አትሮኖስ
280K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
459 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#የመልስ_ጉዞ
:
ክፍል- #አንድ

:
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
ፍእማዊ መንግስታዊ አስተዳደር ፤ፍፁማዊ ማህበረሳብ አወቀቀር፤ፍፁማዊ የተፈጥሮ ሚዛኗን የጠበቀች ሀገር..በዩቶፕያ ፅንሰ ሀሳብ የታነፀች ማለት ያቺ ነች ፡፡በነብያት አዕምሮ ውሰጥ ከዘመናት በፊት ተፀንሳ ትንቢት የተነገረላት ሰማያዊ የመኖሪያ ስፍራ በነአፍላጦስ ምናብ የተፀነሰችና በምድር ለመገንባት የተመኙላት ምድራዊ እንከን አልባ የሰለጠኑና የበቁ ማህበረሰቦች የሚኖሩባት ፤በፍፅም ፍትሀዊነት እና በጋራ ህግ የሚመራ መንግስት ያላት፤ ለገነት የቀረበ ልምላሜ ኖሯት አንድ ቀን በጋራ ስምምነት ፍፅማዊ ደስታ የምታመነጭ ተደርጋ የምትመሰረት ምድራዊ ከተማ ….
ታዲያ ይህቺ የአለማዊው እሳቤ እና የመንፈሳዊው ትንቢት ቀላቅላ የያዘች ዩቶፐያ ከወዴት ነች?የሀይማኖት ነብያት እንደሚሉት በሰማይ ከሞት ቡኃላ ባለው ህይወት የሚያገኞት ወይስ ሰው የልዕለ ሰብነትን ዙፋን ሲቆናጠጥ ፍፁም ፍትሀዊ፤ ፍፁም ዘመናዊ ብቃት ባገኘ ጊዜ በብቃትና በጥበቡ እዚሁ ምድር ላይ የሚመሰርታት….?
ወደ ዩቶፕያ መሄጂያ መንገዱ በየት ነው…ዩቶፕያስ የት ነው እውን ሊሆን የሚችለው ….?
እግዚያብሄር መላክ በምስራቅ በኤደን የአትክልት ስፍራ አዘጋጀ ያበጀውንም ሰው በዛ አኖረው፡፡እግዚያሄር አምላክ ለዓይን የሚያስደስት ለመብልም መልካም የሆነውን ዛፍ ሁሉ በምድር አበቀለ፡፡ በአትክልቱ ቦታ መልካም የህይወት ዛፍ ነበር፡፡እንዲሁም መልካምና ክፍውን መለየት ሚያስችል የዕውቀት ዛፍም ነበር፡፡የአትክልት ስፋራ የሚያጠጣው ወንዝ ከዔደን ይፈስ ነበር ፡፡ከዚያም በአራት ተከፍሎ ይፈስ ነበር፡፡የመጀመሪያው በምድሩ ወርቅ የሚገኝበት በሐዊላ ምድር ዙሪያ ሁሉ የሚፈሰው የፊሶን ወንዝ ነው፡፡ኤውላጥ ምርጥ ሆነ ወርቅ መልካም መአዛ ያለው ከርቤና የከበረ ድንጋይ የሚገኝበት ምደር ነው፡፡ሁለተኛው በኢትዬጳያ ምድር ዙሪያ ሁሉ የሚፈስው ግዬን ወንዝ ነው፡፡ሶስተኛው ከአሶር በስተምስራቅ ሚፈሰው የጤግሮስ ወንዝ ሲሆን አራተኛው የኤፍራጠስ ወንዝ ነው፡፡ (ዘፍጥረት ም 2 ቁጥር 8-14 )
ለመሆኑ ይሄስ ስፍራ የት ነው?፡፡የአዳምና ሄዋን ቀደምት መኖሪያ ስፍራ ..?የእውቀትና የዘላለም ፍሬ የሚበቅልበት ሚስጥራዊ ስፍራ…?በአዳምና ሄዋና የተወከሉት የመጀመሪያዎቹ የሰው ልጆች በፈጣሪያቸው ላይ ከብልሁ እባብ ጋር የመከሩበት ፤የመከሩበት ብቻ ሳይሆን የዶለቱበትም ስፍራ የት ነው?፡ከዛስ እርቃናቸውን እንደሆኑ የተገለፀላቸው…?ያን ሰፊ እፍረታቸውን የጋረዱበት ቅጠልስ ከየትኛው ስፍራ ከየትኛውስ ዛፍ ላይስ የተገንጥለው ይሆን? …ከዛስ ወደየት ተባረሩ ?እንዚህ መሰረታዊ ጥያቄዎች ናቸው፡፡የመልስ ጉዞው ወደዛ ነዋ ፡፡አያቶቾ አዳምና ሄዋን ወደተባሩበት ስፍራ ወደ ሀገረ ገነት ...
ይህቺ ሀገር ኢትዬጵያ ነች፤ ይህቺ ሀገር የአያቴ ህልም ነች…ህልሙ ግን በከፊል እንኳን እውን ሳይሆን እድሜ እየተጫጫነው ነው፡፡ቢሆንም ለዚህ አንድ ዘዴ ዘይዷል …ህልሙ ህልሜ እንዲሆን አድርጎል…እንደሱ እንድመኝ ….እንደእሱ እንዳስብ…. ግን ይሄን ህልም እውን ለማድረግ እኔ ምን ማድረግ አለብኝ…ከሚስቴ ጋ እስክገናኝ ምንም የማውቀው ነገር አልነበረም..
አሁን ግን ወደ እዛች ስፍራ ጉዞ ጀምረናል ፡፡እኔና ሚስቴ ፡፡ሁለታችንም የተለያየ የግል ዓላማ አለን ፡፡ግን የየግል አላማችን ከተሳካን ቡኃላም የጋራም አንድ አላማ አለን፡፡ አዎ እንብርት የሆነውን ስፍራ ካገኘን ቡኃላ ዩቶፐያችንን በስፍራው ደግመን እንገነባለን..እንዴት አድርገን.? ወደፊት አብረን የምናየው ይሆናል፡፡
አሁን ወደዋናው የታሪኩ ክፍል ጠልቄ ከመግባቴ በፊት እራሴን ላስተዋውቃችሁ …መቼስ ታሪኬን ስትሰሙ አንዳንዶቻችሁ የተዛባ አዕምሮ የፈጠራቸው የእድሜ ልክ የቀን ቅዥቶች ልትሉት እንድምትችሉ እገምታለው፡፡ይሁንና የእኔን እውነት ነግራችሆለው፡፡ ሳልኩልና ሳልቀባባ ጥሬ እወነቱን ብቻ፡፡ማመን ያለማመን የእናንተ ፋንታ ነው፡፡ግን ከእኔ ጋር ወዳጅነት መስርታችሁ የምነግራችሁን ለማድመጥ በጣም ትዕግስተኛ እና አስተዋይ መሆን አለባችሁ፡፡ምክንያቱም የሆነ ርዕስ ተከትሎ የነገሮችን ቅደም ተከለተልን ጠብቆ ታሪኩን ከመጀመሪያው እስከመጨረሻው ያጫውተናል ብላቹ ምትጠብቁ ከሆነ ከአሁኑ እርማችሁን አውጡ ፡፡እና ንባባችሁን እዚህ ጋር አቋርጡ፡፡
የገዛ የራሴን ታሪክ ለሌላ ሰው እንዴት ማውጋት እንዳለብኝ መወሰን ስልጣን ያለኝ እኔ ብቻ ነኝ ፡፡ስለዚህ ዘባራቂነቴን ካልወደዳችሁት ምንም ልረዳችሁ አልችልም፡፡ዘባራቂነቴ የነፃነቴ መገለጫ ምልክት ነው፡፡ምናቤ በማንኛውም የስርዓትና የደንብ ሰንሰለት አለመጠፍነጉን የሚያሳይ ልቅ መጋለቢያ ሜዳ አይነት ነው፡፡ወይንም በሆነ ቦታ የታጠረ የኩሬ ውሀ ሳይሆን የአባይ አይነት ሀገር ተሸጋሪ ወንዝ ፡፡አዎ የእኔ አዕምሮ እንደዛ ነው፡፡ለነፍሴ ማደሪያ በተሰጠኝ አካል ያልተወሰነ እንዳምንበት ከቤተሰቤ በውርስ በተሰጠኝ ሀይማኖታዊ ዶግማ ያልታጠረ.. በተወለድኩበት ሀገር ድንበር ያልተከለለ….በተፈጠርኩበት ምድር የልተገደበ…እንደዛ ነው ምናቤ… እንደዛው ነው ሀሳቤ …..
እና ታዲያ እንዴት ሆኖ ነው ካልከኝ በዘመን ሂደት ሰው ያው ሰው ነውና መጎዝና አዲስ ነገር ማሰስ ተፈጥሮአዊው ባህሪው እንደመሆኑ መጠን አካባቢውን እየለቀቀ ሲያፈገፍግ ሲዋለድ ሲራባ ሲያፈገፍግ በሚሊዬን ዓመት ሂደት ውስጥ መቶች ውስጥ አለመን አዳረሰና በዚህ ሂደት ውስት ከተፈጥሮ እና እርስበርሱ በሚያደርገው ትግልና ፍትጊያ አእምሮውን እያዳበረ አዕምሮ ሲዳብር ደግሞ ለአካባቢውም ሆነ ለራሱ የነበረው እይታ እየተቀየረ የማምረቻ መሰሪያዎችን እየፈለሰፈ ንግድና እየጀመረ ሲመጣ መልሶ ወደ መነሻው ማየት ጀመረ…ኢትዬጵያ የሰው ዘር ተፈጥሮ የተበተነባት ምድር መልሶም አንድ ቀን የሚሰበሰብባት፡፡

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍5
#አንድ_ነን

ጠረኔ ሲሸተኝ፤ጠረንህ መሰለኝ
ፊቴን ስዳብሰው፤ፊትህን መሰለኝ
አይኖቼን ሳሻቸው፤ አይኖችህ መሰሉኝ
የራሴው ጆሮዎች፤ የራስህ መስሉኝ

አንድ ነገር ግን፤የኔ የሆነው
ያንተ አልመስልሽ አለኝ
ከሁሉ ነገሬ፤እሱ ግን ቀረብኝ
ትለኝ እንዳልነበር

እኔ ማለት አንቺ፤አንቺ ማለት እኔ
ልዩነት የለንም፤ አንድ ነን ሄዋኔ
ትለኝ እንዳልነበር

ታዲያ ምን ለየው፥መልስልኝ ፍቅሬ
ብዬ ስጠይቅህ፤ገረመኝ ምላሽህ

ድስትና ግጣሙ
የተጋጠሙት፤ልዩ ቢሆኑ ነው
አንድ ላይ የሆኑት

እኔ ማለት አንቺ፤አንቺ ማለት እኔ
በእርግጥም ልክ ነው፤እውነት ነው ሄዋኔ

ፆታችን ቢለያይ፤ምንም አይግረምሽ
ሁልጊዜም አንድ ነው
ነገሬ ነገርሽ፤እንደዚያ ስኖን ነው
እንደ ድስቱ እና፤ ክዳኑን ምንሆነው
አቻም የምንሆነው
#ሆሆ

“ወንድ ሆኖ የማያመነዝር ፤ ወታደር ሆኖ እማይሰነዝር ፤ ነጋዴ ሆኖ እማይዘረዝር የለም ! “ይላል ምኡዝ።
እውነቱን ነው፤ከጥቂቶቻችን በቀር ብዙ ወንድ በህይወቱ ቢያንስ አንዴ በትዳሩ ላይ ያድጠዋል። ድርያ በአርቲስት ላይ ይጋነናል እንጂ ፊትና ጭን ከተሰጠው፤ ገበሬ ነጋዴ ፓስተር ሼህ የንስሃ አባት ሳይቀር እንደሚወሰልት እናውቃለን። መቸም የሴት ገላ ማቀፍ እንዴት እንደሚጥም የቀመሰ ያውቀዋል፤ ግን የሚያስከፍለው ዋጋ ከደስታው ጋር አይመጣጠንም፤ አንድ ጣሳ ደስታ ይሰጥህና አንድ በርሚል ጣጣ ያሸክምሃል!!

#አንድ

የሆነ ጊዜ ላይ አሜሪካ ውስጥ ባንድ ከተማ የተከሰተውን ዜና በራሴ መንገድ ስተርተው ይሄን ይመስላል፤
ሰውየው ሚስቱ ማታ ለስራ በሄደችበት ውሽማውን አምጥቶ በተቀደሰው አልጋ ላይ ይፈትጋታል፤ በፍትጊያ መሀል ኮቴ ሰምቶ ቀና ሲል ሚስቱን አያት፤ ውሽምየዋ እንደስፓይደር ውመን በመስኮት ዘልላ ነካችው፤ ባልየው ብቻውን ከሚስቱ ጋር ተፋጠጠ፤ ሚስትዮዋ ለሰይፍ ሩብ ጉዳይ የቀረው ቢላዋ ይዛለች፤ ባሉካ ለመሮጥ ተመኜ ፤ግን እግሩ ቀጤማ ሆነበት፤ በወዛደር አማርኛ እንግለፀው ከተባለ እድሩ የቡልዶዘር ጎማ ሆነበት፤ ሚስትየው ምንም አላለችም፤ አልጋው ላይ እመርር ብላ ወጣችና አገር አማን ነው ብሎ ቆሞ የሚጠብቀውን ብልቱን ጨብጣ ከስሩ መተረችው፤ ከዛ እንደ ቀይ ስር በቁንጮው አንጠልጥላው ወጣችና በቤቱ ጉዋሮ በሚገኘው ዱር ውስጥ ወርውራው ተሰወረች፤
ብዙ ሳይቆይ አምቡላንስ ስልቡን ሰውየ ይዞ ወድ ሆስፒታ መረሸ፤ ያሜሪካ ፖሊስ በቦታው ደርሶ ፤ ከሲአኤ ጋር በመተባበር አካባቢውን በብረት ለበስ መኪና አጥሮ ተቆርጦ የተጣለውን ወሸላ ፍለጋ ተሰማራ፤፤ ከላይ በሂሊኮፍተር ከታች በአነፍናፊ ውሻ የታገዘ ሰአታትን የፈጀ አሰሳ በሁዋላ የተቆረጠው ብልት የጉንዳን መንጋ ወርሶት ተገኘ፤፤ በመጨረሻ ዶክተሮች ወደ ስልቡ ባል ቀርበው፤ “የጠፋብህ ብልት ይሄ ነውን?” ብለው’ በመስቀልኛ ጥያቄ መርምረው አረጋግጠው፤ በቀዶ ጥገና ተከሉለት፤ትንሽ ከመንሻፈፉ በቀር በድሮው ቦታ ተተከለ ፤እረ እንዴውም ከዱሮው ሳይሻል አይቀርም፤ ሚስት ተብየዋን ደስ አይበላትና ሀኪሞች ፤ እንደ ክንዱ በፈለገ ጊዜ የሚዘረጋውና የሚያጥፈው አድርገው ተከሉለት፤

#ሁለት

ይሄ ደሞ ባልንጀራየ የነገረኝ ነው፤
ዲሲ ውስጥ የሚኖሩ ባልና ሚስት ኢትዮጵያውን የተጋቡበትን አስረኛ አመት በማክበር እየተዝናኑ አመሹ፤ከዚያ ሚስትዮዋ” ቤብ፤ በፍቅራችን ላይ ቅመም የሚጨምር ነገር ላሳይህ ” አለችና ከራቫቱን ፈታችለት፤ አያ ‘ቤብ ‘ ክራቫቱን እያስፈታ ፤ ከታች ስራ እንዳይፈታ፤ ቀበቶውን ፈታ፤
ከጥቂት ደቂቃ በሁዋላ አንድ የትራፊክ ፖሊስ መንገድ ዳር ቆሞ ቫይብሬት የሚያደርግ መኪና ስለተመለከተ ጠጋ ብሎ መስኮቱን አንኩዋኩዋ!
“is there any problem ? officer? “ አለ ባልየው ትንፋሹ እየተቆራረጠ።
“መኪና መሳረር ህገወጥ ስለሆነ ልቀጣችሁ ነው” አለና ፖሊሲ ባልየውን መቶ ዶላር ቀጣው፤ ሚስቲቱን ግን ሁለት መቶ ብር ቅጣት ጣለባት፤
ባልየው ትንሽ ቆይቶ ስለከነከነው ፖሊሱን ተከትሎ ደረሰበትና፤
“ቅጣቱስ ይሁን! ይበለኝ፤ የግሬን ነው ያገኘሁት፤ ግን በምን ምክንያት ነው እኔን መቶ ብር ቀጥተህ ሚስቴን ሁለት መቶ ቀጣሃት?’
ፖሊሱ እንዲህ መለሰ፤
“እ ሷ መኪና ውስጥ እንዲህ አይነት ነገር ስታደርግ ያገኘሁዋት ለሁለተኛ ጊዜ ነው፤ ለዝያ ነው እጥፍ ያስከፈልኩዋት”😳
ባልየው በድንጋጤ ታሞ ይሄው በጎፈንድ ሚ እያስታመምነው እንገኛለን፤

🔘በውቀቱ ስዩም🔘
👍3
#አንድ_ጣት

ሰው ትንሽ ነው” ተብሎ
እንደምን ይናቃል
ለማብራት ለማጥፋት
አንድ ጣቱ ይበቃል።
ጓደኛ ነው:: አብርሃም ነው፡፡

ናትናኤል ትክ ብሎ አለቃውን ተመለከታቸው፡፡ አይናቸውን ሰበሩ።
በጎንና በጎን ያንጠለጠሏቸው ክንዶቻቸው የእርሳቸው የራሳቸው እንዳልሆነ
ሁሉ ረዘሙበት፤ ተንዘላዘሉዐት:: እንደገና ቀና ብለው ሲያዩት ኣይኖቻቸው
ውስጥ የሚጋልበውን ያልተገራ ሌጣ ፍርሃት ተመለከተ። አዘነላቸው፡፡
ተፀየፋቸው፡፡

ግድ የለም፡፡ ብቻውን ወደ ጨለማው ይወጣል፡፡ ያለረዳት ብቻውን አድኖ ይይዛቸዋል፡፡ ቀድሞውንም አለቃውን ተማመኖ አልተነሳም፡፡ ቃል ገብቷል ለአብርሃም አልተዋቸውም ብሎታል፡፡ ሞት? ግድ የለውም::አብርሃም እንኳን ልጁን ትቶ ሄዷል፡፡ እሱ አንድ ነው። ብቻውን ነው፡፡ ቢቀርም ቢሄድም ማንንም አይጎዳም፡፡ርብቃ? አዎ፡፡ ግን ቢጤዋን አታጣም፡፡ ቃል ገብቷል፡፡ ከአሁን ወዲያ አይመለስም፡፡ ህግ ፊት እስኪያቀርባቸው፣ በገመድ ተንጠልጥለው ዥው ዥው ሲሉ እስኪያይ አያርፍም፡፡

“የአመት ፈቃዴን አሁን መውሰድ እችላለሁ?” አላቸው አለቃውን አልትናገሩም ጭንቅላታቸውን በ'አዎንታ ነቀነቁለት፡፡ የዘረጉለትን እጃቸውን ሳይጨብጥ ፊቱን መለሰ፡፡ የቢሮአቸውን መዝጊያ ከፍቶ ከመውጣቱ በፊት የበሩን እጀታ እንደጨበጠ ዞር ብሎ አይኖቹን አጥብቦ ተመለከታቸው::

“ዓርብ እለት አንድ መላምት ላይ እንድደርስ ጠይቀውኝ ነበር፡፡ የጠየቁኝ መላምት ላይ ደርሻለሁ…አዲስ ኣበባ ውስጥ አንድ አውሬ ገብቷል፡፡” አላቸው፡፡

ለአንድ አፍታ አገጫቸው የተንጠለጠለ መሰለው፡፡ የቢሮቸውን በር ዘግቶ ወደ ቢሮው አመራ፡፡

ወደ ቢሮው ተመልሶ ጠረጴዛው ላይ የነበረውን ወረቀት ሁሉ እየሰበሰበ በመሳቢያው ወስጥ ያጭቅ ጀመር፡፡ ብዕሮች፣ ወረቀቶች፣ መስፊያዎች፣ የፋይል ትሪዎች አንድ በአንድ እየተነሱ ከታችኛው መሳቢያ ወስጥ ታጎሩ፡፡ ጠረጴዛው እራቁቱን ሲቀር ከወንበሩ ላይ ተቀመጠና ሁለት መዳፎቹን በባዶው ጠረጴዛ ላይ ጫናቸው፡፡ ካልቨርትን አግኝ… ካልቨርትን የአብርሃም ድምፅ ደጋግሞ ተሰማው፡፡

ሙሉ ሃሣቡን አሰባስቦ አንድ ቦታ ማዋል አለበት… ባለው ኃይሉ ፈጥኖ ማስብ አለበት፡፡ ብቻውን ነው::፡ ጠላቶቹ የዋዛ አይደሉም፡፡ አብርሃም እንዳለው እንደ እሳት እራት ወደፍሙ እየተሽቀዳደመ ነው… መቃጠል የለበትም መንደድ የለበትም…መጋየት የለበትም….ሁልጊዜ . መቅደም አለበት ሁሉጊዜ ከፊት መገኘት አለበት… መበለጥ አይችልም… ሁልጊዜ
መብለጥ አለበት፡፡ አለ እንደ አብርሃም ያበቃል አለዛ ያቆማል…ሁሉም ነገር ያከትማል፡፡ ማክተሙን አያፈራም፡፡ ግን እሳቱን ማጥፋት አለበት፡፡ የንፁሃንን ነፍስ እየቀጠፈ በመሃላቸው የሚመላለሰውን አውሬ አጥምዶ መያዝ አለበት፡፡ ከየት ነው መጀመር ያለበት? ለፖሊስ ማስታወቅ? አዎ ፖሊስ ጋ ሂዶ ጉዳቸውን ማፍረጥረጥ! የስውር ክትትል ዘርግቶ አንድ በአንድ ማስለቀም፡፡ ግን…

የአብርሃም አደራ ታወሰው “ካልቨርትን አግኝ.… ካልቨርትን…” ናትናኤል መሳቢያውን ስቦ ነጭ ወረቀት አወጣ፡፡ ከደረት ኪሱ ውስጥ ብዕር፡፡ ነጩ ወረቀት ላይ ሃሣቡን ያሰፍር ጀመር፡፡

#አንድ፡ በአፍሪካ ኤምባሲዎች የሚሰሩ ወታደራዊ አታሼዎች ወደየአገሮቻ
ቸው እየተጠሩ ሄዱ ማለት የየአገሮቻቸው መንግስታት ሊገልፁላቸው፣ ሊያሳውቋቸው፣ ሊያስጠነቅቋቸው የሚገባ ሁኔታ ተፈጠረ፡፡

#ሁለት፡ አንዳንድ አታሼዎች ሲመለሱ የተቀሩት በሌሎች ተተኩ ማለት…
ገሚሶቹ ለተመደቡበት ሃላፊነት ብቁ ሆነው በመገኘታቸው ሲመለሱ፣
የተቀሩት ለሃላፊነቱ ተስማሚ በሚሆኑ በሌሎች ተተኩ፡፡

#ሶስት፡ ለሥራው ብቁ ተብለው ከተመለሱ አታሼዎች መካከል በአንድ ሳምንት ውስጥ ሁለት ተገድለው ሲገኙ አንድ የገባበት ጠፋ ማለት...
የተሰጣቸውን ማስጠንቀቂያ ችላ በማለታቸው አለበለዚያም ብቃት
ስለጎደላቸው በአውሬው ተበሉ…. ሁለት ተወገዱ ፤አንድ ተሰወረ፡፡

#አራት፡ ሁኔታውን መከታተሉና ማጣራቱ ተገቢ ቢሆንም የኢትዮጵያ መንግሥት አካላትም ሆኑ ሌሎች የኣፍሪካ መንግሥታት ነገሩን መሽፋፈን መረጠ ማለት… የአፍሪካ መንግሥታት እንዳይወጣ የሚሉት ምሥጢር ተፈጠረ አለዚያም በዙሪያቸው የተተበተበው የአውሬው መረብ መነቃነቅ ከለከላቸው፡፡

#አምስት: አንዳንዶቹ የጠፋውን የላይቤርያ አታሼ ለማግኘት በግል ያደረ
ጉት ጥረት ኣደጋ ላይ ጣላቸው ማለት... የላይቤርያው አታሼ አድራሻ እንዳይገኝ የሚሉ ወገኖች ምሥጢሩ እንዳይጋለጥ ሲሉ ነፍስ እስከማጥፋት ይደፍራሉ፡፡

ናትናኤል ድንገት አንድ ጥያቄ ተደነቅረበት፡፡ አብርሃም ብቻ አልነበረም የላይቤርያውን አታሽ አድራሻ ያነፈነፈ። እንዳውም በተቃራኒው ነገር ቆስቋሹ እርሱ ራሱ ነበር፡፡ ታዲያ ለምን አብርሃምን ገደሉት… እሱንስ ለምን ተውት....

💫ይቀጥላል💫
👍2
#አንድ_ሌላ_መንገድ

ገደል ዋሻ ጥቁር እሳት
ተንኮል ክፋት ምቀኝነት
ሸር ደባ ሀጣ ብኩን
በግራ ጎን በቀኝ ጎን
ሕልም ራዕይ አዲስ ሕይወት
ትግል ስኬት ጣፋጭ ስሜት
ረዥም መንገድ ከፊት ለፊት

ትእዛዝ ቁጣ መርገምት ሥራይ

ያ'ዳም ቅርሻት ክፉ ክፋይ
ከላይ
እሾህ ጉድፍ አሜኬላ
ከኋላ
የድካም ድግ ጎታችና ተጎታች
ከታች
.
.
.
አንድ ተአምር ተፈጥሮ
ሕይወት መጋረጃ ቢኖራት
የሚጋረደውን ጋርጄ
ፊት ለፊት ነበረ የማያት።

🔘ሰለሞን ሳህለ🔘
8👍4
#አንዲት_መርፌ_ስንቱን_ቀዳዳ
#ትስፋው?


#አንድ


#በአሌክስ_አብርሃም


ዙቤይዳ ስልክ ደወለችና “አብርሽ…” አለችኝ፤ ድምጿ ውስጥ ምቾት አለ አይጎረብጥም የዙቤይዳ ድምፅ ከዙቤይዳ ቆዳ የተቀመረ ይመስለኛል፤ ቆዳዋ ደግሞ ድምጿን የለበሰ ሁለቱም ነፍሴን ይለሰልሱኛል።

“ወይዬ የኔ ቆንጆ…! የኔ ማር የኔ ለስላሳ... የኔ ሐር! የኔ ፍቅር…የኔ ደስታ…! የኔ .….ሳቅ! ..የኔ ፌሽታ
!…የኔ ሐሴት !የኔ…

ዙቤይዳ ዝም ብላ ስታዳምጠኝ ቆየችና (ዝምታዋ እስክርቢቶና ወረቀት ይዛ ያልኩትን ሁሉ
የምትመዘግብ ነበር የሚያስመስላት) ረጋ ብላ “አባባ ሊያናግሩህ ይፈልጋሉ” አለችኝ።

“ምን…?” ብዬ በድንጋጤ ዝም አልኩ የጨው አምድ ! ይሄማ ቀልድ ነው ። “ ዜድ አንች ደግሞ
በማይቀለደው ትቀልጃለሽ”

“ወላሂ እየቀለድኩ አይደለም አብርሽ” አለችኝ። ረዥም ዝምታ መሃላችን ሰፈነ።

“ምነው ድምፅህ ጠፋ? 'አንበሳ እገድላለሁ የሚለው ባልሽ…ቅጠል ሲንኮሻኮሽ ገደል ገባልሽ' ሂሂሂሂ…” ብላ በሚያምር ሳቋ ተቅጨለጨለች። ይሄው ናት የእኔ ዙቤይዳ፣ በየትኛውም አስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ ብትሆን ወይ ፍንክች ከሳቋ ! የተረጋጋች ! እርጋታዋ ደግሞ የሚያረጋጋ ደግሞ እሷ ላይ ብቻ አይቆምም
ይተላለፋል ..እንደሽቶ ከእርሷ ላይ ይነሳና በመረጋጋት ጠረኑ ነፍስን ያውዳል።

“አባባማ ቅጠል ብቻ አይደሉም ትቀልጃለሽ እንዴ…፤ ግንድ ነው የወደቀብኝ” አልኳት። አባባ
የምትላቸው አባቷን ጋሽ ጀማልን ነው ። በጣም የሚገርመኝና የሚደንቀኝ ነገር የዙቤይዳ እህትና
ወንድሞች በሙሉ አባታቸውን “አንቱ” እያሉ ነው የሚጠሯቸው ! አንድ ቀን ታዲያ ዙቤይዳን
ጠየቅኳት “ዜድዬ እንዴት አባትሽን አንቱ ትያለሽ ?”

“ትልቅ እህቴ ዘሐራ አንቱ ስትል ሰማሁ፤ በዛው ቀጠልኩ። የእኔ ታናናሾችም አንቱ ነው እኮ የሚሏቸው፤”አለችኝ! ትልቅ እህቷ ዘሐራ ጋር (የዛሬን አያድርገውና) እንግባባ ስለነበር ዘሐራንም ጠየቅኳት፣ “ዘሐራ አባት አንቱ ይባላል እንዴ?”

“ትልቅ ወንድማችን አንዋር አንቱ እያለ ይጠራቸው ስለነበር በዛው ለመድኩ።” አለችኝ፤ሲወርድ
ሲዋረድ የመጣ አንቱታ። በጣም የሚያስቀው ታዲያ የመጀመሪያው የአንቱታው ጅማሬ ትልቁ ልጅ
ኡስማን ሲሆን የጋሽ ጀማል ልጅ ሳይሆን ገና ትዳር እንደመሠረቱ ልጅ ሳይወልዱ በፊት አብሯቸው
መኖር የጀመረ የጓደኛቸው ልጅ ነበር። ከዛ በኋላ የተወለዱት ሁሉ አባታቸውን አንቱ እያሉ ቀጠሉ።

የዙቤይዳ አባት ጋሽ ጀማል የተፈሩ፣ የተከበሩ የአገር ሽማግሌ፣በዛላይ አዱኒያ ሞልቶ የተልከሰከሰላቸው ሀብታም ናቸው !በዓመቱ ለረመዳን ዝሆን የሚያካክሉ በሬዎች እያረዱ ሰደቃ ያበላሉ፣ ሚስኪኖችን ያስፈጥራሉ ቤታቸው አስፈሪ ግርማ ሞገስ አለው። ወደ ላይ የአጥሩ ግንብ ርዝመት፣ እንኳን ተራማጅ ፍጥረት በራሪም አዕዋፍት የሚዘሉት አይመስሉም። በዛ ላይ አጥሩ ጫፍ ላይ የተጠማዘዘው ሽቦ … አንዳንዴ የነዙቤይዳን አጥር ስመለከት ከመኖሪያ ቤትነት ይልቅ በሠሩት ወንጀል የዘላለም
እስራት የተፈረደባቸው አደገኛ እስረኞች የታጎሩበት እስር ቤት ይመስለኛል።

ታዲያ ፍቅር የሚባል ጉድ የማያሻግረው ወንዝ፣ የማያዘልለው ከፍታ የለምና መሰላል ሆኖ ይሄን አጥር አዘለለኝ። ምን ማዘለል ብቻ፣ ግቢውን አልፌ፣ የዋናውን ቤት በር በርግጄ እነዙቤይዳ ሳሎን
እዛ የሚያምር ምንጣፍ ላይ ከነጫማዬ ስቆም ቤተሰቡ ተበጣበጠ። ዙቤይዳ የምትባለውን ወርቅ የሆነች ልጃቸውን አፍቅሬ “አገባታለሁ” አልኩ ! ዙቤይዳም ብትሆን የምትይዝ የምትጨብጠውን
እስክታጣ አፍቅራኝ ነበር። ግን ዙቤይዳ እንደ እኔ ማሬ፣ ፍቅሬ ጅኒጃንካ አትልም፤ዝም ብላ ዓለምን በሚያስረሱ ውብ ዓይኖቿ የፍቅር ጅረት እያጎረፈች ነፍሴን በሐሴት ታረሰርሰዋለች።

ዶሮ እንቁላሏን አቅፋ በሙቀቷ ጫጩቶቿን እንደምታስፈለፍል ዙቤይዳም በሩህሩህና ደግ ፀባይ እቅፍ አድርጋኝ ከዚህ ዓለም በሻገተና በክፋት በበሸቀጠ ቅርፊት የተጠቀለልኩ እኔን በፍቅር ትወልደኛለች። በዓይኗ እቅፍ አድርጋ ታሞቀኛለች። ዓይን የተፈጠረው ሁሉን ለማየት ነው ሲሏችሁ አትስሙ። የዙቤይዳ ዓይን የተፈጠረው እኔን ብቻ ለማየት ነው። አቤት ዙቤይዳ ማየት ስትችልበት ! አስተያየቷ
ቅኔ አለው። አስተያየቷ ጀግና ያደርገኛል፤ አስተያየቷ ሁሉ ነገሯን እንደሰጠችኝ የሚያረጋግጥ የብርሃን ፊርማ ነው! ዙቤይዳን በሙሉ ልቤ አፈቅራታለሁ።

እናቷ ቢመክሯት፣ አባቷ ቢዝቱና ቢቆጡ፣ ወንድሞቿ በቀን ሁለት ጊዜ (ጧትና ማታ) ቢሸልሉ ቢፎክሩ… ዙቤይዳ የኔ የፍቅር ሰው ወይ ፍንክች !! “አብርሽን እወደዋለሁ! ወላሂ እወደዋለሁ
ብላቸው እርፍ።

ወንድሟ የዙቤይዳ ነገር አልሆን ቢለው እኔጋ መጣና፣ “ለቀቅ አድርጋት” አለኝ።

"ዜድን እወዳታለሁ! እግዚአብሔርን እወዳታለሁ!” አልኩታ። በዛ በዚህ በመሐላ የታጠረ ፍቅር። በየእምነታችን ለአንድ ፍቅር አምላኮቻችንን ምስክር ጠርተን ወይ ፍንክች አልን። ቤተሰቦቿ ግራ
ሲገባቸው ሳይመርቁንም፣ ሳይረግሙንም ግራ እንደገባቸው በቆሙበት እኛም ፍቅራችንን ዓይናቸው ስር ቀጠልን።

ይሄ የዙቤይዳ እኔን ማፍቀሯና ፍቅሯንም አፍ አውጥታ መናገሯ እነዙቤይዳ ቤት ታላቅ ታሪካዊ
ድፍረት ተደርጎ ተመዘገበ። የቅድም ቅድም ቅድም አያቶቿ ሁሉ ይሄን ድፍረት ቢሰሙ፣ መቃብራቸውን እየፈነቃቀሉ ተነስተው ሃዘን ይቀመጡ ነበር ።
እንደ ቤተሰቦቿ አባባል።

“ይሄ አብርሃም የሚባል ልጅ ፣ወይ አንድ ነገር አስነክቷታል ወይም እህታችንን ኢብሊስት ጠግቷታል”
አለ አሉ ወንድሟ ... ራሷ ዙቤይዳ ናት የነገረችኝ።

“ኢብሊስ ምንድን ነው ዜድዬ?” አልኳት። ዙቤይዳን ስሟን ሳቀናጣው ዜድ አደርገዋለሁ።

“ኢብሊስማ የሸይጧን አለቃ ነገር ነው” አለችና ከት ብላ ሳቀች።

“አሁንስ ወንድምሽ አበዛው! ወይ አንቺ ትርጉሙን አሳስተሽዋል ..ወይ ወንድምሽ ነገር ፈልጎኛል እንዴ ... አሁን ለኔ አለቃነቱን ትቶ ምናለ ተራ ሰይጣን ቢያደርገኝ…”

"ሂሂሂሂሂሂሂ የኔ ቆንጆ ! ተራ ሰይጣንማ ብትሆን እንዲህ በፍቅር አታሳብደኝም” ብላ በፍቅሯ ታሳብደኝና ...በሆነ በምወደው አስተያየት ዓይኖቿን ጣል ታደርግብኛለች። ባየችኝ ቁጥር የሆነ ማዕረግ የተጨመረልኝ ይመስለኛል። የኔ ማር እንዴት እንደማፈቅራት እኮ ! ስትስቅ ብዙ ቀን ምኗን
እንደምስማት ታውቃላችሁ? - ጥርሷን !! ያው ጥርሷን ስሜ ስመለስ አግረ መንገዴን ከንፈሯንም መዘየሬ አይቀርም ታዲያ! እውነቱን ለመናገር ለዙቤይዳ ነፍስህን ስጥ ብባል እሰጣለሁ…፤እሳሳላታለሁ። ሰው ሲያያት የምታልቅብኝ ነው የሚመስለኝ። እንደ ጣፋጭ ከረሜላ ስሟ አፌ ውስጥ ሲሟሟ ይሰማኛል።ፈሳሹ በጉሮሮዬ አድርጎ ልቤን ሁሉ አረስርሶ እስከ እግር ጥፍሬ ውስጤን ሲያጣፍጠው ይታወቀኛል እኔ ራሴ ትልቅ ጣፋጭ የሆንኩ ይመስለኛል፤ንግግሬ ሲጣፍጥ ለራሴ ይሰማኛል !! ዙቤዳ ስሟ
ከፊደላት አይደለም የተፃፈው …. 'አግቹጳርስደፈሬተገፈዴዮ' ከሚባል በገነት ከሚገኝ ፍሬ ጭማቂ ነው ተቀምሞ የተሰራው። ይሄ ፍሬ መልአክቶች ለዓመት በዓል የሚመገቡት ጣፋጭ ፍሬ ነው፤ ቅርፁ የብርቱካን ዓይነት ሆኖ ልጣጩ ከብርሃን የሚሠራ ! እሰይ!! ዙቤይዳዬን እንዲህ ሳደንቃት ሳሞግሳት
ባይወጣልኝም ደስ ይለኛል!ይገባታል! የኔ ውብ !
👍402👎2
#ድንቡጮ_ለምን_ለምን_ሞተ?


#አንድ


#በአሌክስ_አብርሃም

ሰፈራችን ውስጥ መክብብ ግሮሰሪ የምትባል አለች። ማታ ማታ ፀሐይ ሲያዘቀዝቅ ትልልቅ ሰዎች በረንዳዋ ላይ ተሰባስበው እያወሩ ጅን የሚባል መጠጥ ድርፍጭ ባሉ ብርጭቆዎች የሚጠጡባት።በግሮሰሪዋ ሁሉም ዓይነት መጠጥ ቢኖርም በረንዳ ላይ የሚቀመጡት ሽማግሌና ጎልማሶች ግን ልክ ዕድሜ ይቀጥል ይመስል ጅን ብቻ ነበር የሚጠጡት። በሯ ላይ በግራ በኩል እንደ ኤሊ ፍርግርግ
ድንጋይ የለበሰ የሚመስል ግንድ ያለው የዘንባባ ዛፍ የግሮሰሪዋ ግርማ ሞገስ ነው። ይህች የዘንባባ ዛፍ ለጥምቀት ሰፈራችንን አቋርጠዉ የሚያልፉት ሁለት ታቦታት ከመለያየታቸው በፊት የሚቆሙባት የታቦት መቆሚያ ነበረች። ባለቤቱ አባባ መክብብ ይባላሉ።አጭር፣ ሙሉ ፀጉራቸውን ነጭ ሽበት
የወረሰው፣ ከባድ ሌንስ ያለው መነፅር የሚያደርጉ ሰውዬ ናቸው።

አባባ መክብብን ባየኋቸው ቁጥር የሚገርሙኝ ሁለት ነገሮች አሉ። የመጀመሪያው ግርምቴ አፋቸው
ውስጥ ምግብ ኖረም አልኖረም በባዶው ያላምጣሉ። አፋቸው አያርፍም፤ ዝም ብሎ ያላምጣል። በፊት በፊት ማስቲካ የሚያላምጡ ይመስለኝ ነበር። ታዲያ ትልልቅ ሰዎች ማስቲካ ብዙም ስለማያላምጡ አባባ መክብብ ዘመናዊ ሽማግሌ ይመስሉኝ ነበር። በኋላ ከፍ ስል ግን እንደው ልማድ ኾኖባቸው ነው…. ሲባል ሰማሁ። ሲያወሩ ሁሉ በየመሀሉ ባዶ አፋቸውን እንደሚያላምጥ ሰው እያንቀሳቀሱ አየር ያኝካሉ። ሁልጊዜ ሙልጭ ተደርጋ የምትላጭ ትንሽ አገጫቸው ላይና ታች ከፍ ዝቅ ስትል ነው
የምትውለው። ታዲያ አንዳንዴ ሊልኩኝ ፈልገው ወይም ለሆነ ጉዳይ በባዶው በሚያኝኩት አፋቸው “አብራም” ሲሉኝ ስሜን አላምጠው የተፉት ይመስለኛል። በዛ እድሜዬ የሚመስለኝ ነገር ይበዛ ነበር።

ሁለተኛው ከአባባ መክብብ የሚገርመኝ ሱሪያቸው ነው። ሱሪያቸው ከታች እስከላይ ይገርመኛል።ከግርጌው እንደዣንጥላ ጨርቅ ወደ አንድ በኩል ተጠምዝዞ ይጠቀለልና ካልሲያቸው ውስጥ ይጠቀጠቃል። በእርግጥ የእኔም አባት እንደዛ ያደርጋል። ግን አባባ እንደዛ የሚያደርገው ዝናብ ጥሎ
መሬቱ ሲጨቀይ ብቻ ነው። አባባ መክብብ ግን ሁልጊዜም ነው የሚያጭቁት። ከላይ ደግሞ ጥቁር የቆዳ ቀበቷቸው ወገባቸው ላይ ሳይሆን ከእንብርታቸው ከፍ ብሎ ከልባቸው ሥር ... እዛ ላይ ነው ቅብትር ተደርጎ የሚታሰረው። ከነተረቱ ሰፈራችን ውስጥ የሆነ ሰው ሱሪውን ከፍ አድርጎ ከታጠቀ
“ምነው እንደአባባ መክብብ ሱሪህን ደረትህ ላይ ሰቀልከው ?” ይባላል።

ሌላም የረሳሁት ሦስተኛ አስገራሚ ነገር አለ። አባባ መክብብ ደንበኞቻቸውን እያስተናገዱ (ሁሉም ደንበኞቻቸው በርሳቸው ዕድሜ ስለሆኑ ከደንበኛ ይልቅ ጓደኞቻቸው ይመስሉኛል) ከመኪና ላይ ቢራ እያስወረዱ ወይም ግሮሰሪው በር ላይ በጉርድ የብረት በርሚል የተሞላ ፉርሽካ ተዘርግፎላቸው የሚበሉትን ሦስት ሙክት በጎቻቸውን እየተመለከቱ የሚሠሯት አንዲት ነገር አለች፤ ከእጃቸው በማትለየውና የቀንድ እጀታ ባላት የጢም መላጫቸው በደረቁ ጉንጫቸውን፣ አገጫቸውንና የአገጫቸውን ሥር ይፈገፍጋሉ ሁልጊዜ። እንደውም ሰው ሰላም ሲሉ የጢም መላጫቸውን በቀኝ እጃቸው ስለሚይዙ ለመጨበጥ አይመቻቸውም። እናም እንደጨበጧት አይበሉባቸውን
አዙረው ሰላም ወደሚሉት ሰው እጅ ይዘረጉና ነካ አድርገውት እጃቸውን ይመልሳሉ። ታዲያ የጢም መላጫቸውን የበረንዳዋ መከለያ ብረት ላይ ኳ ኳ አድርገው ያራግፏታል ! ድምፁ እስካሁን ጆሮዬ ላይ አለ።

አባባ መክብብ በመንደሩ ሰው በሙሉ “ደግ ሰው ናቸው…” ነው የሚባሉት። ግሮሰሪው በር ላይ
ለበጎቻቸው ፉርሽካ ከሚቀመጥበት ጎራዳ በርሚል ራቅ ብሎ ሰማያዊ የፕላስቲክ በርሚል በውኃ ተሞልቶ ይቀመጣል። በርሚሉ ጋር በረዶ በመሰለች የኤሌክትሪክ ገመድ ጫፏ ተበስቶ የታሰረ ቢጫ
የቲማቲም ሥዕል ያለባት የመርቲ ጣሳ አለች ... በርሚሉና ጣሳው ከድሮ ጀምሮ ስለማይነጣጠሉ
በኤሌክትሪክ ገመድ እትብት የተያያዙ እናትና ልጅ ይመስሉ ነበር። እንግዲህ አላፊ አግዳሚ የኔ ቢጤ ውኃ ከጠማው ከዛ በርሚል በጣሳዋ እየጠለቀ ይጠጣል። ትንሽ ልጆች እንደነበርን ውኃው የተለየ
ነገር ስለሚመስለን እኛም እየተደበቅን እንጠጣ ነበር። በኋላ ግን ወላጆቻችን “ማንም በሚጠጣበት እየጠጡ ኮሌራ ሊያመጡብን…” እያሉ ሲቆጡን አቆምን !

ምንጊዜም የቡሄ በዓል ሲሆን የሰፈር ልጆች ተሰባስበን አንደኛ የምንሄደው አባባ መክብብ ግሮሰሪ ነበር። ፈንታው ድንቡጮ የሚባል ጓደኛችን አውራጅ ይሆናል። አባባ መክብብ ፈንታውን በጣም ነው የሚወዱት። ጉንጩ ድንቡጭ ያለ ስለሆነ ነው መሰል 'ድንቡጮ' እያሉ ነው የሚጠሩት። በዚሁ ሰበብ ጓደኛችን ፈንታው ፈንታው ድንቡጮ ተብሎ ቀረ። ግሮሰሪዋ በር የዘንባባውን ግንድ ተገን አድርጎ
የተቀመጠ ትልቅ ድንጋይ ላይ ካርቶን ጣል አድርጎ እንደ ወንበር በመጠቀም ሊስትሮ ይሠራል።
ጫማውን የሚያስጠርገው ደንበኛ ድንጋዩ ላይ ተቀምጦ የዘንባባውን ግንድ ደገፍ ይልና ከድንጋዩ ሥር
ብሩሹን ይዞ ለሚጠብቀው ፈንታው እግሩን ያቀብለዋል። ታዲያ ያች ድንጋይ የፈንታው ድንቡጮ ድንጋይ' ነው የምትባለው። የእኛ ሰፈር አክሱም ናት. የእኛ ሰፈር ላሊበላ ናት... የእኛ ሰፈር ውቅር የሊስትሮ ወንበር ናት ... የእኛ ሰፈር አፈ ታሪክም ናት!

“በድሮ ጊዜ እግዜር ለቅዱስ ድንቡጮ ተገለጠለትና እንዲህ አለው፣ 'ልጄ ድንቡጮ ሆይ፣ ምድር የእግሬ መርገጫ መሆኑን ሰምተሃል.. እንግዲህ እግሬ ምድር ላይ ሲያርፍ የወርቅ ጫማዬን ትቦርሽ ዘንድ የእግሬን ማረፊያ ድንጋይ በዚህ አስቀምጥ .. የሚል ራዕይ ተገልጦለት ከእንጦጦ ድረስ ይቺን ድንጋይ በኤኔትሬ መኪና አስጭኖ ወደዚህ ሰፈር አመጣት .…”

ታዲያ የሰፈሩ ልጆች ለቡሄ አባባ መክብብ ግሮሰሪ በር ላይ እንሄድና ጭፈራውን እናወርደዋለን።እሳቸውም በጢም መላጫቸው ግራ ቀኝ ጉንጫቸውን በደረቁ እየፈገፈጉና ብረቱ ላይ
ኳኳ አድርገው እያራገፉ ግጥማችንን በጥሞና ያዳምጣሉ፤

“እዛ ማዶ…
ሆ!
አንድ ሞተር
ሆ!
እዚህ ማዶ!
ሆ!
አንድ ሞተር!
ሆ!
የኔ አባባ መከብብ!
ሆ!
ባለ ዲሞፍተር!
"ሂዱ ወዲያ ! የምን ዲሞፍተር ነው …” ይሉና ይቆጣሉ። ረስተነው ነው እንጂ አባባ መክብብ የጦር
መሣሪያ አይወዱም። እንደውም መሣሪያ ታጥቆ ወደ ግሮሰሪያቸው የሚሄድ ደንበኛ ያስወጣሉ
እየተባለ ይወራ ነበር። ታዲያ ይችን አመላቸውን ስለምናውቅ በቁጣቸው አንደነግጥም። ፈንታው ድንቡጮ ወዲያው ግጥሙን ይቀይረዋል … እሳቸውም ወዳቋረጡት ጢም መላጨታቸው ተመልሰው
አንጋጥጠው የአገጫቸውን ሥር እየፈገፈጉ ዓይኖቻቸውን ጨረር እንዳይወጋቸው ጨፍነው
ይሰሙናል ...

“እዛ ማዶ!አንድ አፍንጮ፣
የኔ አባባ መክብብ ባለ ወፍጮ…!
እዛ ማዶ!አንድ በሬ፣
የኔ አባባ መክብብ ጀግና ገበሬ..”

ሃሃሃሃ እንደሱ ነው የሚባለው እደጉ! እደጉ! ድንቡጮ! ... ና ወዲህ …” ይሉና የጢም
መላጫቸውን ወደ ግራ እጃቸው አዘዋውረው በቀኝ እጃቸው አጭሯን የሥራ ገዋን ወደ ቀኝ ገልበው ሱሪያቸው ኪስ ውስጥ እጃቸውን ካስገቡ በኋላ በጣም ብዙ ተዘበራርቆ የተቀመጠ ብር (ድፍን የመቶና የሃምሳ ብር ኖቶች የሚበዙበት) ዘግነው ያወጣሉ። ከዝግኑ መሃል መርጠው ድፍን አምስት ብር ከለዩ
በኋላ (ይሄ ድርጊታቸው ቀልባችንን ስለሚወስደው ጭፈራችን ቀዝቀዝ ይላል…) ሌላውን ብር ወደ ኪሳቸው መልሰው ሲያበቁ ብሩ ላይ ትፍ ትፍ ብለው ድንቡጮ ግንባር ላይ ይለጥፉታል (እንደውም
ግንባሩ ለሽልማት ይመቻል) ..እኛም ሞቅ ይለናል ፤ ጭፈራውን በአዲስ ጉልበት ምርቃቱንም ለየት ባለ ፍቅር እናዥጎደጉደዋለን።
👍25🔥31
#ከሰሀራ_በታች


#አንድ


#በአሌክስ_አብርሃም

የፍቅርተ ጂንስ ሱሪ ታጥቦ ከተሰጣበት የልብስ ማስጫ ገመድ ላይ ጠፋ፡፡ “የትኛው ሱሪ?”
የሚል ይኖራል፤ ፍቅርተ የነበራት አንድ ሱሪ ነበር፡፡ የጠፋውም ይሄው አንድ ለናቱ የሆነ ሱሪ ነው፡፡ የመንደሩ ሱሰኛ ጎረምሶች ለዕለት ሱሳቸው ማስታገሻ ወስደው ሸጠውት ይሁን አልያም ሞገደኛ ነፋስ እያግለበለበ ወስዶ አንዱ ቂርቂራ ሸጉጦት እግዜር ይወቅ፡፡ ግራም ነፈሰ ቀኝ ከተገዛ ገና ስድስት ወር ብቻ የሆነው፣ ግርጌው ቀበኛ ከብት አኝኮ እንደተወው ጨርቅ
የተተፈተፈው የፍቅርተ ጥቁር ጅንስ ሱሪ ታጥቦ ከተሰጣበት ገመድ ላይ ጠፋ፡፡ ትልቅ የአገር
ቅርስ የጠፋ ያህል ነበር አንጀቴ ቁርጥ ያለው፡፡ ደምና አጥንት የተከፈለለት የአገር ድንበር
የተቆረሰ ያህል ነበር ውስጤ በቁጭት የተንገበገበው፡፡

በእርግጥ ይሄ ሱሪ መታጠብ ብዛት የልጅነት ጥቁር ቀለሙ ተገፍፎ ግራጫ መሆን ጀምሮ
ነበር፡፡ ኧረ እንደውም እንደ ሰው ፀጉር በስተርጅና ነጫጭ ጭረት ጣል ጣል ያደረገበት ሱሪ
ነበር፡፡ ቢሆንም እርጅናው ከሱሪው ህያው ዋጋ ላይ ሽራፊ ሳንቲም ሊቀንስ አይቻለውም፡፡
እርጅና የማያደበዝዘው እውነት፣ የዘመን ብዛት የማያጠፋው ሃቅ አለና፤ የዛ እውነት ማህደር
ነው የተወሰደው፡፡

የፍቅርተ ሱሪ ጠፋ ማለት የመንደራችን ባንዲራ ጠፋ እንደማለት ነው፡፡ ይሄ ሱሪ ተራ ሱሪ ብቻ አልነበረም፤ የማንነት መቋጠሪያ ጨርቅ፣ የተገፉ ድሆች እንባ ማበሻ መሃረም፣ የፍቅር
መክተቻ ከረጢት ነበር፡፡ ምን ያደርጋል ! ታጥቦ ከተሰጣበት ገመድ ላይ ጠፋ ፡፡

አንዳንዱ የደላው መንደርተኛ የፍቅርተ ሱሪ መጥፋቱን ሲሰማ “ይሄ ሁሉ ላይ ታች ማለት ለአንድ
አሮጌ ሱሪ ነው ?” እያለ ወደየ ጉዳዩ ይጣደፋል፡፡ “በሰው ቁስል እንጨት ስደድበት” ቢባልም
ቅሉ እንዴት ሰው በራሱ ቁስል እንጨት ይሰድዳል? ስለፍቅርተ ሱሪ የማይመለከተው ማነው?

እኔ በበኩሌ የፍቅርተ ሱሪ ከሚጠፋ የወለዱት ይጥፋ ባይ ነኝ፡፡ ስንለው ስንጮኸው የኖርነው ቃል ነበር የፍቅርተ ሱሪ! አብሮን የኖረ ቃል ጨርቅ ለብሶ የተከሰተው በፍቅርተ ሱሪ ነበር፡፡ ድንገት የቀኝ እጄን ስመለከተው ሁለት ጣቶቼን ከቦታቸው ላይ ባጣቸው እንኳን የዚህን ያህል የምደነግጥ አይመስለኝም፡፡ እዚህ መዲናችን ውስጥ ያለው የአፍሪካ ህብረት ሕንፃ ድንገት ከስሩ ተነቅሎ የደረሰበት ጠፋ ሲባል የፍቅርተን ሱሪ ያህል አያስደነግጠኝም፤ ኧረ ፍቅርተ ራሷ ብትጠፋ የሱሪዋን ያህል
አታስደነግጠኝም፡፡ ስለዚህ ሱሪ የተዳፈነ ተስፋ፣ የተኮላሸ ፍቅር አለና ሱሪው ሱሪ ብቻ አልነበረም፡፡

ሱሪው የጠፋ ቀን ከሰዓት በኋላ ወደ ስምንት ሰዓት አካባቢ ከምማርበት ኮሌጅ ስመለስ እማማ አመለወርቅ በራቸው ስር ሁልጊዜ የሚቀመጡባት ጠፍጣፋ ድንጋይ ላይ ተቀምጠው አገኘኋቸው ዓይናቸው ቡዝዝ ብሎ በሀሳብ በመመሰጣቸው እስካናግራቸው ድረስ አጠገባቸው መድረሴንም
አላዩም ነበር፡፡ ለወትሮው እዚህች ድንጋይ መቀመጫ ላይ የሚቀመጡት እጃቸው አጠር ብላ
ለዕለት ቡና ብር ቢጤ ሲቸግራቸው ነበር፡፡ የድንጋይ ወንበሯ የመተከዣ መድረካቸው ናት::

“ማዘር ምነው ሰላም አይደሉም እንዴ?” አልኳቸው፤

ቀጥ ብለው እንባ ባኳተሩ ዐይኖቻቸው ተመለከቱኝና ሳግ ተናነቀው አሳዛኝ ድምፅ ፣ “የፍቅርን ሱሪ ወሰዱባት አብርሽ!” አሉኝ፤ ሊያናግሩኝ ቀና ሲሉ እያለቀሱ እንደቆዩ ፊታቸው ላይ ዳናውን የተወ እንባቸው ይናገራል፡፡

“እነማን ናቸው የወሰዱት?” አልኳቸው የሰማሁትን ባለማመን፤ ቅስም ከሚሰብር ዜና ኋላ
የተከሰተ የጅል የሚመስል ጥያቄ፡፡

“ምናውቄ ብለህ አብርሽ ! ከዚህ ከተሰጣበት ገመድ ላይ አንስተው ወሰዱት” አሉና እንባቸውን
ዘረገፉት፡፡ ድህነት እንደ ሸንኮራ መጥጦ ካደረቀው ሰውነት ይሄን ያህል እንባ ይወጣል ብዬ
አላሰብኩም ነበር፡፡ ሕይወት ምንጊዜም አዲስ እንባ አላት፡፡ከእንባቸው የበለጠ ፊታቸው ላይ
ያረበበው ሐዘንና ምሬት ያሳዝን ነበር፡፡አንጋጥጬ የልብስ ማስጫ ገመዱን ተመለከትኩት፡፡
ወዲህ የኤሌክትሪክ ምሰሶ ላይ ወዲያ ደግሞ የአንዲት ጎረቤት የቤት ጣራ ማገር ላይ የተወጠረው ገመድ የተወረረ ከተማ መስሏል፡፡ ባንዲራውን እንዳወረዱበት የሰንደቅ ምሰሶ ትከሻው ቀሏል፡፡ ባዶ !! ለፍቅርተ፣ ለእኔ፣ ለእማማ ዓመለ፣ ለመንደሩና ለአገሩ ባዶነትን ትቶልን የሄደው ማነው?

ይሄ ገመድ ባዶውን ውሎ አያውቅም ነበር፡፡ ቢጠፋ ቢጠፋ የጉግሳ አውራ ጣቱ የተሸነቆረ
ካልሲ ወይም አሁን የጠፋው የፍቅርተ ሱሪ ተሰጥቶበት ነበር የሚውለው፡፡ የፍቅርተ ሱሪና
የጉግሳ ካልሲ ሁልጊዜም ገመዱ ላይ ጎን ለጎን ተሰጥተው ስለማያቸው የልብ ወዳጆች ይመስሉኝ ነበር ፡፡የፍቅርተ ሱሪ ከፍ ያሉት ንቀውት ዝቅ ብሎ የካልሲ ጓደኛ የሆነ፡፡ ካልሲውም ቢጤዎቹ ንቀውት ቀን ከገፋው ሱሪ ጋር የዋለ ዓይነት፡፡

አንጋጥጬ ስመለከት ከገመዱ በላይ ጥርት ያለው ሰማይ ተዘርግቷል፡፡ የፍቅርተን ሱሪ የወሰዱት ሌቦች ለወትሮው ሰማዩ ላይ የማይጠፋውን ደመና የወሰዱት ይመስል ነበር፡፡ ሰማዩ ባዶ! የልብስ ማስጫው ገመድ ባዶ!! አይ አይ ሰማዩ እንኳን ባዶ አልነበረም፡፡ ነግቶ የረፈደባት የምትመስል ግማሽ ጨረቃ ትታያለች፡፡ የሱሪ ሌባው ግማሿን ጨረቃ ሸርፎ የወሰዳት ይመስል፡፡
ቆይ ግን ሱሪውን የወሰደው ሌባ ከሆነ ሌባውን ምን ነካው? እንዴት የፍቅርተን ሱሪ ይወስዳል? እሺ
ነፋስም ከሆነ ንፋሱን ምን ነካው ? አቧራ ያስነሳ፣ የቤት ጣራ ይገነጣጥል ቢፈልግ ! ያንን ከሰፈራችን ወደታች ያለውን የአድባር ዛፍ ከስሩ ገርስሶ ይጣለው ! ግን እንዴት የፍቅርተን አንድ ለእናቱ የሆነ ሱሪ ይወስዳል ? ምን ቁርጥ አድርጎት የመንደራችንን ባንዲራ ይደፍራል ? በሌባው ተቆጣሁ
በነፋሱ ተቆጣሁ ፡፡ በፈጣሪም ተቆጣሁ :: መምሬ ልሳኑ ታዲያ (የእማማ አመለ ንስሃ አባት)
የሱሪውን መጥፋት ሲሰሙ፣ እማማ አመለን ለማፅናናት ብለው ይሁን አልያም አምነውበት እንጃ
ብቻ ጥቅስ አጣቀሱ፤ “ላለው ይጨመርለታል፣ ከሌለው ግን ያለውም ይወሰድበታል ወለተ ኪዳን አይዞሽ” በዚህ ማፅናኛቸው በጣም ተበሳጨሁ፤ እንደውም በፈጣሪ ላይ የተሰማኝ ቅሬታ ተባባሰ፡፡

ፈጣሪ የሌባው እጅ ወደ ፍቅርተ ሱሪ ሲዘረጋ እንደ ደረቅ እንጨት ድርቅ አድርጎ ማስቀረት ይችል ነበር፡፡ ነፋስና ማዕበልን የሚገስጽ ፈጣሪ እንዴት ዝም አለ ? እሳት ከሰማይ የሚያወርድ አምላክ ከዚህ በላይ በደል፣ ከዚህ በላይ ግፍ ምን አለና ታገሰ ? የፍቅርተን ሱሪ የወሰደው ንፋስ ከሆነም መገሰጽ ይችል ነበር፣ ስለምን ዝም አለ ? እንኳን አጋጣሚውን አገኘሁ እንጂ ፈጣሪ ጋርማ በፍቅርተ ጉዳይ ብዙ ጥያቄ አለኝ! ብዙ ! ሲጀመር ፍቅርተን ስለምን እንዲህ አድርጎ ፈጠራት…እኮ ለምን !? ለእሱስ ለስሙ ጥሩ ነው ??

“የእናት ሆድ ዥንጉርጉር ነው” ይሉት ብሂል ስጋ ለብሶ የተገለጠው እማማ አመለ ቤት ነበር፡፡እማማ አመለ በመልክ ይሁን በባህሪ የማይገናኙ፣ ከፆታቸው በቀር አንድ የሚያደርጋቸው አንድ
ነገር እንኳን ፈልጎ ማግኘት የሚከብድ ሁለት ሴት ልጆች ያሏቸው፣ እድሜያቸው የገፋ ደግ ሴት ነበሩ ፡፡ ከሁለት ክፍል ቤታቸው አንዷን ተከራይቼ ለአራት ዓመታት ቤታቸው ውስጥ ኖሬያለሁ፡፡
👍262🥰2🔥1
#ሚስቴን_አከሸፏት


#አንድ


#በአሌክስ_አብርሃም


"አብርሃም!”

“አቤት!”

"እ..ለዚች ተልካሻ ምክንያት ብለህ ነው ሚስቴን ልፍታ የምትለው ?” ስትል ዳኛዋ ጠየቀችኝ። እዩት
እንግዲህ ክብርት ዳኛ ቋጥኝ ሴትነቷ ተንዶ ሕዝብና መንግሥት በአደራ የሰጣትን የዳኝነት ኃላፊነቷን ሲጫንባት! እስቲ አሁን ችሎት ላይ የቀረበን የአመልካችን ብሶት ተልካሻ? ብሎ ማጣጣል ተገቢ ነው? አይ መብቴማ ሊከበር ይገባል! ያ..ሌባ ትዝ አለኝ። አንዱ ልማደኛ ሌባ ነው አሉ። ለሠባተኛ ጊዜ ስልክ ነጥቆ ሊያመልጥ ሲሞክር ተይዞ ፍርድ ቤት ይቀርባል…፤ ታዲያ ዳኛው በብስጭት፣

“አንተ ልክስክስ ዛሬም እንደገና ሰርቀህ መጣህ ?” ሲሉት ሌባው ኮስተር ብሎ፣

“ክቡር ዳኛ… እንዲህማ አይዝለፉኝ…ደንበኛ ክቡር ነው!” አለ አሉ።

እውነቱን ነው ደንበኛ መከበር አለበት። የግድ ጉዳዬ እንዲካበድ ሚስቴን ከሌላ ወንድ ጋር አልጋ ላይ ማግኘት አልያም በገጀራ ጨፍጭፌያት ፍርድ ቤት መቆም ነበረብኝ እንዴ ? ለምን ምክንያታችንን ያናንቃሉ…?ምክንያቴን ያቀል ዘንድ የማንን ምክንያት ማን በትከሻው ተሸክሞ መዝኖታል? ደግሞ ስንት ጊዜ ነው ለዚህች ዳኛ ስለጉዳዩ የምነግራት? ከዚህ በፊትም ደጋግማ ጠይቃኝ ደጋግሜ መልሻለሁ…።

“አይ ምክንያቱ ለእኔ ከበቂ በላይ ነው ክብርት ዳኛ ስል በትህትና 'ተልካሻ ብላ ያናናቀችውን
ምክንያት ሚስቴን ለመፍታት በቂ መሆኑን ለማረጋገጥ ሞከርኩ። (ክብርት የሚለው ቃል ከብረት
የተሠራ ይመስል አፌ ላይ ከበደኝ።)

እኮ ሚስቴ ካለፍቃዴ ፀጉሯን ተቆረጠች ብለህ የፍች ጥያቄ ይዘህ ፍርድ ቤት ድረስ መጣህ?” አለች ዳኛዋ አሁንም ተገርማ። ምን አስገረማት?

እዎ ስል ኮስተር ብዬ መለስኩ። ዳኛዋም ዝም ! ችሎቱም ዝም ! ሁሉም ሰው እንደ እብድ
እየተመለከተኝ ነበረ። ዳኛዋ እንደዳኛ ብቻ ሳይሆን እንደሴት መናገር ጀመረች (ፆታዋን ወግና)፤
ስልችት ያለኝን ዝባዝንኬ የሞራል ወግ…

“ስማ አብርሃም ! ባለቤትህ እኮ ሕፃን ልጅ አይደለችም። የሚጠቅምና የሚጎዳትን ነገር በሚገባ ራሷ ታውቃለች። ስትቆም ስትቀመጥ አንተን ማስፈቀድ የለባትም። ምንም እንኳን ባሏ ብትሆንም ያገባሀት በባርነት ልትገዛት እና የአንተን ብቻ ፍላጎት ልትጭንባት አይደለም። ይህ ዘመናዊ አስተሳሰብም
አይደለም። አንተ ወጣት ነህ፣ የተማርክ የከተማ ልጅ ነህ። በመቻቻልና በመተሳሰብ እንዲሁም አንድኛችሁ የአንድኛችሁን ፍላጎት በመረዳት ትዳራችሁን አክብራችሁ…” በለው! ሰውነቷ በእልህ እየተንቀጠቀጠ ምክር ይሁን ግሳፄ ያልለየለት ንግግሯን አንተረተረችው።

አሁን ክብርት ዳኛ የተናገሩት ነገር እንዲሁ ከላይ ሲታይ ትክክል ይመስላል። ግን ይሄ ሁሉ ዝባዝንኬ በፍትሐብሔርም፣ በወንጀለኛም፣ በቤተሰብ ሕግም ላይ በቀጥታ የሰፈረ አይመስለኝም ችሎት ውስጥ
ሳይሆን የእኛ ሰፈር የሴቶች እድር ውስጥ የቆምኩ መሰለኝ። ለነገሩ ዳኛዋ ሴት በመሆኗ ሲጀመርም
ፈርቼ ነበር። በኋላ ሳስበው ሙያ መቼስ ፆታ የለውም፣ ሴት ዳኛ እንጂ ሴት ዳኝነት የለም፣ ሴት ሐኪም እንጂ ሴት ሕክምና የለም። ቢሆንም ፆታው ሙያው ላይ የሚያሳርፈው የራሱ ተፅዕኖ ይኖራል፤ ልክ እንደዚች ዳኛ! ደግሞ ሚስትህ ሕፃን አይደለችም” ትላለች እንዴ፤ ምነው ችሎቱን የሕፃን ችሎት
አደረገችው !

“ሴት በዛ ጎመን ጠነዛ ብዬ ተረትኩ። የተረቱ አንድምታ እኮ ስለሴት አይደለም። ብዙ አዋቂ ሲበዛ ሁሉም ጉዳዩን በራሱ እውቀት ልክ እየጎተተ በቀላሉ ሊሠራ የሚችለውን ነገር ማክረም ይከተላል ለማለት ነው። እንኳንም ተረትኩ። ችሎቱን የሞሉት ሴቶች ናቸው፤ ሚስቴን ጨምሮ (ሚስቴ ስል እንዴት እንደሚቀፈኝ…።)

እስቲ አሁን ባለቤትህ እኮ ሕፃን ልጅ አይደለችም፣ የሚጠቅምና የሚጎዳትን ነገር በሚገባ ራሷ
ታውቃለች… ማለት ይሄ ምን የሚሉት ከንቱ ንግግር ነው። አንዲት ሴት ለራሷ ይጠቅመኛል ያለችውን ማወቅ በቃ ሙሉነት ይመስላቸዋል። ይሄ እኮ ነው የዘመኑ ችግር። ለራሴ አውቃለሁ! የሚሉት የማይረባ መኮፈስ። 'ለራሴ የሚጠቅመኝን እኔ አውቃለሁ' ማለት የትዳር አጋርን ፍላጎት ካላገናዘበ ምኑን ትዳር ሆነው ?!

'ሕፃን ልጅ አይደለሁም፤ የሚጠቅመኝን እኔ አውቃለሁ' ብዬ የፈለግኩበት ባድር ሚስቴ ደስ ይላታል?የሚጠቅመኝን እኔ አውቃለሁ' ብዬ ፀጉሬን ሳላበጥር፣ ጥርሴን ሳልቦርሽ ብወጣ ሚስቴ ዝም ትላለች? የሚጠቅመኝን እኔ አውቃለሁ' ብዬ የጨርቅ ሱሪዬን እንደጌሾ ካልሲዬ ውስጥ ጠቅጥቄው ብወጣ ሚስቴ ዝም ትላለች ? በተራ እሽኮለሌና የሞራል ጩኸት ፍቅር ፀንቶ የሚቆም ሊያስመስሉ ሲቀባጥሩ
ይገርሙኛል።

ይሄ እኮ ሁሉም ሴቶች ከሰውነት መንበር የተገፈተሩ ሲመስላቸው ጨምድደው እንዳይወድቁ
የሚንጠለጠሉበት የተረት ገመድ ነው ! ትዳር ማለት ራስን ማወቅ ብቻ አይደለም፤ የትዳር አጋርንም
ጠንቅቆ ለማወቅ መሞከር ነው። የራስን ፍላጎት ብቻ አንጠልጥሎ ትዳር የለም። እንደዛማ ከሆነ
ሁሉም በየራሱ የእውቀትና የፍላጎት አጥር ውስጥ ከመሸገ ምን አብሮነት አስፈለገ።
ይሄው ነው እውነቱ !!
“ክብርት ዳኛ ያሉት ነገር ከእኔ ጉዳይ ጋር አይገናኝም። እኔ ሚስቴ ፀጉሯን በአጭሩ ስለተቆረጠች ሕፃን ናት አልወጣኝም! እኔ ፀጉሯን በመቆረጧ መፋታት እፈልጋለሁ፣ ከእርሷ ጋር መኖር አልፈልግም ነው እያልኩ ያለሁት። ቀድሜ ፀጉሯን እንዳትቆረጥ ነግሬያት ነበር። የራሷን ምርጫ ተከትላለች። እኔም የራሴን ምርጫ እከተላለሁ !! ደግሞስ የቤተሰብ ሕጉ ሚስትን ለመፍታት የግድ ምክንያት መቅረብ አለበት ይላል ? አይልም !! አንድ ሰው መፋታት ከፈለገ በቃ ይፋታል። ስለዚህ ክቡር ፍርድ ቤቱ
ጥያቄዬን በመቀበል ፍቺውን እንዲያፀድቅልኝ በማክበር እጠይቃለሁ!!” አልኩ።

“ለመሆኑ ስትፋቱ ያላችሁን ንብረት እኩል እንደምትካፈሉ ገብቶሃል ?”

“ኧረ በሙሉ ትውሰድ ... ብቻ እንፋታ” አልኩ በምሬት እየተንገሸገሽኩ። ሚስቴ ፌቨን ከኋላ ስታለቅስ (ስትነፋረቅ ነው እንጂ..) ይሰማኛል። ጩኸቴን ቀማችኝ፤ ማልቀስ የሚያምርብኝስ እኔ ! ነጋቸውን
የፍቅር እና መከባበር ባሕር ከፊታቸው ተዘርግቶ መለቃለቅን ይንቁና እንዲህ ነገር ከእጃቸው
ሲያፈተልክ በራሳቸው እንባ የጨው ባሕር ሠርተው ነፍሳቸውን ይዘፈዝፋሉ። እንባቸውን ገድበው
ቁጭት ያመንጩበት እዛው። እንዴት እንደጠላኋት! የአባቴንም ገዳይ እንዲህ አልጠላ።

ዳኛዋ በትኩረት ተመለከተችኝ፤ እኔም በትኩረት ተመለከትኳት። ፀጉሯ ባጭሩ ተቆርጦ ደማቅ
ወርቃማ ቀለም ተቀብቷል፤ ልክ እንደሚስቴ። ወርቃማ ቀለም ውስጥ ነክረው ያወጡት ቡርሽ ነው የሚመስለው፤ ችፍርግ! ፊቷ ላይ ልክ የሌለው ጥላቻ ይንቀለቀላል። ጠላች አልጠላች በሕግ እንጂ በፍቅር አትፈርድ ድሮስ !ሕግ አይጥላኝ። ጠረጴዛው ላይ በተቀመጠው መዶሻ አናቴን ብትፈጠርቀው
ደስታዋ…። ኧረ ጎበዝ እኔ ስለሚስቴ ፀጉር ማጠር ሳወራ ለካስ ዳኛዋ ስለራሷም ፀጉር ነው
የምትሟገተኝ። ግን ሕግ ነውና እንደምንም ብስጭቷን ዋጥ አድርጋ ጉዳዩን በሌላ ጊዜ ለማየት ቀጠሮ ሰጠችን። ሦስተኛ ቀጠሮ መሆኑ ነው። ቆይ ይቺ ሴትዮ በቀጠሮ ብዛት የሚስቴ ፀጉር የሚያድግና ሐሳቤን የምቀይር መስሏት ይሆን እንዴ ? መክሸፍ አይገባትም ... በቃ ሚስቴ ለእኔ ከሽፋለች !!
👍40😁51👏1
#ዶክተር_አሸብር


#አንድ


#በአሌክስ_አብርሃም


ቦምብ እንዲኖረኝ እፈልግ ነበር!! እንደ እጅ ስልኬ በፈለግኩበት ሰዓት ቁልፎቹን የምጫነው…
የራሴ፣ የግሌ ቦምብ፡፡ ቦምብ ሲባል ግን ይሄ ሰባት ሰው አቁስሎ፣ ሁለት ሰው ገደለ መስተዋት ሰባበረ ግድግዳ ደረመስ የሚባለው ዓይነት ቦንብ ሳይሆን በጅምላ ፊቱን ያጠቆረብንን፣ በጅምላ
የበደለንን፣ በጅምላ የገፋንን ሕዝብ በጅምላ ድራሹን የሚያጠፉ ኒውክሌር ቦምብ።

ቡምምምምምምምምምም ሰፈራችንን የዶግ አመድ አዲሳባን ከነስሟ ድራሿን የሚያጠፋ..

ወይ አዲስ አበበ አወይ ሸገር ሆይ

ከተማ እንደጤዛ እልም ይላል ወይ

እየተባለ እስኪዘፈን ወላ ሙሾ እስኪወርድ ድረስ በቃ አዲስ አበባን ባዶ የሚያደርግ .እንጦጦን
ሳይቀር ከስሩ ነቅሎ ህንድ ውቅያኖስ የሚጥል አዲሳባ የምትባል ከተማ እዚህ ነበረች፡፡ ምክንያቱ ባልታወቀ ፍንዳታ ጠፋች” እንዲሉ ባለታሪኮች፤ ምከንያት ነጋሪ ባለታሪክ አይተርፍማ፡፡

ኒውክሌር ቦምብ እንዲኖረኝ እፈልግ ነበር፡፡ ሰዎች 'የግል ቤትና መኪና ቢኖረን ብለው
እንደሚመኙት ቦምብ ቢኖረኝ እያልኩ እመኝ ነበር፡፡ እዚሀ መሐል አዲስ አበባ ሲፈነዳ ንዝረቱ የሩሲያን የበረዶ ግግር የሚሰነጣጥቅ ካናዳ ሊታጨድ የደረሰውን የስንዴ አዝመራ
የሚያረግፍ ኒውክሌር ቦምብ፡፡
ይሄ የተመኘሁት ቦምብ ቢኖረኝ ለመጥፎ ነገር አልጠቀምበትም፡፡ እንደ ቤት ዕቃ እንደ ፍሪጅ
ቁምሳጥን በቀጥታ ወስጄ አቶ ቀሰመ ወርቅ ቤት ውስጥ መሐሉ ላይ አስቀምጠውና እንዲፈነዳ
ቁልፉን እጫነዋለሁ፡፡ ቡምምምምምምምምም ከእኛ ሰፈር ጀምሮ አፈር ነሽ ድንጋይ፣ ዛፍ ነሽ ተራራ ነሽ እየጠራረገ...ወደታች ወደ ሜክሲኮ ሕንፃውን ሁሉ አመድ እያደረገ መንገዱን ሁሉ
እየገለባበጠ ይወርድና ወደ ጦር ኃይሎች (አቶ ቀለመወርቅ እዛ ወንድም አላቸው ..ከዛ ወደ
አየር ጤና፣ ዓለም ባንክ (አዲስ ቤት እያስገነቡ ነው ተበሏል ዓለም ባንክ አካሳቢ)

በዚህ በኩል ደግሞ ከመስቀል አደባባይ አድርጎ ካዛንችስ ነሽ ሀያ ሁለት፣ መገናኛ፣ መሪ ሲኤምሲ እየጠራረገ በኮተቤ በኩል ሲቪል ሰርቪስ (እዛ የአቶ ቀለመወርቅ ትልቁ ልጃቸው ይማራል ይሄ ደነዝ ተምሮ ላይገባው የመንግሥት እህል ይፈጃል ! ፍንዳታው ወደ ቦሌ፣ ኢምፔርያል ገርጅም መሄድ አለበት በቃ !! ማነው የሚከለክለኝ የፈለግኩትን ማሰብ መብቴ ነው ማንም ሰው በሀሳሱ ቀአንድ ጀምበር ዓለምን ማጥፋት ይችላል እንኳን ይህቺን ቢጢቃ
ካላቅሟ የምትንጠራራ በውራጅ የምትንደላቀቅ አዲስ አበባን ቀርቶ፡፡

አዲስ አበባ አቅፋ ደብቃ ጠጅ እያጠጣች ጮማ አያስቆረጠች አንቱ ብላ ባኖረችው፣ ቀለመወርቅ
በሚባል ሰው በላ ጭራቅ ሽማግሌ ምክንያት አሸብር የሚባል ቂሙን የማይረሳ ጠላት አፍርታለች፡፡

እኔ ነኝ አሸብር፡፡ አዲስ አበባ አዲስነቷን ሳትወድ ተነጥቃ
'አዲስ ፍራሽ' ትሆናታለች የታባቷ !!

መብቴ ነው በሀሳቤ ሕንፃዎቿን የፍርስራሽ ክምር ማድረግ ታሪክ ማድረግ፡፡ “እዚህ ላይ እኮ
ቀልበት መንገድ ነበር” እያለ ድሮ የሚያውቃት እስኪያዝንላት(ለወሬ ነጋሪ የሚተርፍ ካለ) አመድ ማድረግ ይህቺን አመዳም፣ የሰው ፊት እያየች የምታዳላን ወረተኛ ከተማ ንፋስ ያየው ዱቄት ማድረግ፡፡ ደግሞ ከሷም ብሶ አዱ ገነት…ኡኡቴ!!

እንዲህ እያልኩ ሳስብ ነፍሴ ትረካለች ውስጤ ይረጋጋል፡፡ አዲስ አበባን የተበቀልኳት
ይመስለኛል….ደስ ይለኛለ:: በቁጣ የጋላ ሰውነቴ ይቀዘቅዛል። አዕምሮዬም ተረጋግቶ ወደ
ማሰቡ ይመለሳል፤ አበቦች አበባ ሊመስሉኝ ይጀምራሉ፡፡ አይኔም በጎ በጎውን ማየት ይጀምራል፣
ውርውር የሚለውን ሰው እና መኪና ቆንጆዎቹን ሴቶች፣ ባጠቃላይ ሕዝቡን ማየት እጀምራለሁ…ግን ሁሉንም እጠላቸዋለሁ፣ አልወዳቸውም፡፡

ጥላቻ የዘወትር ጸሎቴ ነው፡፡ የጥፋት ምኞት አባታችን ሆይ የዕለት ድጋሜ !! ምነው “በደፈናው ጥላቻ የሚል የእርጎ ዝንብ ሲንጋጋም አዲስ አበባን ከነሕዝቧ አልወዳትም፡፡ ደግሞ “አዲስ አዱዬ…እዱ ገነት” እያሉ ይመፃደቁላታል፡፡ ኡኡቴ አዱ ሲኦል !! የአፍሪካ ዋና ጀሀነም፣ የሰይጣን ንብረት መሰብሰቢያቸውን !!

አልወዳትም አዲሰ አበባን፡፡ አልወደውም ሕዝቡን፡፡ እንዲህ ነበር የማስበው ሁልጊዜም፡፡ ጧት
የአዲስ አበባ ቅዳሴ ከአፅናፍ እስከ አፅናፍ ሲናኝ መስጊዶቿ በአዛን የማለዳ አየሯን ሲሞሉት፣
እናንተ ከፉ ሕዝቦች ደግሞ ነጋላችሁ፡ ለክፉት ተነሱ' የሚሉ ይመስለኝ ነበር፡፡ ማታ ሕዝቡ
በየበረንዳው ተኮልኩሎ ድራፍቱን ሲገለብጥ፣ ቢራውን ሲያጋባ ውስጡ የተከለውን ክፋት
እንዳይደርቅበት ውኃ የሚያጠጣ ይመስለኝ ነበር፡፡ ሕዝቡ ራሱ ስለራሱ ደግነት፣ ስለራሱ ቸርነት፣
ስለራሱ እንግዳ ተቀባይነትና አማኝነት ለራሱ ሲያወራ ይገርመኛል፡፡ ለእኔ የአዲስ አበባ ህዝብ ብዙ አይደለም፤ አንድ አምሳል አንድ አካል ያለው ቀለመወርቅ' የሚባል አንድ ሰው ነው !!


አሸብር ነው ስሜ ዶክተር አሽብር በአምላክ 'በአምላክ' አባቴ አይደለም፣ አያቴም አይደለም
ማን እንደሆነ አላውቅም...እናቴም አታውቅም፡፡ ልክ ለእኔ አሸብር የሚል ሰም እንደወጣልኝ

“አባት' ለሚለውም ቃል በአምላክ የሚል ስም ወጣለት፡፡ የእኔን ስም ያወጣችው ብዙ ላሞች ያሏት ክፋትን እንደ ላም የምታረባ እና ባወራች ቁጥር ከንፈሯን በአውራ ጣቷና በአመልካች ጣቷ በቄንጥ የምትጠርግ ክፉ ባልቴት ነበረች፡፡የአባቴን ስም ያወጣችልኝ ግን እናቴ ናት፡፡ እናቴ አፀደ ! አቲዬ ነው የምላት (በዚህች ምድር ላይ ስሟ ላይ ዩ፥ ጨምሬ እቆላምጬ የምጠራት ብቸኛ ሰው እኔ ልጇ አሸብር ብቻ ነበርኩ፡፡)ደ

አንደኛ ከፍል እስከመዘገብ የአባት ስም አልነበረኝም፡፡ ልክ ትምህርት ቤት አቲዬ ወስዳኝ ስመዝነብ
ጉጉት የመሰለው መዝጋቢ እናቴን እያጣደፈ ጠየቃት፡፡ ድሪቶ ቀሚሷ በዓይኑ ቀፎት እያመናጨቀ
የእኔን ስም ጠየቃት፡፡ የንቀት አስተያየቱን፣ እናቴን ዝቅ የሚያደርግ የፊቱን ገፅታ አይቼዋለሁ በዚያው ድሪቶ ቀሚስ ስር በፍርሃት ተከልዬ.አይቼዋለሁ ቅንድብና ቅንድቡ እስኪነካኩ ሲጠጋጉ እናቴ ላይ ሲኮሳተር፡፡ ለራሷ ኑሮ የገላመጣት እናቴን ሲገላምጣት አይቼዋለሁ፡፡

አቲዩ አስመዝግባኝ ከፊቱ ዞር ስትል ፊቱን ጨፍግጎ መጥፎ ጠረን እንደሚያባርር ሰው ግራ እጁ አየሩን እያራገበ ሲያባርር አይቼዋለሁ፡፡ በእርግጥ አቲዩ እማማ የብርጓል ቤት እንኩሮ እያነኮረች ነበር፡፡ “ምዝገባው ዛሬ ነው የሚያልቀው“ ሲሏት ነው ብድግ ብላ ሳትለቃለቅ የመጣችው፡፡ ቢሆንስ ልክ ቆሻሻ እንደሸተተው ሰው ፊት እንዲያየው አድርጎ እጁን ያራግባል ? የእማማ የብርጓል ቁጥር አንድ የጠላ ደንበኛ እንዳልሆነ ሁሉ፣ አሻሮ ሸተተኝ ብሎ ያዙኝ ልቀቁኝ ይላል ? ነብር አየው !! እንኳን ይህቺን አይቼ እንዲሁም ጥላቻ ጥላቻ ይለኛል፡፡ ያንን የውሻ ልጅ አስተማሪ እንደ ጠመድኩት
ጡረታ ወጣ !! ደግሞኮ አያፍርም መንገድ ላይ ሲያገኘኝ “የእኔ ተማሪ ነው!" እያለ በኩራት ያወራል።

“ስም ” አላት አቲዬን።

“የእኔን ነው ” አለች እየፈራች። ፈሪ ነበረች እናቴ፡፡ ፈሪው የአዲስ አበባ ሕዝብ እንደያቅሙ ደሀ ማስፈራራትን ተክኖበታል፡፡ በትእቢት ማከላፈቱ፣ በክፋት፣ በስድብና ዘለፋው እናቴን ፈሪ
በርጋጊ እድርጓታል፡፡
👍36👏1