አትሮኖስ
279K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
457 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#በኔ_የደረሰ


#ክፍል_አንድ


#በጥላሁን

የኔም የጓደኛዬም ፍቅረኞች ሁለቱም ሀብታም የሚለው ምን አይነት ሀብታም? የሚለን ጥያቄ የማያብራራ ጥቅል መጠሪያ ከማይገልፃቸው ከበቃቸው ሀብታም ቤተሰቦች የተወለዱ ናቸው።
የኔና የጋደኛዬ ቤተሰቦች ለመኖር የማይቸገሩ መካከለኛ የኑሮ ደረጃ በመባል የሚጠራውን አይነት ኑሮ የሚኖሩ ናቸው ። የኔ ፍቅር ሊሊ ስትባል የጋደኛዬ ፍቅረኛ ኪሪያ ትባላለች ትርጉሙስ ካላችሁ እኔን ሳይሆን እራሷን ጠይቋት ።

ገና በአዳማ ዩኒቨርስቲ የአንደኛ አመት የአካውንቲንግ ተማሪ ነኝ ፍቅር የጀመርኩት አስረኛ ክፍል ሆኜ ነው ታድያ ለፍቅር ምን አጣደፈህ አትበሉኝ የደረሰበት እንኳን እንደማይለኝ አውቃለሁ ያልደረሰባችሁ ካላችሁ
" አርፎ ትምህርቱን አይማርም ለፍቅሩ ይደርስበታል!" ምናምን እያለችሁ ብትሞልጩኝም እችለዋለሁ።

መጀመሪያ በጥፊ ተመቶ ቀጥሎ በኮብል የተፈነከተ ሰው የመጀመሪያውን ጥፊ ወድያው ረሳው ቢሉት ባይረሳው ገረመውን ይገርመው ነበር አለ ገረመው

የራሴ አባባል ነች ስለዚህ አሁን በተቆለለብኝ ዱብዳ የተነሳ ጭንቅላቴ ስድብም ብጨቃም ዝልዘላም አይሰማውም አቅማችሁ የቻለውን ያህል ተሳደቡ አጋጣሚውን ተጠቀሙበት።

እናላችሁ ••• ከዚቹ ከኔ ፍቅር ከሊሊ ጋር ፍቅር የጀመርነው ከሁለት አመት በፊት አስረኛ ክፍል እያለሁ ነው ። አንድ ክፍል ነበርን ቀድሜ የወደድኳት እኔ ነበርኩ እንደወደድኳት ግን ነግሪያት አላውቅም እንኳን ለሷ ልነግራት እኔ እራሴ የያዘኝ ፍቅር መሆኑን መች ቶሎ ገባኝና ብቻ እኔ የማውቀው
ስተኛ ትዝ እንደምትለኝ ።
ስበላ እንደማስታውሳት።
ሴት ልጅ ከሩቁ ባየሁ ቁጥር እሷ እንደምትመስለኝ።
ሳትጠራኝ የጠራችኝ እየመሰለኝ ብንን እንደምል።
ጥዋት ገብቼ ለመማር ሳይሆን እሷን ለማየት ከክፍሉ ተማሪ በሙሉ ቀድሜ እንደምገኝ።
ሌሎች ወንዶች ሲያናግራት የሆነ የሚያቃጥል ነገር እንደሚሰማኝ በለው በለው ንከሰው ቦጭቀው እንደሚለኝ።
አጠገቤ ስትቀመጥ ላብ እንደሚያሰምጠኝ ።
ስታወራኝ ምላሴ ወደውስጥ ገብቶ እማወራው ነገር እንደሚጠፋብኝ ።
ቅዳሜና እሁድ የሚባል ነገር እንደሚያስጠላኝ ።
ሰኞ እንደምፅአት ቀን እንደምትርቅብኝ ብቻ ነበር።
ለእንደኔ አይነቱ ጭምት እንኳን ፍቅር ሊጀምር የፍቅር ፊልም እንዲያይ አባቱ የማይፈቅድለት
ከደብተሩና ከቤተሰቦቹ ውጪ ከሌላው አለም ጋር ሳይተዋወቅ ያደገ ልጅ ከላይ የታዩበት ምልክቶች የፍቅር ምልክት መሆናቸውን መለየት ከባድ ነበር አይ ፍቅር ዶክተር አልባ ህመም ።
እናማ በአንድ አጋጣሚ የቤተሰብ ፕሮግራም ላይ ለአንድ የአክስቴ ልጅ የፍቅር ህመም ምልክቶቼን አውራሁለት
በቃ ሳያት ደስ ይለኛል ተለይቻት ፊቷ ከፊቴ ላይ አይጠፋም ለምን እንደሆነ እኔ እንጃ ከሌላ ወንድ ጋር ስታወራ እናደዳለሁ ስለው
ረጅም ሳቅ ሳቀብኝ በትግስት ጠበኩት የትግስቴን ፍሬ ነገረኝ ። "ፍቅር ይዞሀል ሶልዬ " አለኝ። ብትችል ትምህርትህን እስክትጨርስ እንደዚህ አይነት ነገር ውስጥ ባትገባ ይሻል ነበር
አሁን ግን ከነገርከኝ አንፃር ላትመለስ ተዘፍቀህበታል እና ንገራት" የሚለውን አስከትሎ ተለየኝ ። ንገራት! ንገራት! ንገራት! የሚለው ቃሉ ጭንቃላቴ ላይ ሲያቃጭልብኝ አምሽቶ አነጋ ። እነግራታለሁ ወሰንኩ ሰኞ ለሊት አስራ አንድ ሰአት ተነስቼ ገላዬን ታጠብኩ ። ጥዋት ሶስት ፔሬድ ሙሉ የተማርኩትም የፃፍኩትም ትዝ አይለኝም ።
ምን እንደምላት ስፅፍ ስለማመድ ቆየሁ•••

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
1
#በኔ_የደረሰ


#ክፍል_ሁለት


#በጥላሁን

ንገራት ንገራት ንገራት የሚለው ቃሉ ጭንቃላቴ ላይ ሲያቃጭልብኝ አምሽቶ. አነጋ ። እነግራታለሁ ወሰንኩ ሰኛ ለሊት አስራ አንድ ሰአት ተነስቼ ገላዬን ታጠብኩ
ጥዋት ሶስት ፔሬድ ሙሉ የተማርኩትም የፃፍኩትም ትዝ አይለኝም ።
ምን እንደምላት ስፅፍ ስለማመድ ቆየሁ•••
ምን ብዬ እንደምጀምር ምን ብዬ እንደምቀጥል እና ምን ብዬ እንደምደመድም የትኛው ሀሳብ መቅደም የትኛው መከተል እንዳለበት መግቢያ ማጠናከሪያ መደምደሚያ ብዬ ከፋፍዬ ላስቀምጥ ብሞክርም ውስጤ ያለውን የፍቅር ንዳድ በደንብ ሊገልፁላት የሚችሉ ቃላቶች ማግኘት ፈተና ሆነብኝ።

መግቢያ:- ሊሊዬ ለብቻሽ ላናግርሽ የፈለኩት አንድ ጉዳይ ነበረኝ ለዛ ነው ለብቻሽን ላናግርሽ የፈለኩት....
ወይ ጣጣ እሄ ደሞ የፍቅር ጥያቄ ሳይሆን ብድር የሚጠይቅ ሰው የሚጠቀምበት የመግቢያ ንግግር ይመስላ አቦ አልኩና እላዩ ላይ ትልቅ የኤክስ ምልክት አጋድሜ ግድግዳውን ተደግፌ ከክፍሉ ሴት ተማሪዎች በሙሉ እንኳን የትምህርትቤቱን ይንፎርም የተቀዳደደ ጆንያ ለብሳ ብትመጣ ውበቷ የማይጎድልብኝን የለበሰችው የሳቀችው የተናገረችው ሁሉ ልዩ እና ውብ መስሎ የሚታየኝን እኔ ከተቀመጥኩበት በስተግራ እክፍሉ መሀል ላይ ከሁለት ሴት ጓደኛቿ መሀል ላይ ያለችውን ሊሊዬን ከጀርባ እያየሁ የምላትን ማሰብ ጀመርኩ።

የመጣልኝን ሁለተኛውን ሀሳብ መፃፍ ጀመርኩ•••
ፅሁፉ እየመራኝ ይሁን እኔ እየመራሁት ባይገባኝም ፊደሎቹ እየተፈላለጉ መመሳሰል ጀመሩ ። ሳላስበው እንደመግጠምም አደረገኝ•••
ምን መሰለሽ ? እሄውልሽ ሊሊዬ
እኔ ባንቺ ፍቅር ሁሉን ነገር ጥዬ
ሳይሽ ደስ ይለኛል
ካጠገብሽ ስርቅ ጭንቀት ይወረኛል
ሲለው ፍርሀት ፍርሀት ብርድ ብርድ ይለኛል
በቤተሰብ መሀል እቤቴ ቁጭ ብዬ
ብቻዬን የሆንኩኝ ያህል ይሰማኛል
ሳቅሽ ይርበኛል
አንቺ ሳትኖሪ ድምፅሽ ይጠራኛል
በውድቅት ለሊት ሰው ሁሉ ተኝቶ
እኔ አስብሻለሁ
አንቺ ሳትመጪ ኮቴሽ ይሰማኛል
የቱንስ ልንገርሽ የቱኛውን ትቼ
በፍቅርሽ ሳስቼ እራሴን ረስቼ
ምግብ መብላት ትቼ
መኖር እንደጀመርኩ እኔን ላንቺ ትቼ
ስትስቂ ካየሁ ባንቺ ደስታ ስስቅ
የከፋሽ ሲመስለኝ ሲልብኝ ድብልቅልቅ
በጣም የሚገርመው ይህ ሁሉ በኔ ላይ ሲሆን የነበረው በፍቅርሽ መያዜን ከቶም ሳልረዳው ጭራሽ ሳይገባኝ ነው
እናም የኔ ፍቅር
ፍቃድሽ ከሆነ ወድሻለሁና
ያንቺ ልሁንና ላንቺው ፍቅር ልኑር።

አሁን ይሄን ባነብላት ከዚህ በፊት ሁለት ስንኝ ያላት ግጥም ስፅፍ አይታኝ አታውቅ ላንቺ የውስጤን ይገልፅልኛል ብዬ የፃፍኩት ግጥም ነው ብላት ያንን ደስ የሚል ሳቋን ስቃ። አይ ሶልዬ በዳዲ ሞት ሙድ መያዝህን ተውና ግጥሙን ወድጄዋለሁ ይልቅ ኬትኛው መፅሀፍ ላይ ነው ያገኘከው ብትለኝ ምን ይውጠኛል ከዛ ቡሀላ ቁምነገር ነው ብላትም አላግጣብኝ ነው እምትሄደው ይቅርብኝ።

ባይሆን እሄን ግጥም ምናልባት ከሊሊ በላይ ማፍቀሬን ባልነግረውም የሚረዳኝ እና ውስጤን የሚያውቀው የፍቅር አምላክ አሳክቶልኝ እሺ ብላኝ አብራኝ ከሆነች ቡሀላ ባነብላት ይሻላል ።
ይሄም ተሰረዘ ። ግጥሙን የፃፍኩባትን ወረቀት በጥንቃቄ አጣጥፌ ኪሴ ውስጥ ከተትኩና ሌላ ባዶ ወረቀት ፊቴ አስቀመጥኩ።

ይልቅ እንድታምነኝ ንግግሬን በሀይለ ቃል አጅቤ ማዥጎድጎድ እንዳለብኝ ውስጤ ሹክ አለኝ።
በቃ በፍቅርሽ ጨርቄን ጥዬ ማበዴ ነው አልቻልኩም እኔስ አፍቅሬሽ ልበድ ላንቺ ማበዴ አይበዛብሽም ግን ደግሞ የኔ ማበድ ለቤቴሰቦቼ ከባድ ነው የማይቋቋሙት ትልቅ ሀዘን ውስጥ እንደሚገቡ አውቃለሁ ያንን ሳስበው ደሞ እንደዛ የሚንሰፈሰፉልኝ ቤተሰቦቼ በኔ ምክንያት ተጎድተው ከማይ ሞቴን እመርጣለሁ ። እውነቴን ነው ሊሊዬ እኔ አብጄ ሁሌ እያዩኝ የስቃይ ሂወት ከሚገፉ ዛሬውኑ ብሞት ይሻለኛል።
እሄን የፍቅር ጥያቄ ሳይሆን ከፊሉ ዛቻ ከፊሉ ኑዛዜ የመሰለ ፅሁፍ ወረቀት ላይ አስፍሬ የራሴ ሀሳብ ሳይሆን ሰው ፅፎ የሰጠኝ ይመስል መልሼ ሳነበው ተናደድኩ። ወረቀቱን በጫጭቄ ጣልኩት።

ሁለተኛው የትምህርት ክፍለ ግዜ ተጠናቆ ሶስተኛው ተጋመሰ።ሲደወል እረፍት ነው። ሊሊን አዋራታለሁ። እስካሁን ግን ምን እንደምላት አልወሰንኩም ።
ደቂቃዎቹ እያለቁ በሄዱ ቁጥር ንዴቴ እየጨመረ መጣ። የእረፍት ሰአት ሲደወል ።መፃፉን አቃረጥኩና ብእሩን ዴክሱ ላይ አስቀምጬ እጄን አጣጥፌ ከራሴ ጋር ማውራት ጀመርኩ•••
ቆይ ግን ፍቅር እኔን የያዘኝ አለማምዶ ነው እንዴ? ፍቅር ማለት ምን ማለት እንደሆነና እንዴት እንደሚያደርግ እንደማላውቅ እያወቀ አደል እንዴ ዘሎ የተከመረብኝ ታድያ ምን እንደምል እንዴት እንደማስረዳት እንዴት እንደማሳምናት እያሰብኩ ምን አጨናነቀኝ።

ልክ ሳገኛት ለስንት ወራት ውስጤ ተቀምጦ የነበረው ፍቅር እራሱን ይግለጥላት።
ሰው ምን ብዬ ባስረዳት ታምነኛለች እያለ መጨነቅ ያለበት ፍቅሩ የውሸት ከሆነ ብቻ ነው። እኔ እሷን ማፍቀሬ ግን እውነት ነው። እውነት ደሞ እራሱን የሚገልጥበት መንገድ አያጣም። የቃላት ቀመር የንግግር ልምምድ አያስፈልገውም። ምክንያቱም ምን ልበል ብዬ አላስብም የምለው ነገር በሙሉ የሆንኩትን ነው።
የሆነውን ነገር መናገር ቢያቅተኝ እንኳን እሷ ፊት ቆሜ የልቤን ህመም መግለጥ አለመቻሌ በራሱ ፍቅር ነው አልኩና።
ያሰብኩትን ደግሜ ሳስበው ይገርማል ፍቅር ፈላስፋም፣ ዘፋኝም፣ ገጣሚም፣ እብድም፣ ፀሀፊም፣ አልቃሽ ደስተኛም ተካዥም፣ ብቸኛም ያረጋል ሲባል አይገባኝም ነበር ዛሬ ግን ያሰብኩት ምን ማለት እንደሆነ ለራሴም ግራ እስኪገባኝ ፈላስፋ አድርጎኝ አረፈው።
ግን ይሄ መፈላሰፍ ነው እንዴ መፈላሰፍ እራሱ ምን ማለት ነው! ወጣም ወረደም ፍቅር የያዘው ሰው ሁለመናው ማፍቀሩን ስለሚናገር ምን ልናገር ብዬ ባልጨነቅስ!
የእረፍት ሰአት ተደወለና ተያይዘን ትምሽ እንደሄድን
"ለምን ነበር እረፍት ሰአት ልታናግሪኝ የፈለከው ሶልዬ?" ስትለኝ ደንግጬ አይን አይኗን ከማየት በስተቀር ሌላው እንኳን ቢቀር ወዬ ሊሊዬ የምትለውን ቃል ለመናገር ብሞክር
ኔትወርኩ እንደጠፋ ስልክ ምላሴ ላይ እየተሽከረከረች አልወርድ አለችኝ።
የስልክ ኔትወርክስ ቦታ በመቀያየር ይፈለግ ይሆናል የኔን ኔትወርክ ምኑን ቀያይሬ ላምጣው!
ቸርነቱ ብዙ አንደበቱን ሰጥቶኝ
ፍቅሬን እንዳልገልጠው ፍቅርሽ ዲዳ አረገኝ
እባክሽን ማሬ ያንደበቴን ትተሽ
ውስጤን ተረጅልኝ አይኔን ተመልክተሽ!!
ብለው ዘፍነው ይሆን እንዴ ዘፋኛቹ ?
አይመስለኝም •••

💫የቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍1🔥1
#በኔ_የደረሰ


#ክፍል_ሦስት


#በጥላሁን

...እሄ መፈላሰፍ ነው እንዴ መፈላሰፍ እራሱ ምን ማለት ነው! ወጣም ወረደም ፍቅር የያዘው ሰው ሁለመናው ማፍቀሩን ስለሚናገር ምን ልናገር ብዬ ባልጨነቅስ!
የእረፍት ሰአት ተደወለና ተያይዘን ትንሽ እንደሄድን
"ለምን ነበር እረፍት ሰአት ልታናግሪኝ የፈለከው ሶልዬ?" ስትለኝ ደንግጬ አይን አይኗን ከማየት በስተቀር ሌላው እንኳን ቢቀር ወዬ ሊሊዬ የምትለውን ቃል ለመናገር ብሞክር ኔትወርኩ እንደጠፋ ስልክ ምላሴ ላይ እየተሽከረከረች አልወርድ አለችኝ።
የስልክ ኔትወርክስ ቦታ በመቀያየር ይፈለግ ይሆናል የኔን ኔትወርክ ምኑን ቀያይሬ ላምጣው!
ቸርነቱ ብዙ አንደበቱን ሰጥቶኝ
ፍቅሬን እንዳልገልጠው ፍቅርሽ ዲዳ አረገኝ እባክሽን ማሬ ያንደበቴን ትተሽ
ውስጤን ተረጅልኝ አይኔን ተመልክተሽ!!
ብለው ዘፍነው ይሆን እንዴ ዘፋኛቹ ?
አይመስለኝም •••
መጨነቄን በማስተዋል ስታይ የነበረችው ሊሊ
"ሶልዬ አትጨነቅ በቃ እንደምትወደኝ እንኳን እኔ ጓደኛቼም ያውቃሉ!
ታፈቅረኛለህ አደል?
እሱን ልትነግረኝ ፈልገህ ነው አደል እንዲህ ፈንጅ እንደረገጠ ሰው በቆምክበት ደርቀህ ምላስህም ሰውነትህም አልንቀሳቀስ ያለው ?ስትለኝ ጆሮዬን ማመን ተሳነኝ ።
ንግግሯ ምላሴ የታሰረበትን ገመድ በጣጠሰው መሰለኝ
" ሊሊዬ አዎ አፈቅርሻለሁ ግን እንደማፈቅርሽ በምን አውቅሽ ?
ጓደኛችሽ እንዴት አወቁ ? ስላት ሳቋን ለቀቅችው
"አንተስ እንዳፈቀርከኝ በምን አወክ? ብላ ግራ የገባው ጥያቄ በመጠየቅ ግራ አጋባችኝ ቢሆንም ምላሴ ተፈቷልና ለመመለስ አልቦዘንኩም•••
እኔማ እንዴት አላውቅም ሊሊዬ
ለሰከንድ ስላንቺና አንቺን ከማሰብ ተዘናግቼ አላውቅም ።
የሚዘፈነው የፍቅር ዘፈን በሙሉ ላንቺ የተዘፈነ ይመስለኛል ።
በፍቅሯ የሆንኩትን በሙሉ ለመዘርዘር ሲዳዳኝ •••
አንገቴ ላይ ድንገት ተጠምጥማ " እኔም እወድሀለሁኮ ሶልዬ!" ስትለኝ ከደረቴ በታች የሆነ ብቻ ለመግለፅም የሚከብድ እስከዛሬ ተሰምቶኝ የማያውቅ ስሜት ተሰማኝ።
ምን አልሽኝ ሊሊዬ አልኩ እንድትደግምልኝ ፈልጌ ዝም አለች። ደግሜ ለመስማት ፈልጌ በዝምታ ጠብኳት ። ደገመችው ።ደጋገመችው። አብረን ሆንን።
እኔ ከሊሊ ጋር በፍቅር ብን ማለቴ ጨርሶ ያልተዋጠለትና ያልተመቸው ሰው ቢኖር ጓደኛዬ ነው
እሄ ጓደኛዬ ኪሩቤል ይባላል ከወንድ ጓደኛቼ በጣም የምወደውና እንደወንድሜ የማየው ከልጅነት ጀምሮ ለብዙ አመታት ተለይቼው የማላውቅ ጓደኛዬ ነው
ታድያ እንደጓደኛ የማፈቅራት ልጅ እሺ ስላለችኝ እና አብራኝ ስለሆነች መደሰት ሲገባው ወረደብኝ ወረደብኝ አይገልፀውም በተግፃፅ እና በምፀት ደበደበኝ ብል ይቀለኛል
"አንተ ግን ምንድን ነው ወንድ አደለህ እንዴ ቆፍጠን በል እንጂ ምን ያዝረከርክሀል ኧረ በናትህ ለሴት ልጅ እሄን ያህል መሸነፍ መዋረድ ነው ለኔ ፍቅር ምናምን ትላለህ እንዴ ፍቅር አንተ ካልደረስክበት አይደርስብህም አንተ ፊት ካልሰጠከው ድርሽ አይልም ለሴት ልጅ የሚያለቅስ ጓደኛ ስላለኝ በጣም ነው ያፈርህምኩት ጓደኛቿ ሁሉ እኮ በፍቅሯ እግሯ ስር እንደጣለችህ ነው የሚያወሩት ኧረ እኔ ለሴት መቼም ቢሆን እንዳንተ ከምሆን ብሞት ይሻለኛል!"
አለኝ ይህን ፀባዩን እና አመለካከቱን በሌሎች ጓደኛቻችን ላይም ሲያንፀባርቀው ስላየሁ በውስጤ "ደርሶብህ እየው ያኔ ብናወራ ይሻላል ፍቅርን የሚያውቀው ያጣጣመው አልያም አልያም አናቱ ላይ ወጥቶ ያብከነከነው ብቻ ነው" እያልኩ ካጠገቡ ከመሄድ በቀር መልስ አልሰጠሁትም።
እንደው ሰው አማህ አትበሉኝና ጓደኛዬ ከምጣላበት የምወድለት ባህሪው በልጦብኝ ዘለቅን እንጂ የሚያናድድ ጢባር አለበት።
ደፋር ነኝ አደል ሰው አማህ አትበሉኝና ማለቴ ?
ቆይ እንዲህ በሀሜት አንስቼ እያፈረጥኩት
ሰው አማህ ካላላችሁኝ ምን ልትሉኝ ነው ?
ምን ላርግ ሲሉ ሰምቼ ነው።
ሲሉ ሰምቼ ያልኩትም ሲሉ ሰምተው ሲሉ ሰምቼ ነው።
አንዳንድ ሰዎች አንድን ሰው በሀሜት ስጋውን ቦጫጭቀው ባጥንቱ ሊያስቀሩት መንደርደር እንደጀመሩ መግቢያ አድርገው የሚጠቀሙት
"ሰው አማህ(አማሽ) አትበሉኝና!"
የሚለውን ፈንጅ አምካኝ ንግግር ነው ሰው ላይ የሀሜት ፈንጅ እየወረወሩ እነሱ ላይ የሚወረወረውን የትዝብት ፈንጅ የሚያመክኑት "ሰው አማህ /ሰው አማሽ አትበሉኝና" በሚለው ቅድመ ሀሜት ንግግራቸው ነው።
እናም ሁሌም እንደዚህ የሚሉ ሰዎች ሲያጋጥሟችሁ ሰው እያሙ ሰው አማህ ወይም ሰው አማሽ ካላላቹሀቸው ምን ምን እንደምትሏቸው ማሰብ ጀምሩ።
መልሱን ለናንተ ልተወውና ወደ ጉዳዬ ልመለስ
ሰው አማህ አትበሉኝና ጋደኛዬ ክሩቤል በተለይ በተለይ በፍቅር ዙርያ ያለው አመለካከትና በፍቅር መሀል ጣልቃ ለመግባት ያለው ድፍረት ያናድደኛል።
ፍቅርም አይዘኝም ፍቅር የምታስይዘኝም ሴት የለችም መፈክሩ ነው።
አንድ ቀን የኔዋ ሊሊ •••
"ጋደኛዬ ጓደኛህን ክሩቤልን ወዳዋለች ልጁ ግን እሚገባው ነገር አደለም እባክህን አናግረው እስቲ ሶልዬ!" ስትለኝ በጣም ደነገጥኩ ሄጄ ሳናግረው ምን እንደሚለኝ! እንዴት እንደሚላላጥብኝ! አንተን አረከኝ እንዴ ብሎ እንደሚዘልፈኝም አውቀዋለሁ ቢሆንም የማይቻል ወይም ጭራሽ የማይሞከር ካልሆነ በስተቀር ሊሊዬ ምንም አድርግልኝ ብትለኝ የትም ሂድልኝ ብትለኝ እምቢ ለማለት አቅም የለኝምና ኩሩቤልን አናግሬው ምላሹን እንደምነግራት ቃል ገብቼ ተለያየን።
ሄጄ ሳናግረው እንደፈራሁት ተላላጠብኝ ብዙ ነገር አውርቶ በመጨረሻ ጥየው ስሄድ ጮክ ብሎ "ቢጤሽን ፈልጊ በላት "አለኝ ።
ለሊዬ በቃ ልጁ አይሆናትም ይቅርባት ምላሹ ጥሩ አደለም አልኳት። ልጅታ ከሊሊ መልሱን ስትሰማ "ያፈቀረ ሲቆርጥም የመረረ!" እንዲሉ እርግፍ አድርጋ ተወችው ። ከተወሰነ ግዜ ቡሀላ ልጅቷ ከአንድ ልጅ ጋር ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ አዘውትራ መታየት ጀመረች።
ፍቅር ላይ ንጉስ ነኝ የሚለው ጓደኛዬ።
ፍቅሯ ተገልብጦ መቆሚያ መቀመጫ አሳጥቶታል ታግሎ ታግሎ ሲሸነፍ መሸነፉን ሊተነፍሰው ግድ ሆነበት ሲል የነበረውን ያውቀዋልና እንዴት እንደሚነግረኝ ግራ ገብቶት ሁለት ግዜ በጣም እፈልግሀለሁ እያለ ቀጥሮኝ ሳይነግረኝ ተለያየን ። የመጀመሪያው የትምህርት መንፈቀ አመት ተጠናቆ እረፍት ላይ ነበርን ለሶስተኛ ግዜ ቀጥሮኝ እቤታቸው ሄድኩኝ ክፍሉ ስገባ በሆዱ ተኝቶ ያስቴርን ሙዚቃ እያዳመጠ ነበር

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍2
#በኔ_የደረሰ


#ክፍል_አራት


#በጥላሁን

...ፍቅር ላይ ንጉስ ነኝ የሚለው ጓደኛዬ።
ፍቅሯ ተገልብጦ መቆሚያ መቀመጫ አሳጥቶታል ታግሎ ታግሎ ሲሸነፍ መሸነፉን ሊተነፍሰው ግድ ሆነበት
ሲል የነበረውን ያውቀዋልና እንዴት እንደሚነግረኝ ግራ ገብቶት ሁለት ግዜ በጣም እፈልግሀለሁ እያለ ቀጥሮኝ ሳይነግረኝ ተለያየን ። የመጀመሪያው የትምህርት መንፈቀ አመት ተጠናቆ እረፍት ላይ ነበርን ለሶስተኛ ግዜ ቀጥሮኝ እቤታቸው ሄድኩኝ ክፍሉ ስገባ በሆዱ ተኝቶ ያስቴርን ሙዚቃ እያዳመጠ ነው •••
ስገባ ቀና አለ ። ሁኔታውን ሳየው እንኳን እሱ እኔም ሲለኝ የነበረውን ነገር ሁሉ ረሳሁት። አንጀቴን በላኝ ትናንት እንደዛ ስትል እንዳልነበር ዛሬ እያልኩ በፍቅር በወደቀው ዛፍ ላይ መጥረቢያ ማብዛቱን በጭራሽ አልፈለኩም።

እንኳን እንደዛ ልለው የሆነውን ከሁኔታው ተረድቼ ሳለሁ ምን ሆነሀል? ብዬ ላስጨንቀው አልፈለኩም።
እራሴ ወደጉዳዩ ቀጥታ ብገባ ሁለቴ ቀጥሮኝ ለመናገር የከበደውን ነገር እንደማቀልለት አሰብኩና •••
ትናንት ያጣጣልካትን ልጁ መልሰህ ስላፈቀርካት አይሰማህ ጋደኛዬ ይህ ፍቅር ጉልበቱን የሚያሳይበት አንዱ ባህሪው ነውና "ትናንት እሷ አፍቅራኝ ቢጤሽን ፈልጊ ያልኳትን ልጅ እንዴት እንዲህ በፍቅሯ ልንበረከክ ቻልኩ " እያልክ ከራስህ ጋር አትጣላ የደካማነት ስሜትም እንዳይሰማህ።

ማፍቀር መታደል እንጂ መሸነፍ ወይም መዋረድ አይደለም።ስለፍቅር ሊያውም ጥቂቱ የሚያውቀው ያፈቀረ ብቻ ነው ። ትናንት ስለማታውቀው ፍቅር ምንም ብትል አይገርምም።
አሁን ማፍቀር ዝቅ ማለት መሸነፍ መዝረክረክ ሳይሆን መታደል መሆኑን የተረዳህ ይመስለኛል? ይህን ተናግሬ ቀና መልሱን ስጠብቅ ጭንቄቱን በማወዛወዝ አዎንታውን ከገለፀልኝ ቡሀላ
"እና ያኔ ባልኩህ ነገር አልተቀየምከኝም ማለት ነው ጓደኛዬ? ከተቀየምከኝ ግን ይቅርታ!" አለኝ። አነጋገሩ እና አስተያየቱ በጣም ያሳዝን ነበር።
በጭራሽ አልተቀየምኩህም ጓደኛዬ በጣም የምወድህ ጓደኛዬ እኮ ነህ ከልጅነታችን ጀምሮ ብዙ ነገር አብረን ያሳለፍን ወንድማማቾች ነን ።
እኔ እናት እና አባቴ እህት እንጂ ወንድም አልሰጡኝም አንተ ነህ ከፈጣሪ የተሰጠከኝ ወንድሜም ጋደኛዬም ።
ጋደኛማቾች ነን ማለት ግን አንድ አይነት አስተሳሰብና አመለካከት አለን ማለት አይደለም የአመለካከት ወይም የሀሳብ ልዩነት ደግሞ አያቀያይምም። በርግጥ ጣልቃ ገብተህ ስትገስፀኝ እናደድብህ ይሆናል ቢሆንም በፍቅር ዙርያ የነበረን የአመለካከት ልዩነት ጓደኝነታችንን የማሻከር አቅም የለውም። ስለው ተነስቶ አቀፈኝ። ተቃቀፍን።
"እሺ ምንድን ነው የማናደርገው ሶልዬ እኔ የማብድ የማብድ እየመሰለኝ ነው ከልጁ ጋር ፍቅር የጀመሩ ይመስልሀል?" ሲለኝ•••
አይመስለኝም ለሁሉም ነገር መጀመሪያ የኔዋ ሊሊን ያለውን ነገር በግልፅ እንድትነግረኝ እጠይቃታለሁ ከዛ የሷን መልስ ከሰማሁ ቡሀላ ያለህበትን ሁኔታ መንገር ይኑርብኝ አይኑርብኝ ወስናለሁ።
ጋደኛዬ አንድ ነገር ግን ልነግርህ እፈልጋለሁ ልጅቷን በጣም እንዳፈቀርካት ተረድቻለሁ ከተሳካ እሰየው ባይሳካም ግን ሂወት እንደምትቀጥልና ያንተ ብትሆን ኖሮ እንደሚሳካ ያልተሳካው ፈጣሪ እሷን ላንተ ስላላላት መሆኑን አምነህ ለመቀበል ተዠጋጅ።
ካልሆነ ግን ከዚህኛው ጉዳት ያኛው ይከብዳል ። የሰው እንደሆነች እና እንደማታገኛት እያወክ ማፍቀርን የመሰለ ከባድ ህመም የለም።
ህመሙ ባይቀርልህም እንዳይጠናብህና እራስህን እንዳትጥል ቅድም እንዳልኩህ ሌላ ሂወት እንዳለና ያንተ የሆነችውን ለማግኘት ያንተ ያልሆነችውን ረስተህ እራስህን ሳትጥል መጠበቅ እንዳለብህ ማመን አለብህ ያለበለዝያ ያንተ ያልሆነችውን በማይሳካው የፍቅር አለም ውስጥ ስታሳድድ ያንተ የሆነውን ሁሉ ታጣለህ።
በቅድሚያ ከራስህ ትጣላለህ ። በመቀጠል በዙርያህ ያሉ ሰዎች ሁሉ ያስጠሉህና ከነሱም ትጣላለህ ።
ከዛ በየመንገዱ ከድንጋዩም ከግድግዳውም ከአየሩም ከንፋሱም መጣላት ብቻህን ማውራት ትጀምራለህ ። በመጨረሻ አብደህ ከፈጠርህ ጋም ትጣላና የሰይጣን ትሆናለህ።
ስለዚህ በማፍቀርህ ልክ ባይሳካ ለመርሳትም ተዘጋጅ።
እሺ ሶልዬ በጣም አመሰግናለሁ ግን ልጁን የምታፈቅረው ይመስልሀል?"
እኔ በምን አውቃለሁ ጓደኛዬ እኔም እንዳንተው አብረው አየኋቸው እንጂ ሌላ ምንም የማውቀው ነገር የለም ።
ስንቱ ተቃቅፎ እየሄደ በሆዱ በሚሰዳደብባት አለም አብረው ስለተቀመጡና አብረው ስለሄዱ ብቻ ይፋቀራሉ ብሎ መደምደም መጃጃል ነው
"እሺ አሁን ሊሊን መቼ ልታናግራት ወሰንክ ሶልዬ!"
"ነገ እንገናኛለን ነገ አናግራታለሁ "
"ኧረ ሶልዬ እስከነገ ለምን አሁን ብትደውልላት አይሻልም ቢያንስ ከልጁ ጋር ያላትን ጉኑኝነት ሰምቼ ቁርጤን እንዳውቅ!" ከስልክ ይልቅ ሳገኛት ባወራት እንደሚሻል ውስጤ ቢያምን በዚህ ስሜት ውስጥ ሆኖ አልደውልም ብለው ምን ያህል እንደሚከፋው በማሰብ ስልኬን አውጥቼ ደወልኩ።
ሊሊዬ ስልኬን አንስታው የራሳችንን ወሬ ከጨረስን ቡሀላ በጎደኛዋና ሰሞኑን አብራት በሚታየው ልጅ መካከል ያለው ግኑኝነት ምን እንደሆነ ስጠይቃት ገብቷት ነው መሰለኝ ረጅም ሳቅ ሳቀች።
ሳቋን ስትጨርስ ለምን እንደሳቀች ስጠይቃት
"ለምን እንደሳኩ እንድነግርህ አንተ በቅድሚያ ለምን እንደጠየከኝ ንገረኝ?" አለችኝ አሁንም ሙሉ በሙሉ ከሳቋ ሳታባራ።
ምን እንደምላት ጨነቀኝ ፍንጭ ካልሰጠኋት ልትነግረኝ እንደማትችል ስረዳ ከጓደኛዬ ክፍል እየወጣው
" ማንነቱን ሳልነግራት አንድ ጓደኛዬ በፍቅሯ እየትንገላታ መሆኑን ልነግራት ገና በቃ አንድ ጋደኛዬ አፍቅሯት•••
ስል በድጋሚ ሳቋ አቃረጠኝ ከሳቋ ከጠል አድርጋ
"ዋው ቀመራችን ሰርቷል ማለት ነዋ "
አለች የምን ቀመር ሊሊዬ?
ቀመሩ ወንዶች ስትባሉ የጣላችሁትን እንኳን ሲያነስባችሁ እንደምትወዱ አውቀን የቀመርነው ነዋ!"
"ልጁ ዘመዷ ነው አብራ መታየት የጀመረችው ሆን ብለን ተማክረን ነበር ጓደኛህ ወጥመዳችን ውስጥ ዘሎ መግባቱ እንደማይቀር ገምቼ ነበር ስትለኝ ደነገጥኩም ደስ አለኝም።
ስልኩን ዘግቼ የጓደኛዬን ክፍል በር በርግጄ ገባሁ

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
1👍1
#በኔ_የደረሰ


#ክፍል_አምስት


#በጥላሁን

"ዋው ቀመራችን ሰርቷል ማለት ነዋ "
አለች የምን ቀመር ሊሊዬ?ቀመሩ ወንዶች ስትባሉ የጣላችሁትን እንኳን ሲያነስባችሁ እንደምትወዱ አውቀን የቀመርነው ነዋ!"
"ልጁ ዘመዷ ነው አብራ መታየት የጀመረችው ሆን ብለን ተማክረን ነበር ጓደኛህ ወጥመዳችን ውስጥ ዘሎ መግባቱ እንደማይቀር ገምቼ ነበር ስትለኝ ደነገጥኩም ደስ አለኝም።
ስልኩን ዘግቼ የጓደኛዬን ክፍል በር በርግጄ ገባሁ •••
ገብቼ ሊሊዬ ያለችን ስነግረው ያ እንደሀምሌ ወር የፍቅር ደመና የጠቆረው ስሜቱ ፈጎ እንደመስከረም ፀሀይ አብራ።
ወድያው በድጋሚ ሊሊዬ ጋር ደውዬ በነገው ቀጦሮአችን ላይ ኬርያንም ይዛት እንድትመጣ ነገርኳት።

በንጋታው ተገናኝተን ሁሉም ነገር በጣም ደስ በሚል ሁኔታ ተጠናቀቀ። ሁለቱም አብረው ሆኑ።
አራታችንም የይንቨርስቲ መግቢያ ፈተና እስክንፈተን እና እስክንበታተን ድረስ ሁለት አመታትን አስደሳች የፍቅር ግዜ በዛው ትምህርት ቤታችን ውስጥ አሳለፍን ።
የማትሪክ ውጤት እኔ ሊሊዬ እና ስናመጣ ኬርያ አልተሳካላትም
እኔ አዳማ ዩንቨርስቲ ስመደብ ሊሊዬ ድሬ ዳዋ ዩንቨርስቲ ደረሳት ቢሆንም አባቷ ከአጠገቡ ርቃ እንድትሄድ ስላልፈለገ ውጪ ሀገር ልኮ እንደሚያስተምራት ቃል ገብቶ አስቀራት። ጋደኛዬ ጅማ ዩንቨርስቲ ደረሰው ። በተመደበልን ግዜ እኔ ወደ አዳማ እሱ ወደ ጅማ ተጓዝን ።
ፍቅራችን ካለበት ሞቅታ ሳይቀዘቅዝ ጭራሽ መነፋፈቅ እያጋለው ቀጠለ።
ዩንቨርስቲ ገብተን ስድስት ወር ሳንማር አለምን ባስጨነቀው ባዲሱ ወረርሽኝ በኮሮና ምክንያት ሀገሪቱ ውስጥ ያሉት ዩንቨርስቲዎች ተዘግተው ወደየቤታችን እንድንሄድ ተደረገ።
ሊሊዬ ያደገችበት ቤተሰብ እና እኔ ያደኩበት ቤተሰብ ለየቅል ነው ።
በዚህ ምክንያት ፍቅር ሀ ብለን ከጀመርንበት ቀን ጀምሮ የማይዋጥላት ነገር አባቴን አብዝቼ መፍራቴ ነው። ባትረዳኝ አልፈርድባትም። አሁን ከዩንቨርስቲ እቤት ተቀመጡ ተብለን ከመጣን በሳምንቱ ደውላ
"እኔ ዝም ብሎ በስልክ ብቻ አንተን እያገኙ መኖር ከበደኝ ሶልዬ ሳምንት ሆነን እኮ እዚሁ አንድ ከተማ ውስጥ ሆነን ሳምንት ሙሉ አለመገናኘት ምን ማለት እንደሆነ አስበከዋል ቆይ አልናፍቅህም ግን ?
" ኧረ ሊሊዬ በርግጠኝነት የኔን ያህል አትናፍቂም ግን ምን ላድርግ ያባዬን ባህሪ ታውቂው የለ እንኳን ወረርሽኝ ገባ ከቤት አትውጡ ብሎ መንግስት አውጆለት ድሮም ቢሆን መች ያለ ምክንያት መዞር ይፈቀድልኛል?
"ሶልዬ እኔ ጋር መምጣት በቂ ምክንያት ነው ከዚህ በላይ ምን ምክንያት አለ ደሞ ልዙር ፍቀድልኝ በላቸው መች አልኩህ እንገናኝ ልትለኝ ካልሆነ እንዳትደውልልኝ አኩርፌሀለሁ በቃ በቃ የምሬን ነው! "
ሊሊዬ እንዲህ ነች ተናግራ ነው እምታኮርፈው።

እውነቷን ነው ናዝሬት ትምህርት ላይ በነበርኩበት ባለፉት ወራት ቢያንስ በሳምንት አንድ ግዜ እንገናኝ ነበር ።
የምሯን እንደሆነ እንደተናደደችብኝ አውቃለሁ ግን ምን ላድርግ ።
አባዬ እንደሆነ ድሮም ድሮ ነው እሄ ወረርሽኝ ሀገራችን ገባ ከተባለበት ግዜ ጀምሮ መንግስት ብቻ ሳይሆን አባዬም ቤቱን ወደ ቤተሰብ ለይቶ ማቆያ የቀየረው እስኪመስለን ድረስ እኔም እህቴም እናቴም እንኳን ወደ ውጪ ልንወጣ የውጪ በር ሲንኳኳ እንኳን እንድንከፍት አይፈቀድልንም።

አባዬ ከቁጥጥሩም ባልተናነሰ ለኛ ለልጆቹ ያለው ፍቅር እስከጥግ ነበርና ቁጥጥሩ በፍቅሩ ስለሚጣፋ በጭራሽ ላስቀይመው አልፈልግም በኔ አዝኖ ከማየው ሞቴን እምመርጥ ይመስለኛል ።
መቆጣት ሲኖርብት የሚቆጣ ፍቅር መመገብ ሲኖርበት ፍቅሩን ሳይሰስት ለልጆቹ የሚመግብ አባት ነው አባቴ በቁጣው በቁጥጥሩ ውስጤ ሲነድ በፍቅሩ ዝናብ እያጠበ ያበርደኛል።
የተመጣጠነ ምግብ ብቻ ሳይሆን የተመጣጠነ ባህሪ መግቦ ነው ያሳደገን።
ምንም ብለው ስለማይፈቅድልኝ ሊሊዬን ሳልፈልግ ዝም አልኳት ። ስልክም አልደወልኩም ሶስት ቀን ሳንደዋወል ስንቆይ ጨነቀኝ ቢሆንም ቻልኩት።
አምስት ቀን ሞላን።
በአምስተኛው ቀን ልክ ከቀኑ በስምንት ሰአት አልጋዬ ላይ ጋደም ብዬ በፊት ተገናኝተን ደብረዘይት ሀዋሳ እየሄድን በምንዝናናበት ወቅት የተነሳናቸውን ፎቶዎች በተመስጦ እየተመለከትኩ ከፎቶው ጋር ሳወራ ድንገት የጮኸው ስልኬ አስደንግጦ ከሄድኩበት የትዝታ አለም ጎትቶ አወጣኝ።

ሊሊዬ ነበረች የደወለችው ።
የኔ ፍቅር በኔ እንደማይስችልሽ እኮ አውቃለሁ ግን ደናነሽልኝ ስላት •••
" አንተ ግን አስችሎህ ዘጋከኝ አደል ?" አልች ድምጿ ውስጥ መከፋታ ያስተጋባል ።
ምን ላድርግ ሊሊዬ አባዬን ከማስቀይመው ብዬ እኮ ነው
ልክ ነህ አባትህን ከምታስቀይመው እኔን ብታስቀይመኝ ይሻላል ተረዳሁህ
ይቅርታም አረኩልህ ግን ከነገወድያ ልደቴ ነው ልደቴ እንዴት እንደሚከበርልኝ ታውቃለህ የፈለገውን ያህል ቢከበርልኝ አንተ ከሌለህ ግን ምኑም ደስ እንደማይለኝም ታውቃለህ ታድያ ልደቴንም ልትቀር ነው ?
ስትለኝ መሀል አናቴን በዘነዘና የተረከኩት እስኪመስለኝ በቆሙኩበት ስንጥቅ አልኩ። አዋ ልደቷ እንዴት እንደሚከበርላት በደንብ አውቃለሁ ። ለሷ ልደት የሚወጣው ወጪ ሶስት መለስተኛ የድሀ ሰርግ ይሸፍናል ብል አልተጋነነም ።። ቀን የተጀመረ ሲበላ ሲጠጣ ተመሽቶ ማታ ለዚሁ ልደት በተዘገጀው ሌላ ክፍል ውስጥ በድጄው ልብ የሚሰውሩ ሙዚቃዎች ለጉድ ሲቀውጥ ሲጨፈር ይታደራል ።

ትልቁን የህይወት ፈተና እየተፈተንኩ መሰለኝ። ሊሊዬን ልደትሽ ላይ አልገኝም ብላት በተገኘሁበት ላትደርስ ምላ እንደምትለየኝ አልጠራጠርም።
አባዬ ደግሞ በዚህ ግዜ እንኳን ውሎ እና አዳር ልሂድ ልለው ከቤታችን ፊት ለፊት ካለው ሱቅ የሞባይል ካርድ ገዝቼ ልምጣ ስለው ቁጭ በል እኔ አመጣላሀለሁ ብሎ ያረጀች ቮልስ ዋገን መኪናውን እያስጮኸ ሄዶ ያመጣልኛል እንጂ ገዝተህ ና ብሎ እንደማይፈቅድልኝ አውቃለሁ።

ኮሮና ብሎ የተረገመ በሽታ መጥቶ ገና አንድ ወር ሳይሆነው ሂወቴን ፈተና አደረጋት ።
ሊሊዬ በዚህ ሰአት ልክ አምና እንዳከበርሽው ያ ሁሉ ሰው ተጠርቶ ሊከበር ነው ማለቴ ለሊት ጭፈራ ምናምን እኮ በዚህ ግዜ ስል ገና ካፌ ቀብል አድርጋ•••
"ቲቭው ላይ ሰልችቶን ያጠፋነውን በአስቸኳይ በአስገዳጅ የሚሉት አዋጅ የተከለከሉትን ምናምን አንተም ልደግምልኝ ነው ሶል
ደሞ ብዙ ሰው የሚመጣ አይመስለኝም የማታው የጭፈራ ብሮግራም ግን የማይቀር ነው!"
ቲቪውን ከምታጠፉት በሽታውን ባጠፋችሁት ይሻል ነበር እያልኩ ስልጎሞጎም
"ምን አልከኝ ?"አለችኝ ።
አይ ምንም !
"እሺ ትመጣለህ አትመጣም?
መምጣት መጣለሁ ግን ቀን አልመጣም ተረጅኝ ሊሊዬ እኛ ቤት እራት በግዜ ሁለት ሰአት አከባቢ ሁላችንም አብረን ስለምንበላ የግድ እራት ላይ መገኘት አለብኝ ከዛ ክፍሌ ውስጥ ገብቼ የተኛሁ በማስመሰል የበሩን ቁልፍ ሰርቄም ቢሆን ውጥቼ ለመምጣት እሞክራለሁ። አልኳት ደርሶ ሊሂድ አልሂድ ባላውቅም እንደዛ ከማለት ውጪ አማራጭ አልነበተኝም።
"እሺ ይሁን የኔ ፍቅር ፍቅር እኮ ነህ ዋናው መምጣትህ ነው ግን እሞክራለሁ ሳይሆን እመጣለሁ ነው የሚባለው ኪኪኪኪ ደሞ ልትወጣ ቢያንስ ሀያ ደቂቃ ሲቀርህ ደውልልኝ ዳጊን እልከውና ይዞህ ይመጣል እሺ?"
እሺ አልኳት። ዳጊ ሹፌራቸው ነው። ተስነባበትን።ሁለቱን ቀናት እማዬ•••
"ልጄ ትናንት እና ዛሬ በአካል እዚህ ከኛው ጋር ቁጭ ብለህ በሀሳብ ብን ብለህ ስትጠፋ እያስተዋልኩ ነው ምንድን ነው እሱ ምን ሆነሀል?"
ብላ እስክትጠይቀኝ ድረስ በጭንቀት አሳለፍኳቸው የሊሊ ቤተሰቦች ስራቸው በሙሉ ከውጪ ሀገር ጉዞ ጋር የተያያዘ ነው ወንድማ ዱባይና ሳውዲ እየሄደ እቃ ያመጣል አጎቷ አባቷ ከንግድ ስራቸው ጋር በተያያዘ ውጪ
👍1
#በኔ_የደረሰ


#ክፍል_ስድስት


#በጥላሁን

በድንጋጤ ከደረጃው ላይ ቁልቁል ልፈጠፈጥ ምን ቀረኝ በደንብ አየሁት አጎቷ ነው ጉሉኮስ ተደርጎለታል
እንዴ ምን ሆኖ ነው ያ አጎታችሁ ነው አደል ስላት እህቷን
"አዎ ባክህ በቅርቡ ነው ከውጪ የመጣው መጥቶ ትንሽ እንደቆየ ታመመ!"
ታድያ ሀኪም ቤት አልወሰዳችሁትም ?
"ምን ለውጥ አለው ባክህ እዛም ቢሄድ ዶክተር ነው እሚያየው !
እዚህ ድረስ እየመጣ የሚያየው የቤተሰብ ዶክተር አለ!"
እያለችኝ ያጎታቸውን ሳል ሰማሁት ድንብርብሬ እንደወጣ በድን ሆኜ እነ ሊሊ ወዳሉበት ክፍል ስገባ ቤቱ ከጥግ እስከ ጥግ ጢም ብሏል።
ፊትህን አዙረህ እሩጥ እሩጥ እለኝ•••
ገና ብቅ ስል ያየችኝ ሊሊ እየተርገበገበች መጥታ ተጠመጠመችብኝ ብዙ ሰው አይመጣም ብላኝ አልነበር እንዴ እያልኩ በሀሳብ ቢዥታ ውስጥ ሆኜ እኔም አቀፍኳት የሷስ ይሁን ከታዳሚው ተገንጥለው አብረዋት የነበሩ አራት ጓደኛቿ በየተራ "ሰላም ነህ?" ቅብርጥሶ እያሉ በጉንጮቻቸው ጉንጬን ደበደቡት "አትሳሳሙ" የሚለው ማስታወቂያ ትዝ አለኝ ወደ ቤት ከመጣሁና ባባዬ ቁጥጥር ስር ከዋልኩ ወድሂ የመጀሚሪያውን የአትሳሳሙ ህግ ለመጀመሪያ ግዜ ጣስኩ።

በተለይ መጨረሻ ላይ የሳመችኝ የምግብ ብዛት እና አይነቱ እየዘጋት እህል በልታ የማታውቅ የምትመስለው ቅጭጭ ያለች ቀጫጫ ልጅ የፀጉር አሰራራ ነው መሰለኝ እሱን እንድትመስለኝ ያደረገኝ ብቻ የጉንጫ አጥንት ጉንጬን ሲወጋው እራሱ ኮረና ዛሬ አታመልጠኝም አገኘሁህ ያለኝ ነው የመሰለኝ።

ኪሴ ውስጥ ያለችውን በትንሽ ብልቃጥ የያዝኳትን ሳኒታይዘር አውጥቼ እጄን ሳይሆን ፊቴን ልታጠብበት ፈለኩ። ለካ ለእጅ እንጂ ለፊት አይሆንም። ቢሆን ኖሮስ ቤት በኩል ልታጠብ
እንኳን ለመታጠቢያ ለመተንፈሻም ግዜ ሳይሰጡኝ
ሊሊ እና ጓደኞቿ መሀላቸው አስገብተው እያዋከቡ እቤት ውስጥ ወዳሉት ታዳሚዎች መሀል ወሰዱኝ።
እነዛ እቤታቸው ግርግዳ ላይ አንዲት በረሮ ቢያዩ እርርርይ እያሉ ቤቱን ጥለው የሚጠፉ የሀብታም ልጆች ኮሮናን አይፈሩትም ብቻ ሳይሆን ትዝም አይላቸውም ማለት ነው ብዬ እራሴን ጠየኩ ሌላ ማንን እጠይቃለሁ ብጠይቅስ ማን ይመልስልኛል?።

ሁሉንም ሳያቸው ሀገራችንን ጨምሮ በአለም ዙርያ ስለዚህ በሽታ በሚድያ የሚለፈፈውን የሚስበው የኛ ቴሌቭዥን እና ዲሽ ብቻ ነው እንዴ አልኩ።የሚያዳምጠውም የሚያየውም አባዬ ብቻ መስሎ ተሰማኝ።
ጭራሽ ሊሊዬን ሞቀኝ ወደ በሩ አከባቢ ብንሆንስ ብዬ ስጠይቃት የሰመችው ያቺ ኮሮና ስጋ ለብሶ መስላ የታየችኝ ቀጭኗ ልጅ ያጋመሰችውን ቢራ ወደ አፌ እያስጠጋች •••
"እንካ ጎንጨት በልበትና ሞቅ ይበልህ ሞቅ ሲልህ የቤቱ ሙቀት አይታወቅህም ክክክክክክ" አለች። ተከትለዋት ሁሉም ሳቁ ። እኔ እንኳን የምስቅበት የማገጥበትም ጥርስ አልነበረኝም።
አመሰግናለሁ ግን አልጠጣም ብዬ ቢራዋን ከነጇ ከአፌ አከበቢ ገፋ አደረኩት።

ጓደኛዬንና ፍቅረኛውን ከሩቅ አየኋቸው እራሳቸውን አያውቁም በራሳቸው አለም ርቀው ሄደዋል ሊሊዮዬን ጠጋ አልኩና በድጋሚ •••
ስገባ አጎትሽን አየሁት ልበል? አሞታል እንዴ ሊሊዬ? ለምን አልነገርሽኝም እንዳስተዋወቅሽኝ ረስተሽው ነው። መጥቼ እጠይቀው ነበርኮ ።
ዘንድሮ በሽትኛ መጠየቅ ቀርቷል እኮ አልሰማህም እንዴ ኧረ በክህ በልደቷ ቀን ጓደኛዬን ስለበሽታ ስለጥየቃ ምናምን ማውራቱን ተውና ዘና በል " አለችኝ። አሁንም ያችው ልጅ። ወይ ጣጣ ልጅቷ ሊሊ በፊርማዋ አረጋግጣ ውክልና የሰጠቻት ነው እምትመስለው ገና ሊሊን ማናገር ስጀምር ወሬዬን ሳልጨርስ እሷ መልስ እየሰጠች አላስወራ አለችኝ።
ከዛ ቡሀላ አንዳች የሚገላግል ነገር ከዛች ልጅ ካልገላገለኝ በቀር ላለማውራት ወሰንኩ።

ሊሊዬ ከዛም ከዛም እየጠሯት ውክብክብ ስላለች ፍቴን ማየትና መረዳት እንኳን አልቻለችም ነበር።ሁለተኛውን ህግ ጥሻለሁ ርቀቴን ሳልጠብቅ በብዙ የሊሊ ልደት ተጋባዦች መሀል ሆኜ ድንገት ወጥመድ ውስጥ ገብታ መውጫ እንዳጣች ጦጣ ግራ ተጋብቼ ግራ እና ቀኝ ስቁለጨለጭ ቆየሁና በሚጠጡ ፣በሚደንሱ፣ በሚሳሳሙ፣ በሚተሸሹ ሰዎች መሀል ሆኖ በተጨነቀ ፊት መቆየት ከባድ ሆነብኝ።
ይለይለት ብዬ ይሁን ይለይልኝ ብቻ ከቢራውም ከውስኪውም ከወይኑም ቀላቅዬ ስጠጣ ፍርሀት እና ደስታ የተቀላቀለበት ስካር ሰከርኩ።
መጠጡ በላይ በላይ ሲመጣ ፍርሀቱ ጠፍቶ ጊዛዊው ጀግንነት መጣ ድፍረቴ ጨቅ አለ።
ባንድ ግዜ እንደማያ ተለዋውጬላችሁ ቁጭ አልኩ።ኧረ የምናባቱ ኮሮና ሺ አመት አይኖር ሙዚቃውን ከፍ አድርገው ዲጄው ምንድን ነው ለቅሶ ቤት አስመሰለው እኮ ሊሊዬ ዲጄውን ከሰልስት ላይ ነው እንዴ አስነስታችሁ ያመጣችሁት ኬኬኬኬኬኬኬኬ"
እሷም ተከትላኝ
" ኪኪኪኪኪኪኪኪ እሄንን ሶል ነው ስፈልገው የነበረው!" ሊሊም ጓደኞቻም ሳቁ።
ቤቱ አልበቃ አለኝ ከላይ የለበስኩትን ጃኬት አውልቄ ጣልኩት።
ተቀላቀልኩ ፣ ጨፈርኩ ፣ዘለልኩ፣ እየተቀባበልኩ ጠጣሁ፣ ከሊሊዬ ጋር በየደቂቃው መሳሳም፣ መደነስ እስኪደክመን ከጓደኛቿም ጋር ተራ በተራ ጨፈርን አበድን ፣ ከነፍን በረርን ፣
እነሱ የረሱትን ሁሉ ረሳሁ። እነሱ የናቁትን ሁሉ ናቅሁ! እነሱ የሆንኩትን ሁሉ ሆንኩ።
ከለሊቱ ዘጠኝ ሰአት ሲሆን አባዬ ትዝ ብሎኝ ወደቤቴ ካልሸኘሽኝ ብዬ ቤቱን ባንድ እግሩ አቆምኩት በወሰደኝ መኪና ተመልሼ ልክ ግቢያችን በር ላይ ስደርስ ስካሬ ብን ብሎ ጠፋ።
ሹክክ ብዬ እንደወጣሁት ሹክክ ብዬ በመግባት ተጠቀለልኩ።
አይነጋ የለ ነጋ ። ጥዋት 2:30 አከባቢ እማዬ የክፍሌን በር አንኳክታ ሰለሞኔ ተነስ ቁርስ ቀርቧል እየጠበቅንህ ነው ስትለኝ ።መብረቅ ክፍሌ ላይ የወረደባት ይመስል ክው አልኩላችሁ።
ለካ እሄም አለ አሁን እኔ ለሊት እዛ ሁሉ ጉድ ውስጥ አሸሸ ገዳሜ ስል አድሬ እንዴት ነው ከሽማግሌው አባቴና ከአረጊቷ እናቴ ጋር መአድ ባንድ ላይ ቀርቤ እምበላው ?

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👏1
#በኔ_የደረሰ


#ክፍል_ሰባት (የመጨረሻው ክፍል)


#በጥላሁን

ከለሊቱ ዘጠኝ ሰአት ሲሆን አባዬ ትዝ ብሎኝ ወደቤቴ ካልሸኘሽኝ ብዬ ቤቱን ባንድ እግሩ አቆምኩት በወሰደኝ መኪና ተመልሼ ልክ ግቢያችን በር ላይ ስደርስ ስካሬ ብን ብሎ ጠፋ።

ሹክክ ብዬ እንደወጣሁት ሹክክ ብዬ በመግባት ተጠቀለልኩ።
አይነጋ የለ ነጋ ። ጥዋት 2:30 አከባቢ እማዬ የክፍሌን በር አንኳክታ ሰለሞኔ ተነስ ቁርስ ቀርቧል እየጠበቅንህ ነው ስትለኝ ።መብረቅ ክፍሌ ላይ የወረደባት ይመስል ክው አልኩላችሁ።

ለካ እሄም አለ አሁን እኔ ለሊት እዛ ሁሉ ጉድ ውስጥ አሸሸ ገዳሜ ስል አድሬ እንዴት ነው ከሽማግሌው አባቴና ከአረጊቷ እናቴ ጋር መአድ ባንድ ላይ ቀርቤ እምበላው ••••
እምለው እማረገው ሁሉ ጨነቀኝ ቀና ብዬ እዛው አልጋዬ ላይ ቁጭ አልኩና ሁለቱን እጄቼን ወደ ፊት ዘርግቼ እያየኋቸው •••
ማታ እንዳልተለከፍኩ በምን እርግጠኛ ነኝ እራሴን ጠየኩት?
በምንም ደሞ ጉሮሮህ አከባቢ ህመም እየተሰማህ ነው ይዞህ ይሆን እንዴ ? አለኝ ውስጤ
ጉሮሮዬ እንኳን ማታ ብዙ አይነት መጠጥ እየቀላቀልኩ ስለጠጣሁ ሊሆን ይችላል ያመመኝ ።

ላይሆንም ይችላል በሽታውም አንዱ ምልክቱ እንደዛ ነው?
እስቲ አስበው በዚህ እጅህ ስንቱን ነገር ነክተሀል፣ ከስንቱ ጋር ተጎራርሰህ በልተሀል ፣ከስንቱ ጋር እየተቀባበልክ ጠጥተሀል ፣ ስንቱ የተቀባበለውን ቢራ መክፈቻ ተጠቅመሀል
ውስጤ ሌላ ሰው ተቀምጦ የሚያስፈራራኝ መሰለኝ በሁለት ሀሳብ ተከፍዬ ከራሴ ጋር ስከራከር እራሴን አመመኝ።
አንድ ሰው የማንፈልገውን ወይም የሚረብሸንን ወሬ ቢያወራብን ዝም እንዲል አልያም ወሬ እንዲቀይር እንነግረዋለን ካልሆነ ካጠገቡ ተነስተን እንሄዳለን ከሚድያ ላይ የሚወራውን መስማት ካልፈለግን ተነስተን እንጠረቅመዋለን።
ከደጅ የሚመጣን ጩኸት መስማት ካልፈለግን ጆሮአችንን እንይዛለን
ከውስጣችን የሚመጣውን ጩከት መስማት ባንፈልግ ምናችንን እንይዘዋለን ወዴትስ እንሸሻለን?
እማዬ ድጋሚ የክፍሌን በር አንኳኩታ "ኧረ አባትህ እየጠበቀህ ነው ሰለሞኔ ቁርስ ቀርቧል እኮ!" አለችኝ።
ወጥቼ ሻወር ቤት ገባሁና ከሰዉነቴ ክፍሎች ሁሉ እጄን ደጋግሜ ታጠብኩት።
"ውስጥህንስ በምን ታጥበዋለህ ይዞህ ከሆነ በትንፋሽም እኮ ይተላለፋል አለኝ ከበሽታው በላይ ውጋት የሆነብኝ የውጤ ሀሳብ ነው።

እናባዬ ወዳሉበት ሳሎን ገባሁ ። ግን ሳልጠገቸው ፈንጠር ብዬ ብቻዬን ተቀመጥኩ።
"ዛሬ ምን ሆኗል ልጄ ና እንጂ ቁርስ እንብላ አንተን አይደለም እንዴ የምንጠብቀው" አለ አባዬ።
አይ አይሆንም አባ ካሁን ቡሀላ እሄ ክፉ በሽታ ከሀገራችን ተጠራርጎ እስኪወጣ ምግብም ቢሆን አብረን ለመብላት ስንል መቀራረብ የለብንም ። ለብቻዬ ብታቀርብልኝ ይሻላል አይሻልም አባ? ስል•••
እማ ጣልቃ ገብታ " አበስኩ ገበርኩ የደጁን ይሁን ስል ልጆቼንም ከጉያዬ ሊያርቅብኝ ነው እሄ በሽታ ከመች ወዲህ ነው ልጄ መአድ ተነጣጥለን በልተን የምናውቀው መአድ በአንድ ላይ ቀርቦ መብላት ፍቅርን ያደረጃል ልጄ።
ደሞ በኛ መሀል ኬት ይመጣል ከቤት ወጥተን አናውቅ የምንፈልገውን እቃ እንኳን የባታችሁ ወንድም ነው ገዝቶ የሚያመጣልን እቃ ገዝቶ መጥቶ እንኳን በር ላይ አስቀምጠህ ሂድ እንጂ ግባ ብሎት አያውቅ አባታችሁ።
ዛሬ ድንገት ተነስተህ ለብቻዬ አቅርቡልኝ ማለቱን ምን አመጣው ጥሩ ህልም አላየህም ልጄ እስቲ ንገረኝ?" ብላ ዝም ብዬ ሳያት እኔን ትታ ወደአባዬ ፍቷን መለሰችና
"፣እሄው ልጆቼን የፀሀይ ብርሀን እስኪናፍቃቸው ድረስ አላላውስ ብለህ ተጭነህ ስታስጨንቃቸው በጭንቀት ብዛት የልጄን አይምሮ እንዲቃወስ አድርገከው አረፍክ " ብላ ስታፈጥበት
ደና ነኝ እማዬ ምንም የሆንኩት ነገር የለም አባንም እንደዛ ማለት የለብሽም አባ ልክ ነው ። በቃ ተራራቁ ተብሏል እንራራቅ ነው ያልኩት ቀለል አርጋችሁ እዩትና እሺ በሉኝ እናንተ አንድ ላይ ብሉ ለኔ ለብቻዬ ስጪኝ። ስል እህቴ ከነበረችበት ተነስታ •••
"ባክህ የሌለ ነገር እያወራህ አታጨናንቃቸው ተነስና እንብላ!" እያለች እጄን ይዛ ልትጎትተኝ ነው መሰለኝ ወደኔ ስትጠጋ
ከተቀመጥኩበት ተፈናጥሬ በመነሳት እንዳትጠጊኝ እህቴ ነግሬሻለሁ እንዳትጠጊኝ በቃ ስል አባም ግራ ተጋብቶ ተነስቶ ሲቆም
ተጠግቶ ሳይዘኝ ቤቱን ጥየላቸው ብን ብዬ ልጠፋ አሰብኩና እናቴ ልጄ አበደ ብላ እራሷን ከማጥፋት እንደማትመለስ ሳስበው ፈራሁ።
አንተም እንዳትጠጋኝ አባ በቃ ተረዱኝ አትጠጉኝ አልኩ አትጠጉኝ እያልኩ ወደ ክፍሌ በመግባት ከውስጥ ዘጋሁት።
በስንት ውዝግብ አሳምኛቸው ምግብ መስኮት ላይ እየተደረገልኝ በልቼ አጥቤ እየመለስኩ ስምንት ቀን ሆነኝ ። በዘጠነኛው ቀን ጥዋት ጋደኛዬ ደውሎ
የነ ሊሊ ቤተሰቦች በሽተኛ እቤት ውስጥ መኖሩ ተጠቁሞባቸው ቤተሰቡን በሙሉ አፋፍሰው ካስገባቸው ቡሀላ በምርመራ ሌሎቹ የቤተሰብ አባላት ላይም ስለተገኘ ያን ቀን የሊሊ ልደት ላይ የተገኙት በሙሉ እየታደኑ ወደማቆያ እየተወሰዱ ነው አሉ እኛ ጋም መምጣታቸው አይቀርም አልቆልናል ሶል!"
ሲለኝ እኔ እዛው በተኛሁበት አለቀልኝ ። የተኛሁበት በላብ ሲዘፈቅ ትዝ ይለኛል ካልጋዬ ላይ መነሳት አቃተኝ ካንድ ቀን ቡሀላ ብንን ስል መስኮት ላይ ያስቀመጡትን ምግብ ወስጄ አለመብላቴ ያስጨነቃቸው ቤተሰቦቼ እህቴን በመስኮት አዘልለው በማስገባትና ከውስጥ እንድትከፍት በማረግ አልጋዬ ላይ ዙሪያዬን ከበውኝ እስክነቃ በጭንቀት ሲጠባበቁ ተመለከትኩ ። በሂወቴ እንደዛች ቅፅበት መሪር ሀዘን እና የነብሰ ገዳይነት ስሜት ተሰምቶኝ አያውቅም ። እርርይ አልኩ።
በንጋታው ሁላችንንም ወደ ማቆያ ወሰዱን ከቀናት ቡሀላ የምርመራ ውጤቱ ሁላችንም እንዳለብን አመለከተ።
ውጤቱን ስሰማ በተለይ ቤተሰቦቼን በመሉ ማስያዜን ስሰማ ድጋሚ እራሴን ሳትኩ ከሳምንታት ቡሀላ ወደራሴ ስመለስ እና ስነቃ እቤታችን ውስጥ ነኝ።
ሶስታችን አገገምን አባዬ ግን ከመሀላችን
ጎድሏል ።
በነበረበት ስኳር እና ሌላ ተጓዳኝ ህመም ምክንያት በሽታውን መቋቋም አቅቶት በሀገራችን በዚህ በሽታ ከሞቱት ሰዎች መሀል አንዱ ሆነ ።
ይህ ሁሉ በኔ ነው በኔ የደረሰ በማንም አይድረስ!!

💫ተፈፀመ💫

እስቲ ሁላችሁም ይቺን ፅሁፍ በዚች ደቂቃ እያነበባችሁ ያላችሁ #ኮረና የመጣ ጊዜ #ጥንቃቂያችሁ እንዴት ነበር#አሁንስ መልሱን ለራሳችሁ
ግን አሁንም በሽታው ምንም የተቀየረ ነገር የለም መድሃኒት አልተገኘለትም አሁንም የኛ ብቻ ሳይሆን የአለም ስጋት ነው። በየቤታችን እስኪገባ አንጠብቅ እናም ይሄ ታሪክ አንድ ሰው ያስተምራልና #Share እያደረጋቹ።

🛑አሁንም ግን🛑

#እርቀታችንን_እንጠብቅ
#ማክስ_በአግባቡ_እናድርግ
#እጃችንን_በአግባቡ_እንታጠብ
#ከቻልን_ቤት_እንቆይ #ውዶቼ

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
#ሚስቴ_ማነች?


#ክፍል_አንድ


#በጥላሁን

የጫካ ስሜ ፍልፈሉ ይባላል ። አሁን ካለሁበት የሰው ጫካ ከሞላበት ከተማ ውስጥ መኖር ከመጀመሬ በፊት በየዱራዱሩ እና ጫካ ውስጥ ባሉ የተያዩ ዋሻዎች ከ ስምንት እመት በላይ ኖሪያለሁ። ጫካ የምኖረው አውሬ አልያም ከሰው ተቀላቅሎ መኖር የማይችል ልዩ ፍጡር ስለሆንኩ
አልነበረም ።

በግዜውና በነሱ ምልከታ ትክክል የመሰላቸውን እኔም በግዜው ትክክል የመሰለኝን ፈፅሜ ልፈፅም እንጂ።
አስተሳሰብ የሚያቀና እውቀትን አልያም ሀብትና መሬትን ሳይሆን ከፊቱ አደራ የታከለበት በቀልን አውርሰውኝ ከሞተው አባቴ የተቀበልኩትን ገሎ የመበቀል ውርስ ለመፈፀም ባጠፋሁት ነብስ ምክንያት ከሚደርስብኝ የበቀል ዱላና ቅጣት ለመደበቅ መኖሪያዬን በዱር እንዳደርግ ግድ ሆኖብኝ እንጂ ።

ገና አስራ ስምንት አመት ሳይሞላኝ ከሁለት አመት በፊት ከተለየኝ አባቴ የተሰጠኝን ነገር ቢኖር የምበቀለው እነማንን እንደሆነና የት አከባቢ ሊኖሩ እንደሚችሉ እና መሳርያ ብቻ ነበር።

18 አመት እንደሞላኝ ካባቴ የተሰጠችኝን መሳሪያ ጠራርጌ እናቴን ተሰናብቼ ከቤት ወጣሁ ለስድስት ወራት በአከባቢው ካለ ጫካ ውስጥ ተደብቄ የበቀል ኢላማዬ የሚያርፍባቸውን ካባቴ ዘር ነብስ አጥፍተው የተሸሸጉ ሁለት ሰዎችን መውጫያ መግቢያ ሳጠና እና አመቺ ግዜ ስጠብቅ ቆየሁ።

በሶስተኛው አመት መገባደጃ ላይ ግዳጄን እንደፈፀምኩ ከሶስት ቀን በላይ በግር ተጉዤ ከነበርኩበት ራቅ ወዳለ ሌላ ጫካ ገባሁ።
እልፎ እልፎ ከምኖርባት የጫካ ዋሻ በቅርብ ርቀት ባለች አንዲት ተራራማ መንደር እየሄድኩ የሚያስፈልገኝን ይዤ እመለሳለሁ ።

በአምስት አመት ውስጥ በአሳቻ ሰአት እራሴን ቀይሬ ሁለት ግዜ ብቻ እናቴን ጠይቂያታለሁ።
ወደዚች ከተሸሸኩበት ጫካ በቅርብ ርቀት ወዳለች የገጠር መንደር ግን በሳምት ውስጥ ከሁለት ግዜ ብላይ መሄድ ጀመርኩ።

በ አንድ የገና አውዳ አመት እለት ወደ መንደሯ ጎራ ብዬ በግሬ ሳዘግም አንድ ጠላ ቤት በር ላይ እንደደረስኩ ሽታው አወደኝ የሚያውቀኝ ሰው እንዳይኖር ፈራ ተባ እያልኩ ዘው ብዬ ስገባ አመት በአል ስለነበር ከሶስት ጎረምሶችና ካንድ በድሜ ጠና ካለ ሽማግሌ ውጪ ብዙም ሰው አልነበረም። ጥጌን ይዤ እንደተቀመጥኩ አንድ እድሚያቸው በሀምሳዎቹ አፋፍ ላይ የሚሆናቸው ባልቴት ጠላውን ፊት ለፊቴ ባለችው ትንሽ ጠረጴዛ ላይ እያስቀመጡ ደና ዋልህ ልጄ አሉኝ።

ለሰላምታው ምላሽ ሰጥቼ ጠላውን አንስቼ ጎንጨት አልኩት አላወረድኩትም ግሩም ነበርና ባንድ ትንፋሽ ግማሽ አደረስኩት።
እቤቱ ውስጥ ያሉት ሶስት ጎረምሶች ስለ ባለጠላ ቤቷ ሴትዬ ልጅ ቁንጁና ከሚገባው በላይ እያደነቁ ያወራሉ ።

ያን ያመሰለ ውበት ይዛ እስካሁን ባለማግባታ ይደመማሉ። እሷ እዛ የገጠር መንደር ውስጥ ዘናጭ የሆነ ቤት ሰርታ ለብቻዋ እየኖረች የሳቸው ጠላ መሸጥ አይገርምም እያሉ ያሽማጥጣሉ። ሴትዬዋ ጠላውን ሊቀዱላቸው ጠጋ ሲሉ ወሬያቸውን ያቋርጣሉ። ልጅቷን የማየት ጉጉቴ ጨመረ ።አልፎ አልፎ ወደዛ ጠላ ቤት እንድምትመጣ ስለሰማሁ ላይን ያዝ እስኪያደርግ ጠላውን እየደጋገምኩ ብጠብቅም እሷ ሳትመጣ እኔ ሰከርኩ።
ጠላው በሳምት ውስጥ ማክሰኛ እና ቅዳሜ ብቻ ነው የሚኖረው ። የኔም የማክሰኛና ቅዳሜ ውሎ ጫካ ሳይሆን እዛ ቤት ሆነ ከሶስት ሳምንት የማክሰኛና ቅዳሜ ምልልስ ቡሀላ በአራተኛው ሳምንት ቅዳሜ ቁጭ ብዬ ጠላዬን ሳጣጥም ድንገት ዘው ብላ የገባችውን ሴት ስመለከት የተሰማኝ ስሜት ከዛ በፊትም ከዛ ቡኋላም እስከዛሬ ድረስ ተሰምቶኝ አያውቅም።

ምድር ላይ ካሉ ሴቶች ሁሉ ውበት ቀምቶ ለሷ የሰጣት ነው የምትመስለው አይኖቿ ልብ ያሸብራሉ።
ሀር የመሰለው ቀጭን ወገባ ላይ የሚንከባለለው ጥቁር አንፀባራቂ ፀጉሯ ለካ እስከዛሬ ፀጉር አይቼ አላውቅም ያስብላል።

ወደ ውስጥ ስትዘልቅ ከቀጭን ወገባ ቁልቁል ግዛቱን እያሰፋ የሄደው ዳሌዋ ሲውረገረግ ቁጭ ብድግ ያሰኛል። ጥርት ያለው ጠይምነቷ እንኳንም ነጫጭባ ፈረንጅ አልሆንኩ እንኳንም ኢትዬጲያዊ ሆንኩ ያሰኛል ።
ፈገግታዋ ልብ ላይ የተተኮሰ ጥይት ይመስል ልብ ይንዳል ። አንድ ባል አይደለም አንድ ክፍለጦር በውበት አንበርክኮ የሚያስከትል ይሄን ሁሉ ውበት ይዛ ያላገባችበት ምስጢር ምን ይሆን አልኩ ለራሴ።

ተወልጄ ባደግኩበትም ይሁን በሄድኩበት ሁሉ እስከዛሬ ይችን የመሰለች የውበት ሚስጥሩን የገለጠባት ከ
ኮረዳ ተመልክቼ አላውቅም።
ወይ ጣጣ ከፊቴ ተቀምጣ አይኔን እንዴት ከሷ ላይ ልንቀልና ልጠጣ ።

የምትኖርበት መንደር በመሀላቸው ጫካ እርሻ እና ተራራ ያራራቃቸው እዚህም እዛም ተራርቀው ካሉት ውስን ቤቶች በቀር ብዙም ነዋሪ የለም ።
ለመንደሩ አዲስ እንደሆንኩ ታውቋታል መሰለኝ ከናቷ ጋር እያወጋች አልፎ አልፎ እነኛን ውብ እይኖቿ ከብለል እያረገች ትመለከተኛለች ።
እንደተቆጡት ህጣን ልጅ እርበተበታለሁ።
አለባበሷ ግን ከተሜ ቀመስ ትመስላለች እንደው ወደ ከተማ ባል ይኖራት ይሆን? ካላት ታድያ እዚህ ለምን ትኖራለች ?።
ስፈራ ስቸር ቆይቼ አንድ ቃል ካፌ ወጣ።
እናት አለም ጠላ እንጠጣ?
"አባት አለም አልጠጣም! ክክክ"
ደነገጥኩ ስደነግጥ አይታ ይባስበት ይደንብር ብላ ነው መሰል ሳቋን ለቀቀችው።

ስትስቅብኝ ወንድነቴ ኬት እንደመጣ እንጃ ፍርሀቱን ትቼ ደፈር ብዬ አጫውታት ጀመር በስም ብቻ እማውቀው ፍቅር እኔን ለመቆጣጠር ቀጠሮም አላስፈለገው አልቻልኩም ከማክሰኛና ከቅዳሜ ውጪ ጠላ ኖረም አልኖረም ከተደበቅሁበት ዋሻ ወደሷ መሮጥ የየለት ተግባሬ ሆነ እኔ ቀድሜ በፍቅሯ ብወድቅም እሷ ቀስ በቀስ ለምዳኝ ይሁን ወዳኝ እርግጠኛ ባልሆንም ስንለያይ " ነገ ትመጣለህ ?" ማለት ጀመረች።

ማን እንደሆንኩ አንድም ቀን ሳትጠይቀኝ ለምን እስካሁን እንዳላገባች እንድጠይቃት ሳትፈቅድልኝ ከሶስት ወር ምልልስ ቡሀላ ጠቅልዬ ቤቷ ገባሁ። ተጋባን ።

ተጋብተን በሁለተኛው ቀን ግራ የሚያጋባ ነገር ገጠመኝ ማታ አጠገቤ የተኛችው ፍቅሬ እኩለ ለሊት ካለፈ ቡሀሏ ድንገት ስነቃ አጠገቤ የለችም •••

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍4
#ሚስቴ_ማነች?


#ክፍል_ሁለት


#በጥላሁን

ተጋብተን በሁለተኛው ቀን ግራ የሚያጋባ ነገር ገጠመኝ ማታ አጠገቤ የተኛችው ፍቅሬ እኩለ ለሊት ካለፈ ቡሀሏ ድንገት ስነቃ አጠገቤ የለችም።

ደነገጥኩ ቤቱ ሁለት ክፍል ነው ከተኛሁበት ክፍል ተነስቼ ሌላኛው ክፍል ውስጥ መኖር አለመኖሯን ለማረጋገጥ ባስብም ከማሰብ ውጪ ካልጋው ላይ መውረድ አቃተኝ አልቻልኩም።
በተፈጥሮ ከንቅልፍ ነቅተን ለመነሳት ከሚጫጫነን ስሜት እጅግ በላቀ ሁኔታ እንዳልነሳ ተጫጫነኝ ቀና ማለት እየፈለኩ ቀና ማለት ተሳነኝ እስርስር ድብት የሚያረግ መንፈስ ወረሰኝ። መነሳት እየፈለኩ መልሶ እንቅልፍ ጣለኝ።ወፍ ጭጭጭጭ ሲል ነቃሁ። አጠገቤ ተኝታለች። ግራ ተጋባሁ ለሊት ካጠገቤ ያጧኋት በህልሜ ይሁን በውኔ መለየት ፈተና እንደሆነብኝ መምሸቱ አይቀርም ዳግም መሸ።

ትናንት በነቃሁበት በተመሳሳይ ሰአት እኩለ ለሊት እንደተሻገረ ነቃሁ አጠገቤ ተኝታለች። ያን ቀን ደግሞ ከትናንቱ በተቃራኒ አንዴ ከነቃሁ ቡሀላ እንቅልፍ አልወስድ ብሎኝ ስገላበጥ ነጋ ።
አራተኛው ምሽት መጣ ስንጨዋወት አምሽተን እራት በልተን ተኛን። በተለመደው ሰአት በር ሲከፈት ይሁን ሲዘጋ እንጃ ብቻ ድምፅ የሰማሁ መሰለኝና ብንን አልኩ። ኧእምሬዬ ከተኛበት ቢነቃም አይኔ አልተገለጠም ነበርና እጄን ወደ ጎን ልኬ ዳበስ ዳሰስ ሳደርግ ከፍራሹ ካንሶላ እና ከብርድልብሱ ውጪ ማታ አጠገቤ የተኛችው ሚስቴ የለችም ።ፈራሁ። አይኔን መግለጥ ፈራሁ።

በትግል የገለጥኩት አይኔ በፋኖሱ ብርሀን የኔዋ ጉድ አጠገቤም የተኛሁበት ክፍል ውስጥም ያለመኖሯን አረጋገጠልኝ። እቤቱ ውስጥ ምንም ድምፅ የለም ፀጥ ረጭ ብሏል። መነሳት እየፈለኩ አልነሳም መጣራት እየፈለኩ አልጣራም።ጭራሽ ከመነሳት ሀሳቤ ጋር ያልተናበበው አይኔ ካልተከደንኩ እያለ ይታገለኝ ጀመረ ። አይኔ እየተከደነ እንቅልፍ ሊጥለኝ ሲሞክር ላለመተኛት ያደረኩት ትግል ከውስን ደቂቃዎች መሻገር አልቻለም። መሸነፌ የገባኝ ጥዋት ስነቃ ነው ለሊት ያልነበረችው ሚስቴ አጠገቤ ጧ ብላ ተኝታ እራሷን አታውቅም ።

የኔ ፍቅር ማነሽ አቅሌን እስካጣ በፍቅርሽ መውደቄ ይሆን እያቃዥኝ ያለው ።
የፍቅሬ ደረጃ ይሆን ጥለሽኝ የወጣሽ ካጠገቤ የራቅሽ እየመሰለኝ እንድጨነቅ የሚያደርገኝ ነው ወይስ የእውነት ነቅቼ ካጠገቤ እያጣሁሽ ነው ።
እንደዛ ከሆነስ በውድቅት ለሊት የት እየሄድሽ ነው ? መቼስ ባዛ የሰይጣን ሰአት መብራት በሌለበት በዚህ የገጠር መንደር ውስጥ ከቤት መውጣት እንኳን ለሴት ለወንድም ያስፈራል ። ታድያ ምን እየሆንኩ ነው የእውነት ነቅቼ ካጠገቤ አጥቼሽ ከሆነስ ለምንድን ነው ተነስቼ ሁለተኛው ክፍል ውስጥም አለመኖርሽን እና ቤቱ ቤት በኩል እንደተዘጋ ከውጪ ይሁን ከውስጥ ማረጋገጥ ያቃተኝ ።

በለሊት ካጠገቤ ተነስተሽ የት ሄደሽ ነው አልነበርሽም ብዬ እንዳልጠይቅሽ ችግሩ ከኔ ከሆነ እንዳላስቀይምሽ ሰጋሁ። አልኩኝ በውስጤ ብርድልብስም አንሶላም ሳትለብስ ተዘረጋግታ በተኛችው ሚስቴ ላይ እንደጥዋት ፀሀይ ሰውነት የሚያሞቀውን የውበት መአት የፈሰሰበትን ገላ ከታች እስከ ላይ እያየሁ። ምን ዋጋ አለው የትዳር ጣእም የላይ ውበት ሳይሆን የውስጥ ሰላም መሆኑ አሁን ነው የገባኝ።

እሄ ነገር አንድ ቀን እየዘለለ በተመሳሳይ ሁኔታ ቀጠለ። ተአምር የሆነብኝ ነገር ለሊት ስነቃ አጠገቤ ካለች ከነቃሁ ቡሀላ በጭራሽ እንቅልፍ አይወስደኝም ። በሚቀጥለው ቀን ስነቃ ደግሞ አጠገቤ አትኖርም ግን መነሳትም አልችልም በዛ ላይ ወድያው እንቅልፍ ይጥለኛል።ጭንቀቴን ለማን ላዋየው ያለሁት ከሷ ውጪ ማንንም በማላውቅበት ሀገር ነው ።
ጭንቀቴ እና ፍርሀቴ ለሊቱን ብቻ ሳይሆን ቀኑኑም አጨለመብኝ።
እሄን ግዜ ነበር እናቴ ያለችኝ ነገር ትዝ ያለኝ ።
ያባቴን የበቀል ውርስ ልፈፅም ስነሳ ብቻ ብርክክ አለችና ጉልበቶቼን ይዛ "ተው ልጄ የሰው ደም ደግ አይደለም በምድርም በሰማይም ሰላም አይሰጥም ።የሰው ነብስ ያጠፋ የሰላም እንቅልፍ የለውም።የገደለው ሰው ነብስ ታስጨንቀዋለች። አንድ ሰው ስትገድል በህይወት ዘመኑ የሰራው ሀጥያት በሙሉ ወዳንተ ይዞርና እሱ ይፀድቃል አንተ ትኮነናለህ ።
በምድርም በሰማይም ብኩን ሆነህ ትቀራለህ። እሄን ባለማድረግህ አባትህን እንደከዳኸው ቃሉን እንዳላከበርክ አይሰማህ። ይልቅ የነሱን ስተት አትድገመው ካለፈ ነገር ማስቀጠል ያለብን ደግ ደጉንና የሚጠቅመንን እንጂ ክፋቱንና የሚያጠፋንን መሆን የለበትም። ይህን የበቀል መንገድ አንተ ካላቆምከው ማን ያቆመዋል። ሰው በመግደል ጀግንነት ነው ብሎ ማሰብ ሗላ ቀር አመለካከት ነው ። ልጄ ተለመነኝ አትሂድ!"
ልመናዋን መቀበል ፈሪ መሆን ከወንድነት ዝቅ ማለት መስሎ ተሰማኝ ።
እማምዬን ከጉልበቴ ላይ አነሳሗትና ጥያት ወጣሁ። ታድያ አግብቼ ወር ሳይሞላኝ መቋጠሪያውም መፍቻውም የማይታወቅ ፈተና ሲገጥመኝ ። እማማ እንዳለችው ያ ያጠፋሁት ነብስ በቁሜ እያቃዥኝ እንጂ የኔ ንግስት በለሊት የምትወጣበት ምንም ምክንያት ሊኖራት አይችልም ብዬ እራሴን ለማፅናናትም ለመኮነንም ሞከርኩ።

ከብዙ አስጨናቂ ቀናት ቡሀላ አንድ ቀን ወደ ጫካ ወርጄ ለብዙ ሰአት ተቀምጬ ያሳለፍኳት እያንዳንዷን አስጨናቂ ቀን ስፈትሽ ሚስቴ ማታ ማታ ከምታደርጋቸው ነገሮች እስካሁን የተጋረደብኝ እና ያላስተዋልኩት አንድ ነገር ብልጭ አለልኝ።
በድንጋጤ ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ቆምኩ በለሊት ከአጠገቤ የሄደች በመሰሉኝ ቀናት በሙሉ ማታ ማታ ወደ ምኝታዬ ልሄድ ስል በንድ ከቀንድ በተሰራ የጠላ መጠጫ ቀላስ ሙሉ ጠላ ትሰጠኝ ነበር አጠገቤ በነበረችባቸው ለሊቶች ምሽት ግን ያ ጠላ ተሰጥቶኝ እንደማያውቅ ተገለጠልኝ ። ከምኝታዬ እንዳልነሳ ጠፍንጎ የሚይዘኝ ሚስጥር ከጠላው ጋር የተያያዘ መሆን አለበት አልኩ።

ከሩጫ በማይተናነስ እርምጃ ወደ ቤት አመራሁም። ያን ቀን ማታ ጠላው አልተሰጠኝም። እሳም ለሊት አጠገቤ ነበረች።
በሚቀጥለው ቀን ማታ ከራት ቡሀላ ልተኛ ስል "እንካ ጠጣ ለንቅልፍ ይሆንሀል"እያለች ጠላውን በዛው መጣጫ ይዛልኝ መጣች። ተቀብያት ወደ ውስጥ ገባሁና ሳታዬኝ ደፋሁት።
ምኝታዬ ውስጥ ገብቼ የተኛሁ በመምሰል እንቅልፍ ባይኔ ሳይዞር እየተጠባበኩ እኩለ ለሊት አለፈ። በግምት ከለሊቱ ስምንት ሰአት አከባቢ ድምፁ ቀጭን የሰው ሳቅ የሚመስል ጅብ ወደ አለንበት ግቢ ተጠግቶ ማስካካት ጀመረ ። ትንሽ ቆይቶ የማስካካቱ ድምፅ እየቀረበ የሚያሽካኩትም ጅቦች እየበዙ መጡ።
ድምፁን በሰማሁ በሰከንዶች ውስጥ ጉደኛዋ ሚስቴ ድንገት ብድግ አለች። ፊቴን አዙሬ በተኛሁበት በድንጋጤ ላብ አዘፈቀኝ ። ፋኖሱን ይዛ ወደ ሚቀጥለው ክፍል ስትገባ በቀስታ ተነስቾ በመሀለኛው በር ጠርዝ አጮልቄ መመልከት ጀመርኩ። ከመቅፅበት መሶብ ወርቅ ከሚባለው የመሶብ አይነት ውስጥ ቅጠል የመሰለ ነገር አንስታ አፏ ውስጥ ከተተችና ትርጉሙ ባልገባኝ ቋንቋ በጣም በፍጥነት እየለፈለፈች ከግንባሯ በላይ ያለውን የራስ ቅሏን ልክ እንደኮፍያ ከነፀጉራ አውልቃ መሶብ ወርቁን ከፍታ አስቀመጠችው። ወንድነቴ ተፈተነ እግሮቼ መቆም ተሳናቸው በሩን ከፍታ ስትወጣ ከቆምኩበት መንቀሳቀስ አቃተኝ•••

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍1
#ሚስቴ_ማነች?


#ክፍል_ሶስት


#በጥላሁን

የራስቅሏን ከነፀጉራ አውልቃ መሶብ ወርቁን ከፍታ አስቀመጠችው። ወንድነቴ ፈተነኝ እግሮቼ መቆም ተሳናቸው በሩን ከፍታ ስትወጣ ከቆምኩበት መንቀሳቀስ አቃተኝ•••

እዛው የተደገፍኩትን ግድግዳ ተደግፌ ቁልቁል ተንሸራተትኩ። ቁጭ አልኩ። ማን ነች? ምንድን ነች? ምን ላድርግ? ሳትመለስ ውልቅ ብዬ ልጥፋ? ያን ሁሉ አይቼ የማላውቀውን ልቤ ላይ የተቆለለውን የፍቅር ክምር ባንድ ግዜ መናድ ባንድ ግዜ መጥላት እችል ይሆን? ኧረ ፈራሁ! ጫካ ውስጥ ወይ ለመግደል ወይ ለመሞት ወስኜ ካባቴ ጠላቶች ጋር ልፋለም ስወጣ ከነሱ ጋር ፊት ለፊት ስጋፈጥ ቅንጣት ታክል ፍርሀት ስላልተሰማኝ ጀግና ነኝ ብዬ አስብ ነበር።ታድያ አሁን ያ ሁሉ ወኔዬ ወዴት ሄደ። ፍቅር ፈሪ ያደርገል እንዴ? ፍቅር ለካ ከጥይት በላይ ያስፈራል! ፍቅር ለካ ከሞትም በላይ ያስፈራል! ሞት ቢያስፈራኝማ ያኔ በፈራሁ ።አሁን የፈራሁት ሞትን አይደለም ማለት ነው? የፈራሁት በሆነው ምክንያት ያፈቀርኳትን ላጣት ግድ ሊሂንብኝ መሆኑ ነው።
ያስፈራኝ ካሁን ቡሀላ ያን ደስ የሚል የፍቅር ስሜት ቀስ በቀስ ከልቤ ተኖ ሊጠፋ መሆኑ ነው ።

ጨነቀኝ። በሂወቴ እንደዝች ቅፅበት ያስጨነቀኝ ነገር ኖሮ አያውቅም።
እሺ አሁን ምን ላድርግ? ! እዛ መሶብ ወርቅ ውስጥ ያስቀመጠችውን ነገር ላየው ፈለኩ ። ተነስቼ ወደ መሶብ ወርቁ ተጠጋሁ እንዴት ልክፈተው እጄ አልታዘዝ አለኝ። ወንድ ልጁ መሬት የጣለው ክንዴ መሶብ ወርቁን ለመክፈት ጉልበት አጣ። እራሴን አረጋግቼ እሷን ለመጥላትም ማድረግ ያለብኝንም ለመወሰን ግዜ እንደሚያስፈልገኝ አሰብኩ ።
ለብዙ ደቂቃ ግራ ተጋብቼ በቆምኩበት ከውጪ የሆነ ድምፅ የሰማሁ መሰለኝ። በፍጥነት ወደ ምኝታዬ ተመለሼ የሚሆነውን ስጠባበቅ መልሶ ፀጥ ረጭ አለ ።
ከቆይታ ቡሀላ በሩ ሲከፈት ሰማሁ። በኮቴዋ ድምፅ ወደ መሶብ ወርቁ እንደሄደች ተረዳሁ። ወድያው ስትታጠብ ተሰማኝ ። ፍቴን ወደ ግድግዳው አዙሬ ወጪ ገቢ ትንፋሼን የተኛሁ እንዲመስል አደረኩት።
መጥታ አንሶላና ብርድ ልብሱን ገልጣ አጠገቤ ስትተኛ ያቺ የማፈቅራት ቆንጆ ሴት ሳትሆን የሆነ አውሬ አብሮኝ የተኛ መሰለኝ ። ቀፈፈኝ። ገላዩ ከገላዋ እንዳይነካካ ወደ ግድግዳው ተለጠፍኩ። ለደቂቃዎች ቁና ቁና እየተነፈሰች ቆየችና
"ለምንድን ነው ፊትህን አዙረህ ምተኛው ብላ ጎትታ በመገልበጥ በጀርባይ አንጋለለችኝ ።
ብድግ ብላ እላዬ ላይ ጉብ አለች ። ሆዴ ላይ ቁጭ አለች። አይኔን ለግለጥ ድፍረት አጣሁ ። ጎንበስ ብላ ከንፈሬን ጎረሰችው ትንፋሽ አጠረኝ። ከንፈሬን ደምደም እለኝ ከሄዴ ውስጥ አንዳች ነገር ሲገላበጥ ተሰማኝ ። ጥውልውል አደረገኝ። እንደፈለገች ስታደርገኝ እስክትጨርስ አይኔን ጨፍኜ መዝለቁ ከባድ የሚሆንበት ግዜ ላይ ደረስኩኝ።አይኔን ገለጥኩ። እላዬ ላይ የምትጨፍረውን ሴት ሽቅብ ተመለከትኳት ። እራሷ ነች ። ፀጉሯ ፍቷን ሸፍኗት ቁልቁል ይዘናፈላል አቤት ውበት! አቤት ጭንቀት! ወርዳ ተዘረረች ። በተኛችበት ጥያት ልጠፋ አሰብኩ። አሰብኩ እንጂ አላደረኩትም ነጋ ተነስቼ ቁርስ ሳልበላ ወደ ዋሻዬ ወደ ጫካ ሄድኩ ከራሴ ጋር ስማከር ከራሴ ጋር ስከራከር ከራሴ ጋር ስጣላ ቀኑ ተጋመሰ።

ወደ ቤት ተመለስኩ በጥዋት ተነስቼ መጥፋቴ አስቆጣት። ዝምታዬ አስጨነቃት " ምን ሆነሀል? እያለች በተደጋጋሚ ብትጠይቀይኝ መልሴ ምንም ብቻ ነበር። ሁለት የምጥ ቀናት አለፍ
ባፈቀርኳት የመጀመሪያው የፍቅር ሂይወቴ ላይ የተጫወተችውን ፍቅሬን በንጭጩ አምክና ልቤን የሰበረችውን ይቺን ሴት ማንነቷን አጋልጬ በኖረችበት መንደር ላሸማቅቃት ወስኜ ነበር ከጫካ የተመለስኩት። ያን ካደረኩ ቡሀላ ስፍራውን ለቅቄ እግሬ ወደወሰደኝ ልሰደድ ዝግጅቴን አጠናቀኩ።
እንደተለመደው በመጀመሪያው ቀን ያልተሰጠኝ ጠላ በሁለተኛው ቀን ማታ ልተኛ ስል ጠብቃ ሰጠችኝ። ሳታየኝ ደፋቼው ተጠቅልዬ ተኛሁ። እኩለ ለሊት እንዳለፈ ልክ እንደከትናንት ወድያው ጅቦቹ የጥሪ ድምፅ አሰሙ ቤቷን ከበው በጩኸት አነቃነቋት። ብድግ አለች አይኔን ገለጥኩ ። ተነስታ ወረደች ። ወደ ሚቀጥለው ክፍል ስትሄድ ተነሳሁና ተደብቄ ማየት ጀመርኩ። ቅጠሏን በልታ እየለፈለፈች የራስ ቅሏን ከቅንድቧ በላይ እንደ ጀሪካን ክዳን ከፍታ ፀጉሯን ጠቅለል አደረገችና መሶብ ወርቋ ውስጥ አስቀምጣ ወጣች ።

ውስጤ ፍርሀት የሚባል ነገር ሳይሰማኝ ፈጠን ብዬ ፋኖሱን አጠፋሀትና የቤቷን መስኮት በትንሹ ከፍቼ ወደ ውጪ ተመለከትኩ ከ ስድስት በላይ የሚሆኑ ነጭና ጥቁር መልክ ያላቸው ጅቦች ግቢው ውስጥ ተመለከትኩ ። እንደወጣች አንደኛው ጅብ ጀርባ ላይ ቂብ አለች ።

እየጋለበችው ቤቱን ሶስት ግዜ ከዞረች ቡሀላ ከወገቡ ላይ ስትወርድ ባለ ሁለት እግሯ ሴት ባለ አራት እግር ጅብ ሆነች። አይኔን ማመን አቃተኝ ጠፍቶ የነበረው ፍርሀቴ መልሶ ተቆጣጠረኝ።

እሷ ፊት ፊት ሌሎቹ ከጀርባ እየተከተሏት የስሪያ ድምፅ እያሰሙ ከግቢው ወጥተው ተፈተለኩ። እቤት ውስጥ ጥቁር ፌስታል ፈልጌ እንዳገኘሁ ቀጥታ ወደ መሶብ ወርቁ ሄጄ አይኔን ጨፍኜ ውስጥ ያስቀመጠችውን እንደኮፍያ የሚመስል የራስ ቅል ከነ ፀጉሩ አውጥቼ ፌስታሉ ውስጥ ከተትኩት ።
በሩን ከውጪ ስለዘጋችው ይዤው በመስኮት ወጣሁ ። ግቢ ውስጥ ወዳለው ማድ ቤት ገብቼ በፌስታል የያዝኩትን እዛው ማድ ቤት ውስጥ ጥግ ላይ ካለ አንድ ማዳበሪያ ውስጥ ደብቄ ቀድሜ ማድ ቤት ያስቀመጥኩትን መሳሪያዬን ይዤ ቁጭ አልኩ። ፍቅሯን ከነሰንኮፉ ከውስጤ ነቅዬ ለመጣል መጨረሻዋን ለማየት ቁጭ ብልም የተፈጠረው ያልጠበኩት ነበርና ክፉኛ አስደነገጠኝ ።

እንደመጣች ። ገብቷ ፀጉሯን እና እኔን ከነበርንበት ስታጣን በሯን ዘግታ እሪታዋን አቀለጠችው "እርርርይ ጉድ ሆኛለሁ እርርርይ ያዙልኝ እንዳያመልጥ እርርርይ !" በዛ በውድቅት ለሊት መንደሯን በጩኸት አናወጠቻት።

የመንደሩ ሰው ዱላ ያለው ድላውን መሳሪያ ያለው መሳሪያውን እየያዘ ግቢውን ወረረው ተጠግተው "ምን ሆነሻል ? ምን ተፈጠረ?" እያሉ በሩን ሊከፍቱ ሲሞክሩ እንደዛ ሆና እንዳይመለከቷት "በሬን እንዳትትነኩ ! እንዳትገነጥሉ ! ይልቅ ሂዱና ሰውየውን ካለበት ይዛችሁ አምጥሉኝ " ትላለች ዘመዷ ነው መሰለኝ ሁኔታው ገብቶት ይሁን አይሁን ባላውቅም በሯ ላይ ቆሞ በሩ እንዳይከፈት መከላከል ጀመረ ።
የተወሰኑ ሰዎች እኔን መፈለግ ጀመሩ ። አማራጭ ስላልነበረኝ መሳሪያዬን አቀባብዬ አንድ ሰው እንዳይጠጋኝ እያልኩ ከተደበቅሁበት ማድ ቤት ወጣሁ።

ድርጊቴ የማልወጣው ወጥመድ ውስጥ እንደከተትኝ የተረዳሁት እርርርይ ስትል ሰምቶ የተሰበበሰበው የመንደሩ ነዋሪ በሷ ማንነት ከመደነቅ ይልቅ ለኔ ህይወት ማዘናቸውን ሲገልፁልኝ ነው ። ግራ ገባኝ ፍርሀት መላ እኔነቴን እየናጠው ምንም አታረገኝም እኔ ለሷ አንሼ ነው ጭራሽ ለኔ የምታዝኑት እያልኩ ስጮህ
አንድ ፊቱን ስመለከተው ያዘነልኝ የሚመስል ሰው ጠጋ አለኝና •••

" እስቲ ና ወዳጄ ምን አይነት የማትወጣው ጉዱ ውስጥ እራስህን እንዳስገባህ የገባህ አልመሰለኝም ይልቅ ድምፅህን አጥፋና ፀጉሯን የት እንደደበከው ተናግረህ የምታመልጥበትን መንገድ ፈልግ።

ባንተ ቤት ስለነሱ መንደሩ የማያውቅ መስሎህ ጉዳቸውን አጋልጠህ በድንጋይ ተወግሯ የምትሞት መስሎህ ከሆነ ተሳስተሀል ወዳጄ እዚህ መንደር ውስጥ ዘር ማንዘሮቿ እንዳለ እኮ እንደዛ ናቸው ሰፈሩን ጥለህ ካልጠፋህ ከልብስህ በስተቀር ለቀብር እንኳን የሚተርፍ ነገር እንዳይኖርህ በጫጭቀው ደብዛህን ያጠፍቷል!

እየውልህ ቀስ ብለህ ወደዛ ተመልከት እነዛ እዛጋ አይናቸው ደም እንደለበሰ የቆሙት ሶ
👍2
#ሚስቴ_ማነች?


#ክፍል_አራት(የመጨረሻ ክፍል)


#በጥላሁን

ዛፍ ላይ ወጥቼ ለመተኛት ጫካ እስካገኝ ስጓዝ ለሊቱ ተጋመሰ ጫካው ሳይገኝ አጉል ቦታ ላይ አውላላ ሜዳ ላይ ከርቀት ድምፅ ሰምቼ ዘወር ስል ጥቁርና ነጭ መልክ ያላቸው አይናቸው የሚያበራ ከአምስት በላይ የሚሆኑ ጅቦች በከባድ ፍጥነት እየጮሁ ወደኔ አቅጣጫ ሲመጡ ተመለከትኩ መሮጥ ብፈልግም እግሬ አልላወስ አለኝ•••

በዛች በመጨረሻዋ የጭንቀትና የሞት ሽረት ሰአት እራሴን ማረጋግትና የቻልኩትን በሙሉ ማድረግ እንዳለብኝ ለማሰብ ግዜ አላጠፋሁም።
እየቀረቡ ሲመጡ እኔን ፍለጋ እንደመጡ ከሁኔታቸው እርግጠኛ ሆንኩ። ወደ ላይ ቀና ብዬ ፈጣሪዬን ለመለመን ብፈልግም በሰው ነፍስ : በሰው ደም የጎደፈውን ማንነቴን አስቤ ፀሎት እና ልመናዬ የመጀመሪያውን ሰማይ የማይሻገር መስሎ ተሰማኝ ቢሆንም ጨንቆኛልና ፈጣሪዬ እንዲረዳኝ ለመንኩት።

ሮጬ እንደማላመልጥ ስለገባኝ ለመሮጥ አልሞከርኩም። ከጀርባዬ ላይ ያጋደምኩትን መሳሪያ አውርጄ በማቀባበል በተጠንቀቅ ቆምኩ። ብዙ አመት ጫካ ኖሪያለሁ ጅቦች በባህሪያቸው መሬት ሳይጥሉ እንደማይበሉኝ አውቃለሁ። ላለመውደቅ የቻልኩትን አደርጋለሁ በዚህ መሀል የመሳሪያውን ድምፅ ሰምቶ የሚደርስልኝ አላጣም።

ከኔ በቅርብ ርቀት ላይ እንደደረሱ ቆሙ አንደኛው ወጣ አላና ከሁሉም ፊት ቆመ ይቺ የኔዋ ትሆን እንዴ አልኩ። ከፊት የቆመው ጅብ የሆነ ለየት ያለ ድምፅ ሲያወጣ ባንድ ላይ የነበሩት ስድስት ጅቦች ብትንትን ብለው ከበቡኝ።
ሁለቱ ከጀርባዬ ሁለቱ ከፊቴ አንዱ በስተግራዬ አንዱ ደግሞ በስተቀኜ ሆነው ከኔ በተመሳሳይ ርቀት ላይ ቆሙ።
ይህን ተንኮላቸውን ስመለከት "የሰው ጅብ እንደሰው ያስብ ይሆን እንዴ አልኩ ደንግጬ።

ለማመን በሚያስቸግር ሁኔታ ግራና ቀኝ ያሉት ከቆሙበት ሳይንቀሳቀሱ ከፊቴ እና ከጀርባዬ ያሉት በተመሳይ ግዜና ፍጥነት ወደኔ ሲወረወሩ እንኳን አልሞ ለመተኮስ ለማሰብ እንኳን ግዜ አላገኘሁም።
በንፋስ ፍጥነት ታከውኝ ሲተላለፉ ተንገዳግጄ ቆምኩ። አስደንግጠው ሊጥሉኝ ማሰባቸው ገባኝ። ወድያው በነዚህኛቹ ክው ያለውን ቀልቤን ሳላረጋጋ በስተግራና በስተቀኝ ያሉት በተራቸው ወደኔ ተምዘገዘጉ። በደመነፍስ ዝም ብዬ በስተቀኝ በኩል ወደ መጣው ፊቴን አዙሬ መተኮስ ጀመርኩ ሁለቴ እንደተኮስኩ በስተግራ የነበረው ደርሶ ገፍትሮኝ አለፈ አይወድቁ አወዳደቅ ወደኩ ተንደባለልኩ መሳሪያዬም ከጄ ወጣ ከመቅስፈት በወደኩበት ከበቡኝ ። ሁለቱ አልተጠጉኝም።

እሷ የትኛዋ እንደሆነች ባላውቅም አራቱ ዙርያዬን ከበው ቁልቁል ሲመለከቱኝ ነብስ ያዘኝ።ተስፋ ቆረጥኩ።
መግደል ምድራዊ ታሪኬን መደምደም በምትችልባት ቅስፅበት በዛች ውድቅት ለሊት እስትንፋሴን መቋጨት ስትችል እስከምሞት በስቃይ እንድኖር ስለፈለገች ነው መሰለኝ ሁለቱ ግራና ቀኝ እግሬን እያሰቃዩ ዘንጥለው ይዘው ሄዱ ።
አንዱ ግራ እጄን ገንጥሎ እንደሄደ። አንደኛው ግን ብዙም አጥብቆ ያልነከሰውን ቀኝ እጄ ተወልኝ።
እራሴን ከመሳቴ ከሰከንዶች በፊት ሁሉም ጅቦች ወደ መጡበት ሲመለሱ ቀኝ እጄን የተወልኝ ጅብ ተለይቶ በመቅረት ፊት ለፊቴ ቆሞ ሲመለከተኝ ትዝ ይለኛል ምናልባት እሷ ትሆናለች።
ከዛ ቡሀላ ከተማ ወጥተው መንገድ የመሸባቸ ገበሬዎች አግኝተውኝ የሚፈሰውን ደሜን አስረው እቤታቸው እንዳሳደሩኝና በአከባቢው ከነበረ ከአንድ የሀብታም ገበሬ የህል መጋዘን ውስጥ እህል ሊጭን ለመጣ የአይሱዙ ሹፌር ሁኔታውን ነግረው ወደዚህ ይዞኝ እንዲመጣ እንዳደረጉና ሆስፒታል አድርሶኝ እንደሄደ ወደ ራሴ ስመለስ ያገኘኋቸው ዶክተሮች ነገሩኝ ።

ከዛን ግዜ ጀምሮ ለነብሱ ባደረ አንድ ደግ ሰው በተሰጠችኝ በዚች ነገር እየተንቀሳቀስኩ እድሜዬን በልመና አሳለፍኩ።

ለምኜ ሳንቲም የምቀበልባትን
ቆርሼ የምጎርስባትን መቀመጫዬን የምገፋባትን እቺን እጄን ባትተውልኝ እንዴት እሆን ነበር እላለሁ አንዳንዴ።
ዛሬም እዛው የተለመደው ቦታዬ ላይ ስለምን አገኛችሁኝ። ከልመና ያውጣችሁ ልጆቼ ።

ከኔ ታሪክ ከተማራችሁ•••
መርጣችሁ ስሙ ልጆቼ !። መርጣችሁ እሺ በሉ!።
አሉ ፍለፍታቸው የተቀመጥነው እኔ እና እህቴ ፍታችን በእንባ ታጥቧል
ይህን ታሪክ ያጫወቱን ነገ በምንዘክረው የአባታችን ሰባተኛ ሙት አመት ወይም ተስካር ላይ እናቴ የኔቢጤዋችን ብቻ ለማብላት በመወሰኗ ከዛሬ ከዋዜማው ጀምረን እኔ እና እህቴ አዲስ አበባ ውስጥ በየቦታው የወደቁ የኔቢጤዋችን ወደ ቤት ይዘን እንድንመጣ ስላዘዘችን ። አቅማችን የፈቀደውን ያህል የኔቢጤዋች ወደ ሰፊው የመኖሩያችን ግቢ ስናመጣ መሀል ሚክሲኮ አከባቢ ዊልቸር ላይ ተቀምጠው ሲለምኑ ያገኘናቸው ሁለት እግርና አንድ እጅ የለላቸው እድሚያቸው ወደ ሰማንያዎቹ የሚጠጋ ጋሽ ፍልፍሉ ናቸው ።

ፈጣሪ እሄን ታሪክ ለኛ መማሪያ ይሆን ዘንድ እስኪነግሩን ያቆያቸው ይመስል እኔና ታናሽ እህቴ በአባ ፍልፍሉ ታሪክ ልባችንን እንዳዘነ እምባችንን ከፊታችን ላይ ጠራርገን ከጠላውም ከምግቡም ግቢ ውስጥ ላሉት የኔ ብጤዋች አባ ፍልፈሉን ጨምር ስናበላ ስናጠጣ አምሽተን ወደ ቤት ገባን ይህ በሆነ ከሰአታት ቡሀላ ከምሽቱ አምስት ሰአት ላይ ጠላ እየጠጡ በመሀል ትን አላቸው አባባ ፍልፍሉን ።

ትንታቸው እየባሰ ሲርርርር ሲርር ሲሉ አጠገባቸው የነበረ ሌላ የኔብጤ "ኧረ የሰው ያለህ " ጮኸ እኔና እህቴን ጨምሮ እቤት ውስጥ የነበርነው ተሯሩጠን አጠገባቸው ስንደርስ አባባ ፍልፈሉ እንዲህ አሉ •••

" ጠላው አይደለም ትን ያለኝ ልጆቼ እሷ ነች ያነቀችኝ ! አልተርፍም ልጆቼ! አልተርፍም ! ያልኳችሁን አትርሱ
ከኔ ታሪክ ከተማራችሁ•••
መርጣችሁ ስሙ ልጆቼ! መርጣችሁ እሺ በሉ!!።
አባቴን ከምሰማ እናቴን ሰምቻት ቢሆን ይሻለኝ ነበር!"
የአባ ፍልፈሉ የመጨረሻ እስትንፋሳቸው ንግግር።

💫ተፈፀመ💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍4
#እህቴን_ሸጥናት!!


#ክፍል_አንድ


#በጥላሁን

ወደ ሀዋሳ ለመሄድ ያኮበኮበው ሚኒባስ ሞጆ መስቀለኛ ላይ ቆሟል።
ጋቢና ሁለት ወጣት ሴቶች ተቀምጠዋል ከጋቢና ጀርባ ባለው ወንበር ላይ እድሚያቸው ገፋ ያለ ባልና ሚስቶች ሲቀመጡ•••

መሀለኛው ወንበር ላይ የ 18 አመት ልደቷን ካከበረች ከሶስት አመት ብዙ ያልተሻገረች ።
ከልጅነት ወደ አቅመ ሂዋንነት ገብታ ያላበቃች ። ለመላ አካላቷ ከፈጣሪ የተቸራት ውበት ተገልጦ ያላለቀ በመሆኑ ከእለት ወደ እለት ወገባ እየቀጠነ ዳሌዋ እንደፅጌሬዳ አበባ እየፈነዳ እንኳን ወጣት ወንድ ስድስት ልጅ የወለደ ሽማግሌ ባጠገቧ ካለፈ ቡሀላ አንገቱን ጠምዝዞ ዞሮ ደግሞ ደጋግሞ ለማየት የሚያስቆመው ምንም አይነት ሀይል እንዳይኖር የሚያስገድ ምትሀታዊ የውበት ሀይል ተላብሷል ይህ ውብ ዳሌዋ በተመጠነ ርቀት ግራና ቀኝ ሲንገጫገጭ አገጩ አብሮ የማይንገጫገጭ ወንድ በፀሀይም በባትሪም ተፈልጎ አይገኝም።

አይን ውስጥ ለመግባት ተቸግረው የኖሩት ጡቶቿ ዳርና ዳር ተቀባብለው ሲታዩ እይታን የሚፈትን ህቡእ ጨረር ይተፉ ይመስል ድንገት ያያቸው ወንድ ሁሉ•••
ልቡ ስንጥቅ አፎቹ ሳያስቡት ሙልት በምራቅ እስከዛሬ ከነበሩት ምራቆች እሷን እንዳየ አፉ ውስጥ የመነጨው ይህ ምራቅ ብሎት ጥፍጥ አጣጥሞ የማይውጥ ወንድ ማግኘት አይቻልም ባይባልም ይከብዳል ። ፀጉሯን አንዴ ወደ ምስራቅ አንዴ ወደ ምእራብ እየበተነች በውብ ጥርሶቿ ፍልቅልቅ ስትል እንኳን ያያት ወንድና ሴት እራሷንም ሳያስደነግጣት አይቀርም።

የጠየቃት የለም እንጂ ስለውበቷ ምን እንደሚሰማት የጠየቃት ቢኖር እሷ እራሷ የቁም መስታወት ፊት ለፊት ቆማ የራሷን ውበት ስትመለከት ያ ሁሉ የውበት ዝናብ እሷ ላይ መርከፍረፉን ማመን እየተሳናት መስታወት ውስጥ ያየችውን እይታዋን ለማረጋገጥ በእጆቿ ከላይ ወደታች •••
በመጀመሪያ አይኖቿን ነካ •••ዝቅ ትልና ከንፈሮቿን በሁለት ጣቶቿ ከፈት •••አንገቷን ዳበስ••• ቀልቁል ወርዳ ጡቶቿን ያዝ ለቀቅ••• ደሞ ወደ ታች ፈቀቅ ዳሌዋን ነቅነቅ••• በጣቶቻ ጨበጥ ጨመቅ እያደረገች መስታወት ውስጥ ያየችው ውበት በአካል እሷ ላይ መኖሩን ሳታረጋግጥ እንደማትተኛ ትነግረው ነበር።

ይቺ ልእልት ነች እንግዲህ ወደ ሀዋሳ ለመሄድ ሰው እስኪሞላ በሚጠባበቀው ሚኒባስ ውስጥ መሀለኛው ወንበር ላይ ብቿዋን የተቀመጠችው።
ረዳቱ ሚኒባሱ ሞልቶ እስከሚሄድ የቸኮለ ይመስላል ለሰከንዶች ሳያርፍ ይጣራል (ዝዋይ -ሻሸመኔ-ሀዋሳ የሞላ ነይ እሙዬ ሀዋሳ ግቢ ሞልቷል! አንዲት ቀጭን ጠቆር ያለች ሴት ገብታ የመጨረሻ ወንበር ጥግ ላይ እንደተቀመጠች ወድያው ሌሎች ሁለት ወንድ እና አንድ ሴት ባንድ ላይ መጥተው ተከታትለው ገቡ ።

ወንድ ቆንጂየዋን ልጅ ገና በመስታወት ውስጥ እንዳያት ነበር የደነገጠው አጠገቧ መቀመጥ ፈለገ ወደ ጫፍ ጠጋ አለች። ሆን ብሎ እየታከካት አልፎ ጥግ ላይ ተቀመጠ ።
ረዳቱ መጮሁን ቀጥሏል ። ከናዝሬት ወደ አዲስ አበባ የሚሄድ ዶልፊን እየተክለፈለፈ መጣና ቆሞ ሰው እሚጭነው ሚኒባስ አጠገብ እንደደረሰ ቆመ።

ሁለት ሴቶች ወረዱ ቀደም ብላ የወጣችው ሽቲ የለበሰች አይኗ ጎላ ጎላ ያለ መካከለኛ ቁመትና ውፍረት ያላት ሴት ስትሆን በቀኝ ጉንጯ የጫት ተርዚና እንደወጠረች ተከትላት ከወረደችው በዛ ያለ ጫት ከያዘች ጓደኛዋ ጋር መንገድ ላይ የጀመረችውን ወሬ እያወራችላት እና እየተሳሳቁ ወደ ሀዋሳ የሚሄደው ሚኒባስ ውስጥ ተያይዘው ገቡ ጫት የምትቅመው በፀጥታ የተሞላውን የዚህኛውን ሚኒባስ ድባብ ለመቀየር የፈጀባት ግዜ ተደላድላ እስክትቀመጥና አፏ ውስጥ ያለውን በውሃ ሉሉ አድርጋው ሌላ ጫት ቀንጥሳ እስክትጎርስ ብቻ ነበር።

"እዚህ ሚኒባስ ውስጥ የሚቅም ካለ ራብሳ መጠየቅ ይችላል ጫታችን ብዙ ነው !" አለች ሁሉም ወደሷ ተመለከቱና ተሳሳቁ። አብራት የመጣችው ሴት ረዳቱ በትርፍ ያስቀመጣት ቦታ አልመች ብሏት እየተቁነጠነጠች "ኧረ አንቺ ዝም በይ " የሚል መልክት በምልክት ስታሳያት
"ምን ችግር አለው የኛ ህዝብ ይሉኝታ ያጠቃዋል ጫቱን ሲያየው ለመቃም ተወስውሶ ፈርቶ ዝም ያለ አይጠፋም ብዬኮነው" ከማለቷ
"ልክ ብለሻል እንቅማለን ራብሽና ራብሽን " አሉ ከሴቷ ጋር የመጡት ሁለት ወጣት ወንዶች ። ባለጫቷ ፈጠን ብላ " እሄንን ነውኮ ያልኩት በሉ እንኩ" ብላ ስትሰጣቸው ሚኒባሱ ውስጥ ያልሳቀ ቢኖር ከሹፌሩ ጀርባ የተቀመጡት በድሜ ገፋ ያሉ ባልኖ ሚስቶችና በትርፍ ገብቶው አጠገባቸው ተንጠልጥለው የተቀመጡት ሙሉ ሽበት የወረሳቸው የድሜ ባለ ፀጋ አዛውንት ብቻ ናቸው። አዛውንቱ ሰውዬ ጫት የምትቅመውን ሴት ገልመጥ አደረጓት።

ፀጥ ብሎ የነበረው ሚኒባስ ተሟሟቀ ጫወታው ደራ ። ረዳቱ ገብቶ በር ዘጋ ሹፌሩ ቀበቶውን አስሮ ሞተር እንዳስነሳ ። አንድ ነጭ ላንድክሩዘር መኪና እያሽከረከረ የመጣ ፈረንጅ ወደ ሚኒባሱ እየተጠጋ እጁን በማውጣ ያዘው አትሂድ የሚል ምልክት ለሹፌሩ ስላሳየው ግራ በመጋባት ነዳጁ ላይ ያለውን እግሩን ሳይጫን ጠበቀው ።
ፈረንጅ በፕላስቲክ መሰል ማሸጊያ የያዘውን ኢንጆሪ ይዞ በሚኒባሱ በር በኩል ሲመጣ የሚኒባሱ ረዳት በሩን ከፈተው። ከወጣትነት ወደ ጉልምስና ሊሸጋገር ድንበር ላይ የደረሰው መልከመልካም ፈረንጅ ጠጋ አለና ኢንጆሪውን በሁለት እጆቹ ይዞ ሚኒባሱ ውስጥ መሀለኛው ወንበር ላይ ወደተቀመጠችው ቆንጆ ሴት በመዘርጋት " ካን ዩ አክሴፕት ማይ ጊፍት ፕሪቲ ገርል ፕሊስ!" ልጅታ እጃን ዘርግታ ከመቀበል ተቆጠበች ሁሉም ግራ ተጋባ ። ጥያቄውን ደገመው ልጅቷ አሁንም እጇን አልዘረጋችም አልተቀበለችውም።
እሄን ግዜ " ታውቂዋለሽ የኔ ልጅ?" አሉ ሽበታሙ አዛውንት " ኧረ አላውቀውም እኔም ከናንተው ጋር አሁን ገና ነው ያየሁት" አለች
" እንዴ ባታውቂውስ ፈረንጅ እኮ ነው ይልቅ በጥዋት ያለሽበት ድረስ ሰተት ብሎ የመጣውን አሜሪካ ወደ ምትባል ገነት ወደሆነች ሀገር መግቢያ ቁልፍ የያዘ ሪስቅ አትግፊ ተቀበይው እዚ እንደሰርዲን ሚኒባስ ውስጥ ታጭቆ መሄድ አልሰለቸሽም እንዴ ይልቅ ተቀበይውና ወርደሽ መኪናው ውስጥ ግቢ እሄ እድል አያማጥሽ!" አለች የምትቅመዋ ሴት

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍5
#እህቴን_ሸጥናት!!


#ክፍል_ሁለት


#በጥላሁን

" እንዴ ባታውቂውስ ፈረንጅ እኮ ነው ይልቅ በጥዋት ያለሽበት ድረስ ሰተት ብሎ የመጣውን አሜሪካ ወደ ምትባል ገነት ወደሆነች ሀገር መግቢያ ቁልፍ የያዘ ሪስቅ አትግፊ ተቀበይው እዚ እንደሰርዲን ሚኒባስ ውስጥ ታጭቆ መሄድ አልሰለቸሽም እንዴ ይልቅ ተቀበይውና ወርደሽ መኪናው ውስጥ ግቢ ይሄ እድል አያማልጥሽ!" አለች የምትቅመዋ ሴት •••
እረ ልጄ ተይ ልጅቷን አታጣድፊያት በሰው ህይወት እንዲህ አቅልሎ መወሰን በጎም አይደል እናንተ ሰዎች እስቲ ቢያንስ በራሷ መንገድ ትወስን ይቺ ልጅ እኮ ሰው እንጂ እቃ አይደለችም !" አሉ አዛውንቱ ልጅቷ በመውረድና ባለመውረድ ስትወዛገብ ሲመለከቷት ሁኔታው አላምር ብሏቸው።
ሹፌሩ ተበሳጨ "ሰአት አትግደይብኝ እናቱ ወይ ተቀበይው ወይ ረዳቱ በሩን ይዝጋውና እንሂድ"
ከቦታዋ ላይ ሳትነሳ እንጆሪውን ተቀበለችው ፈረንጁም አመስግኖ ወደ መኪናው ሄደ።

የሚኒባሱ በር ተከረቸመ ።ጉዞ ወደ ሀዋሳ ተጀመረ።
ፈረንጁም ላንድክሩዘር መኪናውን ካቅም በታች እየነዳት ከሚኒባሷ ጀርባ በቅርብ ርቀት መከተል ጀመረ።

"እሄ ነጭ ፎንቃ ገብቶለታል የሚፋታሽ አይመስለኝ እየተከተለን ነው ሲል " ሁሉም ዞረው ተመለከቱ እውነትም ተጠግቶ እየተከተላቸው ነበር።
"ኧረ ተይ አንቺ ልጅ እሄ ፈረንጅ ትግስቱ አልቆ ካጠገባችን ከተሰወረ ቡሀል ቆጭቶሽ እንደ በረዶ ከምትማሚ አሁኑኑ ካይንሽ ሳይርቅ ወስኚ"
ልጅቷ ከውጪ እንደምታምረው ውስጣዊ ማንነታ ያን ያህል አልነበረም ምክንያቶቹ ደግሞ እድሜ ፣ አስተዳደግ እና አከባቢያዊ አመለካከት ያሳደሩባት ተፅእኖዎች ናቸው በዚህም ምክንያት ጫት ቃሚዋ ስታነሳሳት ለመሄድ ትነሳሳና ሽማግሌው ሲቃወሙ መልሳ በረድ ትላለች የራሷ የሆነ አቋም አልነበራትም ንፋሱ ወዳወዛወዛት ትወዛወዛለች።

ሁለቱ ከምትቅመው ላይ ጫት የተቀበሉት ወጣቶች እና ሴቷ ሂጂም አትሂጅም ቢሉ "ምናገባህ! ምናገባሽ! አናንተ ናችሁ እንዴ በኔ ሂወት ወሳኙ ብትለኝስ ብትለንስ " በሚል ሀሳብ ፈርተው ጥጋቸውን ይዘው ቢቆዩም ልጅቷ በውጪ ከሚታየው አስደንጋጭ ማራኪ ውበቷ ውስጥ ያለው ማንነቷ ገና ያልበሰለ መሆኑን ከሁኔታዋ ስለተረዱ የጫት ቃሚዋን ሀሳብ ደጋፊ ሆነው ክርክሩን ተቀላቀሉ።

ጫት እምትቅመው ወደአዛውንቱ ሰው እጇን እያወዛወዘች "አባባ እኔ በበኩሉ እሄ ወግ ባህል ስርአት እያላችሁ በማይመለከተው ቦታ ሁሉ እያስገባችሁ የራሳችሁን ግዜ ተጠቅማችሁ በኛ ግዜ እንደፈለግን እንዳንሆን በወግና ባህል ሰበብ በማይበጠስ ሰንሰለት እጅና እግራችንን አሳስራችሁ ቆማ ቀር ሴት የምታበረክቱበት አካሄዳችሁ በፍፁም አይመቸኝም አይገርሞትም።

በዚህ ግዜ! ሽበታሙ ሰውየ ብቻ ሳይሆኑ ከጎናቸው የተቀመጡት እስካሁን ያልተነፈሱት እድሜ ጠገብ ባልና ሚስቶች ተነሱባት ጫት ቃሚዋ ላይ ።
" ልጅሽ ብትሆን አንድም ቀን አይተሽው ለማታውቂው ሰው ይሁን አውሬ ላለየሽው ሰው አሳልፈሽ ትሰጫት ነበር ! ስላንቺ አይመለከተንም ልጅቷን ወደሳት ለመገፍተር? ምን አጣደፈሽ ?ሌላ አላማ አለሽ ? ተረባረቡባት•••

ፈረንጁ በዚህ መሀል ፍጥነት ጨመረና በሚንባሳ ጎን ትይዩ እየሄደ አንገቱን አውጥቶ በሚኒባሱ መስታወት ወደ ውስጥ ለልጅቷ ከንፈሮቹን የእጆቹ ጣቶች ላይ አስቀምጦ እፍፍፍ ብሎ ላከላትና እስም እንደንፋስ ካጠገባቸው እፍፍ ብሎ ጥሏቸው ሽምጥ ጋለበ ። የልጅቷ ፊት ተቀያየረ ።
በወጣቶቹ በኩል ጩኸት በረከተ •••
"አቦ ዝም ብላችሁ ነው እሄን የመሰለ እድል ያስመለጣቹሀት
አመት አወቀችው አንድ ቀን አወቀችው ምን ልዩነት አለው?
አመትም ቢሆን የሚጀምረው ባንድ ቀን ነው!
አንድ ብለው ሳይጀምሩ አመት የሞላቸው አሉ? እስቲ ንገሩን ?
"ህልም ተፈርቶ ሳይተኛ አይታደርም ይላል የኛው አባባል እንዲህ ቢሆንስ እንዲያ ቢሆንስ ብሎ መጥፎ መጥፎውን ከማሰብ እሄ ሰውዬ እሷ ባታውቀውም እሱ ለብዙ ግዜ ሲከታተላት የቆየ አፍቃሪ ነው ብሎ ደግ ደጉን ማሰብስ አይቻልም ያለው ማነው?
በተለይ ጫት ቃሚዋ የፈረንጁ መሄድ እጅግ በሚገርም ሁኔታ ነበር ያንገበገባት ወደ ልጅታ ተነስታ ለመሄድ እየዳዳት •••
" ቆጨሽ አደል ፉትሽ ያስታውቃል አሁንም መጠቀም ከፈለግሽ እድሉ አለሽ ብዙ አራቀንም ሹፌር በናትህ በመጨረሻው ፍጥነት ንዳው እንድረስበት!" ስትል•••
"እንዴ ኧረ ልጆች አሳዳጊዎች ነን እንዳትገለብጠን !ቀስ ብለህ ንዳ ሹፌር ካበዱት ጋር አብረህ አትበድ የኔ ልጅ ቀስ እያልክ ንዳ!" አሉ ባልቴቷ
"እቦ መሞት ካለብን ሮጠም ቆመም መሞታችን አይቀርም " አለች ቃሚዋ በንዴት
ለደቂቃዎች ሁሉም በተከራከሩበት ሀሳብ ዙሪያ እያሰላሰሉ ፀጥታ ሰፈነ በመሀል አንድ ኩርባ መንገድ ላይ ሚኒባሱ እጥፍ እንዳለ ፈረንጁ መኪናውን ካንድ ዛፍ አጠገብ አቁሟት ጥቁር መነፀሩን እንደገረገደ እግሮቹን አጣሞሮ ዛፉን በመደገፍ የህንድ አክተር መስሎ ቆሟል ። ተቀወጠ ።
"ያውና!
ያውና!
ያውልሽ ያው ፈረንጅ "
ሚኒባሷን ሶስት እግሯን ሰቅለው ባንድ እግሯ አቆሟት ማለት ይችላል ።
ሚኒባሱ ፈረንጁን ሲያልፈው ተንጫጩ አቆመው ውረጂና ሂጅ ጨቀጨቋት አዛውንቱ ሰውዬ በሩን ተደግፈው አለቅ ሲሉ ጫት ቃሚዋ የሚኒባሷን የውሀላ በር ከፍታ ልጅታን በዛ በኩል አስወጧት
"ለማንኛውም ስልኳን ተቀበያት አለች ከወንዶቹ ጋር የመጣችው ሴት ጫት ቃሚዋን ።
ተቀበለቻት ።
ሚኒባሱ ፊት ፊት ፈሩንጅ እና አጠገቡ የተቀመጠችው ቆንጆ ሀበሻ ያሉበት መኪና ከውሃላ ሆኖ ጉዞ ቀጠለ።
" ግን በምን ይግባባሉ?" አለች ጋቢና ከተቀመጡት አንዷ
ጫት ቃሚዋ ዘወር ብላ ተመለከተችና " እሄው እየሳቀች እኮ ነው ባይግባቡ ትስቅ ነበር ደሞ የስ እና ኦኬ ማለት ምን ይከብዳል"
ፈረንጅ ከቆይታ ቡሀላ ያን ውሃ የመሰለ መኪና ባየር ላይ እያከነፈ ልጅቷን ይዞ ሚኒባሷን ጥሎ ከአይናቸው ተሰወረ። እሄን ግዜ ከልጅቷ አጠገብ የነበረው ወጣት•••
"እስቲ ለማንኛውም ስልኳን ስጪኝ ልደውልላት" አለ
"አዋ ደውልላት እስቲ በናትህ አልችና ስልኳን ሰጠችው ጫት የምትቅመዋ ሴት።
ቁጥሩን ስልኩ ላይ ከትቦ ሲደውል ያየውን ማመን አልቻለም ነበርና•••
" እንዴ ያባቴ ስም ወጣኮ ምንድን ነው እሄ ስልክ እስቲ ደግመሽ ንገሪኝ "
ደግማ ነገረችው ልክ ነው ያባቱ የድሮ ስልክ እየተርበተበተ ቁጥሩ ላይ ሲደውል ተነሳ
"ሄሎ " አለች ልጅቷ "
ያባቱን ስም በመጥራት ታውቀው እንደሆን ሲጠይቃት ።
"አዋ አባቴኮ ነው እንዴት አላውቀውም ምን አይነት ጥያቄ ነው !"አለችው •••
ስልኩን ከጆሮው ላይ ለቀቀውና "አባቴ ነው አለችኝ አባቴ ከናቴ ውጪ የወለዳት እህቴ ነች ማለት ነው ልጅቷ " አለ
ሹፌሩ በሰማው ነገር ደንግጦ ሲጢጢጢጥ አደረገና ሚኒባሷን ገተራት••

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍2
#እህቴን_ሸጥናት!


#ክፍል_ሶስት (የመጨረሻው ክፍል )


#በጥላሁን

ጫት ቃሚዋ ልታምነው አልፈቀደችም
"አቦ ዛሬ ደግሞ መቃም ሳይጀምር የሚመረቅን ሰው ነው እንዴ ያጋጠመኝ ! ወንድሜ ብላ ስላወራችው እህቱ የሆነች መሰለው እንዴ !
ኧረ ጓደኛዬ አምጪው እስቲ ያንቺን ስልክ የኔ ጨላ ስለለው ደውልላት ብዬ ቁጥሯን ብሰጠው ያጃጅለናል እንዴ! ባንቺ ልደውልላትና አጠገቧ የነበረው ልጅ ገና ፈረንጅ ከመጥበሷ እህቱ አርጓት እንዳረፈው ነግሬ ላስቃት በናትሽ አምጭው ስልክሽን !" አለች ሳቅ እየታገላት።

ሰጠቻት። ደወለች•••
"ሄሎ የኔ ቆንጆ እንዴት ነው ምቾቱ ?
ደሞ አጠገብሽ የነበረውን ልጅ ምን ብለሽው ነው? ባክሽ ! መጀመሪያ ቁጥርሽን ሰጥቼው ስልኩ ላይ እንደፃፈው ያባቴ ስም ወጣ ሲለን ምርቃና ነው ብለን አለፍነው ሲያዋራሽ ጭራሽ ብሶበት ያባቴ ልጅ እህቴ ነች ብሎ በሳቅ ሊገለኝ ፈረንጅ መጥበስ ወንድም ያበዛል አየሽ ኪኪኪ•••"
የልጅቷ ጥያቄ ሳቋን ባጭር ቀጨው•••
" ያባቱ ስም ማነው?አለቻት።
"እንዴ አንቺም ተጠራጠርሽ እንዴ ?"አለችና ልጁን ጠይቃ ነገረቻት
" አመሰግንሀለሁ አምላኬ ! ልክ ነው ወንድሜ ነው! በብቸኝነት ስሰቃይ አድጌ አባቴ ወንድም እንዳለኝ ከነገረኝ ጀምሮ ስንት አመት ሙሉ ነገ ዛሬ እያለ አሳቀቀኝ !ፈጣሪ ፍቃዱ ከሆነ ሰዎች ረድኑንም አልረዱንም በምክንያት ምኞታችንን እና ፍላጎታችንን ለማሳካት የማይታሰበውን አጋጣሚ እውነት ያደርገዋል ። ስሙ ዳግም ነው አይደል?"
እኔ ምን አቅልሻለሁ ስምህ ዳግም ነው እንዴ? ስትለው በድንጋጤ እንደፈዘዘ በአውንታ ጭንቅላቱን ነቀነቀ።

ጫት ቃሚዋ ጩኸቷ ረገብ አለ። ቀዝቀዝ አለች። በረደች።
አዋ አለኮ ወንድምሽ ነው ማለት ነው" እያለቻት በመሀል ድንገት ፈረንጁና ልጅቷ መጨቃጨቅ ጀመሩ ።
ጫት ቃሚዋ ተደናግጣ "እንዴ ምን ሆኑ አሁን ባሁን!" እያለች ሁሉም እንዲሰሙ የስልኩን ድምፅ አጎላችው።
"ሄይ ኢት ኢዝ ኢነፍ ስቶፕ ቶኪንግ ኤንድ ጊቭ ሚ ዩር ፎን" አለ በቁጣ ፈረንጁ
" አቅርቢው እስቲ ላውራው•••
ምንድን ነው ምትለኝ ቆይ እስቲ በናትህ ወንድሜን ላዋራው " የልጅቷ መልስ ነበር እሄን ግዜ ፈረንጅ እንግሊዘኛውን አሽቀንጥሮ የኛኑ አማርኛ ያዥጎደጉደው ጀመር••
"ትሰሚያለሽ አንቺ ልጅ ካሁን ቡሀላ ማንንም ማዋራት አትችይም ወሬሽን ተይና ስልኩን ለኔ ስጪ!" አላት
ልጅቷም ሚኒባስ ውስጥ ያሉት ሰዎችም እኩል ደነገጡ።

ፈረንጁ መኪናውን ድንገት ፍሬን አንቆ ሲያቆመው ከፊት መስታወት ጋር ከመላተም ቀበቶው የታደጋት ልጅ ጮኸች!
"ስልኩን አምጪ!" ብሎ በጥፊ ከመታት ቡሀላ ስልኳን ተቀብሎ ዘጋው።
ሚኒባሱ ውስጥ ድምፅ ማጉያ ላይ የነበረው ስልክ ብቻ ሳይሆን ሁሉም በድንጋጤ ፀጥ አሉ።

ወንድምየው ወይኔ እህቴ ከሷ ፍላጎት በላይ እኛ ነን እህቴን ገፍትረን ላውሬ አሳልፈን የሸጥናት እባክህ ሹፌር አፍጥነው እና ሻሸመኔ ፖሊስ ጣብያ እናመልክት" አለ እየተርበተበተ።
ፖሊስ ጣብያ እንደደረሱ ልጅቷ ሞባይሏን ከነጠቃት ቡሀላ ከዋናው ሞባይላ ውጪ ቦርሳዋ ውስጥ አነስ አና ረከስ ያለች ሞባይል ይዛ ስለነበር መጀመሩያ ወንድሟ የደወለላት ግዜ የወንድሟን ቁጥር ያኛው ስልክ ላይ ያለው ሲም ካርዷ ሙሉ ስለነበር እዚቺኛዋ ስልኳ ላይ ባለው ሲም ላይ ሳያስተውላት ይዛው ነበርና ሳያያት ቀስ ብላ ከቦርሳዋ በማውጣት ስትነካካ ድምፅ እንዳይሰማ ፈጠን ብላ ዝም በዝምታ የሰጧትን እንድትቀበል አፋን ከዘጋቻት ቡሀላ ፈረንጁ በስልክ ከሌሎች ጋር የሚያወራውን እየሰማች ለወንድሟ ያለችበትን ሁኔታ የሚገልፅ የድረስልኝ መልክት ፅፋ ላከች•••
"ወንድሜ እባክህ ድረስልኝ ስልኩን ከቀማኝ ቡሀላ መኪናውን አዙሮ ራቅ ወዳለ አንድ ጫካ ይዞኝ እየገባ ነው ስልክ ሲያወራ እንደሰማሁት ችግሩ ከአባታችን ጋር ነው ስልክ ደወለና •••
"" እዛው ናችሁ አደል ልጅቷን ይዧት እየመጣሁ ነው ። እኔን መጠቀማችሁ ልክ ነበር በቀላሉ ነውኮ ሳር እንዳየ በግ የተከተለችኝ አሁኑኑ ላቧታ ደውሉና ሰነዱ ላይ እንዲፈርም ንገሩት አልፈርምም የሚል ከሆነ ልጁን አቃጥለን ይህን ውብ ገላ ወደ ከሰል ቀይረን በፎቶ እንደምንልክለት አስረዱት ካላመነ ድምፃን እንደደረስኩ ይሰማዋል ሲል ነበር ፈርቻለሁ ወንድሜ የማልተርፍ ከሆነና መሞቴ ግድ ከሆነ ግን ለብዙ ግዜ ላየው ስመኝ የነበረውን አንተን ወንድሜን አጠገቤ ተቀምጠህ አይቼህ ስለሞትኩ •••
አልጨረሰውም ሞባይሉን ወርውሮ የፖሊስ ጣብያው ግርግዳ ላይ ለጠፈው እንክትክት አለ የእህቱን መልክት እጁ እየተንቀጠቀጠ ሲያነብ
እያዳመጡ የነበሩት ፖሊሶችና ሚኒባስ ውስጥ ለነበሩት ሰዎች ቆሌያቸው ተገፈፈ።
ጫት ቃሚዋ ሴት ሹልክ ብላ ካጠገባቸው ተሰወረች።
ጓደኛው ሌላ መልክት ብትልክስ ብሎ ስላሰበ ከተሰበረው ሞባይል ውስጥ ሲምካርዱን አወጣና እሱ ስልክ ውስጥ አደረገው።
ፖሊሶቹ በመደዋወል የፈረንጁ መኪና የት አከባቢ ላይ ሲደርስ ከዋናው መንገድ እንደወጣ ፍንጭ አገኙ።
ወንድሟ እና አብረውት የመጡት ሁለት ጓደኛቹ በመሆን ወደ ቦታው ሲንቀሳቀሱ ከጫት ቃሚዋ ሴት በስተቀር ሌሎቹ መልክም እድል ተመኝተውና ስልኩን ተቀብለው በመጡበት ሚኒባስ ወደ ሀዋሳ ሄዱ።
ፖሊሶቹ የመኪናውን ዳና እየተከተሉ መኪናውን አገኙት ነገር ግን ውስጡ ሰው አልነበረም የፖሊስ መኪናውም ከዛ በላይ የሚሄድበት መንገድ አልነበረምና
"ከዚህ ቡሀላ ያለው ስራ የኛ ብቻ ነው እናንተ እዚሁ ጠብቁን!"
በማለት ወንድሟን እና ጓደኛቹን እዛው ጥለዋቸው በተለያየ አቅስጣጫ በመሰማራት ጫካውን ወረሩት።
ከደቂቃዎች ቡሀላ የቶክስ ድምፅ ተሰማ ። ወድያው ከሻሸመኔ እየከነፈች የመጣችው አንቡላንስ በጭንቀት ወደ ሚፀልዩት ወንድሟ እና ጓደኛቹ ጋር ተጠግታ ቆመች ። ሁለት ፖሊሶች ተሸክመው ያመጧት ሴት ወደ አንቡላንሱ ሲያስገቧት ቀና አለችና ወንድሜ ብዙ አልተጎዳሁም እሺ ተርፊያለሁ አለችው።

💫ተፈፀመ💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍31