#ሮዛ_2
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት( 🔞)
(የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#የሰው_ ልጅ_ዓለምን_ አትርፎ #ነፍሱን_ቢበድል....
ቤይሩት፣ ራፊቅ ሀሪሪ አየር መንገድ
አርብ ሌሊት
በምድር ላይ እጅግ ከምጠላቸው ሕዝቦች መሀል እገኛለሁ፤ ሊባኖስ ቤይሩት አየር መንገድ ውስጥ፤
ወደ አቡዳቢ ለመብረር። አየርመንገዱ በአረቦች ታፍኗል። አረብ አረብ ይሸታል። የተቀቡት ሽቶ አልተስማማኝም፤ እነሱን እንዲህ በጅምላ ማየት ራሱ ያቅለሸልሻል። አመመኝ።
ክትፎ የሚወድ ሰው ጣባውን ሲከፍተው የሚዝለገለጉ ትላትሎች ታጭቀው ቢያይ ሊሰማው የሚችለው ስሜት እኔ አረቦችን እንዲህ ብዙ ሆነው በማየቴ ተሰምቶኛል። አዲስ አበባ በተናጥል አገኛቸው ስለነበር
ለነሱ ያለኝ የጥላቻ ስሜት የዛሬውን ያህል አልበረታብኝም ነበር። አሁን አንድ ሙሉ ተርሚናል በሺ በሚቆጠሩ አረቦች ተሞልቶ ብመለከት ምግብ አልረጋ አለኝ። አመመኝ።
ከአረቦቹ መሀል ብዙ መልካምና ደጋግ ሊኖሩ እንደሚችሉ እረዳለሁ፤ የበርካታ ሺህ ወገኖቼ ህይወት በነሱ ላይ እንደተመሰረተም አውቃለሁ፤ ወላጅ አልባ ህጻናት የሚያሳድጉ ደጋግ አረቦች ብዙ አሉ፤ ይህንንም አልከድም። በሀገሬም ሆነ በሀገራቸው ከወገኖቼ ጋ ፍቅር መስርተው የወለዱና የከበዱ አረቦች
እንዳሉም አልክድም።ለወደዱት ሰው ቤት ንብረታቸውን በሙሉ የሚሰጡ፣ ሀበሻ ሰራተኞቻቸው ሲታመሙ ሚሊዮን ብር ከስከሰው ያሳከሙ አረቦች እንዳሉም ከዚያ የተመለሱ ጓደኞቼ ሲያወሩ
ሰምቻለሁ። እርግጥ ነው፤ የትኛውም ህዝብ ሰናይና እኩይ ሰዎች አሉት፤ አረቦቹም ከዚያ የተለዩ እንዳልሆኑ ጠንቅቄ አውቀዋለሁ።ይህን ሁሉ እየተረዳሁ ግን ለአረቦች ስር የሰደደ ጥላቻ ደሜ ዉስጥ ገብቷል፤ ምን ላድርግ?
ህሊናዬን በብርቱ ከፈተነ ማሰላሰልና መብሰልሰል በኋላ የህይወቴ ቀጣዩ ምእራፍ በአረብ ምድር እንዲሆን ወሰንኩ። በተባበሩት ኢምሬትስ ርእሰ መዲና አቡዳቢ ሬስቶራንትና የውበት ሳሎን ያላትን የአብሮ አደጌን የቢዝነስ አጋርነት ግብዣ ለአመታት አሻፈረኝ ብልም ሰሞኑን ውሳኔዬን ከብዙ የአእምሮ
ጂምናስቲከ በኋላ ቀየርኩ፤ ከዚህ በኋላ እንዴትም ብዬ የህይወት አቅጣጫዬን መለወጥ እንዳለብኝ ተሰምቶኛል።
#ተርሚናሉ_ዉስጥ
.
አረብ ወንዶች ያለመጠን የተርከፈከፉት ሽቶ ራሴ ላይ ወጣ። ተርሚናሉ ዉስጥ እየተዝለገለጉ ወዲያ ወዲህ ሲሉ ሆዴ ታወከ። መታጠቢያ ቤት ሄጄ ፊቴን በቀዝቃዛ ዉኃ ነከርኩ። ትንሽ ሻል ያለ
ስሜት ሲሰማኝ በወርቅ የተለበጠ ከሚመስል አግዳሚ ወንበር ላይ አንድ ጥግ ይዤ አረፍ አልኩኝ።
ለጊዜው በዙርያዬ የሚሆነውን ከማየት ዉጭ ሌላ እድል አልነበረኝም። አይኔን ብጨፍንም አረቦችን አያለሁ። አይኔን ብገልጥም አረቦችን አያለሁ። አማራጭ አልነበረኝም። ለካንስ አይንን መጨፈን ማየት የሚፈልጉትን ከማየት አይጋርድም። ዳያሪዬን ከእጅ ቦርሳዬ ዉስጥ ብታቀፈውም አእምሮዬ ባልተለመደ ሁኔታ ደንዝዞብኛል። በአየር መንገዱ አግዳሚ ቁጭ ብዬ ወጪ ወራጁን ስሜት አልባ ሆኜ አያለሁ።
የአረብ ጎታታ ወንዶች፣ በዚያ በሚዝለገለግ ነጭ ቀሚሳቸው ዉስጥ ሆነው አውሮፕላን ለመሳፈር እንደ
ግመል ይጎተታሉ። የቀሚሳቸው መጎተት ላያንስ በሩዝ የተወደረ ከርሳቸውን ይጎትታሉ፤ የከርሳቸው ሳያንስ ኩንታል ሻንጣቸውን ይጎትታሉ። የሻንጣቸው ሳያንስ ነጠላ ጫማቸውን ይጎትታሉ፤ የነጠላ ጫማቸው ሳያንስ ከረፈፍ ሚስቶቻቸውን ይጎትታሉ፣ የሚስቶቻቸው ሳያንስ ያልተቆነጠጡ አስራ ምናምን ልጆቻቸውን ይጎትታሉ። አራት ሚስቶቻቸውን እየነዱም ቢሆን አምስተኛ ሴት ከማየት አይመለሱም። ከአንድም ሁለት ሦስት አጁዛ አረቦች ከወዲያኛው የተርሚናሉ ሬስቶራንት ሆነው
እየሰረቁ ሲመለከቱኝ ዐይቻለሁ፡፡
በድጋሚ መታጠቢያ ቤት ሄጄ ተመለስኩ። ዛሬ ምግብ አልረጋ ብሎኛል።
ቀልቤ አይወዳቸውም። በተለይ እንዲህ ነጭ ቆብ በነጭ ቀሚስ ለብሰው ሳያቸው፣ በነጭ ኩባያ ወተት ከአናታቸው እየፈሰሰባቸው ስለሚመስለኝ የዝንብ አየር ማረፍያዎች እንጂ ሰዎች ሆነው አይታዩኝም።ሰው ነጭ ለብሶም ንፁህ ሆኖ ካልታየኝ መቼስ የሆነ ችግር አለበት ማለት ነው። ለምንድነው ፈጣሪ እኛን
ድሐ እነሱን ሐብታም ያረገው? እግዜር ምናቸው ማርኮት ይሆን አሻዋቸውን የባረከው? በረሃቸውን ያረጠበው?!
“የአረብ ጥላቻ የተፈጠረብኝ መቼ ነው?” ብዬ ለማስታወስ ሞከርኩ። ትዝ የሚለኝ ነገር የለም። ምናልባት ኡስማን ዘ ፒምፕ ስለሚጠላቸው እሱ ሳያውቀው አጋብቶብኝ ይሆን? አይደለም። ኡስማንን
ሳላውቀው በፊት አረብ የሚባል ፍጥረት ያስጠላኝ ነበር። ልጅ እያለሁ የጀመረኝ ይመስለኛል። አያቴ በነበረችበት ሰፈር። ባደኩበት ሰፈር፣ በነእማማ ዙበይዳ ሰፈር።
ልጅ እያለሁ ለተወሰነ ጊዜ ሴት አያቴ ታሳድገኝ ነበር። በሰፈራችን የምንወዳቸው፣ እማማ ዙበይዳ
የሚባሉ ሴት ነበሩ። የሆኑ ደርባባ አሮጊት ሴትዬ። ሰው ዝም ብሎ ይወዳቸው ነበር። ጎመን መንገድ ላይ ይሸጣሉ። በክረምት ደግሞ በቆሎ ይሸጣሉ። እማማ ዙበይዳን ሰፈሩ ሁሉ ለምን ይወዳቸው እንደነበር ግን በትክክል አላውቅም። እኔም እወዳቸው ነበር። ለምን እንደነበር ግን አላውቅም። “ነይ እስቲ አንቺ
ጎራዳ!" እያሉ ግንባሬን ይስሙኝ እንደነበር ብቻ ነው ትዝ የሚለኝ።
እማማ ዙበይዳ ባልም ዘመድም የላቸውም። በምድር ላይ ያለቻቸው ፋጤ ቀጮ ናት። የሳቸው ብቸኛ ልጅ ፉጤ ቀጮ ጅዳ ሄደች ተባለ። ሰፈሩ ሁሉ እማማ ዙበይዳ በቃ ሻሩ፣ አሁን ወርቅ በወርቅ ሊሆኑ ነው ብሎ ተነበየ። እሳቸውን ያገኘ ሰው ሁሉ “ፋጤ ቀጮ ጅዳ ነው አይደል የሄደችው?”፣
ትደውላለች”፣ “ደህና ናት ታዲያ፣ “አሁን ለመድኩ አለችፖ፣ ግህም፣ “በርቺ በሏት እንግዲህ!
ይለመዳል.ይለመዳል”፣ “ዋናው መበርታት ነውታዲያ”፣ “እ!” እያለ ከእማማ ዙበይዳ የበቆሎ እሸት
ወይ ጎመን ገዝቷቸው ያልፋል። በበጋ ጎመን በከረምት የበቆሎ እሸት በመሸጥ ነበር የሚተዳደሩት።
በዚያ ሁሉ የሰፈር ሰው ሳይታክቱ በዚያ እናታዊ ፈገግታቸው ታጅበው ስለ ልጃቸው ደኅንነት ምላሽ ይሰጣሉ። “እላሙዲሊላ አላሂ ወላሂ ደህና ናት!ዱዋ አርጉላት." ይላሉ፤ መልሰው መላልሰው።
ሲኖሩ ሲኖሩ.…የሆነ ጊዜ ላይ ልጃቸው ስልክ ደውላ አለቀሰች ተባለ። “ምን ሆንሽ” ሲሏት አትናገርም
ሲኖሩ ሲኖሩ…የሆነ ጊዜ ላይ ደግሞ መደወል አቆመች ተባለ። ደህንነቷን የሚነግራቸው ጠፋ። ጎመን ወይ
በቆሎ ለሚገዛቸው የሰፈር ሰው ሁሉ “አረብ አገር ስልክ ማድረግ ታውቅበታለህ?” እያሉ ይጠይቃሉ።
የተማረ የሚመስል ወጣት ሲመለከቱ ደግሞ “ልጄ! እስኪ ባክህ የጅዳ ስልክ ቁጥር ጽፈህ አምጣልኝ? ልጄ ናፈቀችኝ ይሉታል። የሷ ስልክ ቁጥር ግን የላቸውም። አንዳንድ ሰው ነገሩን ሊያስረዳቸው ሞከረ።ኾኖም ሊገባቸው አልቻለም። የሰፈሩን ሰው መሄጃ መቀመጫ አሳጡት። እርስዎ ስልኳን ፈልገው ያምጡ! እኛ እንደውልሎታለን” ሲባሉ እኔ ቁጥሯን ከየት አዉቄ” ነው መልሳቸው። እሷ ካልደወለች
እሳቸው ወደየት ብለው ይደውላሉ? አድራሻዋ አይታወቅ ነገር።
የሰፈሩ ሰው በሙሉ እማማ ዙበይዳ ሲያዝኑ አይቶ አዘነ። እማማ ዙበይዳ የደግነት ምሳሌ ነበሩ። ፋጤ
ቀጮ እጅግ ስትናፍቃቸው ግን ሰው ሰላም ሳይሉ ማለፍ ሁሉ ጀመሩ። የሚሸጡት ጎመን ጠወለገ።
ወዲያው ደግሞ ወገባቸው ጎበጠ። ከመቼው በእድሜያቸው ላይ ምዕተ ዓመት እንደጨመሩ። ሰው የልጁ ናፍቆት እንደ ኤድስ አመንምኖ ሊገድለው እንደሚችል ያየሁት በእማማ ዙበይዳ ነው።
ከ5 ዓመታት በኋላ ልጃቸው ፋጤ መጣች ተባለ። በዊልቸር ላይ ሆና። በጣም ከመወፍሯ የተነሳ ዊልቸሩ ጠበባት። ፋጤ ቀጮ ትባል የነበረችው የሆነች ሲንቢሮ በረሮ ስለበረች ነበር።ታዲያ ለምን ወፈረች? ተስማምቷት ነበር ማለት ነው?
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት( 🔞)
(የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#የሰው_ ልጅ_ዓለምን_ አትርፎ #ነፍሱን_ቢበድል....
ቤይሩት፣ ራፊቅ ሀሪሪ አየር መንገድ
አርብ ሌሊት
በምድር ላይ እጅግ ከምጠላቸው ሕዝቦች መሀል እገኛለሁ፤ ሊባኖስ ቤይሩት አየር መንገድ ውስጥ፤
ወደ አቡዳቢ ለመብረር። አየርመንገዱ በአረቦች ታፍኗል። አረብ አረብ ይሸታል። የተቀቡት ሽቶ አልተስማማኝም፤ እነሱን እንዲህ በጅምላ ማየት ራሱ ያቅለሸልሻል። አመመኝ።
ክትፎ የሚወድ ሰው ጣባውን ሲከፍተው የሚዝለገለጉ ትላትሎች ታጭቀው ቢያይ ሊሰማው የሚችለው ስሜት እኔ አረቦችን እንዲህ ብዙ ሆነው በማየቴ ተሰምቶኛል። አዲስ አበባ በተናጥል አገኛቸው ስለነበር
ለነሱ ያለኝ የጥላቻ ስሜት የዛሬውን ያህል አልበረታብኝም ነበር። አሁን አንድ ሙሉ ተርሚናል በሺ በሚቆጠሩ አረቦች ተሞልቶ ብመለከት ምግብ አልረጋ አለኝ። አመመኝ።
ከአረቦቹ መሀል ብዙ መልካምና ደጋግ ሊኖሩ እንደሚችሉ እረዳለሁ፤ የበርካታ ሺህ ወገኖቼ ህይወት በነሱ ላይ እንደተመሰረተም አውቃለሁ፤ ወላጅ አልባ ህጻናት የሚያሳድጉ ደጋግ አረቦች ብዙ አሉ፤ ይህንንም አልከድም። በሀገሬም ሆነ በሀገራቸው ከወገኖቼ ጋ ፍቅር መስርተው የወለዱና የከበዱ አረቦች
እንዳሉም አልክድም።ለወደዱት ሰው ቤት ንብረታቸውን በሙሉ የሚሰጡ፣ ሀበሻ ሰራተኞቻቸው ሲታመሙ ሚሊዮን ብር ከስከሰው ያሳከሙ አረቦች እንዳሉም ከዚያ የተመለሱ ጓደኞቼ ሲያወሩ
ሰምቻለሁ። እርግጥ ነው፤ የትኛውም ህዝብ ሰናይና እኩይ ሰዎች አሉት፤ አረቦቹም ከዚያ የተለዩ እንዳልሆኑ ጠንቅቄ አውቀዋለሁ።ይህን ሁሉ እየተረዳሁ ግን ለአረቦች ስር የሰደደ ጥላቻ ደሜ ዉስጥ ገብቷል፤ ምን ላድርግ?
ህሊናዬን በብርቱ ከፈተነ ማሰላሰልና መብሰልሰል በኋላ የህይወቴ ቀጣዩ ምእራፍ በአረብ ምድር እንዲሆን ወሰንኩ። በተባበሩት ኢምሬትስ ርእሰ መዲና አቡዳቢ ሬስቶራንትና የውበት ሳሎን ያላትን የአብሮ አደጌን የቢዝነስ አጋርነት ግብዣ ለአመታት አሻፈረኝ ብልም ሰሞኑን ውሳኔዬን ከብዙ የአእምሮ
ጂምናስቲከ በኋላ ቀየርኩ፤ ከዚህ በኋላ እንዴትም ብዬ የህይወት አቅጣጫዬን መለወጥ እንዳለብኝ ተሰምቶኛል።
#ተርሚናሉ_ዉስጥ
.
አረብ ወንዶች ያለመጠን የተርከፈከፉት ሽቶ ራሴ ላይ ወጣ። ተርሚናሉ ዉስጥ እየተዝለገለጉ ወዲያ ወዲህ ሲሉ ሆዴ ታወከ። መታጠቢያ ቤት ሄጄ ፊቴን በቀዝቃዛ ዉኃ ነከርኩ። ትንሽ ሻል ያለ
ስሜት ሲሰማኝ በወርቅ የተለበጠ ከሚመስል አግዳሚ ወንበር ላይ አንድ ጥግ ይዤ አረፍ አልኩኝ።
ለጊዜው በዙርያዬ የሚሆነውን ከማየት ዉጭ ሌላ እድል አልነበረኝም። አይኔን ብጨፍንም አረቦችን አያለሁ። አይኔን ብገልጥም አረቦችን አያለሁ። አማራጭ አልነበረኝም። ለካንስ አይንን መጨፈን ማየት የሚፈልጉትን ከማየት አይጋርድም። ዳያሪዬን ከእጅ ቦርሳዬ ዉስጥ ብታቀፈውም አእምሮዬ ባልተለመደ ሁኔታ ደንዝዞብኛል። በአየር መንገዱ አግዳሚ ቁጭ ብዬ ወጪ ወራጁን ስሜት አልባ ሆኜ አያለሁ።
የአረብ ጎታታ ወንዶች፣ በዚያ በሚዝለገለግ ነጭ ቀሚሳቸው ዉስጥ ሆነው አውሮፕላን ለመሳፈር እንደ
ግመል ይጎተታሉ። የቀሚሳቸው መጎተት ላያንስ በሩዝ የተወደረ ከርሳቸውን ይጎትታሉ፤ የከርሳቸው ሳያንስ ኩንታል ሻንጣቸውን ይጎትታሉ። የሻንጣቸው ሳያንስ ነጠላ ጫማቸውን ይጎትታሉ፤ የነጠላ ጫማቸው ሳያንስ ከረፈፍ ሚስቶቻቸውን ይጎትታሉ፣ የሚስቶቻቸው ሳያንስ ያልተቆነጠጡ አስራ ምናምን ልጆቻቸውን ይጎትታሉ። አራት ሚስቶቻቸውን እየነዱም ቢሆን አምስተኛ ሴት ከማየት አይመለሱም። ከአንድም ሁለት ሦስት አጁዛ አረቦች ከወዲያኛው የተርሚናሉ ሬስቶራንት ሆነው
እየሰረቁ ሲመለከቱኝ ዐይቻለሁ፡፡
በድጋሚ መታጠቢያ ቤት ሄጄ ተመለስኩ። ዛሬ ምግብ አልረጋ ብሎኛል።
ቀልቤ አይወዳቸውም። በተለይ እንዲህ ነጭ ቆብ በነጭ ቀሚስ ለብሰው ሳያቸው፣ በነጭ ኩባያ ወተት ከአናታቸው እየፈሰሰባቸው ስለሚመስለኝ የዝንብ አየር ማረፍያዎች እንጂ ሰዎች ሆነው አይታዩኝም።ሰው ነጭ ለብሶም ንፁህ ሆኖ ካልታየኝ መቼስ የሆነ ችግር አለበት ማለት ነው። ለምንድነው ፈጣሪ እኛን
ድሐ እነሱን ሐብታም ያረገው? እግዜር ምናቸው ማርኮት ይሆን አሻዋቸውን የባረከው? በረሃቸውን ያረጠበው?!
“የአረብ ጥላቻ የተፈጠረብኝ መቼ ነው?” ብዬ ለማስታወስ ሞከርኩ። ትዝ የሚለኝ ነገር የለም። ምናልባት ኡስማን ዘ ፒምፕ ስለሚጠላቸው እሱ ሳያውቀው አጋብቶብኝ ይሆን? አይደለም። ኡስማንን
ሳላውቀው በፊት አረብ የሚባል ፍጥረት ያስጠላኝ ነበር። ልጅ እያለሁ የጀመረኝ ይመስለኛል። አያቴ በነበረችበት ሰፈር። ባደኩበት ሰፈር፣ በነእማማ ዙበይዳ ሰፈር።
ልጅ እያለሁ ለተወሰነ ጊዜ ሴት አያቴ ታሳድገኝ ነበር። በሰፈራችን የምንወዳቸው፣ እማማ ዙበይዳ
የሚባሉ ሴት ነበሩ። የሆኑ ደርባባ አሮጊት ሴትዬ። ሰው ዝም ብሎ ይወዳቸው ነበር። ጎመን መንገድ ላይ ይሸጣሉ። በክረምት ደግሞ በቆሎ ይሸጣሉ። እማማ ዙበይዳን ሰፈሩ ሁሉ ለምን ይወዳቸው እንደነበር ግን በትክክል አላውቅም። እኔም እወዳቸው ነበር። ለምን እንደነበር ግን አላውቅም። “ነይ እስቲ አንቺ
ጎራዳ!" እያሉ ግንባሬን ይስሙኝ እንደነበር ብቻ ነው ትዝ የሚለኝ።
እማማ ዙበይዳ ባልም ዘመድም የላቸውም። በምድር ላይ ያለቻቸው ፋጤ ቀጮ ናት። የሳቸው ብቸኛ ልጅ ፉጤ ቀጮ ጅዳ ሄደች ተባለ። ሰፈሩ ሁሉ እማማ ዙበይዳ በቃ ሻሩ፣ አሁን ወርቅ በወርቅ ሊሆኑ ነው ብሎ ተነበየ። እሳቸውን ያገኘ ሰው ሁሉ “ፋጤ ቀጮ ጅዳ ነው አይደል የሄደችው?”፣
ትደውላለች”፣ “ደህና ናት ታዲያ፣ “አሁን ለመድኩ አለችፖ፣ ግህም፣ “በርቺ በሏት እንግዲህ!
ይለመዳል.ይለመዳል”፣ “ዋናው መበርታት ነውታዲያ”፣ “እ!” እያለ ከእማማ ዙበይዳ የበቆሎ እሸት
ወይ ጎመን ገዝቷቸው ያልፋል። በበጋ ጎመን በከረምት የበቆሎ እሸት በመሸጥ ነበር የሚተዳደሩት።
በዚያ ሁሉ የሰፈር ሰው ሳይታክቱ በዚያ እናታዊ ፈገግታቸው ታጅበው ስለ ልጃቸው ደኅንነት ምላሽ ይሰጣሉ። “እላሙዲሊላ አላሂ ወላሂ ደህና ናት!ዱዋ አርጉላት." ይላሉ፤ መልሰው መላልሰው።
ሲኖሩ ሲኖሩ.…የሆነ ጊዜ ላይ ልጃቸው ስልክ ደውላ አለቀሰች ተባለ። “ምን ሆንሽ” ሲሏት አትናገርም
ሲኖሩ ሲኖሩ…የሆነ ጊዜ ላይ ደግሞ መደወል አቆመች ተባለ። ደህንነቷን የሚነግራቸው ጠፋ። ጎመን ወይ
በቆሎ ለሚገዛቸው የሰፈር ሰው ሁሉ “አረብ አገር ስልክ ማድረግ ታውቅበታለህ?” እያሉ ይጠይቃሉ።
የተማረ የሚመስል ወጣት ሲመለከቱ ደግሞ “ልጄ! እስኪ ባክህ የጅዳ ስልክ ቁጥር ጽፈህ አምጣልኝ? ልጄ ናፈቀችኝ ይሉታል። የሷ ስልክ ቁጥር ግን የላቸውም። አንዳንድ ሰው ነገሩን ሊያስረዳቸው ሞከረ።ኾኖም ሊገባቸው አልቻለም። የሰፈሩን ሰው መሄጃ መቀመጫ አሳጡት። እርስዎ ስልኳን ፈልገው ያምጡ! እኛ እንደውልሎታለን” ሲባሉ እኔ ቁጥሯን ከየት አዉቄ” ነው መልሳቸው። እሷ ካልደወለች
እሳቸው ወደየት ብለው ይደውላሉ? አድራሻዋ አይታወቅ ነገር።
የሰፈሩ ሰው በሙሉ እማማ ዙበይዳ ሲያዝኑ አይቶ አዘነ። እማማ ዙበይዳ የደግነት ምሳሌ ነበሩ። ፋጤ
ቀጮ እጅግ ስትናፍቃቸው ግን ሰው ሰላም ሳይሉ ማለፍ ሁሉ ጀመሩ። የሚሸጡት ጎመን ጠወለገ።
ወዲያው ደግሞ ወገባቸው ጎበጠ። ከመቼው በእድሜያቸው ላይ ምዕተ ዓመት እንደጨመሩ። ሰው የልጁ ናፍቆት እንደ ኤድስ አመንምኖ ሊገድለው እንደሚችል ያየሁት በእማማ ዙበይዳ ነው።
ከ5 ዓመታት በኋላ ልጃቸው ፋጤ መጣች ተባለ። በዊልቸር ላይ ሆና። በጣም ከመወፍሯ የተነሳ ዊልቸሩ ጠበባት። ፋጤ ቀጮ ትባል የነበረችው የሆነች ሲንቢሮ በረሮ ስለበረች ነበር።ታዲያ ለምን ወፈረች? ተስማምቷት ነበር ማለት ነው?
👍4
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...ወደ ሆስፒታል ገሰገሰች
ፍፁም የህክምና ሰወች ተረባርበዉ ትንሽ ነብሱ መለስ አለች
ህመሙን የሚቀንስ መድሀኒት ተሰጥቶት ከዋጠ በኋላ
ከትራሱ ጋር ድጋሜ ጭንቅላቱን አገናኘዉ
እንደ ህመም ከባድ ወቅት የለም በጤነኝነት ስንኖር ዋጋ ሰጥተን
ባናስበዉም ስንታመም እና ስቃይ ዉስጥ ስንሆን ግን ሁሉ ነገራችን ተወስዶ ጤናችን ቢመለስ እንለምናለን
አብዛኞቻችን ለጤናችን አስበን አናዉቅም ጥንቃቄም የለንም
ምኞታችን ብር ላይ ያተኮረ ይሆናል ይለፋል ይለፋል በስተመጨረሻ ጤና ጠፍቶ ስንሰቃይ በህመም እጅ ዉስጥ
ስንወድቅ ብራችንን በሙሉ ለጤናችን መልሰን እናዉላለን
እንደ ፍፁም በአደጋ ህመም ላይ ሲወደቅ ግን ምን ይደረጋል
ሳያስበዉ እና ሳይጠብቀዉ ለዚህ በቃ የዚህ ሁሉ ጦስ ደግሞ
የፍቃዱ ተንኮል በተጨማሪም የቤዛዊት ማገናዘብ አለመቻል ናቸዉ።
እንቅልፍ መተኛት ባይፈልግም አልጋዉ ላይ ጋደም ብሎ
አይኖቹን ያንከራትታል
"እግሬ ለወደፊቱም መራመድ ባይችልስ?"
በድን እግሮቹን ለማንቀሳቀስ እየሞከረ
በፊት ልጅ እያለ ከጉዋደኞቹ ጋር እሩጫ ሲወዳደሩ አንደኛ እንደሚወጣ አስታዉሶ ፈገግ አለ ወደ አሁኑ ያለበት ህይወት ሲያስብ ግን እንባ እና ተስፋ መቁረጥ
ስለሚከቡት ላለማሰብ በብርድ ልብሱ ተጠቅልሎ ተኛ።
ቤዛዊት ብቻዋን እንድትሄድ ቤተሰቦቿ አልፈቀዱላትም ነበር
እህቷ አብራት ነበረች የተኛበትን አልጋም ስለምታዉቀዉ ልታሳያት ተከተለቻት።
ከቦታዉ ደርሰዉ አልጋዉ አጠገብ ቆሙ ተጠቅልሎ የተኛ አካል
በብርድ ልብሱ ቅርፅ ሰርቶ ይታያል ፍፁምን ለማየት የጓጓችዉ
ቤዛዊት እንዲነሳ እግሩን በእጆቿ ነካ ነካ ነረገችዉ አልሰማ አላት
"ፍ ፁ ም ..."
እህቷ የፍፁም እግሮች እንደማይሰሩ እንደማይሰሙ
ብታዉቅም ለመንገር ግን
ከብዷት እህቷ የምታረገዉን በሀዘኔታ ታያለች።
"ፍ ፁ ም ፍፁም..."
የሚሉ ቃላቶች የእዉነት እየሆኑ በቅዠት መልክ ስለተሰሙት
አቤት ለማለት አይኖቹን ከፍቶ ከብርድ ልብሱ ተገለጠ
ፊት ለፊቱ ቤዛዊት ቆማለች የጠቆረች የከሳች የተጎዳች መሰለዉ
ለማማተብ የዘረጋዉን እጁን አይኑን ባለማመን ጠራረገበት
እሷ ፊት ላይ ለስለስ ያለ ፈገግታ እየታየ ቀረበችዉ
ወደ ጉንጮቹ ከመጠጋቷ በፊት እህቷን አየት አርጋት ሳመችዉ
እህቷም ስለገባት እንዲያወሩ ጥላቸዉ ወደ ዉጪ ወጣች
የደረቀ እና የተጣበቀ ከንፈሩን እያለያየ
"እንዴት ነሽ ቤዚ..."
"ደህና ነኝ አንተስ አልተጎዳክም አደል ..."
በእጆቿ እየደባበሰችዉ
"ምንም አልተጎዳሁም..."
ህመሙን ዋጥ እያረገ እሷ ስለመጣች ደስ እያለዉ
ፊቷን አተኩሮ እያየ ፈግታዋ እንደድሮዋ አልደምቅልህ አለዉ
ደህንነቷ አሰጋዉ ጠፍታ ነበር የተባለዉን አስታዉሶ ልጠይቃት
አልጠይቃት እያለ በዉስጡ ማሰብ ጀመረ።
በእስዋ በኩልም ፍፁምን ታሞ አልጋ ላይ ስታየዉ ዉስጧ እርብሽ ብሏል ከትምህርት ቤት እንደተባረረ ወሬ
ስለሰማች በእሷ ምክንያት መሆኑን ገምታለች
የተገጨዉም ይሄኔ እኔን ለማዋራት ትምህርት ቤት ሲመጣ
ነዉ እያለች ሁለቱም በራሳቸዉ ሀሳብ ሰምጠዉ ቆይተዉ
"ቀሚስሽ ደሞ እንዴት ያምራል .."
ጨዋታ ለመጀመር አስቦ ለየት ስላለበት አለባበሷ
"የእማማ ስንቄ ነዉ እንዴት ጥሩ ሰዉ መሰሉክ የሆነ ቀን አብረን ሄደን አስተዋዉቅሀለዉ..."
መራመድ እንደማይችል ትዝ ስላለዉ ማዉራት እየከበደዉ
በመስማማት አንገቱን ነቀነቀ
"ምግብ በልተሀል ለምን ከአልጋ ወርደህ አትቀመጥም "
ፈጠን ያለ ጥያቄ ጠየቀችዉ
"በልቻለሁ.."
ተስፋ በቆረጠ አነጋገር
ቤዛዊት መቀመጥ ብቻ ሳይሆን ተነስቶ ተቃቅፈዉ
የሆድ የሆዳቸዉን እያወሩ ከሚጨንቀዉ ሆስፒታል
ፍፁምን ይዛዉ ብትወጣ ደስታዋ ነዉ
ነገር ግን ፍፁም መንቀሳቀስ የፈለገ አልመሰላትም
"ተቀይመሀኛል እንዴ መጥቼ ስላልጠየኩህ"
ከንፈሯን እያጣመመች
"አረ አልተቀየምኩሽም"
እጆቹን ሰዶ እጆን ያዛት
"እሺ ተነስ..."
አይኖቹን እስዋ ላይ ተክሎ እግሮቹን ለማንቀሳቀስ መታገል ጀመረ
"እ ህ ..........አ"
እየከበደዉ እልህ እየተናነቀዉ በእጆቹ ታግዞ
አልጋዉ ጠርዝ ላይ በመከራ ተቀመጠ
ቤዛዊት ግራ ተጋብታ እያየችዉ ነዉ ልታግዘዉ እየሞከረች
እንዳትረዳዉ በእጆቹ ምልክት ስላሳያት ፈዛ በሀዘኔታ ታየዋለች
በደንብ አልተሻለዉም በማለት እንባዋን ለመቆጣጠር እየታገለች
ከጀርባዋ ያለዉን ዊልቸር እየጠቆማት
"እሱን ጠጋ አርጊልኝ"
አዘዛት
ላለ ማልቀስ እየታገለች አስጠጋችለት ከአልጋዉ ወርዶ
ዊልቸሩ ላይ ሊቀመጥ ሲል ግን
የዊልቸሩ ጎማወች ስለሚንቀሳቀሱ ለመቀመጥ ሲታገል
ሚዛኑን ሳቶ ከመዉደቅ ቤዛዊት በእጆቿ ደግፋ አተረፈችዉ
ተደናግጠዉ ተያዩ ወድያዉ እንዲቀመጥ ካገዘችዉ በኋላ መሳቅ ጀመሩ።
የቤዛዊት እህት ተመልሳ ወደ ፍፁም እና ቤዛዊት ተጠጋች
ልብ አላሏትም ሁለቱም የሞቀ ጨዋታ ላይ ናቸዉ
እስከ አሁን ይነግራታል ብላ በማሰብ
"እግርህ አሁን ለዉጥ አለዉ..."
ወሬያቸዉን አቋርጠዉ ተመለከቷት
"ጥሩ ነዉ ለዉጥ አለዉ "
አላት እና ፈገግ አለ ቤዛዊት ባትኖር መዉደቁ እንደ ነበር
እያስታወሰ የቤዛዊት እህትም ፊቱ ላይ ፈገግታ ስታይ ሳቀች
ፈገግታዋ ከቤዛዊት ጋር ይመሳሰላል ፍፁም ተገርሞ አያት በልቡ
"ቁጭ ቤዛዊትን" እያለ
ቤዛዊት የእህቷን አሳሳቅ አልወደደችዉም ደስ አላላትም
ዉስጧ ንዴት እየተቀጣጠለ ነዉ ህመሟ መንስኤ ነዉ የሚፈልገዉ
በተለይ የፍፁምንም እህቷን እያየ መሳቁን ስታይ
"እገላታለሁ"
ስትል በታመዉ ህሊናዋ እህቷ ላይ ዛተች።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...ወደ ሆስፒታል ገሰገሰች
ፍፁም የህክምና ሰወች ተረባርበዉ ትንሽ ነብሱ መለስ አለች
ህመሙን የሚቀንስ መድሀኒት ተሰጥቶት ከዋጠ በኋላ
ከትራሱ ጋር ድጋሜ ጭንቅላቱን አገናኘዉ
እንደ ህመም ከባድ ወቅት የለም በጤነኝነት ስንኖር ዋጋ ሰጥተን
ባናስበዉም ስንታመም እና ስቃይ ዉስጥ ስንሆን ግን ሁሉ ነገራችን ተወስዶ ጤናችን ቢመለስ እንለምናለን
አብዛኞቻችን ለጤናችን አስበን አናዉቅም ጥንቃቄም የለንም
ምኞታችን ብር ላይ ያተኮረ ይሆናል ይለፋል ይለፋል በስተመጨረሻ ጤና ጠፍቶ ስንሰቃይ በህመም እጅ ዉስጥ
ስንወድቅ ብራችንን በሙሉ ለጤናችን መልሰን እናዉላለን
እንደ ፍፁም በአደጋ ህመም ላይ ሲወደቅ ግን ምን ይደረጋል
ሳያስበዉ እና ሳይጠብቀዉ ለዚህ በቃ የዚህ ሁሉ ጦስ ደግሞ
የፍቃዱ ተንኮል በተጨማሪም የቤዛዊት ማገናዘብ አለመቻል ናቸዉ።
እንቅልፍ መተኛት ባይፈልግም አልጋዉ ላይ ጋደም ብሎ
አይኖቹን ያንከራትታል
"እግሬ ለወደፊቱም መራመድ ባይችልስ?"
በድን እግሮቹን ለማንቀሳቀስ እየሞከረ
በፊት ልጅ እያለ ከጉዋደኞቹ ጋር እሩጫ ሲወዳደሩ አንደኛ እንደሚወጣ አስታዉሶ ፈገግ አለ ወደ አሁኑ ያለበት ህይወት ሲያስብ ግን እንባ እና ተስፋ መቁረጥ
ስለሚከቡት ላለማሰብ በብርድ ልብሱ ተጠቅልሎ ተኛ።
ቤዛዊት ብቻዋን እንድትሄድ ቤተሰቦቿ አልፈቀዱላትም ነበር
እህቷ አብራት ነበረች የተኛበትን አልጋም ስለምታዉቀዉ ልታሳያት ተከተለቻት።
ከቦታዉ ደርሰዉ አልጋዉ አጠገብ ቆሙ ተጠቅልሎ የተኛ አካል
በብርድ ልብሱ ቅርፅ ሰርቶ ይታያል ፍፁምን ለማየት የጓጓችዉ
ቤዛዊት እንዲነሳ እግሩን በእጆቿ ነካ ነካ ነረገችዉ አልሰማ አላት
"ፍ ፁ ም ..."
እህቷ የፍፁም እግሮች እንደማይሰሩ እንደማይሰሙ
ብታዉቅም ለመንገር ግን
ከብዷት እህቷ የምታረገዉን በሀዘኔታ ታያለች።
"ፍ ፁ ም ፍፁም..."
የሚሉ ቃላቶች የእዉነት እየሆኑ በቅዠት መልክ ስለተሰሙት
አቤት ለማለት አይኖቹን ከፍቶ ከብርድ ልብሱ ተገለጠ
ፊት ለፊቱ ቤዛዊት ቆማለች የጠቆረች የከሳች የተጎዳች መሰለዉ
ለማማተብ የዘረጋዉን እጁን አይኑን ባለማመን ጠራረገበት
እሷ ፊት ላይ ለስለስ ያለ ፈገግታ እየታየ ቀረበችዉ
ወደ ጉንጮቹ ከመጠጋቷ በፊት እህቷን አየት አርጋት ሳመችዉ
እህቷም ስለገባት እንዲያወሩ ጥላቸዉ ወደ ዉጪ ወጣች
የደረቀ እና የተጣበቀ ከንፈሩን እያለያየ
"እንዴት ነሽ ቤዚ..."
"ደህና ነኝ አንተስ አልተጎዳክም አደል ..."
በእጆቿ እየደባበሰችዉ
"ምንም አልተጎዳሁም..."
ህመሙን ዋጥ እያረገ እሷ ስለመጣች ደስ እያለዉ
ፊቷን አተኩሮ እያየ ፈግታዋ እንደድሮዋ አልደምቅልህ አለዉ
ደህንነቷ አሰጋዉ ጠፍታ ነበር የተባለዉን አስታዉሶ ልጠይቃት
አልጠይቃት እያለ በዉስጡ ማሰብ ጀመረ።
በእስዋ በኩልም ፍፁምን ታሞ አልጋ ላይ ስታየዉ ዉስጧ እርብሽ ብሏል ከትምህርት ቤት እንደተባረረ ወሬ
ስለሰማች በእሷ ምክንያት መሆኑን ገምታለች
የተገጨዉም ይሄኔ እኔን ለማዋራት ትምህርት ቤት ሲመጣ
ነዉ እያለች ሁለቱም በራሳቸዉ ሀሳብ ሰምጠዉ ቆይተዉ
"ቀሚስሽ ደሞ እንዴት ያምራል .."
ጨዋታ ለመጀመር አስቦ ለየት ስላለበት አለባበሷ
"የእማማ ስንቄ ነዉ እንዴት ጥሩ ሰዉ መሰሉክ የሆነ ቀን አብረን ሄደን አስተዋዉቅሀለዉ..."
መራመድ እንደማይችል ትዝ ስላለዉ ማዉራት እየከበደዉ
በመስማማት አንገቱን ነቀነቀ
"ምግብ በልተሀል ለምን ከአልጋ ወርደህ አትቀመጥም "
ፈጠን ያለ ጥያቄ ጠየቀችዉ
"በልቻለሁ.."
ተስፋ በቆረጠ አነጋገር
ቤዛዊት መቀመጥ ብቻ ሳይሆን ተነስቶ ተቃቅፈዉ
የሆድ የሆዳቸዉን እያወሩ ከሚጨንቀዉ ሆስፒታል
ፍፁምን ይዛዉ ብትወጣ ደስታዋ ነዉ
ነገር ግን ፍፁም መንቀሳቀስ የፈለገ አልመሰላትም
"ተቀይመሀኛል እንዴ መጥቼ ስላልጠየኩህ"
ከንፈሯን እያጣመመች
"አረ አልተቀየምኩሽም"
እጆቹን ሰዶ እጆን ያዛት
"እሺ ተነስ..."
አይኖቹን እስዋ ላይ ተክሎ እግሮቹን ለማንቀሳቀስ መታገል ጀመረ
"እ ህ ..........አ"
እየከበደዉ እልህ እየተናነቀዉ በእጆቹ ታግዞ
አልጋዉ ጠርዝ ላይ በመከራ ተቀመጠ
ቤዛዊት ግራ ተጋብታ እያየችዉ ነዉ ልታግዘዉ እየሞከረች
እንዳትረዳዉ በእጆቹ ምልክት ስላሳያት ፈዛ በሀዘኔታ ታየዋለች
በደንብ አልተሻለዉም በማለት እንባዋን ለመቆጣጠር እየታገለች
ከጀርባዋ ያለዉን ዊልቸር እየጠቆማት
"እሱን ጠጋ አርጊልኝ"
አዘዛት
ላለ ማልቀስ እየታገለች አስጠጋችለት ከአልጋዉ ወርዶ
ዊልቸሩ ላይ ሊቀመጥ ሲል ግን
የዊልቸሩ ጎማወች ስለሚንቀሳቀሱ ለመቀመጥ ሲታገል
ሚዛኑን ሳቶ ከመዉደቅ ቤዛዊት በእጆቿ ደግፋ አተረፈችዉ
ተደናግጠዉ ተያዩ ወድያዉ እንዲቀመጥ ካገዘችዉ በኋላ መሳቅ ጀመሩ።
የቤዛዊት እህት ተመልሳ ወደ ፍፁም እና ቤዛዊት ተጠጋች
ልብ አላሏትም ሁለቱም የሞቀ ጨዋታ ላይ ናቸዉ
እስከ አሁን ይነግራታል ብላ በማሰብ
"እግርህ አሁን ለዉጥ አለዉ..."
ወሬያቸዉን አቋርጠዉ ተመለከቷት
"ጥሩ ነዉ ለዉጥ አለዉ "
አላት እና ፈገግ አለ ቤዛዊት ባትኖር መዉደቁ እንደ ነበር
እያስታወሰ የቤዛዊት እህትም ፊቱ ላይ ፈገግታ ስታይ ሳቀች
ፈገግታዋ ከቤዛዊት ጋር ይመሳሰላል ፍፁም ተገርሞ አያት በልቡ
"ቁጭ ቤዛዊትን" እያለ
ቤዛዊት የእህቷን አሳሳቅ አልወደደችዉም ደስ አላላትም
ዉስጧ ንዴት እየተቀጣጠለ ነዉ ህመሟ መንስኤ ነዉ የሚፈልገዉ
በተለይ የፍፁምንም እህቷን እያየ መሳቁን ስታይ
"እገላታለሁ"
ስትል በታመዉ ህሊናዋ እህቷ ላይ ዛተች።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍5
#ልጩህበት!!
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ምኑን ከምኑ ነው እምመርጠው?
"ወይ ኤደንን እኔ ሄጄ እንዳናግራት መፍቀድ ካልሆነ ከልጅቷ ጋር ፍቅር ጀምረህ ኤደንን መርሳት!"
ጆሲ አምርሯል ግራ ገባኝ ። ኤዱን እንዲያናግራት በጭራሽ እንደማልፈልግ አውቃለሁ ሁለተኛው ምርጫ ደግሞ ጡጫ ሆነብኝ ቢሆንም•••
ውስጤ እንደማይሆን እያወቀው ከዳኒ ጭቅጭቅ ለመገላገል ስል •እሺ አልኩት
በቃ እሺ!
"በቃ እሺ ምን በየትኛው ሀሳብ?"
"በቃ ካልካት ልጅ ጋር እንቀራረባለና!"
አዋ ዳንዬ አንዳንዴ እንኳን እንደዚህ እሺ በለኝ እስቲ ዳንዬ ዋናው መቀራረባችሁ ነው ከዛ ቡሀላ ሌላው ይከተላል ኤዱንስ ቢሆን ሳትቀርባት አላፈቀርካት!"
እሺ አልኩህ እኮ በቃ አልኩት። ከዛች ሰአት ጀምሮ ጆሲ ስራውን ጀመረ ።
ልጅቷን እቤት ያመጣትና መጣሁ ብሎ በመውጣት ጥሎን ይጠፋል።
መቀራረብ ብንጀምርም እውነቱን ለመናገር እሷን ለብቻዋ ከማገኛት ይልቅ ኤዱን ከልጁ ጋር ሆና ባገኛት እመርጥ ነበር።
ለሶስት ወር ልጅቷ እና ጆሲ ስራ አደረጉኝ የተቀየረ ስሜት አልነበረም በመሀል ድንገት ለተከታታይ ቀናት ጥፍት አለች።
ለስድስት ቀን ያህል ድምጿንም ስልኳንም አጥፍታ ከተሰወረች ቡሀላ በሰባተኛው ቀን እኔና ጆሲ ሰፈር ውስጥ ቁጭ ባልንበት እራሷ ጆሲ ስልክ ላይ ደወለች።
ስልኩን ለሁለታችንም እንዲሰማ አደረገና •••
" ምን ሆነሽ ነው የጠፋሽው?" የጆሲ ጥያቄ ነበር
" ምን ላድርግ ጓደኛህ ኤደን የምትባል ሰይጣን አጠናፍራዋለች መሰለኝ በተገናኘን ቁጥር ወሬው ሁሉ ከሷ አያልፍም እንዴ እኔ ልጅቷን ሳላውቃት ሁላ እንድጠላት ነው ያደርገኝ በጣም ነው የተጎዳሁት ጆሲ ከቻልክ ጓደኛህን ወይ አሳክመው ወይ ፀበል ውሰደው " ብላው እርፍ አለች ።
ጆሲ ዘወር ብሎ ሲያፈጥምኝ ተነስቼ ካጠገቡ ሄድኩ።
ከዛን ቀን ቡሀላ ከጆሲ ጋር ስለምንም ነገር ሳናወራ የኤዱ ምርቃት ሰባት ቀን( ሳምንት) ቀረው ።
ስድስት ቀን ሲቀረው ደውላ ቤተሰቦቿ ለምርቃቷ ከሁለት ቀን ቡሀላ እንደሚመጡ እና ከምርቃቷ ቡሀላ አብራቸው ወደ አዲስ አበባ እንደምትሄድ ነገረችኝ ።
ይህ ንግግሯ መብረቅ በሉት ለኔ ።ጨነቀኝ ።
ያን ቀን ጠጥቼ ብገባም እንቅልፍ እንቢ አለኝ እኩለ ለሊት ላይ አንድ ሀሰብ መጣልኝ።
ተነስቼ ለኤዱ ደብዳቤ መፃፍ ጀመርኩ•••
••••• ለኤደን
ኤዱዬ ህይወትን መራራም ጣፋጭም እንድትሆን ካደረጓት ምክንያቶች አንዱ ምን እንደሆነ ታውቂያለሽ?
እኛ ሰዎች ስላለፈው እና ስለ አሁኑ እንጂ ነገ ምን እንደሚፈጠር እለማወቃችን ነው ።
ነገን አለማወቅ የራሱ የሆነ ብዙ ጥሩም መጥፎም ገፅታዎች አሉት።
ነገ የሚከሰተውን መጥፎ ነገር ቀድመን ስናውቅ እና ነገ የሚከሰተውን ጥሩ ነገር ቀድመን ስናውቅ የሚሰሙን ሁለት ተቃራኒ ስሜቶች ናቸው።
እንዲህ ያልኩሽ አሁን የሆንኩትን ነገር ያኔ በዛ በብርድ እዛ ሆቴል በር ላይ ቆመሽ ባየሁሽ ሰአት ቀድሜ ባውቀው ምን እወስን ነበር ብዬ ሁሌም እራሴን ስለምጠይቀው ነው
"አሁን ምን ሆንክ? ትይ ይሆኖል። ምንም አታውቂምና ጥያቄሽ ልክ ነው የኔ ስስት ያኔ ካሁን ቡሀላ ወንድምሽ ነኝ ስልሽ አንቺም ተቀብለሽ የእውነት ወንድም አድርገሽኛልና ምን ሆንክ ብትይኝ ባንቺ አይፈረድም እኔ ግን ብዙ ሆኛለሁ አንቺን በማፍቀሬ እንኳን አንቺ እኔ እንኳን የማላውቀው ሌላ ዳኒ እንደሆኑኩ አውቃለሁ።
ኤዱዬ አፈቅርሻለሁ!
ይህን ስታነቢ ምን ትይኝ ይሆን?
በቃሌ የማልገኝ እራስ ወዳድ ነኝ አደል ኤዱዬ?
በጣም ይቅርታ።
ከግዜ ቡሀላ ለኔም ባልገባኝ መንገድ ውስጤ ተቀያይሮ ካቅሜ በላይ ሆኖብኝ እንጂ ያኔ ወንድም እሆንሻለሁ ከጎንሽ ነኝ እንደወንድምሽ እይኝ ያልኩሽ ግን ከልቤ ነበር!።
ሁሌም ቃሌን ያጠፍኩ መስሎ ይሰማኛል ላንቺ ስላልነገርኩሽ ምንም ባትይኝም ብታውቅ ምን ትለኛለች እያልኩ ከመሸማቀቅ አልዳንኩም።
ፍቅር የሻቱትን ማግኘት ብቻ አይደለምና የኔ እንደማትሆኚ እያሰብኩም አፈቅርሻለሁ።
ከምንም ነገር በላይ አንቺን በእውኔም በህልሜም ማየት፣ ስላንቺ ማሰብ ፣ ስላንቺ ማውራት ያስደስተኛል ። ካንቺ ውጪ ሁሉ ነገር አልጥምህ ካለኝ ወራቶች ተቆጥረዋል።
"ታድያ በነበረን ግዜ በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ውስጥ ከነበርክ እንዴት አልነገርከኝም?
ወይም እንዴት ከፊትህ መረዳት አልቻልኩም? " ትይኝ ይሆናል
በፍቅር ንዳድ ከመለብለብ በላይ በልብ ውስጥ ያለውን የፍቅር እሳት አውጥቶ ላፈቀሩት ሰው ንዳዱን ማሳየት ለብዙ አፍቃሪዎች ከባድ ነው።
እኔን ግን አውጥቶ ከመናገሩም በላይ ከባድ የሆነብኝ ብነግርሽ የሚሰማሽን ስሜት ማሰብ ነው።
ፍቅረኛሽ ሆኜ ቢሆን አሁን ወንድምሽ በመሆኔ የተደሰትሽውን ያክል እምትደሰቺ መስሎ አይታየኝም ።
ካፌ ሻይ ቡና እያልን ፊት ለፊቴ ቁጭ ብለሽ ከናት ካባቴ ባትወለድም አንተን የመሰለ ወንድም በስጦታ ስለሰጠኝ እያልሽ ፈጣሪን ስታመሰግኚ ስሰማ እንኳን ልነግርሽ ማፍቀሬን የምታውቂብኝ እየመሰለኝ ምክንያት ፈጥሬ ካጠገብሽ እሽሻለሁ ።
ጆሲ ጓደኛዬ ምን እንደሚለኝ ታውቂያለሽ ኤዱዬ?
••••" አንተኮ መፍታት ያቃተህ መጀመሪያ ላይ እራስህ አጥብቀህ ያሰርከውን ቋጠሮ ነው አልፈታ ባለህ ቁጥር ደግሞ በንዴት ለመበጠስ እየሞከርክ የበለጠ ታጠብቀዋለህ!" ይለኛል
እውነቱን ነው ትዝ ይልሻል እዱዬ?
ስለመሲ ስናወራ አንድ ሰው ውለታ ውሎልሽ ውለታውን በመንተራስ ከፍላጎትሽ ውጪ የሚጫንሽ ከሆነ ውለታ ሳያስቀድም ተመሳሳይ ጥያቄ ከሚጠይቅሽ ሰው በላይ እርኩስ ነው ብዬሽ ነበር ።
እኔም የፍቅር ጥያቄዬ ካደረኩልሽ ትንሽ ውለታ ጋር እንዳይያያዝብኝ ፈራሁ።
አንቺንም እኔን ወንድም እንጂ ፍቅረኛ የማድረግ ፍላጎት ውስጥሽ ሳይኖር የምጫንሽ ጥያቄዬን ባለመቀበልና እኔን ባለማስከፋት መሀል ሆነሽ የምትጨነቂ መስሎ ታየኝ ።
በዚህ መሀል እናንተ ባታዩኝም ከልጁ ጋር ሆኖችሁ ብዙ ቦታዎች ታጋጥሙኝ ጀመር።
ያኔ በሱም ባንቺም ሳይሆን በራሴ ይበልጥ መናደድ ጀመርኩ ።
ህመምህ መድሀኒት የለውም አትድንም እንደተባለ በሽተኛ የፍቅር ህመሜ ፈውስ የሆንሽውን አንቺን የኔ እንደማላደርግሽ ተረዳሁ ።
ኤዱዬ በመመረቅሽ እንኳን ደስ አለሽ!
በመመረቅሽ የተሰማሽን ደስታ ትንሽ ሳታጣጥሚውና ከድሬ ሳትወጪ አንብበሽው ሌላ ስሜት ውስጥ እንድትገቢ ስላልፈለኩ ነው ይህን ደብዳቤ በእጅሽ ሳልሰጥሽ ከምርቃቷ ቡሀላ ወደ አዲስ አባባ ስሸኛት ሳታየኝ የልብስ ሻንጣዋ ውስጥ አስቀምጥላታለሁ ባየችው ግዜ ትየው ብዬ የወሰንኩት።
በነበረን ስሜት ወንድምሽ ሆኜ ልሸኝሽ ቀናቶች ቀርተዋል ለዛም ተዘጋጅቻለሁ ።
የኔ ኤደን ዛሬም ቢሆን ስላወኩሽ ደስተኛ ነኝ።
የማንም ሁኚ እኔ ግን አፈቅርሻለሁ። መቼም ቢሆን አረሳሽም። ዝምምምም ብዬ ሳፈቅርሽ እኖራለሁ።
ሰላም ሁኚ!
ዳኒ ነኝ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ምኑን ከምኑ ነው እምመርጠው?
"ወይ ኤደንን እኔ ሄጄ እንዳናግራት መፍቀድ ካልሆነ ከልጅቷ ጋር ፍቅር ጀምረህ ኤደንን መርሳት!"
ጆሲ አምርሯል ግራ ገባኝ ። ኤዱን እንዲያናግራት በጭራሽ እንደማልፈልግ አውቃለሁ ሁለተኛው ምርጫ ደግሞ ጡጫ ሆነብኝ ቢሆንም•••
ውስጤ እንደማይሆን እያወቀው ከዳኒ ጭቅጭቅ ለመገላገል ስል •እሺ አልኩት
በቃ እሺ!
"በቃ እሺ ምን በየትኛው ሀሳብ?"
"በቃ ካልካት ልጅ ጋር እንቀራረባለና!"
አዋ ዳንዬ አንዳንዴ እንኳን እንደዚህ እሺ በለኝ እስቲ ዳንዬ ዋናው መቀራረባችሁ ነው ከዛ ቡሀላ ሌላው ይከተላል ኤዱንስ ቢሆን ሳትቀርባት አላፈቀርካት!"
እሺ አልኩህ እኮ በቃ አልኩት። ከዛች ሰአት ጀምሮ ጆሲ ስራውን ጀመረ ።
ልጅቷን እቤት ያመጣትና መጣሁ ብሎ በመውጣት ጥሎን ይጠፋል።
መቀራረብ ብንጀምርም እውነቱን ለመናገር እሷን ለብቻዋ ከማገኛት ይልቅ ኤዱን ከልጁ ጋር ሆና ባገኛት እመርጥ ነበር።
ለሶስት ወር ልጅቷ እና ጆሲ ስራ አደረጉኝ የተቀየረ ስሜት አልነበረም በመሀል ድንገት ለተከታታይ ቀናት ጥፍት አለች።
ለስድስት ቀን ያህል ድምጿንም ስልኳንም አጥፍታ ከተሰወረች ቡሀላ በሰባተኛው ቀን እኔና ጆሲ ሰፈር ውስጥ ቁጭ ባልንበት እራሷ ጆሲ ስልክ ላይ ደወለች።
ስልኩን ለሁለታችንም እንዲሰማ አደረገና •••
" ምን ሆነሽ ነው የጠፋሽው?" የጆሲ ጥያቄ ነበር
" ምን ላድርግ ጓደኛህ ኤደን የምትባል ሰይጣን አጠናፍራዋለች መሰለኝ በተገናኘን ቁጥር ወሬው ሁሉ ከሷ አያልፍም እንዴ እኔ ልጅቷን ሳላውቃት ሁላ እንድጠላት ነው ያደርገኝ በጣም ነው የተጎዳሁት ጆሲ ከቻልክ ጓደኛህን ወይ አሳክመው ወይ ፀበል ውሰደው " ብላው እርፍ አለች ።
ጆሲ ዘወር ብሎ ሲያፈጥምኝ ተነስቼ ካጠገቡ ሄድኩ።
ከዛን ቀን ቡሀላ ከጆሲ ጋር ስለምንም ነገር ሳናወራ የኤዱ ምርቃት ሰባት ቀን( ሳምንት) ቀረው ።
ስድስት ቀን ሲቀረው ደውላ ቤተሰቦቿ ለምርቃቷ ከሁለት ቀን ቡሀላ እንደሚመጡ እና ከምርቃቷ ቡሀላ አብራቸው ወደ አዲስ አበባ እንደምትሄድ ነገረችኝ ።
ይህ ንግግሯ መብረቅ በሉት ለኔ ።ጨነቀኝ ።
ያን ቀን ጠጥቼ ብገባም እንቅልፍ እንቢ አለኝ እኩለ ለሊት ላይ አንድ ሀሰብ መጣልኝ።
ተነስቼ ለኤዱ ደብዳቤ መፃፍ ጀመርኩ•••
••••• ለኤደን
ኤዱዬ ህይወትን መራራም ጣፋጭም እንድትሆን ካደረጓት ምክንያቶች አንዱ ምን እንደሆነ ታውቂያለሽ?
እኛ ሰዎች ስላለፈው እና ስለ አሁኑ እንጂ ነገ ምን እንደሚፈጠር እለማወቃችን ነው ።
ነገን አለማወቅ የራሱ የሆነ ብዙ ጥሩም መጥፎም ገፅታዎች አሉት።
ነገ የሚከሰተውን መጥፎ ነገር ቀድመን ስናውቅ እና ነገ የሚከሰተውን ጥሩ ነገር ቀድመን ስናውቅ የሚሰሙን ሁለት ተቃራኒ ስሜቶች ናቸው።
እንዲህ ያልኩሽ አሁን የሆንኩትን ነገር ያኔ በዛ በብርድ እዛ ሆቴል በር ላይ ቆመሽ ባየሁሽ ሰአት ቀድሜ ባውቀው ምን እወስን ነበር ብዬ ሁሌም እራሴን ስለምጠይቀው ነው
"አሁን ምን ሆንክ? ትይ ይሆኖል። ምንም አታውቂምና ጥያቄሽ ልክ ነው የኔ ስስት ያኔ ካሁን ቡሀላ ወንድምሽ ነኝ ስልሽ አንቺም ተቀብለሽ የእውነት ወንድም አድርገሽኛልና ምን ሆንክ ብትይኝ ባንቺ አይፈረድም እኔ ግን ብዙ ሆኛለሁ አንቺን በማፍቀሬ እንኳን አንቺ እኔ እንኳን የማላውቀው ሌላ ዳኒ እንደሆኑኩ አውቃለሁ።
ኤዱዬ አፈቅርሻለሁ!
ይህን ስታነቢ ምን ትይኝ ይሆን?
በቃሌ የማልገኝ እራስ ወዳድ ነኝ አደል ኤዱዬ?
በጣም ይቅርታ።
ከግዜ ቡሀላ ለኔም ባልገባኝ መንገድ ውስጤ ተቀያይሮ ካቅሜ በላይ ሆኖብኝ እንጂ ያኔ ወንድም እሆንሻለሁ ከጎንሽ ነኝ እንደወንድምሽ እይኝ ያልኩሽ ግን ከልቤ ነበር!።
ሁሌም ቃሌን ያጠፍኩ መስሎ ይሰማኛል ላንቺ ስላልነገርኩሽ ምንም ባትይኝም ብታውቅ ምን ትለኛለች እያልኩ ከመሸማቀቅ አልዳንኩም።
ፍቅር የሻቱትን ማግኘት ብቻ አይደለምና የኔ እንደማትሆኚ እያሰብኩም አፈቅርሻለሁ።
ከምንም ነገር በላይ አንቺን በእውኔም በህልሜም ማየት፣ ስላንቺ ማሰብ ፣ ስላንቺ ማውራት ያስደስተኛል ። ካንቺ ውጪ ሁሉ ነገር አልጥምህ ካለኝ ወራቶች ተቆጥረዋል።
"ታድያ በነበረን ግዜ በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ውስጥ ከነበርክ እንዴት አልነገርከኝም?
ወይም እንዴት ከፊትህ መረዳት አልቻልኩም? " ትይኝ ይሆናል
በፍቅር ንዳድ ከመለብለብ በላይ በልብ ውስጥ ያለውን የፍቅር እሳት አውጥቶ ላፈቀሩት ሰው ንዳዱን ማሳየት ለብዙ አፍቃሪዎች ከባድ ነው።
እኔን ግን አውጥቶ ከመናገሩም በላይ ከባድ የሆነብኝ ብነግርሽ የሚሰማሽን ስሜት ማሰብ ነው።
ፍቅረኛሽ ሆኜ ቢሆን አሁን ወንድምሽ በመሆኔ የተደሰትሽውን ያክል እምትደሰቺ መስሎ አይታየኝም ።
ካፌ ሻይ ቡና እያልን ፊት ለፊቴ ቁጭ ብለሽ ከናት ካባቴ ባትወለድም አንተን የመሰለ ወንድም በስጦታ ስለሰጠኝ እያልሽ ፈጣሪን ስታመሰግኚ ስሰማ እንኳን ልነግርሽ ማፍቀሬን የምታውቂብኝ እየመሰለኝ ምክንያት ፈጥሬ ካጠገብሽ እሽሻለሁ ።
ጆሲ ጓደኛዬ ምን እንደሚለኝ ታውቂያለሽ ኤዱዬ?
••••" አንተኮ መፍታት ያቃተህ መጀመሪያ ላይ እራስህ አጥብቀህ ያሰርከውን ቋጠሮ ነው አልፈታ ባለህ ቁጥር ደግሞ በንዴት ለመበጠስ እየሞከርክ የበለጠ ታጠብቀዋለህ!" ይለኛል
እውነቱን ነው ትዝ ይልሻል እዱዬ?
ስለመሲ ስናወራ አንድ ሰው ውለታ ውሎልሽ ውለታውን በመንተራስ ከፍላጎትሽ ውጪ የሚጫንሽ ከሆነ ውለታ ሳያስቀድም ተመሳሳይ ጥያቄ ከሚጠይቅሽ ሰው በላይ እርኩስ ነው ብዬሽ ነበር ።
እኔም የፍቅር ጥያቄዬ ካደረኩልሽ ትንሽ ውለታ ጋር እንዳይያያዝብኝ ፈራሁ።
አንቺንም እኔን ወንድም እንጂ ፍቅረኛ የማድረግ ፍላጎት ውስጥሽ ሳይኖር የምጫንሽ ጥያቄዬን ባለመቀበልና እኔን ባለማስከፋት መሀል ሆነሽ የምትጨነቂ መስሎ ታየኝ ።
በዚህ መሀል እናንተ ባታዩኝም ከልጁ ጋር ሆኖችሁ ብዙ ቦታዎች ታጋጥሙኝ ጀመር።
ያኔ በሱም ባንቺም ሳይሆን በራሴ ይበልጥ መናደድ ጀመርኩ ።
ህመምህ መድሀኒት የለውም አትድንም እንደተባለ በሽተኛ የፍቅር ህመሜ ፈውስ የሆንሽውን አንቺን የኔ እንደማላደርግሽ ተረዳሁ ።
ኤዱዬ በመመረቅሽ እንኳን ደስ አለሽ!
በመመረቅሽ የተሰማሽን ደስታ ትንሽ ሳታጣጥሚውና ከድሬ ሳትወጪ አንብበሽው ሌላ ስሜት ውስጥ እንድትገቢ ስላልፈለኩ ነው ይህን ደብዳቤ በእጅሽ ሳልሰጥሽ ከምርቃቷ ቡሀላ ወደ አዲስ አባባ ስሸኛት ሳታየኝ የልብስ ሻንጣዋ ውስጥ አስቀምጥላታለሁ ባየችው ግዜ ትየው ብዬ የወሰንኩት።
በነበረን ስሜት ወንድምሽ ሆኜ ልሸኝሽ ቀናቶች ቀርተዋል ለዛም ተዘጋጅቻለሁ ።
የኔ ኤደን ዛሬም ቢሆን ስላወኩሽ ደስተኛ ነኝ።
የማንም ሁኚ እኔ ግን አፈቅርሻለሁ። መቼም ቢሆን አረሳሽም። ዝምምምም ብዬ ሳፈቅርሽ እኖራለሁ።
ሰላም ሁኚ!
ዳኒ ነኝ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍3
#ለኀጥአን_የመጣ
#ክፍል_ሀያ_ሶስት(የመጨረሻ ክፍል)
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
አስር ስዓት ሲሆን አውቶብሱ ካምቢያ ከምትባል ከተማ አደረሰን። የመጨረሻ ፌርማታው ነበር። ፍሪ ታውንን ለቀን
ከመጣን ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳፋሪዎቹ ፊት ተፈታ። ግን ብዙም አልቆየም! ድንበር ለማለፍ ክፍያ ስንጠየቅ የሁሉም ፊት መልሶ ተኮማተረ አጉረመረምን፡፡ ሁሉም ሰው ከካልሲው
ውስጥ፣ ከውስጥ ሱሪ እና ከረባት ሳይቀር የተረፈ ገንዘብ ካለ ፈለገ። ሶስት መቶ ሊዮንስ (የሴራሊዮን ገንዘብ) ነበር
የተጠየቅነው:: አንድ ሰው ከገዛ ሃገር ለቆ ለመውጣት ለምንድን ነው ሚከፍለው? አሰብኩ ግን መከራከር አልችልም:: ከፈልኩ:: የይለፍ ወረቀቱ ላይ ማህተም እንደተደረገልኝ ወዲያው ወደ ጊኒ
ደንበር ተሻገርኩ። ዋና ከተማዋ ኮናክሪ ለመድረስ ደግሞ ገና ብዙ መንገድ ይቀረኛል። ወደ ከተማው የሚወስድ አውቶብስ ለማግኘት ቶሎ ቶሎ መራመድ ጀመርኩ። ጊኒ ውስጥ የሚነገር
የትኛውንም ቋንቋ መናገር አልችልም ምን ማድረግ እንዳለብኝም አላሰብኩበትም ነበር። ትንሽ አስጨነቀኝ ግን ከሃገሬ በህይወት መውጣቴ ትልቅ ነገር ነው::
ኮናክሪ የሚሄድ አውቶብሶች የጊኒ ወታደሮች ባቆሟቸው ኬላዎች በኩል ነበር የሚቆሙት፡፡ በኬላዎቹ ተጠግተው
በፈለጉት መጠን የጊኒን ገንዘብ የሚመነዝሩ ሰዎች ነበሩ።
ወታደሮቹ ይሄን ጥቁር ገበያ የሚከላከሉ መስሎኝ ነበር ግን ግድ አይሰጣቸውም:: ገንዘቤን ቀይሬ ወደ ኬላው ተጠጋሁ። ደንበሩ ላይ ያሉ ወታደሮች ወይ እንግሊዝኛ መናገር አይችሉም ወይ
ደግሞ እንደሚችሉ ማሳወቅ አይፈልጉም:: መሳሪያቸውን ብቻ
በተጠንቀቅ ይዘዋል፡፡ ቀና ብየ ማየት አልፈለኩም። ከዚህ በፊት ወታደር እንደነበርኩ እና አሁን ግን ትቼው እሸሸሁ መሆኑን ማሳበቅ አልፈለኩም::
አውቶብሱን ለማግኘት ጥቁር ቡናማ የሆኑ የጣውላ ቤቶችን ማለፍ ነበረብኝ። ውስጥ ወታደሮች የሰዎችን ሻንጣ ይበረብራሉ።ሰዎች ደግሞ መረጃዎቻቸውን ለሃላፊዎች ያሳያሉ። የእኔ ተራ ሲደርስ ወታደሮቹ ሻንጣየን ከፍተው በውስ ጡ ያለውን ሁሉ መሬት ላይ ዘረገፉት። ብዙ እቃ ስላልነበረኝ ለመሰብሰብ እና መልሶ ለመክተት ብዙም አያስቸግርም፡፡ ሁለት ቲ ሸርት፣ ሁለት
ዉስጥ ሱሪ እና ሶስት ጥንድ ሱሪዎች ብቻ ነበሩ::
ከጣውላ ቤቱ ስወጣ መረጃዎቼን ማሳየት ነበረብኝ፡፡ ብዙ ጠረጴዛዎቹ እና ወታደሮች ደግሞ የማንጎ ዛፍ ስር ነበሩ።
መሳሪዎቻቸው ወንበራቸው ላይ ወይም የአንዳንዶቹ ጠረጴዛዎቹ ላይ ተቀምጦ ነበር፡፡ ለማን ማሳየት እንዳለብኝ
አላውቅም::
አንድ ወታደር ወደ እሱ እንደሄድ ምልክት አሳየኝ። እጁን ዘረጋ እና የይለፍ ወረቀቴን ተቀበለኝ። ወታደሩ በማይገባኝ አንድ
ቋንቋ ተናገረ።የይለፍ ወረቀቴን የደረት ኪሱ ውስጥ አስገባው እና እጁን ጠረጴዛ አድርጎ አትኩሮ ተመለከተኝ። አቀረቀርኩ
ወታደሩ አገጩን ቀና አደረገኝ፡፡ የይለፍ ወረቀቴን ከኪሱ አውጥቶ መረመረ። አይኑ ቀላ ፊቱ ላይ ፈገግታ ይታይ ነበር።
እጁን አጥፎ ተደላድሎ ተቀመጠ። ፈገግ አልኩ እሱም ሳቀ።በቋንቋው የሆነ ነገር አለና እጁን እንደገና ጠረጴዛው ላይ አደረገ።ፈገግታው እየጠፋ ሄደ፡፡ የተወሰነ ገንዘብ እጁ ላይ አስቀመጥኩ።
የይለፍ ወረቀቴን ከኪሱ አውጥቶ ሰጠኝ እና በሩ እንዳልፍ ጠቆመኝ፡፡
ብዙ አውቶብሶች ስለነበሩ ወደ ኮናክሪ ለመሄድ አውቶብስ መያዝ እንዳለብኝ አላውቅም ግራ ገባኝ፡፡ ሰዎችን ለመጠየቅ ብሞክርም ማንም ሊረዳኝ አልቻለም:: የማውቀው ፈረንሳይኛ
ቃል bonjour ቦንጁር ብቻ ነበር፡፡
ግራ ገብቶኝ ቁሜያለሁ አንድ አልፎ ሂያጅ በኪሮ ቋንቋ ሲያጉረመርም ሰማሁትና “ ጤና ይስጥልኝ” ብየ ወደ ኮናክሪ
የሚወስደው አውቶብስ የትኛው እንደሆነ ጠየቅኩት። እሱም ወደ ዛው እንደሚጓዝ ነገረኝ እና ወደ ከአፍ እስከ ገደፉ ጢም
ብሎ የሞላ አውቶብስ ውስጥ ገባን፡፡ በየ ሃምሳ ሜትሩ ወደ አስራ አምስት የሚጠጉ ኬላዎች ላይ ወታደሮች ነበሩ እና ወታደሮቹ ምህረት የለሽ ነበሩ። ወታደሮቹ መክፈል የማችሉትን እየደበደቡ
ከአውቶብሱ ያወርዷቸዋል። እኔ ግን እድለኛ ነበርኩ። ከአጠገቤ የነበረው ሰውየ ልጅ ስለመሰልኳቸው ብዙ ኬላዎችን በነፃ አልፌያለሁ። የእሱን መረጃ ያያሉ እና የሁለታችንንም እሱን
ያስከፍላሉ፡፡ ሰውየው የገባው አይመስለኝም:: ገንዘብ ጉዳዩ አይደለም ኮናክሪ መግባት ብቻ ነበር የሚፈልገው:: የመግቢያ ክፍያው ሶስት መቶ ሊዮንስ እንደሆነ ሰዎች ሲያወሩ ሰማሁ።
መቶ ሊዮንስ ብቻ ነበር የቀረኝ፡፡ ምንድን ነው ማደርገው? ብየ ማሰብ ጀመርኩ። ይሄ ሁሉ መንገድ የመጣሁት ለከንቱ ነው? ወደ ፍሪ ታውን መመለስ እንኳ ብፈልግ የምመለስበት ገንዘብ የለኝም:: አይኖቼ እንባ አቀረሩ። ተረበሽኩ ከዚህ መውጫ መንገዱ አልታይህ አለኝ፡፡ አንድ የይለፍ ወረቀቱ የተመታለት ሰው ከኬላ ወደ አውቶብስ ሲመለስ ሻንጣውን ጥሎ አየሁ። የተወሰነ ካመነታሁ በኋላ እድሉን ልጠቀምበት ወሰንኩ። ሰልፉን ትቼ ሻንጣውን ይዤ ተከልኩት:: አውቶብስ ውስጥ ገብቼ መጨረሻ ወንበር ላይ ተደብቄ ተቀመጥኩ። አውቶብሱ ቀስ ብሎ ከወጣ በኋላ ፍጥነቱን ጨመረ። በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሃገሪቱ
ገባሁ በኋላ ግን ችግር ይሆናል፡፡
አውቶብሱ ወደ ኮናክሪ ሲደርስ መጨነቅ ጀመርኩ። ከደረስኩ በኋላ ምን እንደማደርግ አላውቅም:: የሴራሊዮን አምባሳደር ስደተኞች በጊዜዊነት ግቢው ውስጥ እንደሚያሳድር ሰምቻለሁ
ግን ኢምባሲው የት እንደሆነ እንኳ አላውቅም:: ጃሎህ ከሚባል
ፉላኒ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ አርብቶ አደር ጎሳ) ጋር ነበር የተቀመጥኩት። ጃሎህ ፍሪ ታውን እንደኖረ ነገረኝ፡፡ ስለ ጦርነቱ እና በሃገሪቱ ላይ ስላስከተለው ጉዳት አወራን። በኋላ ስልክ ቁጥሩን ሰጠኝ እና ከተማዋን ስንቀሳቀስ እርዳታ ካስፈለገኝ እንድደውልለት ነገረኝ። ማደሪያ እንደሌለኝ ልነግረው ፈለኩ ግን
ቀድሞኝ ወረደ። አብሮኝ የመጣውን ሴራ ሊዮናዊ ፈለኩ ግን ላገኘው አልቻልኩም። ከደቂቃዎች በኋላ አውቶብሱ ግዙፍ
መናሃሪያ ውስጥ ገባ። ወጥቼ ሁሉም ሲሄድ ተመለከትኩ። ተነፈስኩ እና እጆቼ ራሴ ላይ ጭኜ ወደ አግድም ወንበር ሂጄ
ተቀመጥኩ። ፊቴን በእጆቼ ሸፍኜ “ለሊቱን ሙሉ ከዚህ መቀመጥ አልችልም” ብየ ለራሴ አጉረመረምኩ።
ብዙ ታክሲዎች ነበሩ እና አውቶብሱ መናሃሪያ የደረሱ ሰዎች ሁሉ ይዟቸዎል። እኔም ብቸኛ ሚሄድበት የጠፋው እንግዳ
መስየ መታየት ስላልፈለኩ አንዱ
ታክሲ ውስጥ ገባሁ። ሹፌሩ በፈረንሳይኛ ሲናገር ወዴት እንደምሄድ እየጠቀኝ እንደሆነ ገመትኩ። ሴራ ሊዮን ቆንስላ አ ኢምባሲ” ብየ ነገርኩት።በመስኮት ስመለከት የመብራት ምሶሶዎች ላይ የመንገድ መብራቶቹ ተንበርግገው
ተንጠልጥለዋል። ብርሃናቸው ከጨረቃ ብርሃን ሳይበልጥ አይቀርም። ታክሲው ኢምባሲው ፊት ለፊት ቆመ እና የምፈልገው ቦታ ይዞኝ እንደመጣ
ለማረጋገጥ ወደ አረንጓዴ፣ ነጭ እና ሰማያዊ ባንዴራ ጠቆመኝ፡፡ራሴን በማወዛወዝ ትክክል እንደሆነ ከገለፅኩለት በኋላ ከታክሲው ወረድኩ
በኤንባሲው በር ላይ ጠባቂዎቹ በኪሪዎ የይለፍ ወረቀቴን እንዳሳይ ጠየቁኝ፡፡ አሳየኋቸው እና ወደ ግቢው እንድገባ ፈቀዱልኝ::
በግቢው ውስጥ ከሃምሳ በላይ ሰዎች ሲኖሩ እንደእኔ መጠጊያ ያጡ ሳይሆኑ አይቀሩም፡፡ አብዛኖቹ ትራስ ብቻ አድርገው ተጋድመዋል። ጓዛቸውን ወይም ሻንጣቸውን ከጎናቸው አስቀምጠዋል። ሰዎቹ ማታ ማታ ከዚህ የሚያድሩ ሲሆን ቀን ቀን ወደ ውጭ ይወጣሉ። ጥግ ላይ ቦታ አገኘሁ እና መሬት ተቀምጨ ጀርባየን ወደ ግድግዳው አስጠጋሁ። ስዎቹን ሳይ
ከጦርነቱ ለማምለጥ ያለፍኩባቸው ሰፈሮች ትዝ አሉኝ።
#ክፍል_ሀያ_ሶስት(የመጨረሻ ክፍል)
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
አስር ስዓት ሲሆን አውቶብሱ ካምቢያ ከምትባል ከተማ አደረሰን። የመጨረሻ ፌርማታው ነበር። ፍሪ ታውንን ለቀን
ከመጣን ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳፋሪዎቹ ፊት ተፈታ። ግን ብዙም አልቆየም! ድንበር ለማለፍ ክፍያ ስንጠየቅ የሁሉም ፊት መልሶ ተኮማተረ አጉረመረምን፡፡ ሁሉም ሰው ከካልሲው
ውስጥ፣ ከውስጥ ሱሪ እና ከረባት ሳይቀር የተረፈ ገንዘብ ካለ ፈለገ። ሶስት መቶ ሊዮንስ (የሴራሊዮን ገንዘብ) ነበር
የተጠየቅነው:: አንድ ሰው ከገዛ ሃገር ለቆ ለመውጣት ለምንድን ነው ሚከፍለው? አሰብኩ ግን መከራከር አልችልም:: ከፈልኩ:: የይለፍ ወረቀቱ ላይ ማህተም እንደተደረገልኝ ወዲያው ወደ ጊኒ
ደንበር ተሻገርኩ። ዋና ከተማዋ ኮናክሪ ለመድረስ ደግሞ ገና ብዙ መንገድ ይቀረኛል። ወደ ከተማው የሚወስድ አውቶብስ ለማግኘት ቶሎ ቶሎ መራመድ ጀመርኩ። ጊኒ ውስጥ የሚነገር
የትኛውንም ቋንቋ መናገር አልችልም ምን ማድረግ እንዳለብኝም አላሰብኩበትም ነበር። ትንሽ አስጨነቀኝ ግን ከሃገሬ በህይወት መውጣቴ ትልቅ ነገር ነው::
ኮናክሪ የሚሄድ አውቶብሶች የጊኒ ወታደሮች ባቆሟቸው ኬላዎች በኩል ነበር የሚቆሙት፡፡ በኬላዎቹ ተጠግተው
በፈለጉት መጠን የጊኒን ገንዘብ የሚመነዝሩ ሰዎች ነበሩ።
ወታደሮቹ ይሄን ጥቁር ገበያ የሚከላከሉ መስሎኝ ነበር ግን ግድ አይሰጣቸውም:: ገንዘቤን ቀይሬ ወደ ኬላው ተጠጋሁ። ደንበሩ ላይ ያሉ ወታደሮች ወይ እንግሊዝኛ መናገር አይችሉም ወይ
ደግሞ እንደሚችሉ ማሳወቅ አይፈልጉም:: መሳሪያቸውን ብቻ
በተጠንቀቅ ይዘዋል፡፡ ቀና ብየ ማየት አልፈለኩም። ከዚህ በፊት ወታደር እንደነበርኩ እና አሁን ግን ትቼው እሸሸሁ መሆኑን ማሳበቅ አልፈለኩም::
አውቶብሱን ለማግኘት ጥቁር ቡናማ የሆኑ የጣውላ ቤቶችን ማለፍ ነበረብኝ። ውስጥ ወታደሮች የሰዎችን ሻንጣ ይበረብራሉ።ሰዎች ደግሞ መረጃዎቻቸውን ለሃላፊዎች ያሳያሉ። የእኔ ተራ ሲደርስ ወታደሮቹ ሻንጣየን ከፍተው በውስ ጡ ያለውን ሁሉ መሬት ላይ ዘረገፉት። ብዙ እቃ ስላልነበረኝ ለመሰብሰብ እና መልሶ ለመክተት ብዙም አያስቸግርም፡፡ ሁለት ቲ ሸርት፣ ሁለት
ዉስጥ ሱሪ እና ሶስት ጥንድ ሱሪዎች ብቻ ነበሩ::
ከጣውላ ቤቱ ስወጣ መረጃዎቼን ማሳየት ነበረብኝ፡፡ ብዙ ጠረጴዛዎቹ እና ወታደሮች ደግሞ የማንጎ ዛፍ ስር ነበሩ።
መሳሪዎቻቸው ወንበራቸው ላይ ወይም የአንዳንዶቹ ጠረጴዛዎቹ ላይ ተቀምጦ ነበር፡፡ ለማን ማሳየት እንዳለብኝ
አላውቅም::
አንድ ወታደር ወደ እሱ እንደሄድ ምልክት አሳየኝ። እጁን ዘረጋ እና የይለፍ ወረቀቴን ተቀበለኝ። ወታደሩ በማይገባኝ አንድ
ቋንቋ ተናገረ።የይለፍ ወረቀቴን የደረት ኪሱ ውስጥ አስገባው እና እጁን ጠረጴዛ አድርጎ አትኩሮ ተመለከተኝ። አቀረቀርኩ
ወታደሩ አገጩን ቀና አደረገኝ፡፡ የይለፍ ወረቀቴን ከኪሱ አውጥቶ መረመረ። አይኑ ቀላ ፊቱ ላይ ፈገግታ ይታይ ነበር።
እጁን አጥፎ ተደላድሎ ተቀመጠ። ፈገግ አልኩ እሱም ሳቀ።በቋንቋው የሆነ ነገር አለና እጁን እንደገና ጠረጴዛው ላይ አደረገ።ፈገግታው እየጠፋ ሄደ፡፡ የተወሰነ ገንዘብ እጁ ላይ አስቀመጥኩ።
የይለፍ ወረቀቴን ከኪሱ አውጥቶ ሰጠኝ እና በሩ እንዳልፍ ጠቆመኝ፡፡
ብዙ አውቶብሶች ስለነበሩ ወደ ኮናክሪ ለመሄድ አውቶብስ መያዝ እንዳለብኝ አላውቅም ግራ ገባኝ፡፡ ሰዎችን ለመጠየቅ ብሞክርም ማንም ሊረዳኝ አልቻለም:: የማውቀው ፈረንሳይኛ
ቃል bonjour ቦንጁር ብቻ ነበር፡፡
ግራ ገብቶኝ ቁሜያለሁ አንድ አልፎ ሂያጅ በኪሮ ቋንቋ ሲያጉረመርም ሰማሁትና “ ጤና ይስጥልኝ” ብየ ወደ ኮናክሪ
የሚወስደው አውቶብስ የትኛው እንደሆነ ጠየቅኩት። እሱም ወደ ዛው እንደሚጓዝ ነገረኝ እና ወደ ከአፍ እስከ ገደፉ ጢም
ብሎ የሞላ አውቶብስ ውስጥ ገባን፡፡ በየ ሃምሳ ሜትሩ ወደ አስራ አምስት የሚጠጉ ኬላዎች ላይ ወታደሮች ነበሩ እና ወታደሮቹ ምህረት የለሽ ነበሩ። ወታደሮቹ መክፈል የማችሉትን እየደበደቡ
ከአውቶብሱ ያወርዷቸዋል። እኔ ግን እድለኛ ነበርኩ። ከአጠገቤ የነበረው ሰውየ ልጅ ስለመሰልኳቸው ብዙ ኬላዎችን በነፃ አልፌያለሁ። የእሱን መረጃ ያያሉ እና የሁለታችንንም እሱን
ያስከፍላሉ፡፡ ሰውየው የገባው አይመስለኝም:: ገንዘብ ጉዳዩ አይደለም ኮናክሪ መግባት ብቻ ነበር የሚፈልገው:: የመግቢያ ክፍያው ሶስት መቶ ሊዮንስ እንደሆነ ሰዎች ሲያወሩ ሰማሁ።
መቶ ሊዮንስ ብቻ ነበር የቀረኝ፡፡ ምንድን ነው ማደርገው? ብየ ማሰብ ጀመርኩ። ይሄ ሁሉ መንገድ የመጣሁት ለከንቱ ነው? ወደ ፍሪ ታውን መመለስ እንኳ ብፈልግ የምመለስበት ገንዘብ የለኝም:: አይኖቼ እንባ አቀረሩ። ተረበሽኩ ከዚህ መውጫ መንገዱ አልታይህ አለኝ፡፡ አንድ የይለፍ ወረቀቱ የተመታለት ሰው ከኬላ ወደ አውቶብስ ሲመለስ ሻንጣውን ጥሎ አየሁ። የተወሰነ ካመነታሁ በኋላ እድሉን ልጠቀምበት ወሰንኩ። ሰልፉን ትቼ ሻንጣውን ይዤ ተከልኩት:: አውቶብስ ውስጥ ገብቼ መጨረሻ ወንበር ላይ ተደብቄ ተቀመጥኩ። አውቶብሱ ቀስ ብሎ ከወጣ በኋላ ፍጥነቱን ጨመረ። በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሃገሪቱ
ገባሁ በኋላ ግን ችግር ይሆናል፡፡
አውቶብሱ ወደ ኮናክሪ ሲደርስ መጨነቅ ጀመርኩ። ከደረስኩ በኋላ ምን እንደማደርግ አላውቅም:: የሴራሊዮን አምባሳደር ስደተኞች በጊዜዊነት ግቢው ውስጥ እንደሚያሳድር ሰምቻለሁ
ግን ኢምባሲው የት እንደሆነ እንኳ አላውቅም:: ጃሎህ ከሚባል
ፉላኒ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ አርብቶ አደር ጎሳ) ጋር ነበር የተቀመጥኩት። ጃሎህ ፍሪ ታውን እንደኖረ ነገረኝ፡፡ ስለ ጦርነቱ እና በሃገሪቱ ላይ ስላስከተለው ጉዳት አወራን። በኋላ ስልክ ቁጥሩን ሰጠኝ እና ከተማዋን ስንቀሳቀስ እርዳታ ካስፈለገኝ እንድደውልለት ነገረኝ። ማደሪያ እንደሌለኝ ልነግረው ፈለኩ ግን
ቀድሞኝ ወረደ። አብሮኝ የመጣውን ሴራ ሊዮናዊ ፈለኩ ግን ላገኘው አልቻልኩም። ከደቂቃዎች በኋላ አውቶብሱ ግዙፍ
መናሃሪያ ውስጥ ገባ። ወጥቼ ሁሉም ሲሄድ ተመለከትኩ። ተነፈስኩ እና እጆቼ ራሴ ላይ ጭኜ ወደ አግድም ወንበር ሂጄ
ተቀመጥኩ። ፊቴን በእጆቼ ሸፍኜ “ለሊቱን ሙሉ ከዚህ መቀመጥ አልችልም” ብየ ለራሴ አጉረመረምኩ።
ብዙ ታክሲዎች ነበሩ እና አውቶብሱ መናሃሪያ የደረሱ ሰዎች ሁሉ ይዟቸዎል። እኔም ብቸኛ ሚሄድበት የጠፋው እንግዳ
መስየ መታየት ስላልፈለኩ አንዱ
ታክሲ ውስጥ ገባሁ። ሹፌሩ በፈረንሳይኛ ሲናገር ወዴት እንደምሄድ እየጠቀኝ እንደሆነ ገመትኩ። ሴራ ሊዮን ቆንስላ አ ኢምባሲ” ብየ ነገርኩት።በመስኮት ስመለከት የመብራት ምሶሶዎች ላይ የመንገድ መብራቶቹ ተንበርግገው
ተንጠልጥለዋል። ብርሃናቸው ከጨረቃ ብርሃን ሳይበልጥ አይቀርም። ታክሲው ኢምባሲው ፊት ለፊት ቆመ እና የምፈልገው ቦታ ይዞኝ እንደመጣ
ለማረጋገጥ ወደ አረንጓዴ፣ ነጭ እና ሰማያዊ ባንዴራ ጠቆመኝ፡፡ራሴን በማወዛወዝ ትክክል እንደሆነ ከገለፅኩለት በኋላ ከታክሲው ወረድኩ
በኤንባሲው በር ላይ ጠባቂዎቹ በኪሪዎ የይለፍ ወረቀቴን እንዳሳይ ጠየቁኝ፡፡ አሳየኋቸው እና ወደ ግቢው እንድገባ ፈቀዱልኝ::
በግቢው ውስጥ ከሃምሳ በላይ ሰዎች ሲኖሩ እንደእኔ መጠጊያ ያጡ ሳይሆኑ አይቀሩም፡፡ አብዛኖቹ ትራስ ብቻ አድርገው ተጋድመዋል። ጓዛቸውን ወይም ሻንጣቸውን ከጎናቸው አስቀምጠዋል። ሰዎቹ ማታ ማታ ከዚህ የሚያድሩ ሲሆን ቀን ቀን ወደ ውጭ ይወጣሉ። ጥግ ላይ ቦታ አገኘሁ እና መሬት ተቀምጨ ጀርባየን ወደ ግድግዳው አስጠጋሁ። ስዎቹን ሳይ
ከጦርነቱ ለማምለጥ ያለፍኩባቸው ሰፈሮች ትዝ አሉኝ።
#የታካሚው_ማስታወሻ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)
“ወደ ዚህ ስትመጣ የመጀመሪያህ ነው?”
“አዎ።”
“ትቆያለህ?”
ሳምንት አካባቢ።”
“እዚያ ማዶ ሚታየው አፄ ዮሐንስ አንገታቸው የተቀላበት ቦታ ነው።” እጁን ከመንገዱ በላይ እየጠቆመ::
“መተማ ዮሐንስ ደረስን ማለት ነው?”
“አዎ፡፡ አሁን ገብተናል፡፡” ልቤ ድንግጥ ድንግጥ አለብኝ፡፡ ሚኒባሱ እየቆመ፣ ሰዎችን ያወርዳል። እስከዛሬ ያልተሰማኝ ፍርሀት እየተሰማኝ ነው፡፡ ዝም አልኩ፡፡ ወደ ስንብት እየተጠጋሁ ነው፡፡
የማውራትም የማወቅም ፍላጎት የለኝም፡፡ ዝም ብዬ በዐይኔ ከተማውን መፈለግ ጀምረኩ፡፡ በግራና በቀኝ የተደረደሩ የጭቃ ቤቶች፣ ጭር ያለ ከተማ ነው፡፡ እንደጠበኩት ግርግር የበዛበት ከተማ አይደለም፡፡ ሰዐቴን አየሁ፤ አስር ተኩል፡፡ አብዛኛው ሰው ወርዶ አልቋል፡፡
“መናኸሪያ ትገባለህ?” ወያላው ፊቱን አዙሮ ጠየቀኝ፡፡
“አይ አልገባም፡፡”
“ካልገባህ መጨረሻው እዚህ ነው።”
“እሺ አውርደኝ!”
በጭራሽ እንደገመትኩት አይደለም፡፡ ለማደሪያ ሚሆን አልጋ ቤት እንኳን እስካሁን አላየሁም፡፡ ከተማዋ ትሞቃለች። አስራ አንድ ሰዓት እየሆነ ቢሆንም፣ በጣም ይወብቃል፡፡ ፍርሀት ነው መሰል፣ በጣም እያላበኝ ነው። ዝም ብዬ ዋና መንገዱን ይዤ፣ አልጋ ቤት ፍለጋ
ተጓዝኩኝ፡፡ ነጋዴ የሚርመሰመስበት፣ አዲስ ሰው፣ ፀጉረ ልውጥ ሰው
ከዐይን የማይገባበት ብዬ የገመትኩት ከተማ፣ ትንሽዬ መንደር ሆና አገኘኋት፡፡ መንገድ ዳር በብሎኬት የታጠረ ሰፊ ግቢ ያለው ሆቴል አየሁ፡፡ ሰላም ሆቴል ይላል፡፡ አላንገራገርኩም፡፡ ዘው ብዬ ገባሁ፡፡ ብቻ
አልጋ በኖረ፡፡
“አልጋ አለ?”
“አለ፡፡”
“እስቲ አሳዩኝ?”
“ባለሻወር ነው፣ ያለሻወር?”
“ባለሻወር፡፡” ቁልፍ አመጣችና አሳየችኝ፡፡
“ስንት ነው?”
“አንድ መቶ ሃምሳ ብር፡፡” ብሩን ሰጠኋትና ቦርሳዬን አስቀመጥኩ።
ሻወር ቤት ገብቼ ሻወር ቼክ ሳደርግ ውሀ የለችም፡፡ ዞር ስል፣ውሀ በባልዲ ተቀምጧል፡፡ በጣም አልቦኛል፣ ተለቃለኩኝ፡፡ እራት በልቼ ቢራ መጠጣት ጀመርኩ፡፡ ሙቀት ስለሆነ ተጠጣልኝ፡፡ ማታ ጥሩ እንቅልፍ ተኝቼ አደርኩ፡፡ ቀን ወጥቼ ከተማውን ዙሪያውን ሳይ ዋልኩ፡፡
በፍፁም እኔ እንዳሰብኩት አይደለም፡፡ የከተማው ዙሪያ ለጥ ያለ ለእርሻ የሚውል ሜዳ ሲሆን፣ ዛፎች በእርቀት ነው የሚገኙት፡፡ ስዞር ውዬ አመሻሹ ላይ፣ ቢራዬን እየጠጣሁ ምን እንደሚችል ሳስብ፣ አርሴማ ገዳም የሚል ሀሳብ መጣብኝ፡፡
#ኑሮ_በገዳም
ሽቅብ ዝግዛግ ሆኖ በተሰራውን የጥረጊያ መንገድረገ፣ በግራና በቀኝ በዛፎች ተከቧል፡፡ ከፊት ለፊቴ፣ አጠር ያለ ወጣት፣ የክርስቲያኖ ሮናልዶ ስዕል ያለበት ጥቁር የጨርቅ ሻንጣ በጀርባው ተሸክሞ በዝግታ ያዘግማል። እየተከታተልን ወደ ገዳሙ ዘልቀን ገባን። ከገዳሙ መግቢያ
በር ትንሽ ፈቅ ብላ ያለች የጭቃ ቤት ጋር ስንደርስ፤
“እንኳን ደህና መጣችሁ። ምዝገባ ቢጤ አለች።” አለን ፊቱ መጠጥ ያለ ጠይም ወጣት፡፡
“እሺ!” ብዬ ቆምኩኝ፡፡ ልጁን መዝግቦ ከጨርሰ በኋላ፣ ትንሽ ቆየኝ ብሎት እኔን መመዝግብ ጀመረ፡፡ ስም፣ እድሜ፣ የመጡበት አድራሻ፣ የአደጋ ግዜ ተጠሪ...፣ ሁሉንም ቀይሬ ነገርኩት፡፡
“ለስንት ግዜ ነው ሚቆዩት?”
“ለሦስት ሳምንት፡፡”
“መታወቂያ ይዘዋል?”
“አልያዝኩም፡፡” አልተጫነኝም፡፡
“እሺ፣ እንግዶቻችን፣ እኔ መልካሙ እባላለሁ፡፡ በገዳሙ አስተባባሪ ነኝ፡፡ አሁን ማደሪያ ቦታ እሰጣችኋለው፡፡ ገዳሙን
አስጎበኛችኋለው፤ ስለ ገዳሙ ታሪክ፣ መተዳደሪያ ደንብና ሌሎች መረጃዎችን እነግራችኋለው፡፡ እዚህ ገዳም፣ ማንኛውም አዲስ ሱባኤተኛ ሲገባ እናንተ እንዳደረጋችሁት ተመዝግቦ ነው፡፡ ገዳሙ የአርምሞ ገዳም ነው:: ማውራት ክልክል ነው፡፡ አስገዳጅ ነገር ካላጋጠማችሁ በስተቀር፣ ማውራት አይቻልም፡፡ የግድ ማውራት ካስፈለገ እንኳ፣ ዝግ ባለ ድምፅ፣ በለሆሳስ ነው ማውራት ሚቻለው፡፡ እዚህ መዳን የሚገኘው በአርምሞ ውስጥ ነው፡፡”
ከኛ ውጪ ለሌላ ሰው እንዳይሰማ፣ በሆዱ እንደሚያወራ፣ በጣም ዝግ ባለ ድምፅ ያወራናል፡፡ በአርምሞና በለሆሳስ ማለት እንዲህ ነው' ብዬ አሰብኩ፡፡ የሚያወራው እንዲሰማን፣ አንገታችንን ወደሱ አሰገግን፡፡ እያወራን ወደ ማደሪያችን ወሰደን፡፡ እያንዳንዱ ከሁለት መቶ ምዕመን በላይ የሚይዝ፣ አራት የማደሪያ አዳራሾች አሉ፡፡ ሁለቱ የወንድ፣ ሁለቱ የሴት እንደሆነ ነገረን፡፡ ቦታ ሊሰጠን ወደ አንደኛው አዳራሽ ይዞን ገባ፡፡ በውስጡ ከመቶ ሚበልጡ ምዕመናን አሉ፡፡አሰላሁት። በግምት በገዳሙ አንድ ሺህ የሚጠጉ ሱባኤያተኛ ምዕመናን
እንዳሉ ገመትኩኝ፡፡ ገዳሙ ግን ሰው ያለው አይመስልም፡፡ ዝም፣ ጭጭ፣ ያለ ነው፡፡ ሁሉም በለሆሳስ ፀሎት ላይ ነው፡፡ ሰላምታ እንኳ፣ ጎንበስ ቀና በመባባል ብቻ ነው፡፡ ምንም አይነት የሰው ድምፅ አይሰማም፡፡የወፎች ጭጭታና የዛፎች ሽው ሽውታ ብቻ ነው፡፡ በጣም ደስ ይላል፡፡መንፈስን ያድሳል፡፡ አዕምሮን ያረጋጋል፡፡ ፈውስ በመንፈስ ቅዱስ
ባይላክም እንኳ፣ የቦታው ድባብ ፈውስን ይሰጣል።
“እና ሌላው...” አለ መልካሙ ቦታችንን ሰጥቶን ከአዳራሹ ይዞን እየወጣ፣ “ማንኛውም ምእመን ወደ ገዳሙ ለሱባኤ ሲገባ፤ ፀጉሩን መላጨት፣ ንስሀ መግባትና ስግደት መውሰድ አለበት፡፡” አለን እኔን እኔን እየተመለከተ፡፡
“እሺ፡፡ ማን ነው ሚላጨን?”
“እርስ በእረስ ነው ምትለጫጩት፡፡ ፈራህ እንዴ..? አንተን እኔ ቆንጆ አድርጌ እላጭሃለው፡፡” የከተማ ልጅ መሆኔን አውቆ ነው መሰል፣ ከገባን ጀምሮ እኔን እኔን እየተመለከተ ነው ሲያወራ የነበረው፡፡
“እሺ” አልኩት፡፡ አሁን ስለራሴ ብዙም ግድ የለኝም፡፡ ምላጭ ግቢ ካለው ሱቅ ተገዝቶ ሁለታችንንም ላጨን፡፡ ነብስ ካወኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ፀጉሬን ተላጨሁ፡፡ እየላጨንም ስለ ገዳሙ መተዳደሪያ ደንብ ይነግረናል።
“በገዳሙ፣ በቀን ሁለት ጊዜ ብቻ ነው የሚበላው፡፡ ጥዋት ቅዳሴ እንዳለቀና ማታ አስራ ሁለት ሰዐት። አስራ ሁለት ሰዐት ካለፈ መመገብ አይቻልም፡፡ ገዳሙ መብራት ስለሌለው፣ ማታ ማታ ሻማ ነው
ምትጠቀሙት። ሻማ ከዚህ ሱቅ መግዛት ትችላላችሁ፡፡ የማታ ሦስት ሰዓት ፀሎት ካበቃ ቦሃላ ሻማ ማብራት አይቻልም፡፡ የእንቅልፍ ሰዓት ነው፡፡ እንዳያችሁት፣ የቦታ ጥበት ስላለ አንድ ሰው፣ በአንድ መዳበሪያ በታ ላይ ነው መተኛት ያለበት፡፡ የለሊቱ ዘጠኝ ሰአት ፀሎት ላይ ሁሉም
ምዕመን መገኘት ግዴታ ነው፡፡” ሁለታችንንም ላጭቶ ሲጨርስ አስራ
አንድ ሰዐት ሆኖ የሰርክ ፕሮግራም ተጀመረ።
“በሉ ተነሱ እንሂድ፣ የሚቸግራችሁ ነገር ካለ እዚሁ ስላለን በፈለጋችሁት ሰዓት ጠይቁኝ ፤ ” ብሎ ፕሮግራሙ ወደ ሚካሄድበት ስፍራ ወሰደን፡፡
የገዳም ኑሮዬ ተጀመረ፡፡ ለሊት ዘጠኝ ሰዓት መነሳት በጣም ከባድ ነው፡፡ ግን፣ አማራጭ የለም፡፡ አስተባባሪዎች እየዞሩ ይቀሰቅሳሉ።ያልተነሳ ሰው ላይ ቀዝቃዛ ውሃ ይረጫሉ፡፡ የመጀመሪያ ቀናቶች ላይ
በጣም ከበደኝ፡፡ ከእንቅልፍ ሳልነቃ ውሃ ሲረጩኝ እንደ ኤሌክትሪክ ይነዝረኛል፡፡ ሁለት ሦስት ቀን ሲደጋግሙኝ፣ ገና ድምፃቸውን ስሰማ መነሳት ጀመርኩ፡፡ ፀሎትና ምህላው እስከ ጥዋቱ አስራ ሁለት ሰዓት ይደረጋል፤ ከዛ ወደ ፀበል።
ገዳሙን ቅጥር ግቢ በደንብ ለማማወቅ እየተዟዟርኩ ማየት ጀመርኩ፡፡ የአርሴማ ገዳም በሃገራችን እንዳሉት አብዛኞቹ ገዳማት፣በተራራማ ቦታ ላይ ከየተመሰረተ ነው፡፡ የገዳሙ መስራችና አስተዳዳሪ
የሆኑት መነኩሴ፣ እድሜያቸው ሃምሳ ዓመት ቢሆን ነው፡፡ ገዳሙ በእውቀት እንዲለማ በደንብ አስበውበት እንደመሰረቱት ገዳሙ አፍ አውጥቶ ይናገራል፡፡ ከመሰረቱት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)
“ወደ ዚህ ስትመጣ የመጀመሪያህ ነው?”
“አዎ።”
“ትቆያለህ?”
ሳምንት አካባቢ።”
“እዚያ ማዶ ሚታየው አፄ ዮሐንስ አንገታቸው የተቀላበት ቦታ ነው።” እጁን ከመንገዱ በላይ እየጠቆመ::
“መተማ ዮሐንስ ደረስን ማለት ነው?”
“አዎ፡፡ አሁን ገብተናል፡፡” ልቤ ድንግጥ ድንግጥ አለብኝ፡፡ ሚኒባሱ እየቆመ፣ ሰዎችን ያወርዳል። እስከዛሬ ያልተሰማኝ ፍርሀት እየተሰማኝ ነው፡፡ ዝም አልኩ፡፡ ወደ ስንብት እየተጠጋሁ ነው፡፡
የማውራትም የማወቅም ፍላጎት የለኝም፡፡ ዝም ብዬ በዐይኔ ከተማውን መፈለግ ጀምረኩ፡፡ በግራና በቀኝ የተደረደሩ የጭቃ ቤቶች፣ ጭር ያለ ከተማ ነው፡፡ እንደጠበኩት ግርግር የበዛበት ከተማ አይደለም፡፡ ሰዐቴን አየሁ፤ አስር ተኩል፡፡ አብዛኛው ሰው ወርዶ አልቋል፡፡
“መናኸሪያ ትገባለህ?” ወያላው ፊቱን አዙሮ ጠየቀኝ፡፡
“አይ አልገባም፡፡”
“ካልገባህ መጨረሻው እዚህ ነው።”
“እሺ አውርደኝ!”
በጭራሽ እንደገመትኩት አይደለም፡፡ ለማደሪያ ሚሆን አልጋ ቤት እንኳን እስካሁን አላየሁም፡፡ ከተማዋ ትሞቃለች። አስራ አንድ ሰዓት እየሆነ ቢሆንም፣ በጣም ይወብቃል፡፡ ፍርሀት ነው መሰል፣ በጣም እያላበኝ ነው። ዝም ብዬ ዋና መንገዱን ይዤ፣ አልጋ ቤት ፍለጋ
ተጓዝኩኝ፡፡ ነጋዴ የሚርመሰመስበት፣ አዲስ ሰው፣ ፀጉረ ልውጥ ሰው
ከዐይን የማይገባበት ብዬ የገመትኩት ከተማ፣ ትንሽዬ መንደር ሆና አገኘኋት፡፡ መንገድ ዳር በብሎኬት የታጠረ ሰፊ ግቢ ያለው ሆቴል አየሁ፡፡ ሰላም ሆቴል ይላል፡፡ አላንገራገርኩም፡፡ ዘው ብዬ ገባሁ፡፡ ብቻ
አልጋ በኖረ፡፡
“አልጋ አለ?”
“አለ፡፡”
“እስቲ አሳዩኝ?”
“ባለሻወር ነው፣ ያለሻወር?”
“ባለሻወር፡፡” ቁልፍ አመጣችና አሳየችኝ፡፡
“ስንት ነው?”
“አንድ መቶ ሃምሳ ብር፡፡” ብሩን ሰጠኋትና ቦርሳዬን አስቀመጥኩ።
ሻወር ቤት ገብቼ ሻወር ቼክ ሳደርግ ውሀ የለችም፡፡ ዞር ስል፣ውሀ በባልዲ ተቀምጧል፡፡ በጣም አልቦኛል፣ ተለቃለኩኝ፡፡ እራት በልቼ ቢራ መጠጣት ጀመርኩ፡፡ ሙቀት ስለሆነ ተጠጣልኝ፡፡ ማታ ጥሩ እንቅልፍ ተኝቼ አደርኩ፡፡ ቀን ወጥቼ ከተማውን ዙሪያውን ሳይ ዋልኩ፡፡
በፍፁም እኔ እንዳሰብኩት አይደለም፡፡ የከተማው ዙሪያ ለጥ ያለ ለእርሻ የሚውል ሜዳ ሲሆን፣ ዛፎች በእርቀት ነው የሚገኙት፡፡ ስዞር ውዬ አመሻሹ ላይ፣ ቢራዬን እየጠጣሁ ምን እንደሚችል ሳስብ፣ አርሴማ ገዳም የሚል ሀሳብ መጣብኝ፡፡
#ኑሮ_በገዳም
ሽቅብ ዝግዛግ ሆኖ በተሰራውን የጥረጊያ መንገድረገ፣ በግራና በቀኝ በዛፎች ተከቧል፡፡ ከፊት ለፊቴ፣ አጠር ያለ ወጣት፣ የክርስቲያኖ ሮናልዶ ስዕል ያለበት ጥቁር የጨርቅ ሻንጣ በጀርባው ተሸክሞ በዝግታ ያዘግማል። እየተከታተልን ወደ ገዳሙ ዘልቀን ገባን። ከገዳሙ መግቢያ
በር ትንሽ ፈቅ ብላ ያለች የጭቃ ቤት ጋር ስንደርስ፤
“እንኳን ደህና መጣችሁ። ምዝገባ ቢጤ አለች።” አለን ፊቱ መጠጥ ያለ ጠይም ወጣት፡፡
“እሺ!” ብዬ ቆምኩኝ፡፡ ልጁን መዝግቦ ከጨርሰ በኋላ፣ ትንሽ ቆየኝ ብሎት እኔን መመዝግብ ጀመረ፡፡ ስም፣ እድሜ፣ የመጡበት አድራሻ፣ የአደጋ ግዜ ተጠሪ...፣ ሁሉንም ቀይሬ ነገርኩት፡፡
“ለስንት ግዜ ነው ሚቆዩት?”
“ለሦስት ሳምንት፡፡”
“መታወቂያ ይዘዋል?”
“አልያዝኩም፡፡” አልተጫነኝም፡፡
“እሺ፣ እንግዶቻችን፣ እኔ መልካሙ እባላለሁ፡፡ በገዳሙ አስተባባሪ ነኝ፡፡ አሁን ማደሪያ ቦታ እሰጣችኋለው፡፡ ገዳሙን
አስጎበኛችኋለው፤ ስለ ገዳሙ ታሪክ፣ መተዳደሪያ ደንብና ሌሎች መረጃዎችን እነግራችኋለው፡፡ እዚህ ገዳም፣ ማንኛውም አዲስ ሱባኤተኛ ሲገባ እናንተ እንዳደረጋችሁት ተመዝግቦ ነው፡፡ ገዳሙ የአርምሞ ገዳም ነው:: ማውራት ክልክል ነው፡፡ አስገዳጅ ነገር ካላጋጠማችሁ በስተቀር፣ ማውራት አይቻልም፡፡ የግድ ማውራት ካስፈለገ እንኳ፣ ዝግ ባለ ድምፅ፣ በለሆሳስ ነው ማውራት ሚቻለው፡፡ እዚህ መዳን የሚገኘው በአርምሞ ውስጥ ነው፡፡”
ከኛ ውጪ ለሌላ ሰው እንዳይሰማ፣ በሆዱ እንደሚያወራ፣ በጣም ዝግ ባለ ድምፅ ያወራናል፡፡ በአርምሞና በለሆሳስ ማለት እንዲህ ነው' ብዬ አሰብኩ፡፡ የሚያወራው እንዲሰማን፣ አንገታችንን ወደሱ አሰገግን፡፡ እያወራን ወደ ማደሪያችን ወሰደን፡፡ እያንዳንዱ ከሁለት መቶ ምዕመን በላይ የሚይዝ፣ አራት የማደሪያ አዳራሾች አሉ፡፡ ሁለቱ የወንድ፣ ሁለቱ የሴት እንደሆነ ነገረን፡፡ ቦታ ሊሰጠን ወደ አንደኛው አዳራሽ ይዞን ገባ፡፡ በውስጡ ከመቶ ሚበልጡ ምዕመናን አሉ፡፡አሰላሁት። በግምት በገዳሙ አንድ ሺህ የሚጠጉ ሱባኤያተኛ ምዕመናን
እንዳሉ ገመትኩኝ፡፡ ገዳሙ ግን ሰው ያለው አይመስልም፡፡ ዝም፣ ጭጭ፣ ያለ ነው፡፡ ሁሉም በለሆሳስ ፀሎት ላይ ነው፡፡ ሰላምታ እንኳ፣ ጎንበስ ቀና በመባባል ብቻ ነው፡፡ ምንም አይነት የሰው ድምፅ አይሰማም፡፡የወፎች ጭጭታና የዛፎች ሽው ሽውታ ብቻ ነው፡፡ በጣም ደስ ይላል፡፡መንፈስን ያድሳል፡፡ አዕምሮን ያረጋጋል፡፡ ፈውስ በመንፈስ ቅዱስ
ባይላክም እንኳ፣ የቦታው ድባብ ፈውስን ይሰጣል።
“እና ሌላው...” አለ መልካሙ ቦታችንን ሰጥቶን ከአዳራሹ ይዞን እየወጣ፣ “ማንኛውም ምእመን ወደ ገዳሙ ለሱባኤ ሲገባ፤ ፀጉሩን መላጨት፣ ንስሀ መግባትና ስግደት መውሰድ አለበት፡፡” አለን እኔን እኔን እየተመለከተ፡፡
“እሺ፡፡ ማን ነው ሚላጨን?”
“እርስ በእረስ ነው ምትለጫጩት፡፡ ፈራህ እንዴ..? አንተን እኔ ቆንጆ አድርጌ እላጭሃለው፡፡” የከተማ ልጅ መሆኔን አውቆ ነው መሰል፣ ከገባን ጀምሮ እኔን እኔን እየተመለከተ ነው ሲያወራ የነበረው፡፡
“እሺ” አልኩት፡፡ አሁን ስለራሴ ብዙም ግድ የለኝም፡፡ ምላጭ ግቢ ካለው ሱቅ ተገዝቶ ሁለታችንንም ላጨን፡፡ ነብስ ካወኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ፀጉሬን ተላጨሁ፡፡ እየላጨንም ስለ ገዳሙ መተዳደሪያ ደንብ ይነግረናል።
“በገዳሙ፣ በቀን ሁለት ጊዜ ብቻ ነው የሚበላው፡፡ ጥዋት ቅዳሴ እንዳለቀና ማታ አስራ ሁለት ሰዐት። አስራ ሁለት ሰዐት ካለፈ መመገብ አይቻልም፡፡ ገዳሙ መብራት ስለሌለው፣ ማታ ማታ ሻማ ነው
ምትጠቀሙት። ሻማ ከዚህ ሱቅ መግዛት ትችላላችሁ፡፡ የማታ ሦስት ሰዓት ፀሎት ካበቃ ቦሃላ ሻማ ማብራት አይቻልም፡፡ የእንቅልፍ ሰዓት ነው፡፡ እንዳያችሁት፣ የቦታ ጥበት ስላለ አንድ ሰው፣ በአንድ መዳበሪያ በታ ላይ ነው መተኛት ያለበት፡፡ የለሊቱ ዘጠኝ ሰአት ፀሎት ላይ ሁሉም
ምዕመን መገኘት ግዴታ ነው፡፡” ሁለታችንንም ላጭቶ ሲጨርስ አስራ
አንድ ሰዐት ሆኖ የሰርክ ፕሮግራም ተጀመረ።
“በሉ ተነሱ እንሂድ፣ የሚቸግራችሁ ነገር ካለ እዚሁ ስላለን በፈለጋችሁት ሰዓት ጠይቁኝ ፤ ” ብሎ ፕሮግራሙ ወደ ሚካሄድበት ስፍራ ወሰደን፡፡
የገዳም ኑሮዬ ተጀመረ፡፡ ለሊት ዘጠኝ ሰዓት መነሳት በጣም ከባድ ነው፡፡ ግን፣ አማራጭ የለም፡፡ አስተባባሪዎች እየዞሩ ይቀሰቅሳሉ።ያልተነሳ ሰው ላይ ቀዝቃዛ ውሃ ይረጫሉ፡፡ የመጀመሪያ ቀናቶች ላይ
በጣም ከበደኝ፡፡ ከእንቅልፍ ሳልነቃ ውሃ ሲረጩኝ እንደ ኤሌክትሪክ ይነዝረኛል፡፡ ሁለት ሦስት ቀን ሲደጋግሙኝ፣ ገና ድምፃቸውን ስሰማ መነሳት ጀመርኩ፡፡ ፀሎትና ምህላው እስከ ጥዋቱ አስራ ሁለት ሰዓት ይደረጋል፤ ከዛ ወደ ፀበል።
ገዳሙን ቅጥር ግቢ በደንብ ለማማወቅ እየተዟዟርኩ ማየት ጀመርኩ፡፡ የአርሴማ ገዳም በሃገራችን እንዳሉት አብዛኞቹ ገዳማት፣በተራራማ ቦታ ላይ ከየተመሰረተ ነው፡፡ የገዳሙ መስራችና አስተዳዳሪ
የሆኑት መነኩሴ፣ እድሜያቸው ሃምሳ ዓመት ቢሆን ነው፡፡ ገዳሙ በእውቀት እንዲለማ በደንብ አስበውበት እንደመሰረቱት ገዳሙ አፍ አውጥቶ ይናገራል፡፡ ከመሰረቱት
❤1👍1
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
ሻምበል ብሩክና ትህትና ድንበሩ ከተዋወቁ ዛሬ ልክ አንድ ወራቸው፡፡ የፍቅራቸው ወርሃዊ ልደት ውል የሚበጅበት ቀን በመሣሣም ደረጃ የቆየው ፍቅር ዛሬ ወደ አካላዊ ውህደት ሊሸጋገር እቅድ ተይዞለታል። ሻምበል ብሩክም ሆነ ትህትና የዛሬውን ቀን በልዩ ጉጉት ነው የጠበቁት።
እሁድ ዕለት አሥመራ መንገድ በሚገኘው በሻምበል ብሩክ ቤት ለማደር የወሰነችበት ቀን ነበር፡፡ ወደ ዶክተር ባይከዳኝ ቀጠሮ ስትሄድ የሚሰማት ስሜት ከቀጠሮው በስተጀርባ ባለው ምክንያት አስገዳጅነት እንጂ በፍቅር አስገዳጅነት አልነበረም፡፡
ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር የምትፈጽማቸው ግንኙነቶች እውነተኛ ስሜቷን የምትገልጽባቸው ሳይሆኑ፤ በተላበሰችው ጭምብል እውነተኛ ማንነቷን ደብቃ፤ በመድረክ ላይ ትያትር የምትሰራ ተዋናይ ሆና ነው የምትውለው፡፡ በሻምበል ብሩክ ፍቅር ግን ሰውነቷ እንደሻማ እየቀለጠ፣
ልቧ በዕልልታ እየጨፈረች፤ ሁለንተናዋን አሳልፋ የምትሰጠው በደስታ ስሜት ሰክራ ነው፡፡ በተለይ የመጀመሪያዋ በሆነው የወንድ ልጅ ፍቅር የተረታችለት ሰው፤ እንደዘመኑ ወጣቶች በአንድ ነገር ላይ ብቻ ትኩረት የሚሰጥ ሳይሆን በሷ ቦታ ሆኖ ሁሉን ነገር የሚያስብላትና፤
የሚያጽናናት፤ ሆኖ በመገኘቱ ፈጣሪዋን ታመሰግናለች፡፡
ብቻ አንዳንድ ጊዜ የሰው ልጅ ሥጋ ለባሽ ፍጡር ነውና፣ ሰው ተላላና ደካማ ፍጡር ነውና፤ ሰው ሰው ነውና፤ ይህ ሁሉ ፍቅር ድንገት ብን ብሎ ጠፍቶ፣ ሻምበል ብሩክም ተለውጦ፣ እንዳይከዳት ልቧ
መጠርጠሩ አልቀረም፡፡
እንደዚያ ታስብና ደግሞ አስተሳሰቧ ትክክል ባለመሆኑ እራሷን ወቅሳ “ብሩኬ አይለወጥም”
በማለት መልሳ መጽናናትን ታሳድራለች፡፡ በዛሬው ዕለት ሻምበል ብሩክ ቤት ለማደር ቀጠሮውን በልቧ የወሰደችው በከፍተኛ ደስታ ነው። ምናልባት የዛሬው አዳር ደግሞ ያንን ተንከባክባ ያቆየችውን የልጃገረድነት ወግ፣ ብር አምባሯን የምትፈተሽበት ወቅት ሊሆን ይችላል፡፡ ከዚያ በኋላ “ዞር በይ” ቢላትስ? ልቧ
በመጠራጠርና፤ ባለመጠራጠር፤ስሜት መሀል ገብቶ ሲዋዥቅ ከዋለ በኋላ
አንድ ነገር አሰበች።
ለሻምበል ብሩክ ልጃገረድ መሆኗን ገልጻለት፤ እንደ ወጉ፤ እንደ ሥርዐቱ፤ በጫጉላ ቤት ብር አምባሯን ልትሰጠው ያላትን ምኞች የሱን ስሜትና ፍላጐት ከተረዳች በኋላ ካሳወቀችውና በአጠቃላይ ስለማንኛውም ነገር አብረው በጋራ መወሰን እንደሚችሉ ገምታ፤ በዚሁ ሃሳብ ፀናች።
“እማይዬ ዛሬ አዜቢና ጋ ነው የማድረው ፓርቲ አዘጋጅታለች' በማለት እናቷን ዋሸቻት።
“ባርቲ ደግሞ ምንድነው ትሁቴ?” እናት በመጠራጠር ስሜት፡፡
“ያው ነዋ! ጓደኞቿ ተሰባስበን ስንጫወት ማደር ማለት ነዋ!” እየሳቀች፡፡
አደራሽን የኔ እራስሽን ጠብቂ!!” እናቷ ዐይን ዐይኖቿን እያየቻት።የውጭ አዳር የተሰማው ገና ዛሬ ነው፡፡
“ምንም ችግር የለም:: ማሚ ሙች!” ጉንጫን ሳመቻት፡፡ እናቷ በልቧ
ዝግጅቷን አሰበችው፡፡ በጠዋት ተነስቶ መተጣጠቡ፣ ቀኑን ሙሉ ሲመረጥ የተዋለው ልብስ፣ ሦስት ጊዜ አውልቃ ቀይራለች። መስተዋቱ ሥራ አልፈታም፡፡ መኳኳሉ ሁሉ ያልተለመደ ነበር።
በልቧ ወደ ሻምበል ብሩክ እንደምትሄድ ብታውቀውም የሰጠቻትን ምክንያት ይሁን ብላ ተቀበለቻት፡፡
ዛሬ ሻምበል ብሩክ ጋ የምታድር መሆኗን ለአንዱአለም ስለነገረችው በጊዜ ወደቤት እንዲገባ ተስማምተዋል። በዚህ ላይ የቤት ሰራተኛዋ እታፈራሁ ታክላበት እናቷን በመንከባከብ በኩል ኃላፊነቱን
ስለሚወስዱ የሚያስጨንቃት ነገር አልነበረም፡፡ ሁሉንም አጥብቃ አደራ
ብላ፤ ከቤት የወጣችው ከቀኑ አሥራ ሁለት ሰዓት ላይ ነበር።
ሻምበል ብሩክ ዛሬ ሽር ጉድ ሲል አርፍዷል። አልጋው ቦታ ሲመረጥለት፤ ሲንከራተት፤ የቤቱ ቁሳቁሶች በሙሉ በአዲስ መልክ አንዴ በጭንቅላታቸው፧ አንዴ በእግራቸው፤ ሲቆሙ፤ ቦታ ሲመረጥላቸው ነው የተዋለው፡፡
በዛሬው የቤት ዝግጅት ላይ ሠራተኛዋ ብቻ ሳትሆን ሁለቱም ታናናሽ ወንድሞቹ አብረውት ቤቱን ሲያተራምሱት ነው የዋሉት፡፡
በመጨረሻ ላይ ግን ከዚያ በፊት ያልታየበት ዓይነት ሥርዓትና መልክ ይዞ ሲያይ ሻምበል ብሩክ ተደነቀ፡፡
በእርግጥም ይህ ሁሉ የሆነው በትህትና ምክንያት መሆኑን ሲያስብ፤ የትዳር ውጥኑ አግባብ መሆኑን አመነ። በዚያ በቤቱ ሥርዓት ተማርኮ ወደሌላ ሃሳብ ውስጥ ገባ፡፡
ባለፋቸው መጥፎ ጊዜያቶች ውስጥ የተጐዳ ልቡ፣ በትህትና የወደፊት የትዳር እመቤቱ አማካይነት ሊታደስና፤ ሲታነጽ፤ ታየው።
እናም የትዳር መዓዛ በርቀት ሸተተው፡፡ ይህ በርቀት የሚሸተው የትዳር መዓዛ ቀርቦ እንዲያውደው ተመኘ፡፡
ትህትና እስከምትመጣለት የቀጠሮው ሰዓት እስከሚደርስ ድረስ ተንቆራጠጠ።
ዛሬ የሚነግራት ትልቅ ጉዳይ አለው። እሷም እንደሱ በጉዳዩ
ላይ ፈቃደኛ ከሆነች ጉዳዩ የምሥራች ይሆናል። እሷን የፈለጋት ጊዜያዊ
ፍቅረኛ እንድትሆነው ሳይሆን፤ ዘላቂ የትዳር ጓደኛው እንድትሆን ነው::
ይህ እሱ የጓጓለትን በፀጋ ከተቀበለችለት ደስታው እጥፍ ድርብ ይሆናል፡፡
“ትሁት.. ትሁት.. ትሁት.. ስሟን ደጋገመው። በልቡ፡፡
ልክ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ላይ ታላቋ እንግዳ የዱር ጽጌረዳ መስላ አምራና፤ ደምቃ ከች! አለች፡፡ ቤቱን ከዚህ ቀደም አንድ ሁለት ጊዜ አይታዋለች፡፡ የዛሬውን ልዩ የሚያደርገው ለማደር ወስና የመጣችበት ዕለት በመሆኑ ነው፡፡
ሻምበል ብሩክ ከደጅ ወጥቶ እየተጠባበቃት ነበር። በሁለመናው
አቅፎ ተቀበላት፡፡
ከዚያም አጥሩን ዘልቀው እየተሳሳቁ፣ እጅ ለእኛ ተያይዘው ወደ ቤት ገቡ፡፡
የሻምበል ብሩክ ሁለት ታናናሽ ወንድሞቹ ሰላምታ አቅርበውላት ትንሽ ከተጫወቱ በኋላ የግል ነፃነት ሊሰጧቸው ወጡ።
ዛሬ የሻምበል ብሩክ ቤት ልዩ ሆናለች:: ትህትናም ከዚያ በፊት ያየቸው ቤት መሆኑ እስከሚያጠራጠራት ድረስ የቤት ዕቃዎቹ አቀማመጥ አስደንቋታል፡፡
ሻምበል ብሩክ የትዳር ምኞቱን ሊገልጽላት ሲያሰላስል፤ እሷ ደግሞ ሌላ የምትገልጽለት እጹብ ድንቅ የሆነ የምስራች ነበራት። ሻምበል ብሩክ በፍቅር ቢወድቅላትም፤ ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ ያልገመተውን ገፀ በረከት ልታቀርብለት ማሰቧን ቢያውቅ ኖሮ ምንኛ ደስተኛ ይሆን ነበር?፣
ቀለል ያለ እራት ከበሉ በኋላ ይሄንን የቀዘቀዘ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራቸውን
መኮምኮም ቀጠሉ። ዛሬ ቢራው አልመረራትም። የፍቅር ስኳር
ተጨምሮበት ነው መሰል፤ ከምትወደው ሰው ጋር በፍቅር እየቀለጡ፤ ሲኮመኩሙት ማር ሆነና ቁጭ አለ፡፡ ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር ሆና ስትጠጣው የግራዋ ጭማቂ ያህል ነበር የሚመራት። አሁን ግን ጣፈጣት፡፡
አንዱን ቢራ ጨረስችና በህይወቷ ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለተኛውን የቢራ ጠርሙስ ጨበጠች፡፡ ሻምበል ብሩክ የወደፊት የትዳር ጓደኛው ከምትሆን ቆንጆ ጋር እያሳለፈ ባለው ጊዜ እጅግ ከመደሰቱም በላይ ከረጅም ዓመታት በፊት እጮኛው ከነበረችው በድሏ ጋር ያሳልፉ የነበረውን ዓይነት ልዩ ስሜት አጫረበትና፤ ጨዋታውን በሰፊው ቀጠለ። እየተቃቀፉ መላላሱ ፤ መሳሳሙ፤ ሁሉ ለጉድ ነበር፡፡
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ሲሆን ወደ መኝታ ክፍላቸው መሄድ ፈለጉ።
የመኝታ ክፍሏ በንጽህና የተጠበቀች ናት። እንደገቡ በነጭ ስስ የመጋረጃ ጨርቅ የተሸፈነውን ባለመስታወት መስኮት ሲገልጡት ፍንትው ብላ ደምቃ የወጣችው ጨረቃ ብርሃኗን ወደመኝታ ክፍላቸው ውስጥ አዘለቀችላቸው...
ያንን የጨረቃ ውበት ሲያስተውሉ፤ መብራቱን አጠፉት በዚያች ክፍል
ውስጥ ጨረቃና ፍቅር ነገሱ ከዚያም ልብሳቸውን እንደለበሱ አልጋቸው ላይ ጋደም ብለው መላፋታቸውን ቀጠሉ....
የትህትና ሁኔታ የተለየ ነበር ከዚያ በፊት ለወንድ ልጅ የነበራት ስሜት ምን እንደ ነበረና አሁን ምን እየሆነች እንዳለች
ስታስበው
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
ሻምበል ብሩክና ትህትና ድንበሩ ከተዋወቁ ዛሬ ልክ አንድ ወራቸው፡፡ የፍቅራቸው ወርሃዊ ልደት ውል የሚበጅበት ቀን በመሣሣም ደረጃ የቆየው ፍቅር ዛሬ ወደ አካላዊ ውህደት ሊሸጋገር እቅድ ተይዞለታል። ሻምበል ብሩክም ሆነ ትህትና የዛሬውን ቀን በልዩ ጉጉት ነው የጠበቁት።
እሁድ ዕለት አሥመራ መንገድ በሚገኘው በሻምበል ብሩክ ቤት ለማደር የወሰነችበት ቀን ነበር፡፡ ወደ ዶክተር ባይከዳኝ ቀጠሮ ስትሄድ የሚሰማት ስሜት ከቀጠሮው በስተጀርባ ባለው ምክንያት አስገዳጅነት እንጂ በፍቅር አስገዳጅነት አልነበረም፡፡
ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር የምትፈጽማቸው ግንኙነቶች እውነተኛ ስሜቷን የምትገልጽባቸው ሳይሆኑ፤ በተላበሰችው ጭምብል እውነተኛ ማንነቷን ደብቃ፤ በመድረክ ላይ ትያትር የምትሰራ ተዋናይ ሆና ነው የምትውለው፡፡ በሻምበል ብሩክ ፍቅር ግን ሰውነቷ እንደሻማ እየቀለጠ፣
ልቧ በዕልልታ እየጨፈረች፤ ሁለንተናዋን አሳልፋ የምትሰጠው በደስታ ስሜት ሰክራ ነው፡፡ በተለይ የመጀመሪያዋ በሆነው የወንድ ልጅ ፍቅር የተረታችለት ሰው፤ እንደዘመኑ ወጣቶች በአንድ ነገር ላይ ብቻ ትኩረት የሚሰጥ ሳይሆን በሷ ቦታ ሆኖ ሁሉን ነገር የሚያስብላትና፤
የሚያጽናናት፤ ሆኖ በመገኘቱ ፈጣሪዋን ታመሰግናለች፡፡
ብቻ አንዳንድ ጊዜ የሰው ልጅ ሥጋ ለባሽ ፍጡር ነውና፣ ሰው ተላላና ደካማ ፍጡር ነውና፤ ሰው ሰው ነውና፤ ይህ ሁሉ ፍቅር ድንገት ብን ብሎ ጠፍቶ፣ ሻምበል ብሩክም ተለውጦ፣ እንዳይከዳት ልቧ
መጠርጠሩ አልቀረም፡፡
እንደዚያ ታስብና ደግሞ አስተሳሰቧ ትክክል ባለመሆኑ እራሷን ወቅሳ “ብሩኬ አይለወጥም”
በማለት መልሳ መጽናናትን ታሳድራለች፡፡ በዛሬው ዕለት ሻምበል ብሩክ ቤት ለማደር ቀጠሮውን በልቧ የወሰደችው በከፍተኛ ደስታ ነው። ምናልባት የዛሬው አዳር ደግሞ ያንን ተንከባክባ ያቆየችውን የልጃገረድነት ወግ፣ ብር አምባሯን የምትፈተሽበት ወቅት ሊሆን ይችላል፡፡ ከዚያ በኋላ “ዞር በይ” ቢላትስ? ልቧ
በመጠራጠርና፤ ባለመጠራጠር፤ስሜት መሀል ገብቶ ሲዋዥቅ ከዋለ በኋላ
አንድ ነገር አሰበች።
ለሻምበል ብሩክ ልጃገረድ መሆኗን ገልጻለት፤ እንደ ወጉ፤ እንደ ሥርዐቱ፤ በጫጉላ ቤት ብር አምባሯን ልትሰጠው ያላትን ምኞች የሱን ስሜትና ፍላጐት ከተረዳች በኋላ ካሳወቀችውና በአጠቃላይ ስለማንኛውም ነገር አብረው በጋራ መወሰን እንደሚችሉ ገምታ፤ በዚሁ ሃሳብ ፀናች።
“እማይዬ ዛሬ አዜቢና ጋ ነው የማድረው ፓርቲ አዘጋጅታለች' በማለት እናቷን ዋሸቻት።
“ባርቲ ደግሞ ምንድነው ትሁቴ?” እናት በመጠራጠር ስሜት፡፡
“ያው ነዋ! ጓደኞቿ ተሰባስበን ስንጫወት ማደር ማለት ነዋ!” እየሳቀች፡፡
አደራሽን የኔ እራስሽን ጠብቂ!!” እናቷ ዐይን ዐይኖቿን እያየቻት።የውጭ አዳር የተሰማው ገና ዛሬ ነው፡፡
“ምንም ችግር የለም:: ማሚ ሙች!” ጉንጫን ሳመቻት፡፡ እናቷ በልቧ
ዝግጅቷን አሰበችው፡፡ በጠዋት ተነስቶ መተጣጠቡ፣ ቀኑን ሙሉ ሲመረጥ የተዋለው ልብስ፣ ሦስት ጊዜ አውልቃ ቀይራለች። መስተዋቱ ሥራ አልፈታም፡፡ መኳኳሉ ሁሉ ያልተለመደ ነበር።
በልቧ ወደ ሻምበል ብሩክ እንደምትሄድ ብታውቀውም የሰጠቻትን ምክንያት ይሁን ብላ ተቀበለቻት፡፡
ዛሬ ሻምበል ብሩክ ጋ የምታድር መሆኗን ለአንዱአለም ስለነገረችው በጊዜ ወደቤት እንዲገባ ተስማምተዋል። በዚህ ላይ የቤት ሰራተኛዋ እታፈራሁ ታክላበት እናቷን በመንከባከብ በኩል ኃላፊነቱን
ስለሚወስዱ የሚያስጨንቃት ነገር አልነበረም፡፡ ሁሉንም አጥብቃ አደራ
ብላ፤ ከቤት የወጣችው ከቀኑ አሥራ ሁለት ሰዓት ላይ ነበር።
ሻምበል ብሩክ ዛሬ ሽር ጉድ ሲል አርፍዷል። አልጋው ቦታ ሲመረጥለት፤ ሲንከራተት፤ የቤቱ ቁሳቁሶች በሙሉ በአዲስ መልክ አንዴ በጭንቅላታቸው፧ አንዴ በእግራቸው፤ ሲቆሙ፤ ቦታ ሲመረጥላቸው ነው የተዋለው፡፡
በዛሬው የቤት ዝግጅት ላይ ሠራተኛዋ ብቻ ሳትሆን ሁለቱም ታናናሽ ወንድሞቹ አብረውት ቤቱን ሲያተራምሱት ነው የዋሉት፡፡
በመጨረሻ ላይ ግን ከዚያ በፊት ያልታየበት ዓይነት ሥርዓትና መልክ ይዞ ሲያይ ሻምበል ብሩክ ተደነቀ፡፡
በእርግጥም ይህ ሁሉ የሆነው በትህትና ምክንያት መሆኑን ሲያስብ፤ የትዳር ውጥኑ አግባብ መሆኑን አመነ። በዚያ በቤቱ ሥርዓት ተማርኮ ወደሌላ ሃሳብ ውስጥ ገባ፡፡
ባለፋቸው መጥፎ ጊዜያቶች ውስጥ የተጐዳ ልቡ፣ በትህትና የወደፊት የትዳር እመቤቱ አማካይነት ሊታደስና፤ ሲታነጽ፤ ታየው።
እናም የትዳር መዓዛ በርቀት ሸተተው፡፡ ይህ በርቀት የሚሸተው የትዳር መዓዛ ቀርቦ እንዲያውደው ተመኘ፡፡
ትህትና እስከምትመጣለት የቀጠሮው ሰዓት እስከሚደርስ ድረስ ተንቆራጠጠ።
ዛሬ የሚነግራት ትልቅ ጉዳይ አለው። እሷም እንደሱ በጉዳዩ
ላይ ፈቃደኛ ከሆነች ጉዳዩ የምሥራች ይሆናል። እሷን የፈለጋት ጊዜያዊ
ፍቅረኛ እንድትሆነው ሳይሆን፤ ዘላቂ የትዳር ጓደኛው እንድትሆን ነው::
ይህ እሱ የጓጓለትን በፀጋ ከተቀበለችለት ደስታው እጥፍ ድርብ ይሆናል፡፡
“ትሁት.. ትሁት.. ትሁት.. ስሟን ደጋገመው። በልቡ፡፡
ልክ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ላይ ታላቋ እንግዳ የዱር ጽጌረዳ መስላ አምራና፤ ደምቃ ከች! አለች፡፡ ቤቱን ከዚህ ቀደም አንድ ሁለት ጊዜ አይታዋለች፡፡ የዛሬውን ልዩ የሚያደርገው ለማደር ወስና የመጣችበት ዕለት በመሆኑ ነው፡፡
ሻምበል ብሩክ ከደጅ ወጥቶ እየተጠባበቃት ነበር። በሁለመናው
አቅፎ ተቀበላት፡፡
ከዚያም አጥሩን ዘልቀው እየተሳሳቁ፣ እጅ ለእኛ ተያይዘው ወደ ቤት ገቡ፡፡
የሻምበል ብሩክ ሁለት ታናናሽ ወንድሞቹ ሰላምታ አቅርበውላት ትንሽ ከተጫወቱ በኋላ የግል ነፃነት ሊሰጧቸው ወጡ።
ዛሬ የሻምበል ብሩክ ቤት ልዩ ሆናለች:: ትህትናም ከዚያ በፊት ያየቸው ቤት መሆኑ እስከሚያጠራጠራት ድረስ የቤት ዕቃዎቹ አቀማመጥ አስደንቋታል፡፡
ሻምበል ብሩክ የትዳር ምኞቱን ሊገልጽላት ሲያሰላስል፤ እሷ ደግሞ ሌላ የምትገልጽለት እጹብ ድንቅ የሆነ የምስራች ነበራት። ሻምበል ብሩክ በፍቅር ቢወድቅላትም፤ ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ ያልገመተውን ገፀ በረከት ልታቀርብለት ማሰቧን ቢያውቅ ኖሮ ምንኛ ደስተኛ ይሆን ነበር?፣
ቀለል ያለ እራት ከበሉ በኋላ ይሄንን የቀዘቀዘ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራቸውን
መኮምኮም ቀጠሉ። ዛሬ ቢራው አልመረራትም። የፍቅር ስኳር
ተጨምሮበት ነው መሰል፤ ከምትወደው ሰው ጋር በፍቅር እየቀለጡ፤ ሲኮመኩሙት ማር ሆነና ቁጭ አለ፡፡ ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር ሆና ስትጠጣው የግራዋ ጭማቂ ያህል ነበር የሚመራት። አሁን ግን ጣፈጣት፡፡
አንዱን ቢራ ጨረስችና በህይወቷ ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለተኛውን የቢራ ጠርሙስ ጨበጠች፡፡ ሻምበል ብሩክ የወደፊት የትዳር ጓደኛው ከምትሆን ቆንጆ ጋር እያሳለፈ ባለው ጊዜ እጅግ ከመደሰቱም በላይ ከረጅም ዓመታት በፊት እጮኛው ከነበረችው በድሏ ጋር ያሳልፉ የነበረውን ዓይነት ልዩ ስሜት አጫረበትና፤ ጨዋታውን በሰፊው ቀጠለ። እየተቃቀፉ መላላሱ ፤ መሳሳሙ፤ ሁሉ ለጉድ ነበር፡፡
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ሲሆን ወደ መኝታ ክፍላቸው መሄድ ፈለጉ።
የመኝታ ክፍሏ በንጽህና የተጠበቀች ናት። እንደገቡ በነጭ ስስ የመጋረጃ ጨርቅ የተሸፈነውን ባለመስታወት መስኮት ሲገልጡት ፍንትው ብላ ደምቃ የወጣችው ጨረቃ ብርሃኗን ወደመኝታ ክፍላቸው ውስጥ አዘለቀችላቸው...
ያንን የጨረቃ ውበት ሲያስተውሉ፤ መብራቱን አጠፉት በዚያች ክፍል
ውስጥ ጨረቃና ፍቅር ነገሱ ከዚያም ልብሳቸውን እንደለበሱ አልጋቸው ላይ ጋደም ብለው መላፋታቸውን ቀጠሉ....
የትህትና ሁኔታ የተለየ ነበር ከዚያ በፊት ለወንድ ልጅ የነበራት ስሜት ምን እንደ ነበረና አሁን ምን እየሆነች እንዳለች
ስታስበው
👍2🔥2❤1
#የፍቅር_ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
....ዋናው አዛዥ ብሩዲም ወደ ጉድማን ዞሮ “አንተም ማስታወሻዎቹን
አንብበህ ጨርሰሃል አይደል? እሺ በጆንሰን ሀሳብ ትስማማለህ?”
ጉድማንም የእግሮቹን ንብብሮሽ ስላልተመቸው ቀያየራቸው እና ዶክተር
ሮበርትስ ስለ በሽተኞቿ በማስታወሻዎቿ ላይ የፃፈቻቸውን ነገሮች በውስጡ
መከለስ ጀመረ።
ዶክተር ሮበርትስ ማስታወሻዎቹን ሌላ ሰው ያነባቸዋል ስላልገመተች ስለ በሽተኞቿ የተሰማትን ነገሮች ሁሉ ነው ማስታወሻዋ ላይ ያሰፈረችው። ይህንን ደግሞ ያደረገችው ምናልባት በሚቀጥለው የህክምና ጊዜያቸው ላይ በሽተኞቿን ስታገኛቸው ከግለሰባዊ ባህርያቸው በመነሳት ልትረዳቸው በማሰብ እንደሆነም ያምናል። ግን እዚህ ላይ ጆንሰን ለዶክተሯ ያለው ጥላቻ ወደዚህ አይነት ማጠቃለያ ላይ እንዲደርስ ሊያደርገው እንደሚችል እንዴት አላሰበውም? ይህንን በውስጡ ሲያውጠነጥን ቆየ እና
“መልካም ማስታወሻዎቹ ላይ ስለ ታካሚዎቿ ስነ ባህሪ ግምገማን (ፍርድን)
አካሂዳለች ብዬ አምናለሁ” ብሎ መለሰ፡፡
ይሄኔም ጆንሰን የሹፈት ሳቅ ሳቀበት እና ግምገማ አልክ? ሮበርትስ እኮ ይህቺ ሊዛ ፍላንገን የተባለችን ሴት ትጠላታለች። በማስታወሻዋ ላይ ሊዛ ፍላንገን የምትገልፃት ለድርጊቷ መጠየቅ እንዳለባት ማለትም በሌሎች ሴቶች (ሚስቶች) ላይ ለፈጠረችው ስቃይ መጠየቅ እንዳለባት ነው የማስታወሻዋ ዋነኛ ሀሳብ” አለ፡፡
“ዋነኛው ሀሳብ ደግሞ ምንድነው?” ብሎ አዛዡ ግራ ተጋብቶ ጠየቀው።
ሚኪ ሮበርትስ ውሽማ በሚሆኑ ሴቶች ላይ ሁሉ ቂም አላት” አለ ጆንስን፡፡
“እንዴ ይሄ እኮ ሃጢአቱን እሷ ላይ ማብዛት ነው።” ብሎ ጉድማን
ጣልቃ ገባ ።
“ይመስልሀል? እኔ ግን አይመስለኝም፡፡ ለማንኛውም ማስታወሻዋን
ካነበብኩኝ በኋላ ለምንድነው በሊዛ ፍላንገን ላይ ይህን ይህል ቅሬታ
ያደረባት? ብዬ ራሴን ጠየቅኩኝ” ብሎ ጆንሰን ማብራሪያውን በመቀጠልም
“በመጨረሻም ነገሩ ከሟች ባሏ ጋር በተገናኘ እንደሆነ ለማወቅ በቃሁ”
“ባሏ ሞቶ አይደል እንዴ?” ብሎ አዛዥ ብሩዲ ጉንጩን እያሸ ጠየቀ::
“ልክ ነው ባሏ ሞቷል። ዶክተር ዳግላስ ሮበርትስ ባለፈው ዓመት በ 405 ኛው ጎዳና ላይ የአደጋው ምክንያት ባልታወቀ የመኪና አደጋ ህይወቱን አጥቷል። ግን በወቅቱ መኪናው ውስጥ ከእሱ ጎን ማን እንደነበር እስቲ ገምቱ” አላቸው፡፡ ሁለቱም አዛዥ ብሩዲ እና ጉድማን ግምታቸውን ለማስቀመጥ በጥሩ ስሜት ውስጥ ስላልሆኑ ምላሹን እንዲሰጣቸው
እያፈጠጡበት ዝም አሉ።
“ውሽማው አብራው ነበረች!” ብሎ ጉድማን በመቀጠልም “የሆነች
ሩሲያዊ ሴትን ከጎኑ አስቀምጦ መኪናውን ሲያሽከረክር ነበር አደጋው የደረሰው። በአደጋው ሁለቱም ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡ ያን ዕለት ነበር ዶክተር ኒኪ ሮበርትስ ባሏ ከትዳር ውጪ ያለውን ግንኙነት ለመጀመሪያ ጊዜ ያወቀችው እንግዲህ”
የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች በአደጋው ከነደደ መኪና ውስጥ የሁለት ሰዎችን ሬሳ ሲያወጡ እሷ ምን ሊሰማት እንደሚችል አስቡት እስቲ! የውስጥ ህመሙን? ውርደቱን? ሁሉም ሰው እና እናንተም ጭምር ሁለቱ ምን ያህል የሚቀናበት ትዳር እንዳላቸው ታምኑ አልነበር?” ብሎ ጆንሰን ጉድማንን አገኘሁህ በሚል ስሜት ተመለከተው፡፡
ኒኪም ማታ ላይ ስለ ባሏ በግልፅ ነግራዋለች፡፡ ስለ ባሏ የተናገረችበት
መንገድ ግን ሀዘን እና ንዴት የተቀላቀለበት እንደሆነም በወቅቱ ተረድቶ
ነበር። ያም ቢሆን ግን ስለ ባሏ ውሽማ ምንም አይነት ነገር እንዳልነገረችው
አስታወሰ። በተጨማሪ ደግሞ ኒኪን ያገባ ወንድ ምንጎድሎበት ነው ሌላ ውሽማ የሚይዘው? ዊሊ ባደን ቫለንቲና ስላረጀችበት ሊሆን ይችላል ሌላ
ወጣት ሴት የወሸመው፡፡ ስለዚህም ጆንሰን ሆን ብሎ ነገሩን እንደፈጠረ
ገመተ፡፡
“ይህንን አንተ እንዴት አወቅክ?” ብሎ በቁጣ ድምፅ ጠየቀው፡፡
“በኢንተርኔት ላይ ተገልፆ ነበር፡፡” ብሎ ጆንሰን መለስ እና በመቀጠልም
“ወዲያው አደጋው እንደደረሰ ሳይሆን ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ነው። ታዲያ ዜናው ላይ የተገለፀው:: ከዶክተር ዳግላስ አጠገብ አንዲት ሴት ብቻ
ነበረች ብሎ ነው የዘገበው፡፡ እኔ ግን የዶውግን እና የኒኪን የቅርብ ጓደኞቻቸውን አግኝቼ በመጠየቅ እውነቱን ለማረጋገጥ በቃሁ። ይሄንን አስቀያሚ ሚስጥሯንም ደብቃናለች። ይህ ሚስጥሯም ነው እንግዲህ ከፍተኛ
ንዴት ውስጥ የሚከታት...”
“እሺ ባሏ እንደፈለገ እየማገጠ ነበር እንበል። ታዲያ ይህ ነገር ከሁለቱ
ግድያዎች ጋር ምን ያገናኘዋል?” ብሎ ብሩዲ ጆንሰንን ጠየቀው፡፡
“ጌታዬ እኔ በዚህ ዙሪያ ስላሉ ነገሮች በትንሹም ቢሆን ምርመራዎቼን
ለማድረግ ሞክሬ ነበር። ከሁለት ቀናት በፊት ስለ አደጋው የተደረገውን
ሪፖርትንም ለማየት ሞክሬ ነበር። በዚህም ስለ ዶክተር ዳግላስ እና ስለ
ሩስያዊት ውሽማው ለማወቅ የበኩሌን ጥረት ሳደርግ ነበር።”
ይሄኔም ጉድማን ከተቀመጠበት ፍንጥር ብሎ ተነሳ እና “ይሄን ነገር እኮ
አልነገርከኝም!” ብሎ በመጮጮህ ተቃውሞውን አሰማ፡፡
እንዴ አንተ ሥራ በዝቶብህ ነበር እኮ ታስታውሳለህ?” ብሎ ጆንሰን መለሰለት እና “በዚያ ላይ ደግሞ አንተው ራስህ እንዳወራህልኝ ግልፅ አልነበርክም። ለማንኛውም አታስብ ስለ አደጋው የቀረበ ሪፖርት አንድም የተመዘገበ ነገር አላገኘሁም”
“ምን ማለትህ ነው?” ብሎ ነገሩ እንቆቅልሽ የሆነበት አዛዥ ብሩዲ
ጥያቄውን አቀረበ፡፡
“አዎን ሲስተሙ ላይ አደጋው የተመዘገበ አንድም ሪፖርት የለም ወይንም አደጋው ጨርሶ አልተመዘገበም ወይንም ደግሞ የተመዘገበውን የሆነ ሰው ሰርዞታል” ብሎ ሲናገር አዛዥ ብሩዲ በስልቸታ ፊት ሲያየው ጊዜ ጆንስን ማብራሪያውን ቀጠለ። “ወደ ነጥቤ እየመጣሁ ነው አንዴ ታገሱኝ።ይሄ ደግሞ ነገሩን ይበልጥ እንድመረምረው ምክንያት ሆነኝ። አደጋው እንደደረሰ እንኳን እኔ ማንም ሰው ያውቀዋል። አደጋው በየጋዜጦቹ ላይ
በጊዜው ሲፃፍ ነበር፡፡ በተለይ ደግሞ ኤል.ኤ.ታይምስ ዶክተር ዳግላስ ምን
ያህል ትሁት እና ጨዋ ሰው እንደሆነ፣ ባሏ የሞተባትንም ዶክተር ኒኪንም
ምን ያህል የተጎዳች ቆንጆ መልከ መልካም አድርጎ ነበር ሲፅፍላቸው
ማንኛውም ጋዜጣ ወይንም መፅሄት ግን አብራው ስለሞተችው ሩስያዊት
አልገለፁም፡፡ የሩስያዊቷ ጉዳይ የወጣው ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ነበር።
ለማንኛውም ዶክተር ግላስ ቴስላ መኪናዋን የገዛበትን የመኪና መሸጫ
ቦታን ፈልጌ አገኘሁት:: እዚያም ደርሼ ከአደጋው በኋላ የመኪናውን
የኮምፒውተር ሲስተም የመረመረውን ኢንጅነር አግኝቼው ነበር። እሱ
እንደነገረኝም ከአደጋው በፊት የመኪናው የኮምፒውተር ሲስተም ተበላሽቶ
ነበር።
“ተበላሽቶ ነበር ማለት?”
“በሪሞት ኮንትሮል ሀክ ተደርጎ ነበር” አለ እና ጆንሰን ማብራሪያውን በመቀጠልም “በነገሩ በጣም እርግጠኛ ባይሆንም የመኪናው የኮምፒውተር ሲስተም ኮድ ተዛብቶ ስለነበረ ይሄ የኮድ መዛባት ደግሞ መኪናው የሆነ ፍጥነት ካለፈ በኋላ የፍጥነትና እና የፍሬን ሲስተሙ ተናብበው እንዳይሰሩ እንደሚያደርጋቸው ገምቶ ነበር፡፡ ይህንን ነገርም በወቅቱ ለአለቃው አመልክቶ ነበር። አለቃውም ነገሩን ለፖሊስ ሪፖርት እንዲያደርግም
አሳስቦት ነበር”
“እናስ ጉዳዩን ለፖሊስ አመለከተ አለቃው?” ብሩዲ ጠየቀ፡፡
“ቅድም እንደነገርኳችሁ ስለ አደጋው ሪፖርት የተመዘገበ ነገር የለም::
ስለዚህ የኢንጅነሩ አለቃ ጉዳዩን ለፖሊስ ያመልክት አያመልክት ለማወቅ አልቻልኩም፡፡ የኢንጅነር ዴመን አለቃም ባለፈው ፋሲካ በልብ በሽታ ህይወቱ አልፏል” አላቸው
ጆንስን ይህንን ከተናገረ በኋላ ጉድማን እና የፖሊስ አዛዥ ብሩዲ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
....ዋናው አዛዥ ብሩዲም ወደ ጉድማን ዞሮ “አንተም ማስታወሻዎቹን
አንብበህ ጨርሰሃል አይደል? እሺ በጆንሰን ሀሳብ ትስማማለህ?”
ጉድማንም የእግሮቹን ንብብሮሽ ስላልተመቸው ቀያየራቸው እና ዶክተር
ሮበርትስ ስለ በሽተኞቿ በማስታወሻዎቿ ላይ የፃፈቻቸውን ነገሮች በውስጡ
መከለስ ጀመረ።
ዶክተር ሮበርትስ ማስታወሻዎቹን ሌላ ሰው ያነባቸዋል ስላልገመተች ስለ በሽተኞቿ የተሰማትን ነገሮች ሁሉ ነው ማስታወሻዋ ላይ ያሰፈረችው። ይህንን ደግሞ ያደረገችው ምናልባት በሚቀጥለው የህክምና ጊዜያቸው ላይ በሽተኞቿን ስታገኛቸው ከግለሰባዊ ባህርያቸው በመነሳት ልትረዳቸው በማሰብ እንደሆነም ያምናል። ግን እዚህ ላይ ጆንሰን ለዶክተሯ ያለው ጥላቻ ወደዚህ አይነት ማጠቃለያ ላይ እንዲደርስ ሊያደርገው እንደሚችል እንዴት አላሰበውም? ይህንን በውስጡ ሲያውጠነጥን ቆየ እና
“መልካም ማስታወሻዎቹ ላይ ስለ ታካሚዎቿ ስነ ባህሪ ግምገማን (ፍርድን)
አካሂዳለች ብዬ አምናለሁ” ብሎ መለሰ፡፡
ይሄኔም ጆንሰን የሹፈት ሳቅ ሳቀበት እና ግምገማ አልክ? ሮበርትስ እኮ ይህቺ ሊዛ ፍላንገን የተባለችን ሴት ትጠላታለች። በማስታወሻዋ ላይ ሊዛ ፍላንገን የምትገልፃት ለድርጊቷ መጠየቅ እንዳለባት ማለትም በሌሎች ሴቶች (ሚስቶች) ላይ ለፈጠረችው ስቃይ መጠየቅ እንዳለባት ነው የማስታወሻዋ ዋነኛ ሀሳብ” አለ፡፡
“ዋነኛው ሀሳብ ደግሞ ምንድነው?” ብሎ አዛዡ ግራ ተጋብቶ ጠየቀው።
ሚኪ ሮበርትስ ውሽማ በሚሆኑ ሴቶች ላይ ሁሉ ቂም አላት” አለ ጆንስን፡፡
“እንዴ ይሄ እኮ ሃጢአቱን እሷ ላይ ማብዛት ነው።” ብሎ ጉድማን
ጣልቃ ገባ ።
“ይመስልሀል? እኔ ግን አይመስለኝም፡፡ ለማንኛውም ማስታወሻዋን
ካነበብኩኝ በኋላ ለምንድነው በሊዛ ፍላንገን ላይ ይህን ይህል ቅሬታ
ያደረባት? ብዬ ራሴን ጠየቅኩኝ” ብሎ ጆንሰን ማብራሪያውን በመቀጠልም
“በመጨረሻም ነገሩ ከሟች ባሏ ጋር በተገናኘ እንደሆነ ለማወቅ በቃሁ”
“ባሏ ሞቶ አይደል እንዴ?” ብሎ አዛዥ ብሩዲ ጉንጩን እያሸ ጠየቀ::
“ልክ ነው ባሏ ሞቷል። ዶክተር ዳግላስ ሮበርትስ ባለፈው ዓመት በ 405 ኛው ጎዳና ላይ የአደጋው ምክንያት ባልታወቀ የመኪና አደጋ ህይወቱን አጥቷል። ግን በወቅቱ መኪናው ውስጥ ከእሱ ጎን ማን እንደነበር እስቲ ገምቱ” አላቸው፡፡ ሁለቱም አዛዥ ብሩዲ እና ጉድማን ግምታቸውን ለማስቀመጥ በጥሩ ስሜት ውስጥ ስላልሆኑ ምላሹን እንዲሰጣቸው
እያፈጠጡበት ዝም አሉ።
“ውሽማው አብራው ነበረች!” ብሎ ጉድማን በመቀጠልም “የሆነች
ሩሲያዊ ሴትን ከጎኑ አስቀምጦ መኪናውን ሲያሽከረክር ነበር አደጋው የደረሰው። በአደጋው ሁለቱም ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡ ያን ዕለት ነበር ዶክተር ኒኪ ሮበርትስ ባሏ ከትዳር ውጪ ያለውን ግንኙነት ለመጀመሪያ ጊዜ ያወቀችው እንግዲህ”
የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች በአደጋው ከነደደ መኪና ውስጥ የሁለት ሰዎችን ሬሳ ሲያወጡ እሷ ምን ሊሰማት እንደሚችል አስቡት እስቲ! የውስጥ ህመሙን? ውርደቱን? ሁሉም ሰው እና እናንተም ጭምር ሁለቱ ምን ያህል የሚቀናበት ትዳር እንዳላቸው ታምኑ አልነበር?” ብሎ ጆንሰን ጉድማንን አገኘሁህ በሚል ስሜት ተመለከተው፡፡
ኒኪም ማታ ላይ ስለ ባሏ በግልፅ ነግራዋለች፡፡ ስለ ባሏ የተናገረችበት
መንገድ ግን ሀዘን እና ንዴት የተቀላቀለበት እንደሆነም በወቅቱ ተረድቶ
ነበር። ያም ቢሆን ግን ስለ ባሏ ውሽማ ምንም አይነት ነገር እንዳልነገረችው
አስታወሰ። በተጨማሪ ደግሞ ኒኪን ያገባ ወንድ ምንጎድሎበት ነው ሌላ ውሽማ የሚይዘው? ዊሊ ባደን ቫለንቲና ስላረጀችበት ሊሆን ይችላል ሌላ
ወጣት ሴት የወሸመው፡፡ ስለዚህም ጆንሰን ሆን ብሎ ነገሩን እንደፈጠረ
ገመተ፡፡
“ይህንን አንተ እንዴት አወቅክ?” ብሎ በቁጣ ድምፅ ጠየቀው፡፡
“በኢንተርኔት ላይ ተገልፆ ነበር፡፡” ብሎ ጆንሰን መለስ እና በመቀጠልም
“ወዲያው አደጋው እንደደረሰ ሳይሆን ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ነው። ታዲያ ዜናው ላይ የተገለፀው:: ከዶክተር ዳግላስ አጠገብ አንዲት ሴት ብቻ
ነበረች ብሎ ነው የዘገበው፡፡ እኔ ግን የዶውግን እና የኒኪን የቅርብ ጓደኞቻቸውን አግኝቼ በመጠየቅ እውነቱን ለማረጋገጥ በቃሁ። ይሄንን አስቀያሚ ሚስጥሯንም ደብቃናለች። ይህ ሚስጥሯም ነው እንግዲህ ከፍተኛ
ንዴት ውስጥ የሚከታት...”
“እሺ ባሏ እንደፈለገ እየማገጠ ነበር እንበል። ታዲያ ይህ ነገር ከሁለቱ
ግድያዎች ጋር ምን ያገናኘዋል?” ብሎ ብሩዲ ጆንሰንን ጠየቀው፡፡
“ጌታዬ እኔ በዚህ ዙሪያ ስላሉ ነገሮች በትንሹም ቢሆን ምርመራዎቼን
ለማድረግ ሞክሬ ነበር። ከሁለት ቀናት በፊት ስለ አደጋው የተደረገውን
ሪፖርትንም ለማየት ሞክሬ ነበር። በዚህም ስለ ዶክተር ዳግላስ እና ስለ
ሩስያዊት ውሽማው ለማወቅ የበኩሌን ጥረት ሳደርግ ነበር።”
ይሄኔም ጉድማን ከተቀመጠበት ፍንጥር ብሎ ተነሳ እና “ይሄን ነገር እኮ
አልነገርከኝም!” ብሎ በመጮጮህ ተቃውሞውን አሰማ፡፡
እንዴ አንተ ሥራ በዝቶብህ ነበር እኮ ታስታውሳለህ?” ብሎ ጆንሰን መለሰለት እና “በዚያ ላይ ደግሞ አንተው ራስህ እንዳወራህልኝ ግልፅ አልነበርክም። ለማንኛውም አታስብ ስለ አደጋው የቀረበ ሪፖርት አንድም የተመዘገበ ነገር አላገኘሁም”
“ምን ማለትህ ነው?” ብሎ ነገሩ እንቆቅልሽ የሆነበት አዛዥ ብሩዲ
ጥያቄውን አቀረበ፡፡
“አዎን ሲስተሙ ላይ አደጋው የተመዘገበ አንድም ሪፖርት የለም ወይንም አደጋው ጨርሶ አልተመዘገበም ወይንም ደግሞ የተመዘገበውን የሆነ ሰው ሰርዞታል” ብሎ ሲናገር አዛዥ ብሩዲ በስልቸታ ፊት ሲያየው ጊዜ ጆንስን ማብራሪያውን ቀጠለ። “ወደ ነጥቤ እየመጣሁ ነው አንዴ ታገሱኝ።ይሄ ደግሞ ነገሩን ይበልጥ እንድመረምረው ምክንያት ሆነኝ። አደጋው እንደደረሰ እንኳን እኔ ማንም ሰው ያውቀዋል። አደጋው በየጋዜጦቹ ላይ
በጊዜው ሲፃፍ ነበር፡፡ በተለይ ደግሞ ኤል.ኤ.ታይምስ ዶክተር ዳግላስ ምን
ያህል ትሁት እና ጨዋ ሰው እንደሆነ፣ ባሏ የሞተባትንም ዶክተር ኒኪንም
ምን ያህል የተጎዳች ቆንጆ መልከ መልካም አድርጎ ነበር ሲፅፍላቸው
ማንኛውም ጋዜጣ ወይንም መፅሄት ግን አብራው ስለሞተችው ሩስያዊት
አልገለፁም፡፡ የሩስያዊቷ ጉዳይ የወጣው ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ነበር።
ለማንኛውም ዶክተር ግላስ ቴስላ መኪናዋን የገዛበትን የመኪና መሸጫ
ቦታን ፈልጌ አገኘሁት:: እዚያም ደርሼ ከአደጋው በኋላ የመኪናውን
የኮምፒውተር ሲስተም የመረመረውን ኢንጅነር አግኝቼው ነበር። እሱ
እንደነገረኝም ከአደጋው በፊት የመኪናው የኮምፒውተር ሲስተም ተበላሽቶ
ነበር።
“ተበላሽቶ ነበር ማለት?”
“በሪሞት ኮንትሮል ሀክ ተደርጎ ነበር” አለ እና ጆንሰን ማብራሪያውን በመቀጠልም “በነገሩ በጣም እርግጠኛ ባይሆንም የመኪናው የኮምፒውተር ሲስተም ኮድ ተዛብቶ ስለነበረ ይሄ የኮድ መዛባት ደግሞ መኪናው የሆነ ፍጥነት ካለፈ በኋላ የፍጥነትና እና የፍሬን ሲስተሙ ተናብበው እንዳይሰሩ እንደሚያደርጋቸው ገምቶ ነበር፡፡ ይህንን ነገርም በወቅቱ ለአለቃው አመልክቶ ነበር። አለቃውም ነገሩን ለፖሊስ ሪፖርት እንዲያደርግም
አሳስቦት ነበር”
“እናስ ጉዳዩን ለፖሊስ አመለከተ አለቃው?” ብሩዲ ጠየቀ፡፡
“ቅድም እንደነገርኳችሁ ስለ አደጋው ሪፖርት የተመዘገበ ነገር የለም::
ስለዚህ የኢንጅነሩ አለቃ ጉዳዩን ለፖሊስ ያመልክት አያመልክት ለማወቅ አልቻልኩም፡፡ የኢንጅነር ዴመን አለቃም ባለፈው ፋሲካ በልብ በሽታ ህይወቱ አልፏል” አላቸው
ጆንስን ይህንን ከተናገረ በኋላ ጉድማን እና የፖሊስ አዛዥ ብሩዲ
👍3
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....ቱሉ ሀጤ የተከናነበችውን የጨለማ ካባ አውልቃ ወደዚያ ለመጣል
በመሽኮርመም ላይ ትገኛለች። ጨለማው ብርታቱን ለማሳየት በሚያቅራራበት፣ ንጋትም ብርሃንን ካልፈነጠቅሁ እያለ በሚንጠራራበት በዚያ ውድቅት ለሊት እንቅልፍ በአይኑ አልዞርልህ ያለው ሰው አንዴ በቀኝ ጎኑ አንዴ ደግሞ በግራ ጎኑ እየተገላበጠ ምሽትና ንጋት የበላይነታት
ውን ለማረጋገጥ በገጠሙት የጦርነት አውድማ ላይ ትጥቅ ይዞ ሳይዋጋ
ጉዳት የደረስበት ቁስለኛ ሆኖ ያለዕረፍት ያቃስታል። ድቅድቁ ጨለማ ከዋጣት መንደር የበለጠ የጨለመበት ሙሉ ዳፍንት ሌሊት ሆኖበት ያደረውና ከሚስቱ ፀባይ መለዋወጥ ጋር ሰሞኑን ከህሊናው ጋር ጦርነት ገጥሞ የሰነበተው ገበየው ቱሉ ሃጤ ለበለችውጨለማ በከፋ ሁኔታ
ጨልሞበት ዙሪያው ገደል ሆኖበት በሃሳብና በጭንቀት መወራጨቱን ቀጥሏል...
ባክዎ እማማ ዓለም ፀባይዋን ለምን እንደለወጠችብኝ ይጠይቁልኝ፡፡ ሳላውቀው አስቀይሜአት ከሆነ ይቅርታ ታድርግልኝ፡፡ በድያት ከሆነ እክሳለሁ እንጂ የድሮዋ ዓለሚቱ አልሆነችልኝም” ብሎ ለአማቹ ስሞታ ነግሮ ነበር።
የዓለሚቱ እናት ልጃቸውን በጣም ስለሚወዷትና ስለሚፈሯትም ጭምር
ጣጣውን በልባቸው እያወቁት “እስቲ ቀስ ብለን እንጠይቃታለን ካጠፋች
እናስመክራታለን ጥፋቱ ያንተ ከሆነ ደግሞ ጥፋትህን እንድታርም ሽማግሌ
ፊት እናወቃቅሳችኋለን እስከዚያው ድረስ ታገሳት” ሲሉ ተስፋ ስጥተውት ነበረ፡፡ እሱም ያንን የተስፋ ቃል ስንቆ ሽማግሌ ተሰብስቦ አንተ አጥፍተሀል አንቺ አጥፍተሻል እየተባባሉ የሚወቃቀሱበትን ቀን በናፍቆት እየተጠባበቀ ነው። ዓለሚቱ ግን እየባሰባት እንጂ እየበረደች ልትሄድ
አልቻለችም፡፡ በተለይ የዛሬው ሁኔታዋ ከወትሮው በተለዬ ሁኔታ እጅግ
አስፈሪ ሆነበት።ያ የሚለሰልሰው ገላዋ እንደ አባጨጓሬ ኮሰኮሰው። ጀርባዋን አዞረችበት። ሊዳብሳት ሲፈልጋት ሽሽችው። እጁን ሲዘረጋ አመናጨቀችው። ኤጭ!.. በልቡ ብዙ ነገር ተመኘ፡፡ “ምን አባቱ ለየትኛው ኑሮ ነው? ብርር ብዬ ብጠፋስ? ዐይኔን ማየት ካስጠላት እስከ መጨረሻው ከዐይኗ ብርቅላትስ?” ዝም ብሎ ወደማያውቀው አገር ቢሄድ ዓለሚቱን ሸሽቶ ከአድማስ እስከ አድማስ ቢጓዝ ከዚያም ናፍቆቱ አንገብግቧት
ጥፋተኛነቷ ተሰምቷት እንደ ድሮው “ገበየሁዬ” እያለች እሱን ለማግኘት
እግሯ እስከሚነቃ ድረስ ፍለጋ ብትጓዝ ተመኘ፡፡ አገሩን ጥሉ መንኖ ገዳም ቢገባ፣ የቤተክርስቲያን አገልጋይ ባህታዊ ሆኖ ጢሙን አሳድጎ ስለ ነፍሱ እንጂ ስለ ስጋው የማይጨነቅ መነኩሴ ሆኖ መኖርን ተመኘ፡፡
በዚች በማትጠገብና ነገር ግን በማትጣፍጥ ዓለም ውስጥ ምሬቷን እየተጎነጨ ከመኖር ይልቅ ምናኔን መረጠ፡፡ ግማሽ አካሉ፣ የመኖሩ አለኝታ
ጣፋጫ ዓለሚቱ ጀርባዋን ከሰጠችው ገሀዷ ዓለምም አልፈለገችውምና
ገሀዷ አለም ጠላት፡፡ በእርሻ ሲተዳደር ድካሙ ልፋቱ ሁሉ በዓለሚቱ
ፍቅር ይካካስለት ነበር፡፡ አሁን ግን እሷም ይኸውና ጀርባዋን ሰጥታዋለች፡፡ ለወትሮው ዓለምዬ እባክሽ ትንሽ ይንጋ አትነሺ ትንሽ እንቆይ?"እያላ ከእቅፉ ውስጥ እንዳትወጣ ጭምቅ አድርጎ ሲይዛት እሷም ከጉያው ውስጥ ላለመውጣት በልቧ እየተመኘች የውሽቷን ስትታገለው ለሊቱ ይነጋና ምቀኛው ዶሮ ኩኩሉ!” ኸረ እባካችሁ ነግቷል!” ሲል ያሳብቃል። ከዚያም እሷ ቀድማ ትነሳና ቤቱን ታጫጭስበታለች። ከብቶቹን ለግጦሽ ከማሰማራቱ በፊት ሻይ ታፈላለትና “እስኪ ሞቅ ያድርግህ ገበየሁዬ?” ትለዋለች። ይቺ ለሱ ማር የነበረች ዓለሚቱ፣የሱ አሳቢ ተንከባካቢ የነበረች ዓለሚቱ ፊቷ እንደ ሀምሌ ክረምት መክበድ፣ ሙቅ ሰውነቷ
እንደ በረዶ መቀዝቀዘ ከጀመረና ንግግሯ እንደ ሬት እየመረረ መምጣት ከጀመረ ውሎ አደረ። ሁሉንም መታገሴ ጥፋተኛነቴን ያመንኩ ያስመስልብኛል በማለት ትንሽ ለመቆጣት የሞከረ ቀን ፀቡ ይበልጥ እየተካረረ ይሄዳል። ከዚያም ይደነግጥና ተመልሶ ልምምጡን ይቀጥላል። አንዳንድ ጊዜ ንዴቱ ከኣቅሙ በላይ ይሆንበትና ብድግ ብሎ ቤቱን ጥሎላት ሊጠፋ ይከጅለዋል፡፡ በዚህ ጊዜ ደግሞ እነኝያ በግራና በቀኝ ከበውት ለሀጫቸውን የሚያዝረከርኩበት፣እነኝያ ልቡ ሊጋልብ ሲነሳ ልጓም የሚሆኑበት፣ እነኝያ ልቡ ሲቃጠል ውሃ የሚያፈሱበት ህፃናት ልጆቹ ትውስ ይሉትና ጥሏቸው ለመጥፋት በማሰቡ ራሱን ይወቅሳል።
የዛሬን አያድርገውና ያኔ እንደዚህ እንደ አሁኑ ከሁለትነት ወደ አራትነት ከመሸጋገራቸው በፊት“ዓለምዬ ፍቅራችን እጥፍ ድርብ የሚሆንበት ጊዜ መቼ
ነው?” ብሎ ሲጠይቃት ከፍተኛ የልጅ ጉጉትና ምኞት እንዳለው የምታውቀው ዓለሚቱ በስርጉድ ጉንጮቿ ሳቅ ትልለትና ያበጠ ሆዷን በጣቷ እየጠቆመችው “የማሙሽዬ ወይንም የማሚቱ እናት ስሆን።አንተም የአባትነት ወግ ማዕረግ ሲደርስህ አይደል ገበየሁ?” ትልና ጉንጩን ከንፈሩን ሳም ስታደርገው ደስታ ልቡን ይሞላውና ደግሞ እንደገና አንጠጋ
ገብ ብለው ተቃቅፈው ሲተሻሹ ሲላላሱ በልቧ ማህደር ውስጥ የተደበቀውን የፍቅር ሚስጢር ከዐይኖቿ ውስጥ እንደሚያነብባት ሁሉ ዐይን ዐይኖቿን በፍቅር ትኩር ብሎ ሲመለከታት እንደማፈር ትልና አንገቱ ስር ሽጉጥ ስትልበት ከዚያም ስሜታቸው በእጥፍ ይንርና እንደ ስስት እንጀራ እርስ በርስ መሻማት ሲጀምሩ ይሄ ሁሉ በወረት እንደ ባህር ዛፍ ቅጠል ቦግ ብሎ ወዲያውኑ ድርግም ብሎ የጠፋ ሳይሆን ሰባት ዓመት ሙሉ አብሮአቸው የዘለቀ ነበር፡፡ አሁን ግን ይሄ ሁሉ እንዳልነበረ ሆኖ ከጥቂት ወራት ወዲህ የዓለሚቱ ሙሉ ለሙሉ መለወጥ አእምሮውን ሲበጠብጠው ከረመ፡፡ አለሚቱ ግን ይሄ ሁሉ ገበየሁ የሚታወሰው ትዝታ አንድ
እንኳ ለምልክት ሳይተርፍ ከአእምሮዋ ሙሉ በሙሉ ጠፍቶ የሠራ አካላቷን እንደ ሻማ ለሚያቀልጣት፣ በፍቅር ለተረታችለት፣ ቁመናው ቀጥ ያለ ሽመል ለሚመስለውና በአለንጋ መሳይ ጣቶቹ ሁለመናዋን እያሻሽ ነፍሷን ለሚያስደስትላት ለጎንቻ ፍቅር ስትል የገበየሁ ህይወት ኢምንት ሆኖ ታያት። በተለይ ደግሞ ከጥቂት ጊዜ በኋላ አጠገቧ የተኛው ሰው ቀዝቃዛ በድን እንደሚሆን እየታወቃት እየፈራችው ሰውነቷን ሲነካት እየተሸማቀቀች ከምንጊዜውም በከፋ ሁኔታ ተጠየፈችው። ሸሸችው።ገበየሁ የሆዱን በሆዱ ችሎ የለሊት አዳሩ እየደነቀው ጋቢውን ከላይ ደረበና ቀስ ብሎ ተነሳ፡፡ ዓለሚቱን የያዛት እንቅልፍ የውሽት መሆኑን ሳያውቅ እንዳይቀሰቅሳት ተጠንቅቆ ከአልጋው ላይ ወረደና እንደወትሮው ከብቶቹ ከመታለባቸው በፊት ትንሽ ሳር እንዲግጡ በለሊቱ በረቱን ከፍቶ ይዟቸው ወጣ....
ሰው ከእናቱ ማህፀን ሲወለድ ተረግዞ፣
በሞት ጎዳና ላይ ይጀምራል ጉዞ፡፡
ፊት ለፊት እያየው ትልቁን አደጋ፣
ልቡ ሲያፈገፍግ ዕድሜው ግን ሲጠጋ፣
ሲያውቀው በመሞቱ በጣም ይጨነቃል፣
መሸሻ በማጣት ቆሞ ይጠብቃል፣
የእግዚአብሔርን ፀጋ!
በዕድሜ ባለፀጋነት በማይቀረው የሞት ጎዳና ላይ መጓዝ የተፈጥሮ ህግ ነው። ነገር ግን ወደ ህይወት ጎዳና ለመጓዝ የህይወትን ውጣ ውረድ ፈተና ለማለፍ በሚደረግ ትንቅንቅ ውስጥ ባልተጠበቀ ጊዜ በተለይም እንደ ገበየሁ ላለ ልጆቹን ስሞ ላልጠገበ ሰው ሞት እጅግ አስደንጋጭ ነው። ገበየሁ ከዛሬ ነገ የሚስቱ ፀባይ ተሻሽሉ የሻከረው ልቧ ለስልሶ እርቀ ሰላም በመካከላቸው ወርዶ ትዳሩ ሰምሮ ልጆቻቸውን በፍቅር
የሚያሳድጉበትን ቀን ሲናፍቅ በዚያኛው ወገን ደግሞ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ይቺን ዓለም እንዲስናበታት የማድረግ እቅድ ወጥቶ ዝግጅቱ ተጠናቆ ወደተግባር የሚሽጋገርበት የሞት ድግስ ተደግሶለታል። እሱ በተበደለ እሱ ከነልጆቹ በተሰቃየ እሱ ፍቅሩን በተነጠቀ ጎንቻና አለሚቱ የሞት ፍርድ ከፈረዱበት ስንብተዋል። በዚሁ መሰረት ጎንቻ ሲዘጋጅ
ሾተሉን ሲሞርድ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....ቱሉ ሀጤ የተከናነበችውን የጨለማ ካባ አውልቃ ወደዚያ ለመጣል
በመሽኮርመም ላይ ትገኛለች። ጨለማው ብርታቱን ለማሳየት በሚያቅራራበት፣ ንጋትም ብርሃንን ካልፈነጠቅሁ እያለ በሚንጠራራበት በዚያ ውድቅት ለሊት እንቅልፍ በአይኑ አልዞርልህ ያለው ሰው አንዴ በቀኝ ጎኑ አንዴ ደግሞ በግራ ጎኑ እየተገላበጠ ምሽትና ንጋት የበላይነታት
ውን ለማረጋገጥ በገጠሙት የጦርነት አውድማ ላይ ትጥቅ ይዞ ሳይዋጋ
ጉዳት የደረስበት ቁስለኛ ሆኖ ያለዕረፍት ያቃስታል። ድቅድቁ ጨለማ ከዋጣት መንደር የበለጠ የጨለመበት ሙሉ ዳፍንት ሌሊት ሆኖበት ያደረውና ከሚስቱ ፀባይ መለዋወጥ ጋር ሰሞኑን ከህሊናው ጋር ጦርነት ገጥሞ የሰነበተው ገበየው ቱሉ ሃጤ ለበለችውጨለማ በከፋ ሁኔታ
ጨልሞበት ዙሪያው ገደል ሆኖበት በሃሳብና በጭንቀት መወራጨቱን ቀጥሏል...
ባክዎ እማማ ዓለም ፀባይዋን ለምን እንደለወጠችብኝ ይጠይቁልኝ፡፡ ሳላውቀው አስቀይሜአት ከሆነ ይቅርታ ታድርግልኝ፡፡ በድያት ከሆነ እክሳለሁ እንጂ የድሮዋ ዓለሚቱ አልሆነችልኝም” ብሎ ለአማቹ ስሞታ ነግሮ ነበር።
የዓለሚቱ እናት ልጃቸውን በጣም ስለሚወዷትና ስለሚፈሯትም ጭምር
ጣጣውን በልባቸው እያወቁት “እስቲ ቀስ ብለን እንጠይቃታለን ካጠፋች
እናስመክራታለን ጥፋቱ ያንተ ከሆነ ደግሞ ጥፋትህን እንድታርም ሽማግሌ
ፊት እናወቃቅሳችኋለን እስከዚያው ድረስ ታገሳት” ሲሉ ተስፋ ስጥተውት ነበረ፡፡ እሱም ያንን የተስፋ ቃል ስንቆ ሽማግሌ ተሰብስቦ አንተ አጥፍተሀል አንቺ አጥፍተሻል እየተባባሉ የሚወቃቀሱበትን ቀን በናፍቆት እየተጠባበቀ ነው። ዓለሚቱ ግን እየባሰባት እንጂ እየበረደች ልትሄድ
አልቻለችም፡፡ በተለይ የዛሬው ሁኔታዋ ከወትሮው በተለዬ ሁኔታ እጅግ
አስፈሪ ሆነበት።ያ የሚለሰልሰው ገላዋ እንደ አባጨጓሬ ኮሰኮሰው። ጀርባዋን አዞረችበት። ሊዳብሳት ሲፈልጋት ሽሽችው። እጁን ሲዘረጋ አመናጨቀችው። ኤጭ!.. በልቡ ብዙ ነገር ተመኘ፡፡ “ምን አባቱ ለየትኛው ኑሮ ነው? ብርር ብዬ ብጠፋስ? ዐይኔን ማየት ካስጠላት እስከ መጨረሻው ከዐይኗ ብርቅላትስ?” ዝም ብሎ ወደማያውቀው አገር ቢሄድ ዓለሚቱን ሸሽቶ ከአድማስ እስከ አድማስ ቢጓዝ ከዚያም ናፍቆቱ አንገብግቧት
ጥፋተኛነቷ ተሰምቷት እንደ ድሮው “ገበየሁዬ” እያለች እሱን ለማግኘት
እግሯ እስከሚነቃ ድረስ ፍለጋ ብትጓዝ ተመኘ፡፡ አገሩን ጥሉ መንኖ ገዳም ቢገባ፣ የቤተክርስቲያን አገልጋይ ባህታዊ ሆኖ ጢሙን አሳድጎ ስለ ነፍሱ እንጂ ስለ ስጋው የማይጨነቅ መነኩሴ ሆኖ መኖርን ተመኘ፡፡
በዚች በማትጠገብና ነገር ግን በማትጣፍጥ ዓለም ውስጥ ምሬቷን እየተጎነጨ ከመኖር ይልቅ ምናኔን መረጠ፡፡ ግማሽ አካሉ፣ የመኖሩ አለኝታ
ጣፋጫ ዓለሚቱ ጀርባዋን ከሰጠችው ገሀዷ ዓለምም አልፈለገችውምና
ገሀዷ አለም ጠላት፡፡ በእርሻ ሲተዳደር ድካሙ ልፋቱ ሁሉ በዓለሚቱ
ፍቅር ይካካስለት ነበር፡፡ አሁን ግን እሷም ይኸውና ጀርባዋን ሰጥታዋለች፡፡ ለወትሮው ዓለምዬ እባክሽ ትንሽ ይንጋ አትነሺ ትንሽ እንቆይ?"እያላ ከእቅፉ ውስጥ እንዳትወጣ ጭምቅ አድርጎ ሲይዛት እሷም ከጉያው ውስጥ ላለመውጣት በልቧ እየተመኘች የውሽቷን ስትታገለው ለሊቱ ይነጋና ምቀኛው ዶሮ ኩኩሉ!” ኸረ እባካችሁ ነግቷል!” ሲል ያሳብቃል። ከዚያም እሷ ቀድማ ትነሳና ቤቱን ታጫጭስበታለች። ከብቶቹን ለግጦሽ ከማሰማራቱ በፊት ሻይ ታፈላለትና “እስኪ ሞቅ ያድርግህ ገበየሁዬ?” ትለዋለች። ይቺ ለሱ ማር የነበረች ዓለሚቱ፣የሱ አሳቢ ተንከባካቢ የነበረች ዓለሚቱ ፊቷ እንደ ሀምሌ ክረምት መክበድ፣ ሙቅ ሰውነቷ
እንደ በረዶ መቀዝቀዘ ከጀመረና ንግግሯ እንደ ሬት እየመረረ መምጣት ከጀመረ ውሎ አደረ። ሁሉንም መታገሴ ጥፋተኛነቴን ያመንኩ ያስመስልብኛል በማለት ትንሽ ለመቆጣት የሞከረ ቀን ፀቡ ይበልጥ እየተካረረ ይሄዳል። ከዚያም ይደነግጥና ተመልሶ ልምምጡን ይቀጥላል። አንዳንድ ጊዜ ንዴቱ ከኣቅሙ በላይ ይሆንበትና ብድግ ብሎ ቤቱን ጥሎላት ሊጠፋ ይከጅለዋል፡፡ በዚህ ጊዜ ደግሞ እነኝያ በግራና በቀኝ ከበውት ለሀጫቸውን የሚያዝረከርኩበት፣እነኝያ ልቡ ሊጋልብ ሲነሳ ልጓም የሚሆኑበት፣ እነኝያ ልቡ ሲቃጠል ውሃ የሚያፈሱበት ህፃናት ልጆቹ ትውስ ይሉትና ጥሏቸው ለመጥፋት በማሰቡ ራሱን ይወቅሳል።
የዛሬን አያድርገውና ያኔ እንደዚህ እንደ አሁኑ ከሁለትነት ወደ አራትነት ከመሸጋገራቸው በፊት“ዓለምዬ ፍቅራችን እጥፍ ድርብ የሚሆንበት ጊዜ መቼ
ነው?” ብሎ ሲጠይቃት ከፍተኛ የልጅ ጉጉትና ምኞት እንዳለው የምታውቀው ዓለሚቱ በስርጉድ ጉንጮቿ ሳቅ ትልለትና ያበጠ ሆዷን በጣቷ እየጠቆመችው “የማሙሽዬ ወይንም የማሚቱ እናት ስሆን።አንተም የአባትነት ወግ ማዕረግ ሲደርስህ አይደል ገበየሁ?” ትልና ጉንጩን ከንፈሩን ሳም ስታደርገው ደስታ ልቡን ይሞላውና ደግሞ እንደገና አንጠጋ
ገብ ብለው ተቃቅፈው ሲተሻሹ ሲላላሱ በልቧ ማህደር ውስጥ የተደበቀውን የፍቅር ሚስጢር ከዐይኖቿ ውስጥ እንደሚያነብባት ሁሉ ዐይን ዐይኖቿን በፍቅር ትኩር ብሎ ሲመለከታት እንደማፈር ትልና አንገቱ ስር ሽጉጥ ስትልበት ከዚያም ስሜታቸው በእጥፍ ይንርና እንደ ስስት እንጀራ እርስ በርስ መሻማት ሲጀምሩ ይሄ ሁሉ በወረት እንደ ባህር ዛፍ ቅጠል ቦግ ብሎ ወዲያውኑ ድርግም ብሎ የጠፋ ሳይሆን ሰባት ዓመት ሙሉ አብሮአቸው የዘለቀ ነበር፡፡ አሁን ግን ይሄ ሁሉ እንዳልነበረ ሆኖ ከጥቂት ወራት ወዲህ የዓለሚቱ ሙሉ ለሙሉ መለወጥ አእምሮውን ሲበጠብጠው ከረመ፡፡ አለሚቱ ግን ይሄ ሁሉ ገበየሁ የሚታወሰው ትዝታ አንድ
እንኳ ለምልክት ሳይተርፍ ከአእምሮዋ ሙሉ በሙሉ ጠፍቶ የሠራ አካላቷን እንደ ሻማ ለሚያቀልጣት፣ በፍቅር ለተረታችለት፣ ቁመናው ቀጥ ያለ ሽመል ለሚመስለውና በአለንጋ መሳይ ጣቶቹ ሁለመናዋን እያሻሽ ነፍሷን ለሚያስደስትላት ለጎንቻ ፍቅር ስትል የገበየሁ ህይወት ኢምንት ሆኖ ታያት። በተለይ ደግሞ ከጥቂት ጊዜ በኋላ አጠገቧ የተኛው ሰው ቀዝቃዛ በድን እንደሚሆን እየታወቃት እየፈራችው ሰውነቷን ሲነካት እየተሸማቀቀች ከምንጊዜውም በከፋ ሁኔታ ተጠየፈችው። ሸሸችው።ገበየሁ የሆዱን በሆዱ ችሎ የለሊት አዳሩ እየደነቀው ጋቢውን ከላይ ደረበና ቀስ ብሎ ተነሳ፡፡ ዓለሚቱን የያዛት እንቅልፍ የውሽት መሆኑን ሳያውቅ እንዳይቀሰቅሳት ተጠንቅቆ ከአልጋው ላይ ወረደና እንደወትሮው ከብቶቹ ከመታለባቸው በፊት ትንሽ ሳር እንዲግጡ በለሊቱ በረቱን ከፍቶ ይዟቸው ወጣ....
ሰው ከእናቱ ማህፀን ሲወለድ ተረግዞ፣
በሞት ጎዳና ላይ ይጀምራል ጉዞ፡፡
ፊት ለፊት እያየው ትልቁን አደጋ፣
ልቡ ሲያፈገፍግ ዕድሜው ግን ሲጠጋ፣
ሲያውቀው በመሞቱ በጣም ይጨነቃል፣
መሸሻ በማጣት ቆሞ ይጠብቃል፣
የእግዚአብሔርን ፀጋ!
በዕድሜ ባለፀጋነት በማይቀረው የሞት ጎዳና ላይ መጓዝ የተፈጥሮ ህግ ነው። ነገር ግን ወደ ህይወት ጎዳና ለመጓዝ የህይወትን ውጣ ውረድ ፈተና ለማለፍ በሚደረግ ትንቅንቅ ውስጥ ባልተጠበቀ ጊዜ በተለይም እንደ ገበየሁ ላለ ልጆቹን ስሞ ላልጠገበ ሰው ሞት እጅግ አስደንጋጭ ነው። ገበየሁ ከዛሬ ነገ የሚስቱ ፀባይ ተሻሽሉ የሻከረው ልቧ ለስልሶ እርቀ ሰላም በመካከላቸው ወርዶ ትዳሩ ሰምሮ ልጆቻቸውን በፍቅር
የሚያሳድጉበትን ቀን ሲናፍቅ በዚያኛው ወገን ደግሞ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ይቺን ዓለም እንዲስናበታት የማድረግ እቅድ ወጥቶ ዝግጅቱ ተጠናቆ ወደተግባር የሚሽጋገርበት የሞት ድግስ ተደግሶለታል። እሱ በተበደለ እሱ ከነልጆቹ በተሰቃየ እሱ ፍቅሩን በተነጠቀ ጎንቻና አለሚቱ የሞት ፍርድ ከፈረዱበት ስንብተዋል። በዚሁ መሰረት ጎንቻ ሲዘጋጅ
ሾተሉን ሲሞርድ
#ያልታበሱ_እንባዎች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...«ምነው ሔዩ በር ላይ ቆምሽ?» ሲል ጠየቃት።
«ብዙ ስለቆየሁ ወደ ቤቴ ልሄድ ተነስቼ ነው፡፡ አለችው በእጆቿ ደረቱን እየደባበሰችና ቀና ብላ ዓይኖቹን በዓይኖቿ እየተመለከተች፡፡
«ለሔዩ ምን አደረግሽላት ትርፌ?» አለ እስቻለው ወደ ትርፌ ዞር ብሎ፡፡
«ምንም ጋሼ አስቻለው፤ ወሬ ብቻ»
«ምሳ በልተሽ ሂጂያ ሔዩ!!»
«በፍጹም አስቹ! እት አበባ ስራ መምጫዋ ስለሆነ ብሄድ ይሻላል»
«ስሞት»
«አይሆንም አስቹ በአጋጣሚ መገኛኘታችን በራሱ በቂ ነው፡፡»
አስቻለው አሁንም ከንፈሮቿን ሳም ካደረገ በኃላ «በይ እሺ ከቸኮልሽ»
ሂጂ አለና እስከ ውጭ በር ሸኝቶ ተሰናብቷት ወደ ቤቱ ተመልሶ ገባ፡፡
አልጋው ላይ ቁጭ አለና ያነ በእጁ ይዞት የነበረውን ካኪ ፖስታ በጥድፊያ ይከፍት ጀመር፡፡ ከአሜሪካ ካሊፎርኒያ ግዛት ከዶክተር ደጀኔ አድማሱ የተላክለት ደብዳቤ ነው። አስቻለው ጫማውን አውልቆ አልጋው ላይ ወጣና ትራሶቹን አነባብሮ ከአንገቱ ቀና ብሎ በጀርባው ጋለል በማለት ደብዳቤውን ማንበብ ጀመረ።
«የምወድህና የማከብርህ እንዲሁም የምናፍቅህ ውድ ወንድሜ ነርስ አስቻለው ፍስሃ፥ ከቶ ለጤናህ እንደምን አለህ? ፈጣሪ አምላክ ይመስገን እኔ በጣም ደህና ነኝ።
«የምወድህ አስቻለው፡ የመኪና አደጋ ደርሶብህ እንደነበር አውቃለሁ፡፡ አደጋው ቀደረሰ
በሶስተኛ ቀን በተኛህበት ሆስፒታል ተገኝቼ ልጠይቅህም ሞክሪ ነበር። በወቅቱ ራስህን አታውቅም ነበርና፡ እኔ ደግሞ የበረራ ፕርግራሜ በማግስቱ
ስለነበር ሆዴ እያዘነ ትቼህ ሄጃለሁ። ይሁንና የኢትዮጵያ አየር ክልል ወጥቼ፣ በሱዳንና በግብጽ እንዲሁም በሜድትራኒያን ባህር፡ ከዚያም በአውሮጳ ሰማይ ላይ
ተንሳፍፌ በበረራ ላይ በነበርኩበት ጊዜ ሁሉ ስለ አንተ እያለቀስኩ ነበር፡፡ አሜሪካም ከገባሁ በኋላ የአንተ ነገር ከእዕምርዩ አልወጣ ብሎኝ ለቀናት ያህል ተሰቃይቻለሁ። የኋላ ኋላ ግን ከአደጋው ሙሉ በሙሉ አገግመህ ወደ ስራህ የመመለስህን ዜና
ስስማ አምላኬን ከልብ አመስግኛለሁ። ወደፊትም ፈጣሪህ ከሁሉም ነገር
እንዲጠብቅህ እፀልያለሁ።
«ውድ ወንድሜ አስቻለሁ። መቸም ደብዳቤዬ እንደ ደረሰህ መጀመሪያ የሚታሰብህ ምን ዓይነት ኑሮ እየኖርኩ ስለመሆኔ የምገልጽልህ ነገር ይመስለኛል።
መሰደዴ የመከፋት ውጤት ነውና አሜሪካ ውስጥ ምን ያሆሎ እንደደላኝ ወይም እንዳልደላኝ ለማውቅ ትጓጓ ይሆናል። በኔ በኩል 'ደላኝ' ወይም 'ከፋኝ'ብዬ
ልነግርህ አልፈልግም፡፡ አኗኗሬን ልግለጽልህና ምደባውን ራስህ ፈርጀው፡፡
«የአሜሪካ ውስጥ በእየዕለቱ ያገኘሁትን ሁሉ ስሰራ እውላለሁ። ስራዬን ሳጠናቅቅ ለስራው የተመደበው ገንዘብ በሙሉ ይከፈለኛል። ዛሬ አንዱ ጋር ስስራ
ውዩ ነገ ወደ ሌላው ብሄድ መልቂያ አልጠየቅም፡፡ በስራ ዘመቻ ሰበብ የጉልበቴን
ዋጋ ማንም አይነጥቀኝም፡፡ በስላም ስሰራ ውዬ የሰላም እንቅልፍ እተኛለሁ። «እገሌ
ስለኔ ምን ይላል? ነገ ምን ያደርገኝ ወይም ያስደርገኝ ይሆን? ብዬ አልጨነቅም፡፡
በሰራሁት መጠን ትክክለኛ ክፍያ ስለምቀበል የገንዘብ ችግር አይገባኝም። የልደታ ዕለት ደሞዝ ወስጄ እስከ ቀጣዩ ልደታ ቀቃኝ አልበቃኝ ብዬ ስጨነቅ አልሰነብትም፡፡
እለታዊ አዋዋሌና የሆዴ ነገር ይህን ይመስላል፡፡ የመንፈስህስ ነገር ካልከኝ ግን ጣጣው ብዙ ነው። በመሰረቱ ማንም ሰው በሀገሩ ውስጥ ተከፍቶ በተሰደደበት አገር ደስ ይለዋል ማለት ዘበት ነው ምናልባት 'ከመሞት መሰንበት' ለሚለው
የሃገራችን ብሂል ምላሽ ይሆን እንደሆን እንጂ። ስደት ደግሞ
የመንፈስ ርሃብ ውጤት ነው።
መንፈሱ የተራበ ሰው የቱንም ያህል የጣፈጠና የበዛ ምግበ ቢበላ ሁልጌዜም ውስጡ ባዶ ነው እኔም እንዲሁ ባዶዬን እኖራለሁ።
«አሜሪካ ደግሞ የጭፍን ፖለቲካል ሰለባ ሆነውለተሰደዱባት ሁሉ የባሰ የመንፈስ ረሃብ የምትለቅ ሃገር ነች፡፡ የዚች ደብዳቢየም ዋንኛ ይዘት በዚሁ ዙሪያ የሚያጠነጥን ነውና በፅሞና አንብብልኝ። በዚያው ውስጤንም ትረዳዋለህ።
«አየህ አስቻለው አሜሪካኖች ወደ ስልጣን ሲወጡ መንገዳቸው በህዝብ መሀል ነው። ለስልጣን የሚደረግ ትልቅ ጦርነት አለ። መሳሪያው ግን መድፍና
መትረየስ አይደለም የጠራና የነጠረ ሀሳብ' በሩቅ የሚታይ ራዕይ ከራእዕዩ ጫፍ
የሚደርስ የፖለቲካ አመለካከትና አሰራር ቅደም ተከተል ወይም ፕሮግራዎ" እንጂ።ባሩዳቸው የሰላ ምላስና ርቱዕ አንደበት ነው የጦርነቱ ቦታ ክብ ጠረጴዛ ነው።
የውጊያ ወረዳዎች እልፍ አእላፍን የሚይዙ ሰፋፊ አዳራሾች ናቸው
በዚህ የትግል ሜዳ አሸንፎ ስልጣን ላይ የወጣ ሁሉ ስራውን የሚያከናውነው በሕዝብ
ይሁንታ በፀደቀ ህገ መንግስት መሰረት ነው። ማንም የስልጣን ክልሉን አልፎ ሲገኝ ያለቀጠሮ በሕዝብ ጩህት ስልጣን ይለቃል
ስለሆነም አሜሪካ ባለስልጣን
ሕዝብን ፈርቶ የሚኖርባት እንጂ ሕዝብ ባለ ስልጣንን እየፈራ የሚኖርባት ሀገር አይደለችም።
እንዴት ደ.....ስ የምትል አገር መሰለችህ!!
«የምወድህ አስቻለው፡- እዚህ አሜሪካ ውስጥ ባገኘሁት ብርሃን የሀገሪን ጨለማ አሻግሬ ሳየው አቤት ማስፈራራቱ! አቤት ማስጠላቱ! አቤት ማስጨነቁ!
የመንፈስ ርሀብ የሚለቅብኝም ይህ ሁኔታ ነው። በእውነት ያንቀጠቅጣል! በእውነት ይዘገንናል! በእውነት ያንገፈግፋል! የዚህ ሁሉ ድምር ውጤት እንቅልፍ እያሳጣ እኔንም ሁል ጊዜ ያስለቅሰኛል።
የሀገራችን አምባገነኖች ከየትም ይነሱ፤ በየትም ይምጡ፣ መቸም
ይድረሱ፥ ነገር ግን አንድ የጋራ መለያ ባህሪ አላቸው፤ ይህም በፊትለፊት በህዝባቸው ስም እየማሉ በስውር ግን የገዛ ሕዝባቸውን በጠላትነት የመፈረጅ
መስሪነታቸው ነው። መሠረታዊ ምክንያቱ ደግሞ ስልጣን ላይ የሚወጡት በሀይል እንጂ የህዝብ ይሁንታ አግኝተው ስላልሆነ ነው፡፡ ግን ደግሞ ስልጣኑን ይፈልጉታል። በድሀ ሀገር ስልጣን የሀብት ምንጭ ነውና ከያዙትም በኋላ ሙጭኝ ይሉበታል። ይቆዩበት ዘንድ ጠላታችን የሚሉትን ሕዝብ ያተረማምሱታል።ቢያንስ በሁለት እንዳንዴም ከዚያ በላይ በሆነ አመዳደብ ይከፋፍሉታል። አንዱን
ወገን ወዳጅ አድርገው ሌላውን በጠላትነት ይፈርጁታል። የጠሉትን ወገን የተለያየ
ስም እየለጠፉ ይበልጥ እንዲጠላ አውርተው ያስወሩበታል። በዚህም የጠላታቸውን እርስ በእርስ ጠላትነት ይፈጥራሉ፡፡ ሕዝብና ሕገብ የጎሪጥ እንዲተያይ ያደርጉና
ጥላቻና ጥርጣሬን ያነግሱበታል። በዚህ ጊዜ የራሳቸውን የስልጣን ኮርቻ ያደላድላሉ፣ የችሎታ ሳይሆን የብልጠት አካሄድ
በመነዘረቱ የግጭቶች ሁሉ! የጦርነቶች ሁሉ፣የቅራኔዎች ሁሉ
መሠረታዊ ምክንያት ኢኮኖሚ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ጥቅም!! ፖለቲካ የሚባላው ነገር የዚሁ ፍላጎት ልጣጭ ነው። በተላይ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ድሀ አገሮች አምባገነኖች ከስልጣን ላይ የሚወጡት ይህንኑ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለመቆጣጠር ነው።ሁሉን ነገር በመዳፋቸው ውስጥ ማስገባት የአምባገነኖች ልዩ ባህሪ ነውና፡፡
በዚህ አያበቁም፡ የስልጣን ጊዜያቸው እስከ መቼ ድረስ መሆኑን በውል ስለማያቁት 'ክፉ ቀን' ቢመጣ እያሉ በተለያየ መንገድ መዘጋጀት ይጀምራሉ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...«ምነው ሔዩ በር ላይ ቆምሽ?» ሲል ጠየቃት።
«ብዙ ስለቆየሁ ወደ ቤቴ ልሄድ ተነስቼ ነው፡፡ አለችው በእጆቿ ደረቱን እየደባበሰችና ቀና ብላ ዓይኖቹን በዓይኖቿ እየተመለከተች፡፡
«ለሔዩ ምን አደረግሽላት ትርፌ?» አለ እስቻለው ወደ ትርፌ ዞር ብሎ፡፡
«ምንም ጋሼ አስቻለው፤ ወሬ ብቻ»
«ምሳ በልተሽ ሂጂያ ሔዩ!!»
«በፍጹም አስቹ! እት አበባ ስራ መምጫዋ ስለሆነ ብሄድ ይሻላል»
«ስሞት»
«አይሆንም አስቹ በአጋጣሚ መገኛኘታችን በራሱ በቂ ነው፡፡»
አስቻለው አሁንም ከንፈሮቿን ሳም ካደረገ በኃላ «በይ እሺ ከቸኮልሽ»
ሂጂ አለና እስከ ውጭ በር ሸኝቶ ተሰናብቷት ወደ ቤቱ ተመልሶ ገባ፡፡
አልጋው ላይ ቁጭ አለና ያነ በእጁ ይዞት የነበረውን ካኪ ፖስታ በጥድፊያ ይከፍት ጀመር፡፡ ከአሜሪካ ካሊፎርኒያ ግዛት ከዶክተር ደጀኔ አድማሱ የተላክለት ደብዳቤ ነው። አስቻለው ጫማውን አውልቆ አልጋው ላይ ወጣና ትራሶቹን አነባብሮ ከአንገቱ ቀና ብሎ በጀርባው ጋለል በማለት ደብዳቤውን ማንበብ ጀመረ።
«የምወድህና የማከብርህ እንዲሁም የምናፍቅህ ውድ ወንድሜ ነርስ አስቻለው ፍስሃ፥ ከቶ ለጤናህ እንደምን አለህ? ፈጣሪ አምላክ ይመስገን እኔ በጣም ደህና ነኝ።
«የምወድህ አስቻለው፡ የመኪና አደጋ ደርሶብህ እንደነበር አውቃለሁ፡፡ አደጋው ቀደረሰ
በሶስተኛ ቀን በተኛህበት ሆስፒታል ተገኝቼ ልጠይቅህም ሞክሪ ነበር። በወቅቱ ራስህን አታውቅም ነበርና፡ እኔ ደግሞ የበረራ ፕርግራሜ በማግስቱ
ስለነበር ሆዴ እያዘነ ትቼህ ሄጃለሁ። ይሁንና የኢትዮጵያ አየር ክልል ወጥቼ፣ በሱዳንና በግብጽ እንዲሁም በሜድትራኒያን ባህር፡ ከዚያም በአውሮጳ ሰማይ ላይ
ተንሳፍፌ በበረራ ላይ በነበርኩበት ጊዜ ሁሉ ስለ አንተ እያለቀስኩ ነበር፡፡ አሜሪካም ከገባሁ በኋላ የአንተ ነገር ከእዕምርዩ አልወጣ ብሎኝ ለቀናት ያህል ተሰቃይቻለሁ። የኋላ ኋላ ግን ከአደጋው ሙሉ በሙሉ አገግመህ ወደ ስራህ የመመለስህን ዜና
ስስማ አምላኬን ከልብ አመስግኛለሁ። ወደፊትም ፈጣሪህ ከሁሉም ነገር
እንዲጠብቅህ እፀልያለሁ።
«ውድ ወንድሜ አስቻለሁ። መቸም ደብዳቤዬ እንደ ደረሰህ መጀመሪያ የሚታሰብህ ምን ዓይነት ኑሮ እየኖርኩ ስለመሆኔ የምገልጽልህ ነገር ይመስለኛል።
መሰደዴ የመከፋት ውጤት ነውና አሜሪካ ውስጥ ምን ያሆሎ እንደደላኝ ወይም እንዳልደላኝ ለማውቅ ትጓጓ ይሆናል። በኔ በኩል 'ደላኝ' ወይም 'ከፋኝ'ብዬ
ልነግርህ አልፈልግም፡፡ አኗኗሬን ልግለጽልህና ምደባውን ራስህ ፈርጀው፡፡
«የአሜሪካ ውስጥ በእየዕለቱ ያገኘሁትን ሁሉ ስሰራ እውላለሁ። ስራዬን ሳጠናቅቅ ለስራው የተመደበው ገንዘብ በሙሉ ይከፈለኛል። ዛሬ አንዱ ጋር ስስራ
ውዩ ነገ ወደ ሌላው ብሄድ መልቂያ አልጠየቅም፡፡ በስራ ዘመቻ ሰበብ የጉልበቴን
ዋጋ ማንም አይነጥቀኝም፡፡ በስላም ስሰራ ውዬ የሰላም እንቅልፍ እተኛለሁ። «እገሌ
ስለኔ ምን ይላል? ነገ ምን ያደርገኝ ወይም ያስደርገኝ ይሆን? ብዬ አልጨነቅም፡፡
በሰራሁት መጠን ትክክለኛ ክፍያ ስለምቀበል የገንዘብ ችግር አይገባኝም። የልደታ ዕለት ደሞዝ ወስጄ እስከ ቀጣዩ ልደታ ቀቃኝ አልበቃኝ ብዬ ስጨነቅ አልሰነብትም፡፡
እለታዊ አዋዋሌና የሆዴ ነገር ይህን ይመስላል፡፡ የመንፈስህስ ነገር ካልከኝ ግን ጣጣው ብዙ ነው። በመሰረቱ ማንም ሰው በሀገሩ ውስጥ ተከፍቶ በተሰደደበት አገር ደስ ይለዋል ማለት ዘበት ነው ምናልባት 'ከመሞት መሰንበት' ለሚለው
የሃገራችን ብሂል ምላሽ ይሆን እንደሆን እንጂ። ስደት ደግሞ
የመንፈስ ርሃብ ውጤት ነው።
መንፈሱ የተራበ ሰው የቱንም ያህል የጣፈጠና የበዛ ምግበ ቢበላ ሁልጌዜም ውስጡ ባዶ ነው እኔም እንዲሁ ባዶዬን እኖራለሁ።
«አሜሪካ ደግሞ የጭፍን ፖለቲካል ሰለባ ሆነውለተሰደዱባት ሁሉ የባሰ የመንፈስ ረሃብ የምትለቅ ሃገር ነች፡፡ የዚች ደብዳቢየም ዋንኛ ይዘት በዚሁ ዙሪያ የሚያጠነጥን ነውና በፅሞና አንብብልኝ። በዚያው ውስጤንም ትረዳዋለህ።
«አየህ አስቻለው አሜሪካኖች ወደ ስልጣን ሲወጡ መንገዳቸው በህዝብ መሀል ነው። ለስልጣን የሚደረግ ትልቅ ጦርነት አለ። መሳሪያው ግን መድፍና
መትረየስ አይደለም የጠራና የነጠረ ሀሳብ' በሩቅ የሚታይ ራዕይ ከራእዕዩ ጫፍ
የሚደርስ የፖለቲካ አመለካከትና አሰራር ቅደም ተከተል ወይም ፕሮግራዎ" እንጂ።ባሩዳቸው የሰላ ምላስና ርቱዕ አንደበት ነው የጦርነቱ ቦታ ክብ ጠረጴዛ ነው።
የውጊያ ወረዳዎች እልፍ አእላፍን የሚይዙ ሰፋፊ አዳራሾች ናቸው
በዚህ የትግል ሜዳ አሸንፎ ስልጣን ላይ የወጣ ሁሉ ስራውን የሚያከናውነው በሕዝብ
ይሁንታ በፀደቀ ህገ መንግስት መሰረት ነው። ማንም የስልጣን ክልሉን አልፎ ሲገኝ ያለቀጠሮ በሕዝብ ጩህት ስልጣን ይለቃል
ስለሆነም አሜሪካ ባለስልጣን
ሕዝብን ፈርቶ የሚኖርባት እንጂ ሕዝብ ባለ ስልጣንን እየፈራ የሚኖርባት ሀገር አይደለችም።
እንዴት ደ.....ስ የምትል አገር መሰለችህ!!
«የምወድህ አስቻለው፡- እዚህ አሜሪካ ውስጥ ባገኘሁት ብርሃን የሀገሪን ጨለማ አሻግሬ ሳየው አቤት ማስፈራራቱ! አቤት ማስጠላቱ! አቤት ማስጨነቁ!
የመንፈስ ርሀብ የሚለቅብኝም ይህ ሁኔታ ነው። በእውነት ያንቀጠቅጣል! በእውነት ይዘገንናል! በእውነት ያንገፈግፋል! የዚህ ሁሉ ድምር ውጤት እንቅልፍ እያሳጣ እኔንም ሁል ጊዜ ያስለቅሰኛል።
የሀገራችን አምባገነኖች ከየትም ይነሱ፤ በየትም ይምጡ፣ መቸም
ይድረሱ፥ ነገር ግን አንድ የጋራ መለያ ባህሪ አላቸው፤ ይህም በፊትለፊት በህዝባቸው ስም እየማሉ በስውር ግን የገዛ ሕዝባቸውን በጠላትነት የመፈረጅ
መስሪነታቸው ነው። መሠረታዊ ምክንያቱ ደግሞ ስልጣን ላይ የሚወጡት በሀይል እንጂ የህዝብ ይሁንታ አግኝተው ስላልሆነ ነው፡፡ ግን ደግሞ ስልጣኑን ይፈልጉታል። በድሀ ሀገር ስልጣን የሀብት ምንጭ ነውና ከያዙትም በኋላ ሙጭኝ ይሉበታል። ይቆዩበት ዘንድ ጠላታችን የሚሉትን ሕዝብ ያተረማምሱታል።ቢያንስ በሁለት እንዳንዴም ከዚያ በላይ በሆነ አመዳደብ ይከፋፍሉታል። አንዱን
ወገን ወዳጅ አድርገው ሌላውን በጠላትነት ይፈርጁታል። የጠሉትን ወገን የተለያየ
ስም እየለጠፉ ይበልጥ እንዲጠላ አውርተው ያስወሩበታል። በዚህም የጠላታቸውን እርስ በእርስ ጠላትነት ይፈጥራሉ፡፡ ሕዝብና ሕገብ የጎሪጥ እንዲተያይ ያደርጉና
ጥላቻና ጥርጣሬን ያነግሱበታል። በዚህ ጊዜ የራሳቸውን የስልጣን ኮርቻ ያደላድላሉ፣ የችሎታ ሳይሆን የብልጠት አካሄድ
በመነዘረቱ የግጭቶች ሁሉ! የጦርነቶች ሁሉ፣የቅራኔዎች ሁሉ
መሠረታዊ ምክንያት ኢኮኖሚ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ጥቅም!! ፖለቲካ የሚባላው ነገር የዚሁ ፍላጎት ልጣጭ ነው። በተላይ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ድሀ አገሮች አምባገነኖች ከስልጣን ላይ የሚወጡት ይህንኑ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለመቆጣጠር ነው።ሁሉን ነገር በመዳፋቸው ውስጥ ማስገባት የአምባገነኖች ልዩ ባህሪ ነውና፡፡
በዚህ አያበቁም፡ የስልጣን ጊዜያቸው እስከ መቼ ድረስ መሆኑን በውል ስለማያቁት 'ክፉ ቀን' ቢመጣ እያሉ በተለያየ መንገድ መዘጋጀት ይጀምራሉ
👍10
#ትኩሳት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
የሞት ጥሪ
አማንዳ
ወደ ኤክስ ልንመለስ ሶስት ቀን ሲቀረን ሲልቪ ቤቶቿን ለመሰናበት ሄደች። ጊዜው ንፁህ ብርህንና ለስላሳ ሙቀት በዝግተኛው ነፋስ የሚንሳፈፉበት ውብ የፀደይ ቀን ነበር። የፓሪስ ሴቶች ወደ ሰፊው ስመ ጥሩ ጎዳና ወደ ሻንዜሊዜ እንደሚጎርፉ ታወቀኝ፡፡ በሜትሮ ወደዚያው ሄድኩ ሱቆቹ የፀደይ ሞድ ልብሶቻቸውን መስኮቶቻቸው ላይ ዘርግተዋል፤ ካፌዎቹ ጠረጴዛ ወምበሮቻቸውን ወደ መንገዱ
አውጥተው ከአብዛኛዎቹ ጠረጴዛዎች በላይ በልዩ ልዩ ቀለማት ያጌጡ ሰፋፊ ጃንጥላዎችን ዘርግተዋል። ሰዉ ይንጋጋል፤ ትራፊኩ ይፈሳል። አንዱ ካፈ ውጪ ሰዉ የሚተላለፍበት ቦታ አንዲት ትንሽ ጠረጴዛ አጠገብ ተቀመጥኩ
በፀደይ ቀን ሻንዚሊዜ ጎዳናው ዳር ቁጭ ብሎ ቢራ እየጠጡ
አላፊ አግዳሚዋን ፈረንሳዊት እና የስንትና ስንት ሌላ አገር ሴት
መቃኘት። ከዚህ የበለጠ ምን ደስታ ይገኛል? ሴቶቹ የፀደዩን
ብርሀንና ነፋስ ለመቀበል የፈነዱ አበባዎች ይመስላሉ፡፡ የወፍ ቋንቋ
መሳይ ፈረንሳይኛቸውን በልዝብ ድምፃቸው እንደዘፈን እየተቀባበሉ፣የተነጠፈውን ድንጋይ በረዥም ተረከዛቸው ኳ! ኳ! እያረጉ፤ ውብ ዳሌያቸውን እያወዛወዙ ወደላይና ወደታች ይተላለፋሉ፡፡ አይኔ
አብሯቸው ይመላለሳል
ቀስ እያለ አይኔ ሰከረ፡፡ ውበት በዛበት። የአንዷን ኩሩ አረማመድ ሳደንቅ ትንሽ እንደ ተራመደችልኝ፡ ህዝቡ መሀል ገብታ ትጠፋለች፡፡ የሌላዋ ግሩም ቅርፅ አይኔን ይስባል፡ ከዳሌዋና ከባት ከተረከዟ የቱን እንደምመርጥ ገና ሳልወስን ህዝቡ ይውጣታል። ደሞ
የአንዷ ፀጉርና አንገት ልቤን ይወስደዋል። የምትቀጥለዋ ወጣት ነጭ ጥብቅ ያለ ሱሪ ለብሳ ስታልፍ አይኔ በዳሌዋ እንቅስቃሴ ላይ ይተከላል። እሷንም ሚንጋጋው ህዝብ ይውጣታል። ሌላ ወበት ሌላ ሴት ላይ ተጭኖ ሲሄድ አይኔን ይስባል። እንደዚህ ሰል አይኔ ሰከረ
የቢራዩን ሂሳብ ከፍዬ ወደ ፕላስ ደ ሌትዋል በኩል ስራመድ
የአንዷ ፀጉር አይኔን ማረካው:: ሴትዮዋ ከኋላ ሲያዩዋት ምንም
አትል አረ ሻንለዚ ስላየሁዋት ነው እንጂ ሌላ ቦታ ባያት በጣም ደስ ትላለች። አጠር ያለች ወጣት ናት። ቀይ ቦርሳ አንጠልጥላለች። ገላዋን እቀፍ አርጎ የሚሸፍን፣ ነጭ ባለ ሽንሽን የፀደይ
ቀሚስ ለብሳለች። ወገቧን ሰፊ ቀይ ቀበቶ አቅፎታል። ቀይ
ባለረዥም ተረከዝ ጫማ የረገጡት እግሮቿ ወፈር ብለው፣ ቀለማቸው ወደ ቡናማ የሚያደላ ነው። ወፍራም ዳሌዋ ከነጭ ልብሷ
ስር ሲመዛዝ ያስታውቃል፣ ምኞት ይቀሰቅሳል። ግን ዋናው ውበቷ
ፀጉሯ ነው:: ይሄ ንፁህ ነጭ ፀጉሯ ወደኋላዋ ትከሻዋ ድረስ ተለቆ፣
ፀሀዩ ውስጥ ይብለጨለጫል። የረጋ የጨረቃ ብርህን የሚመስል
ንፁህ ፀጉር ከዚህ በፊት የት ነው ያየሁት? የት? መቼ? የት?
ሴትዮዋ ወደ ቀኝ በኩል ተጠምዛ ከሻንዜሊዜ ወጥታ፣ አንድ
ሌላ መንገድ ይዛ ወደሳይ በኩል መራመድ ጀመረች። ለምን
ተከተልኳት? አላውቅም
መንገዱ ዳር ብዙ መኪናዎች ቆመው ነበር፡ እሷ አንድ ጥቁር
ጃጉዋር ስፖርት መኪና ውስጥ ገባች። አልፌያት ወደ ላይ በኩል
መንገዴን ስቀጥል፣
“Hi there!” አለችኝ። ባለሁበት ቆምኩ፡፡ የአማንዳ፥ ድምፅ!
ጆሮዬን ማመን አልቻልኩም፡፡ ግን ፀጉሩ የሷ ነው። አሁንም
አስታወስኩ። ወደሷ ዞርኩ፡፡ ከመኪናዋ ወጥታ እየሮጠች መጣችና ተጠመጠመችብኝ። ሽቶዋ በጣም ደስ ይላል።
“አማንዳ ነሽ እውነት?
«እዎን»
«ታድያ ያ ሁሉ ጮማ የት ሄደ?»
«ሸጥኩት» አለችና ትንሽ ከኔ ራቅ ብላ አንድ ሁለት ጊዜ
እየተሽከረከረች ምን ይመስልሀል?» አለችኝ
«ተአምር ነው፡፡ በአይኔ ባላይሽ ኖሮ አላምንም ነበር»
"Thank you"
«እውነቴን ነው:: አሁንኮ ማን እንደሆንሽ ሳላውቅ ከኋላሽ
በኩል ሳይሽ የማናት ቆንጆ ፈረንሳይ? እያልኩ ስከተልሽ ነበር»
«አንዲት ሴት ምን መስማት እንደምትወድ ብጥር አርገህ
ታውቃለህ መቸስ፡»
«እውነቴን ነው ኧረ!»
«ደስ ካልኩህ አብረኸኝ ምሳ ብላ እስቲ»
«ጥሩ»
ወደ ቆንጆ ጥቁር መኪናዋ ገባን፡፡ አማንዳ ድሮ ቁምቡርስ
ነበረች፣ አሁን ግን ቢራቢሮ ሆናለች። ትርፍ እገጯ ጠፍቷል፣
አንገቷ ዙርያ ተጠፍጥፎ የነበረው ጯማ ረግፏል። ፊቷ ሙሉ ነው፡
ግን ደስ ይላል፡፡ ከንፈሮቿ ሮዝ ብጤ ቀለም ተቀብተው፣ ሰማያዊ
አይኖቿ በጥንቃቄ ተኩለው፣ ቀይ ጉትቻዋ ከነጭ ፀጉሯ አጠገብ
ሲታይ በረዶ አጠገብ የተንጠለጠለ እንጆሪ ይመስላል።
ከአስቀያሚዎቹ ሴቶች ማህበር ወጥታ፣ ቆንጆዎቹ ማህበር
ገብታለች፡፡ ድምፅዋ ሳይቀር ተለውጧል። ድሮ አልቃሻ ብጤ ነበር፤አሁን ግን ልስልስ ያለ ቆንጆ ድምፅ ነው
«ንገሪኝ እስቲ፡ ምን እንደዚህ ለወጠሽ?» አልኳት
«አንድ ሰካራም አለችኝ
«ምን?»
«ሉን ተሰናብቼ ወደ አገሬ ስሄድ፡ ኤሮፕላኑ ውስጥ አንድ
ሰውዬ አጠገብ ተቀመጥኩ፡፡ ሰውየው ሰክሮ ነበር። ሉ ትዝ እያለኝ ለብቻዬ ሳለቅስ
« ምን ያስለቅስሻል? የወደድሽው ሰውዬ እምቢ አለሽ? ደግ አረገ! በዚህ እድሜሽ ምን እንዲህ አወፈረሽ? አለኝና ያኔውኑ
ረሳኝ፣ እንቅልፍ ወሰደው
«እኔ ግን ቃላቱን እስከ መቼም አልረሳቸውም። ለመጀመርያ
ጊዜ አንድ እውነት ተገለፀልኝ። ይኸውም፣ ጅል ሆኜ ነው እንጂ፣
ውፍረቴን እንደ ጭነት ተሸክሜ መዞር የለብኝም፡፡ ጭነቱን አውርጄ ልጥለው እችላለሁ። ልጥለው ቆረጥኩ። ሳን ፍራንሲስኮ ሄጄ ሙያቸው ክብደት መቀነስ ከሆነ ሰዎች ጋር አራት ወር ሙሉ ሰራሁ። ውጤቱን አንተም አመሰገንክልኝ አለች። ሳቋ ውስጥ ወጣትነትና የህይወት ድል አድራጊነት ይጨፍራል!
ባለ አራት ኮከብ (ማለት ከሁሉ ይበልጥ ምቾት ያለበት) ሆቴሏ
ወሰደችኝ። ክፍሏ ሆነን በቴሌፎን ሁለት ምሳ አዘዘች። አሁንም
አስደነቀችኝ። ኤክስ ሳውቃት ፈረንሳይኛውን በአስቀያሚ የአሜሪካን ቅላፄ ነበር የምታዜመው፣ አሁን ግን የፓሪስ ፈረንሳይኛ ሊሆን ምንም አልቀረው:: እያየችኝ ስትስቅ
“እንደዚህ የሚያስደስት ለውጥ አይቼ አላውቅም።
"Thank you, you re really sweet" አለችኝ
ከምሳ በኋላ «ፓሪስ ምን ትሰራለህ?» አለችኝ፡፡ ነገርኳት፡፡
«አንቺስ?» አልኳት።
«ከኒው ዮርክ የዛሬ ሳምንት መጣሁ፡፡ ይሄ ጃጉዋር ከኢንግላንድ እስኪመጣልኝ ነበር " ምጠብቀው። ነገ ወይም ተነገ ወድያ ወደ ኤክስ መሄዴ ነው:: . . ሉን ማግኘት አለብኝ፡፡ ደህና ነው? አሁንስ የሚፈልገኝ ይመስልሀል? ለጊዜው ሴት አልያዘ እንደሆነ ጥርጥር የለውም። ይዞ እንደሆነ፣ ነጥቄ መውሰድ ይኖርብኛል።»
«ምን?»
«ነጥቄ እወስደዋለሁ። ምነው ገረመህ? የድሮዋ አማንዳ
መስዬህለሁ እንዴ? ተለውጫለሁኮ:: ተዘጋጅቼ ነው የመጣሁት፡፡ ቢያንስ አርባ የሳይኮሎጂ መፅሀፍ አንብቤያለሁ። ደሞ ሉን
አውቀዋለሁ፡፡ ግብረ ስጋ በጣም ይወዳል። ለሱም ተዘጋጅቻለሁ፡፡»
«እንዴት?»
«ለሌላ ሰው ቢሆን ይህን አልነግረውም። አንተ ግን
ትወደኛለህ። ወፍራም ሳለሁም ትወደኝ ነበር፡፡ ለኔ ግድ ነበረህ፡፡
የተሻልኩ ሰው ሆኜ ስላየኸኝ ደሞ በጣም ደስ ብሎሀል። ይሄ ለኔ
ትልቅ ስጦታ ነው። በጣም ተወዳጅ ነህ፡፡ እና ለምን እንደሆነ
ሳላውቅ በጣም አምንሀለሁ፡፡ ለምንድነው እማምንህ?»
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
የሞት ጥሪ
አማንዳ
ወደ ኤክስ ልንመለስ ሶስት ቀን ሲቀረን ሲልቪ ቤቶቿን ለመሰናበት ሄደች። ጊዜው ንፁህ ብርህንና ለስላሳ ሙቀት በዝግተኛው ነፋስ የሚንሳፈፉበት ውብ የፀደይ ቀን ነበር። የፓሪስ ሴቶች ወደ ሰፊው ስመ ጥሩ ጎዳና ወደ ሻንዜሊዜ እንደሚጎርፉ ታወቀኝ፡፡ በሜትሮ ወደዚያው ሄድኩ ሱቆቹ የፀደይ ሞድ ልብሶቻቸውን መስኮቶቻቸው ላይ ዘርግተዋል፤ ካፌዎቹ ጠረጴዛ ወምበሮቻቸውን ወደ መንገዱ
አውጥተው ከአብዛኛዎቹ ጠረጴዛዎች በላይ በልዩ ልዩ ቀለማት ያጌጡ ሰፋፊ ጃንጥላዎችን ዘርግተዋል። ሰዉ ይንጋጋል፤ ትራፊኩ ይፈሳል። አንዱ ካፈ ውጪ ሰዉ የሚተላለፍበት ቦታ አንዲት ትንሽ ጠረጴዛ አጠገብ ተቀመጥኩ
በፀደይ ቀን ሻንዚሊዜ ጎዳናው ዳር ቁጭ ብሎ ቢራ እየጠጡ
አላፊ አግዳሚዋን ፈረንሳዊት እና የስንትና ስንት ሌላ አገር ሴት
መቃኘት። ከዚህ የበለጠ ምን ደስታ ይገኛል? ሴቶቹ የፀደዩን
ብርሀንና ነፋስ ለመቀበል የፈነዱ አበባዎች ይመስላሉ፡፡ የወፍ ቋንቋ
መሳይ ፈረንሳይኛቸውን በልዝብ ድምፃቸው እንደዘፈን እየተቀባበሉ፣የተነጠፈውን ድንጋይ በረዥም ተረከዛቸው ኳ! ኳ! እያረጉ፤ ውብ ዳሌያቸውን እያወዛወዙ ወደላይና ወደታች ይተላለፋሉ፡፡ አይኔ
አብሯቸው ይመላለሳል
ቀስ እያለ አይኔ ሰከረ፡፡ ውበት በዛበት። የአንዷን ኩሩ አረማመድ ሳደንቅ ትንሽ እንደ ተራመደችልኝ፡ ህዝቡ መሀል ገብታ ትጠፋለች፡፡ የሌላዋ ግሩም ቅርፅ አይኔን ይስባል፡ ከዳሌዋና ከባት ከተረከዟ የቱን እንደምመርጥ ገና ሳልወስን ህዝቡ ይውጣታል። ደሞ
የአንዷ ፀጉርና አንገት ልቤን ይወስደዋል። የምትቀጥለዋ ወጣት ነጭ ጥብቅ ያለ ሱሪ ለብሳ ስታልፍ አይኔ በዳሌዋ እንቅስቃሴ ላይ ይተከላል። እሷንም ሚንጋጋው ህዝብ ይውጣታል። ሌላ ወበት ሌላ ሴት ላይ ተጭኖ ሲሄድ አይኔን ይስባል። እንደዚህ ሰል አይኔ ሰከረ
የቢራዩን ሂሳብ ከፍዬ ወደ ፕላስ ደ ሌትዋል በኩል ስራመድ
የአንዷ ፀጉር አይኔን ማረካው:: ሴትዮዋ ከኋላ ሲያዩዋት ምንም
አትል አረ ሻንለዚ ስላየሁዋት ነው እንጂ ሌላ ቦታ ባያት በጣም ደስ ትላለች። አጠር ያለች ወጣት ናት። ቀይ ቦርሳ አንጠልጥላለች። ገላዋን እቀፍ አርጎ የሚሸፍን፣ ነጭ ባለ ሽንሽን የፀደይ
ቀሚስ ለብሳለች። ወገቧን ሰፊ ቀይ ቀበቶ አቅፎታል። ቀይ
ባለረዥም ተረከዝ ጫማ የረገጡት እግሮቿ ወፈር ብለው፣ ቀለማቸው ወደ ቡናማ የሚያደላ ነው። ወፍራም ዳሌዋ ከነጭ ልብሷ
ስር ሲመዛዝ ያስታውቃል፣ ምኞት ይቀሰቅሳል። ግን ዋናው ውበቷ
ፀጉሯ ነው:: ይሄ ንፁህ ነጭ ፀጉሯ ወደኋላዋ ትከሻዋ ድረስ ተለቆ፣
ፀሀዩ ውስጥ ይብለጨለጫል። የረጋ የጨረቃ ብርህን የሚመስል
ንፁህ ፀጉር ከዚህ በፊት የት ነው ያየሁት? የት? መቼ? የት?
ሴትዮዋ ወደ ቀኝ በኩል ተጠምዛ ከሻንዜሊዜ ወጥታ፣ አንድ
ሌላ መንገድ ይዛ ወደሳይ በኩል መራመድ ጀመረች። ለምን
ተከተልኳት? አላውቅም
መንገዱ ዳር ብዙ መኪናዎች ቆመው ነበር፡ እሷ አንድ ጥቁር
ጃጉዋር ስፖርት መኪና ውስጥ ገባች። አልፌያት ወደ ላይ በኩል
መንገዴን ስቀጥል፣
“Hi there!” አለችኝ። ባለሁበት ቆምኩ፡፡ የአማንዳ፥ ድምፅ!
ጆሮዬን ማመን አልቻልኩም፡፡ ግን ፀጉሩ የሷ ነው። አሁንም
አስታወስኩ። ወደሷ ዞርኩ፡፡ ከመኪናዋ ወጥታ እየሮጠች መጣችና ተጠመጠመችብኝ። ሽቶዋ በጣም ደስ ይላል።
“አማንዳ ነሽ እውነት?
«እዎን»
«ታድያ ያ ሁሉ ጮማ የት ሄደ?»
«ሸጥኩት» አለችና ትንሽ ከኔ ራቅ ብላ አንድ ሁለት ጊዜ
እየተሽከረከረች ምን ይመስልሀል?» አለችኝ
«ተአምር ነው፡፡ በአይኔ ባላይሽ ኖሮ አላምንም ነበር»
"Thank you"
«እውነቴን ነው:: አሁንኮ ማን እንደሆንሽ ሳላውቅ ከኋላሽ
በኩል ሳይሽ የማናት ቆንጆ ፈረንሳይ? እያልኩ ስከተልሽ ነበር»
«አንዲት ሴት ምን መስማት እንደምትወድ ብጥር አርገህ
ታውቃለህ መቸስ፡»
«እውነቴን ነው ኧረ!»
«ደስ ካልኩህ አብረኸኝ ምሳ ብላ እስቲ»
«ጥሩ»
ወደ ቆንጆ ጥቁር መኪናዋ ገባን፡፡ አማንዳ ድሮ ቁምቡርስ
ነበረች፣ አሁን ግን ቢራቢሮ ሆናለች። ትርፍ እገጯ ጠፍቷል፣
አንገቷ ዙርያ ተጠፍጥፎ የነበረው ጯማ ረግፏል። ፊቷ ሙሉ ነው፡
ግን ደስ ይላል፡፡ ከንፈሮቿ ሮዝ ብጤ ቀለም ተቀብተው፣ ሰማያዊ
አይኖቿ በጥንቃቄ ተኩለው፣ ቀይ ጉትቻዋ ከነጭ ፀጉሯ አጠገብ
ሲታይ በረዶ አጠገብ የተንጠለጠለ እንጆሪ ይመስላል።
ከአስቀያሚዎቹ ሴቶች ማህበር ወጥታ፣ ቆንጆዎቹ ማህበር
ገብታለች፡፡ ድምፅዋ ሳይቀር ተለውጧል። ድሮ አልቃሻ ብጤ ነበር፤አሁን ግን ልስልስ ያለ ቆንጆ ድምፅ ነው
«ንገሪኝ እስቲ፡ ምን እንደዚህ ለወጠሽ?» አልኳት
«አንድ ሰካራም አለችኝ
«ምን?»
«ሉን ተሰናብቼ ወደ አገሬ ስሄድ፡ ኤሮፕላኑ ውስጥ አንድ
ሰውዬ አጠገብ ተቀመጥኩ፡፡ ሰውየው ሰክሮ ነበር። ሉ ትዝ እያለኝ ለብቻዬ ሳለቅስ
« ምን ያስለቅስሻል? የወደድሽው ሰውዬ እምቢ አለሽ? ደግ አረገ! በዚህ እድሜሽ ምን እንዲህ አወፈረሽ? አለኝና ያኔውኑ
ረሳኝ፣ እንቅልፍ ወሰደው
«እኔ ግን ቃላቱን እስከ መቼም አልረሳቸውም። ለመጀመርያ
ጊዜ አንድ እውነት ተገለፀልኝ። ይኸውም፣ ጅል ሆኜ ነው እንጂ፣
ውፍረቴን እንደ ጭነት ተሸክሜ መዞር የለብኝም፡፡ ጭነቱን አውርጄ ልጥለው እችላለሁ። ልጥለው ቆረጥኩ። ሳን ፍራንሲስኮ ሄጄ ሙያቸው ክብደት መቀነስ ከሆነ ሰዎች ጋር አራት ወር ሙሉ ሰራሁ። ውጤቱን አንተም አመሰገንክልኝ አለች። ሳቋ ውስጥ ወጣትነትና የህይወት ድል አድራጊነት ይጨፍራል!
ባለ አራት ኮከብ (ማለት ከሁሉ ይበልጥ ምቾት ያለበት) ሆቴሏ
ወሰደችኝ። ክፍሏ ሆነን በቴሌፎን ሁለት ምሳ አዘዘች። አሁንም
አስደነቀችኝ። ኤክስ ሳውቃት ፈረንሳይኛውን በአስቀያሚ የአሜሪካን ቅላፄ ነበር የምታዜመው፣ አሁን ግን የፓሪስ ፈረንሳይኛ ሊሆን ምንም አልቀረው:: እያየችኝ ስትስቅ
“እንደዚህ የሚያስደስት ለውጥ አይቼ አላውቅም።
"Thank you, you re really sweet" አለችኝ
ከምሳ በኋላ «ፓሪስ ምን ትሰራለህ?» አለችኝ፡፡ ነገርኳት፡፡
«አንቺስ?» አልኳት።
«ከኒው ዮርክ የዛሬ ሳምንት መጣሁ፡፡ ይሄ ጃጉዋር ከኢንግላንድ እስኪመጣልኝ ነበር " ምጠብቀው። ነገ ወይም ተነገ ወድያ ወደ ኤክስ መሄዴ ነው:: . . ሉን ማግኘት አለብኝ፡፡ ደህና ነው? አሁንስ የሚፈልገኝ ይመስልሀል? ለጊዜው ሴት አልያዘ እንደሆነ ጥርጥር የለውም። ይዞ እንደሆነ፣ ነጥቄ መውሰድ ይኖርብኛል።»
«ምን?»
«ነጥቄ እወስደዋለሁ። ምነው ገረመህ? የድሮዋ አማንዳ
መስዬህለሁ እንዴ? ተለውጫለሁኮ:: ተዘጋጅቼ ነው የመጣሁት፡፡ ቢያንስ አርባ የሳይኮሎጂ መፅሀፍ አንብቤያለሁ። ደሞ ሉን
አውቀዋለሁ፡፡ ግብረ ስጋ በጣም ይወዳል። ለሱም ተዘጋጅቻለሁ፡፡»
«እንዴት?»
«ለሌላ ሰው ቢሆን ይህን አልነግረውም። አንተ ግን
ትወደኛለህ። ወፍራም ሳለሁም ትወደኝ ነበር፡፡ ለኔ ግድ ነበረህ፡፡
የተሻልኩ ሰው ሆኜ ስላየኸኝ ደሞ በጣም ደስ ብሎሀል። ይሄ ለኔ
ትልቅ ስጦታ ነው። በጣም ተወዳጅ ነህ፡፡ እና ለምን እንደሆነ
ሳላውቅ በጣም አምንሀለሁ፡፡ ለምንድነው እማምንህ?»
👍14🤔2
#ሳቤላ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
ለሚስተርና ለሚስዝ ካርላይል ጋብቻ ደስታቸውን ለመግለጽ የአካባቢው ታላላቅ ሰዎች እንደየአቅማቸውና እንደ ደረጃቸው በተለያዩ ሠረገዎች እየሆኑ በልዩ
ልዩ የክብር ልብሶች አጊጠው ጌጠኛ ልብስ በለበሱ አሽከሮች እየታጀቡ ኢስትሊን መግባት ጀመሩ ።
ሚስተር ካርይል መኖሪያውን ኢስት ሊን ቢያደርግም እመቤት ሳቤላ ቬንን ባያገባ ኖሮ እነዚያ ሁሉ መኳንንትና ወይዛዝርት ይኸን ያሀል ክብር ሰጥተው እሱን ጥየቃ ብለው እንደዚህ በብዛት አይንጋጉለትም ነበር "
ደስታቸውን ለመግለጽ ከመጡት ታላላቅ ሰዎች መካከል ጀስቲስ” ሔር'ሚስቱና ልጁ ባርባራ ሔር ነበሩ " በነዚያ ጭራቸው መሬት በሚነካ ኣካላተ ሙሉና ጸጉረ ለስላሳ ፈረሶች ይሳብ የነበረው ጥንታዊ ሠረገላ የሚንቀሳቀሰው እንደ ዛሬው በመሳሰሉ አጋጣሚዎችና ከፍተኛ የበዓል ቀኖች ብቻ ነበር "
እንግዶቹ ኢስት ሊን በደረሱበት ሰዓት ሳቤላ ከመልበሻ ክፍሏ ሆና ጆይስ ከሷ ጋር ስለምትጠቃለልበት መንግድ ትነጋገር ነበር » ጆይስም የደንገጡርነቱን ሥራ ደኅና እየተለማመደችው ስለ ነበርና ሚስ ካርላይልም ያለምምንም ቅሬታ እንደ ምትፈቅድላት ስለምታውቅ ወይዘሮ ሳቤላ ከፈቀደች ደስ እያላት ከሷ ጋር ለመሆን እንደምትፈልግ ስትነግራት ነበር " በዚህ መኻል በር ተንኳኳ " ጆይስ በሩን ስትከፍተው አንዲት የዌስት ሊን ተወላጅ የሆነች አዲስ የተቀጠረች ሠራተኛ ሆና አገኘቻት " ሳቤላ ሁለቱ ሴቶች የሚባባሉትን ትስማ ነበር ።
« እሜቴ አሉ ? »
« አሉ »
« እንግዶች መጥተዋል " ፒተር ንገሪ ብሎ ልኮኝ ነው ። እነማን መሰሉሽ ? ሚስተር “ጀስቲስ” ሔር ከነቤተሰባቸው እሷም አብራ አለች " መቸም ያለባበስ ነገር አታንሺው የራስ መሸፈኛዋ በውስጡ ሰማያዊ ጥሩንባ ቅርጽ አበቦች አሉት " በስተውጪ መጥረጊያ የሚያክል ነጭ ላባ ሰክታበታለች ከሠረገላ ስትወርድ ልብ ብዬ አየኋት " »
« ማናት እሷ ? » አለች ጆይስ ፊቷን ኮስተር አድርጋ
« ሚስ ባርባራ ናታ እስኪ ተመልከች አሁን እሷም ልጠይቅ ብላ መምጣቷ ምን ይባላል ? ይልቅ እሜቴን መርዝ እንዳታጠጣቸው ቢጠነቀቁ ይሻላል »
ጆይስ ሠራተኛይቱን በዛው ሸኝታ ' በሩን ዘጋችና ወደ እመቤቷ ተመለሰች "በሹክሹክታ የተመላለሱትን ነገር ሳቤላ መስማቷን አላወቀችም "
« ሱዛን ናት " እንግዶች መምጣታቸውን ልትነግር ነው የመጣችው • ሚስተር ጀስቲስ ሔር ' ሚስዝ ሔርና ሚስ ባርባራ ከሳሎን ገብተው ተቀምጠዋል ትላለች »
ሳቤላ ሱዛን ስለ ተናረችው ምስጢራዊ ነገር ኢያሰበች እንግዶች ወዶ ዐረፉበት ክፍል ወረደች "
ዳኛው አዲስ ሰው ሠራሽ ጸጉር ያጠለቀ ጉረኛና የተናገረውን ቃል ማያጥፍ ችክ ያለ ሰው ይመስላል ሚስዝ ሔር ልስልስ ግርጥት ያለች ወይዘሮ ስትሆን ባርባራ ደግሞ የምታምር ቆንጆ ናት " ሳቤላ ስትገባ እንዳየቻቸው ያሳደሩባት ስሜት ይህን ይመስል ነበር "
ብዙ ሲጫወቱ ቆዩ " ሳቤላ ያቺን መከረኛና ረቂቅ ወይዘሮ ሚስዝ ሔርን ስታያት በጣም ወደደቻት ሚስ ካርይል ስትግባ እንግዶቹ ለመሔድ ተነሱ" ሚስ ካርላይል ግን ለባርባራ የምታሳያት ነገር ስለ ነበራት እንዲቆዩ ብትሞክርም
በዐሥራ አንድ ሰዓት ከቤቱ እንግዳ ስለጠራና አሁን ግማሽ ሰዓት ብቻ ስለ ቀረው ባርባራ ብትፈልግ ልትቆይ መቻሏን ነግሮ ከሚስቱ ጋር ተያይዘው ሔዱ "
ባርባራ ፊቷ ደም መሰለ ሆኖም ሚስ ኮርኒሊያ ካርላይል ያቀረበችላት የራት ሰዓት ደረሰ ሳቤላ የራት ልብስ ለመልበስ ከፎቅ ወደሚገኘው ክፍል
ወጣች " ጆይስ እዛው ስትጠብቃት አገኘቻት " ወዲያው ከሷ ጋር ስለምትሆንባት
ጉዳይ መነጋግር ጀመሩ
« እሜቴ » አለች ጆይስ « ሚስ ካርላይልን አነጋግሬአቸዋለሁ " ወደ እርስዎ ብዛወር ፈቃደኛ ናቸው " ነገር ግን በታሪኬ አንድ ደስ የማይል ነገር ስለ አለበት
አስቀድሜ መግለጽ እንዳለብኝ ነግረውኛል እኔም ራሴ አስቤበት ነበር " ሚስ ካርላይል ጠባያቸው ደስ አይልም ግን እውነተኛና ቀጥተኛ ሰው ናቸው "
« ምንድን ነው ደስ የማይለው ታሪክሽ ? »
« አባቴ የሚስተር ካርላይል አባት ጸሐፊ ነበር " እናቴ በስምንት ዓመቴ ሞተችና አባቴ የሚስተር ኬን ዋርሳ የምትሆን ሴት አግብቶ አፌ የምትባለዋን እኅቴን ወለዶችለት እሷም አፊ ገና ያመት ልጅ ሳለች ሞተች " ሕፃኗም የናቷ
አክስት ልታሳድጋት ወሰደቻት እኔ ግን ከአባቴ ጋር ሁኘ በልጅነቴ ትምሀርት ቤት እመላለስ ነበር ካደግሁ በኋላ ባርኔጣ ሥራና ልብስ ሰፌት ተማርኩ አባቴ የራሱ
የሆነ ቤት ከጫካው ዳር ነበረው " የቤት ሥራ የምትረዳ የቀን ሠራተኛ ነበረች እሷም በየቀኑ ከኛ ጋር የምትቆየው ለጥቂት ሰአት ብቻ ነበር አባቴን እንዳይከፋው እየተንከባከብኩ ጊዜ ሲኖረኝ ብቻ ከአንዳንድ ወይዛዝርት ቤት እየሔድኩ እሠራ ነበር "
« በዚህ ዐይነት ብዙ ዓመት ከኖርን በኋላ አፊ ተመልሳ መጣችና ከኛ ጋር ተቀመጠች አክስቲቱም ሞተች " ገንዘቧም አብሮ ሞተና ምንም እንኳን አፊን በደንብ ብታሳድጋትም ስትሞት አንድም ነገር ልትተውላት አልቻለችም " እኛም አፊ ፈራናት " አለባበሷና ልዩ ፍሳጐቷ ሰማይ ነበር ደስተኛ መልከኛና የተቅበጠበጠች ነበረች" ከዌስት ሊን የሕዝብ ንባብ ቤት እየተዋሰች የምታመጣቸውን መጻሕፍት ከማንበብ በቀር አንድም ነገር አትሠራም ነበር አባቴ ደግሞ ይኸን ጠባይዋን
አልወደደውም እኛ ለራሳችን ለፍቶ አዳሪዎች ስንሆን እሷ ደግሞ አክስቷ ቤት እንደ ለመደችው ትዘባነንብን ጀመች እንዲህ ስትል ስትል ከሪቻርድ ሔር ተዋወቀች "
ወይዘሮ ሳቤላ ' ቶሎ ቀና ብላ አየቻት
« የሚስተር ጀስቲስ ሔር ብቸኛ ወንድ ልጅና ! የሚስ ባርባራ ወንድም ነው አፊ ፊት ስትሰጠው ጊዜ ፍቅር ያዘው ከዚያም ቀስ በቀስ ሌሎችንም መሳብ ጀመረች አባታችን በሥራ ምክንያት ከቤት በማይኖርበት ጊዜ አጫፋሪዎቿ
የፈለገችውን እየያዘች ከቤት ታመሻለች።
« ከብዙ ወዳጆቿ አንዱና ዋናው ሪቻርድ ሔር ነበር ሌላ ደግሞ ራቅ ካለ ቦታ በፈረስ እየመጣ የሚጠይቃት ወዳጅ ነበራት " እሱ ግን አስከዚህም የነበረ አይመስለኝም " ከሚስተር ሪቻርድ ሔር ጋር የነበራት ግንኙነት ግን አባቴን እስከ ገደለበት ድረስ ቀጠለ "
« ማን ? » አለች ሳቤላ ድንግጥ ብላ ።
« ሪቻርድ ሔር ነዋ . . .እሜቴ » አባቴ እነዚህ የትልቅ ሰዎች ልጆች ድሆች ሴቶች ልጆችን የሚከታተሏቸው ለጋብቻ እያሰቧቸው እንዳልነበር ያውቅ ነበር በርግጥ በሚስተር ሪቻርድ ቀና አመለካከት ባይኖረውና በአፊጉዳት ያደርሳል ብሎ
ቢጠረጥረው ኖሮ ጠበቅ ያለ ገደብ ይፈጥር ነበር " አንድ ቀን ዌስት ሊን ላይ ስዎች የሷን ስም ከሪቻርድ ጋር አዳብለው በክፉ ሰያነሡት ሰማ ማታ ሲጠጣ እኔ ባለሁበት ከሪቻርድ ጋር ያላት ግንኙነት እንዳይቀጥል እሷም ፊት እንዳትሰጠ ለአፊ ነገራት " ይገርምዎታል በበነጋው ማታ ሪቻርድ ሔር አባቴን በጥይት ገደለው » አለቻት።
« አቤት እንዴት ያሳዝናል ልጀ ! »
« ታዲያ ይህ ነገር ሆነ ተብሎ የተፈጸመ ይሁን ወይም ካለመጠንቀቅ ጠበንጃው ጋር ሲታገል ይባርቅበት አልታወቀም ሕዝቡ በማን አለብኝነት የተፈጸመ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
ለሚስተርና ለሚስዝ ካርላይል ጋብቻ ደስታቸውን ለመግለጽ የአካባቢው ታላላቅ ሰዎች እንደየአቅማቸውና እንደ ደረጃቸው በተለያዩ ሠረገዎች እየሆኑ በልዩ
ልዩ የክብር ልብሶች አጊጠው ጌጠኛ ልብስ በለበሱ አሽከሮች እየታጀቡ ኢስትሊን መግባት ጀመሩ ።
ሚስተር ካርይል መኖሪያውን ኢስት ሊን ቢያደርግም እመቤት ሳቤላ ቬንን ባያገባ ኖሮ እነዚያ ሁሉ መኳንንትና ወይዛዝርት ይኸን ያሀል ክብር ሰጥተው እሱን ጥየቃ ብለው እንደዚህ በብዛት አይንጋጉለትም ነበር "
ደስታቸውን ለመግለጽ ከመጡት ታላላቅ ሰዎች መካከል ጀስቲስ” ሔር'ሚስቱና ልጁ ባርባራ ሔር ነበሩ " በነዚያ ጭራቸው መሬት በሚነካ ኣካላተ ሙሉና ጸጉረ ለስላሳ ፈረሶች ይሳብ የነበረው ጥንታዊ ሠረገላ የሚንቀሳቀሰው እንደ ዛሬው በመሳሰሉ አጋጣሚዎችና ከፍተኛ የበዓል ቀኖች ብቻ ነበር "
እንግዶቹ ኢስት ሊን በደረሱበት ሰዓት ሳቤላ ከመልበሻ ክፍሏ ሆና ጆይስ ከሷ ጋር ስለምትጠቃለልበት መንግድ ትነጋገር ነበር » ጆይስም የደንገጡርነቱን ሥራ ደኅና እየተለማመደችው ስለ ነበርና ሚስ ካርላይልም ያለምምንም ቅሬታ እንደ ምትፈቅድላት ስለምታውቅ ወይዘሮ ሳቤላ ከፈቀደች ደስ እያላት ከሷ ጋር ለመሆን እንደምትፈልግ ስትነግራት ነበር " በዚህ መኻል በር ተንኳኳ " ጆይስ በሩን ስትከፍተው አንዲት የዌስት ሊን ተወላጅ የሆነች አዲስ የተቀጠረች ሠራተኛ ሆና አገኘቻት " ሳቤላ ሁለቱ ሴቶች የሚባባሉትን ትስማ ነበር ።
« እሜቴ አሉ ? »
« አሉ »
« እንግዶች መጥተዋል " ፒተር ንገሪ ብሎ ልኮኝ ነው ። እነማን መሰሉሽ ? ሚስተር “ጀስቲስ” ሔር ከነቤተሰባቸው እሷም አብራ አለች " መቸም ያለባበስ ነገር አታንሺው የራስ መሸፈኛዋ በውስጡ ሰማያዊ ጥሩንባ ቅርጽ አበቦች አሉት " በስተውጪ መጥረጊያ የሚያክል ነጭ ላባ ሰክታበታለች ከሠረገላ ስትወርድ ልብ ብዬ አየኋት " »
« ማናት እሷ ? » አለች ጆይስ ፊቷን ኮስተር አድርጋ
« ሚስ ባርባራ ናታ እስኪ ተመልከች አሁን እሷም ልጠይቅ ብላ መምጣቷ ምን ይባላል ? ይልቅ እሜቴን መርዝ እንዳታጠጣቸው ቢጠነቀቁ ይሻላል »
ጆይስ ሠራተኛይቱን በዛው ሸኝታ ' በሩን ዘጋችና ወደ እመቤቷ ተመለሰች "በሹክሹክታ የተመላለሱትን ነገር ሳቤላ መስማቷን አላወቀችም "
« ሱዛን ናት " እንግዶች መምጣታቸውን ልትነግር ነው የመጣችው • ሚስተር ጀስቲስ ሔር ' ሚስዝ ሔርና ሚስ ባርባራ ከሳሎን ገብተው ተቀምጠዋል ትላለች »
ሳቤላ ሱዛን ስለ ተናረችው ምስጢራዊ ነገር ኢያሰበች እንግዶች ወዶ ዐረፉበት ክፍል ወረደች "
ዳኛው አዲስ ሰው ሠራሽ ጸጉር ያጠለቀ ጉረኛና የተናገረውን ቃል ማያጥፍ ችክ ያለ ሰው ይመስላል ሚስዝ ሔር ልስልስ ግርጥት ያለች ወይዘሮ ስትሆን ባርባራ ደግሞ የምታምር ቆንጆ ናት " ሳቤላ ስትገባ እንዳየቻቸው ያሳደሩባት ስሜት ይህን ይመስል ነበር "
ብዙ ሲጫወቱ ቆዩ " ሳቤላ ያቺን መከረኛና ረቂቅ ወይዘሮ ሚስዝ ሔርን ስታያት በጣም ወደደቻት ሚስ ካርይል ስትግባ እንግዶቹ ለመሔድ ተነሱ" ሚስ ካርላይል ግን ለባርባራ የምታሳያት ነገር ስለ ነበራት እንዲቆዩ ብትሞክርም
በዐሥራ አንድ ሰዓት ከቤቱ እንግዳ ስለጠራና አሁን ግማሽ ሰዓት ብቻ ስለ ቀረው ባርባራ ብትፈልግ ልትቆይ መቻሏን ነግሮ ከሚስቱ ጋር ተያይዘው ሔዱ "
ባርባራ ፊቷ ደም መሰለ ሆኖም ሚስ ኮርኒሊያ ካርላይል ያቀረበችላት የራት ሰዓት ደረሰ ሳቤላ የራት ልብስ ለመልበስ ከፎቅ ወደሚገኘው ክፍል
ወጣች " ጆይስ እዛው ስትጠብቃት አገኘቻት " ወዲያው ከሷ ጋር ስለምትሆንባት
ጉዳይ መነጋግር ጀመሩ
« እሜቴ » አለች ጆይስ « ሚስ ካርላይልን አነጋግሬአቸዋለሁ " ወደ እርስዎ ብዛወር ፈቃደኛ ናቸው " ነገር ግን በታሪኬ አንድ ደስ የማይል ነገር ስለ አለበት
አስቀድሜ መግለጽ እንዳለብኝ ነግረውኛል እኔም ራሴ አስቤበት ነበር " ሚስ ካርላይል ጠባያቸው ደስ አይልም ግን እውነተኛና ቀጥተኛ ሰው ናቸው "
« ምንድን ነው ደስ የማይለው ታሪክሽ ? »
« አባቴ የሚስተር ካርላይል አባት ጸሐፊ ነበር " እናቴ በስምንት ዓመቴ ሞተችና አባቴ የሚስተር ኬን ዋርሳ የምትሆን ሴት አግብቶ አፌ የምትባለዋን እኅቴን ወለዶችለት እሷም አፊ ገና ያመት ልጅ ሳለች ሞተች " ሕፃኗም የናቷ
አክስት ልታሳድጋት ወሰደቻት እኔ ግን ከአባቴ ጋር ሁኘ በልጅነቴ ትምሀርት ቤት እመላለስ ነበር ካደግሁ በኋላ ባርኔጣ ሥራና ልብስ ሰፌት ተማርኩ አባቴ የራሱ
የሆነ ቤት ከጫካው ዳር ነበረው " የቤት ሥራ የምትረዳ የቀን ሠራተኛ ነበረች እሷም በየቀኑ ከኛ ጋር የምትቆየው ለጥቂት ሰአት ብቻ ነበር አባቴን እንዳይከፋው እየተንከባከብኩ ጊዜ ሲኖረኝ ብቻ ከአንዳንድ ወይዛዝርት ቤት እየሔድኩ እሠራ ነበር "
« በዚህ ዐይነት ብዙ ዓመት ከኖርን በኋላ አፊ ተመልሳ መጣችና ከኛ ጋር ተቀመጠች አክስቲቱም ሞተች " ገንዘቧም አብሮ ሞተና ምንም እንኳን አፊን በደንብ ብታሳድጋትም ስትሞት አንድም ነገር ልትተውላት አልቻለችም " እኛም አፊ ፈራናት " አለባበሷና ልዩ ፍሳጐቷ ሰማይ ነበር ደስተኛ መልከኛና የተቅበጠበጠች ነበረች" ከዌስት ሊን የሕዝብ ንባብ ቤት እየተዋሰች የምታመጣቸውን መጻሕፍት ከማንበብ በቀር አንድም ነገር አትሠራም ነበር አባቴ ደግሞ ይኸን ጠባይዋን
አልወደደውም እኛ ለራሳችን ለፍቶ አዳሪዎች ስንሆን እሷ ደግሞ አክስቷ ቤት እንደ ለመደችው ትዘባነንብን ጀመች እንዲህ ስትል ስትል ከሪቻርድ ሔር ተዋወቀች "
ወይዘሮ ሳቤላ ' ቶሎ ቀና ብላ አየቻት
« የሚስተር ጀስቲስ ሔር ብቸኛ ወንድ ልጅና ! የሚስ ባርባራ ወንድም ነው አፊ ፊት ስትሰጠው ጊዜ ፍቅር ያዘው ከዚያም ቀስ በቀስ ሌሎችንም መሳብ ጀመረች አባታችን በሥራ ምክንያት ከቤት በማይኖርበት ጊዜ አጫፋሪዎቿ
የፈለገችውን እየያዘች ከቤት ታመሻለች።
« ከብዙ ወዳጆቿ አንዱና ዋናው ሪቻርድ ሔር ነበር ሌላ ደግሞ ራቅ ካለ ቦታ በፈረስ እየመጣ የሚጠይቃት ወዳጅ ነበራት " እሱ ግን አስከዚህም የነበረ አይመስለኝም " ከሚስተር ሪቻርድ ሔር ጋር የነበራት ግንኙነት ግን አባቴን እስከ ገደለበት ድረስ ቀጠለ "
« ማን ? » አለች ሳቤላ ድንግጥ ብላ ።
« ሪቻርድ ሔር ነዋ . . .እሜቴ » አባቴ እነዚህ የትልቅ ሰዎች ልጆች ድሆች ሴቶች ልጆችን የሚከታተሏቸው ለጋብቻ እያሰቧቸው እንዳልነበር ያውቅ ነበር በርግጥ በሚስተር ሪቻርድ ቀና አመለካከት ባይኖረውና በአፊጉዳት ያደርሳል ብሎ
ቢጠረጥረው ኖሮ ጠበቅ ያለ ገደብ ይፈጥር ነበር " አንድ ቀን ዌስት ሊን ላይ ስዎች የሷን ስም ከሪቻርድ ጋር አዳብለው በክፉ ሰያነሡት ሰማ ማታ ሲጠጣ እኔ ባለሁበት ከሪቻርድ ጋር ያላት ግንኙነት እንዳይቀጥል እሷም ፊት እንዳትሰጠ ለአፊ ነገራት " ይገርምዎታል በበነጋው ማታ ሪቻርድ ሔር አባቴን በጥይት ገደለው » አለቻት።
« አቤት እንዴት ያሳዝናል ልጀ ! »
« ታዲያ ይህ ነገር ሆነ ተብሎ የተፈጸመ ይሁን ወይም ካለመጠንቀቅ ጠበንጃው ጋር ሲታገል ይባርቅበት አልታወቀም ሕዝቡ በማን አለብኝነት የተፈጸመ
👍17