#የመልስ_ጉዞ…
:
ክፍል- #አንድ
✍
:
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
ፍእማዊ መንግስታዊ አስተዳደር ፤ፍፁማዊ ማህበረሳብ አወቀቀር፤ፍፁማዊ የተፈጥሮ ሚዛኗን የጠበቀች ሀገር..በዩቶፕያ ፅንሰ ሀሳብ የታነፀች ማለት ያቺ ነች ፡፡በነብያት አዕምሮ ውሰጥ ከዘመናት በፊት ተፀንሳ ትንቢት የተነገረላት ሰማያዊ የመኖሪያ ስፍራ በነአፍላጦስ ምናብ የተፀነሰችና በምድር ለመገንባት የተመኙላት ምድራዊ እንከን አልባ የሰለጠኑና የበቁ ማህበረሰቦች የሚኖሩባት ፤በፍፅም ፍትሀዊነት እና በጋራ ህግ የሚመራ መንግስት ያላት፤ ለገነት የቀረበ ልምላሜ ኖሯት አንድ ቀን በጋራ ስምምነት ፍፅማዊ ደስታ የምታመነጭ ተደርጋ የምትመሰረት ምድራዊ ከተማ ….
ታዲያ ይህቺ የአለማዊው እሳቤ እና የመንፈሳዊው ትንቢት ቀላቅላ የያዘች ዩቶፐያ ከወዴት ነች?የሀይማኖት ነብያት እንደሚሉት በሰማይ ከሞት ቡኃላ ባለው ህይወት የሚያገኞት ወይስ ሰው የልዕለ ሰብነትን ዙፋን ሲቆናጠጥ ፍፁም ፍትሀዊ፤ ፍፁም ዘመናዊ ብቃት ባገኘ ጊዜ በብቃትና በጥበቡ እዚሁ ምድር ላይ የሚመሰርታት….?
ወደ ዩቶፕያ መሄጂያ መንገዱ በየት ነው…ዩቶፕያስ የት ነው እውን ሊሆን የሚችለው ….?
እግዚያብሄር መላክ በምስራቅ በኤደን የአትክልት ስፍራ አዘጋጀ ያበጀውንም ሰው በዛ አኖረው፡፡እግዚያሄር አምላክ ለዓይን የሚያስደስት ለመብልም መልካም የሆነውን ዛፍ ሁሉ በምድር አበቀለ፡፡ በአትክልቱ ቦታ መልካም የህይወት ዛፍ ነበር፡፡እንዲሁም መልካምና ክፍውን መለየት ሚያስችል የዕውቀት ዛፍም ነበር፡፡የአትክልት ስፋራ የሚያጠጣው ወንዝ ከዔደን ይፈስ ነበር ፡፡ከዚያም በአራት ተከፍሎ ይፈስ ነበር፡፡የመጀመሪያው በምድሩ ወርቅ የሚገኝበት በሐዊላ ምድር ዙሪያ ሁሉ የሚፈሰው የፊሶን ወንዝ ነው፡፡ኤውላጥ ምርጥ ሆነ ወርቅ መልካም መአዛ ያለው ከርቤና የከበረ ድንጋይ የሚገኝበት ምደር ነው፡፡ሁለተኛው በኢትዬጳያ ምድር ዙሪያ ሁሉ የሚፈስው ግዬን ወንዝ ነው፡፡ሶስተኛው ከአሶር በስተምስራቅ ሚፈሰው የጤግሮስ ወንዝ ሲሆን አራተኛው የኤፍራጠስ ወንዝ ነው፡፡ (ዘፍጥረት ም 2 ቁጥር 8-14 )
ለመሆኑ ይሄስ ስፍራ የት ነው?፡፡የአዳምና ሄዋን ቀደምት መኖሪያ ስፍራ ..?የእውቀትና የዘላለም ፍሬ የሚበቅልበት ሚስጥራዊ ስፍራ…?በአዳምና ሄዋና የተወከሉት የመጀመሪያዎቹ የሰው ልጆች በፈጣሪያቸው ላይ ከብልሁ እባብ ጋር የመከሩበት ፤የመከሩበት ብቻ ሳይሆን የዶለቱበትም ስፍራ የት ነው?፡ከዛስ እርቃናቸውን እንደሆኑ የተገለፀላቸው…?ያን ሰፊ እፍረታቸውን የጋረዱበት ቅጠልስ ከየትኛው ስፍራ ከየትኛውስ ዛፍ ላይስ የተገንጥለው ይሆን? …ከዛስ ወደየት ተባረሩ ?እንዚህ መሰረታዊ ጥያቄዎች ናቸው፡፡የመልስ ጉዞው ወደዛ ነዋ ፡፡አያቶቾ አዳምና ሄዋን ወደተባሩበት ስፍራ ወደ ሀገረ ገነት ...
ይህቺ ሀገር ኢትዬጵያ ነች፤ ይህቺ ሀገር የአያቴ ህልም ነች…ህልሙ ግን በከፊል እንኳን እውን ሳይሆን እድሜ እየተጫጫነው ነው፡፡ቢሆንም ለዚህ አንድ ዘዴ ዘይዷል …ህልሙ ህልሜ እንዲሆን አድርጎል…እንደሱ እንድመኝ ….እንደእሱ እንዳስብ…. ግን ይሄን ህልም እውን ለማድረግ እኔ ምን ማድረግ አለብኝ…ከሚስቴ ጋ እስክገናኝ ምንም የማውቀው ነገር አልነበረም..
አሁን ግን ወደ እዛች ስፍራ ጉዞ ጀምረናል ፡፡እኔና ሚስቴ ፡፡ሁለታችንም የተለያየ የግል ዓላማ አለን ፡፡ግን የየግል አላማችን ከተሳካን ቡኃላም የጋራም አንድ አላማ አለን፡፡ አዎ እንብርት የሆነውን ስፍራ ካገኘን ቡኃላ ዩቶፐያችንን በስፍራው ደግመን እንገነባለን..እንዴት አድርገን.? ወደፊት አብረን የምናየው ይሆናል፡፡
አሁን ወደዋናው የታሪኩ ክፍል ጠልቄ ከመግባቴ በፊት እራሴን ላስተዋውቃችሁ …መቼስ ታሪኬን ስትሰሙ አንዳንዶቻችሁ የተዛባ አዕምሮ የፈጠራቸው የእድሜ ልክ የቀን ቅዥቶች ልትሉት እንድምትችሉ እገምታለው፡፡ይሁንና የእኔን እውነት ነግራችሆለው፡፡ ሳልኩልና ሳልቀባባ ጥሬ እወነቱን ብቻ፡፡ማመን ያለማመን የእናንተ ፋንታ ነው፡፡ግን ከእኔ ጋር ወዳጅነት መስርታችሁ የምነግራችሁን ለማድመጥ በጣም ትዕግስተኛ እና አስተዋይ መሆን አለባችሁ፡፡ምክንያቱም የሆነ ርዕስ ተከትሎ የነገሮችን ቅደም ተከለተልን ጠብቆ ታሪኩን ከመጀመሪያው እስከመጨረሻው ያጫውተናል ብላቹ ምትጠብቁ ከሆነ ከአሁኑ እርማችሁን አውጡ ፡፡እና ንባባችሁን እዚህ ጋር አቋርጡ፡፡
የገዛ የራሴን ታሪክ ለሌላ ሰው እንዴት ማውጋት እንዳለብኝ መወሰን ስልጣን ያለኝ እኔ ብቻ ነኝ ፡፡ስለዚህ ዘባራቂነቴን ካልወደዳችሁት ምንም ልረዳችሁ አልችልም፡፡ዘባራቂነቴ የነፃነቴ መገለጫ ምልክት ነው፡፡ምናቤ በማንኛውም የስርዓትና የደንብ ሰንሰለት አለመጠፍነጉን የሚያሳይ ልቅ መጋለቢያ ሜዳ አይነት ነው፡፡ወይንም በሆነ ቦታ የታጠረ የኩሬ ውሀ ሳይሆን የአባይ አይነት ሀገር ተሸጋሪ ወንዝ ፡፡አዎ የእኔ አዕምሮ እንደዛ ነው፡፡ለነፍሴ ማደሪያ በተሰጠኝ አካል ያልተወሰነ እንዳምንበት ከቤተሰቤ በውርስ በተሰጠኝ ሀይማኖታዊ ዶግማ ያልታጠረ.. በተወለድኩበት ሀገር ድንበር ያልተከለለ….በተፈጠርኩበት ምድር የልተገደበ…እንደዛ ነው ምናቤ… እንደዛው ነው ሀሳቤ …..
እና ታዲያ እንዴት ሆኖ ነው ካልከኝ በዘመን ሂደት ሰው ያው ሰው ነውና መጎዝና አዲስ ነገር ማሰስ ተፈጥሮአዊው ባህሪው እንደመሆኑ መጠን አካባቢውን እየለቀቀ ሲያፈገፍግ ሲዋለድ ሲራባ ሲያፈገፍግ በሚሊዬን ዓመት ሂደት ውስጥ መቶች ውስጥ አለመን አዳረሰና በዚህ ሂደት ውስት ከተፈጥሮ እና እርስበርሱ በሚያደርገው ትግልና ፍትጊያ አእምሮውን እያዳበረ አዕምሮ ሲዳብር ደግሞ ለአካባቢውም ሆነ ለራሱ የነበረው እይታ እየተቀየረ የማምረቻ መሰሪያዎችን እየፈለሰፈ ንግድና እየጀመረ ሲመጣ መልሶ ወደ መነሻው ማየት ጀመረ…ኢትዬጵያ የሰው ዘር ተፈጥሮ የተበተነባት ምድር መልሶም አንድ ቀን የሚሰበሰብባት፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
:
ክፍል- #አንድ
✍
:
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
ፍእማዊ መንግስታዊ አስተዳደር ፤ፍፁማዊ ማህበረሳብ አወቀቀር፤ፍፁማዊ የተፈጥሮ ሚዛኗን የጠበቀች ሀገር..በዩቶፕያ ፅንሰ ሀሳብ የታነፀች ማለት ያቺ ነች ፡፡በነብያት አዕምሮ ውሰጥ ከዘመናት በፊት ተፀንሳ ትንቢት የተነገረላት ሰማያዊ የመኖሪያ ስፍራ በነአፍላጦስ ምናብ የተፀነሰችና በምድር ለመገንባት የተመኙላት ምድራዊ እንከን አልባ የሰለጠኑና የበቁ ማህበረሰቦች የሚኖሩባት ፤በፍፅም ፍትሀዊነት እና በጋራ ህግ የሚመራ መንግስት ያላት፤ ለገነት የቀረበ ልምላሜ ኖሯት አንድ ቀን በጋራ ስምምነት ፍፅማዊ ደስታ የምታመነጭ ተደርጋ የምትመሰረት ምድራዊ ከተማ ….
ታዲያ ይህቺ የአለማዊው እሳቤ እና የመንፈሳዊው ትንቢት ቀላቅላ የያዘች ዩቶፐያ ከወዴት ነች?የሀይማኖት ነብያት እንደሚሉት በሰማይ ከሞት ቡኃላ ባለው ህይወት የሚያገኞት ወይስ ሰው የልዕለ ሰብነትን ዙፋን ሲቆናጠጥ ፍፁም ፍትሀዊ፤ ፍፁም ዘመናዊ ብቃት ባገኘ ጊዜ በብቃትና በጥበቡ እዚሁ ምድር ላይ የሚመሰርታት….?
ወደ ዩቶፕያ መሄጂያ መንገዱ በየት ነው…ዩቶፕያስ የት ነው እውን ሊሆን የሚችለው ….?
እግዚያብሄር መላክ በምስራቅ በኤደን የአትክልት ስፍራ አዘጋጀ ያበጀውንም ሰው በዛ አኖረው፡፡እግዚያሄር አምላክ ለዓይን የሚያስደስት ለመብልም መልካም የሆነውን ዛፍ ሁሉ በምድር አበቀለ፡፡ በአትክልቱ ቦታ መልካም የህይወት ዛፍ ነበር፡፡እንዲሁም መልካምና ክፍውን መለየት ሚያስችል የዕውቀት ዛፍም ነበር፡፡የአትክልት ስፋራ የሚያጠጣው ወንዝ ከዔደን ይፈስ ነበር ፡፡ከዚያም በአራት ተከፍሎ ይፈስ ነበር፡፡የመጀመሪያው በምድሩ ወርቅ የሚገኝበት በሐዊላ ምድር ዙሪያ ሁሉ የሚፈሰው የፊሶን ወንዝ ነው፡፡ኤውላጥ ምርጥ ሆነ ወርቅ መልካም መአዛ ያለው ከርቤና የከበረ ድንጋይ የሚገኝበት ምደር ነው፡፡ሁለተኛው በኢትዬጳያ ምድር ዙሪያ ሁሉ የሚፈስው ግዬን ወንዝ ነው፡፡ሶስተኛው ከአሶር በስተምስራቅ ሚፈሰው የጤግሮስ ወንዝ ሲሆን አራተኛው የኤፍራጠስ ወንዝ ነው፡፡ (ዘፍጥረት ም 2 ቁጥር 8-14 )
ለመሆኑ ይሄስ ስፍራ የት ነው?፡፡የአዳምና ሄዋን ቀደምት መኖሪያ ስፍራ ..?የእውቀትና የዘላለም ፍሬ የሚበቅልበት ሚስጥራዊ ስፍራ…?በአዳምና ሄዋና የተወከሉት የመጀመሪያዎቹ የሰው ልጆች በፈጣሪያቸው ላይ ከብልሁ እባብ ጋር የመከሩበት ፤የመከሩበት ብቻ ሳይሆን የዶለቱበትም ስፍራ የት ነው?፡ከዛስ እርቃናቸውን እንደሆኑ የተገለፀላቸው…?ያን ሰፊ እፍረታቸውን የጋረዱበት ቅጠልስ ከየትኛው ስፍራ ከየትኛውስ ዛፍ ላይስ የተገንጥለው ይሆን? …ከዛስ ወደየት ተባረሩ ?እንዚህ መሰረታዊ ጥያቄዎች ናቸው፡፡የመልስ ጉዞው ወደዛ ነዋ ፡፡አያቶቾ አዳምና ሄዋን ወደተባሩበት ስፍራ ወደ ሀገረ ገነት ...
ይህቺ ሀገር ኢትዬጵያ ነች፤ ይህቺ ሀገር የአያቴ ህልም ነች…ህልሙ ግን በከፊል እንኳን እውን ሳይሆን እድሜ እየተጫጫነው ነው፡፡ቢሆንም ለዚህ አንድ ዘዴ ዘይዷል …ህልሙ ህልሜ እንዲሆን አድርጎል…እንደሱ እንድመኝ ….እንደእሱ እንዳስብ…. ግን ይሄን ህልም እውን ለማድረግ እኔ ምን ማድረግ አለብኝ…ከሚስቴ ጋ እስክገናኝ ምንም የማውቀው ነገር አልነበረም..
አሁን ግን ወደ እዛች ስፍራ ጉዞ ጀምረናል ፡፡እኔና ሚስቴ ፡፡ሁለታችንም የተለያየ የግል ዓላማ አለን ፡፡ግን የየግል አላማችን ከተሳካን ቡኃላም የጋራም አንድ አላማ አለን፡፡ አዎ እንብርት የሆነውን ስፍራ ካገኘን ቡኃላ ዩቶፐያችንን በስፍራው ደግመን እንገነባለን..እንዴት አድርገን.? ወደፊት አብረን የምናየው ይሆናል፡፡
አሁን ወደዋናው የታሪኩ ክፍል ጠልቄ ከመግባቴ በፊት እራሴን ላስተዋውቃችሁ …መቼስ ታሪኬን ስትሰሙ አንዳንዶቻችሁ የተዛባ አዕምሮ የፈጠራቸው የእድሜ ልክ የቀን ቅዥቶች ልትሉት እንድምትችሉ እገምታለው፡፡ይሁንና የእኔን እውነት ነግራችሆለው፡፡ ሳልኩልና ሳልቀባባ ጥሬ እወነቱን ብቻ፡፡ማመን ያለማመን የእናንተ ፋንታ ነው፡፡ግን ከእኔ ጋር ወዳጅነት መስርታችሁ የምነግራችሁን ለማድመጥ በጣም ትዕግስተኛ እና አስተዋይ መሆን አለባችሁ፡፡ምክንያቱም የሆነ ርዕስ ተከትሎ የነገሮችን ቅደም ተከለተልን ጠብቆ ታሪኩን ከመጀመሪያው እስከመጨረሻው ያጫውተናል ብላቹ ምትጠብቁ ከሆነ ከአሁኑ እርማችሁን አውጡ ፡፡እና ንባባችሁን እዚህ ጋር አቋርጡ፡፡
የገዛ የራሴን ታሪክ ለሌላ ሰው እንዴት ማውጋት እንዳለብኝ መወሰን ስልጣን ያለኝ እኔ ብቻ ነኝ ፡፡ስለዚህ ዘባራቂነቴን ካልወደዳችሁት ምንም ልረዳችሁ አልችልም፡፡ዘባራቂነቴ የነፃነቴ መገለጫ ምልክት ነው፡፡ምናቤ በማንኛውም የስርዓትና የደንብ ሰንሰለት አለመጠፍነጉን የሚያሳይ ልቅ መጋለቢያ ሜዳ አይነት ነው፡፡ወይንም በሆነ ቦታ የታጠረ የኩሬ ውሀ ሳይሆን የአባይ አይነት ሀገር ተሸጋሪ ወንዝ ፡፡አዎ የእኔ አዕምሮ እንደዛ ነው፡፡ለነፍሴ ማደሪያ በተሰጠኝ አካል ያልተወሰነ እንዳምንበት ከቤተሰቤ በውርስ በተሰጠኝ ሀይማኖታዊ ዶግማ ያልታጠረ.. በተወለድኩበት ሀገር ድንበር ያልተከለለ….በተፈጠርኩበት ምድር የልተገደበ…እንደዛ ነው ምናቤ… እንደዛው ነው ሀሳቤ …..
እና ታዲያ እንዴት ሆኖ ነው ካልከኝ በዘመን ሂደት ሰው ያው ሰው ነውና መጎዝና አዲስ ነገር ማሰስ ተፈጥሮአዊው ባህሪው እንደመሆኑ መጠን አካባቢውን እየለቀቀ ሲያፈገፍግ ሲዋለድ ሲራባ ሲያፈገፍግ በሚሊዬን ዓመት ሂደት ውስጥ መቶች ውስጥ አለመን አዳረሰና በዚህ ሂደት ውስት ከተፈጥሮ እና እርስበርሱ በሚያደርገው ትግልና ፍትጊያ አእምሮውን እያዳበረ አዕምሮ ሲዳብር ደግሞ ለአካባቢውም ሆነ ለራሱ የነበረው እይታ እየተቀየረ የማምረቻ መሰሪያዎችን እየፈለሰፈ ንግድና እየጀመረ ሲመጣ መልሶ ወደ መነሻው ማየት ጀመረ…ኢትዬጵያ የሰው ዘር ተፈጥሮ የተበተነባት ምድር መልሶም አንድ ቀን የሚሰበሰብባት፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍5
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ
:
#ክፍል_ሁለት
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
...ኢትዬጵያን በዩቶፐያ ፅንሰ ሀሳብ ዳግም መገንባት ከአያቴ የወረስኩት ህልሜ እና ዓላማዬ እንደሆነ ነግሬያችኃለው …ግን እንዴት አድርጌ ነው የማሳካው …?እንደማሳክው የማምነው ከራሴ በላይ በሚስቴ እምነት ስላለኝ ነው፡፡ሚስቴ …የዋናው የታሪኬ ማጠንጠኛ እሷ ነች፡፡እሷ ደግሞ መንፈስ ነች፡፡ገራሚ መንፈስ፡፡አስፈሪ መንፈስ፤ታሪካዊ መንፈስ፤አፍዛዥ መንፈስ…ሁሉን አድራጊ ፈላጭ ቆራጭ መንፈስ፡፡አዎ ስለእሷ የምነግራችሁ ነገር ቢኖር የደረስኩበትን እና ያወቅኩትን ብቻ ነው፡፡ያንን ስላችሁ በቃ ስለእሷ የማትነግረን ጥቂት ነዋ..?››ብላችሁ ታስቡ ይሆናል፡፡አይደለም:: እንደውም በተቀራኒው የምነግራችሁ ከእሷ ታሪክ አንጻር ጥቂቱን ግን በእኛ በሰውኛ ልኬት ከጆሮአችን የመስማት አቅም በላይ ከአይኖቻችንም የማየት ጉልበት በላይ በሆነ መጠን ነግራችሆለው፡፡
ምክንቱም ይህቺ ፍቅሬ ከሰፈር ጎረምሳነት በአንዴ ስለዓለም መፅአዊ እጣ ሚያስብና ለዛም የሚሰራ የሚተጋ ሰው አድርጋ መልሳ ዳግመኛ የፈጠረቺኝ ሴት ነች፡፡እሷ ደፋርም ገራሚም ፍጡር ነች፡፡ ሁሉ ነገር የማድረግ አቅም እንዳላት አምናለው፡እንዴት አድርጌ የምታደርገው ነገር ሁሉ የምትለውን ሁሉ አምናታለው፡፡የማምናት ጅል ሆኜ አይደልም፡፡በአፍቃሪነቴም ዓየነ-ልቦናይ ታውሮም አይመስለኝም፤የምትሰራቸውን የእጆቾን ተአምራቶች በአይኖቼ ደጋግሜ ሳላየው ላለማመን አልችልም፡፡ ግን ደግሞ ሚስጥሯን ሁሉ ትነግረኛለች ብዬ አላስብም…ከእኔ የተደበቀ የሆነ ዕቅድ ያላት መስሎ ይሰማኛል ፡፡ቢሆንም ደፍሬ ጠይቄያት አላውቅም፡፡
ግን የምታወራው ስለአፈቀርካት ሴት ነው ወይ..? ካላችሁኝ አዎ ስለእሷው ነው፤ግን እንደምታውቋት አይነት ሴት ብቻ አይደለችም… መንፈስም ጭምር ነች፡፡ምን አይነት መንፈስ..?እሱን ወደ ፊት አስረዳችሆለው….
ይህቺን ሴት ያገኘዋት በተለየ አጋጣሚ ነው፡፡በህይወቴ የመጨረሸውን ሀዘን ባዘንኩበት ቀን …የመጨረሻውን እጦት ባጣውበት ቀን…ወደ ልቤ ደም የሚወስዱና የሚመልሱ ትላልቅ የደም ስሮች የተበጠሱ የመሰለኝ ቀን፡፡አዎ የዛን ቀን ነበር ያገኘዋት …፡፡እንዴት እጦቴን በተአምሮ መለሰችልኝ…ሀዘኔን በድንቅ ስራዋ ወደምስራች ቀየረችልኝ…የተበጣጠሱትን የልብን ደም ስሮች ቀጣጥላ ለሞት ከቆረጥኩበት ስሜት አውጥታ መኖርን እንድናፍቅ አደረገቺኝ እና በዛኑ ቅፅበት ይህቺን ሴት ደነዘዝኩላት….፡፡
ወዲያው ነበር እግሯ ስር ተንበርክኬ እንዳፈቀርኳት የነገርኳት..ይቺን ሴት ፍቅሬን እንደተቀበለች ነበር ትንፋሽ ሳልሰጣት እንድታገባኝ የጠየቀኳት፡፡አግቢኝ ስላት ቤት አልነበረኝም .አግቢኝ ስላት ስራ አልነበረኝም…አረ አግቢኝ ስላት የሀይስኩል ትምህርቴን እንኳን አልጨረስኩም…አግቢኝ ስላት የማግባት ዕቅድም አልነበረኝም….አግቢኝ ስላት ዕድሜዬ እንኳን 18 ሊደፍን ገና 3 ወራቶች ይቀሩት ነበር..
ይህ ሁሉ ቢሆንም ዳሩ እንድታገባኝ ስጠይቃት
-እንዳገባህ የጠየቅከኝ ውለታ ስለዋልኩልህ ነው ወይስ ስላፈቀርከኝ›ነበር ያለቺኝ
-ሁለቱም ምክንያት ነው፡፡-መለስኩላት
-ይሁን የመጣውትም አንተን ለማግባት ስለሆነ ተቀብዬሀለው ››አለቺኝ
-አልገባኝ
-ቀስ ብሎ ይገባሀል ..ለማንኛውም ጥያቄህን ተቀብያለው ፡፡አገባሀለው፡፡
መልሶን ስሰማ ደንግጬ ነበር..እሺታዋን ስሰማ ፈዝዤ ነበር፡፡አዎ እሺታዋን አልጠበቅኩም ነበር፡፡
-ግን ቆይ የመጣውት ስትይ ከየት ነው የመጣሽው.?
ከዛኛው አለም ….ላለፈት መቶ አመት እዚህ አልነበርኩም፡፡
-ያው እየቀለደች ነው ብዬ
‹ከዛ በፊትስ?፡›ጠየቅኳት
-ከዛ በፊት አንድ አራት ጊዜ ተመላልሺያለው፡፡ፈርዶብኝ ጀግና ወዳለው፡፡በዚህ አካባቢ ማለቴ በኢትዬጵያ ጀግና መኖሩን ከሰማው በርሬ ለመምጣት ቀናትን አላባክንም›
-ይገርማል…አሁን ታዲያ ማን ተገኝቶ ነው የመጣሺው.?›
-ነገርኩህ አንተን..
-እኔን …እኔ ታዲያ እንዴት ነው ከሌላ አለም የሚመጣልኝ ጀግና የሆንኩት?››ጠየቅኳት ያው በቀልድ ቅላፄ
-አይ እስከአሁን እንኳን ጀግና አይደለህም ….ግን ጀግና የሚሆን ልብ ይዘሀል፡፡በሺ አመት አንዴ የሚገኝ ጀግና ልብ…ስለዚህ አገባሀለው፡፡ግን አንድ አላማ አለኝ ያንን እንዳሳካ ታግዘኛለህ …እርግጥ ለእኔም ብቻ ሳይሆን ለአንተም ይጠቅማል፡፡
-አረ ግድ የለም ፡፡ለአንቺ ብቻ የሚጠቅምም ቢሆን ያልሺኝን ሁሉ አደርገዋለው›አልኳት ከልቤ እንደማደርገው በውስጤ እየማልኩ
የእለቱ ንግግራችንም ሆነ ጠቅላላ ታሪኩ በዚህ አልተቆጨም ሙሉውን ወደፊት አወራችሆለው …አሁን ከዚያች የህይወት አጋጣሚ አክለፍልፋ ወስዳ እሷ እጅ ወይም ልብ ላይ እስክትጥለኝ ድረስ ያሰለፍኩትን የእኔንና የቤተሰቤን ታሪክ ልክ እንደቅምሻ በሚቀጥሉት ክፍል አወራችሁና ስጨርስ ወደመነሻዬ እመልሳችሆለው፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
:
#ክፍል_ሁለት
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
...ኢትዬጵያን በዩቶፐያ ፅንሰ ሀሳብ ዳግም መገንባት ከአያቴ የወረስኩት ህልሜ እና ዓላማዬ እንደሆነ ነግሬያችኃለው …ግን እንዴት አድርጌ ነው የማሳካው …?እንደማሳክው የማምነው ከራሴ በላይ በሚስቴ እምነት ስላለኝ ነው፡፡ሚስቴ …የዋናው የታሪኬ ማጠንጠኛ እሷ ነች፡፡እሷ ደግሞ መንፈስ ነች፡፡ገራሚ መንፈስ፡፡አስፈሪ መንፈስ፤ታሪካዊ መንፈስ፤አፍዛዥ መንፈስ…ሁሉን አድራጊ ፈላጭ ቆራጭ መንፈስ፡፡አዎ ስለእሷ የምነግራችሁ ነገር ቢኖር የደረስኩበትን እና ያወቅኩትን ብቻ ነው፡፡ያንን ስላችሁ በቃ ስለእሷ የማትነግረን ጥቂት ነዋ..?››ብላችሁ ታስቡ ይሆናል፡፡አይደለም:: እንደውም በተቀራኒው የምነግራችሁ ከእሷ ታሪክ አንጻር ጥቂቱን ግን በእኛ በሰውኛ ልኬት ከጆሮአችን የመስማት አቅም በላይ ከአይኖቻችንም የማየት ጉልበት በላይ በሆነ መጠን ነግራችሆለው፡፡
ምክንቱም ይህቺ ፍቅሬ ከሰፈር ጎረምሳነት በአንዴ ስለዓለም መፅአዊ እጣ ሚያስብና ለዛም የሚሰራ የሚተጋ ሰው አድርጋ መልሳ ዳግመኛ የፈጠረቺኝ ሴት ነች፡፡እሷ ደፋርም ገራሚም ፍጡር ነች፡፡ ሁሉ ነገር የማድረግ አቅም እንዳላት አምናለው፡እንዴት አድርጌ የምታደርገው ነገር ሁሉ የምትለውን ሁሉ አምናታለው፡፡የማምናት ጅል ሆኜ አይደልም፡፡በአፍቃሪነቴም ዓየነ-ልቦናይ ታውሮም አይመስለኝም፤የምትሰራቸውን የእጆቾን ተአምራቶች በአይኖቼ ደጋግሜ ሳላየው ላለማመን አልችልም፡፡ ግን ደግሞ ሚስጥሯን ሁሉ ትነግረኛለች ብዬ አላስብም…ከእኔ የተደበቀ የሆነ ዕቅድ ያላት መስሎ ይሰማኛል ፡፡ቢሆንም ደፍሬ ጠይቄያት አላውቅም፡፡
ግን የምታወራው ስለአፈቀርካት ሴት ነው ወይ..? ካላችሁኝ አዎ ስለእሷው ነው፤ግን እንደምታውቋት አይነት ሴት ብቻ አይደለችም… መንፈስም ጭምር ነች፡፡ምን አይነት መንፈስ..?እሱን ወደ ፊት አስረዳችሆለው….
ይህቺን ሴት ያገኘዋት በተለየ አጋጣሚ ነው፡፡በህይወቴ የመጨረሸውን ሀዘን ባዘንኩበት ቀን …የመጨረሻውን እጦት ባጣውበት ቀን…ወደ ልቤ ደም የሚወስዱና የሚመልሱ ትላልቅ የደም ስሮች የተበጠሱ የመሰለኝ ቀን፡፡አዎ የዛን ቀን ነበር ያገኘዋት …፡፡እንዴት እጦቴን በተአምሮ መለሰችልኝ…ሀዘኔን በድንቅ ስራዋ ወደምስራች ቀየረችልኝ…የተበጣጠሱትን የልብን ደም ስሮች ቀጣጥላ ለሞት ከቆረጥኩበት ስሜት አውጥታ መኖርን እንድናፍቅ አደረገቺኝ እና በዛኑ ቅፅበት ይህቺን ሴት ደነዘዝኩላት….፡፡
ወዲያው ነበር እግሯ ስር ተንበርክኬ እንዳፈቀርኳት የነገርኳት..ይቺን ሴት ፍቅሬን እንደተቀበለች ነበር ትንፋሽ ሳልሰጣት እንድታገባኝ የጠየቀኳት፡፡አግቢኝ ስላት ቤት አልነበረኝም .አግቢኝ ስላት ስራ አልነበረኝም…አረ አግቢኝ ስላት የሀይስኩል ትምህርቴን እንኳን አልጨረስኩም…አግቢኝ ስላት የማግባት ዕቅድም አልነበረኝም….አግቢኝ ስላት ዕድሜዬ እንኳን 18 ሊደፍን ገና 3 ወራቶች ይቀሩት ነበር..
ይህ ሁሉ ቢሆንም ዳሩ እንድታገባኝ ስጠይቃት
-እንዳገባህ የጠየቅከኝ ውለታ ስለዋልኩልህ ነው ወይስ ስላፈቀርከኝ›ነበር ያለቺኝ
-ሁለቱም ምክንያት ነው፡፡-መለስኩላት
-ይሁን የመጣውትም አንተን ለማግባት ስለሆነ ተቀብዬሀለው ››አለቺኝ
-አልገባኝ
-ቀስ ብሎ ይገባሀል ..ለማንኛውም ጥያቄህን ተቀብያለው ፡፡አገባሀለው፡፡
መልሶን ስሰማ ደንግጬ ነበር..እሺታዋን ስሰማ ፈዝዤ ነበር፡፡አዎ እሺታዋን አልጠበቅኩም ነበር፡፡
-ግን ቆይ የመጣውት ስትይ ከየት ነው የመጣሽው.?
ከዛኛው አለም ….ላለፈት መቶ አመት እዚህ አልነበርኩም፡፡
-ያው እየቀለደች ነው ብዬ
‹ከዛ በፊትስ?፡›ጠየቅኳት
-ከዛ በፊት አንድ አራት ጊዜ ተመላልሺያለው፡፡ፈርዶብኝ ጀግና ወዳለው፡፡በዚህ አካባቢ ማለቴ በኢትዬጵያ ጀግና መኖሩን ከሰማው በርሬ ለመምጣት ቀናትን አላባክንም›
-ይገርማል…አሁን ታዲያ ማን ተገኝቶ ነው የመጣሺው.?›
-ነገርኩህ አንተን..
-እኔን …እኔ ታዲያ እንዴት ነው ከሌላ አለም የሚመጣልኝ ጀግና የሆንኩት?››ጠየቅኳት ያው በቀልድ ቅላፄ
-አይ እስከአሁን እንኳን ጀግና አይደለህም ….ግን ጀግና የሚሆን ልብ ይዘሀል፡፡በሺ አመት አንዴ የሚገኝ ጀግና ልብ…ስለዚህ አገባሀለው፡፡ግን አንድ አላማ አለኝ ያንን እንዳሳካ ታግዘኛለህ …እርግጥ ለእኔም ብቻ ሳይሆን ለአንተም ይጠቅማል፡፡
-አረ ግድ የለም ፡፡ለአንቺ ብቻ የሚጠቅምም ቢሆን ያልሺኝን ሁሉ አደርገዋለው›አልኳት ከልቤ እንደማደርገው በውስጤ እየማልኩ
የእለቱ ንግግራችንም ሆነ ጠቅላላ ታሪኩ በዚህ አልተቆጨም ሙሉውን ወደፊት አወራችሆለው …አሁን ከዚያች የህይወት አጋጣሚ አክለፍልፋ ወስዳ እሷ እጅ ወይም ልብ ላይ እስክትጥለኝ ድረስ ያሰለፍኩትን የእኔንና የቤተሰቤን ታሪክ ልክ እንደቅምሻ በሚቀጥሉት ክፍል አወራችሁና ስጨርስ ወደመነሻዬ እመልሳችሆለው፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍3
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ
:
#ክፍል_ሶስት
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
....እናቴ ማለት….፨
ለእናቴ ያለኝ እይታ አምልኮ ደረጃ የደረሰ ዓይነት ነወ ፡፡ይሄን ቃል ስናገር በአላዋቂነት ስሜት ልቤን በትዕቢት አጨልሜ አይደለም፤በፍጽም ወይን
ም በእግዜያብሄር የፈጣሪነት ስልጣን ላይ እምነቴ የላላም ስለሆነም አይደለም፡፡አዎ ብቻ እንደዛ ማለት ስላለብኝ ነው፡፡እውነትም ስለሆነ ነው፡፡
የምፈራው እሷን ብቻ ነው፡፡የምሰማውም እንደዛው ፡፡እናቴን በአምስቱም የስሜት ህዋሳቶች ስጠቀም የመጨረሻውን ስሜት የማጣጥምባት ቅዱስ ጨረቃዬ ነች፡፡አፍንጫዬን ተጠቅሜ የመጨረሻው መሳጭ ሽታ ወደውስጤ የምምገው የእናቴን ጠረን ነው፡፡:በምላሴ ቀምሼ የምደነዝዛበት የመጫረሻው ጣፍጭ ጣዕም የእናቴ እጅ የነካው ምግብ ነው፡፡አይኖቼ ሲከፈቱ ሊመለከቷቸው የሚጓጉት የመጨረሻው መሳጭ ውበት የእናቴ ማንነት ነው፡፡በእጆቼ ሲዳሰሱ ስሜት የሚሰጡኝ ልቤን የሚያደነዝዘው የመጨረሻው ለስላሳ ልብ ነዛሪ ገላ የእናቴ ሰውነት ነው፡፡የመጨረሻው የሰማይ መላዕክት የሚደመሙበት አይነት ከያሬድ ዝማሬ የላቀው ጥኡመ ዜማ ከእናቴ አንደበት የሚወጣው ድምጽ ነው፡፡
እርግጥ ይሄ ስለእናቴ ያለኝ ስሜት የእኔ የተዛባ አመለካከት ሊሆነው ይችላል፤ቢሆንም ግድ የለኝም ፡፡እንደውም ይሄንን ስሜት ከውስጤ የሚያጠፋብኝን ጤንነት አልፈልገውም፡፡ለእኔ ዓለም ጠቅላላ ማለት እሷ ነች፡፡እሷ ብቻ ነች፡፡እሷ ብቻ ነች የምታወደኝ፡፡እሷ ብቻ ነች የምትኮራብኝ፡፡እሷ ብቻ ነች ውስጤን አንብባ ነገዬን በድፍረት የምትነግረኝ፡፡እሷ ብቻ ነች ያላትን በጠቅላላ ያለመሰሰት ልትሰጠኝ የማታንገራግር፡፡አሁን እርግጥ ከእናቴ በተጨማሪ ይህች አለም ሌላ እውነት እንዳለት ተረድቼያለው፡፡ሚስቴ …..
እናቴ ወላጄ ነች፡፡ከማይታወቀው አለም ለእናቶች ከእግዚያብሄር በተሰጠ የተፈጥሮዊ ፀጋ በመጠቀም ከሚስጥራዊው ዓለም መዛ አምጥታኝ በቅዱስ ማህፀኖ ዘጠኝ ወር ተንከባክባ ከረቂቅ ህዋስነት ወደ ሰዋዊ ፍጡርነት በመቀየር በሚዳሰሰው ዓለም ላይ እንድኖር ያደረገቺኝ እናቴ፡፡
አንድ ሴት ወደ ማህፀኗ ከገብት 5 ሚሊዬን በላይ የዘር ፍሬዎች መካከል አንዶ እድለኛ በሰበረችው እንቁላል ልጅ ይወለዳል፡፡እንዴት እኔ እንደዛ እድለኛ ሆንኩ..….?እንዴት ከአምሰት ሚሊዬን አንዶ እኔን የያዘች ሴል ተሳካላት…….?እዚህ ላይ የእናቴ አስተዋፅኦ ይኖርበት ይሆን ወይስ የፈጣሪ ፍቃድ….?፡፡የፈጣሪስ ከሆነ ምንድ ነው ምክንያቱ….? ምንድነውስ መስፈርቱ …….?፡፡
ለማንኛውም ይሄን ለጊዜው ልተወው…እናቴ ወደዚህ ምድር አመጣችኝ..ማለት ወለደቺኝ፡፡ይሄ ማኛውም እናት በእውቀትም ሆነ በደመነፍስ የምታደርገው ነገር ነው፡፡የእናቴ ብቃት፤የእናቴ ልዩ መሆን፤የእናቴ ፈጣሪነት ከዛ ቡኃላ የሚገለጽ ነው፡፡መጀመሪያ ወለደቺኝ ከዛ ቀጥላ ፈጠረቺኝ፡፡ቅደም ተከተሉ አዛባውባችሁ አይደል….?፡፡መፈጠር የነገር ሁሉ መጀመሪያ እንደሆነ ስቼው አይደለም፡፡ እናቴ ስትወልደኝ እንደማንኛውም ሰው ሰው ነበርኩ፡፡ግን ዝም ብሎ ስው፡፡እየዳህኩ ሰሄድ ምኔም ምኔም የማይጥም ሰው ነበርኩ፡፡
እራሴን ላስተዋውቃችሁ አይደል፡፡እራስን ማስተዋወቅ እንዴት ነበር.. ….?አዎ ሰዎች እራሳቸውን ማስተዋወቅ የሚጀምሩት ስማቸውን ከመናገር አይደል ….?፡፡ሰው እራስ ወዳድ የመሆኑን አንዱ ማስረጃ ይሄ ነው፡፡ በየምክንያቱ ስሙን መጥራት ስለሚወድ እራሱን ለሌላ እንግዳ ስው የማስተዋወቅ ስርአት ላይ ስምን ቅድሚያ መናገር የሚል ሀረግ አሰፈረ……፡፡
ማህሌት ትባላለች፡፡ማህሌት ገዳ፡፡የእናቴን ሙሉ ስም እየነገርኮችሁ ነው፡፡የእኔ ስም ደግሞ ፀጋ ፡፡ፀጋ ማህሌት ገዳ፡፡ሙሉ ስሜ እስከአያቴ ሲጠራ ነው፡፡የሴት ልጅ ነኝ፤ ለዛ ነው በእናቴ የምጠራው፡፡አባቴን አላውቀውም..እንዳለኝ እንኳን እርግጠኛ አይደለውም፡፡እንዲኖረኝም ፈልጌም ጠብቄም አላውቅም ፡፡የተወለድኩት በ1994 ዓ.ምህረት ነው፡፡ስንት ዓመቴ እንደሆነ ቆጥራችሁ ድረሱበት፡፡እጆቼን ከመሬት አላቅቄ በአየር ላይ በማወናጨፍ ፤በሁለት እግሮቼ ቆሜ ሰው እንደሚያደርገው መራመድ የቻልኩት አራት አመት ካለፈኝ ቡኃላ ነው፡፡ከዛ በፊት ልክ እንደዝንጀሮ ወይም ጦጣ ወይንም ደግሞ እንደተሳቢ እንስሳት ባለአራት እግር ተሳቢ ወይም ተንፎቃቂ ነበርኩ፡፡
እናቴ በዛን ወቅት በተለይ ሁለት ዓመት ካለፈኝ ቡኃላ መራመድ ባለመቻሌ በጣም ተጨንቃ የተለያዩ ቦታ በመውሰድ ዘመናዊውንም ሆነ ባህላዊውን ህክምና እንዳገኝ እና እንደሌሎች እኩዬቼ መራመድና መናገር እንድችል ሞክራ ነበር ፡፡ግን አንዳቸውም ምንም ሊፈይዱልኝ አልቻሉም ነበር፡፡በመጨረሻ እናቴ ተጨንቃ እኔን ማስጨነቁን ለማቆም ከወሰነችና እሰከማንነቴ ልትቀበለኝ ከቆረጠች ቡኃላ ነበር ድንገት ተስፈንጥሬ በመቆም መሄድ የቻልኩት፡፡እንዴት መራመድ ቻልኩ ታሪኩ እንዲህ ነው፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 እያረጋቹ አደለም ያነበበ የተመቸው 👍
እያረጋቹ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
:
#ክፍል_ሶስት
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
....እናቴ ማለት….፨
ለእናቴ ያለኝ እይታ አምልኮ ደረጃ የደረሰ ዓይነት ነወ ፡፡ይሄን ቃል ስናገር በአላዋቂነት ስሜት ልቤን በትዕቢት አጨልሜ አይደለም፤በፍጽም ወይን
ም በእግዜያብሄር የፈጣሪነት ስልጣን ላይ እምነቴ የላላም ስለሆነም አይደለም፡፡አዎ ብቻ እንደዛ ማለት ስላለብኝ ነው፡፡እውነትም ስለሆነ ነው፡፡
የምፈራው እሷን ብቻ ነው፡፡የምሰማውም እንደዛው ፡፡እናቴን በአምስቱም የስሜት ህዋሳቶች ስጠቀም የመጨረሻውን ስሜት የማጣጥምባት ቅዱስ ጨረቃዬ ነች፡፡አፍንጫዬን ተጠቅሜ የመጨረሻው መሳጭ ሽታ ወደውስጤ የምምገው የእናቴን ጠረን ነው፡፡:በምላሴ ቀምሼ የምደነዝዛበት የመጫረሻው ጣፍጭ ጣዕም የእናቴ እጅ የነካው ምግብ ነው፡፡አይኖቼ ሲከፈቱ ሊመለከቷቸው የሚጓጉት የመጨረሻው መሳጭ ውበት የእናቴ ማንነት ነው፡፡በእጆቼ ሲዳሰሱ ስሜት የሚሰጡኝ ልቤን የሚያደነዝዘው የመጨረሻው ለስላሳ ልብ ነዛሪ ገላ የእናቴ ሰውነት ነው፡፡የመጨረሻው የሰማይ መላዕክት የሚደመሙበት አይነት ከያሬድ ዝማሬ የላቀው ጥኡመ ዜማ ከእናቴ አንደበት የሚወጣው ድምጽ ነው፡፡
እርግጥ ይሄ ስለእናቴ ያለኝ ስሜት የእኔ የተዛባ አመለካከት ሊሆነው ይችላል፤ቢሆንም ግድ የለኝም ፡፡እንደውም ይሄንን ስሜት ከውስጤ የሚያጠፋብኝን ጤንነት አልፈልገውም፡፡ለእኔ ዓለም ጠቅላላ ማለት እሷ ነች፡፡እሷ ብቻ ነች፡፡እሷ ብቻ ነች የምታወደኝ፡፡እሷ ብቻ ነች የምትኮራብኝ፡፡እሷ ብቻ ነች ውስጤን አንብባ ነገዬን በድፍረት የምትነግረኝ፡፡እሷ ብቻ ነች ያላትን በጠቅላላ ያለመሰሰት ልትሰጠኝ የማታንገራግር፡፡አሁን እርግጥ ከእናቴ በተጨማሪ ይህች አለም ሌላ እውነት እንዳለት ተረድቼያለው፡፡ሚስቴ …..
እናቴ ወላጄ ነች፡፡ከማይታወቀው አለም ለእናቶች ከእግዚያብሄር በተሰጠ የተፈጥሮዊ ፀጋ በመጠቀም ከሚስጥራዊው ዓለም መዛ አምጥታኝ በቅዱስ ማህፀኖ ዘጠኝ ወር ተንከባክባ ከረቂቅ ህዋስነት ወደ ሰዋዊ ፍጡርነት በመቀየር በሚዳሰሰው ዓለም ላይ እንድኖር ያደረገቺኝ እናቴ፡፡
አንድ ሴት ወደ ማህፀኗ ከገብት 5 ሚሊዬን በላይ የዘር ፍሬዎች መካከል አንዶ እድለኛ በሰበረችው እንቁላል ልጅ ይወለዳል፡፡እንዴት እኔ እንደዛ እድለኛ ሆንኩ..….?እንዴት ከአምሰት ሚሊዬን አንዶ እኔን የያዘች ሴል ተሳካላት…….?እዚህ ላይ የእናቴ አስተዋፅኦ ይኖርበት ይሆን ወይስ የፈጣሪ ፍቃድ….?፡፡የፈጣሪስ ከሆነ ምንድ ነው ምክንያቱ….? ምንድነውስ መስፈርቱ …….?፡፡
ለማንኛውም ይሄን ለጊዜው ልተወው…እናቴ ወደዚህ ምድር አመጣችኝ..ማለት ወለደቺኝ፡፡ይሄ ማኛውም እናት በእውቀትም ሆነ በደመነፍስ የምታደርገው ነገር ነው፡፡የእናቴ ብቃት፤የእናቴ ልዩ መሆን፤የእናቴ ፈጣሪነት ከዛ ቡኃላ የሚገለጽ ነው፡፡መጀመሪያ ወለደቺኝ ከዛ ቀጥላ ፈጠረቺኝ፡፡ቅደም ተከተሉ አዛባውባችሁ አይደል….?፡፡መፈጠር የነገር ሁሉ መጀመሪያ እንደሆነ ስቼው አይደለም፡፡ እናቴ ስትወልደኝ እንደማንኛውም ሰው ሰው ነበርኩ፡፡ግን ዝም ብሎ ስው፡፡እየዳህኩ ሰሄድ ምኔም ምኔም የማይጥም ሰው ነበርኩ፡፡
እራሴን ላስተዋውቃችሁ አይደል፡፡እራስን ማስተዋወቅ እንዴት ነበር.. ….?አዎ ሰዎች እራሳቸውን ማስተዋወቅ የሚጀምሩት ስማቸውን ከመናገር አይደል ….?፡፡ሰው እራስ ወዳድ የመሆኑን አንዱ ማስረጃ ይሄ ነው፡፡ በየምክንያቱ ስሙን መጥራት ስለሚወድ እራሱን ለሌላ እንግዳ ስው የማስተዋወቅ ስርአት ላይ ስምን ቅድሚያ መናገር የሚል ሀረግ አሰፈረ……፡፡
ማህሌት ትባላለች፡፡ማህሌት ገዳ፡፡የእናቴን ሙሉ ስም እየነገርኮችሁ ነው፡፡የእኔ ስም ደግሞ ፀጋ ፡፡ፀጋ ማህሌት ገዳ፡፡ሙሉ ስሜ እስከአያቴ ሲጠራ ነው፡፡የሴት ልጅ ነኝ፤ ለዛ ነው በእናቴ የምጠራው፡፡አባቴን አላውቀውም..እንዳለኝ እንኳን እርግጠኛ አይደለውም፡፡እንዲኖረኝም ፈልጌም ጠብቄም አላውቅም ፡፡የተወለድኩት በ1994 ዓ.ምህረት ነው፡፡ስንት ዓመቴ እንደሆነ ቆጥራችሁ ድረሱበት፡፡እጆቼን ከመሬት አላቅቄ በአየር ላይ በማወናጨፍ ፤በሁለት እግሮቼ ቆሜ ሰው እንደሚያደርገው መራመድ የቻልኩት አራት አመት ካለፈኝ ቡኃላ ነው፡፡ከዛ በፊት ልክ እንደዝንጀሮ ወይም ጦጣ ወይንም ደግሞ እንደተሳቢ እንስሳት ባለአራት እግር ተሳቢ ወይም ተንፎቃቂ ነበርኩ፡፡
እናቴ በዛን ወቅት በተለይ ሁለት ዓመት ካለፈኝ ቡኃላ መራመድ ባለመቻሌ በጣም ተጨንቃ የተለያዩ ቦታ በመውሰድ ዘመናዊውንም ሆነ ባህላዊውን ህክምና እንዳገኝ እና እንደሌሎች እኩዬቼ መራመድና መናገር እንድችል ሞክራ ነበር ፡፡ግን አንዳቸውም ምንም ሊፈይዱልኝ አልቻሉም ነበር፡፡በመጨረሻ እናቴ ተጨንቃ እኔን ማስጨነቁን ለማቆም ከወሰነችና እሰከማንነቴ ልትቀበለኝ ከቆረጠች ቡኃላ ነበር ድንገት ተስፈንጥሬ በመቆም መሄድ የቻልኩት፡፡እንዴት መራመድ ቻልኩ ታሪኩ እንዲህ ነው፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 እያረጋቹ አደለም ያነበበ የተመቸው 👍
እያረጋቹ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍3
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ
:
#ክፍል_አራት
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
አራት አመት ካለፈኝ ቡኃላ አንድ ቀን አናቴ ከጓደኛዋ ጋር የገዛ ቤታችን ውስጥ ታወራለች
‹‹እንደው ስንቱ እያፈቀረሽ እኮ ሁኔታሽን እያየ ነው የሚሸሸሽ››ድንገት ነው ጓደኛዋ አስተያየት የሰነዘረችው
-ሁኔታዬ ምን ሆነ ?
-ያው የልጅሽ ሁኔታ ነዋ
-የልጄ ሁኔታ ምን ሆነ..?በቃ በማንም ሰው ላይ እንደሚያጋጥም የጤና መጓደል አራት አመት ቢሆነውም መናገርና መራመድ አልቻለም..እና ምን ይጠበስ …….?በንዴት እና በሚርገበገብ ድምፅ
-ቀስ በይ ምን ያስቆጣሻል…ለማለት የፈለኩት ሙሉ ህይወትሽን ለእሱ መስዋዕት አድርገሽ ሰጥተሸል ነው፡፡ልጅሽ ቢሆንም አንቺም ሰው ነሽና ለራስሽ ማሰብ መጀመር አለብሽ ልልሽ ፈልጌ ነው….ቀንም ሌትም ከእሱ ጋር ተቆራምደሽ መዋልና ማደሩን አቁሚና ለሰራተኛ ሰጥተሸው እንደድሮሽ ወጣ ወጣ በይ….ወደቢሮ ስራሽም ተመለሺ እያልኩሽ ነው፡፡
-እኔ ወንድ ያስፈልገኛል ብዬ ለማንም ተናግሬ አላውቅም፡፡ወንድ ለማግኘት ከእኔ በስተቀር ሌላ ሰው ሊረዳው የማይችለውን ልጄን ለሰራተኛ ጥዬ ተቆነጃጅቼ ለመውጣት ፍላጎቱ የለኝም፡፡ለምበላውና ለምጠጣው የሚሆን ብር አለኝ፡፡ስለዚህ አትልፊ ከአሁን ቡኃላ ባለው ህይወቴ ዋና አላማዬም ሆነ ቋሚ ስራዬ ልጄ ነው፡፡…እናቴ ፍርጥም ያለ መልስ ትመልስላታለች፡፡
-አይ ተስፋ ለሌለው ነገር እራስሽን መስዋዕት እንድታደርጊ ስለማልፈልግ ነው እንደዚህ የምልሽ..ደግሞ ለአባትሽም ብታስቢላቸው መልካም ነው::
እዚህ ላይ እናቴ ብትበሳጭም የጓደኛው ምክር ግን እንዲሁ ችላ ተብሎ የሚጣል አልነበረም፡፡በተለይ ለአባትሽ ብታስቢላቸው መልካም ነው ያለችው ዝም ብላ ከመሬት ተነሳታ አይደለም፡፡የእናቴ አባት ማለት አያቴ በእናቴ ላይ የነበረው ተስፋ እንዲህ ቀላልና ተራ የሚባ አይነት አልነበረም፡፡እሷ ላይ ብዙ ተስፋ ነበረው፡፡እናቷ በልጅነቷ ስለሞተች ከ10 አመቷ ጀምሮ ብቻውን ነው ያሳደጋት ፡፡ከዛን ጀምሮ ሚስት ላግባ አላለም….ከዛን ጀምሮ ለራሴ ምቾት ላስብ አላለም፡፡ጭንቀቱ እሷብቻ ነበረች፡፡ኢትዬጵዬ ይላታል፡፡አያቴ ሀገሩን ይወደል ፡፡ከሀገሩም እኩል ልጁን ይወዳል፡፡
አያቴ ኮረኔል ነው ፡፡በሀይለስላሴ የመጨረሻዎቹ ዘመን የውትድርናውን አለም ተቀላቅሎ በደርግ ሙሉ ከምስራቅ እስከሰሜን በተለያ አውደውጊያዎችና አገልግሎት ሰጥቶ ኢህአዲግ ሲገባ ጎደኞቹ ሲበተኑ አብሮ የተበተነ ግን ደግሞ እንደእድል ሆኖ ደህና ቤተሰብ ስለነበረው ወደትውልድ ከተማው ሲመለስ በመንደላቅ የሚያኖረው ንብረት ከቤተሰቦቹ በውርስ የጠበቀው ሰው ነው፡፡ እና አያቴ እሱ የጀመረውን ሀገርን ለእድሜ ልክ ማገልገል ልጁም በተለየ መንገድ ቢሆንም እንድትቀጥል ይፈልግ ነበር፡፡‹ጓደኞቼ ለዚህች ሀገር ህይወታቸውን ሰጥተዋል እኔ ደግሞ በአጋጣሚ በህይወት ቆይቼ ልጅ ወልጄ እንድስም ከተፈቀደልኝ ይህቺን ልጅ ለሀገር አገልጋይ እንድትሆን በስርዓት አሳድጌ ፤ በአግባቡ አስተምሬ እንሆ ኢትዬጵያዬ ልጄን እንደልጅሽ ተረከቢኝ ፡የደቀቀ ጎንሽን አሽታ ትጠግንልሽ ዘንድ፤የጎበጠ ወገብሽን ደግፋ ታቃናልሽ ዘንድ..እግርሽን ጣቶች መካከል የተጠቀጠቁትንና ያቆሰሉሽን እሾኮች ቀስ ብላ ህመምሽ እያማት በወረንጦ ለቅማ ታክምሽ ዘንድ ….የአይኖችሽን ዳር አይናሮች አፀዳድታ መታወርሽን በፈዋሽ ጠብታ እንድታድንሽ ዘንድ ….አዎ ህመምሽ ሚያማት፤ ጭንቀትሽ የሚጨንቃት ልጅ አድርጌ አሳድግን አስረክብሻለው፡፡ ብሎ ለዘመናት እየፎከረ አሳደጋት ፡፡ እንዳለው አድርጎ አስተማራት፡፡ዩኒቨርሲቲ ገባች በማእረግ ጨረሰጭ ፡በጥሩ ደሞዝ ጥሩ መስሪያ ቤት ተቀጠረች፡፡አያቴ ተኩራራ ..በራሱም በልጁም ስኬት ታበየ፡፡ድንገት ግን እናቴ ከጋብቻ ውጭ እኔን ፀነሰች፡፡አያቴ ደነገጠ፡፡ተወለድኩና ታየው፡፡ይበልጥ አንገቱን ደፋ፡፡በእኔ ሁኔታ ..ያንን ተከትሎ የእናቴ ስራዋን መልቀቅ ፤እቤት ኩርምት ብሎ መቀመጥ እና መላ ህይወቷን ለእኔ ለበሽተኛ ልጇ መስዋዕት ማድረግ አያቴን ከእርጅናውም ገፍቶ የሞት አፋፍ ላይ አደረሰው …አዎ ይሄ ደግሞ የእናቴን ጓደኛ ቢያሳስባት ያስመሰግናት ይሆናል እንጂ በክፋት አያስቀወቅሳትም…እናቴን ግን ከፋት
ለዚህም ነው -አይ ተስፋ ለሌለው ነገር እራስሽን መስዋዕት እንድታደርጊ ስለማልፈልግ ነው እንደዚህ የምልሽ..ደግሞ ለአባትሽም ብታስቢላቸው መልካም ነው::…ያለቻት
.እንዴት ተስፋ የሌለው ነገር ….?......እናቴ በገረሜታም በንዴትም ጓደኛዋ ላይ ተንዘረዘረች ፡፡
-ለምን ሁሉንም ነገር ዘርግፌ እንድናገር ታስገድጂኛለሽ..….?አሁን አራት አመት አልፎታል.. መናገሩ ይቅር ቢያንስ በእግሮቹ ቆሞ መረመድ ካልቻለ ምን ተስፋ ይኖረዋል፡፡ይሄ ከአዕምሮው ጋር ቀጥታ ግንኙነት ያለው ነው የሚመስለኝ››
-የልጅሽ አዕምሮውም አይሰራም እያልሽኝ ነው….?
-እንግዲህ እንደፈለገሽ ተርጉመሽ ተረጂው…ግን ለሚወዱሽ ሰዎች ስትይ ያልኩሽን ብታደርጊ እመርጣለው፡፡
-በቃ ውጪልኝ..ታያላችሁ ደግሞ ስንት ዓመትም ይፍጅ ስንት ዓመት ልጄ ቆሞ ይሄዳል፡፡ አንደበቱንም ከፍቶ ይናገራል….?አምላኬ በልጄ ላይ ታአምሩን እንደሚገልጽ አምናለው….የዘላለም አምላክ ፈጣሪ …ሁሉን አድራጊና ሁሉን መታሪ ኤልሻዳይ ለጊዜው ዝም ቢለኝም እስከመጨረሻው እንደማይረሳኝ እርግጠኛ ነኝ…የቅድስና እሳት የሚተፉ የማዳን እጆቹን የልጄ ሰውነት ላይ አንድ ቀን ያኖራል፣..አዎ ቀኑ ሲደርስ እንደዛ ያደርጋል››እናቴ በተለመደ መልኩ በፈጣሪዋ ላይ ያላትን እምነት በንዴት እየተንቀጠቀጠች ለጓደኛዋ አነበነበችላት
-አይ…ክርስቲያን ተስፋ አይቆርጥም ሲባል እኮ እንዲህ አይደለም….እንዲሁ የእናት አንጀት ሆኖብሽ ነው..››አላገጠችባት….እኔ ከዛ በላይ ታግሼ እናቴ እቅፍ ውስጥ ተዘፍዝፌ መቀመጥ አልቻልኩም..ወይንም አላውቅም እናቴ የምትተማመንበት ኃያሉ አምላክ እንደጠየቀችው ሚስጥራዊ እሷት የሚተፉትን የድህነት እጆቹን ሰውነቴ ላይ ጭኖብኝም ሊሆን ይችላል፡፡ብቻ የእናቴ ንግግር ተከትሎ በጉንጮቾ እየፈሰሰ ግንባሬ ላይ የሚንጠባጠበው እንባ ወደመሬት ከመውረድ ይልቅ ግንባሬ ላይ እያረፈ ወደ ህብረሰረሰሬ በመስረግ ውስጤን ሲያቃጥለኝ እና በዛው ቅጽበት የሆነ ነዛሪና የሚያንቀጠቅጥ አይነት ኃይል በሰውነቴ ሲራወጥ ታወቀኝ ..ከእናቴ እቅፍ ላይ ተወራጨው እና ተንሸራትቼ በአግሮቼ መሬት ረገጥኩ፡፡
እሷን ይዤ መሬት ረግጪ መቆም ሁሌ የማደርገው ስለሆነ ሁለቱም ትኩረት እልሰጡኝም…ግን ታአምራዊ በሆነ ፍጥነት የእናቴን ድጋፍ ለቅቄ የሩጫ ያህል እየተንደረደርኩ የሴትዬዋን የሚወናጨፍ እጅ ተንጠራርቼ ያዝኩና ወደውጭ እጎትታት ጀመር …..እናቴ እልልታዋን እያሰማች በጉልበቷ ተደፍታ መሬቱን ስትስም ጓደኛዋ ፃረሞት ፊት ለፊቱ እንደተጋረጠበት ሰው እጆን መንጭቃ ከእጆቼ በማስለቀቅ በሩጫ ከቤታችን አምልጣ በመውጣት ከውጭ የአጥር በራፍ ጋር ተላትማ ተዘረረች….
💫ይቀጥላል💫
ከወደዱት ከተመቾ Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሱ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
:
#ክፍል_አራት
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
አራት አመት ካለፈኝ ቡኃላ አንድ ቀን አናቴ ከጓደኛዋ ጋር የገዛ ቤታችን ውስጥ ታወራለች
‹‹እንደው ስንቱ እያፈቀረሽ እኮ ሁኔታሽን እያየ ነው የሚሸሸሽ››ድንገት ነው ጓደኛዋ አስተያየት የሰነዘረችው
-ሁኔታዬ ምን ሆነ ?
-ያው የልጅሽ ሁኔታ ነዋ
-የልጄ ሁኔታ ምን ሆነ..?በቃ በማንም ሰው ላይ እንደሚያጋጥም የጤና መጓደል አራት አመት ቢሆነውም መናገርና መራመድ አልቻለም..እና ምን ይጠበስ …….?በንዴት እና በሚርገበገብ ድምፅ
-ቀስ በይ ምን ያስቆጣሻል…ለማለት የፈለኩት ሙሉ ህይወትሽን ለእሱ መስዋዕት አድርገሽ ሰጥተሸል ነው፡፡ልጅሽ ቢሆንም አንቺም ሰው ነሽና ለራስሽ ማሰብ መጀመር አለብሽ ልልሽ ፈልጌ ነው….ቀንም ሌትም ከእሱ ጋር ተቆራምደሽ መዋልና ማደሩን አቁሚና ለሰራተኛ ሰጥተሸው እንደድሮሽ ወጣ ወጣ በይ….ወደቢሮ ስራሽም ተመለሺ እያልኩሽ ነው፡፡
-እኔ ወንድ ያስፈልገኛል ብዬ ለማንም ተናግሬ አላውቅም፡፡ወንድ ለማግኘት ከእኔ በስተቀር ሌላ ሰው ሊረዳው የማይችለውን ልጄን ለሰራተኛ ጥዬ ተቆነጃጅቼ ለመውጣት ፍላጎቱ የለኝም፡፡ለምበላውና ለምጠጣው የሚሆን ብር አለኝ፡፡ስለዚህ አትልፊ ከአሁን ቡኃላ ባለው ህይወቴ ዋና አላማዬም ሆነ ቋሚ ስራዬ ልጄ ነው፡፡…እናቴ ፍርጥም ያለ መልስ ትመልስላታለች፡፡
-አይ ተስፋ ለሌለው ነገር እራስሽን መስዋዕት እንድታደርጊ ስለማልፈልግ ነው እንደዚህ የምልሽ..ደግሞ ለአባትሽም ብታስቢላቸው መልካም ነው::
እዚህ ላይ እናቴ ብትበሳጭም የጓደኛው ምክር ግን እንዲሁ ችላ ተብሎ የሚጣል አልነበረም፡፡በተለይ ለአባትሽ ብታስቢላቸው መልካም ነው ያለችው ዝም ብላ ከመሬት ተነሳታ አይደለም፡፡የእናቴ አባት ማለት አያቴ በእናቴ ላይ የነበረው ተስፋ እንዲህ ቀላልና ተራ የሚባ አይነት አልነበረም፡፡እሷ ላይ ብዙ ተስፋ ነበረው፡፡እናቷ በልጅነቷ ስለሞተች ከ10 አመቷ ጀምሮ ብቻውን ነው ያሳደጋት ፡፡ከዛን ጀምሮ ሚስት ላግባ አላለም….ከዛን ጀምሮ ለራሴ ምቾት ላስብ አላለም፡፡ጭንቀቱ እሷብቻ ነበረች፡፡ኢትዬጵዬ ይላታል፡፡አያቴ ሀገሩን ይወደል ፡፡ከሀገሩም እኩል ልጁን ይወዳል፡፡
አያቴ ኮረኔል ነው ፡፡በሀይለስላሴ የመጨረሻዎቹ ዘመን የውትድርናውን አለም ተቀላቅሎ በደርግ ሙሉ ከምስራቅ እስከሰሜን በተለያ አውደውጊያዎችና አገልግሎት ሰጥቶ ኢህአዲግ ሲገባ ጎደኞቹ ሲበተኑ አብሮ የተበተነ ግን ደግሞ እንደእድል ሆኖ ደህና ቤተሰብ ስለነበረው ወደትውልድ ከተማው ሲመለስ በመንደላቅ የሚያኖረው ንብረት ከቤተሰቦቹ በውርስ የጠበቀው ሰው ነው፡፡ እና አያቴ እሱ የጀመረውን ሀገርን ለእድሜ ልክ ማገልገል ልጁም በተለየ መንገድ ቢሆንም እንድትቀጥል ይፈልግ ነበር፡፡‹ጓደኞቼ ለዚህች ሀገር ህይወታቸውን ሰጥተዋል እኔ ደግሞ በአጋጣሚ በህይወት ቆይቼ ልጅ ወልጄ እንድስም ከተፈቀደልኝ ይህቺን ልጅ ለሀገር አገልጋይ እንድትሆን በስርዓት አሳድጌ ፤ በአግባቡ አስተምሬ እንሆ ኢትዬጵያዬ ልጄን እንደልጅሽ ተረከቢኝ ፡የደቀቀ ጎንሽን አሽታ ትጠግንልሽ ዘንድ፤የጎበጠ ወገብሽን ደግፋ ታቃናልሽ ዘንድ..እግርሽን ጣቶች መካከል የተጠቀጠቁትንና ያቆሰሉሽን እሾኮች ቀስ ብላ ህመምሽ እያማት በወረንጦ ለቅማ ታክምሽ ዘንድ ….የአይኖችሽን ዳር አይናሮች አፀዳድታ መታወርሽን በፈዋሽ ጠብታ እንድታድንሽ ዘንድ ….አዎ ህመምሽ ሚያማት፤ ጭንቀትሽ የሚጨንቃት ልጅ አድርጌ አሳድግን አስረክብሻለው፡፡ ብሎ ለዘመናት እየፎከረ አሳደጋት ፡፡ እንዳለው አድርጎ አስተማራት፡፡ዩኒቨርሲቲ ገባች በማእረግ ጨረሰጭ ፡በጥሩ ደሞዝ ጥሩ መስሪያ ቤት ተቀጠረች፡፡አያቴ ተኩራራ ..በራሱም በልጁም ስኬት ታበየ፡፡ድንገት ግን እናቴ ከጋብቻ ውጭ እኔን ፀነሰች፡፡አያቴ ደነገጠ፡፡ተወለድኩና ታየው፡፡ይበልጥ አንገቱን ደፋ፡፡በእኔ ሁኔታ ..ያንን ተከትሎ የእናቴ ስራዋን መልቀቅ ፤እቤት ኩርምት ብሎ መቀመጥ እና መላ ህይወቷን ለእኔ ለበሽተኛ ልጇ መስዋዕት ማድረግ አያቴን ከእርጅናውም ገፍቶ የሞት አፋፍ ላይ አደረሰው …አዎ ይሄ ደግሞ የእናቴን ጓደኛ ቢያሳስባት ያስመሰግናት ይሆናል እንጂ በክፋት አያስቀወቅሳትም…እናቴን ግን ከፋት
ለዚህም ነው -አይ ተስፋ ለሌለው ነገር እራስሽን መስዋዕት እንድታደርጊ ስለማልፈልግ ነው እንደዚህ የምልሽ..ደግሞ ለአባትሽም ብታስቢላቸው መልካም ነው::…ያለቻት
.እንዴት ተስፋ የሌለው ነገር ….?......እናቴ በገረሜታም በንዴትም ጓደኛዋ ላይ ተንዘረዘረች ፡፡
-ለምን ሁሉንም ነገር ዘርግፌ እንድናገር ታስገድጂኛለሽ..….?አሁን አራት አመት አልፎታል.. መናገሩ ይቅር ቢያንስ በእግሮቹ ቆሞ መረመድ ካልቻለ ምን ተስፋ ይኖረዋል፡፡ይሄ ከአዕምሮው ጋር ቀጥታ ግንኙነት ያለው ነው የሚመስለኝ››
-የልጅሽ አዕምሮውም አይሰራም እያልሽኝ ነው….?
-እንግዲህ እንደፈለገሽ ተርጉመሽ ተረጂው…ግን ለሚወዱሽ ሰዎች ስትይ ያልኩሽን ብታደርጊ እመርጣለው፡፡
-በቃ ውጪልኝ..ታያላችሁ ደግሞ ስንት ዓመትም ይፍጅ ስንት ዓመት ልጄ ቆሞ ይሄዳል፡፡ አንደበቱንም ከፍቶ ይናገራል….?አምላኬ በልጄ ላይ ታአምሩን እንደሚገልጽ አምናለው….የዘላለም አምላክ ፈጣሪ …ሁሉን አድራጊና ሁሉን መታሪ ኤልሻዳይ ለጊዜው ዝም ቢለኝም እስከመጨረሻው እንደማይረሳኝ እርግጠኛ ነኝ…የቅድስና እሳት የሚተፉ የማዳን እጆቹን የልጄ ሰውነት ላይ አንድ ቀን ያኖራል፣..አዎ ቀኑ ሲደርስ እንደዛ ያደርጋል››እናቴ በተለመደ መልኩ በፈጣሪዋ ላይ ያላትን እምነት በንዴት እየተንቀጠቀጠች ለጓደኛዋ አነበነበችላት
-አይ…ክርስቲያን ተስፋ አይቆርጥም ሲባል እኮ እንዲህ አይደለም….እንዲሁ የእናት አንጀት ሆኖብሽ ነው..››አላገጠችባት….እኔ ከዛ በላይ ታግሼ እናቴ እቅፍ ውስጥ ተዘፍዝፌ መቀመጥ አልቻልኩም..ወይንም አላውቅም እናቴ የምትተማመንበት ኃያሉ አምላክ እንደጠየቀችው ሚስጥራዊ እሷት የሚተፉትን የድህነት እጆቹን ሰውነቴ ላይ ጭኖብኝም ሊሆን ይችላል፡፡ብቻ የእናቴ ንግግር ተከትሎ በጉንጮቾ እየፈሰሰ ግንባሬ ላይ የሚንጠባጠበው እንባ ወደመሬት ከመውረድ ይልቅ ግንባሬ ላይ እያረፈ ወደ ህብረሰረሰሬ በመስረግ ውስጤን ሲያቃጥለኝ እና በዛው ቅጽበት የሆነ ነዛሪና የሚያንቀጠቅጥ አይነት ኃይል በሰውነቴ ሲራወጥ ታወቀኝ ..ከእናቴ እቅፍ ላይ ተወራጨው እና ተንሸራትቼ በአግሮቼ መሬት ረገጥኩ፡፡
እሷን ይዤ መሬት ረግጪ መቆም ሁሌ የማደርገው ስለሆነ ሁለቱም ትኩረት እልሰጡኝም…ግን ታአምራዊ በሆነ ፍጥነት የእናቴን ድጋፍ ለቅቄ የሩጫ ያህል እየተንደረደርኩ የሴትዬዋን የሚወናጨፍ እጅ ተንጠራርቼ ያዝኩና ወደውጭ እጎትታት ጀመር …..እናቴ እልልታዋን እያሰማች በጉልበቷ ተደፍታ መሬቱን ስትስም ጓደኛዋ ፃረሞት ፊት ለፊቱ እንደተጋረጠበት ሰው እጆን መንጭቃ ከእጆቼ በማስለቀቅ በሩጫ ከቤታችን አምልጣ በመውጣት ከውጭ የአጥር በራፍ ጋር ተላትማ ተዘረረች….
💫ይቀጥላል💫
ከወደዱት ከተመቾ Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሱ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍3
#የመልስ_ጉዞ_ወደ_መነሻ
:
#ክፍል_አምስት
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
:
...አሁን እያወራዋችሁ ያለውት ተጨባጭ ስለሆነው እውነታ ነው፡፡ተጨባጭ እውነታ ማለት ምን ማለት ነው ካላችሁኝ በአምስቱ የስሜት ህዋሳቶች ተጠቅመን አዕምሮችን እንዲያስበው ወይም ልባችን እንዲሰማው ማድረግ የምንችለው ነገር ነው፡፡እርግጥ የሰው ልጅ አምስት የስሜት ህዋሳት ብቻ አይደለም ያሉት፡፡ብዙዎቻን የማንረዳውና ስድስተኛው የሆነውን የስሜት ህዋሳት ከተጨባጭ ዓለም ባሻገር ያለውን እወነታ የምን
…..አሁን ስለሌላው ችግሬ ልንገራችሁ..መናገር የቻልኩት ደግሞ በአስር አመቴ ነው፡፡ተገረማችሁ፡፡እውነቴን ነው ልክ እስከአራት አመት ስንፎቀቅ ኖሬ ድንገት ታምራዊ በሆነ መንገድ ብደግ ብዬ መሮጥ ጀመርኩ ፤በአስር አመቴም ድንገት በአንዴ ነው በሁለት ቋንቋ መናገር የቻልኩት፡፡አዎ ገብቶኛል አላመናችሁኝም አይደል፡፡እውነቱ ያነው፡፡
…የእግሬ ጉዳይ ተአምራዊ በሆነ አጋጣሚ እና ሁኔታ እልባት ካገኘ ብኃላ አንደበቴ ግን ባለበት ነበር የቀጠለው…፡፡ .አንዳንድ ትርጉም አልባ የሆኑ ድምፆችን ለምሳሌ ታታታ..ዳዳዳ የመሳሰሉትት ከአንደበቴ ለዛውም በጣም በምበሳጭበት ወቅት ይሰማ ይሆናል እንጂ የሚሰማኝ ስሜት የሚሰጥ ነገር ከእኔ አንደበት ማድመጥ ማይታሰብ ሆኖ ቀጠለ…..
በዚህ ሁኔታዬ የሰፈር ሰዎችም ሆኑ ዘመድ አዝማዶች የሆን በስህተት እንደተፈጠረ ሰው መሳይ ሸክም እንደሆነ ሰው ነበረ የሚያዩኝ፡፡ብዙዎቹ አዕምሮዬም ማሰብ የሚችል ሁሉ አይመስላቸወም ነበር፡፡‹‹ምን አለ ወዲያ ወስዶ በገላገላት ››ብሎ ለፈጣሪው መልሶ እንዲወስደኝ ስለት የሚሳሉ የእናቴ ወዳጆች ቀላል ቁጥር የላቸውም፡፡
ግን እነሱ ያልገባቸው የአዕምሮዬን የማሰብ ብቃት ስል መሆኑን ነው፡፡ከእግሮቼ እና ከአንደበቴ በልተጣጣመ መልኩ እንደውም ፍጽም ተቃራኒ በሆነ መንገድ አዕምሮዬ ክፉና ደጉን መለየት እና የሰላ እሳቤ ማሰብ የጀመረው ገና በጮርቃነቴ ነው ፡፡ይሄንን ግን ከእናቴ በስተቀር ማንም አይረዳልኝም ነበር፡፡እርግጥ አሁንም ድረስ ብዙዎቹ አያውቁም… ቢያውቁም ማመን አይፈልጉምን ፡፡
ከህፃንነቴ ጀምሮ እኔ የምጫወተው ዕቃ ዕቃ በመደርደር፤ወይም ከልጆች ጋር ሌባና ፖሊስ በመሯሯጥ ፤ወይንም ደግሞ ቡድን ለይቷ በሰፊ የሳር ሜዳ ላይ ከውሪ ህፃናት ጋር ተበትኖ በመሯሯጥ ኳስ በመጠለዝ አይደለም… ረጅም የተባለውን የልጅነት ጊዜዬን የቲቪ ስክሪን ላይ አፍጥጬ የተለያዩ አለማቀፍ የቲቪ ቻናሎችን በመከታተል ነው.....፡አረብኛ ቻናሎችን እንግሊዘኛ ቻናሎችን አማራኛ ቻናሎችን ወዘተ…
ከዛ የተረፈኝን ቀሪ ሙሉ ጊዜ ደግሞ በተመስጦ በማሰብ ነው የማሳልፈው፡፡ስለሆነ ነገር በጥልቀት እና በፍዘት ለሳዕታት በመተከዝ ማሰብ....ለዛውም ከተቀመጥኩበት ሳልንፎቀቅ እና አይኖቼን ከተከልኩበት ሳላንቀሳቅስ ..፡፡
የአማልክት ዝርያ ከሌለበት በስተቀር እስቲ አንድ የአምስት እና የስድስት አመት ልጅ በዚህ መልክ ሊያስባቸው የሚችላቸው ነገሮች ከየት ያመጣል…?፡፡ስለሆነ ነገር ለማሰብ እኮ ስለነገሩ ወይ በትምህርት ያገኙት ዕውቀት ካልሆነም በኑሮ ልምድ ያካበቱት የልምድ ክምችት ሊኖር የግድ ነው፡፡ከዛ ያንን መነሻ በማድረግ ስለነገሩ ይበልጥ ለመረዳት ወይንም ካወቅነው ጀርባ ያለን ድብቅ ወይም ሽሽግ ያልታወቀ እውቀትን ለመግለጽ ማሰብ ያለ ነው፡፡በዛ ላይ ለማሰብ እራሱ በመጠኑም ቢሆን የበሰለ አዕምሮ፤የዳበረ ስሜት ፤የበለፀገ እይታ ከሁሉም በላይ የፈካ ንቃተ-ህሊና አስፈላጊ ነው፡፡ሁሉም የሰው ልጅ ከማሰብ ችሎታ ጋር እንደሚፈጠር ባምንም ማሰብ እንደሚችሉ አውቀው በጊዜው ማሰብ የሚጀምሩ ሰዎች ግን ጥቂቶች እንደሆኑ አምናለው፡፡ ብዙዎቹ የማሰብን ፀጋ በተግባር ማጣጣም የሚጀምሩት በእርጅና ዕድሜ ውስጥ ከገቡ ቡኃላ ነው፡፡ወደኃላ በትዝታ እየተሳቡ እና በፀፀት እየተንገላቱ ፡፡ከዛም በባሰ ሁኔታ ከሚስጥራዊው አለም ይዞት የመጣውን ንጽህ አዕምሮ ሳይነካካው ይዞት የሚሞትም የሰው ልጅ ቁጥር ቀላል አይደለም፡፡በደመነፍስ ብቻ በመኖር፡፡
እኔ ታዲያ በተጋነነ ሁኔታ በጮርቃነት ዕድሜዬ እንዲያ ዓይነት ብስለት ከየት አመጣውት…? ይሄንን እናቴ ነች ምታውቀው፡፡ሌላውማ በዛ ሁኔተ ሲታዘበኝ እያሰብኩ እንደሆነ ሳይሆን የሚረዱት በአዕምሮ ዝግመት በሽታ ተጠቅቼ እየነሆለልኩ እንደሆነ ነው፡፡ለነገሩ ማን ነበር ‹በጂኒዬስነትና በእብደት መካከል ያለችው መስመር በጣም ቀጭን ነች ያለው ››….በዚህ እሳቤ እንደእብድ እኔን ማሰባቸው ብዙም አልተሳሳቱም፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
:
#ክፍል_አምስት
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
:
...አሁን እያወራዋችሁ ያለውት ተጨባጭ ስለሆነው እውነታ ነው፡፡ተጨባጭ እውነታ ማለት ምን ማለት ነው ካላችሁኝ በአምስቱ የስሜት ህዋሳቶች ተጠቅመን አዕምሮችን እንዲያስበው ወይም ልባችን እንዲሰማው ማድረግ የምንችለው ነገር ነው፡፡እርግጥ የሰው ልጅ አምስት የስሜት ህዋሳት ብቻ አይደለም ያሉት፡፡ብዙዎቻን የማንረዳውና ስድስተኛው የሆነውን የስሜት ህዋሳት ከተጨባጭ ዓለም ባሻገር ያለውን እወነታ የምን
…..አሁን ስለሌላው ችግሬ ልንገራችሁ..መናገር የቻልኩት ደግሞ በአስር አመቴ ነው፡፡ተገረማችሁ፡፡እውነቴን ነው ልክ እስከአራት አመት ስንፎቀቅ ኖሬ ድንገት ታምራዊ በሆነ መንገድ ብደግ ብዬ መሮጥ ጀመርኩ ፤በአስር አመቴም ድንገት በአንዴ ነው በሁለት ቋንቋ መናገር የቻልኩት፡፡አዎ ገብቶኛል አላመናችሁኝም አይደል፡፡እውነቱ ያነው፡፡
…የእግሬ ጉዳይ ተአምራዊ በሆነ አጋጣሚ እና ሁኔታ እልባት ካገኘ ብኃላ አንደበቴ ግን ባለበት ነበር የቀጠለው…፡፡ .አንዳንድ ትርጉም አልባ የሆኑ ድምፆችን ለምሳሌ ታታታ..ዳዳዳ የመሳሰሉትት ከአንደበቴ ለዛውም በጣም በምበሳጭበት ወቅት ይሰማ ይሆናል እንጂ የሚሰማኝ ስሜት የሚሰጥ ነገር ከእኔ አንደበት ማድመጥ ማይታሰብ ሆኖ ቀጠለ…..
በዚህ ሁኔታዬ የሰፈር ሰዎችም ሆኑ ዘመድ አዝማዶች የሆን በስህተት እንደተፈጠረ ሰው መሳይ ሸክም እንደሆነ ሰው ነበረ የሚያዩኝ፡፡ብዙዎቹ አዕምሮዬም ማሰብ የሚችል ሁሉ አይመስላቸወም ነበር፡፡‹‹ምን አለ ወዲያ ወስዶ በገላገላት ››ብሎ ለፈጣሪው መልሶ እንዲወስደኝ ስለት የሚሳሉ የእናቴ ወዳጆች ቀላል ቁጥር የላቸውም፡፡
ግን እነሱ ያልገባቸው የአዕምሮዬን የማሰብ ብቃት ስል መሆኑን ነው፡፡ከእግሮቼ እና ከአንደበቴ በልተጣጣመ መልኩ እንደውም ፍጽም ተቃራኒ በሆነ መንገድ አዕምሮዬ ክፉና ደጉን መለየት እና የሰላ እሳቤ ማሰብ የጀመረው ገና በጮርቃነቴ ነው ፡፡ይሄንን ግን ከእናቴ በስተቀር ማንም አይረዳልኝም ነበር፡፡እርግጥ አሁንም ድረስ ብዙዎቹ አያውቁም… ቢያውቁም ማመን አይፈልጉምን ፡፡
ከህፃንነቴ ጀምሮ እኔ የምጫወተው ዕቃ ዕቃ በመደርደር፤ወይም ከልጆች ጋር ሌባና ፖሊስ በመሯሯጥ ፤ወይንም ደግሞ ቡድን ለይቷ በሰፊ የሳር ሜዳ ላይ ከውሪ ህፃናት ጋር ተበትኖ በመሯሯጥ ኳስ በመጠለዝ አይደለም… ረጅም የተባለውን የልጅነት ጊዜዬን የቲቪ ስክሪን ላይ አፍጥጬ የተለያዩ አለማቀፍ የቲቪ ቻናሎችን በመከታተል ነው.....፡አረብኛ ቻናሎችን እንግሊዘኛ ቻናሎችን አማራኛ ቻናሎችን ወዘተ…
ከዛ የተረፈኝን ቀሪ ሙሉ ጊዜ ደግሞ በተመስጦ በማሰብ ነው የማሳልፈው፡፡ስለሆነ ነገር በጥልቀት እና በፍዘት ለሳዕታት በመተከዝ ማሰብ....ለዛውም ከተቀመጥኩበት ሳልንፎቀቅ እና አይኖቼን ከተከልኩበት ሳላንቀሳቅስ ..፡፡
የአማልክት ዝርያ ከሌለበት በስተቀር እስቲ አንድ የአምስት እና የስድስት አመት ልጅ በዚህ መልክ ሊያስባቸው የሚችላቸው ነገሮች ከየት ያመጣል…?፡፡ስለሆነ ነገር ለማሰብ እኮ ስለነገሩ ወይ በትምህርት ያገኙት ዕውቀት ካልሆነም በኑሮ ልምድ ያካበቱት የልምድ ክምችት ሊኖር የግድ ነው፡፡ከዛ ያንን መነሻ በማድረግ ስለነገሩ ይበልጥ ለመረዳት ወይንም ካወቅነው ጀርባ ያለን ድብቅ ወይም ሽሽግ ያልታወቀ እውቀትን ለመግለጽ ማሰብ ያለ ነው፡፡በዛ ላይ ለማሰብ እራሱ በመጠኑም ቢሆን የበሰለ አዕምሮ፤የዳበረ ስሜት ፤የበለፀገ እይታ ከሁሉም በላይ የፈካ ንቃተ-ህሊና አስፈላጊ ነው፡፡ሁሉም የሰው ልጅ ከማሰብ ችሎታ ጋር እንደሚፈጠር ባምንም ማሰብ እንደሚችሉ አውቀው በጊዜው ማሰብ የሚጀምሩ ሰዎች ግን ጥቂቶች እንደሆኑ አምናለው፡፡ ብዙዎቹ የማሰብን ፀጋ በተግባር ማጣጣም የሚጀምሩት በእርጅና ዕድሜ ውስጥ ከገቡ ቡኃላ ነው፡፡ወደኃላ በትዝታ እየተሳቡ እና በፀፀት እየተንገላቱ ፡፡ከዛም በባሰ ሁኔታ ከሚስጥራዊው አለም ይዞት የመጣውን ንጽህ አዕምሮ ሳይነካካው ይዞት የሚሞትም የሰው ልጅ ቁጥር ቀላል አይደለም፡፡በደመነፍስ ብቻ በመኖር፡፡
እኔ ታዲያ በተጋነነ ሁኔታ በጮርቃነት ዕድሜዬ እንዲያ ዓይነት ብስለት ከየት አመጣውት…? ይሄንን እናቴ ነች ምታውቀው፡፡ሌላውማ በዛ ሁኔተ ሲታዘበኝ እያሰብኩ እንደሆነ ሳይሆን የሚረዱት በአዕምሮ ዝግመት በሽታ ተጠቅቼ እየነሆለልኩ እንደሆነ ነው፡፡ለነገሩ ማን ነበር ‹በጂኒዬስነትና በእብደት መካከል ያለችው መስመር በጣም ቀጭን ነች ያለው ››….በዚህ እሳቤ እንደእብድ እኔን ማሰባቸው ብዙም አልተሳሳቱም፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍3👏1
#የመልስ_ጉዞ_ወደ_መነሻ
:
#ክፍል_ስድስት
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
..… እንደነርኮችሁ የመራመዴ ጉዳይ ተአምራዊ በሆነ መንገድ እልባት ካገኘ ቡኃላ እናቴ ለአንደበቴ መከፈት መጓጓት ጀመረች፡፡ያው እናት አይደለች ፡፡በተለይ ስድስት አመት ከሞላኝ ቡኃላ እኩዬቼ ሁሉ ወደትምህርት ቤት ሲጓዙ እኔ አንደበቴ መላቀቅ ባለመቻሉ ምክንያት እቤት በመቅረቴ ውስጧ ተጎዳና እንደአዲስ እኔን ለማዳን የምታደርገውን እንቅስቃሴ ጀመረች ፡፡በዚህ እንቅስቃሴዎ ወቅት ስታልፍም ሆነ ስታገድም የሚያገኞት ሰዎች ሁሉ የሆነ ነገር ሳይሏት ዝም ብለው አያልፎትም፡፡
መቼስ ሀበሻ ባህል ውስጥ አንዱ አስቸጋሪው ነገር የሆነ ሰው ችግር ላይ በወደቀ ቁጥር ምክር ሰጪ ሰው መብዛቱ የታወቀ ነው፡፡ለምን ጠበል አትወስጂውም……?አዋቂ ቤት ይሻልሻል……?እዚህ ከተማ ላይ አዲስ ሀኪም መጥቷል አሉ….…? ውጌሻ ጋር አይሻልሽም….የማይባል ነገር የለም፡፡ታዲያ ይሄ ችግር ውስጥ ላለችና ግራ ለገባት እናቴ በወቅቱ ምን ያህል ግራ አጋቢና አስጨናቂ እንደሚሆንባት መገመት አይከብድም፡፡
እናቴ አንደወትሮዋ እኔን ለማዳን ስትንከራተት ውላ ስትመለስ አባቷ ይናገራታል፡፡
-ልጄ በቃ ለአምላክ ተይው…እሱ እንዳደረገ ያድርገው
-እንዴት እንዳደረገ ያድርገው ስትል…?...ትጠይቃለች
-በቃ አንዳንዴ ከአምላክ ጋር እልክ መጋባት አያስፈልግም…አሱን አድናለው ብለሽ ከእዚህ እዛ ስትካለቢ አንቺም ከሰውነት ጓዳና ወጣሽ…እራስሺን እስኪ እይ… የአርባ አመት አሮጊት መስለሻል እኮ…ገና በሀያ ሶስት አመትሽ ፊትሽን ማድያት እየበላው ነው፡፡በዚህ ከቀጠልሽ የከፋ በሽታ ላይ መውደቅሽ አይቀርም፡፡
-እና ምን አድርጊ ነው የምትለኝ፡፡…?
በቃ እሱን አድናለው ብለሽ ከወዲህ ወዲያ መንከራተቱን አቁሚ.. እግዜያብሄር እግሩን ተርትሮልሻል …በቃ በዛ ተመስገን ብለሽ ሌላውን ተይው…ይሄው ለዓመታት ተንከረተሽ፡፡ ..ህክምናውንም ጠበሉንም ሞክረሻል፡፡ይሄ ነው ችግሩ ብሎ ሊነግርሽ የቻለ የህክምና ጠቢብ የለም፡፡ይሄ ማለት ደግሞ የልጅሽ ችግር ሚስጥር በአምላክ እጅ ብቻ እንደሆነ ነው የሚገባኝ፡፡ በእሱ እጅ ከሆነ ደግሞ ታአምሩን የሚያደርግበት የራሱ ቀንና ጊዜ አለው፡፡እሱን በትዕግስት መጠበቅ ነው፡፡ስለሆነም መንከራተቱን አቁሚ፡፡እዚሁ እንከባከበዋለን፡፡ምንም ነገር እንዳይጎልበት ማድረግ እንችላለን፡፡የሚጠብቁት ተጨማሪ ሰራተኞችም ልንቀጥርለት እንችላለን፡፡አንቺ ግን ከዚህ በላይ እራስሽን አትጣይ፡፡ ……
-አባዬ እናቱ እኮ ነኝ፡፡እንዴት ይሄ የእግዜር ስራና ፍቃድ ነው ብዬ እጆቼን አጣጥፌ ተስፋ ቆርጬ ልቀመጥ እችላለው…?፡፡አንተ እኔ እንደዛ ብሆንብህ የሆነችውን ትሁን ብለህ ተስፋ ቆርጠህብኝ ትተወኝ ነበር…?፡፡…….የትዝብት ጥያቄ ጠየቀቺው፡፡
-አይ…ስለልጅ ልጄ እኮ ነው እያወራን ያለነው… ለአንቺ ብቻ ሳይሆን ለእኔም ልጄ ነው፡፡ጨካኘ ሆኜ አይደለም፡፡ግን እሱን ለማደን በሚል ያልተረጋገጠ ተስፋ አንቺን እንዳላጣ ስለፈራው ነው፡፡ሰለጨነቀኝ ነው፡፡
-በቃ አባዬ በቃ …. መቼም በልጄ ተስፋ አልቆርጥም፡፡መቼም እግዜር እንዳደረገ ያድርገው ብዬ ልቤን አረጋግቼ እድሜ ልኩን ከሰው ተገልሎ በተዘጋ ቤት ውስጥ እንዲኖር በመፍረድ እኔ ለመሽቀርቀርና እራሴን ለማሽሞንሞን አልሞክርም…..መቼም፡፡……ብላ ከአባቷ በንዴት እና በለቅሶ ተለይታ እኔን ወደመኝታ ቤት ይዛ ገብታ ግንባሬ ላይ ተደፍታ በእንባ እየታጠበች ከፈጣሪዋ ጋር ለሳዕታት በምሬት ካወራች..(እናንተ ከፀለየች )ብላችሁ ማንበብ ትችላላችሁ አቅፋኝ ትተኛለች፡፡
ማለዳ ሊነጋጋ ሲል ጥርት ያለ ህልም ታያለች፡፡ተመሳሳይ አይነት ህልም እኔም አይቻለው፡፡ልዩነቱ እሷ ያየችውን ህልም ለአባቷ መናገር ስትችል..እኔ ደግሞ ምናገርበት አንደበት ስላልነበረኝ ለእሷ እንኳን መናገር አልቻኩም፡፡
-ህልሙ እንዲህ ነው
ጠይም የተለጠለጠ ኑግ የሚመስል የሰውነት ቀለም ያላቸወ ፊታቸው በአደገ እና በተንዠረገገ ነጭ ፀጉር የተሸፈነ ሽማግሌ መኝታ ክፍላችን ሰተት ብለው ይገባሉ፡፡እናቴ አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀምጣ እኔን ጉልበቷ ላይ ታቅፋ በተመስጦ ላይ ሳለች ሰውዬው ወደእኛ ቀርበው ወለሉ ላይ በርከክ ይሉና ጭንቅላቴን እየዳበሱ
‹‹ ..ልጅሽ ታላቅ ሰው ይሆናል፡፡አንድ ቀን ዓለም ስለእሱ በመደመም ያወራል፡፡ምድራዊውን አለም ከመንፈሳዊው አለም ጋር ድልድይ ሆኖ ያስተሳስራል…ስለዚህ አንቺ መጨነቅሽን አቁሚ .. እሱ በፈለገ ቀን እራሱን ማዳን ይችላል፡፡ ከራሱም ተርፎ ሌላውን ያድናል፡፡ግን ሲፈልግ…ቀኑ ሲደርስ ብቻ ነው እንደዛ የሚያደርገው፡፡
-አባት ስለእኔ ልጅ ነው የሚያወሩት..?በጥርጣሬ እና ያሉትን ባለማመን ትጠይቃለች፡፡
-አዎ ልጄ ..እኔ የአማላክ መልዕክተኛ ነኝ፡፡ አምላክ እንደገለፀልኝ ከሆነ የልጅሽ እውቀት ጥልቅና ከዛኛው አለም ይዞት የመጣው ነው፡፡
-ከዛኛው አለም ሲሉ…?፡፡
ዳግመኛ ስለመወለድ የምታውቂው ነገር አለ ልጄ.?.
-እኔ እንጃ ብቻ ከዚህ በፊት የሰማው መሰለኝ፡፡አዎ ክርስቲያን አይደለው..ሰው ከውሀና ከመንፈስ ዳግመኘ ካልተወለደ በስተቀር ወደመንግስቱ መግባት እንደማይችል አምላክ ተናግሯል፡፡
-ትክክል እኔ ግን እያልኩ ያለውት ልጅሽች ወደ እዚህች ምድር ሲመጣ ለሁለተኛ ጊዜ ነው፡፡ ከሁለት ሺ አመታት በፊት ነፍሱ እዚህች ምድር ላይ ነበረች…የበለፀገ ህይወት እና በእውቀት የተሞላ ስብዕና ነበረው..እና ያንን እውቀት ነፍሱ ይዛው የመጣች ይመስለኛል፡፡
-እና እኔ ምን ላድርግ …?
-ምንም ፤እራሱ ፈልጎ የሆነ ነገር ማድረግ እስኪችል ድረስ አትጫኚው..አንቺም አትባክኚ፡፡ ብቻ በእሱ ላይ ሁሌም እምነት ይኑርሽ..ወስጡ የተቀበረውን እውነትና እውቀት ብቻ እንዲገለፅለት ሁሌ ከጎኑ ሁኚ…ከጎኑ መሆንሽ ብቻ ለእሱ በቂው ነው..ሌላውን በጊዜው እራሱ ያደርገዋል፡፡
-ሽበታሙ መልዕክት አድራሽ ሽማግሊ ከክፍላችን ሳይወጣ ነበር የሰራተኛችን የመኝታ ቤታችንን በራፍ መቆርቆር ሁለታችንንም ከእንቅልፋችን የቀሰቀሰን
-እናቴ ህልሙን ልትረሳ ሰውዬውንም ልትዘነጋ አልቻለችም፡፡ሰራ አልቻለችም..ሰውዬውን ልትዘናጋ.
ዘወትር እንደምታደርገው ማታ አካባቢ ቤተክርስቲያን ሄድን፡፡የተለመደውን የማታ ትምህርት ተከታትላ..ያው እንደወትሮዋ ከአምላኮ ጋር አንሾካሽካ ፤ስትጨርስ ስለህልሞም እያሰበች የመልስ ጉዞ ለማድረግ የቤተክርሲቲያን አጥር ግቢ ወጥተን ብዙም ሳንርቅ እኛ ሁለታችንም በህልማችን ያየናቸው ሽማጊሌ በትክክል እሳቸው ድንገት ከፊታችን ተደንቅረው መንገዳችንን ገቱት.እኔ ብዙም ባይደንቀኝም እናቴ ግን በድንዛዜ ሀውልት መስላ ነበር ባለችበት የቆመችው
-ሰውዬው ለእናቴ ድንጋጤ ብዙም ትኩረት ሳይሰጡ ጎንበስ ብለው እጃቸውን ጭንቅላቴ ላይ አሳርፈው በመዳበስ እይታቸውን ወደእናቴ አድርገው ‹‹ጌታ ችግርሽን ይፍታልሽ…እግዜያብሄር ለቅሶሽን ሰምቶል ››በማለት የብስራት ቃላቸውን አሰሟት
-ተአምር ነው፡፡እርሷ መላአክ ኖት…?
-አይ አይደለውም ሰው ነኝ፡፡ተራ ሰው ለሶስት ቀን በተከታታይ በህልሜ ሳያችሁ ነበር፡፡ህልሜን አምኜ እዚህ ስመጣ ደግሞ በአካል አገኘዋችሁ፡፡››
-እኔም አይቼዎታለው››
-በይ እንግዲህ የምኞትሽ ይሙላልሽ ?
-በህልሞት ምንም እንዲነግሩኝ አልተነገሮትም.››
-አይ ሁሉንም ለእሷ ነግሬያታለው..አንተ ብቻ አግኛትና ልጇን ደባብስላት ነው የተባልኩት፡፡……..ብለው አልፈውን መንገዳቸውን ሲቀጥሉ…እናቴ ከድንዛዜዋ ባና -እሺ እግዜር ይከተሎት..አለቻቸው
-አንቺንም ልጄ....ከእነልጅሽ እግዜያብሄር ይጠብቅሽ ፡፡ብለው ከእይታችን ተሰወሩብን
ከዛ ቡኃላ እናቴ ፍፁም ተረጋጋች
:
#ክፍል_ስድስት
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
..… እንደነርኮችሁ የመራመዴ ጉዳይ ተአምራዊ በሆነ መንገድ እልባት ካገኘ ቡኃላ እናቴ ለአንደበቴ መከፈት መጓጓት ጀመረች፡፡ያው እናት አይደለች ፡፡በተለይ ስድስት አመት ከሞላኝ ቡኃላ እኩዬቼ ሁሉ ወደትምህርት ቤት ሲጓዙ እኔ አንደበቴ መላቀቅ ባለመቻሉ ምክንያት እቤት በመቅረቴ ውስጧ ተጎዳና እንደአዲስ እኔን ለማዳን የምታደርገውን እንቅስቃሴ ጀመረች ፡፡በዚህ እንቅስቃሴዎ ወቅት ስታልፍም ሆነ ስታገድም የሚያገኞት ሰዎች ሁሉ የሆነ ነገር ሳይሏት ዝም ብለው አያልፎትም፡፡
መቼስ ሀበሻ ባህል ውስጥ አንዱ አስቸጋሪው ነገር የሆነ ሰው ችግር ላይ በወደቀ ቁጥር ምክር ሰጪ ሰው መብዛቱ የታወቀ ነው፡፡ለምን ጠበል አትወስጂውም……?አዋቂ ቤት ይሻልሻል……?እዚህ ከተማ ላይ አዲስ ሀኪም መጥቷል አሉ….…? ውጌሻ ጋር አይሻልሽም….የማይባል ነገር የለም፡፡ታዲያ ይሄ ችግር ውስጥ ላለችና ግራ ለገባት እናቴ በወቅቱ ምን ያህል ግራ አጋቢና አስጨናቂ እንደሚሆንባት መገመት አይከብድም፡፡
እናቴ አንደወትሮዋ እኔን ለማዳን ስትንከራተት ውላ ስትመለስ አባቷ ይናገራታል፡፡
-ልጄ በቃ ለአምላክ ተይው…እሱ እንዳደረገ ያድርገው
-እንዴት እንዳደረገ ያድርገው ስትል…?...ትጠይቃለች
-በቃ አንዳንዴ ከአምላክ ጋር እልክ መጋባት አያስፈልግም…አሱን አድናለው ብለሽ ከእዚህ እዛ ስትካለቢ አንቺም ከሰውነት ጓዳና ወጣሽ…እራስሺን እስኪ እይ… የአርባ አመት አሮጊት መስለሻል እኮ…ገና በሀያ ሶስት አመትሽ ፊትሽን ማድያት እየበላው ነው፡፡በዚህ ከቀጠልሽ የከፋ በሽታ ላይ መውደቅሽ አይቀርም፡፡
-እና ምን አድርጊ ነው የምትለኝ፡፡…?
በቃ እሱን አድናለው ብለሽ ከወዲህ ወዲያ መንከራተቱን አቁሚ.. እግዜያብሄር እግሩን ተርትሮልሻል …በቃ በዛ ተመስገን ብለሽ ሌላውን ተይው…ይሄው ለዓመታት ተንከረተሽ፡፡ ..ህክምናውንም ጠበሉንም ሞክረሻል፡፡ይሄ ነው ችግሩ ብሎ ሊነግርሽ የቻለ የህክምና ጠቢብ የለም፡፡ይሄ ማለት ደግሞ የልጅሽ ችግር ሚስጥር በአምላክ እጅ ብቻ እንደሆነ ነው የሚገባኝ፡፡ በእሱ እጅ ከሆነ ደግሞ ታአምሩን የሚያደርግበት የራሱ ቀንና ጊዜ አለው፡፡እሱን በትዕግስት መጠበቅ ነው፡፡ስለሆነም መንከራተቱን አቁሚ፡፡እዚሁ እንከባከበዋለን፡፡ምንም ነገር እንዳይጎልበት ማድረግ እንችላለን፡፡የሚጠብቁት ተጨማሪ ሰራተኞችም ልንቀጥርለት እንችላለን፡፡አንቺ ግን ከዚህ በላይ እራስሽን አትጣይ፡፡ ……
-አባዬ እናቱ እኮ ነኝ፡፡እንዴት ይሄ የእግዜር ስራና ፍቃድ ነው ብዬ እጆቼን አጣጥፌ ተስፋ ቆርጬ ልቀመጥ እችላለው…?፡፡አንተ እኔ እንደዛ ብሆንብህ የሆነችውን ትሁን ብለህ ተስፋ ቆርጠህብኝ ትተወኝ ነበር…?፡፡…….የትዝብት ጥያቄ ጠየቀቺው፡፡
-አይ…ስለልጅ ልጄ እኮ ነው እያወራን ያለነው… ለአንቺ ብቻ ሳይሆን ለእኔም ልጄ ነው፡፡ጨካኘ ሆኜ አይደለም፡፡ግን እሱን ለማደን በሚል ያልተረጋገጠ ተስፋ አንቺን እንዳላጣ ስለፈራው ነው፡፡ሰለጨነቀኝ ነው፡፡
-በቃ አባዬ በቃ …. መቼም በልጄ ተስፋ አልቆርጥም፡፡መቼም እግዜር እንዳደረገ ያድርገው ብዬ ልቤን አረጋግቼ እድሜ ልኩን ከሰው ተገልሎ በተዘጋ ቤት ውስጥ እንዲኖር በመፍረድ እኔ ለመሽቀርቀርና እራሴን ለማሽሞንሞን አልሞክርም…..መቼም፡፡……ብላ ከአባቷ በንዴት እና በለቅሶ ተለይታ እኔን ወደመኝታ ቤት ይዛ ገብታ ግንባሬ ላይ ተደፍታ በእንባ እየታጠበች ከፈጣሪዋ ጋር ለሳዕታት በምሬት ካወራች..(እናንተ ከፀለየች )ብላችሁ ማንበብ ትችላላችሁ አቅፋኝ ትተኛለች፡፡
ማለዳ ሊነጋጋ ሲል ጥርት ያለ ህልም ታያለች፡፡ተመሳሳይ አይነት ህልም እኔም አይቻለው፡፡ልዩነቱ እሷ ያየችውን ህልም ለአባቷ መናገር ስትችል..እኔ ደግሞ ምናገርበት አንደበት ስላልነበረኝ ለእሷ እንኳን መናገር አልቻኩም፡፡
-ህልሙ እንዲህ ነው
ጠይም የተለጠለጠ ኑግ የሚመስል የሰውነት ቀለም ያላቸወ ፊታቸው በአደገ እና በተንዠረገገ ነጭ ፀጉር የተሸፈነ ሽማግሌ መኝታ ክፍላችን ሰተት ብለው ይገባሉ፡፡እናቴ አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀምጣ እኔን ጉልበቷ ላይ ታቅፋ በተመስጦ ላይ ሳለች ሰውዬው ወደእኛ ቀርበው ወለሉ ላይ በርከክ ይሉና ጭንቅላቴን እየዳበሱ
‹‹ ..ልጅሽ ታላቅ ሰው ይሆናል፡፡አንድ ቀን ዓለም ስለእሱ በመደመም ያወራል፡፡ምድራዊውን አለም ከመንፈሳዊው አለም ጋር ድልድይ ሆኖ ያስተሳስራል…ስለዚህ አንቺ መጨነቅሽን አቁሚ .. እሱ በፈለገ ቀን እራሱን ማዳን ይችላል፡፡ ከራሱም ተርፎ ሌላውን ያድናል፡፡ግን ሲፈልግ…ቀኑ ሲደርስ ብቻ ነው እንደዛ የሚያደርገው፡፡
-አባት ስለእኔ ልጅ ነው የሚያወሩት..?በጥርጣሬ እና ያሉትን ባለማመን ትጠይቃለች፡፡
-አዎ ልጄ ..እኔ የአማላክ መልዕክተኛ ነኝ፡፡ አምላክ እንደገለፀልኝ ከሆነ የልጅሽ እውቀት ጥልቅና ከዛኛው አለም ይዞት የመጣው ነው፡፡
-ከዛኛው አለም ሲሉ…?፡፡
ዳግመኛ ስለመወለድ የምታውቂው ነገር አለ ልጄ.?.
-እኔ እንጃ ብቻ ከዚህ በፊት የሰማው መሰለኝ፡፡አዎ ክርስቲያን አይደለው..ሰው ከውሀና ከመንፈስ ዳግመኘ ካልተወለደ በስተቀር ወደመንግስቱ መግባት እንደማይችል አምላክ ተናግሯል፡፡
-ትክክል እኔ ግን እያልኩ ያለውት ልጅሽች ወደ እዚህች ምድር ሲመጣ ለሁለተኛ ጊዜ ነው፡፡ ከሁለት ሺ አመታት በፊት ነፍሱ እዚህች ምድር ላይ ነበረች…የበለፀገ ህይወት እና በእውቀት የተሞላ ስብዕና ነበረው..እና ያንን እውቀት ነፍሱ ይዛው የመጣች ይመስለኛል፡፡
-እና እኔ ምን ላድርግ …?
-ምንም ፤እራሱ ፈልጎ የሆነ ነገር ማድረግ እስኪችል ድረስ አትጫኚው..አንቺም አትባክኚ፡፡ ብቻ በእሱ ላይ ሁሌም እምነት ይኑርሽ..ወስጡ የተቀበረውን እውነትና እውቀት ብቻ እንዲገለፅለት ሁሌ ከጎኑ ሁኚ…ከጎኑ መሆንሽ ብቻ ለእሱ በቂው ነው..ሌላውን በጊዜው እራሱ ያደርገዋል፡፡
-ሽበታሙ መልዕክት አድራሽ ሽማግሊ ከክፍላችን ሳይወጣ ነበር የሰራተኛችን የመኝታ ቤታችንን በራፍ መቆርቆር ሁለታችንንም ከእንቅልፋችን የቀሰቀሰን
-እናቴ ህልሙን ልትረሳ ሰውዬውንም ልትዘነጋ አልቻለችም፡፡ሰራ አልቻለችም..ሰውዬውን ልትዘናጋ.
ዘወትር እንደምታደርገው ማታ አካባቢ ቤተክርስቲያን ሄድን፡፡የተለመደውን የማታ ትምህርት ተከታትላ..ያው እንደወትሮዋ ከአምላኮ ጋር አንሾካሽካ ፤ስትጨርስ ስለህልሞም እያሰበች የመልስ ጉዞ ለማድረግ የቤተክርሲቲያን አጥር ግቢ ወጥተን ብዙም ሳንርቅ እኛ ሁለታችንም በህልማችን ያየናቸው ሽማጊሌ በትክክል እሳቸው ድንገት ከፊታችን ተደንቅረው መንገዳችንን ገቱት.እኔ ብዙም ባይደንቀኝም እናቴ ግን በድንዛዜ ሀውልት መስላ ነበር ባለችበት የቆመችው
-ሰውዬው ለእናቴ ድንጋጤ ብዙም ትኩረት ሳይሰጡ ጎንበስ ብለው እጃቸውን ጭንቅላቴ ላይ አሳርፈው በመዳበስ እይታቸውን ወደእናቴ አድርገው ‹‹ጌታ ችግርሽን ይፍታልሽ…እግዜያብሄር ለቅሶሽን ሰምቶል ››በማለት የብስራት ቃላቸውን አሰሟት
-ተአምር ነው፡፡እርሷ መላአክ ኖት…?
-አይ አይደለውም ሰው ነኝ፡፡ተራ ሰው ለሶስት ቀን በተከታታይ በህልሜ ሳያችሁ ነበር፡፡ህልሜን አምኜ እዚህ ስመጣ ደግሞ በአካል አገኘዋችሁ፡፡››
-እኔም አይቼዎታለው››
-በይ እንግዲህ የምኞትሽ ይሙላልሽ ?
-በህልሞት ምንም እንዲነግሩኝ አልተነገሮትም.››
-አይ ሁሉንም ለእሷ ነግሬያታለው..አንተ ብቻ አግኛትና ልጇን ደባብስላት ነው የተባልኩት፡፡……..ብለው አልፈውን መንገዳቸውን ሲቀጥሉ…እናቴ ከድንዛዜዋ ባና -እሺ እግዜር ይከተሎት..አለቻቸው
-አንቺንም ልጄ....ከእነልጅሽ እግዜያብሄር ይጠብቅሽ ፡፡ብለው ከእይታችን ተሰወሩብን
ከዛ ቡኃላ እናቴ ፍፁም ተረጋጋች
👍4
#የመልስ_ጉዞ_ወደ_መነሻ
:
#ክፍል_ሰባት
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
ትምህርት ቤት ገባው፡፡መናገር ባልችልም የምማረው ከተናጋሪዎች ጋር ነበር፡፡አርግጥ ተማሪዎቹም ሆነ አስተማሪዎቹ ብዙም አይጥሙኝም፡፡ትምህርቱም እንደዛው ፡፡ግን ተማርልኝ ያለቺኝ እናቴ ስለሆነችና እሷ ያለቺኝን ነገር ሁሉ ተመቸኝም አልተመቸኝም …አስደሰተኝም ፤አስከፋኝም ማድረግ ስላለብኝ ነው ያደረኩት፡፡
አንደኛ ክፍል አንደኛ ሴሚስተር በከፍሉ ካሉት 56 ተማሪዎች 55ተኛ ደረጃ ወጣው ፡፡የበለጥኩት አንድ ልጅ በመጨረሻዎቹ የፈተና ቀኖች ትምህርት ቤት ተገኝቶ ዋናውን ፈተና መውሰድ ስላልቻለ እና ካርዱ ላይ የተቀመጠለት ውጤት ቴስት ላይ ያገኛቸው ውጤቶች ብቻ ነበሩ፡፡
እኔ ባመጣውት ውጤት ማንም አልተደነቀም ምክንያቱም ማሰብ እንደምችል እራሱ የሚያምን ሰው ጥቂት ነው፡፡ማሰብ ማይችል ሰው እንዴት መማር ይችላል ብለው ይገምታሉ…?፡፡ ካርዴን ይዤ መጥቼ ለእናቴ ስሰጣት እቤቱ ሙሉ ወዳጅ ዘመድ በተሰበሰበበት ነበር፡፡ልክ ድንበር ሊወር የመጣን የጠላት ወታደር ፊት ለፊት በጀግንነት ተፋልሞ በማሸነፍ የድል ብስራት ለወገኖቹ እንደሚያስር ወታደር ደረቴን በኩራት ገልብጬ…
-አይ ዝም ብለሽ እኮ ነው የምትለፊው…..እቤት ከነበሩት መካከል አንዱ ዘመድ የተናገረው ነበር..
-እንዴት ዝም ብዬ…?
-ትምህርት እኮ ለእሱ ይከብደዋል፡፡እንዲሁ ከልጆች ተቀላቅሎ ይዋል ብለሽ እንደሆነ ይገባናል፡፡ግን ማሰብ ያለብሽ ወደሁለተኛ ክፍል ለመዘዋወር ስንት አመት ይፈጅበታል የሚለውን ነው……?ሶስት……?አራት….…?
.
-ለእኔ ስሜት ሳይጨነቁ እንደአፌ አእምሮዬም ዝግና ዱልዱም መሆኑን እርግጠኛ ሆነው እናቴን የሚያሳቅቁበት መርዝ ንግግር ሰነዘሩ..
እናቴ ከተቀመጥኩበት ወደራሷ ስባኝ ጭኖቾ ላይ በማጋደም ጭንቅላቴን እየዳበሰች…
-ልጄ በአመቱ መጨረሻ ወደ ሁለተኛ ክፍል በበቂ ውጤት አልፎ ካልገባ እኔ ላይ ሳቁብኝ፡፡…አለቻቸው እሷም ልክ እንደእኔው ጀግና ልጅ እንዳለት እርግጠኛ በመሆን ደረቷን ነፍታ..
-አረ ተይ የማይሆነውን ….ብለው ወዲያውኑ ሳቃቸውን የለቀቁት በርከት ይሉ ነበር….እኔ ግን የእናቴ ንግግር ትንሿን አዕምሮዬን ሰንጥቆ ነበር የገባው፡፡‹በዓመቱ መጨረሻ ልጄ ወደ ሁለተኛ ክፍል ካላለፈ ሳቁብኝ›…ፃድቋ እናቴ ላይማ ማንም አይስቅባትም…..ወሰንኩ፡፡
-ማታ ብቻችንን ሆነን ደረቷ ላይ ተኝቼ ማስበው ወደ ሁለተኛ ክፍል ስለማለፍ ነበር፡፡
-ምን ማድረግ አለብኝ…?፡፡በአንደኛ ሲሚስተር እንዴት እንደተማርኩና …?እንዴት እንደተፈተንኩ…? አሰብኩ.. አስተማሪዎች ሲያስተምሩ አንድም ቀን አዳምጬያቸው አላውቅም…አንዳንድ ቀን በመስኮት አሻግሬ ሜዳ የሚጫወቱትን ልጆች ወይም ዛፍ ላይ አርፋ የምትዘምረዋ ወፍ ወይም በሰማይ ላይ የሚጓዘውን ደመና ስመለከት ነው ክፍለ ጊዜው የሚያልቀው፡፡አንዳንዴ ደግሞ ወረቀት ቀድና በምራቄ አለስልሼ ጆሮዬ ውስጥ ጠቀጥቃለው..
---አንድ ቀን ይሄንን ሳደርግ እጅ ከፍንጅ የያዘኝ አንድ መምህር..አንደበትህን እንደዘጋው ጆሮህንም እንዲደፍንልህ ትፈልጋለህ…ሲል ጠየቀኝ በመገረምና በንዴት አፍጥጦብኝ
ግንባሬን በመወዝወዝ‹‹አዎ…›› የሚል ምልክት አሳየውት
አማተበና‹‹አንተንስ ትልቁ አጋንንት ነው የተጠጋህ ››ብሎኝ ወደማስተማሩ ተመለሰ…..ከዛን ቀን ቡኃላ ጭራሽ የዛ ክፍል ተማሪ እንዳልሆንኩ በመቁጠር ረሳኝ … እኔም ተመቸኝ..፡፡
ስለዚህ አሁን በዓመቱ መጨረሻ እኚ ወሬኞች እናቴ ላይ እንዳይስቁባት..አስተማሪዎች የሚሉትን ትንሽ ትንሽም ቢሆን ማዳመጥ መጀመር አለብኝ ብዬ ወሰንኩ፡፡
የትምህርት ዘመኑ ተጠናቆ ..ሰኔ ሰላሳ መጥቶ የወላጆች በዓል ላይ ያልታሰበ ነገር ተከሰተ….ልዩ ተሸላሚ ሆኜ መድረክ ላይ ተጠራው.. ሰው ሁሉ የፀባይ ሽልማት መስሎት ነበር..ያው ድዳ በመሆኔ ተናግሬ መበጥበጥ ስለማልችል በተጨማሪም በፀባዬ ጠማማነትም የተነሳ ከልጆች ጋርም እንደማልገጥም ብዙዎች ስለሚያውቁ የፀባይ ሽልማትማ ይገባዋል… ብለው ነበር ያሰቡት፡፡
-የትምህርት ቤቱ ዳሪክተር ግን እኔን ስራቸው አቁመው ጭንቅላቴን ልክ እንደ አባት እየዳበሱ በአስገምጋሚ ሻካራ ድምፃቸው የትምህርት ቤቱን ግቢ ለሞሉት ተማሪዎቻቸውና ወላጆቻቸው መናገር ጀመሩ…
***
በ25 ዓመት የማስተማር ልምዴ እንዲህ አይነት ተአምር ገጥሞኝ አያውቅም፡፡ማመን አቅቶን ውጤቶቹን ሁሉ ደግመን ፈትሸን ነበር የሚገርመው ምንም እንከን አልተገኘባቸውም ፡፡በአንደኛ ሴሚስተር ከክፍሉ የመጨረሻውን ደረጃ ነበር የያዘው…
ኹ ..ሁሁሁ ብሎ ታደሚው ሁሉ አውካካ..
በዚህኛው ሴሚስተር ደግሞ አንደኛ ….ከሰባት ትምህርት ስድስቱን መቶ.... አንዱን ዘጠና ስምንት ነው ያመጣው፡፡አማካኝ ደረጃው 23ተኛ ደረጃ ፡፡እንዲህ አይነት ለውጥ በማምጣቱ ትምህርት ቤታችን እንዶኮራበት ወላጆቹም ልትኮሩበት ይገባችሆል..በቀጣይ በዚሁ እንዲቀጥልም አስፋላጊውን ድጋፍ አድርጉለት ..በማለት ከአቅሜ በላይ የሚከብድ መዝገበ ቃላት በሽልማት መልክ አሸከሙኝ››
መድረኩን ለቅቄ እየወረድኩ እናቴን አየዋት… ከአምስት ወራት በፊት ሳቁብኝ ብላቸው ወደነበሩ ወዳጆቾ ዞራ ቅዱስ የእርካታ ሳቅ እየሳቀችባቸው ነበር….እኔም በፈገግታ አገዝኳት።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
:
#ክፍል_ሰባት
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
ትምህርት ቤት ገባው፡፡መናገር ባልችልም የምማረው ከተናጋሪዎች ጋር ነበር፡፡አርግጥ ተማሪዎቹም ሆነ አስተማሪዎቹ ብዙም አይጥሙኝም፡፡ትምህርቱም እንደዛው ፡፡ግን ተማርልኝ ያለቺኝ እናቴ ስለሆነችና እሷ ያለቺኝን ነገር ሁሉ ተመቸኝም አልተመቸኝም …አስደሰተኝም ፤አስከፋኝም ማድረግ ስላለብኝ ነው ያደረኩት፡፡
አንደኛ ክፍል አንደኛ ሴሚስተር በከፍሉ ካሉት 56 ተማሪዎች 55ተኛ ደረጃ ወጣው ፡፡የበለጥኩት አንድ ልጅ በመጨረሻዎቹ የፈተና ቀኖች ትምህርት ቤት ተገኝቶ ዋናውን ፈተና መውሰድ ስላልቻለ እና ካርዱ ላይ የተቀመጠለት ውጤት ቴስት ላይ ያገኛቸው ውጤቶች ብቻ ነበሩ፡፡
እኔ ባመጣውት ውጤት ማንም አልተደነቀም ምክንያቱም ማሰብ እንደምችል እራሱ የሚያምን ሰው ጥቂት ነው፡፡ማሰብ ማይችል ሰው እንዴት መማር ይችላል ብለው ይገምታሉ…?፡፡ ካርዴን ይዤ መጥቼ ለእናቴ ስሰጣት እቤቱ ሙሉ ወዳጅ ዘመድ በተሰበሰበበት ነበር፡፡ልክ ድንበር ሊወር የመጣን የጠላት ወታደር ፊት ለፊት በጀግንነት ተፋልሞ በማሸነፍ የድል ብስራት ለወገኖቹ እንደሚያስር ወታደር ደረቴን በኩራት ገልብጬ…
-አይ ዝም ብለሽ እኮ ነው የምትለፊው…..እቤት ከነበሩት መካከል አንዱ ዘመድ የተናገረው ነበር..
-እንዴት ዝም ብዬ…?
-ትምህርት እኮ ለእሱ ይከብደዋል፡፡እንዲሁ ከልጆች ተቀላቅሎ ይዋል ብለሽ እንደሆነ ይገባናል፡፡ግን ማሰብ ያለብሽ ወደሁለተኛ ክፍል ለመዘዋወር ስንት አመት ይፈጅበታል የሚለውን ነው……?ሶስት……?አራት….…?
.
-ለእኔ ስሜት ሳይጨነቁ እንደአፌ አእምሮዬም ዝግና ዱልዱም መሆኑን እርግጠኛ ሆነው እናቴን የሚያሳቅቁበት መርዝ ንግግር ሰነዘሩ..
እናቴ ከተቀመጥኩበት ወደራሷ ስባኝ ጭኖቾ ላይ በማጋደም ጭንቅላቴን እየዳበሰች…
-ልጄ በአመቱ መጨረሻ ወደ ሁለተኛ ክፍል በበቂ ውጤት አልፎ ካልገባ እኔ ላይ ሳቁብኝ፡፡…አለቻቸው እሷም ልክ እንደእኔው ጀግና ልጅ እንዳለት እርግጠኛ በመሆን ደረቷን ነፍታ..
-አረ ተይ የማይሆነውን ….ብለው ወዲያውኑ ሳቃቸውን የለቀቁት በርከት ይሉ ነበር….እኔ ግን የእናቴ ንግግር ትንሿን አዕምሮዬን ሰንጥቆ ነበር የገባው፡፡‹በዓመቱ መጨረሻ ልጄ ወደ ሁለተኛ ክፍል ካላለፈ ሳቁብኝ›…ፃድቋ እናቴ ላይማ ማንም አይስቅባትም…..ወሰንኩ፡፡
-ማታ ብቻችንን ሆነን ደረቷ ላይ ተኝቼ ማስበው ወደ ሁለተኛ ክፍል ስለማለፍ ነበር፡፡
-ምን ማድረግ አለብኝ…?፡፡በአንደኛ ሲሚስተር እንዴት እንደተማርኩና …?እንዴት እንደተፈተንኩ…? አሰብኩ.. አስተማሪዎች ሲያስተምሩ አንድም ቀን አዳምጬያቸው አላውቅም…አንዳንድ ቀን በመስኮት አሻግሬ ሜዳ የሚጫወቱትን ልጆች ወይም ዛፍ ላይ አርፋ የምትዘምረዋ ወፍ ወይም በሰማይ ላይ የሚጓዘውን ደመና ስመለከት ነው ክፍለ ጊዜው የሚያልቀው፡፡አንዳንዴ ደግሞ ወረቀት ቀድና በምራቄ አለስልሼ ጆሮዬ ውስጥ ጠቀጥቃለው..
---አንድ ቀን ይሄንን ሳደርግ እጅ ከፍንጅ የያዘኝ አንድ መምህር..አንደበትህን እንደዘጋው ጆሮህንም እንዲደፍንልህ ትፈልጋለህ…ሲል ጠየቀኝ በመገረምና በንዴት አፍጥጦብኝ
ግንባሬን በመወዝወዝ‹‹አዎ…›› የሚል ምልክት አሳየውት
አማተበና‹‹አንተንስ ትልቁ አጋንንት ነው የተጠጋህ ››ብሎኝ ወደማስተማሩ ተመለሰ…..ከዛን ቀን ቡኃላ ጭራሽ የዛ ክፍል ተማሪ እንዳልሆንኩ በመቁጠር ረሳኝ … እኔም ተመቸኝ..፡፡
ስለዚህ አሁን በዓመቱ መጨረሻ እኚ ወሬኞች እናቴ ላይ እንዳይስቁባት..አስተማሪዎች የሚሉትን ትንሽ ትንሽም ቢሆን ማዳመጥ መጀመር አለብኝ ብዬ ወሰንኩ፡፡
የትምህርት ዘመኑ ተጠናቆ ..ሰኔ ሰላሳ መጥቶ የወላጆች በዓል ላይ ያልታሰበ ነገር ተከሰተ….ልዩ ተሸላሚ ሆኜ መድረክ ላይ ተጠራው.. ሰው ሁሉ የፀባይ ሽልማት መስሎት ነበር..ያው ድዳ በመሆኔ ተናግሬ መበጥበጥ ስለማልችል በተጨማሪም በፀባዬ ጠማማነትም የተነሳ ከልጆች ጋርም እንደማልገጥም ብዙዎች ስለሚያውቁ የፀባይ ሽልማትማ ይገባዋል… ብለው ነበር ያሰቡት፡፡
-የትምህርት ቤቱ ዳሪክተር ግን እኔን ስራቸው አቁመው ጭንቅላቴን ልክ እንደ አባት እየዳበሱ በአስገምጋሚ ሻካራ ድምፃቸው የትምህርት ቤቱን ግቢ ለሞሉት ተማሪዎቻቸውና ወላጆቻቸው መናገር ጀመሩ…
***
በ25 ዓመት የማስተማር ልምዴ እንዲህ አይነት ተአምር ገጥሞኝ አያውቅም፡፡ማመን አቅቶን ውጤቶቹን ሁሉ ደግመን ፈትሸን ነበር የሚገርመው ምንም እንከን አልተገኘባቸውም ፡፡በአንደኛ ሴሚስተር ከክፍሉ የመጨረሻውን ደረጃ ነበር የያዘው…
ኹ ..ሁሁሁ ብሎ ታደሚው ሁሉ አውካካ..
በዚህኛው ሴሚስተር ደግሞ አንደኛ ….ከሰባት ትምህርት ስድስቱን መቶ.... አንዱን ዘጠና ስምንት ነው ያመጣው፡፡አማካኝ ደረጃው 23ተኛ ደረጃ ፡፡እንዲህ አይነት ለውጥ በማምጣቱ ትምህርት ቤታችን እንዶኮራበት ወላጆቹም ልትኮሩበት ይገባችሆል..በቀጣይ በዚሁ እንዲቀጥልም አስፋላጊውን ድጋፍ አድርጉለት ..በማለት ከአቅሜ በላይ የሚከብድ መዝገበ ቃላት በሽልማት መልክ አሸከሙኝ››
መድረኩን ለቅቄ እየወረድኩ እናቴን አየዋት… ከአምስት ወራት በፊት ሳቁብኝ ብላቸው ወደነበሩ ወዳጆቾ ዞራ ቅዱስ የእርካታ ሳቅ እየሳቀችባቸው ነበር….እኔም በፈገግታ አገዝኳት።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍7
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ
:
#ክፍል_ስምንት
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ከዛ ቡኃላ የትምህርት ቤቱ አስደናቂ ኮከብ ተማሪ ሆኜ ቀጠልኩ ፡፡እስከሶስተኛ ክፍል እስካጠናቅቅ ድረስ አንደበቴ እንደተዘጋ ነበር፡፡አስር አመት ከሆነኝ ቡኃላ አንድ ለሊት እኔና እናቴ የሰላም እንቅልፍ ተኝተን እያለ…ባልተለመደ ሰዓትና ሁኔታ የቤታችን መንጓጓት ሁለታችንንም እኩል ከእንቅልፍችን ቀሰቀሰን…. ሁለታችንም እኩል ዙሪያችንን ስንቃይ እቤቱ በድቅድቅ ጨለማ እንደተዋጠ ስለነበር ምንም ሊታየን አልቻለም … መብራቱን ለማብራት እኔም እናቴም እልደፈርንም….. …እናቴ ከክንዷ ላይ እኔን በማውረድ ከእቅፎ አውጥታኝ በዝግታ በመነስታ እና ቁጭ በማለት ምን እንደተፈጠረ ለማረጋጋጥ ጆሮዋን አቀናች..እኔም እሷን ተከትዬ ለመነሳት ስሞክር በእጇ ደፍቃ ባለውበት አስቀረቺኝና ወደጆሮዬ ተጠግታ በሹክሹክታ‹‹..አርፈህ ትንፋሽህን ውጠህ ተኛ..››በማለት አስጠነቀቀቺኝ …
ወዲያው የመኝታ ቤቱ በራፍ ሲበረገድና ባትሪ ግንባራችን ላይ ሲበራ እናቴ ‹ዋይ› የሚል ድምጽ አሰምታ ‹ልጄን ›በማለት እኔ ላይ ድፍት አለች
…ሁሉም ቅፅበታዊ ነበር…ውር ውር የሚል የባትሪ ብርሀን ግድግዳው ላይ ወዲህ ወዲያ ሲራወጥ እና የእግር ኮቴ ሲዘዋወር ይሰማኛል…
‹‹በል ፈትሽ ..ኮመዲኖውን ክፈት››ድምጽ ተሰማ
‹‹እንቀሳቀሳለው ብለሽ አንቺን ሳይሆን ልጅሽን ነው ፀጥ የምናደርግልሽ..››ሌላው እናቴን አስፈራራ…..
እናቴ የራሷን ትንፋሽ ወደውስጧ ማፈኗ ሳያንሳት እኔንም እላዬ ላይ እንደተደፋች በእጆቾም አንደበቴን ከደነችው፡፡
‹‹-አዎ ሁሉንም በሻንጣ ክተት..አዎ ወርቅም አገኘህ…ጥሩ ልብሶቹንም እንዳትተው››ይላል
ሶስት መሆናቸው በድምጻቸው ልዩነት ገምቼያለው፡፡ያው መዘረፋችን ቢያሳዝነኝም ዋናው እናቴን አለመጉዳታቸው ነው ብዬ በመጽናናት ስራቸውን እስኪጨርሱ እናቴ እንዳፈነቺኝ ታፍኚ በተኛውበት ተረጋግቼ የሚያደርጉትን ማየት ባልችልም የሚናገሩትን በትዕግስት እየሰማው ሳለ
በቃ እንሂድ ››በማለት አንዱ የመጡበትን ማጠናቀቃቸውን አበሰረን….››እፎይ ምንልበት ጊዜ ደረሰ.. ስል ተደሰትኩ
‹‹በል እናትዬውን እሰራት..አፎንም አሽገው››የሚል ደባሪ ድምጽ ወደጆሮዬ ገባ
‹‹ለምን አስፈለገ.…?.››ሌላው ጠየቀ
‹‹ትቀልዳለህ እንዴ ..ከዚህ ሳንወጣ ጩኸቷን ብትለቀውስ…?›› ስጋቱን ተናገረ
‹‹እናንተ ብቻ የያዛችሁትን ይዛችሁ በሰላም ውጡልኝ …በልጄ ምላለው ምንም አልጮህም››እናቴ ተማፀነቻቸው
አንደኛው‹‹ዝም በይ..›› ብሏት በምኑ እንደሆነ አላውቅም ከላይ ወገቧን ሲነርታት የህመሙ ስሜት ከስር ያለውትን እኔን ሳይቀር ተሰማኝ …
‹‹ና በል አንሳትና ከእዚህ የአልጋ እግር ጋር ጠፍንገህ እሰራት …ልጇንም እንደዛው….››ሲለውና ሌላው ትዕዛዙን ለማክበር እናቴን መንጭቆ ከላዬ ላይ ሲያነሳት ..የሆነ የማላውቀው ኃይል በሰውነቴ ሲሰራጭ ታወቀኝ
…እናቴ ‹‹ልጄን … ልጄን እንዳትነኩብኝ ››..እያለች ስትወራጭ…የድምፆ ቅጭልጭልታ ጆሮዬን እየነዘረ ወደጭንቅላቴ ሲሰርግ እና የሆነ የማላቀውቀው መንፈስ ሲቆጣጠረኝ አንድ ሆነ…..
ወደእኔ ከመምጣታቸው በፊት ተሸከራከርኩና በተቃራኒው በኩል ከአልጋው ተንከባልዬ ወረድኩ …… አዛዥ ቢጤው‹‹ልጁን ያዘው.. ልጁን ያዘው›› ሲል ይሰማኛል፡፡ አልጋውን ዞሮ ወደእኔ ከመምጣቱ በፊት ለእኔም ግልፅ ባልሆነልኝ የደመነፈስ ውሳኔ እና የእኔ ባልሆነ ፍጥነት የቁም ሳጥኑን መሳቢያ ስቤ ሽጉጥ አወጣውና ወዲያው መብራቱን በማብራት በኮማዲኖ በራፍ መላ አካሌን በመከለል ጭንቅላቴን ብቻ በከፊል ብቅ አድርጌ ሁኔታውን ቃኘው ….፡፡አዎ እንደገመትኩት ሶስት ናቸው፡፡ሁሉም ፊታቸው ላይ ጭንብል አጥልቀዋል፡፡ግን የጠበቅኮቸውን ያህል አስፈሪና ወጠምሻ አይነት አይደሉም…አንዱ የብረት ዱላ ሁለቱ ጩቤ ይዘዋል፡፡አንዱ በራፉ ጋ ቆሞ በቀኝ እጁ የያዘውን ባትሪ እኔ ወዳለውበት ቀስሯል፡፡ማብራቱን ካበራው ቡኃላ እንኳን አላጠፋውም..ሌላ እናቴን እያሰራት ነው..ሶስተኛው ሊይዘኝ ወደእኔ እየተንደረደርረ ነበር ..ሊያንቀኝ ሁለት ሜትር ያህል ብቻ ነበር የሚቀረው፡፡ከተሸሸኩበት ሳልወጣ ልክ ፊልም ላይ ደጋግሜ እንደማየው የያዝኩትን ሽጉጥ ቃቃ አድርጌ በማቀባበል እጄን ወደፊት በግንባሩ አቅጣጫ ቀስሬ ‹‹ ግንባርህን እንዳልፈረክሰው ባለህበት ቁም…››
ስለው ሳያቅማማ ደንዝዞ ትዛዜን አከበረ…እሱ ብቻ ሳይሆን ሶስቱም ያልጠበቁት ስላጋጠማቸው በሉበት ሲርበተበቱ በሰከንድ ሽርፍራፊ ቃኘው …ብዙም ልምድ የሌላቸው የመንደር ሌቦች መሆናቸውን ወዲያው ተረዳው፡፡
አናቴን እያሰራት ወደነበረው ሽጉጡን አዙሬ …‹‹እናቴን ልቀቃት…››ጮህኩበት …
ማሰሩን አቁሞ ቁጢጥ ካለበት በመነሳት ቀጥ ብሎ ቆመ…
ትዕዛዜን ቀጠልኩ ‹‹…አሁን አንድ ሰው ከመግደሌ በፊት እቃውን አስቀምጣችህ እቤቱን ለቃችሁ ውጡ ››
ተያዩና በምልክት በመነጋገር ወደኃላ መሳብ ጀመሩ…በራፍን ካለፉ ቡኃላ በሩጫ አስነኩት…
ከእውነተኛ ሽጉጥ ጋር በእጅ ካልያዙት በስተቀር ምንም ልዩነቱ የማይታወቀውን ልጅ ሆኜ የተገዛልኝን መጫወቻ ሽጉጥ መሬት ጥዬ ወደእናቴ ተንደረደርኩና አፎ ውስጥ የጠቀጠቀውን ጨርቅ ቀድሜ አውጥቼ በመጣል…. እጆቾን ልፈታ ስጣጣር እሷ እልልታዋን እስነካችው…
-እንዴ ምን እየሆነች ነው…?፡፡ግራ ገባኝ፡፡ ሰው እቤቱ ሌባ ሲገባበት ኡኡ ነው ማለት ያለበት ወይስ እልልል….…?
ወይ ድንጋጤ
- …እማ አይዞሽ ተራጋጊ …በማለት እጆን ፈትቼ ስጨርስ ተጠምጥማብኝ እያገላበጠች ትስመኝ ጀመረች
‹‹አደረከው..ልጄ አደረከው….አንድ ቀን እንዲህ እንደሚሆን አምን ነበር…እግዚያብሄር ሁሌም ካንተ ጋ ነው…አዎ አንተ ልዩ ነህ፡፡››
‹‹እማ ..አዎ ደርሼልሻለው … ከአሁን ወዲህ አይኔ እያየ ማንም ሊያጠቃሽና ሊያመናጭቅሽ አይችልም.. ማንም እንደዛ እንዲያደርግ አልፈቅድለትም…››ፎከርኩ
‹‹ እሱ አይደለም ልጄ …እሱ አይደለም..መናገር ቻልክ..ተናገርክ..እያወ
ራሀኝ ነው››ስትለኝ ድንግርግሬ ወጣ….እንዴ እያወራው ነው እንዴ ….…?.ከመገረሜ ሳልወጣ የእናቴን እልልታ የሰሙ የቤታችን ተከራዬች አያቴም ጭምር ከሚጣፍጥ የለሊት እንቅልፋቸው ተነስተው በመምጣት ወደቤታችን ሲንጋጉ ሰማን….
💫ይቀጥላል💫
የኛ ክፍያችን የናንተ ደስታ ነው ስሜታችሁን Like 👍👍 በማድረግ ግለፁልን
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
:
#ክፍል_ስምንት
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ከዛ ቡኃላ የትምህርት ቤቱ አስደናቂ ኮከብ ተማሪ ሆኜ ቀጠልኩ ፡፡እስከሶስተኛ ክፍል እስካጠናቅቅ ድረስ አንደበቴ እንደተዘጋ ነበር፡፡አስር አመት ከሆነኝ ቡኃላ አንድ ለሊት እኔና እናቴ የሰላም እንቅልፍ ተኝተን እያለ…ባልተለመደ ሰዓትና ሁኔታ የቤታችን መንጓጓት ሁለታችንንም እኩል ከእንቅልፍችን ቀሰቀሰን…. ሁለታችንም እኩል ዙሪያችንን ስንቃይ እቤቱ በድቅድቅ ጨለማ እንደተዋጠ ስለነበር ምንም ሊታየን አልቻለም … መብራቱን ለማብራት እኔም እናቴም እልደፈርንም….. …እናቴ ከክንዷ ላይ እኔን በማውረድ ከእቅፎ አውጥታኝ በዝግታ በመነስታ እና ቁጭ በማለት ምን እንደተፈጠረ ለማረጋጋጥ ጆሮዋን አቀናች..እኔም እሷን ተከትዬ ለመነሳት ስሞክር በእጇ ደፍቃ ባለውበት አስቀረቺኝና ወደጆሮዬ ተጠግታ በሹክሹክታ‹‹..አርፈህ ትንፋሽህን ውጠህ ተኛ..››በማለት አስጠነቀቀቺኝ …
ወዲያው የመኝታ ቤቱ በራፍ ሲበረገድና ባትሪ ግንባራችን ላይ ሲበራ እናቴ ‹ዋይ› የሚል ድምጽ አሰምታ ‹ልጄን ›በማለት እኔ ላይ ድፍት አለች
…ሁሉም ቅፅበታዊ ነበር…ውር ውር የሚል የባትሪ ብርሀን ግድግዳው ላይ ወዲህ ወዲያ ሲራወጥ እና የእግር ኮቴ ሲዘዋወር ይሰማኛል…
‹‹በል ፈትሽ ..ኮመዲኖውን ክፈት››ድምጽ ተሰማ
‹‹እንቀሳቀሳለው ብለሽ አንቺን ሳይሆን ልጅሽን ነው ፀጥ የምናደርግልሽ..››ሌላው እናቴን አስፈራራ…..
እናቴ የራሷን ትንፋሽ ወደውስጧ ማፈኗ ሳያንሳት እኔንም እላዬ ላይ እንደተደፋች በእጆቾም አንደበቴን ከደነችው፡፡
‹‹-አዎ ሁሉንም በሻንጣ ክተት..አዎ ወርቅም አገኘህ…ጥሩ ልብሶቹንም እንዳትተው››ይላል
ሶስት መሆናቸው በድምጻቸው ልዩነት ገምቼያለው፡፡ያው መዘረፋችን ቢያሳዝነኝም ዋናው እናቴን አለመጉዳታቸው ነው ብዬ በመጽናናት ስራቸውን እስኪጨርሱ እናቴ እንዳፈነቺኝ ታፍኚ በተኛውበት ተረጋግቼ የሚያደርጉትን ማየት ባልችልም የሚናገሩትን በትዕግስት እየሰማው ሳለ
በቃ እንሂድ ››በማለት አንዱ የመጡበትን ማጠናቀቃቸውን አበሰረን….››እፎይ ምንልበት ጊዜ ደረሰ.. ስል ተደሰትኩ
‹‹በል እናትዬውን እሰራት..አፎንም አሽገው››የሚል ደባሪ ድምጽ ወደጆሮዬ ገባ
‹‹ለምን አስፈለገ.…?.››ሌላው ጠየቀ
‹‹ትቀልዳለህ እንዴ ..ከዚህ ሳንወጣ ጩኸቷን ብትለቀውስ…?›› ስጋቱን ተናገረ
‹‹እናንተ ብቻ የያዛችሁትን ይዛችሁ በሰላም ውጡልኝ …በልጄ ምላለው ምንም አልጮህም››እናቴ ተማፀነቻቸው
አንደኛው‹‹ዝም በይ..›› ብሏት በምኑ እንደሆነ አላውቅም ከላይ ወገቧን ሲነርታት የህመሙ ስሜት ከስር ያለውትን እኔን ሳይቀር ተሰማኝ …
‹‹ና በል አንሳትና ከእዚህ የአልጋ እግር ጋር ጠፍንገህ እሰራት …ልጇንም እንደዛው….››ሲለውና ሌላው ትዕዛዙን ለማክበር እናቴን መንጭቆ ከላዬ ላይ ሲያነሳት ..የሆነ የማላውቀው ኃይል በሰውነቴ ሲሰራጭ ታወቀኝ
…እናቴ ‹‹ልጄን … ልጄን እንዳትነኩብኝ ››..እያለች ስትወራጭ…የድምፆ ቅጭልጭልታ ጆሮዬን እየነዘረ ወደጭንቅላቴ ሲሰርግ እና የሆነ የማላቀውቀው መንፈስ ሲቆጣጠረኝ አንድ ሆነ…..
ወደእኔ ከመምጣታቸው በፊት ተሸከራከርኩና በተቃራኒው በኩል ከአልጋው ተንከባልዬ ወረድኩ …… አዛዥ ቢጤው‹‹ልጁን ያዘው.. ልጁን ያዘው›› ሲል ይሰማኛል፡፡ አልጋውን ዞሮ ወደእኔ ከመምጣቱ በፊት ለእኔም ግልፅ ባልሆነልኝ የደመነፈስ ውሳኔ እና የእኔ ባልሆነ ፍጥነት የቁም ሳጥኑን መሳቢያ ስቤ ሽጉጥ አወጣውና ወዲያው መብራቱን በማብራት በኮማዲኖ በራፍ መላ አካሌን በመከለል ጭንቅላቴን ብቻ በከፊል ብቅ አድርጌ ሁኔታውን ቃኘው ….፡፡አዎ እንደገመትኩት ሶስት ናቸው፡፡ሁሉም ፊታቸው ላይ ጭንብል አጥልቀዋል፡፡ግን የጠበቅኮቸውን ያህል አስፈሪና ወጠምሻ አይነት አይደሉም…አንዱ የብረት ዱላ ሁለቱ ጩቤ ይዘዋል፡፡አንዱ በራፉ ጋ ቆሞ በቀኝ እጁ የያዘውን ባትሪ እኔ ወዳለውበት ቀስሯል፡፡ማብራቱን ካበራው ቡኃላ እንኳን አላጠፋውም..ሌላ እናቴን እያሰራት ነው..ሶስተኛው ሊይዘኝ ወደእኔ እየተንደረደርረ ነበር ..ሊያንቀኝ ሁለት ሜትር ያህል ብቻ ነበር የሚቀረው፡፡ከተሸሸኩበት ሳልወጣ ልክ ፊልም ላይ ደጋግሜ እንደማየው የያዝኩትን ሽጉጥ ቃቃ አድርጌ በማቀባበል እጄን ወደፊት በግንባሩ አቅጣጫ ቀስሬ ‹‹ ግንባርህን እንዳልፈረክሰው ባለህበት ቁም…››
ስለው ሳያቅማማ ደንዝዞ ትዛዜን አከበረ…እሱ ብቻ ሳይሆን ሶስቱም ያልጠበቁት ስላጋጠማቸው በሉበት ሲርበተበቱ በሰከንድ ሽርፍራፊ ቃኘው …ብዙም ልምድ የሌላቸው የመንደር ሌቦች መሆናቸውን ወዲያው ተረዳው፡፡
አናቴን እያሰራት ወደነበረው ሽጉጡን አዙሬ …‹‹እናቴን ልቀቃት…››ጮህኩበት …
ማሰሩን አቁሞ ቁጢጥ ካለበት በመነሳት ቀጥ ብሎ ቆመ…
ትዕዛዜን ቀጠልኩ ‹‹…አሁን አንድ ሰው ከመግደሌ በፊት እቃውን አስቀምጣችህ እቤቱን ለቃችሁ ውጡ ››
ተያዩና በምልክት በመነጋገር ወደኃላ መሳብ ጀመሩ…በራፍን ካለፉ ቡኃላ በሩጫ አስነኩት…
ከእውነተኛ ሽጉጥ ጋር በእጅ ካልያዙት በስተቀር ምንም ልዩነቱ የማይታወቀውን ልጅ ሆኜ የተገዛልኝን መጫወቻ ሽጉጥ መሬት ጥዬ ወደእናቴ ተንደረደርኩና አፎ ውስጥ የጠቀጠቀውን ጨርቅ ቀድሜ አውጥቼ በመጣል…. እጆቾን ልፈታ ስጣጣር እሷ እልልታዋን እስነካችው…
-እንዴ ምን እየሆነች ነው…?፡፡ግራ ገባኝ፡፡ ሰው እቤቱ ሌባ ሲገባበት ኡኡ ነው ማለት ያለበት ወይስ እልልል….…?
ወይ ድንጋጤ
- …እማ አይዞሽ ተራጋጊ …በማለት እጆን ፈትቼ ስጨርስ ተጠምጥማብኝ እያገላበጠች ትስመኝ ጀመረች
‹‹አደረከው..ልጄ አደረከው….አንድ ቀን እንዲህ እንደሚሆን አምን ነበር…እግዚያብሄር ሁሌም ካንተ ጋ ነው…አዎ አንተ ልዩ ነህ፡፡››
‹‹እማ ..አዎ ደርሼልሻለው … ከአሁን ወዲህ አይኔ እያየ ማንም ሊያጠቃሽና ሊያመናጭቅሽ አይችልም.. ማንም እንደዛ እንዲያደርግ አልፈቅድለትም…››ፎከርኩ
‹‹ እሱ አይደለም ልጄ …እሱ አይደለም..መናገር ቻልክ..ተናገርክ..እያወ
ራሀኝ ነው››ስትለኝ ድንግርግሬ ወጣ….እንዴ እያወራው ነው እንዴ ….…?.ከመገረሜ ሳልወጣ የእናቴን እልልታ የሰሙ የቤታችን ተከራዬች አያቴም ጭምር ከሚጣፍጥ የለሊት እንቅልፋቸው ተነስተው በመምጣት ወደቤታችን ሲንጋጉ ሰማን….
💫ይቀጥላል💫
የኛ ክፍያችን የናንተ ደስታ ነው ስሜታችሁን Like 👍👍 በማድረግ ግለፁልን
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍4
#የመልስ_ጉዞ_ወደ_መነሻ
:
#ክፍል_ዘጠኝ
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ከአስር አመት ቡኃላ ማለቴ አንደበቴ ከተፈታ ቡኃላ ያለኝ ህይወት ከዛ በፊት ከነበረው ፍጽም በተቃራኒ መንገድ የተጓዘ ነበር፡፡
በተለይ አንደበቴ እንዲፈታና እንድናገር ምክንያት የሆነው የቤታችን የመዘረፍ ሙከራ እና እኔ እራሴንም ሆነ እናቴን ከጥቃት የታደኩበት ሁኔታ ቅጽበታዊ የአንድ ቀን ክስተት ብቻ ሆኖ አላለፈም ፡፡የህይወቴን አቅጣጫና መላ አመለካከቴንም ሙሉ በሙሉ ነው የቀየረው፡፡
ሌቦቹ ልምድ ያላቸው ደፋርና ጨካኝ ቢሆኑ ኖሮ የዛን ለሊት እኔና እናቴ አልቆልን ነበር ማለት ነው፡፡ወይ ሞተን ወይ ደግሞ አካላ ጎዶሎ ሆነን ነበር፡፡ከዛ ታሪክ የተማርኩት በዚህ አለም ላይ አሸናፊ ሆኖ ለመኖር ብልህነት ብቻ ሳይሆን የአካል ጥንካሬም ወሰኝ እንደሆነ ነው፡፡
ብዙውን ጊዜ ምሉዕ እና ስኬታማ የሆኑ ሰዎች የአዕምሮአዊና እና የአካላዊ ጥንካሬያቸው ምርጥ በሚባል የብቃት ደረጃ የሚገኝ መሆኑን ታሪክ ይመሰክራል ፡፡ያ መሆኑ ሰዎቹ በሚጓዙበት በህይወት መስመር ላይ የፊት መሪ ሆነው ለመመረጣቸው ባይመረጡም እንኳን እራሳቸውን በራሳቸው መሪ አድርጎ ለመሾም እና ለዛም የሚደግፎቸው በርካታ ሰዎች በዙሪያቸው ማሰለፍ የመቻላቸው ሚስጥር የነፍስ ልህቀት ቅኝታቸው እና የአካል ጥንካሬ ብርታታቸው እኩል ዳብሮ መገኘቱ …በማድረግ ብቃታቸው ላይ ሆነ ሌላው ማህበረሰብ ላይ ተፅዕኖ የማሳደር ሚስጥራዊ ሀይል እንደሚያጎናጽፋቸው ገና በጥዋቱ በአስር አመቴ ተገለፀልኝ፡፡እና ሰፈራችን የሚገኝ ቴኮንደ ማሰልጠኛ ቤት መማር እንደምፈልግ ለእናቴ የነገርኮት ወዲያውኑ ነበር፡፡ለምን ፈለከው . ..?ምን ያደርግልሀል..? ምናምን ብላ ሳትጨቀጭቀኝ..ወዲያው የሚከፈለውን ከፍላ ወስዳ እስመዘገበቺኝ፡፡እናቴ የእኔ ጀግና ፡፡
ታዲያ የዛ ውጤት 15 ዓመት ሲሞላኝ ደረቴ ወደፊት የተገለበጠ…ሆዴ እንደብረት ጠጥሮ ወደ ውስጥ የተጠቀለለ…የእጆቼ ጡንቻዎች ፈርጣማ ..ተፈጥሮ ከለገሰኝ ዘለግ ያለ ቁመት ጋር የሀያ አመት ጓረምሳ አስመስለኝ፡፡በአካልም ሆነ በአዕምሮ ከእኩዬቼ አንፃር በጣም በሚባል ደረጃ ቀድሜ አደኩ፡፡ በዚህ ምክንያት ይሁን በተፈጥሮ ባለኝ መስህብ በእንስቶች የፍቅር እይታ ውስጥ በቀላሉ እገባለው፡፡ይቀርቡኛል …ሊፈትኑኝ፡፡ሸሻቸዋለው… እንዳይጥሉኝ ፡፡
ሌላው ትምህርቴን በተመለከተ በቀላል ልፋት አስደማሚ ውጤት ማምጣት ለእኔ የሚወዱትን አስደሳች የካርታ ጫወታ የመጫወትን ያህል ቀላል ሲሆን ለሌላው ተመልካች በተለይ በቀን ስንት ሰዓት እንደማጠና ..?ምን ስሰራ እንደምውል..? ለሚያውቁ ሰዎች እና ጓደኞቼ አስደማሚ እና ግራ አጋቢ ነበር፡፡
‹በልጅነቱ እናቱ አብሾ አግታው ነው ጎበዝ የሆነው ›ብለው ሚያሙኝ እኩዬቼም ሆኑ የሰፈር አዛውንቶች እንዳሉም አውቃለው፡፡
***
ሌላው ባህሪዬ ከትምህርት ጉብዝናዬ ጋር የማይሄድ የማፊያነት ባህሪ ይታይብኝ የጀመረው ገና በጥዋቱ ነበር፡፡መጀመሪያ በእኔ መሪነት የሚንቀሳቀሱ ሶስትና አራት ልጆችን በማስተባበር ጥቃት የሚደርስባቸውን የሰፈር እና ሌሎች የማቀቸውን ሰዎች ከጥቃት በመከላከል ነበር የጀመርኩት፡፡እያደር ግን በትምህርት ቤቱ ስውር መንግስት ሆንኩ፡፡እኔ ያወጣውትን ህግ እንኳን ተማሪዎች አስተማሪዎች ወደውም ሆነ ፈርተው ይተገብሩታል፡፡
ግን ጉልበት አለኝ ብዬ በመታበይ ከመሬት ተነስቼ ሰውን አልጋጭም፡፡በማንም ላይ ከአስፈላጊው በላይ ጉልበትም ሆነ ጫና አልፈፅምም ፡፡ግን ተገቢውን እርምጃ በተገቢው ጊዜና መጠን ለመውሰድ ሰውዬው ማንም ይሁን ማንም አልፈረምም …ላቅማማምም፡፡
ኃይልን በተመለከተ አንድ ምክር ልስጣችሁ ፡፡የሆነ ስልጣን አለኝ ወይም አስተማማኝ ጉልብት አለኝ ብላችሁ ማንኛውንም የመጨረሻ ደካማ ነው የምትሉትን ሰውም ላይ ቢሆን የመጨረሻ ውን ተስፋ እስኪቆርጥ ድረስ አትቅጡትም … አትግፉትም ፡፡..ያንን ካደረጋቹ የራሳችሁን ጉድጓድ እየቆፈራችሁ መሆኑን እወቁት ፡፡ተስፋ የቆረጠ ድመት የነብር አንገት መቀንጠስ ቢያቅተው እንኳን የነብርን አይን ለማጥፋ አይሰንፍም፡፡
እና ምን ጊዜም ይሄ የሀይል አጠቃቀም ለእኔ መመሪያዬ ነው፡፡ያሸነፍኩትን በምን ያህል መጠን መቅጣትና መቼ ይቅር ማለት እንዳብኝ በጥንቃቄ አስብበታለው፡፡
ያው የትምህርት ቤቱ ስውር መንግስት ነኝ ብያችሁ የለ፡፡መጀመሪያ በዘፈቀደ ነበር ነገሮችን የምከውን የነበረው፡፡ዋናው ትኩረቴ የሆነ ታዛዥ ጦር ከኃላዬ ማሰለፌ እና በሚያውቁኝም (እጄን በቀመሱትም) ወይም በዝና ብቻ በሰሙትም ዘንድ መፈራቴ እና መከበሬ ነበር፡፡
በነገራችን ላይ በሄድኩበት ሁሉ የመከበርና እና የመደመጥ ሱስ አለብኝ፡፡ማንም ቢሆን በእድሜ እኩያዬ ይሁን ወይም ታላቄ ትኩረት እንዲነፍገኝ ወይም ዝቅ አድርጎ እንዲያኝ ፈጽሞ አልፈቅድም፡፡ሲያከብሩኝ ደስ ይለኛል፡፡አዎ ማንኛውም ሰው ከቻለ እየወደደ ቢያከብረኝ ደስ ይለኛል ካልሆነ ግን እየጠላኝም ቢሆን እንዲፈራኝና እንዲያከብረኝ ፈልጋለው፡፡በሚወዱኝም ሆነ በሚጠሉኝ ሰዎች እኩል መፈራትና መከበር ፍላጎቴ ነው፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
:
#ክፍል_ዘጠኝ
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ከአስር አመት ቡኃላ ማለቴ አንደበቴ ከተፈታ ቡኃላ ያለኝ ህይወት ከዛ በፊት ከነበረው ፍጽም በተቃራኒ መንገድ የተጓዘ ነበር፡፡
በተለይ አንደበቴ እንዲፈታና እንድናገር ምክንያት የሆነው የቤታችን የመዘረፍ ሙከራ እና እኔ እራሴንም ሆነ እናቴን ከጥቃት የታደኩበት ሁኔታ ቅጽበታዊ የአንድ ቀን ክስተት ብቻ ሆኖ አላለፈም ፡፡የህይወቴን አቅጣጫና መላ አመለካከቴንም ሙሉ በሙሉ ነው የቀየረው፡፡
ሌቦቹ ልምድ ያላቸው ደፋርና ጨካኝ ቢሆኑ ኖሮ የዛን ለሊት እኔና እናቴ አልቆልን ነበር ማለት ነው፡፡ወይ ሞተን ወይ ደግሞ አካላ ጎዶሎ ሆነን ነበር፡፡ከዛ ታሪክ የተማርኩት በዚህ አለም ላይ አሸናፊ ሆኖ ለመኖር ብልህነት ብቻ ሳይሆን የአካል ጥንካሬም ወሰኝ እንደሆነ ነው፡፡
ብዙውን ጊዜ ምሉዕ እና ስኬታማ የሆኑ ሰዎች የአዕምሮአዊና እና የአካላዊ ጥንካሬያቸው ምርጥ በሚባል የብቃት ደረጃ የሚገኝ መሆኑን ታሪክ ይመሰክራል ፡፡ያ መሆኑ ሰዎቹ በሚጓዙበት በህይወት መስመር ላይ የፊት መሪ ሆነው ለመመረጣቸው ባይመረጡም እንኳን እራሳቸውን በራሳቸው መሪ አድርጎ ለመሾም እና ለዛም የሚደግፎቸው በርካታ ሰዎች በዙሪያቸው ማሰለፍ የመቻላቸው ሚስጥር የነፍስ ልህቀት ቅኝታቸው እና የአካል ጥንካሬ ብርታታቸው እኩል ዳብሮ መገኘቱ …በማድረግ ብቃታቸው ላይ ሆነ ሌላው ማህበረሰብ ላይ ተፅዕኖ የማሳደር ሚስጥራዊ ሀይል እንደሚያጎናጽፋቸው ገና በጥዋቱ በአስር አመቴ ተገለፀልኝ፡፡እና ሰፈራችን የሚገኝ ቴኮንደ ማሰልጠኛ ቤት መማር እንደምፈልግ ለእናቴ የነገርኮት ወዲያውኑ ነበር፡፡ለምን ፈለከው . ..?ምን ያደርግልሀል..? ምናምን ብላ ሳትጨቀጭቀኝ..ወዲያው የሚከፈለውን ከፍላ ወስዳ እስመዘገበቺኝ፡፡እናቴ የእኔ ጀግና ፡፡
ታዲያ የዛ ውጤት 15 ዓመት ሲሞላኝ ደረቴ ወደፊት የተገለበጠ…ሆዴ እንደብረት ጠጥሮ ወደ ውስጥ የተጠቀለለ…የእጆቼ ጡንቻዎች ፈርጣማ ..ተፈጥሮ ከለገሰኝ ዘለግ ያለ ቁመት ጋር የሀያ አመት ጓረምሳ አስመስለኝ፡፡በአካልም ሆነ በአዕምሮ ከእኩዬቼ አንፃር በጣም በሚባል ደረጃ ቀድሜ አደኩ፡፡ በዚህ ምክንያት ይሁን በተፈጥሮ ባለኝ መስህብ በእንስቶች የፍቅር እይታ ውስጥ በቀላሉ እገባለው፡፡ይቀርቡኛል …ሊፈትኑኝ፡፡ሸሻቸዋለው… እንዳይጥሉኝ ፡፡
ሌላው ትምህርቴን በተመለከተ በቀላል ልፋት አስደማሚ ውጤት ማምጣት ለእኔ የሚወዱትን አስደሳች የካርታ ጫወታ የመጫወትን ያህል ቀላል ሲሆን ለሌላው ተመልካች በተለይ በቀን ስንት ሰዓት እንደማጠና ..?ምን ስሰራ እንደምውል..? ለሚያውቁ ሰዎች እና ጓደኞቼ አስደማሚ እና ግራ አጋቢ ነበር፡፡
‹በልጅነቱ እናቱ አብሾ አግታው ነው ጎበዝ የሆነው ›ብለው ሚያሙኝ እኩዬቼም ሆኑ የሰፈር አዛውንቶች እንዳሉም አውቃለው፡፡
***
ሌላው ባህሪዬ ከትምህርት ጉብዝናዬ ጋር የማይሄድ የማፊያነት ባህሪ ይታይብኝ የጀመረው ገና በጥዋቱ ነበር፡፡መጀመሪያ በእኔ መሪነት የሚንቀሳቀሱ ሶስትና አራት ልጆችን በማስተባበር ጥቃት የሚደርስባቸውን የሰፈር እና ሌሎች የማቀቸውን ሰዎች ከጥቃት በመከላከል ነበር የጀመርኩት፡፡እያደር ግን በትምህርት ቤቱ ስውር መንግስት ሆንኩ፡፡እኔ ያወጣውትን ህግ እንኳን ተማሪዎች አስተማሪዎች ወደውም ሆነ ፈርተው ይተገብሩታል፡፡
ግን ጉልበት አለኝ ብዬ በመታበይ ከመሬት ተነስቼ ሰውን አልጋጭም፡፡በማንም ላይ ከአስፈላጊው በላይ ጉልበትም ሆነ ጫና አልፈፅምም ፡፡ግን ተገቢውን እርምጃ በተገቢው ጊዜና መጠን ለመውሰድ ሰውዬው ማንም ይሁን ማንም አልፈረምም …ላቅማማምም፡፡
ኃይልን በተመለከተ አንድ ምክር ልስጣችሁ ፡፡የሆነ ስልጣን አለኝ ወይም አስተማማኝ ጉልብት አለኝ ብላችሁ ማንኛውንም የመጨረሻ ደካማ ነው የምትሉትን ሰውም ላይ ቢሆን የመጨረሻ ውን ተስፋ እስኪቆርጥ ድረስ አትቅጡትም … አትግፉትም ፡፡..ያንን ካደረጋቹ የራሳችሁን ጉድጓድ እየቆፈራችሁ መሆኑን እወቁት ፡፡ተስፋ የቆረጠ ድመት የነብር አንገት መቀንጠስ ቢያቅተው እንኳን የነብርን አይን ለማጥፋ አይሰንፍም፡፡
እና ምን ጊዜም ይሄ የሀይል አጠቃቀም ለእኔ መመሪያዬ ነው፡፡ያሸነፍኩትን በምን ያህል መጠን መቅጣትና መቼ ይቅር ማለት እንዳብኝ በጥንቃቄ አስብበታለው፡፡
ያው የትምህርት ቤቱ ስውር መንግስት ነኝ ብያችሁ የለ፡፡መጀመሪያ በዘፈቀደ ነበር ነገሮችን የምከውን የነበረው፡፡ዋናው ትኩረቴ የሆነ ታዛዥ ጦር ከኃላዬ ማሰለፌ እና በሚያውቁኝም (እጄን በቀመሱትም) ወይም በዝና ብቻ በሰሙትም ዘንድ መፈራቴ እና መከበሬ ነበር፡፡
በነገራችን ላይ በሄድኩበት ሁሉ የመከበርና እና የመደመጥ ሱስ አለብኝ፡፡ማንም ቢሆን በእድሜ እኩያዬ ይሁን ወይም ታላቄ ትኩረት እንዲነፍገኝ ወይም ዝቅ አድርጎ እንዲያኝ ፈጽሞ አልፈቅድም፡፡ሲያከብሩኝ ደስ ይለኛል፡፡አዎ ማንኛውም ሰው ከቻለ እየወደደ ቢያከብረኝ ደስ ይለኛል ካልሆነ ግን እየጠላኝም ቢሆን እንዲፈራኝና እንዲያከብረኝ ፈልጋለው፡፡በሚወዱኝም ሆነ በሚጠሉኝ ሰዎች እኩል መፈራትና መከበር ፍላጎቴ ነው፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
#የመልስ_ጉዞ_ወደ_መነሻ
:
#ክፍል_አስር
:
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
...አደኩ፡፡ጎረመስኩ፡፡ጉንጬ ላይ ብጉር አገጬ ላይ ፀጉር አበቀልኩ፡፡ያንንም ተከትሎ
➶➶➶
ፍቅሬ አስትንፋስህ ህይወቴ ነው፡፡ያንተ መኖር ደግሞ ለእኔ ብቸኛ የመኖር ዓላማዬ፡፡አንተ ፀሀዬ ነህ፡፡ እንጦጦ ተራራ ላይ በበቀለ አረንጎዴ ሳር ላይ በጀርባ ተንጋለው ከጥዋት ሦስት ሰዓት አካባቢ የሚሞቋት ሰውነትን የምታፍታታ፤አዕምሮን የምታነቃቃ፤የቆዳን ቀለም የምታፈካ ምጥን የእግዜር ፀሀይ፡፡ አዎ አንተ እንደዛ ነህ፡፡ሙሉ ፀሀይ ከእነግለቷ፤ ሙሉ ፀሀይ ከነኩነቷ ፡፡ከአንተ ሙቀት ተሸርፎ አኔ ጋር የሚደርሰው ሙቀት ፍፅም ያኖረኛል…ፍፅም ያፈካኛል፡፡
እንደእኔው ፈገግታህን ለማድነቅና ከዛም አለፍ ሲል በሙቀትህ ለመቅለጥ በመፈለግ በየእለቱ በዙሪያህ ሲያንዣብቡ የሚውሉ የትምህርት ቤታችን ቆነጃጅቶች እንዳሉ አውቃለው፡፡ግን ደግሞ አንዳቸውም በእኔ መጠን ውብ እንዳልሆኑ በእኔ መጠንም አንተን አንደማያፈቅሩ በእርግጠኝነት አውቃለው፡፡ባውቅም ዳሩ ተረጋግቼ መቀመጥ አልቻልኩም ፡፡..ልቤ በቅናት ያራል….ውስጤ እርብሽብሽ ይላል፡፡አንዳንዴ የሆነ ሽጉጥ ፈልጌ በእየእለቱ አንትን በሙሉ አይኗ ለማየት የምትደፍርን ማንኛዋንም ልጅ-አገረድ ግንባሯን ብቀነድባት ደስታዬ ነው፡፡ግን ያንንነ ለማድረግ ችሎታውም ሆነ ድፍረቱ ለጊዜው የለኝም፡፡በቅርብ ግን አምላክ ኃይሉን እንደሚያጎናፅፈኝ አምናለው..እናም የዛን ጊዜ አደርገዋለው፡፡ለአንተ ስል ከተማ አቃጥላለው፤ ለአንተ ስል ሺ ሰው ገድላለው…ለአንተ ስል እራሴን ከ20 ኛው ፎቅ ላይ ልወረውርም ችላለው…ለአንተ ስል የማላደርገወ ነገረ የለም…አስፈላጊ ከሆነ ለአንተ ስል አንተ ራስህንም መግደል ችላለው፡፡
ጊዜው ደርሷ ሁሉን ማድረግ እስክችል ግን አንተን የመጠበቅ አደራውን ለአንተው ለራስህ ሰጥቼያለው፡፡ የእኔ ጀግና ሴቶችን በተመለከተህ ባለህ አቋም ታኮራኛለህ እናም በዚሁ ቀጥል፡፡ ለአንዳቸውም ፊት አትስጣቸው፤ለአንዷም የልብህን ወርቃማ በር አትክፈትላት…የትኛዋም ብትሆን በብሩህ አይኖችህ አይታ ውስጥ አትግባ…ክንዶችህ የማንኛዋንም ወገብ ለማቀፍ አይሞክሩ …ወለላ ማር የሚንጠባጠብባቸው ሚመስሉ ከንፈሮችህ የማንኛዋም ቆርፋዳ ከንፈር ላይ አይረፍ …ቅዱስ ትንፋሽህን የትኛዋም ሄዋን ከእራሷ ሙትና ደካማ ትንፋሽ ጋር ቀይጣ ወደውስጦ ለመሳብ እድል አታግኝ ፡፡…በማንም ሴት ቀልድ ጥርሶችህ ተፈልቅቀው ፈገግታህ እንዳይረጭ…፡፡ለአንተ የምገባህ እኔ ነኝ..ከጎንህ አጥንት ተፈልቅቄ የተፈጠርኩ ሄዋንህ…ብትረግጠኝ ማይቆረቁረኝ፤ ብትገለኝ ቂም ማሊዝብ፡፡ብታቅፈኝ ማልጎረብጥህ ብትሰመኝ የማስደስትህ፡፡እኔ ለአንተ ጌጥህ እኔ ለአንተ ክብርህ ነኝ …፡፡በፈለከው ደቂቃ ጥራኝ በርሬ ወዲያው መጣለው፡፡ያሰኘህ ቦታ ቅጠረኝ ሲኦልም ቢሆን እገኛለው፡፡ ………..
***
ይሄ አስራ አምስት አመትና የዘጠነኛ ክፍል ተማሪ እያለው ከክፍሌ ልጅ የተፃፈልኝ የመጀመሪያው የፍቅር ደብዳቤዬ ነው፡፡ከዛ ቡኃላ ያለውን የአፍላነት የፍቅር መሳሳቡንና የስሜት መላተሙን አትጠይቁኝ ፡፡ ይሄንን ለእናንተ እንደምሳሌ መናገር የፈለኩት እያደኩ ስመጣ ምን ያህል ማራኪ ወንዳ ወንድ እና ተፈቃሪ ወጣት መሆኔን እንድትገዘቡልኝ ስለፈለኩ ነው።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
:
#ክፍል_አስር
:
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
...አደኩ፡፡ጎረመስኩ፡፡ጉንጬ ላይ ብጉር አገጬ ላይ ፀጉር አበቀልኩ፡፡ያንንም ተከትሎ
➶➶➶
ፍቅሬ አስትንፋስህ ህይወቴ ነው፡፡ያንተ መኖር ደግሞ ለእኔ ብቸኛ የመኖር ዓላማዬ፡፡አንተ ፀሀዬ ነህ፡፡ እንጦጦ ተራራ ላይ በበቀለ አረንጎዴ ሳር ላይ በጀርባ ተንጋለው ከጥዋት ሦስት ሰዓት አካባቢ የሚሞቋት ሰውነትን የምታፍታታ፤አዕምሮን የምታነቃቃ፤የቆዳን ቀለም የምታፈካ ምጥን የእግዜር ፀሀይ፡፡ አዎ አንተ እንደዛ ነህ፡፡ሙሉ ፀሀይ ከእነግለቷ፤ ሙሉ ፀሀይ ከነኩነቷ ፡፡ከአንተ ሙቀት ተሸርፎ አኔ ጋር የሚደርሰው ሙቀት ፍፅም ያኖረኛል…ፍፅም ያፈካኛል፡፡
እንደእኔው ፈገግታህን ለማድነቅና ከዛም አለፍ ሲል በሙቀትህ ለመቅለጥ በመፈለግ በየእለቱ በዙሪያህ ሲያንዣብቡ የሚውሉ የትምህርት ቤታችን ቆነጃጅቶች እንዳሉ አውቃለው፡፡ግን ደግሞ አንዳቸውም በእኔ መጠን ውብ እንዳልሆኑ በእኔ መጠንም አንተን አንደማያፈቅሩ በእርግጠኝነት አውቃለው፡፡ባውቅም ዳሩ ተረጋግቼ መቀመጥ አልቻልኩም ፡፡..ልቤ በቅናት ያራል….ውስጤ እርብሽብሽ ይላል፡፡አንዳንዴ የሆነ ሽጉጥ ፈልጌ በእየእለቱ አንትን በሙሉ አይኗ ለማየት የምትደፍርን ማንኛዋንም ልጅ-አገረድ ግንባሯን ብቀነድባት ደስታዬ ነው፡፡ግን ያንንነ ለማድረግ ችሎታውም ሆነ ድፍረቱ ለጊዜው የለኝም፡፡በቅርብ ግን አምላክ ኃይሉን እንደሚያጎናፅፈኝ አምናለው..እናም የዛን ጊዜ አደርገዋለው፡፡ለአንተ ስል ከተማ አቃጥላለው፤ ለአንተ ስል ሺ ሰው ገድላለው…ለአንተ ስል እራሴን ከ20 ኛው ፎቅ ላይ ልወረውርም ችላለው…ለአንተ ስል የማላደርገወ ነገረ የለም…አስፈላጊ ከሆነ ለአንተ ስል አንተ ራስህንም መግደል ችላለው፡፡
ጊዜው ደርሷ ሁሉን ማድረግ እስክችል ግን አንተን የመጠበቅ አደራውን ለአንተው ለራስህ ሰጥቼያለው፡፡ የእኔ ጀግና ሴቶችን በተመለከተህ ባለህ አቋም ታኮራኛለህ እናም በዚሁ ቀጥል፡፡ ለአንዳቸውም ፊት አትስጣቸው፤ለአንዷም የልብህን ወርቃማ በር አትክፈትላት…የትኛዋም ብትሆን በብሩህ አይኖችህ አይታ ውስጥ አትግባ…ክንዶችህ የማንኛዋንም ወገብ ለማቀፍ አይሞክሩ …ወለላ ማር የሚንጠባጠብባቸው ሚመስሉ ከንፈሮችህ የማንኛዋም ቆርፋዳ ከንፈር ላይ አይረፍ …ቅዱስ ትንፋሽህን የትኛዋም ሄዋን ከእራሷ ሙትና ደካማ ትንፋሽ ጋር ቀይጣ ወደውስጦ ለመሳብ እድል አታግኝ ፡፡…በማንም ሴት ቀልድ ጥርሶችህ ተፈልቅቀው ፈገግታህ እንዳይረጭ…፡፡ለአንተ የምገባህ እኔ ነኝ..ከጎንህ አጥንት ተፈልቅቄ የተፈጠርኩ ሄዋንህ…ብትረግጠኝ ማይቆረቁረኝ፤ ብትገለኝ ቂም ማሊዝብ፡፡ብታቅፈኝ ማልጎረብጥህ ብትሰመኝ የማስደስትህ፡፡እኔ ለአንተ ጌጥህ እኔ ለአንተ ክብርህ ነኝ …፡፡በፈለከው ደቂቃ ጥራኝ በርሬ ወዲያው መጣለው፡፡ያሰኘህ ቦታ ቅጠረኝ ሲኦልም ቢሆን እገኛለው፡፡ ………..
***
ይሄ አስራ አምስት አመትና የዘጠነኛ ክፍል ተማሪ እያለው ከክፍሌ ልጅ የተፃፈልኝ የመጀመሪያው የፍቅር ደብዳቤዬ ነው፡፡ከዛ ቡኃላ ያለውን የአፍላነት የፍቅር መሳሳቡንና የስሜት መላተሙን አትጠይቁኝ ፡፡ ይሄንን ለእናንተ እንደምሳሌ መናገር የፈለኩት እያደኩ ስመጣ ምን ያህል ማራኪ ወንዳ ወንድ እና ተፈቃሪ ወጣት መሆኔን እንድትገዘቡልኝ ስለፈለኩ ነው።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍4
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ_ጉዞ
:
#ክፍል_አስራ_አንድ
:
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
...18 ዓመት ወጣትና የ12 ክፍል ተማሪ ሆኜ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችለኝን ማትሪክ ፈተና ዝግጅት ላይ እያለው አስቀያሚ ነገር ተከሰተ፡፡አስቀያሚ ስላችሁ የመጨረሻ አስቀያሚ ማለቴ ነው፡፡ትምህርት ቤት ክፍል ውስጥ ቁጭ ብዬ በማማር ላይ ሳለው በስልኬ መልዕክት መጣ ፡፡ሳየው ከአያቴ ነው፡፡ያልተለመደ ነገር ነው፡፡የሚያስተምረውን አስተማሪ ትኩረት እንዳልስብ እየተጠነቀኩ ከፈትኩና አነብኩት….ደብተሬን እንኳን አልሰበሰብኩም፡፡ ተስፈንጥሬ ከመቀመጫዬ ተነሳው ፡፡ የክፍሉ ተማሪ አይን ከአስተማሪው ተነቅሎ ወደእኔ አነጣጠረ..አስተማሪው ማስተማሩን አቋርጦ ምን እንደሆንኩ መጠቅ ጀመረ …እየተንደረደርኩ ክፍሉን ለቅቄ ወጣው፡፡ሳይክል ሚጠቀሙ ተማሪዎች ሳይክላቸውን ወደሚያቆሙበት ስፋራ ነው የሮጥኩት፡፡ከመካከሉ ቁልፉ ያልተቆለፈውን አዋጣውና እየጋለብኩ ግቢወን ለቅቄ ወጣው፡፡ ሳይክሉ የማን እንደሆነ አላውቅም ግድም አልነበረኝም..
ሆስፒታል እንደደረስኩ ሳይኩል ወረድኩና ከመንገድ ዳር አጋድሜ ወደውስጥ ሮጥኩ… ኮሪደር ለኮሪደር እየተሸከረከርኩ አያቴን ወይንም ሌላ የማውቀው ሰው መፈለግ ጀመርኩ...አዎ አያቴን አገኘውት
-እናቴ የታለች …?እናቴ ምን ሆነች…??እማ!!
ተረጋጋ…ምን እንደሆነች አናውቅም…ድንገት ነው እራሷን የሳተችው ፡፡እያከሟት ነው፡፡ይውጡና ሚሉትን እንሰማለን፡፡››አለኝ አያቴ በሚርበተበት ድምፅ..
‹‹እራሴን መቆጣጠር አቃተኝ፡፡‹‹ቆይ አያቴ እንደዚህ አይነት ነገር እንዴት ይፈጠራል …?እናቴ ፍጽም ጤነኛ ነበረች፡፡እንኳን እራስ መሳት ይቅርና እራሷንም ሲያማት አይቼ አላውቅም ፡፡››
‹‹ለእኔም አንቆቅልሽ ነው የሆነብኝ ልጄ››አየቴ መለሰልኝ
ንግግሬን ሳልጨርስ እናቴ ስትታከምበት ከነበረው ክፍል አንድ ዶክተር ወጣ… ተንደርድረን ከበብነው፡፡ዶክተሩ እኔንና አያቴን ወደቢሮ ይዞን ሄደ፡፡ ካዘነው በላይ የሚያሳዝን …ከደነገጥነው በላይ የሚያስደነግጥ መርዶ ነገረን፡፡
‹‹የሚቀጥሉትን ሶስት ቀን እዚህ ትቆይና …ከዛ ትወስዶታላችሁ››
‹‹ተመስገን›› አለ አያቴ …ረጅም ግን ደግሞ ደካማ ትንፋሽ ተንፍሶ፡፡
‹‹ዶ/ር በሶስት ቀን ይሻላታል ማለት ነው…?››ጠየቅኩት በመፍለቅለቅ ….ለማረጋገጥ፡፡
ዶክተሩ አንገቱን እንደመድፋት አለና የተወሰነ አየር ወደውስጡ ስቦ ጭንቀት በሚለቅ ድምጽ ‹‹አዝናለው ..ይሻላታል ብዬ ተስፋ ልሰጣችሁ ብችል ደስ ይለኝ ነበር…ግን እሷን የማዳኑ ጉዳይ ረፍዶብናል››
‹‹ማለት …?››
እቤት ወስዳችሁ ያላትን ቀሪ አንድ ወርም ሆነ ሁለት ወር በደስታ አሳልፋ …በሰላም እንድታርፍ ከማድረግ ውጭ ሌላ ምርጫ የላችሁም፡፡››አለ የመለማመጥ ቃና ባለው ድምፀት፡፡
ከመቀመጫዬ ተንሳፍፌ ተነሳውና የሸሚዝኑን የጋወኑን ኮሌታ አንድ ላይ ጨምድጄ ከተቀመጠበት አንጠልጥዬ አስነሳውትና በአየር ላይ አንሳፍኩት…ሰውዬው አይኑ ተጉረጠረጠ..እጆቹን እንድለቀው ማወራጨቱን ቀጠለ
አያቴም ከድንዛዜው እንደምንም ባኖ ይለምነኝ ጀመር
‹‹ልጄ ምን እየሰራህ ነው..…?ሰውዬውን ልቀቀው..…?ልጄ የሰው ሰው እንዳትገል፡፡››
‹‹እናቴን ታድናታለህ አታድናትም.…?››አርገፍግፌ መሬት አድርሼ ለቀቅኩት
ዶክተሩ ጉሮሮውን በእጆቹ እየዳበሰ ደጋግሞ ካሳለ ቡኃላ‹‹.አዝናለው አልችልም…ማንም ሊያድናት አይችልም….››ብሎ ስለበሽታዋ አይነትና ከባድነት የደረሰበትን ደረጃ በተቆራረጠ ቃላት ይዘረዝርልን ቀጠለ.
በእናቴ ስም እምላለው…ከሞተች አገድልሀለው..አንተን ብቻ ሳይሆን ጠቅላላ እዚህ ግቢ ውስጥ ያላችሁትን ሀኪሞች ጨርሳችሆለው …ሆስፒታሉንም አቃጥለዋለው፡፡አረ ከተማወናም ነው የማቃጥለው…››በማለት ቢሮውን ጥዬ ወጣውና እናቴ ወደተኛችበት ክፍል ተንደረደርኩ ፡፡በራፍ ላይ የቆመችውን ነርስ ገፍቼ ፍቃዷንም ሳልጠይቅ ወደውስጥ ገባው፡፡እማዬ ዝርር ብላ ተሰትራ የሆስፒታሉ አልጋ ላይ ተኝታለች፡፡አይኖቾ ተከድነዋል፡፡ትንፋሿም አይሰማም ፡፡በሁለቱ አፍንጫጮ ቀዳዳ ቱቦ በክንዶቾ የግሉኮስ ላስቲክ ተሰክቶል፡፡
በራስጌዋ ሄድኩና ወለሉ ላይ ዝርፍጥ ብዬ ግንባሬን አልጋዋ ላይ ደፍቼ ወደ ፊቷ ተጠግቼ አስደገፍኩና በሹክሹክታ አወራት ጀመር….
ማሂ ምን እየሰራሽ ነው…?፡፡ምንድነው ዶክቱሩ የሚቀባጥረው…?፡፡ጥላህ ልትሄድ ነው እያለኝ ነው፡፡ስለማያውቅሽ ነው የሚቀባጥረው ፡፡አንቺ መቼም መቼም እኔን ጥለሽ መሄድ እንደማትችይ ስለማያውቅ ነው፡፡ገነትም ቢሆን እኔ ከሌለው መኖር እንደማትችይ ስለማውቅ ነው፡፡ማሂ ከተወለድኩበት ቀን አንስቶ ስትበይ እንብላ ብለሺኝ ስትተኚ እንተኛ ብለሺኝ ፤ስትተነፍሺ እንኳን የእኔንም መተንፈስ አረጋግጠሸ ነበር…ታዲያ ዶክተሮቹ እንደሚሊት አሁን ልትሞቺ ከሆነ እንዴት ልንሞት ነወ ተዘጋጅ ሳትይኝ .. …?ነገሩ ተይው እውነት ዶክተሩ አንዳለው ሸውደሺን ለመሞት የተዘጋጀሽ ከሆነም ግድ የለም እኔ ዝግጅት አያስፈልገኝም፡፡
ንግግሬን ከጀርባዬ ሆኖ ሲያዳምጥ የቆየው አያቴ በሽማግሌ አንጀቱ እየተንሰቀሰቀ በማልቀስ ዝቅ ብሎ አስነሳኝና
‹‹ተው ልጄ ተረጋጋ…አይዞህ እግዜር አለ ያድንልናል፡፡››
እንግዲህ እግዚያብሄር አለ የምትል ከሆነ በምትግባቡበት ቋንቋ ንገረው…ተው የሰው እናት አትንጠቅ በለው…እሷን አጥቶ መኖር አይችልም በለው…ከሰማህ ጥሩ ነው ፡፡ ካልሰማህ ደግሞ እኔንም ተሰናበተኝ ፡፡ እናም ከእናቴ ጋር በአንድ ጉድጓድ መቀበር ነው የምፈልገው..እንዳትረሳ በአንድ ጉድጓድ ፡፡ይህ ኑዛዜዬ ነው፡፡››ብዬው ጥዬው ወጣው ፡፡ወደየት እንደምሄድ ባላውቅም የሆስፒታሉን ቅጥር ጊቢ ለቅቄ ወጣው….
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
:
#ክፍል_አስራ_አንድ
:
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
...18 ዓመት ወጣትና የ12 ክፍል ተማሪ ሆኜ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችለኝን ማትሪክ ፈተና ዝግጅት ላይ እያለው አስቀያሚ ነገር ተከሰተ፡፡አስቀያሚ ስላችሁ የመጨረሻ አስቀያሚ ማለቴ ነው፡፡ትምህርት ቤት ክፍል ውስጥ ቁጭ ብዬ በማማር ላይ ሳለው በስልኬ መልዕክት መጣ ፡፡ሳየው ከአያቴ ነው፡፡ያልተለመደ ነገር ነው፡፡የሚያስተምረውን አስተማሪ ትኩረት እንዳልስብ እየተጠነቀኩ ከፈትኩና አነብኩት….ደብተሬን እንኳን አልሰበሰብኩም፡፡ ተስፈንጥሬ ከመቀመጫዬ ተነሳው ፡፡ የክፍሉ ተማሪ አይን ከአስተማሪው ተነቅሎ ወደእኔ አነጣጠረ..አስተማሪው ማስተማሩን አቋርጦ ምን እንደሆንኩ መጠቅ ጀመረ …እየተንደረደርኩ ክፍሉን ለቅቄ ወጣው፡፡ሳይክል ሚጠቀሙ ተማሪዎች ሳይክላቸውን ወደሚያቆሙበት ስፋራ ነው የሮጥኩት፡፡ከመካከሉ ቁልፉ ያልተቆለፈውን አዋጣውና እየጋለብኩ ግቢወን ለቅቄ ወጣው፡፡ ሳይክሉ የማን እንደሆነ አላውቅም ግድም አልነበረኝም..
ሆስፒታል እንደደረስኩ ሳይኩል ወረድኩና ከመንገድ ዳር አጋድሜ ወደውስጥ ሮጥኩ… ኮሪደር ለኮሪደር እየተሸከረከርኩ አያቴን ወይንም ሌላ የማውቀው ሰው መፈለግ ጀመርኩ...አዎ አያቴን አገኘውት
-እናቴ የታለች …?እናቴ ምን ሆነች…??እማ!!
ተረጋጋ…ምን እንደሆነች አናውቅም…ድንገት ነው እራሷን የሳተችው ፡፡እያከሟት ነው፡፡ይውጡና ሚሉትን እንሰማለን፡፡››አለኝ አያቴ በሚርበተበት ድምፅ..
‹‹እራሴን መቆጣጠር አቃተኝ፡፡‹‹ቆይ አያቴ እንደዚህ አይነት ነገር እንዴት ይፈጠራል …?እናቴ ፍጽም ጤነኛ ነበረች፡፡እንኳን እራስ መሳት ይቅርና እራሷንም ሲያማት አይቼ አላውቅም ፡፡››
‹‹ለእኔም አንቆቅልሽ ነው የሆነብኝ ልጄ››አየቴ መለሰልኝ
ንግግሬን ሳልጨርስ እናቴ ስትታከምበት ከነበረው ክፍል አንድ ዶክተር ወጣ… ተንደርድረን ከበብነው፡፡ዶክተሩ እኔንና አያቴን ወደቢሮ ይዞን ሄደ፡፡ ካዘነው በላይ የሚያሳዝን …ከደነገጥነው በላይ የሚያስደነግጥ መርዶ ነገረን፡፡
‹‹የሚቀጥሉትን ሶስት ቀን እዚህ ትቆይና …ከዛ ትወስዶታላችሁ››
‹‹ተመስገን›› አለ አያቴ …ረጅም ግን ደግሞ ደካማ ትንፋሽ ተንፍሶ፡፡
‹‹ዶ/ር በሶስት ቀን ይሻላታል ማለት ነው…?››ጠየቅኩት በመፍለቅለቅ ….ለማረጋገጥ፡፡
ዶክተሩ አንገቱን እንደመድፋት አለና የተወሰነ አየር ወደውስጡ ስቦ ጭንቀት በሚለቅ ድምጽ ‹‹አዝናለው ..ይሻላታል ብዬ ተስፋ ልሰጣችሁ ብችል ደስ ይለኝ ነበር…ግን እሷን የማዳኑ ጉዳይ ረፍዶብናል››
‹‹ማለት …?››
እቤት ወስዳችሁ ያላትን ቀሪ አንድ ወርም ሆነ ሁለት ወር በደስታ አሳልፋ …በሰላም እንድታርፍ ከማድረግ ውጭ ሌላ ምርጫ የላችሁም፡፡››አለ የመለማመጥ ቃና ባለው ድምፀት፡፡
ከመቀመጫዬ ተንሳፍፌ ተነሳውና የሸሚዝኑን የጋወኑን ኮሌታ አንድ ላይ ጨምድጄ ከተቀመጠበት አንጠልጥዬ አስነሳውትና በአየር ላይ አንሳፍኩት…ሰውዬው አይኑ ተጉረጠረጠ..እጆቹን እንድለቀው ማወራጨቱን ቀጠለ
አያቴም ከድንዛዜው እንደምንም ባኖ ይለምነኝ ጀመር
‹‹ልጄ ምን እየሰራህ ነው..…?ሰውዬውን ልቀቀው..…?ልጄ የሰው ሰው እንዳትገል፡፡››
‹‹እናቴን ታድናታለህ አታድናትም.…?››አርገፍግፌ መሬት አድርሼ ለቀቅኩት
ዶክተሩ ጉሮሮውን በእጆቹ እየዳበሰ ደጋግሞ ካሳለ ቡኃላ‹‹.አዝናለው አልችልም…ማንም ሊያድናት አይችልም….››ብሎ ስለበሽታዋ አይነትና ከባድነት የደረሰበትን ደረጃ በተቆራረጠ ቃላት ይዘረዝርልን ቀጠለ.
በእናቴ ስም እምላለው…ከሞተች አገድልሀለው..አንተን ብቻ ሳይሆን ጠቅላላ እዚህ ግቢ ውስጥ ያላችሁትን ሀኪሞች ጨርሳችሆለው …ሆስፒታሉንም አቃጥለዋለው፡፡አረ ከተማወናም ነው የማቃጥለው…››በማለት ቢሮውን ጥዬ ወጣውና እናቴ ወደተኛችበት ክፍል ተንደረደርኩ ፡፡በራፍ ላይ የቆመችውን ነርስ ገፍቼ ፍቃዷንም ሳልጠይቅ ወደውስጥ ገባው፡፡እማዬ ዝርር ብላ ተሰትራ የሆስፒታሉ አልጋ ላይ ተኝታለች፡፡አይኖቾ ተከድነዋል፡፡ትንፋሿም አይሰማም ፡፡በሁለቱ አፍንጫጮ ቀዳዳ ቱቦ በክንዶቾ የግሉኮስ ላስቲክ ተሰክቶል፡፡
በራስጌዋ ሄድኩና ወለሉ ላይ ዝርፍጥ ብዬ ግንባሬን አልጋዋ ላይ ደፍቼ ወደ ፊቷ ተጠግቼ አስደገፍኩና በሹክሹክታ አወራት ጀመር….
ማሂ ምን እየሰራሽ ነው…?፡፡ምንድነው ዶክቱሩ የሚቀባጥረው…?፡፡ጥላህ ልትሄድ ነው እያለኝ ነው፡፡ስለማያውቅሽ ነው የሚቀባጥረው ፡፡አንቺ መቼም መቼም እኔን ጥለሽ መሄድ እንደማትችይ ስለማያውቅ ነው፡፡ገነትም ቢሆን እኔ ከሌለው መኖር እንደማትችይ ስለማውቅ ነው፡፡ማሂ ከተወለድኩበት ቀን አንስቶ ስትበይ እንብላ ብለሺኝ ስትተኚ እንተኛ ብለሺኝ ፤ስትተነፍሺ እንኳን የእኔንም መተንፈስ አረጋግጠሸ ነበር…ታዲያ ዶክተሮቹ እንደሚሊት አሁን ልትሞቺ ከሆነ እንዴት ልንሞት ነወ ተዘጋጅ ሳትይኝ .. …?ነገሩ ተይው እውነት ዶክተሩ አንዳለው ሸውደሺን ለመሞት የተዘጋጀሽ ከሆነም ግድ የለም እኔ ዝግጅት አያስፈልገኝም፡፡
ንግግሬን ከጀርባዬ ሆኖ ሲያዳምጥ የቆየው አያቴ በሽማግሌ አንጀቱ እየተንሰቀሰቀ በማልቀስ ዝቅ ብሎ አስነሳኝና
‹‹ተው ልጄ ተረጋጋ…አይዞህ እግዜር አለ ያድንልናል፡፡››
እንግዲህ እግዚያብሄር አለ የምትል ከሆነ በምትግባቡበት ቋንቋ ንገረው…ተው የሰው እናት አትንጠቅ በለው…እሷን አጥቶ መኖር አይችልም በለው…ከሰማህ ጥሩ ነው ፡፡ ካልሰማህ ደግሞ እኔንም ተሰናበተኝ ፡፡ እናም ከእናቴ ጋር በአንድ ጉድጓድ መቀበር ነው የምፈልገው..እንዳትረሳ በአንድ ጉድጓድ ፡፡ይህ ኑዛዜዬ ነው፡፡››ብዬው ጥዬው ወጣው ፡፡ወደየት እንደምሄድ ባላውቅም የሆስፒታሉን ቅጥር ጊቢ ለቅቄ ወጣው….
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍4❤2
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ_
:
#ክፍል_አስራ_ሁለት
:
✍ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ሶስተኛ ቀን ነው፡፡እንደነጋ እናቴን ይዤ ከሆስፒታል ወደቤት እሄዳለው፡፡ከዛ አስክትሞትበት ቀን ድረስ አብሬያት ስሮ ተኛለው፡፡ስትነቃ ነቃለው ስትተኛ አብሬት ተኛለው፡፡ምንያህል እንድምወዳት ያለማቆረጥ በየቀኑ ነግራታለው፡፡የሚያስደስቷትን ዘፈኖች ዘፍንላታለው፡፡የሚያዝናናትን ታሪክ አወራታለው፡፡የሚትወዳቸውን ምግቦች ሁሉ በገዛ እጆቼ እያበሰልኩ እመግባታለው፡፡ከዛ የመጨረሻው ቀን ደርሶ ስትሞት ደቂቃዎችን ሳላባክን እከተላታለው፡፡እራሴን ለማጥፋት የሚያስፈልገኝ መሳረያ …. እንዴት እንደምሞት እቅድ አውጥጬ ዝግጅቴን ሁሉ ጨርሼያለው፡፡በዚህ ለሊት ሆስፒታል የበሽተኛ አልጋ ላይ ዝርግትግት ብላ ከተኛችወ እናቴ ጎን ካላ ሌላ አልጋ ላይ ተቀምጬ ነው እቅዴን እየከለስኩ ያለውት፡፡ሳላገባድድ የክፍሉ በረፍ በዝግታ ተከፈተ፡፡
በዚህ ሰዓት ነጭ ጋወን የለበሰ ባለሞያ እናቴ ወዳለችበት ክፍል ምምጣት የተለመደ ነገር ነው፡፡አዲስ የሆነው የመጣችው ልጅ ነች ፡፡በጥቁር እና በቅላት መካከል ያለ የሰውነት ከለር ፤የተመዘዘ የሰውነት ቁመት ያላት ቀጭን የምትባል ሀያዎቹ መጀመሪያ ላይ ያለች ፡፡በዚህ ለሊት ይሄ ሁሉ ፈግታ ገረመቺኝ፡፡ባለፉት ቀናት ልምዴ ሁሉም ዶክተሮች ሆኑ ነርሶች ለሊት ሲመጡ ከቀን ሁኔታቸው ባለይ ኮስተር ብለው ነው የማያቸው..ምን አልባ እንቅልፍ እየፈተናቸው ስለሚሆን ነው የሚል የራሴን ግምት ወስጄያለው..ምንም ቢሆን ሰው አይደሉ…?
ይህቺ ግን …ደግሞ ካለዛሬ ኮ አይቼያት አላውቅም፡፡
<<ተኝታለች…?››
<<አዎ ›
<<ወንድሞ ነህ…?››
ወንድሞም፤ጓደኛዋም፤ልጆም ነኝ››
‹‹ገባኝ …ግን እኩያዋ ነህ …ተናሽና ታላቅ እህትና ወንድም ነው የምትመስሉት፡፡በዚህ እድሜዋ አንተን ማድረሶ ሚገርም ነው፡፡››አለቺኝ በፈግታዋ እንደተሞላች በእጆ የያዘችውን እናቴን የህክምና የክትትል ሪከርድ እየተመለከተች
‹‹ልጆ መሆኔን አመንሽ ማለት ነው.…?አልኳት ..እንዴት እርግጠኛ ልትሆን እንደቻለች ግር ብሎኝ
‹‹አዎ ..አንዳንድ ነገሮችን ትንሽ ትኩረት ካደረግኩ ሳይነገረኝም ማወቅ እችላለው፡፡››
‹‹እሺ አንቼ በራፍን ከፍተሸ ከመምጣትሽ በፊት ምን እያሰብኩ ነበር››ዝም ብዬ ለቀልድ ያህል ነበር የጠየቅኳት…?
በእጆ የያዘችውን ወረቀት እናቴ የተኛችበት አልጋ ጠርዝ ላይ አስቀመጠችና በዝግታ እርምጃ ወደእኔ ተጠጋች .፡፡እንደመደንገጥ አልኩ‹‹እጅህን ስጠኝ ››አለቺኝ…ያለጥያቄ ቀኝ እጄን ዘረጋውላት፡፡ በሁለት እጆቾ መካከል አስገብታ ጨበጠችውና በመንፈስ ተሞልቶ እንደሚፀልይ ፓስተር አይኖቾን ጨፈነችና ለተወሰኑ ሰከንዶች ከቆየች ቡኃላ የመወርወር ያህል እጄን ለቃ ወደኃላ አፈገፈገችና ያስቀመጠችውን ወረቀት አንስታ ያዘች
‹‹ምነው ከበደሽ…?››
‹‹እናትህም ባንተ ቦታ ብትሆን እንደዛው ነበር የምታደርገው›› አለቺኝ
‹‹አልገባኝም››
‹‹የታመምከው እና ትሞታለህ የተባልከው አንተ ብትሆን እናትህም እንደአንተው እራሷን ለማጥፋት ዝግጅት ታደርግ ነበር..››
ከተቀመጥኩበት በድንጋጤ ተነሳውና ቆምኩ..መልሼ ቁጭ አልኩ
‹‹እንደዛ እያሰብኩ እንደሆነ እንዴት አወቅሽ…?››
‹‹እርሳው …አለቺኝና የእናቴን ሙቀት መለካት ጀመረች
‹‹አይ አረሳውም…ስለእናቴ የተጠቀሰው በሽታ የእውነት እንዳሉት በአጭር ቀናት ….››ዓ/ነገሩን ልጨርሰው አልቻልኩም፡፡
በብጫቂ ወረቀት ላይ ‹‹አዎ…እናትህ 25 ቀን ብቻ ነው ያላት፡፡››ብላ ፅፋ አቀበለቺኝ
እንደእኔ ሁሉ እሷም በአንደበቶ መናገር ከብዶት ይሁን ወይም እናቴ በእንቅልፍ ልቧም ቢሆን ልትሰማ ትችል ይሆናል ብላ በማሰብ አልገባኝም
ወረቀቱን ከነብኩ ቡኃለ ጠቅልዬ አፌ ውስጥ ከትኩት እና አኝኬ ዋጥኩት…ከዛ ፀጥ አልኩ…ምንም ልላት አልቻልኩም ፡፡የምታደርገውን አድርጋ በል አይዞህ በርታ ብላኝ እንደአመጣጦ ወጥታ ሄደች፡፡
መብሰልሰሌ በእጥፍ ጨመረ ..ይህቺ ዶክተር ማን ነች……?የእውነት ነች ወይስ ከመንፈስ ጋ እያወራው ነበርኩ…?››፡ከተቀመጥኩበት ተነሳውና ክፍሉን ለቅቄ ወጣው፡፡
ተረኛዋን ዶክተር ማናገር እንደምፈልግ ስናገር ቢሮዋ እንዳለች ጠቆሙኝ፡፡ሄድኩና በስሱ አንኳኳው፡፡
‹‹ግባ›› የሚል ድምፅ ከውስጥ ስሰማ …ከፈትኩና ገባው፡፡ አቀርቅራ መፅሀፍ እያነበበች ነበር፡፡አዎ የእውነት ነች ማለት ነው…? ፡፡እየቃዠው አይደለም፡፡
‹‹ቁጭ በል ››
ቁጭ አልኩ
‹‹ሳይሽ ዛሬ የመጀመሪያ ቀኔ ነው፡፡››
‹‹አዲስ ነኝ ፡፡ዛሬ ነው ስራ የጀመርኩት፡፡ይህቺ ለሊት የመጀመሪያ ቀኔ ነች፡፡››ብላ አስገረመቺኝ
‹‹ታዲያ እንዴት በመጀመሪያ ቀን ስራሽ እናቴን 28 ቀን እንደቀራት መናገር ቻልሽ…?››
አንደኛ የህክምና ውጤቱ ሪከርድ ተደርጓል፡፡እዚህ ፊት ለፊቴ ያለው ኮምፒተር ውስጥም አለ፡፡ወደእናንተ ከመምጣቴ በፊት አንብቤዋለው፡፡
‹‹28 ቀን ይቀራታል ይላል…?››ፍርጥም ብዬ ጠየቅኩ፡፡
‹‹አይ ቀኑንማ አይናገርም፡፡እሱ የእኔ ትንበያ ነው፡፡በነገራችን ላይ አንድ ውለታ ልውልልህ እያሰብኩ ነው፡፡››
‹‹ምን አይነት ውለታ…እናቴን የምትድነበት ሆስፒታል ወይም ሀገር ልትጠቁሚኝ ነው…?››
‹‹ፍጽም…እናትህን የሚያድናት ዘመናዊ ህክምና የትም ብትሄድ አታገኝም››
‹‹ታዲያ ሌላ ውለታ ምን ያደርግልኛል…?፡፡አልኮት ለምቦጬን ጥዬ
‹‹አንድ ማውቀው የባህል ህክምና አለ ፡፡ፈጽሞ አያድናትም ግን ቢያንስ ዕድሜዋን በሶስት አመት ያራዝመዋል፡፡››
ከተቀመጥኩበት በድንጋጤ ተነሳው.. ተንደርድሬ እግሯ ላይ ተደፋው…‹‹በፈጠረሽ ..በምታምኚው ይዤሻለው እባክሽ እናቴን አትሪፊልኝ››
‹‹ላተርፋት አልችልም…ሶስት አመት ብቻ›
‹‹ይሁን …ሶስት አመት .››
‹‹ሶስት አመት እኮ ብዙ አይደለም…ሳታስበው ነው የሚደርሰው››
ግድ የለሽም ..አንቺ ብቻ እሱን አድርጊልኝ… እስከዛ የሚሆነውን ማን ያውቃል…?፡፡››
‹‹እሺ ሂድ ከግማሽ ሰዓት ቡኃላ እመጣለው፡፡››
‹‹እመጣለው ስትይ..››
‹‹መድሀኒቱን ይዤ እመጣለው››
አላመንኳትም ፡፡እንዴ ባለፉት ሶስት ቀናቶች እንቅልፍ ባለመተኛቴ አዕምሮዬን እየሳትኩ ይሆን እንዴ …?ይሄ ነገር የእስካሁኑ ሁሉ ህልም እንዳይሆን..…?፡፡ጎንበስ አልኩና የእጄን መዳፍ ጠረጵዛዋ ላይ ዘረግቼ እጆ ላይ ያለውን እስኪሪብቶ ተቀበልኩና በኃይል ወጋውት .የእስኪሪብቶው ጫፍ የተወሰነ ጥልቀት ወደ መዳፌ ውስጥ ሲገባ እግሬ ድረስ ነዘረኝ..
‹‹በህልም ውስጥ አይደለውም ማለት ነው›…?አልኩ
‹‹ይሄ ያደረከው እኮ ማረጋገጫ አይሆንም ፡፡ምክንያቱም በህልምህም ቢሆን ይሄንን የማረጋገጫ ሙከራ ልትሞክር ትችላለህ ፡፡››ብላኝ ከስጋቴ እንዳልወጣ አደረገቺኝ…ለማንኛውም እንዳለቺኝ ቢሮዋን ለቅቄ ወደእናቴ ተመለስኩና በናፍቆትና በጭንቀት እጠብቃት ጀመር።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
:
#ክፍል_አስራ_ሁለት
:
✍ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ሶስተኛ ቀን ነው፡፡እንደነጋ እናቴን ይዤ ከሆስፒታል ወደቤት እሄዳለው፡፡ከዛ አስክትሞትበት ቀን ድረስ አብሬያት ስሮ ተኛለው፡፡ስትነቃ ነቃለው ስትተኛ አብሬት ተኛለው፡፡ምንያህል እንድምወዳት ያለማቆረጥ በየቀኑ ነግራታለው፡፡የሚያስደስቷትን ዘፈኖች ዘፍንላታለው፡፡የሚያዝናናትን ታሪክ አወራታለው፡፡የሚትወዳቸውን ምግቦች ሁሉ በገዛ እጆቼ እያበሰልኩ እመግባታለው፡፡ከዛ የመጨረሻው ቀን ደርሶ ስትሞት ደቂቃዎችን ሳላባክን እከተላታለው፡፡እራሴን ለማጥፋት የሚያስፈልገኝ መሳረያ …. እንዴት እንደምሞት እቅድ አውጥጬ ዝግጅቴን ሁሉ ጨርሼያለው፡፡በዚህ ለሊት ሆስፒታል የበሽተኛ አልጋ ላይ ዝርግትግት ብላ ከተኛችወ እናቴ ጎን ካላ ሌላ አልጋ ላይ ተቀምጬ ነው እቅዴን እየከለስኩ ያለውት፡፡ሳላገባድድ የክፍሉ በረፍ በዝግታ ተከፈተ፡፡
በዚህ ሰዓት ነጭ ጋወን የለበሰ ባለሞያ እናቴ ወዳለችበት ክፍል ምምጣት የተለመደ ነገር ነው፡፡አዲስ የሆነው የመጣችው ልጅ ነች ፡፡በጥቁር እና በቅላት መካከል ያለ የሰውነት ከለር ፤የተመዘዘ የሰውነት ቁመት ያላት ቀጭን የምትባል ሀያዎቹ መጀመሪያ ላይ ያለች ፡፡በዚህ ለሊት ይሄ ሁሉ ፈግታ ገረመቺኝ፡፡ባለፉት ቀናት ልምዴ ሁሉም ዶክተሮች ሆኑ ነርሶች ለሊት ሲመጡ ከቀን ሁኔታቸው ባለይ ኮስተር ብለው ነው የማያቸው..ምን አልባ እንቅልፍ እየፈተናቸው ስለሚሆን ነው የሚል የራሴን ግምት ወስጄያለው..ምንም ቢሆን ሰው አይደሉ…?
ይህቺ ግን …ደግሞ ካለዛሬ ኮ አይቼያት አላውቅም፡፡
<<ተኝታለች…?››
<<አዎ ›
<<ወንድሞ ነህ…?››
ወንድሞም፤ጓደኛዋም፤ልጆም ነኝ››
‹‹ገባኝ …ግን እኩያዋ ነህ …ተናሽና ታላቅ እህትና ወንድም ነው የምትመስሉት፡፡በዚህ እድሜዋ አንተን ማድረሶ ሚገርም ነው፡፡››አለቺኝ በፈግታዋ እንደተሞላች በእጆ የያዘችውን እናቴን የህክምና የክትትል ሪከርድ እየተመለከተች
‹‹ልጆ መሆኔን አመንሽ ማለት ነው.…?አልኳት ..እንዴት እርግጠኛ ልትሆን እንደቻለች ግር ብሎኝ
‹‹አዎ ..አንዳንድ ነገሮችን ትንሽ ትኩረት ካደረግኩ ሳይነገረኝም ማወቅ እችላለው፡፡››
‹‹እሺ አንቼ በራፍን ከፍተሸ ከመምጣትሽ በፊት ምን እያሰብኩ ነበር››ዝም ብዬ ለቀልድ ያህል ነበር የጠየቅኳት…?
በእጆ የያዘችውን ወረቀት እናቴ የተኛችበት አልጋ ጠርዝ ላይ አስቀመጠችና በዝግታ እርምጃ ወደእኔ ተጠጋች .፡፡እንደመደንገጥ አልኩ‹‹እጅህን ስጠኝ ››አለቺኝ…ያለጥያቄ ቀኝ እጄን ዘረጋውላት፡፡ በሁለት እጆቾ መካከል አስገብታ ጨበጠችውና በመንፈስ ተሞልቶ እንደሚፀልይ ፓስተር አይኖቾን ጨፈነችና ለተወሰኑ ሰከንዶች ከቆየች ቡኃላ የመወርወር ያህል እጄን ለቃ ወደኃላ አፈገፈገችና ያስቀመጠችውን ወረቀት አንስታ ያዘች
‹‹ምነው ከበደሽ…?››
‹‹እናትህም ባንተ ቦታ ብትሆን እንደዛው ነበር የምታደርገው›› አለቺኝ
‹‹አልገባኝም››
‹‹የታመምከው እና ትሞታለህ የተባልከው አንተ ብትሆን እናትህም እንደአንተው እራሷን ለማጥፋት ዝግጅት ታደርግ ነበር..››
ከተቀመጥኩበት በድንጋጤ ተነሳውና ቆምኩ..መልሼ ቁጭ አልኩ
‹‹እንደዛ እያሰብኩ እንደሆነ እንዴት አወቅሽ…?››
‹‹እርሳው …አለቺኝና የእናቴን ሙቀት መለካት ጀመረች
‹‹አይ አረሳውም…ስለእናቴ የተጠቀሰው በሽታ የእውነት እንዳሉት በአጭር ቀናት ….››ዓ/ነገሩን ልጨርሰው አልቻልኩም፡፡
በብጫቂ ወረቀት ላይ ‹‹አዎ…እናትህ 25 ቀን ብቻ ነው ያላት፡፡››ብላ ፅፋ አቀበለቺኝ
እንደእኔ ሁሉ እሷም በአንደበቶ መናገር ከብዶት ይሁን ወይም እናቴ በእንቅልፍ ልቧም ቢሆን ልትሰማ ትችል ይሆናል ብላ በማሰብ አልገባኝም
ወረቀቱን ከነብኩ ቡኃለ ጠቅልዬ አፌ ውስጥ ከትኩት እና አኝኬ ዋጥኩት…ከዛ ፀጥ አልኩ…ምንም ልላት አልቻልኩም ፡፡የምታደርገውን አድርጋ በል አይዞህ በርታ ብላኝ እንደአመጣጦ ወጥታ ሄደች፡፡
መብሰልሰሌ በእጥፍ ጨመረ ..ይህቺ ዶክተር ማን ነች……?የእውነት ነች ወይስ ከመንፈስ ጋ እያወራው ነበርኩ…?››፡ከተቀመጥኩበት ተነሳውና ክፍሉን ለቅቄ ወጣው፡፡
ተረኛዋን ዶክተር ማናገር እንደምፈልግ ስናገር ቢሮዋ እንዳለች ጠቆሙኝ፡፡ሄድኩና በስሱ አንኳኳው፡፡
‹‹ግባ›› የሚል ድምፅ ከውስጥ ስሰማ …ከፈትኩና ገባው፡፡ አቀርቅራ መፅሀፍ እያነበበች ነበር፡፡አዎ የእውነት ነች ማለት ነው…? ፡፡እየቃዠው አይደለም፡፡
‹‹ቁጭ በል ››
ቁጭ አልኩ
‹‹ሳይሽ ዛሬ የመጀመሪያ ቀኔ ነው፡፡››
‹‹አዲስ ነኝ ፡፡ዛሬ ነው ስራ የጀመርኩት፡፡ይህቺ ለሊት የመጀመሪያ ቀኔ ነች፡፡››ብላ አስገረመቺኝ
‹‹ታዲያ እንዴት በመጀመሪያ ቀን ስራሽ እናቴን 28 ቀን እንደቀራት መናገር ቻልሽ…?››
አንደኛ የህክምና ውጤቱ ሪከርድ ተደርጓል፡፡እዚህ ፊት ለፊቴ ያለው ኮምፒተር ውስጥም አለ፡፡ወደእናንተ ከመምጣቴ በፊት አንብቤዋለው፡፡
‹‹28 ቀን ይቀራታል ይላል…?››ፍርጥም ብዬ ጠየቅኩ፡፡
‹‹አይ ቀኑንማ አይናገርም፡፡እሱ የእኔ ትንበያ ነው፡፡በነገራችን ላይ አንድ ውለታ ልውልልህ እያሰብኩ ነው፡፡››
‹‹ምን አይነት ውለታ…እናቴን የምትድነበት ሆስፒታል ወይም ሀገር ልትጠቁሚኝ ነው…?››
‹‹ፍጽም…እናትህን የሚያድናት ዘመናዊ ህክምና የትም ብትሄድ አታገኝም››
‹‹ታዲያ ሌላ ውለታ ምን ያደርግልኛል…?፡፡አልኮት ለምቦጬን ጥዬ
‹‹አንድ ማውቀው የባህል ህክምና አለ ፡፡ፈጽሞ አያድናትም ግን ቢያንስ ዕድሜዋን በሶስት አመት ያራዝመዋል፡፡››
ከተቀመጥኩበት በድንጋጤ ተነሳው.. ተንደርድሬ እግሯ ላይ ተደፋው…‹‹በፈጠረሽ ..በምታምኚው ይዤሻለው እባክሽ እናቴን አትሪፊልኝ››
‹‹ላተርፋት አልችልም…ሶስት አመት ብቻ›
‹‹ይሁን …ሶስት አመት .››
‹‹ሶስት አመት እኮ ብዙ አይደለም…ሳታስበው ነው የሚደርሰው››
ግድ የለሽም ..አንቺ ብቻ እሱን አድርጊልኝ… እስከዛ የሚሆነውን ማን ያውቃል…?፡፡››
‹‹እሺ ሂድ ከግማሽ ሰዓት ቡኃላ እመጣለው፡፡››
‹‹እመጣለው ስትይ..››
‹‹መድሀኒቱን ይዤ እመጣለው››
አላመንኳትም ፡፡እንዴ ባለፉት ሶስት ቀናቶች እንቅልፍ ባለመተኛቴ አዕምሮዬን እየሳትኩ ይሆን እንዴ …?ይሄ ነገር የእስካሁኑ ሁሉ ህልም እንዳይሆን..…?፡፡ጎንበስ አልኩና የእጄን መዳፍ ጠረጵዛዋ ላይ ዘረግቼ እጆ ላይ ያለውን እስኪሪብቶ ተቀበልኩና በኃይል ወጋውት .የእስኪሪብቶው ጫፍ የተወሰነ ጥልቀት ወደ መዳፌ ውስጥ ሲገባ እግሬ ድረስ ነዘረኝ..
‹‹በህልም ውስጥ አይደለውም ማለት ነው›…?አልኩ
‹‹ይሄ ያደረከው እኮ ማረጋገጫ አይሆንም ፡፡ምክንያቱም በህልምህም ቢሆን ይሄንን የማረጋገጫ ሙከራ ልትሞክር ትችላለህ ፡፡››ብላኝ ከስጋቴ እንዳልወጣ አደረገቺኝ…ለማንኛውም እንዳለቺኝ ቢሮዋን ለቅቄ ወደእናቴ ተመለስኩና በናፍቆትና በጭንቀት እጠብቃት ጀመር።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍11
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ
:
#ክፍል_አስራ_ሶስት
:
✍ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ዶክተሯ ቃሏን ጠብቃ ከሀያ ደቂቃ ቡሃላ በአነስታኛ ብልቃጥ ሀመራዊ አይነት ዝልግልግ ፈሳሽ ይዛ በምጣት ያለምንም ንግግር መድሀኒቱን ከብልቃጥ ውስጥ በስሪንጅ በምጠጥ ከእናቴ ደምስር ጋር ከቴያያዘው የጉልኮስ የፕላስቲክ ከረጢት ውስጥ ጨመረችውና …እንዳአመጣጦ ምንም ሳትናገር ወጥታ ሄደች፡፡
እኔም ደንዝዤ ስለነበረ የምታርገውን በፅሞና ከመታዘብ በዘለለ አንደበቴን አላቅቄ ቃላት ማውጣት አልቻልኩም..ምን እየተፈጠረ ነው..?እውነት እንዳለችው ይህ መድሀኒት እናቴን ይፈውሳት ይሆን…..?ነው ወይስ እያሾፈችብኝ ይሆን…..?እንደዛማ ከሆነ በህይወቷ ወስናለች ማለት ነው፡፡እዛው የቢሮዋ ወንበር ላይ እንደተቀመጠች በእነዚህ መዳፎቼ አንገቷን ፈጥርቄ ፀጥ ነው የማደርጋት ፡፡….በውስጤ ዛትኩ
በተጋደምኩበት ይሄንን እና የመሳሰሉትን ግትልትል ሀሳቦች እያሰብኩ ሳይታወቀኝ እንቅልፍ ይዞኝ ጭልጥ ብሎ ነበር ለካ ፡፡አይፈረድብኝም የሶስት ሙሉ ቀን እንቅልፍ ነው ያለብኝ፡፡
‹‹…ፀጋ …የእኔ ልጅ››የሚለው ከገነት ከመላዕክት አንደበት የሚፈስ የሚመስል ጡዑም ዜማ ያለው የእናቴ የጥሪ ድምጽ ነበር ከእንቅልፌ የቀሰቀሰኝ… ደንግጬ ከተጋደምኩበት የሆስፒታል አልጋ በርግጌ በመውረድ ወለሉ ላይ እናቴ ፊት ለፊት ተገተርኩ
‹‹..አረ ተረጋጋ የእኔ ጌታ..››ጥርት ያለ ንፅህ የእናቴ ድምፅ..
ማመን አልቻልኩም፡፡በስነስርአት ትራስ እንኳን መንተራስ ሳያስፈልጋ ቁጭ ብላለች፡፡ምንም በበሽታ የመድከም ምልክት በፊቷ አይታይም፡፡
‹‹እማ ደህና ነሽ…..?ተሸለሽ…..?አሁን ምን ይሰማሻል..?››በጥያቄ አጣደፍኳት
‹‹ይሄው እንደምታየው በጣም ደህና እና ፍፅም ጤነኛ ሆኜ ነው የተነሳሁት፡፡ይገርምሀል ለሊ,ት ተኝቼ ጠይም መላዕክ መጥታ ከጭንቅላቴ አንስታ መላ አካላቴን ስትዳብሰኝ ነበር…እግዜያብሄር ያአንተ ፀሎት ሰምቶ ምሮኛል መሰለኝ፡፡››አለቺኝ በተፍለቀለቀ የደስታ ድምፀት
ተንጠራራውና አቀፍኳት ፡፡ግንባሯን …ጉንጮን …አፍንጫዋን እያፈራረቅኩ ሳምኳት ‹‹…አዎ እማ ድነሻል…እግዜያብሄር ይመስገን ተሳክቶልናል…ልጅቷ እንዳለችው ማድረግ ችላለች…ምትገርም ሴት ነች፡››
‹‹ስለማን ነው የምታወራው..?›› አለችኝ መቀባዠሬ ስላልገባት
‹‹አይ በህልሜ አየዋት ስላልሽው መላዕክ ነው ማወራው….ስላዳነችሽ መላአክ››አልኩና ርዕሱን አስቀየርኳት
‹‹አዎ እግዜር ነው የላከልኝ..ሄድ አሁን ሀኪም ጥራልኝ››
‹‹ምነው .. ..?የሚያምሽ ቦታ አለ እንዴ..?›› በድንጋጤ ጠየቅኳት
‹‹አረ በፍጽም… ይሄን ግሉኮስ ከላዬ እንዲነቅሉልኝ ነው…ሽንት ቤት መሄድ ፈልጋለው ›› ስትለኝ..ሮጬ ወጣውና በ10 ደቂቃ ውስጥ ተረኛውን ዶክተር አስከትዬ መጣው፡፡ይሄ ዶክተር እናቴ ሆስፒታል ከገባች ቀን ጀምሮ በዋናነት ስለጤናዋ ይከታተላት የነበረው ስለነበር እንዳያት ደነገጠ..በጣምም ግራ ተጋባ..ከግምቱ ውጭ የሆነ ሁኔታ ላይ ሆና ነው ያገኛት .
‹‹ማህሌት ምን ይሰማሻል. .?››
‹‹ፍጽም ጤነኝነት››
በጣም ጥሩ ..አሁን ወደቤት ከመሄድሽ በፊት ሙሉ ምርመራ ማድረግ አለብን ..››አለና ጉሉኮሱን ከእጇ ላይ በማለያየት ወጥቶ ሄደ …እኔም እሱ ለምርመራ ሚገለገልባቸውን መሳሪያዎች ይዞ እስኪመጣ ድረስ ስልኬን አወጣውና ለአያቴ ደወልኩለት…
‹‹ሄሎ አባ የት ነህ.?››
‹‹የት እሆናለው ልጄ… ቤተክርስቲያን ነኝ…ምነው ልጄ ባሰባት እንዴ .?›› ስብርብር ባለ ተስፋ የቆረጠ ደካማ ድምፅ ጠየቀኝ
‹‹አረ አባ ፍፅም ደህና ነች…ፀሎትህን ከጨረስክ ቀጥታ ወደሀስፒታል ና ››
‹‹አሟታል ማለት ነው ..መች አጣውት …እግዜያብሄር ዘንድሮ ሊያዋርደኝ ነው››አምላኩ ፊት መቆሙን እንኳን ዘንግቶ ተነጫነጨ
‹‹እወነቴን ነው አባ …ቆይ እንደውም…›› ብዬ ስልኩን ከጆሮዬ ላይ አነሳውና ለእናቴ አቀበልኳት ..የጠራ እና የነቃ ድምፆን በስልክ ከሰማ ቡሃላ በደስታ ሰክሮ እልልታውን ሲያቀልጠው በስልኩ ውስጥ ተሰማኝ…በዚህ እድሜው ልጁ ስትሞት አይቶ ባለመሳቀቁ ውስጤን ሀሴት ተሰማው …ቢያንስ ለጊዜው ይደሰት ..
እስከአራት ሰዓት መደረግ ያለበት ምርመራ ሁሉ ተደርጎላት ተጠናቀቀ..ውጤቱም ዶክተሮቹን በጣም ያስደመመ እና የበፊቱን የምርመራ ውጤት እንዲጠራጠሩ ያደረገ ነበር…እኔም ስለሆነው ነገር በውስጤ አፍኜ አብሬያቸው ከማደነቅ ውጭ ምንም ነገር ትንፍሽ ማለት አልቻልኩም…አልፈለኩምም፡፡
አዲሱ የህክምና ውጤት እንደሚያሳየው የእናቴ በሽታ ሙሉ በሙሉ የጠፋ ባይንም ደረጃው ግን 50 ፐርሰንት ወደኃላ የተመልሰል ነበር…ይህ ማለት ደግሞ ዋናው ሀኪምም እንዳረጋገጠልኝ በቅርብ ጊዜ ትሞታለች የሚለው ስጋት በአስተመማኝ ሁኔታ እንደተወገደ ነው፡፡
እንዴት እንደሆነ ባይገባኝም በእናቴ ላይ ተአምር ተፈፅሟል …ሙሴ የእስራኤልን ባህር በበትሩ ከፍሎ ወገኖቹን ያሻገራቸውን አይነተ ተአምር….አስራሁለት አመት ደም ሲፈሳት የነበረች ሴት የክርስቶስን የልብስ ጫፍ በእምነት ዳብሳ ከህመሞ ፈውስ ያገኘችበትን አይነት ተአምር ፡፡እርግጥ ታአምሩ ጅምር ነው…ምን አልባት በዚሁ የሚቀጥል ከሆነ ሙሉ በሙሉ ልትፈወስና እኛንም ይበልጥ ልታስደምመን ትችል ይሆናል፡፡
በሰተመጨረሻ ለመሄድ ዝግጅታችንን እንዳጠናቀቅን ወደዋናው ዶክተር ቀረብኩና ‹‹አመሰግናለው ዶክተር..ሁላችሁንም እግዜር ይስጥልኝ አልኩ››
‹‹ኦኬ ..ያ ማለት ለህይወታችን መስጋት አይጠበቅብንም ማለት ነው..?››
‹‹ማለት . ..?አልገባኘም ..?››
‹‹እንደምትገለን በርግጠኘነት ዝተህብን ነበር…አሁን እናትህ በከፊልም ቢሆን በመዳኗ ለጊዜው የተረፍን ይመስለኛል››አለኝ ፈገግ እያለ
አንገቴን አቀረቀርኩ‹‹በጣም አዝናለው…እናቴ ለእኔ መላ ነገሬ ስለነበረች አብዝቼው ነበር…ያን ያህል ስለታገሳችሁኝ ውለታችሁን መቼም አረሳውም..››
‹‹አረ ስቀልድህ ነው..እኔም ሆንኩ ባለደረቦቼ በወቅቱ የነበርክበትን ሁኔታ በደንብ ስለተረዳን ምንም አይነት ቅሬታ እልተሰማንም …ነገሩን ያነሳውልህ እንዲሁ ልቀልድ ብዬ ነው ›አለኝ
እናቴን በጓደኛቼ በዘመድና በጎረቤት ሰዎች አሳጅቤ እባቴ ስንደርስ አምስት ሰዓት ሆኖ ነበር… እናቴን ወደጆሮዋ ተጠግቼ የምሄድበት ቦታ እንዳለና ልቆይ እንደምችል ነግሬት ከአጀብ ውስጥ ወጥቼ ወደሆስፒታል ተመለስኩ …ከተቻለ ዶክተሯን ለማግኘት ፤ ከለበላዛ እንዴት እዳማገኛትና ከዛም አልፎ ስለማንነቷ መረጃዎችን ከገኘው ለማጣራት…
ምክንያቱም ስለእሷ በአዕምሮዬ ውስጥ የሚጉላሉ ጥያቄዎች ከቁጥጥር ውጭ እያደረጉኝ እና መንፈሴን ክፉኛ እየረበሹት ነው.
1/ይቺ ዶክተር ማነች....?የትኛው ከተማ ወይም የትኛው ገጠር ተወልዳ የትኛው ዩኒቨርሲቲ ገብታ ተምራ እዴት እዚህ ተማድባ መጣች..?
2/እንዲህ አይነት ከሳይንስ አቅም በላይ የሆነ ህምምን ለመፈወስ የሚያስችል የባህል ህክምና ጥበብን በዚህ ዕድሜዋ እንዴት ልትካንበት ቻለች;..?››
3/በምን አይነት ተአምራዊ አጋጣሚ ሄስፒታሉ ለመስራት በተመደበች በመጀመሪያው ቀን የመጀመሪያዋ ታካሚዋ እናቴ ልትሆን ቻለች..?
2/ከእኔ እፈልገዋለው ያለችው በውለታዋ ምላሽ እንድከፍል የሚጠበቅብኝ ምንድነው....?ብር እንዳልሆነ እርግጠኛ ነኝ ፡፡አንገቷ ላይ ያጠለቀችው እባብ የመሰለ ጥምዝ ወርቅ እና ጆሮዋ ላይ ያንጠለጠለችው የከበረ ጌጥ የኑሮ ደረጃዋን ያሳብቅባታል፡፡የባህል መድሀኒት በሆስፒታል ቅጥር ግቢ በድብቅ እየቸረቸረች ገንዘብ የምትሰበስብ አይነት ሰው አይደለችም..አዎ በዛ እርግጠኛ ነኝ ፡፡ግን ምንም እንዳደርግላት ብትጠይቀኝ ግድ የለኝም…እራስህን አጥፋልኝ ብትለኝም አደርገዋለው…
:
#ክፍል_አስራ_ሶስት
:
✍ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ዶክተሯ ቃሏን ጠብቃ ከሀያ ደቂቃ ቡሃላ በአነስታኛ ብልቃጥ ሀመራዊ አይነት ዝልግልግ ፈሳሽ ይዛ በምጣት ያለምንም ንግግር መድሀኒቱን ከብልቃጥ ውስጥ በስሪንጅ በምጠጥ ከእናቴ ደምስር ጋር ከቴያያዘው የጉልኮስ የፕላስቲክ ከረጢት ውስጥ ጨመረችውና …እንዳአመጣጦ ምንም ሳትናገር ወጥታ ሄደች፡፡
እኔም ደንዝዤ ስለነበረ የምታርገውን በፅሞና ከመታዘብ በዘለለ አንደበቴን አላቅቄ ቃላት ማውጣት አልቻልኩም..ምን እየተፈጠረ ነው..?እውነት እንዳለችው ይህ መድሀኒት እናቴን ይፈውሳት ይሆን…..?ነው ወይስ እያሾፈችብኝ ይሆን…..?እንደዛማ ከሆነ በህይወቷ ወስናለች ማለት ነው፡፡እዛው የቢሮዋ ወንበር ላይ እንደተቀመጠች በእነዚህ መዳፎቼ አንገቷን ፈጥርቄ ፀጥ ነው የማደርጋት ፡፡….በውስጤ ዛትኩ
በተጋደምኩበት ይሄንን እና የመሳሰሉትን ግትልትል ሀሳቦች እያሰብኩ ሳይታወቀኝ እንቅልፍ ይዞኝ ጭልጥ ብሎ ነበር ለካ ፡፡አይፈረድብኝም የሶስት ሙሉ ቀን እንቅልፍ ነው ያለብኝ፡፡
‹‹…ፀጋ …የእኔ ልጅ››የሚለው ከገነት ከመላዕክት አንደበት የሚፈስ የሚመስል ጡዑም ዜማ ያለው የእናቴ የጥሪ ድምጽ ነበር ከእንቅልፌ የቀሰቀሰኝ… ደንግጬ ከተጋደምኩበት የሆስፒታል አልጋ በርግጌ በመውረድ ወለሉ ላይ እናቴ ፊት ለፊት ተገተርኩ
‹‹..አረ ተረጋጋ የእኔ ጌታ..››ጥርት ያለ ንፅህ የእናቴ ድምፅ..
ማመን አልቻልኩም፡፡በስነስርአት ትራስ እንኳን መንተራስ ሳያስፈልጋ ቁጭ ብላለች፡፡ምንም በበሽታ የመድከም ምልክት በፊቷ አይታይም፡፡
‹‹እማ ደህና ነሽ…..?ተሸለሽ…..?አሁን ምን ይሰማሻል..?››በጥያቄ አጣደፍኳት
‹‹ይሄው እንደምታየው በጣም ደህና እና ፍፅም ጤነኛ ሆኜ ነው የተነሳሁት፡፡ይገርምሀል ለሊ,ት ተኝቼ ጠይም መላዕክ መጥታ ከጭንቅላቴ አንስታ መላ አካላቴን ስትዳብሰኝ ነበር…እግዜያብሄር ያአንተ ፀሎት ሰምቶ ምሮኛል መሰለኝ፡፡››አለቺኝ በተፍለቀለቀ የደስታ ድምፀት
ተንጠራራውና አቀፍኳት ፡፡ግንባሯን …ጉንጮን …አፍንጫዋን እያፈራረቅኩ ሳምኳት ‹‹…አዎ እማ ድነሻል…እግዜያብሄር ይመስገን ተሳክቶልናል…ልጅቷ እንዳለችው ማድረግ ችላለች…ምትገርም ሴት ነች፡››
‹‹ስለማን ነው የምታወራው..?›› አለችኝ መቀባዠሬ ስላልገባት
‹‹አይ በህልሜ አየዋት ስላልሽው መላዕክ ነው ማወራው….ስላዳነችሽ መላአክ››አልኩና ርዕሱን አስቀየርኳት
‹‹አዎ እግዜር ነው የላከልኝ..ሄድ አሁን ሀኪም ጥራልኝ››
‹‹ምነው .. ..?የሚያምሽ ቦታ አለ እንዴ..?›› በድንጋጤ ጠየቅኳት
‹‹አረ በፍጽም… ይሄን ግሉኮስ ከላዬ እንዲነቅሉልኝ ነው…ሽንት ቤት መሄድ ፈልጋለው ›› ስትለኝ..ሮጬ ወጣውና በ10 ደቂቃ ውስጥ ተረኛውን ዶክተር አስከትዬ መጣው፡፡ይሄ ዶክተር እናቴ ሆስፒታል ከገባች ቀን ጀምሮ በዋናነት ስለጤናዋ ይከታተላት የነበረው ስለነበር እንዳያት ደነገጠ..በጣምም ግራ ተጋባ..ከግምቱ ውጭ የሆነ ሁኔታ ላይ ሆና ነው ያገኛት .
‹‹ማህሌት ምን ይሰማሻል. .?››
‹‹ፍጽም ጤነኝነት››
በጣም ጥሩ ..አሁን ወደቤት ከመሄድሽ በፊት ሙሉ ምርመራ ማድረግ አለብን ..››አለና ጉሉኮሱን ከእጇ ላይ በማለያየት ወጥቶ ሄደ …እኔም እሱ ለምርመራ ሚገለገልባቸውን መሳሪያዎች ይዞ እስኪመጣ ድረስ ስልኬን አወጣውና ለአያቴ ደወልኩለት…
‹‹ሄሎ አባ የት ነህ.?››
‹‹የት እሆናለው ልጄ… ቤተክርስቲያን ነኝ…ምነው ልጄ ባሰባት እንዴ .?›› ስብርብር ባለ ተስፋ የቆረጠ ደካማ ድምፅ ጠየቀኝ
‹‹አረ አባ ፍፅም ደህና ነች…ፀሎትህን ከጨረስክ ቀጥታ ወደሀስፒታል ና ››
‹‹አሟታል ማለት ነው ..መች አጣውት …እግዜያብሄር ዘንድሮ ሊያዋርደኝ ነው››አምላኩ ፊት መቆሙን እንኳን ዘንግቶ ተነጫነጨ
‹‹እወነቴን ነው አባ …ቆይ እንደውም…›› ብዬ ስልኩን ከጆሮዬ ላይ አነሳውና ለእናቴ አቀበልኳት ..የጠራ እና የነቃ ድምፆን በስልክ ከሰማ ቡሃላ በደስታ ሰክሮ እልልታውን ሲያቀልጠው በስልኩ ውስጥ ተሰማኝ…በዚህ እድሜው ልጁ ስትሞት አይቶ ባለመሳቀቁ ውስጤን ሀሴት ተሰማው …ቢያንስ ለጊዜው ይደሰት ..
እስከአራት ሰዓት መደረግ ያለበት ምርመራ ሁሉ ተደርጎላት ተጠናቀቀ..ውጤቱም ዶክተሮቹን በጣም ያስደመመ እና የበፊቱን የምርመራ ውጤት እንዲጠራጠሩ ያደረገ ነበር…እኔም ስለሆነው ነገር በውስጤ አፍኜ አብሬያቸው ከማደነቅ ውጭ ምንም ነገር ትንፍሽ ማለት አልቻልኩም…አልፈለኩምም፡፡
አዲሱ የህክምና ውጤት እንደሚያሳየው የእናቴ በሽታ ሙሉ በሙሉ የጠፋ ባይንም ደረጃው ግን 50 ፐርሰንት ወደኃላ የተመልሰል ነበር…ይህ ማለት ደግሞ ዋናው ሀኪምም እንዳረጋገጠልኝ በቅርብ ጊዜ ትሞታለች የሚለው ስጋት በአስተመማኝ ሁኔታ እንደተወገደ ነው፡፡
እንዴት እንደሆነ ባይገባኝም በእናቴ ላይ ተአምር ተፈፅሟል …ሙሴ የእስራኤልን ባህር በበትሩ ከፍሎ ወገኖቹን ያሻገራቸውን አይነተ ተአምር….አስራሁለት አመት ደም ሲፈሳት የነበረች ሴት የክርስቶስን የልብስ ጫፍ በእምነት ዳብሳ ከህመሞ ፈውስ ያገኘችበትን አይነት ተአምር ፡፡እርግጥ ታአምሩ ጅምር ነው…ምን አልባት በዚሁ የሚቀጥል ከሆነ ሙሉ በሙሉ ልትፈወስና እኛንም ይበልጥ ልታስደምመን ትችል ይሆናል፡፡
በሰተመጨረሻ ለመሄድ ዝግጅታችንን እንዳጠናቀቅን ወደዋናው ዶክተር ቀረብኩና ‹‹አመሰግናለው ዶክተር..ሁላችሁንም እግዜር ይስጥልኝ አልኩ››
‹‹ኦኬ ..ያ ማለት ለህይወታችን መስጋት አይጠበቅብንም ማለት ነው..?››
‹‹ማለት . ..?አልገባኘም ..?››
‹‹እንደምትገለን በርግጠኘነት ዝተህብን ነበር…አሁን እናትህ በከፊልም ቢሆን በመዳኗ ለጊዜው የተረፍን ይመስለኛል››አለኝ ፈገግ እያለ
አንገቴን አቀረቀርኩ‹‹በጣም አዝናለው…እናቴ ለእኔ መላ ነገሬ ስለነበረች አብዝቼው ነበር…ያን ያህል ስለታገሳችሁኝ ውለታችሁን መቼም አረሳውም..››
‹‹አረ ስቀልድህ ነው..እኔም ሆንኩ ባለደረቦቼ በወቅቱ የነበርክበትን ሁኔታ በደንብ ስለተረዳን ምንም አይነት ቅሬታ እልተሰማንም …ነገሩን ያነሳውልህ እንዲሁ ልቀልድ ብዬ ነው ›አለኝ
እናቴን በጓደኛቼ በዘመድና በጎረቤት ሰዎች አሳጅቤ እባቴ ስንደርስ አምስት ሰዓት ሆኖ ነበር… እናቴን ወደጆሮዋ ተጠግቼ የምሄድበት ቦታ እንዳለና ልቆይ እንደምችል ነግሬት ከአጀብ ውስጥ ወጥቼ ወደሆስፒታል ተመለስኩ …ከተቻለ ዶክተሯን ለማግኘት ፤ ከለበላዛ እንዴት እዳማገኛትና ከዛም አልፎ ስለማንነቷ መረጃዎችን ከገኘው ለማጣራት…
ምክንያቱም ስለእሷ በአዕምሮዬ ውስጥ የሚጉላሉ ጥያቄዎች ከቁጥጥር ውጭ እያደረጉኝ እና መንፈሴን ክፉኛ እየረበሹት ነው.
1/ይቺ ዶክተር ማነች....?የትኛው ከተማ ወይም የትኛው ገጠር ተወልዳ የትኛው ዩኒቨርሲቲ ገብታ ተምራ እዴት እዚህ ተማድባ መጣች..?
2/እንዲህ አይነት ከሳይንስ አቅም በላይ የሆነ ህምምን ለመፈወስ የሚያስችል የባህል ህክምና ጥበብን በዚህ ዕድሜዋ እንዴት ልትካንበት ቻለች;..?››
3/በምን አይነት ተአምራዊ አጋጣሚ ሄስፒታሉ ለመስራት በተመደበች በመጀመሪያው ቀን የመጀመሪያዋ ታካሚዋ እናቴ ልትሆን ቻለች..?
2/ከእኔ እፈልገዋለው ያለችው በውለታዋ ምላሽ እንድከፍል የሚጠበቅብኝ ምንድነው....?ብር እንዳልሆነ እርግጠኛ ነኝ ፡፡አንገቷ ላይ ያጠለቀችው እባብ የመሰለ ጥምዝ ወርቅ እና ጆሮዋ ላይ ያንጠለጠለችው የከበረ ጌጥ የኑሮ ደረጃዋን ያሳብቅባታል፡፡የባህል መድሀኒት በሆስፒታል ቅጥር ግቢ በድብቅ እየቸረቸረች ገንዘብ የምትሰበስብ አይነት ሰው አይደለችም..አዎ በዛ እርግጠኛ ነኝ ፡፡ግን ምንም እንዳደርግላት ብትጠይቀኝ ግድ የለኝም…እራስህን አጥፋልኝ ብትለኝም አደርገዋለው…
👍5
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ_ጉዞ
:
#ክፍል_አስራ_አራት
:
✍ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
....ቀጥታ ወደቤቴ በመሄድ ፋንታ ብቻዬን ሆኜ በፀጥታ ወደምተክዝበት ቦታ ነበር የተጓዝኩት፡፡ወደቢሾፍቱ ሀይቅ ሄድኩና ቁጥቆጦ ጥቅጥቅ ካለበት ቦታ ሀይቁ ዳር ላይ ወደሚገኝ ገዘፍ ካለ የድንጋይ አለት ላይ ቁጭ ብዬ አይኖቼን አስፈሪው እና ዙሪያውን በተራራ በተከበበው ሀይቅ ላይ ተክዬ ማሰላሰል ጀመርኩ .፡፡ሙሉ አዕምሮዬን የሞላችው ዶክተሯ ነች…እኔ እንጃ አላውቅም በውስጤ ህይወቴ ሙሉ በሙሉ እንደሚቀየር እና እስከአሁን ስሄድበት ከነበረበት መንገድ ፍፅም በተቃራኒና በማይገመት አይነት መስመር መጎዝ እንደምጀምር እየተሰማኝ ነው፡፡ከሀሳቤ ሳልፈልግ ያናጠበኝ ከቆጥኞቹ ስር የሚሰማዋ መንሾካሾክ ነው፡፡ሰው መጥቶ ፀጥታዬን ሊረብሸው ነው እንዴ ? ብዬ ትኩረቴን ከሀይቁ ወደቁጥቆጦው ስመልስ ያልጠበቅኩት ነገር አየው …..ግዙፍ ዥንጉርጉር ጥቁር እባብ ሽልልል እያለ ከቋጥኙ ውስጥ ቅጠሎችንና ቅርንጫፎቹን እየገላለጠ ወደ እኔ አቅጣጫ እየተሳባ እየመጣ ነው..
ወደእኔ በመገስገስ ላይ ያለውን እባብ ምላሱን በደም ስሬ ሰክቶ መርዙን ወደውስጤ ለመትፈት የቆመጠ በሚያስመስለበት ሁኔታ ጭንቅላቱን በአየር ላይ አንሳፎ አስፈሪውን ሹል ምላሱን ትሪዕታዊ በሆነ ሁኔታ ሲያወዛውዛቸው እያየው ነው፡፡ በድንጋጤም በመገረምም ከተቀመጥኩበት ቋጥኝ በቅልጥፍና ተነሳውና ዙሪያ ገባዬኝ ማቃኘት ጀመርኩ… ጭንቅላቱን ብዬ የምገላግልበት ደህና ዱላ ነገር ፍለጋ …ያን ያህል አስተማማኝ ባይሆንም አንድ ሁለት ክንድ የሚረዝም ደረቅ እንጨት አገኘውና አፈፍ አድርጌ አነሳውና አስተካክዬ ያዝኩትና ለፍልሚያ ተዘጋጀው…….፡፡
በእኔ እና በእባቡ መካከል ያለው ክፍተት ከሁለት ሜትር አይበልጥም…እኔም እንዴት አድርጌ ላጥቃው እያልኩ እስትራቴጂ ሳወጣ 3 የሚሆኑ ደቂቃዎች አለፉ …እባቡም ከእኔ ተመሳሳዩን እያሰበ ይመስለኛል፡፡ከዛ ቀድሞ ያጠቃል ብዬ በምጠብቅበት ጊዜ በሚገርም ፍጥነት ተወርውሮ ወደመጣት ዞረና ተስፈንጥሮ ቁጥቋጦው ውስጥ ተመልሶ ገባ ፡፡ድላዬን እንደቀሰርኩ ተከተልኩት…ሊያመልጠኝ አይገባም..ደረስኩና ቁጥቋጦውን በጥንቃቄ ስገላልጥ በዛኛው ወገን ያልጠበቅኩት ነገር አያው ..ድንጋጤዬ ጨመረ.. ፈጣን ውሳኔ ወሰንኩ ..ቁጥቆጦውን በግራ በኩል አልፌ ተጠምዘዝኩና ስሮ ደረስኩና ወገቧን በአንድ እጄ አቅፌ አንጠለጠልኩና ከቁጥቆጦ ውስጥ አርቄ በመውሰድ መልሼ አስቀመጥኳት..
-ምን እያደረክ ነው?በሳቅና በመኮሳተር መሀል ባለ ስሜት ጠየቀቺኝ፡፡
-አንቺው ንገሪኝ እንጄ .እዚህ ምን እያደረግሽ ነው... ? እንዴት መጣሽ ..?.ለምን መጣሽ..?
-አንተን ለማግኘት ነዋ የመጣውት
-እኔ እዚህ እንዳሆንኩ ማን ነገረሽ… ? ውይ ይቅርታ ለካ አንቺ ነሽ››
-አዎ እኔ ነኝ…ግን ምን አየሆንክ ነው ዱላው ለማን ነው ?
-ባክሽ አንድ እባብ ሊያጠቃኝ ነበር …ግን ሀሳቡን ቀይሮ ወደእዚህ ቋጥኝ ገባብኝ … አንቺንም ሊያጠቃሽ ይችል ነበር
-እኔን እንኳን አያጠቃኝም?
-ለምን ?
-ያየኸው እባብ እራሴው ነበርኩ….እራሴን በራሴ እንዴት ላጠቃ እችላለው?፡፡
-ቀልዴን እንኳን አይደለም…ጭንቅላቱን ማለት ነበረብኝ››
-ለምን.?
-እባብ ደግሞ ለምን ይባላል ? የሰው ልጅ እና እባብ ለዘመናት ያላቸውን ጠብ እያወቅሽ… ? ለማንኛውም ነይ ብዬ ቀድሞ ወደነበርኩበት ቆጥኝ ድንጋይ ይዤት ሄድኩና ቀድሜት ተቀመጥኩ ተከተለቺኝና ከገጎኔ ተቀመጠች፡፡
-እኔ ግን ስለሰው እና እባብ ግንኙነት ተቃራኒውን ነው የማውቀው …በማለት ወደ አቋረጠነው ውይይት መለሰችን
-እንዴት ማለት እስኪ አስረጂኝ አልኳት ? ይህቺ ተምረኛ ልጅ ሳለስበው ባገኘዋት ቅፅበት የመጀመሪያ ውይይታችን ስለእባብ የመሆኑ አጋጣሚ ገርሞኝ፡፡
-እሷ ኮስተር ብላ ማብራራት ጀመረች፡፡
‹‹የእባብና የሰው ልጅ እውቅናም ሆነ ልባዊ ወዳጅነት ጥንታዊና መሰረት ያለው ነው፡፡የሰው ልጅ አግዜያብሄር በመልኩና በሀምሳሉ ፈጠረው፡፡የዘን ጊዜ ከጦጣ ወይም ከዝንጀሮ ብዙም የማይሻል ነበር፡፡አንድ ነገር በቃ ልክ እንደ እኛ እና እንደ እግዜያብሄር ከፈጣራቸው ነገሮች መካከል መናገር የሚችል ቢሆንም ከእኛ እኩል ግን የማሰብ ጥበብ አልነበረውም፡፡እግዜያብሄር እንደዛ እንዲሆን አልፈቀደም ነበር፡፡በዚህ ጊዜ የእኔ አባት ቀዳሚው እባብ በውስጥ ሀዘኔታ ገባው፡፡››
-ቆይ ነገሮችን ግልጽ እያደረግሺልኝ ሂጂ..እያወራሽ ያለሽውን እያስተዋልሽ ነው…እባብ ነኝ እያልሺኝ ነው…የሰው ስጋ ለብሼ እንደሰው ማሰብና እንደሰው መሰራት የምችል ለየት ያልኩ ፍጡር ነኝ እያልሺኝ ነው ? ››
-ለየት ያልኩ ፍጡር መሆኔን ትጠራጠራለህ እንዴ?
-አረ በፍፅም …እባብ ነኝ ያልሺውን ነው ማመን ያልቻልኩት ?
-መብተህ ነው …በሂደት ታምናለህ …እስከዛው ዝም ብለህ ተረት እያወራውህ እንደሆነ አድርገህ ስማኝ ..
-እሺ ተስማምቼያለው..ቀጥይ
- እንዳልኩህ እኛ የእባብ ዝርያዎች ቀደምት ስንፈጠር እንደሰው ልጅ በእግዜያብሄር ሀምሳል ባንፈጠርም ቆሞ በእግር መሄድ፤መናገርና ፤ክፉውንና ደጉን፤ ሚጠቅምና ሚጎዳውን በጥበብ አንጥሮ እንደእግዚያሄር ከማሰብ ፀጋ ጋር ነበር የተፈጠርነው፡፡ይሁን እንጂ እግዚያብሄር በወቅቱ በዛ ነገር ደስተኛ አልነበረም፡፡
-ምን ማለትሽ ነው…? እግዚያብሄር አይደለም የፈጠራችሁ ?››
-አዎ እራሱ ነው ? ››
-ታዲያ እሱ አስቦና ፈቅዶ ከፈጠራችሁ ብኃላ እንዴት ደስተኛ ላይሆን ይችላል ? ፡፡
-በእኛ ብቻ እኮ አይደለም ቡኃላም እናንተን ከፈጠረ ቡኃላ ተፀፅቷል ፤ለዚህ ማስረጃ ደግሞ መፃፍ ቅዱሳችሁ‹‹እግዜያብሄር ሰውን በመፍጠሩ ተፀፀተ››ይላል፡፡
-ገባኝ ተዲያ እንዴት ሆናችሁ?....ጠየቅኳት በተረቷ ተመስጬ
-የእኛ ዝርያ ባለው ጥበብ ልክ እንደ እግዚያብሄር ክፉና ደጉን አንጥሮ ማሰብንና …ያሰበወንም ማድረግ በመቻሉ በወቅቱ በነበሩት ፍጥረታት ላይ ድንጋሬ ነበረ…
-ምን አይነት ድንጋሬ?
-አምላካችን የትኛው ነው.. የሚል?
-እና እግዚያብሄርነት… በጥበብና በፍጽሞና ማሰብን ብቻ ሳይሆን ዘላለማዊነትንና ሁለንተናዊአዋቂነትን መያዝ ይጠይቃል…
በዚህ መካከል የሰው ልጅ እግዜያብሄርን መስሎ ተፈጠረ…ከዛ አባቴም በእግዜያብሄር ላይ አቂሞ ነበርና ለዚህ የስው ልጅ ለሚባል አዲስ ፍጥረት እንዴት እግዜያብሄር እንደሚሆን ላስተምረው ብሎ በቀናነት ተነሳ…
-እርግጠኛ ነሽ በቀናነት ነው ?
-እግዚያብሄር ለመሆን የሚያስፈልጉ ሁሉን አዋቂነት እና ዘላለማዊነትን የሚያስገኙ በገነት አትብሉ ብሎ ያገዳቸውን እንዲበሉ በሴቷ በኩል ምክር ለገሳቸው፡፡…የመጀማሪያዋን በልተው ሁለተኛውን ከመድገማቸው በፊት ግን ሲርበተበቱ ደረሰባቸው …
-ምን ጠቀማቸው ታዲያ ከገነት እንዲባረረ ምክንያት ነው የሆናቸው ? ፡፡..የእኔ አስተያየት ነበር፡፡
-እሱ የራሳቸው መንከርፈፍ ነው..ደግሞ እንዳለው ነው… ክፉና ደጉን ያወቁት አባቴ ብሉ ያለችውን እጽ ከበሉ ቡኃላ ነው ሁለተኛውንም ዕፅ በልተው ቢሆን ኖሮ ልክ እንደ እሱ ይሆኑ ነበር…አባራሪና ተባራሪ አይኖርም ነበር
-ያልገባኝ ነገር ታዲያ አባትሽ ማለቴ አባቡ ከዚህ ምን ይጠቀማል..እንደውም ሁለተኛ እግዚያብሄር በላዩ ላይ ይነግስ ነበር…
-አይ የአባቴ እቅድማ ሶስት እግዚያሄር እንዲኖር ነበር…
-እንዴት ሆኖ ?
-ከሄዋን ጋር ሚስጥራዊ ውለታ ነበራው፡፡አባቴ የሚፈልጋትን ሁለተኛዋን ዕጽ ለእሷ እና ለአዳም ስትቆርጥ ለእሱም ለሚስቱና ለልጁ የሚበቃ እንድታመጣለት፡፡ከዛ በሶስት ግዛቶች የተከፋፈለ ሶስት እግዜያብሄር ይኖር ነበር፡፡እቅዱ እንደዛ ነበር፡፡ከዛ ሲርበተበቱ ተያዙ እራሳቸውም
:
#ክፍል_አስራ_አራት
:
✍ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
....ቀጥታ ወደቤቴ በመሄድ ፋንታ ብቻዬን ሆኜ በፀጥታ ወደምተክዝበት ቦታ ነበር የተጓዝኩት፡፡ወደቢሾፍቱ ሀይቅ ሄድኩና ቁጥቆጦ ጥቅጥቅ ካለበት ቦታ ሀይቁ ዳር ላይ ወደሚገኝ ገዘፍ ካለ የድንጋይ አለት ላይ ቁጭ ብዬ አይኖቼን አስፈሪው እና ዙሪያውን በተራራ በተከበበው ሀይቅ ላይ ተክዬ ማሰላሰል ጀመርኩ .፡፡ሙሉ አዕምሮዬን የሞላችው ዶክተሯ ነች…እኔ እንጃ አላውቅም በውስጤ ህይወቴ ሙሉ በሙሉ እንደሚቀየር እና እስከአሁን ስሄድበት ከነበረበት መንገድ ፍፅም በተቃራኒና በማይገመት አይነት መስመር መጎዝ እንደምጀምር እየተሰማኝ ነው፡፡ከሀሳቤ ሳልፈልግ ያናጠበኝ ከቆጥኞቹ ስር የሚሰማዋ መንሾካሾክ ነው፡፡ሰው መጥቶ ፀጥታዬን ሊረብሸው ነው እንዴ ? ብዬ ትኩረቴን ከሀይቁ ወደቁጥቆጦው ስመልስ ያልጠበቅኩት ነገር አየው …..ግዙፍ ዥንጉርጉር ጥቁር እባብ ሽልልል እያለ ከቋጥኙ ውስጥ ቅጠሎችንና ቅርንጫፎቹን እየገላለጠ ወደ እኔ አቅጣጫ እየተሳባ እየመጣ ነው..
ወደእኔ በመገስገስ ላይ ያለውን እባብ ምላሱን በደም ስሬ ሰክቶ መርዙን ወደውስጤ ለመትፈት የቆመጠ በሚያስመስለበት ሁኔታ ጭንቅላቱን በአየር ላይ አንሳፎ አስፈሪውን ሹል ምላሱን ትሪዕታዊ በሆነ ሁኔታ ሲያወዛውዛቸው እያየው ነው፡፡ በድንጋጤም በመገረምም ከተቀመጥኩበት ቋጥኝ በቅልጥፍና ተነሳውና ዙሪያ ገባዬኝ ማቃኘት ጀመርኩ… ጭንቅላቱን ብዬ የምገላግልበት ደህና ዱላ ነገር ፍለጋ …ያን ያህል አስተማማኝ ባይሆንም አንድ ሁለት ክንድ የሚረዝም ደረቅ እንጨት አገኘውና አፈፍ አድርጌ አነሳውና አስተካክዬ ያዝኩትና ለፍልሚያ ተዘጋጀው…….፡፡
በእኔ እና በእባቡ መካከል ያለው ክፍተት ከሁለት ሜትር አይበልጥም…እኔም እንዴት አድርጌ ላጥቃው እያልኩ እስትራቴጂ ሳወጣ 3 የሚሆኑ ደቂቃዎች አለፉ …እባቡም ከእኔ ተመሳሳዩን እያሰበ ይመስለኛል፡፡ከዛ ቀድሞ ያጠቃል ብዬ በምጠብቅበት ጊዜ በሚገርም ፍጥነት ተወርውሮ ወደመጣት ዞረና ተስፈንጥሮ ቁጥቋጦው ውስጥ ተመልሶ ገባ ፡፡ድላዬን እንደቀሰርኩ ተከተልኩት…ሊያመልጠኝ አይገባም..ደረስኩና ቁጥቋጦውን በጥንቃቄ ስገላልጥ በዛኛው ወገን ያልጠበቅኩት ነገር አያው ..ድንጋጤዬ ጨመረ.. ፈጣን ውሳኔ ወሰንኩ ..ቁጥቆጦውን በግራ በኩል አልፌ ተጠምዘዝኩና ስሮ ደረስኩና ወገቧን በአንድ እጄ አቅፌ አንጠለጠልኩና ከቁጥቆጦ ውስጥ አርቄ በመውሰድ መልሼ አስቀመጥኳት..
-ምን እያደረክ ነው?በሳቅና በመኮሳተር መሀል ባለ ስሜት ጠየቀቺኝ፡፡
-አንቺው ንገሪኝ እንጄ .እዚህ ምን እያደረግሽ ነው... ? እንዴት መጣሽ ..?.ለምን መጣሽ..?
-አንተን ለማግኘት ነዋ የመጣውት
-እኔ እዚህ እንዳሆንኩ ማን ነገረሽ… ? ውይ ይቅርታ ለካ አንቺ ነሽ››
-አዎ እኔ ነኝ…ግን ምን አየሆንክ ነው ዱላው ለማን ነው ?
-ባክሽ አንድ እባብ ሊያጠቃኝ ነበር …ግን ሀሳቡን ቀይሮ ወደእዚህ ቋጥኝ ገባብኝ … አንቺንም ሊያጠቃሽ ይችል ነበር
-እኔን እንኳን አያጠቃኝም?
-ለምን ?
-ያየኸው እባብ እራሴው ነበርኩ….እራሴን በራሴ እንዴት ላጠቃ እችላለው?፡፡
-ቀልዴን እንኳን አይደለም…ጭንቅላቱን ማለት ነበረብኝ››
-ለምን.?
-እባብ ደግሞ ለምን ይባላል ? የሰው ልጅ እና እባብ ለዘመናት ያላቸውን ጠብ እያወቅሽ… ? ለማንኛውም ነይ ብዬ ቀድሞ ወደነበርኩበት ቆጥኝ ድንጋይ ይዤት ሄድኩና ቀድሜት ተቀመጥኩ ተከተለቺኝና ከገጎኔ ተቀመጠች፡፡
-እኔ ግን ስለሰው እና እባብ ግንኙነት ተቃራኒውን ነው የማውቀው …በማለት ወደ አቋረጠነው ውይይት መለሰችን
-እንዴት ማለት እስኪ አስረጂኝ አልኳት ? ይህቺ ተምረኛ ልጅ ሳለስበው ባገኘዋት ቅፅበት የመጀመሪያ ውይይታችን ስለእባብ የመሆኑ አጋጣሚ ገርሞኝ፡፡
-እሷ ኮስተር ብላ ማብራራት ጀመረች፡፡
‹‹የእባብና የሰው ልጅ እውቅናም ሆነ ልባዊ ወዳጅነት ጥንታዊና መሰረት ያለው ነው፡፡የሰው ልጅ አግዜያብሄር በመልኩና በሀምሳሉ ፈጠረው፡፡የዘን ጊዜ ከጦጣ ወይም ከዝንጀሮ ብዙም የማይሻል ነበር፡፡አንድ ነገር በቃ ልክ እንደ እኛ እና እንደ እግዜያብሄር ከፈጣራቸው ነገሮች መካከል መናገር የሚችል ቢሆንም ከእኛ እኩል ግን የማሰብ ጥበብ አልነበረውም፡፡እግዜያብሄር እንደዛ እንዲሆን አልፈቀደም ነበር፡፡በዚህ ጊዜ የእኔ አባት ቀዳሚው እባብ በውስጥ ሀዘኔታ ገባው፡፡››
-ቆይ ነገሮችን ግልጽ እያደረግሺልኝ ሂጂ..እያወራሽ ያለሽውን እያስተዋልሽ ነው…እባብ ነኝ እያልሺኝ ነው…የሰው ስጋ ለብሼ እንደሰው ማሰብና እንደሰው መሰራት የምችል ለየት ያልኩ ፍጡር ነኝ እያልሺኝ ነው ? ››
-ለየት ያልኩ ፍጡር መሆኔን ትጠራጠራለህ እንዴ?
-አረ በፍፅም …እባብ ነኝ ያልሺውን ነው ማመን ያልቻልኩት ?
-መብተህ ነው …በሂደት ታምናለህ …እስከዛው ዝም ብለህ ተረት እያወራውህ እንደሆነ አድርገህ ስማኝ ..
-እሺ ተስማምቼያለው..ቀጥይ
- እንዳልኩህ እኛ የእባብ ዝርያዎች ቀደምት ስንፈጠር እንደሰው ልጅ በእግዜያብሄር ሀምሳል ባንፈጠርም ቆሞ በእግር መሄድ፤መናገርና ፤ክፉውንና ደጉን፤ ሚጠቅምና ሚጎዳውን በጥበብ አንጥሮ እንደእግዚያሄር ከማሰብ ፀጋ ጋር ነበር የተፈጠርነው፡፡ይሁን እንጂ እግዚያብሄር በወቅቱ በዛ ነገር ደስተኛ አልነበረም፡፡
-ምን ማለትሽ ነው…? እግዚያብሄር አይደለም የፈጠራችሁ ?››
-አዎ እራሱ ነው ? ››
-ታዲያ እሱ አስቦና ፈቅዶ ከፈጠራችሁ ብኃላ እንዴት ደስተኛ ላይሆን ይችላል ? ፡፡
-በእኛ ብቻ እኮ አይደለም ቡኃላም እናንተን ከፈጠረ ቡኃላ ተፀፅቷል ፤ለዚህ ማስረጃ ደግሞ መፃፍ ቅዱሳችሁ‹‹እግዜያብሄር ሰውን በመፍጠሩ ተፀፀተ››ይላል፡፡
-ገባኝ ተዲያ እንዴት ሆናችሁ?....ጠየቅኳት በተረቷ ተመስጬ
-የእኛ ዝርያ ባለው ጥበብ ልክ እንደ እግዚያብሄር ክፉና ደጉን አንጥሮ ማሰብንና …ያሰበወንም ማድረግ በመቻሉ በወቅቱ በነበሩት ፍጥረታት ላይ ድንጋሬ ነበረ…
-ምን አይነት ድንጋሬ?
-አምላካችን የትኛው ነው.. የሚል?
-እና እግዚያብሄርነት… በጥበብና በፍጽሞና ማሰብን ብቻ ሳይሆን ዘላለማዊነትንና ሁለንተናዊአዋቂነትን መያዝ ይጠይቃል…
በዚህ መካከል የሰው ልጅ እግዜያብሄርን መስሎ ተፈጠረ…ከዛ አባቴም በእግዜያብሄር ላይ አቂሞ ነበርና ለዚህ የስው ልጅ ለሚባል አዲስ ፍጥረት እንዴት እግዜያብሄር እንደሚሆን ላስተምረው ብሎ በቀናነት ተነሳ…
-እርግጠኛ ነሽ በቀናነት ነው ?
-እግዚያብሄር ለመሆን የሚያስፈልጉ ሁሉን አዋቂነት እና ዘላለማዊነትን የሚያስገኙ በገነት አትብሉ ብሎ ያገዳቸውን እንዲበሉ በሴቷ በኩል ምክር ለገሳቸው፡፡…የመጀማሪያዋን በልተው ሁለተኛውን ከመድገማቸው በፊት ግን ሲርበተበቱ ደረሰባቸው …
-ምን ጠቀማቸው ታዲያ ከገነት እንዲባረረ ምክንያት ነው የሆናቸው ? ፡፡..የእኔ አስተያየት ነበር፡፡
-እሱ የራሳቸው መንከርፈፍ ነው..ደግሞ እንዳለው ነው… ክፉና ደጉን ያወቁት አባቴ ብሉ ያለችውን እጽ ከበሉ ቡኃላ ነው ሁለተኛውንም ዕፅ በልተው ቢሆን ኖሮ ልክ እንደ እሱ ይሆኑ ነበር…አባራሪና ተባራሪ አይኖርም ነበር
-ያልገባኝ ነገር ታዲያ አባትሽ ማለቴ አባቡ ከዚህ ምን ይጠቀማል..እንደውም ሁለተኛ እግዚያብሄር በላዩ ላይ ይነግስ ነበር…
-አይ የአባቴ እቅድማ ሶስት እግዚያሄር እንዲኖር ነበር…
-እንዴት ሆኖ ?
-ከሄዋን ጋር ሚስጥራዊ ውለታ ነበራው፡፡አባቴ የሚፈልጋትን ሁለተኛዋን ዕጽ ለእሷ እና ለአዳም ስትቆርጥ ለእሱም ለሚስቱና ለልጁ የሚበቃ እንድታመጣለት፡፡ከዛ በሶስት ግዛቶች የተከፋፈለ ሶስት እግዜያብሄር ይኖር ነበር፡፡እቅዱ እንደዛ ነበር፡፡ከዛ ሲርበተበቱ ተያዙ እራሳቸውም
👍4❤1👎1