የሚሆነው ደግሞ አዋቂዎች ህጻናትን ለውትድርና መመልመል ሲያቆሙ መሆኑን አስረግጬ ተናገርኩ:: እንደዚህ ነበር የጀመርኩት
ከ ሴራሊዮን ነው የመጣሁት፡፡ ህፃናትን እየጎዳ ያለው ጦርነቱ ሲሆን ጦርነቱ ከቤታችን ወጥተን እንድንሰደድ፣
ቤተሰቦቻቸውን እንድናጣ እና በጫካ ውስጥ እንድንከራተት አድርጎናል፡፡ በዚህ ምክንያት ያለ እድሜያችን በጦርነቱ እንደ
ወታደር እንድንሳተፍ፣ መሳሪያ እንድንሸከም እና ሌሎች አስቸጋሪ ስራዎች እንድንሰራ ተገደናል:: ይሄ ሁሉ የሆነው ደግሞ ስለተራብን ፣ ቤተሰቦቻችን ስላጣን እና የምንጠጋበት ስላጣን ነበር ። ጦሩን የተቀላቀልኩት ቤተሰቦቼን ስላጣሁ እና ስለተራብኩም ጭምር ነው፡፡ የቤተሰቦቼን ደም መመለስ መበቀል
እፈልግ ነበር። በህይወት ለመቀጠል ምግብም ያስፈልገኛል። ይህን ለማድረግ ብቸኛ መንገዱ ጦሩን መቀላቀል ነበር። ወታደር መሆን ቀላል አልነበረም ግን መሆን ነበረብን። አሁን አገግሜ ወጥቻለሁ። አትፍሩኝ፡፡ አሁን ወታደር አይደለሁም። ህጻን ነኝ፡፡ሁላችንም ወንድማማቾች እህትማማቾች ነን፡፡ ካሳለፍኩት ህይወት የተረዳሁት በቀል መልካም አለመሆኑን ነው።ጦሩን
የተቀላቀልኩት የቤተሰቦቼን ደም ለመበቀል እና በህይወት ለመቀጠል ነበር። ግን ቆይቼ የተረዳሁት እኔ ከተበቀልኩ ድርጊቱ ይቀጥላል። እኔ እገድላለሁ፤ የገደልኩት ሰው ዘመዶች ደግሞ ወደ በቀል ይገባሉ። በቀል በቀልን ይወልዳል። በቀል በቀል በቀል
ማቆሚያ የለውም...”
ከንግግሩ በኋላ በጋራ ያዘጋጀነውን መዝሙር ዘመርን።ሌሎች ዘፈኖችንም ዘፈን; አለቀስን፣ ሳቅን ተወዛወዝንም። ልዩ
ቀን ነበር። መለያየታችን ግን ከፋን ምክንያቱም የምንመለስባቸው ቦታዎች ሰላማዊ እንዳልሆኑ አናውቃለን።እጅ ለእጅ ተያይዘን እየዘለልን ጨፈርን።ሎራ ንግግሬ እንደማረካት ነገረችኝ።
ያን ምሽት ለእራት ወደ አንድ የህንድ ምግብ ቤት ሄድን።ሩዝ ስለነበር በጣም ደስተኛ ነበርኩ። ብዙ በላን፣ አወራን፣
አድራሻ ተቀያየርን በኋላ ወደ ሎራ ቤት ሄድን፡፡ የስራ ቤት ወደፊት የምኖርበት ቤት ይሆናል ብየ አልጠበቅኩም ነበር።
ግድግዳው ላይ ከተለያዩ የአለም ክፍሎች የመጡ የባህል ልብሶች
ተንጠልጥለዋል። የታሪክ እና ልብ ወለድ መጻህፍትን የያዘ ትልቅ መደርደሪያ ላይ የእንስሳት ቅርጻ ቅርፅ ሲሰቀል የሸክላ
ጌጣ ደግሞ ጠረጴዛ ተቀምጦ ይታያል። ቤቱ ሰፊ ሲሆን ሃምሳ
ስባት ታዳጊዎችን ያለ ምንም መጣበብ ነበር የያዘን።ምቹ፣
ማራኪና በሚያስደንቁ ታሪኮች የተሞላ ቤት! ሳሎኑ ተቀምጠን
ተረቶች ካወራን በኋላ ለሊቱን በመደነስ አጋመስነው።
የመጨረሻውን ቀን በኒው ዮርክ ለማሳለፍ ትክክለኛው ቦታ
ነበር።
በሚቀጥለው ምሽት ሎራ እና ሻንታህ አንድ ላይ በመሆን
ባህን፣ ዶ/ር ታምባን እና እኔን አየር መንገድ ድረስ ሸኙን::
መጀመሪያ መኪና ውስጥ ዝም ብለን ነበር። ቀስ በቀስ ግን እኔ
እና ባህ ማልቀስ ጀመርን። ተርሚሉ ደርሰን እየተቃቀፍን
ስንሰነባበት ደግሞ እለቅሷችን ጨመረ። ሎራ እና ሻንታ
አድራሻቸውን እና ስልክ ቁጥራቸውን ፅፈው ሰጡን፡ ህዳር 15፡
1996 ኒው ዮርክን ተሰናብተን ወጣን። በረራ ላይ በሃሳብ ጭልጥ
ብየ ነበር። ቆይታየ እንደ ህልም ይመስለኝ ጀመር። ከህልሙ ግን መንቃት አልፈልግም ነበር። ከፍቶኛል! ከኒው ዮርክ መውጣቴ ከፍቶኛል ግን ከሴራ ሊዮን ውጭ ሰው ማፍራቱ አንድ ነገር ነው። መመለስ ማለት ወደ ሞት መገስገስ ነው። ብሞትም የመኖሬ ትዝታ በሌላ አለም ህይው ሁኖ እንደ ሚኖር ግን አውቃለሁ።
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
ከ ሴራሊዮን ነው የመጣሁት፡፡ ህፃናትን እየጎዳ ያለው ጦርነቱ ሲሆን ጦርነቱ ከቤታችን ወጥተን እንድንሰደድ፣
ቤተሰቦቻቸውን እንድናጣ እና በጫካ ውስጥ እንድንከራተት አድርጎናል፡፡ በዚህ ምክንያት ያለ እድሜያችን በጦርነቱ እንደ
ወታደር እንድንሳተፍ፣ መሳሪያ እንድንሸከም እና ሌሎች አስቸጋሪ ስራዎች እንድንሰራ ተገደናል:: ይሄ ሁሉ የሆነው ደግሞ ስለተራብን ፣ ቤተሰቦቻችን ስላጣን እና የምንጠጋበት ስላጣን ነበር ። ጦሩን የተቀላቀልኩት ቤተሰቦቼን ስላጣሁ እና ስለተራብኩም ጭምር ነው፡፡ የቤተሰቦቼን ደም መመለስ መበቀል
እፈልግ ነበር። በህይወት ለመቀጠል ምግብም ያስፈልገኛል። ይህን ለማድረግ ብቸኛ መንገዱ ጦሩን መቀላቀል ነበር። ወታደር መሆን ቀላል አልነበረም ግን መሆን ነበረብን። አሁን አገግሜ ወጥቻለሁ። አትፍሩኝ፡፡ አሁን ወታደር አይደለሁም። ህጻን ነኝ፡፡ሁላችንም ወንድማማቾች እህትማማቾች ነን፡፡ ካሳለፍኩት ህይወት የተረዳሁት በቀል መልካም አለመሆኑን ነው።ጦሩን
የተቀላቀልኩት የቤተሰቦቼን ደም ለመበቀል እና በህይወት ለመቀጠል ነበር። ግን ቆይቼ የተረዳሁት እኔ ከተበቀልኩ ድርጊቱ ይቀጥላል። እኔ እገድላለሁ፤ የገደልኩት ሰው ዘመዶች ደግሞ ወደ በቀል ይገባሉ። በቀል በቀልን ይወልዳል። በቀል በቀል በቀል
ማቆሚያ የለውም...”
ከንግግሩ በኋላ በጋራ ያዘጋጀነውን መዝሙር ዘመርን።ሌሎች ዘፈኖችንም ዘፈን; አለቀስን፣ ሳቅን ተወዛወዝንም። ልዩ
ቀን ነበር። መለያየታችን ግን ከፋን ምክንያቱም የምንመለስባቸው ቦታዎች ሰላማዊ እንዳልሆኑ አናውቃለን።እጅ ለእጅ ተያይዘን እየዘለልን ጨፈርን።ሎራ ንግግሬ እንደማረካት ነገረችኝ።
ያን ምሽት ለእራት ወደ አንድ የህንድ ምግብ ቤት ሄድን።ሩዝ ስለነበር በጣም ደስተኛ ነበርኩ። ብዙ በላን፣ አወራን፣
አድራሻ ተቀያየርን በኋላ ወደ ሎራ ቤት ሄድን፡፡ የስራ ቤት ወደፊት የምኖርበት ቤት ይሆናል ብየ አልጠበቅኩም ነበር።
ግድግዳው ላይ ከተለያዩ የአለም ክፍሎች የመጡ የባህል ልብሶች
ተንጠልጥለዋል። የታሪክ እና ልብ ወለድ መጻህፍትን የያዘ ትልቅ መደርደሪያ ላይ የእንስሳት ቅርጻ ቅርፅ ሲሰቀል የሸክላ
ጌጣ ደግሞ ጠረጴዛ ተቀምጦ ይታያል። ቤቱ ሰፊ ሲሆን ሃምሳ
ስባት ታዳጊዎችን ያለ ምንም መጣበብ ነበር የያዘን።ምቹ፣
ማራኪና በሚያስደንቁ ታሪኮች የተሞላ ቤት! ሳሎኑ ተቀምጠን
ተረቶች ካወራን በኋላ ለሊቱን በመደነስ አጋመስነው።
የመጨረሻውን ቀን በኒው ዮርክ ለማሳለፍ ትክክለኛው ቦታ
ነበር።
በሚቀጥለው ምሽት ሎራ እና ሻንታህ አንድ ላይ በመሆን
ባህን፣ ዶ/ር ታምባን እና እኔን አየር መንገድ ድረስ ሸኙን::
መጀመሪያ መኪና ውስጥ ዝም ብለን ነበር። ቀስ በቀስ ግን እኔ
እና ባህ ማልቀስ ጀመርን። ተርሚሉ ደርሰን እየተቃቀፍን
ስንሰነባበት ደግሞ እለቅሷችን ጨመረ። ሎራ እና ሻንታ
አድራሻቸውን እና ስልክ ቁጥራቸውን ፅፈው ሰጡን፡ ህዳር 15፡
1996 ኒው ዮርክን ተሰናብተን ወጣን። በረራ ላይ በሃሳብ ጭልጥ
ብየ ነበር። ቆይታየ እንደ ህልም ይመስለኝ ጀመር። ከህልሙ ግን መንቃት አልፈልግም ነበር። ከፍቶኛል! ከኒው ዮርክ መውጣቴ ከፍቶኛል ግን ከሴራ ሊዮን ውጭ ሰው ማፍራቱ አንድ ነገር ነው። መመለስ ማለት ወደ ሞት መገስገስ ነው። ብሞትም የመኖሬ ትዝታ በሌላ አለም ህይው ሁኖ እንደ ሚኖር ግን አውቃለሁ።
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#አገሬ 💚💛❤️
አገሬ ውበት ነው፣
ለምለምና ነፋስ የሚጫወትበት፣
ፀሃይ የሞላበት፣ ቀለም የሞላበት።
አገሬ ቆላ ነው፣ ደጋ ወይና ደጋ፣
እዚያ ብርሃን አለ ሌሊቱ እስኪነጋ።
አገሬ ተራራ ሸለቆ ረባዳ፣
አገሬ ጅረት ነው ገደልና ሜዳ፣
ውበት ነው በበጋ ፀሃይ አትፋጅም፣
ክረምቱም አይበርድም፣
አይበርድም፣ አይበርድም።
አገሬ ጫካ ነው፣
እንሰሳት አራዊት የሚፈነጩበት፣
በወጥመድ ሳይገቡ ሳይነካቸው ጠላት።
እዚያ አለ ነፃነት፣
በሃገር መመካት፣
በተወላጅነት፣
በባለቤትነት፣
እዚያ አለ ነፃነት።
አገሬ ሃብት ነው፤
ጎመኑ ስብ ጮማ፣ ቆሎ ክትፎ ስጋ፣
ድርቆሹ ፍትፍት ነው፣ ቃሪያው ሙክት ሠንጋ፣
ጠጁ ነው ወለላ፣
ከኮኛክ ያስንቃል የመንደሩ ጠላ።
እህሉ ጣእም አለው እንጀራው ያጠግባል፣
ከቢራ ከሻምፓኝ ውሃው ይጣፍጣል፣
በዓሉ ይደምቃል፣
ሙዚቃው ያረካል፣
ጭፈራው ዘፈኑ ችግርን ያስረሳል።
እዚያ ዘመድ አለ፣
ሁሉም የናት ልጅ ነው፣
ሁሉም ያባት ልጅ ነው፣
ጠላትም አንዳንዴ ይመጣል መቃብር፣
ባለጋራም ቸር ነው “ያገር ልጅ ሲቸገር” ፤
ገነት ነው አገሬ።
ምነው ምን ሲደረግ ?
ምነው ለምን እንዴት ?
ዘራፊ ቀማኛ ምቀኛ ወንበዴ፣
ጥርኝ አፈር በጁ ስንዝር ወሰን አልፎ፣
የተቀደሰውን ያፍሪቃ ላይ ደሴት፣
ባያገኝ ለማርከስ ጠላት ይመኝ እንዴት።
እምቢኝ አሻፈረኝ፣
አሻፈረኝ እምቢ፣
መቅደስ ነው አገሬ፣
አድባር ነው አገሬ፣
እናትና አባት ድኸው ያደጉበት፣
ካያት ከቅደም አያት የተረካከቡት፣
አፈር የፈጩበት፣
ጥርስ የነቀሉበት።
አገሬ ዓርማ ነው፣ የነጻነት ዋንጫ፣
በቀይ የተጌጠ ባረንጓዴ ቢጫ።
እሾህ ነው አገሬ፣
በጀግናው ልጅ አጥንት የተከሰከሰ፣
ጠላት ያሳፈረ አጥቂን የመለሰ።
አገሬ ታቦት ነው ፣ መቅደስ የሃይማኖት፣
ዘመን የፈተነው በጠበል በጸሎት።
ለምለም ነው አገሬ፣
ውበት ነው አገሬ፣
ብሞት እሄዳለሁ ከመሬት ብገባ፣
እዚያ ነው አፈሩ፣ የማማ ያባባ።
ስሳብ እሔዳለሁ ቢሰበርም እግሬ፣
አለብኝ ቀጠሮ ከትውልድ አገሬ።
አለብኝ ቀጠሮ
ከትውልድ አገሬ፣
ካሳደገኝ ጓሮ።
🔘ሰዓሊ እና ገጣሚ ገብረ ክርስቶስ ደስታ🔘
አገሬ ውበት ነው፣
ለምለምና ነፋስ የሚጫወትበት፣
ፀሃይ የሞላበት፣ ቀለም የሞላበት።
አገሬ ቆላ ነው፣ ደጋ ወይና ደጋ፣
እዚያ ብርሃን አለ ሌሊቱ እስኪነጋ።
አገሬ ተራራ ሸለቆ ረባዳ፣
አገሬ ጅረት ነው ገደልና ሜዳ፣
ውበት ነው በበጋ ፀሃይ አትፋጅም፣
ክረምቱም አይበርድም፣
አይበርድም፣ አይበርድም።
አገሬ ጫካ ነው፣
እንሰሳት አራዊት የሚፈነጩበት፣
በወጥመድ ሳይገቡ ሳይነካቸው ጠላት።
እዚያ አለ ነፃነት፣
በሃገር መመካት፣
በተወላጅነት፣
በባለቤትነት፣
እዚያ አለ ነፃነት።
አገሬ ሃብት ነው፤
ጎመኑ ስብ ጮማ፣ ቆሎ ክትፎ ስጋ፣
ድርቆሹ ፍትፍት ነው፣ ቃሪያው ሙክት ሠንጋ፣
ጠጁ ነው ወለላ፣
ከኮኛክ ያስንቃል የመንደሩ ጠላ።
እህሉ ጣእም አለው እንጀራው ያጠግባል፣
ከቢራ ከሻምፓኝ ውሃው ይጣፍጣል፣
በዓሉ ይደምቃል፣
ሙዚቃው ያረካል፣
ጭፈራው ዘፈኑ ችግርን ያስረሳል።
እዚያ ዘመድ አለ፣
ሁሉም የናት ልጅ ነው፣
ሁሉም ያባት ልጅ ነው፣
ጠላትም አንዳንዴ ይመጣል መቃብር፣
ባለጋራም ቸር ነው “ያገር ልጅ ሲቸገር” ፤
ገነት ነው አገሬ።
ምነው ምን ሲደረግ ?
ምነው ለምን እንዴት ?
ዘራፊ ቀማኛ ምቀኛ ወንበዴ፣
ጥርኝ አፈር በጁ ስንዝር ወሰን አልፎ፣
የተቀደሰውን ያፍሪቃ ላይ ደሴት፣
ባያገኝ ለማርከስ ጠላት ይመኝ እንዴት።
እምቢኝ አሻፈረኝ፣
አሻፈረኝ እምቢ፣
መቅደስ ነው አገሬ፣
አድባር ነው አገሬ፣
እናትና አባት ድኸው ያደጉበት፣
ካያት ከቅደም አያት የተረካከቡት፣
አፈር የፈጩበት፣
ጥርስ የነቀሉበት።
አገሬ ዓርማ ነው፣ የነጻነት ዋንጫ፣
በቀይ የተጌጠ ባረንጓዴ ቢጫ።
እሾህ ነው አገሬ፣
በጀግናው ልጅ አጥንት የተከሰከሰ፣
ጠላት ያሳፈረ አጥቂን የመለሰ።
አገሬ ታቦት ነው ፣ መቅደስ የሃይማኖት፣
ዘመን የፈተነው በጠበል በጸሎት።
ለምለም ነው አገሬ፣
ውበት ነው አገሬ፣
ብሞት እሄዳለሁ ከመሬት ብገባ፣
እዚያ ነው አፈሩ፣ የማማ ያባባ።
ስሳብ እሔዳለሁ ቢሰበርም እግሬ፣
አለብኝ ቀጠሮ ከትውልድ አገሬ።
አለብኝ ቀጠሮ
ከትውልድ አገሬ፣
ካሳደገኝ ጓሮ።
🔘ሰዓሊ እና ገጣሚ ገብረ ክርስቶስ ደስታ🔘
👍1
#ለኀጥአን_የመጣ
#ክፍል_ሀያ_አንድ
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
አንዳንዴ ማታ ማታ ለቤተሰቦቼ መሐመድን ጨምሮ (አሁን ከእኛ ጋር ነው የሚኖረው) ስለ ጉዞዬ እነግራቸው ነበር።
ሁሉንም ነገር አስረዳቸው ነበር፡፡ አየር ማረፊያውን፣ አውሮፐላኖቹን በአውሮፐላን መስኮት አሻግሮ ደመናን ማየት የሚሰጠውን ስሜት ሳይቀር እነግራቸው ነበር፡፡ ስነግራቸው የናፍቆት ስሜት ይሰማኝ ነበር። በአምስተርዳም አየር ማረፊያ እግረኛ መንገድ ስንቀሳቀስ ብዙ ነጮች ቦርሳቸውን እየጣሉ እና በተለያየ አቅጣጫ ሲሯሯጡ ትዝ ይለኛል።
ስለተዋወቅኳቸው ሰዎች፣ ስለ ኒው ዮርክ ረጃጂም ፎቆች፣ ስለ ስስ በረዶቿ እና ሰዎች መንገድ ላይ እንዴት እንደሚሰዳደቡ ሳይቀር ነገርኳቸው።
“የሚገርም ጉዞ ነው” ይላል አጎቴ፡አንዳንዴ በእውኑ አለም የሌለ አዕምሮዬ ውስጥ ለእኔ ብቻ የተከሰተ ይመስለኝ ነበር።
መሐመድ እና እኔ በኤድዋርድ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንደገና ትምህርት ጀመርን። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ሁኜ ጠዋት ትምህርት ቤት ስሄድ ትዝ ይለኛል። የወደቁ የማንጎ ቅጠሎችን የሚጠርጉ መጥረጊያዎች ድምፅ እና የደነበሩ ወፎች ጫጫታ ታጅበን ወደ ትምህርት ቤት ስሄድ ትዝ ይለኛል።ትምህርት ቤቱ በጨቃ ጡብ እና ቆርቆሮ የተሰራ ትንሽ ህንፃ ሲኖረው ህንፃው በር አልነበረውም:: ከጥበቱ የተነሳ ሁሉንም ተማሪ መያዝ አይችልም ነበር። ብዙ ክፍለ ጊዜ ውጭ በማንጎ
ዛፍ ስር ጥላ ነበር የምንማረው:: መሐመድ በ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የነበረውን የትምህርት መሳሪያ እጥረት በደንብ ያስታውሳል። ብዙ ጊዜ ደግሞ መምህራን በእርሻ ያግዝ እንደነበር ይነግረኛል። ዘር በመዝራት፣ በመኮትኮት እና
በማጨድ ያግዝ ነበር። አብዛኞቹ መምህራን ኑሮቸውን በእርሻ ይደጉሙ ነበር። ብዙ ባወራሁት ቁጥር ብዙ ነገር እንደዘነጋሁ ማወቅ ጀምሬለሁ፡፡ ተማሪነትን ክፍል ውስጥ መቀመጥ፣
ማስታወሻ መያዝ፣ የቤት ስራ፣ ጓደኛ መያዝ እና ብሽሽቁን ሁሉ ረስቼዋለሁ ። አሁን ግን እንደገና ወደዛ ለመመለስ ጓጉቻለሁ:: በፍሪ ታውን የመጀመሪያ የትምህርት ቀን ግን ሁሉም ተማሪዎች ከእኔ እና መሐመድ እርቀው ነበር የተቀመጡት::በአንዴ የምንገድላቸው ነበር የመሰላቸው። እንዴት እንደሰሙ
ባላውቅም ታዳጊ ወታደሮች እንደነበርን አውቀዋል፡፡በጦርነቱ ልጅነታችንን ብቻ አይደለም ያጣነው ስማችንም ከዚህ ስቃይ እና መከፋትን ካተረፍንበት መጥፎ ገጠመኝ ጋር እንዲጠራ ሁኖ ጠልሽቷል።
ቀስ ብለን ነበር ቤት ምንመለሰው። ቀስ ብሎ መራመድ ለማሰብ፤ ህይወት ወደየት አቅጣጫ እየተጓዘ እንደሆነ
ለመገምገም እድል ስለሚሰጥ ደስ ይለኝ ነበር። ህይወቴ ካለፈው እንደማይብስ እርግጠኛ ነበርኩ። እሱም የመፅናኛ እና ፈገግታየ ምንጭ ነበር። ቤተሰብ የአንድ ቤተሰብ አባልነትን ገና እየተለማመድኩ ነው፡፡ ለሰዎችም መሐመድ ጓደኛየ እንደሆነ መናገር ስለ ጀመርኩ ብዙ ማብራራት አይጠበቅብኝም።
ያለፈውን ታሪኬን መርሳት እንደማልችል አውቃለሁ። ነገር ግን ስላለፈው ማውራት ማቆም እና ዛሬን በአዲስ ህይወት መኖር
እፈልጋለሁ።
እንደተለመደው በጠዋት ነበር የተነሳሁት። ተነስቼ በቤታችን ጀርባ የሚገኝ ጠፍጣፋ ድንጋይ ላይ ተቀምጨ
የከተማውን መንቃት እጠብቃለሁ። ግንቦት 25, 1997 የተኩስ እሩምታ ሰማሁ።ከተማዋ ከተለመደው ድምፅ ወጥታ በተኩስ እሩምታ ደነቆረች። የተኩስ እሩምታ በሃገሪቱ የህዝብ መወሰኛ ሁሉንም ከእንቅልፍ ቀስቀስ። እኔም ደጃፍ ላይ ወደ ነበረው አጎቴ
ምክር ቤት አካባቢ ነበር የሚሰማው።የተኩስ እሩምታው
ምን እየተካሄደ እንደለ አላወቅንም። ወታደሮች ግን በፓዲባ መንገድ ሲሯሯጡ የጦር መኪኖች ሲንቀሳቀሱ አይተናል። የተኩስ እሩምታው እየጨመረ ሌሎች የከተማውን ክፍሎች እያካለለ ነበር የቀጠለው:: የከተማው አዋቂ ስዎች ደንግጠው በፍርሃት እየረዱ በራቸው
ደጃፍ ላይ ተቀምጠዋል። መሐመድ እና እኔ ተያየን። ወደሱ ተጠጋሁ።
ረፋድ ሲሆን ማዕከላዊ እስር ቤት ተከፍቶ እስረኞች ተለቀቁ። ከእስር ከመውጣታቸው በተጨማሪ አዲሱ መንግስት ለእስረኞች መሳሪያ አደለ። አንዳንዶቹ በቀጥታ ወደ ፈረዱባቸው ዳኞች እና ጠበቆች በመሄድ እነሱን እና ቤተሰቦቻቸውን ገደሉ ቤታቸውንም
አቃጠሉ፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ወታደሮች ቀድሞው የጀመሩትን ዘረፋ ተቀላቀሉ:: የሚቃጠሉ ቤቶች ጪስ አየሩን ሞልቶ ከተማዋን በጭጋግ ሸፈናት::
አንድ ሰው በሬዲዩ ወጥቶ ራሱን አዲሱ የሴራ ሊዮን ፕሬዝደንት እንደሆነ አወጀ:: ስሙ ጆኒ ፖል ኮሮማ ሲሆን የአብዮታዊ ጦር ኃይሎች ምክር ቤት መሪ እንደነበር ተናገረ። ምክር ቤቱ በዲሞክራሲያዊ ምርጫ የተመረጠውን ፕሬዝደንት
ቲጃን ከባህን ከስልጣን ለማስወገድ በጦር መኮንኖች የተመሰረተ ነበር።
የኮሮማ መፈንቅለ መንግስቱን ለማካሄድ እንዳቀረበው ምክንያት መጥፎ ነበር፡፡ ሁሉም ነገር በቁጥጥር ስር እንደሆነ እና ሁሉም ሰው ወደ ስራ እንዲወጣ ምክር ሰጠ።
ከንግግሩ ጀርባ ግን የተኩስ እሩምታ እና የተቆጡ ወታደሮች ሲሳደቡ ሲጨፍሩ ይሰማል።
ምሽት ላይ በሌላ አዋጅ አማጺዎች እና ጦሩ የሲቪሉን መንግስት “ለሃገር ጥቅም” ሲባል ለመገልበጥ እንደተቀናጁ
በሬድዮ ተነገረ። አማጺዎች እና ጦር ግንባር የነበሩ ወታደሮችከተማውን ማጥለቅለቅ ጀመሩ፡፡ ሃገሪቱ ሙሉ ለሙሉ ወደ ስርዓት አልበኝነት ገባች። እየሆነ ያለው ሁሉ አላማረኝም:: ጠላሁት ወደ ቀድሞ ህይወቴ መመለስ አልችልም:: አሁን ግን በህይወት የማመልጥ አልመስልህ አለኝ፡፡
አማጺዎች እና ወታደሮቹ የባንክ ካዝናን መስበር፣ ፈንጅ ማፈንዳት፣ ሰዎችን አስቁሞ መበርበር መዝረፍ ጀመሩ::
ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን እና የዮኒቨርሲቲ ግቢዎችን ተቆጣጠሩ። ደጅ ተቀምጦ ከመመልከት በስተቀር ምንም
የሚሰራ ነገር የለም:: አጎቴ የጀመረውን ቤት ለመጨረስ ወሰነ።በጠዋት ጀምረን እስከ ረፋድ ድረስ መስራት ጀመርን። የተኩስ እሩምታው ከቀን ቀን እየባሰ ከቤት መውጣት አስፈሪ እየሆነ መጣ፡፡ በጀምላ ብዙ ሰዎች ተገደሉ። ስለዚህ ብዙም ሳንቆይ ስራውን አቆምነው።
የታጠቁት ኃይሎች በከተማው ሱቆች እና ገበያ የሚገኘውን ምግብ በጉልበት ነጥቀው ወሰዱ። ከውጭ የሚመጣው ምግብ እና ከክፍለ ሃገር ወደ ከተማ የሚገባው ምግብ ቆሟል። ሎራ
ገንዘብ ትልክልኝ ስለነበር የቆጠብኩት ትንሽ ገንዘብ ነበረኝ ። ወደ ከተማው ወጥቼ ሩዝ፣ ደሮ፣ አሳ እና ሌሎች የታሸጉ ምግቦችን ለመግዛት ወሰንኩ፡፡ ወደ ገበያ መሄድ ግን አደጋ ነበረው። የበፊት
የጦር ሜዳ ጓደኞቼን ቢገኙኝ እና ከጦርነቱ እራሴን ማግለሌን
ቢያውቁ ይገሉኛል። ቤት መቀመጥ ደግሞ አልችልም ምግ መፈለግ ይኖርብኛል።
አንድ ድብቅ ገበያ እንዳለ እና የተለያዩ የማይገኙ የምግብ አይነቶች ለተራው ህዝብ እንደሚሸጥ ሰማን፡፡ ዋጋው ገበያ
ከመደበኛ ዋጋ ሁለት እጥፍ ቢሆንም ከአደጋ ያተርፋል።በጠዋት ማንም አንዳያየን አንገታችንን ደፍተን ወደ ገበያው
አመራን። ሩዝ፣ የወይራ ዘይት፣ ጨው፣ አሳ ገዝተን ልንወጣ ስንል መኪና እና ወታደሮች ዘለው ወረዱ። ወደ ህዝቡ
በመጠጋት የማስጠንቀቂያ ተኩስ ወደ ሰማይ ተኮሱ። በድምጸ ማጉያ አዛዡ የምግብ ዘምቢላችንን መሬት ላይ እንድናስቀምጥ እና እጃችንን ራሳችን ላይ እንድናስቀምጥ ትዕዛዝ ሰጠ።በድንጋጤ ለመሮጥ የሞከረች አንዲት ሴት ግንባሯ በጥይትተመታ:: ሁሉም ሰው ተረበሸ። እኛም ምግባችንን ይዘን ሮጥን።
ወደ ዋናው መንገድ ስንደርስ “ግድያ ይቁም” የሚል መፈክር ያነገቡ ሰልፈኞች አየን፡፡ ነጭ ቲሸርት እና ራሳቸው ላይ ነጭ
#ክፍል_ሀያ_አንድ
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
አንዳንዴ ማታ ማታ ለቤተሰቦቼ መሐመድን ጨምሮ (አሁን ከእኛ ጋር ነው የሚኖረው) ስለ ጉዞዬ እነግራቸው ነበር።
ሁሉንም ነገር አስረዳቸው ነበር፡፡ አየር ማረፊያውን፣ አውሮፐላኖቹን በአውሮፐላን መስኮት አሻግሮ ደመናን ማየት የሚሰጠውን ስሜት ሳይቀር እነግራቸው ነበር፡፡ ስነግራቸው የናፍቆት ስሜት ይሰማኝ ነበር። በአምስተርዳም አየር ማረፊያ እግረኛ መንገድ ስንቀሳቀስ ብዙ ነጮች ቦርሳቸውን እየጣሉ እና በተለያየ አቅጣጫ ሲሯሯጡ ትዝ ይለኛል።
ስለተዋወቅኳቸው ሰዎች፣ ስለ ኒው ዮርክ ረጃጂም ፎቆች፣ ስለ ስስ በረዶቿ እና ሰዎች መንገድ ላይ እንዴት እንደሚሰዳደቡ ሳይቀር ነገርኳቸው።
“የሚገርም ጉዞ ነው” ይላል አጎቴ፡አንዳንዴ በእውኑ አለም የሌለ አዕምሮዬ ውስጥ ለእኔ ብቻ የተከሰተ ይመስለኝ ነበር።
መሐመድ እና እኔ በኤድዋርድ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንደገና ትምህርት ጀመርን። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ሁኜ ጠዋት ትምህርት ቤት ስሄድ ትዝ ይለኛል። የወደቁ የማንጎ ቅጠሎችን የሚጠርጉ መጥረጊያዎች ድምፅ እና የደነበሩ ወፎች ጫጫታ ታጅበን ወደ ትምህርት ቤት ስሄድ ትዝ ይለኛል።ትምህርት ቤቱ በጨቃ ጡብ እና ቆርቆሮ የተሰራ ትንሽ ህንፃ ሲኖረው ህንፃው በር አልነበረውም:: ከጥበቱ የተነሳ ሁሉንም ተማሪ መያዝ አይችልም ነበር። ብዙ ክፍለ ጊዜ ውጭ በማንጎ
ዛፍ ስር ጥላ ነበር የምንማረው:: መሐመድ በ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የነበረውን የትምህርት መሳሪያ እጥረት በደንብ ያስታውሳል። ብዙ ጊዜ ደግሞ መምህራን በእርሻ ያግዝ እንደነበር ይነግረኛል። ዘር በመዝራት፣ በመኮትኮት እና
በማጨድ ያግዝ ነበር። አብዛኞቹ መምህራን ኑሮቸውን በእርሻ ይደጉሙ ነበር። ብዙ ባወራሁት ቁጥር ብዙ ነገር እንደዘነጋሁ ማወቅ ጀምሬለሁ፡፡ ተማሪነትን ክፍል ውስጥ መቀመጥ፣
ማስታወሻ መያዝ፣ የቤት ስራ፣ ጓደኛ መያዝ እና ብሽሽቁን ሁሉ ረስቼዋለሁ ። አሁን ግን እንደገና ወደዛ ለመመለስ ጓጉቻለሁ:: በፍሪ ታውን የመጀመሪያ የትምህርት ቀን ግን ሁሉም ተማሪዎች ከእኔ እና መሐመድ እርቀው ነበር የተቀመጡት::በአንዴ የምንገድላቸው ነበር የመሰላቸው። እንዴት እንደሰሙ
ባላውቅም ታዳጊ ወታደሮች እንደነበርን አውቀዋል፡፡በጦርነቱ ልጅነታችንን ብቻ አይደለም ያጣነው ስማችንም ከዚህ ስቃይ እና መከፋትን ካተረፍንበት መጥፎ ገጠመኝ ጋር እንዲጠራ ሁኖ ጠልሽቷል።
ቀስ ብለን ነበር ቤት ምንመለሰው። ቀስ ብሎ መራመድ ለማሰብ፤ ህይወት ወደየት አቅጣጫ እየተጓዘ እንደሆነ
ለመገምገም እድል ስለሚሰጥ ደስ ይለኝ ነበር። ህይወቴ ካለፈው እንደማይብስ እርግጠኛ ነበርኩ። እሱም የመፅናኛ እና ፈገግታየ ምንጭ ነበር። ቤተሰብ የአንድ ቤተሰብ አባልነትን ገና እየተለማመድኩ ነው፡፡ ለሰዎችም መሐመድ ጓደኛየ እንደሆነ መናገር ስለ ጀመርኩ ብዙ ማብራራት አይጠበቅብኝም።
ያለፈውን ታሪኬን መርሳት እንደማልችል አውቃለሁ። ነገር ግን ስላለፈው ማውራት ማቆም እና ዛሬን በአዲስ ህይወት መኖር
እፈልጋለሁ።
እንደተለመደው በጠዋት ነበር የተነሳሁት። ተነስቼ በቤታችን ጀርባ የሚገኝ ጠፍጣፋ ድንጋይ ላይ ተቀምጨ
የከተማውን መንቃት እጠብቃለሁ። ግንቦት 25, 1997 የተኩስ እሩምታ ሰማሁ።ከተማዋ ከተለመደው ድምፅ ወጥታ በተኩስ እሩምታ ደነቆረች። የተኩስ እሩምታ በሃገሪቱ የህዝብ መወሰኛ ሁሉንም ከእንቅልፍ ቀስቀስ። እኔም ደጃፍ ላይ ወደ ነበረው አጎቴ
ምክር ቤት አካባቢ ነበር የሚሰማው።የተኩስ እሩምታው
ምን እየተካሄደ እንደለ አላወቅንም። ወታደሮች ግን በፓዲባ መንገድ ሲሯሯጡ የጦር መኪኖች ሲንቀሳቀሱ አይተናል። የተኩስ እሩምታው እየጨመረ ሌሎች የከተማውን ክፍሎች እያካለለ ነበር የቀጠለው:: የከተማው አዋቂ ስዎች ደንግጠው በፍርሃት እየረዱ በራቸው
ደጃፍ ላይ ተቀምጠዋል። መሐመድ እና እኔ ተያየን። ወደሱ ተጠጋሁ።
ረፋድ ሲሆን ማዕከላዊ እስር ቤት ተከፍቶ እስረኞች ተለቀቁ። ከእስር ከመውጣታቸው በተጨማሪ አዲሱ መንግስት ለእስረኞች መሳሪያ አደለ። አንዳንዶቹ በቀጥታ ወደ ፈረዱባቸው ዳኞች እና ጠበቆች በመሄድ እነሱን እና ቤተሰቦቻቸውን ገደሉ ቤታቸውንም
አቃጠሉ፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ወታደሮች ቀድሞው የጀመሩትን ዘረፋ ተቀላቀሉ:: የሚቃጠሉ ቤቶች ጪስ አየሩን ሞልቶ ከተማዋን በጭጋግ ሸፈናት::
አንድ ሰው በሬዲዩ ወጥቶ ራሱን አዲሱ የሴራ ሊዮን ፕሬዝደንት እንደሆነ አወጀ:: ስሙ ጆኒ ፖል ኮሮማ ሲሆን የአብዮታዊ ጦር ኃይሎች ምክር ቤት መሪ እንደነበር ተናገረ። ምክር ቤቱ በዲሞክራሲያዊ ምርጫ የተመረጠውን ፕሬዝደንት
ቲጃን ከባህን ከስልጣን ለማስወገድ በጦር መኮንኖች የተመሰረተ ነበር።
የኮሮማ መፈንቅለ መንግስቱን ለማካሄድ እንዳቀረበው ምክንያት መጥፎ ነበር፡፡ ሁሉም ነገር በቁጥጥር ስር እንደሆነ እና ሁሉም ሰው ወደ ስራ እንዲወጣ ምክር ሰጠ።
ከንግግሩ ጀርባ ግን የተኩስ እሩምታ እና የተቆጡ ወታደሮች ሲሳደቡ ሲጨፍሩ ይሰማል።
ምሽት ላይ በሌላ አዋጅ አማጺዎች እና ጦሩ የሲቪሉን መንግስት “ለሃገር ጥቅም” ሲባል ለመገልበጥ እንደተቀናጁ
በሬድዮ ተነገረ። አማጺዎች እና ጦር ግንባር የነበሩ ወታደሮችከተማውን ማጥለቅለቅ ጀመሩ፡፡ ሃገሪቱ ሙሉ ለሙሉ ወደ ስርዓት አልበኝነት ገባች። እየሆነ ያለው ሁሉ አላማረኝም:: ጠላሁት ወደ ቀድሞ ህይወቴ መመለስ አልችልም:: አሁን ግን በህይወት የማመልጥ አልመስልህ አለኝ፡፡
አማጺዎች እና ወታደሮቹ የባንክ ካዝናን መስበር፣ ፈንጅ ማፈንዳት፣ ሰዎችን አስቁሞ መበርበር መዝረፍ ጀመሩ::
ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን እና የዮኒቨርሲቲ ግቢዎችን ተቆጣጠሩ። ደጅ ተቀምጦ ከመመልከት በስተቀር ምንም
የሚሰራ ነገር የለም:: አጎቴ የጀመረውን ቤት ለመጨረስ ወሰነ።በጠዋት ጀምረን እስከ ረፋድ ድረስ መስራት ጀመርን። የተኩስ እሩምታው ከቀን ቀን እየባሰ ከቤት መውጣት አስፈሪ እየሆነ መጣ፡፡ በጀምላ ብዙ ሰዎች ተገደሉ። ስለዚህ ብዙም ሳንቆይ ስራውን አቆምነው።
የታጠቁት ኃይሎች በከተማው ሱቆች እና ገበያ የሚገኘውን ምግብ በጉልበት ነጥቀው ወሰዱ። ከውጭ የሚመጣው ምግብ እና ከክፍለ ሃገር ወደ ከተማ የሚገባው ምግብ ቆሟል። ሎራ
ገንዘብ ትልክልኝ ስለነበር የቆጠብኩት ትንሽ ገንዘብ ነበረኝ ። ወደ ከተማው ወጥቼ ሩዝ፣ ደሮ፣ አሳ እና ሌሎች የታሸጉ ምግቦችን ለመግዛት ወሰንኩ፡፡ ወደ ገበያ መሄድ ግን አደጋ ነበረው። የበፊት
የጦር ሜዳ ጓደኞቼን ቢገኙኝ እና ከጦርነቱ እራሴን ማግለሌን
ቢያውቁ ይገሉኛል። ቤት መቀመጥ ደግሞ አልችልም ምግ መፈለግ ይኖርብኛል።
አንድ ድብቅ ገበያ እንዳለ እና የተለያዩ የማይገኙ የምግብ አይነቶች ለተራው ህዝብ እንደሚሸጥ ሰማን፡፡ ዋጋው ገበያ
ከመደበኛ ዋጋ ሁለት እጥፍ ቢሆንም ከአደጋ ያተርፋል።በጠዋት ማንም አንዳያየን አንገታችንን ደፍተን ወደ ገበያው
አመራን። ሩዝ፣ የወይራ ዘይት፣ ጨው፣ አሳ ገዝተን ልንወጣ ስንል መኪና እና ወታደሮች ዘለው ወረዱ። ወደ ህዝቡ
በመጠጋት የማስጠንቀቂያ ተኩስ ወደ ሰማይ ተኮሱ። በድምጸ ማጉያ አዛዡ የምግብ ዘምቢላችንን መሬት ላይ እንድናስቀምጥ እና እጃችንን ራሳችን ላይ እንድናስቀምጥ ትዕዛዝ ሰጠ።በድንጋጤ ለመሮጥ የሞከረች አንዲት ሴት ግንባሯ በጥይትተመታ:: ሁሉም ሰው ተረበሸ። እኛም ምግባችንን ይዘን ሮጥን።
ወደ ዋናው መንገድ ስንደርስ “ግድያ ይቁም” የሚል መፈክር ያነገቡ ሰልፈኞች አየን፡፡ ነጭ ቲሸርት እና ራሳቸው ላይ ነጭ
ጨርቅ አስረዋል። እንዳለየ ትተናቸው ልንሄድ ስንሞክር ወታደሮች ወደ እኛ መጡ። ስለዚህ ያለን ምንም አማራጭ
ከሰልፈኞቹ ጋር ተቀላቀልን።ታጠቂዎቹ አስለቃሽ ጭስ መልቀቅ ጀመሩ፡፡ሰዎች አፍንጫቸው መድማት ጀመረ:: ሁሉም በአገኘው መንገድ መሮጥ ጀመረ።
እግሬ አውጭኝ! አፍንጫየን በእጄ እንደሸፈንኩ በሌላ እጄ ዘምቢሌን አጥብቄ ይዤ ከመሐመድ ጋር ሮጥኩ። እንባየ ጉንጩ ላይ ፈስስ ፤ አይኔም ከበደኝ፡፡
መውጫ በመፈለግ ከህዝብ ጋር መሮጣችንን ቀጠልን። ከህዝቡ ተነጥለን ትንሽ ነፋስ አገኘን። ብዙም ሳይቆይ ሌሎች
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
ከሰልፈኞቹ ጋር ተቀላቀልን።ታጠቂዎቹ አስለቃሽ ጭስ መልቀቅ ጀመሩ፡፡ሰዎች አፍንጫቸው መድማት ጀመረ:: ሁሉም በአገኘው መንገድ መሮጥ ጀመረ።
እግሬ አውጭኝ! አፍንጫየን በእጄ እንደሸፈንኩ በሌላ እጄ ዘምቢሌን አጥብቄ ይዤ ከመሐመድ ጋር ሮጥኩ። እንባየ ጉንጩ ላይ ፈስስ ፤ አይኔም ከበደኝ፡፡
መውጫ በመፈለግ ከህዝብ ጋር መሮጣችንን ቀጠልን። ከህዝቡ ተነጥለን ትንሽ ነፋስ አገኘን። ብዙም ሳይቆይ ሌሎች
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#ምስጠረ_ሰውነት
ወፍ መሳይዋ ፍጥረት ፣ ፍጠኚ ገስግሺ
ካ'ድማስ ተሻገሪ ፤ አድማስን ልበሺ።
ካስማ መቅደስሽን
ማረፊያ ጎጆሽን
ቅጽር አበጅተሽ ፣
ከባሕር የሚዘልቅ
ልብ ላይ የሚጠልቅ
ምስጢሬን አንግተሽ፤
ፍጠኝ ከዕድሜ ዥረት ፣ ከጊዜ ምናኔ
ደመናውን ፍቺ ፣ ባ'ካልሽ ውብ ቅኔ
ኺጂ ተሻገሪ . . .!
ከተራራው ግርጌ ሳትመሽጊ ደርሶ
የተፈጥሮ ዑደት ኺደቱን ጨርሶ
ፊትሽ ሳይደርስብሽ ፣
እንግዳን ይቀበል ፣ ያማሕፀን ደጅሽ።
ያያ'ርባ መሻገሪያ ሠላሳ ክረምቱ
የመከራን ዕድል አሐዱ ቍጥረቱ፣
ይህ ነው ሕግጋቱ . . .!
በ'ኩሌታ መሞት በ'ኩሌታ መትረፍ
ከሱባዔ መክተም ፣ በምናኔ ማለፍ።
( . . . ልክ እንደ ወፊቱ . . .!)
መንቆርሽ ሳይቆዝም ፣ ጥፍርሽ ሳይታጠፍ
ክንፍሽ ኃይሉ ሳይዝል ፤ ማሕፀንሽ ሳይሠንፍ ፣
ወፍ መሳይዋ ፍጥረት ፣ ፍጠኚ፤ ገስግሺ
ካ'ድማስ ተሻገሪ አድማስን ልበሺ ፤
እውነትሽን እውነቴን ...
ካ'ካሌ ላይ ወስደሽ ፣ አካልሽ ላይ ጻፊ!!
🔘ተሰፋሁን ከበደ🔘
ወፍ መሳይዋ ፍጥረት ፣ ፍጠኚ ገስግሺ
ካ'ድማስ ተሻገሪ ፤ አድማስን ልበሺ።
ካስማ መቅደስሽን
ማረፊያ ጎጆሽን
ቅጽር አበጅተሽ ፣
ከባሕር የሚዘልቅ
ልብ ላይ የሚጠልቅ
ምስጢሬን አንግተሽ፤
ፍጠኝ ከዕድሜ ዥረት ፣ ከጊዜ ምናኔ
ደመናውን ፍቺ ፣ ባ'ካልሽ ውብ ቅኔ
ኺጂ ተሻገሪ . . .!
ከተራራው ግርጌ ሳትመሽጊ ደርሶ
የተፈጥሮ ዑደት ኺደቱን ጨርሶ
ፊትሽ ሳይደርስብሽ ፣
እንግዳን ይቀበል ፣ ያማሕፀን ደጅሽ።
ያያ'ርባ መሻገሪያ ሠላሳ ክረምቱ
የመከራን ዕድል አሐዱ ቍጥረቱ፣
ይህ ነው ሕግጋቱ . . .!
በ'ኩሌታ መሞት በ'ኩሌታ መትረፍ
ከሱባዔ መክተም ፣ በምናኔ ማለፍ።
( . . . ልክ እንደ ወፊቱ . . .!)
መንቆርሽ ሳይቆዝም ፣ ጥፍርሽ ሳይታጠፍ
ክንፍሽ ኃይሉ ሳይዝል ፤ ማሕፀንሽ ሳይሠንፍ ፣
ወፍ መሳይዋ ፍጥረት ፣ ፍጠኚ፤ ገስግሺ
ካ'ድማስ ተሻገሪ አድማስን ልበሺ ፤
እውነትሽን እውነቴን ...
ካ'ካሌ ላይ ወስደሽ ፣ አካልሽ ላይ ጻፊ!!
🔘ተሰፋሁን ከበደ🔘
#ለኀጥአን_የመጣ
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
ሰዎች በፍጥነት እየሮጡ በእኛ በኩል መጡ። ከኋላ ወታደሮች ያባሯቸው ነበር፡፡ እኛም ከፊት መምራት ጀመርን። መሐመድ እና እኔ በውስጥ ለውስጥ መንገዶች ሩጠን በታጠረ መንገድ
ደረስን። ታጣቂዎች አካባቢውን ይጠብቁ ነበር። ምሽት እስኪሆን የውሃ መውረጃ ቦይ ውስጥ ለስድስት ስዓታት ተንጋላን ተኛን።
ከሞት ለመትረፍ በለሊቱ መንቀሳቀስ ሳይሻል አይቀርም ብለን ነበር እስኪመሽ ፀየቆየነው:: ከእኛ ጋር የተወሰኑ ሰዎች ነበሩ:: ሰማያዊ ቲ ሸርት ያደረገ እና ግንባሩን እያለበው በተደጋጋሚ
የሚጠርግ ተማሪ፣ በፍርሃት የምትንቀጠቀጥ በሃያዎቹ
የምትገኝ ሴት እና ቲ ሸርቱ በሌላ ሰው ደም የተጨማለቀ ፂማም ሰውየ አብረውን ነበሩ። በጣም አዝኛለሁ መጥፎ ስሜትም
ተሰምቶኛል ግን ጦርነት እንደማያቁት እንደ እነዚህ ሰዎች አልፈራሁም። አጎቴ እንዳይጨነቅ ብቻ ነበር ሃሳቤ። የፍርድ ቀንን እንደመጠበቅ ምሽቱ በጣም ራቀብን። በመጨረሻ ቀስ ብሎ
እየጨለመ ድንግግዝ ካለ ብኋላ ሙሉ ጨለማ ሆነ ምሽት ገባ።
አጎቴ አይኖቹ እንባ አዝለው ደጃፍ ተክዞ ተቀምጦ አገኘሁት። ሲያየኝ ከተቀመጠበት ዘሎ ተነስቶ አቀፈኝ። በእቅፉ ውስጥ እንዳለሁ ከዚህ በኋላ ወደ ከተማ መሄድ እንደለለብን ነገረን።
አማራጭ ግን አልነበረንም! ምግብ ለማግኘት መውጣት ነበረብን፡፡
ተኩሱ ለተከታታይ አምስት ወራት የከተማው የማጀቢያ ድምፅ እስኪመስል ቀጠለ፡፡ ጠዋት ቤተሰቦች ደጃፍ ላይ
ተቀምጠው ይመለከታሉ። ታጣቂዎቹ ሲዘረፉ፣ ሲገድሉ እና ሴቶችን ሲደፍሩ ከልካይ አጡ። በሚቃጠሉ ቤቶች የፌዝ ሲስቁ ይስማል።አንድ ምሽት ጎረቤታችን ሬዲዮ ከፍቶ መንግስትን የሚወነጅል ጣቢያ ያዳምጣል። ወዲያው ገልባጭ መኪና ሙሉ ወታደር መጣና ቤታቸው ፊት ለፊት ቆመ፡፡ ሰውየውን፣ባለቤቱን እና ልጆቹን አውጥተው ተኩሰው ገደሏቸው::
ለሶስት ሳምንታት ያህል ከቤት መውጣት ፈራን፡፡ ቆይቶ ግን ተኩሱም እብደቱም ተለመድ፡፡ ተባራሪ ጥይት ሊገድላቸው
ቢችልም ሰዎች ግን የቀን ተቀን ንሮቸውን ቀጠሉ፡፡ ህጻናት ምን እንደተተኮስ በመገመት ይጫወታሉ። AK47 G3 HPG ወይም መትረጊስ እያሉ ይገምታሉ። ከመሐመድ ጋር አለት ላይ ዝም ብለን ተቀምጠን እናስባለን። ከጦርነቱ ለማምለጥ የተጓዝነው
ረጅሙን መንገድ አስታውስኩ። ረጅም መንገድ ብንጓዝም አሁን ጦርነቱ ደርሶብናል።
ኒው ዮርክ ካለችው ሎራ ጋር ለአምስት ወራት ያህል መገናኘት አልቻልኩም። ከዛ በፊት በየጊዜው ደብዳቤ እንለዋወጥ
ነበር። ደህና እንደሆነችና ራሴን እንድጠብቅ ትነግረኛለች።ደብዳቤዎቿ ለስራ ከምትንቀሳቀስባቸው የተለያዩ ሃገሮች ነበር የሚመጡት። ልደውልላት ብፈልግም አልቻልኩም። የሴራሊዮን ቴሌ ኮም ሴራ ቴል ስራ አቁሟል። በየቀኑ የስዓት እላፊ እስከሚደርስ ደጃፍ ላይ ቁጭ ብለን ከተማውን እንመለከታለን።
ተረት ማውራት፣ ቀልድ እና መዚቃ ከቆሙ ቆይተዋል። ነገሮች ብለን ተስፋ ብናደርግም በተቃራኒው ሁኔታው
እየባሰበት ነበር የሚሄደው:: አጎቴም አመመው። በቅርብ ከሚገኘው ሱቅ ማስታገሻ ብገዛለትም ህመሙ እየበረታበት መጣ፡፡ አክስቴ ሳሊ በግድ ልታበላው ብትፈልግም ይተፋዋል።
ሁሉም ሆስፒታሎች እና መድሃኒት ቤቶች ተዘግተዋል።በከተማ የሚገኙ ዶክተሮች እና ነርሶችን ማፈላለግ ጀመርን።
አብዛኞቹ ሃገር ለቀው ተሰደዋል፡፡ ሃገር ለቀው ያልወጡት ደግሞ ከቤት ,መውጣት ይፈራሉ፡፡ አንድ ምሽት አጎቴ በሽታው ባሰበት ሰውነቱ እተንቀጠጠ እኔን ተመለከተኝ። ተስፋው ተሟጦ ማለቁ ከአይኖቹ ይታያል። ከንፈሩ የሆነ ነገር ሊናገር ተንቀጥቅጠው
ቆሙ። አጎቴ አረፈ። ደነገጥኩ። እንዴት ነው ለባለቤቱ ምነግራት?! እሷ እኮ ውሃ እያሞቀችለት ነበር። ትንሽ ቆይታ
ውሃውን ይዛ መጣች እና ከሁለታችን ላይ ለቀቀችብን። የባሏን ህልፈት ማመን አልቻለችም:: የኔ የምላቸውን ሰዎች እንዳጣሁ ነው።
ቤቱ በለቅሶ ተደባለቀ። የአጎቴ ልጆች ከእንግዲህ ማን ሊንከባከበን ነው? እንዴት በዚህ አስቸጋሪ ወቅት እንዴት ይሄ
ይሆንብናል ይሄዳል ? እያሉ ያለቅሱ ነበር።
የአጎቴ ቀብር በሚቀጥለው ቀን ተፈፀመ። አስቸጋሪ ወቅት ቢሆንም ብዙ ሰዎች በቀብሩ ቦታ ተገኙ። አክስቴ መምጣት
ብትፈልግም አልቻለችም:: ከቤት ከመውጣታችን በፊት ተዝለፍልፋ ወደቀች። በመቃብሩ ቦታ ኢማሙ ሱራ ካደረሰ በኋላ አጎቴ ግብአተ መሬቱ ተፈፀመ። ሰዎች ወዲያው ወደ ቤታቸው
ተበተኑ። መቃብሩ ጎን ተቀምጩ አጎቴን አወራሁት። አጎቴ “የሚረዳህ ሰው ስላላገኘን ይቅርታ” አልኩ። በጣም እንደምወደው እና አድጌ እንዲያየኝ እፈልግ እንደነበር እንደሚያውቅ ተስፋ
አደረኩ፡፡ እጆቼን አፈር ጨብጬ አለቀስኩ።
የአጎቴ ቀብር ከተፈፀመ ከተወሰኑ ቀኖች በኋላ ሎራን በስልክ ማግኘት ቻልኩ፡፡ ኒው ዮርክ መምጣት ከቻልኩ እሷ ቤት ማረፍ እንደምችል ጠየቅኳት፡፡ እሽ አለች።
በሃሳቤ ይታየኛል” አልኳት። ጊኒ
ጊኒ ኮናክሪ ስደርስ እንደምደውልላት ነገርኳት፡፡ ኮናክሪ የጊኒ ዋና ከተማ ስትሆን በጊዜው ጊኒ ብቸኛዋ ሰላማዊ ጎረቤት ሃገር እና ብቸዋ ከሴራ ሊዮን መውጫ በር ነበረች:: መውጣት ነበረብኝ፡፡ ከቆየሁ ተመልሼ ወታደር እሆናለሁ ወይም እምቢ ብየ የቀድሞ ጓደኞቼ ይገድሉኛል። አገግመው የነበረ አንዳንድ ጓደኞቼ እንደገና ወደ ጦር ተቀላቅለዋል።
በደረቅ ለሊት ፍሪ ታውንን ለቅቄ ወጣሁ። ከመሐመድ በስተቀር መሄዴን
ለማንም አልተናገርኩም:: አክስቴ
ከተፅናናች በኋላ የእኔን መሄድ እንደሚነግራት ከመሐመድ
ተነጋግረናል። ከባሏ ሞት በኋላ ጀርባዋን ለአለም እና በአለም ለሚኖር ሁሉ ሰጥታለች፡፡ ህዳር 1 1997 ነበር የወጣሁት።ሳይነጋ መውጣት ነበረብኝ፡፡ በለሊት መጓዙ ከ ደህንነት አንፃር
የተሻለ ነበር። ግማሾቹ ታጣቂዎች ተኝተዋል የቀሩት ወታደሮች ደግሞ በለሊት ከሩቅ ማየት ይከብዳል። የተኩስ እሩምታው ፀጥ ረጭ ባለው ከተማ ይስተጋባል። ብርድ አየር እየመታኝ የሽተተ አስክሬን እና ባሩድ እያሸተትኩ መጓዝ ጀመርኩ። ለመሐመድ ስደርስ አሳውቅሃለሁ ብየ ተጨባበጥን። ትክሻየን መታ መታ ከማድረግ ውጪ ምንም አልተናገረም::
የተወሰኑ ልብሶቼን የያዘ አንድ ትንሽ ቆሻሻ ሻንጣ ብቻ ነበር የያዝኩት:: ትልቅ እና የሚስብ ሻንጣ መያዝ ለአደጋ ያጋልጣል።
ታጣቂዎች ከፍ ያለ ዋጋ ያለው ጠቃሚ ነገር እያሸሽህ ስለሚመስላቸው ሊተኩስብህ ይችላሉ። መሐመድን ትቼ ጎህ ሳይቀድ ፈጠን ብየ መጓዜን ቀጠልኩ፡፡ ጨለማው ግን ያስፈራል።
የስልክ እንጨት ተደግፌ ተነፈስኩ። ራሴን ማበረታታት ጀመርኩ:: መውጣት አለብኝ ካልሆነ ወደ ጦሩ መመለሴ ነው።
ይሄን ማሰብ እንኳ አልፈልግም፡፡ የመኪና ድምፅ ስሰማ ቶሎ ብየ ወደ ቦይ ነገር በመግባት ተደበቅኩ፡፡ በመንገድ ላይ ብቸኛው ሲቭል እኔ ነበርኩ፡፡ የፍተሻ ጣቢያዎችን አንዳንዴ ቦይ ውስጥ
በጉልበቴ እየዳሁ ወይም በቤቶች ጀርባ ተደብቄ አለፍኩ። በሰላም ወደ አንድ አሮጌ የአውቶብስ ጣቢያ ደረስኩ። ብዙ ሰዎች ነበሩ።በሰላሳዎች የሚገኙ ወንዶች፣ ሴቶች እና ህፃናት። በአውቶብስ
ውስጥ መጨረሻ ወንበር ላይ ተቀመጥኩ። ሹፌሩ እየዞረ ሂሳብ
ከተቀበለ በኋላ ጉዞ ጀመረ፡፡ መንገዱ ለብዙ አመታት አገልግሎት ውጭ ስለነበር አውቶብሱ ከቅጠል እና ቅርንጫፍ
ጋር እየተላተመ በዱር ውስጥ የሚሄድ ነበር የሚመስለው። ጎህ እስኪቀድ ቀስ ብሎ ነበር የተጓዘው:: አንድ ቦታ ላይ ሁላችን ወርደን መኪናው አንድ ዳገት መውጣት ነበረበት፡፡ ሁላችንም
ዝም ብለን ፊታችን በፍርሃት ከብዶ ነበር፡፡ ወደ አውቶብሱ ተመልሰን ከገባን በኋላ
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
ሰዎች በፍጥነት እየሮጡ በእኛ በኩል መጡ። ከኋላ ወታደሮች ያባሯቸው ነበር፡፡ እኛም ከፊት መምራት ጀመርን። መሐመድ እና እኔ በውስጥ ለውስጥ መንገዶች ሩጠን በታጠረ መንገድ
ደረስን። ታጣቂዎች አካባቢውን ይጠብቁ ነበር። ምሽት እስኪሆን የውሃ መውረጃ ቦይ ውስጥ ለስድስት ስዓታት ተንጋላን ተኛን።
ከሞት ለመትረፍ በለሊቱ መንቀሳቀስ ሳይሻል አይቀርም ብለን ነበር እስኪመሽ ፀየቆየነው:: ከእኛ ጋር የተወሰኑ ሰዎች ነበሩ:: ሰማያዊ ቲ ሸርት ያደረገ እና ግንባሩን እያለበው በተደጋጋሚ
የሚጠርግ ተማሪ፣ በፍርሃት የምትንቀጠቀጥ በሃያዎቹ
የምትገኝ ሴት እና ቲ ሸርቱ በሌላ ሰው ደም የተጨማለቀ ፂማም ሰውየ አብረውን ነበሩ። በጣም አዝኛለሁ መጥፎ ስሜትም
ተሰምቶኛል ግን ጦርነት እንደማያቁት እንደ እነዚህ ሰዎች አልፈራሁም። አጎቴ እንዳይጨነቅ ብቻ ነበር ሃሳቤ። የፍርድ ቀንን እንደመጠበቅ ምሽቱ በጣም ራቀብን። በመጨረሻ ቀስ ብሎ
እየጨለመ ድንግግዝ ካለ ብኋላ ሙሉ ጨለማ ሆነ ምሽት ገባ።
አጎቴ አይኖቹ እንባ አዝለው ደጃፍ ተክዞ ተቀምጦ አገኘሁት። ሲያየኝ ከተቀመጠበት ዘሎ ተነስቶ አቀፈኝ። በእቅፉ ውስጥ እንዳለሁ ከዚህ በኋላ ወደ ከተማ መሄድ እንደለለብን ነገረን።
አማራጭ ግን አልነበረንም! ምግብ ለማግኘት መውጣት ነበረብን፡፡
ተኩሱ ለተከታታይ አምስት ወራት የከተማው የማጀቢያ ድምፅ እስኪመስል ቀጠለ፡፡ ጠዋት ቤተሰቦች ደጃፍ ላይ
ተቀምጠው ይመለከታሉ። ታጣቂዎቹ ሲዘረፉ፣ ሲገድሉ እና ሴቶችን ሲደፍሩ ከልካይ አጡ። በሚቃጠሉ ቤቶች የፌዝ ሲስቁ ይስማል።አንድ ምሽት ጎረቤታችን ሬዲዮ ከፍቶ መንግስትን የሚወነጅል ጣቢያ ያዳምጣል። ወዲያው ገልባጭ መኪና ሙሉ ወታደር መጣና ቤታቸው ፊት ለፊት ቆመ፡፡ ሰውየውን፣ባለቤቱን እና ልጆቹን አውጥተው ተኩሰው ገደሏቸው::
ለሶስት ሳምንታት ያህል ከቤት መውጣት ፈራን፡፡ ቆይቶ ግን ተኩሱም እብደቱም ተለመድ፡፡ ተባራሪ ጥይት ሊገድላቸው
ቢችልም ሰዎች ግን የቀን ተቀን ንሮቸውን ቀጠሉ፡፡ ህጻናት ምን እንደተተኮስ በመገመት ይጫወታሉ። AK47 G3 HPG ወይም መትረጊስ እያሉ ይገምታሉ። ከመሐመድ ጋር አለት ላይ ዝም ብለን ተቀምጠን እናስባለን። ከጦርነቱ ለማምለጥ የተጓዝነው
ረጅሙን መንገድ አስታውስኩ። ረጅም መንገድ ብንጓዝም አሁን ጦርነቱ ደርሶብናል።
ኒው ዮርክ ካለችው ሎራ ጋር ለአምስት ወራት ያህል መገናኘት አልቻልኩም። ከዛ በፊት በየጊዜው ደብዳቤ እንለዋወጥ
ነበር። ደህና እንደሆነችና ራሴን እንድጠብቅ ትነግረኛለች።ደብዳቤዎቿ ለስራ ከምትንቀሳቀስባቸው የተለያዩ ሃገሮች ነበር የሚመጡት። ልደውልላት ብፈልግም አልቻልኩም። የሴራሊዮን ቴሌ ኮም ሴራ ቴል ስራ አቁሟል። በየቀኑ የስዓት እላፊ እስከሚደርስ ደጃፍ ላይ ቁጭ ብለን ከተማውን እንመለከታለን።
ተረት ማውራት፣ ቀልድ እና መዚቃ ከቆሙ ቆይተዋል። ነገሮች ብለን ተስፋ ብናደርግም በተቃራኒው ሁኔታው
እየባሰበት ነበር የሚሄደው:: አጎቴም አመመው። በቅርብ ከሚገኘው ሱቅ ማስታገሻ ብገዛለትም ህመሙ እየበረታበት መጣ፡፡ አክስቴ ሳሊ በግድ ልታበላው ብትፈልግም ይተፋዋል።
ሁሉም ሆስፒታሎች እና መድሃኒት ቤቶች ተዘግተዋል።በከተማ የሚገኙ ዶክተሮች እና ነርሶችን ማፈላለግ ጀመርን።
አብዛኞቹ ሃገር ለቀው ተሰደዋል፡፡ ሃገር ለቀው ያልወጡት ደግሞ ከቤት ,መውጣት ይፈራሉ፡፡ አንድ ምሽት አጎቴ በሽታው ባሰበት ሰውነቱ እተንቀጠጠ እኔን ተመለከተኝ። ተስፋው ተሟጦ ማለቁ ከአይኖቹ ይታያል። ከንፈሩ የሆነ ነገር ሊናገር ተንቀጥቅጠው
ቆሙ። አጎቴ አረፈ። ደነገጥኩ። እንዴት ነው ለባለቤቱ ምነግራት?! እሷ እኮ ውሃ እያሞቀችለት ነበር። ትንሽ ቆይታ
ውሃውን ይዛ መጣች እና ከሁለታችን ላይ ለቀቀችብን። የባሏን ህልፈት ማመን አልቻለችም:: የኔ የምላቸውን ሰዎች እንዳጣሁ ነው።
ቤቱ በለቅሶ ተደባለቀ። የአጎቴ ልጆች ከእንግዲህ ማን ሊንከባከበን ነው? እንዴት በዚህ አስቸጋሪ ወቅት እንዴት ይሄ
ይሆንብናል ይሄዳል ? እያሉ ያለቅሱ ነበር።
የአጎቴ ቀብር በሚቀጥለው ቀን ተፈፀመ። አስቸጋሪ ወቅት ቢሆንም ብዙ ሰዎች በቀብሩ ቦታ ተገኙ። አክስቴ መምጣት
ብትፈልግም አልቻለችም:: ከቤት ከመውጣታችን በፊት ተዝለፍልፋ ወደቀች። በመቃብሩ ቦታ ኢማሙ ሱራ ካደረሰ በኋላ አጎቴ ግብአተ መሬቱ ተፈፀመ። ሰዎች ወዲያው ወደ ቤታቸው
ተበተኑ። መቃብሩ ጎን ተቀምጩ አጎቴን አወራሁት። አጎቴ “የሚረዳህ ሰው ስላላገኘን ይቅርታ” አልኩ። በጣም እንደምወደው እና አድጌ እንዲያየኝ እፈልግ እንደነበር እንደሚያውቅ ተስፋ
አደረኩ፡፡ እጆቼን አፈር ጨብጬ አለቀስኩ።
የአጎቴ ቀብር ከተፈፀመ ከተወሰኑ ቀኖች በኋላ ሎራን በስልክ ማግኘት ቻልኩ፡፡ ኒው ዮርክ መምጣት ከቻልኩ እሷ ቤት ማረፍ እንደምችል ጠየቅኳት፡፡ እሽ አለች።
በሃሳቤ ይታየኛል” አልኳት። ጊኒ
ጊኒ ኮናክሪ ስደርስ እንደምደውልላት ነገርኳት፡፡ ኮናክሪ የጊኒ ዋና ከተማ ስትሆን በጊዜው ጊኒ ብቸኛዋ ሰላማዊ ጎረቤት ሃገር እና ብቸዋ ከሴራ ሊዮን መውጫ በር ነበረች:: መውጣት ነበረብኝ፡፡ ከቆየሁ ተመልሼ ወታደር እሆናለሁ ወይም እምቢ ብየ የቀድሞ ጓደኞቼ ይገድሉኛል። አገግመው የነበረ አንዳንድ ጓደኞቼ እንደገና ወደ ጦር ተቀላቅለዋል።
በደረቅ ለሊት ፍሪ ታውንን ለቅቄ ወጣሁ። ከመሐመድ በስተቀር መሄዴን
ለማንም አልተናገርኩም:: አክስቴ
ከተፅናናች በኋላ የእኔን መሄድ እንደሚነግራት ከመሐመድ
ተነጋግረናል። ከባሏ ሞት በኋላ ጀርባዋን ለአለም እና በአለም ለሚኖር ሁሉ ሰጥታለች፡፡ ህዳር 1 1997 ነበር የወጣሁት።ሳይነጋ መውጣት ነበረብኝ፡፡ በለሊት መጓዙ ከ ደህንነት አንፃር
የተሻለ ነበር። ግማሾቹ ታጣቂዎች ተኝተዋል የቀሩት ወታደሮች ደግሞ በለሊት ከሩቅ ማየት ይከብዳል። የተኩስ እሩምታው ፀጥ ረጭ ባለው ከተማ ይስተጋባል። ብርድ አየር እየመታኝ የሽተተ አስክሬን እና ባሩድ እያሸተትኩ መጓዝ ጀመርኩ። ለመሐመድ ስደርስ አሳውቅሃለሁ ብየ ተጨባበጥን። ትክሻየን መታ መታ ከማድረግ ውጪ ምንም አልተናገረም::
የተወሰኑ ልብሶቼን የያዘ አንድ ትንሽ ቆሻሻ ሻንጣ ብቻ ነበር የያዝኩት:: ትልቅ እና የሚስብ ሻንጣ መያዝ ለአደጋ ያጋልጣል።
ታጣቂዎች ከፍ ያለ ዋጋ ያለው ጠቃሚ ነገር እያሸሽህ ስለሚመስላቸው ሊተኩስብህ ይችላሉ። መሐመድን ትቼ ጎህ ሳይቀድ ፈጠን ብየ መጓዜን ቀጠልኩ፡፡ ጨለማው ግን ያስፈራል።
የስልክ እንጨት ተደግፌ ተነፈስኩ። ራሴን ማበረታታት ጀመርኩ:: መውጣት አለብኝ ካልሆነ ወደ ጦሩ መመለሴ ነው።
ይሄን ማሰብ እንኳ አልፈልግም፡፡ የመኪና ድምፅ ስሰማ ቶሎ ብየ ወደ ቦይ ነገር በመግባት ተደበቅኩ፡፡ በመንገድ ላይ ብቸኛው ሲቭል እኔ ነበርኩ፡፡ የፍተሻ ጣቢያዎችን አንዳንዴ ቦይ ውስጥ
በጉልበቴ እየዳሁ ወይም በቤቶች ጀርባ ተደብቄ አለፍኩ። በሰላም ወደ አንድ አሮጌ የአውቶብስ ጣቢያ ደረስኩ። ብዙ ሰዎች ነበሩ።በሰላሳዎች የሚገኙ ወንዶች፣ ሴቶች እና ህፃናት። በአውቶብስ
ውስጥ መጨረሻ ወንበር ላይ ተቀመጥኩ። ሹፌሩ እየዞረ ሂሳብ
ከተቀበለ በኋላ ጉዞ ጀመረ፡፡ መንገዱ ለብዙ አመታት አገልግሎት ውጭ ስለነበር አውቶብሱ ከቅጠል እና ቅርንጫፍ
ጋር እየተላተመ በዱር ውስጥ የሚሄድ ነበር የሚመስለው። ጎህ እስኪቀድ ቀስ ብሎ ነበር የተጓዘው:: አንድ ቦታ ላይ ሁላችን ወርደን መኪናው አንድ ዳገት መውጣት ነበረበት፡፡ ሁላችንም
ዝም ብለን ፊታችን በፍርሃት ከብዶ ነበር፡፡ ወደ አውቶብሱ ተመልሰን ከገባን በኋላ
እስከ አንድ አሮጌ ድልድይ አደረሰን።
የዛገውን ድልድይ ሁለት ሁለት እየሆን ከተሻገርን በኋላ ሌላ አውቶብስ እስክናገኝ ድረስ ሙሉ ቀን ተጓዝን። ይሄ ሁሉ ታጣቂዎች ወይም የአዲሱ መንግስት ታዳጊ ወታደሮች ሳይገሉን
በህይወት ከ ፍሪታውን ለመውጣት ብቻ ነበር። ሰው ከከተማው ሲወጣ አይወዱም::
አውቶብስ መቆሚያው ላይ መሬት ላይ ተቀምጠን ለሊቱን ሙሉ ጠበቅን። ስላሳ ነበርን፡፡ ማንም ትንፍሽ ብሎ ያወራ
አልነበርም:: ገና ከእብደቱ አላመለጥነም። አንዳንዶቹ መሬት
መሬት ሲያዩ ሌሎቹ ደግሞ በድንጋይ ይጫወቱ ነበር። ተኩስ በሩቅ ይሰማል። ከዚህ ጦርነት መሸሸ ማቆመው መቼ ነው? አውቶብሱ ካልመጣስ? ፍሪ ታውን ያለ ጎረቤቴ ነበር ይሄን መንገድ የነገረኝ፡፡ እስካሁን ሰላም ነው ባልገመትናቸው ፍጥነት እንደሚቀየር አውቃለሁ። ለሊቱን
ሙሉ ስለ አጎቴን ቀጥሎ ስለ አባቴ፣ እናቴ፣ ወንድሞቼ እና ሳስብ አደርኩ። ከእኔ በስተቀር ሰዎች ተከታትለው ለምንድን ነው የሚሞቱት?
ጠዋት ሰዎች ተነስተው ልብሳቸውን አራገፉ፡፡ የአንዳንዶቹ በጤዛ ታጥቦ ነበር። ቅጠሎችን አራገፉ ከፊታቸው ላይ የውሃ
እንጥባቢ አባበሱ። ለስዓታት ከቆየን በኋላ የሞተር ድምፅ ሰማን። አውቶብስ መሆኑን አላወቅንም ስለዚህ ሻንጣችንን ይዘን በዱሩ ውስጥ ተደበቅን፡፡ የሞተሩ ድምፅ ደምቆ መሰማት ጀመረ።
በኋላ አውቶብሱ ሲታየን እየሮጥን ከጫካው ወጥተን አውቶብሱ
እንዲቆምልን ተጣራን። ተጣድፈን ወጣን እና መንቀሳቀሱን ቀጠለ። ረዳቱ ሂሳብ መሰብሰብ ጀመረ፡፡ ከአስራ ስምንት አመት በታች ስለሆንኩ ግማሽ ሂሳብ ከፈልኩ። በዛ ጊዜ ግማሹ ክፍያ
በሰላም ጊዜ ከሚከፈለው ሙሉ ክፍያ ይበልጥ ነበር። በመስኮት
በኩል ዛፎቹ ወደ ኋላ ሲሄዱ እያየሁ መጓዝ ቀጠልኩ።አውቶብሱ ፍጥነቱን ሲቀንስ ዛፎቹ መሳሪያቸውን ባነጣጠሩ
ወታደሮች ተተካ። ሁሉም ሰዉ ከአውቶብሱ እንዲወርድ ጠየቁ፡፡
በኋላ ወደ ማገጃው መሐል ይዘውን ሄዱ። ዘወር ዘወር ብየ ሳይ መሳሪያ የታጠቁ ቦንብ የያዙ ሰዎች አየሁ።አሰላለፋቸውን ሳይ
ከአንድ ወታደር ልጋጪ ነበር። ደም በለበሱ አይኖቹ እያየኝ “ ከፈለኩ እገልሃለሁ ምንም አይመጣም” አለኝ፡፡ አዲስ ሰው አልሆነብኝም::
አውቶብሱን ማንም ሰው ባልገባው ምክንያት ፈተሹ።ከደቂቃዎች በኋላ ሁሉም ተሳፋሪ ተመልሶ ገባ። መንቀሳቀስ
ስንጀምር የመንገድ ማገጃ አጥሩ እየጠፋ ሲመጣ በፊት እንደዚህ አይነት የመንገድ
ማገጃዎች እንዴት እንደምናፈርስ
አስታወስኩ፡፡ በሃሳቡ ብዙ መቆየት አልፈለኩም። ወታደሮቹ ከአንዳንዶች ገንዘብ ፧ ገንዘብ ከሌላቸው ደግሞ የእጅ ስዓት፣ ጌጣ ጌጦች እና ሌላ ዋጋ ሚያወጡ ነገሮችን ይወስዳሉ። ስለዚህ
መንገድ በተዘጋ ቁጥር በሰላም እንዳልፍ ፀሎቴን መድገም እጀምራለሁ።
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
የዛገውን ድልድይ ሁለት ሁለት እየሆን ከተሻገርን በኋላ ሌላ አውቶብስ እስክናገኝ ድረስ ሙሉ ቀን ተጓዝን። ይሄ ሁሉ ታጣቂዎች ወይም የአዲሱ መንግስት ታዳጊ ወታደሮች ሳይገሉን
በህይወት ከ ፍሪታውን ለመውጣት ብቻ ነበር። ሰው ከከተማው ሲወጣ አይወዱም::
አውቶብስ መቆሚያው ላይ መሬት ላይ ተቀምጠን ለሊቱን ሙሉ ጠበቅን። ስላሳ ነበርን፡፡ ማንም ትንፍሽ ብሎ ያወራ
አልነበርም:: ገና ከእብደቱ አላመለጥነም። አንዳንዶቹ መሬት
መሬት ሲያዩ ሌሎቹ ደግሞ በድንጋይ ይጫወቱ ነበር። ተኩስ በሩቅ ይሰማል። ከዚህ ጦርነት መሸሸ ማቆመው መቼ ነው? አውቶብሱ ካልመጣስ? ፍሪ ታውን ያለ ጎረቤቴ ነበር ይሄን መንገድ የነገረኝ፡፡ እስካሁን ሰላም ነው ባልገመትናቸው ፍጥነት እንደሚቀየር አውቃለሁ። ለሊቱን
ሙሉ ስለ አጎቴን ቀጥሎ ስለ አባቴ፣ እናቴ፣ ወንድሞቼ እና ሳስብ አደርኩ። ከእኔ በስተቀር ሰዎች ተከታትለው ለምንድን ነው የሚሞቱት?
ጠዋት ሰዎች ተነስተው ልብሳቸውን አራገፉ፡፡ የአንዳንዶቹ በጤዛ ታጥቦ ነበር። ቅጠሎችን አራገፉ ከፊታቸው ላይ የውሃ
እንጥባቢ አባበሱ። ለስዓታት ከቆየን በኋላ የሞተር ድምፅ ሰማን። አውቶብስ መሆኑን አላወቅንም ስለዚህ ሻንጣችንን ይዘን በዱሩ ውስጥ ተደበቅን፡፡ የሞተሩ ድምፅ ደምቆ መሰማት ጀመረ።
በኋላ አውቶብሱ ሲታየን እየሮጥን ከጫካው ወጥተን አውቶብሱ
እንዲቆምልን ተጣራን። ተጣድፈን ወጣን እና መንቀሳቀሱን ቀጠለ። ረዳቱ ሂሳብ መሰብሰብ ጀመረ፡፡ ከአስራ ስምንት አመት በታች ስለሆንኩ ግማሽ ሂሳብ ከፈልኩ። በዛ ጊዜ ግማሹ ክፍያ
በሰላም ጊዜ ከሚከፈለው ሙሉ ክፍያ ይበልጥ ነበር። በመስኮት
በኩል ዛፎቹ ወደ ኋላ ሲሄዱ እያየሁ መጓዝ ቀጠልኩ።አውቶብሱ ፍጥነቱን ሲቀንስ ዛፎቹ መሳሪያቸውን ባነጣጠሩ
ወታደሮች ተተካ። ሁሉም ሰዉ ከአውቶብሱ እንዲወርድ ጠየቁ፡፡
በኋላ ወደ ማገጃው መሐል ይዘውን ሄዱ። ዘወር ዘወር ብየ ሳይ መሳሪያ የታጠቁ ቦንብ የያዙ ሰዎች አየሁ።አሰላለፋቸውን ሳይ
ከአንድ ወታደር ልጋጪ ነበር። ደም በለበሱ አይኖቹ እያየኝ “ ከፈለኩ እገልሃለሁ ምንም አይመጣም” አለኝ፡፡ አዲስ ሰው አልሆነብኝም::
አውቶብሱን ማንም ሰው ባልገባው ምክንያት ፈተሹ።ከደቂቃዎች በኋላ ሁሉም ተሳፋሪ ተመልሶ ገባ። መንቀሳቀስ
ስንጀምር የመንገድ ማገጃ አጥሩ እየጠፋ ሲመጣ በፊት እንደዚህ አይነት የመንገድ
ማገጃዎች እንዴት እንደምናፈርስ
አስታወስኩ፡፡ በሃሳቡ ብዙ መቆየት አልፈለኩም። ወታደሮቹ ከአንዳንዶች ገንዘብ ፧ ገንዘብ ከሌላቸው ደግሞ የእጅ ስዓት፣ ጌጣ ጌጦች እና ሌላ ዋጋ ሚያወጡ ነገሮችን ይወስዳሉ። ስለዚህ
መንገድ በተዘጋ ቁጥር በሰላም እንዳልፍ ፀሎቴን መድገም እጀምራለሁ።
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍2
#ለኀጥአን_የመጣ
#ክፍል_ሀያ_ሶስት(የመጨረሻ ክፍል)
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
አስር ስዓት ሲሆን አውቶብሱ ካምቢያ ከምትባል ከተማ አደረሰን። የመጨረሻ ፌርማታው ነበር። ፍሪ ታውንን ለቀን
ከመጣን ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳፋሪዎቹ ፊት ተፈታ። ግን ብዙም አልቆየም! ድንበር ለማለፍ ክፍያ ስንጠየቅ የሁሉም ፊት መልሶ ተኮማተረ አጉረመረምን፡፡ ሁሉም ሰው ከካልሲው
ውስጥ፣ ከውስጥ ሱሪ እና ከረባት ሳይቀር የተረፈ ገንዘብ ካለ ፈለገ። ሶስት መቶ ሊዮንስ (የሴራሊዮን ገንዘብ) ነበር
የተጠየቅነው:: አንድ ሰው ከገዛ ሃገር ለቆ ለመውጣት ለምንድን ነው ሚከፍለው? አሰብኩ ግን መከራከር አልችልም:: ከፈልኩ:: የይለፍ ወረቀቱ ላይ ማህተም እንደተደረገልኝ ወዲያው ወደ ጊኒ
ደንበር ተሻገርኩ። ዋና ከተማዋ ኮናክሪ ለመድረስ ደግሞ ገና ብዙ መንገድ ይቀረኛል። ወደ ከተማው የሚወስድ አውቶብስ ለማግኘት ቶሎ ቶሎ መራመድ ጀመርኩ። ጊኒ ውስጥ የሚነገር
የትኛውንም ቋንቋ መናገር አልችልም ምን ማድረግ እንዳለብኝም አላሰብኩበትም ነበር። ትንሽ አስጨነቀኝ ግን ከሃገሬ በህይወት መውጣቴ ትልቅ ነገር ነው::
ኮናክሪ የሚሄድ አውቶብሶች የጊኒ ወታደሮች ባቆሟቸው ኬላዎች በኩል ነበር የሚቆሙት፡፡ በኬላዎቹ ተጠግተው
በፈለጉት መጠን የጊኒን ገንዘብ የሚመነዝሩ ሰዎች ነበሩ።
ወታደሮቹ ይሄን ጥቁር ገበያ የሚከላከሉ መስሎኝ ነበር ግን ግድ አይሰጣቸውም:: ገንዘቤን ቀይሬ ወደ ኬላው ተጠጋሁ። ደንበሩ ላይ ያሉ ወታደሮች ወይ እንግሊዝኛ መናገር አይችሉም ወይ
ደግሞ እንደሚችሉ ማሳወቅ አይፈልጉም:: መሳሪያቸውን ብቻ
በተጠንቀቅ ይዘዋል፡፡ ቀና ብየ ማየት አልፈለኩም። ከዚህ በፊት ወታደር እንደነበርኩ እና አሁን ግን ትቼው እሸሸሁ መሆኑን ማሳበቅ አልፈለኩም::
አውቶብሱን ለማግኘት ጥቁር ቡናማ የሆኑ የጣውላ ቤቶችን ማለፍ ነበረብኝ። ውስጥ ወታደሮች የሰዎችን ሻንጣ ይበረብራሉ።ሰዎች ደግሞ መረጃዎቻቸውን ለሃላፊዎች ያሳያሉ። የእኔ ተራ ሲደርስ ወታደሮቹ ሻንጣየን ከፍተው በውስ ጡ ያለውን ሁሉ መሬት ላይ ዘረገፉት። ብዙ እቃ ስላልነበረኝ ለመሰብሰብ እና መልሶ ለመክተት ብዙም አያስቸግርም፡፡ ሁለት ቲ ሸርት፣ ሁለት
ዉስጥ ሱሪ እና ሶስት ጥንድ ሱሪዎች ብቻ ነበሩ::
ከጣውላ ቤቱ ስወጣ መረጃዎቼን ማሳየት ነበረብኝ፡፡ ብዙ ጠረጴዛዎቹ እና ወታደሮች ደግሞ የማንጎ ዛፍ ስር ነበሩ።
መሳሪዎቻቸው ወንበራቸው ላይ ወይም የአንዳንዶቹ ጠረጴዛዎቹ ላይ ተቀምጦ ነበር፡፡ ለማን ማሳየት እንዳለብኝ
አላውቅም::
አንድ ወታደር ወደ እሱ እንደሄድ ምልክት አሳየኝ። እጁን ዘረጋ እና የይለፍ ወረቀቴን ተቀበለኝ። ወታደሩ በማይገባኝ አንድ
ቋንቋ ተናገረ።የይለፍ ወረቀቴን የደረት ኪሱ ውስጥ አስገባው እና እጁን ጠረጴዛ አድርጎ አትኩሮ ተመለከተኝ። አቀረቀርኩ
ወታደሩ አገጩን ቀና አደረገኝ፡፡ የይለፍ ወረቀቴን ከኪሱ አውጥቶ መረመረ። አይኑ ቀላ ፊቱ ላይ ፈገግታ ይታይ ነበር።
እጁን አጥፎ ተደላድሎ ተቀመጠ። ፈገግ አልኩ እሱም ሳቀ።በቋንቋው የሆነ ነገር አለና እጁን እንደገና ጠረጴዛው ላይ አደረገ።ፈገግታው እየጠፋ ሄደ፡፡ የተወሰነ ገንዘብ እጁ ላይ አስቀመጥኩ።
የይለፍ ወረቀቴን ከኪሱ አውጥቶ ሰጠኝ እና በሩ እንዳልፍ ጠቆመኝ፡፡
ብዙ አውቶብሶች ስለነበሩ ወደ ኮናክሪ ለመሄድ አውቶብስ መያዝ እንዳለብኝ አላውቅም ግራ ገባኝ፡፡ ሰዎችን ለመጠየቅ ብሞክርም ማንም ሊረዳኝ አልቻለም:: የማውቀው ፈረንሳይኛ
ቃል bonjour ቦንጁር ብቻ ነበር፡፡
ግራ ገብቶኝ ቁሜያለሁ አንድ አልፎ ሂያጅ በኪሮ ቋንቋ ሲያጉረመርም ሰማሁትና “ ጤና ይስጥልኝ” ብየ ወደ ኮናክሪ
የሚወስደው አውቶብስ የትኛው እንደሆነ ጠየቅኩት። እሱም ወደ ዛው እንደሚጓዝ ነገረኝ እና ወደ ከአፍ እስከ ገደፉ ጢም
ብሎ የሞላ አውቶብስ ውስጥ ገባን፡፡ በየ ሃምሳ ሜትሩ ወደ አስራ አምስት የሚጠጉ ኬላዎች ላይ ወታደሮች ነበሩ እና ወታደሮቹ ምህረት የለሽ ነበሩ። ወታደሮቹ መክፈል የማችሉትን እየደበደቡ
ከአውቶብሱ ያወርዷቸዋል። እኔ ግን እድለኛ ነበርኩ። ከአጠገቤ የነበረው ሰውየ ልጅ ስለመሰልኳቸው ብዙ ኬላዎችን በነፃ አልፌያለሁ። የእሱን መረጃ ያያሉ እና የሁለታችንንም እሱን
ያስከፍላሉ፡፡ ሰውየው የገባው አይመስለኝም:: ገንዘብ ጉዳዩ አይደለም ኮናክሪ መግባት ብቻ ነበር የሚፈልገው:: የመግቢያ ክፍያው ሶስት መቶ ሊዮንስ እንደሆነ ሰዎች ሲያወሩ ሰማሁ።
መቶ ሊዮንስ ብቻ ነበር የቀረኝ፡፡ ምንድን ነው ማደርገው? ብየ ማሰብ ጀመርኩ። ይሄ ሁሉ መንገድ የመጣሁት ለከንቱ ነው? ወደ ፍሪ ታውን መመለስ እንኳ ብፈልግ የምመለስበት ገንዘብ የለኝም:: አይኖቼ እንባ አቀረሩ። ተረበሽኩ ከዚህ መውጫ መንገዱ አልታይህ አለኝ፡፡ አንድ የይለፍ ወረቀቱ የተመታለት ሰው ከኬላ ወደ አውቶብስ ሲመለስ ሻንጣውን ጥሎ አየሁ። የተወሰነ ካመነታሁ በኋላ እድሉን ልጠቀምበት ወሰንኩ። ሰልፉን ትቼ ሻንጣውን ይዤ ተከልኩት:: አውቶብስ ውስጥ ገብቼ መጨረሻ ወንበር ላይ ተደብቄ ተቀመጥኩ። አውቶብሱ ቀስ ብሎ ከወጣ በኋላ ፍጥነቱን ጨመረ። በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሃገሪቱ
ገባሁ በኋላ ግን ችግር ይሆናል፡፡
አውቶብሱ ወደ ኮናክሪ ሲደርስ መጨነቅ ጀመርኩ። ከደረስኩ በኋላ ምን እንደማደርግ አላውቅም:: የሴራሊዮን አምባሳደር ስደተኞች በጊዜዊነት ግቢው ውስጥ እንደሚያሳድር ሰምቻለሁ
ግን ኢምባሲው የት እንደሆነ እንኳ አላውቅም:: ጃሎህ ከሚባል
ፉላኒ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ አርብቶ አደር ጎሳ) ጋር ነበር የተቀመጥኩት። ጃሎህ ፍሪ ታውን እንደኖረ ነገረኝ፡፡ ስለ ጦርነቱ እና በሃገሪቱ ላይ ስላስከተለው ጉዳት አወራን። በኋላ ስልክ ቁጥሩን ሰጠኝ እና ከተማዋን ስንቀሳቀስ እርዳታ ካስፈለገኝ እንድደውልለት ነገረኝ። ማደሪያ እንደሌለኝ ልነግረው ፈለኩ ግን
ቀድሞኝ ወረደ። አብሮኝ የመጣውን ሴራ ሊዮናዊ ፈለኩ ግን ላገኘው አልቻልኩም። ከደቂቃዎች በኋላ አውቶብሱ ግዙፍ
መናሃሪያ ውስጥ ገባ። ወጥቼ ሁሉም ሲሄድ ተመለከትኩ። ተነፈስኩ እና እጆቼ ራሴ ላይ ጭኜ ወደ አግድም ወንበር ሂጄ
ተቀመጥኩ። ፊቴን በእጆቼ ሸፍኜ “ለሊቱን ሙሉ ከዚህ መቀመጥ አልችልም” ብየ ለራሴ አጉረመረምኩ።
ብዙ ታክሲዎች ነበሩ እና አውቶብሱ መናሃሪያ የደረሱ ሰዎች ሁሉ ይዟቸዎል። እኔም ብቸኛ ሚሄድበት የጠፋው እንግዳ
መስየ መታየት ስላልፈለኩ አንዱ
ታክሲ ውስጥ ገባሁ። ሹፌሩ በፈረንሳይኛ ሲናገር ወዴት እንደምሄድ እየጠቀኝ እንደሆነ ገመትኩ። ሴራ ሊዮን ቆንስላ አ ኢምባሲ” ብየ ነገርኩት።በመስኮት ስመለከት የመብራት ምሶሶዎች ላይ የመንገድ መብራቶቹ ተንበርግገው
ተንጠልጥለዋል። ብርሃናቸው ከጨረቃ ብርሃን ሳይበልጥ አይቀርም። ታክሲው ኢምባሲው ፊት ለፊት ቆመ እና የምፈልገው ቦታ ይዞኝ እንደመጣ
ለማረጋገጥ ወደ አረንጓዴ፣ ነጭ እና ሰማያዊ ባንዴራ ጠቆመኝ፡፡ራሴን በማወዛወዝ ትክክል እንደሆነ ከገለፅኩለት በኋላ ከታክሲው ወረድኩ
በኤንባሲው በር ላይ ጠባቂዎቹ በኪሪዎ የይለፍ ወረቀቴን እንዳሳይ ጠየቁኝ፡፡ አሳየኋቸው እና ወደ ግቢው እንድገባ ፈቀዱልኝ::
በግቢው ውስጥ ከሃምሳ በላይ ሰዎች ሲኖሩ እንደእኔ መጠጊያ ያጡ ሳይሆኑ አይቀሩም፡፡ አብዛኖቹ ትራስ ብቻ አድርገው ተጋድመዋል። ጓዛቸውን ወይም ሻንጣቸውን ከጎናቸው አስቀምጠዋል። ሰዎቹ ማታ ማታ ከዚህ የሚያድሩ ሲሆን ቀን ቀን ወደ ውጭ ይወጣሉ። ጥግ ላይ ቦታ አገኘሁ እና መሬት ተቀምጨ ጀርባየን ወደ ግድግዳው አስጠጋሁ። ስዎቹን ሳይ
ከጦርነቱ ለማምለጥ ያለፍኩባቸው ሰፈሮች ትዝ አሉኝ።
#ክፍል_ሀያ_ሶስት(የመጨረሻ ክፍል)
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
አስር ስዓት ሲሆን አውቶብሱ ካምቢያ ከምትባል ከተማ አደረሰን። የመጨረሻ ፌርማታው ነበር። ፍሪ ታውንን ለቀን
ከመጣን ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳፋሪዎቹ ፊት ተፈታ። ግን ብዙም አልቆየም! ድንበር ለማለፍ ክፍያ ስንጠየቅ የሁሉም ፊት መልሶ ተኮማተረ አጉረመረምን፡፡ ሁሉም ሰው ከካልሲው
ውስጥ፣ ከውስጥ ሱሪ እና ከረባት ሳይቀር የተረፈ ገንዘብ ካለ ፈለገ። ሶስት መቶ ሊዮንስ (የሴራሊዮን ገንዘብ) ነበር
የተጠየቅነው:: አንድ ሰው ከገዛ ሃገር ለቆ ለመውጣት ለምንድን ነው ሚከፍለው? አሰብኩ ግን መከራከር አልችልም:: ከፈልኩ:: የይለፍ ወረቀቱ ላይ ማህተም እንደተደረገልኝ ወዲያው ወደ ጊኒ
ደንበር ተሻገርኩ። ዋና ከተማዋ ኮናክሪ ለመድረስ ደግሞ ገና ብዙ መንገድ ይቀረኛል። ወደ ከተማው የሚወስድ አውቶብስ ለማግኘት ቶሎ ቶሎ መራመድ ጀመርኩ። ጊኒ ውስጥ የሚነገር
የትኛውንም ቋንቋ መናገር አልችልም ምን ማድረግ እንዳለብኝም አላሰብኩበትም ነበር። ትንሽ አስጨነቀኝ ግን ከሃገሬ በህይወት መውጣቴ ትልቅ ነገር ነው::
ኮናክሪ የሚሄድ አውቶብሶች የጊኒ ወታደሮች ባቆሟቸው ኬላዎች በኩል ነበር የሚቆሙት፡፡ በኬላዎቹ ተጠግተው
በፈለጉት መጠን የጊኒን ገንዘብ የሚመነዝሩ ሰዎች ነበሩ።
ወታደሮቹ ይሄን ጥቁር ገበያ የሚከላከሉ መስሎኝ ነበር ግን ግድ አይሰጣቸውም:: ገንዘቤን ቀይሬ ወደ ኬላው ተጠጋሁ። ደንበሩ ላይ ያሉ ወታደሮች ወይ እንግሊዝኛ መናገር አይችሉም ወይ
ደግሞ እንደሚችሉ ማሳወቅ አይፈልጉም:: መሳሪያቸውን ብቻ
በተጠንቀቅ ይዘዋል፡፡ ቀና ብየ ማየት አልፈለኩም። ከዚህ በፊት ወታደር እንደነበርኩ እና አሁን ግን ትቼው እሸሸሁ መሆኑን ማሳበቅ አልፈለኩም::
አውቶብሱን ለማግኘት ጥቁር ቡናማ የሆኑ የጣውላ ቤቶችን ማለፍ ነበረብኝ። ውስጥ ወታደሮች የሰዎችን ሻንጣ ይበረብራሉ።ሰዎች ደግሞ መረጃዎቻቸውን ለሃላፊዎች ያሳያሉ። የእኔ ተራ ሲደርስ ወታደሮቹ ሻንጣየን ከፍተው በውስ ጡ ያለውን ሁሉ መሬት ላይ ዘረገፉት። ብዙ እቃ ስላልነበረኝ ለመሰብሰብ እና መልሶ ለመክተት ብዙም አያስቸግርም፡፡ ሁለት ቲ ሸርት፣ ሁለት
ዉስጥ ሱሪ እና ሶስት ጥንድ ሱሪዎች ብቻ ነበሩ::
ከጣውላ ቤቱ ስወጣ መረጃዎቼን ማሳየት ነበረብኝ፡፡ ብዙ ጠረጴዛዎቹ እና ወታደሮች ደግሞ የማንጎ ዛፍ ስር ነበሩ።
መሳሪዎቻቸው ወንበራቸው ላይ ወይም የአንዳንዶቹ ጠረጴዛዎቹ ላይ ተቀምጦ ነበር፡፡ ለማን ማሳየት እንዳለብኝ
አላውቅም::
አንድ ወታደር ወደ እሱ እንደሄድ ምልክት አሳየኝ። እጁን ዘረጋ እና የይለፍ ወረቀቴን ተቀበለኝ። ወታደሩ በማይገባኝ አንድ
ቋንቋ ተናገረ።የይለፍ ወረቀቴን የደረት ኪሱ ውስጥ አስገባው እና እጁን ጠረጴዛ አድርጎ አትኩሮ ተመለከተኝ። አቀረቀርኩ
ወታደሩ አገጩን ቀና አደረገኝ፡፡ የይለፍ ወረቀቴን ከኪሱ አውጥቶ መረመረ። አይኑ ቀላ ፊቱ ላይ ፈገግታ ይታይ ነበር።
እጁን አጥፎ ተደላድሎ ተቀመጠ። ፈገግ አልኩ እሱም ሳቀ።በቋንቋው የሆነ ነገር አለና እጁን እንደገና ጠረጴዛው ላይ አደረገ።ፈገግታው እየጠፋ ሄደ፡፡ የተወሰነ ገንዘብ እጁ ላይ አስቀመጥኩ።
የይለፍ ወረቀቴን ከኪሱ አውጥቶ ሰጠኝ እና በሩ እንዳልፍ ጠቆመኝ፡፡
ብዙ አውቶብሶች ስለነበሩ ወደ ኮናክሪ ለመሄድ አውቶብስ መያዝ እንዳለብኝ አላውቅም ግራ ገባኝ፡፡ ሰዎችን ለመጠየቅ ብሞክርም ማንም ሊረዳኝ አልቻለም:: የማውቀው ፈረንሳይኛ
ቃል bonjour ቦንጁር ብቻ ነበር፡፡
ግራ ገብቶኝ ቁሜያለሁ አንድ አልፎ ሂያጅ በኪሮ ቋንቋ ሲያጉረመርም ሰማሁትና “ ጤና ይስጥልኝ” ብየ ወደ ኮናክሪ
የሚወስደው አውቶብስ የትኛው እንደሆነ ጠየቅኩት። እሱም ወደ ዛው እንደሚጓዝ ነገረኝ እና ወደ ከአፍ እስከ ገደፉ ጢም
ብሎ የሞላ አውቶብስ ውስጥ ገባን፡፡ በየ ሃምሳ ሜትሩ ወደ አስራ አምስት የሚጠጉ ኬላዎች ላይ ወታደሮች ነበሩ እና ወታደሮቹ ምህረት የለሽ ነበሩ። ወታደሮቹ መክፈል የማችሉትን እየደበደቡ
ከአውቶብሱ ያወርዷቸዋል። እኔ ግን እድለኛ ነበርኩ። ከአጠገቤ የነበረው ሰውየ ልጅ ስለመሰልኳቸው ብዙ ኬላዎችን በነፃ አልፌያለሁ። የእሱን መረጃ ያያሉ እና የሁለታችንንም እሱን
ያስከፍላሉ፡፡ ሰውየው የገባው አይመስለኝም:: ገንዘብ ጉዳዩ አይደለም ኮናክሪ መግባት ብቻ ነበር የሚፈልገው:: የመግቢያ ክፍያው ሶስት መቶ ሊዮንስ እንደሆነ ሰዎች ሲያወሩ ሰማሁ።
መቶ ሊዮንስ ብቻ ነበር የቀረኝ፡፡ ምንድን ነው ማደርገው? ብየ ማሰብ ጀመርኩ። ይሄ ሁሉ መንገድ የመጣሁት ለከንቱ ነው? ወደ ፍሪ ታውን መመለስ እንኳ ብፈልግ የምመለስበት ገንዘብ የለኝም:: አይኖቼ እንባ አቀረሩ። ተረበሽኩ ከዚህ መውጫ መንገዱ አልታይህ አለኝ፡፡ አንድ የይለፍ ወረቀቱ የተመታለት ሰው ከኬላ ወደ አውቶብስ ሲመለስ ሻንጣውን ጥሎ አየሁ። የተወሰነ ካመነታሁ በኋላ እድሉን ልጠቀምበት ወሰንኩ። ሰልፉን ትቼ ሻንጣውን ይዤ ተከልኩት:: አውቶብስ ውስጥ ገብቼ መጨረሻ ወንበር ላይ ተደብቄ ተቀመጥኩ። አውቶብሱ ቀስ ብሎ ከወጣ በኋላ ፍጥነቱን ጨመረ። በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሃገሪቱ
ገባሁ በኋላ ግን ችግር ይሆናል፡፡
አውቶብሱ ወደ ኮናክሪ ሲደርስ መጨነቅ ጀመርኩ። ከደረስኩ በኋላ ምን እንደማደርግ አላውቅም:: የሴራሊዮን አምባሳደር ስደተኞች በጊዜዊነት ግቢው ውስጥ እንደሚያሳድር ሰምቻለሁ
ግን ኢምባሲው የት እንደሆነ እንኳ አላውቅም:: ጃሎህ ከሚባል
ፉላኒ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ አርብቶ አደር ጎሳ) ጋር ነበር የተቀመጥኩት። ጃሎህ ፍሪ ታውን እንደኖረ ነገረኝ፡፡ ስለ ጦርነቱ እና በሃገሪቱ ላይ ስላስከተለው ጉዳት አወራን። በኋላ ስልክ ቁጥሩን ሰጠኝ እና ከተማዋን ስንቀሳቀስ እርዳታ ካስፈለገኝ እንድደውልለት ነገረኝ። ማደሪያ እንደሌለኝ ልነግረው ፈለኩ ግን
ቀድሞኝ ወረደ። አብሮኝ የመጣውን ሴራ ሊዮናዊ ፈለኩ ግን ላገኘው አልቻልኩም። ከደቂቃዎች በኋላ አውቶብሱ ግዙፍ
መናሃሪያ ውስጥ ገባ። ወጥቼ ሁሉም ሲሄድ ተመለከትኩ። ተነፈስኩ እና እጆቼ ራሴ ላይ ጭኜ ወደ አግድም ወንበር ሂጄ
ተቀመጥኩ። ፊቴን በእጆቼ ሸፍኜ “ለሊቱን ሙሉ ከዚህ መቀመጥ አልችልም” ብየ ለራሴ አጉረመረምኩ።
ብዙ ታክሲዎች ነበሩ እና አውቶብሱ መናሃሪያ የደረሱ ሰዎች ሁሉ ይዟቸዎል። እኔም ብቸኛ ሚሄድበት የጠፋው እንግዳ
መስየ መታየት ስላልፈለኩ አንዱ
ታክሲ ውስጥ ገባሁ። ሹፌሩ በፈረንሳይኛ ሲናገር ወዴት እንደምሄድ እየጠቀኝ እንደሆነ ገመትኩ። ሴራ ሊዮን ቆንስላ አ ኢምባሲ” ብየ ነገርኩት።በመስኮት ስመለከት የመብራት ምሶሶዎች ላይ የመንገድ መብራቶቹ ተንበርግገው
ተንጠልጥለዋል። ብርሃናቸው ከጨረቃ ብርሃን ሳይበልጥ አይቀርም። ታክሲው ኢምባሲው ፊት ለፊት ቆመ እና የምፈልገው ቦታ ይዞኝ እንደመጣ
ለማረጋገጥ ወደ አረንጓዴ፣ ነጭ እና ሰማያዊ ባንዴራ ጠቆመኝ፡፡ራሴን በማወዛወዝ ትክክል እንደሆነ ከገለፅኩለት በኋላ ከታክሲው ወረድኩ
በኤንባሲው በር ላይ ጠባቂዎቹ በኪሪዎ የይለፍ ወረቀቴን እንዳሳይ ጠየቁኝ፡፡ አሳየኋቸው እና ወደ ግቢው እንድገባ ፈቀዱልኝ::
በግቢው ውስጥ ከሃምሳ በላይ ሰዎች ሲኖሩ እንደእኔ መጠጊያ ያጡ ሳይሆኑ አይቀሩም፡፡ አብዛኖቹ ትራስ ብቻ አድርገው ተጋድመዋል። ጓዛቸውን ወይም ሻንጣቸውን ከጎናቸው አስቀምጠዋል። ሰዎቹ ማታ ማታ ከዚህ የሚያድሩ ሲሆን ቀን ቀን ወደ ውጭ ይወጣሉ። ጥግ ላይ ቦታ አገኘሁ እና መሬት ተቀምጨ ጀርባየን ወደ ግድግዳው አስጠጋሁ። ስዎቹን ሳይ
ከጦርነቱ ለማምለጥ ያለፍኩባቸው ሰፈሮች ትዝ አሉኝ።
ነገ ምን አይነት ችግር ይገጥመኝ ይሆን ብየ ፈርቻለሁ ተጨንቂያለሁ። ቢሆንም ግን ከፍሪ ታውን በመውጣቴ እና ድጋሚ ወታደር ከመሆን ስላመለጥኩ ደስ ብሎኛል። በዚህ ተፅናናሁ፤ የቀረኝን ሩዝ ከሻንጣየ በማውጣት መብላት ጀመርኩ። ከ እኔ ትንሽ ራቅ ብሎ አንዲት ሴት ከሰባት አመት የማይበልጡ ወንድ እና ሴት
ልጆቿ ጋር ተቀመጣለች፡፡ ሌሎች ሰዎችን ላለመረበሽ ቀስ ብላ ለልጆቿ ተረት ታንሾካሽካለች። እጆቿን ስታንቀሳቅስ ልጅ ሁኜ ብዙ ጊዜ የሰማሁት አንድ ተረት ትዝ አለኝ።
ለሊት ነበር እና እሳት ዳር ቁጭ ብለን እጆቻችንን ወደ ነበልባሉ እያስጠጋን እየሞቅን ተረት እናዳምጣለን። ጨረቃ እና
ኮኮቦች ሲርቁ እናያለን፡፡ ቀይ ፍም ፊታችንን ሲያበራ ጭሱ ወደ
ሰማይ ተግተልትሎ ይወጣ ነበር። ከ ጓደኞቼ የአንዱ አያት የሆነው አባ ሲሳይ በዛ ምሽት ብዙ ተረቶችን ነግሮናል። ግን
የመጨረሻ ተረቱን ሲነግረን ደጋግሞ “ ይሄ በጣም ጠቃሚ ተረት ነው” ይል ነበር። ጎሮሮውን ጠራረገና ጀመረ።
“ዝንጀሮ ለመግደል ወደ ጫካ የወረደ አዳኝ ነበር። ዘወር ዘወር ብሎ ሲቃኝ የዛፍ ቅርንጫፍ ላይ ተደላድሎ የተቀመጠ ዝንጀሮ አየ።ዝንጀሮው የአዳኙ ኮቴ በደረቅ ቅጠሎች ሲያልፍ ድምፅ ቢያሰማም እስኪጠጋው ድረስ ብዙም ትኩረት አልሰጠውም::አዳኙ ዝንጀሮ በደንብ ወደ ሚታይበት ቦታ ሲደርስ መሳሪያውን
አዘጋጅቶ አነጣጠረ፡፡ ምላጩን ከመሳቡ በፊት ግን ዝንጀሮው እንዲህ ሲል ተናገረ:
ከተኮስክብኝ እናትህ ትሞታለች ፤ ካልተኮስክ ደግሞ አባትህ ይሞታል።” ዝንጀሮው ተስተካክሎ ተቀመጠ እና ምግቡን ማለመጥ፣ እራሱን ማከክ እና ሆዱን ማሻሸት ቀጠለ።
አዳኙ አንተ ብትሆን ምን ታደርግ ነበር?”
እኔ በአደኩበት መንደር ይሄ ተረት ለወጣቶች በአመት አንዴ ይነገራል። ተረት ተናጋሪው ሽማግሌ ተረቱን ከተናገረ በኋላ
ይህን ለመመለስ የሚያስቸግር ጥያቄ በህፃናቱ ወላጆች ፊት ነበር የሚያቀርበው። ሁሉም ልጆች አንድ በአንድ መልሳቸውን እንዲያቀረቡ ይጠየቃሉ። ወላጆቻቸው ከጎናቸው ስለሚሆኑ አንድም ልጅ መልሶ አያውቅም:: ተረት ተናጋሪውም መልሱን
ተናግሮ አያውቅም:: በእንደዚህ አይነት ስብስብ መልስ እንድሰጥ ስጠየቅ ሁሌም መልሴ ላስብበት ነበር። አጥጋቢ መልስ
አልነበረም::በእነዚህ ስብስቦች እኔ እና ጓደኞቼ ወላጆቻችንን ከሞት የሚያስቀር መልስ ለማግኘት የተለያዩ መልሶችን እናስብ ነበር።ግን አንድም አልነበረም:: ዝንጀሮ ከተውነው አንድ ሰው
ይሞታል፤ ዝንጀሮን ከገደልነው ደግሞ ሌላ ሰው ይሞታል።ያ ምሽት ግን በአንድ መልስ ተስማማን ግን ተቀባይነት
አላገኘም:: አባ ሲሳይን አዳኙ እኛ ከሆን ዝንጀሮዎች ለማደን አንወጣም ብለን ነገርናቸው:: “ለአደን የሚሆኑ ሌሎች እንስሳት ብለን ነገርናቸው።
ለምሳሌ አጋዘን “በፍፁም ይሄ ተቀባይነት የሌለው መልስ ነው” አሉ:: መሳሪያውን አነጣጥሮ ውሳኔ ስለቀረው ሰው ነው የምናወራው” አሉ የወይን እቃቸውን ከፍተው ከመጠጣታቸው በፊት ፈገግ
አሉ።
የሰባት ዓመት ልጅ እያለሁ ለዚህ ጥያቄ መልስ ነበረኝ። እናቴ ምን ይሰማታል በሚል ግን ለማንም ተናግሬው አላውቅም:: ለራሴ የደመደምኩት ግን አዳኙ ብሆን ዝንጀሮውን እገድለው እና
ሌሎች አዳኞች በእንደዚህ አይነት ቅርቃር ውስጥ እንዳይገቡ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ እታደጋቸው ነበር።
✨ተፈፀመ ✨
ውድ #የአትሮኖስ ቻናል ተከታታዬቼ #የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ ይህን ይመስላል ብዙዎቻቹ አስተያየታችሁን በየክፍሉ ሰታችሁኛል የተመቸውም ያልተመቸውም አለ በኔ በኩል ያለኝን አስተያየት በየግል ስልክ ነበር አሁን ላይ ጠቅለል ሳደርገው ፅሁፉ በጣም የተመቸኝ እውነተኛ ታሪክ ነው ለዛም ነው ለናተ ያቀረብኩት #ያልተመቸኝ ነገር ከናንተ የመጣ ነገር ባይኖርም #ተርጓሚው ላይ ቅሬታ አለኝ ሲተረጎም የቃላት አጠቃቀም ላይ ለኛ ትርጉሙን የሚያዛባ አንዳንዴ ከሌላ ቋንቋ ወደእኛ ቀጥታ ሲተሮገም ስሜት የማይሰጡ አረፍተ ነገሮች አሉ እነሱ በዚ ታሪክ ላይ ብዙ አጋጥመውኛል አንዳንዴ የታሪክ ፍሰቱም መዘባረቅ ነበረበት እኔም ባለችኝ አቅም ለማስተካከል ሞክሪያለው...አስቲ እናንተም በታሪኩ ላይ እንዲሁም ከላይ ባነሳሁት ላይ ያላችሁን አስተያየት አድርሱኝ።
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
ልጆቿ ጋር ተቀመጣለች፡፡ ሌሎች ሰዎችን ላለመረበሽ ቀስ ብላ ለልጆቿ ተረት ታንሾካሽካለች። እጆቿን ስታንቀሳቅስ ልጅ ሁኜ ብዙ ጊዜ የሰማሁት አንድ ተረት ትዝ አለኝ።
ለሊት ነበር እና እሳት ዳር ቁጭ ብለን እጆቻችንን ወደ ነበልባሉ እያስጠጋን እየሞቅን ተረት እናዳምጣለን። ጨረቃ እና
ኮኮቦች ሲርቁ እናያለን፡፡ ቀይ ፍም ፊታችንን ሲያበራ ጭሱ ወደ
ሰማይ ተግተልትሎ ይወጣ ነበር። ከ ጓደኞቼ የአንዱ አያት የሆነው አባ ሲሳይ በዛ ምሽት ብዙ ተረቶችን ነግሮናል። ግን
የመጨረሻ ተረቱን ሲነግረን ደጋግሞ “ ይሄ በጣም ጠቃሚ ተረት ነው” ይል ነበር። ጎሮሮውን ጠራረገና ጀመረ።
“ዝንጀሮ ለመግደል ወደ ጫካ የወረደ አዳኝ ነበር። ዘወር ዘወር ብሎ ሲቃኝ የዛፍ ቅርንጫፍ ላይ ተደላድሎ የተቀመጠ ዝንጀሮ አየ።ዝንጀሮው የአዳኙ ኮቴ በደረቅ ቅጠሎች ሲያልፍ ድምፅ ቢያሰማም እስኪጠጋው ድረስ ብዙም ትኩረት አልሰጠውም::አዳኙ ዝንጀሮ በደንብ ወደ ሚታይበት ቦታ ሲደርስ መሳሪያውን
አዘጋጅቶ አነጣጠረ፡፡ ምላጩን ከመሳቡ በፊት ግን ዝንጀሮው እንዲህ ሲል ተናገረ:
ከተኮስክብኝ እናትህ ትሞታለች ፤ ካልተኮስክ ደግሞ አባትህ ይሞታል።” ዝንጀሮው ተስተካክሎ ተቀመጠ እና ምግቡን ማለመጥ፣ እራሱን ማከክ እና ሆዱን ማሻሸት ቀጠለ።
አዳኙ አንተ ብትሆን ምን ታደርግ ነበር?”
እኔ በአደኩበት መንደር ይሄ ተረት ለወጣቶች በአመት አንዴ ይነገራል። ተረት ተናጋሪው ሽማግሌ ተረቱን ከተናገረ በኋላ
ይህን ለመመለስ የሚያስቸግር ጥያቄ በህፃናቱ ወላጆች ፊት ነበር የሚያቀርበው። ሁሉም ልጆች አንድ በአንድ መልሳቸውን እንዲያቀረቡ ይጠየቃሉ። ወላጆቻቸው ከጎናቸው ስለሚሆኑ አንድም ልጅ መልሶ አያውቅም:: ተረት ተናጋሪውም መልሱን
ተናግሮ አያውቅም:: በእንደዚህ አይነት ስብስብ መልስ እንድሰጥ ስጠየቅ ሁሌም መልሴ ላስብበት ነበር። አጥጋቢ መልስ
አልነበረም::በእነዚህ ስብስቦች እኔ እና ጓደኞቼ ወላጆቻችንን ከሞት የሚያስቀር መልስ ለማግኘት የተለያዩ መልሶችን እናስብ ነበር።ግን አንድም አልነበረም:: ዝንጀሮ ከተውነው አንድ ሰው
ይሞታል፤ ዝንጀሮን ከገደልነው ደግሞ ሌላ ሰው ይሞታል።ያ ምሽት ግን በአንድ መልስ ተስማማን ግን ተቀባይነት
አላገኘም:: አባ ሲሳይን አዳኙ እኛ ከሆን ዝንጀሮዎች ለማደን አንወጣም ብለን ነገርናቸው:: “ለአደን የሚሆኑ ሌሎች እንስሳት ብለን ነገርናቸው።
ለምሳሌ አጋዘን “በፍፁም ይሄ ተቀባይነት የሌለው መልስ ነው” አሉ:: መሳሪያውን አነጣጥሮ ውሳኔ ስለቀረው ሰው ነው የምናወራው” አሉ የወይን እቃቸውን ከፍተው ከመጠጣታቸው በፊት ፈገግ
አሉ።
የሰባት ዓመት ልጅ እያለሁ ለዚህ ጥያቄ መልስ ነበረኝ። እናቴ ምን ይሰማታል በሚል ግን ለማንም ተናግሬው አላውቅም:: ለራሴ የደመደምኩት ግን አዳኙ ብሆን ዝንጀሮውን እገድለው እና
ሌሎች አዳኞች በእንደዚህ አይነት ቅርቃር ውስጥ እንዳይገቡ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ እታደጋቸው ነበር።
✨ተፈፀመ ✨
ውድ #የአትሮኖስ ቻናል ተከታታዬቼ #የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ ይህን ይመስላል ብዙዎቻቹ አስተያየታችሁን በየክፍሉ ሰታችሁኛል የተመቸውም ያልተመቸውም አለ በኔ በኩል ያለኝን አስተያየት በየግል ስልክ ነበር አሁን ላይ ጠቅለል ሳደርገው ፅሁፉ በጣም የተመቸኝ እውነተኛ ታሪክ ነው ለዛም ነው ለናተ ያቀረብኩት #ያልተመቸኝ ነገር ከናንተ የመጣ ነገር ባይኖርም #ተርጓሚው ላይ ቅሬታ አለኝ ሲተረጎም የቃላት አጠቃቀም ላይ ለኛ ትርጉሙን የሚያዛባ አንዳንዴ ከሌላ ቋንቋ ወደእኛ ቀጥታ ሲተሮገም ስሜት የማይሰጡ አረፍተ ነገሮች አሉ እነሱ በዚ ታሪክ ላይ ብዙ አጋጥመውኛል አንዳንዴ የታሪክ ፍሰቱም መዘባረቅ ነበረበት እኔም ባለችኝ አቅም ለማስተካከል ሞክሪያለው...አስቲ እናንተም በታሪኩ ላይ እንዲሁም ከላይ ባነሳሁት ላይ ያላችሁን አስተያየት አድርሱኝ።
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#ባርቾ
:
:
#በሕይወት_እምሻው
በ12 ዓመቴ...ስቅስቅ ብዬ» አልቅሼ ስጨርስ ፣ በለቅሶ ይባስ የጠቋቆረ ጥቁር ፊቴን በቀኝ እጄ አይበሉባ እያሻሸሁ ወደ ቤት ስገባ ፣ እማዬን በር ላይ አገኘኋት: :
“ምን፣ ሆንሽ ባርቾ? ... ምነው?”
“ምንም! ” አልኳት ፡ : የደረሰብኝ ነገር ደግሞ ማውራቱ ይበልጥ የሚ ያስለቅሰኝ መስኰ ስለተሰማኝ : :
“ምን... ምንም ትይኛለሽ? ስታለቅሺ አልነበርም?” እማማ ተቆጣች ፡ :
“ትምህርት፥ ቤት ...” አልኩ አልቅሼ የጨረስኩት የመሰኝ እንባዬ እንደ
አዲስ ዐይኔ ውስጥ ሲሞላ እየተሰማኝ ፡ :
“ምን ሆንሽ .. ? ከማን ጋር ተጣካሽ?”
“አማርኛ አስተማሪ ... ቲቸር ስንሻው ...”
“ገረፈሽ ...? ጎሽ! የቤት ሥራ ሳትሰሪ ሄደሽ ገርፎሽ ነው አይደለም?
ደግ አደረገ፡”
“አይደለም አረ... እኔ የቤት ስራዬን ሰርቻለሁ ...”
አህስ... ስትርብሺ ዐይቶሽ ነው አይደለም? እያስተማረ ስቶረብሺ? ነይ
እንዲውም እኔም እጨምርልሻለሁ!” አለች እማዬ ቱግ እያለች ፡ :
አሁን ቀበቶ ፍለጋ ወደ ጎዳ ስትገባ ዐየሁና ጮክ ብዬ፣ አይደለም
እማዬ... እግዚአብሔርን፣... የገና ድራማ አትሠሪም ብሎኝ ነው አልኳት ፣ ስር ስሯ እየተከተልኳት።
ቀበቶውን፣ መፈለጓን ትታ ዞር ብላ አየችኝና ፣ “የገና ምን... ምን አትይም
ብሎኝ ነው? ” ብላ ጠየቀችኝ : :
“የገና ድራማ አትሰሪም ብሎኝ ነው እማዬ” አልኳት : :
ምንድነው ደግሞ የገና ድራማ?”
ባለፈው... ለገና በዓል የክርስቶስ፣ መወለድ በድራማ ትሰራላኝሁ ተብለናል ብዬ ከብሩኬ ጋር ሳጠና አልነበረም እማዬ?”
"ያ ... ሁሉንም በቃሌ መያዝ አለብኝ ስትይው የነበረው ነው እሱ? ”
“አዎ... እማዬ: :
“ታዲያ ፈቅዶልሽ አይደለም እንዴ አጥኚ የተባልሽው?”
“አዎ... እማዬ” አልኳት ፣ እንባዬ ሲመለስ እየተሰማኝ : :
“እና ታዲያ ምንድነው አትሰሪም ያለሽ አሁን?”
“አትሰሪም አትሰሪም አይደለም እኮ ያለኝ ” አልኩ ለቅሶዬን ጀምሬ : :
“ልጅቷ ያማታል እንዴ ...? ምንድነው የምትቀባጥሪው? አትሰሪም አለኝ
አላልሽም አሁን?” አለች እማዬ ቁጣዋ ተመልሶ : :
እኔ የፈለኩት እመቤቴ ማርያምን፣ ሆኜ መስራት ነበር ፡ : ሳጠና የነበረው እኮ የእመቤቴ ማርያምን፣ ነው ... እሱ ግን...
“እሱ ግን…? ምን አለሽ ታድያ ? ”
“እሱ ግን ቲቸሮች ሁኑ ተነጋግረንበት ነበር : :አንቺ በደንብ ብታጠኚውም ጥቁር ስለሆንሽ ማርያምን፣ ሆነሽ መስራት አትችይም : :
ሩት ናት ማርያምን የምትሆነው አለ” ብዬ ለቅሶዬን በነጻነት አድምቄ ጀመርኩት ፡ :
እማዬ ካሁን አሁን ተሰምቷት መጥታ እቅፍ ታደርገኝና ፣ እምባዬን ታብሰውና ፣
የሚይረባ! የኔ ልጅ ናት ማርያምን፤ ሆና የማትሰራው?
ነገውኑ ከአባትሽ ጋር ሄደን ለዲሪክተሩ ነገርነ ነው የምናስባርረው... አይዞሽ
ልጄ” ትለኛለች ብዬ ስጠብቅ ፣
“እውነቱን ነዋ! እስቲ የእመቤቴን ምስል
ዕይው! ምኗ ነው ከቶ አንቺን የሚመስል? አስተማሪሽ የሚልሽን፣ ስሚ ! ልክ ነው!” ብላ፤ ወደ ኩሽና ገባች: :
የዛን ዕለት እመቤቴ ማርያምን፣ ሆኜ ለመጫወት የነበረኝን ጉጉት ባጭር
የቀጩትን “ቲቸሮቼን፡” ፣ ድራማውን፤ በማጥናት ከእሷ 0ሥር እጅ
ብሻልም ቀይና ሰልካካ ስለሆነች ብቻ ማርያምን ሁኚ ተብላ የተመረጠችውን፣
ሩትን፣ ካልጠፋ ቕላት ጥቁር አድርጎ የፈጠረኝን፣ ፈጣሪንም በአንድነት
አማረርኩ ፡ :
ምሽት ላይ ፤ እኔ ፣ ትልቋ እና ቀይዋ እህቴ ፣ ቀዩ ወንድሜ ፣ ጠይሙ አባቴና በጣም ቀይዋ እናቴ ተሰብስበን ቴሌቪዥን እናያለን። ለነገሩ ቴሌቪዥኑን የሚያዩት እነሱ እንጂ እኔ የማየው እነሱንና ቅላታቸውን፣ ነው : : እያየኋቸው እናደሚከተለው አሰባለሁ ፣
...እስቲ አሁን በእመቤቴ ፣ እኔ ከየት መጥቼ ጠቆርኩ? አባቴ ጠይም
ነው ፤ እናቴ በጣም ቀይ ናት ፡ : ሁለቱ ሲቀላቀሉ እንደ እህቴ ስህንና እንደ ወንድሜ ብሩክ ቀይ ሰው ባይፈጥሩ እንኳን እንደኔ ጠቋራ ሰው መፍጠር ነበረባቸው? የእህቴስ ይሁን፡ : ሴት ናት : : በዛ ላይ ታላቄ ናት ፡ ይሁንላት ትቅላ ፤ ግን አሁን እኔ ከምጠቁር ወንድሜ ቢጠቁር ምናለበት እስቲ…? ደግሞ እኮ እኔ ብቻ አይደለሁም : :ሁሉም ሰው የሚለው ነገር
ነው : : እማዬ ሁል ጊዜ ብሩክንና እኔን ይዛን ወጣ ስትል ፣
አይ ወይዘሮ ኤልሳቤጥ! ሴቷን ልጅ አጥቁረሽ ቅላትሽን፣ ሁኩ ወንዱ ልጅ
ላይ አባከንሽው! መልክ ለወንድ ልጅ ምን ያደርጋል አሁን? አሄሄ!” ይላሉ
እኔ እንዲህና እንዲያ ሳስብ ቴሌቪዢኑ ላይ ጓድ መንግስቱ ሐይለማርያም
የዛንቢያውን፣ ፕሬዝዳንት ኬኔት ካውንዳን፤ ሲቀበሉ የሚያሳይ ምስል መጣ ፡ :
መንግስቱ ኃይለማርያም ቴሌቪዥን ላይ ፣ በመጣ ቁጥር የሚቀልዱብኝ ቀልድ
እስኪጅምር ጠበቅኩ ፤ “መንጌ እኮ አባትሽ ነው” ሊሉኝ ነው ።ጠበቅኳቸው።
እህቴ ቀደመችና ፣ ይሄውልሽ ሜሮን አጎትሽ አባትሽን ለመጠይቅ አዲስ
አበባ መጣ!” ሁኩም ሣቁ።
እኔ ግን ነጭ መሃረብ እያርገበገበ ከአውሮፕላን የሚወርደውን፣ “አጎቴ፣” ኬኔት ካውንዳን እየያየሁ እግዚአብሔር ከነነጭ መሃረቡ በአውሎ ንፋስ ጥ...ር...ግ አድርጎ ወደ መጣበት ቢመልሰው እቸተመኘሁ ከእንባዬ ተናነቅሁ : : ደግሞ በዚህ ጥቁርቱ ላይ ነጭ መዓርብ የሚይዘው አማረብኝ ብሎ ነው? ...ወይስ ከሩቅ እንዲታይ? አንጀቴን
አሳረረው : :
“ዕያት ... ዕያት ... በሸቀች! በሸቀች” ይላሉ እየተቀባበሉ።
“አትናደጂ! ይባስ ያጠቁርሻል” አለ
ብሩክ ፣ አጠገቤ መጥቶ እየሣቅ ።
የማርያም አጃቢ ሆኜ የገናውን ድራማ በሰራሁ በሁለት ሳምንቴ አስራ ሶስት
ዓመት ሞላኝ : : ሁሌም ለልደቴ እንደምናደርገው ድፎ ዳቦ ዳቦና
ሻማ ፣ ከተወሰኑ የለስላሳ ጠርሙሶች ጋር ይዘን የልደት ፎቶ ልንነሳ ከእማዬ ፣ አባዬ ፣ ስህንና ብሩክ ጋር አስረስ ፎቶ ቤት ሄድን ጋሽ አስርስ ይወደኛል ፤ “ኮረሪማ!” ይለኛል ገና ከሩቅ ሲያየኝ : :
“ኮረሪማ አረጀሽ በቃ! ትልቅ ሰው ... ትልቅ ኮረሪማ” አለኝ፤ ገና ከመግባታችን። ሣቅኹ ።መጣና እቅፍ አድርጎ ከሳመኝ በኋላ ለፎቶው መዘጋጀት ጀመርኩ።
ጋሽ አስርስ ሁሉን ነገር አሰናድቶ ለማንፀሳት ሲያነጣጥር አባቴ ጮክ አለና
“አስረስ ፣ ይህን መጋረጃ ቀይረው እንጂ ” አለው።
“የቱን? ” አለ ጋሽ አስረስ ፣ ካሜራው፣ ከእነ አንትገ ማንጠልጠያው፥
ከፊቱ ወደ ደረቱ፥ እየመለሰ ።
“ከኋላዋ ያለውን ጥቁር መጋርጃ!” አለ አባቴ : :
ኋላ ላይ ሻማው ፣ ጥርሷና ሚሪንዳው ብቻ ይወጣልህና ጉድ እንዳትሆን!” ሲለው ፤ ይወደኝ የመሰለኝ፤ ጋሽ አስረስ ከቀያዮቹ ቤተሰቦቼ ጋር ተደርቦ ሲስቅ ጠላሁት : :
።።።።።
በሃያ ሁለት ዓመቴ...
እንዲህ እንዲህ ሲብስ ሲብስ ፣ “ባርቾ እኮ ጭንቅላት ባይኖራት ጉዷ ነበር!
“አንቺ፤ ግን ሀበሻ ነሽ? ጋና እኮ ነው የምትመስይው!”
.
:
ሲሻል ደግሞ ፣ ብትቀላ ቆንጆ ነበረች፡ : እየተባልኩ፣ በቀያይ ቤተሰቦቼና ዘመዶቼ እየተቀለደብኝ ኖርኩ ፡ : በሃያ ሁለት ዓመቴም የትወና ጥበብ ተምሬ ጨርስኩና የጊዜውን የፊልም ሥራ በርከት ለመቋደስ ብዙ ቦታ ተመዝግቤ መፈተን ጀመርኩ። ከኮሌጅ ሰቅዬ
ነበር የተመረቕኩት ፣ ግን ደህና የፊልምም የቲያትርም የትወና ሥራ ማግኘት አልቻልኩም : : “በጣም አሪፍ ነው ፡ ፡ እናደውልልሻለን። ይሉኝና አይደውሉም።
ሌሎቹ ደግሞ ፣ ለትወና ሥራ አመልክቼ ፣ “ፐ! አንቺ በጣም ጎበዝ ተዋናይ ነሽ... ለምን፣ ማስተማር አትሞክሪም? ” ይሉኝና ያሰናብቱኛል። ነገሩ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ግልጥልጥ ያለልኝ ፤ ታሪኩንና ስክሪፕቱ
:
:
#በሕይወት_እምሻው
በ12 ዓመቴ...ስቅስቅ ብዬ» አልቅሼ ስጨርስ ፣ በለቅሶ ይባስ የጠቋቆረ ጥቁር ፊቴን በቀኝ እጄ አይበሉባ እያሻሸሁ ወደ ቤት ስገባ ፣ እማዬን በር ላይ አገኘኋት: :
“ምን፣ ሆንሽ ባርቾ? ... ምነው?”
“ምንም! ” አልኳት ፡ : የደረሰብኝ ነገር ደግሞ ማውራቱ ይበልጥ የሚ ያስለቅሰኝ መስኰ ስለተሰማኝ : :
“ምን... ምንም ትይኛለሽ? ስታለቅሺ አልነበርም?” እማማ ተቆጣች ፡ :
“ትምህርት፥ ቤት ...” አልኩ አልቅሼ የጨረስኩት የመሰኝ እንባዬ እንደ
አዲስ ዐይኔ ውስጥ ሲሞላ እየተሰማኝ ፡ :
“ምን ሆንሽ .. ? ከማን ጋር ተጣካሽ?”
“አማርኛ አስተማሪ ... ቲቸር ስንሻው ...”
“ገረፈሽ ...? ጎሽ! የቤት ሥራ ሳትሰሪ ሄደሽ ገርፎሽ ነው አይደለም?
ደግ አደረገ፡”
“አይደለም አረ... እኔ የቤት ስራዬን ሰርቻለሁ ...”
አህስ... ስትርብሺ ዐይቶሽ ነው አይደለም? እያስተማረ ስቶረብሺ? ነይ
እንዲውም እኔም እጨምርልሻለሁ!” አለች እማዬ ቱግ እያለች ፡ :
አሁን ቀበቶ ፍለጋ ወደ ጎዳ ስትገባ ዐየሁና ጮክ ብዬ፣ አይደለም
እማዬ... እግዚአብሔርን፣... የገና ድራማ አትሠሪም ብሎኝ ነው አልኳት ፣ ስር ስሯ እየተከተልኳት።
ቀበቶውን፣ መፈለጓን ትታ ዞር ብላ አየችኝና ፣ “የገና ምን... ምን አትይም
ብሎኝ ነው? ” ብላ ጠየቀችኝ : :
“የገና ድራማ አትሰሪም ብሎኝ ነው እማዬ” አልኳት : :
ምንድነው ደግሞ የገና ድራማ?”
ባለፈው... ለገና በዓል የክርስቶስ፣ መወለድ በድራማ ትሰራላኝሁ ተብለናል ብዬ ከብሩኬ ጋር ሳጠና አልነበረም እማዬ?”
"ያ ... ሁሉንም በቃሌ መያዝ አለብኝ ስትይው የነበረው ነው እሱ? ”
“አዎ... እማዬ: :
“ታዲያ ፈቅዶልሽ አይደለም እንዴ አጥኚ የተባልሽው?”
“አዎ... እማዬ” አልኳት ፣ እንባዬ ሲመለስ እየተሰማኝ : :
“እና ታዲያ ምንድነው አትሰሪም ያለሽ አሁን?”
“አትሰሪም አትሰሪም አይደለም እኮ ያለኝ ” አልኩ ለቅሶዬን ጀምሬ : :
“ልጅቷ ያማታል እንዴ ...? ምንድነው የምትቀባጥሪው? አትሰሪም አለኝ
አላልሽም አሁን?” አለች እማዬ ቁጣዋ ተመልሶ : :
እኔ የፈለኩት እመቤቴ ማርያምን፣ ሆኜ መስራት ነበር ፡ : ሳጠና የነበረው እኮ የእመቤቴ ማርያምን፣ ነው ... እሱ ግን...
“እሱ ግን…? ምን አለሽ ታድያ ? ”
“እሱ ግን ቲቸሮች ሁኑ ተነጋግረንበት ነበር : :አንቺ በደንብ ብታጠኚውም ጥቁር ስለሆንሽ ማርያምን፣ ሆነሽ መስራት አትችይም : :
ሩት ናት ማርያምን የምትሆነው አለ” ብዬ ለቅሶዬን በነጻነት አድምቄ ጀመርኩት ፡ :
እማዬ ካሁን አሁን ተሰምቷት መጥታ እቅፍ ታደርገኝና ፣ እምባዬን ታብሰውና ፣
የሚይረባ! የኔ ልጅ ናት ማርያምን፤ ሆና የማትሰራው?
ነገውኑ ከአባትሽ ጋር ሄደን ለዲሪክተሩ ነገርነ ነው የምናስባርረው... አይዞሽ
ልጄ” ትለኛለች ብዬ ስጠብቅ ፣
“እውነቱን ነዋ! እስቲ የእመቤቴን ምስል
ዕይው! ምኗ ነው ከቶ አንቺን የሚመስል? አስተማሪሽ የሚልሽን፣ ስሚ ! ልክ ነው!” ብላ፤ ወደ ኩሽና ገባች: :
የዛን ዕለት እመቤቴ ማርያምን፣ ሆኜ ለመጫወት የነበረኝን ጉጉት ባጭር
የቀጩትን “ቲቸሮቼን፡” ፣ ድራማውን፤ በማጥናት ከእሷ 0ሥር እጅ
ብሻልም ቀይና ሰልካካ ስለሆነች ብቻ ማርያምን ሁኚ ተብላ የተመረጠችውን፣
ሩትን፣ ካልጠፋ ቕላት ጥቁር አድርጎ የፈጠረኝን፣ ፈጣሪንም በአንድነት
አማረርኩ ፡ :
ምሽት ላይ ፤ እኔ ፣ ትልቋ እና ቀይዋ እህቴ ፣ ቀዩ ወንድሜ ፣ ጠይሙ አባቴና በጣም ቀይዋ እናቴ ተሰብስበን ቴሌቪዥን እናያለን። ለነገሩ ቴሌቪዥኑን የሚያዩት እነሱ እንጂ እኔ የማየው እነሱንና ቅላታቸውን፣ ነው : : እያየኋቸው እናደሚከተለው አሰባለሁ ፣
...እስቲ አሁን በእመቤቴ ፣ እኔ ከየት መጥቼ ጠቆርኩ? አባቴ ጠይም
ነው ፤ እናቴ በጣም ቀይ ናት ፡ : ሁለቱ ሲቀላቀሉ እንደ እህቴ ስህንና እንደ ወንድሜ ብሩክ ቀይ ሰው ባይፈጥሩ እንኳን እንደኔ ጠቋራ ሰው መፍጠር ነበረባቸው? የእህቴስ ይሁን፡ : ሴት ናት : : በዛ ላይ ታላቄ ናት ፡ ይሁንላት ትቅላ ፤ ግን አሁን እኔ ከምጠቁር ወንድሜ ቢጠቁር ምናለበት እስቲ…? ደግሞ እኮ እኔ ብቻ አይደለሁም : :ሁሉም ሰው የሚለው ነገር
ነው : : እማዬ ሁል ጊዜ ብሩክንና እኔን ይዛን ወጣ ስትል ፣
አይ ወይዘሮ ኤልሳቤጥ! ሴቷን ልጅ አጥቁረሽ ቅላትሽን፣ ሁኩ ወንዱ ልጅ
ላይ አባከንሽው! መልክ ለወንድ ልጅ ምን ያደርጋል አሁን? አሄሄ!” ይላሉ
እኔ እንዲህና እንዲያ ሳስብ ቴሌቪዢኑ ላይ ጓድ መንግስቱ ሐይለማርያም
የዛንቢያውን፣ ፕሬዝዳንት ኬኔት ካውንዳን፤ ሲቀበሉ የሚያሳይ ምስል መጣ ፡ :
መንግስቱ ኃይለማርያም ቴሌቪዥን ላይ ፣ በመጣ ቁጥር የሚቀልዱብኝ ቀልድ
እስኪጅምር ጠበቅኩ ፤ “መንጌ እኮ አባትሽ ነው” ሊሉኝ ነው ።ጠበቅኳቸው።
እህቴ ቀደመችና ፣ ይሄውልሽ ሜሮን አጎትሽ አባትሽን ለመጠይቅ አዲስ
አበባ መጣ!” ሁኩም ሣቁ።
እኔ ግን ነጭ መሃረብ እያርገበገበ ከአውሮፕላን የሚወርደውን፣ “አጎቴ፣” ኬኔት ካውንዳን እየያየሁ እግዚአብሔር ከነነጭ መሃረቡ በአውሎ ንፋስ ጥ...ር...ግ አድርጎ ወደ መጣበት ቢመልሰው እቸተመኘሁ ከእንባዬ ተናነቅሁ : : ደግሞ በዚህ ጥቁርቱ ላይ ነጭ መዓርብ የሚይዘው አማረብኝ ብሎ ነው? ...ወይስ ከሩቅ እንዲታይ? አንጀቴን
አሳረረው : :
“ዕያት ... ዕያት ... በሸቀች! በሸቀች” ይላሉ እየተቀባበሉ።
“አትናደጂ! ይባስ ያጠቁርሻል” አለ
ብሩክ ፣ አጠገቤ መጥቶ እየሣቅ ።
የማርያም አጃቢ ሆኜ የገናውን ድራማ በሰራሁ በሁለት ሳምንቴ አስራ ሶስት
ዓመት ሞላኝ : : ሁሌም ለልደቴ እንደምናደርገው ድፎ ዳቦ ዳቦና
ሻማ ፣ ከተወሰኑ የለስላሳ ጠርሙሶች ጋር ይዘን የልደት ፎቶ ልንነሳ ከእማዬ ፣ አባዬ ፣ ስህንና ብሩክ ጋር አስረስ ፎቶ ቤት ሄድን ጋሽ አስርስ ይወደኛል ፤ “ኮረሪማ!” ይለኛል ገና ከሩቅ ሲያየኝ : :
“ኮረሪማ አረጀሽ በቃ! ትልቅ ሰው ... ትልቅ ኮረሪማ” አለኝ፤ ገና ከመግባታችን። ሣቅኹ ።መጣና እቅፍ አድርጎ ከሳመኝ በኋላ ለፎቶው መዘጋጀት ጀመርኩ።
ጋሽ አስርስ ሁሉን ነገር አሰናድቶ ለማንፀሳት ሲያነጣጥር አባቴ ጮክ አለና
“አስረስ ፣ ይህን መጋረጃ ቀይረው እንጂ ” አለው።
“የቱን? ” አለ ጋሽ አስረስ ፣ ካሜራው፣ ከእነ አንትገ ማንጠልጠያው፥
ከፊቱ ወደ ደረቱ፥ እየመለሰ ።
“ከኋላዋ ያለውን ጥቁር መጋርጃ!” አለ አባቴ : :
ኋላ ላይ ሻማው ፣ ጥርሷና ሚሪንዳው ብቻ ይወጣልህና ጉድ እንዳትሆን!” ሲለው ፤ ይወደኝ የመሰለኝ፤ ጋሽ አስረስ ከቀያዮቹ ቤተሰቦቼ ጋር ተደርቦ ሲስቅ ጠላሁት : :
።።።።።
በሃያ ሁለት ዓመቴ...
እንዲህ እንዲህ ሲብስ ሲብስ ፣ “ባርቾ እኮ ጭንቅላት ባይኖራት ጉዷ ነበር!
“አንቺ፤ ግን ሀበሻ ነሽ? ጋና እኮ ነው የምትመስይው!”
.
:
ሲሻል ደግሞ ፣ ብትቀላ ቆንጆ ነበረች፡ : እየተባልኩ፣ በቀያይ ቤተሰቦቼና ዘመዶቼ እየተቀለደብኝ ኖርኩ ፡ : በሃያ ሁለት ዓመቴም የትወና ጥበብ ተምሬ ጨርስኩና የጊዜውን የፊልም ሥራ በርከት ለመቋደስ ብዙ ቦታ ተመዝግቤ መፈተን ጀመርኩ። ከኮሌጅ ሰቅዬ
ነበር የተመረቕኩት ፣ ግን ደህና የፊልምም የቲያትርም የትወና ሥራ ማግኘት አልቻልኩም : : “በጣም አሪፍ ነው ፡ ፡ እናደውልልሻለን። ይሉኝና አይደውሉም።
ሌሎቹ ደግሞ ፣ ለትወና ሥራ አመልክቼ ፣ “ፐ! አንቺ በጣም ጎበዝ ተዋናይ ነሽ... ለምን፣ ማስተማር አትሞክሪም? ” ይሉኝና ያሰናብቱኛል። ነገሩ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ግልጥልጥ ያለልኝ ፤ ታሪኩንና ስክሪፕቱ
👍1👏1
ን አንብቤው በመሪ ተዋናይነት ልሠራበት የተንሰፈሰፍኩት ፣ “የማይነጋ ሌሊት” የተሰኘ ፊልም ላይ ለመቀጠር ፈተናው፤ ከጨርስኩ በኋላ ነበር : : ፈተናዬን፣ እንደኔ አስተሳሰብ ፣ “በሚያስገርም ብቃት” ፤ እንደ አዘጋጁ አባባል ፣ “በሚደንቅ ችሎታ” ከጨረስኩ በኋላ ልወጣ ስል ፤ አዘጋጁ የቀኝ እጁን በ“ወደኔ ነይ” ዓይነት ሲወዘውዝ ዐየሁት
ሄድኩ ፡ :
“ሜሮን በጣም በጣም ጎበዝ ተዋናይት ነሽ”
“እግዜር ይስጥልኝ... በጣም ነው ካራክተሯን' የወደድኳት! ብሠራት፥ ደስ
ይለኛል” አልኩት : : ጎበዝ ስላለኝ ደስ ብሎኝ እየሣቅኹ: :
“እኔም ደስ ይለኝ ነበር... የእውነት ሁላችንም ደስ ይለን ነበር ፣ ግን
ትወና ከመቻልሽ ውጪ የሰላንም፣ ካራክተር በምንም አትመስይም” አለኝ፤ በደንብ እያየኝ።
“እንዴት? ... የካራክተሯን ገለፃ ሳነበው ደፋር ፣ ጠንካራና ቁጡ ነው የሚለው : :
እሱን፤ አላሳየሁህም? ”
እ... እሱንማ በደንብ ነው የሰራሽው ... ግን፤... እሱ አይደለም...”
“ታዲያ ምንድነው?”
“ካራክተሯ ቀይ ናት ፡ : ”
“አቤት”
“ሰላም ቀይ ናት : : ”
“የቱ ጋር ነው ቀይ ናት የሚለው? ገለጻው ላይ የሚለው ደፋር ፣ ጠንራካ እና ቁጡ ብቻ ነው...” አልኩት ደሜ እየፈላ ፡ :
“ሜሮን! ሰላም የኔ ፈጠራ ናት ፡ : ቀይ ናት ካልኩ ቀይ ናት ፡ : መሪ ተዋናይት ሆና ጥቁር እንድትሆን ጠብቀሽ ነበር...? እስኪ አስቢው ፓስተሩን..!” አለኝ፤ ፣ እሱም ንዴት ንዴት እያለው : :
በሐዘን ዝም ብዬ ዐየሁትና ጀርባዬን ሰጥቼው ወጣሁ : :
ግቢው በር ላይ ሰደርስ የአዘጋጁ ድምጽ ሲጠራኝ ሰማሁ : : በአሸናፊነት ጮክ
ብዬ ተነፈስኩና ዞር አልኩ ፡ : አጠገቡ ስደርስ ፣ “ ይሄውልሽ
ሜሮን ፣ አንቺ ፣ ጎበዝ ተዋናይት ነሽ ...
እና ለፊልምህ ጎበዝ ተዋናይ እንጂ ቀይ ሰው እንደምትፈልግ አሁን ገባህ?” አልኩት ፣ ኩራትም ደስታም አያቁነጠነጠኝ : :
“እ... ይህን የመሰለ ታለንት ዌስትድ'” ከሚሆን ለምን የእልፌን፣ ካራክተር
አትሠሪውም ብዬ ነው...”
ግራ ገብቶኝ ዐየሁትና ፣ እልፌ ደሞ ማናት? እዚሁ ፊልም ውስጥ
ናት?” አልኩት : :
“አዎ... የእነ ሰላም ሰራተኛ ናት ፡ : ግን፤ በጣም ብዙ ሮል ነው ያላት...ዕይው ከፈከግሽ ስክራፕቱን፣“...” ብሎ ከያዛቸው ወረቀቶች መሃከል የተወሰኑ፥ ለመምረጥ ሲዋከብ ሳየው ነገሩ ሁኩ ቅዠት መሰኝ ፤
እንዴት፥ ከግቢው እንደወጣሁ ሳላስተውል ፤ ትንሽ ራቅ እንዳልኩ ከእንባዬ ጋር እየታገልኩ ስልኬን አወጣሁና ውጪ ሀገር ላለችው ታላቅ እህቴ የሚከተለውን የፅሁፍ መልዕክት ላኩላት : :
እንዴት ነሽ ስህን? ባለፈው ያልሽኝን፣ በዐሥራ አምስት ቀን ቆዳ የሚያቀላውን ክሬም ቶሎ ላኪልኝ አደራ !!
✨አልቋል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
ሄድኩ ፡ :
“ሜሮን በጣም በጣም ጎበዝ ተዋናይት ነሽ”
“እግዜር ይስጥልኝ... በጣም ነው ካራክተሯን' የወደድኳት! ብሠራት፥ ደስ
ይለኛል” አልኩት : : ጎበዝ ስላለኝ ደስ ብሎኝ እየሣቅኹ: :
“እኔም ደስ ይለኝ ነበር... የእውነት ሁላችንም ደስ ይለን ነበር ፣ ግን
ትወና ከመቻልሽ ውጪ የሰላንም፣ ካራክተር በምንም አትመስይም” አለኝ፤ በደንብ እያየኝ።
“እንዴት? ... የካራክተሯን ገለፃ ሳነበው ደፋር ፣ ጠንካራና ቁጡ ነው የሚለው : :
እሱን፤ አላሳየሁህም? ”
እ... እሱንማ በደንብ ነው የሰራሽው ... ግን፤... እሱ አይደለም...”
“ታዲያ ምንድነው?”
“ካራክተሯ ቀይ ናት ፡ : ”
“አቤት”
“ሰላም ቀይ ናት : : ”
“የቱ ጋር ነው ቀይ ናት የሚለው? ገለጻው ላይ የሚለው ደፋር ፣ ጠንራካ እና ቁጡ ብቻ ነው...” አልኩት ደሜ እየፈላ ፡ :
“ሜሮን! ሰላም የኔ ፈጠራ ናት ፡ : ቀይ ናት ካልኩ ቀይ ናት ፡ : መሪ ተዋናይት ሆና ጥቁር እንድትሆን ጠብቀሽ ነበር...? እስኪ አስቢው ፓስተሩን..!” አለኝ፤ ፣ እሱም ንዴት ንዴት እያለው : :
በሐዘን ዝም ብዬ ዐየሁትና ጀርባዬን ሰጥቼው ወጣሁ : :
ግቢው በር ላይ ሰደርስ የአዘጋጁ ድምጽ ሲጠራኝ ሰማሁ : : በአሸናፊነት ጮክ
ብዬ ተነፈስኩና ዞር አልኩ ፡ : አጠገቡ ስደርስ ፣ “ ይሄውልሽ
ሜሮን ፣ አንቺ ፣ ጎበዝ ተዋናይት ነሽ ...
እና ለፊልምህ ጎበዝ ተዋናይ እንጂ ቀይ ሰው እንደምትፈልግ አሁን ገባህ?” አልኩት ፣ ኩራትም ደስታም አያቁነጠነጠኝ : :
“እ... ይህን የመሰለ ታለንት ዌስትድ'” ከሚሆን ለምን የእልፌን፣ ካራክተር
አትሠሪውም ብዬ ነው...”
ግራ ገብቶኝ ዐየሁትና ፣ እልፌ ደሞ ማናት? እዚሁ ፊልም ውስጥ
ናት?” አልኩት : :
“አዎ... የእነ ሰላም ሰራተኛ ናት ፡ : ግን፤ በጣም ብዙ ሮል ነው ያላት...ዕይው ከፈከግሽ ስክራፕቱን፣“...” ብሎ ከያዛቸው ወረቀቶች መሃከል የተወሰኑ፥ ለመምረጥ ሲዋከብ ሳየው ነገሩ ሁኩ ቅዠት መሰኝ ፤
እንዴት፥ ከግቢው እንደወጣሁ ሳላስተውል ፤ ትንሽ ራቅ እንዳልኩ ከእንባዬ ጋር እየታገልኩ ስልኬን አወጣሁና ውጪ ሀገር ላለችው ታላቅ እህቴ የሚከተለውን የፅሁፍ መልዕክት ላኩላት : :
እንዴት ነሽ ስህን? ባለፈው ያልሽኝን፣ በዐሥራ አምስት ቀን ቆዳ የሚያቀላውን ክሬም ቶሎ ላኪልኝ አደራ !!
✨አልቋል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍3
#የድሃ_ልደት
መሬት ላይ እየተኙ እግር ስር እየወደቁ
ኑሮ በሚባል ከስክስ ጫማ ተረግጠው እየደቀቁ፣
“አለን ይመስገን ይላሉ
በሰው ጥላ ስር እየዋሉ፡፡
ምቹ ማረፊያ ያጣን ተንሳፋፊ ብናኞች
ፍርፋሪ ፍለጋ የሰው ፊት ምናይ ትንኞች ፧
ይኼንም ኑሮ አልነውና
አንድ ቀን እንኳ ሳይደላን አንድ ቀን እንኳ ሳንዝናና፣
ስጋ ውስጥ ነብስ ተፈጥሮ
በእስትንፋስ ዕድሜ ተቆጥሮ ፤
ሃምሳ አመት ሞላው ይባላል
ሰው በቁጥር ይደለላል፡፡
ወዲያ የድሃ ልደት፣
ወዲያ የደሃ ኑሮ!
የቁጥር ብቻ ቋጠሮ፡፡
🔘ሙሉቀን🔘
መሬት ላይ እየተኙ እግር ስር እየወደቁ
ኑሮ በሚባል ከስክስ ጫማ ተረግጠው እየደቀቁ፣
“አለን ይመስገን ይላሉ
በሰው ጥላ ስር እየዋሉ፡፡
ምቹ ማረፊያ ያጣን ተንሳፋፊ ብናኞች
ፍርፋሪ ፍለጋ የሰው ፊት ምናይ ትንኞች ፧
ይኼንም ኑሮ አልነውና
አንድ ቀን እንኳ ሳይደላን አንድ ቀን እንኳ ሳንዝናና፣
ስጋ ውስጥ ነብስ ተፈጥሮ
በእስትንፋስ ዕድሜ ተቆጥሮ ፤
ሃምሳ አመት ሞላው ይባላል
ሰው በቁጥር ይደለላል፡፡
ወዲያ የድሃ ልደት፣
ወዲያ የደሃ ኑሮ!
የቁጥር ብቻ ቋጠሮ፡፡
🔘ሙሉቀን🔘
#የታካሚው_ማስታወሻ(ህመም አልባው በሽታ)
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ(MD)
1.ቅድመ ታሪክ
ከአንድ ዓመት ስራ መፍታት በኋላ፣ እንደገና ስራ ልጀምር ነው። በማኔጅመንት ሁለተኛ ድግሪና ከአስር ዓመት በላይ የስራ ልምድ አለኝ። ያለ ስራ በቆየሁበት ግዜ፣ ያጠራቀምኩትን ገንዘብ ጨርሼ
ንብረቶቼን ሸጥኩ፡፡ አሁን መኪናዬን ለመሸጥ በማሰብ ላይ ሳለሁ ስራ
አገኘሁ፡፡ ከባድ ግዜ ነበር፡፡ ንብረት ከማጣት በተጨማሪ፣ የስነ ልቦና ጉዳቱ ይሄ ነው ሚባል አይደለም፡፡ በራሴ ያለኝ መተማመን በከፍተኛ ደረጃ አሽቆልቁሏል፡፡ ከዚህ በፊትም፣ በተመሳሳይ ስራ ለቅቄ እስክፀፀት
ተቸግሬ አውቃለሁ፡፡ ሁለተኛ ብዬ ለራሴ ቃል ገብቼ ነበር፡፡ ቃሌን መጠበቅ አቅቶኝ፣ ይኸው ለአመት ተንከራተትኩ፡፡
የመጨረሻው ድርጅቴ በጣም ጥሩ ክፍያን ይከፍለኝ ነበር፡፡በተጨማሪም፣ ለሙያዬ እድገት የሚረዱኝ የተለያዩ የስልጠና እድሎችን በሃገር ውስጥና በውጪ ሃገራት ያመቻችልኝ ነበር፡፡ በጣም ደስተኛ ሆኜ ነበር፡፡ ብዙ እንደምቆይበት ተሰምቶኝ ነበር፡፡ ከተወሰነ ግዜ በኋላ ግን፣ሰራተኛው የተከፋፈለና በየቀኑ የሚካሰስ እንደሆነ እየተሰማኝ መጣ፡፡እኔ ደግሞ እንደ አስተዳደር ስራዬ መዳኘት ነው፤ አንዱን በዳይ፣አንዱን ተበዳይ አድርጎ መፍረድ፡፡ እኔ ደግሞ፣ ከመፍረድና ከመቅጣት ይልቅ፣ ችግሩን በማስታረቅ መፍታት የተሻለ መስሎ ተሰማኝ፡፡ እንደዛ ሞከርኩ። አይሳካም፡፡ ጭራሽ ወደኋላ አምስት፣ አስር ዓመት
ተመልሰው፣ “እርሱ/እርሷ፣ ባለፈውም እንዲህ በድሎኝ/ላኝ፣” እያሉ ሌላ
የክስ ቱባ ይተረትራሉ።
ጓደኛ ሆኜ ቀርቤያቸው፣ መሰረታዊ የፀባቸውን መንስኤ ለማወቅ
ሞከርኩ፡፡ ከአሉባልታ የዘለለ፣ ይሄ ነው የሚባል የከፋ ነገር የላቸዉም፡፡ክሶቻቸው ከጥርጣሬና፣ ሳይቀድመኝ ልቅደመው ከማለት የሚመነጩ ናቸው። እኩል ቀርቤ፣ እንደ ድልድይ ላቀራርባቸው ሞከርኩ፡፡ የሚሆን አይደለም፡፡ ያለበቂ ምክንያት፣ ላይታረቁ ተጣልተዋል፡፡ ለተጣላ ሰው ደግሞ፣ መካሰሻ ምክንያት አሽዋ ነው፡፡ መዳኘት ስራዬ ቢሆንም፣
ሰለቸኝ፡፡ ሁሉም ተበደልኩ ባይ ነው፡፡ ቀስ በቀስ ደስታዬ ተነነ፣ ሳቄና ጨዋታዬም ጠፋ፡፡ ብስጩና ነጭናጫ ሆንኩ፡፡ ወደ ስራዬ መሄድ ይሰለቸኝና ይጨንቀኝ ጀመረ። ስራተኛውና ድርጅቱ አንገሸገሹኝ፡፡ ካሁን በኋላ ስራ በፍፁም አለቅም ብዬ የገባሁትን ቃል መጠበቅ አቃተኝ፡፡ ሌላ ስራ እንኳን ሳላገኝ እንደዘበት መልቀቂያ አስገብቼ ጠፋሁ፡፡ ለአመት ተንከራተትቼ አዲስ ስራ አገኘሁ፡፡ አሁንም፣ እንደገና አይለምደኝም ብዬ
ስራ ልጀምር ነው፡፡
#እንደገና
“..ቋ..ቋ...ቋ...” ከአለቃዬ ቢሮ እንደወጣሁ፣ ኮሪደሩ ላይ፣ የሂል
ጫማ ድምፅ ተቀበለኝ፡፡ ድምፁን ወደሰማሁበት ቀና ብዬ ተመለከትኩ።
ፈዘዝ ያለ ቢጫ ቦዲ፣ በጥቁር ጨርቅ ሱሪ፣ የሚያምር የሰውነት ቅርፅ፣በረጅም ሂል ጫማ የተጫማች ልጅ ወደኔ አቅጣጫ እየመጣች ነው።ከአለቃዬ ቢሮ፣ የኔ ቢሮ ሩቅ ሚባል አይደለም፡፡ የጎረምሳ ነገር ልጅቷን በቅርበት ሳላያት ወደቢሮዬ መግባት አልፈለኩም፡፡ እንድትደርስብኝ እንደ ኤሊ ተጎተትኩ፡፡ አልተሳካም! ቢሮዬ በር ደረስኩ፡፡ ይሄኔ የሚመጣው
ሰው ማልፈልገው ሆኖ እንዳላየ ለመግባት ብጣደፍኮ ኖሮ.....። መጠበቅ
አለብኝ፡፡ ከአለቃዬ የተቀበልኩትን ወረቀት፣ የቢሮዬ በር ላይ ቆሜ
ማንበብ ጀመርኩ፡፡
ሄይ! አዲሱ ስታፋችን?” እጇን ዘረጋችልኝ..
“አዎ! ያቤዝ እባላለሁ፡፡” እጇን ጨብጬ ከላይ እስከታች በዐይኔ እየዳበስኳት፡፡
“ማሂ ቆንጆ እባላለሁ፡፡”
“እመሰክራለሁ! በጣም ቆንጆ ነሽ!፡፡”
ኪ.ኪ...ኪ...፣ አመሰግናለሁ፡፡ እንኳን ደህና መጣህ፡፡
በስርዓት አቀባበል እናደርጋለን፡፡” ብላ፣ የቆምኩበት ትታኝ፣ ወደ አለቃዬ
ቢሮ መሄድ ጀመረች፡፡
“አመሰግናለሁ!” እያልኩ፣ የጀርባ ውበቷን ለማረጋገጥ ካንገቴ ዞሬ በዐይኔ ተከተልኳት፡፡ ትንሽ እንደተራመደች እያየኋት እንደሆነ ለማረጋገጥ ይመስል፣ ድንገት ዞር ስትል ዐይን ለዐይን ተጋጨን፡፡ ወደ ቢሮዬ ተስፈንጥሬ ገባሁ፡፡ ሃሳቤ ግን ተከትሏት ሄዷል፡፡ ውበቷ ሙጫ ነው፣ ተጣብቆ የሚቀር፡፡ ማራኪ ነች፡፡ በዛ ላይ በደንብ ተኳኩላለች።ቢሆንም፣ ሲፈጥራትም ልቅም ያለች ቆንጆ ነች፡፡ ሃም...፣ ጥሩ ጥቅማ ጥቅም ያለው አሪፍ መስሪያ ቤት ነው የገባሁት፡፡ ይሄንን ቢነግሩኝ ኖሮ፣መች ደሞዙን እንደዛ እጨቃጨቃቸው ነበር፡፡ ምን ክፍል ይሆን
ምትሰራው...?”
ቢሮዬን ዝም ብዬ ተመለከትኩት፡፡ የሰለቸው የወንደ ላጤ ቤት መስሎ ተዝረክርኳል፡፡ እዚህ ቢሮ ውስጥ በቀን ስምንት ሰዓት መቆየት በራሱ ያደክማል፡፡ የጠረጴዛና ወንበሮቹ አቀማመጥ በዘፈቀደ ነው።ማስተካከል ጀመርኩ፡፡ ለስራ በሚመቸኝና ቢሮው የተሻለ እይታ
እስኪኖረው መላልሼ አዟዟርኳቸው፡፡ ማልፈልጋቸውን ወረቀቶች አስወገድኩ፤ ያስፈልጋሉ ምላቸውን፣ በየዘርፍ በየዘርፍ አድርጌ ፋይል ውስጥ አስቀመጥኳቸው፡፡ ስሰራ ሃሳቤ እንዲሰረቅ አልፈልግም፡፡ ቢሮ ውስጥ ያሉ ኮተቶችና ምስቅልቅሎች ሃሳብን ያናጥባሉ። በነፃነትና በትኩረት ስራዬን ለመስራት፣ በምችለው መጠን ቢሮዬን ስርዓት ያለውና ነፃ አደረኩት፡፡ ይህ በቀደሙት መስሪያ ቤቶቼም የምከውነው የመጀመሪያ ቀን ተግባሬ ነው፡፡ ጎንበስ ቀና ያልኩበት፣ እቃዎቹን
የጎተትኩበት ድካም ተሰማኝ፡፡ እርጅና ሊመጣ ነው፡፡ ትንፋሽ ለመውሰድ
ወንበር ላይ አረፍ አልኩ፡፡ ሰዓቴን ስመለከት የሻይ ሰዓት ደርሷል።
ሻይ በኋላ የቀረውን አስተካክለዋለሁ ብዬ እያሰብኩ፤
“ጤና ይስጥልኝ!...” ብለው አለቃዬ ወደ ቢሮዬ ገቡ። እጄን ጨብጠው ሰላምታ ተለዋወጥን፡፡ አለቃዬ መልከ መልካም፣ እድሜያቸው ጎልማሳነትን የዘለለ ይመስላሉ፡፡
“እንኳን ደህና መጡ!”
“ደግሞ ከመቼው ቢሮውን እንዲህ አሳመርከው...?፣ ይሄ ቢሮ እንዲህ ያምር ነበር እንዴ...?” በፈገግታ ጥርሳቸውን ፈልቀቅ አድርገው፡፡
“እንዲመቸኝ ትንሽ ነው የነካካሁት፡፡”
“ሌላ ቢሮ አስመስለህ አሳምረከዋል እንጂ፡፡ አይ ወጣት! መቼም ውበት ትወዳላችሁ! በል ና አሁን ቡና ልጋብዝህ፤ በዛውም ስታፎቻችንን ላስተዋውቅህ፤” ብለውኝ ከቢሮዬ ወጡ፡፡
“እሺ!” ብዬ ቢሮዬን ቆልፌ ተከተላኳቸው፡፡
ካፍቴሪያ ስንደርስ፣ ክብ ሰርተው እየተንጫጩ ሻይ ቡና የሚጠጡ ሰዎች ጋር ወስደው ቀላቀሉኝ፡፡ እየጮሁ ያወራሉ፤ እየጮሁ ይሳሳቃሉ፡፡ ይህ የግቢው አውራ ቡድን እንደሆነ ሁኔታቸው ይናገራል፡፡እየተሸቀዳደሙ ያወራሉ፤ ከፍ አድርገው ይስቃሉ፤ ያሽካካሉ፤ ሌላ ሰው
ይሰማናል፣ እንረብሻለን፣ ምን ይሉናል ሚሉት ነገሮች ሚያሳስቧቸው አይመስሉም፡፡
“ጎበዝ አዲሱ አድሚናችንን ትተዋወቁት ዘንድ ይዤው መጥቻለሁ፡፡ ያቤዝ ይባላል፡፡ እናንተ ደግሞ እራሳችሁን አስተዋውቁት፧”ብለው ወንበር ስበው ተቀመጡ፡፡ ጫጫታቸውን አቁመው፣ ፀጥ ብለው ካዳመጡ በኋላ፣ በአንድ ላይ፣ “እንኳን ደህና መጣህ! ዌል ካም!›› ብለው አልጎመጎሙ:: አራት ሴትና ሶስት ወንድ ናቸው፡፡ ሴቶቹ ወጣትና ቆነጃጅት ሲሆኑ፣ ወንዶቹ በእድሜ ከፍ ከፍ ያሉና፣ ሙሉ ሰውነት ያልደረሱ ጎልማሶች ናቸው።
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ(MD)
1.ቅድመ ታሪክ
ከአንድ ዓመት ስራ መፍታት በኋላ፣ እንደገና ስራ ልጀምር ነው። በማኔጅመንት ሁለተኛ ድግሪና ከአስር ዓመት በላይ የስራ ልምድ አለኝ። ያለ ስራ በቆየሁበት ግዜ፣ ያጠራቀምኩትን ገንዘብ ጨርሼ
ንብረቶቼን ሸጥኩ፡፡ አሁን መኪናዬን ለመሸጥ በማሰብ ላይ ሳለሁ ስራ
አገኘሁ፡፡ ከባድ ግዜ ነበር፡፡ ንብረት ከማጣት በተጨማሪ፣ የስነ ልቦና ጉዳቱ ይሄ ነው ሚባል አይደለም፡፡ በራሴ ያለኝ መተማመን በከፍተኛ ደረጃ አሽቆልቁሏል፡፡ ከዚህ በፊትም፣ በተመሳሳይ ስራ ለቅቄ እስክፀፀት
ተቸግሬ አውቃለሁ፡፡ ሁለተኛ ብዬ ለራሴ ቃል ገብቼ ነበር፡፡ ቃሌን መጠበቅ አቅቶኝ፣ ይኸው ለአመት ተንከራተትኩ፡፡
የመጨረሻው ድርጅቴ በጣም ጥሩ ክፍያን ይከፍለኝ ነበር፡፡በተጨማሪም፣ ለሙያዬ እድገት የሚረዱኝ የተለያዩ የስልጠና እድሎችን በሃገር ውስጥና በውጪ ሃገራት ያመቻችልኝ ነበር፡፡ በጣም ደስተኛ ሆኜ ነበር፡፡ ብዙ እንደምቆይበት ተሰምቶኝ ነበር፡፡ ከተወሰነ ግዜ በኋላ ግን፣ሰራተኛው የተከፋፈለና በየቀኑ የሚካሰስ እንደሆነ እየተሰማኝ መጣ፡፡እኔ ደግሞ እንደ አስተዳደር ስራዬ መዳኘት ነው፤ አንዱን በዳይ፣አንዱን ተበዳይ አድርጎ መፍረድ፡፡ እኔ ደግሞ፣ ከመፍረድና ከመቅጣት ይልቅ፣ ችግሩን በማስታረቅ መፍታት የተሻለ መስሎ ተሰማኝ፡፡ እንደዛ ሞከርኩ። አይሳካም፡፡ ጭራሽ ወደኋላ አምስት፣ አስር ዓመት
ተመልሰው፣ “እርሱ/እርሷ፣ ባለፈውም እንዲህ በድሎኝ/ላኝ፣” እያሉ ሌላ
የክስ ቱባ ይተረትራሉ።
ጓደኛ ሆኜ ቀርቤያቸው፣ መሰረታዊ የፀባቸውን መንስኤ ለማወቅ
ሞከርኩ፡፡ ከአሉባልታ የዘለለ፣ ይሄ ነው የሚባል የከፋ ነገር የላቸዉም፡፡ክሶቻቸው ከጥርጣሬና፣ ሳይቀድመኝ ልቅደመው ከማለት የሚመነጩ ናቸው። እኩል ቀርቤ፣ እንደ ድልድይ ላቀራርባቸው ሞከርኩ፡፡ የሚሆን አይደለም፡፡ ያለበቂ ምክንያት፣ ላይታረቁ ተጣልተዋል፡፡ ለተጣላ ሰው ደግሞ፣ መካሰሻ ምክንያት አሽዋ ነው፡፡ መዳኘት ስራዬ ቢሆንም፣
ሰለቸኝ፡፡ ሁሉም ተበደልኩ ባይ ነው፡፡ ቀስ በቀስ ደስታዬ ተነነ፣ ሳቄና ጨዋታዬም ጠፋ፡፡ ብስጩና ነጭናጫ ሆንኩ፡፡ ወደ ስራዬ መሄድ ይሰለቸኝና ይጨንቀኝ ጀመረ። ስራተኛውና ድርጅቱ አንገሸገሹኝ፡፡ ካሁን በኋላ ስራ በፍፁም አለቅም ብዬ የገባሁትን ቃል መጠበቅ አቃተኝ፡፡ ሌላ ስራ እንኳን ሳላገኝ እንደዘበት መልቀቂያ አስገብቼ ጠፋሁ፡፡ ለአመት ተንከራተትቼ አዲስ ስራ አገኘሁ፡፡ አሁንም፣ እንደገና አይለምደኝም ብዬ
ስራ ልጀምር ነው፡፡
#እንደገና
“..ቋ..ቋ...ቋ...” ከአለቃዬ ቢሮ እንደወጣሁ፣ ኮሪደሩ ላይ፣ የሂል
ጫማ ድምፅ ተቀበለኝ፡፡ ድምፁን ወደሰማሁበት ቀና ብዬ ተመለከትኩ።
ፈዘዝ ያለ ቢጫ ቦዲ፣ በጥቁር ጨርቅ ሱሪ፣ የሚያምር የሰውነት ቅርፅ፣በረጅም ሂል ጫማ የተጫማች ልጅ ወደኔ አቅጣጫ እየመጣች ነው።ከአለቃዬ ቢሮ፣ የኔ ቢሮ ሩቅ ሚባል አይደለም፡፡ የጎረምሳ ነገር ልጅቷን በቅርበት ሳላያት ወደቢሮዬ መግባት አልፈለኩም፡፡ እንድትደርስብኝ እንደ ኤሊ ተጎተትኩ፡፡ አልተሳካም! ቢሮዬ በር ደረስኩ፡፡ ይሄኔ የሚመጣው
ሰው ማልፈልገው ሆኖ እንዳላየ ለመግባት ብጣደፍኮ ኖሮ.....። መጠበቅ
አለብኝ፡፡ ከአለቃዬ የተቀበልኩትን ወረቀት፣ የቢሮዬ በር ላይ ቆሜ
ማንበብ ጀመርኩ፡፡
ሄይ! አዲሱ ስታፋችን?” እጇን ዘረጋችልኝ..
“አዎ! ያቤዝ እባላለሁ፡፡” እጇን ጨብጬ ከላይ እስከታች በዐይኔ እየዳበስኳት፡፡
“ማሂ ቆንጆ እባላለሁ፡፡”
“እመሰክራለሁ! በጣም ቆንጆ ነሽ!፡፡”
ኪ.ኪ...ኪ...፣ አመሰግናለሁ፡፡ እንኳን ደህና መጣህ፡፡
በስርዓት አቀባበል እናደርጋለን፡፡” ብላ፣ የቆምኩበት ትታኝ፣ ወደ አለቃዬ
ቢሮ መሄድ ጀመረች፡፡
“አመሰግናለሁ!” እያልኩ፣ የጀርባ ውበቷን ለማረጋገጥ ካንገቴ ዞሬ በዐይኔ ተከተልኳት፡፡ ትንሽ እንደተራመደች እያየኋት እንደሆነ ለማረጋገጥ ይመስል፣ ድንገት ዞር ስትል ዐይን ለዐይን ተጋጨን፡፡ ወደ ቢሮዬ ተስፈንጥሬ ገባሁ፡፡ ሃሳቤ ግን ተከትሏት ሄዷል፡፡ ውበቷ ሙጫ ነው፣ ተጣብቆ የሚቀር፡፡ ማራኪ ነች፡፡ በዛ ላይ በደንብ ተኳኩላለች።ቢሆንም፣ ሲፈጥራትም ልቅም ያለች ቆንጆ ነች፡፡ ሃም...፣ ጥሩ ጥቅማ ጥቅም ያለው አሪፍ መስሪያ ቤት ነው የገባሁት፡፡ ይሄንን ቢነግሩኝ ኖሮ፣መች ደሞዙን እንደዛ እጨቃጨቃቸው ነበር፡፡ ምን ክፍል ይሆን
ምትሰራው...?”
ቢሮዬን ዝም ብዬ ተመለከትኩት፡፡ የሰለቸው የወንደ ላጤ ቤት መስሎ ተዝረክርኳል፡፡ እዚህ ቢሮ ውስጥ በቀን ስምንት ሰዓት መቆየት በራሱ ያደክማል፡፡ የጠረጴዛና ወንበሮቹ አቀማመጥ በዘፈቀደ ነው።ማስተካከል ጀመርኩ፡፡ ለስራ በሚመቸኝና ቢሮው የተሻለ እይታ
እስኪኖረው መላልሼ አዟዟርኳቸው፡፡ ማልፈልጋቸውን ወረቀቶች አስወገድኩ፤ ያስፈልጋሉ ምላቸውን፣ በየዘርፍ በየዘርፍ አድርጌ ፋይል ውስጥ አስቀመጥኳቸው፡፡ ስሰራ ሃሳቤ እንዲሰረቅ አልፈልግም፡፡ ቢሮ ውስጥ ያሉ ኮተቶችና ምስቅልቅሎች ሃሳብን ያናጥባሉ። በነፃነትና በትኩረት ስራዬን ለመስራት፣ በምችለው መጠን ቢሮዬን ስርዓት ያለውና ነፃ አደረኩት፡፡ ይህ በቀደሙት መስሪያ ቤቶቼም የምከውነው የመጀመሪያ ቀን ተግባሬ ነው፡፡ ጎንበስ ቀና ያልኩበት፣ እቃዎቹን
የጎተትኩበት ድካም ተሰማኝ፡፡ እርጅና ሊመጣ ነው፡፡ ትንፋሽ ለመውሰድ
ወንበር ላይ አረፍ አልኩ፡፡ ሰዓቴን ስመለከት የሻይ ሰዓት ደርሷል።
ሻይ በኋላ የቀረውን አስተካክለዋለሁ ብዬ እያሰብኩ፤
“ጤና ይስጥልኝ!...” ብለው አለቃዬ ወደ ቢሮዬ ገቡ። እጄን ጨብጠው ሰላምታ ተለዋወጥን፡፡ አለቃዬ መልከ መልካም፣ እድሜያቸው ጎልማሳነትን የዘለለ ይመስላሉ፡፡
“እንኳን ደህና መጡ!”
“ደግሞ ከመቼው ቢሮውን እንዲህ አሳመርከው...?፣ ይሄ ቢሮ እንዲህ ያምር ነበር እንዴ...?” በፈገግታ ጥርሳቸውን ፈልቀቅ አድርገው፡፡
“እንዲመቸኝ ትንሽ ነው የነካካሁት፡፡”
“ሌላ ቢሮ አስመስለህ አሳምረከዋል እንጂ፡፡ አይ ወጣት! መቼም ውበት ትወዳላችሁ! በል ና አሁን ቡና ልጋብዝህ፤ በዛውም ስታፎቻችንን ላስተዋውቅህ፤” ብለውኝ ከቢሮዬ ወጡ፡፡
“እሺ!” ብዬ ቢሮዬን ቆልፌ ተከተላኳቸው፡፡
ካፍቴሪያ ስንደርስ፣ ክብ ሰርተው እየተንጫጩ ሻይ ቡና የሚጠጡ ሰዎች ጋር ወስደው ቀላቀሉኝ፡፡ እየጮሁ ያወራሉ፤ እየጮሁ ይሳሳቃሉ፡፡ ይህ የግቢው አውራ ቡድን እንደሆነ ሁኔታቸው ይናገራል፡፡እየተሸቀዳደሙ ያወራሉ፤ ከፍ አድርገው ይስቃሉ፤ ያሽካካሉ፤ ሌላ ሰው
ይሰማናል፣ እንረብሻለን፣ ምን ይሉናል ሚሉት ነገሮች ሚያሳስቧቸው አይመስሉም፡፡
“ጎበዝ አዲሱ አድሚናችንን ትተዋወቁት ዘንድ ይዤው መጥቻለሁ፡፡ ያቤዝ ይባላል፡፡ እናንተ ደግሞ እራሳችሁን አስተዋውቁት፧”ብለው ወንበር ስበው ተቀመጡ፡፡ ጫጫታቸውን አቁመው፣ ፀጥ ብለው ካዳመጡ በኋላ፣ በአንድ ላይ፣ “እንኳን ደህና መጣህ! ዌል ካም!›› ብለው አልጎመጎሙ:: አራት ሴትና ሶስት ወንድ ናቸው፡፡ ሴቶቹ ወጣትና ቆነጃጅት ሲሆኑ፣ ወንዶቹ በእድሜ ከፍ ከፍ ያሉና፣ ሙሉ ሰውነት ያልደረሱ ጎልማሶች ናቸው።
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍3👏2