YeneTube
119K subscribers
31.3K photos
483 videos
79 files
3.85K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
#በኤርትራ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በነገው ዕለት በይፋ ስራ ይጀምራል::

#የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ፣ የኤርትራው ፕሬዚዳንት #ኢሳያስ አፈወርቂ እና የሁለቱ ሃገራት ከፍተኛ ባለስልጣናት ኤምባሲውን መርቀው #የሚከፍቱት ይሆናል።

በአየርላንድ የኢትዮጵያ ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር የሆኑት አቶ #ሬድዋን ሁሴን በኤርትራ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው መሾማቸው ይታወቃል።

#ኤርትራ በኢትዮጵያ የሚገኘው ኤምባሲዋን ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በኢትዮጵያ ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት መክፈቷ ይታወሳል።

ባለፈው ሃምሌ ወር የተከፈተው የኤርትራ #ኤምባሲ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።

©fbc
@YeneTube @mycase27
#በኤርትራ #የኢትዮጵያ ኤምባሲ በዛሬው ዕለት በይፋ ተከፍቶ ስራ ጀመረ።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ፣ የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ እና የሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ ባለስልጣናት ኤምባሲውን በዘሬው እለት መርቀው ከፍተዋል።
©fbc
@yenetube @mycase27
#የትግራይ ክልል ርእሰ መስተዳደር ዶ/ር #ደብረፅዮን ገብረሚካኤል #በኤርትራ ፕሬዚዳንት ኢሣያሥ አፈወርቂ በተደረገላቸው የጥሪ ግብዣን መሰረት በማድረግ በሚቀጥሉት ሳምንት ወደ አስመራ ይጓዛሉ።

ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል በአስመራ ጉዞአቸው በኤርትራ እና በትግራይ ህዝብ መሀል ያለውን ወንድማዊ ትስስሩን የበለጠ ለማጠናከር ከኢሳያስ ኣፈወርቂ ጋር በሰፊው ይመካከራሉ።

📌ሼር ያድርጉ!!
©ዋልታ ቴሌቨዠን
@YeneTube @Fikerassefa
#በኤርትራ ለዓመታት የትጥቅ ትግል ለመድረግ ሲንቀሳቀስ የነበረው #የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ትህዴን) ሁለት ሺህ ያህል ታጣቂዎች ወደ ሀገር ቤት ተመለሱ።

ወታደሮቹ በጉዞ ላይ እንዳሉ በደረሰ የመኪና አደጋ ቢያንስ ሶስት ወታደሮች ሲሞቱ በርከት ያሉ ቆስለዋል።

ወደ ዛለምበሳ የሚያመራ ወታደሮቹ የተሳፈሩበት የጭነት መኪና በመገልበጡ አደጋው መድረሱን እማኞች ተናግረዋል። ትህዴን በኤርትራ ከፍተኛ ቁጥር ካላቸው ታጣቂ ቡድኖች #አንዱ ነው።

ድርጅቱ ወደ ሀገር ቤት የተመለሰው ከመንግስት ጋር ባደረገው ድርድር በሰላማዊ ትግል ለመሳተፍ በመወሰኑ ነው።
ቀሪ ወታደሮችም በቀጣዮቹ ቀናት #ይመለሳሉ
ምንጭ ፦ ዋዜማ ራዲዮ
@yenetube @mycase27
በኢትዮዽያና #በኤርትራ ድንበር የሚገኘው የመከላከያ ሰራዊት አካባቢውን ለቆ እንዲወጣ #እየተደረገ መሆኑን የመከላከያ ሎጀስቲክ ዘርፍ ሀላፊ ሌተናል ጀነራል ሞላ ኅ/ማርያም አስታወቁ።

ጀነራሉ የሰራዊቱን እንቅስቃሴ #ማደናቀፍ እንደማይቻልም የገለጹ ሲሆን፣ በሚያደናቅፉት ላይ #እርምጃ ይወሰዳል ብለዋል።

-ELU
@YeneTube @FikerAssef
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በኤርትራ የሚገኘውን ጨምሮ አስር ኤምባሲዎችን ለመዝጋት ማቀዱ ተገለጸ

የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር #በኤርትራ እና ደቡብ #ሱዳን የሚገኙትን ጨምሮ 10 የአሜሪካ ኤምባሲዎችን ለመዝጋት ማቀዱ ተገለጸ።

ከኤምባሲዎቹ በተጨማሪ 17 ቆንስላዎቹንም ለመዝጋት የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ ማቀዱን ኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጣ ተመለከትኩት ያለው ያስተዳደሩን ማስታወሻ ዋቢ በማድረግ ባቀረበው ዘገባው ጠቁሟል።

የትራንፕ አስተዳደር እንዲዘጉ በሚል በእቅድ በያዛቸው ሀገራት ውስጥ በሚገኙ ኤምባሲዎች ይከናወኑ የነበሩ ስራዎች በአጎራባች ሀገራት ባሉ ኤምባሲዎች ለማከናወን ማቀዱንም ዘገባው አስታውቋል።

የኤምባሲዎቹ እና ቆንስላዎቹ መዘጋት የትራንፕ አስተዳደር የፌደራል መንግስትን ባጀት ለመቀነስ እየወሰደ ያለው እርምጃ አካል ነው ተብሏል።

የትራንፕ አስተዳደር ከሚዘጋቸው አስር ኤምባሲዎች መካከል ስድስቱ በአፍሪካ የሚገኙ መሆናቸውን ዘገባው አስታውቋል።

የአስተዳደሩ እቅድ ዩናይትድ ስቴትስ የነበራት የዲፕሎማሲ የበላይነት ያሳጣታል፣ ለቻይና አዲስ እድል ይፈጥርላታል የሚሉ አስተያየቶች እየተሰነዘሩ እንደሚገኙም ዘገባው አመላክቷል።

እቅዱ ተግባራዊ ከሆነ ቻይና በአፍሪካ ያላትን የዲፕሎማሲ የበላይነት ይበልጥ ያጠናክርላታል መባሉን ዘገባው አካቷል።

ጋዜጣው በተጨማሪም በሶማሊያ ሞቃዲሾ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ሙሉ በሙሉ እንዲዘጋ ካልሆነ ደግሞ በከፍተኛ ቁጥር ሰራተኞቹ እንዲቀነሱ ሃሳብ መቅረቡን አመላክቷል።


@Yenetube @Fikerassefa
👍141🔥1