አትሮኖስ
286K subscribers
120 photos
3 videos
41 files
570 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ምርጫ_አልባ_ምርጫ


#ክፍል_አምስት


#በሜሪ_ፈለቀ

እኔ ወደ ህይወቱ ብቅ ማለቴን አክሎ ነገረኝ።

እናቱ በግልፅ “ስራህን ከቁስልህ መደበቂያ አድርገኸዋል። ያንተን
ድርቅናና የሟች ሚስትህን ትዝታ ማስታመም እየሰለቸኝ ነው::"
ብለውት ልቡ መድቀቁን ሲነግረኝ ግን ያቺ ከቀናት በፊት ሊያያት እንደማይፈልግ ሲሆንባት ለነበረችው ረቂቅ እየተናገረ አይመስልም።

"በዚህ ከቀጠልኩ እነርሱ እንደሚፈሩት ከዓመታት በኋላ የድርጅቱንም ሆነ የቤተሰባችንን ህልውና አደጋ ላይ ልጥለው እንደምችል ማሰቤ ይባስ ውጥንቅጥ ውስጥ ይከተኛል::" ሲለኝ
ይሄን ሀሳብ ለጥዝጠዛ ለማመቻቸት ወሳኙ ጊዜ መሆኑን አሳሰበኝ።

"ጥቅሙ የሚያመዝን ከሆነ ለምን በቤተሰቦችህ ሀሳብ አትስማማም?"

"አንደኛ አሳማኝ አይደለም፡፡ በግሌ ከማስተዳድራቸው ዘርፎች
በላይ ፋብሪካው ትርፋማ እየሆነ በመጣበት ወቅት በተለይ የእማዬ እንዲሸጥ መወትወት አልዋጥልህ ነው ያለኝ፡፡ ሁለተኛኀአባዬ ያስረከበኝን ምንም
ነገር ማብዛት እንጂ ማጉደል አልፈልግም።

መቃብሩ ጋር ጥዬው የሄድኩ ዕለት ራሱን ስቶ ሀኪም ቤት ገብቶ ነበር፡፡ ማረፍ እንዳለበት በሀኪም ስለታዘዘ ለወንድሙ
ውክልና ፈርሞለት እረፍት መሆኑን እና ላይደውልልኝ ከራሱ ጋር ብዙ ቢሟገትም ቀኖቹ አላልቅ ብለውት አማራጭ ሲያጣ
እነደደወለልኝ ሳይደብቅ ነገረኝ።

አሁን ጓደኝነቴን አምነህ ብትቀበል ነው የሚያዋጣህ።"

"ምን ያህል “ኮስት ያደርገኛል?"

እንነጋገርበታለን::" አልኩት:: ፈገግ አለ፡፡ መስማማቱ ነው።

"ስለሴት ልጅ የምትወደውን ሶስት ነገሯን ንገረኝ እስቲ?" አልኩት እራት መብላት ጨርሰን ወደ ቤት እየሸኘኝ፡፡ ጠዋት
ወደ ላንጋኖ ልንሄድ ተቀጣጥረናል።

"እናትነቷን"

ሶስት ነው ያልኩህ::"

"እኔ ስለሴት ልጅ ይሄ የምለው የተለየ ነገር አልወድም። ራሷን ስትሆን፣ የራሷ እምነት ፣ የራሷ ፋሽን፣ የራሷ ኩራት! በቃ
የራሷ ነገር ሲኖራት ራሷን ስትሆን ደስ ትለኛለች:: የሰው ልጅ ምርጥ እየሆነ የሚመስለኝ ራሱን ወደ መሆን ሲያድግ ነው።"

“ለምሳሌ?"

“ለምሳሌ እንዳንቺ!! እራት ቀጥሬሽ ቁምጣ በቲሸርት ለብሰሽ
ትመጫለሽ" አለኝ ቁምጣዬን እያየ::" ቤዚካሊይ የራስሽ የሆነውን ነገር ሰው ለማስደሰት ብለሽ አትቀይሪውም::"

"በቻይንኛ ወድጄሻለሁ እንደማለት”

ባህሪሽ ደስ ይለኛል ማለት በቻይንኛ ወድጄሻለሁ እንደማለት መሆኑን አላውቅም ነበር።" ፈገግ አለ።"አንቺስ?"

"እኔ ምን?"

"አባትነቱን"

"ሶስት ነው ያልኩሽ?" አለ እየተንፈቀፈቀ::

"ባክህ የወንድ ሁሉ ተምሳሌቴ ወንድሜ ነው፡፡ ዓይንህን ብቻ አይቶ ጥልቅ ስሜትህ የሚገባው አይነት ነው። የወንድ መለኪያዬ እሱ ነው።

ወዲያው ስልኬ ጠራ። አያሌው ነው። ኤፍሬምን ቀና ብዬ አየሁት። አንሺው፣ ችግር የለውም::” እንደማለት ምልክት
አሳየኝ፡፡ ለኔ ግን የገባኝ፡፡ 'አምንሻለሁ እንዳለኝ ነበር:: አነሳሁት።

"እድል ካንቺ ጋር የሆነች ይመስላል፡፡ ተጠቀሚባት:: እንደሌሎቹ
ወንዶች አጣጥሞሽ ሲበቃው ከነድህነትሽ ጥሎሽ እንዲሄድ
አትፍቀጂለት" አለኝ፡

፡መልስ ሳልሰጠው ዘጋሁት።

"ምን እያሰብክ ነው?" አልኩት ላንጋኖ ሀይቁ ዳር አሸዋው ላይ እንደተቀመጥን፡፡ እኩለ ለሊት ሆኗል፡፡ ከመጣን ሶስተኛ ቀናችን ነው።

"አንቺን" አለኝ፡፡ በኤፍሬም ድምፅ ይሄን መስማት ብዙ ነገር ነበር፡፡

"እቀፈኝ!"

ግን እንደዛ አላደረገም:: ከአጠገቤ ተነስቶ ከጀርባዬ በኩል እግሮቹ
መሃል አድርጎኝ ተቀመጠ። በግዙፍ ሰውነቱ ሙሉ ውስጡ ደበቀኝ። ከብዙ ክፋቶች የተጠበቅኩ መሰለኝ፡፡ አንገቴ ስር የሚሰማኝ ሞቅታ ትንፋሹ እጠብቅሻለሁ፣ አለሁልሽ' ያለኝ
መሰለኝ፡፡ የማንም ወንድ ገላ በዚህ መጠን ናፍቆኝ ማወቁን እጠራጠራለሁ
"እንግባ?" ከማለቱ እኔ ተነስቻለሁ። ገብቶታል።እንደህፃን ልጅ ብድግ አድርጎ ከመሬት አንስቶ እንደታቀፈኝ አልጋው ጋረሸ አደረሰኝ።

መች ነው እንዲህ ለሱ የተሰማኝ? ከዛሬ በፊት በነበሩት ቀናት?፣ከአዲስ አበባ ስንመጣ እግሮቹ ላይ እንቅልፌን ተኝቼ መኪና ሲነዳ?፣ ሀይቁ ውስጥ ስንዋኝ?፣ የጠረጴዛ ቴኒስ ስንጫወት?፣
ቼዝ ሲያለማምደኝ?፣ ካንፋየር አጠገብ እራት እየበላን ውስኪ ስንጠጣ? ክፍላችን ውስጥ በድሮ ሙዚቃ የድሮ ዳንስ ስንደንስ?እግሩ ስር አስቀምጦኝ ፀጉሬን ሲያበጥርልኝ ካርታ ተጫውተን አሸንፌው በውርርዱ አዝሎኝ ጊቢውን ዞር በአንዱ ወይም በሁሉም ሰዓት የተለየ ስሜት ተሰምቶኛል።

ቁርስ መብላት ደስ የሚለኝ ፍርፍር በሻይ ነው::" አለኝ ጠዋት እቅፉ ውስጥ እንዳለሁ።

"ፍርፍር? ፍርፍር? ስጋ ሳይኖረው?"

ቢኖረው ጥሩ! ባይኖረውም ከሌላ ምግብ ፍርፍር ምርጫዬ ነው:" አለኝ ከአልጋው ለመነሳት ያቀፈኝን እጁን በቀስታ እያነሳ።

"እንቆይ? እንደዚህ ትንሽ እንቆይ? አቅፈኸኝ ትንሽ እንተኛ?" አልኩት:: ተመልሶ አጥብቆ አቅፎኝ ተኛ።

መታቀፍ የተለየ ትርጉም እና ስሜት የሚሰጠኝ ነገር ነው። ለአቃፊው የምሰጠው ዋጋ የትርጉሙን ልኬት የሚያወጣና የሚያወርደው ቢሆንም ያቀፈኝ ሰው ስሜቴን ብነግረው ባልነግረውም ያጋባሁበት እነደሆነ ነው የሚሰማኝ።ባቀፈኝ ቅፅበት ሸክሜን የተጋራልኝ፣ ካለሁበት ትርምስ የደበቀኝ ነው የሚመስለኝ፡፡ ይሄን ትርጉም በትክክል የሚያሟላልኝ የእማዬና
የበርዬ እቅፍ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ተሰምቶኝ በማያውቅ ልክ የኤፍሬም።


ከሶስት ቀናት በኋላ ከራሴ እውነት ጋር መላተም ጀመርኩ::አያሌው እቤት ድረስ መጥቶ አስር ሺህ ብር አስቀምጦልኝ
መሄዱን በርዬ ነገረኝ፡፡

"እሺ ልመልስለት:: ከዛስ? ከዛ ምን እንብላ? ከዛ ለእማዬ ምን
እንሰርላት? ከዛ ገንዘብ ፍለጋ የማልወደው ገላ ላይ ልጣድ?
ንገረኛ?" ብሩን መልሺለት ስላለኝ ነው በርዬ ላይ የምጮኸው።ለኤፍሬም እውነቱን እንድነግረው ሲወተውተኝ፡፡
በርዬ አቀረቀረ:: አድርጌው እንደማላውቅ
ሁሉ ለገንዘባቸው ከምተኛላቸው ወንዶች ጋር መሆን ቀፋፊ ነገር ሆነብኝ፡፡

ከኤፍሬም ጋር የስራሁትን ፍቅር ማርከስ መሰለኝ፡፡ የሆነ ልክ ከኤፍሬም ጋር ከተኛሁ በኋላ ገላዬ የተቀደሰ ነገር መሰለኝ፡፡ ያንን ማርከስ መሰለኝ፡፡ በእርግጥ ኤፍሬምን ገንዘብ ብጠይቀው
ይከለክለኝ ነበር? አይከለክለኝም ይሆናል፡፡ በግልፅ ምክንያት
የአያሌውን ገንዘብ ብመልስለት ለኤፍሬም እውነቱን እንደሚነግረው አስፈራርቶኛል፡፡ በድብቅ ምክንያቴ ግን ኤፍሬም ጋር ያለኝ ነገር ከዚህ በፊት ከማውቃቸው ወንዶች ጋር እንደነበረኝ ስራ እንደሆነ እንዲሰማኝና እንዲቀልብኝ
አልፈለግኩም:: ሌላው አማራጭ ግን እንደገሃነም አስፈሪ ነው፡፡እውነቱን መናገር! ለኤፍሬም የቀረብኩህ ተከፍሎኝ ነውኀልበለው? ከዛስ? ጥሎኝ ሲሄድ ትርፌ ምንድነው? ፊልም ላይ
ብቻ ነው ይሄ የሚሰራው:: አባዬ ራሱን ያጠፋው የቤተሰቡን ምስቅልቅል መሸከም ስለከበደው ነበር:: ያንን የተሸናፊ ፊቱን ልረሳው አልችልም፡፡ እኔ እማዬንና በርዬን የራሳቸው ጉዳይ ብዬ
ህሊናን መምረጥ አልችልም።የኔ ህሊና
ንፅህና የቤት ኪራያችንን አይከፍልም ወይም የበርዬን ትምህርት ቤት ክፍያ
አያጠናቅቅም አልያም ለእማዬ ስንቅ አይሆንም።ህሊና በአገልግል አይቆጠርም።

ከኤፍሬም ጋር ሳንገናኝ የዋልንበት ቀን ጠፋ። እቤት ከማድርበት ከኤፍሬም ጋር የማድርበት ቀን በለጠ፡፡ ሀኪም ያዘዘለትን ሀያ የእረፍት ቀን አረፍንበት። አብሬው አሳለፍኩ፡ እሱ በትክክል ምን እንደሚሰማው ግን አሁንም ማወቅ አልቻልኩም:: ከነዚህ ቀናት በኋላ አሁን ጥያቄዬ ህሊና ብቻ አይደለም ኤፍሬምን ማጣት ማሰብ ያስፈራኝ ጀምሯል። ኤፍሬም ሊዲያ የሞተችበት
ረቡዕ ዕለት ሁሌም መቃብሯጋ እንደሚሄድ ስለማውቅ
👍61🔥1
#ምርጫ_አልባ_ምርጫ


#ክፍል_ስድስት


#በሜሪ_ፈለቀ

“ወንድ ልጅ! ስራ አልናፈቀህም ማለት እኮ ፍቅር አስይዤሃለሁ ማለት ነው።" አልኩት እንደመደነስ እያደረገኝ።

"አልወጣኝም::" አለ በሁኔታዬ ፈገግ እያለ፡፡

"ጉረኛ!! አታምንም አይደል?"

ስራ በጀመረባቸው ቀናት ለየት ያለ የምሳ ግብዣ ላይ አብሬው እንድሄድ ጋበዘኝ፡፡ ከአንድ ባለሀብት ጋር የንግድ ድርድር ነው።የባለሀብቱን ሚስት ተከትዬ መፀዳጃ ቤት ገባሁ:: ኤፍሬም
የገዛልኝ ቀሚስ ፕሮቶኮላም አድርጎኛል፡፡ እንደዛ የለበስኩት እርሱ በሰጠኝ ክብር ልክም ባይሆን የሚገባውን ላደርግላት
ስለፈለግኩ ነው:: የወንዶቹ ወሬ እንደኔ ካሰለቻት ከሰውየው ሚስት ጋር ቀላል ወሬዎች ተጫወትን። ከኔ የባሰች ለፍላፊ
ነገር ስለነበረች በደቂቃዎች ውስጥ ብዙ ነገር አወራችኝ፡፡ ወደ ጠረጴዛው ስመለስ የወንዶቹ ድርድር ቀልቤን ሳበው:: ባለሀብቱ ከነኤፍሬም የእንስሳት ማደለቢያ ማዕከል ወደውጪ የከብት ስጋ ለመላክ ነው በሚያዋጣቸው ድርሻ የሚደራደሩት፡፡ ሰውየው የሚያዋጣኝ ስድሳ አምስት በመቶ ድርሻ ሲኖረኝ ነው ብሎ ግግም አለ፡፡ የተቀረው ሰላሳ አምስት በመቶ ድርሻ የኛ ሊሆን
ማለት ነው። (ቡፍፍ! የኛ አልኩ እንዴ? እኔ ከስሙኝ ብዙ አወራ የለ? ባልስማ እለፉኝ፡፡) ኤፍሬም ሲያቅማማ አየሁት፡፡

የኛ ድርጅት አያዋጣውም።አርባ አምስት በሃምሳ አምስት ካዋጣህ መቀጠል እንችላለን፡፡" አልኩኝ ጣልቃ ገብቼ፡፡ ኤፍሬም ዘወር ብሎ የተናገርኩትን ባለማመን አየኝ፡፡

"እመነኝ እሺ ያዋጣዋል፡፡" አልኩት በጆሮው።

"እመቤት አንቺ የገባሽ አልመሰለኝም።" አለ ባለሃብቱ እንደማፌዝ እያደረገው።

“ምኑ ነው የገባኝ ያልመሰለህ? መልካም እንግዲህ፡፡ ሀሳብህን ከቀየርክ ደውልልን።" ብዬው ተነሳሁ:: ኤፍሬም ግራ በመጋባት ተከተለኝ። ሰውየው እየተበሳጨ ጠረጴዛውን ከነረተ በኋላ "እሺ ተቀመጡ!!" አለ።

"ምንድነበር ያደረግሽው?" አለኝ ኤፍሬም ተፈራርመው ከሆቴሉ ወጥተን መኪና ውስጥ እየገባን።

“ከሚስቱ ጋር የሴቶች ወሬ አውርተን ነበር። ብታያት ከኔ የባሰች ቀዳዳ ናት! ለባሏ በጣም አንገብጋቢ ድርድር መሆኑን ፣የሚወዳት ልጁን ልደት ትቶ እንደአምላክ ቀጠሮ የማይሰረዝ
ያለው ምሳ ላይ መምጣቱን ምናምን ነገረችኝ፡፡ አንተ ግን እንዴት አመንከኝ?

"አላውቅልሽም:: ሁሌም ሳምንሽ ከራሴ ጋር አልማከርም::" አለኝ እየገረመው አፍጥጦብኝ፡፡

ቆይ ግን የምር እስከምንድነው የተማርሽው?" አለኝ ለጥያቄው ተገቢ ይሆናል ያለውን ቃል እየመረጠ።

እውይ! አራተኛ ክፍል ሳይንስ መፅሃፍ ላይ እባብ በከለር አይቼ ደንብሬ እንደቀረሁ ነው::" መለስኩለት፡፡

'የምር? የምር ንገሪኝ?" አለኝ እየሳቀ፡፡ እስከ አስር መማሬን እና ውጤት ቢመጣልኝም ለመማር እንዳልተመቸኝ ነገርኩት።ገብቶት ይመስለኛል '
ለምን?” ብሎ አላጨናነቀኝም!

"የጭንቅላትሽ ከፍታ እኮ። ግን ማትሪክት የመንጣብሽ አይመሰልም።ብሎኝ የሽቶ እቃ እያቀበለኝ ቅድም ነው የገዛሁልሽ አለኝ።ሽቶውን ከፍቼ እያሸተትኩት ዝም ብዬ አየሁት፡፡

"አንተ ግን በእናትህ እመን ፍቅር ይዞሃል አይደል?" አልመለሰልኝም።ዝም ብሎ ብቻ ሳመኝ።

እስከማስታውሰው ማታ ደህና እደሪልኝ እንዲለኝ ጠዋት ደህና ዋይልኝ እንዲለኘሸ ስልኩን በናፍቆት የጠበቅኩትን ሰው
አላስታውስም፡፡ ኤፍሬም ሳይደውል ያረፈደ ቀን በእንቅልፍ ልቡ የእናቱን ጡት እንደሚፈልግ ህፃን ያንሰፈስፈኛል።
በስህተት ደህና ዋይልኝ ያላለኝ ቀን ቀኔ ደህና ቀኔ ደህና አይሆንልኝም የሆነ እሁድ ቀን ጠዋት ስልኩን እንደዘጋው ከሊ.ዲ.ያ ጋር ይኖር የነበረበት
ቤት ለመሄድ ታክሲ ተሳፈርኩ፡፡

እንዴት እዚህ መሆኔን አወቅሽ?" አለኝ የአጥሩን በር እየከፈተ።

"ደበረኝ አላልከኝም? ሲደብርህ ከዚህ ቤትና ከኔ ውጪ የትም እባክ መሄጃ እንደሌለህ አውቃለሁኣ።” መለስኩለት፡፡ አቀፈኝ።ወዲያውኑ ለቤተክርስቲያን የለበስኩትን ረዥም ቀሚስና ነጠላ
በጥያቄ እየሆኑ።

ዛሬ የዓመቷ ኪዳነ-ምህረት ናት፡፡”
ስለውም ጥያቄውን የጨረሰ አልመሰለም።


"ባክህ የእግዜር ሰው ሆኜ አይደለም። እማዬ ስለምታደርገው ነው::" አልኩት። ቤተክርስቲያን ሄደን አረፈድን። አመሻሹን
የሊዲያን አትክልቶች መኮትኮት ልምድ ስለነበረው ወደ ቤት ተመለስን። አበቦቿን የሚነካበት መንገድ ቅጠል ሳይሆን
የእርሷን ሰውነት እየነካ ነው የሚመስለው። እዛው ቤት ሳሎኑ ውስጥ ፍራሽ አንጥፈን አደርን ጠዋት እንዳልረብሸው ተጠንቅቄ ተነስቼ የእርሱን ሸሚዝ ብቻ ለብሼ ፍርፍር አበሰልኩለት።ሲነቃ የሚደሰት ነው የመሰለኝ።የተፈጠረው ግን ተቃራኒው ነው።አበደብኝ!የእርሷን ቦታ ለመተካት ያሰብኩት እራሴን እንደምን ቆጥሬው እንደሆነ አፈጠጠብኝ።

"እኔ እንዳልደርስበት የምትጠብቀው የህይወትህ ክፍል እንዳለ ይገባኛል እኮ የቀረብኩህ ስለመሰለኝ እንጂ እኔ ለሷ ያለህን ፍቅርና ዋጋ አከብርልሃለሁ:: ግን አበዛኸው....." አልኩት ትቼው ልሄድ እየለባበስኩ።

"ለሷ ልሰጣት የሚገባኝን የፍቅር ልክ አንቺ አትነግሪኝም::" አለኝ
ልሄድ መነሳቴ እንኳን ግድ ሳይለው።
ኡኡቴ እንደምትሉ አውቃለሁ። እኔም ማነኝ ብዬ እንዳስብኩ እንጃ! ሳይገባኝ ግን በሟች ሚስቱ ቀናሁ። ወደቤቴ
እንደሄድኩ ስልኬን አጠፋሁ።
የተፈጠረውን ለበርዬ ነገርኩት። የሚያባብለኝ ነበር የመሰለኝ፡፡
እሱ ግን ያለማቋረጥ ሳቀ፡፡ ከልቡ ሳቀ፡፡

"ምን ያስገለፍጥሃል? አሁን ይሄ ምን የሚያስቅ ነገር አለው?"

ፍቅር ይዞሻል!" አለኝ አንዳንዴ እንደሚያደርገው አንደታላቅ ወንድም እያየኝ፡፡

የማደርገው ሳይገባኝ ከበርዬ መፅሃፍቶች ውስጥ የሊዲያን መፅሀፍት ለይቼ አንዱን ማንበብ ጀመርኩ፡፡ በርዬ ይፅፋል። እኔ
አነባለሁ። በመሃል እናወራለን፡፡

ከሁለት ቀን በኋላ ስልኬን ስከፍተው ኤፍሬም ስምንት የይቅርታ መልዕክት ልኮልኛል። ደወልኩለት፡፡

"ላግኝሽ?"

“አሪፍ ምክንያት ካቀረብክ?"

ካንቺ ጋር መሆን ደስ ስለሚያሰኘኝ!"

“ቀሽም ምክንያት"

"ይህን አይደል መስማት የምትፈልጊው? አዎን ካንቺ ፍቅር

"እሺ ይቅርታ ልጠይቅሽ ስለምፈልግ

"ጭራሽ የወረደ ምክንያት"

"እሺ ስለናፈቅሽኝ"

"የት እንገናኝ?"

"ቢሮ ነኝ ነይና አብረን ምሳ እንወጣለን።"

"ቢሮ?"

አዎን!"

ሳየው ምን ያህል እንደናፈቀኝ ገባኝ፡፡ ስስመው በሩን እንኳን ያለመዝጋቴን ያወቅኩት ፀሃፊው ስትገባ ነው።ምሳ በልተን እቤቱ ይዞኝ ሄደ።እቃዎቹን በአዲስ እቃ ቀይሯቸዋል።
የቤቱንም ቀለም ቀይሮታል፡፡

"እርግጠኛ ነህ?" አልኩት በመገረም እያየሁት።

"እንደዚህ እርግጠኛ የሆንኩበት ነገር የለም::" መለሰልኝ።

"ይህን አይደል መስማት የምትፈልጊው? አዎን ካንቺ ፍቅር ይዞኛል።" አለኝ ከመቀመጣችን፡፡

ከንፈሩን ያለማቋረጥ ሳምኩት፡፡ ምክንያቱም ዝም እንዲለኝ ፈለግኩ።ገና መናገር እንደለመደ ህፃን እየቦረቀ ነው።
የሚያወራው። ድንገት መሳሙን አቁሞ "ሩካ?" አለኝ፡፡ ጥሪው ውስጥ ምንድነው አብሬ የሰማሁት? ልቤን ምን አስደለቀው? ሰውነቴን ምን አሞቀው?

"ወይዬ?"

“አንቺ ለኔ ከፈጣሪ እንደተላከ መላዕክ በመጥፎ ሰዓቶቼ ሁሉ ከጎኔ አገኝሻለሁ፣ እያስቀየምኩሽ እንኳን ትረጂኛለሽ:፡ እኔ ግን ላንቺ ጥሩ ጓደኛሽ እንኳን አይደለሁም::"

“በምን ምክንያት?" አልኩት፡፡

"ስላንቺ የማውቀው አንድ ነገር ቢኖር ለመኖር እንድጓጓ እንዳደረግሽኝ ብቻ ነው።"


"ታዲያ መላዕክ እኮ ጥሩም መጥፎም ቀን የለውም፡፡ አንተ ደስተኛ እንድትሆንልኝ ብቻ ከሆነስ የታዘዝኩት?" ይሄን በአፌ ልበለው እንጂ በእርግጥ
ለምን ስለራሴ እንዳልነገርኩት
ምክንያቴን
👍7
#ምርጫ_አልባ_ምርጫ


#ክፍል_ሰባት


#በሜሪ_ፈለቀ


ድጋሚ አንቺን ባጣ የሚተርፍ ልብ አይኖረንም።” አለኝ ቀጠለና፡፡ አሁን ራሴን ጠላሁት። ረቂቅ መሆኔን ተፀየፍኩት።
የእማዬ እና የአባዬ ልጅ፣ የበርዬ እህት መሆኔን አምርሬ ጠላሁት።ከእውነት መደበቅ አማረኝ ከእርሱ የተሻለ መደበቂያ ደግሞ የለኝም።

"ዝም ብለህ ሳመኝ!" አልኩት የሽሚዙን አንገትጌ በሁለት እጄ ይዤ። ከንፈሮቹ እስከዛሬ እንደሳምኳቸው ከንፈሮች ስጋ ብቻ አይደሉም፡፡ ስመውኝ ለልቤ የሚደምሩት ሀሴት አላቸው።
ለነፍሴ ሹክ የሚሏት ጥፍጥና አላቸው:: እጆቹ እያንዳንዱን የሰውነት አካሌን ሲነኩ ሰውነቱን መናፈቅ ብቻ አይደለም
የሚፈጥሩት ነፍሴ እንኳን ማቃሰቷ ይገባኛል።የገባኝ ነገር ከሌሎች ወንዶች ጋር ያደረግኩትን ወሲብ አይደለም ከኤፍሬም ጋር ያደረግኩት። ፍቅር ነው የሰራነው። ኤፍሬም እንደሌሎቹ
ወንዶች ስጋዬን ብቻ አይደለም የሚወስበው ነፍሴንም በስጋዬ
ቅኝት ውስጥ ያወሳስባታል።

"ንግስቴ ነሽ!" ይለኛል ሲያቆላጵሰኝ፡፡ እርሱ የሰጠኝን ክብር ማንም ወንድ ሰጥቶኝ አያውቅም።ያላስገባኝ የህይወቱ ክፍል የለም። ስራው፣ ቤተሰቡ፣ ቤቱ: በኩራት ከጎኑ ይዞኝ ሲዞር የምር ንግስቱ እንደሆንኩ ይሰማኛል፡፡ በማይገባኝ የስራ ጉዳይ እንኳን ሊያደርግ ያሰበውን ያማክረኛል።

እማዬና ዘሪሁን ከአያሌው ጋር አብረው ሊያፈነዱኝ ነው።"
አለኝ አንድ ማታ እቅፉ ውስጥ አድርጎኝ ዓይን ዓይኔን እያየ፡፡

"ለምን?" አልኩት ለመጠየቅ ያህል እንጂ አያሌው እናትየውና ወንድሙ እንደሚደግፉት በተደጋጋሚ ነግሮኛል።

"ምንም በማይዋጥልኝ ምክንያት የዚህ ፋብሪካ ድርሻ መሸጥ የቤተሰቡን ሰላም በጥብጦታል። እማዬን ላስቀይማት
አልፈልግም።" አለኝ። ኤፍሬም እናቱና አባቱ ተፋተው አሁን እማዬ የሚላቸው እንጀራ እናቱ ናቸው ያሳደጓት።በጣም ስለሚወዳቸው በስህተት እንኳን እንዲከፉበት አይፈልግም።ከወላጅ እናት በላይ ተንከባክበው እንዳሳደጉት አውርቶኛል። እርሱም ወላጅ እናቱን ከስንት አንዴ ከመጠየቅ ያለፈ ግድ የለውም።እማዬ የሚለው የእንጅራ እናቱን ነው።ወንድሜ የሚለውም የአባቱ ልጅ ሳይሆን የእንጀራ እናቱ ልጅ ነው።

"አባትህ ቢሆኑ ባንተ ቦታ ምን ይወስኑ ነበር?"

"በእርግጠኝነት አባዬ ቤተሰቡን ሳያማክር ምንም አይነት ትልቅ ውሳኔ አይወስንም። በተለይ እማዬን፡፡ አባዬም ቢሆን በዚህ
ጉዳይ መስማማቱን እጠራጠራለሁ።" ሲያስረዳኝ በቅንነት እና በፍቅር ነው።

አልፈልግም::" አለኝ፡፡ ኤፍሬም እናቱና አባቱ ተፋተው አሁን እማዬ የሚላቸው እንጀራ እናቱ ናቸው ያሳደጉት። በጣም
ስለሚወዳቸው በስህተት እንኳን እንዲከፉበት አይፈልግም::
ከወላጅ እናት በላይ ተንከባክበው እንዳሳደጉት አውርቶኛል። እርሱም ወላጅ እናቱን ከስንት አንዴ ከመጠየቅ ያለፈ ግድ የለውም:: እማዬ የሚለው እንጀራ እናቱን ነው። ወንድሜ
የሚለውም የአባቱ ልጅ ሳይሆን የእንጀራ እናቱ ልጅ ነው።

"አባትህ ቢሆኑ ባንተ ቦታ ምን ይወስኑ ነበር?"


"በእርግጠኝነት አባዬ ቤተሰቡን ሳያማክር ምንም አይነት ትልቅ ውሳኔ አይወስንም። በተለይ እማዬን፡፡ አባዬም ቢሆን ግን በዚህ ጉዳይ መስማማቱን እጠራጠራለሁ።" ሲያስረዳኝ በቅንነት እና በፍቅር ነው።

አንዳንዴ በገንዘብ የማትገዛቸውና የማታስተካክላቸው ነገሮች
አሉ::" አልኩት።

ሩካዬ እኔ ቤተሰቤንና ቁስን ለንፅፅር የማቀርብ ቀሽም ሰው አይደለሁም።ብቻ ምክንያታዊ አይደሉም አልተዋጠልኝም::"
ተጨንቆ ሳየው አሳዘነኝ።

"ዛሬ እኔጋ ነው አይደል የምታድሪው?" አለኝ፡፡

"አሪፍ ምክንያት ካቀረብክ!”

"ሱሴ.....ስለማፈቅርሽ"

አያሌው በተደጋጋሚ እየደወለ ብዙ ጊዜ መፍጀቴን ይነግረኛል::
ስራ ቢሰጥሽ ፍቅር ታደሪያለሽ እንዴ?” እያለ ይዘባበታል፡፡ሲያሻው በውስጡ ብታፈገፍጊ ለኤፍሬም እውነቱን እነግረዋለው።የሚል አንድምታ ያለው ማስፈራርያ ይቦጠለቃል።በተጨማሪ ሌላ አስር ሺ ብር እቤት አስቀምጦልኛል።
መቀበሉም አለመቀበሉም ለውጥ ስላልነበረው አስቀመጥኩት። አያሌው እኔን ሲነተርክ፣ እኔ በኤፍሬም ፍቅር፣
በህሊናዬ እና በምኖረው እውነት ተወጥሬ፣ ኤፍሬም በቤተሰቡ ንዝንዝ እና ከኔጋር በጀመረው አዲስ ፍቅር ሲዋከብ ሶስት ወራት አለፉ።

ሩካዬ? አግቢኝ!” ያለኝ ማታ ስሜቴ ተደበላለቀ። ደስታና ሀዘን፣ተስፋና ፀፀት ውስጤ ተሳከረ፡፡ አልመለስኩለትም።

"ሱሴ የኔ ሁኚልኝ!" ደገመው። ዝምታዬን ደገምኩት።

'የኔ መሆን አትፈልጊም? አታፈቅሪኝም?"

“እሱማ አፈቅርሃለሁ።"

"እሱማ ምን?"

"ጊዜ ስጠኝ ኤፊ" አልኩት አፌ እንዳመጣልኝ እንጂ ጊዜ
ከማወሳሰብ አልፎ የሚፈታው የኔ ጉዳይ እንደሌለ አውቃለሁ።

"የፈለግሽውን ያህል ጊዜ ውሰጂና አስቢበት።የመጨረሻው መልስሽ ብቻ እሺ ይሁን።" አለኝ፡፡ ዓይኔ በእንባ መሞላቱ አስደነገጠው።

"ደስ የሚልሽ ነበር የመሰለኝ!" አለ ቅር እየተሰኘ፡

"ደስ ብሎኝ ነው! አንተ ለኔ የምትገባ ሰው አልነበርክም። ይሄ ክብር የሚገባኝ ሴት አይደለሁም።" እንባዬን ከዚህ በላይ ማቆም አልቻልኩም።ሳይገባው አባበለኝ።

"ኤፍዬ በናትህ ከእቅፍህ አታስወጣኝ! እቀፈኝ!" አልኩት። እቅፉ ውስጥ ተደብቄ እንቅልፍ ወሰደኝ። ብቸኛው ሰላም የማገኝበት ቦታዬ ከእውነታው የምሸሽበት ዋሻዬ ፍረዱኝ እስኪ ምን ነበር ማድረግ የነበረብኝ? እውነቱን መንገር አትሉኝም?

ጠዋት ስራ ከመሄዱ በፊት የሰራሁለትን
ቁርስ እየበላ ስለአያሌው ድርሻ ጉዳይ አነሳልኝ።

"ሌሎቹ ዘርፎች ትርፍ ስለቀነሱ ገበያው ላይ እያተረፈ ያለ ፋብሪካ ድርሻ መሸጥ ምኑ ነው የሚያሳምነው?" አለኝ ከኔ ሀሳብ እየፈለገ።

"ምናልባት ብዙ ያሳደደ አንድ አይዝም እንዳይሆንብህ ብለው ይሆናል" መለስኩለት። ሊጎርስ ያዘጋጀውን ሰሀኑ ላይ መልሶ እያፈጠጠብኝ "አንቺም በመሸጡ ትስማሚያለሽ?" አለኝ፡፡

“በመጠኑ!"

"አሳምኚኝ!!" አለኝ ምንም ክፋትና እልህ
በሌለበት አንደበት።

“አንደኛ ፋብሪካው የጋራ ነው።ምንም ውሳኔ የራስህ ብቻ የማይሆንበት። የቀሩት ዘርፎች ግን የግልህ ናቸው:: በራስህ እጅ ብቻ ያለ ነገር ዋስትናው የተሻለ ነው። ባንተ ብቻ የሚተዳደር
ያላነሰ ንግድ እያለ አንድ ፋብሪካ ውስጥ ላለህ ድርሻ እንዲህ ከቤተሰብ ጋር የመቃረኛ ነጥብ እስኪሆን ድረስ ትልቅ ጉዳይ መሆኑ የሚዋጥ አደለም
ሁለተኛ በአጭር ጊዜ እንደታዘብኩት
የግልህ የሆኑት ዘርፎች ሶስት ዓመት ሙሉ ምንም ለውጥና እድሳት አልተደረገባቸውም፡፡ ላድርግም ብትል
በዛ ያለ ገንዘብ ያስፈልግሃል::ያን ደግሞ ፋብሪካው ውስጥ ያለህን ድርሻ ሸጠህ ካልተጠቀምክ በቀር አቅም ያንስሃል።”

“እሱ ይህን ያህል ገንዘብ ፕሮፖዝ ሲያደርግልኝ የወደፊትትርፉን አስልቶ አይመስልሽም?"

"ይሆናል።ትርፍና ኪሳራውን ሳያመዛዝን እንደማይወስን ግልፅ ነው።ያንተ ድርጅቶችም ቢሆኑ አባትህና ሊዲያ
በሚያስተዳድሩባቸው ዓመታት እጅግ ትርፋማ የነበሩ ናቸው።አሁንም በትንሽ ጥረት ወደ ቀድሞ ቦታቸው የማይመለሱበት ምክንያት አይታየኝም::"

"እደግመዋለሁ የጭንቅላትሽ ምጥቀት እኮ ማትሪክ የመጣብሽ አትመስይም::" አለኝ ወደ ቁርሱ እየተመለሰ። ቀጠል አድርጎ
"አሁንም አይዋጥልኝም፡፡ ከነሱ ግን ያንቺ ምክንያት የተሻለ አሳማኝ ነው::"

ከዚህ በኋላ ለተከታታይ ቀናት ይሄን ጉዳይ ሳናነሳ ነግቶ የመሸ ቀን አልነበረም፡፡ ከቤት እናቱና ወንድሙ ስለሚጨቀጭቁት መጥቶ የሚተነፍሰው እኔጋ ነው።

እኔም እየጨቀጨቅኩት እንደሆነ ተሰምቶኛል፡፡

“ሩካዬ በዚህ ጉዳይ ካሁን በኋላ ካንቺም ከቤተሰቤም ጋር መጨቃጨቅ አልፈልግም::" አለኝ የሆነ ቀን
እያደረሰኝ፡፡ ደስ አላለኝም:: የኔና
👍7
#ምርጫ_አልባ_ምርጫ


#ክፍል_ስምንት


#በሜሪ_ፈለቀ

ጥቁርና ነጭ አይደሉ? ቢሆንም የከዳሁት ልቡ አንደኛውን ሲሄድ ህመሜን ደምሬ ልታመም ወስኜ ዛሬ አብሬው ጠፋሁ። እኔ የጊዜ ዑደትን ማስላት ምን ሊረባኝ ያልኖርኩባትን ነገ ትቶኝ ይሄዳል ብዬ ዛሬዬን ልብከንከን? ኤፍሬምን በተመለከተ ከነገ እውነት የዛሬ ስሜቴ ልክ ነው። ከእርሱ ጋር አንድ ቀን ዘልአለም ነው አንድ አይደለም። ከእርሱ ጋር አንድ ቀን ዘለዓለም ነው። ዘለዓለም
ደግሞ ውሱን አይደለም፡፡ ዛሬ ዘለዓለም ናት! ስለዚህ ከርሱ ጋር ዘለዓለም መኖር ምርጫዬ ሆነ፡፡

"ደህና እደሪ" ሲለኝ ፀጉሩን እንደዳበሱት ህፃን አንቀላፋሁ።

"እወድሻለሁ" ያለኝ ቃል በጆሮዬ ለብዙ ዘለዓለም ቀናት ተንቆረቆረ።

ዘለዓለም ጥግ ኣልባ ነውና ዛሬ ለኔ ያለው ስሜት ጥግ አልባ ነው። ያንን ብቻ አምናለሁ። ነገ ስለመለያየቴ መርሳት ፈለግኩ፡፡ዘለዓለም ከእርሱ ጋር አለሁና! እስከሁሌው እቅፍ ውስጥ ብኖር
ብዬ ሳሳሁ። ጠዋት ተመልሰን ስለየው የመጨረሻዬ እንደሆነ እያወቅኩ ነበር በስስት የሳምኩት።እናም "ደህና ዋይልኝ" ሲለኝ ቀጥሎ ሊፈጠር ስለሚችለው ክስተት ሳላስብ ከደህና በላይ ሆንኩ፡፡ ከእርሱ ተለይቼ ብዙም ሳልቆይ አያሌው ደወለልኝ። እመኑኝ ኤፍሬምን ላለማጣት እናትና ወንድሜን አያስከፍለኝ
እንጂ ምንም አደርግ ነበር፡፡ አሁን ግን
ተመሳቅሏል፡፡እውነቱን ብነግረውም አብሮኝ ስለመዝለቁ ዋስትና
የለኝም፡፡

“ምን ብታቀምሺው ነው? ንግስቴን አመስግናት ሲለኝ እንኳን ያላፈረኝ?" አለኝ፡፡ ዝም አልኩት፡፡

“ከሰላሳ ደቂቃ በኋላ ላግኝሽ?" ብሎ ቀጠረኝ:: በድኔን እየጎተትኩ
ደረስኩ። ብሩን በቦርሳ በካሽ ሰጠኝ:: የማይሆን ነገር ባስብ በበርዬ ያስፈራራኝን ደገመልኝ።ከአንድ ሰዓት በኋላ እንደሚፈርምለት እየፈነጠዘ ነግሮኝ ተለያየን።ታክሲ ይዤ እየሄድኩ በመስኮቱ
አሻግሬ አያለሁ።ታክሲው ጎን የቤት መኪና አየሁ ውስጡ የነበሩት ሰዎች ትኩረቴን ሳቡት።አያሌውን የኤፍሬም እናት።አልተሳሳትኩም፡፡ ከንፈር ለከንፈር እየተሳሳሙ ነው ያየሁት።በደስታ
የሰከሩ ይመስላሉ፡፡ እናትየው የፋብሪካው ድርሻ እንዲሽጥ መወትወታቸው የተለየ ምክንያት ሊኖረው
እንደሚችል እንዴት አልጠረጠርኩም? የማደርገው ጠፋኝ፡፡

ቢሮው እያለከለኩ ስደርስ ብዙም አልዘገየሁም። የማደርገው ነገር የሚያመጣውን ቀውስ ማሰብ አልፈለግኩም፡፡ ሊፈርም
ያዘጋጃቸውን ሰነዶች እንደያዘ ኤፍሬም ፈዞ ያየኛል። የሆነውን አንድ በአንድ ነገርኩት። ገንዘቡን ለአያሌው ጠረጴዛው ላይ አስቀመጥኩለት።

"እኔጋ የሚቀርህን ገንዘብ እመልስልሃለሁ፡፡" ብዬው ስወጣ
ለመጨረሻ ጊዜ የኤፍሬምን ፊት አየሁት:: ደንዝዟል።ለመጨረሻ ጊዜ ይህን አለ፡፡

"ያ ሁሉ ለክፍያ ነበር?"

ኤፍሬም ድጋሚ ሊያየኝ እንደማይፈልግ የስንብት በሚመስል የመጨረሻ መልዕክቱ በስልክ አሳውቆኛል: ህይወት አስጠላኝ፣ እማዬና በርዬ እኔን ማባበል ስለቻቸው።በርዬ መፅሀፉን
የሚያሳትምለት አሳታሚ ድርጅት አጊንቶ ከስድስት ወር በኋላ ታተመለት:: ርዕሱ 'ምርጫ አልባ ምርጫ መሆኑን ያወቅኩት
ልናስመርቅ ስንሰናዳ ነው:: ሁሉ ነገር ቢያስጠላኝም የበርዬ ህልም መሳካቱ በተወሰነ መልኩ የደስታ ምንጭ ሆኖልኛል።መደበቂያዬ መፅሀፍ ማንበብ ሆኗል፡፡ ከማይገፋ የብቸኝነት ወራት በኋላ በርዬ ሱፍ ለብሶ፣ እኔ የሀበሻ ቀሚስ ለብሼ የመፅሀፉ ምረቃ ዝግጅት ላይ ከመታደማችን በፊት እማዬጋ
ሄድን፡፡ በደስታ አነባች:: መገኘት ባትችልም በልጆቿ ደስታ በማያባራ እንባ ታጠበች። ይህቺን ቀን እውን ለማድረግ ብዙ አልፌያለሁ እና አብሪያት አለቀስኩ፡፡

አዳራሽ ውስጥ ስንገባ ሰዓት ገና ቢሆንም ወዲህ ወዲያ የሚሉ
ሰዎች ነበሩ፡፡

"ሩካ?" የሰማሁትን ድምፅ ማመን አቅቶኝ ዞርኩ፡፡ ኤፍሬም የበርዬ መፅሀፍ ምረቃ ላይ ምን ይሰራል? አላችሁ? እኔም
ራሴን እንዲያ ከጠየቅኩ በኋላ ወዲያው
እስካሁን ያላስተዋልኩትን ነገር አስታወስኩ፡፡ የመፅሀፉ ሽፋን ላይ
አሳታሚና አከፋፋይ ተብሎ የተፃፈው የኤፍሬም ድርጅት ስም ነው።

"ወይዬ” አልኩት የምለው ጠፍቶኝ፡፡ በርዬ ዊልቸሩን እየገፋ አጠገቤ ሲደርስ ፍፁም በወዳጅነት መንፈስ ተቀላልደው አልፎን ሄደ፡፡ እንደትንግርት የሚሆነውን ከማየት ውጪ ምርጫ አልሰጡኝም:: በርዬ አልፎኝ ከሄደ በኋላ በአይኑ ጠቀሰኝ፡፡ እንዴትና የት ተግባቡ

“ይሄን መፅሀፍ ካነበብኩ በኋላ እንደገና ላውቅሽ እንደሚገባ ወሰንኩ።ኤፍሬም!!" አለኝ እጁን እየዘረጋልኝ፡፡

"ረቂቅ" አልኩት እጄ ሳላዘው ሊጨብጠው እየተዘረጋ።

።።።።።።።።
እኔና አንተ አንድ ቦታ ላይ በተለያየ አቅጣጫ ፊታችንን አዙረን ብንቆም የእኔ ቀኝ ያንተ ግራ ነው።ያንተ ግራ የኔ ቀኝ ነው 'ቀኝ ይሄ ነው ወይም ግራ ይሄ ነው ብዬ ብከራከርህ ቂል ነኝ ። እንዳንተ አቋቋም ያንተ እውነት ይሆናል።እንደኔ አቋቋም ደግሞ የኔ ትክክል ይሆናል። ባንተ እውነት ለማመን ያንተን ጫማ መዋስ አለብኝ።የቆምኩበት ሆኜ ለስህተትህ ሒሳብ እየሰራው ስዳኝህ እቀሽማለው።
።።።

#በረከት

እሷ ዋሸኸኝ ነው የምትለኝ፡፡ እኔ ደግሞ አልነገርኳትም እንጂ ዋሸኋት ብዬ አላሰብኩም ወይም እንደዛ ማመን አልፈልግም።በእርግጥ ያልነገርኳት አለመነገር የሚችል አልያም ባይነገርም
በእኔ እና በሷ ግንኙነት ሂደት ለውጥ የማይፈጥር ዝባዝንኬ ሆኖ አልነበረም
እሷን እስከማጣት የሚስቀጣኝ ሊሆን
እንደሚችል አውቅ ነበር።ግን ማወቅ ከባድ አይደለም መኖር እንጂ! ያወቁትን ሁሉ መኖር የሚቻል ቢሆን ኖሮ ይህች ዓለም ከብዙ ስህተቶችና ጥፋቶች በተረፈች ነበር። ምክንያቱም የማይረቡ የምንላቸውን ጭምር አብዛኛዎቹ ጥፋቶች ባለማወቅ የሚደረጉ አይደሉም።

"ይቅርታ ውዴ! አንቺን ለመጉዳት ብዬ ያደረግኩት ምንም ነገር የለም። እመኚኝ፡፡" ብዬ የስልኬ መልዕክት መፃፊያ ሳጥን ውስጥ ካሰፈርኩ በኋላ ስልኩን አቀበልኳት::

“ታዲያ ለምን ዋሽኸኝ? ያን ሁላ ጊዜ ስንፃፃፍ ላንተ ጨዋታ ነበረ? እያሾፍክብኝ ነበር?" እኔ ከፃፍኩላት ስር ይሄን ፅፋ
ስልኩን መለሰችልኝ፡፡ በኖርኩባቸው የሃያ ሰባት ዓመት የዕድሜዬ ቁጥር ልክ ብዙዎች በተለያየ ምክንያት ሲያዝኑ እና ሲሰበሩ አይቼ አውቃለሁ። እሷ ላይ በማነበው ልክ ፊት ላይ የተገለጠ መሰበር አስተውዬ ማወቄን እጠራጠራለሁ፡፡ ምክንያቱ እኔ መሆኔ ደግሞ በሰባት ዓመቴ ወድቄ የተሰበረ እጄ ሲታከም ከተሰማኝ ህመም በላይ ያማል።

“በፍፁም አልነበረም:: የፃፍኩልሽን እያንዳንዷን ቃል እና ስሜት
ከልቤ ነው ያልኩሽ! የፃፍሽልኝ እያንዳንዱ ቃል ደግሞ በዘመኔ ሁሉ እየመነዘርኩት ደስታን የምሸምትበት ሀብቴ ነው ።
ስለሚቀጥለው ግንኙነታችን ልብሽ የሚልሽን አድርጊ ስላለፈው
ግን እመኚኝ የተሰማሽም የተሰማኝም እውነት ነበር። በዛሬው ጥርጣሬሽ ትናንትናችንን አታርክሺው ይሄን ፅፌ አቀበልኳት።አንብባ ስትጨርስ መልስ መፃፍ ጀመረች፡፡ ስልኩን መልሳ
ስታቀብለኝ ግን ምንም የተፃፈ መልዕክት የለዉም፡፡ ልቧን በቃላት ማስፈር የተሰማትን ስሜት ማቅለል ሆነባት የተወችው መሰለኝ።

ሩካ እና ኤፍሬም በእኔና በማርቲ መሃከል የተከወነውን የስልክ መቀባበል እንዳላስተዋለ ለማስመሰል ለቡና ቁርስነት የቀረበው ፈንድሻ ላይ ራሳቸውን ጠምደዋል፡፡ሁላችንም በፀጥታ
ሀሳቦቻችንን እያላመጥን መሰለኝ ሩካ ቡናውን ፉት ስትል
ፉፉፉፉፉፉትታዋ እንኳን አንድ ጠረጴዛ ለከበብነው አራት ሰዎች ከጊቢ ውጪ ለሚያልፍ ሂያጅ የ'ቡና ጠጡልኝ መልዕክት ይነግራል፡፡

"አቦል ልድገማችሁ?" የሚለው የሳራ ድምፅ (ሩካ ከሶስት ወር በፊት የቀጠረቻት በእድሜ ገፋ ያለች የቤት ሰራተኛችን ናት፡፡
👍21😁1
#ምርጫ_አልባ_ምርጫ


#ክፍል_ዘጠኝ


#በሜሪ_ፈለቀ

"ከዛሬ በፊት ነግሬሽ ቢሆን ኖሮ ምንድን ነበር የሚፈጠረው?ከነጉድለቴ ትወጂኝስ ነበር?" አስቀድሜ ስልኬ ላይ ፅፌው ልሰጣት ሳመነታ የነበረውን አቀበልኳት
አቀበልኳት: አንብባው ቀና ስትል ያፈጠጠባት ዓይኔን ቀለበችው:: በዝቅተኛ ግን በቁጣ ድምፅ "ማድረግ የነበረብህ ያን ነበር፡፡ ግድ ሊልህ የሚገባው ነገር የእኔ ስሜት ለውጥ ወይም ውሳኔዬ ሳይሆን ያንተ ሀቀኝነት ነበር። ታውቃለህ? በእውነተኛ
ታሪክ ላይ የተመሰረተ ልብ-ወለድ መፃፍ ትክክለኛ ተስዕጦህ ነው:: በእኔና ባንተ መሃከል የነበረው ነገር ላንተ እንደዛ ነበር::
አንዷን ገፀ-ባህሪህን እንደምታዋራት እና እንደምታስወራት ያህል የምትዝናናበት ልብ-ወለድ!!" ብላኝ ስልኬን ከጠረጴዛው
አጋጭታ አስቀምጣ ወደ ውጪ ወጣች:: እየሆነ የነበረውን እየተከታተሉ እንደነበር በሚያሳብቅባቸው አኳኋን ሩካ እና
ኤፍሬም ተከታትለው ወደ ሳሎን ብቅ አሉ፡፡ ኤፍሬም በ'አይዞህ!'
ባይነት ትከሻዬን ጨበጥ አድርጎ ማርቲን ያረፈችበት ሆቴል ሊያደርሳት ተከትሏት ወደ ውጪ ወጣ፡፡

"ያልጠበቅከው ነገር አልነበረም የተፈጠረው:: ለእርሷም ዱብ-ዕዳ ነው የሆነባት፡፡ ጊዜ ስጣትና የሚሆነውን እንጠብቅ፡፡" አለችኝ ሩካ የከፋኝ ሲመስላት ሁሌ እንደምታደርገው በሁለቱ
እጆቿ ጉልበቴን ተደግፋ እግሬ ስር ቁጢጥ ብላ የተሰማኝን ለመረዳት ዓይን ዓይኔን እያየች፡፡ ላስረዳት ከምፍጨረጨረው በላይ ቀድማ የእኔን ህመም በራሴው
እንደምትታመምልኝ ስለማውቅ መልስ ልሰጣት አልደከምኩም።ፀጉሮቿ መካከል ጣቶቼን ሰድጄ የራስ ቅሏን ቆዳ እየነካካሁ
ደቂቃዎች አለፉ። ጉልበቴ ላይ ግንባሯን ደፍታ ሳላወራ ሰማችኝ፡፡ ሳላስረዳት ገባኋት፡፡ እንባዬ በዓይኔ ባይገነፍልም
ማልቀሴን አየችው። ሩካ ናታ! ግነት የለውም፡፡ እንደውም አልገለፅኳትም። ሩካ የሌላ ሰው ስሜት የራሱን ያህል በተጠጋጋ ቅርበት የሚሰማት ለነፍስ የቀረበች ፍጡር ናት!

በረከትን ሆኜ በምተውነው ራሴን ካወቅኩበት ጊዜ ጀምሮ እስከአሁን ባለ መደበኛ የየዕለት የኑሮ ተውኔት ውስጥ በጉልህ የደመቁ ሶስት ሴቶች የሀሳቤን አቅጣጫ ፈቃዴን እያዛቡ ያንዥዋዥውታል። እማዬ ሩካ እና ማርቲ።

እማዬ ያው እማዬ ናት።ለእኔ ለልጇ ብላ አስር የዘመኗ ቁጥር በእስር ቤት እየተቆረጠመባት ያለች እናቴ! በየቱም ድርጊቴ የከፈለችልኝን መስዋዕትነት ጥቂት ሽራፊ እንኳን ላካክስላት
እንደማልችል ሳስብ ከንቱነቴ ይገንብኛል፡፡ ማድረግ የምችለው ብቸኛ ነገር የእማዬ ፊት ላይ ለሚታይ የፈገግታ ፍንጣቂ
ምክንያት ለመሆን ቢያቅተኝ እንኳን ቢያንስ በጉንጫ ላይ ለሚወርድ አንዲት የእንባ ዘለላዋ ምክንያት ላለመሆን
መፍጨርጨር ነው።

ረቂቅ ታናሽ እህቴ ናት፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ፍቅረኛዋ በሚጠራት ቁልምጫ ሩካ እያልኩ ነው የምጠራት:: ብቸኛዋ
እህቴ! ስለሩካ ማብራራት ቀላልም ከባድም የሚሆንበት ምክንያት ብዙ ነው። ልክ ለመሰላት ነገር የማታመነታ ቆራጥ መሆኗን ባመንኩ ልቤ በየደማቅ አበባው ተዟዙራ መዓዛውን ቀስማ
የማትረካ ቀልቃላ ቀለማም ቢራቢሮ ትመስለኛለች፡፡ ብዙም ሳይቆይ ውስብስብ የሆነች ጭምት ትሆንብኛለች
በጭምትነቷ ሳልረጋ ስስና ተሰባሪ ትሆንብኛለች።ሩካ የህይወቴም የመፅሐፌም ዋና ገፀ ባህሪ ናት! መፅሐፍ መፃፌን ነገርኳችሁ? ከወራት በፊት አንድ መፅሐፍ ፅፌ ለንባብ
አብቅቻለሁ። ለስነ ጥበባዊ ውበቱ መጠነኛ ቅብ ከመጨመሬ ውጪ ሙሉ ለሙሉ የሩካ ታሪክ ነው:: ርዕሱ "ምርጫ አልባምርጫ!!! የተሰኘ ነው:: የመጨረሻዋ ሴት ማርቲ የተከሰተችው በዚህ መፅሐፍ ሰበብ ነው፡፡

ስለእነርሱ ማንነት ከምፅፍላችሁ ቀድሞ የተውኔቱን ያልሰነበተ ትዕይንት የማርቲ
ልብ የተሰበረበትን ገፅ እንደምትፈልጉ አውቃለሁ። ምን አስቸኮላችሁ? ልክ ነበርክ ወይም ተሳስተሃል ብሎ ለመፍረድ ምን ከዳኝነታችሁ በፊት እኔን ማወቁ ለፍርዱ አይረዳችሁም ብላችሁ
ነው? ይመስለኛል። ለነገሩ እኔም ብሆን ያደረግኩትን ያደረገው ሌላ ሰው ቢሆን የፍርድ ወንበሬ ላይ ለመሰየም እጣደፍ ነበር::የፍርድ አንቀፅን በመዶሻ ድለቃ አጅቦ ማንበብ ከባድ የሚሆነው
የተፈራጅ እግርን ተውሶ በቆመበት ማጥ መቆም ሲቻል ነው።ነገር ግን የእኔ የልክነት ጥግ' ነው ብዬ ያመንኩበት የግሌ እውነት ለእናንተም የልክነት ጣሪያ መሆን አለበት ብዬ እናንተን በተሳሳች ሂሳብ መዳኘት ከቂልነቴ ባሻግር የጠበበ
የሀሳብ ምህዳሬን ገልቦ አደባባይ ማስጣት ይመስለኛል።

እኔ የቆምኩበትን ጫማስ “ስህተት ብላችሁ ለመዳኘት ለመሆኑ
የእናንተ ልክ በየትኛው ሚዛንና በማን ዳኝነት ተሰፍሮ ነው ልክነቱ የተረጋገጠው?

አይደለም ለሌላ ሰው ለራሳችን እንኳን “ልክ ነው ያልነውን እምነታችንን ጊዜ አላንጓለለብንም? የዛሬ ምናምን ዓመት በፊት የልክነት ጫፍ የመሰለን በጠበበም ወይ በሰፋ አስተሳሰባችን ሳቢያ ዛሬ አልተቀየረም? እንዴት ነው በጊዜ፣ በመረዳታችን መጠን፣ በቦታና በበሽቃጣ የህይወት ክስተቶች እንደማይቀየር
ዋስትና በሌለን ልክነት ሌላውን በስህተት የምንዳኘው?

የኔ ስህተት ውስጥ ተዘፍቆ ላገኘሁት ሰው ከመዳኘቴ በፊት የዝፍቀቱን ሰበብ መረዳቱ ይቀል አልነበር? ምክንያቱ ደግሞ
የእኔ ልክ የልክ ጣሪያ ሊሆን አይችልም፡፡ የሆነ ቦታ.... የሆነ ጊዜ.....ለሆነ ሰው ስህተቱ ሊሆን ይችላል፡፡

እኔና አንተ አንድ ቦታ ላይ በተለያየ አቅጣጫ ፊታችንን አዙረን ብንቆም የእኔ ቀኝ ያንተ ግራ ነው። ያንተ ግራ የኔ ቀኝ ነው። ቀኝ ይሄ ነው ወይም ግራ ይሄ ነው ብዬ ብከራከርህ ቂል ነኝ፡፡
እንዳንተ አቋቋም ያንተ እውነት ይሆናል። እንደ እኔ አቋቋም ደግሞ የእኔ እውነት ይሆናል። ባንተ እውነት ለማመን ያንተን
ጫማ መዋስ አለብኝ፡፡ የቆምኩበት ሆኜ ለስህተትህ ሒሳብ እየሰራሁ ስዳኝህ እቀሽማለሁ፡፡

እግሬን አውሻችሁ የዳከርኩበትን ስትዳክሩት አሁን ካለሁበት
የጊዜ ካብ ወራትን ወደኋላ ንጄ አፍ ውስጥ እየጣፈጠ የሚሟሟ
ግን እንዳያልቅ እንደሚሳሱለት፤ ያልቃል ብለው ማጣጣሙን እንዳይተውት ጥፍጥናው እንደሚያባብል ጣፋጭ ከረሜላ የሚጣፍጠውን የኑሮ ተውኔቴን ገፅ ላስነብባችሁ። እዚህ የጊዜ
ካብ ላይ ለማማረር ምክንያቶቼ የሚዘቅጡብኝ፤ የመጀመሪያ መፅሐፌን ለንባብ ያበቃሁ፤ የከበቡኝ ሰዎች የተደላደለ ቀን የሚያልፉበት፤ እማዬ በደስታ ያነባችበት እና የመፅሐፌን
አንባቢ አስተያየት በኢሜሌ እያነበብኩ ተስፋዬን የምስቅል በረከት ነበርኩ። በኤፍሬም ማተሚያ ቤት አማካኝነት
ማስታወቂያ ተሰርቶለት ስለነበር መፅሐፌ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተደራሽነቱ ሰፊ ሆኖ ነበር፡፡ በመፅሐፌ ቀደምት ገፆች አንዱ ገፅ ላይ በተፃፈው የኢሜል አድራሻዬ የሚደርሱኝን የአንባቢያን
አስተያየት ማንበብ የሚደፍነው የስሜት ሽንቁር አለው፡፡

አንዳንዶቹ እንደዚህኛው ቦታ ላይ ታሪኩ እንደዚህ ባይሆን:መጨረሻው እንደዚህ ቢሆን የሚሉ ናቸው:: እንዲህና እንዲያ
ቢሆን የተባሉትን መልዕክቶች ስጨምቃቸው እኔ ከፃፍኩት በአንድ መስመር የማይገናኝ ሌላ ታሪክ እንደሚሆን እያሰብኩ ፈገግ እላለሁ። አብዛኛዎቻችን ስናነብ ደራሲው
ያሰበውን ሳይሆን እኛ የምናስበውን ቢፅፍልን እንፈልጋለን፡፡በተዘዋዋሪ የመፅሃፉ ደራሲ ራሳችን መሆን ነው የምንሻው::ለፃፈልኝ በሙሉ በምስጋና ብመልስም ጥያቄዎቹን ከራሴ ህይወት እውነታ ጋር እያዛመድኩ ለራሴ እመልሳለሁ::

'የምንትስ ገፀ ባህሪ ታሪክ መጨረሻው አልታወቀም:: ሲሉኝ
በእውነተኛው ዓለም መጨረሻቸው ያልተቋጨ ወይ ያልታወቀ
ታሪክ ባለቤቶች ብዙ አይደሉ? እላለሁ አባቴና ሰራተኛችን ሙሉ የነበራቸው ድብቅ ፍቅር መጨረሻው ምን
ነበር? እማዬ ወደ ስራ ሩካ
👍41
#ምርጫ_አልባ_ምርጫ


#ክፍል_አስር


#በሜሪ_ፈለቀ

...የእውነታው ኑሯችን ለፍፁምነት የተጠጋጋ እንኳን አይደለም፡፡በመፅሐፌ ውስጥ ፍፅምናን ለምን ይጠብቃሉ? መፅሐፌ የሀሳቤና የኑራችን ግልባጭ እንጂ እነርሱ የሚመኙት የ'ቢሆን ዓለም ሊሆን እንዴት ይችል ነበር?

በአንዱ ቀን እንደተለመደው ኢሜሌን ስከፍት ረዥም ሀተታ ያለው መልዕክት ደረሰኝ፡፡ ማርቲ ነበረች፡፡ ስለመፅሃፉ ይዘት
ተያያዥ ሀሳቦች ከተነተነች በኋላ ስለተሰማት ስሜት የፃፈችው ጭብጥ መልዕክቱ እንዲህ የሚል ነበር።

ታሪኬን ነግሬህ የፃፍከው እስኪመስለኝ ያለፍኩትን መንገድ እና የተሰማኝን ስሜት ነው የፃፍከው:: ወንድ ሆነህ እንዲህ የሴትን ጥልቅ ስሜት መፃፍህ እስገርሞኛል፡፡ መፅሐፍህን እያነበብኩኝ
የምታውቀኝ የምታውቀኝ አይነት ነበር የሚሰማኝ። በቅርቡ ከሀገር ቤት የመጣች ጓደኛዬ ገዝታልኝ ከመጣቻቸው አዳዲስ መፅሐፍት ውስጥ አንዱ ምርጫ አልባ ምርጫ ነበር፡፡ ይሄን መልዕክት ስፅፍልህ መፅሐፍህን ለሶስተኛ ጊዜ አንብቤዋለሁ::"የሚል ነበር። ተመሳሳይ አስተያየት አንብቤ ባውቅም አንድም ይሄኛው ጥልቀት ያለው ትንተና የተካተተበት መሆኑ ሁለትም ማብራራት በማልችለው ምክንያት ከሌሎቹ ተመሳሳይ መልስ አልመለስኩም። ይሄ መልዕክት ከፊደላቱና ከሀሳቡ በተጨማሪ መንፈስ ነበረው:: አውስትራሊያ ሆና የፃፈችበትን ስሜት አዲስ መንፈስ አጋብቶብኛል።

"ውድ ማርታ ስለመፅሐፌ ለፃፍሻቸው ውብ ሙገሳዎች ከልቤ አመሰግናለሁ። በፃፍሽልኝ መልዕክት ስለመፅሐፍት ያለሽን ሰፊ ግንዛቤ ማወቅ በመቻሌ ምክንያት ያንቺን አድናቆት ማግኘት
ከፍ ያለ ደስታ አለው። ያንቺ የኑሮ መንገድ ከየትኛው የመፅሐፉ ታሪክ ጋር እንደተመሳሰለ ባላውቅም ከፃፍኩት ታሪክ ውስጥ በአንዱ ተመሳሳይ ጉዳት እንኳን ተጎድተሽ ከነበር ላለፍሽው
ሀዘን አዝናለሁ:: አንዳንዴ የተሰማሽን መተንፈስ ከፈለግሽ እና ይረዳኛል ብለሽ ካሰብሽ ፃፊልኝ፡፡ በድጋሚ አመሰግናለሁ::" ብዬ መለስኩላት:: የእኔና የማርቲ እውቂያ የጀመረው በእነዚህ
የመልዕክት ልውውጦች ነበር፡፡ በተደጋጋሚ ከተፃፃፍን በኋላ የብዕር ጓደኛሞች ለመሆን ተስማምተን በየቀኑ መፃፃፍ ቀጠልን፡፡ በቀን ሁለቴ... ሶስቴ... አራቴ አምስቴ...መቁጠር አቆምን፡፡ ያወቅኳት መሰለኝ፡፡ ያወቀችኝ መሰላት።በየሰዓቱ ስለምታደርገው ጥቃቅን ነገር ሳይቀር ከፎቶዎቿ ጋር
እያያያዘች ትፅፍልኛለች:: ከሁለት
የዘለለ ልኬላት ባላውቅም ፤ አዋዋሌን በሙሉ ባልፅፍላትም ለፃፈችልኝ ቁጥር
ያህል ጊዜ መልስ እፅፍላታለሁ፡፡ በጠዋት ዓይኖቼን ስገልጥ ማየት የምመኘው የእርሷን መልዕክት ሆነ። በሆነ ምክንያት ሳትፅፍልኝ ካረፈደች ስጋቴ እያንዳንዷን ደቂቃ የመላ ምት ቁልል እየደረመሰ ሊያሳብደኝ ይደርሳል፡፡ ምክንያቱም ለማርቲ ምንም ጥቅምም ሆነ ዕውቀት የማይደምርላት ዝባዝንኬ ሳይቀር ስፅፍላት በዊልቸር እንደምሄድ እና መናገር እንደማልችል ፅፌላት አላውቅም:: አታውቅም! ማርቲ ስልክ ደውላ ድምፄን መስማት ሳትፈልግ ቀርታ ወይም ምስሌን እያየች ልታወራኝ
ሳትጨቀጭቀኝ እረስታ አልነበረም አጋጣሚው ያልተፈጠረው፡፡ለቀናት እስከመኮራረፍ ያደረሰን ምክንያት ሆኖ ያውቃል፡፡በደሌን የምትቆልልብኝ የምሰጣትን ቀሽም ምክንያት ሁሉ
ስታምነኝ ነው። በእርግጥ በሆነኛው ቀን በስካይፒ ካላየሁህ ብላ ከልቧ ስላመረረች የሚከሰተውን ለመቀበል
ራሴን አሳምኜ ኮምፒተሬ ፊት ተቀምጬላትም ነበር፡፡ በሚቆራረጠው ኔትወርክ ምክንያት ከሰከንዶች የዘለለ መተያየት አልቻልንምና በቅን ልቧ ኔትወርኩ ብልሹ ስለነበር ድምፄን መስማት አለመቻሏን እንጂ
ዲዳነቴን አልተጠራጠረችም።

ለእንደኔ ዓይነት ሰው ይሄን እድል ማን ይሰጠው ነበር? ማርቲስ ብትሆን እውነቱን ብታውቅ የሰጠችኝን ፍቅርና ያሳየችኝን ህልም መሰል ቀን ትሰጠኝ ነበር? ምንም መጨረሻው ከህልም
መንቃት ዓይነት ቢሆንም እነዚህን ቃላት ማጣጣም የተለየ ነገር ነበረው፡፡ እና ለምን ብዬ እውነቱን ነግሪያት የደስታ ቀኔን
ላሳጥር? እንኳን ለመፈቀር መብቃት እንደሙሉ ሰው መታየት የሚናፍቀኝ ሰው ነኝ፡፡ በየመንገዱ የሚያየኝ ሰው አንዳች አሳዛኝ ገር እንደተመለከተ ከንፈሩን ሲመጥልኝ ስበግን የኖርኳቸው ዓመታት ጥቂት አይደሉምና በፍቅር መቆለጳጰስ ይቅርብኝ ማለት አልችልም ነበር፡፡ አንዳንዶች አፍ አውጥተው ይሄን
የመሰለ ልጅ... “እግዜር ለራሱ የሰራውን ያሳምራል:: የመሳሰሉ አሳማሚ አባባሎች ሲሉ እየሰማሁ የገፋሁት ቀን ጥቂት
አይደለምና ከማርቲ ፍቅር እውነቱን ነግሪያት የሚመጣውን መቀበል መምረጥ አይቻለኝም።

ቤክዬ ልይህ ስልህ ስትከለክለኝ እኮ አስቀያሚ ነህ ብዬ ደምድሜ ነበር፡፡ የላክልኝን ፎቶዎች እንኳን መጠራጠር ጀምሬ መፅሐፍህ ጀርባ ላይ ካለው ጉርድ ፎቶህ ጋር ስንቴ እንዳመሳሰልኳቸው
ባየህ!" ብላ ፅፋልኝ ነበር በዚያው ዕለት:: የፃፍኩላትን በሙሉ ባላምንበትም ደግማ እንተያይ ወይም ልደውልልህ እያለች
እንዳትጨቃጨቀኝ ፍቅር ከሚታየው ሳይሆን ከልብ መዋሃድ ጋር ብቻ መሆኑን በውብ ቃላትና ገለፃ አንዳንዴም በሚያሳምን ምሳሌ እያጣቀስኩ እፅፍለታለሁ። በእርግጠኝነት ያላመነችኝ
እንኳን ቢሆን ለትክክለኛው ምክንያት የቀረበ ግምት

አይኖራትም ነበር፡፡ ጉረኛ፣ ኩራተኛ፣ ቀብራራ፣ በራሱ የሚተማመን፣ የተረጋጋ...... ልታየኝና ልትሰማኝ አለመፈለጌን የምታመኃኝባቸው ፀባዮቼ ናቸው።

የምትዋሸው ወይ የምትደብቀው ታሪክህ የምታፍርበት ነው::ትላለች የኔዋ ረቂቅ:: ምናልባት ደግሞ የምትወደውን ነገር
የሚያሳጣህ ሊሆንም ይችላል። በእርግጥ እኔ የደበቅኳት ታሪኬን
ሳይሆን ተፈጥሮዬን ነው። እኔ በረከት ነኝ፡፡ መራመድም መናገርም የማልችል በረከት ለመሆን ያበረከትኩት አንዳችም
ጠጠር የለም:: ከአባዬ እና ከእማዬ ለመወለድ የሩካ ወንድም ለመሆን የኔ ፈቃድና ምኞት አይደለም:: የሆንኩትን ሆኜ ለመፈጠሬ የእኔ አስተዋፅኦ
ባዶ ነበር። ግንሳ? ፈቅጄ ባልመረጥኩት አፈጣጠሬ ጉድለት ሳቢያ ቀኖቼ ጎዶሎ ሆነውብኝ ነው ለመደበቅ የተገደድኩት።

ከአሁን ወደ ኋላ ንጄ ካስነበብኳችሁ ጣፋጭ ገፅ ወደ ፊት የጊዜን ካብ ስደረድር የኑሮን ጥፍጥና ለማጎምዘዝ ጊዜው የንስር ክንፍ ተውሶ ይንደረደር ነበር፡፡ እነዚህ ገዖች ጉራማይሌ ስሜት
የታጨቀባቸው ነበሩ።

"አንተ? ማታ እስኪሪብቶህን አገንፍለህ ነው እንዴ ያደርከው?"

"አንቺ ባለጌ ታላቅሽ እኮ ነኝ፡፡ አፍሽን አትክፈቺ!" እላታለሁ በእጆቼ ምልክት የእውነት እያፈርኳት፡፡ ክትክት ብላ በማፈሬ ትስቅብኛለች፡፡ ያሳፈረኝ የእርሷ ንግግር ብቻ አይደለም። ያለችው
እውነት መሆኑም ተደምሮ እንጂ፡፡
ከእንቅልፌ ከባነንኩ በኋላ ለማስታወስ ስሞክር ያልተከሰተልኝ መልክ ያላት ሴት ፈዛዛ የወይን ጠጅ ቀለም ያለው ስስ ቀሚስ ለብሳ የአልጋዬ ጠርዝ ላይ ተቀምጣ ስታጫውተኝ ነው ያደረችው:: ቁልጭ ብሎ ቅርፀ ምስሏ ባይታወሰኝም ቆንጆ እንደሆነች ይታሰበኛል።....

💫ይቀጥላል💫

Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍5
#ምርጫ_አልባ_ምርጫ


#ክፍል_አስራ_አንድ (የመጨረሻ ክፍል)


#በሜሪ_ፈለቀ

....በቀኝ እጅዋ የሌባ ጣት እንደመዳበስ ትነካካኛለች ምኔጋ እንደነካችኝ እንደነበረም ማስታወስ አልቻልኩም። ከእንቅልፌ ስባንን ጠዋት ሆኖ ሩካ ልትቀሰቅሰኝ በሬን እያንኳኳች ነበር። ከላዬ ተገፎ ከግማሽ በላዩ መሬት በተነጠፈ የልጋ ልብሴ አንሶላዬን እየሸፈንኩ እንድትገባ ነገርኳት
ይሄኔ ገብታ ነው “እስኪሪብቶህን
አገነፈልክ የምትለኝ።

“ተነስ እሺ አሁን ቁርስ እንብላ!"

“ማርቲ ልትመጣ ነው!" አልኳት የሚያስጮኃት አጀንዳ መሆኑን
ባውቅም እንደዚህ የምትዘል አልመሰለኝም ነበር፡፡ ጭንቀቴ
ወዲያው ጨንቋት ፈንጠዝያዋን ትታ ሀሳብ የገባት መሰለች::

"መቼ ነው የምትመጣው?" አለችኝ ማጥኛ ጠረጴዛዬ ጠርዝ ላይ
በግማሽ መቀመጫዋ እየተቀመጠች

“ከስድስት ቀን በኋላ! እና ምን ማድረግ እንዳለብኝ አላውቅም፡፡የማብድ እየመሰለኝ ነው:: የምትመጣው እኔን ብላ ነው።ያንቺንም ሰርግ ለመታደም ነው:: ሳትመጣ እውነቱን ብነግራት
አትመጣም:: ጭራሽ ዓይኗን ላላየው ነው:: መጥታ እውነቱን ስታየው ልትጠላኝ እንደምትችልም አውቃለሁ፡፡ የቱን መምረጥ እንዳለብኝ መወሰን አቃተኝ::” ከገለፅኩት ስሜቴ በላይ በጥልቀት
ምን እንደሚሰማኝ ሩካ እንደሚገባት አውቃለሁ።

“በርዬ በእውነተኛነት ስለመቆም ካንተ የተሻለ ልምዱ የለኝም፡፡የፍቅር ግንኙነትን አስመልክቶ ግን የተሻለ ልምድ ሳይኖረኝ
አይቀርም ነገሮችን ለመረዳትም ሆነ ለማስረዳት በአካል መገናኘትና በርቀት መነጋገር የትየለሌ ልዩነት አለው እስክትመጣ አፍህን ሰብስበህ ስትመጣ ሊፈጠር የሚችለውን ነገር ለመቀየር ወይም ለመቀበል ራስህን ብታዘጋጅ የተሻለ ይመስለኛል።" አለችኝ ጭንቀቴን ልታቀልልኝ እየሞከረች።ያለችውን ቀላል አድርጋ ትበለው እንጂ ሊገጥመኝ የሚችለውን አስባ እንደፈራችልኝ አውቅባታለሁ፡፡ ልቤ እንዳይሰበር
ፈርታልኛለች:: እንዳልጨነቃት ስታስመስል አሁንም አሁንም ግንባሯን ታሻሻለች። አንዱ ከአንዱ የማይያያዝ ወሬ
ትዘላብዳለች፡፡ ቁርሴን ሰርታ አብልታኝ ስለማያገባኝ ሁሉ ነገር ዘባርቃልኝ ከቤት ወጣች፡፡

ማርቲ የረቂቅ ሰርግ መድረሱን ስታውቅ ለመምጣት መወሰኗን ስትነግረኝ ላስቆማት ብችል ደስ ባለኝ፡፡ በየትኛውም ጨዋታዬ ስለሩካ አለመጥቀስ የማልችለው ነገር ነውና ታውቃታለች:: ሩካ
እኔ ሳላውቅ ነበር መጀመሪያ የፃፈችላትና የተዋወቁት፡፡ በስልክም የተወሰኑ ቀናት አውርተዋል። የማውቃት የማውቃት
ይመስለኛል፡፡ ትለኝ ነበር ማርቲ ስለ እህቴ ስትፅፍልኝ። በምን ፍጥነት ተወዳጅተው መቆለጳጰስ እንደጀመሩ ግራ ያጋቡኝ
የሩካን የሙሽራ ቀሚስ በጋራ እንደመረጡ ሩካ የነገረችኝ ጊዜ
ነበር፡፡ በስካይፒ እንደሚያወሩ ያወቅኩት ስለማርቲ ቁንጅና የምትነግረኝ ቀን ነው:: በስምንት ወራት ውስጥ ከማርቲ ጋር
የተቆራኘንበትን ጥብቀት እያሰብኩ ወደ መኝታ ቤቴ ስገባ ሳራ አንሶላዎቼን እየቀየረችልኝ ነበር። ዊልቸሬን ወደ ጠረጴዛዬ አስጠግቼ ኮንፒውተሬን ከፈትኩ፡፡ የማርቲን መልዕክት ፍለጋ።
የሳራ ዓይኖች ትከሻዬን ስለተጫኑኝ ለማራገፍ ቀና አልኩ።አልተሳሳትኩም:: የቀየረቻቸውን የቆሸሹ አንሶላዎች በእጇ ይዛ ቆማ ዓይኗን ጭናብኛለች፡፡ በጥያቄ አየኋት።

"አንሶላዎቹን ላጥባቸው ነው::" አለችኝ በቃሏ። አስተያየቷን ደምሬ ስሰማት ልትነግረኝ የፈለገችው አንሶላዎቹ የረጠቡበትን ምክንያት እንዳወቀች ነው የመሰለኝ፡፡ የማብሸቅ ዓይነት ፈገግታ
እያሳየችኝ ክፍሌን ለቃ ወጣች።

ስድስት ቀን እንዲህ አጭር ነው? በእንዲህ ያለ ውዝግብ ቀናት ውስጥ
ጊዜው የብርሃንን ፍጥነት ይዋሳል ፣ እሷ ልታገኘኝ ስለጓጓች ረዘመብኝ አለችኝ።እኔ ግን መገናኘታችን የሚጎትተው መዘዝ ፍራቻ ስለቆነደደኝ እንዲረዝም ብመኝም አጠረብኝ። እንዲህ የተወዛገበ ቀን ለራሴ እፈጥርለታለሁ ብየ አስቤ አላውቅም።

መምጫዋ ቀን ደረሰ:: እናም ሩካ እና ኤፍሬም አጅበውኝ እየጠበቅኳት ነው።
ከፍርሃቴ የተነሳ ልቤን የምተፋት
እስኪመስለኝ እየደለቀች ነው።እጆቼ እየተንቀጠቀጠ እና እያላባቸው የዊልቸሬን መደገፊያ በወጉ መንተራስ እቅቷቸዋል፡፡የለበስኩትን ስስ ሸሚዝ ማውለቅ እስኪያሰኘኝ እየሞቀኝ ነው፡፡
ሩካና ኤፍሬም ሀሳቤን በጭንቅ ከተሞላው ጥበቃዬ ለማሸሽ
ጨዋታ ይፈጥራሉ። ስለሰርጋቸው ጣጣ
ይነግሩኛል፡፡አልሰማቸውም ወይም ደግሞ ብሰማም አይስበኝም፡፡ በጭንቅላቴ ውስጥ እዚህም እዛም እኳትናለሁ።

“ብቻህን ብትቀበለኝ ነው ደስ የሚለኝ፡፡ እንዳገኘሁህ ሰው አየኝ አላየኝ ሳልል እስክጠግብህ ልስምህ ነው የምፈልገው::"ትናንትና ማታ ከፃፈችልኝ መሃል አሰብኩ፡፡

“የምትጠብቂው ዓይነት ሰው ሆኜ ባታገኚኝስ?" ብዬ መልሼ ፅፌላታለሁ።

'የምጠብቀው ዓይነት የለኝም:: የማውቀው ፍቅረኛ ነው ያለኝ፡፡
ጥቃቅን ልዩነቶች አያሳስቡኝም::" ነበር መልሳ የፃፈችልኝ፡፡

ትንፋሼ ቀጥ ልትል ትንሽ ሲቀራት ሻንጣዋን እየጎተተች ዓይኗን
በፍለጋ እያቅበዘበዘች ብቅ አለች:: ዊልቸሬን ወደኋላ አዙሬ መመለስ ነበር ያሰብኩት።ኤፍሬም ትከሻዬን ጨበጥ ጨበጥ ሲያደርገኝ ለመረጋጋት መጣር ጀመርኩ።በአንድ እይታ አወቅኳት፡፡ አቅራቢያዬ ሆናም ፍለጋዋን አላቆመችም። ሩካን አይታት ለፈገግታ ለማሸሽ የጀመረችውን ከንፈሯን ጨርሳ
ሙሉ ፈገግታ ከማሳየቷ በፊት አየችኝ። ከንፈሯን ሰበሰበችው።እኔ እንዴት ነው
ያልኩት? ፈገግኩ?አፈጠጥኩባት? ዓይኔን አሸሁ? የሆንኩትን እንጃ ብቻ
ድንጋጤዋ አቃዠኝ፡፡ ረቂቅ ብዙ ቅርቢያ እንዳለው ሰው ተጠመጠመችባት:: ማርቲ ደርቃ ቀርታለች፡፡ ዓይኗ ከዊልቸሬ
ላይ አልተነቀለም ነበር፡፡ ልቅረባት ልራቃት እያሰብኩበት ባልነበረበት ደቂቃ ኤፍሬም ዊልቸሬን ገፍቶ እግሯ ስር አደረሰው እና ለሰላምታ እጁን ዘረጋላት፡፡

"ኤፍሬም! የሩካ እጮኛ ነኝ! ስላንቺ ብዙ ሰምቻለሁ። እንኳን ደህና መጣሽ!" ለዘረጋላት እጅ አፀፋ እጁን እየዘረጋች
የተናገረውን የሰማችው አልመሰለኝም:: ፈዝዛ እያየችኝ ነው።ፈገግ አልኩ መሰለኝ። ከዛም እጄን ዘረጋሁላት በዘገምተኛ ሂደት ከኤፍሬም እጅ ያላቀቀችውን እጇን ሰዳ ጨበጠችኝ፡፡

"እንዴ? አትሳሳሙም እንዴ?" አለች ሩካ ምንም ያልተከሰተ እያስመሰለች፡፡ ጉንጬን ልትስመኝ ዝቅ አለች፡፡ አዟዙሬ
አቀበልኳት፡፡ ለተወሰነ ሰከንድ የሚያሳብድ ዓይነት ረጭታ ሆነ።

"እንንቀሳቀስ አይደል? የተቀረውን ናፍቆታችሁን እቤት ትወጡታላችሁ።" አለች አሁንም ሩካ ቶሎ ተሽቀዳድማ
አንደኛውን ሻንጣ ለመግፋት እየተሰናዳች፡፡ ሌላኛውን ሻንጣ
ኤፍሬም ያዘ፡፡ ዊልቸሬን ለመንቀሳቀስ አዞርኩ፡፡ ማርቲ እስከአሁን ዓይኗ ከእኔ ላይ አልተነቀለም።

"አይይ እኔ እንኳን ሆቴል ሄጄ ትንሽ ባርፍ ሳይሻለኝ አይቀርም።" አለች በደከመ ድምፅ:: በእርግጥ እቅዳችን እቤት
ከነሩካ ጋር ምሳ በልተን አብረን ወደ ሆቴሏ መሄድ ነበር። እኔ ማለቷ የጠበቅኩት ስለነበር ብዙም አልገረመኝም፡፡

“ኸረ በጭራሽ! እቤት ላንቺ ተብሎ ምሳ ተዘጋጅቷል፡፡ ሻወር መውሰድ ከፈለግሽም እቤት ትተጣጠቢያለሽ!" አለቻት ሩካ።መልስ ሳትመልስ ወደ መኪናችን ተከተለችን። ከዊልቸሬ ወደ
መኪና ለመግባት ተደግፌ ስነሳና ተንፏቅቄ ስቀመጥ እንደ ተዓምር አፍጥጣ እያየችኝ ነበር፡፡

ይሄ አቃጣሪ ጊዜ ህይወቴን ጣእም አልባ ሊያደርገው እንደሚናድ ድንጋይ ካብ ተንደርድሮ አሁን ላይ ደረሰ። ማርቲ ምሳ አብራን ከታደመች በኋላ ወደ ሆቴሏ ከሄደች ሁለት ቀን አለፈ።ላልቆጠርኩት ያህል ጊዜ ፃፍኩላት። ለአንዱም አልመለሰችልኝም።ሆቴሏንም መልቀቋን አረጋገጥኩ ኢትዬጵያ ውስጥ ልትጠይቀው የምትችለው ዘመድ እንደሌላት አውቃለሁ። ወይ ወደ ሃገሯ ተመልሳለች
👍4
#ቀላውጦ_ማስመለስ


#ክፍል_አንድ


#በሜሪ_ፈለቀ

ሲገባኝ ሁሉም ሰው የሆነች "የለውጥ ኩርባ" አለችው አስተሳሰቡ ወይ ስሜቱ ወይ ድርጊቱ የሚቀየርበት።ወደ አዲስ ምእራፍ የሚታጠፍበት ወይም ከወደቀበት መቀመቅ የሚስፈነጠርበት ወይም ለዛለው ጉልበቱ አቅም የሚያገኝበት።

=========================
“ማታ ከማን ጋር ባድር ደስ ይልሃል?” ወሬዋ እንዲያምርላት እና የወሬው አካል እንደሆንኩ እንዲሰማኝ (አብዛኛውን ጊዜ አይደለሁም::) ስትፈልግ ጥያቄ ታስመስለዋለች እንጂ ከእኒ መልስ ጠብቃ አታውቅም፡፡ ዝም ብላ ነው የምታወራው የምታወራልኝን ነገር መስማቴን ብቻ ካረጋገጠች ያለእረፍት
ትለፈልፋለች። እራሷ ትጠይቃለች። እራሷው ትመልሳለች።

"ከፍቃዱ ጋር!"

“ፍቃዱ ማን ነው?” ስላት በእርሷ ላይ እንዲሰማኝ የምትፈልገው የባለቤትነት ስሜት የተሰማኝ መስሏት ነው መሰለኝ ደስ ተሰኝታ ወሬዋን አድምቃ ቀጠለች። የማይገባኝ ባህርይዋ ይሄ ነው፡፡
በእርሷ ላይ ባለመብት እንድሆን ትፈልጋለች። ሌላ ሰው አየብኝ፣
ነካብኝ ኸረ አሰበብኝ ብዬ ሁሉ ዘራፍ! ብል ደስ ይላታል፡፡

“አርቲስቱ ነዋ! መጀመሪያ ስንሳሳም ነበር። በቃ ሲስመኝ ሲስመኝ...
ሊስመኝ ቆየና ምን ብናደርግ ጥሩ ነው?” እንዲህ ብዙ ጊዜ ያለማሰሪያ የምትበትነው ፀጉሯ እየተርገበገበ እና በእጆቿ አየሩን እየቀዘፈች እየተቅጠበጠች ስታወራ መላ ሰውነቷ
ከመወራጨቱ የተነሳ ልትበር የምታኮበኩብ ነው የምትመስለኝ።

“ምንም ብታደርጉ ጥሩ አይደለም፡፡” አልኳት ከአፏ ቀልቤ፡፡

“ጅል!” አለች። ከፍቃዱ ጋር ስትሰራ ያደረችውን የድሪያ ወሬዋን ስላናጠብኩባት በሽቃ፡፡ እንደዚህ ስትለኝ እንደሚያስጠላኝ ታውቃለች። ግን አትተውም። በበሽቀች ሰዓት ሁሉ “ጅል
ትለኛለች። የምጠላው ደግሞ ጅል መባል ብልጥ ከመባል ጋር ተነፃፅሮ ውድቀት ስለሆነብኝ አይደለም፡፡ ብቸኛው ምክንያቴ እናቴ ትለኝ ስለነበረ ነው። እናቴ የምትለኝ የነበረውን ነገር ሁሉ እጠላዋለሁ (እናቴ ውዳሴ ከአፉ አይወጣም እንጂ ውዳሴም ቢሆን ከስድቦቿ እንደአንዱ የሚሆንብኝ ይመስለኛል።)ምክንያቱም ከመገለፅ በላይ እጠላታለሁ።

ሴት ከብዙ አርጩሜና ከትንሽ ሰውነት የተሰራች ፍጥረት ትመስለኛለች፡፡ መግረፊያንና ሴትን ምን አገናኛቸው? ወለላ! ወለላን እናትህ ስለሚሉኝ እናቴ ናት እላለሁ። ከልቤ ግን ወለላን
ምኔም ባልላት ደስ ይለኛል፡፡

“የአባትህ ልጅ! ጅል የጅል ዘር!” የሚለው ስድቧ ገላዬ ላይ ከሚያርፈው ዱላዋ እኩል በቀን ለመዓት ጊዜ የምሰማው ነው፡፡ የአባቴ ካልሆነ የማን ልጅ ልሆን ነበር? ሲመስለኝ አባቴ እኔን
እንደሚመስል ስታወራ ሰምቻለሁ፡፡ ያን ማለቷ ይሆን? ወይስ አባቴ ጅል ነበር? እናቴን ጨምሮ ጅል የሚሉኝ ሁሉ የማይገባኝ ነገራቸው አለመዋሸቴን፣ አለማስመሰሌን፣ ያልመሰለኝን
አለማድረጌን፣ ለሚጠይቁኝ ጥያቄ ቀጥተኛ መልስ መመለሴን፣
ተንኮል አለማወቄን እና እነርሱ ብልጠት የሚሉትን ነገር ለመልመድ ራሴን አለማጣቴን ለምን ጅልነት እንደሚሉት ነው::
በተቃራኒው አፈቀላጤነትን፣ ያልሆኑትን መስሎ መታየትን፣መዋሽትን፣ ተንኮለኛነትን... እንደ ብልጥነት መቁጠራቸው ምነኛ አስተሳሰብ ይሆን?

ረድኤት አዳሯን እየነገረችኝ ከማታው የተረፈ ቡረቃዋ እንዳለቀቃት ነው የተሰማኝ፡፡ እኔ ግን ከልቤ ነበር፡፡ ፍቅረኛው ከሌላ ወንድ ጋር ያውም በዝና፣ በገንዘብ፣ በውበት እንደውም በቁመትም ጭምር ከሚበልጠው ታዋቂ አርቲስት ጋር ያሳለፈችውን የአዳር ተረክ ስትነግረው ጥሩ ነው' የሚል ፍቅረኛ
ይኖር ይሆን? በእርግጥ የኔ ፍቅረኛ ከፍቃዱ ጋር የባለገችው በህልሟ ነው፡፡ ቢሆንም 'ጥሩ አይደለም፡፡ አብሯት ማደሩን ከነገረችኝ ሰውዬ ጋር ራሴን ማነፃፀር የጀመርኩበት ምክንያት
ውሉ አልገባኝም፡፡ ህልሟን ባሰብኩ ቁጥር የሚረብሸኝ የትኛው እንደሆነ መነጠል አቃተኝ፡፡ እርሷ የሌላ ሰው መሆኗ ወይስ ሌላኛው ሰው እንደሚበልጠኝ ማሰቤ? ራሴን ከሌላ ሰው ጋር አነፃፅሬ ማወቄን እንጃ! ለንፅፅር የምቀርብ ስለመሆኔም እንጃ እኔ
በቃ ስህተት ነኛ! ስህተት ስሜ ነው ፣
መገለጫዬ ፣ ማንነቴ! ወለላ ልጇ መሆኔን እንኳን ለመናገር የምታፍርብኝ እናቴ ነበረች፣ ሰፈር ብዙ ሰው አያውቀኝም::
ቢያውቀኝም በስሜ ማንም አይጠራኝም እሷኑ ይለጥፉብኛል።የ'ወለላ ልጅ':: ትምህርት ቤት ስታስመዘግበኝ አፏን ሳያዳልጣት

“ስሙ ማን ነው?” ስትባል::
“ስህተት ወለላ” ብላ ነው ያስመዘገበችኝ፡፡ በህይወቴ ውስጥ
ትልቁን ስህተት ማስመዝገቧ አልገባትም፡፡ እሷ ከራሷ ውጪ
ለማንስ ግድ አላት? እኔ ለሷ ከዛ ያለፈ አልነበርኩም ስህተቷ ነኝ፡፡ ታዲያ ስህተት በምን ስሌት ለንፅፅር ይቀርባል?

የረድኤትን ህልም እያደረ ሳስበው በውን ብትባልግ ሳይሻል አይቀርም ነበር፡፡ ምክንያቱም ፍቅረኛዬ ይሄን ህልሟን ከነገረችኝ በኋላ ባህርይዋ የተቀየረ እየመሰለኝ መጣ፡፡ ቤት መዋል
የማትወደው ፍቅረኛዬ ስራ እየቀረች መተኛት ስትጀምር በህልሟ ያደረገችው ድሪያ እየወሰወሳት ልትደጋግም እየመሰለኝ ማሰብ ማቆም አቃተኝ። አጠገቤ ተኝታ በእንቅልፍ ልቧ ድምፅ
ባስማች ቁጥር ከፍቃዱ ጋር እየተላፋች እየመሰለኝ በቅናት ተብሰከሰኩ፡፡ 'አትተኚ አይባል? ህልም አታልሚ አይባል?
ህልሟን ጠላሁት፡፡ የማልጋፋው ባላጋራ ሆነብኝ፡፡ አንድ ዕለት በውድቅት ለሊት በውል ያልሰማሁትን ነገር ስታጉተመትም
ነቃሁ፡፡

“ረዲዬ.... ረዲ....”

“በስመአብ ወ ወልድ! ምነው?” አለችኝ ብርግግ ብላ ከእንቅልፏ እየባነነች።

“ምነው ፍቅሬ ከፈቃዱ ጋር እንትን እያደረግሽ ነበር እንዴ?”ስላት መብራቱን አብርታ ካፈጠጠች በኋላ “ጂላጅል! ከፈቃዱ ጋር አይደለም ከአለሙ ጋር ነው::” አለችኝ፡፡

“አለሙ ደግሞ ማነው? እሱም አርቲስት ነው?”

“እንከፍ! ኸረ ምን ዓይነቱን ነው የጣለብኝ?” ብላ እየተቆናጠረች
ጀርባዋን ሰጥታኝ ተኛች።

እሷ ህልሟን ካቆመችበት ለመቀጠል ይመስለኛል እንቅልፍ ጥሏት ስትወራጭ፣ ስታንኮራፋ እንቅልፍ አጥቼ እሰማታለሁ፡፡
ወለላ ደብድባኝ ስታበቃ ምንም የሚጎዳኝ ነገር እንዳላደረገች ተኝታ እንደምታንኮራፋው አልያም እያንጎራጎረች እንደምትኳኳለው።ወለላ እኔን ከመግረፍ በሚተርፋት ጊዜ የኔን
አባት ሳይጨምር እኔ የማውቃቸውን አምስት ባሎች አግብታ ፈታለች፡፡ አባቴን ጨምሮ ሁሉም ባሎቿ ጥለዋት ለመሄዳቸው ምክንያት እኔ እንደሆንኩ ትነግረኛለች፡፡ ምን እንደሚያገናኘው
ዛሬም ድረስ አይገባኝም፡፡ እሷ እንዳለችኝ አባቴ ማርገዟን ስትነግረው ጥሏት ስለሄደ እሺ ብዬ ገፊነቴን ልቀበልላት፡፡
ከአምስቱ ስንተኛው መሆኑን የማላስታውስው አንድም ዓመት
አብሯት ከኖረ በኋላ “አንቺ እኮ ልጅ እንዳለሽ እንኳን ያወቅኩት ካገባሁሽ በኋላ ነው:: ድብቅ ነሽ” ሲላት ሰምቻለሁ፡፡ ይሁን ለዚህኛውም ምክንያት ልሁናት፡፡ ከመታመሟ በፊት ለመጨረሻ
ጊዜ ያገባችው ባሏም ድሮ ሰራተኛዋ የነበረች ሴት ወልዳኝ ጥላባት ሄዳ እሷ እያሳደገችኝ እንደሆነ እንደነገረችው ሳላውቅ እናቴ መሆኗን ስነግረው መጨቃጨቃቸው ትዝ ይለኛል፡፡
ይሁንላት ለዚህኛውም ሰበብ ልሁናት፡ እራሷ ላጠፋችው ጥፋት፣ ባሎቿ ላጠፉት ጥፋት፣ ራሴም ላጠፋሁት ጥፋት
የምቀጠቀጠው እኔ ነኝ፡፡ እንደውም የማላውቃቸውን እና አብሬያቸው እንድጫወት የማትፈቅድልኝን የሰፈራችንን ልጆች ጥፋትም እኔ ሳልሆን እቀራለሁ የምቀጠቀጠው? የሰፈሩ እናቶች በሙሉ ቅጣታቸውን ሳይሰጧት ይቀራሉ?

ከረድኤት አጠገብ ተጋድሜ ሊነጋ ገደማ አንድ መላ መጣልኝ፡፡ 'እሾህን በእሾህ!!”

“መሌ በህልምህ ከሴት ጋር አድረህ ታውቃለህ? ማለቴ እንትን አድርገህ?” አልኩት መላኩን ሱቄ በር ላይ ከተሰበሰቡት
👍51🥰1
#ቀላውጦ_ማስመለስ


#ክፍል_ሁለት


#በሜሪ_ፈለቀ

“እኔንጃ!! ትዝ አይለኝም ግን አጥፍቼ ነው።”

“ወላዲተ=አምላክ!!!!:: ቆይ በምንድነው እንዲህ የመታችህ?”

“እኔንጃ በጫማዋ ሹል መሰለኝ፡፡” እያየኋት ድርቅ ብላለች።

“ምነው አንቺ አትገረፊም እንዴ?”

“ወላዲተ አምላክ!!!! ሰው እንዴት እንዲህ አድርጎ ልጁን ይመታል? አንተ እኮ ትልቅ ሆነሃል!!”

ምን እንዳለችኝ በትክክል የገባኝ ከዛን ዕለት በኋላ ጠዋት ጠዋት ከሰፈራችን የሚያስወጣው መታጠፊያ ላይ መኪናቸው ቆማ እየጠበቀችኝ ትምህርት ቤት አብረን መሄድ ከጀመርን በኋላ
ነበር፡፡ ትምህርት ቤት ደርሰን ስትወርድ አባቷ እንዴት ነበር ያደረጓት? የአንደኛውን እጃቸወሁን ጣቶች ፀጉሮቿ መሃል
እንደማበጠሪያ ሰክተው ወደራሳቸው አስጠጓት፡፡ እንደተለመደ ነገር እንደትክክል ሁሉ ነበር የሚያደርጉት፡፡ ከጉንጭዋ ይልቅ ለአንገቷ የቀረበ ቦታ ላይ ሳሟት። ለኔ ግን የመሰለኝ እንደዛ
አይደለም፡፡ በጆሮዋ የሆነ መለኮታዊ ልሳን ያወሩላት፣በከንፈራቸው ወደሳሟት ቦታ አንዳች ልገልፀው የማልችለው
ዓይነት ምትሃተኛ ነገር እንዳስተላለፉላት፣ በጣቶቻቸው በሆነ ትስስር እንዳሰሯት
እንደዛ ነገር፡፡ መልሳ ጉንጫቸውን
ሳመቻቸው ልበል? በየጠዋቱ ይሄን ትዕይንት ማየት ልክ የሆነ ሌላ ዓለም መኖሩን ነገረኝ፡፡ የምፈራው፣ ያልኖርኩበት እና የማላውቀው የሆነ በሰው ልጆች መሃል ያለ መሳሳብ መኖሩን ነገረኝ፡፡ ወለላ ገረፈችኝ፡፡ ረድኤት ማን ናት? ለምንስ ት/ቤት ያደርሱሃል? ምን አሉህ? ወለላ ሴሰኛ ናት አሉህ? ወለላ ምን
አድርጋው ነው አባትህ ጥሏት የሄደው አሉህ? የማላስታውሰው ጥያቄ እየጠየቀችኝ ደበደበችኝ፡፡ ይሄን ግርፊያ
የሚለየው እንባዬ አልወጣ አለኝ፡፡ አልለመንኳትም፡፡ ፀጥ!ጭጭ ብዬ ተመታሁላት፡፡ አልታገልኳትም፡፡ መምታቷን አቁማ አየችኝ፡፡

“ምን ሆነሃል?”

“ምን ሆንኩ?”

“ምን ይዘጋሃል? ምን አስበህ ነው?” ዝም አልኳት፡፡ ያ የመጨረሻ ዱላዋ ነበር፡፡ “ምን ትጠላለህ?' በሉኝ ወለላን ቀጥለህ
ምን ትጠላለህ?” በሉኝ ወለላን ከዛ በተረፈህ ጥላቻ ምን ትጠላለህ?' በሉኝ ወለላን!!

በሚቀጥለው ቀን የአጥሩ በር ተንኳኳ፡ ረድኤት ነበረች፡፡ለሰላምታ እጄን ዘረጋሁላት፡፡ እጄን ጨብጣ ወደራሷ
አስጠጋችኝና ጉንጬን ሳመችኝ፡፡ አዎ ጉንጬን በከንፈሯ ነካችው። እርጥበቷ ጉንጩ ላይ ታትሞ የቀረ መሰለኝ፡፡

“ለምንድነው ትምህርት ቤት የቀረኸው?”

“ከዛሬ በኋላ ት/ቤት አልመጣም!!”

“እንዴ ለምን?”

“አንቺ ምን አገባሽ? የሚበጀውን ራሱ አውቋል፡፡ ምን ቤት ነኝ ነው?” ወለላ ናት ከየት መጣች ሳልላት አጠገቤ ደርሳ
የመለሰችላት፡፡

“ደሞ ስሚ ሁለተኛ ደጄ ድርሽ ብትዪ ውርድ ከራሴ” አለቻት ቀጥላ፡፡

ረድኤት መልስ ሳትሰጣት ጊቢያችንን ለቃ ወጣች። እኔም ት/ቤት ቀረሁ፡፡ ወለላ ለረድኤት አባት ስሞታ ስለተናገረችባት እቤትም መጥታ አታውቅም፡፡ መንገድ ብታየኝም በርቀት በግንባሯ ሰላም
ብላኝ ታልፋለች እንጂ አትጠጋኝም፡፡ ወለላን ትፈራታለች፡፡ወለላ ደግሞ የኔ ጥላ ናት፡፡ ከዚህ በኋላ ረድኤትን በቅርበት
ያየኋት የዩንቨርስቲ ተማሪ ከሆነች በኋላ አባቷ የሞቱ ጊዜ ነበር፡፡ ስታለቅስ በህይወቴ ከፍተኛውን ሀዘን ያዘንኩበት ቀን ይመስለኛል፡፡ አሳዘነችኝ፡፡ ከዓመታት በፊት በጆሮዋ ሹክ ያሏት የመሰለኝ የመለኮታዊ ቃል ትዝ አለኝ፡፡ ከሰው መሃል ስታየኝ ሮጣ መታ ተጠመጠመችብኝ
ምን ማለቷ እንደሆነ ገብቶኛል አባቷን እያስታወሰችኝ ነው።ሰዎች ቃል ሳይለዋወጡ የሚለዋወጡት ስሜት እንዳለ ገብቶኛል፡፡ ወደራሴ
አስጠግቼ መልሼ አቀፍኳት። ምን እንደተረዳችኝ ባይገባኝም ያለቃል እኔ የነገርኳት “አባትሽ ላንቺ ምን ማለት እንደሆኑ ይገባኛል፡፡ የሀዘንሽ ጥልቀት ተሰምቶኛል የሚለውን ነበር፡፡
ከረድኤት አባት ሞት በኋላ ብዙም ባልራቀ ጊዜ ወለላ ልትቆጣጠራቸው ባልቻለቻቸው ሱሶቿ ምክንያት ማገገሚያ
ገባች፡፡ ከዚያ ቀናት ቀደም ብሎ የምንኖርበትን ቤት ካርታ ሰጠችኝ፡፡በራሷ ስም ነው ያለው ያጠረቀመችውንም በዛ ያለ ገንዘብ ሰጠችኝ (ሱቅ የከፈትኩት በዚያ ብር ነው፡፡)

ወለላ ማገገሚያ ከገባች በኋላ ረድኤት እንደልቧ ቤቴ መመላለስ ጀምራለች፡፡ በሆነ ትምህርት ተመርቃ ስራ እየፈለገች ነበር።አንድ የሆነ ቀን እቤት ተቀምጬ እያለሁ መጣች። ዝም ብላ አጠገቤ ያለ ወንበር ላይ ተቀመጠች። እጄን ከጭኔ ላይ አንስታ እንደማሸት ነገር እንደመዳበስ አደረገችው፡፡ ዝም ብዬ አየኋት።

“ለምን እንደምወድህ ታውቃለህ?”

“አይደለም ምክንያቱን እንደምትወጂኝም አላውቅም፡፡” ስላት አናደድኳት መሰለኝ ተበሳጨችብኝ፡፡ የሚቀጥለውን ለመናገር
ጊዜ ወሰደች፡፡ ከልቤ ነው ያልኳት በማንም ስለመወደድም ማንንም ስለመውደድ ግድ ሰጥቶኝም አስቤም አላውቅም፡፡

“እወድሃለሁ!! የምወድህ ደግሞ ልብህ ስለሚያምር ነው፡፡”

“ልብህ ስለሚያምር?”

“አዎን ብዙ እውነትና ትንሽ ጥላቻ የተሸከመ ንፁህ ልብ ነው ያለህ!”

“ጥላቻ የሚያምር ነገር መሆኑን አላውቅም፡፡ ጥላቻን የተሸከመ
ልብ ንፁህ መባሉም አይገባኝም፡፡” አልኳት።

“አያምርም፡፡ አዎን ጥላቻ አያምርም፡፡ አየህ እውነትህን? ሁሉም ሰው በልቡ ለማንም ማሳየት የማይፈልገው ቆሻሻ ይኖረዋል፡፡ጥላቻ፣ ክፋት፣ ግልፍተኝነት፣ ራስን መውደድ... አንዱ ይኖርበታል፡፡ ልዩነቱ ብዙዎቻችን ያ ባህሪያችን በአስገዳጅ ሁኔታ ፈንቅሎን ካልተገለጠ በስተቀር ንፁህ ፣ ቅን እና ፍፁም
እንደሆንን እናስመስላለን፡፡ አንተ እንደዛ አይደለህም፡፡የተሰማህንና የሆንከውን ብቻ ነው የምትኖረው፡፡ የኖርከው
ህይወት የፈጠረብህን ጥላቻና ሽሽት አትደብቀውም፡፡ ያ ደግሞ እንድትድን ያደርግሃል፡፡ አንተ ክፉ ልብ የለህም፡፡ ማንንም መጉዳት አስበህ አትጎዳም፡፡”

ያወራችው ብዙው አልገባኝም፡፡ ከዚህም በላይ ብዙ ነገር አውርታለች፡፡ ከወሬዋ ይልቅ እጄን እየዳበሰችው ያለችው የእጇ
ድብሻ ደስ ብሎኛል፡፡ ረዣዥም የእጇን ጣቶች በትኩረት እያየሁ የምታወራውን ሙሉ በሙሉ አልሰማኋትም፡፡ ተጠጋችኝ
መሰለኝ፡፡ በየትኛው ቅፅበት ከንፈሯ ከንፈሬ ላይ እንዳረፈ አላውቅም፡፡ መሳም ብቻ አይደለም የሳመችኝ : አንድ የሆነ ነገር አድርጋኛለች፡፡ ከገለፃ በላይ የሆነ ምትሃተኛ ነገር፣ ደም የሚመላለስበት አካሌ ብቻ ሳይሆን ፀጉርና ጥፍሬ እንኳን
የሚሰማው ዓይነት ምትሃት!በደነዘዝኩበት ጥላኝ ወጣች፡፡

ከዚያ ቀን በኋላ ግን ውስጤ አንድ የሆነ አዲስ ነገር ተፈጥሯል።
ወለላ ማገገሚያ መግባቷን ሳውቅም ልጠይቃት አልሄድኩም።እንደውም እንደማትመለስ እርግጠኛ እንደሆንኩ ሁሉ ወይም ባትመለስ ምኞቴ እንዲሰምር እየፈለግኩ ተነስቼ የወለላን የግል ንብረቶች መበርበር ጀመርኩ፡፡ምን እንደምፈልግ እንኳን በትክክል ሳላውቅ የሆነ ነገር እፈልጋለሁ። ያን ማድረጌ ረድኤት ያለችኝን በልቤ ያለች ትንሽዬ ጥላቻ ለመቀነስ ወይም ለማጥፋት
ይሆን? በየዕለቱ እያነበበች የምታለቅስባቸውን ደብዳቤዎቿን
ይዛቸው መሄዷን ስገነዘብ ለአፍታም ቢሆን ማን እንደሚፅፍላት የማወቅ ጉጉት አደረብኝ፡፡ በካርቶን ያጠረቀመቻቸው ብዙ ፖስታዎች ናቸው:: እስከቅርብ ዓመታት በየወሩ ፖስታ ቤት
እየሄደች አንድ አዲስ ፖስታ ይዛ ትመጣለች፡፡ አንብባ ስትጨርስ
ከቀደሙት ጋር ብትቀላቅለውም ሁሌም ብቻዋን ስትሆን ከምትቆልፍበት መሳቢያ ውስጥ እያወጣች ደጋግማ ታነባቸዋለች። አባቴ ይሆን? ወይ ከባሎቿ አንዱ? አልያም ከተለያየ ሰው የሚላክ ይሆናል። ብቻ ቅጥ ያጣ ራስ ወዳድነቷን ዘልቆ በልቧ ቦታ ያገኘ ሰው መሆን አለበት ምናልባት የበደለችው ሰው አልያም ደብዳቤውን መፃፍ ያቆመው ሞቶ
መሆን አለበት።
👍5
#ቀላውጦ_ማስመለስ


#ክፍል_ሶስት


#በሜሪ_ፈለቀ

ትለኛለች።እውነቱን ሳወራት ይከፋታል። አኮረፈች። ጥላኝ ግን አልሄደችም።

"አንተጋ ልደር?” አለችኝ፡፡“

“ደስ ይለኛል!” አልኳት እንድትሄድ አልፈለግኩም፡፡

“የት እተኛለሁ?”

"የተመቸሽ ቦታ"

የተመቻት ቦታ ከኔጋ አልጋዬ ላይ መተኛት ነበር፡፡ እንደዛ አደረገች፡፡ እንደብዙ ነገር አደረገች፡፡ ልብሶቼን ከላዬ እንዴት ገፋ
ጣለቻቸው? ከመቼው አልጋው ላይ ወደቅን?ከላዬ ነበረች? በየትኛው ቅፅበት ከስሬ አገኘኋት? የማላውቃት የሆነች ልጅ ነበረች፡፡ የደስታ ሲቃዬን ያበዛችው ግን የማላውቃት ባዕድ ነገር የሆነችብኝ፡፡ ከሰውነቴ አጣብቄ እንዳቀፍኳት ነጋ፡፡

“አትሂጂ አብረሽኝ ኑሪ!” አልኳት፡፡

ትወደኛለህ?” ብላ ጠየቀችኝ።

“እኔንጃ!” መለስኩላት።

ከእናቷ ጋር ብዙ ከተነታረከች በኋላ አብራኝ መኖር ጀመረች፡፡ልክ ያልሆነ ነገር ያለው አኗኗር መሆኑ ይገባኛል፡፡ አብራኝ
ልትኖር የወሰነች ቀን ማታ በድጋሚ “ትወደኛለህ ወይ?” ብላ ጠየቀችኝ፡፡ በማላውቀው ምክንያት ይሄ ጥያቄዋ የሚከብድ ነገር አለው፡፡ መውደድ፣ ናፍቆት፣ ፍቅር ዓይነት ላሉ ስሜቶች
እርግጠኛነቴን እንጃ፡፡ ስሜቱ ምን ስለመምሰሉም አላውቅም።

“ስትስሚኝ ደስ ይለኛል፡ ባለፈው ዕለት እንትን ስናደርግም በጣም ነው ደስ ያለኝ።

“አብሮ ለመኖር ይሄ በቂ አይደለም፡፡ ፍቅር ነው ዋናው! እንደወደድከኝ እስኪሰማህ ድረስ አብሬህ እሆናለሁ፡፡ ነገር ግን ምንም አናደርግም፡፡” ያለችው ምን ያህሉ እንደገባኝ አልገባኝም፡፡

“ቆይ አንቺ ስናደርግ ደስ አላለሽም ነበር?”

“ፍቅር የሌለበት ወሲብ ማድረግ አልፈልግም፡፡” የምጠይቃትና
የምትመልስልኝ አልገጣጠም ይለኛል፡፡ እኔ እስከገባኝ ያደረግነው የሁለታችንም ደስታ የነበረበት ነገር ነበር፡፡ ብቻዬን ያደረግኩ፣ደስታው የእኔ ብቻ እንደነበር፣ እርካታው የግሌ ብቻ እንደሆነ እንዲሰማኝ ለምን እንደምታደርግ አይገባኝም፡፡ እንድዋሻት ትፈልጋለች፡፡ ምክንያቱም ራስዋን መዋሸት ስለምትፈልግ።በፍቅር ስም ለፍቅር ብላ ጭኖቿን እንደከፈተችልኝ እንጂ ለስሜትዋና ለደስታዋ ስትል ከማይወዳት ወንድ ጋር እንዳደረገችው በማሰብ ለራሷ ያላትን ግምት ዝቅ ማድረግ አትፈልግም፡፡ ደስታን መፈለግ ክፋቱ አይገባኝም፡፡ ለምን ሌላ ምክንያት ይለጠፍበታል? ለሁለት ወራት እንደዚህ አብረን ከኖርን በኋላ ነበር ህልሟን የነገረችኝ፡፡ ከፈቃዱ ጋር የሰራችውን የህልም ፍቅር!

በመላኩ ምክር ቅደም ተከተል መሰረት ከመተኛቴ በፊት አንዲት ፍቅረኛዬ የምታደንቃትን ታዋቂ ሴት አርቲስት ገላ ለማሰብ ሞከርኩ፡፡ከፍቅረኛዬ ውጪ የማንም ሴት ገላ ሊከሰትልኝ አልቻለም፡፡ ከዛሬ ሁለት ወር በፊት ለመጀመሪያም ለመጨረሻም ጊዜ ከላዬ ሆና ዛር እንዳለበት ሰው ካበደችው እብደት ውጪ
ምንም ወደ ሀሳቤ ሊመጣልኝ አልቻለም፡፡ በእርግጥ እንዴትስ ማሰብ ይቻለኝ ነበር? ከሷ ውጪ የሴት እርቃን በፊልም እንኳን
ማየቴ ትዝ አይለኝም፡፡ ያየኋቸውን በአንድ የእጅ ጣት የሚቆጠሩ ፊልሞችም እሷው ናት ያሳየችኝ፡፡ ሴቶቹ ልብሳቸውን አውልቀው የሚያሳይ ቦታ ነበረው? አላስታውስም፡፡

“እ? ተሳካልሽ? ማታ ቺኳ ከች አለች?” አለኝ መላኩ ሱቄን ጠዋት እንደከፈትኩ ለወሬ ቸኩሎ።

“አላለችም ::አንተ ነህ ከች ያልክብኝ!! አልኩት መናደዴን እንዲያውቅ ጥርሴን ነክሼ።ላለመሳቅ እየታገለ።

“ምን ሳደርግ?” አለኝ።

“ብዙውን አላስታውስም፡፡ በጥፊ ስታልሰኝ ነው ከእንቅልፌ የባነንኩት” ስለው እስኪበቃው አገጠጠ፡፡ በህልሜ ረድኤትን የማስቀናቱ ሀሳብ አልተሳካልኝም።

“መነጋገር አለብን!” አልኳት አዋርቻት በማላውቀው ድምፀት፡፡ስታወራ እሰማታለሁ እንጂ ራሴ ርዕስ ፈጥሬ አዋርቻት አላውቅም።

"ዛሬ ወለላን ሄደን መጠየቅ አለብን።" አለችኝ ያልኳትን እንዳልሰማች ሁሉ ርዕስ ቀይራ:: ትናንትና ከሰዓት የወለላ ነፍስ
አባት እቤት ድረስ መጥተው ጉበቷ አደገኛ ደረጃ ላይ ስለደረስ ከማገገሚያ ወጥታ ከፍተኛ ሆስፒታል ከተኛች መክረሟን ከነገሩን ሰዓት ጀምሮ በዚህ ጉዳይ ፀብ ቀረሽ ንትርክ ላይ ነን፡፡
እኔ እናቴን ላያት አልፈልግም፡፡ እርሷ ደግሞ ምንም ቢሆን እናቴ ስለሆነች የኛ ጥየቃ ይገባታል እያላች ችክ ብላለች። እኔ
ላናግራት የፈለግኩት በየእርምጃዬ ልረሳው ስላልቻልኩት ህልሜ ነበር። ጭቅጭቋ ሊያሳብደኝ ስለደረሰ ቁርስ እንደበላን ሆስፒታል ሄድን፡፡ ወለላ ጉዷ ተጎትቶ የማያልቅ ሴት መሆኗን ባውቅም
ለአፍታ ሽው ባለች ቅፅበት አስቤው የማላውቀው ነገር ገጠመኝ።
የወለላ ልጅ የእኔ ታላቅ ወንድም ሲያስታምማት አገኘሁት፡፡የተፈጠረው ነገር የሆነ የተልወሰወሰ ነገር አለው። መቼ ነው የወለደችው? አላሳደገችውም ማለት ነው? ለነገሩ ተገላገለ ከድብደባ ነው የተረፈው። ያላሳደገችውን እናቱን እንዴት እናቴ ብሎ ይጠራታል? እንዴትስ እያደረ ያስታምማታል? ይሄን
የማስበው የወለላ ልጅ መሆኑን በነገረኝ ቅፅበት ረድኤት እየተውረገረገች ወንድሙ መሆኔን ስትነግረው እርሱም እልፍ እያሰበ በመሰለኝ ሽርፍራፊ የጊዜ ክፍተት ነው። ምክንያቱም እሱም ወንድም እንዳለው አያውቅም። እርሱ ዝም አላለም።የሰማው ነገር ልክ መሆኑን ሲያረጋግጥ እድሜዬን ጠየቀኝ እና
ከራሱ ጋር ማስላት ጀመረ። በስምንት ዓመት እንደሚበልጠኝ ነገረኝ። ስራ እንዳለበት ነግሮን ሲወጣ አንድ ጥያቄ ብቻ ጠየቅኩት።

"ደብዳቤ የምትፅፍላት አንተ ነበርክ?" በመገረም እያስተዋለኝ አለመሆኑን ነግሮኝ ወጣ: ወንድም ማግኘቴ ከመገረም ልቆ የሰጠኝን ስሜት አላወቅኩትም።ወንድሜ ጥሩ ሰው ይመስላል፡፡ወለላን መውደዱን ግን ማመን አልቻልኩም። ረድኤት ከስራ
እስክትመለስ ሱቅ ቆሜ በሀሳብ እዚህ እዚያ ስረግጥ ዋልኩኝ።ዛሬ ሳላናግራት አላድርም እያልኩ ስዝት ውዬ መጣች።

“ጠዋት ስለምን ነበር ልታወራኝ የነበረው?” አለችኝ እራት የበላንበትን ሰሃን እያነሳሳች።

“እየቀናሁ ነው!” አልኳት፡፡

“አልገባኝም!!” አለችኝ የያዘችውን ሰሃን መልሳ እያስቀመጠች።

“አየሁት ካልሽኝ ህልም ውጪ ምንም ማሰብ አልቻልኩም፡፡”ስላት ሳቀች፡፡ ከት ብላ ሳቀች፡፡

“ጅል ነህ! ጅልነትህን ግን እወደዋለሁ፡፡"

“ጅል አትበይኝ! አትበይኝ በቃ!! የኔ ብቻ እንድትሆኚ መፈለግ ጅልነት ነው? ሌላ ሰው እንዳይነካብኝ መሳሳት ጅልነት ነው?
ስራ ውለሽ እስክትመጪ ላይሽ መጓጓቴ ነው ጅልነት? አቅፌሽ እያደርኩ ለራሴ ስሜት ሳይሆን ላንቺ ቃል መጠንቀቄ ጅልነት ነው? የቱ ነው ጅልነት? ከንፈርሽን መናፈቄ ነው ጅልነት?ንገሪኝ ይሄ ጅልነት ነው?” እንደዚህ መናገር መቻሌን ያወቅኩት ዛሬ ነው።

“አይደለም፡፡” አለችኝ እኔ ከምናገርበት የቁጣ ጩኸት ተቃራኒ በሆነ ለስላሳ አንደበት፡፡

“ይሄ ጅልነት አይደለም ፍቅር ነው ማሬ” አለችኝ፡፡ በፈገግታዋ መሃል ዓይኖቿ እንባ ሲያረግዙ አየኋቸው፡፡ ሳማት ሳማት
የሚለኝን ስሜቴን ማቆም አልቻልኩም። ከማድረጌ ቀድሞ ግን ስልኬ ጠራ! ወንድሜ ነው:: ዛሬ ጠዋት አውቆኝ ፍቅር ፍቅር ሊጫወት ከሆነ እየተገረምኩ ዝም ብዬ ስልኩን አየዋለሁ።የማንሳት ጉጉት አልነበረኝም።ረድኤት እንዳነሳው ስትነግረኝ ግን አነሳሁት፡፡ ምንድነው ያለኝ?

"ስህተት እናታችን ሞታለች:: ማለቴ ተገድላለች::"ሲለኝ መሞቷ አልገረመኝም: አላሳዘነኝምም:: አሟሟቷ እንጂ!
ወለላ እኔን ስትቀጠቅጥ እና ባሎች አግብታ ስትፈታ ኖራ......ኖራ......... ኖራ........ የረሳሁላት ከፍተኛ ምግባር አለ፡፡ስትራገም ኖራ ኖራ....... በተጨማሪ ደብዳቤ ስታነብ ኖራ...ኖራ... ለእኔ የማያልቅ ከሚመስል ዘመን በኋላ በሀያ ሁለት ዓመቴ ሞተች፡፡ እሰይ ሞተች!
👍31
#ቀላውጦ_ማስመለስ


#ክፍል_አምስት


#በሜሪ_ፈለቀ

ውድ አንባብያን ምንም የተቀየረ ድርሰት የለም እስካሁን የቀረቡትም በቀጣይም የሚቀርበውም #የቀላውጦ_ማስመለስ ተከታይ ክፍሎች ናቸው ነገር ግን ሃሳቦች በሙሉ ላያልቁ ይችላሉ እነዲዚ ሲያጋጥም በራሳችሁ እየጨረሳቹ አንዳንድ ታሪኮች ደሪሲው ብቻ አይጨርሳቸውም አመሰግናለው።
=========================

ስምሪት ነቅታ ተንቀሳቀሰች። ዓይኖቿ ስትገልጣቸው ድልህ መስለዋል። በመጠኑ እፎይታ ተሰማኝ። አርሴማ መንቃቷን ስታውቅ ቦረቀች::

"ወደ ቤት መልሰኝ ምንም አልሆንም አንዳንዴ እንዲህ ያደርገኛል" አለችኝ የሆነውን ከነገርኳት በኋላ፡፡

"አንዳንዴ? መታየት አለብሽ?"

“እንቅልፍ ተኚ፣ እረፍት አድርጊ፣ ፈሳሽ ውስጂ” ነው የሚሉኝ" አለች ከእግሮቼ ላይ ለመነሳት እየተነቃቃች። ብዙ
በእንቢታዋ ፀናች፡፡ ሀሳቧን እንድትቀይር
እየነተረኳት ወደ ቤት ተመለስን፡፡ ምንም የማውራት ፍላጎት አልነበረኝም፡፡ እሷም እቤቷ መቀመጤ ምቾት የሰጣት
አይመስለኝም፡፡ አርሴማ እናቷ ጉያ ተሸጉጣ ቁልጭ ቁልጭ እያለች አንዴ እኔን አንዴ እናቷን ታያለች።

"ደህና ትሆኛለሽ? ልሂድ?" አልኳት፡፡

"አዎን ደህና እሆናለሁ ሂድ!" አለችኝ የመገላገል አይነት ስሜት ባለው ድምፅ።

ከቤቷ ወጥቼ በእግሬ ብዙ መንገድ እየተጓዝኩ ጭንቅላቴ ስለስምሪት የግርታ ቁልል መደርመሱን አላቆመም:: (ይህቺ ሴት ማናት? አላውቃትም ነበር ማለት ነው? ወይም የፖሊስ ልብሷን ስታወልቅ ቁሌታም ትሆናለች?) እንዲህ የማስበው መታጠቢያ ቤቷ ውስጥ ተዘርራ ያየሁት ሰውነቷ አንድ በአንድ ሲታወሰኝ
ነው። መሬቱ ላይ ተዘርራ አልፎ አልፎ የሳሙና አረፋ ሰውነቷ ላይ መኖሩ ሸራ ላይ የተሳለች ስዕል አስመስሏት ነበር። ከፊል ፀጉሯ ወለሉ ላይ ተበትኗል፡፡ ከፊሉ በትከሻዋ አልፎ ደረቷንና የግራ ጡቷን ሸፍኖታል፡፡ (ፀጉሯን ሁሌም ጠቅልላ ነው
የማውቃት ረዥም ፀጉር እንዳላት አስቤ አላውቅም፡፡ ኸረ ፀጉር እንዳላትም ትኩረት ሰጥቼ አይቻት አላውቅም።) የቀኝ እጇ የቀኝ ጡቷን በከፊል ከልሎ ዘንፈል ብሏል፡፡ ጡቶቿ በአንድ ጨረፍታ እይታ ብቻ በጭንቅላት ውስጥ ይሳላሉ፡፡ የግራ እጇ ወለሉ ላይ ተጥሏል።ከጀርባዋ የተጣበቀው ሆዷ እና ከታችኛው አካሏ ጋር ሲተያይ የሌላ ቀጭን ሴት የሚመስል የሰመጠ ወገቧ በአንድ ጎኗ ወለሉን ተደግፈዋል፡፡ እግሮቿ በመጠኑ ገርበብ ብለው ቀኙ አጠፍ ብሎ ግራው ተዘርግቷል። አይቼ አለመገረም ያቃተኝ
ዙሪያውን ተላጭታው ለ'እሙሙዬዋ" የቀረበ ቦታ ላይ ትንሽዬ ሶስት ማዕዘን ቅርፅ የተወችለት ጭገሯ ነው፡፡ ይህቺን ሴት በፍፁም አላውቃትም።

ራሴን ፣እሷን፣ ልጇን፣ እየዛቆሉ የሚኖሩትን ይህ በስባሳ ኑሮ እያሰብኩ ሳይታወቀኝ ብዙ ተጓዝኩ፡፡ረበሸኝ፡፡ ግድ የለኝም፣ ረስቼዋለሁ፣ ተሻግሬዋለሁ ትላንት ልቤን እየጨመደደ ሲፈነቅለኝ ይታወቀኛል። ደጋግሜ አጨስኩ።ራስ ምታት ጀመረኝ፡፡

ያለፈው በሚመጣው ላይ ምንም ጥቀርሻ መተው የለበትም ብዬ ያለፈውን ከኔ አርቄ የጣልኩ ይመስለኝ ነበር፡፡ ምናልባት አይቻል ይሆናል፡፡ ዛሬ ከተከሰተው ክስተት ምኑ ከኔጋ እንደሚያያዝ አላውቅም።የሰው
ልጅ ሁሉ ከትላንቱ ተጋብቶ ሳይሆን
አይቀርም የሚኖረው። ዛሬው የትላንት ጭማቂ ነዋ!! የዛሬ ግቡ የትናንት ምክንያቱ ነበራ! ከዓመታት በፊት እናቴ ወይ አባቴ ያነቡት እንባ ምክንያቱን እንኳን ሳይቀይር በልጃቸው ጉንጭ
ላይ ሊወርድ ይችላል፡፡ አባቶች በበሉት መራር ፍሬ የልጆች ጥርስ በለዘ አይነት ሆኖብኝ ትላንት ትዝታ ብቻ አለመሆኑ
የገባኝ ዛሬ ነው፡፡ ትናንት ትውልድን እንኳን ጥሶ እንደሚያልፍ አስቤ አላውቅም ነበር፡፡ ሀበሻ ሙዚቃው ውስጥ እንኳን ትዝታ ስልት መኖሩ ከትናንት መፋታት አለመፈለጉ ወይ አለመቻሉ ይሆናል፡፡ ስልኬ ጮኸ፡ ስምሪት ናት። ደነገጥኩ።

"ወዬ ምነው? አመመሽ እንዴ?"

“ኸረ ደህና ነኝ። ቅድም ስላልተረጋጋሁ አመሰግናለሁ እንኳን ሳልልህ!”

“አሁን አልሺኝ!" ብያት ስልኬን ዘጋሁት:: ከትናንትናዬ መዘጋጋት ግን አቃተኝ።

እናቴ ሸርሙጣ ነበረች፡፡ ሀገር ያወቃት ሽርሙጣ፡፡ ስለእርሷ ሲወራ የምሰማው የባሎቿን ብዛት እና የወንዶቿን መደራረብ
ነበር፡፡ እኔን እንኳን ከማን እንደወለደችኝ አታውቅም:: ባሏ ነው የሷ ዲቃላ መሆኔን የሚነግረኝ፡፡ እሷም ጋንጩራ የሰፈረባት
ቀን ሂድ ከዚህ ጥፋ! ዲቃላ ትለኛለች ስትሰድበኝ የሌላ ሰው ነውር እንደሆንኩ ሁላ... እናቴ ምንም አትገባኝም:
አንዳንዴ አቅፋኝ ስቅስቅ ብላ ታለቅሳለች፡፡ ወዲያው መልሳ ለዓይኗ እቀፋትና ዞር በልልኝ ትለኛለች፡፡ ቆንጆ ናት።ህልም የመሰለች ቆንጆ! ባሏ ደግሞ ጥንቅቅ ያለ ሱሰኛ ነው:: እናቴንና ባሏን በተመለከተ ብዙ ያልጠየቅኳቸው ያልተመለሱልኝ
ጥያቄዎች አሉ። ማወቅም አለማወቅም የሚሰጠኝ ሽራፊ ስሜት አልነበረም፡፡ እናቴ እንዴት አንድ ዘመድ እንኳን አይኖራትም? አላውቅም! የምንኖርበትን ቪላ አወረሱኝ የምትላቸው ቤተቦቿ
እንዴት አንዲት የዘር ትራፊ አይኖራቸውም? ለምን በየቀኑ
ከተለያየ ወንድ ጋር ትሆናለች? ሲያሻት ራሱ ጠባቂ ለሚያስፈልገው ባሏ ትታኝ የት ነው ከርማ የምትመጣው? ባሏስ
ከመስከር ውጪ የሚያደርገው የመልስ
ምት እንዴት አይኖርም? አላውቅም። እነሱ ለኔ ግድ እንደሌላቸው ሁሉ እኔም
ጉድጓድ ቢገቡ ግድ አልነበረኝም፡፡ አብራን በምትሆንባቸው ምሽቶች እሱ ሰክሮ ይገባል። እሷ ተኳኩላ ትወጣለች፡፡ ለቀናት ጥላን የምትጠፋበት ጊዜም የእድሜዬ ግማሽ ያህል ነው።
ለዓመታት ያልነበረችበት ዘመንም ነበረ። የስምንት ዓመት ልጅ ስሆን ጥላን ሄደች:: የት መሆኑን ባሏም አያውቅም፡፡ ከሁለት ዓመት በኋላ ስትመለስም የማንንም ጥያቄ ያለመመለስ መብትና እብሪት ነበራት። የሚቀጥለውን አራት ዓመት አብራን ስሆን ብቅ ጥልቅ ማለቷ ቀርቶ ለባሏ ጥላኝ ሄደች።እሷ ኖረችም
ሄደች ለውጡ ምንም ነው። ልጥገብ ወይ ልራብ፣ ልደስተ ወይ ልዘን፣ ልክሳ ወይ ልወፍር፣ ልማር ወይ ሜዳ ልዋል፣
ልታመም ወይ ጤነኛ ልሁን ሁለቱም ግዳቸው አይደለሁም ምናቸውም አልነበርኩም። አብሬያቸው ሆኜ የረሱኝ ይመስላሉ።

በእርግጥ በፍቅር ከመደኅየታችን ውጪ በኑሮ የጎደለ ሽንቁር አላስታውስም።እሷ በማትኖርበት ጊዜም ከምንኖርበት ትልቁ ቤት ጀርባ የሚከራዩ ሰርቪስ ቤቶች በየወሩ ገቢ ስለነበረን አንቸገርም ነበር።

“እናትህ ሸርሙጣ ናት! ወንድ አትጠግብም።ለገንዘብ ብላ አይደለም የምትሸረሙጠው ሽርሙጥና ሱስ ሆኖባት ነው።ይለኛል ባሏ ይዞ ከመጣው ቢራ እየቀዳልኝ:: ጠዋት ግን ገንዘብ
ስትሰጠው አየዋለሁ።ከርሱ ጋር በየቀኑ እየሰከርኩ ማደር ልምዱ ነበር። ይቀዳልኛል፣ ይቀደድልኛል፣ ቀደዳውንም
ቢራውንም እጋታለሁ። አጣጩ እንጂ የማድግ ልጁ አይደለሁምና በየቀኑ የሚግተኝ አልኮል ምን እንደሚጎትትብኝ
ግድ አልነበረውም።እንደባል የሚጫወተው ምንም ካለመኖሩ
የተነሳ ለማመን ምንም ታክል የማይቀረኝን ሀሜት ስለእርሱ
ሳድግ ሰምቻለሁ። እናቴን ያገባት ትሰራ ከነበረችበት ሽርሙጥናዋ አስትቷት እንደነበር እራሱም ሲያወራ ሰምቻለሁ።
ሆቴል ስትሰራ ደንበኛዋ ከነበረ ሰው ጋር በትገባኛለች ፀብ አክሱሙ ከጥቅም ውጪ መሆኑን ሲያሙት በተደጋጋሚ
ሰምቻለሁ። ለወጉ በዓመቱ መጀመሪያ እንድታስመዘግበኝ ተለማምጫት ወይም እርሱን ለምኜው ት/ቤት እገባለሁ።
ዓመቱን ሙሉ እመላለሳለሁ፡፡ ስንተኛ ክፍል እንደሆንኩ አያውቁም። እድሜዬንም ይዘነጉታል። የትምህርት ቤት ስሜን ሁሉ የማስታውሳቸው እኔ ነኝ። የአባቴ ስም የባሏ ስም ነው።

"የማንም ዲቃላ አባት አይደለሁም:: አባትህን ሄደህ ፈልግ::"ይለኛል ከሷ ጋር ሲጣላ፡፡ እኔ ለነሱ የለሁም
👍2
#ቀላውጦ_ማስመለስ


#ክፍል_ስድስት


#በሜሪ_ፈለቀ

ግፈኛዋ እናቴን መሰልሽኝ፡፡ ግን በተለየ ወደድኩሽ፡ ነው የምላት? እንኳን ለርሷ ለራሴ የተደበላለቀ ነገር አለው። ለርሷ
ላስረዳት ቀርቶ ለራሴም አልገባኝም፡፡ እኔም አልገባኝም። ስምሪት ለምን እናቴን አስታወሰችኝ? “ስምረት ሞተች የሚለው
የአርሴማ ጥሪ የፈጠረብኝ ድንጋጤ እንዴት ብሽቅ ለሆነው የአሁኑ ስሜቴ ጎታች ምክንያት ሆነ? በውል ያልለየሁት
ለስምሪት የተሰማኝ ስሜት በምን ስሌት ወደልጅነት ትዝታዬ አሽመጠጠኝ? አላውቅም!! ምናልባት እስከማስታውሰው ለሰው ግድ የሰጠኝ በዚህ ክስተት ስለሆነ? ምናልባት ሰው መሆን ለሰው ማሰብን ያካትት ይሆን? ምናልባት ሰው ሆኜ ይሆን? ምናልባት ሰው በሆንኩ ቅፅበት እንደሰው ግድ ሳይሰጡኝ
ያለፍኳቸውን ክስተቶች ማሰላሰል መጀመሬ ይሆን? አላውቅም!!
ብቻ ምንም ሽራፊ ስሜት አይሰጠኝም ያልኳቸው ስንጣቂ የኑሮ ሰበዞቼን ሳይቀር ሳልፈልግ እያሰብኳቸው ነው።

"እያስጨነቅኩህ ነው?" አለችኝ ስምሪት ደጋግማ የማልወዳትን እናቴን እና የተለየ ስሜት የፈጠረችብኝን ሴት ምን
እንዳመሳሰላቸው ስትጠይቀኝ ቆይታ።

"እናቴን እንደማልወዳት እርግጠኛ እየሆንኩ አይደለም።" መለስኩላት። በእርግጥ የሚሰማኝ የትኛው እንደሆነ
አልለየሁትም። አቅፋኝ ታለቅስ ለነበረችው እናቴ ይሁን ቁብ ለማትሰጠኝ እናቴ የማልለየው ሀዘን ይቦረቡረኛል፡፡ ደግሞ
ተመልሶ የሚያንገሸግሽ ንዴት እና ጥላቻ ይግተለተልብኛል፡፡
ስምሪት ፀጥ አለችኝ፡፡ ዓይኖቿን አጥብባ ስታየኝ ቆየችና።

"ለምን አታረጋግጥም?" አለችኝ፡፡

"ምኑን?"

"ለእናትህ የሚሰማህን ስሜት?"

"እንዴት? በምን?"

“ፈልጋቸዋ!! ፈልገህ አግኛቸው።"

“የት ብዬ? ትሙት? ትኑር? እንኳን ማወቅ
ይከብዳል፡፡ብዙ ዓመት አልፏል።" ይሄን ለሷ ስመልስላት ራሴን ሰማሁት።ጥያቄዬ ልፈልጋት? ወይስ አልፈልጋት? የሚለውን እርከን አልፏል። 'አልፈልጋትም'የሚለውን
ጭራሽ አለማሰቤ አስገረመኝ። እሷም ይህ የገባት መሰለኝ፡፡ ፈጠን ብላ።

"ራስህን ዝግጁ ካደረግክ ፍንጭ የምናጣ አይመስለኝም::" አለችኝ
ዝግጁነቴን ለማረጋገጥ ነው መሰል ከአፌ የሚወጣውን ቃል አፏን ከፍታ እየጠበቀች፡፡ ፀጥ አልኩ። ፀጥ አለችኝ፡፡ እያየኋት እንደሆነ ሲገባት ታቀረቅራለች፡፡ እያየችኝ እንደሆነ ሳውቅ ዓይኖቼን በሌላ አቅጣጫ አርቄ እልካቸዋለሁ።

"ስምሪት?"

"አቤት?"

“እስኪ አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ?" ራሷን በመነቅነቅ እንድቀጥል ተስማማችልኝ፡፡

"ለምንድነው ከሌላ ሰው በተለየ የምትቀርቢኝ? የምትሰሚኝ?
የምታወሪኝ?" የጠበቀችው ሌላ ጥያቄ እንደሆነ ሁሉ ፊቷ ረገበ።

ከአይምሮ ይልቅ ልብ ይማርከኛል፡፡" መልሷ እርግጠኛነት ነበረው፡፡

"ማለት?"

| “ከእውቀት ይልቅ ለቅንነት ዋጋ እሰጣለሁ ማለት ነዋ!! ቅንነት የሌለበት እውቀት በዜሮ ይባዛብኛል፡፡ቅንነት የሞላበት አለማወቅ እንኳን ይገዛኛል። ልብህ ቅን ነው::" ብላኝ ከኔ መልስ
እንደማትጠብቅ ተደላደለች። እሷ በገለፀችኝ ልክ ልበ ቅን መሆኔን እጠራጠራለሁ። ምክንያቱም ቅንነት ይመነዘራል ይመስለኛል፡፡ እኔ ስለራሴ እስከማውቀው ከራሴ ውጪ ለማንም
ግድ ኖሮኝ ለሰዎች ቀና ለማድረግም ሆነ ቀና ለማስብ ተጨንቄ አላውቅም። ማንም ጉዳዬ አይደለም።እሷ ሁሌም እንደዚህ ናት፡፡ ስለእኔ ስታወራ ባለቤቱ እርግጠኛ ከሆንኩት በላይ እርግጠኛ ናት፡፡ ምናልባት እኔ ራሴን ከማዳምጠው በላይ እሷ ስለምታዳምጠኝ ይሆናል። ሁሌም የምትጠቁመኝ ኪሩቤል መድረስ የሚችልበትን ጫፍ እንጂ ሰዎች ወይ እሷ መዳረሻ ብለው የሰቀሉትን ጫፍ አይደለም።

"ስምሪት?" ባልጠራትም እየሰማችኝ እንደሆነ አውቃለሁ።ከእስከዛሬው ሁሉ በተለየ እንድትሰማኝ ፈለግኩ፡፡

"አቤት?"

“ከዛን ቀን በኋላ አንቺን እንደአለቃዬ ወይም እንደጓደኛዬ ማሰብ እየቻልኩ አይደለም።" አልኳት። ከአፌ እስኪወጣ እየጠበቀችው ያለ ንግግር እንደሆነ ሁሉ መገረምም መደንገጥም ሳይታይባት

"አንድ እርምጃ ጠልቀህ ያወቅከኝ ስለመሰለህ ነው?" መልስ
የምትፈልግም አትመስልም።

“ማለት?" አልኳት ያለችው ሳይገባኝ ቀርቶ ሳይሆን የማስረዳት አቅም ከድቶኝ፡፡

"ኪሩ ልብሳቸውን ስትገፍ ያወቅካቸው እንደሚመስሉህ ሴቶች እርቃኔን ስላየኸኝ ገበናዬን የገለብክ አይምሰልህ፡፡"
የምታወራበት ቅላፄ የማላውቀውና ምሬት የተቀላቀለበት ነው፡፡ ምን
እንደምላት እና ለሷና ለማውቃቸው ሴቶች የሚሰማኝን የአንድ ጤፍ ፍሬና የተራራ ያህል የገዘፈ የስሜት ልዩነት ማስረዳት ባለመቻሌ ተናደድኩ።

"እንደዛ አይደለም የተሰማኝ። ውስጤ የቀረውን የገላሽን ምስል ሳስበው አብሬሽ መተኛት አይደለም የሚሰማኝ፡፡ ተሰምቶኝ በማያውቅ መልኩ ከወለሉ ላይ አንስቼሽ አልጋ ላይ ያደረስኩሽ ቅፅበት የእድሜ ዘመኔን ያህል ረዥም እንዲሆን ነው የሚሰማኝ፡፡ ክንዴ ላይ እንዳቀፍኩሽ የተከደኑ ዓይኖችሽን በስስት እያየሁ ዘመኖቼ ቢያልቁ ነው የተሰማኝ፡፡” ይግባት አይግባት እንጃ ከዚህ በላይ ማስረዳት ግን አቃተኝ፡፡ ደቂቃዎችን ትንፋሽ ያጠረኝ እስኪመስለኝ ፀጥ አለች፡፡
ሲገባኝ ሁሉም ሰው የሆነች "የለውጥ ኩርባ" አለችው።አስተሳሰቡ ወይ ስሜቱ፡ ወይ ድርጊቱ የሚቀየርባት።ወደ አዲስ ምዕራፍ የሚታጠፍበት ወይም ከወደቀበት መቀመቅ የሚስፈነጠርበት ወይም ለዛለው ጉልበቱ አቅም የሚያገኝበት፡፡ለውጥ ወደ ተሻለ ማደግ ብቻ አይደለምና ኩርባውን ሲታጠፍ
ውድቀትም ሊሆን ይችላል፡፡ ያቺ የለውጥ ኩርባ አንድ የሆነች ኢምንት ክስተት ልትሆን ትችላለች ወይም ዓረፍተ ነገር ወይም አንዲት ቃል ምናልባት አንዲት መሳም ወይም የአንዲት ደቂቃ
መታቀፍ ወይም...

የኔ የለውጥ ኩርባ ያቺ ቀን ነበረች።

"ልክ አይሆንም። እኔና አንተ ከዚህ ቀደም ከነበረን የዘለለ ግንኙነት ሊኖረን አይችልም::" አለችኝ፡፡

"ቅድም 'ከአእምሮ ይልቅ ልብ ይማርከኛል አልሺኝ አይደል?

" እህ... " የምቀጥለውን ለመስማት እየሰገገች።

"ሲገባኝ ሌላ ፍቺው ከስሌት ይልቅ ለስሜት ቅርብ ነኝ ማለትሽ መሰለኝ፡፡ ልክና ስህተቱን በስሌት ልቀምርልሽ አልችልም። ባንቺ ፍቅር ከመውደቅ በላይ ልክ የሆነ ስሜት ተሰምቶኝ እንደማያውቅ ግን ላረጋግጥልሽ፡፡" አልኳት አሁንም ምን ያህል እንተረዳችኝ ባይገባኝም።

"ምናልባት እስክጋደምልህ ይሆናል። ፍላጎትህ እስኪረግብ!"ከአፉ የሚወጣው ቃልም ድምፀትም የሷ አይመስልም:: ጥርሷን እያፏጨች ነው የተናገረችው። በመጀመሪያ ደነገጥኩ፡፡ ስምሪት
እንዲህ ስትናገር ሰምቼ አላውቅም:: በመቀጠል ተናደድኩ።በፍፁም እየተረዳችኝ አልነበረም።በመሰለስ ግን ስለዚህች ሴት የማላውቀው ብዙ ነገር መኖሩን ማሰብ ጀመርኩ፡፡

ስደነግጥ

ለኔ ሳይሆን ለእርሷ ማንነት የማይመጥናት የመሰሉኝን ቃላቶች
በማውራቷ ዓይኖቼን ጎልጎዬ አፈጠጥኩባት።

ስናደድ

“እየገባሁሽ አይደለም።ስለሴክስ እያወራሁ አይደለም። እዚህ ጋር(ልቤን በእጄ ደግፌ) ስለሚሰማኝ ስሜት ነው እየነገርኩሽ የነበረው።" አልኳት በአፏ አልመለሰችልኝም:: ፊቷ ግን ስልችት
አሳየኝ፡፡

ማሰብ ስጀምር

"ማነው?" አልኳት

“ማን?" መለሰችልኝ

እንዲህ እንዲሰማሽ ያደረገሽ?" በረዥሙ ተንፍሳ ፀጥ አለች።


💫ይቀጥላል💫

Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍4