አትሮኖስ
286K subscribers
119 photos
3 videos
41 files
568 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_አንድ


#በአሌክስ_አብርሃም

የዛሬ አሥራ ሦስት ዓመት እግዚእብሔርን ለመሆን ተመኝቼ ነበር፤ አልተሳካልኝም፡፡ .
እግዚእብሐርን መሆን ስላልተሳካልኝ “በቃ ለምን ሰይጣን አልሆንም?” የሚል ሐሳብ
ውል ብሎብኝ፡ ሰይጣን ለመሆን ሞከርኩ እሱም ቢሆን እንዲህ እንደሚወራው ቀላል አልነበረም(ክፋት በሰይጣን እጅ ያምር፤ሲይዙት ያደናግር) እንግዲህ ሁለቱንም ካልሆንኩ ራሴን ልሁነውና የመጣውን ልጋፈጠው” ብዬ እግዜርነትንና ሰይጣንነት ልለካ አውልቄ ያስቀመጥኩትን እኔነት ፍለጋ ዙሪያዬን ባስስ ራሴም የለሁም፡፡ ይሄ ደግሞ ማነው?” እስክል ራሴን ፈጽሞ የማላውቀው አዲስ ፍጡር ሆኖ አገኘሁት፡፡ይኼው እስራ ሦስት ዓመት ጊዜ ፈጣን ነው፡፡ እንደ ደራሽ ጎርፍ ጠራርጎ የማይወሰድብን እያግበሰበሰም አምጥቶ የማይጭንብን ጉድ የለም፡፡

የአሥራ ሁለተኛ ክፍል የማትሪክ ውጤት የተነገረበት ሰሞን ነበር፤ ከብዙዎች ተመርጠን ወደ ዩኒቨርስቲ መግቢያ ከፍተኛ ውጤት ስላመጣን “በምድር ላይ መከፈት የማንችለው በር የለም! የሚል የወጣትነት የዋህ ትዕቢት፣ ወጣት ልባችንን የሞላበት ጊዜ፣ የሰፈሩ
ወጣት ሴቶች እናተ ልጆች ያሻችሁን ጠይቁን” በሚል ዘወርዋራ ፈገግታ፡ የዕድሜ እኩያ እንዳልገንን ሁሉ ለትልቅ ሰው ከሚሰጥ አክብሮት ጋር ይሽኮረመሙልን የነረበት ጊዜ( ለእናተ ያልሆነ ሴትነት ዓይነት) ትምህርት ላይ ደከም ያሉ የሰፈራችን ልጆች
በወላጆቻቸው እንደነሱ አትሆኑም?” እየተባሉ ስማችን ከኩርኩም ዝናብ በፊት
እንደመብረቅ ጆሯቸው ላይ ይንባረቅባቸው የነበረበት ጊዜ “ምነው እነዚህን ልጆት ከዚህ ሰፈር በነቀለልን”ብለው በሆዳቸው ሳይረግሙን አልቀሩም (መማር ባይሆንላቸው
መራገም አያቅታቸው) አላፊ አግዳሚው በኩራት ፈገገ ይልልን በነበረበት ጊዜ ይኼም ፈገግታ ትምህርት ሚንስቴር እውቅና ሰጥቶቷቸው ከፈተነን “ኬሚስትሪና ማተማቲክስ ምናምን 'ሰብጀክቶች በላይ፡ የሰፈሩ ሰው በአደራ ሰጥቶን በከፍተኛ ውጤት ላለፍነው
“በጎ አርአያነት ነፍሳችን ካርድ ላይ የሚያስቀምጠው “A” በነበረ ጊዜ
ያ ጊዜ ሕይወት ያለ የሌለ እንደ በረዶ የነጣ ጥርሷን ፈገግ ብላ ታሳየን የነበረችበት የክረምት ወር ነበር፡፡ ለእኔና ለጓደኛዩ መሐሪ! “ምን ጓደኛ ናቸው እነዚህ፣ ወንድማማች እንጂ እማምላክንም ይሉ ነበር የሚያውቁን ሁሉ፡፡ አልተጋነነም፡፡ አንድ ሰፈር ነው
ተወልደን ያደግነው፡፡ በቤታችንና በቤታቸው መሃል ያሉት አንድ አምስት ቤቶችና፣የሰፈሩ ልጆች ኳስ የምንጫወትበት አቧራማ ሜዳ ብቻ ነበሩ የመሃሪ እናት ዝንጥ ያለች የቢሮ ሠራተኛ ነበረች፡ ማሚ የምንላት መልከመልካም እናት፤ አገር ምድሩ እትዬ ሮሚ” የሚላት፡ ዘርፋፋ ባለ ከሸከሽ ቀሚስ በመቀነት ሸብ አድርገው ነጠላ በሚያጣፉ እናቶች መሃል ጉልበቷ ድረስ ያጠረ ቀሚስ የምትለብስ፣ ቀጥ ያለ አቋም ያላትና ጸጉሯን ባጭሩ የምትቆረጥ በእውቅ የተቀረጹ ዓምዶች በመሳሰሉ ውብ ጠይም እግሮቿ በተራመደች ቁጥር፣ እንደ ሙዚቃ በተመጠነ ርቀት ቋ ቋ ቋ የሚል ድምፅ በሚያወጣ ባለረዥም ተረከዝ ጫማ የምትውረገረግ ዘመናዊ እናት፡፡ ባሏ የጸሐፊነት ሥራዋን እንድታቆም አድርጓት በኋላ ተወችው እንጂ፡ በፊት በፊት መሐሪን ጧት እቤታችን አምጥታ ለእናቴ ትተወውና ወደ ሥራዋ ትሄዳለች፤ ስትመለስ ትወስደዋለች።አብረን ነው ያደግነው፡፡ ነገሩ ዋጋ ተቆርጦለት የልጅ ጠባቂነት አይሁን እንጂ፡ ለቤተሰቦቼ
በሰበብ አስባቡ ገንዘብም ቁሳቁስም መደገፏ አይቀርም ነበር፡፡ ከዚያ
ዕድሜያችን ጀምሮ እኔም ሆንኩ መሐሪ ሌሎች የመንደሩ ልጆች ጋር ቅርበታችን
እምብዛም ነበር፡፡

ማሚ ሁለታችንንም ግራና ቀኝ ይዛን ቄስ ትምህርት ቤት ስትወስደን ትዝ ይለኛል፡፡
በሕፃንነት ዕድሜያችን (አምስት ዓመት ቢሆነን ነው) ያኔ መንገድ ላይ ሰላም ያሏትን ሰዎች ስም ዝርዝር ብባል፣ አንድ ባንድ አስታውሳቸዋለሁ፤ በተለይ ወንዶቹ
የሚያሽቆጠቁጣቸው ነገር ነበር!

ታዲያ መምሬ ምስሉ ለተባሉ ፊደል አስቆጣሪ ስታስረክበን፣ በሹክሹክታ እንዲህ ስትላቸው ሰማኋት"የኔታ አንድ ላይ ከተቀመጡ መላም የለው፧ አነጣጥለው ያስተምሯቸው መሐሪ ግን እንዲህ ስትል አልሰማኋትም አለኝ፡ አቋቋማችን እኮ ከእኔ ይልቅ እሱ ይቀርብ ነበር፡፡ ስንት ዓመት አልፎ፣ ካደግን በኋላ፣ ማሚን ስንጠይቃት “ውይ! በምን አስታወስከው ልጄ?” ብላ በሳቅ ፍርስ አለችና ብያቸዋለሁ እውነትህን ነው ብላ አመነች። መሐሪ እየሳቀ የሆነ ሼባ ነገር ነው ነገር አይረሳም አለ ሁልጊዜም
ዝንጉቱን የሚያስተባብለው፤ እኔን ነገር ከነከስኩ የማለቅ ሽማግሌ በማድርግ ነበር፡፡
ጎን ለጎን ተቀምጠን ሰዎቸ ለሁለታችንም ያወሩልንን አለፍ ስንል “ምናሉ? ብሎ
የሚጠይቅበኝ ጊዜ ብዙ ነው ለዙሪያው ቸልተኛ ነበር!

መምሬ ምስሉ የማሚን አደራ ለመጠበቅ በቁጣም በአለንጋም ሊነጣጥሉን ብለው
ብለውን አልሆን ስላላቸው እኒህ ልጆች፣ እንደ ዳዊትና የዮናታንን ጓደኝነት ነብሳቸው አብሮ የተሰፋ ነው!” ከሚል ምሳሌ ጋር እንደ ፍጥርጥራችሁ ብለው ተውን፡፡ ለረዥም ጊዜ ዳዊትና ዮናታን ረባሽ የቄስ ትምህርት ቤት ሕፃናት ይመስሉኝ ነበር፣ ሮሐ ናት በኋላ በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉ ጓደኛሞች መሆናቸውን የነገረችን (ሰንበት ትምህርት
ቤት ተማርኩ ብላ) ይኼንንም የነገረችን ቀን አብረን ሰምተን ዞር ስትል መሐሪ
ምናለች” ብሎኛል፣ አድጎም አልለቀቀው! ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አስራ ሁለተኛ ክፍል
እስክንደርስ እኔና መሐሪ ተነጣጥለን አናውቅም።አንድ ክፍል፣ አንድ ወንበር፣ አልፎ አልፎ ጎን ለጎን ያሉ ክፍሎች፡ ግን አንድ ትምህርት ቤት ነበር ያሳለፍነው።

ዐሥረኛ ክፍል ስንደርስና መሐሪ ሮሐ ከምትባል ልጅ ፍቅር ሲጀማምረው ነበር፣ ሦስተኛ ሰው አብሮን የታየው፤ያኔ ታዲያ ሮሐን ወደድኩ ሲል (ባይወዳት ነበር የሚገርመኝ ሁለታችንም ብርክ ያዘን፤ ነገሩ ጋሼ ጋር ከደረሰ ሁለታችንንም ከገጸ-ምድር ያጠፋናል የሚል ፍርሃት ነበር ያራደን፡፡ ጋሼ የምንለው የመሐሪን አባት ነው፡፡ ጋሽ ዝናቡ ዶፍ ቢሉት ይሻል ነበርኮ” እንባባላለን እኔና መሐሪ ስናማው። ጋሽ ዝናቡ ሲቆጣ፣ ቁጣው ልክ እንደ ርዕደ መሬት ከሰው አልፎ የቤቱን እቃዎችና የግቢውን ዛፎች የሚያንዘፈዝፍ ይመስል ነበር፡፡ ፊቱ የማይፈታ፣ ረዥም ቦክሰኛ የሚመስል ሰው ነበር፡፡ ዳኛ ስለሆነ ነው መስል ቤታቸው ፍርድ ቤት ነበር የሚመስለኝ፡፡ መሐሪም፣ ማሚም ተሽቆጥቁጠው ነው
የሚኖሩት፡፡ ደግነቱ ቁጣው በየአራት ዓመት አንዴ የሚከለት የተፈጥሮ አደጋ ዓይነት ነበር፡፡ ያንን መሬት አንቀጥቅጥ ቁጣውን ያስነሳሉ ተብለው በቤተሰቡ የታወቁ እና ቤተሰቡ እንደተላጠ የኤሌክትሪክ ሽቦ ላለመንካት የሚጠነቀቃቸው፣እንደ ዐሠርቱ
ትዕዛዛት ከቤተሰቡ አልፎ በእኔም ልብ በፍርሃት ፊደላት የተቀረጹ ምክንያቶች ቢበዙ ከሦስት አይበልጡም ነበር

የመጀመሪያው ምክንያት ዝርዝሩ አይገባኝም እንዲሁ እቤታቸው ጎራ ባልኩበት ጊዜ ሁሉ ከለቃቀምኩት ደመ ነፍሳዊ መረጃ ገባኝ ያልኩት ወደ እውነት የሚጠጋ ጥርጣሬ ነው በማሚ(በሚስቱ) እንደሚበሳጭ ይገባኝ ነበር …ነገረ ሥራዋ ያበሳጨዋል! ምንጊዜም እቤት ሲገባ አጋጣሚ ቤት ውስጥ ከሌለች በቁጣ ይጠይቃል “የት ሄደች?” መሐሪ በፍርሃት እየተንተባተበ ማሚ የሄደችበትን ያስረዳል፡፡ ብዙ ጊዜ ወይ የታመመ
ልትጠይቅ፣ አልያም ለቅሶ ልትደርስ ነው የሚሆነው መልሱ! ጋሽ ዝናቡ ታዲያ “የሷ ለቅሶ አያልቅም!” ይላል! ድምፁ ውስጥ መነጫነጭ አለ! ጋሽ ዝናቡ እንዲህ ይጠይቅ እንጂ፣ ማሚን እቤት ቢያገኛት ደግሞ፣ ሰላም እንኳን ሳይላት አልፎ ነበር የሚገባው…ብዙ ጊዜ እንደባልና ሚስት ፈታ ብለው አይነጋገሩም
1👍1
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_ሁለት


#በአሌክስ_አብርሃም


የሌላውን ተማሪ እንጃ፣ እኔ ግን ብርድ ብርድ ነበር የሚለኝ።ነገረ ስራዋ ሁሉ የሚሸክክ ሴትዮ።በፊቷ ላይ ሳቅም ቁጣም የለም፣ ድምፁዋ ዝቅም ከፍም አይል። እራሷ አጅብሰም ምናምን ተፈልፍላ የተሰራች እጅ ሥራ ነገር ነበር የምትመስለኝ።ገና በመጀመሪያው ቀን የእጅ ሥራ የሚባለውን ትምህርት ስንጀምር፣ ሰላም ! ከሰፈነበት ክፍላችን አሰልፋ የእግር ኳስ ሜዳውን ተሻግሮ ወደ ሚገኘው “የእጅ ሥራ ክፍሉ ወደሚባል ሕንፃ ወሰደችን፡፡ ከትልልቅ ጥርብ ድንጋዮች የተሠራና ግራጫ የሸክላ ጣሪያ
የተደፋበት ግብ ቤት ነው፡፡ በድንጋዮቹ መጋጠሚያ ላይ እረንጓዴ ሻጋታ እንደ
አረንጓዴ ሽበት የጋገረበት ጣሪያው ላይ ብዙ ሣር ያበቀለበት፣ ለሞላ የወፍ ዘር
ድብርታም ዋነሶች ብቻ የሚሰፍሩበት ዕድሜ ጠገብ ግንብ ቤት ነው፡፡ ዱሮ ጣሊያን ሰዎችን እያሰረ የሚያሰቃይበት
እስር ቤት ነበር ይባላል! በመስኮቱ ትክክል በዕድሜ ብዛት የዛገ የ በ ቅርጽ ያለው የብረት ጎል አለ፡፡እስረኞችን ከዚህ ክፍል እያወጡ እዚህ ብረት ላይ በስቅላት ይቀጧቸው ነበር፡፡ ሆነ ብለው ነው በመስኮቱ ትክክል የሰሩት፡፡
እስረኞቹ ሰው ሲሰቀል በመስኮት በኩል አሻግረው እንዲመለከቱና ሞትን ፈርተው
ጣልያንን እንዲተባበሩ፡፡ ነገሩ ነበር ብቻ ሳይሆን፣ ምስክር ያለው ታሪክም ነው።

አፈሩ ይቅለላቸውና፣ ከዓመት እስከ ዓመት የጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ጥበቃ ሆነው ይሠሩ የነበሩ፣ በየዓመቱ የአርበኞች ቀን ሲከበር ደረቱ ላይ ግራና ቀኝ ብዙ ሜዳሊያ የተደረደረበት የአርበኛ ካኪ ልብሳቸውን ለብሰውና፤ ወርቃማ የዘንባባ ጥልፍ ያለበት ባርኔጣቸውን ደፍተው፣ አሮጌ ጦር እየሰበቁ (በኋለኛው ዘመን እርጅናው ተጭኗቸው ተውት እንጂ ትልቅ ጋሻም ነበራቸው) በቴሌቪዥን የሚቀርቡት ሰውዬ ታሪክ ሲናገሩ
በጆሮዬ ሰምቻቸዋለሁ “ጥሊያን አርበኞቹ በዱር በገደል ሲያስቸግሯት፣ የአርበኞች
ቤተሰቦች ማሰቃየት ጀመረች እዚህ ታች አሁን “አጤ ብልጣሶር ተማሪ ቤት” የተባለው ውስጥ፣ የግንብ እስር ቤት ሠርታ ሰውን ሁሉ እየሰበሰበች ማጎር፣ ጠቁሙ እያለች መግረፍ፣ መስቀል ጀመረች እስከ አሁን ያ እስር ቤት ተማሪ ቤቱ ውስጥ አለ” ሲሉ ሰምቻለሁ፡፡ “ዓፄ ብልጣሶር አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት” ማለት እንግዲህ፣ የኛ ትምህርት ቤት ነው።

ያች አስተማሪ ታዲያ አሰልፋ የወሰደችን ወደዚያ ከፍል ነበር፡፡ ውስጡ በጠራራ ፀሐይ እንኳን የሚያንዘፈዝፍ ብርድ ያለበት ሰፊ አዳራሽ፣ የንብረት ማስቀመጫ ሆኖ በመከረሙና ተጸድቶ ባለማወቁ፣ እምክ እምክ የሚሸትና በአቧራ የተሸፈነ ነበር።ግማሽ የሚሆነው የአዳራሹ ክፍል ተማሪዎች ከወረቀት፣ ከካርቶን፣ ከጣውላና ከብዙ ዓይነት ቁሳቁስ በሠሯቸው የእንስሳትና ሰው ቅርጻ ቅርጾች፣ በተሰባበሩ ወንበሮች፡
በተከመሩ እሮጌ መጻሕፍትና ገና ባልተከፈቱ ብዙ ካርቶን ጠመኔዎች የተሞላ ነበር

እንግዲህ በመጀመሪያ ከፍለ ጊዜ ስሟን እንኳን በወጉ ሳታስተዋውቀን በዚያ ቅዝዝ ባለ ድምፅ ይሄን አዳራሽ አፅዱ!” አለችን፡፡ ከዚያን ቀን ጀምሮ ያ ክፍል እኔም መሐሪም ማየት ራሱ ያንገሸግሸን ነበር፡፡ ከስንት ዓመት በኋላ ትምህርት ቤቱ ሙሉ ለሙሉ ፈርሶ ሲታደስ፣ ያ…የድንጋይ ከፍል ቅርስ ነው!” ተብሎ እንዳለ ነበር የተተወው፡፡ በኋላ እኔና መሀሪ አስራ ሁለተኛ ክፍል እንደጨረስን ሮሐን በመሀላችን አድርገን በሩ ላይ ፎቶ ተነስተናል፡፡ እሷ እንዳካበዳትሁት አይደለም ያምራል” አለች! ተያይተን በሳቅ ፈረስን!

የዚች አስተማሪ ሌላው አስገራሚ ሥራ፣ አንድ ቀን ከቀንም ቀን ቅዳሜ ቀን ጧት
ትምህርታዊ ጉብኝት እናደርጋለን፡፡” ብላ ጠራችን፡፡ ቅዳሜን በሚያህል ቀን ትምህርት ቤት መጠራታችን ሳያንስ፤ልታስጎበኘን የወሰደችብን ቦታ ይኼው ሩብ ክፍለ ዘመን ሊሆነው ተቃርቦ እንኳን ትዝ ሊለኝ ይዘገንነኛል፡፡ ያው እንግዲህ እሷ እንደምትለውና ድሮ እጅ ሥራ ደብተሬ የመጀመሪያ ገጽ ላይ ጽፌው እንደተኘው የእጅ ሥራ ትምህርት መሠረታዊ ዓላማው የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት እና የአምራችነት ፍላጎት
ከፍ በማድረግ አምራች ዜጋ ማፍራት ነው" ይህን ከህሎት ያዳበሩና ለእኛ አርአያ ሊሆኑን የሚችሉ የእጅ-ሥራ ጥበብ ባለሙያዎች ወደሚገኙበት ቦታ ነበር ለጉብኝት የወሰደችን፡፡ የከተማው ማረሚያ ቤት! ከጣሊያን እስር ቤት ወደ ሐበሻ እስር ቤት፡፡

የማረሚያ ቤቱ የግንብ አጥር የተሠራበት ድንጋይ የትምህርት ቤታችን የእጅ-ሥራ ክፍል ከተሠራበት ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ ድንጋዩ ብቻ ሳይሆን፣ አሰካኩም አንድ ዓይነት ነበር፤ ወይ ይኼንንም ጣሊያን ሠርቶታል አልያም ከጣሊያን እግር ሥር ቁጭ ብለው የተማሩ የአበሻ መሐንዲሶች አንጸውታል፤ መቼስ ደግደጉን መማር ባንዳነት አያስብል፡፡ የማማው ከፍታ ደመናውን ሰንጥቆ የገባ ነበር የሚመስለው፡፡ ከብዙ ፍተሻ ሰኋላ ከባዱ
ተንሸራታች የብረት በር በሁለት መሣሪያ በታጠቁ ወታደሮች እየተገፋና ሲጢጢጢ እያለ ሲከፈት፣ የሚያለቅስ ይመስል ነበር… በሰሩ መንሸራተቻ የብረት ሃዲድ ላይ የተደፈደፈው የጆሮ ኩክ የመሰለ ግራሶ እንደእንባ ግራ ቀኝ ቀልጦ ይፈስሳል፡፡

ወደ ግቢው በሰልፍ ስንገባ፣ በሕይወቴ ይኖራል ብዬ የማላስበው ዓለም፣ ፊት ለፊቴ ተጋረጠ… መጨረሻቸው የማይታይ፣ በጣም ብዙ እሮጌ የቆርቆሮ ቤቶች ከስንትና ከስንትና ዓመታት በፊት ፋሽናቸው ነፍሶበት ወደ ቅርስነት የሚያዘግሙ፣ የተረሱ የድሮ ፎቶዎች
ላይ ብቻ የማውቃቸውን ልብሶች የለበሱ ታራሚዎች ግቢውን ሞልተውታል።

እንዳንዶቹ አቧራው እንደ ደመና የሚነሳ ሜዳ ላይ እየተጯጯሁ መረብ ኳስ ይጫወታሉ።ግቢው ራሱ ይኼ ነው የማይባል የተለየ ሽታ ነበረው።ለምንም ነገር ግድ የሌላቸው የሚመስሉ ታራሚዎች፣ በቸልታ ያዩናል …ደግሞ ለከፋቱ ገና በሩ ላይ እንደደረስን የአእምሮ ሕመምተኛ የሆነ ታራሚ ፊት ለፊታችን ገጠመን፡፡ ልብሱ እላዩ ላይ አልቋል፣ በባዶ እግሩ ነበር … ልጋጉ ይዝረበረባል፣ እግርና እጁ የታሰረበትን ከባድ ሰንሰለት እያቅጨለጨለ ሳያቋርጥ ቻው ቻው ቻው መውጣት የለም ቻው በቃ ገባችሁ፣ መውጣት የለም …” ይለናል ያ ድምፅ እስከ ዛሬ ጆሮዬ ላይ አለ።

እንደተሰለፍን በእስረኞች መሃል አልፈን፣ የእደ ጥበብ ክፍል ወደሚባለው ትልቅ የቆርቆሮ አዳራሽ ተወሰድን፡፡ ወደ ውስጥ ስንገባ ብዙ የሽመና ሥራ የሚሰሩ
ታራሚዎች እግራቸውን ጉድጓድ ውስጥ ቀብረው ነጠላ ጋቢ ይሰራሉ…አንዳንዶቹ
ረዣዥም የክር ድር እዚያና እዚህ ግድግዳ ላይ በተሰኩ ሚስማሮች ላይ ያደራሉ።ግርግሩ ለጉድ ነው፣ ጫጫታው ይጨንቃል፡፡ አስተማሪያችን ሰብሰብ አደረገችንና “ወደሚሰሩት ሰዎች እየሄዳችሁ፣ ምን እንደሚሰሩ? እንዴት እንደሚሰሩ? የመሥሪያ መሣሪያዎቻቸው ስም ምን እንደሚባል እየጠየቃችሁ ማስታወሻ ያዙ:” አለችን፡፡ግራ
እንደገባን እኔና መሐሪ ወደ አንዱ ጸጉሩን ወደተላጨ ሸማኔ ጠጋ ብለን ከግራ ወደቀኝ ከቀኝ ወደግራ የሚወረውራትን፣ ውስጧ የሚተረተር ነጭ ክር ያለባትን መወርወሪያ ስንመለከት፣ ሸማኔው ድንገት በዜማ፤

ተማሪ ውሻ ቀባሪ ውሻ ሲቀብር… አነቀው ነብር…” አለና ልክ እንደ ነብር ጥፍር
ጣቱን ለቀልድ እንጨፍርሮ ሲቃጣን፤ ደንግጠን ወደኋላ ስናፈገፍግ ሌሎቹ በሳቅ አውካኩ።

ወይ የዘንድሮ ተማሪ ቤት ….እንደያው እሁን ምን ሊያስተምሩ እዚህ ሲኦል
አመጧችሁ?” አለን፣ ለራሱ በሚመስል አነጋገር፡፡ ትኩስ የተላጨው ሞላላ አናቱ ላይ አልፎ አልፎ ቋቁቻና ጠባሳ ነገር አለው፡፡

“ለምንድነው የታሰርከው” አልኩት ድንገት፡፡ ያልጠበቀው ጥያቄ ስለሆነ የገረመው ይመስል፣ አንዴ እኛን፣ አንዴ ጓደኞቹን ተመለከተና፣
👍3
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_ሶስት


#በአሌክስ_አብርሃም

ከጉብኝቱ በኋላ በነበረን የእጅ ሥራ ክፍለ ጊዜ “ስለጉብኝቱ ጥያቄ ካላችሁ ጠይቁ!”
በተባልነው መሠረት፣ መሐሪ ቀድሞ እጁን አወጣና “ቲቸር እስረኞቹ ግን ለምን በሌሊት አያመልጡም?” ብሎ ጠየቀ፡፡ “ቲቸር” ምንም ምንም ሳትናገር ቁማ መሐሪን ስታየው ቆየች፤ እናም ረጋ ባለ ድምፅ እንዲህ አለች፣

ሌላ ጥያቄ ያለው?

ይኼ ሁሉ ነገር ሳያንሰን፣ አስተማሪያችን ሥሩ እያለች የምታዘው ነገር ሁሉ ያበሳጨን ነበር። እኔና መሐሪ አንድም ቀን የምታዘውን ሠርተን እናውቅም… ከሙቅና ከወረቀት ሰሃን ሥሩ አለችን ድፍን የከፍሉ ልጅ የወረቀት ሰሀኑን፣ ሰባት ቀን ያደረ ደረቅ ቂጣ አስመስሎ ሲመጣ(ደግሞ ሽታው ሲያስጠላ) ሁለታችን ብቻ ባዶ እጃችንን ቁልጭ ቁልጭ እያልን ተገኘን፡፡ ከሃያ ዜሮ ሰጠችን!! ከሃያ ዜሮም፣ ከሃያው ሃያም ስትሰጥ ፊቷ ላይ ምንም የተለየ ስሜት አይነበብም ነበር፡፡ የመሐሪን እናት ማሚ ስለሙቁ ስንነግራት ፈገግ ብላ “መሥራት ነበረባችሁ!” አለችን፡፡ ተባብረን ልናሳምናት ሞከርን፡፡

እንዴ ማሚ! ስንት ሕዝብ በሚራብበት አገር፣ በእርዳታ የሚገኝ ስንዴ ለእጅ ሥራ እያልን...

ትክ ብላ አየችንና “ወሬኞች!” ብላ ወደ ሥራዋ ሄደች፡፡ ፊቷ ላይ ግን ፈገግታ ነበር፡፡ማሚ ሁልጊዜ እኛ ጋር ስታወራ፣ ፊቷ ላይ ወይ ለይቶለት የማይፈነዳ፣ አልያም ለይቶለት የማይከስም፣ ልክ እንደጥዋት ጤዛ የተንጠለጠለ ውብ ፈገግታ ነበር፡፡ ፈገግታው ሁልጊዜ
ዓይኗ ላይ ነበር፣ ከእንድ ቀን በስተቀር፡፡

ከማረሚያ ቤት ጉብኝታችን የተመለስን ቀን፣ ማሚ ጋር ስላየነው ነገር ስናወራ መሐሪ ካለወትሮው ዝም ብሎ፤ እኔ ነበርኩ የባጥ የቆጡን የማወራው፡፡ ማሚ በጣቷ ጉንጩን ነካ እያደረገች “ምነው ለምቦጭህን ጣልክ?” ስትለው ነበር ዝም ማለቱ ትዝ ያለኝ!እንዳቀረቀረ ሹክሹክታ በሚመስል ድምፅ “ሚስቱን የገደለ ሰውዬ አዬን እዚያ ታስሯል!” አላት፡፡ ማሚ ኮስተር ብላ…

እ? አለች

እኔ ነበርኩ ወሬውን የጨረስኩት፡፡ ስለ ሰውዬው ነገርኳት፡፡ በተለይ ስለ ራሱ ሞላላነትና ስለ መላጣው …ስለ ሚስቱም ጉዳይ!

ማሚ መሐሪን ድንገት ወደ ራሷ ሳብ አድርጋ አቀፈችው፡፡ አጥብቃ አቀፈችው፤ እሱም ታፋዋን አቅፎ ቀሚሷ ውስጥ ተሸጎጠ እና እንዲህ አለች “ሕፃን ስለሆናችሁ እየቀለዱባችሁ ነው” ግን እንደዛም እያለች ማሚ ዓይኖቿ በእንባ ተሞልተው ከንፈሯ ይንቀጠቀጥ ነበር…መሐሪን ትንሽ ገፋ አደረገችውና፣ አፏን በመዳፏ አፍና ወደ ውስጥ እየተጣደፈች ገባች! ወደ መኝታ ቤቷ !
ሌላኛው ጠላታችን የሙዚቃ ትምህርት ነበር! ሙዚቃ አስተማሪያችን ከዓመት በፊት የትምህርት ቤታችን ሜዳ የሚጠበው ስፖርት አስተማሪ ነበር፡፡ የመኪና አደጋ ደርሶበት ግራ እግሩ በከባድ ጀሶ ተጠቅልሎ፣ በአንድ የብረት ምርኩዝ እየታገዘ መሄድ ከጀመረ
በኋላ ነው የሙዚቃ አስተማሪ የሆነው ድፍን መንፈቅ ዓመቱን ውጭ ሜዳ ላይ
እያስወጣ “ ተጫወቱ!” ይለንና አንዲት ዛፍ ሥር ተቀምጦ፣ ጥርሱን በቀጭን የወይራ እንጨት እየፋቀ ያየናል፡፡ የፈተና ቀን ሲደርስ ግን፣ “በየተራ ተማሪ ፊት እየወጣችሁ ዝፈኑ፣ ሀምሳ ማርክ አለው!” አለን፡፡ “እዚች አገር እንኳን እኛ፣ ዘፋኙ ራሱ ሃምሳ ማርክ አያገኝም!" እያልን አላገጥን እኔና መሐሪ። ብንደረግ ብንሠራ አንዘፍንም አልን፡፡ “ዝፈኑ ስትባሉ ማልቀስ ከፈለጋችሁ ጥሩ!” ብሎ ከሀምሳው ዜሮ አከናነበን፡፡

በኋላ ጎበዝ ተማሪዎች ናቸው እባክህ በሌላም መንገድ ቢሆን ፈትናቸው” ተብሎ በስም ጠሪያችን አማላጅነት ተለምኖና አዝኖልን (እኔ ግን ስጠረጥር ጎበዝ ነን በሚል ትዕቢት ተወጥረው የሙዚቃ ክፍለ ጊዜን እንደናቁ አስተነፍሳቸዋለሁ በሚል ቂም በቀል)
እያንዳንዱ ጥያቄ ዐሥር ነጥብ ያለው የቃል ፈተና ፈተነን፡፡

በገና ስንት ክር አለው …?

ባስብ ባስብ አልመጣልህ አለኝ፡፡ መቼም መንፈሳዊ ነገር ላይ ሰባት ቁጥር አይጠፋም ብዬ ሰባት አልኩ፡፡ፊቱ ላይ የነበረው ቁጣ በሆዱ ለሰባት ይቆራርጥህ!” የሚል አስመስሎት ነበር፡፡ ከፈተናው በኋላ እልህ ይዞን፣ ሰፈራችን ወደ አለው መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን መዝሙር ቤት ሄድን፡፡ መዝሙር ቤቷ በር ላይ ተቀምጦ ያገኘነውን ዘበኛ “በገና ስንት ክር አለው? “ስንለው፣ እኔ አላቅም! መሪ ጌታ ሲመጡ ጠይቁ ብሎ
በቆምንበት ረሳን ፡፡ በገናውኮ ከኋላው ነበር፡፡ እሺ! እንቁጠረው ስንል፣ መሪ ጌታ
ካልፈቀዱ አይቻልም ብሎ ጠመመ! በዚያው ረሳነው!

2ኛ እምቢልታ ከምን ያሠራል?

እምቢልታ ራሱ ምን እንደሆነ አላውቅም…እምቢልታ ማለት ብሎ በሚነጫነጭ ድምፅ በሰፊው እብራራልኝ፣ ያውም ያልጠየቀውን ነጋሪት ሁሉ ጨምሮ! “የሆነ ሆኖ አልመለስከውም” ከሚል መደምደሚያ ጋር፡፡ ስለ እምቢልታና ነጋሪት የዚያን ቀን
አውቅሁ!

3ኛ የኢትዮጵያ የሙዚቃ ቅኝቶች ምን ምን ናቸው?

ትዝታ፣ ብዬ ጀመርኩ፡፡ ሌሎቹን ማወቅ አልቻልኩም፡፡ መምህሩ በስክርቢቶው ጫፍ ጢረጴዛውን ሲጠቀጥቅ ቆየና፣ ትክ ብሎ እየተመለከተኝ .. ሌላው ይቅር… ሰው እንዴት አምባሰል ይጠፋዋል? እንዴት ባቲ ይጠፋዋል? አላየንም ጎበዝ ተማሪ !" አለና ወደ ቀጣይ ጥያቄው አለፈ፡፡

4ኛ ሦስት የክር የሙዚቃ መሣሪያዎችን ጥቀስ (ይኼ ሰውዬ የሙዚቃ አስተማሪ ነው ወይስ የዳንቴል ሥራ?ክር ክር ብሎ ሊሞት ነው እንዴ! እያልኩ በውስጤ
ክራር ፣ በጎና ፣ ጊታር ተመስገን!” አለ፡፡ አነጋገሩ ያበሳጭ ነበር ፡፡ በጣም ያበሳጨኝና፣ ሰውየው ነገር መፈለጉ የገባኝ ከዚህ ሁሉ ጥያቄ በኋላ ወደመጀመሪያው ነገር ሲመለስ
ነበር፡፡

የምታውቀውን የአንድ ዘፈን አዝማች በዜማ አንጎራጉር አስተማሪ አይጥመድ! ከዛም ብሶቱን ተነፈሳት “ስማ! ጎበዝ ሁነህ ናሳ ብትቀጠር ፣ጨረቃ… ማርስ ብትረግጥ፣ ካለባህሪ ዋጋ የለውም፣ ዋናው ትሕትና ነው:: ይች አገር ገና
ከጥንት ከአክሱምና ከዛገዌ ዘመን
ጀምሮ፣ ስንት ሊቃውንት፣ ስንት ጠቢባን ነበሯት፣አሏትም፡፡አዋቂ ነጥፎባት
አያወቅም ትሕትና ነው ዋናው ትሕትና! እኔ ተፈሪ ሃያ ሦስት ዓመት ሳስተምር፣ ማንም
እከሌን ፈትን፣ እከሌን ፈተና ቀይርለት ብሎኝ አያውቅም…” ብሎ፣ ግማሽ ዛቻ… ግማሽ ፉከራ የቀላቀለ ረዥም ምከር ከመከረኝ በኋላ፣ መሐሪን ጠራው፡፡
መሐሪም የኔው ዕጣ ነበር ያጋጠመው፡፡ በሕይወት ዘመኔ ለመጀመሪያ ጊዜ ከመቶው ሃያ ሦስት ያመጣሁበት ትምህርት ሆነ፡፡ የሚገርመው ነገር መሐሪ ከመቶው ሠላሳ አምስት ማምጣቱ ነበር እንዴት ሠላሳ አምስት ሰጠህ?” ብለው፡፡

“ዘፈንኩ!” አለኝ።

ከምርህ ነው? … "

ታዲያ! ጋሽ ዝናቡ እኔንም ማሚንም ከሚገለን ብዘፍን አይሻልም” ከዚያን ቀን ጀምሮ ለስንት ዓመት፣ እኔም ፍቅረኛው ሮሐም ምን እንደዘፈነ እንዲነግረን ብንጠይቀው፣ ብንለምነው ምስጢር ነው ብሎ ሳይነግረን ቀረ፡፡ ባሕሪው እንደዚህ ነው:: አንድ ነገር ምስጢር ነው ካለ፣ ለምን አይገድሉትም ትንፍሽ አይልም፡፡

በእነዚህ ይዞ ሟች ትምህርቶች ምክንያት፣ እኔና መሐሪ ተያይዘን ገደል ገባን! መብረቅ የወደቀብን ያህል ነበር የደነገጥነው! …ቀድሞ እንዴት እንዳልታየን አልገባኝም፡፡ እኔ እንኳን አራተኛ፣ አርባ አራተኛም ብወጣ “እሰይ ዋናው ጤና! የምትል እናትና አብርሃም ስትመለስ ታሳየኛለህ፤ እስቲ ሂድና ዕቁብ ከፍለህ ና!” በሚል አባት ተባርኪያለሁ፡፡ ለመሐሪ ነበር ሁለታችንም የደነገጥነው፤ እንዲያውም ያንን ካርድ ይዘን ስንመለስ፣ እንደፍጥርጥርህ ብዬው ወደ ቤቴ ልሄድ ነበር፡፡ መሐሪ ግን በቁጣ ቦግ ብሎ
እኔን አጋፍጠኸኝ ልትሄድ ነው እንዴ? አታስብም?” ሲለኝ፣ አሳዝኖኝ አብሬው መብረቅ ልመታ
👍1
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_አራት


#በአሌክስ_አብርሃም

…መሐሪ ካርዱ ከእጁ አምልጦት ወደቀ! ጋሽ ዝናቡ ወንበሩን ማወዛወዙን አቆመና፣ እጁን ወደፊት ዘርግቶ “እስቲ አምጣው!?” አለ፡፡ ዓይኑን በወደቀው ካርድ ላይ ተከሎ፤ መሐሪ መንቀሳቀስ ስላልቻለ፣ እኔ ያለ የሌለ ድፍረቴን አሰባስቤ ካርዱን እነሳሁና፣ ደረጃውን ወጥቼ ሰጠሁት፡፡ ካርዱን አሰጣጤ ለሆነ ተናካሽ
እንስሳ ሥጋ እንደሚወረውር ሰው በጥንቃቄ ነበር!... ከእጄ እንዳይወስደው!

ከዘላለም የረዘመ ለሚመስል ጊዜ ካርዱን ሲመረምር ቆየቶ፣ በረዥሙ እህህ ብሎ
አቃሰተ እና እዚህ መርዶ ላይ የሚፈርም አባት አለኝ ብለህ አንከርፍፈህ መጣህ እ
" ብሎ በሚያስደነግጥ ፍጥነት ምንጥቅ ብሎ ሲነሳ፣ ሁለታችንም ወደኋላ ሸሸት አልን ጋሼ ተነሰቶ ሲሄድ ተቀምጦበት የበረው ወንበር፣ ከዚህ ጉድ ሩጦ ማምለጥ ፈልጎ አቅም ያነሰው ይመስል፣ ባለበት ሆኖ ወደ ኋላና ወደፊት ተራወጠ፡፡ ወንበሩ ላይ የነበረው በፈዛዛ ቀይ ጨርቅ ከረጢት የተቋጠረው የስፖንጅ ድልዳል ተንሸራቶ መሬት ላይ ወደቀ፡፡

መሐሪ በድንጋጤ የተሰነዘረበትን ቡጢ እንደሚከላከል ቦክሰኛ ፊቱን በቀጫጫ ክንዶቹ መህል ቀብሮ ነበር ወደ ኋላው የሸሸው::ያች አቋቋሙ እስካሁን እንደፎቶ ቁልጭ ብላ ትታየኛለች፡፡ ሸሽቶ ደግሞ ከእኔ ኋላ ነበር የተደበቀው፡፡ ጋሼ እቆምንበት ትቶን ወደ ውስጥ ሲገባ እንኳን፣ መሐሪ አላየውም!! ነገሩ ጸጥ ሲልበትና የጠበቀው ኩርኩም
ሲዘገይ፣ ቀስ ብሎ ከከንዶቹ መሀል ቀና አለ፡፡ የጋሼን አለመኖር ሲያይ፣ ድንገት “ማሚን ገደላት!” ብሎ ወደ ውስጥ ሮጠ!እኔ ባለሁበት አንዴ የግቢውን በር፣ አንዴ አባትና ልጅ ተከታትለው የገቡበትን የቤቱን ዋና በር እየተመለከትኩ እንደቆምኩ፣ ከውስጥ የሆነ ከባድ እቃ ሲወድቅና ሲሰባበር ሰማሁ፡፡ ምን እንደገፋኝ እንጃ በሩጫ ተከትያቸው
ገባሁ፡፡ ደመነፍሴ ጓደኛህን ታደግ ብሎ ገፍቶኝም እንደሆነ እንጃ:: ከዋናው ቤት ጋር ተያይዞ ወደተሠራው ኩሽና በሚወስደው በር ላይ ተቀምጦ የነበረው ተደራራቢ የአበባ ማሰቀመጫ፣ ወለሉ ላይ ወድቆ ብትንትኑ ወጥቷል፡፡ ጋሽ ዝናቡ ኩሽናው ውስጥ ገብቶ በዚያ ንጋሪትና እምቢልታ ቢጨመርበት የክተት ጥሪን በሚያስንቅ ድምፁ ማሚ ላይ ያንባርቅበታል …

“ለስሙ ሴት ነሽ! …እናት ነሽ! እዚህ ተጎልተሸ እየዋልሽ፣ አንድ ልጅ እንኳን እንድ ልጅ መቆጣጠር ያቃተሸ ዳሩ በልደትና ሰርግ ሰበብ ማን እየተኳኳለና እግሩን እያነሳ ይዙርልሽ? አራተኛ …አራተኛ … ምን ማለት ነው ይኼ? , እ? ….ዳሩ አራተኛ ይሁን አስራ አራተኛ አይገባሽ አንች .…አራተኛ .…” ማሚ ምን መዓት ወረደብኝ ብላ ነው መሰል
ድምፅዋ አይሰማም! ለነገሩ እንኳንስ እንዲህ ዓይነት ውርጅብኝ ፊት ቁማ መመላለስ ቀርቶ በሰላሙም ቀን ንግግሯ የተቆጠበ ነው !

መሐሪ፣ አባቱን ያረጋጋ መስሎት እንዲህ ሲል ሰማሁት “ጋሽ፣ አብርሽኮ አምስተኛ ነው የወጣው” ወደኋላዬ ልሮጥ ነበር፤ ምነካው… እንዴት በዚህ እሳት ውስጥ ስሜን ያንሳል? እያልኩ ሳስብ

“ኧረ? ይኼ ነው “ኤክስኪውዝህ?”… በማኀበር ነው የሞትነው በለኛ ?,ደሞ አብርሽ ይባልልኛል …ግም ለግም አብረህ አዝግም ምድረ ድኩማን! ጧ! “ ጥፊ መሆን አለበት!" እቆምኩበት ሁኜ ጉንጬ ሲግል ተሰማኝ፡፡ ስለዛች “ጧ” ከዚያ በኋላ ሁለታችንም አንስተን አናውቅም !

“አትምታው! …ልጄን አትምታው!! ..ጆሮውን ልታደነቆረው ነው እንዴ?” ከዚያም በፊትም ሆነ ከዚያም በኋላ ሰምቼው የማላውቀው የማሚ ቁጡ ድምፅ አንባረቀ!

“ይችን ይወዳል ዝናቡ! …ለኔ ነው ቢላ ያነሳሽው? …እኮ ለኔ? …ግደይውና ነይ አብረን እንኑር አለሽ? …ታዲያ መርዝ አይሻልሽም? እ!” እንደፈለክ በል! ብቻ ልጄን ትነካውና ውርድ ከራሴ …እስቲ አሁን ምናለ? አብሮት ከሚያጠናው ጓደኛው ጋር ትምህርት ከበዳቸው፣ እሱ ብቻ አይደለም …ይኼ ያስመታል?
ደግሞ ወደ ስድስት አልፈዋል …በቃ

“ፓ! አንችም ብሎ ማብራሪያ ሰጭ .
ወደ ስድስት አልፈዋል ትላለች እንዴ? በዚህ የሞተ ውጤት ከአምስት ወደ ስድስት ወድቀዋል ነው የሚባለው … ማለፍ ሁሉ ስኬት አይደለም ..ከገባሽ! እንዲያውም አብርሃም የሚባል ካንተ የባሰ እንቅልፋም! ሁለተኛ እዚች ቤት ድርሽ ይልና .

ተው እንጂ አልበዛም” አለች ማሚ

በዛ እንዴ? እንዴት ለልጅሽ ውድቀት ጠበቃ ትሆኛለሽ ?……እንዲያውም አሳይሻለሁ ብሎ ወደ ሳሎን በቁጣ ሲመለስ፣ እንደጨው ዓምድ ደርቄ በቆምኩበት ተገጣጠምን፡፡
በረንዳው ላይ ነው ያለው ብሎ አስቦኝ ሳለ፣ ሳሎን ውስጥ ስላገኘኝ ትንሽ እንደመደናገር አለውና በዚያው ድምፅ

ስማ አንተ ሁለተተኛ እዚህ ቤት አይህና ውርድ ከራሴ! … ሁለተኛ… ሂድ አሁን
ወጥቼ ወደ ቤቴ ተፈተለከሁ! የእውነት ምርር ያለ ድንጋጤና ሐፍረት ተሰምቶኝ ነበር !
እቤቴ እስክደርስ ኤልቆምኩም፡፡ እቤታችን በር ላይ ስደርስ የከሰል ምድጃ ላይ የተቀጣጠለ እሳት ይዛ ከቤት የምትወጣው እናቴ ጋር ልጋጭ ለትንሽ ተረፍኩ፡፡

ምን እያባረረህ ነው?' ብላ እንደ መሳቅም እንደ መደንገጥም አለች! ሁልጊዜ ሳኮርፍ
የምመናቀረው ነገር (እንደሷ አባባል) ያስቃታል! ለእናቴ የሆነውን ነገር አልነገርኳትም.. ጥያቄዋ ሲበዛብኝ ካርዴን ሰጥቻት “አምስተኛ ወጣሁ” አልኳት፡፡ ካርዱ እንዳይቆሸሽ፣
በሥራ የቆሸሽ እጁን ልብሷ ላይ ጠራረገችና ተቀብላኝ፣ አንዴ እንኳን ሳታየው እና እንኳን አምስተኛ ለምን መጨረሻ አትወጣም… እንዲህ እሳት ውስጥ እስክትማገድ ያመናቅራል እንዴ? ሳመኝ ና! ጎበዝ! ጎበዝ!" እያለች ካርዱን ጠረጴዛው ላይ አስቀምጣ እራሷ መጥታ አገላብጣ ሳመችኝ :: አባቴ ለምሳ እንደመጣ ፍልቅልቅ እያለች፣ ካርዴን
ልክ እንደምሳ አቀረበችለትና “አብርሽ አምስተኛ ወጣ!” አለችው፡፡

አምስት? . ብሎ በዛው ሌላ ወሬ ቀጠለበት እንደው ይኼን የጫማ ሶል በምን ብታጥቢው ነው እንዲህ የቆረፈደው?…ያልተላገ እንጨት ላይ ስራመድ የዋልኩ ነው የመሰለኝ ማታ በቅባት ካላሸሽልኝ፣ እግሬ ዋጋም የለው

“አንተ ደሞ! እስቲ ጎበዝ በለው :

እህ አልኩትኮ የኔ ልጅ ባይባልስ አገር ያወቀው አይደለም እንዴ …ማነው ስሙ
ይኼ የኛ ዕቁብ ሰብሳቢ ልጅ፣ ዘንድሮም ወደቀ መሰል፣ እዚያ ቦኖ ውሃው ግንብ ሥር ተቀምጦ ይነፋረቃል፡፡ ትምርቱስ ይከበደው መቼም ሰው እንዴት አሳምሮ ማልቀስ ያቅተዋል? " አባባ በቃ እንዲህ ነው።በራሱ ዓለም የሚኖር፡፡

የጋሽ ዝናቡ ነገር እንዲቹ ሲያብሰለስለኝ ዋለ! ወደማታ ላይ ከምሽቱ አንድ ሰዓት አካባቢ ታዲያ፣ የቤታችን በር ተንኳኳ፤ ጋሽ ዝናቡ ነበር: በጓሮ በር ወጥቼ ልሮጥ ሳስብ፣በተረጋጋ ድምፁ ከእናቴ ጋር ሰላምታ ሲለዋወጡ ስሰማ ተረጋጋሁ፡፡ እናቴ እንዲገባ ትለምነዋለች ረጋ ብሎ ወደ ቤት ገባ፡፡ ቡኒ የሱፍ ካፖርቱን እስከ አንገቱ ቆልፎ ለብሷል ጥቁር ቴክሳስ ባርኔጣውን በእጁ እያፍተለተለ …ቤታችን መሀል ላይ ቆመ! ረዥም ነው፡፡ አንገቴን ሳቀረቅር ተወልውሎ ከሚያብረቀርቅ ጥቁር ቆዳ ጫማው ጋር ተፋጠጥኩ፡፡

“ተቀመጥ! ጋሽ ዝናቡ፣ ምነው ከመሻ? በሰላም?” ሰላም ነው!ሰላም ነው አትጨነቂ! …ቀን ለምን ውጤታችሁ ዝቅ አለ ብዬ ልጆቹ ላይ አጓጉል ጮኸኩባቸው .…የኔን ነገር ታውቂው የለም … የኔውስ ለምዶታል አብርሃምን
አስደነገጥኩት መሰለኝ ይቅርታ ልጠይቅ ነው የመጣሁት …. አማልጅኝ እንግዲህ!” አለ።

እናቴ ወደኔ እያየች “ኧረ የታባቱ ደሞ ለሱ ይቅርታ! አንደኛ የሚወጡ ልጆች አምስተኛ ሲወጡ፣ ላይጮህባቸው ነበር ታዲያ ሲያርሱ ነው ሲያርሙ ዱላም ሲያንስ ነው ትንሽማ ቀበጥ ብለዋል …ተነስ አንተ!” አለችኝ በርግጌ ተነሳሁና
👍1
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_አምስት


#በአሌክስ_አብርሃም

ለስላሳና ኬክ ጋብዘን፡፡ ስንወጣ ኬክ አስጠቅልሎ ለመሐሪ እያቀበለው “ለእናት ውሰድላት አለው፡፡

መሐሪ፣ ሮሐን አፈቀርኩ ሲል ቀድሞ በሐሳቤ የመጣው ታዲያ፣ ይኼው የጋሽ ዝናቡ ቁጣ ነበር፡፡ አራተኛ መውጣቱ ትልቅ ነገር ሆኖ፣ መላእክት እና ሰዎች ቢቧደኑ፣ መሀል ላይ የምትቆም ማሚንና ባለቤቷን ጋሽ ዝናቡን ቢለዋ ያማዘዘ፣ መሐሪ ከአንዲት ሴት ጋር ፍቅር ጀመረ የሚል ወሬ ጋሼ ጆሮ ሲደርስ፣ …ማሰቡ ራሱ አስፈርቶኝ ነበር! ቢሆንም ከመሐሪ ጎን ከመቆም ውጭ፣ ምናባቴ አማራጭ አለኝ ደግሞ ለከፋቱ ሮሐም ለመሐሪ
በፍቀር ክንፍ ብላ ተያይዘው ማበዳቸው እንዲያውም አንድ ቀን እኛ ቤት ነኝ ብሎ
ከሮሐ ጋር ማምሻቱ አስፈርቶኝ በቀጣዩ ቀን

ኧረ አንት ልጅ ሥርዓት ያዝ ጋሽ ቢሰማ ስለው ….በቁጣ ቱግ ብሎ…

“የራሱ ጉዳይ ነው! ከፈለገ ቤቱን ለቅቄለት እወጣለሁ!እለኝ፡፡ በውስጤ እሱንኳን ተወው! ያንን ቤት ለቆ ከወጣ የሚወጣው ነፍስህ ነው!” እያልኩ ዝም አልኩ፡፡ መሐሪ ባለችው ትርፍ ሰዓት ሁሉ ከሮሐ ጋር ተያይዘው የት እንደሚሄዱ እንጃ፣ መጥፋት ሆነ ሥራቸው፡፡ ሊያመሽ ከፈለገ ብቻ እየተጣደፈ “እናንተ ቤት ነኝ ይለኝና ነብሱን ስቶ ወደ ሮሐ ይበራል! ታዲያ ጋሽ ዝናቡን እየፈራሁም ቢሆን፣ ለጓደኛዬ ለመሐሪ ግን ልቤ በደስታ ይፈነጥዝ ነበር፡፡ ከሮሐ ጋር አብረው ሳያቸው፣ ልጁን እንደዳረ አባት ሐሤት አደርጋለሁ፡፡ ደግሞ ሲያምሩ፣ ከዓይናቸው የሚረጨው የፍቅር ብርሃን ድምቀቱ ሰው ፍቅር ለምን ያዘህ? አይባልም፡፡ሰው ላፈቀርካት ሴት ለምን ልብስህን ጣልክ? አይባልም እንዲያው ቀንበር ጠቦኝ እንጂ… እንደ ሮሐ ሥጋም በነፍስም ሲበዛ ውብ የሆነች ልጅ ያፈቀረ ጓደኛዬን፣ ባለፉበት ሁሉ ከፊታቸው ቀድሜ ያውም እንደ ንጉሥ ሰልፍ ነጋሪትና እንቢልታ አስይዤ “ይች ምናላት በደንብ እበዱ ወፎች ከበላያችሁ ያርግዱ ተማሪዎች በዙሪያችሁ ተኮልኩለው በፍቅራችሁ መልካም መዓዛ ይታወዱ …" እያልኩ ማወጅ ያምረኛል! ውብ ልጅ ነበረች ሮሐ ፈረንጅ የመሰለች” ይሏታል ፈረንጅ አትመስልም! ለኔ ቅላቷ በፈረንጅ ቀለም ላይ ትንሽ ጠይምነት ጠብ ተደርጎበት የተሰራ ለስላሳ ፍካት ነው፡፡
ልክ ወተት ላይ ቡና ጠብ እንደሚደረገው፡፡ ውብ ነበረች፣ ውብ፡፡ በዚያ የውብ ቆዳ መደብ ላይ፡ ምንኛ ዓይንን ተጠበበት የምለው፣ ዓይኗ ሲያርፍብኝ ነው፤አፍንጫን አንደም
አድርጎ አሳካው የምለው ከዓይኖቿ መሃል እስከ ላይኛው ከንፈሯ የተዘረጋ ቀጭን የገነት መንገድ አስመስሎ ቢያሰምረው ነው …የታችኛው ከንፈሯ ትንሽ ወደ ታች ወረድ ብሎ ቀበጥ አኩራፊ አስመስሏታል፡፡ የደላው ሰውነት አላት፡፡ ከረዥም ሉጫ ጸጉር ጋር ውብ ነበረች ሮሐን ለዐሥረኛ ክፍል ተማሪ ይኼ ሁሉ ውበት አልበዛም?እላለሁ እንዳንዴ ባየኋት ቁጥር፣ ስሙ ለተጠራ የዘራፊዎች መንደር፣ ያውም በጨለማ ወርቅ
ተሸከማ የምትሄድ ምስኪን ትመስለኛለች፡፡ ከመሬት ተነስቼ ሰዎች የሚጎዷት ይመስለኛል፡፡ መሐሪ ጋር በፍቅር አበዱ! እኔም ከዚያ ዝናቡ ከሚባል ሰውዬ ዶፍ ላስጥላቸው ራሴን ዣንጥላ እድርጌ ከበላያቸው ዘረጋሁ!!

አስባለሁ፤ሁልጊዜ አስባለሁ!… አእምሮዬ እንደ እስፖንጅ መጦ የያዘው ትላንታችንን፣ ፈሳሽ ትዝታ አድርጎ እየጨመቀ፣ ዙሪያዬን በጨቀየ ነበር ይከበዋል! ኤልረሳም፣ ያየሁ
የስማሁትን ነገር አልረሳም፡፡ ሰዎች ነገሬ ብለው የማይመለከቷቸውን ነገሮች እንኳን
ጨምድዶ ከያዘ የማይለቅ ተፈጥሮ ነው ያለኝ፡፡ ቆይቶ ይኼ ተፈጥሮዬ ከኋላዬ እየተከተለ የእኔኑ ጀርባ የሚገርፍ የእሳት ጅራፍ እየሆነ ሲያሰቃየኝ ብጠላውም፣ ልላቀቅ ያልቻልኩት መከራ እንደሆነ ይከተለኛል፡፡ እንደመርሳት ምን ፈውሽ አለ?!

ድንገት ካለምንም ምክንያት (ከመሬት ተነስቶ እንደሚሉት) በተቀመጥኩበት የሚያናውዝ ትውስታ እንደደራሽ ጎርፍ እያላጋ ወደራቀ ጊዜ ይወስደኛል፡፡ ዛሬዬን አጣጥሜ መኖር አልቻልኩም፡፡ ትዝታው ከአእምሮዬ አልፎ ሰውነቴንም ስለሚያዝለኝ ልወደውም፡፡ ትዝታ ግን ታሪክ ነው? በታሪክና በትዝታ መካከል ያለው ልዩነት ምንድነው? ትዝታ
ታሪክ ከሆነ፣ ለምንድነው ሰዎች ታሪክ አውርተው ሲጨርሱ ከድካም ይልቅ በወኔ የሚሞሉት? አስባለሁ ወደኋላ ተመልሸ አስባለሁ፣ ወደ ልጅነታችን …

እኔና መሐሪ የ3 ከፍል ተማሪዎች ሆነን አንድ ነገር ተፈጠረ፡፡ አልረሳም፡፡ ከትምህርት ቤት ሰፈራችን እስከምንደርስ ድረስ መንገድ ላይ የምናደርጋቸውን ነገሮች አንድ በአንድ አስታውሳለሁ፡፡ ቦርሳችንን በጀርባትን አዝለን መንገድ ለማቋረጥ ግራ ቀኝ እንመለከትና፣
የመኪናዎቹን ርቀት ገምቼ ለመሻገር መንገድ ስጀምር፣ መሐሪ ልብሴን አንቆ ወደኋላ ይጎትተኛል ይኼ ነገሩ ያበሳጨኛል፡፡ እሱ ደግሞ ድፍረቴ ያበሳጨዋል …እንነዛነዛለን

ገና የትና የት ያለ መኪና የምትፈራው፣ አንተ የገጠር ሰው ነህ እንዴ?”

“የትናየት እይደለም …እውር ነህ አታይም? ..አጠገባችን ደርሶ ነበር”

ነዳጅ ማደያው አጠገባችን ነው …እዛጋ ነበር መኪናው ትንሽ ብንጠብቅ ምን ትሆናለህ…ትሞታለህ?” መሐሪ መኪና ይፈራ ነበር።

እና ቆሜ ላድርልህ ነው? ከፈለክ አንተ ቆመህ እደር…ምናይነቱ ነው?!' በቆመበት ትቼውመንገዱንም በፈጣን ሩጫ ሳቋርጥ፣ ከባዱን የቦርሳውን ማንገቻ ግራና ቀኝ ደረቱ ላይ እንቁ፣
መገዱን ወዲያና ወዲህ እያየ በሩጫ ይከተለኛል፡፡ ቦርሳው ሁልጊዜ ከባድ ነው።የማያጭቀው፣ የማያዝለው ነገር የለም፡፡ ድንገት ዝናብ ቢጥል እያለች፣ ማሚ ጃኬት አጣጥፋ ታስገባለታለች… “ውሃ ደግሞ ጥሩ ነው ቶሎ ቶሎ ጠጣ” ትልና ክዳን ባለው ትልቅ የፕላስቲክ ኮዳ ሞልታ ታሸክመዋለች፡፡ አንድም ቀን ግን ጠጥቶት አያውቅም አንዳንዴ መንገድ ላይ እንረጭበታለን፡፡

ጋሽ ዝናቡ በተራው “አረፍ ስትል አትራገጥ…እንብብ!”ብሎ የሆነ መጽሐፍ ሸክሙ ላይ ይጨምርለታል፡፡ ያኔ ነው ከበደ ሚካኤል የሚባሉ ደራሲ መኖራቸውን ያወቅነው።አንዳንዴ የቦርሳው ክብደት ስለሚያደክመው “አግዘኝ!” ይለኛል፡፡ ሂድ ወደዚያ! ኩሊ
መሰልኩህ እንዴ” እያልኩ…ቦርሳችንን እንቀያየራለን፡፡ እየተነጫነጭኩም ቢሆን ሸከምን መሸከሜ አይቀርም፡፡ ታዲያ ሸክሙ ሲበዛብን (መቸስ ጋሽ ዝናቡን ማስቆም የማይታሰብ ነው) ማሚን አሳምነን ጃኬትና ውሃውን ለማስተው ተከራከርናት ፤ እየተቀባበልን
“እንዴ ማሚ አማርኛ መጽሐፍ አለ”
“እንግሊዝኛ መጽሐፍ ትተን መሄድ አንችልም …”
“ሒሳብ መጽሐፍ ይዘን ካልሄድን አስተማሪያችን ያብዳል …ምን እንደሚያክል ደግሞ
በዛ ላይ ደብተር! ተባብረን ስናጣድፋት፣ አንዴ እኔን… አንዴ መሐሪን እየተመለከተች ፊቷ ላይ ለይቶለት የማይፈነዳ ሳቅ እንዳረበበ እንደፈለጋችሁ አታድርቁኝ ኋላ ግን ብላ እጅ ሰጠች፡፡ከመሐሪ ቦርሳ ጃኬትና ውሃ ቀነስን፡፡ መንገድ ላይ ቀላሉን ቦርሳ ወደ
ላይ እያጓንን በመያዝ ድላችንን አጣጣምናት፡፡

መሐሪ ዕድለኛ ልጅ አልነበረም፡፡ በጭራሽ ዕድለኛ ልጅ አልነበረም፡፡ የዚያኑ ቀን
ከትምህርት ቤት ስንመለስ፣ ሰማዩን ቀዶ የተዘረገፈ የሚመስል ድንገተኛ ዶፍ ወረደ፡፡እቤት ስንደርስ ውሃ ውስጥ ነክረው ያወጧት ድመት መስለን ነበር፡፡ በተለይ መሐሪ ለአንድ ሳምንት የቆየ ትክትክ ሲያጣድፈው ከረመ ማሚ ከመጀመሪያው ይበልጥ የከበደ ባለወፍራም ገበር ጃኬት ገዝታ፣ መሐሪ ቦርሳ ውስጥ ጠቀጠቀችው፡፡ ዓመቱን
ሙሉ ያ ጃኬት ከቦርሳው ተለይቶ አያውቅም ነበር፡፡

መንገዱን ከተሻገርን በኋላ እየተነጫነጨ፣ “መገጨት ከፈለክ ራስህ ተገጭ አያገባኝም” ይላል፡፡ ከዋናው መንገድ ወደ ቤታችን ወደሚወስደው የኮረኮች መንገድ መገንጠያ ድረስ ተኮራርፈን በእግሮቻችን መንገድ
👍4
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_ስድስት


#በአሌክስ_አብርሃም

ሳሌም፣ እኔና መሐሪን ገና ከሩቅ ስታየን፣ በሚቅጨለጨል ሳቋ ታጅባ ወደኛ ትሮጣለች፡፡ እናቷ ቀስ!.…ቀስ!” እያለች በዓይኗ ትከተላታለች፡፡ በየተራ እንስማታለኝ፡፡ መሃላችን ገብታ በማይገባን ቋንቋ ትኮላተፋለች፡፡ እጅና እጇን ይዘን ኦፕ! ኦፕ! እያለች ወደ እናቷ እንወስዳታለን፡፡ እንዳንዴ ትተናት ወደቤታችን ስንሄድ፣ ካልወሰዳችሁኝ ብላ መንገዱ ላይ በደረቷ ተኝታ ታለቅስ ነበር::

እኔና መሐሪ ለውዝ አሰፍረን በየኪሳችን እንይዝና፣ ለሳሌም እናካፍላታለን፡፡ ለለውዙ አንከፍልም፡፡ ለጋሽ ዝናቡ እንዳትናገር አስጠንቅቀን በዱቤ እንወስዳለን፤ ያው ቅዳሜ ልብስ ለማጠብ እነ መሐሪ ቤት ስትመጣ ማሚ “ምን ይሻላቸዋል? እነዚህ አንበጣ የሆኑ
ልጆች እያለች ትከፍላለች፡፡ ሳሌምን የዱቤ ለውዝ አስለምደናት፣ ገና ሲሰፈር መሬት
ላይ በቂጧ ዝርፍጥ ትልና ቀሚሷን ዘርግታ ታመቻቻለች፡፡ ለውዙን እንደ ዶሮ ጥሬ ቀሚሷ ላይ እንስትንላታለን፡፡ በትንንሽ እጆቿ እየለቀመች ትቆረጥማለች አንዳንዴ አንዲት የለውዝ ፍሬ ታመልጣትና፣ ያችን ለመያዝ ስትነሳ፣ የቀሚሷ ላይ በሙሉ መንገዱ
ላይ ይበታተናል፡፡ ብዙ ጊዜ ለውዟን ከያዘች ቻው ስንላት እንኳን ቀና ብላ አታየንም፤ ሐሳቧ ለውዙ ላይ ነው… “አንቺ! ቻው በያቸው እንጂ?” ትላለች እናትየዋ በሐፍረት፤ ሚስኪን የገጠር ሴት ናት፡፡

እየተሳሳቅንና ለውዛችንን እየቆረጠምን፣ ወደ ቤታችን እናዘግማለን፡፡ ለውዝ አበላላችን በራሱ ትንሽ ትርኢት ይመረቅበት ነበር፡፡ ገለባውን አራግፈን ወደላይ እንወረውርና፣ አፋችንን ከፍተን እንጠብቀዋለን…ብዙውን ጊዜ ብንካንበትም አልፎ አልፎ ግን
ከጥርሳችን ጋር እየተጋጨ አልያም አፋችን ስቶ መሬት ላይ ይወድቃል፡፡ አንስተን መብላታችን አይቀርም፡፡ ብዙ ጊዜ የሚስተው መሐሪ ነበር፡፡ ጥርሳም ስለሆንከ ነው እለዋለሁ፡፡ መላፋት እንጀምራለን፡፡ እንዲህ ነበር ደርሶ መልሳችን!

አንድ ቀን ከትምህርት ቤት ስንመለስ፣ የኢየሩስ ጉሊት ባዶ ሆኖ አገኘነው፡፡
የምትቀመጥበት ድንጋይ ብቻ ነበር ያለው፡፡ የት ሄደው ነው? ተባብለን አለፍን፡፡ በቀጣዩም ቀን ባዶ ነበር፡፡ በሦስተኛው ቀን መሐፊ እቤቷ ሄደን እንያት አለኝ፡፡ ደብተሬን አስቀምጨ ተመለስኩና፣ መሐሪን ስጠራው “ማሚ ነገ ቅዳሜ እንያትና፣ ካልመጣች ትሄዳላችሁ” ብላለች” እለኝ፡፡ ረቡዕ፣ ሐሙስና ዓርብ መሆን አለባቸው ቀናቱ
ምክንያቱም በቀጣዩ ቀን ማሚ እንዳለችው ጥድቄ እነመሐሪ ቤት መጥታ ነበር፡፡ ገና በጧቱ መሐሪ እቤታችን መጣና፣ ሁልጊዜ ሲጨነቅ እንደሚያደርገው እጁን እያፍተለተለ
“ባሏ ደብድቧት ነው የጠፋችው?” አለኝ፡፡

“ማን?

“ጥድቄ”

“መጣች እንዴ?” አልኩት …

"ጧት መጣች፤ ልብስ ልታጥብ፡፡ ማሚ ግን እንዲህ ሁነሽማ እታጥቢም! ምናምን ብላት ቁጭ ብለው እያውሩ ነው፡፡ እንዳለ ፊቷ በሞላ እባብጧል፡፡ በቢለዋ ሊያርዳት ነበር፤ አምልጣ ጎረቤት ቤት ተደበቀች

አረ!?”

ራሷ ናት ለማሚ እያለቀሰች የነገረቻት፡፡ ፊቷ ሁሉ እንዳለ አባብጧል…ጥርሴ ተነቃንቋል ብላለች!” መሐሪ ሊያወራ በፍጥነት ነበር፡፡ ልክ እሱ ራሱ ሲደበደብ አምልጦ በሩጫ የመጣ ዓይነት፡፡ ሁልጊዜም ሲጨነቅ ወይ ሲፈራ፣ እንደዚህ ነው አወራሩ፡፡ ተያይዘን
ወደቤታቸው ሄድን:: ገና በሩ ላይ ስንደርስ ሳሌም ኦፕ! ኦፕ! እያለች ወደኛ ሮጠች!
ጥድቄ ዓይኗ ሁሉ አባብጦ ከንፈሯ ደም አርግዞ ከልብስ ማጠቢያው አጠገብ ባለ
አግዳሚ የድንጋይ ወንበር ላይ፣ ከማሚ ጋር ጎን ለጎን ተቀምጠው ነበር፡፡

ማሚ በጣም ከመበሳጨቷ የተነሳ፣ ከመሐሪ ጋር ተከታትለን ስንገባ፣ እንደወትሮው ስላም እንኳን አላለችኝም፡፡ በየመሀሉ እየደጋገመች “ወይ ጥጋብ! ወይ ጥጋብ! ወይ ጥጋብ!” እያለች ከድምፅዋ እኩል ቸብ ቸብ እያደረገች ታጨበጭባለች፡፡ እንዲህ
እንደተቀመጡ ጋሽ ዝናቡ ነጭና ጥቁር መስመር ያለበት በልኩ የተስፋ የሜዳ አህያ ቆዳ በሚመስል ዥጉርጉር የሌሊት ልብሱ ላይ፣ ከጥጥ የተሠራ ነጭ ጸጉራም ካፖርት ደርቦ እየተንጠራራ ከቤት ወጣና በረንዳው ላይ ቆሞ አዛጋ፡፡ ሲያዛጋ ድምፁ በሌሊት ከሩቅ የሚስማ የጫካ እንሰሳ ዓይነት ድምፅ ይመስል ነበር፤አዋአዋዋአዋአዋአዋአዋአዋእዋእዋ!
“ጎሽ! ተነስቷል” አለች ማሚ ! እሱን እየጠበቁ ነበር
ማሚ ወደ በረንዳው መጣች፡፡ እኔና መሐሪ ደረጃው ላይ ተቀምጠን ከህጻኗ ጋር እየተጫወትን ስለነበር፣ እንድታልፍ ጠጋ አልንላት፡፡ እዚያው ደረጃው ሥር እንደቆመች ጋሽ ዝናቡን ሽቅብ እያየች፣

“ይኼ ባለጌ የሠራውን አየህ?” አለች።

“ማነው” አሉ ኮስተር ብሎ፡፡

ወደ ጥድቄ እየጠቆመች ባል ተብየው ነዋ!” አለች፡፡ጋሽ ዝናቡ ጥድቄን ገና ያኔ ያያት ይመስል ደህና አደርሽ?” አላት::

ከተቀመጠችበት ተነስታ ጎንበስ ቀና እያለች እግዚሃር ይመስገን! ጋሽ ደህና አደሩ” አለች።

እንዲህ ሕግ ባለበት አገር፣ እንደ እባብ ቀጥቅጦ ቀጥቅጦ፣ ጎረቤትኮ ነው ነብሷን ያተረፈው:: ነይ ወደዚህ አሳይው!” አለች፤ ማሚ፡፡ እንደዚህ ቀን ስትበሳጭ አይቻት አላውቅም፡፡ ጥድቄ ቀረብ አለች፤ ስትራመድ ታነከስ ነበር…

“አንድ ነገርማ አድርግ ዝናቡ እንዲህ ዓይነቱን ጥጋበኛማ “ሀይ!” ካላሉት፣ ነገ ተነስቶ ሰው ይገድላል፣ የምታረገውን አርግ በቃ!” ጋሽ ዝናቡ፣ ማሚ ተማምናበት የሆነ ውለታ ስለጠየቀችው ይሁን ወይም በጕዳዩ አዝኖ፣ ብቻ ፊቱ ላይ የሆነ ኩራትና ወንድነት
እንዣበበት፡፡

ፊቷን በትኩረት ከተመለከተና ምን ልሁን ብሎ ነው እንዲህ ያደረገሽ?” አለ፡፡

“ጥጋብ ነው ጋሸ

“ምንድነው ጥጋብ? በደንብ ንገሪኝ አለ ጋሼ ችሎት ላይ እንደተሰየመ ዳኛ ነበር
አነጋገሩ፡፡
ለኔ የነገርሽኝ እንድ ባንድ ንገሪው አትፍሪ እሱ መላ አያጣም” አለች ማሚ፡፡ ብስጭት ብላ ነበር ።

ንገሪኝ አትፍሪ! አለ ጋሼ ጋሽ ዝናቡና ማሚ በአንድ ጉዳይ ላይ እንዲህ
ተስማምተው ሲያወሩ ሳያቸው፣ የመጀመሪያዬ ነበር፡፡

እኔ ሰይጣን ይላካቸው ጠላት፣ ምናባቴ አውቄ.. እዚህ ፈረንጆቹ ቤት ውስጥ ያሉ
ሁለት ፈረንጆች፤ምን ፈረንጅ ናቸው አማረኛውን ሲያቀላጥፉት ያዩ እንደሆነ፣ ለጉድ ነው ጋሽ፣ እኔም እንደነሱ አይፍታታልኝ:: መጡና ባል አለሽ ወይ? አሉኝ፡፡ አዎ! ስላቸው ጊዚ
ባለቤትሽ ቤት በሚኖርበት ቀን ሁለታችሁንም እናነጋግራለን፣ እቤትሽ ውሰጅን አሉ:: እኔ ደሞ መቼም ደሀ ጉጉ ነው፣ እርዳታ ይሰጣሉ ሲባል ሰምቼ፣ አዝነውልኝ ሊሰጡኝ ይሆናል ብያለሁ፣ በኋላ ማክሰኞ አመሻሹ ላይ ተቃጥረን ሦስት ሁነው እቤቴ መጡ፡፡
መጡና 'ይችን ልጃችሁን ፈረንጅ አገር ልከን እናስተምራት፣ ለሷም ለእናተም ጥሩ ነው:: አሉ”

“አሃ …ማደጎ” አለ፤ ጋሽ ::

“ማደጎ ይሁን? ምን ይሁን? ምናባቴ አውቄ ብለው፡፡ ከመሬት ተነስተው ከፈቀዳችሁ እንውሰዳት፤ እዚህ መንገድ ለመንገድ ከምትበላሽ አሉ እንጅ! …ኋላ እንደው እንዲህ ሲሉ ነጥቀው የወሰዱብኝ መሰለኝ አንዘፈዘፈኝ፤ ጋሽ! አንዘፈዘፈኝ !ሌላ ምን ተስፋ አለኝ
ምን የዓይን ማረፊያ አለኝ … ልጄን አቅፌ ውጡልኝ ከዚህ ቤት ብዬ ኡኡ! አልኩ፡፡
አስቡበት ብለው ወጥተው ሄዱ …
እሽ! " አለ፣ ጋሽ ብዙም የገረመው አይመስልም፡፡
“ፈረንጆቹ ወጣ እንዳሉ፣ ባለቤቴም ከተል ብሎ ወጥቶ ሄደ፡፡ ካለወትሮው እስከ እኩለ ሌሊት አምሽቶ፣ ስክር ብሎ መጣ፣ መጣና የልጄን ዕድል ልታበላሽ ደህና እግዜር ያያትን፤ ትሄዳለች፤ እኔ አባቷ ፈቅጃለሁ፤ ፈረንጅ አገር በአውሮፕላን ሽው! …እዚህ ማስክ የለም! ጭርንቁስ.…እከካም! ትሄዳለች” አለኝ፡፡ ልጄን ሊነጥቁኝ ሲማከሩብኝ ያመሹ
መሰለኝ ጋሸ፡፡ ሰካራም ነው፡፡ አንድ
👍1
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_ሰባት


#በአሌክስ_አብርሃም

...ማሚና ኢየሩስ ተያይዘው ወደ ውስጥ ከገቡ በኋላ፣ ጋሽ ዝናቡ በረንዳው ላይ ባለው ተወዛዋዥ ወንበር ላይ ተቀምጦ በዝምታ ወደ ፊትና ወደ ኋላ ሲወዛወዝ ቆየና፣ ረጋ ባለ ድምፅ፣

“መሐሪ ቦርሳዬን ኣቀብለኝ” አለ፡፡

ሁል ጊዜ ሥራሲሄድ የሚያንጠጥለሰውን ቡናማ የቆዳ ቦርሳ ከፍቶ ወረቀቶች፣ የወንጀለኛ መቅጫ ሕግ መድሐፍና እና ጥቁር ብድር አወጣ፡፡

ልጅቱን ጥራት አለው መሐሪን በአገጩ ወደገባችበት እየጠቆመ ፡፡ ማሚና ትድቄ
ተያይዘው መጡ።

"የባለቤትሽ ስም ማነው?"

ጋንጩር ነው እንጂ ምን ስም አለው ብላ በብስጭት ከተናገረች በኋላ፣ ማሚ በከንዷ ግሸም ስታደርጋት ተረፈ! ተረፈ መርጊያ ምን ይተርፋል ይኼ ጦሱ ነው የተረፈን አለች

“ከዚህ በፊት ደብድቦሽ አልያም ሰድቦሽና እስፈራርቶሽ ያውቃል …”

ስድብና ማስፈራርያማ ስንቁ ነው…ምሳና ራቴ … ድንገት ያሰረችውን ሻሽ ከራሷ ላይ መንጭቃ ፈታችና የተጎሳቆለ ጸጉሯን ከጆሮዋ በላይ ገለጥ ገለጥ አድርጋ …"ይኼው የዛሬ ዓመት በቡና ስኒ ወርውሮ የፈነከተኝ፡ ሐኪም ዘንድ ሄጄ ተሰፍቼ ነው!እስካሁንም ቅዝቃዜ
ሲሆን ያመኛል ፡ ያዞረኛል” አለች፡፡ ማሚ አዲስ የሰማችው ነገር ስለሆነ ተንጠራርታ ጠባሳውን አየችና ወይ ጥጋብ!" ብላ በብስጭት ተነፈሰች፡፡

ጋሽ ዝናቡ ጥድቄን የተለያየ ነገር እየጠየቀ፡ አንድ ገጽ ከግማሽ የሚሆን የክስ ማመልከቻ ፅፎ ጨረሰና ጉሮሮውን ጠርጎ በጎርናና ድምፁ አነበበላት፡፡ “በተደጋጋሚ በሚያደርስብኝ
አካላዊ ጥቃት የእኔም ሆ የልጄ ሕይዎት አደጋ ላይ በመውደቁ እያለ፣ እንብቦ ሲጨርስ ጥድቄ ስቅስቅ ብላ አለቀሰች፡፡ ወረቀቱ ግርጌ ላይ በጣቷ አስፈርሟት፡፡
መፅሀፍቱን ወደ ቦርሳው ጨማመረና፡ ለራሱ በሚመስል ድምፅ “በቃ! ሰኞ ክስ እንመሰርታለን አለ።

ማሚ ወደኋላ ቀረት አለችና ጋሽ ዝናቡን

“ቡና ላፍላ እንዴ? አለችው።

"እሽ" አለ ሁለቱም ንግግራቸው ለስለስብሎ ነበር
በስንተኛው ቀን እንደሆነ እንጃ፣ የጥድቄ ባል ታሰረ ብሎ መሐሪ ነገረኝ፡፡ ለሁኔ ግን መልኩን እንኳን ከማላውቀው ሰውዬ እስር በላይ፣ እስካሁን ውስጤ የቀረው ማሚ
ከጥድቄ ጋር ፍርድ ቤት ሂዳ ያየችውን ስታወራ ጣል ያደረገችው ነገር ነበር፡፡ ባልየው ችሎት ገብቶ ዳኛው ፊት ሲቆም፣ መርፌ ቢወድቅ በማያሰማው የችሎቱ ጸጥታ ውሰጥ አባባ ባቦ የሚል ድምፅ ተሰማ፡፡ ሳሌም ነበረች

ዐመሉ ውሻ ነው እንጂ፤ ማታ ሲገባ ለልጁ በኪሱ ዳቦ ሳይዝ አይገባም ነበር አለች ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ጥድቄና ሳሌም እነ መሐሪ ሴት እቃ ቤት” የምንላት፡ በዋናው ቤት ኋላ ባለች ሰርቪስ ቤት ውስጥ መኖር ጀመሩ፡፡ ይኼንንም ሐሳብ ያመጣው መሐሪ ይሁን እንጂ ሙግቱ ላይ ነበርኩበት፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ እኔና መሐሪ አገር ምድሩ ያውቃው ዳኛ፡
ጋሽ ዝናቡ ፊት በድፍረት ቁመን የራሱን ቤት ለአንዲት ደሀ ያካፍል ዘንድ የሞገትንበት፣ ሞግተንም ያሸንፍንበት ፋይላችን ነበር፡፡ ዝም ብሎ ሲሰማን ቆየና

“ጥሩ ጠበቃ ወጥቷችሁ የለም እንዴ ጃል” ብሎ ፈቀደ፡፡ ያኔ ሳሌም ዕድሜዋ ከሁለት ዓመት አለፍ ቢል ነበር፡፡ ሲበዛ ሁለት ዓመት ከአምስት ወር!

አባቴ ጎበዝ አናጺ ነበር፣ ከአናጺነት የካኪ ቱታው ውጭ የክት ልብስ ሲለብስ ይጨንቀዋል፡፡ በተለይ ጋቢ ሲለብስ አንዴ ከትከሻው እየጠንሸራተት፣ ሌላ ጊዜ መሬት ለመሬት እየተጎተተ ያስመርረው ነበር፡፡ የፈለገ ቢዘንጥና ቢታጠብ፡ ልብሱ ላይ የተለጠፈ፣ አልያም ጸጉሩ ላይ የተሰካ አንዳች የእንጨት ፍቃፋቂ አይጠፉም፡፡ ብዙ ማውራትና ብዙ መቀመጥ አይሆንለትም፡፡ በሕይወቱ ዘለግ ያለ ነገር አወራ ከተባለ፣ ወይ
ስለዕቁብ ነው፣ ካልሆነም ስለ እንጨት እና ሚስማር መወደድ ነው:: ዘወርወር ያለ ዉሬ በቀላሉ የሚረዳ ሰው አልነበረም። ነገሩ ሁሉ አጭርና ቀጥ ያለ ነው። ይኼንን ነገሩን እኔ ብወድለትም፣ እናቴ ግን ሁልጊዜ ምን ቢያደርጉት ይሻላል ይኼ ሰው ነገር መዘንኮር እያለች ትበሳጫለች፡፡
ታዲያ እንደ ሁልጊዜው በእናቴ እስገዳጅነት ጧት ተነስቶ ቤተክርስቲያን ደረስ ብሎ መመለሱ ነበር፡፡ በር ላይ ቁሜ እጁን እያስታጠብኩት ነው፣

ከሰብከቱ ሁሉ የማይዋጥልኝ፣ ይኼ ክርስቶስ አናጢ ነበር የሚሉት ነገር ነው ..
ታዲያ ቢሆን እና ምንህ ተነካ ሥራህን ተሻማህ!?…ሆ” አለች እናቴ፡፡

እኔ ምኔ ይነካል እንደው የመምሬ አፈወርቅ ነገር ቢገርመኝ ነው እንጅ!”
እሳቸው አልጻፉት መጽሐፉን ነው የሰበኩት!” አባቴ ዝም ብሎ ቆየና ድንገት
ክርስቶስ መምህር ነበር ሲሉን አይደለም እንዴ፤ ይኼው ቄስና መምህሩን ሁሉ
የምንፈራና የምናከብር

እና አለች እናቴ ሐሳቡ ኤልያያዝ ብሏት፡፡

“አናጢ ነበር ካሉ፣ ለምን አናጢ አያከብሩም ታዲያ? መምሬ አፈወርቅ ራሳቸው የሚያከራዩትን ሁለት ክፍል ቤት የሠራሁበትን የላቤን ዋጋ እስካሁን መች ከፈሉኝ? እንግዲህ በክርስቶስ አምሳል መዶሻ ያነሳውን የመንደርሽን አናጢ ካላከበርሽ፣ ክርስቶስንስ መች ታከብሪያለሽ! መስቀል ላይ ስላልቸነከሩኝ ነው እንዴ? ይሄው የዕቁብ ከፍይ ጎደለብኝ

እናቴ ዝም አለች፡፡ ይኼኛው ዝምታዋ የኩርፊያ ነው፡፡ በዝምታዋና በዝምታዋ መካከል ያለውን ልዩነት፣ ፊቷን እንኳን ባላይ መለየት እችላለሁ፡፡ እንዴት እንደሆን እንጃ፤ ወሬ ለማስቀየር ይሁን፣ አልያም በአባቴ ብስጭት ንዴቷን እኔ ላይ ለመወጣት፣ “ምናለ እንዲያው እሁድ እንኳን ቤተክርስቲያን ብትስም፣ ይኼው መሐሪን እንኳ ስሞ ሲመለስ
አገኘነው የተባረከ ልጅ አለች፡፡ መሐሪ ለምን ቤተክርስቲያን እንደሚሄድ ስለማውቅ፣ሳቄን አፍኜ ዝም አልኩ፡፡ በቤተ ክርስቲያን ሰበብ ወጥተው ከሮሐ ጋር እሁድ እሁድ ጧት ይገናኛሉ፡፡ ዛሬም አብረው ነው ያገኟቸው…

አባቴ ድንገት “አብራው የነበረችው ልጅ የግርማ ልጅ አይደለችም እንዴ?” ብሎ ጠየቀ።

ብትሆንሳ ታዲያ? አብረው ነው የሚማሩት?” እናቴ ስለተበሳጨች ንጭንጭ ብላለች፡፡

እሱማ ..እንዲያው ግን፣ የግርማ ልጅና የዝናቡ ልጅ አብረው ሳይ

ነሽ እቴ …የማያሳስበው ያሳስብሃል”

“ግርማ ጥሩ ሰው ነበር …ሆቴሉን በጠገንኩ ቁጥር አክብሮ ክፍያውስ ቢሆን፡ ከጥሩ ሰው ልጅ ጋር መግጠም ጥሩ ነው” አለ አባቴ፡፡ የሮሐ አባት ጋሽ ግርማ ከተማው ውስጥ የታወቀ ሀብታም ነው::ወደኋላ ክብልስ የሚል ጸጉር ያለው፣ የህንድ የፊልም አክተሮች የመሰለ፣ ፈገግታ ከፊቱ የማይጠፋ ሰውዬ፡፡ የነዳጅ ማደያ እና ትልቅ ሆቴል አለው::
ከሁለት ዓመት በፊት በሆነ ጉዳይ ተከሶ ፍርድ ቤት ይቀርባል ፡፡ጉዳዩ በትክክል ምን እንደሆን እንጃ፤ ከመንግሥት ጨረታ ጋር የተያያዘ ነገር ነው ሲሉ ነው የሰማሁት

ዳኛው ጋሽ ዝናቡ ነበር፡፡ እንግዲህ እንደሚወራው፤ ጋሽ ግርማ ነገሩ አላምር ሲለው፤ ከክሱ ነፃ ለመውጣት ሲል ለጋሽ ዝናቡ ጠቀም ያለ ብር ጉቦ ለመስጠት አማላጅ ይልካል፡፡ ጋሽ ዝናቡ አማላጁንም ጋሽ ግርማንም ጠራርጎ እስር ቤት አስወረወራቸው።ጭራሽ የሮሐን አባት፣ በተከሰሰበትም ጒዳይ የሁለት ዓመት እስር አከናንቦት፣ ፍርዱ ወደ ገንዘብ ተቀይሮለት ነው የተፈታው ይባላል። ሮሐና መሐሪ ታዲያ የአባቶቻቸውን ታሪክ
ለአባቶቻቸው ትተው የጦፈ ፍቅር ውስጥ አሸሼ ይላሉ!

ሮሐ አባቷ ለመሐሪ ቤተሰቦች ያለውን ጥላቻ ስትገልጽ ታዲያ፣ እየሳቀች እንዲህ ትላለች
“መሐሪ እኛ ቤት ሽማግሌ ቢልክ፣ ዳዲ ገና ሊያገባኝ የጠየቀው የጋሽ ዝናቡ ልጅ መሆኑን ሲያውቅ፣ ሁሉንም ነው የሚረሽናቸው ሂሂሂሂ፡፡ እኛም እንዲህ ነበር የምናስበው:: ጋሽ ዝናቡ መሐሪ ሴት ማፍቀር ብቻ ሳይሆን የጋሽ ግርማን ልጅ ማፍቀሩን ቢሰማማ

ለዚያም ነበር ያንን ሁሉ ጊዜ
👍1
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_ስምንት


#በአሌክስ_አብርሃም

ወደ አስራ ሁለተኛ ክፍል አልፈን ለማትሪክ የምንዘጋጅበትን መጽሐፍና፣ያለፉ ዓመታት
ተፈታኞችን የፈተና ወረቀቶች ሰብስበን እንሙት ባልንበት ክረምት ታዲያ፣ ይሆናል
ብለን ያላሰብነው፣ የልብ ምታችንን ቀጥ አድርጎ ሊያቆም የሚችል፣ ድንገተኛ ነገር
ተፈጠረ (የሰው ልብ አቻቻሉ )

ትምህርት ቤት ለክረምት ከተዘጋ በኋላ፣ በተለይ ቅዳሜ ቅዳሜ ሄኖክ የሚባል አብሮን የሚማርና ሮሐን ክፉኛ ይከጅል የነበረ ልጅ፣ ተስፋ ቆርጦ ይሁን አልያም እሷን ባላገኛትም እንኳን፣ ጠረኗ ቤቴን ይሙላው ብሎ …ብቻ ለጥናት በሚል ሰበብ፣ የተከራያትን አንዲት ክፍል ቤት ለመሐሪና ሮሐ ይለቅላቸውና ዓለማቸውን ሲቀጩ ይውላሉ፡፡ የዓለም ቀጨታው ከመሳሳም አያልፍም” ቢልም ወዳጄ መሐሪ … ነፍሴ እሺ ብላ አታምንም ነበር፡፡ እንዲያው ይሁንልህ በሚል ቸልተኛ መሸነፍ አምኘለት እናልፈዋለን፡፡

ታዲያ ሲመሻሽ ሄኖክን ለቤቱ አመስግነን ሮሐን በአሳቻ መንገዶች እያቆራረጥን
እስከቤቷ አቅራቢያ ሸኝተን (የት ዋልሽ ስትባል የት እንደምትል እንጃ ወደ ቤታችን
እናዘግማለን፡፡ መሐሪና ሮሐ ሁልጊዜ ከዚህ ቤት ሲወጡ ዝምተኛና አንገታቸውን የደፉ የሚሆኑበት ነገር አለ፥ ምን ሆናችሁ አልልም፡፡ በሌለሁበት ጉዳይ መተፋፈሩ እኔም ላይ ተጋብቶ አፌን ይዘጋኛል፡፡ ወደ ቤት ስንመለስ በመንገዳችን፣ መሐሪ ዓይኔ ቀላ እንዴ? ከንፈሬ አበጠ እንዴ? - ጸጉሬ እንዴት ነው? የሚሉ አንዳንድ ወላጅ ሊያውቃቸው የማይገቡ ነገሮችን ማድረጉን ሊጠቁሙ የሚችሉ ምልክቶችን ተባብረን አሻራ እናጠፋለን፡፡ እቤት የሚጠብቀው ሣር ቅጠሉን የሚጠራጠር የዳኛ ዓይን ነው!

የዚያን ቀን ቅዳሜ ማታ መሐሪ፣ “ግባና ሰላም ብለሃቸው ትሄዳለህ ብሎ ገፋፍቶኝ
(ሁልጊዜ ራሳቸው ቤት ውስጥ ብቻውን መግባት ለምን እንደሚፈራ አይገባኝም) …ወደ ቤታቸው ተያይዘን ገባን፡፡ ጋሽ ዝናቡ በረንዳው ላይ ተቀምጦ መጽሐፍ ያነብባል፡፡
መጽሐፉን አጠፍ አድርጎ ጎረምሶች ከየት ነው” አለ።

እግራችንን እናፍታታ ብለን .” አልኩ (ተከላካይ ጠበቃ ይመስል የምፈጥነው ነገር አለ)

"ሙሉ ከሰዓት እግር ስታፍታቱ …መልካም ዝም ተባባልን፡፡

እንግዲህ ወደ መጨረሻው መጀመሪያ እየቀረባችሁ ነው፣ ዝግጅት እንዴት ነው?
“ያው …" መሐሪ ተንተባተስ ድንገት ጋሽ ዝናቡ ሂዱ እስቲ ወንበር ይዛችሁ ኑ!” አለ፡፡ የየራሳችንን ወንበር ይዘን መጠንና፣ ፊት ለፊቱ ተቀመጥን፡፡ ተጨንቀናል። ጋሽ ዝናቡ ቁጭ በሉ አለ ማለት፣ ልክ አሰተማሪ ውጣ ተንበርከክ እንደሚለው ዓይነት፣ የቅጣት ስሜት ያለው ነገር ነው፡፡

እና እግር ማፍታታቱ የት የት ወሰዳችሁ?” አለን ድንገት፡፡ እኔና መሐሪ ተያየን
አብርሃም” አለኝ (የማሪያምን ብቅል ፈጭቻለሁ ብል ደስታዬ)

"አቤት ጋሸ”

“መሐሪ ወንድምህ ማለት ነው፤ እናንተ አሁን ጓደኛ አትባሉም፣ ለኛም ቢሆን ከመሐሪ ለይተን የማናይህ ልጃችን ማለት ነህ፣ የመሐሪ ነገር የእኔን ያህል የእናቱን ያህል ሊያሳስብህ ይገባል፡፡ እፈለጋችሁበት ስትሄዱ፣ የት ወጣህ? የት ገባህ? የማንለው ለምን ይመስልሃል? ስላደገ ችላ ብለን ነው? አይደለም! አንተን ስለምናምንህ፣ ጥሩ ልጅ ስለሆንክና፣ መጥፎ ቦታ ሲውል ዝም ብለህ እንደማትመለከተው ስለምናምን ነው፡፡
ይገባኛል ጓደኝነታችሁ፣ እርስ በርስ ነገሮችን የምትሸፋፍኑት ነገር፥ ግን ደግሞ
ከሪያሊቲው ብዙ መራቅ የለባችሁም፡፡” ብሎ ተራ በተራ አዬንና

ስለ ሮሐ ሁሉንም ነገር አውቃለሁ፡፡” አለን:: የመሐሪ ጉሮሮ ገርገጭ ሲል ሰማሁት፡፡ ምራቁን ሳይሆን ሰላሳ ሁለት ጥርሱን ባንዴ የዋጠው ነበር የሚመስለው፡፡
“ሮሐ ኧረ ሮሐን አናውቃትም …ማናት? …” ብዬ ወደ መሐሪ ስዞር፣ አንገቱን ደፍቶ
መሬት መሬቱን ይመለከታል ፡፡

“መሐሪ እናተ ቤት ነኝ እያለ፣ የት ያመሽ እንደነበር አውቃለሁ፡፡ ከመጀመሪያው
አውቃለሁ ኢትስ ኦኬ” አሁን ልወቅሳችሁ አልያም ልከሳችሁ አይደለም ዕድሜያችሁ ነው፡፡ ሰው እናትና አባቱን ይተዋል…” ይላል መጽሐፉም አይደለም እንዴ መሐሪ እሁድ ጧት ቤተክርስቲያን ስትሄድ እንደዛ ሲሉ አልሰማህም?…” እለና ሃሃሃሃ ብሎ ሳቀ፡፡አሳሳቁ የመሐሪን የእሁድ ጧት ጉዳይ እንዳወቀ የሚያሳብቅ ዓይነት ነበር፡፡ “ሕፃን አይደላችሁም፤ በመደባበቅ ጫካ ለጫካ በመሄድ፣ የጥናት ጊዚያችሁን ማባከን የለባችሁም ያውም ባለቀ ሰዓት ትምህርት ዋናው ጉዳይ ነው፡፡ ትምህርት!
ትምህርት! ባለማመን ቀስ ብዬ የጋሽ ዝናቡን ፊት ስመለከተው ዓይን ለዓይን
ተገጣጠምን፡፡ መልሼ አቀረቀርኩ ፡፡

“መሐሪ”

“እቤት ጋሽ”

“ስሚመቻት ቀን አምጣትና ከእኔም ከእናትህም ጋር እስተዋውቀን፡፡ ከዚህ በኋላ ጢሻ ለጢሻ እየዞራችሁ ጊዚያችሁን ስማይረባ ድብብቆሽ እንዳታሳልፉ፡፡መገናኘት ሲኖርባችሁ እዚሁ ትምጣ

“ማን መሐሪ ተንተባተበ፡፡

“ከዚህ ሳምንት እንዳያልፍ! አሁን ሂዱ” ማሚን እንኳን ገብቼ ሰላም ሳልላት በቀጥታ ከበረንዳው ወደ ቤቴ ሮጥኩ፡፡

መንገድ ላይ ለራሴ እንዲህ እያልኩ ነበር፡፡ “ከስብከቱ ሁሉ የማይዋጥልኝ ይኼ ሰው እናትና አባቱን ይተዋል የሚሉት ነገር …አሁን ጋሽ ዝናቡ ልተውህስ ቢሉት የሚተው ሰው ነው ?
👍1
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_ዘጠኝ


#በአሌክስ_አብርሃም

ጋሼ መቀለድ ሁሉ
ጀመረኮ” ስንላት “ይኼ ስራው ኮስታራ አደረገው እንጂ፣ ድሮማ ጥርስ አያስከድንም ነበር አለን፡፡ መሐሪ ታዲያ ከዚያ በኋላ በሆነ ነገር ሲጨናነቅ “ሳቃቸውን ድሮ ጨርሰው እኛ ያጨናንቀናል” ይላል፡፡

ጋሽ ዝናቡ ለምሳ ወደቤት ካልተመለሰ፣ በቀን አንዴ እየደወለ እሺ! ጥናት እንዴት
ነው?” እያለ ይሰልለናል፡፡ ያን ሰሞን ሥራ ይበዛበት ስለነበር (ተዘዋዋሪ ችሎት የሚባል ነገር) ብዙ ባያገኘንም አምሽቶ ሲመጣ፣ በቀጥታ ወደ ከፍላችን ብቅ ይልና በሩን ያንኳኳል፡፡ እንደማሚ በርግዶ አይገባም፣ እንዲያውም ወደ ውስጥ አይገባም እንዴት እየሄደ ነው?” ይለናል፡፡ አፋችን እየተንተባተበና ቃላት አፋችን ላይ እየተጋጩ “ጥሩ ነው! ምንም አይል፡፡” እንላለን፡፡ “አይዞን!” ብሎ ተመልሶ ይሄዳል፡፡ ዓርብ ዓርብ ታዲያ
እዚያዉ በር ላይ እንደቆመ ዋሌቱን ከኋላ ኪሱ ያወጣና፣ ድፍን አምሳ ብር መዞ በሩ ሥር የቆመች የመጽሐፍ መደርደሪያ ጫፍ ላይ አስቀምጦልን ይሄዳል፡፡ ብዙ ጊዜ ሮሐንን እንጋብዝዎታለን፡፡ በተረፈው ለሳሌም እና ለማሚ ኬክ እንገዛላቸዋለን፡፡ ሁለቱም ኬክ ይወዱ ነበር፡፡ ማሚ ኬክ በኛ ጊዜ ቀረ …እያለች፣ ሳሌም ነገም ኬክ እንበላለን እያለች ትዝታና ተስፋን ዛሬ ላይ እንጋብዛለን፡፡

ሮሐ ቅዳሜ ቅዳሜ እነ መሐሪ ቤት መምጣት ከጀመረች ሰነባብታ ነበር፡፡ ጋሽ ዝናቡ ወታደራዊ ትዕዛዝ መሠረት በስንት ክርከርና ፍርሃት (መሐሪ አይሆንም ብሎ በኔው ውትወታ) አምጥተን ካስተዋወቅናት በኋላ፤ ከእኛም በላይ ቤተኛ ሆና ቁጭ አለች፡፡
“በምን ቀን ነው ያስተዋወቅናትም እስከምንል፡፡ በተለይ ማሚ ልክ እንደ ልጇ ሚስት ነበር አቀባበሏ፡፡ ታዲያ መሐሪን ለብቻው እንደዚህ ስለው ሚስት ናትና ይለኛል፡፡ማሚም ፊት ይሁን ጋሽ ዝናቡ ፊት፣ ሮሐ በመጣች ቁጥር ግን ሁልጊዜ ያፍራል። ፍቅረኛው እቤቱ መምጣቷ ብዙ ምቾት የሰጠው አይመስለኝም ፡፡ እውነቱን ለመናገር
እኔም የሮሐ ነገር ምቾት ነስቶኝ ነበር፡፡

እስተዳደጓ ይሁን አልያም ተፈጥሮዋ፣ ሮሐ ፍርሃት የሚባል ነገር ያልፈጠረባት ልጅ ነበረች፡፡ ከልክ ያለፈ ነጻነቷም በመሸማቀቅ ጭብጦ ላከልነው ለእኔና መሐሪ በቀላሉ የሚለመድ ነገር አልሆን ብሎ ተቸግረን ነበር፡፡ መሐሪ ወላጆቹ ባሉበት ሮሐን ፈጽሞ አጠገቡ እንድትቀመጥ አይፈልግም፡፡ ሮሐ ደግሞ ጎኑ ከመቀመጥ አልፋ ክንዱን ትከሻው
ላይ ጣል ታደርጋለች፡፡ ጋሽ ዝናቡ ፊት ጭምር እንደዚያ ታደርጋለች፡፡ መሐሪ ታዲያ ክንዷ ባረፈበት ቁጥር፣ ዝንብ እንዳረፈበት ፈረስ ሰውነቱን እያነዘረ ክንዷን ሊያባርረው ይታገላል፡፡ አቤት ያ ትዕይንት እንዴት እንደሚያዝናናኝ፡፡

አንድ ቀን ማትሪክ ወስደን ዕረፍት ላይ በነበርንበት ሰሞን፣ ሮሐ እነመሐሪ ቤት መጥታ ሰብሰብ ብለን እናወራለን፡፡ ልክ እንደ ጓደኛዋ ነበር ጋሽ ዝናቡን የምታወራው፡ስትጠራው ሁሉ “አንተ” እያለች ነው፡፡ ድንገት “ጋሺ ማሚ ጋር እንዴት ተገናኛችሁ ግን አለችው፡፡ እንዲሁ አለችው፡፡ እኔና መሐሪ ተሳቀን ልንሞት፡፡ መሐሪ በቀስታ አመልካች ጣቱን ከጆሮው በላይ ራሱ ላይ ሰክቶ እንደቡለን መፍቻ እያዞረ አሳየኝ፣ የማታል እንዴ?” ማለቱ ነበር: ትከሻዬን ሽቅብ ሰበቅኩና ሳቄን አፍኜ ዝም አልኩ፡፡ ተነሽና ከዚህ ቤት ውጭ ቢላትስ እያልኩ ሳስብም ነበር: ጋሽ ዝናቡ ግን፣ ከት ከት ብሎ ስቆ ራሷ ትንገርሽ እኔ እርጅናው ነው መሰል ነገር እየረሳሁ ነው? አላት

በእነዚያ ወራት ያ በጋሽ ዝናቡ የቁጣ መንፈስ የተሞላ ሰፊ ግቢ፣ የጥሩ ቤተሰብ ድባብ አርብቦበት ነበር፡፡ የተቋጠረው የጋሸ ፊት እነመሐሪ ግቢ እንደልጅ ተንቀባራ ባደገችው
ሳሌም የልጅነት ቡረቃ ተፈቶ ዘና ሲል አይቸዋለሁ በሮሐ ግዴለሽ ወሬ ሳይወድ በግዱ የተለጎመ አፉ ተፈቶ ሲያወራ ታዝቢያለሁ! “ጋሼ ይኼኮ በቃ የሥራ ጐዳይ ነው አጋጣሚ ነው …ለምን ከአባባ ጋር አትታረቁም ትለዋለች፡፡ ጋሽ ዝናቡ እየሳቀ አባትሽ ከሕግ ጋር እንጂ መች ከእኔ ጋር ተጣላ” ይላታል።

“ዋትኤቨር ብትታረቁ ይሻላችኋል …እዚች ጠባብ ከተማ ውስጥ በተገናኛቹ ቁጥር
ከምትገለማመጡ፡፡ ጋሽ እያያት ይስቃል፡፡ አንድ ቀን ታዲያ ጋሽ ለእኔና መሐሪ ሮሐ
ጥሩ ልብ ያላት ልጅ ናት፤እንዳታስቀይሟት ብሎን አረፈው፡፡ መሐሪስ እሽ፣ እኔ ምን
ቤት ነኝ እያልኩ ተገረምኩ፡፡ አድናቆቱ ወደማሚም ተጋብቶባት ነበር ሮሐዬ ድንጋይ የምታናግር ተጨዋች አሉ እንጅ የኛ ዝጎት፣ ማልጎምጎም ብቻ፤ ወይ ፈታ ብለው አያወሩ " አለች ወደኔና መሐሬ እያየች፡፡ ሮሐ ታዲያ ኧረ ጋሽ እንደምታካብዱት አይደለም፣ ደስ የሚል ፈታ ያለ ሰው ነው ትለናለች! እኔና መሐሪ በአንድ አፍ ያልተያዘ … ብለን እንሳሳቃለን:: የዚያ ሰሞን የአስራ ሁለተኛ ክፍል የአማርኛ። ላይ የነበረ ጥያቄን እያስታወስን፡

ጥያቄ ቁጥር 7. ያልተያዘ.........
ሀ መያዝ አለበት

ሊ ግልግል ያውቃል

ሔ መያዙ አይቀርም

መ. ሁሉም መልስ ነው፡፡ ይች 'ለ' የሆነች ልጅ ጋሽ ዝናቡን “ዘና ያለ ሰው ነው” አለችን።

የዚያ አዚማም ግቢ ሌላዋ ድምቀት ሳሌም ነበረች፡፡ ማሚና ጋሽ ዝናቡ አንድ መሐሪን ብቻ ወልደው የረሱትን የልጅ ሳቅ እንደገና እያስታወስች፣ በትዝታ የምታነጉዳቸው ውብ ፍጥረት። ግቢው ውስጥ ቢራቢሮዎችን ተከትላ ስትቦርቅ ጋሽ ዝናቡ የሚወዛወዝ ወንበሩ ላይ ተቀምጦ በፈገግታ ይመለከታታል ማሚ ብቅ እያለች ቀስ እንዳትወድቂ
ቃቢዳ ትላታለች፡፡ ቃቢዳ ነበር የምትላት፡፡ ሳሌም የምትበላው ከመሐሪ ፣
የምትቀመጠው ከመሐሪ ጋር፣ የመሐሪ ነገር ሞቷ ነበር፡፡ እኔና መሐሪ የአሥራ ሁለተኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ስንወስድ ፈረንጆቹ ቤት” በተቋቋመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ የአምስተኛ ክፍል ተማሪ ሆና ነበር…ሰማያዊ አጭር ባለማንገቻ ቀሚስ፣ ጉልበቷ ድረስ የሚደርሰ ነጭ ካልሲ ለብሳ፣ ገና በዚያ ዕድሜዋ ወገቧ ላይ የደረሰ ጥቁር
ጸጉሯ ቁጥርጥር ተሠርቶና ጫፉ ላይ በቀይ ቢራቢሮ ቅርፅ ባላት የፀረር ማስያዣ ተይዞላት(ማሚ ነበረች ብዙ ጊዜ የምትስሠራት) ቀተራመደች ቁጥር እንደ ጅራት እየተወዛወዘ፣ ስትሄድና ስትመጣ እስካሁን ዓይኔ ላይ አለች፡፡

እስከ ዛሬ እንደ ሳሌም ዓይነት ቆንጆ ሕፃን አይቼ አላውቅም፤ ስለምወዳትም እንደሆን እንጃ፡፡ በዚያ ላይ አፏ ዝም የማይል ፈጣንና ወሬኛ ነበረች፡፡ ስታድግ ምኞቷ ዶክተር መሆንና መሐሪን ማግባት እንደሆነ ለማሚ ነግራታለች፡፡ ካቶሊኮች ትምህር ቤት ከገባች በኋላ ግን፣ ምኞቶቿ ወደ ሦስት ከፍ ብለው ነበር ዶክተር መሆን ፣መሐሪን ማግባትና የካቶሊክ መነኩሌ መሆን፡፡ ሮሐ ይኼን ስትሰማ እየሳቀች “ይች ካሁኑ ቁልት ያደረጋት
ልጅ መሐሪን ማሚ እንኳን እንደሷ የት ወጣህ? የት ገባህ? አትለውምኮ እኔን ስታይ እንዴት ፊቷ እንሚቀያየር ትላለች፡፡

አረ ሕጻን አይደለችም እንዴ! ምን ታውቃለች? ይላል መሐሪ።
አንዳንዴ ሮሐና ሳሌም ይከራከራሉ …ሮሐ ድምፅዋን ቀንሳ (ማሚ እንዳትሰማት)
ሳሌም፣ መሐሪ የኔ ባል ነው፣ ይዤው እሄዳለሁ እሺ?” ትላታለች።

ኧረ ባክሽ! የኔ ባል ነው …ብትፈልጊ ሌላ ሰው አግቢ”

ሌላ ሰው የለም

“ይኼው አብርሽን አግቢ” ትልና ወደ እኔ ትጠቁማታለች በሐፍረት ዓይኔን የማሳርፈበት ይጠፋኛል፡፡ ሮሐ እንደ ቀልድ በጀመረችው ክርክር እንደ ትልቅ ሰው በሳሌም ትበሳጫለች፡፡

አንቺ ሕፃን ነሽ …ባል ምን ያደርግልሻል?” ትላታለች ፍጥጥ ብላ፡፡

ያስጠናኛል፣ የቤት ሥራ ይሠራልኛል፣ኬክ ይገዛልኛል .…አንችስ ባል ምን ያደርግልሻል?” ይች ሕፃን አይደለችም ትላለች ሮሒ

"ቅድም ሕፃን ነሽ አላልሽም? …ሂሂሂ”
👍1
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_አስር


#በአሌክስ_አብርሃም

ከቤታችን እስከዚህ ግቢ በተዘረጋችው
አቧራማ መንገድ ላይ የታተሙት የጫማዬ ዳናዎች ቢቀጣጠሉ ሰው አልረገጣቸውም ብለው ካስተማሩን ፕላኔቶች አንዱን ነክተው በተመለሱ፤ ግን ከመንገዱ ይልቅ ልቤ ላይ ነበር እያንዳንዱ እርምጃዬ በጋለ ብረት ማኅተሙን የተወው፡፡

ጋሽ ዝናቡ በደስታ ሁለት እጆቹን በሰፊው ዘርግቶ እፊቱ ያገኛትን ማሚን ቢያቅፋት (አፈሳት ቢባል ይሻላል) በቁሟ እጥፍጥፍ ብላ እንደ ከረባት በሰፊው ደረቱ ላይ ተቀመጠች፡፡በዚያ ሰዓት እፊቱ የኤሌክትሪክ ምሰሶም ቢያገኝ የሚያቅፈው ይመስለኛል።
መሐሪን አቅፎ ግንባሩን ጸጉሩን ሳመው::መሐሪን እንዳቀፈው እኔንም ጎትቶ ጫጩቶቿን በክንፎቿ ሥር እንደምታሳድር ዶሮ ግራና ቀኝ አቅፎ ሰፊ ደረቱ ላይ ለጠፈን፡፡ በረዥሙ ተንፍሶ ለቀቀንና ትክ ብሎ እያየን፣ ልክ ሴቶች እንደሚያለቅሱ ጠይም ፊቱ ላይ እንባው
ድንገት እየፈሰስ ችፍርግ ባለዉ ፂሙ መሃል ሰረገ፡፡ መሐረሙን አውጥቶ ዓይኑን
ጢረገና፣ ሶሪ ብሉን ወደ ውስጥ ገባ፡፡ ማሚ እንደ ፎካሪ ሳሎኑ ውስጥ እየተንራደደች ደጋግማ በየተራ ጉንጫችንን አገላብጣ እየሳመች “የኔ አንበሶች እንዲህ ነዋ! እንደ ዛሬም
ኮርቼ አላውቅ ትላለች፡፡

ጋሽ ዝናቡ ፊቱ በደስታ እንደተጥለቀለቀ ተመልሶ መጣና “ሮሐ እንዴት ሆነች?” አለ ስሪ ፖይት ቱ አለ መሐሪ፡፡

እጅግ በጣም ጥሩ ውጤት …ዋናው ያችን በር አልፎ ሙግባቱ ነው

የማትሪክ ውጤት ተነግሮ ነበር፡፡ እኔም መሐሪም አራት ነጥብ አምጥተን ዩኒቨርስቲ እንኳን የረገጠ ተማሪ በሌለበት ሰፈር ታሪክ ተባለልን፡፡ ገድላችን ከላይ እስከታች ተወራ፡፡ ጠባብ ከተማችን ሐውልት አታቆምልን ነገር ቸገራት እንጂ ስማችን አየሩን ሞላው እነዚያ መንትያ የሚመስሉት ልጆች ነቀነቁት” ተባለ፡፡ ይኼ የዳኛው የዝናቡ ልጅ እና በቀደም ቆርቆሮ ሲጠግን ከጣራ ላይ የወደቀው አናጢ ልጅ፣ ሁለቱም አራት ነጥብ
(እባቴ ከአስራ አምስት ቀን በፊት ከመሰላል ላይ ወድቆ እግሩን ወለም ብሎት እቤት ውሎ ነበር፡፡ ይኼም ወሬ ሁኖ ምልክት ሆነ)
መሐሪ ጋር ተያይዘን ወደ እኛ ቤት ሄድን፡፡ እቤት ስንደርስ፣ እናቴ ደስ ብሏት በእልልታ
ተቀበለችን፡፡ ቀድማ ሰምታ ነበር፡፡ ወሬው ቀድሞን ነበር፡፡ አገላብጣ ስማን ስታበቃ
ወደኔ ዞር ብላ ታዲያ አሁን ዩንበርስቲ ሌላ አገር ልትሄድ ነው? ብላ ጠየቀችኝ፡፡
ድምፅዋ ውስጥ እንባ የሚያቀባብል ሊተኮስ የተዘጋጀ ለቅሶ ነበር፡፡ አባቴ ጋደም ባለበት ና ሳመኝ ና የኔ ግስላ! …” ብሎ ሳመኝ፡፡(መሐሪ ከዚያች ቀን በኋላ ለሳምንት ግስላው እያለ ያበሽቀኝ ነበር፡፡ አባባ ታዲያ እየሳመኝ እዚያው ላይ እቁቡን ተቀብሎ ስለሚገዛልኝ ምን የመሰለ ልብስ” ነገረኝ፡፡ እናም በዚያው የዕቁብ ወሬ ሊጀምር ዳር ዳር ሲል፣ እናቴ
ገስጻ ወደ እኔ ውጤት መለሰችው፡፡ አይ አባባ! በጣም እኮ ነው የምወደው እንደው ዩኒቨርስቲ ስለ ዕቁብ የሚያጠና ራሱን የቻለ የትምህርት ክፍል በኖረና፤ አጥንቼ በከተማችን ትልቁን እቁብ በመሠረትኩለት እስከምል፣ በጣም ነው የምወደው አባባን፡፡ በምድር ላይ ተስፋ የሚያደርገው ብቸኛ ነገር ቢኖር ዕቁብ ነው! ልጀ ተምሮ ይጦረኛል የሚል ተስፋ እንኳን ያለው አይመስለኝም!! አሁን ራሱ ልጅህ አራት ነጥብ አመጣ ከሚለው ዜና ይልቅ፤ ልጅህ ዕቁብ ደረስው ቢሳል፣ የእግሩን ወለምታ ረስቶ ዘሎ ሳይቆም
ይቀራል? …እባባና ዕቁብ !

ውጤታችንን ስለማን ልክ በአስራ አምስተኛ ቀኑ፣ ማሚና ጋሽ ዝናቡ ድል ያለ ድግስ ደግሰው፣ ከመንደሩ ሰው እስከ ትምህርት ቤት አስተማሪዎቻችን ጓደኞቻችን ድረስ ጠሩ፡፡ ከተማው ውስጥ ያለ ጠበቃና ዳኛም አልቀረም፡፡ እንዲያውም ጋሽ ዝናቡ ሮሐን
እንዲህ አላት እሽ ካለና ከመጣ ለአባትሽ ይኼን መጥሪያ ስጭው' ብሎ የሮሐ አባት እንዲገኝ ጥሪ ላከለት፡፡ “ቢመጣም ባይመጣም እኛ እንቀውጠዋለን አለች ሮሐ፡ ጋሸ ታዲያ ፈገግ ብሎ “ እብድ የሆንሽ ልጅ፤ ወይ መጥሪያውን መሰጠት እንዳትረሸ

እሰጠዋለሁ፣ ብቻ የፍርድ ቤት መጥሪያ መስሎት አባቴን ካገር እንዳታስጠፋው ጋሽ?”

“ሀሀሀሀሀሀሀሀ” ብሎ ሳቀ ጋሼ፡፡ ከዚያ በፊትም ከዚያ በኋላም እንደዚያ ሲስቅ
አላየሁትም፡፡

የድግሱ ቀን፣ ነጫጭ የፕላስቲክ ወንበሮች ግቢውን በመደዳ ሞልተው ሲታይ፣ የግቢው ጥርሶች ይመስሉ ነበር፡፡ ያ ፈዛዛ ግቢ የሚስቅ ዓይነት፡፡ በቤቱ በረንዳ ላይ ትልልቅ ድምፅ ማጉሊያዎች ግራና ቀኝ ቆመው ግቢው ላይ የሰፈረውን የዝምታ አጋንንት ሊያባርሩ ከባሕላዊ እስከ ዘመናዊ ዘፈን ይረጫሉ ከበረንዳው ሥር ተቀጣጥለው የተቀመጡና ነጭ ጨርቅ የለበሱ ረዣዥም ጠረጴዛዎች ላይ የተደረደረው ምግብ፣ እንኳን ቢበሉት እያነሱ ቢደፉት የሚያልቅ አይመስልም፡፡ ከጠረጴዛዎቹ እለፍ ብሎ በቀይ የፕላስቲክ ሳጥን በብዙ መደዳ ቢራ ተከምሯል ..

ጋሽ ዝናቡ እዲስ ጥቁር ሙሉ ልብስ ለብሶና፣ ጥቁር የቴክሳስ ባርኔጣውን አናቱ ላይ ደፍቶ፤ በእንግዶቹ መሀል እየዞረ፣ ብሉልኝ ጠቱልኝ ይላል፡፡ ማሚ በበኩሏ እንደዛን ቀን አምራ አይቻት አላውቅም ከወትሮው ረዘም ያለ ሹል ተረከዝ ያለው ደማቅ ቀይ ጫማ
ለረዥም ቅዱ ጉልበቷ ድረስ የሚዘልቅ ቀይ ቀሚስ ለብሳ በተጋባዥ መካከል
ትውረገረጋለች፡፡ ሰርግ ነበር የሚመስለው::ሳሌም ከኋላዋ ማሰሪያ ያላት ነጭ ቀሚስ ለብሳ እንደ ትንሽ ነጭ ቢራቢሮ በሰው መሀል እየተሸሎከለከች መሐሪ በሄደበት ትከተለዋለች፡፡ ማረፊያዋም መነሻዋም መሐሪ ነው፡፡ ሮሐ ታዲያ ዛሬ እንኳን ብትፋታው ምናለበት” ትላለች፡፡

ከሳምንት በፊት መሐሪ ማሚን “ይኼ ነገር ግን አልሰፋም” ብሏት ነበር፡፡ ለድግሱ ስትሯሯጥ፤ “ዝም በል ወደዛ! ይኼን የፈዘዘ ግቢ ምን ምክንያት አግኝቼ ባጫጫስኩበት ስል ነው የኖርኩት፣ ገና ስትዳሩ " ብላ የሁለታችንንም ትከሻ ቸብ አደረገችና ሂሂሂ እያለች ወደ ሥራዋ ተመለሰች፡፡ እንዳለችውም ከማጫጫስ አልፎ በምግብና በመጠጥ፣በዘፈንና በዳንስ ግቢው አበደ፡፡ በዚያ ምሽት የእኔና መሐሪ ስም እየተነሳ ጀብዷችን ሲወሳ አመሸ፡፡ ዕድሜ ከተጫጫናቸው የፊደል አስተማሪያችን ከመምሬ
ምስሉ ጀምሮ እስከ አስራ ሁለተኛ ክፍል መምህራኖቻችን ድረስ “የቀለም ብልቃጥነታችንና ያነገይቱ ኢትዮጵያ በተስፋ የምትጠብቀን ወጣቶች መሆናችንን መሰከሩ፡፡ እንኳን እኛ
አጉል ወጣቶች፣ ዓለም ለምኔ ብሎ ለነፍሱ ያደረ ሰው እንኳን ቢሆን፣ በእንደዚህ ዓይነት አጋጣሚ ህዝብ ፊት ሲሞካሽና ሲደነቅ ሁለት ጭልፋ ኩራት፣ አንድ የሾርባ ማንኪያ መታበይና፣ ግማሽ የሻይ ማንኪያ ትዕቢት የተቀላቀለበት ፅንስ ልቡ ውስጥ መፈጠሩ አይቀርም፡፡ ደረቴ ሲነፋፋ ይሰማኝ ነበር፡፡ እንዲያው ድንገት ትን ብሎኝ ብሞት፣ አገሪቱ
አብራኝ ድፍት ብላ የምትቀር፣ ከኔ ሌላ ሰው የሌላት መሰለኝ፡፡
ይባስ ብሎ በዚህ ስሜት ላይ ጋሽ ዝናቡ ሁለት የቢራ ጠርሙዞች ይዞ ወደኔና መሐሪ መጣና ደሽ ደሽ እያደረገ ከፍቶ ለዛሬ ብቻ ዋ!” ብሎ ከማስጠንቀቂያ ጋር ሰጥቶን እየሳቀ ሄደ፡፡ እኔም መሐሪም ከዚያ በፊት አልኮል ቀምሰን አናውቅም፡፡ የመጀመሪያችን ነበር፡፡
ሮሐ ጋሽ ዝናቡ ገና ከመሄዱ እንደመደነስ እያደረጋት መጣችና ሄይ ዐይኔ ነው ወይስ ጋሽ ዝናቡ ቢራ ሰጣችሁ” አለችን፡፡ ሁለታችንም ጠርሙዛችንን ከፍ አድርገን ችርስ አልናት፡፡ ፍልቅልቅ እያለች ጠብቁኝ አለችና፣ በሰው መካከል እየተሽለኮለከች ሂዳ ወዲያው ተመለሰች፡፡ ከላይ የምትደርበውን ጃኬት በእጇ ይዛ ነበር፡፡ አጠገባችን ደርሳ ለልጥ ስታደርገው ግን፣ አንድ ጠርሙዝ ውስኪ ነበር “ጋሼ እንዳያየን ደብቄውኮ ነው፣ እንቀምቅመው በቃ” ብላ ሳቀች

“ኖ” አለ መሐሪ
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_አስራ_አንድ


#በአሌክስ_አብርሃም

....ደግሞ ተጠርቶ ያልመጣው ማን አባቱ ስለሆነ ነው ?…የሱ አሮጌ ሆቴል እና አሮጌ ነዳጅ ማደያና …አሮጌ መኪናና
አሮጌ ምናምን የሚገርመኝ መሰለው እንዴ? መሐሪ ነኝ መሐሪ ዝናቡ አውላቸው .. ሐሳቡን ሳይጨርስ ወደ ሮሐ ዞሮ…
እንዲህ ለብሰሽ…ምን ለብሰሽ ተራቁተሸ የመጣሽው ሳይጨርሰው ጋሽ ዝናቡ ከየት እንደመጣ ሳላየው ድንገት ደርሶ የመሐሪን ክንድ አፈፍ እደረገውና ግማሽ መግፋት በተቀላቀለበት ማባበል ወደ ቤት ሊወስደው ሲሞክር ጭራሽ ወደ ጋሽ ዝናቡም ዙሮ፣

ጋሼ ቆይ አትግፉኝ፡ አሁን ሕፃን ልጅ አይደለሁም፤ የዚችን አባት ጠርተኸዋል አይደል? ማንን መናቁ ነው ያልመጣው እኛ የታሰረው በራሱ ጥፋት እንጅ ጋሼ መሐሪን እየገፋ ወደ ቤት ወሰደው፡፡ ሳሌም ተጨንቃ ከኋላ ከኋላቸው የመሐሪን ቲሸርት ይዛ ተከትላቸው ገባች ፡

ሮሐ ግራ በመጋባት ትንሽ ቆማ ሲገቡ አየቻቸውና ድንገት ፊቷን አዙራ ወደ ግቢው በር በቁጣ አመራች፡፡ የውስኪውን ጠርሙስ ግቢው ጥግ ችፍርግ ብለው ወደበቀሉት አበቦች ወርውራ፣ ከሩጫ በማይተናነስ እርምጃ ወደ ውጭ ስትገሰግስ ተከትያት ሮጥኩ፡፡
“ሮሐ! ትንሽ ጠጥቷል የሚናገረውን አያውቅም”

“እም ፋይን!” ዝም ብዬ ከጎኗ መራመድ ቀጤልኩ፡፡ ከግቢው እንደወጣን ኮረኮንቹ
አላራምዳት ስላለ፣ ጫማዋን አውልቃ በእጇ አንጠለጠለችውና በባዶ እግሯ መንገድ ጀመረች፡፡ ስትራመድ ትንሽ ትንገዳገድ ነበር፡፡ ብዙ ጠጥታለች፡፡ የተቀባችው ሽቶና ከሰውነቷ ላይ የሚተነው የአልኮል ሽታ ያፍናል፡፡ ምን እንደምላት ግራ እንደገባኝ ከንዷን
ያዝ አድርጌ አስቆምኳት፡፡ እንባዋ ተዘረገፈ !

“ስቱፒድ ነገር ነው!”

እሺ! ነገ ሁሉንም ነገር እንነጋገራለን፣ መንገዱ በጠርሙዝ ስብርባሪና በምናምን የተሞላ ነው፣ አሁን ከቤት የሆነ ጫማ ላምጣልሽ ፕሊስ”
አሁን ገና ያየችው ይመስል ወደ ባዶ
እግሯ አቀርቅራ ተመለከተች፣ የእግሮቿን ጣቶች አንቀሳቀሰቻቸው፡፡ አቧራማው ኮረኮንች ላይ አርፈው ግቢው አጥር ላይ በተተከለው ቀይ መብራት የደመቁት ውብ እግሮቿ፣ ደማቅ ቀይ የጥፍር ቀለም ከተቀቡ ረዥም ጣቶቿ ጋር፣ በብዙ ጭንቀት የተነሳ የሆነ የጥፍር ቀለም ማስታውቂያ ውብ ፎቶ እንጂ
ሕያው እግር አይመስሉም ነበር፡፡
ሳሎን ሶፋው ሥር ፍላት ጫማ አስቀምጨረ ነበር፡፡ ካላስቸገርኩህ አቀብለኝ?” አለችኝ፡፡
የቆመችበት ትቻት ወደ ግቢ ሮጥኩና ጫማውን ይዠ ስመለስ፣ ልክ የተተከለች ይመስል ሳትንቀሳቀስ እዛው ጋ ቁማ አገኘኋት፡፡ ጫማውን ለማድረግ አንድ እግሯን ስታነሳ፣ ክፉኛ ተንገዳገደች፡፡ በርከክ ብዬ በእጄ ትከሻዬን ተደግፋ የአንድ እግር ጫማዋን እንዳጠለኵላት፣ ሳቅ ስምቼ ዞርኩ፡፡ መሐሪ ነበር ከኋላው ሳሌም ተከትለዋለች፡፡

በማላጋጥ አጨበጨበ እና፣ ወገቡን በሁለት እጁ ይዞ ቁሞ፣ ባለጌ ጓደኛህ በደንብ ብልግናው እንዲጎላ እስከ መንበርከከ የሚደርስ ጨዋነት እያሳየህ ነው ….? ጥሩ ነው ምድረ ኢዲየት!' ሂድ እቤቷ አዝለህ አድርሳት! አባቷ ለሚድራት ሀብታም አዝለህ አድርስለት… አቃጣሪ” ብሎኝ ጀርባውን አዙሮ ወደግቢው ተመለሰ፡፡ ሳሌም ተከትላው ከሥር ከሥሩ ትሮጣለች፡፡

ለምን እንደሆነ ባይገባኝም፣ እስካሁን ያልተነቀለ ቅሬታ በዚያች ቅጽበት ልቤን ወግቶኝ ቀረ፡፡ ስካር ቀድሞ ውስጣችን የሌለ ነገር ይፈጥራል ወይ? ወይንስ ያለውን ነው የሚያጎላው? እያልኩ እብሰለሰላለሁ፡፡ ስካሩም ሳይሆን ይኼ የሴትና የወንድ ጉዳይም ሳይሆን፣ መሐሪ ድምፅ ውስጥ የሰማሁት ንቀት አመመኝ፡፡ ጨለማ ውስጥ አጭር ቀሚስ
የለበሰች ፍቅረኛው እግር ሥር ተንበርክኬ ጫማ ማጥለቄ በሄኖክ እንደቀናው
አላስቀናውም፡፡ (አውቀዋለሁ ሙሉ ዘመናችንን ጓደኞች ነን) እንደወንድ አይደለም ያየኝ እንደ አሽከር ነው እንደ አሽከር አይደለም… እንደ አቃጣሪና በመሃላቸው ክፍተት ለመፍጠር እንደምሞክር እኩይ ገፀባህሪ ዓይነት ነው ያየኝ፡፡ ለሆነ ሰው ሮሐን አዝዬ
አድራሽ፤ ድምፁ ውስጥ አንዳች ቦታዬን ደረጃዬን የሚጠቁም ትዕቢተኛ ቃና ነበር
ጓደኛ አልነበርንም!! ለሚያነክስ ሰው ምርኩዝ አብሮት ዘላለም ቢቆይ ጓደኛው ሆነ ማለት አይደለም፡፡ በመሐሪ የተጎዳ ሥነ ልቦናውን እደግፍ ዘንድ፣ ምርኩዙ ሆኜ የኖርኩ ሰው ነበርኩ፡፡ ፍቅረኛው ግኡዝ ምርኩዙን ነው ተደግፋ ያገኛት፤ ሰክሮ ነው ብዬ ማድበስበስ እልቻልኩም፡፡

ሁለቱም አስጠሉኝ፡፡ ሮሐም መሐሪም መሀል መንገድ ላይ ጥያት መመለስ ግን
አልፈለኩም፡፡ ሁልጊዜ የምንሸኝባት ቦታ ግዙፉ ባለ ሁለት ፎቅ ቤታቸው ፊት ለፊት
ያለች አሳቻ ጨለማ ድረስ ሸኝቻት ልመለስ ስል፣ ክንዴን ይዛ ወደ ራሷ
ሳበችኝና፣ አቅፋ ጉንጨን ሳመችኝ! አሳሳሟ ድምፅ፣ ሙቀትና ኃይል ያለው ነበር፡፡ ልክ ማኅተም ወረቀት ላይ እንደሚመታው ዓይነት ነበር ከንፈሮቿ ከጉንጬ ጋር የተጋጩት፡፡ ምናልባት
ስለሰከረች ሚዛኗን መጠበቅ አቅቷትም እንደሆን እንጃ፡፡ ስመለስ ወደነመሐሪ ቤት
አልገባሁም …ጭፈራና ጩኸት ከውስጥ ይሰማል፡፡ እንደዋልኩበት ቤት ሳይሆን ልክ እንደማላውቀው ምንድነው እዚህ ግቢ ውስጥ ዛሬ ያለው? ብሎ እንደሚያልፍ መንገደኛ አልፌ ወደ ቤቴ ሄድኩ፡፡ ገና ትላንት መሐሪ እዚሁ ነው የምታድረው፣ እቤት ንገራቸው ብሎኝ ስለነበር እንደማድር ለእናቴ ነግሪያት ነበር፡፡

በነገራችን ላይ ስደርስ፣ ቆሜ ወደ ሰማይ አንጋጠጥኩ፡፡ ሰማዩ የዘመናት ጥላሸት ተሸክሞ እንደ ረገበ አሮጌ የማዳበሪያ ኮርኒስ የተቆዘረ ዥንጉርጉር ሆዱን አንጠልጥሎታል! አልፎ አልፎ ከሚያስተጋባው ጉርምርምታ ጋር ተዳምሮ አንዳች እንግዳ ፍጡር ሊወልድ
የሚያምጥ ነፍሰጡር ፍጥረት ይመስል ነበር! “አህያ የማይችለው ዝናብ መጣ ይላሉ በመንገዱ ከሚያልፉ ሰዎች መሃል አንዲት አሮጊት፣ ጨለማው ከባድ ስለነበር
ከቆምኩበት ሁኜ ሰዎቹ የለበሱት ነጠላ በድንግዝግዙ ሲንቀሳቀስ እንጂ መልካቸውን ማየት አልችልም ነበር፡፡ እንደገና ወደ ሰማይ ፊቴን አንጋጠጥኩ፡፡ ደመናው በሆነ ሹል ነገር ወጋ ቢያደርጉት፣ ውሃ ሳይሆን ጥላሸት የሚያዘንብ ነበር የሚመስለው !
ወደ ቤት ገባሁ፡፡ እናቴ ለአባባ ስለ ድግሱ ድምቀት እያወራችለት ነበር፡፡ እግሩን ክፉኛ ስለታመመ አልሄደም፡፡ ከፊቱ ማሚ ቋጥራ የላከችለት የድግስ ምግብ ከትልቅ ጎድጓዳ ሰሃን ላይ ተቀንሶ ቀርቦለት አልጋው ላይ ደገፍ እንዳለ ይበላል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ድህነት የሚባለው ነገር እንደሳትራት በቤታችን ፈዛዛ አምፖል ዙሪያ ሲበርና ትርኪምርኪው የቤት
እቃ ላይ ሲያርፍ ታየኝ፡፡ ልክ ያጠለቁበትን ጥቁር ጭንብል የማያውቀው ቦታ ወስደው ድንገትም እንዳነሱለት ሰው ነበር የቤታችንን ዙሪያ የቃኘሁት፡፡ እንዳላደግሁለት፣ ዛሬ ገና እንዳየሁት ዓይነት፡፡ እናቴ ታዲያ እንዲህ አለችኝ፣
“ውይ መጣህ እንዴ የምታድር መስሎኝ ደሞ ጉንጭህ ላይ የምን ቀለም ነው?” በመዳፌ ጠረኩት …የሮሐ ሊፕስቲክ ነበር፡፡ ወደ መኝታዬ አልፌ ከነልብሴ አልጋዬ ላይ በጀርባዬ ዘፍ አልኩና፣ ተንጋልዬ ተኛሁ፡፡ ከሁለቱ ክፍሎች የውስጠኛዋ ላይ የተዘረጋች የሽቦ
አልጋ ናት መኝታዬ፡፡ በሁለቱ ክፍሎች መግቢያ በር ላይ አንዲት ያደፈች የጨርቅ
መጋረጃ ተሰቅላለች፡፡ ዙሪያ ግርግዳው ላይ መጥበሻው፣ ድስቱ፣ የበረት ምጣዱ፣
ሰፌዱ፣ ወደ አንድ ጥግ የተቀመጠ የእንጀራ ሞሰብ፣ ግድግዳው ጋር ተጣብቆ በተሰራው የጣውላ መደርደሪያ ላይ ስኒዎት፣ ጀበና፣ ብርጭቆ ተደርድሯል፡፡ እዚያ ፊት ለፊት
ደግሞ የአባቴ የአናጺነት እቃዎች የታጨቁበት ትልቅ የቆዳ ከረጢት፡፡ እና እዚህ ሁሉ መሀል እኔ …! እኔ ውስጥ አልቅስ አልቅስ የሚል፣ እንደቀመስኩት ቢራ የሚጎመዝዝ ስሜት!!
👍1
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_አስራ_ሁለት


#በአሌክስ_አብርሃም

ከግቢው ውስጥ የጥድቄ ለቅሶ የቀላቀለ ጩኸት ይሰማል፡፡ የሆኑ ወንዶች የጎረነነና
የተጣደፈ ድምፅም ይሰማል፤ የሚያወሩት ግን አይሰማም ነበር፡፡ ወዲያው አንዲት አምቡላንስ ሳይነሯን እያሸች መጥታ ልክ ማታ እኔና ሮሐ ቆመንበት በነበረው ቦታ ላይ ስትደርስ ቆመች፣ ሁለት ሠራተኞች ከኋላ ቃሬዛ አውጥተው ወደግቢው በር
ተጠግተው ቆሙ:: ቃሬዛውን ሳይ እንደሐሞት የመረረ ፈሳሽ በአፍና በአፍንጫየ ሊወጣ ሲተናነቀኝ ይሰማኝ ነበር፡፡ አምቡላንሱ መኪና አናት ላይ የሚሽከረከረው ደማቅ ቀይ መብራት፡ ከነጭ ሰሀን ላይ እየጨለፈ አካባቢው ላይ ደም የሚረጭ አንዳች ነገር
ይመስል ነበር፡፡ የመኪናው የፊት መብራት የፈጠረው ረዣዥም የሰዎች ጥላ ወዳቦ
ወዲህ ሲንቀሳቀስ አስፈሪ ሕልም ይመስላል፡፡ ጋሽ ዝናቡ ማሚን አንድ ነገር እንዳደረጋት አልተጠራጠርኩም፡፡

እንዱ ፖሊስ የግቢውን በር እንጓጉቶ አምቡላንስ መጥቷል” ብሎ ጮኸ፡፡ ወዲያው በሩ ተከፍቶ፣ አንድ የሰፈራችን ልጅ በወጠምሻ ከንዶቹ ጋቢ የለበሰ ሰው አንከብክቦ አቅፎ መጣ፡፡ ገና ከላይ ከደረቡላት ጋቢ ወጥቶ የተንጠለጠለ ጸጉሯን ሳይ ብርክ ያዘኝ፡፡ ሳሌም
ነበረች፡፡ ከአንገቷ ጀምሮ በጋቢ ተሸፍናለች፡፡ እየጮኸች እና እጁን እያወራጨት ታለቅሳለች::ቃሬዛ ላይ አስተኝተውና የሚወራጭ እጅና እግሯን ይዘው፣ ወደአምቡላንሱ ይዘዋት ሮጡ፡፡ ወዲያው ጥድቄ ተከትላ ወጣች፡፡ ግቢው በር ላይ ድፍት ብላ በቁሟ ወድቃ ፌቷን እየነጨች ኡኡ ትል ጀመር፡፡

አገር ፍረደኝ: አንዲት ፍሬ ልጅ ጉድ ሠሩኝ ኡኡኡኡ " በጩኸት ብዛት ድምፅዋ
ጎርንኖ በየመሀሉ ሹክሹክታ ይሆናል፡፡ “
ጉድ ሠሩኝ ጉድ ሰሩኝ ይኼ ምን ዕድል
ነው ምን ጭካኔ ነው? ተሰምቶ ያቃል ወይ? በሰው ደርሶ ያውቃል ወይ? ፊቷን
በሁለቱም በኩል ከዓይኖቿ በታች ክፉኛ ተልትላው ይደማል፡፡ የደም እምባ የሚፈስስት ነብር የሚመስለው፡፡ የሰፈሩ ሴቶች አብረዋት ኡኡ ሲሉ፣ ትኩስ ሬሳ የወጣበት ቤት መሰለ፡፡ሰዎች ክንዷን ይዘው ከወደቀችበት ሊያነሷት ሲሞከሩ፣መሬቱ ላይ ተንከባለለች፡፡
ቀሚሷ ተገላልቦ ሰውነቷ ሲጋላጥ፣ እንዲት ሴትዮ ነጠላቸውን ከራሳቸው ትከሻ ላይ ገፈው ሊሸፍኗት ሞከሩ፣ ግን እልሆነላቸውም፡፡ በዛ ያሉ ሰዎች አፋፍሰው እዚያው አምቡላንሱ ውስጥ አስገቧት፡፡ የአምቡላንሱ በር ከመዘጋቱ በፊት ጥድቄ እንዲህ እያለች ትጮህ ነበር
“በሳሌም? በሳሌም?… በሳሌም? በእህትህ መሐሪ በላሌም? እኮ በሳሌም? በእህትህ ጨክነህ መሐሪ ….በሳሌም? በሳሌ.. በሩ ጓ ብሎ ሲዘጋ ድምጿ ቆመ፡፡ ፍዝዝ ብዬ እንደቆምኩ የግቢው በር እንደገና ተከፍቶ ሁለት ፖሊሶች መሐሪን መሃላቸው አድርገው ይዘውት ወጡ፡፡ እጁ በካቴና ወደፊት ታስሮ ነበር፡፡ ክንድና ክንዱን ይዘው እንዳተኝ ሳብ አደረጉት፡፡ እንዳቀረቀረ ፍጥነቱን ጨምሮ፣ ቶሎ ቶሎ ተራመደ፡፡ ማሚ ቀን ለብሳው በዋለችው ቀሚስ ላይ ነጠላ እንደደረበች ተከትላው ከኋላ ከኋላ ትሮጣለች፡፡
ፖሊሶቹ እንደከበቡት ወደ ዋናው መንገድ በሚወስደው ጨለም ያለ ኮረኮች በኩል፣
እያጣደፉ ይዘውት ሄዱ፡፡ ሕዝቡ ግር ብሎ ተከትሎ ወደፖሊስ ጣቢያ ተመመ
በቆምኩበት ከእግሬ ጀምሮ ወደላይ ሰውነቴ እየደነዘዘ ሲሄድ ይታወቀኝ ነበር።
የተሰበሰበው ሰው ይሳደባል፣ ይራገማል፣ ግማሹ ቀን ድግሱ ላይ ሲመርቅ ሲያመሰግን የዋለ ነው፡፡

ግራ ግብት እንዳለኝ፣ አንድ ድምፁ እንደ ጣውላ መሰንጠቂያ ማሽን የሚጮህ ሰው “ይኼም ጓደኛው ነው!” ብሎ ከኋላ ጀርባዬን በከዘራው ጫፍ ወጋ አደረገኝ፡፡
የሚጠዘጥዝ መጠርቆስ ነበር፤ ዞር አልኩና ባለ በሌለ ኃይሌ የከዘራውን ጫፍ ይዠ ወደኔ ሳብኩት፣ እየተንገዳገደ ሲጠጋኝ በጥፊ አቃጠልኩት፡ትልቅ ሰው ነበር፤ ግድ አልሰጠኝም፡፡ የተሰበስቡት ሰዎች እግር ሥር እንደ ትል ጥቅልል ብሎ ወድቆ በህግ አምላክ” እያለ ሲጮህ እዚያው ልረጋግጠው ፈልጌ ነበር፡፡ ከየት እንደመጣች እንጂ፣ እናቴ ክንዴን ይዛ ስትጎትተኝ ወደኋላዬ ተመለስኩ፡፡ እየጎተተችኝ ወደ ቤት ስትገሰግስ
ልክ እንደለማዳ በግ በዝምታ ተከተልኳት፡፡ እቤት ስንደርስ፣ እናቴ ተንጠራርታ ጥብቅ
አድርጋ አቀፈችኝና፣ አለቀሰች፡፡ እኔም እየተነፋረቅሁ መሆኑ የገባኝ፣ እንባዬን
ስትጠርግልኝ ነበር!

“ምንድነው” ይላል አባቴ የእግሩ ወለምታ ስላላስኬደው እዚያው እተኛበት ሆኖ
የሆነውን ለመስማት ጓጉቷል፡፡ “ምንድነው? አትናገሩም እንዴ?”

“ምንም አይደል አንተ ደግሞ ዝም ብለህ ተኛ

ምን እተኛለሁ ...ን ከፍተሸብኝ ሂደሽ፣ ንፋስ ገባ መሰለኝ ይኼው ደህና የተሻለኝን እግሬን እየጠዘጠዘኝ ነው!”

ቆም ብዬ አባቴን እየሁትና “እና ቢጠዘጥዝህ ትሞታለህ”አልኩት

እ...አለ ደንግጦ፡፡

ወደ ውስጥ ገብቼ አልጋ ላይ በፊቴ ተደፍቼ ተኛሁ፡፡ ምንም ነገር አልገባኝም፣ ምንም ነገር አላሰብኩም፡፡ አንድ ነገር ብቻ፣ እግዚአብሔርን መሆነ ሰዓቶቹን ወደኋላ መመለስ! ብዙ አይደለም፣ በቃ
እንድ አምስት ሰዓቶች ብቻ ወደኋላ መመለስ:: እግዚአብሔር ይችን ቢያደርግ ምን ይጎዳል? ምናልባት የሆነ ነገር ከአምስት ሰዓት በፊት ሎተሪ የደረሰው ደሃ፣ መልሶ ወደ ለመደው ድህነት ቢመለስ ነው! ድህነት ወንጀል
አይደል፣ ቢበዛ በድስትና በሰሃን በተከበበች ምኝታ ቤት ቢተኛ ነው …ምናለበት … ይችን ብቻ ይችን ብቻ!! ድንገት ቀን ስበላው የዋልኩት በቅመም ያበደ ቀይ ወጥና አልጫ ሆዴ ውስጥ እንደ ማዕበል ተገለባብጦ፤ ወደ ጉሮሮዬ ሊወነጨፍ፣ ከአልጋዬ። ዘልዬ ተነሳሁ፡፡ ዘግይቼ ነበር፤ ከአልጋዬ ሥር ባለው ላስቲክ በተነጠፈበት ወለል ላይ
ትውከቴን ለቀኩት !

“ልጄን! ልጄን እያለች እናቴ ወደ እኔ ስትሮጥ ይሰማኛል …ቀለል አለኝ !

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍1