#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
.....አምናን ካቻምናን ከዚያ በፊት የተቆጠሩ ዓመታትን ጨምሮ ለብዙ ጊዜ የደከሙበት ትምህርት የሚቋጨው ዘንድሮ ነው። ጌትነትና አማረች ከጓደኞቻቸው ጋር በቡድን በቡድን ሆነው እያሽመቁ ጥናታቸውን ሲለበልቡ የከረሙበት ላለፉት ረጅም አመታት ትምህርታቸውን በመከታተልና የሚሰጣቸውን አድካሚ የቤት ስራዎችን ከመደበኛ ሥራቸው ጋር አጣምረው በመስራት ከፍተኛ ዋጋ የከፈሉበት የነዚያ ሁሉ አመታት ልፋት ድምር ውጤት የሚደመደምበትና የሚመረቁበት አመት ዘንድሮ ነው።
ሁለቱ ፍቅረኛሞች በአዋሳ ላንጋኖ ሃይቅ ውስጥ ተክለው ያለመለሙት ፍቅራቸው የሚያስቀና ሆኗል። ጌትነት የመልካሙ ተበጀ አዋሳ ላንጋኖ
ዘፈን አስቀድሞ የሚወደው ቢሆንም ለሱ የተዘፈነለት እስከሚመስለው ድረስ በይበልጥ የወደደውና አብሮ ማቀንቀን የጀመረው ከላንጋኖ ሽርሽር
በኋላ ነው።
አዋሳ ላንጋኖ ለሽርሽር ሄጄ ያየሁሽ፣
የሲዳሞ ቆንጆ እንዴት ነሽ?
ሽንጥና ተረከዝ ዳሌና ጡትሽ...
አዲስ አበባ ውስጥ ለሁለት አመታት ሲመኛት ቢኖርም በፍቅር ያወቃት በአዋሳ ላንጋኖ ሀይቅ ውስጥ ነበረና ያንን ዘፈን ሲሰማ የአዋሳ ላንጋኖው ሃይቅና ያ ውብና ምንጊዜም ከህሊና የማይጠፋ አስደሳች ዓለም ከነሙሉ
ጓዙ ተጠቅልሎ በሃሳቡ እየመጣበት ዘፈኑን ነፍሱ ምንጥቅ ብላ እስከምትወጣ ድረስ ወደደው። በዚህ የተነሳ የሲዳሞ ቆንጆ በሚለው ምትክ የአዲስ አበባ ቆንጆ እንዴት ነሽ በሚል ተክቶ ከዘፋኙ ጋራ አብሮ ሲያቀነቅን የሚሰማው ስሜት የተለዬ ነበር፡፡ አማረች ለሁለት አመታት ስትመኘው የነበረው ጉዳይ በመሳካቱ እጅግ ደስተኛ ከመሆኗ በላይ ከምትወደው ልጅ ጋር በትዳር ተሳስራ በመኖር የወላጆቿን ፍላጎት ለማሟላት
የሚያስችላት መልካም አጋጣሚ መፈጠሩ በአንድ ጠጠር ሁለት ወፍ ሆኖላታል። ወላጆቿ ልጃቸው ትዳር እንድትይዝላቸው ከፍተኛ ጉጉት አላቸው፡፡ “መቼ ይሆን የአያትነት ወግ ማእረግ የምታሳይኝ ልጄ? እንግዲህ ጀርባዬ ሳይጎብጥ ጉልበቴ ሳይዝል ጥሩ እስክስታ እንድመታልሽ ከፈለግሽ ይሄን ጊዜ ነው ጉልበቴን መሻማት” እያሉ የሚወተውቷት አባቷ
ይህንን ውሳኔዋን ሲሰሙ ደስታቸው ወደር እንደማይኖረው ጥርጥር አልነበራትም፡፡እናቷ አማረችን የሚያይዋት እንደ ልጃቸው ሳይሆን እንደ ታናሽ እህታቸው ነው። አማረችም እናቷን እንደ ታላቅ እህት እንጂ
እንደ እናት አይደለም የምታያቸው፡፡ ታሪኩን ያጫወተቻቸውም እሳቸው
በነገር ወጋ አድርገዋት ነው፡፡
“አማሩዬ? እኔ የምለው? እኛ የምናመጣልሽ ባል እንደማይኖር
በጠዋቱ አስጠነቀቅሽን
አንቺ የምታመጭውን ብንጠብቅ ደግሞ የማሚታይ ነገር ጠፋ።
ምን ይሻላል ልጄ? የሁልጊዜ ምክንያትሽ ትምህርቴን ልጨርስ ነው። ትዳር ተይዞ መማርን ምን ይከለክለዋል? አባትሽ ትዳር ትዳር እያልኩ ስጨቀጭቃት ሸክም ሆንሽብኝ ያልኳት እንዳይመስላት እንዳትሳቀቅብኝ እያለ እየፈራ እንጂ ከኔ የበለጠ የቸኮለ እሱ ነው፡፡ እንዲያው ለጤናው ያድርግለት ችኩል ብሏል”
የትዳሯ ነገር ያጓጓቸው፤ የሰርጉ ቀን የናፈቃቸው መሆኑን አጫወቷት።አማረች ቀኝ ክንዷን በቀኝ ጉልበቷ ላይ አገጯን በመዳፏ ደገፍ አድርጋ
በፍቅር ዐይን ዐይናቸውን እየተመለከተች ነበር የምታዳምጣቸው፡፡
ፊቷ ወይን ጠጅ መስሏል፡፡ ከረጅም ጊዜ ሚስጥር በኋላ እጮኛ ያላት መሆኑን ወላጆቿ ያላወቁት የትዳር ጥንስስ በልቧ ውስጥ ተጠንስሶ መቆየቱን ልትነግራቸው ፈለገች። ከዘንድሮ ምረቃ በኋላ ለትዳር የወጠነቸው
ጓደኛ ያላት መሆኑን ለእናቷ ለማብሰር ፈለገችና ጥርት ያለው ፊቷ በእፍረት ሲቀላባት የወይን ጠጅ መልክ እየያዘ ሄደ።
ከአማረች የመኝታ ክፍል ውስጥ ሆነው ነበር የሚጨዋወቱት፡፡ አማረች ስለፍቅረኛዋ ማስረዳቱን ቀጠለች፡፡ የዐይነ ህሊናዋ ካሜራ በጌትነት ላይ አነጣጥሮ ያሳለፉትን ጣፋጭ የፍቅር ጊዚያት አንድ በአንድ እንደ ፊልም
እየቀረፀና የአዋሳው ትዝታ ፊቷ ላይ ድቅን እያለ፡ “ትንሽ ነው የቀረኝ በጣም ትንሽ ጊዜ፡፡ በጣት የሚጠለቀውን ቀለበት አላጠለኩም እንጂ ታጭቻለሁ። ለረጅም ጊዜ የተዋወቅኩት የምወደው ፍቅረኛ አለኝ፡፡ እስከ አሁን በደንብ ተጠናንተናል። ተግባብተናል። ተዋደናል። ያንቺና የአባዬ ብቻ ሳይሆን በትዳር የመኖሩ ጉጉት በኔ ብሷል። ዩኒቨርስቲ አብሮኝ የሚማር
ልጅ ነው፡፡ ላንቺም ለአባዬም የማስተዋውቅበት ጊዜው ደርሷል። ሁላታችንም በዚህ ዓመት እንመረቃለን፡፡ እስከዛሬም የደበቅኩሽ ትምህርቴን
ከመጨረሴ በፊት ሠርጉ ይፋጠን የሚል ጥያቄ እንዳታቅርቡልኝ ነው።አሁንም ቢሆን ላንቺ ብቻ ነው የምነግረው፡፡ ለአባዬ ጊዜው ሲደርስ አንቺ ትነግሪዋለሽ” የአማረች እናት ልባቸው በደስታ ዘለለች። እንኳን የተማረ! እንኳን ያፈቀረችውን ይቅርና ሱሪ ይልበስ እንጂ እሷ ተመችቶኛል ትዳር
መያዝ እፈልጋለሁ ብላ ፈቃደኝነቷን ከገለፀች ከማንም ጋር ቢሆን ድል ባለ ሠርግ ሊድሯት ሁሌም የሚቃዡበት ምኞታቸው ነበረና፣ እንደ
ዕድሜ እኩዮቻቸው “ልጃችንን ዳርናት” እያሉ አፋቸውን ሞላ አድርገው ለመናገርና እርጅና ከመምጣቱ በፊት የአያትነት ወግ ማእረግ ሊያገኙ ነውና የሰሙት የምስራች እንደ ትንሽ ልጅ እያስቦረቃቸው የባለቤታቸውን ደስታ ጭምር አገላብጠው ሳሟት፡፡
“ለምን የፈለገው አይሆንም አማሩዬ? ይህችን አሁን ያሰማሽኝን የምስራች ይቺን እኔ የሰማኋትን ሚስጥር እሱም ቢሰማ ኖሮ በደስታ አስር
ዓመት ወደ ኋላ ያስቆጥር ነበር” በዜናው እጅግ ተደስተው ወደር የማይገኝለት የእናትነት ፍቅራቸውን እቅፍ አድርገው በመሳም ገለፁላት።አባቷ የሚወዷት የመጀመሪያ ልጃቸው ትምህርቷን ጨርሳ በዲግሪ ተመርቃ
የምትወደውን ፀባየ ሸጋና ጠንበለል ልጅ ይዛላቸው ከተፍ ስትልሳቸው ከደስታቸው የተነሳ ቦሌ አካባቢ ያሰሩትን አምስት ክፍል ቪላ ቤት ጀባ እንደሚሏቸው ጥርጥር የለውም፡፡ ይህንን ጠንቅቃ ስለምታውቅ ጌትነትና ስለመኖሪያ ቤት እያነሳ ሲጨናነቅ በልቧ ትስቅ ነበር። አማረች የምስራቹን ለእናቷ ባደረሰችበት በመመረቂያቸው ዓመት ላይ ጌትነትና እሷ የዓመት ዕረፍት ፈቃዳቸውን ወስደው ለመጨረሻው ፈተና እየተዘ
ጋጁ ነበር።
ትናንትና ለእናቷ የነገረቻቸውን ልትነግረው ፈለገች። አሁንም እንደ
አማረች በሆነ ባልሆነው “ጌትሽ ድረስ!” ሆኗል ዜማዋ፡፡ ዕቃ ሲሰበር አዲስ ፊቷ በእፍረት እየተለወጠ እየቀላ ሄደ፡፡ አሁን አሁን ደግሞ “ጌትዬ ድረስ!" ሆኗል ዜማዋ ምናምን ካስደነገጣት ጌትሽ” ብቻ ለሁሉም ነገር "ጌትሽ
ነጠላ ዜማ ሆኗል፡፡ ይሄ ነገር እናቷንም ግራ ሲያጋባቸው የኖረ ጉዳይ ነበር፡፡ በመጨረሻው ላይ እቅጩን ነገረቻቸው እንጂ ደጋግመው ስምተዋታል "ጌትዬ! ጌትዬ" ስትል፡፡
በዩኒቨርስቲው የመማሪያ ክፍል ውስጥ ከሁለቱ በስተቀር ማንም አልነበረም፡፡ባዶ ነው።ኃይለኛ ንፋስ መስኮቱን ጓ! አደረገና አላጋው። እንደልማዷ”ጌትሽ ድረስ!” በማለት ሄዳ ልጥፍ አለችበትና” ለማዘር ነገርኳት እኮ!"
አለችው እየተፍነከነከች።የመስኮቱ ጩኸት እፍረቷን አቡንኖታል።
“ምኑን?" ፈገግ እንዳለ ዘቅዝቆ እየተመለከታት፡፡
“በቃ ላስተዋውቅህ መሆኑን? እና እንትኔ መሆንህን፡ ባሌ መሆንህን!" አንገቱን እቅፍ አድርጋ ከንፈሩን ሳመችው። ቅብጥ ስትል ያለማጋነን ደስ ትላለች። የአንዳንዱ ቅብጠት ያስጠላል። አማረች ግን የቅብጠት ቅመሙን ጣል አድርጐባት ነው መሰል ቅብጥብጥ ስትል የበለጠ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
.....አምናን ካቻምናን ከዚያ በፊት የተቆጠሩ ዓመታትን ጨምሮ ለብዙ ጊዜ የደከሙበት ትምህርት የሚቋጨው ዘንድሮ ነው። ጌትነትና አማረች ከጓደኞቻቸው ጋር በቡድን በቡድን ሆነው እያሽመቁ ጥናታቸውን ሲለበልቡ የከረሙበት ላለፉት ረጅም አመታት ትምህርታቸውን በመከታተልና የሚሰጣቸውን አድካሚ የቤት ስራዎችን ከመደበኛ ሥራቸው ጋር አጣምረው በመስራት ከፍተኛ ዋጋ የከፈሉበት የነዚያ ሁሉ አመታት ልፋት ድምር ውጤት የሚደመደምበትና የሚመረቁበት አመት ዘንድሮ ነው።
ሁለቱ ፍቅረኛሞች በአዋሳ ላንጋኖ ሃይቅ ውስጥ ተክለው ያለመለሙት ፍቅራቸው የሚያስቀና ሆኗል። ጌትነት የመልካሙ ተበጀ አዋሳ ላንጋኖ
ዘፈን አስቀድሞ የሚወደው ቢሆንም ለሱ የተዘፈነለት እስከሚመስለው ድረስ በይበልጥ የወደደውና አብሮ ማቀንቀን የጀመረው ከላንጋኖ ሽርሽር
በኋላ ነው።
አዋሳ ላንጋኖ ለሽርሽር ሄጄ ያየሁሽ፣
የሲዳሞ ቆንጆ እንዴት ነሽ?
ሽንጥና ተረከዝ ዳሌና ጡትሽ...
አዲስ አበባ ውስጥ ለሁለት አመታት ሲመኛት ቢኖርም በፍቅር ያወቃት በአዋሳ ላንጋኖ ሀይቅ ውስጥ ነበረና ያንን ዘፈን ሲሰማ የአዋሳ ላንጋኖው ሃይቅና ያ ውብና ምንጊዜም ከህሊና የማይጠፋ አስደሳች ዓለም ከነሙሉ
ጓዙ ተጠቅልሎ በሃሳቡ እየመጣበት ዘፈኑን ነፍሱ ምንጥቅ ብላ እስከምትወጣ ድረስ ወደደው። በዚህ የተነሳ የሲዳሞ ቆንጆ በሚለው ምትክ የአዲስ አበባ ቆንጆ እንዴት ነሽ በሚል ተክቶ ከዘፋኙ ጋራ አብሮ ሲያቀነቅን የሚሰማው ስሜት የተለዬ ነበር፡፡ አማረች ለሁለት አመታት ስትመኘው የነበረው ጉዳይ በመሳካቱ እጅግ ደስተኛ ከመሆኗ በላይ ከምትወደው ልጅ ጋር በትዳር ተሳስራ በመኖር የወላጆቿን ፍላጎት ለማሟላት
የሚያስችላት መልካም አጋጣሚ መፈጠሩ በአንድ ጠጠር ሁለት ወፍ ሆኖላታል። ወላጆቿ ልጃቸው ትዳር እንድትይዝላቸው ከፍተኛ ጉጉት አላቸው፡፡ “መቼ ይሆን የአያትነት ወግ ማእረግ የምታሳይኝ ልጄ? እንግዲህ ጀርባዬ ሳይጎብጥ ጉልበቴ ሳይዝል ጥሩ እስክስታ እንድመታልሽ ከፈለግሽ ይሄን ጊዜ ነው ጉልበቴን መሻማት” እያሉ የሚወተውቷት አባቷ
ይህንን ውሳኔዋን ሲሰሙ ደስታቸው ወደር እንደማይኖረው ጥርጥር አልነበራትም፡፡እናቷ አማረችን የሚያይዋት እንደ ልጃቸው ሳይሆን እንደ ታናሽ እህታቸው ነው። አማረችም እናቷን እንደ ታላቅ እህት እንጂ
እንደ እናት አይደለም የምታያቸው፡፡ ታሪኩን ያጫወተቻቸውም እሳቸው
በነገር ወጋ አድርገዋት ነው፡፡
“አማሩዬ? እኔ የምለው? እኛ የምናመጣልሽ ባል እንደማይኖር
በጠዋቱ አስጠነቀቅሽን
አንቺ የምታመጭውን ብንጠብቅ ደግሞ የማሚታይ ነገር ጠፋ።
ምን ይሻላል ልጄ? የሁልጊዜ ምክንያትሽ ትምህርቴን ልጨርስ ነው። ትዳር ተይዞ መማርን ምን ይከለክለዋል? አባትሽ ትዳር ትዳር እያልኩ ስጨቀጭቃት ሸክም ሆንሽብኝ ያልኳት እንዳይመስላት እንዳትሳቀቅብኝ እያለ እየፈራ እንጂ ከኔ የበለጠ የቸኮለ እሱ ነው፡፡ እንዲያው ለጤናው ያድርግለት ችኩል ብሏል”
የትዳሯ ነገር ያጓጓቸው፤ የሰርጉ ቀን የናፈቃቸው መሆኑን አጫወቷት።አማረች ቀኝ ክንዷን በቀኝ ጉልበቷ ላይ አገጯን በመዳፏ ደገፍ አድርጋ
በፍቅር ዐይን ዐይናቸውን እየተመለከተች ነበር የምታዳምጣቸው፡፡
ፊቷ ወይን ጠጅ መስሏል፡፡ ከረጅም ጊዜ ሚስጥር በኋላ እጮኛ ያላት መሆኑን ወላጆቿ ያላወቁት የትዳር ጥንስስ በልቧ ውስጥ ተጠንስሶ መቆየቱን ልትነግራቸው ፈለገች። ከዘንድሮ ምረቃ በኋላ ለትዳር የወጠነቸው
ጓደኛ ያላት መሆኑን ለእናቷ ለማብሰር ፈለገችና ጥርት ያለው ፊቷ በእፍረት ሲቀላባት የወይን ጠጅ መልክ እየያዘ ሄደ።
ከአማረች የመኝታ ክፍል ውስጥ ሆነው ነበር የሚጨዋወቱት፡፡ አማረች ስለፍቅረኛዋ ማስረዳቱን ቀጠለች፡፡ የዐይነ ህሊናዋ ካሜራ በጌትነት ላይ አነጣጥሮ ያሳለፉትን ጣፋጭ የፍቅር ጊዚያት አንድ በአንድ እንደ ፊልም
እየቀረፀና የአዋሳው ትዝታ ፊቷ ላይ ድቅን እያለ፡ “ትንሽ ነው የቀረኝ በጣም ትንሽ ጊዜ፡፡ በጣት የሚጠለቀውን ቀለበት አላጠለኩም እንጂ ታጭቻለሁ። ለረጅም ጊዜ የተዋወቅኩት የምወደው ፍቅረኛ አለኝ፡፡ እስከ አሁን በደንብ ተጠናንተናል። ተግባብተናል። ተዋደናል። ያንቺና የአባዬ ብቻ ሳይሆን በትዳር የመኖሩ ጉጉት በኔ ብሷል። ዩኒቨርስቲ አብሮኝ የሚማር
ልጅ ነው፡፡ ላንቺም ለአባዬም የማስተዋውቅበት ጊዜው ደርሷል። ሁላታችንም በዚህ ዓመት እንመረቃለን፡፡ እስከዛሬም የደበቅኩሽ ትምህርቴን
ከመጨረሴ በፊት ሠርጉ ይፋጠን የሚል ጥያቄ እንዳታቅርቡልኝ ነው።አሁንም ቢሆን ላንቺ ብቻ ነው የምነግረው፡፡ ለአባዬ ጊዜው ሲደርስ አንቺ ትነግሪዋለሽ” የአማረች እናት ልባቸው በደስታ ዘለለች። እንኳን የተማረ! እንኳን ያፈቀረችውን ይቅርና ሱሪ ይልበስ እንጂ እሷ ተመችቶኛል ትዳር
መያዝ እፈልጋለሁ ብላ ፈቃደኝነቷን ከገለፀች ከማንም ጋር ቢሆን ድል ባለ ሠርግ ሊድሯት ሁሌም የሚቃዡበት ምኞታቸው ነበረና፣ እንደ
ዕድሜ እኩዮቻቸው “ልጃችንን ዳርናት” እያሉ አፋቸውን ሞላ አድርገው ለመናገርና እርጅና ከመምጣቱ በፊት የአያትነት ወግ ማእረግ ሊያገኙ ነውና የሰሙት የምስራች እንደ ትንሽ ልጅ እያስቦረቃቸው የባለቤታቸውን ደስታ ጭምር አገላብጠው ሳሟት፡፡
“ለምን የፈለገው አይሆንም አማሩዬ? ይህችን አሁን ያሰማሽኝን የምስራች ይቺን እኔ የሰማኋትን ሚስጥር እሱም ቢሰማ ኖሮ በደስታ አስር
ዓመት ወደ ኋላ ያስቆጥር ነበር” በዜናው እጅግ ተደስተው ወደር የማይገኝለት የእናትነት ፍቅራቸውን እቅፍ አድርገው በመሳም ገለፁላት።አባቷ የሚወዷት የመጀመሪያ ልጃቸው ትምህርቷን ጨርሳ በዲግሪ ተመርቃ
የምትወደውን ፀባየ ሸጋና ጠንበለል ልጅ ይዛላቸው ከተፍ ስትልሳቸው ከደስታቸው የተነሳ ቦሌ አካባቢ ያሰሩትን አምስት ክፍል ቪላ ቤት ጀባ እንደሚሏቸው ጥርጥር የለውም፡፡ ይህንን ጠንቅቃ ስለምታውቅ ጌትነትና ስለመኖሪያ ቤት እያነሳ ሲጨናነቅ በልቧ ትስቅ ነበር። አማረች የምስራቹን ለእናቷ ባደረሰችበት በመመረቂያቸው ዓመት ላይ ጌትነትና እሷ የዓመት ዕረፍት ፈቃዳቸውን ወስደው ለመጨረሻው ፈተና እየተዘ
ጋጁ ነበር።
ትናንትና ለእናቷ የነገረቻቸውን ልትነግረው ፈለገች። አሁንም እንደ
አማረች በሆነ ባልሆነው “ጌትሽ ድረስ!” ሆኗል ዜማዋ፡፡ ዕቃ ሲሰበር አዲስ ፊቷ በእፍረት እየተለወጠ እየቀላ ሄደ፡፡ አሁን አሁን ደግሞ “ጌትዬ ድረስ!" ሆኗል ዜማዋ ምናምን ካስደነገጣት ጌትሽ” ብቻ ለሁሉም ነገር "ጌትሽ
ነጠላ ዜማ ሆኗል፡፡ ይሄ ነገር እናቷንም ግራ ሲያጋባቸው የኖረ ጉዳይ ነበር፡፡ በመጨረሻው ላይ እቅጩን ነገረቻቸው እንጂ ደጋግመው ስምተዋታል "ጌትዬ! ጌትዬ" ስትል፡፡
በዩኒቨርስቲው የመማሪያ ክፍል ውስጥ ከሁለቱ በስተቀር ማንም አልነበረም፡፡ባዶ ነው።ኃይለኛ ንፋስ መስኮቱን ጓ! አደረገና አላጋው። እንደልማዷ”ጌትሽ ድረስ!” በማለት ሄዳ ልጥፍ አለችበትና” ለማዘር ነገርኳት እኮ!"
አለችው እየተፍነከነከች።የመስኮቱ ጩኸት እፍረቷን አቡንኖታል።
“ምኑን?" ፈገግ እንዳለ ዘቅዝቆ እየተመለከታት፡፡
“በቃ ላስተዋውቅህ መሆኑን? እና እንትኔ መሆንህን፡ ባሌ መሆንህን!" አንገቱን እቅፍ አድርጋ ከንፈሩን ሳመችው። ቅብጥ ስትል ያለማጋነን ደስ ትላለች። የአንዳንዱ ቅብጠት ያስጠላል። አማረች ግን የቅብጠት ቅመሙን ጣል አድርጐባት ነው መሰል ቅብጥብጥ ስትል የበለጠ
👍3❤1
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...ፀጉሩን ተላጨና ቁምጣ ሱሪውን አወለቀ! በምትኩ ቀጭን ቦላሌውን ለበሰ፡፡ ከላይ ሸሚዝና ኮቱን ደርቦ ሽክ.. ኳ! ብሎ ሲታይ ያ ጎንቻ! ያ አስፈሪው ጎንቻ! ያ ባለጎፈሬው ሽፍታ! መሆኑን እንኳንስ የማያውቀው የሚ
ያውቀውም ቢሆን ለማመን ይቸገር ነበር፡፡ውስጣዊ እሱነቱ ሳይሆን ውጫዊ ማንነቱ ተቀይሯል። የከተማው ሰው
የሚለብሰውን ልብስ ለብሶ ሰው መሰል አውሬነቱን የሚያሳስት አይነት ሆኗል።
በዚያች ምሽት በጠፍ ጨረቃ ከዓለሚቱ ጋር ተያይዘው ጠፉ... ከኢተያ ከተማ እስከ ዴራ ከተማ በእግራቸው ተጓዙ በሌሊት መኪና ተሳፈሩና ናዝሬት ገቡ፡፡ ከዚያም ወደ አዲስ አበባ ወደዚያ የከተማ ጫካ፣ ወደዚያ የከተማ ዋሻ ገብተው ሊደባለቁ በአዲስ አበባ መኪና ላይ ተሳፈሩ። ከእንግዲህ በኋላ ጎንቻን ፈልጎ ማግኘት ከእንግዲህ በኋላ ዓላሚቱን ፈልጎ
ማግኘት ቁና አሸዋ ውስጥ የወደቀች ጤፍ ለማግኘት እንደመሞከር ነው፡፡ ከእንግዲህ ወዲያ ዓለሚቱ ባሏን ያስገደለች እየተባለች ከምትጠበስበት የሀሜት ምላስ ልትድን እፎይ ልትል ነው፡፡ እነኝያ የገደ ቢስ
ልጆች ጨርሰው ከዐይኖቿ ሊርቁላትና ሰላማዊ ሰዎች መስለው ከአዲስ አበባ ህዝብ ጋር ሊቀላቀሉ የቀራቸው በሰዓታት የሚቆጠር ጊዜ ብቻ
ነው፡፡
ከእንግዲህ ወዲያ የጎንቻን ፍቅር ሙቀቱ እስከሚያቃጥላት ድረስ እንደ ልቧ ልትሟሟቀው ሁኔታው ተመቻችቶላታል። ከእንግዲህ በኋላ የልታጌጥ፣ እንደፈለገችው ልትዘል፣ ልትቦርቅ ልጓሙ ተፈቶላታል።
ጎንቻም አንጎሉን ሲያዞረው በኖረው በዓለሚቱ ፍቅር ወፈፍ በሚያደርገው በዓለሚቱ ናፍቆት ክፉኛ ተጎድቶ ነበር። አብዛኛውን ጊዜ በጫካ ውስጥ ትዝታዋን ብቻ እያቀፈ በማደር ሲሰቃይ ኖሯልና ናፍቆቷ ነፍሱን መንጥቆ ሳያወጣው በፊት ጥሩ ዘዴ ፈጥራ ይዛው በመኮብለሏ አልተከፋም፡፡ያንን ቢያሽተው ቢምገው የማይጠግበው መዓዛዋን በየቀኑ በየደቂቃው ሊያጣጥመው ነውና ኩብለላው ብዙም አላስጨነቀውም ነበር። የተሳፈሩበት ሎንቺና ወስዶ ለገሃር ጣላቸው፡፡
ጎንቻ ከጫካ ያመለጠ አውሬነቱ የታወቀው ገና ከመኪና ላይ እንደወረደ ነበር፡፡ ተይዛ ያመለጠች ሚዳቋ መሰለ፡፡ ሽው!...ሽው!... ውር!... ውር
በሚሉት መኪኖች መሀል ሲገባ ሮጦ ሊያመልጥ ሞከረ። እንጣጥ!
እንጣጥ! እያለ የአንዱ መኪና ራት ሊሆን ትንሽ ቀረው። መንገዱ መሀል ሲደርስ ሰግጠጥ.. ሰግጠጥ እያደረገው አንዴ ወደ ፊት አንዴ ደግሞ ወደ ኋላ ለማምለጥ ዓለሚቱን ክፉኛ ታገላት።እሷም መደናበሯ አልቀረም ቆይ ጎንቻዬ እኔን ተከተለኝ፡፡ ቀስ በል። እኔ ወደምሄድበት ረጋ ብለህ ተራመድ። መኪኖቹን አትመልከት። ያዞርሃል ... ቀስ ...አዎ እንደሱ ጎሽ
..እጆቹን ግጥም አድርጋ ያዘችው እንደምንም ብለው እየተጓተቱ አስፋልቱን ተሻገሩ።
“እሺ ...አዞረኝ እኮ…ቆይ ቁጭ ልበል" አላት፡፡ ደገፈችውና ወደ አንድ ህንፃ አጥር ጥግ ሄዱ፡፡ ተረከዙ ላይ እንደ ዝንጀሮ ቁጢጥ አለ፡፡ ጭውው..አለበት። ጭንቅላቱን በሁለት እጆቹ ያዘው። ዐይኖቹ ጭፍን ክድን ጭፍን
ክድን አሉ፡፡ መኪና ላይ ያልተሰማው የማጥወልወል ስሜት ተሰማው፡፡
"ርቦህ ይሆናል ጌታዬ ርቦህ ነው። ቆይ እዚህ ጋር የማየው ሆቴል ቤት ነው መሰለኝ" ባሻገር ከሚታየው ቤት ላይ ጣቷን ቀስራ አሳየችው።ቆዳቸው የተገፈፈ በጎች ሳይበለቱ ተሰቅለዋል። የሰንጋ ብልቶች በአይነት በአይነታቸው በስርአት ተዘጋጅተው በወረንጦ ላይ ተንጠልጥለዋል፡፡
ልክ ነው ምግብ ቤት ነው" አለችውና ከተቀመጠበት አስነስታው ተያይዘው
ትደጋግፈው ወደ ስጋ ቤቱ አመሩ....
የሚበላ ነገር አለ?" ብላ ጠየቀች፡፡
“አዎን!” አለ ሻጩ፡፡
“ምን አለ?"
“ሁሉም ነገር አለ፡፡ የፈለጋችሁትን..." ወደ ውስጥ እንደመዝለቅ አለችና የሻጩን ዐይን ዐይን በልምምጥ ተመለከተችው።
“በል እስቲ ቀይ ወጥ በእንጀራ..“ፈራ ተባ እያለች ጠየቀቸው። ዓለሚቱ ከልጁ ጋር ስትነጋገር ጎንቻን እንደ ህፃን ልጅ ግራ እጁን ግጥም አድርጋ
ይዛው ነበር፡፡ ጎንቻ...ያ ወንዱ..ጎንቻ... ያ አስፈሪው ጎንቻ አስፈሪነቱ ጀግንነቱ ከሹሩባው ጋር አብሮ እንደተላጨ ሁሉ ወኔው በኛሮ ጫካ ውስጥ ተጥሎ እንደቀረ ሁሉ ዐይኖቹ ፈጠው ርቦት ሲቁለጨለጭ ቀበሮ
የፈሳባት ጦጣ መስሎ ሲታይ እሱነቱን የማይክድ አልነበረም።
“በሉ ጥፉ ከዚህ! ፋራዎች! ገገማዎች! ይሄ የሥጋ መሸጫ ሉካንዳ እንጂ የእንጀራ መሽጫ ጉሊት መስለሽ?! አይተሽ አትጠይቂም?!” ጮኸባት።
ሽምቅቅ አሉ፡፡ አቤት አደነጋገጥ ወጥቶ ፀብ እንዳይፈጥር ጎንቻም በንዴት እልህ ውስጥ እንዳይገባና ገና አንዱንም ሳይይዙት መዘዝ ውስጥ እንዳይገባ ፈራች ፀብ ከተፈጠረ ፖሊስ ይዞ እንዳያንገላታቸው ስጋት አደረባትና
ዐይኖቹ መቅላት ልቡ የንዴት ደም መርጨት ሰውነቱ መቆጣት
የጀመረው ጎንቻን ሙጭጭ አድርጋ ይዛ የስድብ መዓት ከሚያወርድባቸው ጎረምሳ ሽሹ...ጎንቻ አንድ ቂም በልቡ ቋጠረ፡፡ ርቦት ሆዱ የእህል
ያለህ! በሚልበት ሰዓት ወስፋት የሚቆልፍና ወሽመጥ የሚበጥስ የስድብ መርዝ ቀመሰ። እንደምንም ብለው እየተጓተቱ ሄዱና እንጀራ የሚሽጥበት ምግብ ቤት በጠቋሚ አገኙ። በሉ፣ጠጡ፣ ጠገቡ። ጊዜው እየመሸ
ሲመጣ አሁንም በጥቆማ አልቤርጎ ተከራዩ። ምን ችግር አለ? ብር እንደሆነ ዕድሜ ለጎንቻ! በሽበሽ ነው፡፡ ከሰባት ሺህ ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ ይዘዋል። ጎንቻን ትንሽ ያስቸገረው መብራቱ ነበር፡፡ ብርሃን በጣም በዛበት። ዐይኑ በአንድ ጊዜ የአምፖሉን ብርሃን መቋቋም አልቻለም፡፡
ሊተኙ አካባቢ አምፖሉን ቀድሞ ለማጥፋት የሞከረው እሱ ነበር፡፡ “ኡፍ ኡፍፍ. ኡፍፍፍ..!" እንደ ኩራዙ ሞከረ። በኋላ ግን ዓለሚቱ በድርጊቱ እየሳቀች ማጥፊያውን ቀጭ... ቋ! አድርጋ አጠፋችውና በችሎታዋ እየተኩራራችበት ተቃቅፈው ተኙ፡፡
ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት አካባቢ ጎንቻ ሽንቱ ወጠረውና የመኝታ ቤቱን በር ቷ! አድርጎ ከፍቶ ወጣ፡፡ የተከፈተውን ድምፅ የሰማው ሽማግሌ ዘበኛ
“ማነው?” አለ በተጎተተ ድምፅ፡፡
"እኔ ነኝ!" አለ ጎንቻ።
"ወዴት ነው?"
ለውሃ ሽንት!"
“የውሃ ሽንት ተሆነ ቦቦው አለልህ አይደለም?! የት ልትሸና ነው? አሁን የሽንት ቤቱ በር ቁልፍ ነው" አለና ዘበኛው ቁጣ ቀረሽ መልስ ሰጠው፡፡
"የምን ቦቦ ነው የምትለኝ ጃል?! ሽንቴ መጥቷል እኮ ነው የምልህ!... "
በዘበኛው ኃይለ ቃል ልክ መለሰለት።
“ጤናም የለው እንዴ ሰውየው?" ዘበኛው ካፖርቱን እላዩ ላይ ጣል
አድርጎ አጭር ዱላውን ይዞ ወጣ፡፡
ሂድ ግባ! ቦቦው የተዘጋጀው ላንተ እኮ ነው!" አለና ጮኹ፡፡
“የት ነው የምሄድልህ?!"
"አልጋው ስር አለልህ እኮ ነው የምልህ!"
“አልጋ ስር ሽና ነው የምትለኝ?!"
እዚህ ደጅ ግን መሽኛ ቦታ የለም! ያንተ ቢጤ ሰካራሞች ናቸው እዚህ እንኳን አልጋ ስር አልጋህም ላይ ሽናው! እሱ የኔ ችግር አይደለም!
ሽንታቸውን እየሸኑ የጉንፋን መጫወቻ ያደረጉኝ!” በንዴት ጮኸ፡ በዚህ በሁለቱ ጭቅጭቅ መሃል ዓለሚቱ ልቧ በፍርሃት ተውጦ እያዳመጠች ና። የውሽማዋን አመል ስለምታውቅ ሽማግሌውን ሲጥ!
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...ፀጉሩን ተላጨና ቁምጣ ሱሪውን አወለቀ! በምትኩ ቀጭን ቦላሌውን ለበሰ፡፡ ከላይ ሸሚዝና ኮቱን ደርቦ ሽክ.. ኳ! ብሎ ሲታይ ያ ጎንቻ! ያ አስፈሪው ጎንቻ! ያ ባለጎፈሬው ሽፍታ! መሆኑን እንኳንስ የማያውቀው የሚ
ያውቀውም ቢሆን ለማመን ይቸገር ነበር፡፡ውስጣዊ እሱነቱ ሳይሆን ውጫዊ ማንነቱ ተቀይሯል። የከተማው ሰው
የሚለብሰውን ልብስ ለብሶ ሰው መሰል አውሬነቱን የሚያሳስት አይነት ሆኗል።
በዚያች ምሽት በጠፍ ጨረቃ ከዓለሚቱ ጋር ተያይዘው ጠፉ... ከኢተያ ከተማ እስከ ዴራ ከተማ በእግራቸው ተጓዙ በሌሊት መኪና ተሳፈሩና ናዝሬት ገቡ፡፡ ከዚያም ወደ አዲስ አበባ ወደዚያ የከተማ ጫካ፣ ወደዚያ የከተማ ዋሻ ገብተው ሊደባለቁ በአዲስ አበባ መኪና ላይ ተሳፈሩ። ከእንግዲህ በኋላ ጎንቻን ፈልጎ ማግኘት ከእንግዲህ በኋላ ዓላሚቱን ፈልጎ
ማግኘት ቁና አሸዋ ውስጥ የወደቀች ጤፍ ለማግኘት እንደመሞከር ነው፡፡ ከእንግዲህ ወዲያ ዓለሚቱ ባሏን ያስገደለች እየተባለች ከምትጠበስበት የሀሜት ምላስ ልትድን እፎይ ልትል ነው፡፡ እነኝያ የገደ ቢስ
ልጆች ጨርሰው ከዐይኖቿ ሊርቁላትና ሰላማዊ ሰዎች መስለው ከአዲስ አበባ ህዝብ ጋር ሊቀላቀሉ የቀራቸው በሰዓታት የሚቆጠር ጊዜ ብቻ
ነው፡፡
ከእንግዲህ ወዲያ የጎንቻን ፍቅር ሙቀቱ እስከሚያቃጥላት ድረስ እንደ ልቧ ልትሟሟቀው ሁኔታው ተመቻችቶላታል። ከእንግዲህ በኋላ የልታጌጥ፣ እንደፈለገችው ልትዘል፣ ልትቦርቅ ልጓሙ ተፈቶላታል።
ጎንቻም አንጎሉን ሲያዞረው በኖረው በዓለሚቱ ፍቅር ወፈፍ በሚያደርገው በዓለሚቱ ናፍቆት ክፉኛ ተጎድቶ ነበር። አብዛኛውን ጊዜ በጫካ ውስጥ ትዝታዋን ብቻ እያቀፈ በማደር ሲሰቃይ ኖሯልና ናፍቆቷ ነፍሱን መንጥቆ ሳያወጣው በፊት ጥሩ ዘዴ ፈጥራ ይዛው በመኮብለሏ አልተከፋም፡፡ያንን ቢያሽተው ቢምገው የማይጠግበው መዓዛዋን በየቀኑ በየደቂቃው ሊያጣጥመው ነውና ኩብለላው ብዙም አላስጨነቀውም ነበር። የተሳፈሩበት ሎንቺና ወስዶ ለገሃር ጣላቸው፡፡
ጎንቻ ከጫካ ያመለጠ አውሬነቱ የታወቀው ገና ከመኪና ላይ እንደወረደ ነበር፡፡ ተይዛ ያመለጠች ሚዳቋ መሰለ፡፡ ሽው!...ሽው!... ውር!... ውር
በሚሉት መኪኖች መሀል ሲገባ ሮጦ ሊያመልጥ ሞከረ። እንጣጥ!
እንጣጥ! እያለ የአንዱ መኪና ራት ሊሆን ትንሽ ቀረው። መንገዱ መሀል ሲደርስ ሰግጠጥ.. ሰግጠጥ እያደረገው አንዴ ወደ ፊት አንዴ ደግሞ ወደ ኋላ ለማምለጥ ዓለሚቱን ክፉኛ ታገላት።እሷም መደናበሯ አልቀረም ቆይ ጎንቻዬ እኔን ተከተለኝ፡፡ ቀስ በል። እኔ ወደምሄድበት ረጋ ብለህ ተራመድ። መኪኖቹን አትመልከት። ያዞርሃል ... ቀስ ...አዎ እንደሱ ጎሽ
..እጆቹን ግጥም አድርጋ ያዘችው እንደምንም ብለው እየተጓተቱ አስፋልቱን ተሻገሩ።
“እሺ ...አዞረኝ እኮ…ቆይ ቁጭ ልበል" አላት፡፡ ደገፈችውና ወደ አንድ ህንፃ አጥር ጥግ ሄዱ፡፡ ተረከዙ ላይ እንደ ዝንጀሮ ቁጢጥ አለ፡፡ ጭውው..አለበት። ጭንቅላቱን በሁለት እጆቹ ያዘው። ዐይኖቹ ጭፍን ክድን ጭፍን
ክድን አሉ፡፡ መኪና ላይ ያልተሰማው የማጥወልወል ስሜት ተሰማው፡፡
"ርቦህ ይሆናል ጌታዬ ርቦህ ነው። ቆይ እዚህ ጋር የማየው ሆቴል ቤት ነው መሰለኝ" ባሻገር ከሚታየው ቤት ላይ ጣቷን ቀስራ አሳየችው።ቆዳቸው የተገፈፈ በጎች ሳይበለቱ ተሰቅለዋል። የሰንጋ ብልቶች በአይነት በአይነታቸው በስርአት ተዘጋጅተው በወረንጦ ላይ ተንጠልጥለዋል፡፡
ልክ ነው ምግብ ቤት ነው" አለችውና ከተቀመጠበት አስነስታው ተያይዘው
ትደጋግፈው ወደ ስጋ ቤቱ አመሩ....
የሚበላ ነገር አለ?" ብላ ጠየቀች፡፡
“አዎን!” አለ ሻጩ፡፡
“ምን አለ?"
“ሁሉም ነገር አለ፡፡ የፈለጋችሁትን..." ወደ ውስጥ እንደመዝለቅ አለችና የሻጩን ዐይን ዐይን በልምምጥ ተመለከተችው።
“በል እስቲ ቀይ ወጥ በእንጀራ..“ፈራ ተባ እያለች ጠየቀቸው። ዓለሚቱ ከልጁ ጋር ስትነጋገር ጎንቻን እንደ ህፃን ልጅ ግራ እጁን ግጥም አድርጋ
ይዛው ነበር፡፡ ጎንቻ...ያ ወንዱ..ጎንቻ... ያ አስፈሪው ጎንቻ አስፈሪነቱ ጀግንነቱ ከሹሩባው ጋር አብሮ እንደተላጨ ሁሉ ወኔው በኛሮ ጫካ ውስጥ ተጥሎ እንደቀረ ሁሉ ዐይኖቹ ፈጠው ርቦት ሲቁለጨለጭ ቀበሮ
የፈሳባት ጦጣ መስሎ ሲታይ እሱነቱን የማይክድ አልነበረም።
“በሉ ጥፉ ከዚህ! ፋራዎች! ገገማዎች! ይሄ የሥጋ መሸጫ ሉካንዳ እንጂ የእንጀራ መሽጫ ጉሊት መስለሽ?! አይተሽ አትጠይቂም?!” ጮኸባት።
ሽምቅቅ አሉ፡፡ አቤት አደነጋገጥ ወጥቶ ፀብ እንዳይፈጥር ጎንቻም በንዴት እልህ ውስጥ እንዳይገባና ገና አንዱንም ሳይይዙት መዘዝ ውስጥ እንዳይገባ ፈራች ፀብ ከተፈጠረ ፖሊስ ይዞ እንዳያንገላታቸው ስጋት አደረባትና
ዐይኖቹ መቅላት ልቡ የንዴት ደም መርጨት ሰውነቱ መቆጣት
የጀመረው ጎንቻን ሙጭጭ አድርጋ ይዛ የስድብ መዓት ከሚያወርድባቸው ጎረምሳ ሽሹ...ጎንቻ አንድ ቂም በልቡ ቋጠረ፡፡ ርቦት ሆዱ የእህል
ያለህ! በሚልበት ሰዓት ወስፋት የሚቆልፍና ወሽመጥ የሚበጥስ የስድብ መርዝ ቀመሰ። እንደምንም ብለው እየተጓተቱ ሄዱና እንጀራ የሚሽጥበት ምግብ ቤት በጠቋሚ አገኙ። በሉ፣ጠጡ፣ ጠገቡ። ጊዜው እየመሸ
ሲመጣ አሁንም በጥቆማ አልቤርጎ ተከራዩ። ምን ችግር አለ? ብር እንደሆነ ዕድሜ ለጎንቻ! በሽበሽ ነው፡፡ ከሰባት ሺህ ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ ይዘዋል። ጎንቻን ትንሽ ያስቸገረው መብራቱ ነበር፡፡ ብርሃን በጣም በዛበት። ዐይኑ በአንድ ጊዜ የአምፖሉን ብርሃን መቋቋም አልቻለም፡፡
ሊተኙ አካባቢ አምፖሉን ቀድሞ ለማጥፋት የሞከረው እሱ ነበር፡፡ “ኡፍ ኡፍፍ. ኡፍፍፍ..!" እንደ ኩራዙ ሞከረ። በኋላ ግን ዓለሚቱ በድርጊቱ እየሳቀች ማጥፊያውን ቀጭ... ቋ! አድርጋ አጠፋችውና በችሎታዋ እየተኩራራችበት ተቃቅፈው ተኙ፡፡
ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት አካባቢ ጎንቻ ሽንቱ ወጠረውና የመኝታ ቤቱን በር ቷ! አድርጎ ከፍቶ ወጣ፡፡ የተከፈተውን ድምፅ የሰማው ሽማግሌ ዘበኛ
“ማነው?” አለ በተጎተተ ድምፅ፡፡
"እኔ ነኝ!" አለ ጎንቻ።
"ወዴት ነው?"
ለውሃ ሽንት!"
“የውሃ ሽንት ተሆነ ቦቦው አለልህ አይደለም?! የት ልትሸና ነው? አሁን የሽንት ቤቱ በር ቁልፍ ነው" አለና ዘበኛው ቁጣ ቀረሽ መልስ ሰጠው፡፡
"የምን ቦቦ ነው የምትለኝ ጃል?! ሽንቴ መጥቷል እኮ ነው የምልህ!... "
በዘበኛው ኃይለ ቃል ልክ መለሰለት።
“ጤናም የለው እንዴ ሰውየው?" ዘበኛው ካፖርቱን እላዩ ላይ ጣል
አድርጎ አጭር ዱላውን ይዞ ወጣ፡፡
ሂድ ግባ! ቦቦው የተዘጋጀው ላንተ እኮ ነው!" አለና ጮኹ፡፡
“የት ነው የምሄድልህ?!"
"አልጋው ስር አለልህ እኮ ነው የምልህ!"
“አልጋ ስር ሽና ነው የምትለኝ?!"
እዚህ ደጅ ግን መሽኛ ቦታ የለም! ያንተ ቢጤ ሰካራሞች ናቸው እዚህ እንኳን አልጋ ስር አልጋህም ላይ ሽናው! እሱ የኔ ችግር አይደለም!
ሽንታቸውን እየሸኑ የጉንፋን መጫወቻ ያደረጉኝ!” በንዴት ጮኸ፡ በዚህ በሁለቱ ጭቅጭቅ መሃል ዓለሚቱ ልቧ በፍርሃት ተውጦ እያዳመጠች ና። የውሽማዋን አመል ስለምታውቅ ሽማግሌውን ሲጥ!
👍4❤2
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_አርባ
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....እሱም ዓለሚቱም ለአገሩ እንግዶች በመሆናቸው ምክንያት ፍላጎቱን በአስቸኳይ ማሳካት አልቻለም፡፡ ይሁን እንጂ እየዋለ እያደረ እሱ የሚፈልጋት ወንጀል እሱ የተጠማት ደም ወዳጅዋን ፍለጋ ዳዴ እያለች እየመጣችለት ነበር።
እንደ ልማዱ የአንበሶቹን ግቢ አጥር አንቆ አንበሶቹን ይመለከታል።
“ሲያዩት ገና ከገጠር የመጣ ነው" አለ ከወዲያ ማዶ ሆኖ ሁኔታውን ሲከታተል የነበረው ጆብሬ፡፡በአዲስ ልብሱ በቦላሌ ሱሪው ውስጥ ደንበኛ ባላገርነቱን አነበበ፡፡ በሃሳቡ ከኮት ኪሱ ውስጥ ከብብቱ ስር ገብቶ ሲሞዠልቀው ታየው።
እጅሬ የእርሻ በሬዋን ወይንም የጎተራ ጥሬዋን ሸጣ በርካታ ብር ሳትይዝ አትቀርም"ብሎ ገመተና "ልዳብሳት!"ሲል ወሰነ፡፡ አስፋልቱን ተሻገረና ወደ አንበሶቹ ግቢ መጣ፡፡ ጠጋ አለ። ወደ ጎንቻ፡ ሽቦውን በሁለት እጆቹ ግጥም አድርጎ ይዞ "ፓ! ወይኔ! ኧረረረ!!…አፉን እንዴት ነው የሚከፍተው በእናታችሁ?!” የጎንቻን የባላገሯን ልብ ሰልቦ ትኩረቷን በአንበሳው
ላይ እንድትጥል ለማድረግና ከዚያም ያለ ሀሳብ ኪሷን ለመዳበስ ነበር።
በጆብሬ አመለካከት ጎንቻ አፏን ከፍታ የቀረችው አንበሳ አይታ ስለማታውቅ ነው፡፡ ያላወቁ አለቁ! አሉ?…ቀስ በቀስ ባላገሯን ተጠጋት። እባቡ ጎንቻ! እንኳንስ ስው ጥላውን የሚጠራጠረው ጎንቻ የጆብሬን እንቅስቃሴ ቀርቶ ሃሳቡን ከነቃበት ቆይቷል። የበግ ለምድ የለበስ የቀበሮ ባህታዊነቱን ያላወቀው ጆብሬ ሲፈርድበት እነዚያ በልምድ የዳበሩ ጣቶቹን
በመቀስ ፎርም ወደ ጎንቻ የኮት ኪስ ሰደዳቸው።
“ሌንጨ ቦሩ!!" አለና ፎከረ እንደ ልማዱ።
ሂድ!ጀጋ! ምን አባክ ሆነሃል?!! ገገማ!!. ጆብሬ ዐይኖቹ እንደፈጠጡ እንደማፈግፈግም እንደማስፈራራትም አደረገው፡፡ ጡንቻውንም እንደማሳየት ቃጣው። ዳሩ ምን ያደርጋል? ያ ባላገር ፤ላጆብሬም እንደ ህልም ሆኖ በሚታወሰው ኃይል ከብረት ምጣዱ ላይ ተሰቅስቆ እንደሚነሳ ቂጣ ሰቅስቆ ወደ ሰማይ አነሳና አስፋልቱ ላይ አነጠፈው። ሲሰርቀው ኪሱ ሊገባ የተመለከቱ ሰዎች ከበቡ። ጆብሬ ሌባ
መሆኑን ከሚመስክረው የተጫጫረ ፊቱ ሌላ የሚያውቁትም ነበሩ፡፡
“ጎሽ! ጎሽ! እሰይ! ወንድ!.. ይበለው! ይበለው ይንጫጩ ጀመር፡፡
“ባላገር መስላ አጅሬ ወንድ ናት!!" ጎንቻን አደነቁ፡፡ ጎንቻም አዲስ አበባ ከገባ ከአንድ ወር በኋላ ደም ካየ ደም ከተጠማ ከአንድ ወር በኋላ ምንም እንኳን ትርፍ የሌለውና ጥቅም የማያስገኝ ቢሆንም ደፍሮ ኪሱ የገባ
ጠላቱን ወደ መሬት ደፍቶ በአፍንጫና በአፉ ደም አስደፈቀው...ጎንቻ ደም አየ። ተደሰተ፡፡ በብዙ ሰው ኃይልና በበርካታ ክንዶች ወደ ላይ በግድ
ተጎትቶ ተነሳ። ቀልጣፋው ጆብሬ፣ አንበሳው ጆብሬ ጣቶቹ አነጣጥረው የማይስቱት ጆብሬ፣ ጉልበቱ የጅብ የነበረው ጆብሬ በጎንቻ ክንድ ውርደት ቀመሰ፡፡ ፍፁም ያልገመተው ነበርና ጎንቻን በአድናቆት ተመለከተው።
ጎንቻን ፈራው፡፡ በፍርሃትና በአድናቆቱ ውስጥም ወደደው። ደሙን ጠራረገና ሄደ። ራቅ ብሎ ከሄደ በኋላ እንደገና ዘወር ብሎ ጎንቻን በጥንቃቄ አስተዋለው፡፡ በአድናቆት ጭንቅላቱን እያከከ ተመልሶ መጣ፡፡
“ወንድ ነህ! ወንድ ጀግና!" እጁን በአድናቆት ዘረጋለት፡፡ ወንድነቱን አምኖ ተሸናፊነቱን ተቀብሎ እጁን የሰጠውን ምርኮኛ ሊያሳፍረው አልፈለገም::ያን ሲመኘው የነበረ፣ ያን ሲያቅበጠብጠው የከረመ ስራ የሚጀምርበትን ቀን ምክንያት አድርጎ ይሆን ጆብሬን የጣለለት? ማን ያውቃል?እጁን ሲዘረጋለት እሱም እየሳቀ ወዘወዘው፡፡ እንደገና ተቃቀፉ፡፡
"አንበሳ ነህ!" ሲል ጆብሬ በድጋሚ አደነቀው። ይሄ ሁሉ እርቀ ሰላም
የወረደው ፀቡ ከበረደና ለወሬ የተሰበሰበው ሰው ከተበተነ በኋላ ሆነ እንጂ ሁኔታቸውን ከመጀመሪያ ጀምሮ ለተከታተለ ሰው ጉድ የሚያሰኝ ነበር፡፡ እንደዚያ ተናንቀው ሲደባደቡ የነበሩት ሰዎች የደም ማግኔት አሳሳባቸውና አንደኛው አድናቂ ሌላው ተደናቂ ሆነው ጨዋታ ጀመሩ።
“ጆብሬ ጫን ያለው እባላለሁ!"
“ጎንቻ ሀጂ ቦሩ" እሰኛለሁ፡፡
"በጣም ወድጄሃለሁ ልጋብዝህ እፈልጋለሁ።"
“ዛሬ አልጋበዝልህም፡፡ ከፈለክ ለነገ እንቀጣጠር” አንድም ቶሎ ብሎ ተጋባዥ ላለመሆን ሁለተኛው ደግሞ የጆብሬን ቁም ነገረኛነት ለማወቅ
እንዲያስችለው በማግስቱ እዚያው አንበሶቹ ግቢ በራፉ ላይ ለመገናኘት ተቀጣጥረው ተለያዩ፡ ጆብሬ ሀቀኛ ስዓት አክባሪነቱንና ጎንቻን ለቁም ነገር የሚፈልገው መሆኑን አረጋገጠ፡፡ ከቀጠሮው ቀድሞ እየጠበቀው ነበር። ተቃቀፉ፡፡
“ቦታ ይዘን እንጫወት" አለውና ጆብሬ ወደ ሚኒሊክ ሆስፒታል በሚወስደው መንገድ ቁልቁል ይዞት ወረደ። ከዚያም አረቄ ቤት ይዞት ገባና አረቄ እየጠጡ ጨዋታው ደራ። ጆብሬ የህይወት ታሪኩን ይተርክለት ጀመር፡፡
"ወላጆች ነበሩኝ፡፡ መቼም ሰው ያለወላጅ አይፈጠርም! የኔ ወላጆች ግን በአንድ የመንግሥት መሥሪያ ቤት ውስጥ ጥሩ ደመወዝ የሚከፈለው አንደኛው ራስ ወዳድ ሌላው ለኔ አሳቢ ሆኑና በሀሳብ ተለያዩ። አባቴ
ተቀጣሪ ነበር፡፡ እናቴ የቤት እመቤት ነበረች። ገና የሰባት ዓመት ልጅ ሆኜ በቤት ውስጥ ጭቅጭቅና ንትርክ በዛ። አባቴ መጠጥ ይወድ ነበር።
ወላ ሚስቴ የለ ወላ ልጄ የለ! ደመወዙን በአራጣ ለሚበደራቸውና በዱቤ
መጠጥ ለሚሸጡለት ሰዎች ከፋፍሎ ይጨርስና ዐይኑን አፍጥጦ በአል ኮል ነብዞ ይገባል። እናቴ ትንሽ ልትናገረው ከሞከረች አበቃላት። ዛሬን አያድርገው ዛሬን አትውደደኝና በጣም ትወደኝ፣ በጣም ታፈቅረኝ ነበር፡፡ለእኔ ስትል ታገሰችው፡፡ ሲደበድባት ተደብድባ ሲረግጣት መሬት ሆና ብዙ ቻለችው። እንደዚያ የሚያደርገው ቤቱን ጥላለት እንድትጠፋ ሆን
ብሎ ነበር። ጥላው እንዳትሄድ የኔ ነገር ጨነቃት። ከዚያ ቤት ውጭ
የማድግ አልመሰላትም። የአባት ፍቅር እጦት እንዳይጎዳኝ አሰበች፡፡ በመጨረሻ ላይ ግን ሁሉም ነገር ከአቅሟና ከትዕግስቷ በላይ ሆነባትና እኔን ይዛ ቤቱን ትታለት ጠፋች። ደስ አለው፡፡ ሊፈልጋት አልሞከረም፡፡ወዲያውኑ ሌላ ሚስት አገባ። እኔና እናቴ ከእህቷ ቤት ለኔ አክስት መሆኗ
ነው ከአክስቴ ቤት ገባን። አክስቴ ጠላና አረቄ ትሸጥ ነበር፡፡ እናቴ
እዚያው እሷን እየረዳች መኖር ጀመርን፡፡በዚሁ መሃል እናቴን አንዱ ካላገባሁሽ አላት። አገባችውና እኔን ይዛኝ ቤቱ ገባች፡፡ አዲሱ ባሏ እሷን ይወዳታል።እኔን ግን አይወደኝም፡፡ ዲቃላ! እያለ ይሰድበኝና ያሸማቅቀኝ ነበር።አባዬ ስለው አባት ይንሳህ የለማኝ ልጅ እያለ ያሳቅቀኝ ነበር።
ይሄን የሚያደርገው እናቴ ሳትሰማ ነው። እናቴ በጣም እንደምትወደኝ
ያውቃል። እሷ ፊት ይስመኛል። እሷ ዘወር ስትል ጭንቅላቴ እስከሚበሳ ድረስ በኩርኩም ያጋጨኝና ሳለቅስ እውላለሁ። የእንጀራ አባቴ ቀስ በቀስ ሰው ሳይሆን ጭራቅ እየመሰለኝ ሄደ። ሁል ጊዜ "ዲቃላ! ዲቃላ!
ዲቃላ!” እያለ እየሰደበ እየደበደበ ራሴንም እሱንም እንድጠላ አደረገኝ።
ይሄ ጥላቻዬ ደግሞ ለሱ ጥሩ እንዳልሆን መጥፎ ስራ እንድሰራ ይገፋፋኝ ጀመር፡፡ ቀስ በቀስ ገንዘብ ከኪሱ መስረቅ ጀመርኩ። የሱን ገንዘብ ሰርቄ ብስኩት ገዝቼ ስበላ ይጣፍጠኛል። የጠላት ገንዘብ ይጣፍጣል። እናቴ
፡
፡
#ክፍል_አርባ
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....እሱም ዓለሚቱም ለአገሩ እንግዶች በመሆናቸው ምክንያት ፍላጎቱን በአስቸኳይ ማሳካት አልቻለም፡፡ ይሁን እንጂ እየዋለ እያደረ እሱ የሚፈልጋት ወንጀል እሱ የተጠማት ደም ወዳጅዋን ፍለጋ ዳዴ እያለች እየመጣችለት ነበር።
እንደ ልማዱ የአንበሶቹን ግቢ አጥር አንቆ አንበሶቹን ይመለከታል።
“ሲያዩት ገና ከገጠር የመጣ ነው" አለ ከወዲያ ማዶ ሆኖ ሁኔታውን ሲከታተል የነበረው ጆብሬ፡፡በአዲስ ልብሱ በቦላሌ ሱሪው ውስጥ ደንበኛ ባላገርነቱን አነበበ፡፡ በሃሳቡ ከኮት ኪሱ ውስጥ ከብብቱ ስር ገብቶ ሲሞዠልቀው ታየው።
እጅሬ የእርሻ በሬዋን ወይንም የጎተራ ጥሬዋን ሸጣ በርካታ ብር ሳትይዝ አትቀርም"ብሎ ገመተና "ልዳብሳት!"ሲል ወሰነ፡፡ አስፋልቱን ተሻገረና ወደ አንበሶቹ ግቢ መጣ፡፡ ጠጋ አለ። ወደ ጎንቻ፡ ሽቦውን በሁለት እጆቹ ግጥም አድርጎ ይዞ "ፓ! ወይኔ! ኧረረረ!!…አፉን እንዴት ነው የሚከፍተው በእናታችሁ?!” የጎንቻን የባላገሯን ልብ ሰልቦ ትኩረቷን በአንበሳው
ላይ እንድትጥል ለማድረግና ከዚያም ያለ ሀሳብ ኪሷን ለመዳበስ ነበር።
በጆብሬ አመለካከት ጎንቻ አፏን ከፍታ የቀረችው አንበሳ አይታ ስለማታውቅ ነው፡፡ ያላወቁ አለቁ! አሉ?…ቀስ በቀስ ባላገሯን ተጠጋት። እባቡ ጎንቻ! እንኳንስ ስው ጥላውን የሚጠራጠረው ጎንቻ የጆብሬን እንቅስቃሴ ቀርቶ ሃሳቡን ከነቃበት ቆይቷል። የበግ ለምድ የለበስ የቀበሮ ባህታዊነቱን ያላወቀው ጆብሬ ሲፈርድበት እነዚያ በልምድ የዳበሩ ጣቶቹን
በመቀስ ፎርም ወደ ጎንቻ የኮት ኪስ ሰደዳቸው።
“ሌንጨ ቦሩ!!" አለና ፎከረ እንደ ልማዱ።
ሂድ!ጀጋ! ምን አባክ ሆነሃል?!! ገገማ!!. ጆብሬ ዐይኖቹ እንደፈጠጡ እንደማፈግፈግም እንደማስፈራራትም አደረገው፡፡ ጡንቻውንም እንደማሳየት ቃጣው። ዳሩ ምን ያደርጋል? ያ ባላገር ፤ላጆብሬም እንደ ህልም ሆኖ በሚታወሰው ኃይል ከብረት ምጣዱ ላይ ተሰቅስቆ እንደሚነሳ ቂጣ ሰቅስቆ ወደ ሰማይ አነሳና አስፋልቱ ላይ አነጠፈው። ሲሰርቀው ኪሱ ሊገባ የተመለከቱ ሰዎች ከበቡ። ጆብሬ ሌባ
መሆኑን ከሚመስክረው የተጫጫረ ፊቱ ሌላ የሚያውቁትም ነበሩ፡፡
“ጎሽ! ጎሽ! እሰይ! ወንድ!.. ይበለው! ይበለው ይንጫጩ ጀመር፡፡
“ባላገር መስላ አጅሬ ወንድ ናት!!" ጎንቻን አደነቁ፡፡ ጎንቻም አዲስ አበባ ከገባ ከአንድ ወር በኋላ ደም ካየ ደም ከተጠማ ከአንድ ወር በኋላ ምንም እንኳን ትርፍ የሌለውና ጥቅም የማያስገኝ ቢሆንም ደፍሮ ኪሱ የገባ
ጠላቱን ወደ መሬት ደፍቶ በአፍንጫና በአፉ ደም አስደፈቀው...ጎንቻ ደም አየ። ተደሰተ፡፡ በብዙ ሰው ኃይልና በበርካታ ክንዶች ወደ ላይ በግድ
ተጎትቶ ተነሳ። ቀልጣፋው ጆብሬ፣ አንበሳው ጆብሬ ጣቶቹ አነጣጥረው የማይስቱት ጆብሬ፣ ጉልበቱ የጅብ የነበረው ጆብሬ በጎንቻ ክንድ ውርደት ቀመሰ፡፡ ፍፁም ያልገመተው ነበርና ጎንቻን በአድናቆት ተመለከተው።
ጎንቻን ፈራው፡፡ በፍርሃትና በአድናቆቱ ውስጥም ወደደው። ደሙን ጠራረገና ሄደ። ራቅ ብሎ ከሄደ በኋላ እንደገና ዘወር ብሎ ጎንቻን በጥንቃቄ አስተዋለው፡፡ በአድናቆት ጭንቅላቱን እያከከ ተመልሶ መጣ፡፡
“ወንድ ነህ! ወንድ ጀግና!" እጁን በአድናቆት ዘረጋለት፡፡ ወንድነቱን አምኖ ተሸናፊነቱን ተቀብሎ እጁን የሰጠውን ምርኮኛ ሊያሳፍረው አልፈለገም::ያን ሲመኘው የነበረ፣ ያን ሲያቅበጠብጠው የከረመ ስራ የሚጀምርበትን ቀን ምክንያት አድርጎ ይሆን ጆብሬን የጣለለት? ማን ያውቃል?እጁን ሲዘረጋለት እሱም እየሳቀ ወዘወዘው፡፡ እንደገና ተቃቀፉ፡፡
"አንበሳ ነህ!" ሲል ጆብሬ በድጋሚ አደነቀው። ይሄ ሁሉ እርቀ ሰላም
የወረደው ፀቡ ከበረደና ለወሬ የተሰበሰበው ሰው ከተበተነ በኋላ ሆነ እንጂ ሁኔታቸውን ከመጀመሪያ ጀምሮ ለተከታተለ ሰው ጉድ የሚያሰኝ ነበር፡፡ እንደዚያ ተናንቀው ሲደባደቡ የነበሩት ሰዎች የደም ማግኔት አሳሳባቸውና አንደኛው አድናቂ ሌላው ተደናቂ ሆነው ጨዋታ ጀመሩ።
“ጆብሬ ጫን ያለው እባላለሁ!"
“ጎንቻ ሀጂ ቦሩ" እሰኛለሁ፡፡
"በጣም ወድጄሃለሁ ልጋብዝህ እፈልጋለሁ።"
“ዛሬ አልጋበዝልህም፡፡ ከፈለክ ለነገ እንቀጣጠር” አንድም ቶሎ ብሎ ተጋባዥ ላለመሆን ሁለተኛው ደግሞ የጆብሬን ቁም ነገረኛነት ለማወቅ
እንዲያስችለው በማግስቱ እዚያው አንበሶቹ ግቢ በራፉ ላይ ለመገናኘት ተቀጣጥረው ተለያዩ፡ ጆብሬ ሀቀኛ ስዓት አክባሪነቱንና ጎንቻን ለቁም ነገር የሚፈልገው መሆኑን አረጋገጠ፡፡ ከቀጠሮው ቀድሞ እየጠበቀው ነበር። ተቃቀፉ፡፡
“ቦታ ይዘን እንጫወት" አለውና ጆብሬ ወደ ሚኒሊክ ሆስፒታል በሚወስደው መንገድ ቁልቁል ይዞት ወረደ። ከዚያም አረቄ ቤት ይዞት ገባና አረቄ እየጠጡ ጨዋታው ደራ። ጆብሬ የህይወት ታሪኩን ይተርክለት ጀመር፡፡
"ወላጆች ነበሩኝ፡፡ መቼም ሰው ያለወላጅ አይፈጠርም! የኔ ወላጆች ግን በአንድ የመንግሥት መሥሪያ ቤት ውስጥ ጥሩ ደመወዝ የሚከፈለው አንደኛው ራስ ወዳድ ሌላው ለኔ አሳቢ ሆኑና በሀሳብ ተለያዩ። አባቴ
ተቀጣሪ ነበር፡፡ እናቴ የቤት እመቤት ነበረች። ገና የሰባት ዓመት ልጅ ሆኜ በቤት ውስጥ ጭቅጭቅና ንትርክ በዛ። አባቴ መጠጥ ይወድ ነበር።
ወላ ሚስቴ የለ ወላ ልጄ የለ! ደመወዙን በአራጣ ለሚበደራቸውና በዱቤ
መጠጥ ለሚሸጡለት ሰዎች ከፋፍሎ ይጨርስና ዐይኑን አፍጥጦ በአል ኮል ነብዞ ይገባል። እናቴ ትንሽ ልትናገረው ከሞከረች አበቃላት። ዛሬን አያድርገው ዛሬን አትውደደኝና በጣም ትወደኝ፣ በጣም ታፈቅረኝ ነበር፡፡ለእኔ ስትል ታገሰችው፡፡ ሲደበድባት ተደብድባ ሲረግጣት መሬት ሆና ብዙ ቻለችው። እንደዚያ የሚያደርገው ቤቱን ጥላለት እንድትጠፋ ሆን
ብሎ ነበር። ጥላው እንዳትሄድ የኔ ነገር ጨነቃት። ከዚያ ቤት ውጭ
የማድግ አልመሰላትም። የአባት ፍቅር እጦት እንዳይጎዳኝ አሰበች፡፡ በመጨረሻ ላይ ግን ሁሉም ነገር ከአቅሟና ከትዕግስቷ በላይ ሆነባትና እኔን ይዛ ቤቱን ትታለት ጠፋች። ደስ አለው፡፡ ሊፈልጋት አልሞከረም፡፡ወዲያውኑ ሌላ ሚስት አገባ። እኔና እናቴ ከእህቷ ቤት ለኔ አክስት መሆኗ
ነው ከአክስቴ ቤት ገባን። አክስቴ ጠላና አረቄ ትሸጥ ነበር፡፡ እናቴ
እዚያው እሷን እየረዳች መኖር ጀመርን፡፡በዚሁ መሃል እናቴን አንዱ ካላገባሁሽ አላት። አገባችውና እኔን ይዛኝ ቤቱ ገባች፡፡ አዲሱ ባሏ እሷን ይወዳታል።እኔን ግን አይወደኝም፡፡ ዲቃላ! እያለ ይሰድበኝና ያሸማቅቀኝ ነበር።አባዬ ስለው አባት ይንሳህ የለማኝ ልጅ እያለ ያሳቅቀኝ ነበር።
ይሄን የሚያደርገው እናቴ ሳትሰማ ነው። እናቴ በጣም እንደምትወደኝ
ያውቃል። እሷ ፊት ይስመኛል። እሷ ዘወር ስትል ጭንቅላቴ እስከሚበሳ ድረስ በኩርኩም ያጋጨኝና ሳለቅስ እውላለሁ። የእንጀራ አባቴ ቀስ በቀስ ሰው ሳይሆን ጭራቅ እየመሰለኝ ሄደ። ሁል ጊዜ "ዲቃላ! ዲቃላ!
ዲቃላ!” እያለ እየሰደበ እየደበደበ ራሴንም እሱንም እንድጠላ አደረገኝ።
ይሄ ጥላቻዬ ደግሞ ለሱ ጥሩ እንዳልሆን መጥፎ ስራ እንድሰራ ይገፋፋኝ ጀመር፡፡ ቀስ በቀስ ገንዘብ ከኪሱ መስረቅ ጀመርኩ። የሱን ገንዘብ ሰርቄ ብስኩት ገዝቼ ስበላ ይጣፍጠኛል። የጠላት ገንዘብ ይጣፍጣል። እናቴ
❤1👍1
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....አሜሪካን ግቢ፣ጌሾ ተራ፣ ዶሮ ማነቂያ፣ ሠራተኛ ሰፈር፣ እሪ በከንቱ በጎንቻ ቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡ የጆብሬና የጎንቻ ጓደኝነት ከሁለትነት ወደ አራትነት ተሸጋገረ። ጎንቻ ጀግንነቱን ለመጀመሪያ ጊዜ ያስመሰከረው
በፈጣን የአንገት ጥምዘዛ ነበር፡
አንድ ምሽት በሀብተ ጊዮርጊስ ድልድይ አካባቢ ለወሊድ የደረሰች ሚስቱን በሌሊት ሆስፒታል አድርሶ የመመለሻ መኪና አጥቶ ወደ ቤቱ ኩስ ኩስ የሚል ምስኪን አንገት እንደ ዶሮ ጠምዝዞ በመጣል ማንነቱን አሳየው።
ጆብሬ ፍጥነቱንና ቅልጥፍናውን የበለጠ አደነቀው።ከዚያን ግዜ ጀምሮ የበለጠ እያከበረውና እየፈራው መጣ፡፡ገንዘብ በሽበሽ ሆነ፡፡ ጆብሬ ኪስ ይዳብሳል።ጎንቻ ማጅራት ይመታል። ክርክር ከበዛ አንገት እንደ ፎጣ ጠምዝዞ ይጨምቅና ይበረብራል"ለካስ በከንቱ ኖሯል ኛሮ ኛሮ ያሰኘኝ?”
አለ፡፡ ኛሮን በአሜሪካ ግቢ ውስጥ፣ ኛሮን በጌሾ ተራ ውስጥ፣ ኛሮን በዶሮ ማነቂያ ውስጥ፣ ኛሮን በሠራተኛ ሰፈር ውስጥ፣ ኛሮን በእሪ በከንቱ ውስጥ አገኘው
ከኛሮ የቀረ የቀረበት ነገር ቢኖር
ዋሻውና የአውሬ ስጋው ብቻ ነበር፡፡በአዲስ አበባ ውስጥ የወላጆቹን ሃይማኖት ቀይሮ የዓለሚቱ ሃይማኖት ተከታይ ሆኖ አብረው ጮማ ይቆርጣሉ፡፡
አልኮል ይጨልጣሉ። ከዓለሚቱ ጋር በአረግራጊ ሽቦ አልጋ ላይ ያረገርጋሉ። ከዓላሚቱ ጋር እንደዚህ ዓለምን እየቀጩ በአዲስ አበባ ውስጥ መኖርን ቀስ በቀስ እየለመደው፣ እየወደደው መጣ፡፡ አዲስ አበባ ጣመችው፡፡ ጆብሬም
እውነተኛ ታማኝ ጓደኛነቱን አስመሰከረ ጎንቻን ጋሻ መከታው አደረገ፡፡ፀብ ከተነሳ ጎንቻ ገላጋይ መስሎ ተበዳይ ላይ ጉብ ነው፡፡ ጆብሬ የደነዘዘ ሰውነት ካገኘ ሞሽልቆ ያመልጣል። ከተነቃበትም ጎንቻ አለኝታው
ነው። ትርዒቱ ቀጠለ፡፡ አንደኛው የአደጋ ጣይ ቡድን ከሌላው ጋር
ተዋወቀ። በጎንቻ የበላይነት በዓለሚቱ ንብረት ተቀባይነትና አስቀማጭነት ወዳጅነቱ ተጧጧፈ።ሌሎቹ የቡድኑ አባላትም ዓለሚቱን በጥሩ አስተናጋጅነቷ ወደዷት። ፍቅር በፍቅር ሆኑ። መኖሪያ ቤታቸውንም ከእንጦጦ ወደ ዋናው መስሪያ ቤታቸው ወደ እሪ በከንቱ አዛወሩና አንድ ሰፊ ክፍል ቤት ተከራዩ።
በገንዘብ ላይ ገንዘብ ተጨመረ፡፡ እያለቀ፣ እየመነመነ የመጣው ገንዘብ ሲያሳስባት የቆየችው ዓለሚቱ ለመቁጠር እስከሚታክታት ድረስ ተንበሽበሸች፡፡ አራጣ በማበደር ሌላ የገቢ ምንጭ ከፈተች፡፡ በውበቷ ላይ ውበት፣
በጌጣጌጦቿ ላይ ጌጣጌጥ፣ በብር ላይ ብር አከማቸች።
ዛሬም በዓለሚቱ ካዳሚነት ጫት እየተቃመ የተዘረፈው ንብረት የሚቆጠርበት፣ ክፍፍል የሚደረግበት፣ እየተመረቀነ፣ እየተፈረሽ ውይይት የሚካ
ሄድበት፣ ተጨማሪ ዕቅድ የሚወጣበት፣ ስትራቴጂ የሚቀየስበትና ስልት
የሚነደፍበት ዕለት ነው፡፡ በቤቱ ውስጥ ያሉት ከዓለሚቱ ጋር አምስት ሲሆኑ ከጆብሬ ሌላ በቅፅል ስሙ “መቀስ" እየተባለ የሚጠራው አንበሴና
በጫት ምርቃና ላይ የሚንተፋተፈው አበራም ይገኙበታል። ጫት ከመጀመሩ በፊት ዓለሚቱ ሳር ጎዝጉዛ ፍራሽ አንጥፋ፣ ከሰል አያይዛ ሁሉን
ነገር አዘገጃጅታለች፡፡
የሜቱ ሥነ ሥርዓት የሚጠይቀው የቄጤማው ጉዝጓዝ ሰንደሉ ዕጣኑ
ሁሉ የተሟላ ነው፡፡ እውነተኛ ካዳሚነቷን አረጋግጣለች ማለት ይቻላል። የሰላም አምባሳደሮች፣ የሳይንስና ምርምር ፕሮፌሰሮች፣ የዕድገት መሀንዲሶች፣ ጥበበኞች እና ምሁራኖችን የምታስተናግድ ካዳሚ..እግሮቻቸውን አጣጥፈው ቦታ ቦታቸውን እንደያዙ ጎንቻ ግድግዳው ላይ ወዳን
ጠለጠለው ኮት ኪሱ ውስጥ ገባና በርካታ ነገሮችን ማውጣት ጀመረ።
በደም የተለወስ የአንገት ሀብል... ትላልቅ የጆሮ ጉትቻዎች… ከወርቅ
የተሰሩ የሴት የእጅ አምባሮች የተለያዩ የብር ኖቶች ያሉበት ትንሽ
ቦርሳ ያ ሁሉ ንብረት ከጥቂት ሰዓታት በፊት አንቆ የዘረፋት ሴት
ሀብት ነበር፡፡ ጆብሬ ዛሬ የሰራውን ሁለት መቶ ብር ከደረት ኪሱ ላጥ
አድርጎ አወጣና አስቀመጠ፡፡ አበራ አልቀናውም፡፡ አንበሴ ዛሬ እንደ አንበሳነቱ ሳይሆን ውርደት ቀምሶ ቡጢ ልሶ ነው የመጣው። ሁለቱ የሰሩትን ሲያወጡ ሁለቱ አፈጠጡ። ወላ ሀባ ጭቅጭቅ ንትርክ የለም። አንዱ ከቀናው ላልቀናው ያካፍላል ዛሬ ባይቀናው ነገ እንደሚክስ የታወቀ ነው፡፡
ይሁን እንጂ መቀስ በጣም አብዝቶታል። ያንን መልካም ቁመናውን ብቻ ዋቤ አድርጎ ዕይኖቹን ያስለመልምና ድርሻውን ላፍ አድርጎ መሰስ ይላል። የቀናው ዕለት እንኳ የረባ ነገር አበርክቶ አያውቅም። እፍኝ ቆሎ ይዞ ከአሻሮ መጠጋት አብዝቷል፡፡ በማንኪያ ሰጥቶ በአካፋ መዛቁን እየደጋገመ መጥቷል።
የተማመነው በማን ይሆን? ጎንቻ ጆብሬ ያስቀመጠውን አየና ወደ ሁለቱ ፊቱን አዙሮ በምልክት
እጃችሁ ከምን? ሲል በእንቅስቃሴ ጠየቃቸው፡፡ ያገኘው መልስ ግን የፈጠጡ አራት ዐይኖች ሲንከባሉና ሲቁለጨለጩ ከማየት ሊዘል አልቻለም።
“ስማ መቀስ ብዙ ብልጥ መሆን አያስፈልግም! የምታገኘውን ላፍ አድርገህ ትሄዳለህ፡፡ ይዘህ የምትመጣው የሰራኸውን ሳይሆን በብልጠት እየቀነጨብክለት መሆኑን ሁላችንም እናውቃለን። በመካከላችን ዋናው ቁም ነገር መተማመን ነው! አንተ ግን ሁኔታህን ደጋግሜ ስመለከ
ተው እምነት የጎደለህ ትመስላለህ፡፡ ሁል ጊዜ የሌላውን ድካም ጠባቂ መሆን ብልጥነት ብቻ ሳይሆን ዐይን አውጣነት ነው!” ተቆጣ፡፡ 'የአበራ ጉዳይ እንኳ ምንም አይደለም የታወቀ ነው። ቶሉ ቶሎ ባይቀናውም
አንዴ ከቀናው በሽ በሽ ስለሆነ ግድ የለም። አንተ ግን አበዛኸው። ከዚህ ውስጥ ምንም የሚደርስህ ነገር እንደማይኖር አረጋግጥልሀለሁ! በርጫህን ቅመህ ለጨብሲ የምትሆን አስር ብር በቂህ ስለሆነ ሌላውን እን
ዳትጠብቅ!" ቁርጡን ነገረው፡፡ ከጎንቻ ያላነሰ የአረመኔነት ባህሪ የነበረው መቀስ ለግላጋ ቁመቱና ወንዳወንድነቱ ከውጭ ለሚያየው ሰው የሚስብ ነው። መቀስ በጎንቻ አነጋገር ወሽመጡ ብጥስ አለ። በጉምዥት አፉን የሞላው ምራቅ በድንገት ደረቀ፡፡ ጎንቻ የበላይነቱን በመያዙ እኔስ ከማን አንሼ? በማለት ሊቀናቀነው የሚሞክር ሰው ነው። የቡድኑን የመሪነት ሥልጣን ለመውሰድ ከመመኘት ባለፈ በጎንቻ ላይ ንቀት ነበረው። ይህንን ንቀቱን በተግባር ለማሳየት ደግሞ ዓለሚቱን አጥምዷታል። ጎንቻ ያን የመሰለ አንጀት
የሚበጥስ ንግግር ሲናገረው ቀስ ብሎ ዓለሚቱን በቆረጣ ተመለከታት፡፡ እሷም የጎንቻን ዐይኖችና የሌሎቹንም
እንቅስቃሴ ጠብቃ ማንም ሳያያት ተደብቃ "ጥቅስ" አደረገችው። ፀብ አትፍጠር ማለቷ ነው፡፡ ምን አሳስበህ? ማለቷ ነው። ተረጋጋ....
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ከሶስት ዓመታት የላምበረት ኑሮ በኋላ ዘይኑን ዳግማዊ ሚኒሊክ ትምህርት ቤት አስገባት። ከላምበረት ዳግማዊ ሚኒሊክ ትምህርት ቤት ከምትመላለስ በአቅራቢያው ቤት መከራየት ፈለገና እሪ በከንቱ አካባቢ ሰራተኛ
ስፈር ሁለት ክፍል ያላት ቤት አግኝቶ ተከራየ፡፡ ዘይኑ ለትምህርት ቤቷ ቅርብ የሆነ ቤት አገኘች። ትንሽ ደስ ያላላት ላምበረት የትውልድ መንደሯን ዓይነት ፀጥታ የሰፈነበት ሲሆን እሪ በከንቱ ግን የተጨናነቀና ሁካታ የበዛበት መሆኑ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ረጅም መንገድ ከመመላለስ ታድጓታልና ጉዳቱን በጥቅሙ አካክሳ ተቀብላዋለች፡፡ ጌትነት እህቱን በቅርበት እየተከታተለ ለጥሩ ውጤት እንድትበቃ ማድረጉ፣ በትምህርት ቤት ተጀምሮ ለሁለት አመታት የዘለቀውና ውስጥ ውስጡን ሲያሰቃየው የኖረው ፍቅር መቋጫው አምሮ ከሚወዳት ከአማረች ጋር አስደሳች
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....አሜሪካን ግቢ፣ጌሾ ተራ፣ ዶሮ ማነቂያ፣ ሠራተኛ ሰፈር፣ እሪ በከንቱ በጎንቻ ቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡ የጆብሬና የጎንቻ ጓደኝነት ከሁለትነት ወደ አራትነት ተሸጋገረ። ጎንቻ ጀግንነቱን ለመጀመሪያ ጊዜ ያስመሰከረው
በፈጣን የአንገት ጥምዘዛ ነበር፡
አንድ ምሽት በሀብተ ጊዮርጊስ ድልድይ አካባቢ ለወሊድ የደረሰች ሚስቱን በሌሊት ሆስፒታል አድርሶ የመመለሻ መኪና አጥቶ ወደ ቤቱ ኩስ ኩስ የሚል ምስኪን አንገት እንደ ዶሮ ጠምዝዞ በመጣል ማንነቱን አሳየው።
ጆብሬ ፍጥነቱንና ቅልጥፍናውን የበለጠ አደነቀው።ከዚያን ግዜ ጀምሮ የበለጠ እያከበረውና እየፈራው መጣ፡፡ገንዘብ በሽበሽ ሆነ፡፡ ጆብሬ ኪስ ይዳብሳል።ጎንቻ ማጅራት ይመታል። ክርክር ከበዛ አንገት እንደ ፎጣ ጠምዝዞ ይጨምቅና ይበረብራል"ለካስ በከንቱ ኖሯል ኛሮ ኛሮ ያሰኘኝ?”
አለ፡፡ ኛሮን በአሜሪካ ግቢ ውስጥ፣ ኛሮን በጌሾ ተራ ውስጥ፣ ኛሮን በዶሮ ማነቂያ ውስጥ፣ ኛሮን በሠራተኛ ሰፈር ውስጥ፣ ኛሮን በእሪ በከንቱ ውስጥ አገኘው
ከኛሮ የቀረ የቀረበት ነገር ቢኖር
ዋሻውና የአውሬ ስጋው ብቻ ነበር፡፡በአዲስ አበባ ውስጥ የወላጆቹን ሃይማኖት ቀይሮ የዓለሚቱ ሃይማኖት ተከታይ ሆኖ አብረው ጮማ ይቆርጣሉ፡፡
አልኮል ይጨልጣሉ። ከዓለሚቱ ጋር በአረግራጊ ሽቦ አልጋ ላይ ያረገርጋሉ። ከዓላሚቱ ጋር እንደዚህ ዓለምን እየቀጩ በአዲስ አበባ ውስጥ መኖርን ቀስ በቀስ እየለመደው፣ እየወደደው መጣ፡፡ አዲስ አበባ ጣመችው፡፡ ጆብሬም
እውነተኛ ታማኝ ጓደኛነቱን አስመሰከረ ጎንቻን ጋሻ መከታው አደረገ፡፡ፀብ ከተነሳ ጎንቻ ገላጋይ መስሎ ተበዳይ ላይ ጉብ ነው፡፡ ጆብሬ የደነዘዘ ሰውነት ካገኘ ሞሽልቆ ያመልጣል። ከተነቃበትም ጎንቻ አለኝታው
ነው። ትርዒቱ ቀጠለ፡፡ አንደኛው የአደጋ ጣይ ቡድን ከሌላው ጋር
ተዋወቀ። በጎንቻ የበላይነት በዓለሚቱ ንብረት ተቀባይነትና አስቀማጭነት ወዳጅነቱ ተጧጧፈ።ሌሎቹ የቡድኑ አባላትም ዓለሚቱን በጥሩ አስተናጋጅነቷ ወደዷት። ፍቅር በፍቅር ሆኑ። መኖሪያ ቤታቸውንም ከእንጦጦ ወደ ዋናው መስሪያ ቤታቸው ወደ እሪ በከንቱ አዛወሩና አንድ ሰፊ ክፍል ቤት ተከራዩ።
በገንዘብ ላይ ገንዘብ ተጨመረ፡፡ እያለቀ፣ እየመነመነ የመጣው ገንዘብ ሲያሳስባት የቆየችው ዓለሚቱ ለመቁጠር እስከሚታክታት ድረስ ተንበሽበሸች፡፡ አራጣ በማበደር ሌላ የገቢ ምንጭ ከፈተች፡፡ በውበቷ ላይ ውበት፣
በጌጣጌጦቿ ላይ ጌጣጌጥ፣ በብር ላይ ብር አከማቸች።
ዛሬም በዓለሚቱ ካዳሚነት ጫት እየተቃመ የተዘረፈው ንብረት የሚቆጠርበት፣ ክፍፍል የሚደረግበት፣ እየተመረቀነ፣ እየተፈረሽ ውይይት የሚካ
ሄድበት፣ ተጨማሪ ዕቅድ የሚወጣበት፣ ስትራቴጂ የሚቀየስበትና ስልት
የሚነደፍበት ዕለት ነው፡፡ በቤቱ ውስጥ ያሉት ከዓለሚቱ ጋር አምስት ሲሆኑ ከጆብሬ ሌላ በቅፅል ስሙ “መቀስ" እየተባለ የሚጠራው አንበሴና
በጫት ምርቃና ላይ የሚንተፋተፈው አበራም ይገኙበታል። ጫት ከመጀመሩ በፊት ዓለሚቱ ሳር ጎዝጉዛ ፍራሽ አንጥፋ፣ ከሰል አያይዛ ሁሉን
ነገር አዘገጃጅታለች፡፡
የሜቱ ሥነ ሥርዓት የሚጠይቀው የቄጤማው ጉዝጓዝ ሰንደሉ ዕጣኑ
ሁሉ የተሟላ ነው፡፡ እውነተኛ ካዳሚነቷን አረጋግጣለች ማለት ይቻላል። የሰላም አምባሳደሮች፣ የሳይንስና ምርምር ፕሮፌሰሮች፣ የዕድገት መሀንዲሶች፣ ጥበበኞች እና ምሁራኖችን የምታስተናግድ ካዳሚ..እግሮቻቸውን አጣጥፈው ቦታ ቦታቸውን እንደያዙ ጎንቻ ግድግዳው ላይ ወዳን
ጠለጠለው ኮት ኪሱ ውስጥ ገባና በርካታ ነገሮችን ማውጣት ጀመረ።
በደም የተለወስ የአንገት ሀብል... ትላልቅ የጆሮ ጉትቻዎች… ከወርቅ
የተሰሩ የሴት የእጅ አምባሮች የተለያዩ የብር ኖቶች ያሉበት ትንሽ
ቦርሳ ያ ሁሉ ንብረት ከጥቂት ሰዓታት በፊት አንቆ የዘረፋት ሴት
ሀብት ነበር፡፡ ጆብሬ ዛሬ የሰራውን ሁለት መቶ ብር ከደረት ኪሱ ላጥ
አድርጎ አወጣና አስቀመጠ፡፡ አበራ አልቀናውም፡፡ አንበሴ ዛሬ እንደ አንበሳነቱ ሳይሆን ውርደት ቀምሶ ቡጢ ልሶ ነው የመጣው። ሁለቱ የሰሩትን ሲያወጡ ሁለቱ አፈጠጡ። ወላ ሀባ ጭቅጭቅ ንትርክ የለም። አንዱ ከቀናው ላልቀናው ያካፍላል ዛሬ ባይቀናው ነገ እንደሚክስ የታወቀ ነው፡፡
ይሁን እንጂ መቀስ በጣም አብዝቶታል። ያንን መልካም ቁመናውን ብቻ ዋቤ አድርጎ ዕይኖቹን ያስለመልምና ድርሻውን ላፍ አድርጎ መሰስ ይላል። የቀናው ዕለት እንኳ የረባ ነገር አበርክቶ አያውቅም። እፍኝ ቆሎ ይዞ ከአሻሮ መጠጋት አብዝቷል፡፡ በማንኪያ ሰጥቶ በአካፋ መዛቁን እየደጋገመ መጥቷል።
የተማመነው በማን ይሆን? ጎንቻ ጆብሬ ያስቀመጠውን አየና ወደ ሁለቱ ፊቱን አዙሮ በምልክት
እጃችሁ ከምን? ሲል በእንቅስቃሴ ጠየቃቸው፡፡ ያገኘው መልስ ግን የፈጠጡ አራት ዐይኖች ሲንከባሉና ሲቁለጨለጩ ከማየት ሊዘል አልቻለም።
“ስማ መቀስ ብዙ ብልጥ መሆን አያስፈልግም! የምታገኘውን ላፍ አድርገህ ትሄዳለህ፡፡ ይዘህ የምትመጣው የሰራኸውን ሳይሆን በብልጠት እየቀነጨብክለት መሆኑን ሁላችንም እናውቃለን። በመካከላችን ዋናው ቁም ነገር መተማመን ነው! አንተ ግን ሁኔታህን ደጋግሜ ስመለከ
ተው እምነት የጎደለህ ትመስላለህ፡፡ ሁል ጊዜ የሌላውን ድካም ጠባቂ መሆን ብልጥነት ብቻ ሳይሆን ዐይን አውጣነት ነው!” ተቆጣ፡፡ 'የአበራ ጉዳይ እንኳ ምንም አይደለም የታወቀ ነው። ቶሉ ቶሎ ባይቀናውም
አንዴ ከቀናው በሽ በሽ ስለሆነ ግድ የለም። አንተ ግን አበዛኸው። ከዚህ ውስጥ ምንም የሚደርስህ ነገር እንደማይኖር አረጋግጥልሀለሁ! በርጫህን ቅመህ ለጨብሲ የምትሆን አስር ብር በቂህ ስለሆነ ሌላውን እን
ዳትጠብቅ!" ቁርጡን ነገረው፡፡ ከጎንቻ ያላነሰ የአረመኔነት ባህሪ የነበረው መቀስ ለግላጋ ቁመቱና ወንዳወንድነቱ ከውጭ ለሚያየው ሰው የሚስብ ነው። መቀስ በጎንቻ አነጋገር ወሽመጡ ብጥስ አለ። በጉምዥት አፉን የሞላው ምራቅ በድንገት ደረቀ፡፡ ጎንቻ የበላይነቱን በመያዙ እኔስ ከማን አንሼ? በማለት ሊቀናቀነው የሚሞክር ሰው ነው። የቡድኑን የመሪነት ሥልጣን ለመውሰድ ከመመኘት ባለፈ በጎንቻ ላይ ንቀት ነበረው። ይህንን ንቀቱን በተግባር ለማሳየት ደግሞ ዓለሚቱን አጥምዷታል። ጎንቻ ያን የመሰለ አንጀት
የሚበጥስ ንግግር ሲናገረው ቀስ ብሎ ዓለሚቱን በቆረጣ ተመለከታት፡፡ እሷም የጎንቻን ዐይኖችና የሌሎቹንም
እንቅስቃሴ ጠብቃ ማንም ሳያያት ተደብቃ "ጥቅስ" አደረገችው። ፀብ አትፍጠር ማለቷ ነው፡፡ ምን አሳስበህ? ማለቷ ነው። ተረጋጋ....
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ከሶስት ዓመታት የላምበረት ኑሮ በኋላ ዘይኑን ዳግማዊ ሚኒሊክ ትምህርት ቤት አስገባት። ከላምበረት ዳግማዊ ሚኒሊክ ትምህርት ቤት ከምትመላለስ በአቅራቢያው ቤት መከራየት ፈለገና እሪ በከንቱ አካባቢ ሰራተኛ
ስፈር ሁለት ክፍል ያላት ቤት አግኝቶ ተከራየ፡፡ ዘይኑ ለትምህርት ቤቷ ቅርብ የሆነ ቤት አገኘች። ትንሽ ደስ ያላላት ላምበረት የትውልድ መንደሯን ዓይነት ፀጥታ የሰፈነበት ሲሆን እሪ በከንቱ ግን የተጨናነቀና ሁካታ የበዛበት መሆኑ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ረጅም መንገድ ከመመላለስ ታድጓታልና ጉዳቱን በጥቅሙ አካክሳ ተቀብላዋለች፡፡ ጌትነት እህቱን በቅርበት እየተከታተለ ለጥሩ ውጤት እንድትበቃ ማድረጉ፣ በትምህርት ቤት ተጀምሮ ለሁለት አመታት የዘለቀውና ውስጥ ውስጡን ሲያሰቃየው የኖረው ፍቅር መቋጫው አምሮ ከሚወዳት ከአማረች ጋር አስደሳች
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....በዚህ ላይ ደግሞ አቶ አባይነህ ስራቸው ተጋልጦ ከሥልጣናቸው ዝቅ እንዲሉ ምክንያት በመሆኑ እያቶኮቶኩ ነገር ያቀጣጥላሉ።
እውነትህን ነው ይሄ ጦሰኛ ጦሳችንን ይዞ ካልሄደ በስተቀር ምን ሰላም እናገኛለን?!” በማለት ብሶቱን ያባብሳሉ፡፡ በዚህ ምክንያት የምረቃ በአሉ ለጌትነት ለቤተሰቦቹና ለወዳጅ ዘመዶቹ ልዩ የደስታ ቀን ሆኖ ሲውል
ለልኡልሰገድ ግን መርዶ ነው የሆነበት። ይህንን መጥፎ ስሜቱን ለማብረድ ደግሞ ሰሞኑን ሲሯሯጥ ሰንብቷል። ትጉህ ሰራተኛነቱ እንኳንስ አብረውት በሚሰሩ የስራ ባልደረቦቹ ቀርቶ በሚጠሉት ሰራተኞች ጭምር
የታወቀ ነው፡፡ ዲግሪውን ይዞ ሲመጣ ያንን እንደቀላዋጭ ውሻ ከንፈሩን እየላሰ ሲጎመዥለት የኖረውን የሂሳብ ዋና ክፍል ሃላፊ ቦታ እንደ ሚወስደው የታወቀ ነው፡፡ በሱ እምነት ያንን እድገት ለማግኘት ጌትነት ከዚያ አካባቢ ገለል ማለት አለበት።እሱ ገለል እስካላለ ድረስ ሊረጋጋ አይችልም፡፡ አንዳንዱ ሰው እድገት ለማግኘት ሲል ከፊት ለፊቱ የቆመው ሰው በሆነ ምክንያት ገለል እንዲልለት ይመኛል። ፀሎት ያደርሳል፡በዚህ የተነሳ ከፊት ለፊቱ በሚታየው የተስፋ ጭላንጭል ላይ የተንጠለጠለ የምኞት እስረኛ ሆኖ ይቀራል።ከጭላንጭሉ በስተጀርባ ዕድል ደማቅ የብርሃን ውጋጋኗን አብርታ እየጠበቀችው መሆኑን በፍጹም አያስብም፡፡ በፈጠራት ጠባብ ዓለም ውስጥ ራሱን ወስኖ በማስቀረት ለትንሹ
ነገር ሲጓጓ የሱ የነበረው ትልቁና መልካሙ ነገር በድቅድቁ ጨለማ
ውስጥ ተውጦ ይቀራል። ልኡልሰገድም ተምሮ ራሱን በመለወጥ ከዚያ የተሻለ ወፍራም እንጀራ መብላት ሲችል የተመኛትን ትንሽ ሹመት እንዳይቀማው በመስጋት የጌትነትን ሞት ተመኘ፡፡ በምረቃ ስነ ስርአቱ ላይም ሳይገኝ ቀረ። ጌትነት አለቃው በጥሪው ቦታ ሳይገኝ በመቅረቱ ቅር ቢለውም ጥሪውን አክብረው የመጡ ጓደኞቹ እቅፍ አበባ እያበረከቱ ሲስሙት ተፅናና፡፡ እናቱን እቅፍ እያደረገ ከአማረች እና ከቤተሰቦቿ ጋር እንደዚሁም ከትምህርት ቤት ጓደኞቹና ከሽመልስ ጋር በርከት ያሉ ፎቶ
ግራፎችን ተነሱ፡፡ እናቱ እጮኛነቷን ባታውቅም የልጇ ፍቅረኛ መሆን
ዋን ገምታ ከአማረች ጋር በፍቅር እየተቃቀፈች በርከት ያሉ የማስታወሻፎቶግራፎችን ስትነሳ ዋለች::
የፎቶ ግራፍ ስነ ስርአቱ እንዳበቃ ጥሪውን አክብረው በመጡ ጓደኞቹ ታጅቦ ከእናትና ከእህቱ ጋርም ተያይዘው ወደ መኖሪያ ቤቱ ሄዱ። ጌትነት እምብዛም በማይወደው ሰፈር ውስጥ የተከራያት ጎጆውን የወደዳት ገና ዛሬ ነው፡፡ ዛሬ ከጓደኞቹና ከሚወዳቸው ቤተሰቦቹ ጋር ደማቅ የደስታ ጊዜ እያሳለፈባት ነውና ሰፈሩን ዘንግቶ ጎጆውን ቢወድ የሚደንቅ አይሆንም ጌትነት የተከራያት ቤት መሀሏ በመጋረጃ ተከፍሎ ከመጋረጃው ውስጥ
አንድ ሰፊ የሞዝቮልድ አልጋና ዘይኑ የምትተኛበት አንድ ታጣፊ
አልጋ አለ፡፡ የወዲህኛው ክፍል በሳሎንነት የሚጠቀሙበት ሲሆን አንድ ትልቅ ጠረጴዛና አራት የእንጨት ወንበሮች መሀል ላይ ጉብ ብለዋል።
ከጥግ ላይ አንድ አግዳሚ ወንበር አለ፡፡ ቤቱ ከውጭ እንደሚታየው
አይደለም፡፡ በዘይኑ ከፍተኛ ጥንቃቄና ጥረት ፅዳቱ ተጠብቆ ያምራል።
ዘይኑና እናቷ ላባቸውን ጠብ አድርገው የጠመቁት ጠላ ከውስኪ ያስንቃል።
"በሉ አረፍ በሉ!" አለች የጌትነት እናት ለመስተንግዶው ተፍ ተፍ
እያለች። ጌትነት ግን ልቡ ወደ አማረች በሯል። የሱን ደሳሳ ጎጆ የምታያት ዛሬ ነበር፡፡ከወዳጅ ዘመዱ ጋር በይፋ የሚያስተዋውቃትና በቅርቡ
የሚያገባት እጮኛው መሆንኗ የሚያበስርበት ቆንጆ አጋጣሚ ዛሬ በደስታው ቀን ነበር፡፡ ግን ምን ያደርጋል? እሷም ተመራቂ ነችና በወላጆቿ ቤት ከሠርግ መልስ ግብዣ ተደርጎ ዓለም እየታየ በመሆኑ አልተቻለም፡፡
“ሰውዬው በል እንጂ ምሳችንን ቶሎ አስቀርብልን፡፡ አንተ ልብህ ወዴት እንደኮበለለ አውቄዋለሁ"ባልቻ እየሳቀ በነገር ወጋ አደረገው፡፡
"አንተ ቡዳ! ምንድነው የምታውቀው ደግሞ?" እሱም ሳቀና ጎሽመው ባልቻ የአማረችና የጌትነትን ፍቅርን ጠንቅቆ የሚያውቅ የትምህርት ቤት
ጓደኛው ነው።እሱም የሚቀጥለው ዓመት ተመራቂ ነው፡፡
“ዘይንዬ! እባክሽ ገላግይኝ ሰዎቹ ጠላው አናታቸው ላይ እየወጣ ነው መስለኝ ምሳ! ምሳ!! ቶሎ በይ!” አለና ዘይኑን ተጣራ። ዘይኑ ከእናቷ ጋር ተጋግዛ በፍጥነት ምሳ አቀረበችና መመገብ ጀመሩ።
"እንግዲህ እርስዎም እዚሁ ከልጆችዎ ጋር መጠቃለል አለብዎት እማማ በመመላለስ ይጎዳሉ..." አለ ዘበነ፡፡
“አይ የኔ ልጅ እዚህ ከልጆቼ ጋር መቀመጡን ጠልቼው መሰለህ ? ደስታውን አልችለውም ነበር፡፡ እነሱን ተለይቼ የምኖረው ኑሮ አይደለም፡፡
በሬሳ ውስጥ አስሮ ያስቀመጠኝ የሟች አባታቸው ቃል ነው "
“እንዴ?! ለምን?” ባልቻና ዘበነ በአንድ ላይ ጠየቁ፡፡
“መኩሪያ አሁን ያለሁበትን ቤት ተአባቱ የወረሰው ነው። የአባቱ አስክሬን ከወጣበት ቤት ነው የሱም የወጣው፡፡ ታዲያ ሊሞት ሲያጣጥር ከዚች ቀዬ ንቅንቅ እንዳትይ መታመሚያሽ፣ መሞቻሽ መቀበሪያሽ እዚች ጎጆ እዚች መንድር ውስጥ ይሁን አደራ! ብሎ አስሮኝ ነው ያረፈው"
በሬሳን መልቀቅ የማትችልበትን ምክንያት አጫወተቻቸው። ለነገሩ በመኩሪያ ቃል አሳበበች እንጂ ያቺን ጎጆ መልቀቅ የማትፈልግበት እንዲህ ነው ብላ ልትገልፀው የማትችለው የራሷ ምክንያት ነበራት፡፡ጌትነት ሽመልስን ለእናቱ ሲያስተዋውቃት "እማዬ ሽመልስ ማለት እሱ ነው በህይወቴም ሆነ በህይወታችን ውስጥ ታላቅ ለውጥን ያስገኘልን ወንድሜ ነው፡፡
ስለ እውነት ሲል የተሟገተ፡፡ የገባውን ቃል ያከበረ.." ቃላት አጥረውት ስለ ሽመልስ ማንነት ገለፀላት፡፡
“እሰይ! እስይ! እግዚአብሔር የሱንም ኑሮ እንደዚሁ ያሳምርለት። ለሰው ደግ መስራት ከምድር ባይገኝ እሱ ፈጣሪ ውለታውን በሰማይ ይከፍለዋል" ሽመልስን አመሰገነችለት፡፡ በዚህ ሁኔታ በተሰባስቡ ወዳጅ ዘመዶቹና ጎረቤቶቹ የጌትነት ቤት ተጣባ ደስታውን ተደስተው ፅዋቸውን
እያነሱ ሲያጋጩ ሲጫወቱ ሲጨፍሩ ዋሉ.....
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የወይዘሮ ባንቺደሩ ጎጆ የሞት ጥላ እያንዣበበባት ነው። ጨካኙ
ሞት ህፃን፣ አዋቂ፣ ሴት፣ ወንድ አይመርጥም፡፡ እንደ ቋያ እሳት ያገ
ኘውን በእጁ የወደቀለትን ሁሉ እየበላ እያኘከ መሄድ ነው። ምህረት የለም፡፡ አሮጊቷ ወይዘሮ ባንቺደሩ በአንድ በኩል የዕድሜ ጫና በሌላ በኩል ደግሞ የሙት ልጆችና እናታቸው ጥላቸው የኮበለለች ሁለት ህፃናትን ለማሳደግ መከራቸውን እያዩ ናቸው፡፡ የአያትነት ግዴታ በላያቸው ወድቆ በስተርጅና የልጃቸውን ልጆች በህይወት ለማቆየት ብዙ ደከሙ፡፡ በበሽታ ክፉኛ የተደቆሰው ምትኬ እናቱንና አባቱን ክፉኛ እየናፈቀ አባቱን በአካል ሲያጣው እየተሳቀቀ እናቱ እንደ ድሮው እንድትሆንለት እየተመኘ እናቱ ስትጨክንበት፣ ሀሳብ አደቀቀውና፣ ተሳቀቀና ለጋ
የህፃንነት አዕምሮው በሀዘን ቆስለ። ቀስ በቀስ እየመነመነ በሽተኛ እየሆነ ሄደ፡፡ አሮጊቷ በአብዛኛው የሚሰጡት ርዳታ እንባቸውን ማፍሰስ ብቻ
ነበር። "አብዬ የኔ ጌታ አይዞህ!...እኔ ልጨነቅ. እኔ ልጠበብ እህ!...”ምትኬ ግን በሳቸው እንባ ሊጠነክርና ሊለመልም አልቻለም፡፡
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....በዚህ ላይ ደግሞ አቶ አባይነህ ስራቸው ተጋልጦ ከሥልጣናቸው ዝቅ እንዲሉ ምክንያት በመሆኑ እያቶኮቶኩ ነገር ያቀጣጥላሉ።
እውነትህን ነው ይሄ ጦሰኛ ጦሳችንን ይዞ ካልሄደ በስተቀር ምን ሰላም እናገኛለን?!” በማለት ብሶቱን ያባብሳሉ፡፡ በዚህ ምክንያት የምረቃ በአሉ ለጌትነት ለቤተሰቦቹና ለወዳጅ ዘመዶቹ ልዩ የደስታ ቀን ሆኖ ሲውል
ለልኡልሰገድ ግን መርዶ ነው የሆነበት። ይህንን መጥፎ ስሜቱን ለማብረድ ደግሞ ሰሞኑን ሲሯሯጥ ሰንብቷል። ትጉህ ሰራተኛነቱ እንኳንስ አብረውት በሚሰሩ የስራ ባልደረቦቹ ቀርቶ በሚጠሉት ሰራተኞች ጭምር
የታወቀ ነው፡፡ ዲግሪውን ይዞ ሲመጣ ያንን እንደቀላዋጭ ውሻ ከንፈሩን እየላሰ ሲጎመዥለት የኖረውን የሂሳብ ዋና ክፍል ሃላፊ ቦታ እንደ ሚወስደው የታወቀ ነው፡፡ በሱ እምነት ያንን እድገት ለማግኘት ጌትነት ከዚያ አካባቢ ገለል ማለት አለበት።እሱ ገለል እስካላለ ድረስ ሊረጋጋ አይችልም፡፡ አንዳንዱ ሰው እድገት ለማግኘት ሲል ከፊት ለፊቱ የቆመው ሰው በሆነ ምክንያት ገለል እንዲልለት ይመኛል። ፀሎት ያደርሳል፡በዚህ የተነሳ ከፊት ለፊቱ በሚታየው የተስፋ ጭላንጭል ላይ የተንጠለጠለ የምኞት እስረኛ ሆኖ ይቀራል።ከጭላንጭሉ በስተጀርባ ዕድል ደማቅ የብርሃን ውጋጋኗን አብርታ እየጠበቀችው መሆኑን በፍጹም አያስብም፡፡ በፈጠራት ጠባብ ዓለም ውስጥ ራሱን ወስኖ በማስቀረት ለትንሹ
ነገር ሲጓጓ የሱ የነበረው ትልቁና መልካሙ ነገር በድቅድቁ ጨለማ
ውስጥ ተውጦ ይቀራል። ልኡልሰገድም ተምሮ ራሱን በመለወጥ ከዚያ የተሻለ ወፍራም እንጀራ መብላት ሲችል የተመኛትን ትንሽ ሹመት እንዳይቀማው በመስጋት የጌትነትን ሞት ተመኘ፡፡ በምረቃ ስነ ስርአቱ ላይም ሳይገኝ ቀረ። ጌትነት አለቃው በጥሪው ቦታ ሳይገኝ በመቅረቱ ቅር ቢለውም ጥሪውን አክብረው የመጡ ጓደኞቹ እቅፍ አበባ እያበረከቱ ሲስሙት ተፅናና፡፡ እናቱን እቅፍ እያደረገ ከአማረች እና ከቤተሰቦቿ ጋር እንደዚሁም ከትምህርት ቤት ጓደኞቹና ከሽመልስ ጋር በርከት ያሉ ፎቶ
ግራፎችን ተነሱ፡፡ እናቱ እጮኛነቷን ባታውቅም የልጇ ፍቅረኛ መሆን
ዋን ገምታ ከአማረች ጋር በፍቅር እየተቃቀፈች በርከት ያሉ የማስታወሻፎቶግራፎችን ስትነሳ ዋለች::
የፎቶ ግራፍ ስነ ስርአቱ እንዳበቃ ጥሪውን አክብረው በመጡ ጓደኞቹ ታጅቦ ከእናትና ከእህቱ ጋርም ተያይዘው ወደ መኖሪያ ቤቱ ሄዱ። ጌትነት እምብዛም በማይወደው ሰፈር ውስጥ የተከራያት ጎጆውን የወደዳት ገና ዛሬ ነው፡፡ ዛሬ ከጓደኞቹና ከሚወዳቸው ቤተሰቦቹ ጋር ደማቅ የደስታ ጊዜ እያሳለፈባት ነውና ሰፈሩን ዘንግቶ ጎጆውን ቢወድ የሚደንቅ አይሆንም ጌትነት የተከራያት ቤት መሀሏ በመጋረጃ ተከፍሎ ከመጋረጃው ውስጥ
አንድ ሰፊ የሞዝቮልድ አልጋና ዘይኑ የምትተኛበት አንድ ታጣፊ
አልጋ አለ፡፡ የወዲህኛው ክፍል በሳሎንነት የሚጠቀሙበት ሲሆን አንድ ትልቅ ጠረጴዛና አራት የእንጨት ወንበሮች መሀል ላይ ጉብ ብለዋል።
ከጥግ ላይ አንድ አግዳሚ ወንበር አለ፡፡ ቤቱ ከውጭ እንደሚታየው
አይደለም፡፡ በዘይኑ ከፍተኛ ጥንቃቄና ጥረት ፅዳቱ ተጠብቆ ያምራል።
ዘይኑና እናቷ ላባቸውን ጠብ አድርገው የጠመቁት ጠላ ከውስኪ ያስንቃል።
"በሉ አረፍ በሉ!" አለች የጌትነት እናት ለመስተንግዶው ተፍ ተፍ
እያለች። ጌትነት ግን ልቡ ወደ አማረች በሯል። የሱን ደሳሳ ጎጆ የምታያት ዛሬ ነበር፡፡ከወዳጅ ዘመዱ ጋር በይፋ የሚያስተዋውቃትና በቅርቡ
የሚያገባት እጮኛው መሆንኗ የሚያበስርበት ቆንጆ አጋጣሚ ዛሬ በደስታው ቀን ነበር፡፡ ግን ምን ያደርጋል? እሷም ተመራቂ ነችና በወላጆቿ ቤት ከሠርግ መልስ ግብዣ ተደርጎ ዓለም እየታየ በመሆኑ አልተቻለም፡፡
“ሰውዬው በል እንጂ ምሳችንን ቶሎ አስቀርብልን፡፡ አንተ ልብህ ወዴት እንደኮበለለ አውቄዋለሁ"ባልቻ እየሳቀ በነገር ወጋ አደረገው፡፡
"አንተ ቡዳ! ምንድነው የምታውቀው ደግሞ?" እሱም ሳቀና ጎሽመው ባልቻ የአማረችና የጌትነትን ፍቅርን ጠንቅቆ የሚያውቅ የትምህርት ቤት
ጓደኛው ነው።እሱም የሚቀጥለው ዓመት ተመራቂ ነው፡፡
“ዘይንዬ! እባክሽ ገላግይኝ ሰዎቹ ጠላው አናታቸው ላይ እየወጣ ነው መስለኝ ምሳ! ምሳ!! ቶሎ በይ!” አለና ዘይኑን ተጣራ። ዘይኑ ከእናቷ ጋር ተጋግዛ በፍጥነት ምሳ አቀረበችና መመገብ ጀመሩ።
"እንግዲህ እርስዎም እዚሁ ከልጆችዎ ጋር መጠቃለል አለብዎት እማማ በመመላለስ ይጎዳሉ..." አለ ዘበነ፡፡
“አይ የኔ ልጅ እዚህ ከልጆቼ ጋር መቀመጡን ጠልቼው መሰለህ ? ደስታውን አልችለውም ነበር፡፡ እነሱን ተለይቼ የምኖረው ኑሮ አይደለም፡፡
በሬሳ ውስጥ አስሮ ያስቀመጠኝ የሟች አባታቸው ቃል ነው "
“እንዴ?! ለምን?” ባልቻና ዘበነ በአንድ ላይ ጠየቁ፡፡
“መኩሪያ አሁን ያለሁበትን ቤት ተአባቱ የወረሰው ነው። የአባቱ አስክሬን ከወጣበት ቤት ነው የሱም የወጣው፡፡ ታዲያ ሊሞት ሲያጣጥር ከዚች ቀዬ ንቅንቅ እንዳትይ መታመሚያሽ፣ መሞቻሽ መቀበሪያሽ እዚች ጎጆ እዚች መንድር ውስጥ ይሁን አደራ! ብሎ አስሮኝ ነው ያረፈው"
በሬሳን መልቀቅ የማትችልበትን ምክንያት አጫወተቻቸው። ለነገሩ በመኩሪያ ቃል አሳበበች እንጂ ያቺን ጎጆ መልቀቅ የማትፈልግበት እንዲህ ነው ብላ ልትገልፀው የማትችለው የራሷ ምክንያት ነበራት፡፡ጌትነት ሽመልስን ለእናቱ ሲያስተዋውቃት "እማዬ ሽመልስ ማለት እሱ ነው በህይወቴም ሆነ በህይወታችን ውስጥ ታላቅ ለውጥን ያስገኘልን ወንድሜ ነው፡፡
ስለ እውነት ሲል የተሟገተ፡፡ የገባውን ቃል ያከበረ.." ቃላት አጥረውት ስለ ሽመልስ ማንነት ገለፀላት፡፡
“እሰይ! እስይ! እግዚአብሔር የሱንም ኑሮ እንደዚሁ ያሳምርለት። ለሰው ደግ መስራት ከምድር ባይገኝ እሱ ፈጣሪ ውለታውን በሰማይ ይከፍለዋል" ሽመልስን አመሰገነችለት፡፡ በዚህ ሁኔታ በተሰባስቡ ወዳጅ ዘመዶቹና ጎረቤቶቹ የጌትነት ቤት ተጣባ ደስታውን ተደስተው ፅዋቸውን
እያነሱ ሲያጋጩ ሲጫወቱ ሲጨፍሩ ዋሉ.....
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የወይዘሮ ባንቺደሩ ጎጆ የሞት ጥላ እያንዣበበባት ነው። ጨካኙ
ሞት ህፃን፣ አዋቂ፣ ሴት፣ ወንድ አይመርጥም፡፡ እንደ ቋያ እሳት ያገ
ኘውን በእጁ የወደቀለትን ሁሉ እየበላ እያኘከ መሄድ ነው። ምህረት የለም፡፡ አሮጊቷ ወይዘሮ ባንቺደሩ በአንድ በኩል የዕድሜ ጫና በሌላ በኩል ደግሞ የሙት ልጆችና እናታቸው ጥላቸው የኮበለለች ሁለት ህፃናትን ለማሳደግ መከራቸውን እያዩ ናቸው፡፡ የአያትነት ግዴታ በላያቸው ወድቆ በስተርጅና የልጃቸውን ልጆች በህይወት ለማቆየት ብዙ ደከሙ፡፡ በበሽታ ክፉኛ የተደቆሰው ምትኬ እናቱንና አባቱን ክፉኛ እየናፈቀ አባቱን በአካል ሲያጣው እየተሳቀቀ እናቱ እንደ ድሮው እንድትሆንለት እየተመኘ እናቱ ስትጨክንበት፣ ሀሳብ አደቀቀውና፣ ተሳቀቀና ለጋ
የህፃንነት አዕምሮው በሀዘን ቆስለ። ቀስ በቀስ እየመነመነ በሽተኛ እየሆነ ሄደ፡፡ አሮጊቷ በአብዛኛው የሚሰጡት ርዳታ እንባቸውን ማፍሰስ ብቻ
ነበር። "አብዬ የኔ ጌታ አይዞህ!...እኔ ልጨነቅ. እኔ ልጠበብ እህ!...”ምትኬ ግን በሳቸው እንባ ሊጠነክርና ሊለመልም አልቻለም፡፡
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሦስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...ዛሬም በሱ የቡድን መሪነት ውስጥ በአባልነት በታቀፈው በሸጋው አንበሴ ቁመናና የዐይኖቹ ውበት ተማርካ በመልከ
መልካምነቱ ልቧ ተሸንፎ በፍቅሩ ነዳለት ጎንቻን ደብቃ ፍቅሯን እያስኮመኮመችው አለማቸውን እየቀጩ ነው።
ይሄንን ያላወቀው ጎንቻ ደግሞ ስሞኑን በብዙ አፈላላጊ ከተገናኘው ሰው ላይ ቀብድ ለመቀበል ተፈልጎ ሄዷል መቀስ ያንን ሹልክ እያለ እየመጣ
የሚቀምሰውን ፍቅር ለመቅመስ በዚያውም ተጨማሪ ገንዘብ ለመበደር ነበር የጎንቻን እግር ጠብቆ የገባው፡፡ እንደተገናኙ ተቃቀፉና አልጋው ላይ ወደቁ፡፡ ያንን የስርቆሽ ፍትወት ከፈፀሙ በኋላ በጀርባቸው ተንጋለሉ። ዓለሚቱ ልቧ ድው ድው ማለት ጀመረ።ስርቆሹን ትወደዋለች፡፡
ይጣፍጣታል።የሚያስከትለውን መዘዝ ስታሰላስለው ግን ትሰጋለች። ትርበተበታለች። በዚያ የስሜት እሳት ውስጥ ገብታ ፍሙን፣ ረመጡን እስከምታጣጥመው ድረስ ምንም አይነት የፍርሃት ስሜት አያድርባትም፡፡አደጋው አይታወሳትም፡፡ ሁሉ ነገር ጎልቶ የሚታያት ከዚያ በኋላ ነው፡፡ አሁንም የፍትወት ስሜቷን ካረካች በኋላ ስጋቷ በረታና መተንፈስ ግድ ሆነባት።
"አይታወቅም የሱ ነገር ወይ በመሀል ከተፍ ይላል። ቶሎ ቶሎ ተጨዋውተን በጊዜ ብትሄድ አይሻልም?" አለችው፡፡
"ልክ ነሽ፡፡ እውነትሽን ነው። እኔም ሳስበው ነበር። እሱ እኮ ስላቢ ነው፡፡ በድንገት ከች! ሊል ይችላል ፡ጉሮሮ ለጉሮሮ ሳንያያዝና በእጄ ሰበብ ሳይሆንብኝ ብሄድ ይሻላል” አለና ከአልጋው ላይ ተነስቶ ሱሪውን ማጥለቅ ጀመረ፡፡ እሷም ተነሳች፡፡ዓለምዬ ዛሬ ችስታ ወግሮኛል ሁለት መቶ ብር ትጨምሪልኛለሽ፡፡ አንድ
ላይ ወደ አንድ ሺህ መጠጋቱ ነው" አላት፡፡“ትቀልዳለህ እንዴ አንበሴ?! እንዲያውም ስሞኑን የሌለበትን የገንዘብ
መቆጣጠር ፀባይ እያሳየ ነው፡፡ አሁን በድንገት ውለጂ ቢለኝ ምን እመልስለታለሁ? ዛሬ ሁሉንም ይዘህ ትመጣለህ ብዬ ነበር የገመትኩት። አንተ ግን ጭራሽ በላይ በላዩ ልትጨምር ትፈልጋለህ፡ የበላችው ያስገሳታል በላይ በላዩ ያጎርሳታልሆነ አሁንስ!" በስጨት ብላ ተናገረችው።
አንበሴ ያልጠበቀው ነበር፡፡ በሱ ቤት ተደብቆ እየመጣ የሚያቀምሳት ፍቅር ጣፍጧት ስለሚጠይቃት ገንዘብ ደንታ የሌላት መስሎት ነበር።
ተወድጃለሁ የፈለኩትን እንድታደርግልኝ ባዝዛት ትፈፅማለች ባይ ነበር፡፡
ለእንቢታው አንደበቷ የሚፈታ የተጠየቀችውን ገንዘብ ላጥ አድርጎ ለመስጠት እጅዋ የሚያጥር አልመሰለውም ነበር፡፡ በዓለሚቱና በገንዘብ መካከል ግን ቀልድ አልነበረም።
ሲቀር ፍቅሩ ተሽቀንጥሮ ይቀራል እንጂ ብሯን የምትበትን ሆና አልተገኘችም። እንደዚያም ሆኖ ግን ለሱ እጇ ብዙም አይጨክንም ነበር። ከዚያ በፊት ያለውን በደስታ ነው የሰጠችው
ዛሬ በዛባትና ፊት ነሳችው እንጂ፡፡ ባሏ ጎንቻ የቡድኑ ገንዘብ አዛዥ ሆኖ የበለጠውን ድርሻ መውሰዱ ውስጥ ውስጡን በቅናት ቢያቃጥለውም ቁልፉን በእጁ ይዟል። የገንዘቡን ካዝና የዓለሚቱን ልብ ተቆጣጥሯልና
በተዘዋዋሪ መንገድ እየተካስ ይፅናናል።ይሄ በመሆኑ እንጂ እንደ ጎንቻ አያያዝ ቢሆን ኖሮ ገና ድሮ ድብልቅልቅ ብለው በተጣሉ ነበር፡፡ ዓለሚቱ ቀስ ትልና ብሩንም ፍቅሩንም እየሰረቀች ትሰጠዋለች። ይቀዘቅዛል፡፡
"ተይ እንጂ ዓለሚቱ! ምን ማለትሽ ነው? ገንዘቡን ለጥብቅ ጉዳይ ስለምፈልገው ነው እኮ!ደግሞ ብዙ ችግር እንደሌለብኝ ታውቂያለሽ፡፡ በሙሉ እምነት ነው ወዳንቺ የመጣሁት። ዓለሚቱ ካንቺ ሌላ ማንንም ብድር
መጠየቅ አልፈልግም!"
“አንበሴ ሙት አትቀልድ! ይልቁንስ የወሰድከውን ቶሎ መልስ እንዳን
ጣላ!"
ትቀልጃለሽ እንዴ ዓለሚቱ?"
አልቀለድኩም አንተ ነህ የምትቀልደው!"
“ኧረ በናትሽ ዓለሚቱ?!"
“አይገባህም እንዴ?!" ቁጣዋ ባሰ...የበለጠ ተደናገጠ፡፡ ፕሮግራሙ ሊከሽፍ ነው፡፡ የበርጫውና የጨብሲው... ከአዲሷ የሴት ጓደኛው ጋር የያዘው ቀጠሮ ዜሮ…ደግሞም ባለሥልጣን ነኝ ብሉ የዋሻት፣ ልቡ የወደዳት ቆንጆ ልጅ....
“በቃ እንጣላ?!"
«አንበሴ ሙት በዚህስ እንጣላ! በዚህስ የፈለከውን አምጣ እንጂ አላደርገውም! ትንሽ አታስብም እንዴ?! ያምነኛል እንጂ ገንዘቡን ያውቀዋል እኮ! ምን ልለው ነው በተለይ እንደዚህ መንገብገቡ ከሴት ጋር ቀጠሮ ቢኖረው ነው ብላ ስለገመተች ጨከነችበት።
“በዚህ ላይ አንተ ጋ ያለው ብቻ አይደለም፡፡ በአራጣ ያበደርኳቸው
ብዙዎቹ መክፈል እያቃታቸው አሮጌ ዕቃ እያግበሰበሱልኝ ነው። አሮጌ እቃ ለኔ ምን ያደርግልኛል? የረቡ ዕቃዎች ያየሃቸው ሀብሎችና ቀለበቶች ብቻ ናቸው። ሌላው ዝባዝንኬ ቅራቅንቦ ነው!”
"ገባኝ!... እኔን እኮ እንደሌላው አራጣ ተበዳሪ ማየት የለብሽም። ማወቅ ያለብሽ ነገር ገንዘቡን በጋራ የሰራነው መሆኑን ጭምር ነው! የንዴት ትኩሳት ማተኮስ ጀመረውና ሳያስበው ተስፋ በመቁረጥ ውስጥ የወጣ
ንግግር ተናገራት፡፡
"ኧረ? በጋራ?! በል ተወው! የራስህን ድርሻማ እየላፍከው ሄደሃል። ከዚህ ውስጥ ሰባራ ሳንቲም የባለቤትነት መብት የለህም! በጠየከኝ ቁጥር እያ
ወጣሁ ያስታቀፍኩህ እኮ የተግባባን መስሎኝ ነበር! ለካስ የራስህ ገንዘብ አድርገህ ነዋ እስካሁን ያልመለስከው?! አንበሴ ሙት እንደዚህ አይነት የማይረባ አስተሳሰብ ያለህ ሰው አትመስለኝም ነበር፡፡ ወይ የሰው ነገር? ለካ ሰው እያደር ነው የሚታወቀው?! እና የወሰድከውን ለመመለስ ሀሳብ የለህም ማለት ነው?! እንዴት ያለኸው ቀላል ነህ ባክህ?! ይህንን ያዳፈረህ ጎንቻን ደብቄ ቀሚሴን ስለገለብኩልህ ይሆን እንዴ ? እሱ ይሆናል
እንጂ ያናናቀን! ለምነህ የወሰድከውን ከምስጋና ጋር መመለስ ሲገባህ ጭራሽ..." ፊቷ በንዴት ቀላ፡፡
“እና አሁን አትሰጭኝም?!"
“እስቲ ድብን ያደርግህ እንደሆነም ጉድ አያለሁ! ሰባራ ሳንቲም! " አንበሴ የዓለሚቱን ንዴት ሲመለከት አጉል እልህ ምንም ዋጋ እንደሌለው ተረዳ፡፡ ከብዙ ጉልበት ትንሽ ብልሃት የምትበልጥበትን ጊዜ አሰበ፡፡ በዘዴ አባብሎ ብዙ ነገር ማድረግ ሲችል ብጥብጥ ፈጥሮ ቢሄድ ራሱን ይጎዳል እንጂ እሷን አይጎዳትም ይሄን ማመዛዘን ጀመረ፡፡ ቀስ በቀስ ረገበና ልምምጡን ቀጠለ፡፡ ከውስጡ ንዴትና ብሽቀት ቢያቃጥሉትም ከውጭ ሌላ ሆነ፡፡ ፈገግ አለ፡፡
“እሺ ዓለምዬ እንዳልሽው ይሁን። ማወቅ ያለብሽ ግን እኔን ልቤን የነሳሽው ጣፋጭ ፍቅርሽ እንጂ ገንዘብሽ ያለመሆኑን ነው። ገንዘብ ገደል ይግባ! ፍላጎቴ ፍቅር ሳይሆን ገንዘብ ቢሆን ኖሮ በሴት ብር ብቻ ፎቅ ቤት መስራት እችል ነበር፡፡ ያንን ግን አልፈልገውም፡፡ እዚህ የባልሽን ኮቴ እየጠበኩ ስር ስርሽ የሚያስሮጠኝ ፍቅርሽ ብቻ ነው። አሁንም ቢሆን እኔ የምፈልገው ገንዘብሽን ሳይሆን ፍቅርሽን ነውና አለብህ የም
ትይኝን በሙሉ አምጥቼ እወረውርልሻለሁ። አንቺነትሽን እንደዚህ የለወጣው ገንዘብ ከሆነ ካንቺ የሚተርፍ ገንዘብ አስታቅፍሻለሁ። እውነቴን
ነው የምልሽ ሩቅ ቦታ ስላስቀመጥኩት እንጂ እንኳን ለራሴ ለሌላ የምትርፍ ስው ነኝ ጉራውን ቸረቸረላት።
ዓለሚቱ ልቧ ወከክ... አለ፡፡ እውነትም አንበሴ ገንዘብ በገንዘብ ሲያደርጋት ታያት። በአምስቱ ጣቶቹ ላይ የደረደራቸው የወርቅ ቀለበቶቹ በየቀኑ የሚቀያይራቸው ፋሽን ልብሶቹ ሁሉ ነገሩ የገንዘብ ችግር የሌለበት መሆኑን ይመሰክራሉ። ገንዘብ ስጠኝ ብላ ባለመጠየቋ እንጂ ብትጠይቀው ሊያንበሸብሻት እንደሚችል ተስፋ አደረገች፡፡ በአንድ ጊዜ' በደስታ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሦስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...ዛሬም በሱ የቡድን መሪነት ውስጥ በአባልነት በታቀፈው በሸጋው አንበሴ ቁመናና የዐይኖቹ ውበት ተማርካ በመልከ
መልካምነቱ ልቧ ተሸንፎ በፍቅሩ ነዳለት ጎንቻን ደብቃ ፍቅሯን እያስኮመኮመችው አለማቸውን እየቀጩ ነው።
ይሄንን ያላወቀው ጎንቻ ደግሞ ስሞኑን በብዙ አፈላላጊ ከተገናኘው ሰው ላይ ቀብድ ለመቀበል ተፈልጎ ሄዷል መቀስ ያንን ሹልክ እያለ እየመጣ
የሚቀምሰውን ፍቅር ለመቅመስ በዚያውም ተጨማሪ ገንዘብ ለመበደር ነበር የጎንቻን እግር ጠብቆ የገባው፡፡ እንደተገናኙ ተቃቀፉና አልጋው ላይ ወደቁ፡፡ ያንን የስርቆሽ ፍትወት ከፈፀሙ በኋላ በጀርባቸው ተንጋለሉ። ዓለሚቱ ልቧ ድው ድው ማለት ጀመረ።ስርቆሹን ትወደዋለች፡፡
ይጣፍጣታል።የሚያስከትለውን መዘዝ ስታሰላስለው ግን ትሰጋለች። ትርበተበታለች። በዚያ የስሜት እሳት ውስጥ ገብታ ፍሙን፣ ረመጡን እስከምታጣጥመው ድረስ ምንም አይነት የፍርሃት ስሜት አያድርባትም፡፡አደጋው አይታወሳትም፡፡ ሁሉ ነገር ጎልቶ የሚታያት ከዚያ በኋላ ነው፡፡ አሁንም የፍትወት ስሜቷን ካረካች በኋላ ስጋቷ በረታና መተንፈስ ግድ ሆነባት።
"አይታወቅም የሱ ነገር ወይ በመሀል ከተፍ ይላል። ቶሎ ቶሎ ተጨዋውተን በጊዜ ብትሄድ አይሻልም?" አለችው፡፡
"ልክ ነሽ፡፡ እውነትሽን ነው። እኔም ሳስበው ነበር። እሱ እኮ ስላቢ ነው፡፡ በድንገት ከች! ሊል ይችላል ፡ጉሮሮ ለጉሮሮ ሳንያያዝና በእጄ ሰበብ ሳይሆንብኝ ብሄድ ይሻላል” አለና ከአልጋው ላይ ተነስቶ ሱሪውን ማጥለቅ ጀመረ፡፡ እሷም ተነሳች፡፡ዓለምዬ ዛሬ ችስታ ወግሮኛል ሁለት መቶ ብር ትጨምሪልኛለሽ፡፡ አንድ
ላይ ወደ አንድ ሺህ መጠጋቱ ነው" አላት፡፡“ትቀልዳለህ እንዴ አንበሴ?! እንዲያውም ስሞኑን የሌለበትን የገንዘብ
መቆጣጠር ፀባይ እያሳየ ነው፡፡ አሁን በድንገት ውለጂ ቢለኝ ምን እመልስለታለሁ? ዛሬ ሁሉንም ይዘህ ትመጣለህ ብዬ ነበር የገመትኩት። አንተ ግን ጭራሽ በላይ በላዩ ልትጨምር ትፈልጋለህ፡ የበላችው ያስገሳታል በላይ በላዩ ያጎርሳታልሆነ አሁንስ!" በስጨት ብላ ተናገረችው።
አንበሴ ያልጠበቀው ነበር፡፡ በሱ ቤት ተደብቆ እየመጣ የሚያቀምሳት ፍቅር ጣፍጧት ስለሚጠይቃት ገንዘብ ደንታ የሌላት መስሎት ነበር።
ተወድጃለሁ የፈለኩትን እንድታደርግልኝ ባዝዛት ትፈፅማለች ባይ ነበር፡፡
ለእንቢታው አንደበቷ የሚፈታ የተጠየቀችውን ገንዘብ ላጥ አድርጎ ለመስጠት እጅዋ የሚያጥር አልመሰለውም ነበር፡፡ በዓለሚቱና በገንዘብ መካከል ግን ቀልድ አልነበረም።
ሲቀር ፍቅሩ ተሽቀንጥሮ ይቀራል እንጂ ብሯን የምትበትን ሆና አልተገኘችም። እንደዚያም ሆኖ ግን ለሱ እጇ ብዙም አይጨክንም ነበር። ከዚያ በፊት ያለውን በደስታ ነው የሰጠችው
ዛሬ በዛባትና ፊት ነሳችው እንጂ፡፡ ባሏ ጎንቻ የቡድኑ ገንዘብ አዛዥ ሆኖ የበለጠውን ድርሻ መውሰዱ ውስጥ ውስጡን በቅናት ቢያቃጥለውም ቁልፉን በእጁ ይዟል። የገንዘቡን ካዝና የዓለሚቱን ልብ ተቆጣጥሯልና
በተዘዋዋሪ መንገድ እየተካስ ይፅናናል።ይሄ በመሆኑ እንጂ እንደ ጎንቻ አያያዝ ቢሆን ኖሮ ገና ድሮ ድብልቅልቅ ብለው በተጣሉ ነበር፡፡ ዓለሚቱ ቀስ ትልና ብሩንም ፍቅሩንም እየሰረቀች ትሰጠዋለች። ይቀዘቅዛል፡፡
"ተይ እንጂ ዓለሚቱ! ምን ማለትሽ ነው? ገንዘቡን ለጥብቅ ጉዳይ ስለምፈልገው ነው እኮ!ደግሞ ብዙ ችግር እንደሌለብኝ ታውቂያለሽ፡፡ በሙሉ እምነት ነው ወዳንቺ የመጣሁት። ዓለሚቱ ካንቺ ሌላ ማንንም ብድር
መጠየቅ አልፈልግም!"
“አንበሴ ሙት አትቀልድ! ይልቁንስ የወሰድከውን ቶሎ መልስ እንዳን
ጣላ!"
ትቀልጃለሽ እንዴ ዓለሚቱ?"
አልቀለድኩም አንተ ነህ የምትቀልደው!"
“ኧረ በናትሽ ዓለሚቱ?!"
“አይገባህም እንዴ?!" ቁጣዋ ባሰ...የበለጠ ተደናገጠ፡፡ ፕሮግራሙ ሊከሽፍ ነው፡፡ የበርጫውና የጨብሲው... ከአዲሷ የሴት ጓደኛው ጋር የያዘው ቀጠሮ ዜሮ…ደግሞም ባለሥልጣን ነኝ ብሉ የዋሻት፣ ልቡ የወደዳት ቆንጆ ልጅ....
“በቃ እንጣላ?!"
«አንበሴ ሙት በዚህስ እንጣላ! በዚህስ የፈለከውን አምጣ እንጂ አላደርገውም! ትንሽ አታስብም እንዴ?! ያምነኛል እንጂ ገንዘቡን ያውቀዋል እኮ! ምን ልለው ነው በተለይ እንደዚህ መንገብገቡ ከሴት ጋር ቀጠሮ ቢኖረው ነው ብላ ስለገመተች ጨከነችበት።
“በዚህ ላይ አንተ ጋ ያለው ብቻ አይደለም፡፡ በአራጣ ያበደርኳቸው
ብዙዎቹ መክፈል እያቃታቸው አሮጌ ዕቃ እያግበሰበሱልኝ ነው። አሮጌ እቃ ለኔ ምን ያደርግልኛል? የረቡ ዕቃዎች ያየሃቸው ሀብሎችና ቀለበቶች ብቻ ናቸው። ሌላው ዝባዝንኬ ቅራቅንቦ ነው!”
"ገባኝ!... እኔን እኮ እንደሌላው አራጣ ተበዳሪ ማየት የለብሽም። ማወቅ ያለብሽ ነገር ገንዘቡን በጋራ የሰራነው መሆኑን ጭምር ነው! የንዴት ትኩሳት ማተኮስ ጀመረውና ሳያስበው ተስፋ በመቁረጥ ውስጥ የወጣ
ንግግር ተናገራት፡፡
"ኧረ? በጋራ?! በል ተወው! የራስህን ድርሻማ እየላፍከው ሄደሃል። ከዚህ ውስጥ ሰባራ ሳንቲም የባለቤትነት መብት የለህም! በጠየከኝ ቁጥር እያ
ወጣሁ ያስታቀፍኩህ እኮ የተግባባን መስሎኝ ነበር! ለካስ የራስህ ገንዘብ አድርገህ ነዋ እስካሁን ያልመለስከው?! አንበሴ ሙት እንደዚህ አይነት የማይረባ አስተሳሰብ ያለህ ሰው አትመስለኝም ነበር፡፡ ወይ የሰው ነገር? ለካ ሰው እያደር ነው የሚታወቀው?! እና የወሰድከውን ለመመለስ ሀሳብ የለህም ማለት ነው?! እንዴት ያለኸው ቀላል ነህ ባክህ?! ይህንን ያዳፈረህ ጎንቻን ደብቄ ቀሚሴን ስለገለብኩልህ ይሆን እንዴ ? እሱ ይሆናል
እንጂ ያናናቀን! ለምነህ የወሰድከውን ከምስጋና ጋር መመለስ ሲገባህ ጭራሽ..." ፊቷ በንዴት ቀላ፡፡
“እና አሁን አትሰጭኝም?!"
“እስቲ ድብን ያደርግህ እንደሆነም ጉድ አያለሁ! ሰባራ ሳንቲም! " አንበሴ የዓለሚቱን ንዴት ሲመለከት አጉል እልህ ምንም ዋጋ እንደሌለው ተረዳ፡፡ ከብዙ ጉልበት ትንሽ ብልሃት የምትበልጥበትን ጊዜ አሰበ፡፡ በዘዴ አባብሎ ብዙ ነገር ማድረግ ሲችል ብጥብጥ ፈጥሮ ቢሄድ ራሱን ይጎዳል እንጂ እሷን አይጎዳትም ይሄን ማመዛዘን ጀመረ፡፡ ቀስ በቀስ ረገበና ልምምጡን ቀጠለ፡፡ ከውስጡ ንዴትና ብሽቀት ቢያቃጥሉትም ከውጭ ሌላ ሆነ፡፡ ፈገግ አለ፡፡
“እሺ ዓለምዬ እንዳልሽው ይሁን። ማወቅ ያለብሽ ግን እኔን ልቤን የነሳሽው ጣፋጭ ፍቅርሽ እንጂ ገንዘብሽ ያለመሆኑን ነው። ገንዘብ ገደል ይግባ! ፍላጎቴ ፍቅር ሳይሆን ገንዘብ ቢሆን ኖሮ በሴት ብር ብቻ ፎቅ ቤት መስራት እችል ነበር፡፡ ያንን ግን አልፈልገውም፡፡ እዚህ የባልሽን ኮቴ እየጠበኩ ስር ስርሽ የሚያስሮጠኝ ፍቅርሽ ብቻ ነው። አሁንም ቢሆን እኔ የምፈልገው ገንዘብሽን ሳይሆን ፍቅርሽን ነውና አለብህ የም
ትይኝን በሙሉ አምጥቼ እወረውርልሻለሁ። አንቺነትሽን እንደዚህ የለወጣው ገንዘብ ከሆነ ካንቺ የሚተርፍ ገንዘብ አስታቅፍሻለሁ። እውነቴን
ነው የምልሽ ሩቅ ቦታ ስላስቀመጥኩት እንጂ እንኳን ለራሴ ለሌላ የምትርፍ ስው ነኝ ጉራውን ቸረቸረላት።
ዓለሚቱ ልቧ ወከክ... አለ፡፡ እውነትም አንበሴ ገንዘብ በገንዘብ ሲያደርጋት ታያት። በአምስቱ ጣቶቹ ላይ የደረደራቸው የወርቅ ቀለበቶቹ በየቀኑ የሚቀያይራቸው ፋሽን ልብሶቹ ሁሉ ነገሩ የገንዘብ ችግር የሌለበት መሆኑን ይመሰክራሉ። ገንዘብ ስጠኝ ብላ ባለመጠየቋ እንጂ ብትጠይቀው ሊያንበሸብሻት እንደሚችል ተስፋ አደረገች፡፡ በአንድ ጊዜ' በደስታ
👍2😱1
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...ጭንቀት በጭንቀት ሆነች። ብቅ ጥልቅ ወጣ ገባ.አበዛች። ለመጀመሪያ ጊዜ ማምሸቱ ያሳሰባት ዘይኑ የምትሆነውን አጣች። ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ተኩል ጀምሮ ነበር መጠባበቅ የጀመረችው። እንደበፊቱ ትምህርት ቤት እንዳትል ትምህርቱን ጨርሷል። ምን ነክቶት ይሆን? ተርበተበተች፡፡ ስዓቱ እየገፋ እየሄደ ነው። ስጋት ከጀመረችበት ጊዜ ጀምሮ ጌትነት
አደጋ ላይ እስከወደቀበት እስከ ምሽቱ አራት ሰዓት ተኩል ድረስ...
ከዚያም ሙሉውን ለሊት ስታምጥ አነጋች፡፡ ወንድም ጋሻዋ..ድምጡ
ጠፋ፡፡ የውሃ ሽታ ሆነ፡፡ ለሊቱን ተቅማጥ ሲያጣድፋት አደረ። ጎረቤታቸው ወይዘሮ ጤናዳም ደግሞ ሲያፅናኗት አነጉ።
"ምንም አይደለም ወንድ ልጅ አንዳንድ ጊዜ አመሉ ነው። አይዞሽ ጠዋት ይመጣልሻል"እያሉ ሞራል ሲሰጧት አደሩ። መንጋት አይበለው እንደ ምንም ነጋላት። ወንድም ጋሻዋን የበላችባት ወፍ ግን ድምጿን አላሰማ አለች፡፡ እዬዬ... ኡኡታ... ዋይታ…ቁጭ ብድግ.. በዚያች እሷ በጭንቀት በምትሸበርባት ማለዳ አንድ ሰው ወደ ስራ በማምራት ላይ እያለ እሪ በከንቱ ዳገቱ ላይ ወደተፈጠረው ትርምስ ጎራ አለ።
ታደሰ ገብረማሪያም ይባላል። በአሰቃቂ ሁኔታ የተደበደበውን ወጣት ሲመለከት ዐይኖቹ በእንባ ተሞሉ፡፡ አደጋውን ለፖሊስ ቀድሞ ሪፖርት ያደረገው እሱ ነበር፡፡ ፖሊስ ከስፍራው ሲደርስ ነፍሱ አልወጣችም እንጂ ያ ወጣት የሞት ያክል ከባድ ጉዳት ደርሶበት ተገኘ፡፡ ወጣቱ በአንቡላንስ ወደ ዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል ከተወሰደ በኋላ ታደስ ወደ መስሪያ
ቤቱ ቢያመራም የእለት ተግባሩን በአግባቡ መከወን ተስኖት ነበር። ገና በጠዋቱ ከቤቱ እንደወጣ ባየው አሰቃቂ አደጋ ቀኑን ሙሉ ሲረበሽ ውሎ ሲመሽ ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡
ታደሰ የጨለማ ድባብ በዋጣት ጠባብ ክፍሉ ውስጥ ብረቱ የዛገ የሽቦ አልጋውን ተንተርሶ በሃሳቡ ጭልጥ ብሎ ሄደ። የዚያ በደም ተለውሶ የተንጋላለ ወጣት ሁኔታ ከፊቱ እየተመላለሰ ሰላም አየነሳው ነበር።
መንግሥትና ህግ ባሉበት አገር ውስጥ እዚያ ጥግ የደረሰ አስከፊ ወንጀል በአደባባይ መፈፀሙ እያስቀጨነቀው፣ የቀማኞችና የነፍሰ በላዎች መሸሽጊያ ዋሻ እሪ በከንቱ የሚፀዳበት ጊዜ እየናፈቀው እንቅልፍ የሚባል ነገር
በአይኑ ሳይዞር ሰማይና ምድር ተላቀቁ።
ታደሰ በጠዋቱ ተነሳና ወንበር ላይ አጣጥፎ ያስቀመጣቸው ልብሶቹን
ለባብሶ በየማዕዘኑ ሸረሪት ያደራባት ጎጆውን ከውጪ ቆለፈና እንደ ልማዱ ወደ መስሪያ ቤቱ የሚያደርሰውን ሰርቪስ ለመያዝ ወጣ፡፡ያ አሳዛኝ ወጣት ወድቆበት የነበረውን አካባቢ በጥላቻ ወደ ጎን እየተመለከተ ወደ ፊት በር አቀና፡፡
አንገቱን አቀርቅሮ እጆቹን እያወራጨ ሲራመድና ለራሱ ሲያወራ የተመለከተ ሰው ከአዕምሮው ጤነኛ አለመሆኑን ቢጠራጠር የሚፈረድበት
አይሆንም፡፡ ለሰው ልጅ ህይወት ደንታ ሳይኖራቸው እየነጠቁና ደም
እያፈሰሱ በእሪ በከንቱ ዋሻ ውስጥ ተደብቀው የሚኖሩ ግፈኞች ጉዳይ በእጅጉ እያሳስበውና ነገ ከነገ ወዲያ የዚያ ወጣት እጣ ፈንታ በሱ ላይ
የማይደርስ ስለመሆኑ ዋስትና በማጣት ጭምር እየተጨነቀ ነው። ታደሰ ይሄ ጉዳይ ክፉኛ ስላሳሰበው አቅሙ በፈቀደ መጠን ወንጀልና ወንጀለኞችን ለመፋለም ለራሱ ቃል ገብቷል። "ምነው ታዴ እንደ እብድ ብቻሽን ታወሪ ጀመር እንዴ ?" አለው ጓደኛው አማኑኤል፡፡
"እብደት አልከኝ አማኑኤል? ልክ ነህ አእምሮ ጫና ሲበዛበትና ፊውዙ ሲቃጠል ተከታዩ እብደት ሊሆን ይችላል። የኔ አዕምሮ ፊውዝ ግን የነሱን ሳያቃጥል በቀላሉ አይቃጠልም!!" ፊቱን ቅጭም አደረገ፡፡ አማኑኤል በታደሰ አነጋገር ግራ ተጋባ፡፡
"እነማንን ነው የምትለው ታዴ?"
"እነዚያን የሰውን ልጅ ህይወት በጩቤ ጀልባ እየቀዘፉ በደም ውቅያኖስ ውስጥ የሚዋኙትን፣ እነዚያን የንፁሃንን ጉሮሮ ያለርህራሄ የሚበጥሱትን፣ እነዚያን ሳይሐፉ፣ሳይደክሙ በደም የተለወሰ እንጀራ የሚበሉትን!"
አማኑኤል ከዩኒቨርስቲ ተመርቆ ስራውን ከጀመረ ሁለት ዓመት እንኳን አልሞላውም ነበር፡፡ ከታደስ ጋር በዚህ መስሪያ ቤት ውስጥ ከተዋወቁበት ጊዜ ጀምሮ ተግባብተውና ተሳስቀው ስራቸውን በትጋት ከማከናወን
ባለፈ የዚህ ዓይነቱን የመረረ ሁኔታ አይቶበት አያውቅም ነበር ።
አስቃቂ ድርጊትም አከለለት።
“ባልና ሚስትን ደብድበው ንብረታቸውን ዘርፈው ተሰወሩ፣ እገሌን ማጅራቱን መቱት፣ የለበሰውን ልብስ ገፈው ቱቦ ውስጥ ጥለውት ሄዱ፤
እገሌን ሃንግ አደረጉ..." ሌላም ሌላም፡፡ በዚያ ወጣት ላይ ደርሶ ያየውን አሰቃቂ ድርጊት አከለለት
“ይሄ አረመኔነት የተጠናወተው ሰይጣናዊ ተግባር ነው። ይሄ እኩይ መቆሚያ ካልተበጀለት የእያንዳንዳችን ጉሮሮ ተራ በተራ መታነቁ የማይቀር ነው" አለ በብስጭት።
"አቦ ተወና ታዴ! ያልበላህን እያከክ ነው እንዴ?! እሱ የኛ ችግር አይደለም! ይሄ ለዚሁ ተግባር የተሰማሩ የፖሊሶች ስራ ነው፡፡ የሰው ስራ አትሻማ!” አለው።
“እንደሱ አይደለም አማኑኤል!.….በፍፁም አትሳሳት!…አንዱ ለሌላው ፖሊስ ሊሆን ይገባል፡፡ የኛ ድጋፍ፣ የኛ ትብብር በሌለበት ፖሊስ ብቻውን ተአምር ሊፈጥር አይችልም፡፡ የሌላው ቤት ሲፈተሽ፣ ሲበረበር፣ ሌላው አንገቱ ሲመታ፣ሲታነቅ እንደ ዶሮ ሲጠመዘዝ እያየን እንዳላየ ፊታችንን አዙረን የመሄዱን አስከፊ ልማድ እስካልቀየርነው ድረስ የደህንነት ዋስትናችን አደጋ ላይ መውደቁ የማይቀር ነው፡፡ የሰው ልጅ ጥሮ ግሮ ያፈራው አንጡራ ሀብቱን በገሃድ መነጠቁ አንሶ ህይወቱ መጥፋት የለበትም። በየሜዳውና በየድልድዩ ውስጥ መደፋት የለበትም፡፡ ወንጀለኞቹ
ገንዘብ ብቻ ዘርፈው አይሄዱም እኮ! እሱ ብቻውን አያረካቸውም፡፡የሚያረካቸው ደሙ ሲንዠቀዠቅ፣ እስትንፋሱ ስትቆም ማየት ነው"
እና መፍትሄው ምንድን ነው ታዴ ? ምንስ ማድረግ ትችላለህ?"
ከዚች ደቂቃና ሴኮንድ ጀምሮ ምሽጋቸውን ለመናድ ከተደራጀው ሰራዊት ጎን ቆሜ እኩይ ተግባራቸውን ለማስቆም የበኩሌን ጥረት አደርጋለሁ” አለው በፅናት፡፡
'ተው እንጂ ታደስ? ለምን በአንገትህ ላይ ሸምቀቆ ታስገባለህ? ለምን ራስህን ለአደጋ ተጋልጣለህ?ፖሊስ የሚፋለማቸውኮ በተገቢው ትጥቅ ተደራጅቶ ነው፡፡ አንተ ግን ባዶ እጅህን ነህ በባዶ እጅ ያዋጣል? እንኳን በባዶ እጅ በትጥቅም አልተቻሉም ወዳጄ!.."
ተራህ እስከሚደርስ ቁጭ ብለህ ጠብቃቸው እያልከኝ ነው?"
“ታዴ ብቻህን ተቆርቋሪ በመሆንህ ወይንም ራስህን ለጥቃት በማጋለጥህ ለችግሩ መፍትሄ ትሆናለህ ብዬ ስለማላምን ነው። ጨለምተኛ እንዳትለኝ እንጂ መፍትሄው ያለው በመንግሥት እጅ ብቻ ነው።ማጅራት መቺው፣ ቤት ሰርሳሪው፣ ኪስ አውላቂው ሁሉ የየራሳቸው የሆነ የተለያየ ታሪክ ያላቸውና በተለያዩ ጊዜያት ተይዘው እስር ቤት የገቡ፣ የተገረፉ፣ የተደበደቡ ጭምር ናቸው፡፡ ምክንያታቸው ደግሞ የስራ መስክ አልተፈጠረልንም፣ ሰርተን የምንኖርበት ሁኔታ አልተመቻቸልንም የሚል ነው።
ዘላቂ መፍትሄ የሚገኘው እነሱን በማጥፋት ብቻ ሳይሆን እነሱን
የሚፈለፍለውን የኋላ ቀርነት ማሽን ከስር መሰረቱ በማጥፋት ነው።
ወንጀልና ወንጀለኛን መከላከል የሚቻለው ስራ አጥነትን፣ የትምህርት እድል እጦትን፣ ረሃብን ፣ በሽታን ፣ ድንቁርናን በአጠቃላይ በድህነት ሰፊ ማህፀን ውስጥ የሚፀነሱ ችግሮችን በመዋጋት ነው። ለዚህ ደግሞ በቂ የስራ እድል በመፍጠር፣ ህብረተሰቡ ለስራ ያለውን ዝቅተኛ አመለካከቱን እንዲለውጥ በማስተማር፣ መሃይምነትን በመታገል እና ሌሎች ተመሳሳይ ስራዎችን በመስራት እንጂ ወንጀለኛን በማሳደድ ብቻ ማስቆም የሚቻል አይሆንም፡፡ ይሄ እጅግ ሰፊ አገራዊ ችግርና አጀንዳ ስለሆነ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...ጭንቀት በጭንቀት ሆነች። ብቅ ጥልቅ ወጣ ገባ.አበዛች። ለመጀመሪያ ጊዜ ማምሸቱ ያሳሰባት ዘይኑ የምትሆነውን አጣች። ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ተኩል ጀምሮ ነበር መጠባበቅ የጀመረችው። እንደበፊቱ ትምህርት ቤት እንዳትል ትምህርቱን ጨርሷል። ምን ነክቶት ይሆን? ተርበተበተች፡፡ ስዓቱ እየገፋ እየሄደ ነው። ስጋት ከጀመረችበት ጊዜ ጀምሮ ጌትነት
አደጋ ላይ እስከወደቀበት እስከ ምሽቱ አራት ሰዓት ተኩል ድረስ...
ከዚያም ሙሉውን ለሊት ስታምጥ አነጋች፡፡ ወንድም ጋሻዋ..ድምጡ
ጠፋ፡፡ የውሃ ሽታ ሆነ፡፡ ለሊቱን ተቅማጥ ሲያጣድፋት አደረ። ጎረቤታቸው ወይዘሮ ጤናዳም ደግሞ ሲያፅናኗት አነጉ።
"ምንም አይደለም ወንድ ልጅ አንዳንድ ጊዜ አመሉ ነው። አይዞሽ ጠዋት ይመጣልሻል"እያሉ ሞራል ሲሰጧት አደሩ። መንጋት አይበለው እንደ ምንም ነጋላት። ወንድም ጋሻዋን የበላችባት ወፍ ግን ድምጿን አላሰማ አለች፡፡ እዬዬ... ኡኡታ... ዋይታ…ቁጭ ብድግ.. በዚያች እሷ በጭንቀት በምትሸበርባት ማለዳ አንድ ሰው ወደ ስራ በማምራት ላይ እያለ እሪ በከንቱ ዳገቱ ላይ ወደተፈጠረው ትርምስ ጎራ አለ።
ታደሰ ገብረማሪያም ይባላል። በአሰቃቂ ሁኔታ የተደበደበውን ወጣት ሲመለከት ዐይኖቹ በእንባ ተሞሉ፡፡ አደጋውን ለፖሊስ ቀድሞ ሪፖርት ያደረገው እሱ ነበር፡፡ ፖሊስ ከስፍራው ሲደርስ ነፍሱ አልወጣችም እንጂ ያ ወጣት የሞት ያክል ከባድ ጉዳት ደርሶበት ተገኘ፡፡ ወጣቱ በአንቡላንስ ወደ ዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል ከተወሰደ በኋላ ታደስ ወደ መስሪያ
ቤቱ ቢያመራም የእለት ተግባሩን በአግባቡ መከወን ተስኖት ነበር። ገና በጠዋቱ ከቤቱ እንደወጣ ባየው አሰቃቂ አደጋ ቀኑን ሙሉ ሲረበሽ ውሎ ሲመሽ ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡
ታደሰ የጨለማ ድባብ በዋጣት ጠባብ ክፍሉ ውስጥ ብረቱ የዛገ የሽቦ አልጋውን ተንተርሶ በሃሳቡ ጭልጥ ብሎ ሄደ። የዚያ በደም ተለውሶ የተንጋላለ ወጣት ሁኔታ ከፊቱ እየተመላለሰ ሰላም አየነሳው ነበር።
መንግሥትና ህግ ባሉበት አገር ውስጥ እዚያ ጥግ የደረሰ አስከፊ ወንጀል በአደባባይ መፈፀሙ እያስቀጨነቀው፣ የቀማኞችና የነፍሰ በላዎች መሸሽጊያ ዋሻ እሪ በከንቱ የሚፀዳበት ጊዜ እየናፈቀው እንቅልፍ የሚባል ነገር
በአይኑ ሳይዞር ሰማይና ምድር ተላቀቁ።
ታደሰ በጠዋቱ ተነሳና ወንበር ላይ አጣጥፎ ያስቀመጣቸው ልብሶቹን
ለባብሶ በየማዕዘኑ ሸረሪት ያደራባት ጎጆውን ከውጪ ቆለፈና እንደ ልማዱ ወደ መስሪያ ቤቱ የሚያደርሰውን ሰርቪስ ለመያዝ ወጣ፡፡ያ አሳዛኝ ወጣት ወድቆበት የነበረውን አካባቢ በጥላቻ ወደ ጎን እየተመለከተ ወደ ፊት በር አቀና፡፡
አንገቱን አቀርቅሮ እጆቹን እያወራጨ ሲራመድና ለራሱ ሲያወራ የተመለከተ ሰው ከአዕምሮው ጤነኛ አለመሆኑን ቢጠራጠር የሚፈረድበት
አይሆንም፡፡ ለሰው ልጅ ህይወት ደንታ ሳይኖራቸው እየነጠቁና ደም
እያፈሰሱ በእሪ በከንቱ ዋሻ ውስጥ ተደብቀው የሚኖሩ ግፈኞች ጉዳይ በእጅጉ እያሳስበውና ነገ ከነገ ወዲያ የዚያ ወጣት እጣ ፈንታ በሱ ላይ
የማይደርስ ስለመሆኑ ዋስትና በማጣት ጭምር እየተጨነቀ ነው። ታደሰ ይሄ ጉዳይ ክፉኛ ስላሳሰበው አቅሙ በፈቀደ መጠን ወንጀልና ወንጀለኞችን ለመፋለም ለራሱ ቃል ገብቷል። "ምነው ታዴ እንደ እብድ ብቻሽን ታወሪ ጀመር እንዴ ?" አለው ጓደኛው አማኑኤል፡፡
"እብደት አልከኝ አማኑኤል? ልክ ነህ አእምሮ ጫና ሲበዛበትና ፊውዙ ሲቃጠል ተከታዩ እብደት ሊሆን ይችላል። የኔ አዕምሮ ፊውዝ ግን የነሱን ሳያቃጥል በቀላሉ አይቃጠልም!!" ፊቱን ቅጭም አደረገ፡፡ አማኑኤል በታደሰ አነጋገር ግራ ተጋባ፡፡
"እነማንን ነው የምትለው ታዴ?"
"እነዚያን የሰውን ልጅ ህይወት በጩቤ ጀልባ እየቀዘፉ በደም ውቅያኖስ ውስጥ የሚዋኙትን፣ እነዚያን የንፁሃንን ጉሮሮ ያለርህራሄ የሚበጥሱትን፣ እነዚያን ሳይሐፉ፣ሳይደክሙ በደም የተለወሰ እንጀራ የሚበሉትን!"
አማኑኤል ከዩኒቨርስቲ ተመርቆ ስራውን ከጀመረ ሁለት ዓመት እንኳን አልሞላውም ነበር፡፡ ከታደስ ጋር በዚህ መስሪያ ቤት ውስጥ ከተዋወቁበት ጊዜ ጀምሮ ተግባብተውና ተሳስቀው ስራቸውን በትጋት ከማከናወን
ባለፈ የዚህ ዓይነቱን የመረረ ሁኔታ አይቶበት አያውቅም ነበር ።
አስቃቂ ድርጊትም አከለለት።
“ባልና ሚስትን ደብድበው ንብረታቸውን ዘርፈው ተሰወሩ፣ እገሌን ማጅራቱን መቱት፣ የለበሰውን ልብስ ገፈው ቱቦ ውስጥ ጥለውት ሄዱ፤
እገሌን ሃንግ አደረጉ..." ሌላም ሌላም፡፡ በዚያ ወጣት ላይ ደርሶ ያየውን አሰቃቂ ድርጊት አከለለት
“ይሄ አረመኔነት የተጠናወተው ሰይጣናዊ ተግባር ነው። ይሄ እኩይ መቆሚያ ካልተበጀለት የእያንዳንዳችን ጉሮሮ ተራ በተራ መታነቁ የማይቀር ነው" አለ በብስጭት።
"አቦ ተወና ታዴ! ያልበላህን እያከክ ነው እንዴ?! እሱ የኛ ችግር አይደለም! ይሄ ለዚሁ ተግባር የተሰማሩ የፖሊሶች ስራ ነው፡፡ የሰው ስራ አትሻማ!” አለው።
“እንደሱ አይደለም አማኑኤል!.….በፍፁም አትሳሳት!…አንዱ ለሌላው ፖሊስ ሊሆን ይገባል፡፡ የኛ ድጋፍ፣ የኛ ትብብር በሌለበት ፖሊስ ብቻውን ተአምር ሊፈጥር አይችልም፡፡ የሌላው ቤት ሲፈተሽ፣ ሲበረበር፣ ሌላው አንገቱ ሲመታ፣ሲታነቅ እንደ ዶሮ ሲጠመዘዝ እያየን እንዳላየ ፊታችንን አዙረን የመሄዱን አስከፊ ልማድ እስካልቀየርነው ድረስ የደህንነት ዋስትናችን አደጋ ላይ መውደቁ የማይቀር ነው፡፡ የሰው ልጅ ጥሮ ግሮ ያፈራው አንጡራ ሀብቱን በገሃድ መነጠቁ አንሶ ህይወቱ መጥፋት የለበትም። በየሜዳውና በየድልድዩ ውስጥ መደፋት የለበትም፡፡ ወንጀለኞቹ
ገንዘብ ብቻ ዘርፈው አይሄዱም እኮ! እሱ ብቻውን አያረካቸውም፡፡የሚያረካቸው ደሙ ሲንዠቀዠቅ፣ እስትንፋሱ ስትቆም ማየት ነው"
እና መፍትሄው ምንድን ነው ታዴ ? ምንስ ማድረግ ትችላለህ?"
ከዚች ደቂቃና ሴኮንድ ጀምሮ ምሽጋቸውን ለመናድ ከተደራጀው ሰራዊት ጎን ቆሜ እኩይ ተግባራቸውን ለማስቆም የበኩሌን ጥረት አደርጋለሁ” አለው በፅናት፡፡
'ተው እንጂ ታደስ? ለምን በአንገትህ ላይ ሸምቀቆ ታስገባለህ? ለምን ራስህን ለአደጋ ተጋልጣለህ?ፖሊስ የሚፋለማቸውኮ በተገቢው ትጥቅ ተደራጅቶ ነው፡፡ አንተ ግን ባዶ እጅህን ነህ በባዶ እጅ ያዋጣል? እንኳን በባዶ እጅ በትጥቅም አልተቻሉም ወዳጄ!.."
ተራህ እስከሚደርስ ቁጭ ብለህ ጠብቃቸው እያልከኝ ነው?"
“ታዴ ብቻህን ተቆርቋሪ በመሆንህ ወይንም ራስህን ለጥቃት በማጋለጥህ ለችግሩ መፍትሄ ትሆናለህ ብዬ ስለማላምን ነው። ጨለምተኛ እንዳትለኝ እንጂ መፍትሄው ያለው በመንግሥት እጅ ብቻ ነው።ማጅራት መቺው፣ ቤት ሰርሳሪው፣ ኪስ አውላቂው ሁሉ የየራሳቸው የሆነ የተለያየ ታሪክ ያላቸውና በተለያዩ ጊዜያት ተይዘው እስር ቤት የገቡ፣ የተገረፉ፣ የተደበደቡ ጭምር ናቸው፡፡ ምክንያታቸው ደግሞ የስራ መስክ አልተፈጠረልንም፣ ሰርተን የምንኖርበት ሁኔታ አልተመቻቸልንም የሚል ነው።
ዘላቂ መፍትሄ የሚገኘው እነሱን በማጥፋት ብቻ ሳይሆን እነሱን
የሚፈለፍለውን የኋላ ቀርነት ማሽን ከስር መሰረቱ በማጥፋት ነው።
ወንጀልና ወንጀለኛን መከላከል የሚቻለው ስራ አጥነትን፣ የትምህርት እድል እጦትን፣ ረሃብን ፣ በሽታን ፣ ድንቁርናን በአጠቃላይ በድህነት ሰፊ ማህፀን ውስጥ የሚፀነሱ ችግሮችን በመዋጋት ነው። ለዚህ ደግሞ በቂ የስራ እድል በመፍጠር፣ ህብረተሰቡ ለስራ ያለውን ዝቅተኛ አመለካከቱን እንዲለውጥ በማስተማር፣ መሃይምነትን በመታገል እና ሌሎች ተመሳሳይ ስራዎችን በመስራት እንጂ ወንጀለኛን በማሳደድ ብቻ ማስቆም የሚቻል አይሆንም፡፡ ይሄ እጅግ ሰፊ አገራዊ ችግርና አጀንዳ ስለሆነ
👍1
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...ሰሞኑን ያየችው ህልም ክፉኛ ያስደነገጣት እናት አመዱን ይነሰንስባት ጀምሯል። የወትሮ ህልሟ ተስፋን የሚያበስር መሆኑን ስለምታውቅ ፊቷ እንደ ፀሀይ እያበራ በደስታ መንፈስ ለቡና ማህበረተኞቿ ታወራላቸው ነበር፡፡ ከማህበርተኞቿ ውስጥ ደግሞ በህልም ፈቺነታቸው ወይዘሮ
ተዋበችን የሚደርስባቸው የለም፡፡ ህልም ሲፈቱ እንከን አይወጣላቸውም ተብሎ በአብዛኛው ነዋሪ ስለሚታመንባቸው ህልም ለመፍታት ኩራታቸው አይጣል ነው። ትንሽ ካላስለመኑ ህልም አይፈቱም፡፡ ከልመና በኋላ ግን መተንተን ይጀምራሉ፡፡
ሲሳይ ነው! ዓለም ነው!አቤት ደስታ! ልጅ ልትወልጂ ነው...ስለትሽ ሊደርስ ነው፣ በዚህ ሊገባ በዚህ ሊወጣ ነው፡፡ የተጣላው ሊታረቅ፣ የደለው ሊሞላ.. ብቻ ጥሩ ጥሩውን ሁሉ ልታገኙ ነው እያሉ አላሚውን
ተስፋ በተስፋ ያደርጉታል፡፡ ከሁሉ የበለጠ የህልም ደንበኛቸው ግን
አስካለ ነበረች። ያየችውን ህልም ስትነግራቸው ሁሌም የሚያያይዙት ከልጆቿ ጋር ነው፡፡
አቤት! አቤት! በውነት ህልም አይደለም ያየሽለት ራዕይ ነው፡፡ ጉድ! ደሞዙ ከፍ ሥልጣኑም ከፍ ሊል ነው፡፡ ጥሩ ደረጃ ላይ ሊደርስልሽ ነው! ትንሿም ደስ ብሏታል ያንቺ ናፍቆት አለባት መሰለኝ እዚህ ጋ ትንሽ ቅር
እንዳላት አያለሁ፡፡ ይሁን ግድ የለም ትምህርት ቤት ሲዘጋ ትመጣለች።
ጥሩ ህልም ነው ይሏታል የቡናው አሻራ ያረፈበትን ባዶ ስኒ ዘቅዝቀው እየተመለከቱ፡፡ ከዚያም አስካለ በደስታ መፈንደቅ ነው። በዚህ ሁሉ ቆንጆ ቆንጆ ህልሞቿ ጣልቃ ስሞኑን ያየችው መጥፎ ህልም ግን ክፉኛ አስደንግጧታል
ለማንም ሳትናገር ፍርሃትና ሃሣብ ውስጥ ውስጡን ሲያካት ቆይቶ በትንሽ ጊዜ ውስጥ ወዛም ነበረ ፊቷ ላይ አመዱን ይነዛበት ገባ።
"ተነሳብሽ ደግሞ አንቺ ሴት! ለመሆኑ ሄደሽ ከመጣሽ ሁለት ወር እንኳ ይሞላዋል እንዴ? ናፈቁኝ ነው ወይስ ምን አዲስ ነገር ተገኘና ነው እንዴዚህ ነጭ እስከምትሆኚ ድረስ ራስሽን መጣል ያመጣሽው?” ለመሽፋፈን ጥረት ብታደርግም ሃሳብ እየወዘወዛት መሆኑ የገባቸው ወይዘሮ ተዋቡ ተቆጡ።አስካለ የመጀመሪያ መጥፎ ህልሟን አይታ መረበሽ ከጀመረች
በኋላ ጭንቀቱ ነው መሰል በላይ በላዩ የሚያስፈራራ ህልም እየደጋገመ አስቸገራት። የአሁኑ ደግሞ ፍፁም የተለየ ሆነባት።
ጌትነት ይመስላታል፡፡ እንደ ልጅነቱ አብሯት እንጨት ለቀማ ይሄዳሉ።
ከአንዱ ዛፍ ወደ ሌላው ዛፍ እየዘለለ ጥሩ ጥሩውን እንጨት እየሰበረ ኢያቀበላት የቆመበት ቅርንጫፍ ተገንጥሎ መሬት ላይ ይወድቃል። ከዚያም
ይንከባለላል. በዚያው እንደ ሙቀጫ ጅው ብሎ ተንከባሎ ቁልቁል ይወርዳል። ለካስ ከስሩ ገደል ነበር፡፡ ከታች ገደል መኖሩን፣ ልጅዋ አደጋ ላይ መውደቁን ያየች እናት ኡኡ! ልጄን! ልጄን!.. ልጄን! እየጮኸች አብራው ልትገባ ወደ እሱ ትሮጣለች። ጌትነት ገደሉ ውስጥ ተወርውሮ ከመግባት ለትንሽ የተረፈው የሆነ ቁጥቋጦ ነገር እጁ ውስጥ ስለገባ ነበር፡፡
ከዚያም እናቱ ጉዳት ላይ እንዳትወድቅበት ውትወታውን ይቀጥላል።
“እማዬ! እማዬ!ደህና ነኝ! ምንም አልሆንኩም! እዚያው ቁሚ! መጣሁ! መጣሁ! መጣሁ!" ወደሱ ስትሮጥ ወድቃ እንዳትሰበር ፈርቶ ይጮሀል። እሷ ደግሞ አሻፈረኝ ብላ ወደ ገደሉ እየሮጠች ትመጣና ገደሉ ጫፍ ላይ
ሆና “ጌትዬ! ተረፍክ የኔ ጌታ?!” ቁልቁል እያየችው ትጠይቀዋለች::
"ተርፌአለሁ! ተርፌአለሁ!አይዞሽ! ምንም አልሆንኩም በቃ እዚያው ጋ ሁኚ!" ይላትና በአንድ ትልቅ ቋጥኝ ላይ ተጋድሞ በተንጠለጠለ ወፍራም
ሀረግ አማካኝነት እየተሳበ ሽቅብ መውጣት ጀመረ። ወጣ ወጣ...
ወጣና አጠገቧ ሊደርስ ትንሽ ቀረው። ደክሞታል። አልቦታል። ..
“አይዞህ ጌትዬ በርታ የኔ ልጅ... ቆይ እጅህን ልያዝልህ" ጐንበስ
ትላለች።
“ተይ !ተይ! እማዬ ተይ! እንዳያንሸራትትሽ !እኔ ቀስ እያልኩ እወጣ ለሁ ተይ!!"
“ግዴለህም ይልቁንስ እጅህን አቀብለኝ" ትለውና ሄዳ ከገደሉ ጫፍ ላይ ተንጠልጥላ የቀኝ እጇን ትልክለታለች። አልደርስብሽ ይላታል። እንደገና ብሃይል ወደሱ ተንጠራርታ እጇን ልትስጠው ጐንበስ ትላለች። በግራ እጅዋ አንድ ትልቅ ጉቶ ይዛ ነበር፡፡ አሁንም አልደርስብሽ ይላታል።
ጭንቅቱ አስጨንቋት ቶሎ ልታወጣው ቸኩላለች። እሱም አወጣዋለሁ ብላ ስትፍጨረጨር ጉዳት ላይ እንዳትወድቅ ፈርቶ እጅዋን ቶሎ ለመያዝ ይንደፋደፋል። ተቃረበ ። ሊይዛት ትንሽ ብቻ ቀረው። በጣም
ተንጠራራ። እጇን ልታስይዘው አብዛኛው ሚዛኗን በገደሉ አፋፍ ላይ ወጥራ በሃይል ተንጠራራች። ጣቶቻቸው ሊነካኩ የስንዝር ያክል ልዩነት ብቻ ነበር የቀራቸው። በዚሁ መሀል ግን ከየት መጣ ሳይባል አንድ ትልቅ ጭልፊት አሞራ ይመጣና ፊቷን በጥፊ ይላታል። ደንግጣ አሞራውን ለማየት ቀና ስትል ጌትነት የተንጠለጠለበት ሀረግ ቷ!! ብሎ ከመስረቱ ተነቀለና ቁልቁል እየተምዘገዘገ ይዞት ሲወርድ አየች።
ገደሉ ርቀት ነበረው። ጌትነት ጥረቱ ሳይሳካለት ቀረና ሄዶ በአናቱ ተደፋ። ጭንቅላቱ ያረፈው አለት ድንጋይ ላይ ነበር፡፡ በጀርባው እንደተዘረረ ደሙ እንደ ምንጭ ውሃ ቡልቅ! ሲል እናቱ ተመለከተች፡፡
“ወይኔ..ልጄን!እኔ ልደፋ!” ባለ በሌለ ሀይሏ ወደ ገደሉ ራሷን ወረወረች... ከእንቅልፏ እየተወራጨች የባነነችው በዚህ አስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ እያለች ነበር፡፡ በዚህ እጅግ አሰቃቂ በሆነ ህልሟ ምክንያት ሰውነቷ ይንዘፈዘፍ፣ ወባ እንደተነሳበት ስው ይንቀጠቀጥ ጀመር፡፡
እውን... እውን መሰላት። ከአልጋዋ ላይ ተነሳችና መንታ መንታውን
አወረደችው። ስቅስቅ ብላ አለቀሰች፡፡ ማልቀስ ካቆመች ረጅም ጊዜ ሆኗት ነበር፡፡ የተጠራቀመ እምባዋን እንደ ጐርፍ ለቀቀችው
"ወይኔ ጉዴ?! ወይኔ ልጆቼ?! ምን ዓይነት ህልም ነው? የኔ ደም
ክንብል ይበል። ዛሬ ፈጣሪዬ ምኑን አሳየኽኝ? ደግሞ የምን ጭልፊት
ነው? ዐይኔን ሊያጠፋው ነበረኮ! እስቲ አንተ ታውቃለህ? " ከዚህ አሰቃቂ ህልሟ በኋላ መንፈሷ በፍፁም አልረጋጋ አላት። ጭንቀቱ እረፍት ነሳትና ዳቦ ቆሎ መቁረጥ ጀመረች። በሌላ ጊዜ ደግሞ ትልቅ እባብ ሲያባርረው አየች። ይሄንን ግን ለወይዘሮ ተዋበች አልደበቀቻቸውም፡፡
“ምቀኛ ነው! ምቀኛ! ለመሆኑ ነደፈው?" ብለው ጠየቋት።
የለም! የለም! አልነደፈውም ብቻ ሲያባርረው ሮጦ አመለጠው'
ባለመነደፉ ነው ህልሟን የተናገረችው እንጂ ነድፎት ቢሆን ኖሮ አትነግራቸውም ነበር፡፡
“ጐሽ!...ጎሽ! እባብ ምቀኛ ነው። ምቀኞቹን ሁሉ ድል አድርጓል ማለት ነው፡፡ ቢነድፈው ኖሮ ጥሩ አልነበረም፡፡ ካመለጠው እንኳ ከጠላት፣ ከምቀኛ ተንኮል አምልጧል ማለት ነው፡፡ ማለፊያ ህልም ነው ያየሽለት!”
ሲሉ አጽናኗት። የወላድ አንጀት፣ የልብ ፍቅር እውነትም አንዳንድ ጊዜ ሹክ የሚለው መንፈስ አለ፡፡ ጌትነት የዚያን አይነት አሳዛኝ አደጋ ሊደርስበት ሳምንት ሲቀረው ጀምሮ በሃሣብና በጭንቀት ተወጥራ እየተብሰለሰላች በሆነ ባልሆነው ልቧ ድንግጥ ድንግጥ እያለባት እንቅልፍ እንቢ እያላት
እያቃዣት ሰውነቷ መጨማደድ ጀመረና በጥቂት ቀናት ውስጥ
ተለወጠች፡፡ ለተመልካች ግራ እስከሚገባው ድረስ በአንድ ጊዜ ቆረቆዘች።ጉዷን ያላወቀች እናት። በሷ ቤት የሳምንት ተጓዥ መንገደኛ ናት።የስንቅ ጣጣዋን ጨርሳ ወደ ልጅዋ ለመሄድ ዝግጅቷን በማጠናቀቅ ላይ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...ሰሞኑን ያየችው ህልም ክፉኛ ያስደነገጣት እናት አመዱን ይነሰንስባት ጀምሯል። የወትሮ ህልሟ ተስፋን የሚያበስር መሆኑን ስለምታውቅ ፊቷ እንደ ፀሀይ እያበራ በደስታ መንፈስ ለቡና ማህበረተኞቿ ታወራላቸው ነበር፡፡ ከማህበርተኞቿ ውስጥ ደግሞ በህልም ፈቺነታቸው ወይዘሮ
ተዋበችን የሚደርስባቸው የለም፡፡ ህልም ሲፈቱ እንከን አይወጣላቸውም ተብሎ በአብዛኛው ነዋሪ ስለሚታመንባቸው ህልም ለመፍታት ኩራታቸው አይጣል ነው። ትንሽ ካላስለመኑ ህልም አይፈቱም፡፡ ከልመና በኋላ ግን መተንተን ይጀምራሉ፡፡
ሲሳይ ነው! ዓለም ነው!አቤት ደስታ! ልጅ ልትወልጂ ነው...ስለትሽ ሊደርስ ነው፣ በዚህ ሊገባ በዚህ ሊወጣ ነው፡፡ የተጣላው ሊታረቅ፣ የደለው ሊሞላ.. ብቻ ጥሩ ጥሩውን ሁሉ ልታገኙ ነው እያሉ አላሚውን
ተስፋ በተስፋ ያደርጉታል፡፡ ከሁሉ የበለጠ የህልም ደንበኛቸው ግን
አስካለ ነበረች። ያየችውን ህልም ስትነግራቸው ሁሌም የሚያያይዙት ከልጆቿ ጋር ነው፡፡
አቤት! አቤት! በውነት ህልም አይደለም ያየሽለት ራዕይ ነው፡፡ ጉድ! ደሞዙ ከፍ ሥልጣኑም ከፍ ሊል ነው፡፡ ጥሩ ደረጃ ላይ ሊደርስልሽ ነው! ትንሿም ደስ ብሏታል ያንቺ ናፍቆት አለባት መሰለኝ እዚህ ጋ ትንሽ ቅር
እንዳላት አያለሁ፡፡ ይሁን ግድ የለም ትምህርት ቤት ሲዘጋ ትመጣለች።
ጥሩ ህልም ነው ይሏታል የቡናው አሻራ ያረፈበትን ባዶ ስኒ ዘቅዝቀው እየተመለከቱ፡፡ ከዚያም አስካለ በደስታ መፈንደቅ ነው። በዚህ ሁሉ ቆንጆ ቆንጆ ህልሞቿ ጣልቃ ስሞኑን ያየችው መጥፎ ህልም ግን ክፉኛ አስደንግጧታል
ለማንም ሳትናገር ፍርሃትና ሃሣብ ውስጥ ውስጡን ሲያካት ቆይቶ በትንሽ ጊዜ ውስጥ ወዛም ነበረ ፊቷ ላይ አመዱን ይነዛበት ገባ።
"ተነሳብሽ ደግሞ አንቺ ሴት! ለመሆኑ ሄደሽ ከመጣሽ ሁለት ወር እንኳ ይሞላዋል እንዴ? ናፈቁኝ ነው ወይስ ምን አዲስ ነገር ተገኘና ነው እንዴዚህ ነጭ እስከምትሆኚ ድረስ ራስሽን መጣል ያመጣሽው?” ለመሽፋፈን ጥረት ብታደርግም ሃሳብ እየወዘወዛት መሆኑ የገባቸው ወይዘሮ ተዋቡ ተቆጡ።አስካለ የመጀመሪያ መጥፎ ህልሟን አይታ መረበሽ ከጀመረች
በኋላ ጭንቀቱ ነው መሰል በላይ በላዩ የሚያስፈራራ ህልም እየደጋገመ አስቸገራት። የአሁኑ ደግሞ ፍፁም የተለየ ሆነባት።
ጌትነት ይመስላታል፡፡ እንደ ልጅነቱ አብሯት እንጨት ለቀማ ይሄዳሉ።
ከአንዱ ዛፍ ወደ ሌላው ዛፍ እየዘለለ ጥሩ ጥሩውን እንጨት እየሰበረ ኢያቀበላት የቆመበት ቅርንጫፍ ተገንጥሎ መሬት ላይ ይወድቃል። ከዚያም
ይንከባለላል. በዚያው እንደ ሙቀጫ ጅው ብሎ ተንከባሎ ቁልቁል ይወርዳል። ለካስ ከስሩ ገደል ነበር፡፡ ከታች ገደል መኖሩን፣ ልጅዋ አደጋ ላይ መውደቁን ያየች እናት ኡኡ! ልጄን! ልጄን!.. ልጄን! እየጮኸች አብራው ልትገባ ወደ እሱ ትሮጣለች። ጌትነት ገደሉ ውስጥ ተወርውሮ ከመግባት ለትንሽ የተረፈው የሆነ ቁጥቋጦ ነገር እጁ ውስጥ ስለገባ ነበር፡፡
ከዚያም እናቱ ጉዳት ላይ እንዳትወድቅበት ውትወታውን ይቀጥላል።
“እማዬ! እማዬ!ደህና ነኝ! ምንም አልሆንኩም! እዚያው ቁሚ! መጣሁ! መጣሁ! መጣሁ!" ወደሱ ስትሮጥ ወድቃ እንዳትሰበር ፈርቶ ይጮሀል። እሷ ደግሞ አሻፈረኝ ብላ ወደ ገደሉ እየሮጠች ትመጣና ገደሉ ጫፍ ላይ
ሆና “ጌትዬ! ተረፍክ የኔ ጌታ?!” ቁልቁል እያየችው ትጠይቀዋለች::
"ተርፌአለሁ! ተርፌአለሁ!አይዞሽ! ምንም አልሆንኩም በቃ እዚያው ጋ ሁኚ!" ይላትና በአንድ ትልቅ ቋጥኝ ላይ ተጋድሞ በተንጠለጠለ ወፍራም
ሀረግ አማካኝነት እየተሳበ ሽቅብ መውጣት ጀመረ። ወጣ ወጣ...
ወጣና አጠገቧ ሊደርስ ትንሽ ቀረው። ደክሞታል። አልቦታል። ..
“አይዞህ ጌትዬ በርታ የኔ ልጅ... ቆይ እጅህን ልያዝልህ" ጐንበስ
ትላለች።
“ተይ !ተይ! እማዬ ተይ! እንዳያንሸራትትሽ !እኔ ቀስ እያልኩ እወጣ ለሁ ተይ!!"
“ግዴለህም ይልቁንስ እጅህን አቀብለኝ" ትለውና ሄዳ ከገደሉ ጫፍ ላይ ተንጠልጥላ የቀኝ እጇን ትልክለታለች። አልደርስብሽ ይላታል። እንደገና ብሃይል ወደሱ ተንጠራርታ እጇን ልትስጠው ጐንበስ ትላለች። በግራ እጅዋ አንድ ትልቅ ጉቶ ይዛ ነበር፡፡ አሁንም አልደርስብሽ ይላታል።
ጭንቅቱ አስጨንቋት ቶሎ ልታወጣው ቸኩላለች። እሱም አወጣዋለሁ ብላ ስትፍጨረጨር ጉዳት ላይ እንዳትወድቅ ፈርቶ እጅዋን ቶሎ ለመያዝ ይንደፋደፋል። ተቃረበ ። ሊይዛት ትንሽ ብቻ ቀረው። በጣም
ተንጠራራ። እጇን ልታስይዘው አብዛኛው ሚዛኗን በገደሉ አፋፍ ላይ ወጥራ በሃይል ተንጠራራች። ጣቶቻቸው ሊነካኩ የስንዝር ያክል ልዩነት ብቻ ነበር የቀራቸው። በዚሁ መሀል ግን ከየት መጣ ሳይባል አንድ ትልቅ ጭልፊት አሞራ ይመጣና ፊቷን በጥፊ ይላታል። ደንግጣ አሞራውን ለማየት ቀና ስትል ጌትነት የተንጠለጠለበት ሀረግ ቷ!! ብሎ ከመስረቱ ተነቀለና ቁልቁል እየተምዘገዘገ ይዞት ሲወርድ አየች።
ገደሉ ርቀት ነበረው። ጌትነት ጥረቱ ሳይሳካለት ቀረና ሄዶ በአናቱ ተደፋ። ጭንቅላቱ ያረፈው አለት ድንጋይ ላይ ነበር፡፡ በጀርባው እንደተዘረረ ደሙ እንደ ምንጭ ውሃ ቡልቅ! ሲል እናቱ ተመለከተች፡፡
“ወይኔ..ልጄን!እኔ ልደፋ!” ባለ በሌለ ሀይሏ ወደ ገደሉ ራሷን ወረወረች... ከእንቅልፏ እየተወራጨች የባነነችው በዚህ አስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ እያለች ነበር፡፡ በዚህ እጅግ አሰቃቂ በሆነ ህልሟ ምክንያት ሰውነቷ ይንዘፈዘፍ፣ ወባ እንደተነሳበት ስው ይንቀጠቀጥ ጀመር፡፡
እውን... እውን መሰላት። ከአልጋዋ ላይ ተነሳችና መንታ መንታውን
አወረደችው። ስቅስቅ ብላ አለቀሰች፡፡ ማልቀስ ካቆመች ረጅም ጊዜ ሆኗት ነበር፡፡ የተጠራቀመ እምባዋን እንደ ጐርፍ ለቀቀችው
"ወይኔ ጉዴ?! ወይኔ ልጆቼ?! ምን ዓይነት ህልም ነው? የኔ ደም
ክንብል ይበል። ዛሬ ፈጣሪዬ ምኑን አሳየኽኝ? ደግሞ የምን ጭልፊት
ነው? ዐይኔን ሊያጠፋው ነበረኮ! እስቲ አንተ ታውቃለህ? " ከዚህ አሰቃቂ ህልሟ በኋላ መንፈሷ በፍፁም አልረጋጋ አላት። ጭንቀቱ እረፍት ነሳትና ዳቦ ቆሎ መቁረጥ ጀመረች። በሌላ ጊዜ ደግሞ ትልቅ እባብ ሲያባርረው አየች። ይሄንን ግን ለወይዘሮ ተዋበች አልደበቀቻቸውም፡፡
“ምቀኛ ነው! ምቀኛ! ለመሆኑ ነደፈው?" ብለው ጠየቋት።
የለም! የለም! አልነደፈውም ብቻ ሲያባርረው ሮጦ አመለጠው'
ባለመነደፉ ነው ህልሟን የተናገረችው እንጂ ነድፎት ቢሆን ኖሮ አትነግራቸውም ነበር፡፡
“ጐሽ!...ጎሽ! እባብ ምቀኛ ነው። ምቀኞቹን ሁሉ ድል አድርጓል ማለት ነው፡፡ ቢነድፈው ኖሮ ጥሩ አልነበረም፡፡ ካመለጠው እንኳ ከጠላት፣ ከምቀኛ ተንኮል አምልጧል ማለት ነው፡፡ ማለፊያ ህልም ነው ያየሽለት!”
ሲሉ አጽናኗት። የወላድ አንጀት፣ የልብ ፍቅር እውነትም አንዳንድ ጊዜ ሹክ የሚለው መንፈስ አለ፡፡ ጌትነት የዚያን አይነት አሳዛኝ አደጋ ሊደርስበት ሳምንት ሲቀረው ጀምሮ በሃሣብና በጭንቀት ተወጥራ እየተብሰለሰላች በሆነ ባልሆነው ልቧ ድንግጥ ድንግጥ እያለባት እንቅልፍ እንቢ እያላት
እያቃዣት ሰውነቷ መጨማደድ ጀመረና በጥቂት ቀናት ውስጥ
ተለወጠች፡፡ ለተመልካች ግራ እስከሚገባው ድረስ በአንድ ጊዜ ቆረቆዘች።ጉዷን ያላወቀች እናት። በሷ ቤት የሳምንት ተጓዥ መንገደኛ ናት።የስንቅ ጣጣዋን ጨርሳ ወደ ልጅዋ ለመሄድ ዝግጅቷን በማጠናቀቅ ላይ
👍2
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
#አዲስ_ዓለም
..የመንገዱ መብራቶች ተበላሽተው ብርሃን አይሰጡም። አካባቢው ፀጥ እረጭ ብሏል። ትናንትና ማታ እስከ ስድስት ሰዓት የነበረው ጩኸት፣ ሁካታ የሰካራሞች ልፍለፋ፣ የሴተኛ አዳሪዎች ስድብ፣ በየቀይ መብራቱ ውስጥ የነበዙ ጠጪዎች ዳንኪራና ጭፈራ ትርምሱ ሁሉ እዚህ ቦታ
የነበረ መሆኑ የሚያጠራጥር ነው፡፡ የሥጋ ቤቶቹ ብርሃን ድምቀት፣ከቡና ቤት ቡና ቤት የሚያማርጠው ጠጪ ብዛት፣ የሙዚቃው ጩኽትና የመኪናው ኳኳታ ጆሮ ሲያደነቁር እንዳላመሽ ሁሉ እንደዚህ እንደ አሁኑ እረጭ ብሎ ሲታይ በግርግርና በፀጥታ መካከል ያለውን ልዩነት
ለማሳየት ደፈጣ የያዘ ይመስል ነበር፡፡
የወዳደቀ አጥንት ለመለቃቀም የሚያነፈንፉ ውሾች ውር ውር
ይላሉ፡፡ በዚህ ሁሉ ጊዜ ውስጥ ግን ያን ሰው የማይታይበትን አካባቢ ፀጥታ በማደፍረስ የጠዋት ገበያዋን ለመላፍ የተጣደፈች ታክሲ ከእሪ በከንቱ ወደ አራት ኪሎ አቅጣጫ በረረች፡፡ በዚያው ቅጽበት ደግሞ
ቁልቁል ከፒያሳ ወደ እሪ በከንቱ እየዘለለ የሚወርድ ሰው ታዬ። መላ ሰውነቱን ሬንጅና ጥላሸት የተቀባ ፀጉሩ እዚህም እዚያም ተገምዶ እንደ ጭራሮ የቆመ፣ ጎድኖቹ ሥጋ ባልለበሰ አጥንት የገጠጡት እብዱ ምን ሽንሽ! ብቻውን በመንገዱ ግራና ቀኝ ቱር ቱር እያለ እየተሯሯጠ ሽቅብ
ይወጣል ቁልቁል ይወርዳል። ዐይኖቹ እንደ በርበሬ ቀልተው ለተመልካች ያስፈራራሉ። ከወገቡ በታች እዚህም እዚያም የተቦጫጨቀ ሱሪ መልበስ
ከተባለ ለብሷል። ቆም ይልና ድንጋይ ይፈነቅላል ያነሳውን መልሶ ይወረውረዋል። ደግሞ ወደታች ይወርዳል። ከዚያም ጉንበስ ይልና የሲጋራ ቁራጭ ለመልቀም ያነፈንፋል።እንደገና ወደ ላይ ይወጣል። የዚያ አስፈሪ
የጨለማ ንጉሥ ሁሉም በየቤቱ በተከተተበት ሰዓት እሱ እየዘለለና እየቦረቀ ብቻውን በየመንገዱ ላይ ሲሯሯጥ ምሽቱን ለብርሃን ለማስረከብ የተዘጋጀ ባለሥልጣን ይመስል ነበር።
ከለሊቱ አሥራ አንድ ሰዓት ሆኗል። ወደየጠቅላይ ግዛቱ የሚጓዙ መንገደኞች አውቶቡስ ተራ ለመድረስ በዋናው አስፋልት መንገድ ላይ ብቅ ብቅ ብለዋል። በዚያ ሰዓት በእግር የሚጓዝ መንገደኛ አንድም በራሱ የተማመነ አሊያም ከወሮበላና ከማጅራት መቺው ሰይፍ እግዚአብሔር እንዲጠብቀው በልቡ ፀሎት እያደረስ በፍርሃት የሚራመድበት እንጂ ልቡ
በድፍረት ተሞልቶ የሚንቀሳቀስበት ሰዓት አልነበረም፡፡ ለሁሉ ነገር ግድ
የለሌው ለማጅራት መቺው ለብርዱ ለፀሀዩ ለሞትም ለህይወትም ደንታ የሌለው እብዱ ምንሽንሽ ብቻ ነበር። የእሪ በከንቱን ድልድይ ተሻግሮ
ወደ አራት ኪሎ ሲያቀና አንድ ዕድሜው ከሰላሳ ስምንት እስከ አርባ አመት የሚገመት ወደ ወሎ ጠቅላይ ግዛት ለመሄድ የሚገስግስ ሰው ብቅ! አለ። ሰውዬው ምንሽንሽን ሲያየው “በስመአብ ወልድ ጌታዬ” አለና
አማተበ፡ የሰይጣን ቤት አጋፋሪ የመሰለውን እብድ ሲመለከት ከመንገዱ ፈንጠር አለና ወደ ዳር ወጣ፡፡ ካደረበት ከዘውዲቱ ሆቴል ቁልቁል ወደ እሪ በከንቱ የሚወስደውን መንገድ ሲጀምረው ዳፍንቱ በብርሃን ባለመተካቱ ልቡ ፈራ ተባ እያለ ጉዞውን ቀጠለ፡፡
የአራት ልጆች አባት የሆነው ጓንጉል ቢሆነኝ አዲስ አበባ የመጣው ያደለባቸውን ሁለት ሠንጋዎች ወልዲያ ገበያ ሸጦ ባገኘው ገንዘብ ለሚስቱና ለልጆቹ ልብስና ጫማ ለራሱ ደግሞ የፋሲካን በዓል መዋያ ልብስ
አማርጦ በርካሽ ዋጋ ገዝቶ ቀሪውን ገንዘብ ለልዩ ልዩ ችግሮች ማቃለያ ሊያደርግና በኮተቤ መምህራን ማሰልጠኛ የመጀመሪያ አመት ተማሪ የሆነችው የታናሽ እህቱን ልጅ ሊጠይቅ በዚያውም የኢትዮጵያ ዋና ከተማ የሆነችው አዲስ አበባን ሊጎበኛት ነው።
በዚሁ መሠረት ጣጣውን ጨርሶ ለአራቱ ልጆቹ ልብስ ሲያማርጥ ቆይቶ ሻንጣ ገዝቶ ከቆጣጠረና አዳሩን ዘውዲቱ ሆቴል ካደረገ በኋላ ወደ ቤተሰቦቹ ለመገስገስ ከዚያም ቤት ደርሶ ልጆቹና ሚስቱ ከበውት ሲንጫጩ የኔ ያምራል የኔ ይበልጣል እያሉ ህፃናቱ እርስ በርሳቸው ሲሟገቱ፣ሚስቱ ደግሞ የገዛላትን ቀሚስ እየላካች ረዝሞ ከሆነ ሰነፍ ልኬን እንኳን
የማታውቅ? ስትለው፣ ልኳ ከሆነ ደግሞ እሰይ የኔ አንበሳ” ብላ ስታደንቀው፣ ጉንጬን ሳም ስታደርገው በሀሳቡ እየታየው ቶሎ ሊደርስላቸው ነበር ለሊቱ አልነጋልህ ብሎት ዐይኑ ፈጥጦ ያደረውና ከለሊቱ ለአሥራ
አንድ ሰዓት ሩብ ጉዳይ ያውም የረፈደበት መስሎት ልብሱን በፍጥነት ለባብሶ የወጣው...
ጓንጉል ምንሽንሽን ሲያየው በድንገጤ እግሩ ተሽመደመደበት እንደዚህ አይነት አጋንንት መሳይ ሰው ሚልኪው ጥሩ አይደለም አለ በልቡ። የሰው ዘር ሳያይ ዐይኑ ያረፈው በእብዱ ላይ ነበር። እብዱ ምንሽንሽ ወደሱ እንደመጠጋት ብሎ ፊት ለፊት ሲመጣበት በድንጋጤ ወደ ግራ
በኩል እሸሻለሁ ሲል አደናቀፈው።
“ወንዱ!” አለና ፎክሮ ተንገዳገደ። እብዱ ጠጋ አለውና እጁን ዘረጋለት።
ፍራንክ እንደሚጠይቀው አወቀ። ወይ ይቺ ፍራንክ? አለ በልቡ።እብዱም፣ጤነኛውም፣አዋቂውም፣ ህፃኑም ሁሉም ይወዷታል ሲል ተገረመ::
የመጨረሻዋ የስድስት ወር ህፃን ልጁ እንኳን ወሪቀት በግራ እጁ ብር በቀኝ እጁ ይዞ ሲያስጠጋላት እጅዋ ወደ ቀኝ እጁ ነበር የሄደው። ይሄን አስታወሰና ትንሽ እንደ መሳቅ ብሎ እጁን ወደ ኪሱ ከተተና ያገኘውን ድፍን ሃያ አምስት ሣንቲም ኣውጥቶ ወረወረለት። ምንሽንሽ ሳንቲሟን
ለማንሳት ጐንበስ ሲል እሱ ደግሞ አውቶቡሱ እንዳያመልጠው በሩጫ ዳገቱን ተያያዘው፡፡
የሆነ ነገር ውልብ አለበት፡፡ የሰው ቁመና መስለው። ከግራ ወደ ቀኝ
የሮጠ ነገር ነበር፡፡
“ጅብ ነው! ጅብ መሆን አለበት። ከወዲህኛው ገደል ዘሎ ወደዚያኛው መግባቱ ነው! ልክ ነው አውሬ መሆን አለበት! አቋረጠኝ እኮ ልክ ነው ደግሞ ጠቆር ያለ ነገር ነው! ወይኔ ዛሬ እግዚአብሔር ከዚህ ጉድ ያውጣኝ እንጂ ያጋጠመኝን ሁሉ ቤት ገብቼ ለሚስቴ ነው የማጫውታት፡፡ ገና በጠዋቱ ቀንዳም ጋኔን የመሰለ እብድ ለከፈኝ እሱን ሳልፍ ደግሞ ይኸውና ጥቁር ጅብ አቋረጠኝ። እግዚአብሔር ያውቃል” እያለ በልቡ እያወራ ወደ ድልድዩ ተጠጋ፡፡ ሰግጠጥ እንደማለት
አደረገው። ድልድዩ ላይ ሲደርስ ከበደው፡፡ ገልመጥ፣ ገልመጥ አለ። ሰላም ይመስላል። ፀጥ ረጭ ብሏል። ብቅ ብቅ ብለው መታየት የጀመ ሩት ሰዎች በተለያየ አቅጣጫ ሄደዋል። በዚያ መንገድ ላይ ተፍ ተፍ የሚለው እሱ ብቻ ነበር፡፡
“ስው ሊሆን አይችልም፡፡ በዚህ ሰዓት ሰው እዚህ ድንጋይ ውስጥ እገደል ስር ምን ይሰራል? ሰው አይደለም አውሬ መሆን አለበት...” ፈራ ተባ እያለ ወደ ድልድዩ ገባ፡፡ እንደፈራው አይደለም፡፡ ምንም ነገር የለም።
ወደ ኋላው ገልመጥ ብሎ አየ፡፡ እብዱ በተሰጠው ሳንቲም ተደስቶ እየዘለለ ወደ አራት ኪሎ ሲያቀና ተመለከተው፡፡ አካባቢው ጭር.እረጭ...ያሉ የሞት ጥላ የሚያንዣብብበት መሰለ፡፡ ሁለቱን ሠንጋዎቹን ሸጦ ሸቀጣ ሸቀጥ ከሽመተበት ሌላ በኪሱ ውስጥ ሁለት መቶ አርባ ብር ቀርታዋለች፡፡
እሷንም ጥሩ ቦታ አስቀምጧታል፡፡ መጀመሪያ ከሱሪው ኪስ ከተታት፡፡ ደስ አላለውም፡፡ ወደ ኮቱ የውስጥ ኪስ ወሰዳት። አላመናትም፡፡ የአንድ ዓመት ሙሉ የልፋቱ ውጤት እነዚያ ቤት ቤት የሚያካክሉ ሠንጋዎቹ የተለወጡባት ትንሽ ነገር ብትጠፋ ሁለት ሠንጋዎች ቀለጡ ማለት ነው። በየኪሱ ሁሉ አዟዟራት። በመጨረሻ ላይ ጥሩ የማስቀመጫ ቦታ አገኘላት። በጥንቃቄ የሚደብቀበት አስተማማኝ ቦታ! ወደ ጫማው ወረደ። እንደገና እጁን መለሰው። አሁንም አሰላስለ። ፊቱ ፈካ አለ፡፡የመጨረሻውን አስተማማኝ ቦታ አገኘላት። በመታጠቂያው ዘልቆ በውስጥ ሱሪው መካከል በደንብ አድርጐ አጣጥፎ ቀረቀራት። የአሁኑ ከፍተኛ ሥጋቱ ይቺኑ እንቅልፍ ያጣባትን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
#አዲስ_ዓለም
..የመንገዱ መብራቶች ተበላሽተው ብርሃን አይሰጡም። አካባቢው ፀጥ እረጭ ብሏል። ትናንትና ማታ እስከ ስድስት ሰዓት የነበረው ጩኸት፣ ሁካታ የሰካራሞች ልፍለፋ፣ የሴተኛ አዳሪዎች ስድብ፣ በየቀይ መብራቱ ውስጥ የነበዙ ጠጪዎች ዳንኪራና ጭፈራ ትርምሱ ሁሉ እዚህ ቦታ
የነበረ መሆኑ የሚያጠራጥር ነው፡፡ የሥጋ ቤቶቹ ብርሃን ድምቀት፣ከቡና ቤት ቡና ቤት የሚያማርጠው ጠጪ ብዛት፣ የሙዚቃው ጩኽትና የመኪናው ኳኳታ ጆሮ ሲያደነቁር እንዳላመሽ ሁሉ እንደዚህ እንደ አሁኑ እረጭ ብሎ ሲታይ በግርግርና በፀጥታ መካከል ያለውን ልዩነት
ለማሳየት ደፈጣ የያዘ ይመስል ነበር፡፡
የወዳደቀ አጥንት ለመለቃቀም የሚያነፈንፉ ውሾች ውር ውር
ይላሉ፡፡ በዚህ ሁሉ ጊዜ ውስጥ ግን ያን ሰው የማይታይበትን አካባቢ ፀጥታ በማደፍረስ የጠዋት ገበያዋን ለመላፍ የተጣደፈች ታክሲ ከእሪ በከንቱ ወደ አራት ኪሎ አቅጣጫ በረረች፡፡ በዚያው ቅጽበት ደግሞ
ቁልቁል ከፒያሳ ወደ እሪ በከንቱ እየዘለለ የሚወርድ ሰው ታዬ። መላ ሰውነቱን ሬንጅና ጥላሸት የተቀባ ፀጉሩ እዚህም እዚያም ተገምዶ እንደ ጭራሮ የቆመ፣ ጎድኖቹ ሥጋ ባልለበሰ አጥንት የገጠጡት እብዱ ምን ሽንሽ! ብቻውን በመንገዱ ግራና ቀኝ ቱር ቱር እያለ እየተሯሯጠ ሽቅብ
ይወጣል ቁልቁል ይወርዳል። ዐይኖቹ እንደ በርበሬ ቀልተው ለተመልካች ያስፈራራሉ። ከወገቡ በታች እዚህም እዚያም የተቦጫጨቀ ሱሪ መልበስ
ከተባለ ለብሷል። ቆም ይልና ድንጋይ ይፈነቅላል ያነሳውን መልሶ ይወረውረዋል። ደግሞ ወደታች ይወርዳል። ከዚያም ጉንበስ ይልና የሲጋራ ቁራጭ ለመልቀም ያነፈንፋል።እንደገና ወደ ላይ ይወጣል። የዚያ አስፈሪ
የጨለማ ንጉሥ ሁሉም በየቤቱ በተከተተበት ሰዓት እሱ እየዘለለና እየቦረቀ ብቻውን በየመንገዱ ላይ ሲሯሯጥ ምሽቱን ለብርሃን ለማስረከብ የተዘጋጀ ባለሥልጣን ይመስል ነበር።
ከለሊቱ አሥራ አንድ ሰዓት ሆኗል። ወደየጠቅላይ ግዛቱ የሚጓዙ መንገደኞች አውቶቡስ ተራ ለመድረስ በዋናው አስፋልት መንገድ ላይ ብቅ ብቅ ብለዋል። በዚያ ሰዓት በእግር የሚጓዝ መንገደኛ አንድም በራሱ የተማመነ አሊያም ከወሮበላና ከማጅራት መቺው ሰይፍ እግዚአብሔር እንዲጠብቀው በልቡ ፀሎት እያደረስ በፍርሃት የሚራመድበት እንጂ ልቡ
በድፍረት ተሞልቶ የሚንቀሳቀስበት ሰዓት አልነበረም፡፡ ለሁሉ ነገር ግድ
የለሌው ለማጅራት መቺው ለብርዱ ለፀሀዩ ለሞትም ለህይወትም ደንታ የሌለው እብዱ ምንሽንሽ ብቻ ነበር። የእሪ በከንቱን ድልድይ ተሻግሮ
ወደ አራት ኪሎ ሲያቀና አንድ ዕድሜው ከሰላሳ ስምንት እስከ አርባ አመት የሚገመት ወደ ወሎ ጠቅላይ ግዛት ለመሄድ የሚገስግስ ሰው ብቅ! አለ። ሰውዬው ምንሽንሽን ሲያየው “በስመአብ ወልድ ጌታዬ” አለና
አማተበ፡ የሰይጣን ቤት አጋፋሪ የመሰለውን እብድ ሲመለከት ከመንገዱ ፈንጠር አለና ወደ ዳር ወጣ፡፡ ካደረበት ከዘውዲቱ ሆቴል ቁልቁል ወደ እሪ በከንቱ የሚወስደውን መንገድ ሲጀምረው ዳፍንቱ በብርሃን ባለመተካቱ ልቡ ፈራ ተባ እያለ ጉዞውን ቀጠለ፡፡
የአራት ልጆች አባት የሆነው ጓንጉል ቢሆነኝ አዲስ አበባ የመጣው ያደለባቸውን ሁለት ሠንጋዎች ወልዲያ ገበያ ሸጦ ባገኘው ገንዘብ ለሚስቱና ለልጆቹ ልብስና ጫማ ለራሱ ደግሞ የፋሲካን በዓል መዋያ ልብስ
አማርጦ በርካሽ ዋጋ ገዝቶ ቀሪውን ገንዘብ ለልዩ ልዩ ችግሮች ማቃለያ ሊያደርግና በኮተቤ መምህራን ማሰልጠኛ የመጀመሪያ አመት ተማሪ የሆነችው የታናሽ እህቱን ልጅ ሊጠይቅ በዚያውም የኢትዮጵያ ዋና ከተማ የሆነችው አዲስ አበባን ሊጎበኛት ነው።
በዚሁ መሠረት ጣጣውን ጨርሶ ለአራቱ ልጆቹ ልብስ ሲያማርጥ ቆይቶ ሻንጣ ገዝቶ ከቆጣጠረና አዳሩን ዘውዲቱ ሆቴል ካደረገ በኋላ ወደ ቤተሰቦቹ ለመገስገስ ከዚያም ቤት ደርሶ ልጆቹና ሚስቱ ከበውት ሲንጫጩ የኔ ያምራል የኔ ይበልጣል እያሉ ህፃናቱ እርስ በርሳቸው ሲሟገቱ፣ሚስቱ ደግሞ የገዛላትን ቀሚስ እየላካች ረዝሞ ከሆነ ሰነፍ ልኬን እንኳን
የማታውቅ? ስትለው፣ ልኳ ከሆነ ደግሞ እሰይ የኔ አንበሳ” ብላ ስታደንቀው፣ ጉንጬን ሳም ስታደርገው በሀሳቡ እየታየው ቶሎ ሊደርስላቸው ነበር ለሊቱ አልነጋልህ ብሎት ዐይኑ ፈጥጦ ያደረውና ከለሊቱ ለአሥራ
አንድ ሰዓት ሩብ ጉዳይ ያውም የረፈደበት መስሎት ልብሱን በፍጥነት ለባብሶ የወጣው...
ጓንጉል ምንሽንሽን ሲያየው በድንገጤ እግሩ ተሽመደመደበት እንደዚህ አይነት አጋንንት መሳይ ሰው ሚልኪው ጥሩ አይደለም አለ በልቡ። የሰው ዘር ሳያይ ዐይኑ ያረፈው በእብዱ ላይ ነበር። እብዱ ምንሽንሽ ወደሱ እንደመጠጋት ብሎ ፊት ለፊት ሲመጣበት በድንጋጤ ወደ ግራ
በኩል እሸሻለሁ ሲል አደናቀፈው።
“ወንዱ!” አለና ፎክሮ ተንገዳገደ። እብዱ ጠጋ አለውና እጁን ዘረጋለት።
ፍራንክ እንደሚጠይቀው አወቀ። ወይ ይቺ ፍራንክ? አለ በልቡ።እብዱም፣ጤነኛውም፣አዋቂውም፣ ህፃኑም ሁሉም ይወዷታል ሲል ተገረመ::
የመጨረሻዋ የስድስት ወር ህፃን ልጁ እንኳን ወሪቀት በግራ እጁ ብር በቀኝ እጁ ይዞ ሲያስጠጋላት እጅዋ ወደ ቀኝ እጁ ነበር የሄደው። ይሄን አስታወሰና ትንሽ እንደ መሳቅ ብሎ እጁን ወደ ኪሱ ከተተና ያገኘውን ድፍን ሃያ አምስት ሣንቲም ኣውጥቶ ወረወረለት። ምንሽንሽ ሳንቲሟን
ለማንሳት ጐንበስ ሲል እሱ ደግሞ አውቶቡሱ እንዳያመልጠው በሩጫ ዳገቱን ተያያዘው፡፡
የሆነ ነገር ውልብ አለበት፡፡ የሰው ቁመና መስለው። ከግራ ወደ ቀኝ
የሮጠ ነገር ነበር፡፡
“ጅብ ነው! ጅብ መሆን አለበት። ከወዲህኛው ገደል ዘሎ ወደዚያኛው መግባቱ ነው! ልክ ነው አውሬ መሆን አለበት! አቋረጠኝ እኮ ልክ ነው ደግሞ ጠቆር ያለ ነገር ነው! ወይኔ ዛሬ እግዚአብሔር ከዚህ ጉድ ያውጣኝ እንጂ ያጋጠመኝን ሁሉ ቤት ገብቼ ለሚስቴ ነው የማጫውታት፡፡ ገና በጠዋቱ ቀንዳም ጋኔን የመሰለ እብድ ለከፈኝ እሱን ሳልፍ ደግሞ ይኸውና ጥቁር ጅብ አቋረጠኝ። እግዚአብሔር ያውቃል” እያለ በልቡ እያወራ ወደ ድልድዩ ተጠጋ፡፡ ሰግጠጥ እንደማለት
አደረገው። ድልድዩ ላይ ሲደርስ ከበደው፡፡ ገልመጥ፣ ገልመጥ አለ። ሰላም ይመስላል። ፀጥ ረጭ ብሏል። ብቅ ብቅ ብለው መታየት የጀመ ሩት ሰዎች በተለያየ አቅጣጫ ሄደዋል። በዚያ መንገድ ላይ ተፍ ተፍ የሚለው እሱ ብቻ ነበር፡፡
“ስው ሊሆን አይችልም፡፡ በዚህ ሰዓት ሰው እዚህ ድንጋይ ውስጥ እገደል ስር ምን ይሰራል? ሰው አይደለም አውሬ መሆን አለበት...” ፈራ ተባ እያለ ወደ ድልድዩ ገባ፡፡ እንደፈራው አይደለም፡፡ ምንም ነገር የለም።
ወደ ኋላው ገልመጥ ብሎ አየ፡፡ እብዱ በተሰጠው ሳንቲም ተደስቶ እየዘለለ ወደ አራት ኪሎ ሲያቀና ተመለከተው፡፡ አካባቢው ጭር.እረጭ...ያሉ የሞት ጥላ የሚያንዣብብበት መሰለ፡፡ ሁለቱን ሠንጋዎቹን ሸጦ ሸቀጣ ሸቀጥ ከሽመተበት ሌላ በኪሱ ውስጥ ሁለት መቶ አርባ ብር ቀርታዋለች፡፡
እሷንም ጥሩ ቦታ አስቀምጧታል፡፡ መጀመሪያ ከሱሪው ኪስ ከተታት፡፡ ደስ አላለውም፡፡ ወደ ኮቱ የውስጥ ኪስ ወሰዳት። አላመናትም፡፡ የአንድ ዓመት ሙሉ የልፋቱ ውጤት እነዚያ ቤት ቤት የሚያካክሉ ሠንጋዎቹ የተለወጡባት ትንሽ ነገር ብትጠፋ ሁለት ሠንጋዎች ቀለጡ ማለት ነው። በየኪሱ ሁሉ አዟዟራት። በመጨረሻ ላይ ጥሩ የማስቀመጫ ቦታ አገኘላት። በጥንቃቄ የሚደብቀበት አስተማማኝ ቦታ! ወደ ጫማው ወረደ። እንደገና እጁን መለሰው። አሁንም አሰላስለ። ፊቱ ፈካ አለ፡፡የመጨረሻውን አስተማማኝ ቦታ አገኘላት። በመታጠቂያው ዘልቆ በውስጥ ሱሪው መካከል በደንብ አድርጐ አጣጥፎ ቀረቀራት። የአሁኑ ከፍተኛ ሥጋቱ ይቺኑ እንቅልፍ ያጣባትን
👍3
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...በአረቄና በጠላ ሽያጭ የሚተዳደሩት እማማ ወደር የለሽ ከጐረቤታቸው ከወይዘሮ አረጋሽ ጋር ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያንን ተሳልመው እየተመለሱ
ነበር፡፡ አሳዛኙ ጓንጉል ጨሌ ያጣች ሚዳቋ መስሎ አፉን ከፍቶ ድልድዩ ላይ ተቀምጧል። አላፊ አግዳሚውን በዐይኖቹ ይማፀናል። ችግሩን ጠይቀው አዝነው አንድ መፍትሄ እንዲሰጡት በአጠገቡ ሰው ካለፈ ዕይኖቹን ክርትት ክርትት ያደርጋቸዋል። ቀርቦ የሚያናግር ችግሩ ምን
እንደሆነ የሚጠይቀው ስው ግን አጣ፡፡ “አይዞህ!” የምትለው ቃል ብቻ ለሱ እንደዚያ ልቡ በሀዘን ተሰበረ ሰው ትልቅ የማፅናኛ የተስፋ ቃል ነበረች፡፡ ሌላው ሁሉ ቀርቶ ያቺ የራቀችበትን “የአይዞህ ወንድሜን” ቃል የሚለግሰውና በሃዘን ከንፈሩን የሚመጥለት አንድ ሰው እንኳን በማጣቱ
እየተንገበገበ የእንባ እጢው እስከሚደርቅ ድረስ አለቀሰ፡፡ ወይዘሮ ወደሬ ግን እንደሌላው ዝም ብለው አላለፉትም፡፡
“ውይ በሞትኩት! ይሄ ሰው ምን ነክቶት ነው እንደ ሴት ልጅ እንባ
ውን የሚያፈስው? ወይ ወንድሜ ምን አጋጥሞት ይሆን በሌሊት እዚህ ተቀምጦ እንባውን የሚረጨው?” አሉና ጠጋ አሉት። ከዚያ ሁሉ ሰው መካከል እማማ ወደሬን ጣለለት። “የኔ ወንድም ችግርህ ምንድነው?”ብሎ አንጀቱ የተቃጠለበትን ምክንያት እንዲተነፍስ ዕድል የሰጠው ሰው
አንድ ወይዘሮ ወደሬን በማግኘቱ ደስ አለው። የደረሰበትን አሳዛኝ አደጋ ተናግሮ ምንም ባያደርጉለት እንኳ ከንፈራቸውን የሚመጡለት ጠያቂ በማግኘቱ ደስ ቢለውም ሆዱ ባባና ፊቱ በሀዘን ተከፋ።
ምን ሆነሃል ወንድሜ? በለሊቱ እዚህ ተቀምጠህ ታለቅሳለህሳ?” ብለው ጠየቁት ፡፡ ወይዘሮ አረጋሽም ፈራ ተባ እያሉ
እየተጠራጠሩ ወይዘሮ ወደሬን ተከትለው ወደ ጓንጉል አመሩ።
“ደህናም አይደለህ እንዴ የኔ ወንድም? ምን ችግር ገጠመህ?” ሲሉ እሳቸውም አክለው ጠየቁት፡፡
ምን ደህንነት አለኝ እናቶች? ምን ደህንነት? ምን አገር? ምን ሰው
አለና ደህና እሆናለሁ?” ቁዝም አለ፡፡ ሁለቱም እርስ በርሳቸው ተያዩ። የስውዬው ሁኔታ አሳዝኗቸዋል።
የምንረዳህ ነገር ካለ የሆንከውን ብትነግረን?” አሉ ወይዘሮ ወደሬ፡፡
የለም የኔ እናቶች አትቸገሩ እሱ ያመጣብኝን ጣጣ እሱ እስኪመልስልኝ ድረስ ጉዴን ለብቻዬ እሸከመዋለሁ። እናንተን የማስቸግርበት ምክንያት
የለም፡፡ ወይኔ ጓንጉል? ወይኔ ልጆቼ? ወይ ሚስቴ?! ” ስሙን ሲናገር ወይዘሮ ወደሬ ተጠራጠሩ።
“ከየት አገር ነው የመጣኸው? የዚሁ የአዲስ አበባ ስው ነህ? ወይስ ከጠቅላይ ግዛት?” የአማርኛ አጣጣል ዘዬው እሳቸው የገመቱት አገር ሰው መሆኑን ይመሰክራል።
“ኸወሉ” አለ ጓንጉል።
“ወይኔ! እኔን አፈር ይብላኝ፡፡ የኔው አገር ስው ነሃ! አፈር ስሆን ምን
ሁነህ ነው?ለመሆኑ ወሎ እምኑ ጋ?”
“ወልዲያ!”
“ኸረገኝና እናንተ ሆዬ የኔው ሰው ነሃ! እነ አያ እገሌን እነ እገሊትን ታውቃለህ?” የቅርብና የሩቅ ዘመዶቻቸውን ስም እየጠሩ ጠየቁት።
ጭውውቱ ቀጠለ፡፡ እሳቸው የሚጠራቸውን ሰዎች በብዛት የሚያውቃቸው ነበሩ፡፡ ወይዘሮ ወደሬ በጣም ደስ አላቸው፡፡
“በል እስቲ የሆንከውን ንገረኝእማ ለካ የኔው ሰው ሁነህ ኑሯል አንጀቴን የበላኸው? በል አሁን አንድም ሳትደብቅ ንገረኝ ሌባ ነጠቀህ? ወይስ ምን ሆንክ?”
“ሌባም አይደለም እናቴ እንደዚህ አይነት ሌብነት አይቼም ሰምቼም አላውቅም፡፡ ጅቦች ናቸው የበሉኝ፡፡ ጅቦች! ህይወቴን እስከምስት ድረስ ማጅራቴን መትተው ከጣሉኝ በኋላ ተቀራምተውኝ ሄዱ። አይ እኔ? ወይ ድካሜ?”
“በል አሁን ተዚህ ተነሳና እቤት አረፍ ብለህ አዋይሃለሁ” እጁን ሳብ አደረጉት። ሳይደግስ አይጣላም፡፡ ከዚያ ሁሉ ህዝብ መካከል የአገሩን ልጅ ወይዘሮ ወደሬን አምጥቶ ለጣለለት አምላክ ምስጋና በልቡ አደረሰና አብሯቸው ማዝገም ጀመረ። ከቤት ሲደርሱ ወይዘሮ ወደሬ ያቀረቡለትን እንጀራ በበርበሬ አፍ አውጥቶ መጮህ ወደ ጀመረው ሆዱ ቁልቁል ይልከው ጀመር፡፡ በደንብ አድርጉ እስከሚጠግብ ድረስ በላ፡፡ በጣሳ የቀረበለትን ጠላ ጠጣ፡፡ “
እፎይ..” አለና የሆነውን ሁሉ ያጫውታቸው ጀመር፡፡
“አይ ልጄ? ወንድሜን! አይ አለማወቅ? በለሊቱ ገስግስህ በተከፈተ አፋቸው ውስጥ ስተት ብለህ ገባህላቸው? ለመሆኑ በስንት ሰዓት ላይዐነው እንደዚህ ጉድ ያደረጉህ?”
“እኔማ ኦቶቡስ እንዳያመልጠኝ መጣደፌ ነበር ለካ ለሊቱን ሙሉ እንቅልፌን አጥቼ ያደርኩት የነሱ ሲሳይ ለመሆን ነበር?”
“አይ የኔ ልጅ ጉድ አደረጉህ አይደለም? ለመሆኑ ምን ያክል ቀሙህ?”አሉ ወይዘሮ ወደሬ ለራሳቸው ጠላ በብርጭቆ ቀድተው በርጩማቸው
ላይ እየተቀመጡ።
“እባክዎት ልፋቴን ድካሜን ሁሉ ውሃ በላው። ሁለት ዓመት ሙሉ የቀለብኳቸው ሠንጋዎች ቀለጡ” አለና ፊቱ በንዴት ጠቆረ።
“በጥሬ ገንዘብ ሁለት መቶ አርባ ብር፡፡ ሌላውን ይተዉት። ለልጆቼ፣
ለሚስቴ፣ለራሴም የገዛኋቸው ልብሶች ከነሙሉ ሻንጣው" የአገራቸው ልጅ ጓንጉል በለሊት ተነስቶ የጩሉሌዎች ሲሳይ መሆኑ በጣም አሳዘናቸው። በተቻላቸው አቅም ሊረዱት ፈለጉ። ጓንጉል ዕድለኛ ሆነና ውሃ የሚያጠጣው ችግሩን የሚካፈልለት ሰው አገኘ፡፡
“ለመሆኑ እማማ? እንዲያው አዲስ አበባ ውስጥ ስው እንደፈለገው መውጣት መግባት አይችልም ማለት ነው? እንኳንስ በንጋቱ በጠዋቱ ይቅርና በውድቀት ጨለማ ሲሄድ ቢያድር መንግሥት ባለበት አገር
እንዴት እንደዚህ ያለው ዓይን ያወጣ ዝርፊያ ይፈፀማል? እንዴ?!
እንዴ?! እንዴ?!” ግርም፣ ድንቅ አለው፡፡
“አይ ልጀ አዲስ አበባ እንደ አገር ቤት መስሎሃል? አዲስ አበባ እኮ
ሁሉም ዓይነት ሰው የተሰበሰበበት አገር ነው። እንደኔ ለፍቶ አዳሪው
እንዳለ ሁሉ ስላቢው፣ ቡዳው፣ ቀማኛው፣ቤት ሰርሳሪው፣ ነፍሰ ገዳዩ ፣ማጅራት መቺው ምኑን ትቼ ምኑን ልንገርህ? ሁሉም አይነት የተጠረቃቀመበት የጉድ አገር ነው። በቀማኛውና በማጅራት መቺው አለመቀደም እንጂ አንዴ ከተቀደሙ ምን ማድረግ ይቻላል? እንኳንም ህይወትህ ተረፈ እንኳንም የልጆችህ አምላክ ከጉድ አወጣህ እንጂ ገድለውህስ ቢሆን ኖሮ? ማን ይይዛቸው ነበር? ገንዘብ ምንአባቱ አንተ እስካለህ
ድረስ ነገ ተነገ ወዲያ ሰርተህ ትተካዋለህ” የአሮጊቷ ምክር ልቡን መለስ አደረገው፡፡ እውነትም ማጅራቱን ብለውት እንደወደቀ በዚያው ቅርት ቢልስ? ልጆቹ ያለ አባት ሊቀሩ ትዳሩ ሊፈርስ ነበር ማለት ነው።
“ሆቸ ጉድ!” ነገ ተነገ ወዲያ እንዳሉት እሱ በህይወት እስካለ ድረስ የሚተካው ገንዘብ ነው። ወይ የፈጣሪ ሥራ ይህም አለ ለካ? በአንዱ ሲያማርሩ ይብስን አታምጣን ማስብ ትልቅ ነገር ነው ሲል ተፅናና፡፡ ዳሩ አንድ ጊዜ ቀልጦ ለቀረ ገንዘብ ሲብከነከን ምን ዋጋ አለው? በፍርድ ቤት
ተሟግቶ ነጣቂውን አስይዞ ለማስመለስ የሌቦቹ ፍንጭና ዱካ አይታወቅም፡፡ ቢያለቅስ ቢዘል ቢፈርጥ ምን ዋጋ አለው? ይህን ሁሉ ቀስ በቀስ ማስብ ማሰላሰል ጀመረ።
“አሁን ለመሳፈሪያ የሚሆን ምንም የለህም አይደል?” በሃሣቡ የሚጉላላ ችግሩን ተረድተው ሲጠይቁት ደስ አለው። የውለታቸው ነገር ከብዶት
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...በአረቄና በጠላ ሽያጭ የሚተዳደሩት እማማ ወደር የለሽ ከጐረቤታቸው ከወይዘሮ አረጋሽ ጋር ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያንን ተሳልመው እየተመለሱ
ነበር፡፡ አሳዛኙ ጓንጉል ጨሌ ያጣች ሚዳቋ መስሎ አፉን ከፍቶ ድልድዩ ላይ ተቀምጧል። አላፊ አግዳሚውን በዐይኖቹ ይማፀናል። ችግሩን ጠይቀው አዝነው አንድ መፍትሄ እንዲሰጡት በአጠገቡ ሰው ካለፈ ዕይኖቹን ክርትት ክርትት ያደርጋቸዋል። ቀርቦ የሚያናግር ችግሩ ምን
እንደሆነ የሚጠይቀው ስው ግን አጣ፡፡ “አይዞህ!” የምትለው ቃል ብቻ ለሱ እንደዚያ ልቡ በሀዘን ተሰበረ ሰው ትልቅ የማፅናኛ የተስፋ ቃል ነበረች፡፡ ሌላው ሁሉ ቀርቶ ያቺ የራቀችበትን “የአይዞህ ወንድሜን” ቃል የሚለግሰውና በሃዘን ከንፈሩን የሚመጥለት አንድ ሰው እንኳን በማጣቱ
እየተንገበገበ የእንባ እጢው እስከሚደርቅ ድረስ አለቀሰ፡፡ ወይዘሮ ወደሬ ግን እንደሌላው ዝም ብለው አላለፉትም፡፡
“ውይ በሞትኩት! ይሄ ሰው ምን ነክቶት ነው እንደ ሴት ልጅ እንባ
ውን የሚያፈስው? ወይ ወንድሜ ምን አጋጥሞት ይሆን በሌሊት እዚህ ተቀምጦ እንባውን የሚረጨው?” አሉና ጠጋ አሉት። ከዚያ ሁሉ ሰው መካከል እማማ ወደሬን ጣለለት። “የኔ ወንድም ችግርህ ምንድነው?”ብሎ አንጀቱ የተቃጠለበትን ምክንያት እንዲተነፍስ ዕድል የሰጠው ሰው
አንድ ወይዘሮ ወደሬን በማግኘቱ ደስ አለው። የደረሰበትን አሳዛኝ አደጋ ተናግሮ ምንም ባያደርጉለት እንኳ ከንፈራቸውን የሚመጡለት ጠያቂ በማግኘቱ ደስ ቢለውም ሆዱ ባባና ፊቱ በሀዘን ተከፋ።
ምን ሆነሃል ወንድሜ? በለሊቱ እዚህ ተቀምጠህ ታለቅሳለህሳ?” ብለው ጠየቁት ፡፡ ወይዘሮ አረጋሽም ፈራ ተባ እያሉ
እየተጠራጠሩ ወይዘሮ ወደሬን ተከትለው ወደ ጓንጉል አመሩ።
“ደህናም አይደለህ እንዴ የኔ ወንድም? ምን ችግር ገጠመህ?” ሲሉ እሳቸውም አክለው ጠየቁት፡፡
ምን ደህንነት አለኝ እናቶች? ምን ደህንነት? ምን አገር? ምን ሰው
አለና ደህና እሆናለሁ?” ቁዝም አለ፡፡ ሁለቱም እርስ በርሳቸው ተያዩ። የስውዬው ሁኔታ አሳዝኗቸዋል።
የምንረዳህ ነገር ካለ የሆንከውን ብትነግረን?” አሉ ወይዘሮ ወደሬ፡፡
የለም የኔ እናቶች አትቸገሩ እሱ ያመጣብኝን ጣጣ እሱ እስኪመልስልኝ ድረስ ጉዴን ለብቻዬ እሸከመዋለሁ። እናንተን የማስቸግርበት ምክንያት
የለም፡፡ ወይኔ ጓንጉል? ወይኔ ልጆቼ? ወይ ሚስቴ?! ” ስሙን ሲናገር ወይዘሮ ወደሬ ተጠራጠሩ።
“ከየት አገር ነው የመጣኸው? የዚሁ የአዲስ አበባ ስው ነህ? ወይስ ከጠቅላይ ግዛት?” የአማርኛ አጣጣል ዘዬው እሳቸው የገመቱት አገር ሰው መሆኑን ይመሰክራል።
“ኸወሉ” አለ ጓንጉል።
“ወይኔ! እኔን አፈር ይብላኝ፡፡ የኔው አገር ስው ነሃ! አፈር ስሆን ምን
ሁነህ ነው?ለመሆኑ ወሎ እምኑ ጋ?”
“ወልዲያ!”
“ኸረገኝና እናንተ ሆዬ የኔው ሰው ነሃ! እነ አያ እገሌን እነ እገሊትን ታውቃለህ?” የቅርብና የሩቅ ዘመዶቻቸውን ስም እየጠሩ ጠየቁት።
ጭውውቱ ቀጠለ፡፡ እሳቸው የሚጠራቸውን ሰዎች በብዛት የሚያውቃቸው ነበሩ፡፡ ወይዘሮ ወደሬ በጣም ደስ አላቸው፡፡
“በል እስቲ የሆንከውን ንገረኝእማ ለካ የኔው ሰው ሁነህ ኑሯል አንጀቴን የበላኸው? በል አሁን አንድም ሳትደብቅ ንገረኝ ሌባ ነጠቀህ? ወይስ ምን ሆንክ?”
“ሌባም አይደለም እናቴ እንደዚህ አይነት ሌብነት አይቼም ሰምቼም አላውቅም፡፡ ጅቦች ናቸው የበሉኝ፡፡ ጅቦች! ህይወቴን እስከምስት ድረስ ማጅራቴን መትተው ከጣሉኝ በኋላ ተቀራምተውኝ ሄዱ። አይ እኔ? ወይ ድካሜ?”
“በል አሁን ተዚህ ተነሳና እቤት አረፍ ብለህ አዋይሃለሁ” እጁን ሳብ አደረጉት። ሳይደግስ አይጣላም፡፡ ከዚያ ሁሉ ህዝብ መካከል የአገሩን ልጅ ወይዘሮ ወደሬን አምጥቶ ለጣለለት አምላክ ምስጋና በልቡ አደረሰና አብሯቸው ማዝገም ጀመረ። ከቤት ሲደርሱ ወይዘሮ ወደሬ ያቀረቡለትን እንጀራ በበርበሬ አፍ አውጥቶ መጮህ ወደ ጀመረው ሆዱ ቁልቁል ይልከው ጀመር፡፡ በደንብ አድርጉ እስከሚጠግብ ድረስ በላ፡፡ በጣሳ የቀረበለትን ጠላ ጠጣ፡፡ “
እፎይ..” አለና የሆነውን ሁሉ ያጫውታቸው ጀመር፡፡
“አይ ልጄ? ወንድሜን! አይ አለማወቅ? በለሊቱ ገስግስህ በተከፈተ አፋቸው ውስጥ ስተት ብለህ ገባህላቸው? ለመሆኑ በስንት ሰዓት ላይዐነው እንደዚህ ጉድ ያደረጉህ?”
“እኔማ ኦቶቡስ እንዳያመልጠኝ መጣደፌ ነበር ለካ ለሊቱን ሙሉ እንቅልፌን አጥቼ ያደርኩት የነሱ ሲሳይ ለመሆን ነበር?”
“አይ የኔ ልጅ ጉድ አደረጉህ አይደለም? ለመሆኑ ምን ያክል ቀሙህ?”አሉ ወይዘሮ ወደሬ ለራሳቸው ጠላ በብርጭቆ ቀድተው በርጩማቸው
ላይ እየተቀመጡ።
“እባክዎት ልፋቴን ድካሜን ሁሉ ውሃ በላው። ሁለት ዓመት ሙሉ የቀለብኳቸው ሠንጋዎች ቀለጡ” አለና ፊቱ በንዴት ጠቆረ።
“በጥሬ ገንዘብ ሁለት መቶ አርባ ብር፡፡ ሌላውን ይተዉት። ለልጆቼ፣
ለሚስቴ፣ለራሴም የገዛኋቸው ልብሶች ከነሙሉ ሻንጣው" የአገራቸው ልጅ ጓንጉል በለሊት ተነስቶ የጩሉሌዎች ሲሳይ መሆኑ በጣም አሳዘናቸው። በተቻላቸው አቅም ሊረዱት ፈለጉ። ጓንጉል ዕድለኛ ሆነና ውሃ የሚያጠጣው ችግሩን የሚካፈልለት ሰው አገኘ፡፡
“ለመሆኑ እማማ? እንዲያው አዲስ አበባ ውስጥ ስው እንደፈለገው መውጣት መግባት አይችልም ማለት ነው? እንኳንስ በንጋቱ በጠዋቱ ይቅርና በውድቀት ጨለማ ሲሄድ ቢያድር መንግሥት ባለበት አገር
እንዴት እንደዚህ ያለው ዓይን ያወጣ ዝርፊያ ይፈፀማል? እንዴ?!
እንዴ?! እንዴ?!” ግርም፣ ድንቅ አለው፡፡
“አይ ልጀ አዲስ አበባ እንደ አገር ቤት መስሎሃል? አዲስ አበባ እኮ
ሁሉም ዓይነት ሰው የተሰበሰበበት አገር ነው። እንደኔ ለፍቶ አዳሪው
እንዳለ ሁሉ ስላቢው፣ ቡዳው፣ ቀማኛው፣ቤት ሰርሳሪው፣ ነፍሰ ገዳዩ ፣ማጅራት መቺው ምኑን ትቼ ምኑን ልንገርህ? ሁሉም አይነት የተጠረቃቀመበት የጉድ አገር ነው። በቀማኛውና በማጅራት መቺው አለመቀደም እንጂ አንዴ ከተቀደሙ ምን ማድረግ ይቻላል? እንኳንም ህይወትህ ተረፈ እንኳንም የልጆችህ አምላክ ከጉድ አወጣህ እንጂ ገድለውህስ ቢሆን ኖሮ? ማን ይይዛቸው ነበር? ገንዘብ ምንአባቱ አንተ እስካለህ
ድረስ ነገ ተነገ ወዲያ ሰርተህ ትተካዋለህ” የአሮጊቷ ምክር ልቡን መለስ አደረገው፡፡ እውነትም ማጅራቱን ብለውት እንደወደቀ በዚያው ቅርት ቢልስ? ልጆቹ ያለ አባት ሊቀሩ ትዳሩ ሊፈርስ ነበር ማለት ነው።
“ሆቸ ጉድ!” ነገ ተነገ ወዲያ እንዳሉት እሱ በህይወት እስካለ ድረስ የሚተካው ገንዘብ ነው። ወይ የፈጣሪ ሥራ ይህም አለ ለካ? በአንዱ ሲያማርሩ ይብስን አታምጣን ማስብ ትልቅ ነገር ነው ሲል ተፅናና፡፡ ዳሩ አንድ ጊዜ ቀልጦ ለቀረ ገንዘብ ሲብከነከን ምን ዋጋ አለው? በፍርድ ቤት
ተሟግቶ ነጣቂውን አስይዞ ለማስመለስ የሌቦቹ ፍንጭና ዱካ አይታወቅም፡፡ ቢያለቅስ ቢዘል ቢፈርጥ ምን ዋጋ አለው? ይህን ሁሉ ቀስ በቀስ ማስብ ማሰላሰል ጀመረ።
“አሁን ለመሳፈሪያ የሚሆን ምንም የለህም አይደል?” በሃሣቡ የሚጉላላ ችግሩን ተረድተው ሲጠይቁት ደስ አለው። የውለታቸው ነገር ከብዶት
👍2
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....ወይዘሮ ወደሬ ከእሪ በከንቱ ወደ ፊት በር በሚወስደው መንገድ በስተግራ በኩል ከአፋፉ ላይ በመኖሪያና በመሸታ ቤትነት የሚጠቀሙበት ሁለት ክፍል ቤት አላቸው፡፡ አሻሻጫ ቀን ቀን በግርድና ማታ ማታ ደግሞ ልብሷን ቀያይራ፣ ፀጉሯን አበጣጥራ በሴተኛ አዳሪነት ብቅ የምትለው ጽጌ ነበረች፡፡ ጽጌ ከአካባቢዋ ሴተኛ አዳሪዎች ጋር ጥሩ መግባባት አላት። ኑሯቸውን እየኖረች ቀን ቀን የቤት ስራተኛ ማታ ማታ ደግሞ ሴተኛ አዳሪ እየሆነች ስትገለባበጥ ኖራለች።
ፅጌ ከኩሽና ንግስትነት እስከ አረግራጊው አልጋ ፊታውራሪነት... ሁለቱንም የህይወት ተሞክሮ እኩል እየኖረች ስፊ ልምድ ያዳበረች ሴት ነች።አዲሷ አሻሻጭ ሰላማዊት ወደ እማማ ወደሬ ቤት ከመምጣቷ በፊት ፅጌ ብቸኛዋ የወንዶች አይን ማረፊያ ነበረች። ሰላማዊት በአሻሻጭነት ስራ
ልትጀምር የአሮጊቷ የእማማ ወደሬን ቤት ከአራት አመታት በፊት ከተቀላቀለች በኋላ ግን የተፈላጊነት ደረጃዋ እያሽቆለቆለ ሄዶ ነበር ሰላማዊት የእማማ ወደሬ ጓደኛ የሆኑት የወይዘሮ አረጋሽ ልጅ የቅድስት ጓደኛ ስትሆን “ እማማ ወደሬ ቤት ይሻልሻል” ብላ ይዛት የሄደችው
ቅድስት ነበረች።
የአሻሻጭ ችግር የነበረባቸው እማማ ወደሬ ቀንበጥ የመሰለችው የቆፍጣናው ገበሬ ልጅ እቤታቸው ድረስ ሰተት ብላ የመጣችላቸው እለት ፈጣሪያቸውን አመሰገኑ። ገበያቸው በሰላማዊት ምክንያት ሲደራ፣ ሲጧጧፍ ደንበኞቻቸው መሸታ ቤቱን ሲያጣብቡት በሷ የአሻሻጭነት ተግባር ውስጥ የዕለት ገቢያቸው በእጥፍ ድርብ ሲጨምር ወለል ብሎ ታያቸው።
ደንበኞቻቸው ቦታ ቦታቸውን ይዘው እየጠጡ ነበር፡፡ በሞቅታ ሃይል
ግማሹ ይዘፍናል ከፊሉ የቤቱን ጣጣ፣ የሚስቱን ጉድ... የመሥሪያ ቤት ችግሩን... የአለቃውን ተንኮል....ሁሉም የየራሱን ወሬ ያወራል። የሰከረው ብዙውን ጊዜ ከማዳመጥ ይልቅ ማውራት ስለሚቀናው መደማመጥ ይጠፋና አውራው የጠፋበት የንብ መንጋ ይመስል አየሩ በጫጫታ
ይሞላል። የተጀመረው የወሬ ርዕስ መቋጫ ሳያገኝ ሌላ የወሬ ርዕስ ይከፈታል። እሱም በወጉ ሳይሰማ አዲስ ርዕስ ይጀመራል። ምን እንደተወራ ርዕሱ በውል ሳይታወቅ እንደገና ሌላ ርዕስ ይቀጥላል፡፡ አንዳንድ ጊዜ የተጀመረው አዲስ ርዕስ ምን እንደሆነ እንኳንስ አድማጩ ተናጋሪው ራሱ በውል አያውቀውም፡፡ ዝም ማለት በህግ የተከለከለ ይመስል ማውራት..
ማውራት.. ማውራት... መጮህ... የአንድ ቀን ትውውቅ የሌለው በስካር መንፈስ መጠጥ ቤት ውስጥ ይተዋወቅና ወዲያውኑ መሳሳም ይጀምራል።ሰክሮ እጁ የማይፈታ፣ የማይጋብዝ፣ ሰክሮ ጥሩ ዘፋኝ፣ ጥሩ ስዓሊ...ጥሩ ደራሲ...ጥሩ የእግር ኳስ ተጫዋች የማይሆን ስለአንበሳ ቦክሰኛነቱ የማያወራ ጥቂቱ ነው። በዚያን ዕለትም እንደተለመደው ጠጪው የእማማ ወደሬን ቤት ከአፍ እስከገደፉ ሞልቶ አጨናንቋት ነበር ደላላው፣ ተሸካሚው፣አናፂው፣ግንበኛው፣ አስተማሪው... በያይነቱ...
እማማ ወደሬ የዶሮ ዓይን የመሰለ ጠላቸውና የነጠረ ካቲካላቸው ለመድኃኒትነት ይፈለጋሉ እየተባለ ዝናን ስላተረፉላቸው ቤታቸው ምንጊዜም ቀዝቅዞ አያውቅም ነበር፡፡ እማማ ወደሬ ደስ ያላቸው ቀን ከጠጪው መሃል ይደባለቁና ጨዋታውን ያጧጡፉታል። በዚያን ጊዜ የግብዣው መዓት ይወርድላቸዋል፡፡
እሳቸውም ፈታ ብለው ስለ ትኩስ ዘመን የፍቅር ታሪካቸው፣ ስለ ባልንጀሮቻቻው፣ ስለ ውሽሞቻቸው፣ስለ ጣፋጭነታቸው እያነሳሱ እንደ ዋዛ አለፈ እያሉ ጠጪውን ያዝናናሉ፣ ያፍነክንካሉ በጨዋታ ያሰክራሉ። ሰላማዊትን ለገበያ ባቀረቡበት በዚያን ዕለትም ልባቸው በሀሴት ተሞልቶ
ፊታቸው በፈገግታ በርቶ ነበር፡፡ ለደንበኞቻቸው አዲስ ዜና የሚያስ
ሙበት ቀን በመሆኑ በኩራት ትከሻቸው ሁሉ ሰፍቷል። አንድ ሁለት መለኪያ ወስዱና ሳቅ...ፈገግ.…አሉ፡፡
ከወዲያ ማዶ ከትንሽ በርጩማ ላይ ቁጭ እንዳሉ ነበር፡፡ አፋቸውን በቀኝ እጃቸው እብስ እብስ ካደረጉ በኋላም ማስታወቂያውን አሰሙ።
“ልጃገረድ የምሽልመውና ዋጋውን የሚከፍለኝ?” ጠጪዎቹን እየተዟዟሩ
በዐይኖቻቸው ቃኙና ንቅሳታም ጥርሶቻቸውን እንደ ፋኖስ እያበሩ የምስራቹን አበሰሩ። በዚህ ጊዜ ጠጪው በሙሉ በአንድ ላይ በሳቅ አውካካ.
“ምን ያስቃችኋል? ይልቁንስ አትጃጃሉ! ማርያምን እውነቴን ነው” አሉ ከወዲያ ጥግ ተቀምጦ የነበረ አንድ ግንበኛ “እንዴ?! እትዬ ወደሬ ልጃገረዷ እኔው ነኝ እንዳይሉን ብቻ?! ካ! ካ.ካ..ካ” አለና አስካካ:: ሁሉም የግል ወሬአቸውን አቋረጡና ተከትለውት በሳቅ ፈነዱ፡፡
“ግድየላችሁም እትዬ ወደሬ እንደዚህ ደፍረው የሚናገሩት ያለምክንያት አይመስለኝም የሚያውቁት አንድ ሚስጥር ቢኖር ነው” አለ ከጎኑ የተቀመጠ ጓደኛው።
“ጉሽ አንተ ትሻላለህ እንዲያውም ላንተ ነው የምድራት ማርያምን! ሌሎቻችሁ እንደሴቃችሁ ትቀሯታላችሁ” መጋረጃውን ገለጡ። “ሰላማዊት!..ነይ እስቲ ወደዚህ ብቅ በይ የኔ ልጅ፡፡ እንግዲህ ዐይን አፋርነቱ ይበቃል፡፡ ሳምንት ያክል ተደብቀሽ ከረምሽ፡፡ ደፈር ደፈር ማለት ነው እንጂ እስከመቼ ጓዳ ውስጥ ተወሽቀሽ ትዘልቂዋለሽ ልጄ? የኛ ሥራ
ወጣ ወጣ ማለት ያስፈልገዋል። በይ ተደንበኞቼም ጋር ተዋወቂ፡፡ ሳቅ ሳቅ እያልሽ አስተናግጃቸው” ብድግ ብለው ከፊት አስቀደሟት። ከወዲያ ጥግ ፅጌ በአንድ ሰካራም እየተጋበዘችና ጡቶቿ ወተት እስከሚያመነጩ ድረስ እየታሸች በመስለምለም ላይ ነበረች።
የሁሉም ዐይኖች በሰላማዊት ላይ ተተክለው መቅረታቸውን ስታስተውል የሆነ የቅናት ስሜት ቆነጠጣት።ስራዋን ልትጫረትባት “ሀ” ብላ የአሻሻጭነት ስራ የምትጀምረውን ልጅ በጥላቻ ዐይን ተመለከተቻት።
ወንዶቹ ሰላማዊትን ካዩበት ቅፅበት ጀምሮ የምራቅ ዕጢዎቻቸው በከፍተኛ የምርት ሂደት ተጠምደው ነበር፡፡ ብዙዎቹ ወይዘሮ ወደሬ የሚቀልዱ
መስሏቸው ነበር፡፡በሁለመናዋ የምትስብ ልብ የምትሰርቅ ትንሽ ልጅ! በይብልጥ ዐይኖቻቸው የተሰኩት በዳሌዋ ላይ ነበር፡፡ አቤት ቅርፅ?!...
“እንዴ! እትዬ ወደሬ” አንዱ አረቄ ጠጪ በአድናቆት ጮኸና ጓደኛውን ጐሽመው።
እንዴት አይነት መረቅ የሆነች ልጅ ናት በናትህ?” እርስ በርስ ተጐሻ
ሸሙ:: “እትዬ ወደሬ ይሄ በፍፁም ከኔ ማምለጥ የለበትም” የሁልጊዜም ደንበኛቸው አዳሙ ጮኽ፡፡
“እንግዲህ ያልኩትን ቁጭ ማድረግ ከቻልክ ነዋ!” ወይዘሮ ወደሬ መለኪያቸውን አንስተው ጨለጡና የተወለጋገዱ ጥርሶቻቸውን ብልጭ አደረጉለት።
የፈለገውን እትዬ ወደሬ ምንም ይሁን ምን!”
ኖ...ኖ! እትዬ ወደሬ በቃላችን መሰረት ላንተ ነው ያሉት ለኔ መሆን አለበት፡፡ደግሞ እኔ ሳላዋጣዎ አልቀርም!”ዳንኤል አረቄውን እየጨለጠ ተከራከረ። በዚህ ሁሉ ጊዜ ውስጥ ግን ገበያ እንደወጣ በግ በዋጋ የሚከ
ራከሩባት ልጅ ስለምን እንደሚያወሩ ለሷ ግልጽ አልነበረም፡፡ ሄዳ ከአግዳሚው ወንበር ጫፍ ላይ ከአረቄ ጠርሙስ መደርደሪያው አጠገብ ቁጭ አለችና አንገቷን ድፍት አድርጋ መሬት መሬቱን እያየች ተሽኮረመመች፡፡
አጠገቧ የነበረው ደጀኔ እነሱ ሲከራከሩ አጠገቡ መጥታ ቁጭ ያለችለትን እንኮይ ለቀም አደረጋት፡፡ በዋጋ ከመከራከር በእጅ ይዞ እያሻሹና እያሟ
ሟቁ መቀላጠፉ ሳይሻል አይቀርም ሲል ለራሱ አወራ፡፡
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....ወይዘሮ ወደሬ ከእሪ በከንቱ ወደ ፊት በር በሚወስደው መንገድ በስተግራ በኩል ከአፋፉ ላይ በመኖሪያና በመሸታ ቤትነት የሚጠቀሙበት ሁለት ክፍል ቤት አላቸው፡፡ አሻሻጫ ቀን ቀን በግርድና ማታ ማታ ደግሞ ልብሷን ቀያይራ፣ ፀጉሯን አበጣጥራ በሴተኛ አዳሪነት ብቅ የምትለው ጽጌ ነበረች፡፡ ጽጌ ከአካባቢዋ ሴተኛ አዳሪዎች ጋር ጥሩ መግባባት አላት። ኑሯቸውን እየኖረች ቀን ቀን የቤት ስራተኛ ማታ ማታ ደግሞ ሴተኛ አዳሪ እየሆነች ስትገለባበጥ ኖራለች።
ፅጌ ከኩሽና ንግስትነት እስከ አረግራጊው አልጋ ፊታውራሪነት... ሁለቱንም የህይወት ተሞክሮ እኩል እየኖረች ስፊ ልምድ ያዳበረች ሴት ነች።አዲሷ አሻሻጭ ሰላማዊት ወደ እማማ ወደሬ ቤት ከመምጣቷ በፊት ፅጌ ብቸኛዋ የወንዶች አይን ማረፊያ ነበረች። ሰላማዊት በአሻሻጭነት ስራ
ልትጀምር የአሮጊቷ የእማማ ወደሬን ቤት ከአራት አመታት በፊት ከተቀላቀለች በኋላ ግን የተፈላጊነት ደረጃዋ እያሽቆለቆለ ሄዶ ነበር ሰላማዊት የእማማ ወደሬ ጓደኛ የሆኑት የወይዘሮ አረጋሽ ልጅ የቅድስት ጓደኛ ስትሆን “ እማማ ወደሬ ቤት ይሻልሻል” ብላ ይዛት የሄደችው
ቅድስት ነበረች።
የአሻሻጭ ችግር የነበረባቸው እማማ ወደሬ ቀንበጥ የመሰለችው የቆፍጣናው ገበሬ ልጅ እቤታቸው ድረስ ሰተት ብላ የመጣችላቸው እለት ፈጣሪያቸውን አመሰገኑ። ገበያቸው በሰላማዊት ምክንያት ሲደራ፣ ሲጧጧፍ ደንበኞቻቸው መሸታ ቤቱን ሲያጣብቡት በሷ የአሻሻጭነት ተግባር ውስጥ የዕለት ገቢያቸው በእጥፍ ድርብ ሲጨምር ወለል ብሎ ታያቸው።
ደንበኞቻቸው ቦታ ቦታቸውን ይዘው እየጠጡ ነበር፡፡ በሞቅታ ሃይል
ግማሹ ይዘፍናል ከፊሉ የቤቱን ጣጣ፣ የሚስቱን ጉድ... የመሥሪያ ቤት ችግሩን... የአለቃውን ተንኮል....ሁሉም የየራሱን ወሬ ያወራል። የሰከረው ብዙውን ጊዜ ከማዳመጥ ይልቅ ማውራት ስለሚቀናው መደማመጥ ይጠፋና አውራው የጠፋበት የንብ መንጋ ይመስል አየሩ በጫጫታ
ይሞላል። የተጀመረው የወሬ ርዕስ መቋጫ ሳያገኝ ሌላ የወሬ ርዕስ ይከፈታል። እሱም በወጉ ሳይሰማ አዲስ ርዕስ ይጀመራል። ምን እንደተወራ ርዕሱ በውል ሳይታወቅ እንደገና ሌላ ርዕስ ይቀጥላል፡፡ አንዳንድ ጊዜ የተጀመረው አዲስ ርዕስ ምን እንደሆነ እንኳንስ አድማጩ ተናጋሪው ራሱ በውል አያውቀውም፡፡ ዝም ማለት በህግ የተከለከለ ይመስል ማውራት..
ማውራት.. ማውራት... መጮህ... የአንድ ቀን ትውውቅ የሌለው በስካር መንፈስ መጠጥ ቤት ውስጥ ይተዋወቅና ወዲያውኑ መሳሳም ይጀምራል።ሰክሮ እጁ የማይፈታ፣ የማይጋብዝ፣ ሰክሮ ጥሩ ዘፋኝ፣ ጥሩ ስዓሊ...ጥሩ ደራሲ...ጥሩ የእግር ኳስ ተጫዋች የማይሆን ስለአንበሳ ቦክሰኛነቱ የማያወራ ጥቂቱ ነው። በዚያን ዕለትም እንደተለመደው ጠጪው የእማማ ወደሬን ቤት ከአፍ እስከገደፉ ሞልቶ አጨናንቋት ነበር ደላላው፣ ተሸካሚው፣አናፂው፣ግንበኛው፣ አስተማሪው... በያይነቱ...
እማማ ወደሬ የዶሮ ዓይን የመሰለ ጠላቸውና የነጠረ ካቲካላቸው ለመድኃኒትነት ይፈለጋሉ እየተባለ ዝናን ስላተረፉላቸው ቤታቸው ምንጊዜም ቀዝቅዞ አያውቅም ነበር፡፡ እማማ ወደሬ ደስ ያላቸው ቀን ከጠጪው መሃል ይደባለቁና ጨዋታውን ያጧጡፉታል። በዚያን ጊዜ የግብዣው መዓት ይወርድላቸዋል፡፡
እሳቸውም ፈታ ብለው ስለ ትኩስ ዘመን የፍቅር ታሪካቸው፣ ስለ ባልንጀሮቻቻው፣ ስለ ውሽሞቻቸው፣ስለ ጣፋጭነታቸው እያነሳሱ እንደ ዋዛ አለፈ እያሉ ጠጪውን ያዝናናሉ፣ ያፍነክንካሉ በጨዋታ ያሰክራሉ። ሰላማዊትን ለገበያ ባቀረቡበት በዚያን ዕለትም ልባቸው በሀሴት ተሞልቶ
ፊታቸው በፈገግታ በርቶ ነበር፡፡ ለደንበኞቻቸው አዲስ ዜና የሚያስ
ሙበት ቀን በመሆኑ በኩራት ትከሻቸው ሁሉ ሰፍቷል። አንድ ሁለት መለኪያ ወስዱና ሳቅ...ፈገግ.…አሉ፡፡
ከወዲያ ማዶ ከትንሽ በርጩማ ላይ ቁጭ እንዳሉ ነበር፡፡ አፋቸውን በቀኝ እጃቸው እብስ እብስ ካደረጉ በኋላም ማስታወቂያውን አሰሙ።
“ልጃገረድ የምሽልመውና ዋጋውን የሚከፍለኝ?” ጠጪዎቹን እየተዟዟሩ
በዐይኖቻቸው ቃኙና ንቅሳታም ጥርሶቻቸውን እንደ ፋኖስ እያበሩ የምስራቹን አበሰሩ። በዚህ ጊዜ ጠጪው በሙሉ በአንድ ላይ በሳቅ አውካካ.
“ምን ያስቃችኋል? ይልቁንስ አትጃጃሉ! ማርያምን እውነቴን ነው” አሉ ከወዲያ ጥግ ተቀምጦ የነበረ አንድ ግንበኛ “እንዴ?! እትዬ ወደሬ ልጃገረዷ እኔው ነኝ እንዳይሉን ብቻ?! ካ! ካ.ካ..ካ” አለና አስካካ:: ሁሉም የግል ወሬአቸውን አቋረጡና ተከትለውት በሳቅ ፈነዱ፡፡
“ግድየላችሁም እትዬ ወደሬ እንደዚህ ደፍረው የሚናገሩት ያለምክንያት አይመስለኝም የሚያውቁት አንድ ሚስጥር ቢኖር ነው” አለ ከጎኑ የተቀመጠ ጓደኛው።
“ጉሽ አንተ ትሻላለህ እንዲያውም ላንተ ነው የምድራት ማርያምን! ሌሎቻችሁ እንደሴቃችሁ ትቀሯታላችሁ” መጋረጃውን ገለጡ። “ሰላማዊት!..ነይ እስቲ ወደዚህ ብቅ በይ የኔ ልጅ፡፡ እንግዲህ ዐይን አፋርነቱ ይበቃል፡፡ ሳምንት ያክል ተደብቀሽ ከረምሽ፡፡ ደፈር ደፈር ማለት ነው እንጂ እስከመቼ ጓዳ ውስጥ ተወሽቀሽ ትዘልቂዋለሽ ልጄ? የኛ ሥራ
ወጣ ወጣ ማለት ያስፈልገዋል። በይ ተደንበኞቼም ጋር ተዋወቂ፡፡ ሳቅ ሳቅ እያልሽ አስተናግጃቸው” ብድግ ብለው ከፊት አስቀደሟት። ከወዲያ ጥግ ፅጌ በአንድ ሰካራም እየተጋበዘችና ጡቶቿ ወተት እስከሚያመነጩ ድረስ እየታሸች በመስለምለም ላይ ነበረች።
የሁሉም ዐይኖች በሰላማዊት ላይ ተተክለው መቅረታቸውን ስታስተውል የሆነ የቅናት ስሜት ቆነጠጣት።ስራዋን ልትጫረትባት “ሀ” ብላ የአሻሻጭነት ስራ የምትጀምረውን ልጅ በጥላቻ ዐይን ተመለከተቻት።
ወንዶቹ ሰላማዊትን ካዩበት ቅፅበት ጀምሮ የምራቅ ዕጢዎቻቸው በከፍተኛ የምርት ሂደት ተጠምደው ነበር፡፡ ብዙዎቹ ወይዘሮ ወደሬ የሚቀልዱ
መስሏቸው ነበር፡፡በሁለመናዋ የምትስብ ልብ የምትሰርቅ ትንሽ ልጅ! በይብልጥ ዐይኖቻቸው የተሰኩት በዳሌዋ ላይ ነበር፡፡ አቤት ቅርፅ?!...
“እንዴ! እትዬ ወደሬ” አንዱ አረቄ ጠጪ በአድናቆት ጮኸና ጓደኛውን ጐሽመው።
እንዴት አይነት መረቅ የሆነች ልጅ ናት በናትህ?” እርስ በርስ ተጐሻ
ሸሙ:: “እትዬ ወደሬ ይሄ በፍፁም ከኔ ማምለጥ የለበትም” የሁልጊዜም ደንበኛቸው አዳሙ ጮኽ፡፡
“እንግዲህ ያልኩትን ቁጭ ማድረግ ከቻልክ ነዋ!” ወይዘሮ ወደሬ መለኪያቸውን አንስተው ጨለጡና የተወለጋገዱ ጥርሶቻቸውን ብልጭ አደረጉለት።
የፈለገውን እትዬ ወደሬ ምንም ይሁን ምን!”
ኖ...ኖ! እትዬ ወደሬ በቃላችን መሰረት ላንተ ነው ያሉት ለኔ መሆን አለበት፡፡ደግሞ እኔ ሳላዋጣዎ አልቀርም!”ዳንኤል አረቄውን እየጨለጠ ተከራከረ። በዚህ ሁሉ ጊዜ ውስጥ ግን ገበያ እንደወጣ በግ በዋጋ የሚከ
ራከሩባት ልጅ ስለምን እንደሚያወሩ ለሷ ግልጽ አልነበረም፡፡ ሄዳ ከአግዳሚው ወንበር ጫፍ ላይ ከአረቄ ጠርሙስ መደርደሪያው አጠገብ ቁጭ አለችና አንገቷን ድፍት አድርጋ መሬት መሬቱን እያየች ተሽኮረመመች፡፡
አጠገቧ የነበረው ደጀኔ እነሱ ሲከራከሩ አጠገቡ መጥታ ቁጭ ያለችለትን እንኮይ ለቀም አደረጋት፡፡ በዋጋ ከመከራከር በእጅ ይዞ እያሻሹና እያሟ
ሟቁ መቀላጠፉ ሳይሻል አይቀርም ሲል ለራሱ አወራ፡፡
👍2
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገ
...አፍንጫ ጎራዳነቷ ውበቷን አደመቀው እንጂ አላደበዘዘውም፡፡ ስላማዊት ብዙ ሰው ቢረባረብባትም ከሁሉ የበለጠ የምትቀርበውና ወዳጇ
መሆኑ በብዙዎቹ ዘንድ እየታወቀ የመጣው ታደሰ ነው። ታደሰ መልኩ ጥቁር ሆኖ ረዘም ያለ ጉብል ነው፡፡ እሱ ሲመጣ ሰላማዊት ማንንም አታነጋግርም፡፡ ሄዳ እሱ ላይ ጥብቅ ነው። ይሄ ሁኔታ በፅጌ አማካኝነት ለሰፈሩ ሴተኛ አዳሪዎች ሁሉ ስለተወራ ታደሰ ብቅ ማለቱን ሲያዩ ስሟን
እንደማስቲካ ሲያኝኩት ይውላሉ።
“አሳበዳት እንጂ! ነፍሷን አጠፋላት!ታደሰን አታውቂውም እንዴ? ደላላ ነው እኮ! ኸረ በሌላም የሚጠረጠር ሰው ነው አሉ። አንዱ ውሽማዬ ስለሱ ነግሮኛል።ነጭ ለባሽ ነው ተብሎ ይጠረጠራል ብሎ አጫውቶኛል”
“አረ እባክሽ?! ነጭ ለባሽ ?ምን አስነክቷት ይሆን እንደዚህ በፍቅር የከነፈችለት?”
“ትቀልጃለሽ እንዴ? ያቅማታላ! ብር እንደ አሸዋ ይበትንላታላ! እስቲ ይታይሽ? ደላላ ነው። በዚህ ላይ ደግሞ በነጭ ለባሽነቱ መንግሥት ይከፍለዋል! ገንዘብ ካለ በሰማይ መንገድ አለ ነው
“ምን እያቀመሰቻቸው ይሆን ወንዶቹ ሁሉ እንደዚህ በሷ ላይ የሚረባረቡት በናትሽ?”
“ወረት ነው እባክሽ! ወረት! አዲስ ጀማሪ አይደለችም? በወረት ነው እንደ ንብ የሚከቧት”
የታደሰ ደግሞ ባሰ፡፡ ፍቅር ድብን አድርጎ ገድሎታል እኮ፡፡ ምን ማለትሽ ነው? አሁን አሁንማ ግንባሯን ሳይሳለም አይውልምኮ! እኔም ሳላየው የዋልኩበት ቀን የለም”
“ምን ታደርጊዋለሽ አጅሬ የወረት ፍቅር ነዋ!” ተንሾካሾኩባት። እውነትም ከዚያ ሁሉ የወንድ መንጋ መካከል ለታደስ ልዩ ፍቅር ነበራት። ታደሰ ፍቅሩን በብዙ መልኩ የሚገለፅላትና የሚያስፈልጋትን ሁሉ የሚያሟላላት የስካር ሳይሆን እውነተኛ ጓደኛዋ ነበር።
ዛሬም እንደ ወትሮው ካፖርቱን ከላይ ጣል አድርጉ ባርኔጣውን ደፍቶ አንገቱ ላይ ሻርፕ ጠምጥሞ ተፍተፍ የሚለው ወደሷ ነበር፡፡ ከሁለተኛ ፖሊስ ጣቢያ ወደ ቀኝ ተገንጥሎ ወደ እሪ በከንቱ የሚወስደውን ቀጭን የአስፋልት መንገድ ተከትሎ ወደ ፍቅረኛው ወደ ሰላማዊት ለመድረስ እየተጣደፈ ነበር፡፡
ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ሆኗል። በአላፊ አግዳሚ ላይ ዐይኖቻቸውን እያፈጠጡ የሚያስፈራሩ ሴተኛ አዳሪዎች ብቅ ብቅ ማለት ጀምረዋል። በዚህ
ሰዓት እብዱ ምንሽንሽ ከአካባቢው አይታጣም ነበር፡፡ አንዴ ወዲህ አንዴ ወዲያ እየዘለለ ድንጋይ እያነሳ ድንጋይ እየጣለ ይሯሯጥ ነበር፡፡ ሣንቲም
ይለምናል። ከሰጡት ይቀበላል፡፡ ዝም ካሉት ደንታም የለው። የሱ ቁም ነገር መዝለል፣ መዝለል፣ ድንጋይ መፈንቀል፣ ድንጋይ ማንሳት ድንጋይ መጣል ብቻ ነው፡፡ ዛሬ ግን በሱ ምትክ ሰካራሙ ታከለ ያንን የማያስከፍል ድራማውን እያሳየ ለሴተኛ አዳሪዎች መሳለቂያና መደበሪያ ሆኖላቸው ነበር፡፡ መጀመሪያ ቀይ አጣብቂኝ ሱሪ ለብሳ ፀጉሯን እንደ ገዳይ ጐፈሬ ወዳቆመችው ሴት ቤት ጥልቅ ብሎ ገባ..
ሰካራሙ ታከለ ትዳሩን በመጠጥ ምክንያት ካፈረሰ በኋላ መቅኖ አጥቶ በደሞዝ ሰሞን ሲጠጣ፣ያገኘውን ሲጋብዝ፣ ሲሸልም፣ ሲበትን ይከርምና
ባዶ ኪሱን ጨረቃ አስመስሎ መውጣት ልማዱ ነው። እንደምንሽንሽ ሲለይለት አንድ ሀሙስ ብቻ ነው የቀረው፡፡ ሴትዮዋ በሯን ዘጋችና...
“እሺ ሂሣብ በቅድሚያ!” አለችው።
“ም. ን. ድ. ነው... ቅርሚያ ቅርሚያ! የምትይው? እኔን አታ..
አታምኝ.. ኝ.. ኝምምም?” አላት ልፍድድ ባለ የስካር ንግግር።
“ኡፋ! ሰውዬ ወሬ አታብዛ ! የምትከፍል ከሆነ በቅድሚያ ክፈልና እሺ። አለበለዚያ ውጣልኝ!ገበያዬን አትዝጋ!” አለችና አንባረቀችበት። ታከለ በጠጅና በአረቄ ብዛት የደነበሹ ዐይኖቹን ብልጥጥ አድርጎ ሲመለከታት ተንኮል የቋጠረ አመፀኛ ዝንጀሮ እንጂ ለጉዳይ የገባ እንግዳ አይመስልም ነበር።
በል ተናገር?! ያለበለዚያ ውጣ!” የዘጋችውን በር መልሳ እየከፈተች ጭኽችበት።
“ቆይ .. እ- ሺ ቆይ! ቆይ!” አለና ወደ ኪሱ ገባ፡፡ ያገኘው ሰላሳ አምስት ሣንቲም ብቻ ነበር።
እሺ ያው..ልሽ!
አትፈልጊምምም.?” እየተንተባተበ፡፡ ብልጭ አለባት።
ከኋላው አሽቀንጥራ ስትወረውረው ከፊት ለፊቱ ካለው ቆሻሻ ውሃ ከሚ ወርድበት ቦይ ውስጥ ሂዶ ተወተፈ፡፡ ከዚያም እየተውተረተረ ተነሳና ሣንቲምቹን መለቃቀም ጀመረ፡፡ እንደምንም ብሎ ሃያ አምስት ሣንቲም አገኘ።
ትርዒቱን እያዩ ወደሚሳሳቁት ግራና ቀኙን ወደተኮለኮሉ ሴተኛ አዳሪዎች እየተመለከተ“ይህቺን... ፈላጊ!.. ይህቺን... ይህቺን.” እያለ ሳንቲ ሞቹን ሽክ... ሽክ... ሽክ ሲያደርጋቸው የበለጠ በሳቅ ፈነዱ።
“አንተ ጠንባራ ሰካራም ድራሽህ ይጥፋ! የቀረችህ እሷ ናት። ሂድና ለሚስትህ ቀሚስ ግዛበት ፉዞ!” የስድብ መአት አወረዱበት። እሱም እየተንገዳገደ ቁልቁል ወረደ። ታደሰ ይህ ትርዒት የሚካሄድበትን አካባቢ
አልፎ ወደ ሰላማዊት ዘንድ ሊደርስ ትንሽ ቀርቶታል። አስፋልቱን ከመሻገሩ በፊት ግን ቆም ብሎ ምን ይዞላት እንደሚሄድ አሰላሰለ። እንደ
ሴተኛ አዳሪነቷ ሳይሆን እንደ ሚስቱ ያስብላት ስለጀመረ ወደ መኖሪያ ቤቱ የሚሄድ አባወራ እንጂ ወደ መሸታ ቤት የሚሄድ ጠጪ አይመስልም ነበር፡፡ ሰላማዊትም ከልቧ ስለምትወደው እሱ ከመጣ ሌላው ጠጪ
ሰው መስሎ አይታያትም፡፡ እንደሚጨነቅላት ስለምታውቅ አፀፋውን ፍቅር እየሰጠችው ነው፡፡ ታደስ ከእማማ ወደሬ ቤት ከፍ ብሎ ወደሚገኘው ሉካንዳ ቤት ገባና ከሽንጥ ሥጋ ላይ ሁለት ኪሎ ግራም አስቆርጦ አስጠቅልሎ ሄደ። ወይዘሮ ወደሬ የታደሰ ውለታ እየከበዳቸው ስለመጣ በሱ ምክንያት ሰላማዊትን ማክበርና መፍራት ጀምረዋል። ታደሰ ወደ ቤት ሊገባ ካለ በኋላ ምናምን እንዳቋረጠው ሰው ወደ ኋላው ሰግጠጥ አለና ቆመ፡፡ቀስ ብሎ በጓሮ በኩል ዞረ። የጓሮውን በር ያለሱ የሚደፍረው የለም።
“ሰላምን ጥሪያት” አላት ላፅጌ። ሰላማዊት ፅጌ ስትነግራት ሮጣ መጣች።
“ውይ ታዴ!”እቅፍ አድርጋ ሳመችውና በእጁ የያዘውን ተቀበለችው።
በጓሮ በኩል ዞሮ የገባው የያዘውን ሊሰጣት መሰላት። ድርጊቱ የበለጠ ገረማት። ማንም እሱ የሚያደርገውን አያደርግላትም። የፈለገውን ያክል ገንዘብ አስታቅፈዋት ቢሄዱ ታደሰ የሚያስበውን ያክል አስበውላት አያውቁም፡፡ በበዓላት ቀን ሹልክ ብሎ ይመጣና ገንዘብ ይሰጣታል። እንዳይደብርሽ እያለ ትያትርና ሙዚቃ ቤት ወስዶ ያዝናናታል፡፡
“አይ ታደሰ?አሁንስ አበዛው ምነው እሱ እንዲህ ተጨነቀ? እኔ ውለታ
ሲበዛብኝ ደስ አይለኝም፡፡ ይከብደኛል። ከሌላው የተለየ ለሱ ምን የተደረገለት ነገር አለ?” ወይዘሮ ወደሬ ስለታደሰ ተጨነቁ፡፡
“ታድዬ እቤት ትገባለህ ወይስ እዚሁ ጠላ ይዤልህ ልምጣ?” ስትል ጠየቀችው።
“እቤት አልገባም እዚችው ጓሮ ቁጭ ብለን ትንሽ አጫውቺኝና ጠላ ጠጥቼ እሄዳለሁ” አሁን አሁን የገባው ጠጪ ሁሉ እንደፈለገው እየጎተተ ሲያሻሻት፣ ሲያቅፋት፣ ሲስማት፣ ሲደባብሳት ማየት እያስጠላው መጥቷል።
“እሺ የኔ ቆንጆ ይዤልህ ልምጣ” አለችና ተመልሳ ገባች።
“ታዴ ወደ ቤት አይገባም እንዴ ሰላም?” አሉ ወይዘሮ ወደሬ።
“ውጭ ይሻለኛል ብሉኝ እኮ ነው”
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገ
...አፍንጫ ጎራዳነቷ ውበቷን አደመቀው እንጂ አላደበዘዘውም፡፡ ስላማዊት ብዙ ሰው ቢረባረብባትም ከሁሉ የበለጠ የምትቀርበውና ወዳጇ
መሆኑ በብዙዎቹ ዘንድ እየታወቀ የመጣው ታደሰ ነው። ታደሰ መልኩ ጥቁር ሆኖ ረዘም ያለ ጉብል ነው፡፡ እሱ ሲመጣ ሰላማዊት ማንንም አታነጋግርም፡፡ ሄዳ እሱ ላይ ጥብቅ ነው። ይሄ ሁኔታ በፅጌ አማካኝነት ለሰፈሩ ሴተኛ አዳሪዎች ሁሉ ስለተወራ ታደሰ ብቅ ማለቱን ሲያዩ ስሟን
እንደማስቲካ ሲያኝኩት ይውላሉ።
“አሳበዳት እንጂ! ነፍሷን አጠፋላት!ታደሰን አታውቂውም እንዴ? ደላላ ነው እኮ! ኸረ በሌላም የሚጠረጠር ሰው ነው አሉ። አንዱ ውሽማዬ ስለሱ ነግሮኛል።ነጭ ለባሽ ነው ተብሎ ይጠረጠራል ብሎ አጫውቶኛል”
“አረ እባክሽ?! ነጭ ለባሽ ?ምን አስነክቷት ይሆን እንደዚህ በፍቅር የከነፈችለት?”
“ትቀልጃለሽ እንዴ? ያቅማታላ! ብር እንደ አሸዋ ይበትንላታላ! እስቲ ይታይሽ? ደላላ ነው። በዚህ ላይ ደግሞ በነጭ ለባሽነቱ መንግሥት ይከፍለዋል! ገንዘብ ካለ በሰማይ መንገድ አለ ነው
“ምን እያቀመሰቻቸው ይሆን ወንዶቹ ሁሉ እንደዚህ በሷ ላይ የሚረባረቡት በናትሽ?”
“ወረት ነው እባክሽ! ወረት! አዲስ ጀማሪ አይደለችም? በወረት ነው እንደ ንብ የሚከቧት”
የታደሰ ደግሞ ባሰ፡፡ ፍቅር ድብን አድርጎ ገድሎታል እኮ፡፡ ምን ማለትሽ ነው? አሁን አሁንማ ግንባሯን ሳይሳለም አይውልምኮ! እኔም ሳላየው የዋልኩበት ቀን የለም”
“ምን ታደርጊዋለሽ አጅሬ የወረት ፍቅር ነዋ!” ተንሾካሾኩባት። እውነትም ከዚያ ሁሉ የወንድ መንጋ መካከል ለታደስ ልዩ ፍቅር ነበራት። ታደሰ ፍቅሩን በብዙ መልኩ የሚገለፅላትና የሚያስፈልጋትን ሁሉ የሚያሟላላት የስካር ሳይሆን እውነተኛ ጓደኛዋ ነበር።
ዛሬም እንደ ወትሮው ካፖርቱን ከላይ ጣል አድርጉ ባርኔጣውን ደፍቶ አንገቱ ላይ ሻርፕ ጠምጥሞ ተፍተፍ የሚለው ወደሷ ነበር፡፡ ከሁለተኛ ፖሊስ ጣቢያ ወደ ቀኝ ተገንጥሎ ወደ እሪ በከንቱ የሚወስደውን ቀጭን የአስፋልት መንገድ ተከትሎ ወደ ፍቅረኛው ወደ ሰላማዊት ለመድረስ እየተጣደፈ ነበር፡፡
ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ሆኗል። በአላፊ አግዳሚ ላይ ዐይኖቻቸውን እያፈጠጡ የሚያስፈራሩ ሴተኛ አዳሪዎች ብቅ ብቅ ማለት ጀምረዋል። በዚህ
ሰዓት እብዱ ምንሽንሽ ከአካባቢው አይታጣም ነበር፡፡ አንዴ ወዲህ አንዴ ወዲያ እየዘለለ ድንጋይ እያነሳ ድንጋይ እየጣለ ይሯሯጥ ነበር፡፡ ሣንቲም
ይለምናል። ከሰጡት ይቀበላል፡፡ ዝም ካሉት ደንታም የለው። የሱ ቁም ነገር መዝለል፣ መዝለል፣ ድንጋይ መፈንቀል፣ ድንጋይ ማንሳት ድንጋይ መጣል ብቻ ነው፡፡ ዛሬ ግን በሱ ምትክ ሰካራሙ ታከለ ያንን የማያስከፍል ድራማውን እያሳየ ለሴተኛ አዳሪዎች መሳለቂያና መደበሪያ ሆኖላቸው ነበር፡፡ መጀመሪያ ቀይ አጣብቂኝ ሱሪ ለብሳ ፀጉሯን እንደ ገዳይ ጐፈሬ ወዳቆመችው ሴት ቤት ጥልቅ ብሎ ገባ..
ሰካራሙ ታከለ ትዳሩን በመጠጥ ምክንያት ካፈረሰ በኋላ መቅኖ አጥቶ በደሞዝ ሰሞን ሲጠጣ፣ያገኘውን ሲጋብዝ፣ ሲሸልም፣ ሲበትን ይከርምና
ባዶ ኪሱን ጨረቃ አስመስሎ መውጣት ልማዱ ነው። እንደምንሽንሽ ሲለይለት አንድ ሀሙስ ብቻ ነው የቀረው፡፡ ሴትዮዋ በሯን ዘጋችና...
“እሺ ሂሣብ በቅድሚያ!” አለችው።
“ም. ን. ድ. ነው... ቅርሚያ ቅርሚያ! የምትይው? እኔን አታ..
አታምኝ.. ኝ.. ኝምምም?” አላት ልፍድድ ባለ የስካር ንግግር።
“ኡፋ! ሰውዬ ወሬ አታብዛ ! የምትከፍል ከሆነ በቅድሚያ ክፈልና እሺ። አለበለዚያ ውጣልኝ!ገበያዬን አትዝጋ!” አለችና አንባረቀችበት። ታከለ በጠጅና በአረቄ ብዛት የደነበሹ ዐይኖቹን ብልጥጥ አድርጎ ሲመለከታት ተንኮል የቋጠረ አመፀኛ ዝንጀሮ እንጂ ለጉዳይ የገባ እንግዳ አይመስልም ነበር።
በል ተናገር?! ያለበለዚያ ውጣ!” የዘጋችውን በር መልሳ እየከፈተች ጭኽችበት።
“ቆይ .. እ- ሺ ቆይ! ቆይ!” አለና ወደ ኪሱ ገባ፡፡ ያገኘው ሰላሳ አምስት ሣንቲም ብቻ ነበር።
እሺ ያው..ልሽ!
አትፈልጊምምም.?” እየተንተባተበ፡፡ ብልጭ አለባት።
ከኋላው አሽቀንጥራ ስትወረውረው ከፊት ለፊቱ ካለው ቆሻሻ ውሃ ከሚ ወርድበት ቦይ ውስጥ ሂዶ ተወተፈ፡፡ ከዚያም እየተውተረተረ ተነሳና ሣንቲምቹን መለቃቀም ጀመረ፡፡ እንደምንም ብሎ ሃያ አምስት ሣንቲም አገኘ።
ትርዒቱን እያዩ ወደሚሳሳቁት ግራና ቀኙን ወደተኮለኮሉ ሴተኛ አዳሪዎች እየተመለከተ“ይህቺን... ፈላጊ!.. ይህቺን... ይህቺን.” እያለ ሳንቲ ሞቹን ሽክ... ሽክ... ሽክ ሲያደርጋቸው የበለጠ በሳቅ ፈነዱ።
“አንተ ጠንባራ ሰካራም ድራሽህ ይጥፋ! የቀረችህ እሷ ናት። ሂድና ለሚስትህ ቀሚስ ግዛበት ፉዞ!” የስድብ መአት አወረዱበት። እሱም እየተንገዳገደ ቁልቁል ወረደ። ታደሰ ይህ ትርዒት የሚካሄድበትን አካባቢ
አልፎ ወደ ሰላማዊት ዘንድ ሊደርስ ትንሽ ቀርቶታል። አስፋልቱን ከመሻገሩ በፊት ግን ቆም ብሎ ምን ይዞላት እንደሚሄድ አሰላሰለ። እንደ
ሴተኛ አዳሪነቷ ሳይሆን እንደ ሚስቱ ያስብላት ስለጀመረ ወደ መኖሪያ ቤቱ የሚሄድ አባወራ እንጂ ወደ መሸታ ቤት የሚሄድ ጠጪ አይመስልም ነበር፡፡ ሰላማዊትም ከልቧ ስለምትወደው እሱ ከመጣ ሌላው ጠጪ
ሰው መስሎ አይታያትም፡፡ እንደሚጨነቅላት ስለምታውቅ አፀፋውን ፍቅር እየሰጠችው ነው፡፡ ታደስ ከእማማ ወደሬ ቤት ከፍ ብሎ ወደሚገኘው ሉካንዳ ቤት ገባና ከሽንጥ ሥጋ ላይ ሁለት ኪሎ ግራም አስቆርጦ አስጠቅልሎ ሄደ። ወይዘሮ ወደሬ የታደሰ ውለታ እየከበዳቸው ስለመጣ በሱ ምክንያት ሰላማዊትን ማክበርና መፍራት ጀምረዋል። ታደሰ ወደ ቤት ሊገባ ካለ በኋላ ምናምን እንዳቋረጠው ሰው ወደ ኋላው ሰግጠጥ አለና ቆመ፡፡ቀስ ብሎ በጓሮ በኩል ዞረ። የጓሮውን በር ያለሱ የሚደፍረው የለም።
“ሰላምን ጥሪያት” አላት ላፅጌ። ሰላማዊት ፅጌ ስትነግራት ሮጣ መጣች።
“ውይ ታዴ!”እቅፍ አድርጋ ሳመችውና በእጁ የያዘውን ተቀበለችው።
በጓሮ በኩል ዞሮ የገባው የያዘውን ሊሰጣት መሰላት። ድርጊቱ የበለጠ ገረማት። ማንም እሱ የሚያደርገውን አያደርግላትም። የፈለገውን ያክል ገንዘብ አስታቅፈዋት ቢሄዱ ታደሰ የሚያስበውን ያክል አስበውላት አያውቁም፡፡ በበዓላት ቀን ሹልክ ብሎ ይመጣና ገንዘብ ይሰጣታል። እንዳይደብርሽ እያለ ትያትርና ሙዚቃ ቤት ወስዶ ያዝናናታል፡፡
“አይ ታደሰ?አሁንስ አበዛው ምነው እሱ እንዲህ ተጨነቀ? እኔ ውለታ
ሲበዛብኝ ደስ አይለኝም፡፡ ይከብደኛል። ከሌላው የተለየ ለሱ ምን የተደረገለት ነገር አለ?” ወይዘሮ ወደሬ ስለታደሰ ተጨነቁ፡፡
“ታድዬ እቤት ትገባለህ ወይስ እዚሁ ጠላ ይዤልህ ልምጣ?” ስትል ጠየቀችው።
“እቤት አልገባም እዚችው ጓሮ ቁጭ ብለን ትንሽ አጫውቺኝና ጠላ ጠጥቼ እሄዳለሁ” አሁን አሁን የገባው ጠጪ ሁሉ እንደፈለገው እየጎተተ ሲያሻሻት፣ ሲያቅፋት፣ ሲስማት፣ ሲደባብሳት ማየት እያስጠላው መጥቷል።
“እሺ የኔ ቆንጆ ይዤልህ ልምጣ” አለችና ተመልሳ ገባች።
“ታዴ ወደ ቤት አይገባም እንዴ ሰላም?” አሉ ወይዘሮ ወደሬ።
“ውጭ ይሻለኛል ብሉኝ እኮ ነው”
❤1