#ከ ‹‹ፈሮግራምህ›› #ውልፍት_የለም !
አንሾ ባልታወቀ ምክንያት የምትወደው ባሏ አባተ ጋር ትጣላለች ,,,,,እናም ኮብልላ ወላጆቿ ቤት ታድራለች ! በበነጋታው የአገር ሽማግሌወች ባልና ሚስትን ሊያስታርቁ ሽምግልና ይቀመጣሉ !
‹‹ ችግርሽ ምንድነው ?››
‹‹ምንም››
‹‹እንዴት ያለምንም ችግር ትዳርሽን ታፈርሻለሽ ››
‹‹ በቃ አልፈልግም ››
‹‹እኮ ለምን ?›› አሉ ሽማግሌወች በማግባባት አንሾ ስትፈራ ስትቸር አንዲት ነገር ተናገረች ‹‹ አሱ ሰው አይደለም ዝንጆሮ ነው ›› ሽማግሌወቹ ገባቸው ! ባሏ እንደዝንጆሮ ወሲብ ያበዛል አልቻለችውም ማለት ነበር ትረጉሙ…. እናም ሽማግሌወቹ ጉዳዩን በዝርዝር እንድታስረዳቸው ጠየቁ… እ,ሷም አንዴ ከአፏ ወጥቷልና በዝርዝር ጉዳዩን ታስረዳ ጀመረ !
‹‹ እንደው በኔ የደረሰ አይድረስባችሁ … ባለቤቴ ሳያገባኝ በፊት ጎበዝ ገበሬ …. አገር ያወቀው ጀግና ነበር ታውቃላችሁ መቸስ ….ከተጋባን ጀምሮ መሬቱ ሁሉ ጦም አደረ በሬወቹ እንደተጠመዱ ትቷቸው ይመጣና እኔን ይጠምደኛል …. ሌሊት ወገቤ አያርፍ እግሬ አይገጠም ጧት በግድ ተነስቸ ያዘጋጀሁትን ቁርስ ቀመስ አድርጎ ይተውና ወደመደቡ መጎተት ነው ….ውሃ ቀድቸ ስመለስ እንስራየን አውርዶ ወዲያ ይወረውርና ‹ያዥ እንግዲህ › ነው … አልቻልኩም በዛብኝ ምነው ሸዋ ! ›› አለችና ሽማግሌወቹ ፊት አለቀሰች ! ሽማግሌወቹም ችግሯን ስለተረዱ እዛው ተቀምጦ ጉዱን የሚሰማውን ባሏን ጠሩና መከሩት
‹‹አባተ ››
‹‹አቤት አባቶቸ ›› አለ እየተቅለሰለሰ
‹‹እንግዲህ የተባለውን ሰምተሃል እውነት ነው ሃሰት ? ››
‹‹ኧረ ሃቅ ነው አባቶቸ ….›› ሲል አመነ
‹‹ ጥሩ እንግዲህ ጥፋት አይተንብሃል በል አሁን የምንመክርህን ስማ ›› አሉና ሽማግሌወቹ ተመካክረው በአንድ ወግ አዋቂ ሽማግሌ በኩል እንዲህ አሉት
‹‹ እንግዲህ አባተ <እንትን > እንደሆነ ዝም ብለው ቢውሉበት ቁርስ አይሆን ምሳ ርስት አይሆን ሃብት …. እየናፈቀ ሲገኝ ነው ደጉ …ይሄው አረጀንበት ከልጅነት እስከእውቀት ኖርንበት እሱ እንደሆን እያደር አዲስ ነው ከምን እንደሰራው አንድየ ይወቀው …..እና አሁንም አንተም ሚስትህን አንሻን እንዳታማርራት በ ‹ፈሮግራም › እንዲሆን ወስነንበሃል ›› ሲሉ አስረዱ
‹‹ እሽ አባቶቸ እንዳላችሁ ….ግ…..ን ‹ፈሮግራሙ› እንዴት እንዴት ነው ›› አለ አባተ
‹‹ እንግዲህ ፈሮግራሙ እንዲህ ነው …. ቀን ቀን እቤት ድርሽ ሳትል እርሻላህ ላይ ትውልና ማታ ጀምበር ሲያዘቀዝቅ ከብቶችህን አስገብተህ ስታበቃ አንሾም ናፍቃህ ትውል የለም …..አንደዜ ! ….ደሞ ራት ተተበላ በኋላ ኩራዝ ጠፍቶ ጋደም ስትሉ ….አንደዜ ! ወደንጋጋቱ ላይ ዶሮ ሲጮህ ደሞ አንደዜ ! ሶስት ሃቅህ ነው !›› አሉት
አባተ ቅር እያለው እንዲህ አለ ‹‹ እንደ…..ው ኣባቶቸ ምክራችሁ ጥሩ ነበር ግ…..ን እነደው …. ለጠራራውም ለውሃ ጥሙም ቀን ላይ አንደዜ ብትጨምሩልኝ ›› ሲል ጠየቀ
አንሾ በተራዋ ‹‹ የዶሮ ጩኸቱን ብታነሱልኝ ምናለ …. ሁለቴ ካገኘ ምን አነሰው ›› ስትል ቅሬታዋን አቀረበች ! ሽማግሌወቹ ግራ ቀኙን አድምጠው ‹‹ አንሾ አንችም አትሰስች ….አንተም ከ ‹ፈሮግራምህ› ውልፍት የለም ! ከተሜው ሁሉ እንዲሁ ነው የሚያረግ ›› አሉና በውሳኔያቸው ፀኑ !
አንሾና አባተም እርቅ አውርደው ወደቤታቸው ሄዱ ! ልክ እቤታቸው ሲደርሱ ጀምበር አዘቅዝቆ ስለነበር አባተ እየተጣደፈ አንሾን ወደመደቡ ጎተታት …. አንሾም ተጣልተው ስለቆዩ ናፍቋት ስለነበር አልከፋትም ኧረ እንደውም ደስ አላት !
‹‹ አንድ በል ቁጥር እነዳትስት ›› አለች ቀሚሷን እያጠለቀች ! አፍታ ሳይቆይ አባተ አንሾ አማረችው ! አለፍ ስትል ሳብ አደረገና እነሆ ! ሁለት ! ገና እራት ሳይቀርብ አንሾ ጉድ ጉድ ስትል ጠይም ፊቷ በምድጃው እሳት ወጋገን ወርቅ መስሎ ታየው አባተ አላስችል አለው በቃ ሳብ አደረጋና ሶስተኛውን ሃቁን አነሳ !
እራት ቀርቦ በሉና ጋደም እንዳሉ አባተ የአንሾ አርቲ እና አሽኩቲ ጠረን አቅሉን ነሳው ! ሽማግሌወች የወሰኑለትን ኮታ ደግሞ ጨርሷል እናም በጨለማው ውስጥ ቀስ ብሎ እንዲህ አለ ‹‹አንሾ ››
‹‹ምን ፈለክ…..የዛሬውን ድርሻ ሶስትህን ጨርስሃል ነገር ትፈልገኝና ውርድ ከራሴ ›› አለች አንሾ በቁጣ
‹‹ እንደው አፈር ትሆንልሽ …..ተነገው አንድ አበድሪኝ አንሾዋ ›› አላት ያልሆነ ቦታ እየደባበሳት .....አንሾ አሰብ አደረገች እሽ እንዳትል ኩራቷ ያዛት እምቢ እንዳትል የአባተ እጅ ቀልቧን ወስዶታል እናም እንዲህ አለች ‹‹ ምን የነገውን አበዳደረህ የትላንቱስ ሶስቱ መች ተነካ ›› ትላንት ተጣልተው አብረው አላደሩም !!
ወደቁም ነገራችን ስንመለስ በባልና በሚስት እንዲሁም በፍቅረኞች መሃል ለሚፈጠሩ ችግሮች መፍትሄው ሶስተኛ ወገን ሳይሆን ፍቅር ራሱ ነው #ፍቅር_ብቻ !!!!
አንሾ ባልታወቀ ምክንያት የምትወደው ባሏ አባተ ጋር ትጣላለች ,,,,,እናም ኮብልላ ወላጆቿ ቤት ታድራለች ! በበነጋታው የአገር ሽማግሌወች ባልና ሚስትን ሊያስታርቁ ሽምግልና ይቀመጣሉ !
‹‹ ችግርሽ ምንድነው ?››
‹‹ምንም››
‹‹እንዴት ያለምንም ችግር ትዳርሽን ታፈርሻለሽ ››
‹‹ በቃ አልፈልግም ››
‹‹እኮ ለምን ?›› አሉ ሽማግሌወች በማግባባት አንሾ ስትፈራ ስትቸር አንዲት ነገር ተናገረች ‹‹ አሱ ሰው አይደለም ዝንጆሮ ነው ›› ሽማግሌወቹ ገባቸው ! ባሏ እንደዝንጆሮ ወሲብ ያበዛል አልቻለችውም ማለት ነበር ትረጉሙ…. እናም ሽማግሌወቹ ጉዳዩን በዝርዝር እንድታስረዳቸው ጠየቁ… እ,ሷም አንዴ ከአፏ ወጥቷልና በዝርዝር ጉዳዩን ታስረዳ ጀመረ !
‹‹ እንደው በኔ የደረሰ አይድረስባችሁ … ባለቤቴ ሳያገባኝ በፊት ጎበዝ ገበሬ …. አገር ያወቀው ጀግና ነበር ታውቃላችሁ መቸስ ….ከተጋባን ጀምሮ መሬቱ ሁሉ ጦም አደረ በሬወቹ እንደተጠመዱ ትቷቸው ይመጣና እኔን ይጠምደኛል …. ሌሊት ወገቤ አያርፍ እግሬ አይገጠም ጧት በግድ ተነስቸ ያዘጋጀሁትን ቁርስ ቀመስ አድርጎ ይተውና ወደመደቡ መጎተት ነው ….ውሃ ቀድቸ ስመለስ እንስራየን አውርዶ ወዲያ ይወረውርና ‹ያዥ እንግዲህ › ነው … አልቻልኩም በዛብኝ ምነው ሸዋ ! ›› አለችና ሽማግሌወቹ ፊት አለቀሰች ! ሽማግሌወቹም ችግሯን ስለተረዱ እዛው ተቀምጦ ጉዱን የሚሰማውን ባሏን ጠሩና መከሩት
‹‹አባተ ››
‹‹አቤት አባቶቸ ›› አለ እየተቅለሰለሰ
‹‹እንግዲህ የተባለውን ሰምተሃል እውነት ነው ሃሰት ? ››
‹‹ኧረ ሃቅ ነው አባቶቸ ….›› ሲል አመነ
‹‹ ጥሩ እንግዲህ ጥፋት አይተንብሃል በል አሁን የምንመክርህን ስማ ›› አሉና ሽማግሌወቹ ተመካክረው በአንድ ወግ አዋቂ ሽማግሌ በኩል እንዲህ አሉት
‹‹ እንግዲህ አባተ <እንትን > እንደሆነ ዝም ብለው ቢውሉበት ቁርስ አይሆን ምሳ ርስት አይሆን ሃብት …. እየናፈቀ ሲገኝ ነው ደጉ …ይሄው አረጀንበት ከልጅነት እስከእውቀት ኖርንበት እሱ እንደሆን እያደር አዲስ ነው ከምን እንደሰራው አንድየ ይወቀው …..እና አሁንም አንተም ሚስትህን አንሻን እንዳታማርራት በ ‹ፈሮግራም › እንዲሆን ወስነንበሃል ›› ሲሉ አስረዱ
‹‹ እሽ አባቶቸ እንዳላችሁ ….ግ…..ን ‹ፈሮግራሙ› እንዴት እንዴት ነው ›› አለ አባተ
‹‹ እንግዲህ ፈሮግራሙ እንዲህ ነው …. ቀን ቀን እቤት ድርሽ ሳትል እርሻላህ ላይ ትውልና ማታ ጀምበር ሲያዘቀዝቅ ከብቶችህን አስገብተህ ስታበቃ አንሾም ናፍቃህ ትውል የለም …..አንደዜ ! ….ደሞ ራት ተተበላ በኋላ ኩራዝ ጠፍቶ ጋደም ስትሉ ….አንደዜ ! ወደንጋጋቱ ላይ ዶሮ ሲጮህ ደሞ አንደዜ ! ሶስት ሃቅህ ነው !›› አሉት
አባተ ቅር እያለው እንዲህ አለ ‹‹ እንደ…..ው ኣባቶቸ ምክራችሁ ጥሩ ነበር ግ…..ን እነደው …. ለጠራራውም ለውሃ ጥሙም ቀን ላይ አንደዜ ብትጨምሩልኝ ›› ሲል ጠየቀ
አንሾ በተራዋ ‹‹ የዶሮ ጩኸቱን ብታነሱልኝ ምናለ …. ሁለቴ ካገኘ ምን አነሰው ›› ስትል ቅሬታዋን አቀረበች ! ሽማግሌወቹ ግራ ቀኙን አድምጠው ‹‹ አንሾ አንችም አትሰስች ….አንተም ከ ‹ፈሮግራምህ› ውልፍት የለም ! ከተሜው ሁሉ እንዲሁ ነው የሚያረግ ›› አሉና በውሳኔያቸው ፀኑ !
አንሾና አባተም እርቅ አውርደው ወደቤታቸው ሄዱ ! ልክ እቤታቸው ሲደርሱ ጀምበር አዘቅዝቆ ስለነበር አባተ እየተጣደፈ አንሾን ወደመደቡ ጎተታት …. አንሾም ተጣልተው ስለቆዩ ናፍቋት ስለነበር አልከፋትም ኧረ እንደውም ደስ አላት !
‹‹ አንድ በል ቁጥር እነዳትስት ›› አለች ቀሚሷን እያጠለቀች ! አፍታ ሳይቆይ አባተ አንሾ አማረችው ! አለፍ ስትል ሳብ አደረገና እነሆ ! ሁለት ! ገና እራት ሳይቀርብ አንሾ ጉድ ጉድ ስትል ጠይም ፊቷ በምድጃው እሳት ወጋገን ወርቅ መስሎ ታየው አባተ አላስችል አለው በቃ ሳብ አደረጋና ሶስተኛውን ሃቁን አነሳ !
እራት ቀርቦ በሉና ጋደም እንዳሉ አባተ የአንሾ አርቲ እና አሽኩቲ ጠረን አቅሉን ነሳው ! ሽማግሌወች የወሰኑለትን ኮታ ደግሞ ጨርሷል እናም በጨለማው ውስጥ ቀስ ብሎ እንዲህ አለ ‹‹አንሾ ››
‹‹ምን ፈለክ…..የዛሬውን ድርሻ ሶስትህን ጨርስሃል ነገር ትፈልገኝና ውርድ ከራሴ ›› አለች አንሾ በቁጣ
‹‹ እንደው አፈር ትሆንልሽ …..ተነገው አንድ አበድሪኝ አንሾዋ ›› አላት ያልሆነ ቦታ እየደባበሳት .....አንሾ አሰብ አደረገች እሽ እንዳትል ኩራቷ ያዛት እምቢ እንዳትል የአባተ እጅ ቀልቧን ወስዶታል እናም እንዲህ አለች ‹‹ ምን የነገውን አበዳደረህ የትላንቱስ ሶስቱ መች ተነካ ›› ትላንት ተጣልተው አብረው አላደሩም !!
ወደቁም ነገራችን ስንመለስ በባልና በሚስት እንዲሁም በፍቅረኞች መሃል ለሚፈጠሩ ችግሮች መፍትሄው ሶስተኛ ወገን ሳይሆን ፍቅር ራሱ ነው #ፍቅር_ብቻ !!!!
👍3
#ብሌን 🇪🇹
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በዮርዳኖስ
"እና መጀመሪያ ምንድነው ምንገዛው?" አለችኝ።ገበያ ደርሰን ነበር ገበያው ያን ያህል አልደራም ቢሆንም በቂ ሱቆች ተከፍተዋል።"አንቺ የፈለግሽውን" አልኳት
"እንደዛ ከሆነ ነይ በዚ እንቁላል እና ወተት አንግዛ"
በአትክልት ተራው አልፈን ወደ እህል ተራ በሚወስደው መንገድ ስንደርስ በአንደኛው መታጠፊያ ይዛኝ ገባች።ወደ ትልቁ የገበያ አዳራሽ ማዕክል እና የቤት እቃዎች በመሸጫዎች መሀል አቋርጠን እዛው ወዳለው ወደ ወተት ተራው ገባን።"ደንበኛዬ አልመጣችም በዛ ላይ ሀይላንድ ያስፈልገኛል መጣው እዚሁ ጠብቂኝ"ብላኝ ሔደች ትኩረቴ እሷ ጋር ስላልነበረ ግድ አልሰጠኝም ነበር።ግራና ቀኙን መቃኘት ጀመርኩ አንዳንድ እቃው ባለሱቆች ገና ከፍተው እቃ በማውጣጣት ላይ ሲሆኑ አብዛኛው ጨርሶ ቁጭ ብሏል።የማውቀውን ሰው ፍለጋ ይመስል ሁሉንም እያስተዋልኩ አያለው።
"ኧረ እማ እንሒድ በቃ ለኔኮ ጫማ አልገዛንም..."
"አይ የልጅ ነገር በቃ ከራስህ ውጪ አታስብም አይደል መጀመሪያ የምንበላውን ልገዛ እስኪ" እናትና ልጅ ትኩረቴን ስለሳቡኝ እሰማቸው ጀመር።
"ገና እኮ ጠዋት ነው ማሙሽ ሱቁም በደንብ ይከፈት እናትህን አታስቸግራት እንጂ" ሌላኛዋ ሴት እንቁላል ለእናትየው እያቀበለቻት የእንቁላል ነጋዴ ነች።
"እሺ እዛጋ ያንን"ህፃኑ ለናቱ እየጠቆማት እድሜው በግምት ወደ ሰባትና ስምንት የሚጠጋ ይመስላል።
"ምን የቱ ጋር?" አለች እናቱ።እኔም ጥቆማውን ተከትዬ አይኔን ጣልኩ
"ምንድ ነው እሱ አትናገርም እንዴ?" እናትየው የታያት አይመስልም እኔ ግን በትክክል አይቼዋለው የልጁ እሳቤ ቀድም የነገረኝ ይመስል ተረድቼዋለው።በቀስታ ወዳየሁት ነገር መራመድ ጀመርኩ።
"ያውና ሰው የሚታረድበት ነገር እኮ ነው!!"
"ምን.... ?በስመአብ በወልድ በመንፈስቅዱስ!!"
እናትየው እንቁላሉን ስትለቅ ይሰማኛል።እግሬ አየተንቀጠቀጠ ቀረብኩ በቁጥር በዛ ያሉ ስለታቸወና አዲስነታቸው ከሩቅ የሚያብለጨልጭ ባንጋዎች ናቸው ሰውነቴን አየሰቀጠጠኝ አጠገቡ ቆሜ ወደታች አየውት።
"ደሞ ኬት አመጣኸው ይሄንን? ሁለተኛ አንደዚ እንዳትል እሺ አባቴ ሁለተኛ!! ና ከዚ እንሒድ"የናትየው ድንጋጤ ከድምጿ ቃና ይታወቀኛል።የሷ ብቻ አይደለም እኔም ፍርሀቴ ሲጀምረኝ እና ወደነዛ ቀናት በትውስታ የተመለስኩ ሲመስለኝ ይተወቀኛል። ህፃኑ ያለው በአይምሮዬ ተስሎ ታየኝ።
ይሄ ነው እንግዲ የማንነት የትውልድ ኪሳራ፣ ይሄ ነው እንግዲ አዲሱ ለትውልድ የምናስተላልፈው ታሪክ እና ገድላችን ፣ይሄ ነው እንግዲ ሰውነት ከእንስሳነትም ከእቃነትም ተራ አልፎ የረከሰበትና የቀለለበት ዘመንና ትውልድ ፤ይሄ ነው የማንነት ክስረት። ይሄንን የማንነት ውደቀታችን ነው በታናናሾቻችንና በልጆቻችን አይምሮ እየሞላንና እየቀረፅን ያለነው።
"ጉድ እኮ ነው አንቺ ይሄ ህፃን እንኳ እንዲ ይናገር....አጃኢብ!!!
"ሰማሽ አይደል ለነገሩ ምን ያድርግ በሱም አይፈረድም።እነሱስ ቢሆኑ ሰው እንደዚ በተጨካከነበትና በሚጨራረስበት ወቅት እንደዚ በሰፊው ይሄን መነገዳቸው ምን ማለታቸው ነው? እንዲያው ሲያዮት እንኳ አንዴት ይዘገንናል!"።
"ሔዊ ምነው" ደንዝዤ ከቆምኩበት የቡርቴ ጥሪ ከኋላዬ ተሰማኝ።"እንዴ እያለቀሽ ነው እንዴ ሔዋን ምነው የኔ ወድ?"
የተናነቀኝን እንባ እያየች።ግን የድንጋጤ እና የፍረሀት ወይም
የሀዘን እንባ አልነበረም ቁጭትና እልህ እና ንዴት እንጂ።
"የኔ ጥፋት ነው ይዤሽ መውጣትም ሆነ ብቻሽን መተው አልነበረብኝም"እንባዬን አየጠረገች።
"ቡርቴ..?"አልኳት"ሁለቱን ሳምንት ታግቼ ነበር አይደል? ለነገሩ እሱ በጣም ግልፅ ነው ደሞም ይሄንን አባቴም ሆነ አንቺም በደንብ ታውቃላቹ!!
"ምን...? ለምንድነው እንደዚ የምትይው ነይ ከዚ አንሂድ መዳኒትሽን መውሰድ አለብሽ..."እጄን ይዛ ጎተተችኝ።
"አይ አይሆንም ለቀቂኝ!"እጄን አስለቀኳት
"አቁሚ በጭራሽ አልሄድም አሁን ባልሺኝ መሰረት የምጠይቅሽን እሺ በማለት ታደረጊያለሽ!"ጥያቄ ሳይሆን ትዕዛዝ ነበር።
#ሕዳር 20/12 ቀን የታገቱ ተማሪዎች እስካሁን ድምፃቸው አልተሰማም።
ይላል ሙሉ ዜናውን ለማግኘት ፔጁን ተቀላቀልኩ።
January 24
#ከ 35 ሺህ በላይ ተማሪዎች ቤታቸው ናቸው።በአንዳንድ የሀገሪቱ ዮኒቨርስቲዎች ውስጥ በተፈጠረው የፀጥታ ችግር ምክንያት መደበኛ ት/ታቸውን አቋርጠው የተመለሱ ተማሪዎች ወደ ትም/ት ገበታቸው አልተመለሱም።
#የኢትዮጵያ የሳይንስና የከፍተኛ ት/ት ሚኒስተር በ22ቱ ዮኒቨርስቲዎች ባካሄደው ምርመራ እና ቅኝት በግማሽ መንፈቅ ዓመት ብቻ የ12 ተማሪዎች ሕይወት ማለፉ ተገልጿል።
=> ታህሳስ 27
ሌሎች የታገቱ ተማሪዎች እንዳሉና ቁጥራቸውም 4 እንደሚደርስ የክልሉ ርዕሰ መስተዳዶር በጋዜጣዊ መግለጫ የገለፁበት ቀን
#በሕዳር 20/12 ስለታገቱ ተማሪዎች የጠቅላይ ሚንስተሩ ፅ/ቤት የፕሬስ ሴክሬተርያት በሰጡት መግለጫ፦አጠቃላይ 27 ተማሪዎች ታግተው እንደነበረና 21ዱ መለቀቃቸው 6ቱ ደግሞ ታግተው እንዳሉ ገልፀዋል።የሚልና ሌሎች ተመሳሳይ የወጡ ዜናዎችን በብዛት ካየሁ ቡሗላ
አሁን ሁሉም በግልፅ የገባኝ መሰለኝ።
የሰጠሗትን ትዕዛዝ ላለመቀበል ጋሼ ቢጠየቁኝስ ምን እላቸዋለው?"ነበር ያለችኝ እኔም
ቃል በገባሁላት መሰረት አባቴ ሳይመለስ ቀድሜ ቤት ለመገኘት ከሷ እንደተለየው ጊዜ ሳላባክን ወደ ኢንተርኔት ቤት ነበር ያመራሁት።እና የምፈልገውን ካየው ቡሗላ ቶሎ እሷ ጋር መሄድ ስለነበረብኝ ባጃጅ አስቁሜ ገባው ውስጤ ብዙ ሀሳብ ይመላለሳል ግን የትኛውን በትክክል መስማት እንዳለብኝ እንጃ። እስካሁን ምንም ባለማወቄ እና በዝምታዬ የተሞኘውም መሰለኝ
ሀገሪቱ ላይ የሚካሄደውና የሰው ሁኔታ ግን ግርምትን የሚያጭር ነው። ምንም እንዳልተፈጠረ መኖራችን አስገርሞኛል። ለምሳሌ ያለሁበት ባጃጅ ሹፌር ዕድሜው ከኔው ጋር ተመሳሳይ ነው። እርግጠኛ ነኝ በነዛ ወጣቶች ላይ የተፈጠረውን/ይቅርታ በኛ ላይ ልበል እንጂ ስለተፈጠረውና ስለተፈፀመው ድርጊት በሚገባ ሰምቷል።እና ናላ በሚያዞር ምንነቱ በማይገባ ዘፈን ባጃጁን መጓጓዣ ሳይሆን ክለብ አስመስሎ እስከቂጡ ከፍቶ ባጃጇን እንደ አየር ያከንፋታል። ተማሪዎች ከየት/ት ቤታቸው ተለቀው በተለያየ ዮኒፎርማቸው ሲተራመሱ ይታያሉ። ይሄን ሁሉ ጊዜ ቤት መጥቼ ቁጭ ስልም ሆነ ስወጣ ማንም ሰው ስለነዛ ልጆች ሲያወራ ና ሲያነሳ አጋጥሞኝ አለማወቁም የማይታመን ነው
ሚድያዎቻችንም ቢሆኑ
ከምንም በላይ ያስገረመኝ ግን የራሴው አባት ነው።ምንም ያሀል ልጁን የሚወድ አባት ሊሆን ይችላል ግን ደሞ ይሄ ትልቅ ራስ ወዳድነት ይመስለኛል።ስለኔ ብቻ ሳይሆን የሌሎቹም ነብስና መጨረሻ ሊያሳስበው ይገባ ነበር።
ለማንኛውም ግን ማወቄንም ሆነ ማስታወሴን በድብቅ ለመያዝ እና ለመቀጠል ወስኛለው ምክንያቱም ማንኛውም ወላጅ ቢሆን ለጁ እንዲያደርግ እማይፈልገውን ነገር ለማድረግ ስለወሰንኩ ነው።በርግጥ አንደማንኛውም ሰባዊ ሰው ሲታይ ልክ የሆነና ተገቢ ድርጊት ሊሆን ይችላል።እንደ ወላጅ ግን አይደለም!
" ደርሳሻል እናት"አለኝ ወጣቱ ባለባጃጅ ድምፁን ከፍ አድርጓ፤ እስኪ ምናለበት ከመጮህ ዘፈኑን ቢቀንሰው ያለኝን ብር ከፍዬ በፍጥነት ወደቤት ገባው።አባቴ ገና አልመምጣቱ ካረጋገጥኩ ቡሗላ ወደ ቡርቴ ሮጥኩ
"ውይ ተመስገን ለትንሽ ነው የደረሽው"አለችኝ
"ቡርቴ..?"
"እ...?"
"ብሌንስ...??"ውስጤ ሲመላለስ የነበረውን ጥያቄ ጠየኳት።
፡
፡
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየታችሁ እንዲሁም ማስተካከል ያለባት ነገር በ @yemirtwutet ላኩላት
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በዮርዳኖስ
"እና መጀመሪያ ምንድነው ምንገዛው?" አለችኝ።ገበያ ደርሰን ነበር ገበያው ያን ያህል አልደራም ቢሆንም በቂ ሱቆች ተከፍተዋል።"አንቺ የፈለግሽውን" አልኳት
"እንደዛ ከሆነ ነይ በዚ እንቁላል እና ወተት አንግዛ"
በአትክልት ተራው አልፈን ወደ እህል ተራ በሚወስደው መንገድ ስንደርስ በአንደኛው መታጠፊያ ይዛኝ ገባች።ወደ ትልቁ የገበያ አዳራሽ ማዕክል እና የቤት እቃዎች በመሸጫዎች መሀል አቋርጠን እዛው ወዳለው ወደ ወተት ተራው ገባን።"ደንበኛዬ አልመጣችም በዛ ላይ ሀይላንድ ያስፈልገኛል መጣው እዚሁ ጠብቂኝ"ብላኝ ሔደች ትኩረቴ እሷ ጋር ስላልነበረ ግድ አልሰጠኝም ነበር።ግራና ቀኙን መቃኘት ጀመርኩ አንዳንድ እቃው ባለሱቆች ገና ከፍተው እቃ በማውጣጣት ላይ ሲሆኑ አብዛኛው ጨርሶ ቁጭ ብሏል።የማውቀውን ሰው ፍለጋ ይመስል ሁሉንም እያስተዋልኩ አያለው።
"ኧረ እማ እንሒድ በቃ ለኔኮ ጫማ አልገዛንም..."
"አይ የልጅ ነገር በቃ ከራስህ ውጪ አታስብም አይደል መጀመሪያ የምንበላውን ልገዛ እስኪ" እናትና ልጅ ትኩረቴን ስለሳቡኝ እሰማቸው ጀመር።
"ገና እኮ ጠዋት ነው ማሙሽ ሱቁም በደንብ ይከፈት እናትህን አታስቸግራት እንጂ" ሌላኛዋ ሴት እንቁላል ለእናትየው እያቀበለቻት የእንቁላል ነጋዴ ነች።
"እሺ እዛጋ ያንን"ህፃኑ ለናቱ እየጠቆማት እድሜው በግምት ወደ ሰባትና ስምንት የሚጠጋ ይመስላል።
"ምን የቱ ጋር?" አለች እናቱ።እኔም ጥቆማውን ተከትዬ አይኔን ጣልኩ
"ምንድ ነው እሱ አትናገርም እንዴ?" እናትየው የታያት አይመስልም እኔ ግን በትክክል አይቼዋለው የልጁ እሳቤ ቀድም የነገረኝ ይመስል ተረድቼዋለው።በቀስታ ወዳየሁት ነገር መራመድ ጀመርኩ።
"ያውና ሰው የሚታረድበት ነገር እኮ ነው!!"
"ምን.... ?በስመአብ በወልድ በመንፈስቅዱስ!!"
እናትየው እንቁላሉን ስትለቅ ይሰማኛል።እግሬ አየተንቀጠቀጠ ቀረብኩ በቁጥር በዛ ያሉ ስለታቸወና አዲስነታቸው ከሩቅ የሚያብለጨልጭ ባንጋዎች ናቸው ሰውነቴን አየሰቀጠጠኝ አጠገቡ ቆሜ ወደታች አየውት።
"ደሞ ኬት አመጣኸው ይሄንን? ሁለተኛ አንደዚ እንዳትል እሺ አባቴ ሁለተኛ!! ና ከዚ እንሒድ"የናትየው ድንጋጤ ከድምጿ ቃና ይታወቀኛል።የሷ ብቻ አይደለም እኔም ፍርሀቴ ሲጀምረኝ እና ወደነዛ ቀናት በትውስታ የተመለስኩ ሲመስለኝ ይተወቀኛል። ህፃኑ ያለው በአይምሮዬ ተስሎ ታየኝ።
ይሄ ነው እንግዲ የማንነት የትውልድ ኪሳራ፣ ይሄ ነው እንግዲ አዲሱ ለትውልድ የምናስተላልፈው ታሪክ እና ገድላችን ፣ይሄ ነው እንግዲ ሰውነት ከእንስሳነትም ከእቃነትም ተራ አልፎ የረከሰበትና የቀለለበት ዘመንና ትውልድ ፤ይሄ ነው የማንነት ክስረት። ይሄንን የማንነት ውደቀታችን ነው በታናናሾቻችንና በልጆቻችን አይምሮ እየሞላንና እየቀረፅን ያለነው።
"ጉድ እኮ ነው አንቺ ይሄ ህፃን እንኳ እንዲ ይናገር....አጃኢብ!!!
"ሰማሽ አይደል ለነገሩ ምን ያድርግ በሱም አይፈረድም።እነሱስ ቢሆኑ ሰው እንደዚ በተጨካከነበትና በሚጨራረስበት ወቅት እንደዚ በሰፊው ይሄን መነገዳቸው ምን ማለታቸው ነው? እንዲያው ሲያዮት እንኳ አንዴት ይዘገንናል!"።
"ሔዊ ምነው" ደንዝዤ ከቆምኩበት የቡርቴ ጥሪ ከኋላዬ ተሰማኝ።"እንዴ እያለቀሽ ነው እንዴ ሔዋን ምነው የኔ ወድ?"
የተናነቀኝን እንባ እያየች።ግን የድንጋጤ እና የፍረሀት ወይም
የሀዘን እንባ አልነበረም ቁጭትና እልህ እና ንዴት እንጂ።
"የኔ ጥፋት ነው ይዤሽ መውጣትም ሆነ ብቻሽን መተው አልነበረብኝም"እንባዬን አየጠረገች።
"ቡርቴ..?"አልኳት"ሁለቱን ሳምንት ታግቼ ነበር አይደል? ለነገሩ እሱ በጣም ግልፅ ነው ደሞም ይሄንን አባቴም ሆነ አንቺም በደንብ ታውቃላቹ!!
"ምን...? ለምንድነው እንደዚ የምትይው ነይ ከዚ አንሂድ መዳኒትሽን መውሰድ አለብሽ..."እጄን ይዛ ጎተተችኝ።
"አይ አይሆንም ለቀቂኝ!"እጄን አስለቀኳት
"አቁሚ በጭራሽ አልሄድም አሁን ባልሺኝ መሰረት የምጠይቅሽን እሺ በማለት ታደረጊያለሽ!"ጥያቄ ሳይሆን ትዕዛዝ ነበር።
#ሕዳር 20/12 ቀን የታገቱ ተማሪዎች እስካሁን ድምፃቸው አልተሰማም።
ይላል ሙሉ ዜናውን ለማግኘት ፔጁን ተቀላቀልኩ።
January 24
#ከ 35 ሺህ በላይ ተማሪዎች ቤታቸው ናቸው።በአንዳንድ የሀገሪቱ ዮኒቨርስቲዎች ውስጥ በተፈጠረው የፀጥታ ችግር ምክንያት መደበኛ ት/ታቸውን አቋርጠው የተመለሱ ተማሪዎች ወደ ትም/ት ገበታቸው አልተመለሱም።
#የኢትዮጵያ የሳይንስና የከፍተኛ ት/ት ሚኒስተር በ22ቱ ዮኒቨርስቲዎች ባካሄደው ምርመራ እና ቅኝት በግማሽ መንፈቅ ዓመት ብቻ የ12 ተማሪዎች ሕይወት ማለፉ ተገልጿል።
=> ታህሳስ 27
ሌሎች የታገቱ ተማሪዎች እንዳሉና ቁጥራቸውም 4 እንደሚደርስ የክልሉ ርዕሰ መስተዳዶር በጋዜጣዊ መግለጫ የገለፁበት ቀን
#በሕዳር 20/12 ስለታገቱ ተማሪዎች የጠቅላይ ሚንስተሩ ፅ/ቤት የፕሬስ ሴክሬተርያት በሰጡት መግለጫ፦አጠቃላይ 27 ተማሪዎች ታግተው እንደነበረና 21ዱ መለቀቃቸው 6ቱ ደግሞ ታግተው እንዳሉ ገልፀዋል።የሚልና ሌሎች ተመሳሳይ የወጡ ዜናዎችን በብዛት ካየሁ ቡሗላ
አሁን ሁሉም በግልፅ የገባኝ መሰለኝ።
የሰጠሗትን ትዕዛዝ ላለመቀበል ጋሼ ቢጠየቁኝስ ምን እላቸዋለው?"ነበር ያለችኝ እኔም
ቃል በገባሁላት መሰረት አባቴ ሳይመለስ ቀድሜ ቤት ለመገኘት ከሷ እንደተለየው ጊዜ ሳላባክን ወደ ኢንተርኔት ቤት ነበር ያመራሁት።እና የምፈልገውን ካየው ቡሗላ ቶሎ እሷ ጋር መሄድ ስለነበረብኝ ባጃጅ አስቁሜ ገባው ውስጤ ብዙ ሀሳብ ይመላለሳል ግን የትኛውን በትክክል መስማት እንዳለብኝ እንጃ። እስካሁን ምንም ባለማወቄ እና በዝምታዬ የተሞኘውም መሰለኝ
ሀገሪቱ ላይ የሚካሄደውና የሰው ሁኔታ ግን ግርምትን የሚያጭር ነው። ምንም እንዳልተፈጠረ መኖራችን አስገርሞኛል። ለምሳሌ ያለሁበት ባጃጅ ሹፌር ዕድሜው ከኔው ጋር ተመሳሳይ ነው። እርግጠኛ ነኝ በነዛ ወጣቶች ላይ የተፈጠረውን/ይቅርታ በኛ ላይ ልበል እንጂ ስለተፈጠረውና ስለተፈፀመው ድርጊት በሚገባ ሰምቷል።እና ናላ በሚያዞር ምንነቱ በማይገባ ዘፈን ባጃጁን መጓጓዣ ሳይሆን ክለብ አስመስሎ እስከቂጡ ከፍቶ ባጃጇን እንደ አየር ያከንፋታል። ተማሪዎች ከየት/ት ቤታቸው ተለቀው በተለያየ ዮኒፎርማቸው ሲተራመሱ ይታያሉ። ይሄን ሁሉ ጊዜ ቤት መጥቼ ቁጭ ስልም ሆነ ስወጣ ማንም ሰው ስለነዛ ልጆች ሲያወራ ና ሲያነሳ አጋጥሞኝ አለማወቁም የማይታመን ነው
ሚድያዎቻችንም ቢሆኑ
ከምንም በላይ ያስገረመኝ ግን የራሴው አባት ነው።ምንም ያሀል ልጁን የሚወድ አባት ሊሆን ይችላል ግን ደሞ ይሄ ትልቅ ራስ ወዳድነት ይመስለኛል።ስለኔ ብቻ ሳይሆን የሌሎቹም ነብስና መጨረሻ ሊያሳስበው ይገባ ነበር።
ለማንኛውም ግን ማወቄንም ሆነ ማስታወሴን በድብቅ ለመያዝ እና ለመቀጠል ወስኛለው ምክንያቱም ማንኛውም ወላጅ ቢሆን ለጁ እንዲያደርግ እማይፈልገውን ነገር ለማድረግ ስለወሰንኩ ነው።በርግጥ አንደማንኛውም ሰባዊ ሰው ሲታይ ልክ የሆነና ተገቢ ድርጊት ሊሆን ይችላል።እንደ ወላጅ ግን አይደለም!
" ደርሳሻል እናት"አለኝ ወጣቱ ባለባጃጅ ድምፁን ከፍ አድርጓ፤ እስኪ ምናለበት ከመጮህ ዘፈኑን ቢቀንሰው ያለኝን ብር ከፍዬ በፍጥነት ወደቤት ገባው።አባቴ ገና አልመምጣቱ ካረጋገጥኩ ቡሗላ ወደ ቡርቴ ሮጥኩ
"ውይ ተመስገን ለትንሽ ነው የደረሽው"አለችኝ
"ቡርቴ..?"
"እ...?"
"ብሌንስ...??"ውስጤ ሲመላለስ የነበረውን ጥያቄ ጠየኳት።
፡
፡
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየታችሁ እንዲሁም ማስተካከል ያለባት ነገር በ @yemirtwutet ላኩላት
❤1👍1