#ባርቾ
:
:
#በሕይወት_እምሻው
በ12 ዓመቴ...ስቅስቅ ብዬ» አልቅሼ ስጨርስ ፣ በለቅሶ ይባስ የጠቋቆረ ጥቁር ፊቴን በቀኝ እጄ አይበሉባ እያሻሸሁ ወደ ቤት ስገባ ፣ እማዬን በር ላይ አገኘኋት: :
“ምን፣ ሆንሽ ባርቾ? ... ምነው?”
“ምንም! ” አልኳት ፡ : የደረሰብኝ ነገር ደግሞ ማውራቱ ይበልጥ የሚ ያስለቅሰኝ መስኰ ስለተሰማኝ : :
“ምን... ምንም ትይኛለሽ? ስታለቅሺ አልነበርም?” እማማ ተቆጣች ፡ :
“ትምህርት፥ ቤት ...” አልኩ አልቅሼ የጨረስኩት የመሰኝ እንባዬ እንደ
አዲስ ዐይኔ ውስጥ ሲሞላ እየተሰማኝ ፡ :
“ምን ሆንሽ .. ? ከማን ጋር ተጣካሽ?”
“አማርኛ አስተማሪ ... ቲቸር ስንሻው ...”
“ገረፈሽ ...? ጎሽ! የቤት ሥራ ሳትሰሪ ሄደሽ ገርፎሽ ነው አይደለም?
ደግ አደረገ፡”
“አይደለም አረ... እኔ የቤት ስራዬን ሰርቻለሁ ...”
አህስ... ስትርብሺ ዐይቶሽ ነው አይደለም? እያስተማረ ስቶረብሺ? ነይ
እንዲውም እኔም እጨምርልሻለሁ!” አለች እማዬ ቱግ እያለች ፡ :
አሁን ቀበቶ ፍለጋ ወደ ጎዳ ስትገባ ዐየሁና ጮክ ብዬ፣ አይደለም
እማዬ... እግዚአብሔርን፣... የገና ድራማ አትሠሪም ብሎኝ ነው አልኳት ፣ ስር ስሯ እየተከተልኳት።
ቀበቶውን፣ መፈለጓን ትታ ዞር ብላ አየችኝና ፣ “የገና ምን... ምን አትይም
ብሎኝ ነው? ” ብላ ጠየቀችኝ : :
“የገና ድራማ አትሰሪም ብሎኝ ነው እማዬ” አልኳት : :
ምንድነው ደግሞ የገና ድራማ?”
ባለፈው... ለገና በዓል የክርስቶስ፣ መወለድ በድራማ ትሰራላኝሁ ተብለናል ብዬ ከብሩኬ ጋር ሳጠና አልነበረም እማዬ?”
"ያ ... ሁሉንም በቃሌ መያዝ አለብኝ ስትይው የነበረው ነው እሱ? ”
“አዎ... እማዬ: :
“ታዲያ ፈቅዶልሽ አይደለም እንዴ አጥኚ የተባልሽው?”
“አዎ... እማዬ” አልኳት ፣ እንባዬ ሲመለስ እየተሰማኝ : :
“እና ታዲያ ምንድነው አትሰሪም ያለሽ አሁን?”
“አትሰሪም አትሰሪም አይደለም እኮ ያለኝ ” አልኩ ለቅሶዬን ጀምሬ : :
“ልጅቷ ያማታል እንዴ ...? ምንድነው የምትቀባጥሪው? አትሰሪም አለኝ
አላልሽም አሁን?” አለች እማዬ ቁጣዋ ተመልሶ : :
እኔ የፈለኩት እመቤቴ ማርያምን፣ ሆኜ መስራት ነበር ፡ : ሳጠና የነበረው እኮ የእመቤቴ ማርያምን፣ ነው ... እሱ ግን...
“እሱ ግን…? ምን አለሽ ታድያ ? ”
“እሱ ግን ቲቸሮች ሁኑ ተነጋግረንበት ነበር : :አንቺ በደንብ ብታጠኚውም ጥቁር ስለሆንሽ ማርያምን፣ ሆነሽ መስራት አትችይም : :
ሩት ናት ማርያምን የምትሆነው አለ” ብዬ ለቅሶዬን በነጻነት አድምቄ ጀመርኩት ፡ :
እማዬ ካሁን አሁን ተሰምቷት መጥታ እቅፍ ታደርገኝና ፣ እምባዬን ታብሰውና ፣
የሚይረባ! የኔ ልጅ ናት ማርያምን፤ ሆና የማትሰራው?
ነገውኑ ከአባትሽ ጋር ሄደን ለዲሪክተሩ ነገርነ ነው የምናስባርረው... አይዞሽ
ልጄ” ትለኛለች ብዬ ስጠብቅ ፣
“እውነቱን ነዋ! እስቲ የእመቤቴን ምስል
ዕይው! ምኗ ነው ከቶ አንቺን የሚመስል? አስተማሪሽ የሚልሽን፣ ስሚ ! ልክ ነው!” ብላ፤ ወደ ኩሽና ገባች: :
የዛን ዕለት እመቤቴ ማርያምን፣ ሆኜ ለመጫወት የነበረኝን ጉጉት ባጭር
የቀጩትን “ቲቸሮቼን፡” ፣ ድራማውን፤ በማጥናት ከእሷ 0ሥር እጅ
ብሻልም ቀይና ሰልካካ ስለሆነች ብቻ ማርያምን ሁኚ ተብላ የተመረጠችውን፣
ሩትን፣ ካልጠፋ ቕላት ጥቁር አድርጎ የፈጠረኝን፣ ፈጣሪንም በአንድነት
አማረርኩ ፡ :
ምሽት ላይ ፤ እኔ ፣ ትልቋ እና ቀይዋ እህቴ ፣ ቀዩ ወንድሜ ፣ ጠይሙ አባቴና በጣም ቀይዋ እናቴ ተሰብስበን ቴሌቪዥን እናያለን። ለነገሩ ቴሌቪዥኑን የሚያዩት እነሱ እንጂ እኔ የማየው እነሱንና ቅላታቸውን፣ ነው : : እያየኋቸው እናደሚከተለው አሰባለሁ ፣
...እስቲ አሁን በእመቤቴ ፣ እኔ ከየት መጥቼ ጠቆርኩ? አባቴ ጠይም
ነው ፤ እናቴ በጣም ቀይ ናት ፡ : ሁለቱ ሲቀላቀሉ እንደ እህቴ ስህንና እንደ ወንድሜ ብሩክ ቀይ ሰው ባይፈጥሩ እንኳን እንደኔ ጠቋራ ሰው መፍጠር ነበረባቸው? የእህቴስ ይሁን፡ : ሴት ናት : : በዛ ላይ ታላቄ ናት ፡ ይሁንላት ትቅላ ፤ ግን አሁን እኔ ከምጠቁር ወንድሜ ቢጠቁር ምናለበት እስቲ…? ደግሞ እኮ እኔ ብቻ አይደለሁም : :ሁሉም ሰው የሚለው ነገር
ነው : : እማዬ ሁል ጊዜ ብሩክንና እኔን ይዛን ወጣ ስትል ፣
አይ ወይዘሮ ኤልሳቤጥ! ሴቷን ልጅ አጥቁረሽ ቅላትሽን፣ ሁኩ ወንዱ ልጅ
ላይ አባከንሽው! መልክ ለወንድ ልጅ ምን ያደርጋል አሁን? አሄሄ!” ይላሉ
እኔ እንዲህና እንዲያ ሳስብ ቴሌቪዢኑ ላይ ጓድ መንግስቱ ሐይለማርያም
የዛንቢያውን፣ ፕሬዝዳንት ኬኔት ካውንዳን፤ ሲቀበሉ የሚያሳይ ምስል መጣ ፡ :
መንግስቱ ኃይለማርያም ቴሌቪዥን ላይ ፣ በመጣ ቁጥር የሚቀልዱብኝ ቀልድ
እስኪጅምር ጠበቅኩ ፤ “መንጌ እኮ አባትሽ ነው” ሊሉኝ ነው ።ጠበቅኳቸው።
እህቴ ቀደመችና ፣ ይሄውልሽ ሜሮን አጎትሽ አባትሽን ለመጠይቅ አዲስ
አበባ መጣ!” ሁኩም ሣቁ።
እኔ ግን ነጭ መሃረብ እያርገበገበ ከአውሮፕላን የሚወርደውን፣ “አጎቴ፣” ኬኔት ካውንዳን እየያየሁ እግዚአብሔር ከነነጭ መሃረቡ በአውሎ ንፋስ ጥ...ር...ግ አድርጎ ወደ መጣበት ቢመልሰው እቸተመኘሁ ከእንባዬ ተናነቅሁ : : ደግሞ በዚህ ጥቁርቱ ላይ ነጭ መዓርብ የሚይዘው አማረብኝ ብሎ ነው? ...ወይስ ከሩቅ እንዲታይ? አንጀቴን
አሳረረው : :
“ዕያት ... ዕያት ... በሸቀች! በሸቀች” ይላሉ እየተቀባበሉ።
“አትናደጂ! ይባስ ያጠቁርሻል” አለ
ብሩክ ፣ አጠገቤ መጥቶ እየሣቅ ።
የማርያም አጃቢ ሆኜ የገናውን ድራማ በሰራሁ በሁለት ሳምንቴ አስራ ሶስት
ዓመት ሞላኝ : : ሁሌም ለልደቴ እንደምናደርገው ድፎ ዳቦ ዳቦና
ሻማ ፣ ከተወሰኑ የለስላሳ ጠርሙሶች ጋር ይዘን የልደት ፎቶ ልንነሳ ከእማዬ ፣ አባዬ ፣ ስህንና ብሩክ ጋር አስረስ ፎቶ ቤት ሄድን ጋሽ አስርስ ይወደኛል ፤ “ኮረሪማ!” ይለኛል ገና ከሩቅ ሲያየኝ : :
“ኮረሪማ አረጀሽ በቃ! ትልቅ ሰው ... ትልቅ ኮረሪማ” አለኝ፤ ገና ከመግባታችን። ሣቅኹ ።መጣና እቅፍ አድርጎ ከሳመኝ በኋላ ለፎቶው መዘጋጀት ጀመርኩ።
ጋሽ አስርስ ሁሉን ነገር አሰናድቶ ለማንፀሳት ሲያነጣጥር አባቴ ጮክ አለና
“አስረስ ፣ ይህን መጋረጃ ቀይረው እንጂ ” አለው።
“የቱን? ” አለ ጋሽ አስረስ ፣ ካሜራው፣ ከእነ አንትገ ማንጠልጠያው፥
ከፊቱ ወደ ደረቱ፥ እየመለሰ ።
“ከኋላዋ ያለውን ጥቁር መጋርጃ!” አለ አባቴ : :
ኋላ ላይ ሻማው ፣ ጥርሷና ሚሪንዳው ብቻ ይወጣልህና ጉድ እንዳትሆን!” ሲለው ፤ ይወደኝ የመሰለኝ፤ ጋሽ አስረስ ከቀያዮቹ ቤተሰቦቼ ጋር ተደርቦ ሲስቅ ጠላሁት : :
።።።።።
በሃያ ሁለት ዓመቴ...
እንዲህ እንዲህ ሲብስ ሲብስ ፣ “ባርቾ እኮ ጭንቅላት ባይኖራት ጉዷ ነበር!
“አንቺ፤ ግን ሀበሻ ነሽ? ጋና እኮ ነው የምትመስይው!”
.
:
ሲሻል ደግሞ ፣ ብትቀላ ቆንጆ ነበረች፡ : እየተባልኩ፣ በቀያይ ቤተሰቦቼና ዘመዶቼ እየተቀለደብኝ ኖርኩ ፡ : በሃያ ሁለት ዓመቴም የትወና ጥበብ ተምሬ ጨርስኩና የጊዜውን የፊልም ሥራ በርከት ለመቋደስ ብዙ ቦታ ተመዝግቤ መፈተን ጀመርኩ። ከኮሌጅ ሰቅዬ
ነበር የተመረቕኩት ፣ ግን ደህና የፊልምም የቲያትርም የትወና ሥራ ማግኘት አልቻልኩም : : “በጣም አሪፍ ነው ፡ ፡ እናደውልልሻለን። ይሉኝና አይደውሉም።
ሌሎቹ ደግሞ ፣ ለትወና ሥራ አመልክቼ ፣ “ፐ! አንቺ በጣም ጎበዝ ተዋናይ ነሽ... ለምን፣ ማስተማር አትሞክሪም? ” ይሉኝና ያሰናብቱኛል። ነገሩ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ግልጥልጥ ያለልኝ ፤ ታሪኩንና ስክሪፕቱ
:
:
#በሕይወት_እምሻው
በ12 ዓመቴ...ስቅስቅ ብዬ» አልቅሼ ስጨርስ ፣ በለቅሶ ይባስ የጠቋቆረ ጥቁር ፊቴን በቀኝ እጄ አይበሉባ እያሻሸሁ ወደ ቤት ስገባ ፣ እማዬን በር ላይ አገኘኋት: :
“ምን፣ ሆንሽ ባርቾ? ... ምነው?”
“ምንም! ” አልኳት ፡ : የደረሰብኝ ነገር ደግሞ ማውራቱ ይበልጥ የሚ ያስለቅሰኝ መስኰ ስለተሰማኝ : :
“ምን... ምንም ትይኛለሽ? ስታለቅሺ አልነበርም?” እማማ ተቆጣች ፡ :
“ትምህርት፥ ቤት ...” አልኩ አልቅሼ የጨረስኩት የመሰኝ እንባዬ እንደ
አዲስ ዐይኔ ውስጥ ሲሞላ እየተሰማኝ ፡ :
“ምን ሆንሽ .. ? ከማን ጋር ተጣካሽ?”
“አማርኛ አስተማሪ ... ቲቸር ስንሻው ...”
“ገረፈሽ ...? ጎሽ! የቤት ሥራ ሳትሰሪ ሄደሽ ገርፎሽ ነው አይደለም?
ደግ አደረገ፡”
“አይደለም አረ... እኔ የቤት ስራዬን ሰርቻለሁ ...”
አህስ... ስትርብሺ ዐይቶሽ ነው አይደለም? እያስተማረ ስቶረብሺ? ነይ
እንዲውም እኔም እጨምርልሻለሁ!” አለች እማዬ ቱግ እያለች ፡ :
አሁን ቀበቶ ፍለጋ ወደ ጎዳ ስትገባ ዐየሁና ጮክ ብዬ፣ አይደለም
እማዬ... እግዚአብሔርን፣... የገና ድራማ አትሠሪም ብሎኝ ነው አልኳት ፣ ስር ስሯ እየተከተልኳት።
ቀበቶውን፣ መፈለጓን ትታ ዞር ብላ አየችኝና ፣ “የገና ምን... ምን አትይም
ብሎኝ ነው? ” ብላ ጠየቀችኝ : :
“የገና ድራማ አትሰሪም ብሎኝ ነው እማዬ” አልኳት : :
ምንድነው ደግሞ የገና ድራማ?”
ባለፈው... ለገና በዓል የክርስቶስ፣ መወለድ በድራማ ትሰራላኝሁ ተብለናል ብዬ ከብሩኬ ጋር ሳጠና አልነበረም እማዬ?”
"ያ ... ሁሉንም በቃሌ መያዝ አለብኝ ስትይው የነበረው ነው እሱ? ”
“አዎ... እማዬ: :
“ታዲያ ፈቅዶልሽ አይደለም እንዴ አጥኚ የተባልሽው?”
“አዎ... እማዬ” አልኳት ፣ እንባዬ ሲመለስ እየተሰማኝ : :
“እና ታዲያ ምንድነው አትሰሪም ያለሽ አሁን?”
“አትሰሪም አትሰሪም አይደለም እኮ ያለኝ ” አልኩ ለቅሶዬን ጀምሬ : :
“ልጅቷ ያማታል እንዴ ...? ምንድነው የምትቀባጥሪው? አትሰሪም አለኝ
አላልሽም አሁን?” አለች እማዬ ቁጣዋ ተመልሶ : :
እኔ የፈለኩት እመቤቴ ማርያምን፣ ሆኜ መስራት ነበር ፡ : ሳጠና የነበረው እኮ የእመቤቴ ማርያምን፣ ነው ... እሱ ግን...
“እሱ ግን…? ምን አለሽ ታድያ ? ”
“እሱ ግን ቲቸሮች ሁኑ ተነጋግረንበት ነበር : :አንቺ በደንብ ብታጠኚውም ጥቁር ስለሆንሽ ማርያምን፣ ሆነሽ መስራት አትችይም : :
ሩት ናት ማርያምን የምትሆነው አለ” ብዬ ለቅሶዬን በነጻነት አድምቄ ጀመርኩት ፡ :
እማዬ ካሁን አሁን ተሰምቷት መጥታ እቅፍ ታደርገኝና ፣ እምባዬን ታብሰውና ፣
የሚይረባ! የኔ ልጅ ናት ማርያምን፤ ሆና የማትሰራው?
ነገውኑ ከአባትሽ ጋር ሄደን ለዲሪክተሩ ነገርነ ነው የምናስባርረው... አይዞሽ
ልጄ” ትለኛለች ብዬ ስጠብቅ ፣
“እውነቱን ነዋ! እስቲ የእመቤቴን ምስል
ዕይው! ምኗ ነው ከቶ አንቺን የሚመስል? አስተማሪሽ የሚልሽን፣ ስሚ ! ልክ ነው!” ብላ፤ ወደ ኩሽና ገባች: :
የዛን ዕለት እመቤቴ ማርያምን፣ ሆኜ ለመጫወት የነበረኝን ጉጉት ባጭር
የቀጩትን “ቲቸሮቼን፡” ፣ ድራማውን፤ በማጥናት ከእሷ 0ሥር እጅ
ብሻልም ቀይና ሰልካካ ስለሆነች ብቻ ማርያምን ሁኚ ተብላ የተመረጠችውን፣
ሩትን፣ ካልጠፋ ቕላት ጥቁር አድርጎ የፈጠረኝን፣ ፈጣሪንም በአንድነት
አማረርኩ ፡ :
ምሽት ላይ ፤ እኔ ፣ ትልቋ እና ቀይዋ እህቴ ፣ ቀዩ ወንድሜ ፣ ጠይሙ አባቴና በጣም ቀይዋ እናቴ ተሰብስበን ቴሌቪዥን እናያለን። ለነገሩ ቴሌቪዥኑን የሚያዩት እነሱ እንጂ እኔ የማየው እነሱንና ቅላታቸውን፣ ነው : : እያየኋቸው እናደሚከተለው አሰባለሁ ፣
...እስቲ አሁን በእመቤቴ ፣ እኔ ከየት መጥቼ ጠቆርኩ? አባቴ ጠይም
ነው ፤ እናቴ በጣም ቀይ ናት ፡ : ሁለቱ ሲቀላቀሉ እንደ እህቴ ስህንና እንደ ወንድሜ ብሩክ ቀይ ሰው ባይፈጥሩ እንኳን እንደኔ ጠቋራ ሰው መፍጠር ነበረባቸው? የእህቴስ ይሁን፡ : ሴት ናት : : በዛ ላይ ታላቄ ናት ፡ ይሁንላት ትቅላ ፤ ግን አሁን እኔ ከምጠቁር ወንድሜ ቢጠቁር ምናለበት እስቲ…? ደግሞ እኮ እኔ ብቻ አይደለሁም : :ሁሉም ሰው የሚለው ነገር
ነው : : እማዬ ሁል ጊዜ ብሩክንና እኔን ይዛን ወጣ ስትል ፣
አይ ወይዘሮ ኤልሳቤጥ! ሴቷን ልጅ አጥቁረሽ ቅላትሽን፣ ሁኩ ወንዱ ልጅ
ላይ አባከንሽው! መልክ ለወንድ ልጅ ምን ያደርጋል አሁን? አሄሄ!” ይላሉ
እኔ እንዲህና እንዲያ ሳስብ ቴሌቪዢኑ ላይ ጓድ መንግስቱ ሐይለማርያም
የዛንቢያውን፣ ፕሬዝዳንት ኬኔት ካውንዳን፤ ሲቀበሉ የሚያሳይ ምስል መጣ ፡ :
መንግስቱ ኃይለማርያም ቴሌቪዥን ላይ ፣ በመጣ ቁጥር የሚቀልዱብኝ ቀልድ
እስኪጅምር ጠበቅኩ ፤ “መንጌ እኮ አባትሽ ነው” ሊሉኝ ነው ።ጠበቅኳቸው።
እህቴ ቀደመችና ፣ ይሄውልሽ ሜሮን አጎትሽ አባትሽን ለመጠይቅ አዲስ
አበባ መጣ!” ሁኩም ሣቁ።
እኔ ግን ነጭ መሃረብ እያርገበገበ ከአውሮፕላን የሚወርደውን፣ “አጎቴ፣” ኬኔት ካውንዳን እየያየሁ እግዚአብሔር ከነነጭ መሃረቡ በአውሎ ንፋስ ጥ...ር...ግ አድርጎ ወደ መጣበት ቢመልሰው እቸተመኘሁ ከእንባዬ ተናነቅሁ : : ደግሞ በዚህ ጥቁርቱ ላይ ነጭ መዓርብ የሚይዘው አማረብኝ ብሎ ነው? ...ወይስ ከሩቅ እንዲታይ? አንጀቴን
አሳረረው : :
“ዕያት ... ዕያት ... በሸቀች! በሸቀች” ይላሉ እየተቀባበሉ።
“አትናደጂ! ይባስ ያጠቁርሻል” አለ
ብሩክ ፣ አጠገቤ መጥቶ እየሣቅ ።
የማርያም አጃቢ ሆኜ የገናውን ድራማ በሰራሁ በሁለት ሳምንቴ አስራ ሶስት
ዓመት ሞላኝ : : ሁሌም ለልደቴ እንደምናደርገው ድፎ ዳቦ ዳቦና
ሻማ ፣ ከተወሰኑ የለስላሳ ጠርሙሶች ጋር ይዘን የልደት ፎቶ ልንነሳ ከእማዬ ፣ አባዬ ፣ ስህንና ብሩክ ጋር አስረስ ፎቶ ቤት ሄድን ጋሽ አስርስ ይወደኛል ፤ “ኮረሪማ!” ይለኛል ገና ከሩቅ ሲያየኝ : :
“ኮረሪማ አረጀሽ በቃ! ትልቅ ሰው ... ትልቅ ኮረሪማ” አለኝ፤ ገና ከመግባታችን። ሣቅኹ ።መጣና እቅፍ አድርጎ ከሳመኝ በኋላ ለፎቶው መዘጋጀት ጀመርኩ።
ጋሽ አስርስ ሁሉን ነገር አሰናድቶ ለማንፀሳት ሲያነጣጥር አባቴ ጮክ አለና
“አስረስ ፣ ይህን መጋረጃ ቀይረው እንጂ ” አለው።
“የቱን? ” አለ ጋሽ አስረስ ፣ ካሜራው፣ ከእነ አንትገ ማንጠልጠያው፥
ከፊቱ ወደ ደረቱ፥ እየመለሰ ።
“ከኋላዋ ያለውን ጥቁር መጋርጃ!” አለ አባቴ : :
ኋላ ላይ ሻማው ፣ ጥርሷና ሚሪንዳው ብቻ ይወጣልህና ጉድ እንዳትሆን!” ሲለው ፤ ይወደኝ የመሰለኝ፤ ጋሽ አስረስ ከቀያዮቹ ቤተሰቦቼ ጋር ተደርቦ ሲስቅ ጠላሁት : :
።።።።።
በሃያ ሁለት ዓመቴ...
እንዲህ እንዲህ ሲብስ ሲብስ ፣ “ባርቾ እኮ ጭንቅላት ባይኖራት ጉዷ ነበር!
“አንቺ፤ ግን ሀበሻ ነሽ? ጋና እኮ ነው የምትመስይው!”
.
:
ሲሻል ደግሞ ፣ ብትቀላ ቆንጆ ነበረች፡ : እየተባልኩ፣ በቀያይ ቤተሰቦቼና ዘመዶቼ እየተቀለደብኝ ኖርኩ ፡ : በሃያ ሁለት ዓመቴም የትወና ጥበብ ተምሬ ጨርስኩና የጊዜውን የፊልም ሥራ በርከት ለመቋደስ ብዙ ቦታ ተመዝግቤ መፈተን ጀመርኩ። ከኮሌጅ ሰቅዬ
ነበር የተመረቕኩት ፣ ግን ደህና የፊልምም የቲያትርም የትወና ሥራ ማግኘት አልቻልኩም : : “በጣም አሪፍ ነው ፡ ፡ እናደውልልሻለን። ይሉኝና አይደውሉም።
ሌሎቹ ደግሞ ፣ ለትወና ሥራ አመልክቼ ፣ “ፐ! አንቺ በጣም ጎበዝ ተዋናይ ነሽ... ለምን፣ ማስተማር አትሞክሪም? ” ይሉኝና ያሰናብቱኛል። ነገሩ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ግልጥልጥ ያለልኝ ፤ ታሪኩንና ስክሪፕቱ
👍1👏1