አትሮኖስ
279K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
457 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ቀላውጦ_ማስመለስ


#ክፍል_አምስት


#በሜሪ_ፈለቀ

ውድ አንባብያን ምንም የተቀየረ ድርሰት የለም እስካሁን የቀረቡትም በቀጣይም የሚቀርበውም #የቀላውጦ_ማስመለስ ተከታይ ክፍሎች ናቸው ነገር ግን ሃሳቦች በሙሉ ላያልቁ ይችላሉ እነዲዚ ሲያጋጥም በራሳችሁ እየጨረሳቹ አንዳንድ ታሪኮች ደሪሲው ብቻ አይጨርሳቸውም አመሰግናለው።
=========================

ስምሪት ነቅታ ተንቀሳቀሰች። ዓይኖቿ ስትገልጣቸው ድልህ መስለዋል። በመጠኑ እፎይታ ተሰማኝ። አርሴማ መንቃቷን ስታውቅ ቦረቀች::

"ወደ ቤት መልሰኝ ምንም አልሆንም አንዳንዴ እንዲህ ያደርገኛል" አለችኝ የሆነውን ከነገርኳት በኋላ፡፡

"አንዳንዴ? መታየት አለብሽ?"

“እንቅልፍ ተኚ፣ እረፍት አድርጊ፣ ፈሳሽ ውስጂ” ነው የሚሉኝ" አለች ከእግሮቼ ላይ ለመነሳት እየተነቃቃች። ብዙ
በእንቢታዋ ፀናች፡፡ ሀሳቧን እንድትቀይር
እየነተረኳት ወደ ቤት ተመለስን፡፡ ምንም የማውራት ፍላጎት አልነበረኝም፡፡ እሷም እቤቷ መቀመጤ ምቾት የሰጣት
አይመስለኝም፡፡ አርሴማ እናቷ ጉያ ተሸጉጣ ቁልጭ ቁልጭ እያለች አንዴ እኔን አንዴ እናቷን ታያለች።

"ደህና ትሆኛለሽ? ልሂድ?" አልኳት፡፡

"አዎን ደህና እሆናለሁ ሂድ!" አለችኝ የመገላገል አይነት ስሜት ባለው ድምፅ።

ከቤቷ ወጥቼ በእግሬ ብዙ መንገድ እየተጓዝኩ ጭንቅላቴ ስለስምሪት የግርታ ቁልል መደርመሱን አላቆመም:: (ይህቺ ሴት ማናት? አላውቃትም ነበር ማለት ነው? ወይም የፖሊስ ልብሷን ስታወልቅ ቁሌታም ትሆናለች?) እንዲህ የማስበው መታጠቢያ ቤቷ ውስጥ ተዘርራ ያየሁት ሰውነቷ አንድ በአንድ ሲታወሰኝ
ነው። መሬቱ ላይ ተዘርራ አልፎ አልፎ የሳሙና አረፋ ሰውነቷ ላይ መኖሩ ሸራ ላይ የተሳለች ስዕል አስመስሏት ነበር። ከፊል ፀጉሯ ወለሉ ላይ ተበትኗል፡፡ ከፊሉ በትከሻዋ አልፎ ደረቷንና የግራ ጡቷን ሸፍኖታል፡፡ (ፀጉሯን ሁሌም ጠቅልላ ነው
የማውቃት ረዥም ፀጉር እንዳላት አስቤ አላውቅም፡፡ ኸረ ፀጉር እንዳላትም ትኩረት ሰጥቼ አይቻት አላውቅም።) የቀኝ እጇ የቀኝ ጡቷን በከፊል ከልሎ ዘንፈል ብሏል፡፡ ጡቶቿ በአንድ ጨረፍታ እይታ ብቻ በጭንቅላት ውስጥ ይሳላሉ፡፡ የግራ እጇ ወለሉ ላይ ተጥሏል።ከጀርባዋ የተጣበቀው ሆዷ እና ከታችኛው አካሏ ጋር ሲተያይ የሌላ ቀጭን ሴት የሚመስል የሰመጠ ወገቧ በአንድ ጎኗ ወለሉን ተደግፈዋል፡፡ እግሮቿ በመጠኑ ገርበብ ብለው ቀኙ አጠፍ ብሎ ግራው ተዘርግቷል። አይቼ አለመገረም ያቃተኝ
ዙሪያውን ተላጭታው ለ'እሙሙዬዋ" የቀረበ ቦታ ላይ ትንሽዬ ሶስት ማዕዘን ቅርፅ የተወችለት ጭገሯ ነው፡፡ ይህቺን ሴት በፍፁም አላውቃትም።

ራሴን ፣እሷን፣ ልጇን፣ እየዛቆሉ የሚኖሩትን ይህ በስባሳ ኑሮ እያሰብኩ ሳይታወቀኝ ብዙ ተጓዝኩ፡፡ረበሸኝ፡፡ ግድ የለኝም፣ ረስቼዋለሁ፣ ተሻግሬዋለሁ ትላንት ልቤን እየጨመደደ ሲፈነቅለኝ ይታወቀኛል። ደጋግሜ አጨስኩ።ራስ ምታት ጀመረኝ፡፡

ያለፈው በሚመጣው ላይ ምንም ጥቀርሻ መተው የለበትም ብዬ ያለፈውን ከኔ አርቄ የጣልኩ ይመስለኝ ነበር፡፡ ምናልባት አይቻል ይሆናል፡፡ ዛሬ ከተከሰተው ክስተት ምኑ ከኔጋ እንደሚያያዝ አላውቅም።የሰው
ልጅ ሁሉ ከትላንቱ ተጋብቶ ሳይሆን
አይቀርም የሚኖረው። ዛሬው የትላንት ጭማቂ ነዋ!! የዛሬ ግቡ የትናንት ምክንያቱ ነበራ! ከዓመታት በፊት እናቴ ወይ አባቴ ያነቡት እንባ ምክንያቱን እንኳን ሳይቀይር በልጃቸው ጉንጭ
ላይ ሊወርድ ይችላል፡፡ አባቶች በበሉት መራር ፍሬ የልጆች ጥርስ በለዘ አይነት ሆኖብኝ ትላንት ትዝታ ብቻ አለመሆኑ
የገባኝ ዛሬ ነው፡፡ ትናንት ትውልድን እንኳን ጥሶ እንደሚያልፍ አስቤ አላውቅም ነበር፡፡ ሀበሻ ሙዚቃው ውስጥ እንኳን ትዝታ ስልት መኖሩ ከትናንት መፋታት አለመፈለጉ ወይ አለመቻሉ ይሆናል፡፡ ስልኬ ጮኸ፡ ስምሪት ናት። ደነገጥኩ።

"ወዬ ምነው? አመመሽ እንዴ?"

“ኸረ ደህና ነኝ። ቅድም ስላልተረጋጋሁ አመሰግናለሁ እንኳን ሳልልህ!”

“አሁን አልሺኝ!" ብያት ስልኬን ዘጋሁት:: ከትናንትናዬ መዘጋጋት ግን አቃተኝ።

እናቴ ሸርሙጣ ነበረች፡፡ ሀገር ያወቃት ሽርሙጣ፡፡ ስለእርሷ ሲወራ የምሰማው የባሎቿን ብዛት እና የወንዶቿን መደራረብ
ነበር፡፡ እኔን እንኳን ከማን እንደወለደችኝ አታውቅም:: ባሏ ነው የሷ ዲቃላ መሆኔን የሚነግረኝ፡፡ እሷም ጋንጩራ የሰፈረባት
ቀን ሂድ ከዚህ ጥፋ! ዲቃላ ትለኛለች ስትሰድበኝ የሌላ ሰው ነውር እንደሆንኩ ሁላ... እናቴ ምንም አትገባኝም:
አንዳንዴ አቅፋኝ ስቅስቅ ብላ ታለቅሳለች፡፡ ወዲያው መልሳ ለዓይኗ እቀፋትና ዞር በልልኝ ትለኛለች፡፡ ቆንጆ ናት።ህልም የመሰለች ቆንጆ! ባሏ ደግሞ ጥንቅቅ ያለ ሱሰኛ ነው:: እናቴንና ባሏን በተመለከተ ብዙ ያልጠየቅኳቸው ያልተመለሱልኝ
ጥያቄዎች አሉ። ማወቅም አለማወቅም የሚሰጠኝ ሽራፊ ስሜት አልነበረም፡፡ እናቴ እንዴት አንድ ዘመድ እንኳን አይኖራትም? አላውቅም! የምንኖርበትን ቪላ አወረሱኝ የምትላቸው ቤተቦቿ
እንዴት አንዲት የዘር ትራፊ አይኖራቸውም? ለምን በየቀኑ
ከተለያየ ወንድ ጋር ትሆናለች? ሲያሻት ራሱ ጠባቂ ለሚያስፈልገው ባሏ ትታኝ የት ነው ከርማ የምትመጣው? ባሏስ
ከመስከር ውጪ የሚያደርገው የመልስ
ምት እንዴት አይኖርም? አላውቅም። እነሱ ለኔ ግድ እንደሌላቸው ሁሉ እኔም
ጉድጓድ ቢገቡ ግድ አልነበረኝም፡፡ አብራን በምትሆንባቸው ምሽቶች እሱ ሰክሮ ይገባል። እሷ ተኳኩላ ትወጣለች፡፡ ለቀናት ጥላን የምትጠፋበት ጊዜም የእድሜዬ ግማሽ ያህል ነው።
ለዓመታት ያልነበረችበት ዘመንም ነበረ። የስምንት ዓመት ልጅ ስሆን ጥላን ሄደች:: የት መሆኑን ባሏም አያውቅም፡፡ ከሁለት ዓመት በኋላ ስትመለስም የማንንም ጥያቄ ያለመመለስ መብትና እብሪት ነበራት። የሚቀጥለውን አራት ዓመት አብራን ስሆን ብቅ ጥልቅ ማለቷ ቀርቶ ለባሏ ጥላኝ ሄደች።እሷ ኖረችም
ሄደች ለውጡ ምንም ነው። ልጥገብ ወይ ልራብ፣ ልደስተ ወይ ልዘን፣ ልክሳ ወይ ልወፍር፣ ልማር ወይ ሜዳ ልዋል፣
ልታመም ወይ ጤነኛ ልሁን ሁለቱም ግዳቸው አይደለሁም ምናቸውም አልነበርኩም። አብሬያቸው ሆኜ የረሱኝ ይመስላሉ።

በእርግጥ በፍቅር ከመደኅየታችን ውጪ በኑሮ የጎደለ ሽንቁር አላስታውስም።እሷ በማትኖርበት ጊዜም ከምንኖርበት ትልቁ ቤት ጀርባ የሚከራዩ ሰርቪስ ቤቶች በየወሩ ገቢ ስለነበረን አንቸገርም ነበር።

“እናትህ ሸርሙጣ ናት! ወንድ አትጠግብም።ለገንዘብ ብላ አይደለም የምትሸረሙጠው ሽርሙጥና ሱስ ሆኖባት ነው።ይለኛል ባሏ ይዞ ከመጣው ቢራ እየቀዳልኝ:: ጠዋት ግን ገንዘብ
ስትሰጠው አየዋለሁ።ከርሱ ጋር በየቀኑ እየሰከርኩ ማደር ልምዱ ነበር። ይቀዳልኛል፣ ይቀደድልኛል፣ ቀደዳውንም
ቢራውንም እጋታለሁ። አጣጩ እንጂ የማድግ ልጁ አይደለሁምና በየቀኑ የሚግተኝ አልኮል ምን እንደሚጎትትብኝ
ግድ አልነበረውም።እንደባል የሚጫወተው ምንም ካለመኖሩ
የተነሳ ለማመን ምንም ታክል የማይቀረኝን ሀሜት ስለእርሱ
ሳድግ ሰምቻለሁ። እናቴን ያገባት ትሰራ ከነበረችበት ሽርሙጥናዋ አስትቷት እንደነበር እራሱም ሲያወራ ሰምቻለሁ።
ሆቴል ስትሰራ ደንበኛዋ ከነበረ ሰው ጋር በትገባኛለች ፀብ አክሱሙ ከጥቅም ውጪ መሆኑን ሲያሙት በተደጋጋሚ
ሰምቻለሁ። ለወጉ በዓመቱ መጀመሪያ እንድታስመዘግበኝ ተለማምጫት ወይም እርሱን ለምኜው ት/ቤት እገባለሁ።
ዓመቱን ሙሉ እመላለሳለሁ፡፡ ስንተኛ ክፍል እንደሆንኩ አያውቁም። እድሜዬንም ይዘነጉታል። የትምህርት ቤት ስሜን ሁሉ የማስታውሳቸው እኔ ነኝ። የአባቴ ስም የባሏ ስም ነው።

"የማንም ዲቃላ አባት አይደለሁም:: አባትህን ሄደህ ፈልግ::"ይለኛል ከሷ ጋር ሲጣላ፡፡ እኔ ለነሱ የለሁም
👍2