አትሮኖስ
280K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
461 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ
:
#ክፍል_ሁለት
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

...ኢትዬጵያን በዩቶፐያ ፅንሰ ሀሳብ ዳግም መገንባት ከአያቴ የወረስኩት ህልሜ እና ዓላማዬ እንደሆነ ነግሬያችኃለው …ግን እንዴት አድርጌ ነው የማሳካው …?እንደማሳክው የማምነው ከራሴ በላይ በሚስቴ እምነት ስላለኝ ነው፡፡ሚስቴ …የዋናው የታሪኬ ማጠንጠኛ እሷ ነች፡፡እሷ ደግሞ መንፈስ ነች፡፡ገራሚ መንፈስ፡፡አስፈሪ መንፈስ፤ታሪካዊ መንፈስ፤አፍዛዥ መንፈስ…ሁሉን አድራጊ ፈላጭ ቆራጭ መንፈስ፡፡አዎ ስለእሷ የምነግራችሁ ነገር ቢኖር የደረስኩበትን እና ያወቅኩትን ብቻ ነው፡፡ያንን ስላችሁ በቃ ስለእሷ የማትነግረን ጥቂት ነዋ..?››ብላችሁ ታስቡ ይሆናል፡፡አይደለም:: እንደውም በተቀራኒው የምነግራችሁ ከእሷ ታሪክ አንጻር ጥቂቱን ግን በእኛ በሰውኛ ልኬት ከጆሮአችን የመስማት አቅም በላይ ከአይኖቻችንም የማየት ጉልበት በላይ በሆነ መጠን ነግራችሆለው፡፡
ምክንቱም ይህቺ ፍቅሬ ከሰፈር ጎረምሳነት በአንዴ ስለዓለም መፅአዊ እጣ ሚያስብና ለዛም የሚሰራ የሚተጋ ሰው አድርጋ መልሳ ዳግመኛ የፈጠረቺኝ ሴት ነች፡፡እሷ ደፋርም ገራሚም ፍጡር ነች፡፡ ሁሉ ነገር የማድረግ አቅም እንዳላት አምናለው፡እንዴት አድርጌ የምታደርገው ነገር ሁሉ የምትለውን ሁሉ አምናታለው፡፡የማምናት ጅል ሆኜ አይደልም፡፡በአፍቃሪነቴም ዓየነ-ልቦናይ ታውሮም አይመስለኝም፤የምትሰራቸውን የእጆቾን ተአምራቶች በአይኖቼ ደጋግሜ ሳላየው ላለማመን አልችልም፡፡ ግን ደግሞ ሚስጥሯን ሁሉ ትነግረኛለች ብዬ አላስብም…ከእኔ የተደበቀ የሆነ ዕቅድ ያላት መስሎ ይሰማኛል ፡፡ቢሆንም ደፍሬ ጠይቄያት አላውቅም፡፡
ግን የምታወራው ስለአፈቀርካት ሴት ነው ወይ..? ካላችሁኝ አዎ ስለእሷው ነው፤ግን እንደምታውቋት አይነት ሴት ብቻ አይደለችም… መንፈስም ጭምር ነች፡፡ምን አይነት መንፈስ..?እሱን ወደ ፊት አስረዳችሆለው….
ይህቺን ሴት ያገኘዋት በተለየ አጋጣሚ ነው፡፡በህይወቴ የመጨረሸውን ሀዘን ባዘንኩበት ቀን …የመጨረሻውን እጦት ባጣውበት ቀን…ወደ ልቤ ደም የሚወስዱና የሚመልሱ ትላልቅ የደም ስሮች የተበጠሱ የመሰለኝ ቀን፡፡አዎ የዛን ቀን ነበር ያገኘዋት …፡፡እንዴት እጦቴን በተአምሮ መለሰችልኝ…ሀዘኔን በድንቅ ስራዋ ወደምስራች ቀየረችልኝ…የተበጣጠሱትን የልብን ደም ስሮች ቀጣጥላ ለሞት ከቆረጥኩበት ስሜት አውጥታ መኖርን እንድናፍቅ አደረገቺኝ እና በዛኑ ቅፅበት ይህቺን ሴት ደነዘዝኩላት….፡፡
ወዲያው ነበር እግሯ ስር ተንበርክኬ እንዳፈቀርኳት የነገርኳት..ይቺን ሴት ፍቅሬን እንደተቀበለች ነበር ትንፋሽ ሳልሰጣት እንድታገባኝ የጠየቀኳት፡፡አግቢኝ ስላት ቤት አልነበረኝም .አግቢኝ ስላት ስራ አልነበረኝም…አረ አግቢኝ ስላት የሀይስኩል ትምህርቴን እንኳን አልጨረስኩም…አግቢኝ ስላት የማግባት ዕቅድም አልነበረኝም….አግቢኝ ስላት ዕድሜዬ እንኳን 18 ሊደፍን ገና 3 ወራቶች ይቀሩት ነበር..
ይህ ሁሉ ቢሆንም ዳሩ እንድታገባኝ ስጠይቃት
-እንዳገባህ የጠየቅከኝ ውለታ ስለዋልኩልህ ነው ወይስ ስላፈቀርከኝ›ነበር ያለቺኝ
-ሁለቱም ምክንያት ነው፡፡-መለስኩላት
-ይሁን የመጣውትም አንተን ለማግባት ስለሆነ ተቀብዬሀለው ››አለቺኝ
-አልገባኝ
-ቀስ ብሎ ይገባሀል ..ለማንኛውም ጥያቄህን ተቀብያለው ፡፡አገባሀለው፡፡
መልሶን ስሰማ ደንግጬ ነበር..እሺታዋን ስሰማ ፈዝዤ ነበር፡፡አዎ እሺታዋን አልጠበቅኩም ነበር፡፡
-ግን ቆይ የመጣውት ስትይ ከየት ነው የመጣሽው.?
ከዛኛው አለም ….ላለፈት መቶ አመት እዚህ አልነበርኩም፡፡
-ያው እየቀለደች ነው ብዬ
‹ከዛ በፊትስ?፡›ጠየቅኳት
-ከዛ በፊት አንድ አራት ጊዜ ተመላልሺያለው፡፡ፈርዶብኝ ጀግና ወዳለው፡፡በዚህ አካባቢ ማለቴ በኢትዬጵያ ጀግና መኖሩን ከሰማው በርሬ ለመምጣት ቀናትን አላባክንም›
-ይገርማል…አሁን ታዲያ ማን ተገኝቶ ነው የመጣሺው.?›
-ነገርኩህ አንተን..
-እኔን …እኔ ታዲያ እንዴት ነው ከሌላ አለም የሚመጣልኝ ጀግና የሆንኩት?››ጠየቅኳት ያው በቀልድ ቅላፄ
-አይ እስከአሁን እንኳን ጀግና አይደለህም ….ግን ጀግና የሚሆን ልብ ይዘሀል፡፡በሺ አመት አንዴ የሚገኝ ጀግና ልብ…ስለዚህ አገባሀለው፡፡ግን አንድ አላማ አለኝ ያንን እንዳሳካ ታግዘኛለህ …እርግጥ ለእኔም ብቻ ሳይሆን ለአንተም ይጠቅማል፡፡
-አረ ግድ የለም ፡፡ለአንቺ ብቻ የሚጠቅምም ቢሆን ያልሺኝን ሁሉ አደርገዋለው›አልኳት ከልቤ እንደማደርገው በውስጤ እየማልኩ
የእለቱ ንግግራችንም ሆነ ጠቅላላ ታሪኩ በዚህ አልተቆጨም ሙሉውን ወደፊት አወራችሆለው …አሁን ከዚያች የህይወት አጋጣሚ አክለፍልፋ ወስዳ እሷ እጅ ወይም ልብ ላይ እስክትጥለኝ ድረስ ያሰለፍኩትን የእኔንና የቤተሰቤን ታሪክ ልክ እንደቅምሻ በሚቀጥሉት ክፍል አወራችሁና ስጨርስ ወደመነሻዬ እመልሳችሆለው፡፡

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍3
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ
:
#ክፍል_ሶስት
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
....እናቴ ማለት….፨
ለእናቴ ያለኝ እይታ አምልኮ ደረጃ የደረሰ ዓይነት ነወ ፡፡ይሄን ቃል ስናገር በአላዋቂነት ስሜት ልቤን በትዕቢት አጨልሜ አይደለም፤በፍጽም ወይን
ም በእግዜያብሄር የፈጣሪነት ስልጣን ላይ እምነቴ የላላም ስለሆነም አይደለም፡፡አዎ ብቻ እንደዛ ማለት ስላለብኝ ነው፡፡እውነትም ስለሆነ ነው፡፡
የምፈራው እሷን ብቻ ነው፡፡የምሰማውም እንደዛው ፡፡እናቴን በአምስቱም የስሜት ህዋሳቶች ስጠቀም የመጨረሻውን ስሜት የማጣጥምባት ቅዱስ ጨረቃዬ ነች፡፡አፍንጫዬን ተጠቅሜ የመጨረሻው መሳጭ ሽታ ወደውስጤ የምምገው የእናቴን ጠረን ነው፡፡:በምላሴ ቀምሼ የምደነዝዛበት የመጫረሻው ጣፍጭ ጣዕም የእናቴ እጅ የነካው ምግብ ነው፡፡አይኖቼ ሲከፈቱ ሊመለከቷቸው የሚጓጉት የመጨረሻው መሳጭ ውበት የእናቴ ማንነት ነው፡፡በእጆቼ ሲዳሰሱ ስሜት የሚሰጡኝ ልቤን የሚያደነዝዘው የመጨረሻው ለስላሳ ልብ ነዛሪ ገላ የእናቴ ሰውነት ነው፡፡የመጨረሻው የሰማይ መላዕክት የሚደመሙበት አይነት ከያሬድ ዝማሬ የላቀው ጥኡመ ዜማ ከእናቴ አንደበት የሚወጣው ድምጽ ነው፡፡
እርግጥ ይሄ ስለእናቴ ያለኝ ስሜት የእኔ የተዛባ አመለካከት ሊሆነው ይችላል፤ቢሆንም ግድ የለኝም ፡፡እንደውም ይሄንን ስሜት ከውስጤ የሚያጠፋብኝን ጤንነት አልፈልገውም፡፡ለእኔ ዓለም ጠቅላላ ማለት እሷ ነች፡፡እሷ ብቻ ነች፡፡እሷ ብቻ ነች የምታወደኝ፡፡እሷ ብቻ ነች የምትኮራብኝ፡፡እሷ ብቻ ነች ውስጤን አንብባ ነገዬን በድፍረት የምትነግረኝ፡፡እሷ ብቻ ነች ያላትን በጠቅላላ ያለመሰሰት ልትሰጠኝ የማታንገራግር፡፡አሁን እርግጥ ከእናቴ በተጨማሪ ይህች አለም ሌላ እውነት እንዳለት ተረድቼያለው፡፡ሚስቴ …..
እናቴ ወላጄ ነች፡፡ከማይታወቀው አለም ለእናቶች ከእግዚያብሄር በተሰጠ የተፈጥሮዊ ፀጋ በመጠቀም ከሚስጥራዊው ዓለም መዛ አምጥታኝ በቅዱስ ማህፀኖ ዘጠኝ ወር ተንከባክባ ከረቂቅ ህዋስነት ወደ ሰዋዊ ፍጡርነት በመቀየር በሚዳሰሰው ዓለም ላይ እንድኖር ያደረገቺኝ እናቴ፡፡
አንድ ሴት ወደ ማህፀኗ ከገብት 5 ሚሊዬን በላይ የዘር ፍሬዎች መካከል አንዶ እድለኛ በሰበረችው እንቁላል ልጅ ይወለዳል፡፡እንዴት እኔ እንደዛ እድለኛ ሆንኩ..….?እንዴት ከአምሰት ሚሊዬን አንዶ እኔን የያዘች ሴል ተሳካላት…….?እዚህ ላይ የእናቴ አስተዋፅኦ ይኖርበት ይሆን ወይስ የፈጣሪ ፍቃድ….?፡፡የፈጣሪስ ከሆነ ምንድ ነው ምክንያቱ….? ምንድነውስ መስፈርቱ …….?፡፡
ለማንኛውም ይሄን ለጊዜው ልተወው…እናቴ ወደዚህ ምድር አመጣችኝ..ማለት ወለደቺኝ፡፡ይሄ ማኛውም እናት በእውቀትም ሆነ በደመነፍስ የምታደርገው ነገር ነው፡፡የእናቴ ብቃት፤የእናቴ ልዩ መሆን፤የእናቴ ፈጣሪነት ከዛ ቡኃላ የሚገለጽ ነው፡፡መጀመሪያ ወለደቺኝ ከዛ ቀጥላ ፈጠረቺኝ፡፡ቅደም ተከተሉ አዛባውባችሁ አይደል….?፡፡መፈጠር የነገር ሁሉ መጀመሪያ እንደሆነ ስቼው አይደለም፡፡ እናቴ ስትወልደኝ እንደማንኛውም ሰው ሰው ነበርኩ፡፡ግን ዝም ብሎ ስው፡፡እየዳህኩ ሰሄድ ምኔም ምኔም የማይጥም ሰው ነበርኩ፡፡
እራሴን ላስተዋውቃችሁ አይደል፡፡እራስን ማስተዋወቅ እንዴት ነበር.. ….?አዎ ሰዎች እራሳቸውን ማስተዋወቅ የሚጀምሩት ስማቸውን ከመናገር አይደል ….?፡፡ሰው እራስ ወዳድ የመሆኑን አንዱ ማስረጃ ይሄ ነው፡፡ በየምክንያቱ ስሙን መጥራት ስለሚወድ እራሱን ለሌላ እንግዳ ስው የማስተዋወቅ ስርአት ላይ ስምን ቅድሚያ መናገር የሚል ሀረግ አሰፈረ……፡፡
ማህሌት ትባላለች፡፡ማህሌት ገዳ፡፡የእናቴን ሙሉ ስም እየነገርኮችሁ ነው፡፡የእኔ ስም ደግሞ ፀጋ ፡፡ፀጋ ማህሌት ገዳ፡፡ሙሉ ስሜ እስከአያቴ ሲጠራ ነው፡፡የሴት ልጅ ነኝ፤ ለዛ ነው በእናቴ የምጠራው፡፡አባቴን አላውቀውም..እንዳለኝ እንኳን እርግጠኛ አይደለውም፡፡እንዲኖረኝም ፈልጌም ጠብቄም አላውቅም ፡፡የተወለድኩት በ1994 ዓ.ምህረት ነው፡፡ስንት ዓመቴ እንደሆነ ቆጥራችሁ ድረሱበት፡፡እጆቼን ከመሬት አላቅቄ በአየር ላይ በማወናጨፍ ፤በሁለት እግሮቼ ቆሜ ሰው እንደሚያደርገው መራመድ የቻልኩት አራት አመት ካለፈኝ ቡኃላ ነው፡፡ከዛ በፊት ልክ እንደዝንጀሮ ወይም ጦጣ ወይንም ደግሞ እንደተሳቢ እንስሳት ባለአራት እግር ተሳቢ ወይም ተንፎቃቂ ነበርኩ፡፡
እናቴ በዛን ወቅት በተለይ ሁለት ዓመት ካለፈኝ ቡኃላ መራመድ ባለመቻሌ በጣም ተጨንቃ የተለያዩ ቦታ በመውሰድ ዘመናዊውንም ሆነ ባህላዊውን ህክምና እንዳገኝ እና እንደሌሎች እኩዬቼ መራመድና መናገር እንድችል ሞክራ ነበር ፡፡ግን አንዳቸውም ምንም ሊፈይዱልኝ አልቻሉም ነበር፡፡በመጨረሻ እናቴ ተጨንቃ እኔን ማስጨነቁን ለማቆም ከወሰነችና እሰከማንነቴ ልትቀበለኝ ከቆረጠች ቡኃላ ነበር ድንገት ተስፈንጥሬ በመቆም መሄድ የቻልኩት፡፡እንዴት መራመድ ቻልኩ ታሪኩ እንዲህ ነው፡፡

💫ይቀጥላል💫

Like 👍 እያረጋቹ አደለም ያነበበ የተመቸው 👍
እያረጋቹ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍3
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ
:
#ክፍል_አራት
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
አራት አመት ካለፈኝ ቡኃላ አንድ ቀን አናቴ ከጓደኛዋ ጋር የገዛ ቤታችን ውስጥ ታወራለች
‹‹እንደው ስንቱ እያፈቀረሽ እኮ ሁኔታሽን እያየ ነው የሚሸሸሽ››ድንገት ነው ጓደኛዋ አስተያየት የሰነዘረችው
-ሁኔታዬ ምን ሆነ ?
-ያው የልጅሽ ሁኔታ ነዋ
-የልጄ ሁኔታ ምን ሆነ..?በቃ በማንም ሰው ላይ እንደሚያጋጥም የጤና መጓደል አራት አመት ቢሆነውም መናገርና መራመድ አልቻለም..እና ምን ይጠበስ …….?በንዴት እና በሚርገበገብ ድምፅ
-ቀስ በይ ምን ያስቆጣሻል…ለማለት የፈለኩት ሙሉ ህይወትሽን ለእሱ መስዋዕት አድርገሽ ሰጥተሸል ነው፡፡ልጅሽ ቢሆንም አንቺም ሰው ነሽና ለራስሽ ማሰብ መጀመር አለብሽ ልልሽ ፈልጌ ነው….ቀንም ሌትም ከእሱ ጋር ተቆራምደሽ መዋልና ማደሩን አቁሚና ለሰራተኛ ሰጥተሸው እንደድሮሽ ወጣ ወጣ በይ….ወደቢሮ ስራሽም ተመለሺ እያልኩሽ ነው፡፡
-እኔ ወንድ ያስፈልገኛል ብዬ ለማንም ተናግሬ አላውቅም፡፡ወንድ ለማግኘት ከእኔ በስተቀር ሌላ ሰው ሊረዳው የማይችለውን ልጄን ለሰራተኛ ጥዬ ተቆነጃጅቼ ለመውጣት ፍላጎቱ የለኝም፡፡ለምበላውና ለምጠጣው የሚሆን ብር አለኝ፡፡ስለዚህ አትልፊ ከአሁን ቡኃላ ባለው ህይወቴ ዋና አላማዬም ሆነ ቋሚ ስራዬ ልጄ ነው፡፡…እናቴ ፍርጥም ያለ መልስ ትመልስላታለች፡፡
-አይ ተስፋ ለሌለው ነገር እራስሽን መስዋዕት እንድታደርጊ ስለማልፈልግ ነው እንደዚህ የምልሽ..ደግሞ ለአባትሽም ብታስቢላቸው መልካም ነው::
እዚህ ላይ እናቴ ብትበሳጭም የጓደኛው ምክር ግን እንዲሁ ችላ ተብሎ የሚጣል አልነበረም፡፡በተለይ ለአባትሽ ብታስቢላቸው መልካም ነው ያለችው ዝም ብላ ከመሬት ተነሳታ አይደለም፡፡የእናቴ አባት ማለት አያቴ በእናቴ ላይ የነበረው ተስፋ እንዲህ ቀላልና ተራ የሚባ አይነት አልነበረም፡፡እሷ ላይ ብዙ ተስፋ ነበረው፡፡እናቷ በልጅነቷ ስለሞተች ከ10 አመቷ ጀምሮ ብቻውን ነው ያሳደጋት ፡፡ከዛን ጀምሮ ሚስት ላግባ አላለም….ከዛን ጀምሮ ለራሴ ምቾት ላስብ አላለም፡፡ጭንቀቱ እሷብቻ ነበረች፡፡ኢትዬጵዬ ይላታል፡፡አያቴ ሀገሩን ይወደል ፡፡ከሀገሩም እኩል ልጁን ይወዳል፡፡
አያቴ ኮረኔል ነው ፡፡በሀይለስላሴ የመጨረሻዎቹ ዘመን የውትድርናውን አለም ተቀላቅሎ በደርግ ሙሉ ከምስራቅ እስከሰሜን በተለያ አውደውጊያዎችና አገልግሎት ሰጥቶ ኢህአዲግ ሲገባ ጎደኞቹ ሲበተኑ አብሮ የተበተነ ግን ደግሞ እንደእድል ሆኖ ደህና ቤተሰብ ስለነበረው ወደትውልድ ከተማው ሲመለስ በመንደላቅ የሚያኖረው ንብረት ከቤተሰቦቹ በውርስ የጠበቀው ሰው ነው፡፡ እና አያቴ እሱ የጀመረውን ሀገርን ለእድሜ ልክ ማገልገል ልጁም በተለየ መንገድ ቢሆንም እንድትቀጥል ይፈልግ ነበር፡፡‹ጓደኞቼ ለዚህች ሀገር ህይወታቸውን ሰጥተዋል እኔ ደግሞ በአጋጣሚ በህይወት ቆይቼ ልጅ ወልጄ እንድስም ከተፈቀደልኝ ይህቺን ልጅ ለሀገር አገልጋይ እንድትሆን በስርዓት አሳድጌ ፤ በአግባቡ አስተምሬ እንሆ ኢትዬጵያዬ ልጄን እንደልጅሽ ተረከቢኝ ፡የደቀቀ ጎንሽን አሽታ ትጠግንልሽ ዘንድ፤የጎበጠ ወገብሽን ደግፋ ታቃናልሽ ዘንድ..እግርሽን ጣቶች መካከል የተጠቀጠቁትንና ያቆሰሉሽን እሾኮች ቀስ ብላ ህመምሽ እያማት በወረንጦ ለቅማ ታክምሽ ዘንድ ….የአይኖችሽን ዳር አይናሮች አፀዳድታ መታወርሽን በፈዋሽ ጠብታ እንድታድንሽ ዘንድ ….አዎ ህመምሽ ሚያማት፤ ጭንቀትሽ የሚጨንቃት ልጅ አድርጌ አሳድግን አስረክብሻለው፡፡ ብሎ ለዘመናት እየፎከረ አሳደጋት ፡፡ እንዳለው አድርጎ አስተማራት፡፡ዩኒቨርሲቲ ገባች በማእረግ ጨረሰጭ ፡በጥሩ ደሞዝ ጥሩ መስሪያ ቤት ተቀጠረች፡፡አያቴ ተኩራራ ..በራሱም በልጁም ስኬት ታበየ፡፡ድንገት ግን እናቴ ከጋብቻ ውጭ እኔን ፀነሰች፡፡አያቴ ደነገጠ፡፡ተወለድኩና ታየው፡፡ይበልጥ አንገቱን ደፋ፡፡በእኔ ሁኔታ ..ያንን ተከትሎ የእናቴ ስራዋን መልቀቅ ፤እቤት ኩርምት ብሎ መቀመጥ እና መላ ህይወቷን ለእኔ ለበሽተኛ ልጇ መስዋዕት ማድረግ አያቴን ከእርጅናውም ገፍቶ የሞት አፋፍ ላይ አደረሰው …አዎ ይሄ ደግሞ የእናቴን ጓደኛ ቢያሳስባት ያስመሰግናት ይሆናል እንጂ በክፋት አያስቀወቅሳትም…እናቴን ግን ከፋት
ለዚህም ነው -አይ ተስፋ ለሌለው ነገር እራስሽን መስዋዕት እንድታደርጊ ስለማልፈልግ ነው እንደዚህ የምልሽ..ደግሞ ለአባትሽም ብታስቢላቸው መልካም ነው::…ያለቻት
.እንዴት ተስፋ የሌለው ነገር ….?......እናቴ በገረሜታም በንዴትም ጓደኛዋ ላይ ተንዘረዘረች ፡፡
-ለምን ሁሉንም ነገር ዘርግፌ እንድናገር ታስገድጂኛለሽ..….?አሁን አራት አመት አልፎታል.. መናገሩ ይቅር ቢያንስ በእግሮቹ ቆሞ መረመድ ካልቻለ ምን ተስፋ ይኖረዋል፡፡ይሄ ከአዕምሮው ጋር ቀጥታ ግንኙነት ያለው ነው የሚመስለኝ››
-የልጅሽ አዕምሮውም አይሰራም እያልሽኝ ነው….?
-እንግዲህ እንደፈለገሽ ተርጉመሽ ተረጂው…ግን ለሚወዱሽ ሰዎች ስትይ ያልኩሽን ብታደርጊ እመርጣለው፡፡
-በቃ ውጪልኝ..ታያላችሁ ደግሞ ስንት ዓመትም ይፍጅ ስንት ዓመት ልጄ ቆሞ ይሄዳል፡፡ አንደበቱንም ከፍቶ ይናገራል….?አምላኬ በልጄ ላይ ታአምሩን እንደሚገልጽ አምናለው….የዘላለም አምላክ ፈጣሪ …ሁሉን አድራጊና ሁሉን መታሪ ኤልሻዳይ ለጊዜው ዝም ቢለኝም እስከመጨረሻው እንደማይረሳኝ እርግጠኛ ነኝ…የቅድስና እሳት የሚተፉ የማዳን እጆቹን የልጄ ሰውነት ላይ አንድ ቀን ያኖራል፣..አዎ ቀኑ ሲደርስ እንደዛ ያደርጋል››እናቴ በተለመደ መልኩ በፈጣሪዋ ላይ ያላትን እምነት በንዴት እየተንቀጠቀጠች ለጓደኛዋ አነበነበችላት
-አይ…ክርስቲያን ተስፋ አይቆርጥም ሲባል እኮ እንዲህ አይደለም….እንዲሁ የእናት አንጀት ሆኖብሽ ነው..››አላገጠችባት….እኔ ከዛ በላይ ታግሼ እናቴ እቅፍ ውስጥ ተዘፍዝፌ መቀመጥ አልቻልኩም..ወይንም አላውቅም እናቴ የምትተማመንበት ኃያሉ አምላክ እንደጠየቀችው ሚስጥራዊ እሷት የሚተፉትን የድህነት እጆቹን ሰውነቴ ላይ ጭኖብኝም ሊሆን ይችላል፡፡ብቻ የእናቴ ንግግር ተከትሎ በጉንጮቾ እየፈሰሰ ግንባሬ ላይ የሚንጠባጠበው እንባ ወደመሬት ከመውረድ ይልቅ ግንባሬ ላይ እያረፈ ወደ ህብረሰረሰሬ በመስረግ ውስጤን ሲያቃጥለኝ እና በዛው ቅጽበት የሆነ ነዛሪና የሚያንቀጠቅጥ አይነት ኃይል በሰውነቴ ሲራወጥ ታወቀኝ ..ከእናቴ እቅፍ ላይ ተወራጨው እና ተንሸራትቼ በአግሮቼ መሬት ረገጥኩ፡፡
እሷን ይዤ መሬት ረግጪ መቆም ሁሌ የማደርገው ስለሆነ ሁለቱም ትኩረት እልሰጡኝም…ግን ታአምራዊ በሆነ ፍጥነት የእናቴን ድጋፍ ለቅቄ የሩጫ ያህል እየተንደረደርኩ የሴትዬዋን የሚወናጨፍ እጅ ተንጠራርቼ ያዝኩና ወደውጭ እጎትታት ጀመር …..እናቴ እልልታዋን እያሰማች በጉልበቷ ተደፍታ መሬቱን ስትስም ጓደኛዋ ፃረሞት ፊት ለፊቱ እንደተጋረጠበት ሰው እጆን መንጭቃ ከእጆቼ በማስለቀቅ በሩጫ ከቤታችን አምልጣ በመውጣት ከውጭ የአጥር በራፍ ጋር ተላትማ ተዘረረች….

💫ይቀጥላል💫

ከወደዱት ከተመቾ Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሱ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍3
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ
:
#ክፍል_ስምንት
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ከዛ ቡኃላ የትምህርት ቤቱ አስደናቂ ኮከብ ተማሪ ሆኜ ቀጠልኩ ፡፡እስከሶስተኛ ክፍል እስካጠናቅቅ ድረስ አንደበቴ እንደተዘጋ ነበር፡፡አስር አመት ከሆነኝ ቡኃላ አንድ ለሊት እኔና እናቴ የሰላም እንቅልፍ ተኝተን እያለ…ባልተለመደ ሰዓትና ሁኔታ የቤታችን መንጓጓት ሁለታችንንም እኩል ከእንቅልፍችን ቀሰቀሰን…. ሁለታችንም እኩል ዙሪያችንን ስንቃይ እቤቱ በድቅድቅ ጨለማ እንደተዋጠ ስለነበር ምንም ሊታየን አልቻለም … መብራቱን ለማብራት እኔም እናቴም እልደፈርንም….. …እናቴ ከክንዷ ላይ እኔን በማውረድ ከእቅፎ አውጥታኝ በዝግታ በመነስታ እና ቁጭ በማለት ምን እንደተፈጠረ ለማረጋጋጥ ጆሮዋን አቀናች..እኔም እሷን ተከትዬ ለመነሳት ስሞክር በእጇ ደፍቃ ባለውበት አስቀረቺኝና ወደጆሮዬ ተጠግታ በሹክሹክታ‹‹..አርፈህ ትንፋሽህን ውጠህ ተኛ..››በማለት አስጠነቀቀቺኝ …
ወዲያው የመኝታ ቤቱ በራፍ ሲበረገድና ባትሪ ግንባራችን ላይ ሲበራ እናቴ ‹ዋይ› የሚል ድምጽ አሰምታ ‹ልጄን ›በማለት እኔ ላይ ድፍት አለች
…ሁሉም ቅፅበታዊ ነበር…ውር ውር የሚል የባትሪ ብርሀን ግድግዳው ላይ ወዲህ ወዲያ ሲራወጥ እና የእግር ኮቴ ሲዘዋወር ይሰማኛል…
‹‹በል ፈትሽ ..ኮመዲኖውን ክፈት››ድምጽ ተሰማ
‹‹እንቀሳቀሳለው ብለሽ አንቺን ሳይሆን ልጅሽን ነው ፀጥ የምናደርግልሽ..››ሌላው እናቴን አስፈራራ…..
እናቴ የራሷን ትንፋሽ ወደውስጧ ማፈኗ ሳያንሳት እኔንም እላዬ ላይ እንደተደፋች በእጆቾም አንደበቴን ከደነችው፡፡
‹‹-አዎ ሁሉንም በሻንጣ ክተት..አዎ ወርቅም አገኘህ…ጥሩ ልብሶቹንም እንዳትተው››ይላል
ሶስት መሆናቸው በድምጻቸው ልዩነት ገምቼያለው፡፡ያው መዘረፋችን ቢያሳዝነኝም ዋናው እናቴን አለመጉዳታቸው ነው ብዬ በመጽናናት ስራቸውን እስኪጨርሱ እናቴ እንዳፈነቺኝ ታፍኚ በተኛውበት ተረጋግቼ የሚያደርጉትን ማየት ባልችልም የሚናገሩትን በትዕግስት እየሰማው ሳለ
በቃ እንሂድ ››በማለት አንዱ የመጡበትን ማጠናቀቃቸውን አበሰረን….››እፎይ ምንልበት ጊዜ ደረሰ.. ስል ተደሰትኩ
‹‹በል እናትዬውን እሰራት..አፎንም አሽገው››የሚል ደባሪ ድምጽ ወደጆሮዬ ገባ
‹‹ለምን አስፈለገ.…?.››ሌላው ጠየቀ
‹‹ትቀልዳለህ እንዴ ..ከዚህ ሳንወጣ ጩኸቷን ብትለቀውስ…?›› ስጋቱን ተናገረ
‹‹እናንተ ብቻ የያዛችሁትን ይዛችሁ በሰላም ውጡልኝ …በልጄ ምላለው ምንም አልጮህም››እናቴ ተማፀነቻቸው
አንደኛው‹‹ዝም በይ..›› ብሏት በምኑ እንደሆነ አላውቅም ከላይ ወገቧን ሲነርታት የህመሙ ስሜት ከስር ያለውትን እኔን ሳይቀር ተሰማኝ …
‹‹ና በል አንሳትና ከእዚህ የአልጋ እግር ጋር ጠፍንገህ እሰራት …ልጇንም እንደዛው….››ሲለውና ሌላው ትዕዛዙን ለማክበር እናቴን መንጭቆ ከላዬ ላይ ሲያነሳት ..የሆነ የማላውቀው ኃይል በሰውነቴ ሲሰራጭ ታወቀኝ
…እናቴ ‹‹ልጄን … ልጄን እንዳትነኩብኝ ››..እያለች ስትወራጭ…የድምፆ ቅጭልጭልታ ጆሮዬን እየነዘረ ወደጭንቅላቴ ሲሰርግ እና የሆነ የማላቀውቀው መንፈስ ሲቆጣጠረኝ አንድ ሆነ…..
ወደእኔ ከመምጣታቸው በፊት ተሸከራከርኩና በተቃራኒው በኩል ከአልጋው ተንከባልዬ ወረድኩ …… አዛዥ ቢጤው‹‹ልጁን ያዘው.. ልጁን ያዘው›› ሲል ይሰማኛል፡፡ አልጋውን ዞሮ ወደእኔ ከመምጣቱ በፊት ለእኔም ግልፅ ባልሆነልኝ የደመነፈስ ውሳኔ እና የእኔ ባልሆነ ፍጥነት የቁም ሳጥኑን መሳቢያ ስቤ ሽጉጥ አወጣውና ወዲያው መብራቱን በማብራት በኮማዲኖ በራፍ መላ አካሌን በመከለል ጭንቅላቴን ብቻ በከፊል ብቅ አድርጌ ሁኔታውን ቃኘው ….፡፡አዎ እንደገመትኩት ሶስት ናቸው፡፡ሁሉም ፊታቸው ላይ ጭንብል አጥልቀዋል፡፡ግን የጠበቅኮቸውን ያህል አስፈሪና ወጠምሻ አይነት አይደሉም…አንዱ የብረት ዱላ ሁለቱ ጩቤ ይዘዋል፡፡አንዱ በራፉ ጋ ቆሞ በቀኝ እጁ የያዘውን ባትሪ እኔ ወዳለውበት ቀስሯል፡፡ማብራቱን ካበራው ቡኃላ እንኳን አላጠፋውም..ሌላ እናቴን እያሰራት ነው..ሶስተኛው ሊይዘኝ ወደእኔ እየተንደረደርረ ነበር ..ሊያንቀኝ ሁለት ሜትር ያህል ብቻ ነበር የሚቀረው፡፡ከተሸሸኩበት ሳልወጣ ልክ ፊልም ላይ ደጋግሜ እንደማየው የያዝኩትን ሽጉጥ ቃቃ አድርጌ በማቀባበል እጄን ወደፊት በግንባሩ አቅጣጫ ቀስሬ ‹‹ ግንባርህን እንዳልፈረክሰው ባለህበት ቁም…››
ስለው ሳያቅማማ ደንዝዞ ትዛዜን አከበረ…እሱ ብቻ ሳይሆን ሶስቱም ያልጠበቁት ስላጋጠማቸው በሉበት ሲርበተበቱ በሰከንድ ሽርፍራፊ ቃኘው …ብዙም ልምድ የሌላቸው የመንደር ሌቦች መሆናቸውን ወዲያው ተረዳው፡፡
አናቴን እያሰራት ወደነበረው ሽጉጡን አዙሬ …‹‹እናቴን ልቀቃት…››ጮህኩበት …
ማሰሩን አቁሞ ቁጢጥ ካለበት በመነሳት ቀጥ ብሎ ቆመ…
ትዕዛዜን ቀጠልኩ ‹‹…አሁን አንድ ሰው ከመግደሌ በፊት እቃውን አስቀምጣችህ እቤቱን ለቃችሁ ውጡ ››
ተያዩና በምልክት በመነጋገር ወደኃላ መሳብ ጀመሩ…በራፍን ካለፉ ቡኃላ በሩጫ አስነኩት…
ከእውነተኛ ሽጉጥ ጋር በእጅ ካልያዙት በስተቀር ምንም ልዩነቱ የማይታወቀውን ልጅ ሆኜ የተገዛልኝን መጫወቻ ሽጉጥ መሬት ጥዬ ወደእናቴ ተንደረደርኩና አፎ ውስጥ የጠቀጠቀውን ጨርቅ ቀድሜ አውጥቼ በመጣል…. እጆቾን ልፈታ ስጣጣር እሷ እልልታዋን እስነካችው…
-እንዴ ምን እየሆነች ነው…?፡፡ግራ ገባኝ፡፡ ሰው እቤቱ ሌባ ሲገባበት ኡኡ ነው ማለት ያለበት ወይስ እልልል….…?
ወይ ድንጋጤ
- …እማ አይዞሽ ተራጋጊ …በማለት እጆን ፈትቼ ስጨርስ ተጠምጥማብኝ እያገላበጠች ትስመኝ ጀመረች
‹‹አደረከው..ልጄ አደረከው….አንድ ቀን እንዲህ እንደሚሆን አምን ነበር…እግዚያብሄር ሁሌም ካንተ ጋ ነው…አዎ አንተ ልዩ ነህ፡፡››
‹‹እማ ..አዎ ደርሼልሻለው … ከአሁን ወዲህ አይኔ እያየ ማንም ሊያጠቃሽና ሊያመናጭቅሽ አይችልም.. ማንም እንደዛ እንዲያደርግ አልፈቅድለትም…››ፎከርኩ
‹‹ እሱ አይደለም ልጄ …እሱ አይደለም..መናገር ቻልክ..ተናገርክ..እያወ
ራሀኝ ነው››ስትለኝ ድንግርግሬ ወጣ….እንዴ እያወራው ነው እንዴ ….…?.ከመገረሜ ሳልወጣ የእናቴን እልልታ የሰሙ የቤታችን ተከራዬች አያቴም ጭምር ከሚጣፍጥ የለሊት እንቅልፋቸው ተነስተው በመምጣት ወደቤታችን ሲንጋጉ ሰማን….

💫ይቀጥላል💫

የኛ ክፍያችን የናንተ ደስታ ነው ስሜታችሁን Like 👍👍 በማድረግ ግለፁልን

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍4
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ_ጉዞ
:
#ክፍል_አስራ_አንድ
:
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
...18 ዓመት ወጣትና የ12 ክፍል ተማሪ ሆኜ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችለኝን ማትሪክ ፈተና ዝግጅት ላይ እያለው አስቀያሚ ነገር ተከሰተ፡፡አስቀያሚ ስላችሁ የመጨረሻ አስቀያሚ ማለቴ ነው፡፡ትምህርት ቤት ክፍል ውስጥ ቁጭ ብዬ በማማር ላይ ሳለው በስልኬ መልዕክት መጣ ፡፡ሳየው ከአያቴ ነው፡፡ያልተለመደ ነገር ነው፡፡የሚያስተምረውን አስተማሪ ትኩረት እንዳልስብ እየተጠነቀኩ ከፈትኩና አነብኩት….ደብተሬን እንኳን አልሰበሰብኩም፡፡ ተስፈንጥሬ ከመቀመጫዬ ተነሳው ፡፡ የክፍሉ ተማሪ አይን ከአስተማሪው ተነቅሎ ወደእኔ አነጣጠረ..አስተማሪው ማስተማሩን አቋርጦ ምን እንደሆንኩ መጠቅ ጀመረ …እየተንደረደርኩ ክፍሉን ለቅቄ ወጣው፡፡ሳይክል ሚጠቀሙ ተማሪዎች ሳይክላቸውን ወደሚያቆሙበት ስፋራ ነው የሮጥኩት፡፡ከመካከሉ ቁልፉ ያልተቆለፈውን አዋጣውና እየጋለብኩ ግቢወን ለቅቄ ወጣው፡፡ ሳይክሉ የማን እንደሆነ አላውቅም ግድም አልነበረኝም..
ሆስፒታል እንደደረስኩ ሳይኩል ወረድኩና ከመንገድ ዳር አጋድሜ ወደውስጥ ሮጥኩ… ኮሪደር ለኮሪደር እየተሸከረከርኩ አያቴን ወይንም ሌላ የማውቀው ሰው መፈለግ ጀመርኩ...አዎ አያቴን አገኘውት
-እናቴ የታለች …?እናቴ ምን ሆነች…??እማ!!
ተረጋጋ…ምን እንደሆነች አናውቅም…ድንገት ነው እራሷን የሳተችው ፡፡እያከሟት ነው፡፡ይውጡና ሚሉትን እንሰማለን፡፡››አለኝ አያቴ በሚርበተበት ድምፅ..
‹‹እራሴን መቆጣጠር አቃተኝ፡፡‹‹ቆይ አያቴ እንደዚህ አይነት ነገር እንዴት ይፈጠራል …?እናቴ ፍጽም ጤነኛ ነበረች፡፡እንኳን እራስ መሳት ይቅርና እራሷንም ሲያማት አይቼ አላውቅም ፡፡››
‹‹ለእኔም አንቆቅልሽ ነው የሆነብኝ ልጄ››አየቴ መለሰልኝ
ንግግሬን ሳልጨርስ እናቴ ስትታከምበት ከነበረው ክፍል አንድ ዶክተር ወጣ… ተንደርድረን ከበብነው፡፡ዶክተሩ እኔንና አያቴን ወደቢሮ ይዞን ሄደ፡፡ ካዘነው በላይ የሚያሳዝን …ከደነገጥነው በላይ የሚያስደነግጥ መርዶ ነገረን፡፡
‹‹የሚቀጥሉትን ሶስት ቀን እዚህ ትቆይና …ከዛ ትወስዶታላችሁ››
‹‹ተመስገን›› አለ አያቴ …ረጅም ግን ደግሞ ደካማ ትንፋሽ ተንፍሶ፡፡
‹‹ዶ/ር በሶስት ቀን ይሻላታል ማለት ነው…?››ጠየቅኩት በመፍለቅለቅ ….ለማረጋገጥ፡፡
ዶክተሩ አንገቱን እንደመድፋት አለና የተወሰነ አየር ወደውስጡ ስቦ ጭንቀት በሚለቅ ድምጽ ‹‹አዝናለው ..ይሻላታል ብዬ ተስፋ ልሰጣችሁ ብችል ደስ ይለኝ ነበር…ግን እሷን የማዳኑ ጉዳይ ረፍዶብናል››
‹‹ማለት …?››
እቤት ወስዳችሁ ያላትን ቀሪ አንድ ወርም ሆነ ሁለት ወር በደስታ አሳልፋ …በሰላም እንድታርፍ ከማድረግ ውጭ ሌላ ምርጫ የላችሁም፡፡››አለ የመለማመጥ ቃና ባለው ድምፀት፡፡
ከመቀመጫዬ ተንሳፍፌ ተነሳውና የሸሚዝኑን የጋወኑን ኮሌታ አንድ ላይ ጨምድጄ ከተቀመጠበት አንጠልጥዬ አስነሳውትና በአየር ላይ አንሳፍኩት…ሰውዬው አይኑ ተጉረጠረጠ..እጆቹን እንድለቀው ማወራጨቱን ቀጠለ
አያቴም ከድንዛዜው እንደምንም ባኖ ይለምነኝ ጀመር
‹‹ልጄ ምን እየሰራህ ነው..…?ሰውዬውን ልቀቀው..…?ልጄ የሰው ሰው እንዳትገል፡፡››
‹‹እናቴን ታድናታለህ አታድናትም.…?››አርገፍግፌ መሬት አድርሼ ለቀቅኩት
ዶክተሩ ጉሮሮውን በእጆቹ እየዳበሰ ደጋግሞ ካሳለ ቡኃላ‹‹.አዝናለው አልችልም…ማንም ሊያድናት አይችልም….››ብሎ ስለበሽታዋ አይነትና ከባድነት የደረሰበትን ደረጃ በተቆራረጠ ቃላት ይዘረዝርልን ቀጠለ.
በእናቴ ስም እምላለው…ከሞተች አገድልሀለው..አንተን ብቻ ሳይሆን ጠቅላላ እዚህ ግቢ ውስጥ ያላችሁትን ሀኪሞች ጨርሳችሆለው …ሆስፒታሉንም አቃጥለዋለው፡፡አረ ከተማወናም ነው የማቃጥለው…››በማለት ቢሮውን ጥዬ ወጣውና እናቴ ወደተኛችበት ክፍል ተንደረደርኩ ፡፡በራፍ ላይ የቆመችውን ነርስ ገፍቼ ፍቃዷንም ሳልጠይቅ ወደውስጥ ገባው፡፡እማዬ ዝርር ብላ ተሰትራ የሆስፒታሉ አልጋ ላይ ተኝታለች፡፡አይኖቾ ተከድነዋል፡፡ትንፋሿም አይሰማም ፡፡በሁለቱ አፍንጫጮ ቀዳዳ ቱቦ በክንዶቾ የግሉኮስ ላስቲክ ተሰክቶል፡፡
በራስጌዋ ሄድኩና ወለሉ ላይ ዝርፍጥ ብዬ ግንባሬን አልጋዋ ላይ ደፍቼ ወደ ፊቷ ተጠግቼ አስደገፍኩና በሹክሹክታ አወራት ጀመር….
ማሂ ምን እየሰራሽ ነው…?፡፡ምንድነው ዶክቱሩ የሚቀባጥረው…?፡፡ጥላህ ልትሄድ ነው እያለኝ ነው፡፡ስለማያውቅሽ ነው የሚቀባጥረው ፡፡አንቺ መቼም መቼም እኔን ጥለሽ መሄድ እንደማትችይ ስለማያውቅ ነው፡፡ገነትም ቢሆን እኔ ከሌለው መኖር እንደማትችይ ስለማውቅ ነው፡፡ማሂ ከተወለድኩበት ቀን አንስቶ ስትበይ እንብላ ብለሺኝ ስትተኚ እንተኛ ብለሺኝ ፤ስትተነፍሺ እንኳን የእኔንም መተንፈስ አረጋግጠሸ ነበር…ታዲያ ዶክተሮቹ እንደሚሊት አሁን ልትሞቺ ከሆነ እንዴት ልንሞት ነወ ተዘጋጅ ሳትይኝ .. …?ነገሩ ተይው እውነት ዶክተሩ አንዳለው ሸውደሺን ለመሞት የተዘጋጀሽ ከሆነም ግድ የለም እኔ ዝግጅት አያስፈልገኝም፡፡
ንግግሬን ከጀርባዬ ሆኖ ሲያዳምጥ የቆየው አያቴ በሽማግሌ አንጀቱ እየተንሰቀሰቀ በማልቀስ ዝቅ ብሎ አስነሳኝና
‹‹ተው ልጄ ተረጋጋ…አይዞህ እግዜር አለ ያድንልናል፡፡››
እንግዲህ እግዚያብሄር አለ የምትል ከሆነ በምትግባቡበት ቋንቋ ንገረው…ተው የሰው እናት አትንጠቅ በለው…እሷን አጥቶ መኖር አይችልም በለው…ከሰማህ ጥሩ ነው ፡፡ ካልሰማህ ደግሞ እኔንም ተሰናበተኝ ፡፡ እናም ከእናቴ ጋር በአንድ ጉድጓድ መቀበር ነው የምፈልገው..እንዳትረሳ በአንድ ጉድጓድ ፡፡ይህ ኑዛዜዬ ነው፡፡››ብዬው ጥዬው ወጣው ፡፡ወደየት እንደምሄድ ባላውቅም የሆስፒታሉን ቅጥር ጊቢ ለቅቄ ወጣው….

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍42
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ_
:
#ክፍል_አስራ_ሁለት
:
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ሶስተኛ ቀን ነው፡፡እንደነጋ እናቴን ይዤ ከሆስፒታል ወደቤት እሄዳለው፡፡ከዛ አስክትሞትበት ቀን ድረስ አብሬያት ስሮ ተኛለው፡፡ስትነቃ ነቃለው ስትተኛ አብሬት ተኛለው፡፡ምንያህል እንድምወዳት ያለማቆረጥ በየቀኑ ነግራታለው፡፡የሚያስደስቷትን ዘፈኖች ዘፍንላታለው፡፡የሚያዝናናትን ታሪክ አወራታለው፡፡የሚትወዳቸውን ምግቦች ሁሉ በገዛ እጆቼ እያበሰልኩ እመግባታለው፡፡ከዛ የመጨረሻው ቀን ደርሶ ስትሞት ደቂቃዎችን ሳላባክን እከተላታለው፡፡እራሴን ለማጥፋት የሚያስፈልገኝ መሳረያ …. እንዴት እንደምሞት እቅድ አውጥጬ ዝግጅቴን ሁሉ ጨርሼያለው፡፡በዚህ ለሊት ሆስፒታል የበሽተኛ አልጋ ላይ ዝርግትግት ብላ ከተኛችወ እናቴ ጎን ካላ ሌላ አልጋ ላይ ተቀምጬ ነው እቅዴን እየከለስኩ ያለውት፡፡ሳላገባድድ የክፍሉ በረፍ በዝግታ ተከፈተ፡፡
በዚህ ሰዓት ነጭ ጋወን የለበሰ ባለሞያ እናቴ ወዳለችበት ክፍል ምምጣት የተለመደ ነገር ነው፡፡አዲስ የሆነው የመጣችው ልጅ ነች ፡፡በጥቁር እና በቅላት መካከል ያለ የሰውነት ከለር ፤የተመዘዘ የሰውነት ቁመት ያላት ቀጭን የምትባል ሀያዎቹ መጀመሪያ ላይ ያለች ፡፡በዚህ ለሊት ይሄ ሁሉ ፈግታ ገረመቺኝ፡፡ባለፉት ቀናት ልምዴ ሁሉም ዶክተሮች ሆኑ ነርሶች ለሊት ሲመጡ ከቀን ሁኔታቸው ባለይ ኮስተር ብለው ነው የማያቸው..ምን አልባ እንቅልፍ እየፈተናቸው ስለሚሆን ነው የሚል የራሴን ግምት ወስጄያለው..ምንም ቢሆን ሰው አይደሉ…?
ይህቺ ግን …ደግሞ ካለዛሬ ኮ አይቼያት አላውቅም፡፡
<<ተኝታለች…?››
<<አዎ ›
<<ወንድሞ ነህ…?››
ወንድሞም፤ጓደኛዋም፤ልጆም ነኝ››
‹‹ገባኝ …ግን እኩያዋ ነህ …ተናሽና ታላቅ እህትና ወንድም ነው የምትመስሉት፡፡በዚህ እድሜዋ አንተን ማድረሶ ሚገርም ነው፡፡››አለቺኝ በፈግታዋ እንደተሞላች በእጆ የያዘችውን እናቴን የህክምና የክትትል ሪከርድ እየተመለከተች
‹‹ልጆ መሆኔን አመንሽ ማለት ነው.…?አልኳት ..እንዴት እርግጠኛ ልትሆን እንደቻለች ግር ብሎኝ
‹‹አዎ ..አንዳንድ ነገሮችን ትንሽ ትኩረት ካደረግኩ ሳይነገረኝም ማወቅ እችላለው፡፡››
‹‹እሺ አንቼ በራፍን ከፍተሸ ከመምጣትሽ በፊት ምን እያሰብኩ ነበር››ዝም ብዬ ለቀልድ ያህል ነበር የጠየቅኳት…?
በእጆ የያዘችውን ወረቀት እናቴ የተኛችበት አልጋ ጠርዝ ላይ አስቀመጠችና በዝግታ እርምጃ ወደእኔ ተጠጋች .፡፡እንደመደንገጥ አልኩ‹‹እጅህን ስጠኝ ››አለቺኝ…ያለጥያቄ ቀኝ እጄን ዘረጋውላት፡፡ በሁለት እጆቾ መካከል አስገብታ ጨበጠችውና በመንፈስ ተሞልቶ እንደሚፀልይ ፓስተር አይኖቾን ጨፈነችና ለተወሰኑ ሰከንዶች ከቆየች ቡኃላ የመወርወር ያህል እጄን ለቃ ወደኃላ አፈገፈገችና ያስቀመጠችውን ወረቀት አንስታ ያዘች
‹‹ምነው ከበደሽ…?››
‹‹እናትህም ባንተ ቦታ ብትሆን እንደዛው ነበር የምታደርገው›› አለቺኝ
‹‹አልገባኝም››
‹‹የታመምከው እና ትሞታለህ የተባልከው አንተ ብትሆን እናትህም እንደአንተው እራሷን ለማጥፋት ዝግጅት ታደርግ ነበር..››
ከተቀመጥኩበት በድንጋጤ ተነሳውና ቆምኩ..መልሼ ቁጭ አልኩ
‹‹እንደዛ እያሰብኩ እንደሆነ እንዴት አወቅሽ…?››
‹‹እርሳው …አለቺኝና የእናቴን ሙቀት መለካት ጀመረች
‹‹አይ አረሳውም…ስለእናቴ የተጠቀሰው በሽታ የእውነት እንዳሉት በአጭር ቀናት ….››ዓ/ነገሩን ልጨርሰው አልቻልኩም፡፡
በብጫቂ ወረቀት ላይ ‹‹አዎ…እናትህ 25 ቀን ብቻ ነው ያላት፡፡››ብላ ፅፋ አቀበለቺኝ
እንደእኔ ሁሉ እሷም በአንደበቶ መናገር ከብዶት ይሁን ወይም እናቴ በእንቅልፍ ልቧም ቢሆን ልትሰማ ትችል ይሆናል ብላ በማሰብ አልገባኝም
ወረቀቱን ከነብኩ ቡኃለ ጠቅልዬ አፌ ውስጥ ከትኩት እና አኝኬ ዋጥኩት…ከዛ ፀጥ አልኩ…ምንም ልላት አልቻልኩም ፡፡የምታደርገውን አድርጋ በል አይዞህ በርታ ብላኝ እንደአመጣጦ ወጥታ ሄደች፡፡
መብሰልሰሌ በእጥፍ ጨመረ ..ይህቺ ዶክተር ማን ነች……?የእውነት ነች ወይስ ከመንፈስ ጋ እያወራው ነበርኩ…?››፡ከተቀመጥኩበት ተነሳውና ክፍሉን ለቅቄ ወጣው፡፡
ተረኛዋን ዶክተር ማናገር እንደምፈልግ ስናገር ቢሮዋ እንዳለች ጠቆሙኝ፡፡ሄድኩና በስሱ አንኳኳው፡፡
‹‹ግባ›› የሚል ድምፅ ከውስጥ ስሰማ …ከፈትኩና ገባው፡፡ አቀርቅራ መፅሀፍ እያነበበች ነበር፡፡አዎ የእውነት ነች ማለት ነው…? ፡፡እየቃዠው አይደለም፡፡
‹‹ቁጭ በል ››
ቁጭ አልኩ
‹‹ሳይሽ ዛሬ የመጀመሪያ ቀኔ ነው፡፡››
‹‹አዲስ ነኝ ፡፡ዛሬ ነው ስራ የጀመርኩት፡፡ይህቺ ለሊት የመጀመሪያ ቀኔ ነች፡፡››ብላ አስገረመቺኝ
‹‹ታዲያ እንዴት በመጀመሪያ ቀን ስራሽ እናቴን 28 ቀን እንደቀራት መናገር ቻልሽ…?››
አንደኛ የህክምና ውጤቱ ሪከርድ ተደርጓል፡፡እዚህ ፊት ለፊቴ ያለው ኮምፒተር ውስጥም አለ፡፡ወደእናንተ ከመምጣቴ በፊት አንብቤዋለው፡፡
‹‹28 ቀን ይቀራታል ይላል…?››ፍርጥም ብዬ ጠየቅኩ፡፡
‹‹አይ ቀኑንማ አይናገርም፡፡እሱ የእኔ ትንበያ ነው፡፡በነገራችን ላይ አንድ ውለታ ልውልልህ እያሰብኩ ነው፡፡››
‹‹ምን አይነት ውለታ…እናቴን የምትድነበት ሆስፒታል ወይም ሀገር ልትጠቁሚኝ ነው…?››
‹‹ፍጽም…እናትህን የሚያድናት ዘመናዊ ህክምና የትም ብትሄድ አታገኝም››
‹‹ታዲያ ሌላ ውለታ ምን ያደርግልኛል…?፡፡አልኮት ለምቦጬን ጥዬ
‹‹አንድ ማውቀው የባህል ህክምና አለ ፡፡ፈጽሞ አያድናትም ግን ቢያንስ ዕድሜዋን በሶስት አመት ያራዝመዋል፡፡››
ከተቀመጥኩበት በድንጋጤ ተነሳው.. ተንደርድሬ እግሯ ላይ ተደፋው…‹‹በፈጠረሽ ..በምታምኚው ይዤሻለው እባክሽ እናቴን አትሪፊልኝ››
‹‹ላተርፋት አልችልም…ሶስት አመት ብቻ›
‹‹ይሁን …ሶስት አመት .››
‹‹ሶስት አመት እኮ ብዙ አይደለም…ሳታስበው ነው የሚደርሰው››
ግድ የለሽም ..አንቺ ብቻ እሱን አድርጊልኝ… እስከዛ የሚሆነውን ማን ያውቃል…?፡፡››
‹‹እሺ ሂድ ከግማሽ ሰዓት ቡኃላ እመጣለው፡፡››
‹‹እመጣለው ስትይ..››
‹‹መድሀኒቱን ይዤ እመጣለው››
አላመንኳትም ፡፡እንዴ ባለፉት ሶስት ቀናቶች እንቅልፍ ባለመተኛቴ አዕምሮዬን እየሳትኩ ይሆን እንዴ …?ይሄ ነገር የእስካሁኑ ሁሉ ህልም እንዳይሆን..…?፡፡ጎንበስ አልኩና የእጄን መዳፍ ጠረጵዛዋ ላይ ዘረግቼ እጆ ላይ ያለውን እስኪሪብቶ ተቀበልኩና በኃይል ወጋውት .የእስኪሪብቶው ጫፍ የተወሰነ ጥልቀት ወደ መዳፌ ውስጥ ሲገባ እግሬ ድረስ ነዘረኝ..
‹‹በህልም ውስጥ አይደለውም ማለት ነው›…?አልኩ
‹‹ይሄ ያደረከው እኮ ማረጋገጫ አይሆንም ፡፡ምክንያቱም በህልምህም ቢሆን ይሄንን የማረጋገጫ ሙከራ ልትሞክር ትችላለህ ፡፡››ብላኝ ከስጋቴ እንዳልወጣ አደረገቺኝ…ለማንኛውም እንዳለቺኝ ቢሮዋን ለቅቄ ወደእናቴ ተመለስኩና በናፍቆትና በጭንቀት እጠብቃት ጀመር።

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍11
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ
:
#ክፍል_አስራ_ሶስት
:
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ዶክተሯ ቃሏን ጠብቃ ከሀያ ደቂቃ ቡሃላ በአነስታኛ ብልቃጥ ሀመራዊ አይነት ዝልግልግ ፈሳሽ ይዛ በምጣት ያለምንም ንግግር መድሀኒቱን ከብልቃጥ ውስጥ በስሪንጅ በምጠጥ ከእናቴ ደምስር ጋር ከቴያያዘው የጉልኮስ የፕላስቲክ ከረጢት ውስጥ ጨመረችውና …እንዳአመጣጦ ምንም ሳትናገር ወጥታ ሄደች፡፡
እኔም ደንዝዤ ስለነበረ የምታርገውን በፅሞና ከመታዘብ በዘለለ አንደበቴን አላቅቄ ቃላት ማውጣት አልቻልኩም..ምን እየተፈጠረ ነው..?እውነት እንዳለችው ይህ መድሀኒት እናቴን ይፈውሳት ይሆን…..?ነው ወይስ እያሾፈችብኝ ይሆን…..?እንደዛማ ከሆነ በህይወቷ ወስናለች ማለት ነው፡፡እዛው የቢሮዋ ወንበር ላይ እንደተቀመጠች በእነዚህ መዳፎቼ አንገቷን ፈጥርቄ ፀጥ ነው የማደርጋት ፡፡….በውስጤ ዛትኩ
በተጋደምኩበት ይሄንን እና የመሳሰሉትን ግትልትል ሀሳቦች እያሰብኩ ሳይታወቀኝ እንቅልፍ ይዞኝ ጭልጥ ብሎ ነበር ለካ ፡፡አይፈረድብኝም የሶስት ሙሉ ቀን እንቅልፍ ነው ያለብኝ፡፡
‹‹…ፀጋ …የእኔ ልጅ››የሚለው ከገነት ከመላዕክት አንደበት የሚፈስ የሚመስል ጡዑም ዜማ ያለው የእናቴ የጥሪ ድምጽ ነበር ከእንቅልፌ የቀሰቀሰኝ… ደንግጬ ከተጋደምኩበት የሆስፒታል አልጋ በርግጌ በመውረድ ወለሉ ላይ እናቴ ፊት ለፊት ተገተርኩ
‹‹..አረ ተረጋጋ የእኔ ጌታ..››ጥርት ያለ ንፅህ የእናቴ ድምፅ..
ማመን አልቻልኩም፡፡በስነስርአት ትራስ እንኳን መንተራስ ሳያስፈልጋ ቁጭ ብላለች፡፡ምንም በበሽታ የመድከም ምልክት በፊቷ አይታይም፡፡
‹‹እማ ደህና ነሽ…..?ተሸለሽ…..?አሁን ምን ይሰማሻል..?››በጥያቄ አጣደፍኳት
‹‹ይሄው እንደምታየው በጣም ደህና እና ፍፅም ጤነኛ ሆኜ ነው የተነሳሁት፡፡ይገርምሀል ለሊ,ት ተኝቼ ጠይም መላዕክ መጥታ ከጭንቅላቴ አንስታ መላ አካላቴን ስትዳብሰኝ ነበር…እግዜያብሄር ያአንተ ፀሎት ሰምቶ ምሮኛል መሰለኝ፡፡››አለቺኝ በተፍለቀለቀ የደስታ ድምፀት
ተንጠራራውና አቀፍኳት ፡፡ግንባሯን …ጉንጮን …አፍንጫዋን እያፈራረቅኩ ሳምኳት ‹‹…አዎ እማ ድነሻል…እግዜያብሄር ይመስገን ተሳክቶልናል…ልጅቷ እንዳለችው ማድረግ ችላለች…ምትገርም ሴት ነች፡››
‹‹ስለማን ነው የምታወራው..?›› አለችኝ መቀባዠሬ ስላልገባት
‹‹አይ በህልሜ አየዋት ስላልሽው መላዕክ ነው ማወራው….ስላዳነችሽ መላአክ››አልኩና ርዕሱን አስቀየርኳት
‹‹አዎ እግዜር ነው የላከልኝ..ሄድ አሁን ሀኪም ጥራልኝ››
‹‹ምነው .. ..?የሚያምሽ ቦታ አለ እንዴ..?›› በድንጋጤ ጠየቅኳት
‹‹አረ በፍጽም… ይሄን ግሉኮስ ከላዬ እንዲነቅሉልኝ ነው…ሽንት ቤት መሄድ ፈልጋለው ›› ስትለኝ..ሮጬ ወጣውና በ10 ደቂቃ ውስጥ ተረኛውን ዶክተር አስከትዬ መጣው፡፡ይሄ ዶክተር እናቴ ሆስፒታል ከገባች ቀን ጀምሮ በዋናነት ስለጤናዋ ይከታተላት የነበረው ስለነበር እንዳያት ደነገጠ..በጣምም ግራ ተጋባ..ከግምቱ ውጭ የሆነ ሁኔታ ላይ ሆና ነው ያገኛት .
‹‹ማህሌት ምን ይሰማሻል. .?››
‹‹ፍጽም ጤነኝነት››
በጣም ጥሩ ..አሁን ወደቤት ከመሄድሽ በፊት ሙሉ ምርመራ ማድረግ አለብን ..››አለና ጉሉኮሱን ከእጇ ላይ በማለያየት ወጥቶ ሄደ …እኔም እሱ ለምርመራ ሚገለገልባቸውን መሳሪያዎች ይዞ እስኪመጣ ድረስ ስልኬን አወጣውና ለአያቴ ደወልኩለት…
‹‹ሄሎ አባ የት ነህ.?››
‹‹የት እሆናለው ልጄ… ቤተክርስቲያን ነኝ…ምነው ልጄ ባሰባት እንዴ .?›› ስብርብር ባለ ተስፋ የቆረጠ ደካማ ድምፅ ጠየቀኝ
‹‹አረ አባ ፍፅም ደህና ነች…ፀሎትህን ከጨረስክ ቀጥታ ወደሀስፒታል ና ››
‹‹አሟታል ማለት ነው ..መች አጣውት …እግዜያብሄር ዘንድሮ ሊያዋርደኝ ነው››አምላኩ ፊት መቆሙን እንኳን ዘንግቶ ተነጫነጨ
‹‹እወነቴን ነው አባ …ቆይ እንደውም…›› ብዬ ስልኩን ከጆሮዬ ላይ አነሳውና ለእናቴ አቀበልኳት ..የጠራ እና የነቃ ድምፆን በስልክ ከሰማ ቡሃላ በደስታ ሰክሮ እልልታውን ሲያቀልጠው በስልኩ ውስጥ ተሰማኝ…በዚህ እድሜው ልጁ ስትሞት አይቶ ባለመሳቀቁ ውስጤን ሀሴት ተሰማው …ቢያንስ ለጊዜው ይደሰት ..
እስከአራት ሰዓት መደረግ ያለበት ምርመራ ሁሉ ተደርጎላት ተጠናቀቀ..ውጤቱም ዶክተሮቹን በጣም ያስደመመ እና የበፊቱን የምርመራ ውጤት እንዲጠራጠሩ ያደረገ ነበር…እኔም ስለሆነው ነገር በውስጤ አፍኜ አብሬያቸው ከማደነቅ ውጭ ምንም ነገር ትንፍሽ ማለት አልቻልኩም…አልፈለኩምም፡፡
አዲሱ የህክምና ውጤት እንደሚያሳየው የእናቴ በሽታ ሙሉ በሙሉ የጠፋ ባይንም ደረጃው ግን 50 ፐርሰንት ወደኃላ የተመልሰል ነበር…ይህ ማለት ደግሞ ዋናው ሀኪምም እንዳረጋገጠልኝ በቅርብ ጊዜ ትሞታለች የሚለው ስጋት በአስተመማኝ ሁኔታ እንደተወገደ ነው፡፡
እንዴት እንደሆነ ባይገባኝም በእናቴ ላይ ተአምር ተፈፅሟል …ሙሴ የእስራኤልን ባህር በበትሩ ከፍሎ ወገኖቹን ያሻገራቸውን አይነተ ተአምር….አስራሁለት አመት ደም ሲፈሳት የነበረች ሴት የክርስቶስን የልብስ ጫፍ በእምነት ዳብሳ ከህመሞ ፈውስ ያገኘችበትን አይነት ተአምር ፡፡እርግጥ ታአምሩ ጅምር ነው…ምን አልባት በዚሁ የሚቀጥል ከሆነ ሙሉ በሙሉ ልትፈወስና እኛንም ይበልጥ ልታስደምመን ትችል ይሆናል፡፡
በሰተመጨረሻ ለመሄድ ዝግጅታችንን እንዳጠናቀቅን ወደዋናው ዶክተር ቀረብኩና ‹‹አመሰግናለው ዶክተር..ሁላችሁንም እግዜር ይስጥልኝ አልኩ››
‹‹ኦኬ ..ያ ማለት ለህይወታችን መስጋት አይጠበቅብንም ማለት ነው..?››
‹‹ማለት . ..?አልገባኘም ..?››
‹‹እንደምትገለን በርግጠኘነት ዝተህብን ነበር…አሁን እናትህ በከፊልም ቢሆን በመዳኗ ለጊዜው የተረፍን ይመስለኛል››አለኝ ፈገግ እያለ
አንገቴን አቀረቀርኩ‹‹በጣም አዝናለው…እናቴ ለእኔ መላ ነገሬ ስለነበረች አብዝቼው ነበር…ያን ያህል ስለታገሳችሁኝ ውለታችሁን መቼም አረሳውም..››
‹‹አረ ስቀልድህ ነው..እኔም ሆንኩ ባለደረቦቼ በወቅቱ የነበርክበትን ሁኔታ በደንብ ስለተረዳን ምንም አይነት ቅሬታ እልተሰማንም …ነገሩን ያነሳውልህ እንዲሁ ልቀልድ ብዬ ነው ›አለኝ
እናቴን በጓደኛቼ በዘመድና በጎረቤት ሰዎች አሳጅቤ እባቴ ስንደርስ አምስት ሰዓት ሆኖ ነበር… እናቴን ወደጆሮዋ ተጠግቼ የምሄድበት ቦታ እንዳለና ልቆይ እንደምችል ነግሬት ከአጀብ ውስጥ ወጥቼ ወደሆስፒታል ተመለስኩ …ከተቻለ ዶክተሯን ለማግኘት ፤ ከለበላዛ እንዴት እዳማገኛትና ከዛም አልፎ ስለማንነቷ መረጃዎችን ከገኘው ለማጣራት…
ምክንያቱም ስለእሷ በአዕምሮዬ ውስጥ የሚጉላሉ ጥያቄዎች ከቁጥጥር ውጭ እያደረጉኝ እና መንፈሴን ክፉኛ እየረበሹት ነው.
1/ይቺ ዶክተር ማነች....?የትኛው ከተማ ወይም የትኛው ገጠር ተወልዳ የትኛው ዩኒቨርሲቲ ገብታ ተምራ እዴት እዚህ ተማድባ መጣች..?
2/እንዲህ አይነት ከሳይንስ አቅም በላይ የሆነ ህምምን ለመፈወስ የሚያስችል የባህል ህክምና ጥበብን በዚህ ዕድሜዋ እንዴት ልትካንበት ቻለች;..?››
3/በምን አይነት ተአምራዊ አጋጣሚ ሄስፒታሉ ለመስራት በተመደበች በመጀመሪያው ቀን የመጀመሪያዋ ታካሚዋ እናቴ ልትሆን ቻለች..?
2/ከእኔ እፈልገዋለው ያለችው በውለታዋ ምላሽ እንድከፍል የሚጠበቅብኝ ምንድነው....?ብር እንዳልሆነ እርግጠኛ ነኝ ፡፡አንገቷ ላይ ያጠለቀችው እባብ የመሰለ ጥምዝ ወርቅ እና ጆሮዋ ላይ ያንጠለጠለችው የከበረ ጌጥ የኑሮ ደረጃዋን ያሳብቅባታል፡፡የባህል መድሀኒት በሆስፒታል ቅጥር ግቢ በድብቅ እየቸረቸረች ገንዘብ የምትሰበስብ አይነት ሰው አይደለችም..አዎ በዛ እርግጠኛ ነኝ ፡፡ግን ምንም እንዳደርግላት ብትጠይቀኝ ግድ የለኝም…እራስህን አጥፋልኝ ብትለኝም አደርገዋለው…
👍5
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ_ጉዞ
:
#ክፍል_አስራ_አራት
:
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
....ቀጥታ ወደቤቴ በመሄድ ፋንታ ብቻዬን ሆኜ በፀጥታ ወደምተክዝበት ቦታ ነበር የተጓዝኩት፡፡ወደቢሾፍቱ ሀይቅ ሄድኩና ቁጥቆጦ ጥቅጥቅ ካለበት ቦታ ሀይቁ ዳር ላይ ወደሚገኝ ገዘፍ ካለ የድንጋይ አለት ላይ ቁጭ ብዬ አይኖቼን አስፈሪው እና ዙሪያውን በተራራ በተከበበው ሀይቅ ላይ ተክዬ ማሰላሰል ጀመርኩ .፡፡ሙሉ አዕምሮዬን የሞላችው ዶክተሯ ነች…እኔ እንጃ አላውቅም በውስጤ ህይወቴ ሙሉ በሙሉ እንደሚቀየር እና እስከአሁን ስሄድበት ከነበረበት መንገድ ፍፅም በተቃራኒና በማይገመት አይነት መስመር መጎዝ እንደምጀምር እየተሰማኝ ነው፡፡ከሀሳቤ ሳልፈልግ ያናጠበኝ ከቆጥኞቹ ስር የሚሰማዋ መንሾካሾክ ነው፡፡ሰው መጥቶ ፀጥታዬን ሊረብሸው ነው እንዴ ? ብዬ ትኩረቴን ከሀይቁ ወደቁጥቆጦው ስመልስ ያልጠበቅኩት ነገር አየው …..ግዙፍ ዥንጉርጉር ጥቁር እባብ ሽልልል እያለ ከቋጥኙ ውስጥ ቅጠሎችንና ቅርንጫፎቹን እየገላለጠ ወደ እኔ አቅጣጫ እየተሳባ እየመጣ ነው..
ወደእኔ በመገስገስ ላይ ያለውን እባብ ምላሱን በደም ስሬ ሰክቶ መርዙን ወደውስጤ ለመትፈት የቆመጠ በሚያስመስለበት ሁኔታ ጭንቅላቱን በአየር ላይ አንሳፎ አስፈሪውን ሹል ምላሱን ትሪዕታዊ በሆነ ሁኔታ ሲያወዛውዛቸው እያየው ነው፡፡ በድንጋጤም በመገረምም ከተቀመጥኩበት ቋጥኝ በቅልጥፍና ተነሳውና ዙሪያ ገባዬኝ ማቃኘት ጀመርኩ… ጭንቅላቱን ብዬ የምገላግልበት ደህና ዱላ ነገር ፍለጋ …ያን ያህል አስተማማኝ ባይሆንም አንድ ሁለት ክንድ የሚረዝም ደረቅ እንጨት አገኘውና አፈፍ አድርጌ አነሳውና አስተካክዬ ያዝኩትና ለፍልሚያ ተዘጋጀው…….፡፡
በእኔ እና በእባቡ መካከል ያለው ክፍተት ከሁለት ሜትር አይበልጥም…እኔም እንዴት አድርጌ ላጥቃው እያልኩ እስትራቴጂ ሳወጣ 3 የሚሆኑ ደቂቃዎች አለፉ …እባቡም ከእኔ ተመሳሳዩን እያሰበ ይመስለኛል፡፡ከዛ ቀድሞ ያጠቃል ብዬ በምጠብቅበት ጊዜ በሚገርም ፍጥነት ተወርውሮ ወደመጣት ዞረና ተስፈንጥሮ ቁጥቋጦው ውስጥ ተመልሶ ገባ ፡፡ድላዬን እንደቀሰርኩ ተከተልኩት…ሊያመልጠኝ አይገባም..ደረስኩና ቁጥቋጦውን በጥንቃቄ ስገላልጥ በዛኛው ወገን ያልጠበቅኩት ነገር አያው ..ድንጋጤዬ ጨመረ.. ፈጣን ውሳኔ ወሰንኩ ..ቁጥቆጦውን በግራ በኩል አልፌ ተጠምዘዝኩና ስሮ ደረስኩና ወገቧን በአንድ እጄ አቅፌ አንጠለጠልኩና ከቁጥቆጦ ውስጥ አርቄ በመውሰድ መልሼ አስቀመጥኳት..
-ምን እያደረክ ነው?በሳቅና በመኮሳተር መሀል ባለ ስሜት ጠየቀቺኝ፡፡
-አንቺው ንገሪኝ እንጄ .እዚህ ምን እያደረግሽ ነው... ? እንዴት መጣሽ ..?.ለምን መጣሽ..?
-አንተን ለማግኘት ነዋ የመጣውት
-እኔ እዚህ እንዳሆንኩ ማን ነገረሽ… ? ውይ ይቅርታ ለካ አንቺ ነሽ››
-አዎ እኔ ነኝ…ግን ምን አየሆንክ ነው ዱላው ለማን ነው ?
-ባክሽ አንድ እባብ ሊያጠቃኝ ነበር …ግን ሀሳቡን ቀይሮ ወደእዚህ ቋጥኝ ገባብኝ … አንቺንም ሊያጠቃሽ ይችል ነበር
-እኔን እንኳን አያጠቃኝም?
-ለምን ?
-ያየኸው እባብ እራሴው ነበርኩ….እራሴን በራሴ እንዴት ላጠቃ እችላለው?፡፡
-ቀልዴን እንኳን አይደለም…ጭንቅላቱን ማለት ነበረብኝ››
-ለምን.?
-እባብ ደግሞ ለምን ይባላል ? የሰው ልጅ እና እባብ ለዘመናት ያላቸውን ጠብ እያወቅሽ… ? ለማንኛውም ነይ ብዬ ቀድሞ ወደነበርኩበት ቆጥኝ ድንጋይ ይዤት ሄድኩና ቀድሜት ተቀመጥኩ ተከተለቺኝና ከገጎኔ ተቀመጠች፡፡
-እኔ ግን ስለሰው እና እባብ ግንኙነት ተቃራኒውን ነው የማውቀው …በማለት ወደ አቋረጠነው ውይይት መለሰችን
-እንዴት ማለት እስኪ አስረጂኝ አልኳት ? ይህቺ ተምረኛ ልጅ ሳለስበው ባገኘዋት ቅፅበት የመጀመሪያ ውይይታችን ስለእባብ የመሆኑ አጋጣሚ ገርሞኝ፡፡
-እሷ ኮስተር ብላ ማብራራት ጀመረች፡፡
‹‹የእባብና የሰው ልጅ እውቅናም ሆነ ልባዊ ወዳጅነት ጥንታዊና መሰረት ያለው ነው፡፡የሰው ልጅ አግዜያብሄር በመልኩና በሀምሳሉ ፈጠረው፡፡የዘን ጊዜ ከጦጣ ወይም ከዝንጀሮ ብዙም የማይሻል ነበር፡፡አንድ ነገር በቃ ልክ እንደ እኛ እና እንደ እግዜያብሄር ከፈጣራቸው ነገሮች መካከል መናገር የሚችል ቢሆንም ከእኛ እኩል ግን የማሰብ ጥበብ አልነበረውም፡፡እግዜያብሄር እንደዛ እንዲሆን አልፈቀደም ነበር፡፡በዚህ ጊዜ የእኔ አባት ቀዳሚው እባብ በውስጥ ሀዘኔታ ገባው፡፡››
-ቆይ ነገሮችን ግልጽ እያደረግሺልኝ ሂጂ..እያወራሽ ያለሽውን እያስተዋልሽ ነው…እባብ ነኝ እያልሺኝ ነው…የሰው ስጋ ለብሼ እንደሰው ማሰብና እንደሰው መሰራት የምችል ለየት ያልኩ ፍጡር ነኝ እያልሺኝ ነው ? ››
-ለየት ያልኩ ፍጡር መሆኔን ትጠራጠራለህ እንዴ?
-አረ በፍፅም …እባብ ነኝ ያልሺውን ነው ማመን ያልቻልኩት ?
-መብተህ ነው …በሂደት ታምናለህ …እስከዛው ዝም ብለህ ተረት እያወራውህ እንደሆነ አድርገህ ስማኝ ..
-እሺ ተስማምቼያለው..ቀጥይ
- እንዳልኩህ እኛ የእባብ ዝርያዎች ቀደምት ስንፈጠር እንደሰው ልጅ በእግዜያብሄር ሀምሳል ባንፈጠርም ቆሞ በእግር መሄድ፤መናገርና ፤ክፉውንና ደጉን፤ ሚጠቅምና ሚጎዳውን በጥበብ አንጥሮ እንደእግዚያሄር ከማሰብ ፀጋ ጋር ነበር የተፈጠርነው፡፡ይሁን እንጂ እግዚያብሄር በወቅቱ በዛ ነገር ደስተኛ አልነበረም፡፡
-ምን ማለትሽ ነው…? እግዚያብሄር አይደለም የፈጠራችሁ ?››
-አዎ እራሱ ነው ? ››
-ታዲያ እሱ አስቦና ፈቅዶ ከፈጠራችሁ ብኃላ እንዴት ደስተኛ ላይሆን ይችላል ? ፡፡
-በእኛ ብቻ እኮ አይደለም ቡኃላም እናንተን ከፈጠረ ቡኃላ ተፀፅቷል ፤ለዚህ ማስረጃ ደግሞ መፃፍ ቅዱሳችሁ‹‹እግዜያብሄር ሰውን በመፍጠሩ ተፀፀተ››ይላል፡፡
-ገባኝ ተዲያ እንዴት ሆናችሁ?....ጠየቅኳት በተረቷ ተመስጬ
-የእኛ ዝርያ ባለው ጥበብ ልክ እንደ እግዚያብሄር ክፉና ደጉን አንጥሮ ማሰብንና …ያሰበወንም ማድረግ በመቻሉ በወቅቱ በነበሩት ፍጥረታት ላይ ድንጋሬ ነበረ…
-ምን አይነት ድንጋሬ?
-አምላካችን የትኛው ነው.. የሚል?
-እና እግዚያብሄርነት… በጥበብና በፍጽሞና ማሰብን ብቻ ሳይሆን ዘላለማዊነትንና ሁለንተናዊአዋቂነትን መያዝ ይጠይቃል…
በዚህ መካከል የሰው ልጅ እግዜያብሄርን መስሎ ተፈጠረ…ከዛ አባቴም በእግዜያብሄር ላይ አቂሞ ነበርና ለዚህ የስው ልጅ ለሚባል አዲስ ፍጥረት እንዴት እግዜያብሄር እንደሚሆን ላስተምረው ብሎ በቀናነት ተነሳ…
-እርግጠኛ ነሽ በቀናነት ነው ?
-እግዚያብሄር ለመሆን የሚያስፈልጉ ሁሉን አዋቂነት እና ዘላለማዊነትን የሚያስገኙ በገነት አትብሉ ብሎ ያገዳቸውን እንዲበሉ በሴቷ በኩል ምክር ለገሳቸው፡፡…የመጀማሪያዋን በልተው ሁለተኛውን ከመድገማቸው በፊት ግን ሲርበተበቱ ደረሰባቸው …
-ምን ጠቀማቸው ታዲያ ከገነት እንዲባረረ ምክንያት ነው የሆናቸው ? ፡፡..የእኔ አስተያየት ነበር፡፡
-እሱ የራሳቸው መንከርፈፍ ነው..ደግሞ እንዳለው ነው… ክፉና ደጉን ያወቁት አባቴ ብሉ ያለችውን እጽ ከበሉ ቡኃላ ነው ሁለተኛውንም ዕፅ በልተው ቢሆን ኖሮ ልክ እንደ እሱ ይሆኑ ነበር…አባራሪና ተባራሪ አይኖርም ነበር
-ያልገባኝ ነገር ታዲያ አባትሽ ማለቴ አባቡ ከዚህ ምን ይጠቀማል..እንደውም ሁለተኛ እግዚያብሄር በላዩ ላይ ይነግስ ነበር…
-አይ የአባቴ እቅድማ ሶስት እግዚያሄር እንዲኖር ነበር…
-እንዴት ሆኖ ?
-ከሄዋን ጋር ሚስጥራዊ ውለታ ነበራው፡፡አባቴ የሚፈልጋትን ሁለተኛዋን ዕጽ ለእሷ እና ለአዳም ስትቆርጥ ለእሱም ለሚስቱና ለልጁ የሚበቃ እንድታመጣለት፡፡ከዛ በሶስት ግዛቶች የተከፋፈለ ሶስት እግዜያብሄር ይኖር ነበር፡፡እቅዱ እንደዛ ነበር፡፡ከዛ ሲርበተበቱ ተያዙ እራሳቸውም
👍41👎1