ቃል አልመርጥም!
ቃል ሁሉ እኩል ነው መነሻው ከፊደል፤
አይከብድም ወይ ታዳ ሺህ ቃላት መበደል፡፡
ያኛው አይመጥንም ቤት ያፈርሳል ደርሶ
እንዴት ሰው ፊት ይቀርባል የግጥም ህግ ጥሶ
በሚል አጉል ልማድ ብዬ ቤት ለመድፋት
በቃላት ዘር ላይ አልፈፅምም ጥፋት፡፡
By @Abuugida
@getem
@getem
@getem
ቤት ለመድፋት በሚል ሰበብ አሳብቤ
እንቅልፌን ሰውቼ ቃላትን ሰብስቤ
ከቶ አልማግጥም ቃል በቃል ደርቤ፡፡
ማንስ ሆኜና ነው ቃላትን ምመርጠው
አንደኛው ከሌላው የማበላልጠው?
ላንዲት ተራ ግጥም
ወይ ሊጥም ወይ ላይጥም
የአንዱን ክብር ጥዬ ሌላ ቃል አልመርጥም!
ቃል ሁሉ እኩል ነው መነሻው ከፊደል፤
አይከብድም ወይ ታዳ ሺህ ቃላት መበደል፡፡
ያኛው አይመጥንም ቤት ያፈርሳል ደርሶ
እንዴት ሰው ፊት ይቀርባል የግጥም ህግ ጥሶ
በሚል አጉል ልማድ ብዬ ቤት ለመድፋት
በቃላት ዘር ላይ አልፈፅምም ጥፋት፡፡
By @Abuugida
@getem
@getem
@getem
❤65👍19😁11🔥8🤩4👎3🎉3
( ፈቀቅ በል )
==========
ከቆይታህ ትዝላለህ
ከቆይታህ ይደክምሀል
ተስፋ ማጣት መጨላለም
የሀዘን እሾህ ይወጋሀል
ስትባክን እንደመሸ
ሌቱም እንዲያ .. ይነጋብሃል
ግዴለህም ' ፈቀቅ በል '
ብትሰማው ይሻልሀል !
ቸር መዳፉ .. ኋላ ደርሶ ለታመነ
ስንት ባርያ ዋስ ሲሆነው
የእረፍት ውሃ ሰላም ደስታን
ከደጃፉ ሲያዘግነው
አንተ ልጁ እስከመች ነው
በዓለም ጉያ ምትባክነው ??
(ጴጥሮስ ጓዴ)
እርሳ የቀን መከራህን
መረብህን ዳግም ጣለው
በባዶነት የሚሰራ
ቸር አምላክ ነው ፊትህ ያለው
'ፈቀቅ በል ' ጥቂት ስንዝር
ከትላንቱ ድካም ብክነት
የመከነ ተስፋህ ግቡ
በርሱ ቃል ነው ሚሰምርለት !!
By @Kiyorna
@getem
@getem
@paappii
==========
ከቆይታህ ትዝላለህ
ከቆይታህ ይደክምሀል
ተስፋ ማጣት መጨላለም
የሀዘን እሾህ ይወጋሀል
ስትባክን እንደመሸ
ሌቱም እንዲያ .. ይነጋብሃል
ግዴለህም ' ፈቀቅ በል '
ብትሰማው ይሻልሀል !
ቸር መዳፉ .. ኋላ ደርሶ ለታመነ
ስንት ባርያ ዋስ ሲሆነው
የእረፍት ውሃ ሰላም ደስታን
ከደጃፉ ሲያዘግነው
አንተ ልጁ እስከመች ነው
በዓለም ጉያ ምትባክነው ??
(ጴጥሮስ ጓዴ)
እርሳ የቀን መከራህን
መረብህን ዳግም ጣለው
በባዶነት የሚሰራ
ቸር አምላክ ነው ፊትህ ያለው
'ፈቀቅ በል ' ጥቂት ስንዝር
ከትላንቱ ድካም ብክነት
የመከነ ተስፋህ ግቡ
በርሱ ቃል ነው ሚሰምርለት !!
By @Kiyorna
@getem
@getem
@paappii
❤54👍10🔥2
"አማኝ ነን ባዬች"
ከአፍ ከክንድህ እየጠረቡ
በድንክ ህልማቸው
በዘር መትረው ሰውን ገነቡ
ከፈረሰ አምላክ
ፈጣሪ የሌለው ፍጡር ተሰራ
እንዳያምን ገፉት እንዳይሸሽህ ፈራ
°
°
እናም
. . . . .የዚህ ታሪክ ፍቺው ሲተነተን
ምድር አይገባም በዘር ለሚበተን
❛❛በብሄር ነው ቢባል
በቀለም ነው ቢባል
በሀገር ነው ቢባል ❜❜
በዘር መካፋፈል መንስኤ ምንነቱ
አንድ ላይ መሆን ነው የሰው ልዩነቱ
በሀገር ያጣመሩት በእምነት ይጣረሳል
በብሄር የገነቡት በቀለም ይፈርሳል
ልቡናው ያልቀናለት
ካፈርም ዘር መርጦ ከስጋው ይዋቀሳል
በማፍረስ አይጸናም
-------ኬላ 'ና ድንበር ስለ'ገረሰሱ
በመለያየት ነው አንድ የመሆን መልሱ
አንቺም ካለሽበት እኔም ካለሁበት
ባንድ ላይ ተጋርተን
የአንድ ዛፍ እስትንፋስ የአንድ ጸሀይ ጮራ
ገላሽም ገላዬን
ልብሽ ልቦናዬን ከሸሸ ከፈራ
ዘር በእንባ ቢወድም ሀገር ቢፈራርስ
ይቅርታ ብቻ ነው ፍቅርን የሚመልስ
በብሄር አይደለ
በቀለም አይደለ
በሀገር አይደለ የሰው ልዩነቱ
በፈረሰ እምነት ላይ ስለተገነባ
----------አይጸናም እውነቱ
አንዲት ጸሀይ ሞቀን
በአንዲት ጀንበር ደምቀን
ጦር የሚያማዝዘን
ሀገርም አይደለ ብሄርም አይደለ
ከልባችን ላይ ነው ኬላው የተሳለ!
By የአብስራ ሳሙኤል
@getem
@getem
@getem
❤41👍8🔥2🎉1🤩1
እሷን ይመስለኛል
.
.
በብሩሽ ቢቀለም የሴትነት መልኩ፤
ተለክቶ ቢሰፈር የቀሚሷ ልኩ፤
እሷን ይመስለኛል.........
በጥለቷ እራፊ እንባዋን ሸፍና፤
የልቧንን እህታ በሳቋ አፍና፤
ለደከሙት ሁሉ 'ምታበረታዋን፤
ራሷ ጀግና 'ምታጀግነዋን፤
የዘወትር አመስጋኝ ደጃፉን ናፋቂ፤
አድባር የመረቃት ጠበኛ አስታራቂ፤
ቃሏ 'ማይታበይ እዉነተኛይቱን፤
የአምላክን ወዳጅ ባለማተቢቱን።
እሷን ይመስለኛል........እ'..ሷ'..'ን
✍✍ዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
.
.
በብሩሽ ቢቀለም የሴትነት መልኩ፤
ተለክቶ ቢሰፈር የቀሚሷ ልኩ፤
እሷን ይመስለኛል.........
በጥለቷ እራፊ እንባዋን ሸፍና፤
የልቧንን እህታ በሳቋ አፍና፤
ለደከሙት ሁሉ 'ምታበረታዋን፤
ራሷ ጀግና 'ምታጀግነዋን፤
የዘወትር አመስጋኝ ደጃፉን ናፋቂ፤
አድባር የመረቃት ጠበኛ አስታራቂ፤
ቃሏ 'ማይታበይ እዉነተኛይቱን፤
የአምላክን ወዳጅ ባለማተቢቱን።
እሷን ይመስለኛል........እ'..ሷ'..'ን
✍✍ዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
❤39👍13
◈━━━━━━━━━━━━━━━◈
የብርሃን ዕድሜ
◈━━━━━━━━━━━━━━━◈
አየሽ ሊስትሮዬን
ነውሬን እንዲሸፍን በሰጠሁት ጫማ
ቁሱሉን ይጠግናል አቁስሎ እያደማ
በመኖሮ መንገድ ላይ
የጉጠቶች መብዛት ነፍሱን ሲያናጥበው
በጊዜ ፍላጻ ህይወት አያከመው
ሰውም እንደዚህ ነው ከህመም የሚጸና
የወደቁ ዕለት ነው መንገድ የሚቀና
«ማን ቀማኝ ምርኩዜን?
ማን ሰበረው ክንፌን?
መኖርን ሳትጀምር
ምንድን ነው ያታከተህ?
የውጣ ውረዱን መብዛት ተመልክተህ
ህልምህን ከበዓት ስለምን ሰወርከው?
የአይምሮህን ፈኖስ በ«አልችልም» ሰርበከው
ምርጫ ባይሆን እንኳ ማበብና መክሰም
ብርሃን ነው እድሜው የተሰራ ከሰም»።
by የአብስራ ሳሙኤል
@getem
@getem
@getem
የብርሃን ዕድሜ
◈━━━━━━━━━━━━━━━◈
አየሽ ሊስትሮዬን
ነውሬን እንዲሸፍን በሰጠሁት ጫማ
ቁሱሉን ይጠግናል አቁስሎ እያደማ
በመኖሮ መንገድ ላይ
የጉጠቶች መብዛት ነፍሱን ሲያናጥበው
በጊዜ ፍላጻ ህይወት አያከመው
ሰውም እንደዚህ ነው ከህመም የሚጸና
የወደቁ ዕለት ነው መንገድ የሚቀና
(ጫማዬን እያየ
ልቤ እንዲህ ይለኛል....)
«ማን ቀማኝ ምርኩዜን?
ማን ሰበረው ክንፌን?
መኖርን ሳትጀምር
ምንድን ነው ያታከተህ?
የውጣ ውረዱን መብዛት ተመልክተህ
ህልምህን ከበዓት ስለምን ሰወርከው?
የአይምሮህን ፈኖስ በ«አልችልም» ሰርበከው
(አየህ.....)
ምርጫ ባይሆን እንኳ ማበብና መክሰም
ብርሃን ነው እድሜው የተሰራ ከሰም»።
by የአብስራ ሳሙኤል
@getem
@getem
@getem
❤37🔥10👍3
እኔ ምን አውቄ
ፊደላት ሳታጥፊ
ቃል ሳትከለስፊ
ከሆሄያት አምባ
ሳትደክሚ ሳትለፊ
ሳትፈላሰፊ
ይደርሰኛል መልሱ
ለነብሴ ጥያቄ
አይንሽ ይመልሳል
ልብሽን ጠይቄ
እኔ ምን አውቄ።
By @poetkidus
@getem
@getem
@getem
ፊደላት ሳታጥፊ
ቃል ሳትከለስፊ
ከሆሄያት አምባ
ሳትደክሚ ሳትለፊ
ሳትፈላሰፊ
ይደርሰኛል መልሱ
ለነብሴ ጥያቄ
አይንሽ ይመልሳል
ልብሽን ጠይቄ
እኔ ምን አውቄ።
By @poetkidus
@getem
@getem
@getem
❤33👍5
( አጭሯ ፍቅሬ )
===========
አሁን በቀደም ለት
ለሐምሌ መባቻ አንድ ሳምንት ሲቀር
ያቺ የቀድሞ ፍቅሬ
ሠርክ የምትጓጓለት ልደቷ ቀን ነበር ..
እንደ ሰው ምሰጣት
ኢምንት ባይኖረኝ
በዚህ የደስታ ቀን ከምትቀየመኝ
ለክፉ ቀን ብዬ ከሸሸግኩት ቃላት
ውዱን መርጬላት
ለዘመናት ይዤው ከቆየሁት ጥበብ
ጥቂት ሰውቼላት
ማንም የማይደርሰው
ድንቅ ረጅጅጅጅጅጅጅም ግጥም
ስጦታ ጻፍኩላት !
ግና ከዚያ ወዲያ ታሪክ ተቀየረ
ፍቅሬ አኮረፈችኝ ፈገግታዋም ቀረ
ስንት ተጨንቄ የዘረፍኩት ቅኔ
ልቧን ሰባበረ ...
ወዮ !
የልቤን ጭማቂ የከንፈሬን ፍሬ
ነበር ያቀበልኳት
አረ በሚካኤል የሰማ እስቲ ይፍረደኝ
ምን እንደበደልኳት
ብዬ ወገን ዘመድ ልኬ ሳስጠይቃት
(መልሷ እኔኑ አሳቀኝ)
ግጥሜ መርዘሙ ነበር ለካ ያስከፋት
የረሳሁት ነገር ... ፍቅሬ ለካ አጭር ናት
የረዘመ ሁሉ አሽሙር የሚመስላት !!
እኒያ ከዚያ ወዲያ
እንደ ጎልማሳ ጢም ግጥም ስከረክም
አንድ ሃረግ ሳወጣ አንድ ሃሳብ ሲደክም
እንደኛው ሲጎላ አንደኛው ሲጨልም
እንደነበር ተውኩት
በእርሷም ጨከንኩባት
ምን ልታረግልኝ ሀሳብ ካማሳጠር
የሷን ቁመት ማርዘም መቅለሉ ካልገባት !!!
By @kiyorna
@getem
@getem
@getem
===========
አሁን በቀደም ለት
ለሐምሌ መባቻ አንድ ሳምንት ሲቀር
ያቺ የቀድሞ ፍቅሬ
ሠርክ የምትጓጓለት ልደቷ ቀን ነበር ..
እንደ ሰው ምሰጣት
ኢምንት ባይኖረኝ
በዚህ የደስታ ቀን ከምትቀየመኝ
ለክፉ ቀን ብዬ ከሸሸግኩት ቃላት
ውዱን መርጬላት
ለዘመናት ይዤው ከቆየሁት ጥበብ
ጥቂት ሰውቼላት
ማንም የማይደርሰው
ድንቅ ረጅጅጅጅጅጅጅም ግጥም
ስጦታ ጻፍኩላት !
ግና ከዚያ ወዲያ ታሪክ ተቀየረ
ፍቅሬ አኮረፈችኝ ፈገግታዋም ቀረ
ስንት ተጨንቄ የዘረፍኩት ቅኔ
ልቧን ሰባበረ ...
ወዮ !
የልቤን ጭማቂ የከንፈሬን ፍሬ
ነበር ያቀበልኳት
አረ በሚካኤል የሰማ እስቲ ይፍረደኝ
ምን እንደበደልኳት
ብዬ ወገን ዘመድ ልኬ ሳስጠይቃት
(መልሷ እኔኑ አሳቀኝ)
ግጥሜ መርዘሙ ነበር ለካ ያስከፋት
የረሳሁት ነገር ... ፍቅሬ ለካ አጭር ናት
የረዘመ ሁሉ አሽሙር የሚመስላት !!
እኒያ ከዚያ ወዲያ
እንደ ጎልማሳ ጢም ግጥም ስከረክም
አንድ ሃረግ ሳወጣ አንድ ሃሳብ ሲደክም
እንደኛው ሲጎላ አንደኛው ሲጨልም
እንደነበር ተውኩት
በእርሷም ጨከንኩባት
ምን ልታረግልኝ ሀሳብ ካማሳጠር
የሷን ቁመት ማርዘም መቅለሉ ካልገባት !!!
By @kiyorna
@getem
@getem
@getem
❤56😁33👍5🔥3👎1
ጉድፍ ሳይታከለው ሳይኖረው ጥላሸት
መልኩን ሳይለዋውጥ በቀንም በመሸት
ምላስ ያልበዛበት የሽንገላዎች ቃል
ልብሽን ማፍቀሬ ከአይኖቼ ያስታውቃል
ፀሃይ ከጨረቃ ከዋክብት ደመና
ሰማይና ጠፈር ጎህ አየር ቀረና
ላንቺነትሽ ቃላት ላንቺነት ምሳሌ
ረቂቅ ሆኖበት ምላሴና ቃሌ
ምንም ባደርግ ምንም
ከጥጎች እስከ ጥግ
ለንዳንቺ አይነት ቆንጆ
የለውምና ህግ
መሰየሜን ተውኩት
ቃላት አያገኙም ልብሽን ለሚያውቁት
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
መልኩን ሳይለዋውጥ በቀንም በመሸት
ምላስ ያልበዛበት የሽንገላዎች ቃል
ልብሽን ማፍቀሬ ከአይኖቼ ያስታውቃል
ፀሃይ ከጨረቃ ከዋክብት ደመና
ሰማይና ጠፈር ጎህ አየር ቀረና
ላንቺነትሽ ቃላት ላንቺነት ምሳሌ
ረቂቅ ሆኖበት ምላሴና ቃሌ
ምንም ባደርግ ምንም
ከጥጎች እስከ ጥግ
ለንዳንቺ አይነት ቆንጆ
የለውምና ህግ
መሰየሜን ተውኩት
ቃላት አያገኙም ልብሽን ለሚያውቁት
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
❤26🔥5👍3
ከ ልክ በላይ ነብስን ማጥፋት
ለማይሆኑ ልብን ማልፋት
ሰርክ ማለም ተንቀልቅሎ
ቀልብን ልብን ላንድ ጥሎ
በነሱ ዘንድ አለመዋል
በሳቅ ብቻ ለይስሙላ
ትርፉ ድካም ትርፉ ብክነት
መውደቅ ብቻ ወደኋላ
ኑሮን መሳል ካንድ ወገን
አሳብቦ አሳብዶ
ከሁለት ባንዳቸው
አንዱ ብቻ ጠልቶ
አንዱ ብቻ ወዶ።
ልክ ላልሆነ መፈላለግ
እንደገባኝ እንደገባን
ባይን ብቻ ቀርቶ
ቃላት ካላግባባን
ለይስሙላ መኖር አንድ ሆንን እያሉ
አይሰምረውምና ፍቅር ይዘት ውሉ
ልክን ለማበጀት
እቅድን አስምርን ለአንድ አመት በጀት
እንሞክር ግድ የለም
ብዙ ማፍቀር ልክ አይደለም።
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
ለማይሆኑ ልብን ማልፋት
ሰርክ ማለም ተንቀልቅሎ
ቀልብን ልብን ላንድ ጥሎ
በነሱ ዘንድ አለመዋል
በሳቅ ብቻ ለይስሙላ
ትርፉ ድካም ትርፉ ብክነት
መውደቅ ብቻ ወደኋላ
ኑሮን መሳል ካንድ ወገን
አሳብቦ አሳብዶ
ከሁለት ባንዳቸው
አንዱ ብቻ ጠልቶ
አንዱ ብቻ ወዶ።
ልክ ላልሆነ መፈላለግ
እንደገባኝ እንደገባን
ባይን ብቻ ቀርቶ
ቃላት ካላግባባን
ለይስሙላ መኖር አንድ ሆንን እያሉ
አይሰምረውምና ፍቅር ይዘት ውሉ
ልክን ለማበጀት
እቅድን አስምርን ለአንድ አመት በጀት
እንሞክር ግድ የለም
ብዙ ማፍቀር ልክ አይደለም።
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
❤30🔥4
ትተነው ላልመጣነው ልጅነት
.
መክሰስ አትሆንም ለራት አትበቃም
መርጠህ አታውቅም ፈቅደህ አትነቃም
ብዬ ላፈንኩህ ሳላመነታ
ልጅነቴ ሆይ ባክህ ይቅርታ!
ልትስቅ ስትል ላልኩህ በኩርኩም
ልራመድ ስትል
አርፈህ ተቀመጥ ላልኩህ አትቁም
በሳቅህ ግርጌ ቁጣ ፀንሼ
ትልቁን ህፃን
አዋቂ ላልኩህ ከድሜህ ቀንሼ!
ሌት ባታሸንፍ ቀን ባትረታ
አብራኝ በቀረች አንዲት ትርታ
ልጅነቴ ሆይ ባክህ ይቅርታ!
አንጠልጥዬህ ባልፍ በትዝታ ቋት
የጊዜን መንገድ
ሊጓዟት እንጂ ከቶ ላይርቋት
ትቼህ የመጣሁ ጥንት ቢሆንም
የርምጃ ያህል አልተራራቅንም።
ለተሞላበት ችኮላ ጥድፊያ
እሰጥ ይመስል ምቹ ማረፊያ
ስላመጣሁህ
ወደማይገባህ የማደግ ልፊያ
ልጅነቴ ሆይ ባክህ ይቅርታ!
By Yadel Tizazu
@getem
@getem
@paappii
.
መክሰስ አትሆንም ለራት አትበቃም
መርጠህ አታውቅም ፈቅደህ አትነቃም
ብዬ ላፈንኩህ ሳላመነታ
ልጅነቴ ሆይ ባክህ ይቅርታ!
ልትስቅ ስትል ላልኩህ በኩርኩም
ልራመድ ስትል
አርፈህ ተቀመጥ ላልኩህ አትቁም
በሳቅህ ግርጌ ቁጣ ፀንሼ
ትልቁን ህፃን
አዋቂ ላልኩህ ከድሜህ ቀንሼ!
ሌት ባታሸንፍ ቀን ባትረታ
አብራኝ በቀረች አንዲት ትርታ
ልጅነቴ ሆይ ባክህ ይቅርታ!
አንጠልጥዬህ ባልፍ በትዝታ ቋት
የጊዜን መንገድ
ሊጓዟት እንጂ ከቶ ላይርቋት
ትቼህ የመጣሁ ጥንት ቢሆንም
የርምጃ ያህል አልተራራቅንም።
ለተሞላበት ችኮላ ጥድፊያ
እሰጥ ይመስል ምቹ ማረፊያ
ስላመጣሁህ
ወደማይገባህ የማደግ ልፊያ
ልጅነቴ ሆይ ባክህ ይቅርታ!
By Yadel Tizazu
@getem
@getem
@paappii
❤43👍9😢3🔥2
ያኔ ...ትምህርት ቤት ሳለን፤
ሰዓት አሳለፉ አረፈዱ ተብለን፤
በደረቅ አርጬሜ እንገረፋለን፤
ነገር ግን በህይወት.....
ይደርሳል እያልን፤
ጥቂት ካረፈድን፤
ህይወታችን ሁሉ ይመሰቃቀላል፤
ዳግም ላይመለስ ይዘበራረቃል።
..........................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
ሰዓት አሳለፉ አረፈዱ ተብለን፤
በደረቅ አርጬሜ እንገረፋለን፤
ነገር ግን በህይወት.....
ይደርሳል እያልን፤
ጥቂት ካረፈድን፤
ህይወታችን ሁሉ ይመሰቃቀላል፤
ዳግም ላይመለስ ይዘበራረቃል።
..........................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
❤37😢5🔥3
፨፨፨ ፨፨፨
አጥቤ እንዳነፃው
በምህረት ተሰጥቶኝ
ተጨማሪ እድል፡
ጨለማ አይደለውም
ሚስተካከል ቀኔን
በእንባ የምገድል
ስህተት አትቁጠሩ
ጣታቹ የኔን ግብር
እያመለከተ፦
ምንም ልምድ የለኝም፥
መጀመሪያዬ ነው
ስኖር እንደናንተ።
@mikiyas_feyisa
@getem
@paappii
አጥቤ እንዳነፃው
በምህረት ተሰጥቶኝ
ተጨማሪ እድል፡
ጨለማ አይደለውም
ሚስተካከል ቀኔን
በእንባ የምገድል
ስህተት አትቁጠሩ
ጣታቹ የኔን ግብር
እያመለከተ፦
ምንም ልምድ የለኝም፥
መጀመሪያዬ ነው
ስኖር እንደናንተ።
@mikiyas_feyisa
@getem
@paappii
❤32👍2😱2🔥1🤩1
[የእንባ
ቅብብል]
ይታየኛል ከአድማሱ ስር ከጀንበሯ ፈቀቅ ብሎ
ድል ነው ብሎ የሚሸል የወዳጁን ስጋ ጥሎ
ለጋ ሚስኪን እናቱ የሀዘን ማቋን ለብሳ
ልጇን ትጠብቃለች የባሏን አፈር መልሳ
የአብስራ ሳሙኤል
@getem
@getem
@getem
ቅብብል]
ይታየኛል ከአድማሱ ስር ከጀንበሯ ፈቀቅ ብሎ
ድል ነው ብሎ የሚሸል የወዳጁን ስጋ ጥሎ
ለጋ ሚስኪን እናቱ የሀዘን ማቋን ለብሳ
ልጇን ትጠብቃለች የባሏን አፈር መልሳ
የእንባ ቅብብል ነው ደም እያፈሰሱ
ለቅሶ ይቀመጣሉ ከድል ሲመለሱ
የሰው ልጅ በቃሉ መቼ ፍሬ ያፈራል?
ሰይፍ እየመዘዘ ለሞት ይጠራራል?
ይብቃ! ግድ አይደለም!
ሽንፈት አይደለም!
ያቃቃረን የቂም ቁርሾ
ያዘማመተን ለበቀል
በአንዲት ጀንበር ባይካስም
ግዳይ ጠርቶ ሰውን መጣል
----ጨለማውን አይመልስም!
የአብስራ ሳሙኤል
@getem
@getem
@getem
❤29👍6