#ሮዛ_2
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት( 🔞)
(የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#የሰው_ ልጅ_ዓለምን_ አትርፎ #ነፍሱን_ቢበድል....
ቤይሩት፣ ራፊቅ ሀሪሪ አየር መንገድ
አርብ ሌሊት
በምድር ላይ እጅግ ከምጠላቸው ሕዝቦች መሀል እገኛለሁ፤ ሊባኖስ ቤይሩት አየር መንገድ ውስጥ፤
ወደ አቡዳቢ ለመብረር። አየርመንገዱ በአረቦች ታፍኗል። አረብ አረብ ይሸታል። የተቀቡት ሽቶ አልተስማማኝም፤ እነሱን እንዲህ በጅምላ ማየት ራሱ ያቅለሸልሻል። አመመኝ።
ክትፎ የሚወድ ሰው ጣባውን ሲከፍተው የሚዝለገለጉ ትላትሎች ታጭቀው ቢያይ ሊሰማው የሚችለው ስሜት እኔ አረቦችን እንዲህ ብዙ ሆነው በማየቴ ተሰምቶኛል። አዲስ አበባ በተናጥል አገኛቸው ስለነበር
ለነሱ ያለኝ የጥላቻ ስሜት የዛሬውን ያህል አልበረታብኝም ነበር። አሁን አንድ ሙሉ ተርሚናል በሺ በሚቆጠሩ አረቦች ተሞልቶ ብመለከት ምግብ አልረጋ አለኝ። አመመኝ።
ከአረቦቹ መሀል ብዙ መልካምና ደጋግ ሊኖሩ እንደሚችሉ እረዳለሁ፤ የበርካታ ሺህ ወገኖቼ ህይወት በነሱ ላይ እንደተመሰረተም አውቃለሁ፤ ወላጅ አልባ ህጻናት የሚያሳድጉ ደጋግ አረቦች ብዙ አሉ፤ ይህንንም አልከድም። በሀገሬም ሆነ በሀገራቸው ከወገኖቼ ጋ ፍቅር መስርተው የወለዱና የከበዱ አረቦች
እንዳሉም አልክድም።ለወደዱት ሰው ቤት ንብረታቸውን በሙሉ የሚሰጡ፣ ሀበሻ ሰራተኞቻቸው ሲታመሙ ሚሊዮን ብር ከስከሰው ያሳከሙ አረቦች እንዳሉም ከዚያ የተመለሱ ጓደኞቼ ሲያወሩ
ሰምቻለሁ። እርግጥ ነው፤ የትኛውም ህዝብ ሰናይና እኩይ ሰዎች አሉት፤ አረቦቹም ከዚያ የተለዩ እንዳልሆኑ ጠንቅቄ አውቀዋለሁ።ይህን ሁሉ እየተረዳሁ ግን ለአረቦች ስር የሰደደ ጥላቻ ደሜ ዉስጥ ገብቷል፤ ምን ላድርግ?
ህሊናዬን በብርቱ ከፈተነ ማሰላሰልና መብሰልሰል በኋላ የህይወቴ ቀጣዩ ምእራፍ በአረብ ምድር እንዲሆን ወሰንኩ። በተባበሩት ኢምሬትስ ርእሰ መዲና አቡዳቢ ሬስቶራንትና የውበት ሳሎን ያላትን የአብሮ አደጌን የቢዝነስ አጋርነት ግብዣ ለአመታት አሻፈረኝ ብልም ሰሞኑን ውሳኔዬን ከብዙ የአእምሮ
ጂምናስቲከ በኋላ ቀየርኩ፤ ከዚህ በኋላ እንዴትም ብዬ የህይወት አቅጣጫዬን መለወጥ እንዳለብኝ ተሰምቶኛል።
#ተርሚናሉ_ዉስጥ
.
አረብ ወንዶች ያለመጠን የተርከፈከፉት ሽቶ ራሴ ላይ ወጣ። ተርሚናሉ ዉስጥ እየተዝለገለጉ ወዲያ ወዲህ ሲሉ ሆዴ ታወከ። መታጠቢያ ቤት ሄጄ ፊቴን በቀዝቃዛ ዉኃ ነከርኩ። ትንሽ ሻል ያለ
ስሜት ሲሰማኝ በወርቅ የተለበጠ ከሚመስል አግዳሚ ወንበር ላይ አንድ ጥግ ይዤ አረፍ አልኩኝ።
ለጊዜው በዙርያዬ የሚሆነውን ከማየት ዉጭ ሌላ እድል አልነበረኝም። አይኔን ብጨፍንም አረቦችን አያለሁ። አይኔን ብገልጥም አረቦችን አያለሁ። አማራጭ አልነበረኝም። ለካንስ አይንን መጨፈን ማየት የሚፈልጉትን ከማየት አይጋርድም። ዳያሪዬን ከእጅ ቦርሳዬ ዉስጥ ብታቀፈውም አእምሮዬ ባልተለመደ ሁኔታ ደንዝዞብኛል። በአየር መንገዱ አግዳሚ ቁጭ ብዬ ወጪ ወራጁን ስሜት አልባ ሆኜ አያለሁ።
የአረብ ጎታታ ወንዶች፣ በዚያ በሚዝለገለግ ነጭ ቀሚሳቸው ዉስጥ ሆነው አውሮፕላን ለመሳፈር እንደ
ግመል ይጎተታሉ። የቀሚሳቸው መጎተት ላያንስ በሩዝ የተወደረ ከርሳቸውን ይጎትታሉ፤ የከርሳቸው ሳያንስ ኩንታል ሻንጣቸውን ይጎትታሉ። የሻንጣቸው ሳያንስ ነጠላ ጫማቸውን ይጎትታሉ፤ የነጠላ ጫማቸው ሳያንስ ከረፈፍ ሚስቶቻቸውን ይጎትታሉ፣ የሚስቶቻቸው ሳያንስ ያልተቆነጠጡ አስራ ምናምን ልጆቻቸውን ይጎትታሉ። አራት ሚስቶቻቸውን እየነዱም ቢሆን አምስተኛ ሴት ከማየት አይመለሱም። ከአንድም ሁለት ሦስት አጁዛ አረቦች ከወዲያኛው የተርሚናሉ ሬስቶራንት ሆነው
እየሰረቁ ሲመለከቱኝ ዐይቻለሁ፡፡
በድጋሚ መታጠቢያ ቤት ሄጄ ተመለስኩ። ዛሬ ምግብ አልረጋ ብሎኛል።
ቀልቤ አይወዳቸውም። በተለይ እንዲህ ነጭ ቆብ በነጭ ቀሚስ ለብሰው ሳያቸው፣ በነጭ ኩባያ ወተት ከአናታቸው እየፈሰሰባቸው ስለሚመስለኝ የዝንብ አየር ማረፍያዎች እንጂ ሰዎች ሆነው አይታዩኝም።ሰው ነጭ ለብሶም ንፁህ ሆኖ ካልታየኝ መቼስ የሆነ ችግር አለበት ማለት ነው። ለምንድነው ፈጣሪ እኛን
ድሐ እነሱን ሐብታም ያረገው? እግዜር ምናቸው ማርኮት ይሆን አሻዋቸውን የባረከው? በረሃቸውን ያረጠበው?!
“የአረብ ጥላቻ የተፈጠረብኝ መቼ ነው?” ብዬ ለማስታወስ ሞከርኩ። ትዝ የሚለኝ ነገር የለም። ምናልባት ኡስማን ዘ ፒምፕ ስለሚጠላቸው እሱ ሳያውቀው አጋብቶብኝ ይሆን? አይደለም። ኡስማንን
ሳላውቀው በፊት አረብ የሚባል ፍጥረት ያስጠላኝ ነበር። ልጅ እያለሁ የጀመረኝ ይመስለኛል። አያቴ በነበረችበት ሰፈር። ባደኩበት ሰፈር፣ በነእማማ ዙበይዳ ሰፈር።
ልጅ እያለሁ ለተወሰነ ጊዜ ሴት አያቴ ታሳድገኝ ነበር። በሰፈራችን የምንወዳቸው፣ እማማ ዙበይዳ
የሚባሉ ሴት ነበሩ። የሆኑ ደርባባ አሮጊት ሴትዬ። ሰው ዝም ብሎ ይወዳቸው ነበር። ጎመን መንገድ ላይ ይሸጣሉ። በክረምት ደግሞ በቆሎ ይሸጣሉ። እማማ ዙበይዳን ሰፈሩ ሁሉ ለምን ይወዳቸው እንደነበር ግን በትክክል አላውቅም። እኔም እወዳቸው ነበር። ለምን እንደነበር ግን አላውቅም። “ነይ እስቲ አንቺ
ጎራዳ!" እያሉ ግንባሬን ይስሙኝ እንደነበር ብቻ ነው ትዝ የሚለኝ።
እማማ ዙበይዳ ባልም ዘመድም የላቸውም። በምድር ላይ ያለቻቸው ፋጤ ቀጮ ናት። የሳቸው ብቸኛ ልጅ ፉጤ ቀጮ ጅዳ ሄደች ተባለ። ሰፈሩ ሁሉ እማማ ዙበይዳ በቃ ሻሩ፣ አሁን ወርቅ በወርቅ ሊሆኑ ነው ብሎ ተነበየ። እሳቸውን ያገኘ ሰው ሁሉ “ፋጤ ቀጮ ጅዳ ነው አይደል የሄደችው?”፣
ትደውላለች”፣ “ደህና ናት ታዲያ፣ “አሁን ለመድኩ አለችፖ፣ ግህም፣ “በርቺ በሏት እንግዲህ!
ይለመዳል.ይለመዳል”፣ “ዋናው መበርታት ነውታዲያ”፣ “እ!” እያለ ከእማማ ዙበይዳ የበቆሎ እሸት
ወይ ጎመን ገዝቷቸው ያልፋል። በበጋ ጎመን በከረምት የበቆሎ እሸት በመሸጥ ነበር የሚተዳደሩት።
በዚያ ሁሉ የሰፈር ሰው ሳይታክቱ በዚያ እናታዊ ፈገግታቸው ታጅበው ስለ ልጃቸው ደኅንነት ምላሽ ይሰጣሉ። “እላሙዲሊላ አላሂ ወላሂ ደህና ናት!ዱዋ አርጉላት." ይላሉ፤ መልሰው መላልሰው።
ሲኖሩ ሲኖሩ.…የሆነ ጊዜ ላይ ልጃቸው ስልክ ደውላ አለቀሰች ተባለ። “ምን ሆንሽ” ሲሏት አትናገርም
ሲኖሩ ሲኖሩ…የሆነ ጊዜ ላይ ደግሞ መደወል አቆመች ተባለ። ደህንነቷን የሚነግራቸው ጠፋ። ጎመን ወይ
በቆሎ ለሚገዛቸው የሰፈር ሰው ሁሉ “አረብ አገር ስልክ ማድረግ ታውቅበታለህ?” እያሉ ይጠይቃሉ።
የተማረ የሚመስል ወጣት ሲመለከቱ ደግሞ “ልጄ! እስኪ ባክህ የጅዳ ስልክ ቁጥር ጽፈህ አምጣልኝ? ልጄ ናፈቀችኝ ይሉታል። የሷ ስልክ ቁጥር ግን የላቸውም። አንዳንድ ሰው ነገሩን ሊያስረዳቸው ሞከረ።ኾኖም ሊገባቸው አልቻለም። የሰፈሩን ሰው መሄጃ መቀመጫ አሳጡት። እርስዎ ስልኳን ፈልገው ያምጡ! እኛ እንደውልሎታለን” ሲባሉ እኔ ቁጥሯን ከየት አዉቄ” ነው መልሳቸው። እሷ ካልደወለች
እሳቸው ወደየት ብለው ይደውላሉ? አድራሻዋ አይታወቅ ነገር።
የሰፈሩ ሰው በሙሉ እማማ ዙበይዳ ሲያዝኑ አይቶ አዘነ። እማማ ዙበይዳ የደግነት ምሳሌ ነበሩ። ፋጤ
ቀጮ እጅግ ስትናፍቃቸው ግን ሰው ሰላም ሳይሉ ማለፍ ሁሉ ጀመሩ። የሚሸጡት ጎመን ጠወለገ።
ወዲያው ደግሞ ወገባቸው ጎበጠ። ከመቼው በእድሜያቸው ላይ ምዕተ ዓመት እንደጨመሩ። ሰው የልጁ ናፍቆት እንደ ኤድስ አመንምኖ ሊገድለው እንደሚችል ያየሁት በእማማ ዙበይዳ ነው።
ከ5 ዓመታት በኋላ ልጃቸው ፋጤ መጣች ተባለ። በዊልቸር ላይ ሆና። በጣም ከመወፍሯ የተነሳ ዊልቸሩ ጠበባት። ፋጤ ቀጮ ትባል የነበረችው የሆነች ሲንቢሮ በረሮ ስለበረች ነበር።ታዲያ ለምን ወፈረች? ተስማምቷት ነበር ማለት ነው?
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት( 🔞)
(የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#የሰው_ ልጅ_ዓለምን_ አትርፎ #ነፍሱን_ቢበድል....
ቤይሩት፣ ራፊቅ ሀሪሪ አየር መንገድ
አርብ ሌሊት
በምድር ላይ እጅግ ከምጠላቸው ሕዝቦች መሀል እገኛለሁ፤ ሊባኖስ ቤይሩት አየር መንገድ ውስጥ፤
ወደ አቡዳቢ ለመብረር። አየርመንገዱ በአረቦች ታፍኗል። አረብ አረብ ይሸታል። የተቀቡት ሽቶ አልተስማማኝም፤ እነሱን እንዲህ በጅምላ ማየት ራሱ ያቅለሸልሻል። አመመኝ።
ክትፎ የሚወድ ሰው ጣባውን ሲከፍተው የሚዝለገለጉ ትላትሎች ታጭቀው ቢያይ ሊሰማው የሚችለው ስሜት እኔ አረቦችን እንዲህ ብዙ ሆነው በማየቴ ተሰምቶኛል። አዲስ አበባ በተናጥል አገኛቸው ስለነበር
ለነሱ ያለኝ የጥላቻ ስሜት የዛሬውን ያህል አልበረታብኝም ነበር። አሁን አንድ ሙሉ ተርሚናል በሺ በሚቆጠሩ አረቦች ተሞልቶ ብመለከት ምግብ አልረጋ አለኝ። አመመኝ።
ከአረቦቹ መሀል ብዙ መልካምና ደጋግ ሊኖሩ እንደሚችሉ እረዳለሁ፤ የበርካታ ሺህ ወገኖቼ ህይወት በነሱ ላይ እንደተመሰረተም አውቃለሁ፤ ወላጅ አልባ ህጻናት የሚያሳድጉ ደጋግ አረቦች ብዙ አሉ፤ ይህንንም አልከድም። በሀገሬም ሆነ በሀገራቸው ከወገኖቼ ጋ ፍቅር መስርተው የወለዱና የከበዱ አረቦች
እንዳሉም አልክድም።ለወደዱት ሰው ቤት ንብረታቸውን በሙሉ የሚሰጡ፣ ሀበሻ ሰራተኞቻቸው ሲታመሙ ሚሊዮን ብር ከስከሰው ያሳከሙ አረቦች እንዳሉም ከዚያ የተመለሱ ጓደኞቼ ሲያወሩ
ሰምቻለሁ። እርግጥ ነው፤ የትኛውም ህዝብ ሰናይና እኩይ ሰዎች አሉት፤ አረቦቹም ከዚያ የተለዩ እንዳልሆኑ ጠንቅቄ አውቀዋለሁ።ይህን ሁሉ እየተረዳሁ ግን ለአረቦች ስር የሰደደ ጥላቻ ደሜ ዉስጥ ገብቷል፤ ምን ላድርግ?
ህሊናዬን በብርቱ ከፈተነ ማሰላሰልና መብሰልሰል በኋላ የህይወቴ ቀጣዩ ምእራፍ በአረብ ምድር እንዲሆን ወሰንኩ። በተባበሩት ኢምሬትስ ርእሰ መዲና አቡዳቢ ሬስቶራንትና የውበት ሳሎን ያላትን የአብሮ አደጌን የቢዝነስ አጋርነት ግብዣ ለአመታት አሻፈረኝ ብልም ሰሞኑን ውሳኔዬን ከብዙ የአእምሮ
ጂምናስቲከ በኋላ ቀየርኩ፤ ከዚህ በኋላ እንዴትም ብዬ የህይወት አቅጣጫዬን መለወጥ እንዳለብኝ ተሰምቶኛል።
#ተርሚናሉ_ዉስጥ
.
አረብ ወንዶች ያለመጠን የተርከፈከፉት ሽቶ ራሴ ላይ ወጣ። ተርሚናሉ ዉስጥ እየተዝለገለጉ ወዲያ ወዲህ ሲሉ ሆዴ ታወከ። መታጠቢያ ቤት ሄጄ ፊቴን በቀዝቃዛ ዉኃ ነከርኩ። ትንሽ ሻል ያለ
ስሜት ሲሰማኝ በወርቅ የተለበጠ ከሚመስል አግዳሚ ወንበር ላይ አንድ ጥግ ይዤ አረፍ አልኩኝ።
ለጊዜው በዙርያዬ የሚሆነውን ከማየት ዉጭ ሌላ እድል አልነበረኝም። አይኔን ብጨፍንም አረቦችን አያለሁ። አይኔን ብገልጥም አረቦችን አያለሁ። አማራጭ አልነበረኝም። ለካንስ አይንን መጨፈን ማየት የሚፈልጉትን ከማየት አይጋርድም። ዳያሪዬን ከእጅ ቦርሳዬ ዉስጥ ብታቀፈውም አእምሮዬ ባልተለመደ ሁኔታ ደንዝዞብኛል። በአየር መንገዱ አግዳሚ ቁጭ ብዬ ወጪ ወራጁን ስሜት አልባ ሆኜ አያለሁ።
የአረብ ጎታታ ወንዶች፣ በዚያ በሚዝለገለግ ነጭ ቀሚሳቸው ዉስጥ ሆነው አውሮፕላን ለመሳፈር እንደ
ግመል ይጎተታሉ። የቀሚሳቸው መጎተት ላያንስ በሩዝ የተወደረ ከርሳቸውን ይጎትታሉ፤ የከርሳቸው ሳያንስ ኩንታል ሻንጣቸውን ይጎትታሉ። የሻንጣቸው ሳያንስ ነጠላ ጫማቸውን ይጎትታሉ፤ የነጠላ ጫማቸው ሳያንስ ከረፈፍ ሚስቶቻቸውን ይጎትታሉ፣ የሚስቶቻቸው ሳያንስ ያልተቆነጠጡ አስራ ምናምን ልጆቻቸውን ይጎትታሉ። አራት ሚስቶቻቸውን እየነዱም ቢሆን አምስተኛ ሴት ከማየት አይመለሱም። ከአንድም ሁለት ሦስት አጁዛ አረቦች ከወዲያኛው የተርሚናሉ ሬስቶራንት ሆነው
እየሰረቁ ሲመለከቱኝ ዐይቻለሁ፡፡
በድጋሚ መታጠቢያ ቤት ሄጄ ተመለስኩ። ዛሬ ምግብ አልረጋ ብሎኛል።
ቀልቤ አይወዳቸውም። በተለይ እንዲህ ነጭ ቆብ በነጭ ቀሚስ ለብሰው ሳያቸው፣ በነጭ ኩባያ ወተት ከአናታቸው እየፈሰሰባቸው ስለሚመስለኝ የዝንብ አየር ማረፍያዎች እንጂ ሰዎች ሆነው አይታዩኝም።ሰው ነጭ ለብሶም ንፁህ ሆኖ ካልታየኝ መቼስ የሆነ ችግር አለበት ማለት ነው። ለምንድነው ፈጣሪ እኛን
ድሐ እነሱን ሐብታም ያረገው? እግዜር ምናቸው ማርኮት ይሆን አሻዋቸውን የባረከው? በረሃቸውን ያረጠበው?!
“የአረብ ጥላቻ የተፈጠረብኝ መቼ ነው?” ብዬ ለማስታወስ ሞከርኩ። ትዝ የሚለኝ ነገር የለም። ምናልባት ኡስማን ዘ ፒምፕ ስለሚጠላቸው እሱ ሳያውቀው አጋብቶብኝ ይሆን? አይደለም። ኡስማንን
ሳላውቀው በፊት አረብ የሚባል ፍጥረት ያስጠላኝ ነበር። ልጅ እያለሁ የጀመረኝ ይመስለኛል። አያቴ በነበረችበት ሰፈር። ባደኩበት ሰፈር፣ በነእማማ ዙበይዳ ሰፈር።
ልጅ እያለሁ ለተወሰነ ጊዜ ሴት አያቴ ታሳድገኝ ነበር። በሰፈራችን የምንወዳቸው፣ እማማ ዙበይዳ
የሚባሉ ሴት ነበሩ። የሆኑ ደርባባ አሮጊት ሴትዬ። ሰው ዝም ብሎ ይወዳቸው ነበር። ጎመን መንገድ ላይ ይሸጣሉ። በክረምት ደግሞ በቆሎ ይሸጣሉ። እማማ ዙበይዳን ሰፈሩ ሁሉ ለምን ይወዳቸው እንደነበር ግን በትክክል አላውቅም። እኔም እወዳቸው ነበር። ለምን እንደነበር ግን አላውቅም። “ነይ እስቲ አንቺ
ጎራዳ!" እያሉ ግንባሬን ይስሙኝ እንደነበር ብቻ ነው ትዝ የሚለኝ።
እማማ ዙበይዳ ባልም ዘመድም የላቸውም። በምድር ላይ ያለቻቸው ፋጤ ቀጮ ናት። የሳቸው ብቸኛ ልጅ ፉጤ ቀጮ ጅዳ ሄደች ተባለ። ሰፈሩ ሁሉ እማማ ዙበይዳ በቃ ሻሩ፣ አሁን ወርቅ በወርቅ ሊሆኑ ነው ብሎ ተነበየ። እሳቸውን ያገኘ ሰው ሁሉ “ፋጤ ቀጮ ጅዳ ነው አይደል የሄደችው?”፣
ትደውላለች”፣ “ደህና ናት ታዲያ፣ “አሁን ለመድኩ አለችፖ፣ ግህም፣ “በርቺ በሏት እንግዲህ!
ይለመዳል.ይለመዳል”፣ “ዋናው መበርታት ነውታዲያ”፣ “እ!” እያለ ከእማማ ዙበይዳ የበቆሎ እሸት
ወይ ጎመን ገዝቷቸው ያልፋል። በበጋ ጎመን በከረምት የበቆሎ እሸት በመሸጥ ነበር የሚተዳደሩት።
በዚያ ሁሉ የሰፈር ሰው ሳይታክቱ በዚያ እናታዊ ፈገግታቸው ታጅበው ስለ ልጃቸው ደኅንነት ምላሽ ይሰጣሉ። “እላሙዲሊላ አላሂ ወላሂ ደህና ናት!ዱዋ አርጉላት." ይላሉ፤ መልሰው መላልሰው።
ሲኖሩ ሲኖሩ.…የሆነ ጊዜ ላይ ልጃቸው ስልክ ደውላ አለቀሰች ተባለ። “ምን ሆንሽ” ሲሏት አትናገርም
ሲኖሩ ሲኖሩ…የሆነ ጊዜ ላይ ደግሞ መደወል አቆመች ተባለ። ደህንነቷን የሚነግራቸው ጠፋ። ጎመን ወይ
በቆሎ ለሚገዛቸው የሰፈር ሰው ሁሉ “አረብ አገር ስልክ ማድረግ ታውቅበታለህ?” እያሉ ይጠይቃሉ።
የተማረ የሚመስል ወጣት ሲመለከቱ ደግሞ “ልጄ! እስኪ ባክህ የጅዳ ስልክ ቁጥር ጽፈህ አምጣልኝ? ልጄ ናፈቀችኝ ይሉታል። የሷ ስልክ ቁጥር ግን የላቸውም። አንዳንድ ሰው ነገሩን ሊያስረዳቸው ሞከረ።ኾኖም ሊገባቸው አልቻለም። የሰፈሩን ሰው መሄጃ መቀመጫ አሳጡት። እርስዎ ስልኳን ፈልገው ያምጡ! እኛ እንደውልሎታለን” ሲባሉ እኔ ቁጥሯን ከየት አዉቄ” ነው መልሳቸው። እሷ ካልደወለች
እሳቸው ወደየት ብለው ይደውላሉ? አድራሻዋ አይታወቅ ነገር።
የሰፈሩ ሰው በሙሉ እማማ ዙበይዳ ሲያዝኑ አይቶ አዘነ። እማማ ዙበይዳ የደግነት ምሳሌ ነበሩ። ፋጤ
ቀጮ እጅግ ስትናፍቃቸው ግን ሰው ሰላም ሳይሉ ማለፍ ሁሉ ጀመሩ። የሚሸጡት ጎመን ጠወለገ።
ወዲያው ደግሞ ወገባቸው ጎበጠ። ከመቼው በእድሜያቸው ላይ ምዕተ ዓመት እንደጨመሩ። ሰው የልጁ ናፍቆት እንደ ኤድስ አመንምኖ ሊገድለው እንደሚችል ያየሁት በእማማ ዙበይዳ ነው።
ከ5 ዓመታት በኋላ ልጃቸው ፋጤ መጣች ተባለ። በዊልቸር ላይ ሆና። በጣም ከመወፍሯ የተነሳ ዊልቸሩ ጠበባት። ፋጤ ቀጮ ትባል የነበረችው የሆነች ሲንቢሮ በረሮ ስለበረች ነበር።ታዲያ ለምን ወፈረች? ተስማምቷት ነበር ማለት ነው?
👍4
#የሰው_ነገር (1)
በዚህች
ውሸት በነገሰችበት
እውነት አንገቷን በደፋችበት ፤
ያወራ በሚከብርባት
የሰራ በሚገፋባት
..........ደሴት ውስጥ
በዚህች
አህዛብ ባልተማረባት
የተማረም በማያውቅባት፤
ልብሷን በተገፈፈች
እርቃኗን ገጣ በቆመች
...........ደሴት ውስጥ
በዚህች
መጠላለፍ በበዛባት
ጭፍን ፈራጅ በሞላባት፤
ሆድ ዕቃ በገዘፈባት
ህሊና በኮስሰባት
..........ደሴት ውስጥ
በድንን ሳይሆን ህይወትን
ቅርጥፍ አድርጎ የሚበላ
........
ሰው ራሱ ነው የሰው ምስጥ፡፡
🔘በሙሉቀን🔘
በዚህች
ውሸት በነገሰችበት
እውነት አንገቷን በደፋችበት ፤
ያወራ በሚከብርባት
የሰራ በሚገፋባት
..........ደሴት ውስጥ
በዚህች
አህዛብ ባልተማረባት
የተማረም በማያውቅባት፤
ልብሷን በተገፈፈች
እርቃኗን ገጣ በቆመች
...........ደሴት ውስጥ
በዚህች
መጠላለፍ በበዛባት
ጭፍን ፈራጅ በሞላባት፤
ሆድ ዕቃ በገዘፈባት
ህሊና በኮስሰባት
..........ደሴት ውስጥ
በድንን ሳይሆን ህይወትን
ቅርጥፍ አድርጎ የሚበላ
........
ሰው ራሱ ነው የሰው ምስጥ፡፡
🔘በሙሉቀን🔘
👍1
#የሰው_ነገር (2)
በዚህች
በሰው በተገነባች
በሰው በተከበበች ፤
ስለሰው ተብላ ተፈጥራ
ስለ ሰው ስትል በኖረች
..........ደሴት ውስጥ
በዚህች
ሰዎች በመጠቁባት
ተመራምረው ባወቁባት፤
ግዙፍና ሩቅ እያለች
ትንሽ መንደር በመሰለች
.............ደሴት ውስጥ
በዚህች
በህብረ ቀለም ተውባ
በተፈጥሮዋ አብባ፤
ሰርክ አዲስ በሚታይባት
ተዓምር በሚሰማባት
...........ደሴት ውስጥ
ለሰው ልጅ ራሱ ሰው ነው
ችግርን አብሮ ተካፍሎ
......ለህይወት ተስፋን የሚሰጥ፡፡
🔘በሙሉቀን🔘
በዚህች
በሰው በተገነባች
በሰው በተከበበች ፤
ስለሰው ተብላ ተፈጥራ
ስለ ሰው ስትል በኖረች
..........ደሴት ውስጥ
በዚህች
ሰዎች በመጠቁባት
ተመራምረው ባወቁባት፤
ግዙፍና ሩቅ እያለች
ትንሽ መንደር በመሰለች
.............ደሴት ውስጥ
በዚህች
በህብረ ቀለም ተውባ
በተፈጥሮዋ አብባ፤
ሰርክ አዲስ በሚታይባት
ተዓምር በሚሰማባት
...........ደሴት ውስጥ
ለሰው ልጅ ራሱ ሰው ነው
ችግርን አብሮ ተካፍሎ
......ለህይወት ተስፋን የሚሰጥ፡፡
🔘በሙሉቀን🔘