( ተረት ተረት )
============
ያኔ በጥንት ወራት ...
በጣም ሚዋደዱ ጎረቤት ነበሩ
ወይን ይመስል ግተውት በፍቅር የሰከሩ
ቤታቸው አጥር አልባ ሆኖ የሚኖሩ
በድህነት በእርቃን ማይተፉፈሩ
ለሚያያቸው ሁሉ ተስፋን የሚዘሩ
ሁለት ' አንድ ' የሆኑ .. ጎረቤት ነበሩ
ግና ከሰው ስህተት አይጠፋም እንዲሉ
ከዕለታት ባንዱ ቀን
ከአንተ ርቄ ህይወት ከአንተ ርቄ ኑሮ
ለኔ አይከብድ እያሉ
ከቤታቸው መሐል ግድግዳ ተከሉ
ከደጃቸው የእሾህ አጥር አስከለሉ
በለጋ ፍቅራቸው አጉል ቀበጡበት
ተሸነጋገሉ !!
ታዲያ ቀን ሲገፋ ናፍቆት ሲያነዳቸው
የአንዱ ህይወት ያላንዱ አልሞላ ሲላቸው
ዳግም ፍቅር ሲሹ ...
በሞኝነት ተክለው ያቆሙት ግድግዳ
መሠረቱ ጸንቶ አልፈርስም አላቸው
ብቻ በትዝታ ብቻ በወዮታ
በናፍቆት አውራጃ አለፈ ህይወታቸው !
ፍቅሬ ...
እኔና አንቺም ያኔ
እንደኒህ ምስኪናን ጎረቤቶች ነበርን
ብዙ ተጎንጭተን በፍቅር የሰከርን
ከአይን ያውጣቹ እያለ ያየ ሚመርቀን
ግና እንደማይጠፋ ከብረትም ዝገት
ከአንተ ርቄ ኑሮ ካንቺ ርቄ ህይወት
ያላንተ ሳቅ ፌሽታ ያላንቺ መደሰት
አይከብድም እያልን በትኩስ ፍቅራችን
አጉል ቀብጠንበት ..
ክፍተታችን ሰፋ ጉድለታችን በዛ
በእልህ በሞኝነት !!
ታዲያ ጊዜ ደጉ ቀጥቶ ሲያስተምረን
የኔን ጉዞ ያላንቺ .. ያንቺን ጉዞ ያለኔ
ኦናነት ሲነግረን
ምን መልሶ ማፍቀር አንድ መሆን ቢያምረን
ቀብጠን የሄድነውን የየግል ጎዳን
እስክንመለሰው .. አያ ሞት ቀደመን
ትላንት ላይ ብቻ በነበሩ ቀረን !!
By @Kiyorna
@getem
@getem
@paappii
============
ያኔ በጥንት ወራት ...
በጣም ሚዋደዱ ጎረቤት ነበሩ
ወይን ይመስል ግተውት በፍቅር የሰከሩ
ቤታቸው አጥር አልባ ሆኖ የሚኖሩ
በድህነት በእርቃን ማይተፉፈሩ
ለሚያያቸው ሁሉ ተስፋን የሚዘሩ
ሁለት ' አንድ ' የሆኑ .. ጎረቤት ነበሩ
ግና ከሰው ስህተት አይጠፋም እንዲሉ
ከዕለታት ባንዱ ቀን
ከአንተ ርቄ ህይወት ከአንተ ርቄ ኑሮ
ለኔ አይከብድ እያሉ
ከቤታቸው መሐል ግድግዳ ተከሉ
ከደጃቸው የእሾህ አጥር አስከለሉ
በለጋ ፍቅራቸው አጉል ቀበጡበት
ተሸነጋገሉ !!
ታዲያ ቀን ሲገፋ ናፍቆት ሲያነዳቸው
የአንዱ ህይወት ያላንዱ አልሞላ ሲላቸው
ዳግም ፍቅር ሲሹ ...
በሞኝነት ተክለው ያቆሙት ግድግዳ
መሠረቱ ጸንቶ አልፈርስም አላቸው
ብቻ በትዝታ ብቻ በወዮታ
በናፍቆት አውራጃ አለፈ ህይወታቸው !
ፍቅሬ ...
እኔና አንቺም ያኔ
እንደኒህ ምስኪናን ጎረቤቶች ነበርን
ብዙ ተጎንጭተን በፍቅር የሰከርን
ከአይን ያውጣቹ እያለ ያየ ሚመርቀን
ግና እንደማይጠፋ ከብረትም ዝገት
ከአንተ ርቄ ኑሮ ካንቺ ርቄ ህይወት
ያላንተ ሳቅ ፌሽታ ያላንቺ መደሰት
አይከብድም እያልን በትኩስ ፍቅራችን
አጉል ቀብጠንበት ..
ክፍተታችን ሰፋ ጉድለታችን በዛ
በእልህ በሞኝነት !!
ታዲያ ጊዜ ደጉ ቀጥቶ ሲያስተምረን
የኔን ጉዞ ያላንቺ .. ያንቺን ጉዞ ያለኔ
ኦናነት ሲነግረን
ምን መልሶ ማፍቀር አንድ መሆን ቢያምረን
ቀብጠን የሄድነውን የየግል ጎዳን
እስክንመለሰው .. አያ ሞት ቀደመን
ትላንት ላይ ብቻ በነበሩ ቀረን !!
By @Kiyorna
@getem
@getem
@paappii
❤53👍7🔥3😱3
ሚዛኑ ቢያደላ፤ ጊዜ ሆኖ ዳኛ
ቋንቋ ቀለም ሆነ፤ የሰው መመዘኛ።
ትገል እደው ግደል፤ ታድን እንደው አድን
ጠባሳ አይዝም፤ መርቅዞ የሚድን።
ብዬ ባዜምበት ....
ይፈትለው ጀመረ ቃል አጠቃቀሜን
ምንሽር አንስቼ ላላሳየው አቅሜን
ማንስ ገሎ ዳነ ማን ሞቶ ተረሳ ?
ፍጻሜው ሰይፍ ነው፤ ሰይፍ ለሚያነሳ።
***
ስለዚህ፤ ትርጉሙን
"ሀገር" ማለት ብባል?
"ሀገር" ማለት "ሰው ነው" አልልም ደፍሬ።
ሀገር የሚሆን ሰው፤ አታለች ሀገሬ።
By @YabisraSamuel
@getem
@getem
@paappii
❤54🔥16👍7
እኔ እና ገጣሚው
(Desu Fikriel)
ዛሬም ባይገባኝም - እንዴት እንዳመንኩሽ - እንዴት እንዳሳትሽኝ
"ፍቅር ይኑር እንጅ ገንዘብ ምን ያደርጋል" ብለሽ አሳመንሽኝ።
ካመንኩሽ በኋላ...
በቅጡ ሳንኖር ሳምንት ሳይሞላ
"ዋናው ገንዘቡ ነው ፍቅር አይበላ"
ብለሽ ክደሽኛል
ፍቅር ባያውረኝ - እንኳን ለኔ ቀርቶ - ለልጅ አይሳትም
የዘመን ሀቅ ነው - ፍቅር 'በድሀ ደንብ' - አይመሰረትም
ከካድሽኝ በኋላ
ሱራፌል መልአኩን - ከ'ሳት ሰይፉ ጋራ - ልቤ ዳር አቁሜ
ሴት ውስጤ ላትገባ - ዳግም ላላፈቅር - ማልኩኝ ደጋግሜ
የምልሽ ገብቶሻል?
ለነገሩ ተይው
ቢገባሽም እንኳን - ገብቶኛል አትይም - መካድ ለምዶብሻል
በርግጥ አታነቢም (ምናልባት ከሰማሽ)
አንድ ባለቅኔ
ፍቅረኛውን ቀጥሮ - ትንሽ በማርፈዷ - ብዙ የበሸቀ
ምድሩ አልበቃ ብሎት ከጨረቃዋ ጋር በእልህ ተናነቀ
ፍቅረኛውን መክራ ያስቀረች ይመስል ዓለምን ጠልቷታል
የሚቀኝላትን
የሚሳሳላትን ጨረቃዋን እንኳ 'እናቷን' ብሏታል
የምልሽ ገብቶሻል?
ለነገሩ ተይው
ቢገባሽም እንኳን - ገብቶኛል አትይም - መካድ ለምዶብሻል
ይሄን ባለቅኔ
ያረፈደችው ሴት (አንቺ እንዳደረግሽው) ከድታው ቢሆን ኖሮ
ከፈጣሪው ጋራ መሟገቱ አይቀርም ፍጡሩን ተሻግሮ
እያልኩ አስባለሁ
ህመም በወለደው አስታማሚ ቅኔ ቁስሌን አሻሻለሁ
የሚገርምሽ ነገር
ግጥም ልፅፍ ነበር
'ያማል' የሚል ርዕስ ከዚህ ሰው አንስቼ
ግን አስቢው እስኪ የእሱ ሴት አርፍዳ እኔ ተከድቼ
አንድ አይነት ስንቀኝ
ሳስበው ራሱ ብቻየን ቁጭ ብዬ እንደ ጅል አሳቀኝ
የምልሽ ገብቶሻል?
ለነገሩ ተይው
ቢገባሽም እንኳን - ገብቶኛል አትይም - መካድ ለምዶብሻል
@getem
@getem
@paappii
(Desu Fikriel)
ዛሬም ባይገባኝም - እንዴት እንዳመንኩሽ - እንዴት እንዳሳትሽኝ
"ፍቅር ይኑር እንጅ ገንዘብ ምን ያደርጋል" ብለሽ አሳመንሽኝ።
ካመንኩሽ በኋላ...
በቅጡ ሳንኖር ሳምንት ሳይሞላ
"ዋናው ገንዘቡ ነው ፍቅር አይበላ"
ብለሽ ክደሽኛል
ፍቅር ባያውረኝ - እንኳን ለኔ ቀርቶ - ለልጅ አይሳትም
የዘመን ሀቅ ነው - ፍቅር 'በድሀ ደንብ' - አይመሰረትም
ከካድሽኝ በኋላ
ሱራፌል መልአኩን - ከ'ሳት ሰይፉ ጋራ - ልቤ ዳር አቁሜ
ሴት ውስጤ ላትገባ - ዳግም ላላፈቅር - ማልኩኝ ደጋግሜ
የምልሽ ገብቶሻል?
ለነገሩ ተይው
ቢገባሽም እንኳን - ገብቶኛል አትይም - መካድ ለምዶብሻል
በርግጥ አታነቢም (ምናልባት ከሰማሽ)
አንድ ባለቅኔ
ፍቅረኛውን ቀጥሮ - ትንሽ በማርፈዷ - ብዙ የበሸቀ
ምድሩ አልበቃ ብሎት ከጨረቃዋ ጋር በእልህ ተናነቀ
ፍቅረኛውን መክራ ያስቀረች ይመስል ዓለምን ጠልቷታል
የሚቀኝላትን
የሚሳሳላትን ጨረቃዋን እንኳ 'እናቷን' ብሏታል
የምልሽ ገብቶሻል?
ለነገሩ ተይው
ቢገባሽም እንኳን - ገብቶኛል አትይም - መካድ ለምዶብሻል
ይሄን ባለቅኔ
ያረፈደችው ሴት (አንቺ እንዳደረግሽው) ከድታው ቢሆን ኖሮ
ከፈጣሪው ጋራ መሟገቱ አይቀርም ፍጡሩን ተሻግሮ
እያልኩ አስባለሁ
ህመም በወለደው አስታማሚ ቅኔ ቁስሌን አሻሻለሁ
የሚገርምሽ ነገር
ግጥም ልፅፍ ነበር
'ያማል' የሚል ርዕስ ከዚህ ሰው አንስቼ
ግን አስቢው እስኪ የእሱ ሴት አርፍዳ እኔ ተከድቼ
አንድ አይነት ስንቀኝ
ሳስበው ራሱ ብቻየን ቁጭ ብዬ እንደ ጅል አሳቀኝ
የምልሽ ገብቶሻል?
ለነገሩ ተይው
ቢገባሽም እንኳን - ገብቶኛል አትይም - መካድ ለምዶብሻል
@getem
@getem
@paappii
❤63🔥16👍6😱3
የምርቃና_ግፉ
(በረከት በላይነህ)
የሙዚቃ ሊቁ፣
ሙዚቃ ቀማሚው ዜማ እየቀመረ
ጠባቧ "ስቲዲዮ" ጫት ሞልቷት ነበረ።
ሳተናው ነጋዴ ትርፉን እያሰላ
ሊቅም ቁርሱን በላ።
ሹማምንቶቻችን ፣
ገንቢ አፍራሾቻችን ፣
ዕቅዱን ሲጽፉ ፣
በትዕዛዝ ያደገ አወደይ ቀጠፉ።
ጎረምሳው አፍቃሪሽ ጫት በዱቤ ቅሞ፣
ደብዳቤ ፃፈልሽ ከገረባ መሃል
ምርቅን ቃላት ለቅሞ።
እናስ!
መሪ ከተከታይ፣
ፍትህ ከተበዳይ፣
ጥበብ ከአድናቂው፣
መላሽ ከጠያቂው፣
የነቃ ከእውኑ
የተኛ ከሕመሙ
ውበት ከቀለሙ
እኮ በምን ስሌት? እንደምን ይስማማ?
ሰጪና ተቀባይ ፣ እኩል አልቃሙማ።
@getem
@getem
@paappii
(በረከት በላይነህ)
የሙዚቃ ሊቁ፣
ሙዚቃ ቀማሚው ዜማ እየቀመረ
ጠባቧ "ስቲዲዮ" ጫት ሞልቷት ነበረ።
ሳተናው ነጋዴ ትርፉን እያሰላ
ሊቅም ቁርሱን በላ።
ሹማምንቶቻችን ፣
ገንቢ አፍራሾቻችን ፣
ዕቅዱን ሲጽፉ ፣
በትዕዛዝ ያደገ አወደይ ቀጠፉ።
ጎረምሳው አፍቃሪሽ ጫት በዱቤ ቅሞ፣
ደብዳቤ ፃፈልሽ ከገረባ መሃል
ምርቅን ቃላት ለቅሞ።
እናስ!
መሪ ከተከታይ፣
ፍትህ ከተበዳይ፣
ጥበብ ከአድናቂው፣
መላሽ ከጠያቂው፣
የነቃ ከእውኑ
የተኛ ከሕመሙ
ውበት ከቀለሙ
እኮ በምን ስሌት? እንደምን ይስማማ?
ሰጪና ተቀባይ ፣ እኩል አልቃሙማ።
@getem
@getem
@paappii
❤36😁22🔥4👍2🤩2
አንተ ማለት እኮ......
.
.
የአይኖችህ ማማር፤
ዉስጥ የሚሰረስር፤
የጥርሶችህ ፀዳል ልብ የሚሰነጥቅ፤
ፈገግታህ ሚወደድ መንፈስን የሚሰርቅ፤
አንተ ማለት እኮ......
የሹማምንት አብራክ የመኳንንት ዘር፤
ነቅዕ ያልተገኘብህ የዉቦች ሀሉ ዳር፤
ልቡ 'ሚደነግጥ ያየ የሚመኝህ፤
በነጋ በጠባ ሁሉ የሚያልምህ፤
አንተ ማለት እኮ........
በፈራሽ ዉበትህ ሠርክ የምትመካ፤
በለበስከዉ አልባስ ሰዉን የምትለካ፤
ከራስህ ተጣልተህ ሰላምህን ያጣህ፤
መደሰት የራቀህ አንተ ማለት ይህ ነህ።
...............................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
.
.
የአይኖችህ ማማር፤
ዉስጥ የሚሰረስር፤
የጥርሶችህ ፀዳል ልብ የሚሰነጥቅ፤
ፈገግታህ ሚወደድ መንፈስን የሚሰርቅ፤
አንተ ማለት እኮ......
የሹማምንት አብራክ የመኳንንት ዘር፤
ነቅዕ ያልተገኘብህ የዉቦች ሀሉ ዳር፤
ልቡ 'ሚደነግጥ ያየ የሚመኝህ፤
በነጋ በጠባ ሁሉ የሚያልምህ፤
አንተ ማለት እኮ........
በፈራሽ ዉበትህ ሠርክ የምትመካ፤
በለበስከዉ አልባስ ሰዉን የምትለካ፤
ከራስህ ተጣልተህ ሰላምህን ያጣህ፤
መደሰት የራቀህ አንተ ማለት ይህ ነህ።
...............................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
❤30👍4🔥4
የአብስራ ሳሙኤል
ማንበብ ቢሳነን እንጂ
ቅንጣት እውነት መች ይጠፋል?
ህይወት በምድር ገጽ ላይ
ገጸ ሰቡን ማልዶ ይጽፋል.
▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔
፩
አሁን አሁን ያለፈችው
ቆንጅዬ ወጣት —
የእንባ ካፍያ፣ ያ'ረጠበው
ጉንጯ መንጣት.
ንስንስ ጸጉሯ ያዘለው
የግንጥል አበባ ገላ፣
ዝም ብላን ያለፈች
እንዲያው እንዲሁ... ዝም ብላ!
ልቡሰ ህሊናው ለመራው
ስውር እውነት እዚህ ይገኛል!
እንዲህ እንዲህ ይለኛል —
❛❛አለመንኩም ብዙ ነገር
አልማለድኩም ምቾት ድሎት፣
መገፋት ላሳሳት ነፍሴ
ለ'ልቧ ልቤን ልሰጣት፣
የልጅነት ትኩስ ህልሜን
ተይ ስላሉኝ መች ቀጨሁት?
ሰው አይደለሁ ተመኘሁት.
እንዲህ እንዲህ በቃል ቢሉት
አይገባውም ያልቀመሰ፣
ለፍቅር ጎኑን ብጠጋው
የፍትወት ፍሙን ለበሰ።
ወንድ እንዲህ ነው አልልህም፣
እሱ ግን እንዲህ ነበረ —
ወድጄ ክብሬን ብሰጠው
የማፍቀር ቅስሜን ሰበረ.
የአበባ ጉንጉን አንጥፎ
በመባው ማሳ ደፈረኝ...
ፈቅጄ ከተኛ'ሁለት;
ከእንግዲህ እውነት ምን ቀረኝ❜❜?
፪
ደሞ ከሷ፣ አሁን አሁን
ካለፈችው ወጣት እግር ስር፣
የነበረች የኔ ቢጤ
ምስኪን ለማኝ፣
ነጠላዋን ለጎዳናው ያነጠፈች፣
እንደ ጤዛ በማለዳው የረገፈች።
ምኞት ህልሟን ምስጥ
የበላው የእግሮቿን ስር፣
ልቡሰ ልቦናህን አንቃው፣
እዚህም እውነት አይጠፋም!
ክብርን በዲናር ከመቸርቸር
መለመን እንዴት አይከፋም?
እንዲህ እንዲህ ትለኛለች
❛❛ይጸድቃሉ በመስጠት፣
ውስጥ ማግኘት አለ!"
ሰው በደለኝ አልልህም፤
የጊዜ እንጂ የሰው ጌታ
ወዴት አለ?
የማውቀው ሰው፦
የሚሰጥም፣ የሚነሳም፣
የሚጥልም፣ የሚያነሳም❜❜።
፫
ደሞ ደሞ
ከሚስኪኗ የኔ ቢጤ ከአይኗ ሳያርቅ
ለጋ እድሜውን በጎዳና የሚቦርቅ፣
አፍ ሲፈታ "የዳቦ አለህ?"
የሚል ቃላት የቀመሰ፣
ለእግሩ ጠጠር ..
ለሌሊቱ ቁር ንፋስ ያንተራሰ።
አዲስ ትውልድ! አዲስ ሀገር!
አዲስ ታሪክ የሚናገር፣
❛❛በዚህ በጎዳና፦
ከሚያልፍ፣ ከሚመጣው፣
ከሚመላለሰው፣
ከመንገደኛው ሰው —
ሁሉም የግሉ ድብቅ እውነት አለው!
የሚያነጣጥለው፣
የሚያመሳሰለው።
ከመልኩ ገጽ ላይ
ተመልከት ሀዘኑን አስተውል ደስታውን፤
ቢተራመስ እንጂ
ማንም አያውቀውም
መድረሻ ቦታውን።
አልፎ፣ ሂያጅ መንገደኛ ነው
የሰው ልጅ በዚች ምድር —
ከልቦናው መቅረዝ በእኩል
ተስፋ ምኞት የሚያሳድር!
እናም እኔ፦
የማውቀው ሰው፦
**የሚሰጥም፣ የሚነሳም፣
የሚጥልም፣ የሚያነሳም❜❜።
@getem
@getem
@getem
❤31👍5
ይህ ቀዥቃዣ ዝናብ - ገላሽን ይንካና
ወዮለት ሰማዩ - ወዮለት ደመና !
ወፍ አይዘምርልሽ - ዛፍ አያስጠልልሽ
በቃ እኔ አለሁልሽ !
ደግሞ ይሄን እወቂ !
ሆዴ እንደሚበላኝ ፥ ካለኔ ስትስቂ
እንቅልፍ እንደማጣ ፥ በፀሐይ ስትፈኪ
ምራቄ እንደሚመር ፥ በእግዜር ስትመኪ !
እኔ ነኝ ጠባቂሽ !
እኔ ደስታሽ !
እኔ ፈገግታሽ !
ሁሉንም የምሆን ... !
እግዜር ፥ አላህ ፥ ሰማይ
ንፋስ ፥ ውሃ ፥ ድንጋይ
ያንቺ ብቻ አገልጋይ !
ያንቺ ብቻ ታጋይ !
"ክነፍ !" በዪኝ - ልክነፍ
"እረፍ !" በዪኝ - ልረፍ
ብቻ ደስታሽ ሁሉ ፥ በእኔ በኩል ይለፍ !!!
by Habtamu hadera
@getem
@getem
@paappii
ወዮለት ሰማዩ - ወዮለት ደመና !
ወፍ አይዘምርልሽ - ዛፍ አያስጠልልሽ
በቃ እኔ አለሁልሽ !
ደግሞ ይሄን እወቂ !
ሆዴ እንደሚበላኝ ፥ ካለኔ ስትስቂ
እንቅልፍ እንደማጣ ፥ በፀሐይ ስትፈኪ
ምራቄ እንደሚመር ፥ በእግዜር ስትመኪ !
እኔ ነኝ ጠባቂሽ !
እኔ ደስታሽ !
እኔ ፈገግታሽ !
ሁሉንም የምሆን ... !
እግዜር ፥ አላህ ፥ ሰማይ
ንፋስ ፥ ውሃ ፥ ድንጋይ
ያንቺ ብቻ አገልጋይ !
ያንቺ ብቻ ታጋይ !
"ክነፍ !" በዪኝ - ልክነፍ
"እረፍ !" በዪኝ - ልረፍ
ብቻ ደስታሽ ሁሉ ፥ በእኔ በኩል ይለፍ !!!
by Habtamu hadera
@getem
@getem
@paappii
❤52🤩9👎8👍7😁5😱5🔥4
የአብስራ ሳሙኤል
@getem
@getem
@getem
ኖሮ ማለፍ ብቻ አይደለም የህይወቴ ጥግጋቱ
በሀብት በዕቁባት አይለካም የዐላማዬ ጽናቱ
ቁና ባይሞላ ከቁብ፣ ከእፍኝ ባይቆጠር
የድርሻዬን ልጣል ጠጠር...
የድርሻዬን ላዋጣላት
ሀገሬኮ ማንም የላት!
***
እንዲህ እንዲህ፣ በዚህ በዚህ
በየጎዳናው ላይ
ደም እንደ ወራጅ ውሀ በሚገበርበት
ሀዘን እሮሮ'ችን
እንባችን በዝናብ በሚታበስበት
ሰቂቃና ሰቆቃ ባደቀቃት ሀገር
መኖር ብቻ አይበቃም
***
በዘመን ድልድይ ላይ ኦናነት ማሻገር
የድርሻዬን መንገድ ልያዝ
የድርሻዬን ፋና ልቅደድ
ቀጣይ ትውልድ ተተክቶኝ
ወደሚሻው እንዲራመድ ...
***
ስብከት መሰል አይደል?
ድሮም እውነት ይሰለቻል
ያልገነቡት ሀገር ማውረስ
ለቀብር መች ይመቻል?
ብቻ ብቻ፣ እንዲሁ ማለፍ እፈራለሁ!
"ምን ሰራህ?" ይለኛል ነፍሴ
ከጥገትሽ ጠብቶ ባይጸናም
"አለሁሽ!" ይላል መንፈሴ
"አልደላሺኝም ለኔም !
ሳር ቅጠልሽ መቼ ጣመኝ?
እንዴት ትቼ ልተውሽ?
ህመምሽ ሰርክ እያመመኝ!"
***
እማ እማ እናት አለም...
ኖሮ ማለፍ ጀብድ አይደለም!
ጀንበርን በስካር እየተደበቁ
ከየጎዳናው ላይ ቢነሱ፣ ቢወድቁ...
***
ታሪክ አያድስም፣ ዘመን አያቀናም
ወዝ ያልፈሰሰበት በምኞት አይጸናም
ጥቂት ጠጠር እናዋጣ እፍኝ መባ እንገብራት
ከእኛ ሌላ፣..ሀገሬኮ ማንም የላት!
@getem
@getem
@getem
❤16🔥1
ጥያቄ??
አሁን በእኛ ዘመን ፍቅር የምንለዉ፤
በቅዱስ መፅሐፍ ሠርክ የምናነበዉ፤
ካፋችን ማይጠፋ ቀን በቀን ምንጠራዉ፤
ፍቺዉ የጠፋብን ፍቅር ግን ምንድነዉ??
..................................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
አሁን በእኛ ዘመን ፍቅር የምንለዉ፤
በቅዱስ መፅሐፍ ሠርክ የምናነበዉ፤
ካፋችን ማይጠፋ ቀን በቀን ምንጠራዉ፤
ፍቺዉ የጠፋብን ፍቅር ግን ምንድነዉ??
..................................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
❤29👍5🔥3
መንገደኛው ልቤ ቅጽበት'ዓት ከአንቺ ያደረ
መሄድ አመል ሆኖበት ደሞ ሌላ አፈቀረ
ደሞ ከሌላ አደረ አዲስ ምዕራፍ ተጀመረ
‧˚‧༘
ቀን ያሻገረኝ ዛጎሌን ጥዬ
ሁሉም እንዳንቺ አይደለም ብዬ
ነፍሴን ላጽናናት ወይ ልደልላት
ናፍቆት ትዝታው ይበቃል ስላት
༄
ተቀበለቺኝ
❛❛ይሁና አለቺኝ❜❜
በል ሂድ እንግዲ...
⸻
#ከአዲስ መስክ ላይ
ልዬ የሆነ ብስራት አይጠፋም
ከንፎ መሰበር ሮጦ መውደቅ
ህልምን ከመስበር ፍጹም አይከፋም
✨
ደሞ ወደ አዲስ ጠረን
ደሞ ወደ አዲስ ገላ
ይሁን ብላ ህይወት ስታባብለኝ
⸻•⸻
ይኀው ደሞ ትዝ አለኝ
ተሳሰረብኝ እግሬ
በአንቺም ጊዜ አኮብኩቧል
ክንፎቹን ልክ እንደ ዛሬ
💧
ትዝ አለሽ ያኔ?
በሀዘን በእንባ የተማጸንኩሽ
የበደሌ ስር ቅሉ ሳይገባኝ
ይቅርታ ያልኩሽ
🕯
ገፍተሽ መሄድሽ
ብቻዬን ስሆን ዛሬም ያመኛል
አንዴ የቆሰለ ማደሪያስ
ቢያገኝ መች አምኖ ይተኛል?
✨
ግና ፍቅሬ...
ቢሆንም ባይሆንም
ክንፋም ህልሞች እንጂ
ጨለማ አልለምንም
ትሏ ህይወቴ
በጀንበር ብስራት ክንፍ ያበቀለ
☾
ሁሉም እንዳንቺ አይደለም ያለ
ደሞ ሌላ አፈቀረ
አዲስ ምዕራፍ ተጀመረ
𓇢
አንድ አይኑን ለመንገድ ገልጦ
ከሌላ ልቡ ውስጥ አደረ...
የአብስራ ሳሙኤል
@getem
@getem
@getem
መሄድ አመል ሆኖበት ደሞ ሌላ አፈቀረ
ደሞ ከሌላ አደረ አዲስ ምዕራፍ ተጀመረ
‧˚‧༘
ቀን ያሻገረኝ ዛጎሌን ጥዬ
ሁሉም እንዳንቺ አይደለም ብዬ
ነፍሴን ላጽናናት ወይ ልደልላት
ናፍቆት ትዝታው ይበቃል ስላት
༄
ተቀበለቺኝ
❛❛ይሁና አለቺኝ❜❜
በል ሂድ እንግዲ...
⸻
#ከአዲስ መስክ ላይ
ልዬ የሆነ ብስራት አይጠፋም
ከንፎ መሰበር ሮጦ መውደቅ
ህልምን ከመስበር ፍጹም አይከፋም
✨
ደሞ ወደ አዲስ ጠረን
ደሞ ወደ አዲስ ገላ
ይሁን ብላ ህይወት ስታባብለኝ
⸻•⸻
ይኀው ደሞ ትዝ አለኝ
ተሳሰረብኝ እግሬ
በአንቺም ጊዜ አኮብኩቧል
ክንፎቹን ልክ እንደ ዛሬ
💧
ትዝ አለሽ ያኔ?
በሀዘን በእንባ የተማጸንኩሽ
የበደሌ ስር ቅሉ ሳይገባኝ
ይቅርታ ያልኩሽ
🕯
ገፍተሽ መሄድሽ
ብቻዬን ስሆን ዛሬም ያመኛል
አንዴ የቆሰለ ማደሪያስ
ቢያገኝ መች አምኖ ይተኛል?
✨
ግና ፍቅሬ...
ቢሆንም ባይሆንም
ክንፋም ህልሞች እንጂ
ጨለማ አልለምንም
ትሏ ህይወቴ
በጀንበር ብስራት ክንፍ ያበቀለ
☾
ሁሉም እንዳንቺ አይደለም ያለ
ደሞ ሌላ አፈቀረ
አዲስ ምዕራፍ ተጀመረ
𓇢
አንድ አይኑን ለመንገድ ገልጦ
ከሌላ ልቡ ውስጥ አደረ...
የአብስራ ሳሙኤል
@getem
@getem
@getem
❤12👍11😱1
(በዕምዓዕላፍ)
ወደ ውስጥ ፈሶ
ወደ ውስጥ አልቅሶ
መሬት ሳትረሰርስ
እምባውን ጨርሶ
ይሆናል እያልኩኝ በመላምት ተስፋ
ምኞት ላያፀናኝ ነፍሴ ተቀስፋ
የልቤ መናወዝ
የኔ መንጠራወዝ
ስለ አንቺ ነበረ
ፍቅርሽ መስቀል ሆኖ የተቸነከረ
በጠባብ ማነቆ ቀንበር ተሸክሜ
የፍቅርን መቀነት በተስፋ አገልድሜ
ከእድሜ
ቀድሜ
እንሆ አሰስኩሽ.......
ለዘመናት ባጀሁ
አመታትን ፈጀሁ
አንጋጥጬ እያዬሁ የማይወርድ መና
ሰማዩን ከልሎት የማይዘንብ ደመና
እያዬሁ ሳላምን
እግዜርን ስለምን
እኔ ወበከንቱ
የትም ቀረሁ እቱ
@getem
@getem
@getem
ወደ ውስጥ ፈሶ
ወደ ውስጥ አልቅሶ
መሬት ሳትረሰርስ
እምባውን ጨርሶ
ይሆናል እያልኩኝ በመላምት ተስፋ
ምኞት ላያፀናኝ ነፍሴ ተቀስፋ
የልቤ መናወዝ
የኔ መንጠራወዝ
ስለ አንቺ ነበረ
ፍቅርሽ መስቀል ሆኖ የተቸነከረ
በጠባብ ማነቆ ቀንበር ተሸክሜ
የፍቅርን መቀነት በተስፋ አገልድሜ
ከእድሜ
ቀድሜ
እንሆ አሰስኩሽ.......
ለዘመናት ባጀሁ
አመታትን ፈጀሁ
አንጋጥጬ እያዬሁ የማይወርድ መና
ሰማዩን ከልሎት የማይዘንብ ደመና
እያዬሁ ሳላምን
እግዜርን ስለምን
እኔ ወበከንቱ
የትም ቀረሁ እቱ
@getem
@getem
@getem
👍12❤7😢2🔥1