ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
▶️ እነዚህንና እነዚህን የመሳሰሉት #ሀሳቦች በሙሉ #የተፈለሰፉት #ማርያም <<ከፍጡራን በላይ ከፈጣሪ በታች>> እንደሆነች #መጽሀፍ ቅዱስ እንደሚናገር በማሰብ ሲሆን ከላይ እንደተገለጸው #ከእግዚአብሄር #ቀጥላ #ሁለተኛ #አምልኮት የሚቀርብላት ሆናለች። ነገር ግን #መልአኩ #ገብርኤልም፣ #ኤልሳቤጥም የተናገሩት አንድ አይነት ቃል <<ከሴቶች በላይ፣ ከፍጡራን ሁሉ በላይ>> ሳይሆን <<ከሴቶች #መካከል>>…
▶️ እስቲ እነዚህን ጥቅሶች ይመልከቷቸው።
〽️ ሐዋ 1፤ 9-11፦
<<ይህንም ከተናገረ በኋላ እነርሱ እያዩት ከፍ ከፍ አለ፤ ደመናም ከዓይናቸው ሰውራ ተቀበለችው። እርሱም ሲሄድ ወደ ሰማይ ትኵር ብለው ሲመለከቱ ሳሉ፥ እነሆ፥ ነጫጭ ልብስ የለበሱ ሁለት ሰዎች በአጠገባቸው ቆሙ፤ ደግሞም። የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደሰማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል አሉአቸው።>>
⁉️ #ኢየሱስ ወደ #ሰማይ ሲያርግ ሁሉም #ደቀመዛሙርትና #ሴቶች #ማርያምም ጭምር #በደብረ ዘይት ተራራ #ዕርገቱን ሲመለከቱ ሁለቱ #መላእክት በአጠገባቸው #ቆመው < #ለማርያም ብቻ> ወይም < #በማርያም #በኩል> ሳይሆን የተናገሩት ለሁሉም #በእኩል አይን <<የገሊላ ሰዎች ሆይ...>> በማለት ነበር።
〽️ ሐዋ 1፤ 12-14፦
<<በዚያን ጊዜ ደብረ ዘይት ከሚባለው ተራራ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፥ እርሱም ከኢየሩሳሌም የሰንበት መንገድ ያህል የራቀ ነው። በገቡም ጊዜ ወደሚኖሩበት ሰገነት ወጡ፥ ጴጥሮስና ዮሐንስም፥ ያዕቆብም፥ እንድርያስም፥ ፊልጶስም፥ ቶማስም፥ በርተሎሜዎስም፥ ማቴዎስም፥ የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብም፥ ቀናተኛ የሚባለው ስምዖንም፥ የያዕቆብ ልጅ ይሁዳም። እነዚህ ሁሉ ከሴቶችና ከኢየሱስ እናት ከማርያም ከወንድሞቹም ጋር በአንድ ልብ ሆነው ለጸሎት ይተጉ ነበር።>>
⁉️ #ከክርስቶስ #እርገት ቡሀላ ወደ #ኢየሩሳሌም ሲመለሱ #ማርያም #ከሐዋሪያቶቹ ጋር ሌሎችም #በርካታ #ሴቶች ያለምንም #ልዩነት ለአንድነት #ለጸሎት #ይተጉ ነበር። ይህ ደግሞ #ማርያም #ከፍጡራን #የተለየች ወይም #ወጣ ያለች እንዳልነበረች አንብቦ #መረዳት አያቅትም።
〽️ ሐዋ 1፥15፦
<<በዚህም ወራት ጴጥሮስ መቶ ሀያ በሚያህል በሰዎች ማኅበር አብረው በነበሩ በወንድሞቹ መካከል ተነሥቶ አለ።>>
⁉️ የጸሎቱም #መሪ ሐዋሪያው #ጴጥሮስ ነበር እንጂ #ማርያም #ከጉባኤው ጋር #ምእመን ከመሆን ውጪ #የአምልኮው #መሪ እንኳን አልነበረችም። ይህ #ከፍጡራን #የተለየች ናት እንድንል አያደርገንም።
〽️ ሐዋ 1፥16፦
<<ወንድሞች ሆይ፥ ኢየሱስን ለያዙት መሪ ስለሆናቸው ስለ ይሁዳ መንፈስ ቅዱስ አስቀድሞ በዳዊት አፍ የተናገረው የመጽሐፍ ቃል ይፈጸም ዘንድ ይገባ ነበር፤>>
⁉️ ማርያም ባለችበት #ጉባኤ ተነስቶ <<ወንድሞች ሆይ>> በማለት #በቀጥታ #ንግግሩን ጀመረ እንጂ #በመካከላቸው ለነበረችው #ማርያም #ስግደት ወይም የተለየ #አክብሮት አላቀረበም። ይህም ከእነሱ #የተለየች እንዳልነበረች ያስረዳል።
〽️ ሐዋ 1፤ 21-22፦
<<ስለዚህ ከዮሐንስ ጥምቀት ጀምሮ ከእኛ ዘንድ እስካረገበት ቀን ድረስ፥ ጌታ ኢየሱስ በእኛ መካከል በገባበትና በወጣበት ዘመን ሁሉ ከእኛ ጋር አብረው ከነበሩት ሰዎች፥ ከእነዚህ አንዱ ከእኛ ጋር የትንሣኤው ምስክር ይሆን ዘንድ ይገባል።>>
⁉️ አሁንም ሐዋሪያው #ጴጥሮስ #ማርያም ባለችበት በዚህ #ጉባዔ #በይሁዳ ምትክ ሌላ #ሐዋሪያ እንዲተካ #ሃሳብ ሲያቀርብ <<ከእነዚህ አንዱ ከእኛ ጋር #የትንሳኤው ምስክር ይሆን ዘንድ ይገባል>> አለ እንጂ ስለ #ማርያም #ምስክር የሚሆን አለማለቱ በአሁኑ #ዘመን ለእኛ #ምስክርነታችን መሆን የሚገባው #ስለክርስቶስ እንጂ #ስለማርያም #መመስከር #የሐዋሪያት #ትምህርት እንዳልሆነ #የሚያስረዳ ነው።
〽️ ሐዋ 1፥25፦
<<ሲጸልዩም። የሁሉን ልብ የምታውቅ አንተ ጌታ ሆይ፥ ይሁዳ ወደ ገዛ ራሱ ስፍራ ይሄድ ዘንድ በተዋት በዚህች አገልግሎትና ሐዋርያነት ስፍራን እንዲቀበል የመረጥኸውን ከእነዚህ ከሁለቱ አንዱን ሹመው አሉ።>>
⁉️ ይሄው ጉባዔ #ማርያም ባለችበት <<ሲጸልዩም የሁሉንም ልብ የምታውቅ አንተ ጌታ ሆይ>> ብለው #ቀጥታ ወደ #ጌታ ጸለዩ እንጂ እሷ #ከፍጡራን #በላይ ነች ብለው ወደ #ማርያም ወይም #በማርያም #ስም #አልጸለዩም። ይህም በግልጽ #ማርያም #ከሰው #የተለየች እንዳልሆነች ያሳያል።
〽️ ሐዋ 2፤ 1-4፦
<<በዓለ ኀምሳ የተባለውም ቀን በደረሰ ጊዜ፥ ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው አብረው ሳሉ፥ ድንገት እንደሚነጥቅ ዓውሎ ነፋስ ከሰማይ ድምፅ መጣ፥ ተቀምጠው የነበሩበትንም ቤት ሁሉ ሞላው። እንደ እሳትም የተከፋፈሉ ልሳኖች ታዩአቸው፤ በያንዳንዳቸውም ላይ ተቀመጡባቸው። በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፥ መንፈስም ይናገሩ ዘንድ እንደ ሰጣቸው>>
⁉️ በዓለ #ሀምሳ የተባለውም #ቀን በደረሰ ጊዜ ሁሉም #በአንድ #ልብ ሆነው አብረው ሳሉ #መንፈስቅዱስ #በጉባዔው መካከል ከነበረችው #ከማርያም ወይም #በማርያም #በኩል ሳይሆን #ከሰማይ #መምጣቱ አንዳንዶች እንደሚሉት #ማርያም #መለኮታዊ መነሻ ወይም #ምንጭ ወይም #ሰጪ እንዳልሆነችም ያስረዳናል።
〽️ ሐዋ 2፤ 3-4፦
<<እንደ እሳትም የተከፋፈሉ ልሳኖች ታዩአቸው፤ በያንዳንዳቸውም ላይ ተቀመጡባቸው። በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፥ መንፈስም ይናገሩ ዘንድ እንደ ሰጣቸው በሌላ ልሳኖች ይናገሩ ጀመር።>>
⁉️ #መንፈስቅዱስም ሲወርድ ሁሉም ላይ #እኩል ወረደ እንጂ #ለማርያም የተለየ #ጸጋ(መንፈስ) አለመሰጠቱ #በእግዚአብሄር ፊት ያው እንደማንኛውም #ክርስቲያን #እኩል እንደሆነች #እንጂ የተለየች ወይም #ከፍጡራን #የምትበልጥ እንደሆነች አያሳይም።
〽️ ሐዋ 2፤ 5-10፦
<<ከሰማይም በታች ካሉ ሕዝብ ሁሉ በጸሎት የተጉ አይሁድ በኢየሩሳሌም ይኖሩ ነበር፤ ይህም ድምፅ በሆነ ጊዜ ሕዝብ ሁሉ ተሰበሰቡ፥ እያንዳንዱም በገዛ ቋንቋው ሲናገሩ ይሰማ ስለ ነበር የሚሉትን አጡ። ተገርመውም ተደንቀውም እንዲህ አሉ። እነሆ፥ እነዚህ የሚናገሩት ሁሉ የገሊላ ሰዎች አይደሉምን?...>>
⁉️ #በኢየሩሳሌም ይኖሩ የነበሩት #አይሁዶች በሁሉም ላይ #ከወረደው #ከመንፈስ ቅዱስ የተነሳ በገዛ #ቋንቋዎቻቸው ሲናገሩ እየሰሙ በሁሉም ተገረሙ እንጂ #ለማርያም የተለየ #አትኩሮት አልሰጡም። ይህም #ማርያም እንደነሱ #እኩል #ማንነትና #ጸጋ እንደነበራት ያሳያል።
〽️ ሐዋ 2፤ 9-12፦
<<የጳርቴና የሜድ የኢላሜጤም ሰዎች፥ በሁለት ወንዝም መካከል በይሁዳም በቀጰዶቅያም በጳንጦስም በእስያም፥ በፍርግያም በጵንፍልያም በግብፅም በቀሬናም በኩል ባሉት በሊቢያ ወረዳዎች የምንኖር፥ በሮሜም የምንቀመጥ፥ አይሁድም ወደ ይሁዲነትም የገባን፥ የቀርጤስና የዓረብ ሰዎች፥ የእግዚአብሔርን ታላቅ ሥራ በልሳኖቻችን ሲናገሩ እንሰማቸዋለን።...>>
⁉️ እነዚህ #የኢየሩሳሌምና #የአረብ ሰዎች <<የእግዚአብሄርን ታላቅ ስራ በልሳኖቻችን ሲናገሩ እንሰማቸዋለን>> አሉ እንጂ አንዳንዶች እንደሚሉት #የማርያምን #ታላቅ #ስራ ሲናገሩ #ሰማን ስላላሉ እንደ ሐዋሪያት #ምስክርነታችን <<የእግዚአብሔርን ታላቅ ስራ>> እንጂ #ስለማርያም #መስበክ #የሀዋሪያት #ፈለግ እንዳልነበረ ያስተምረናል።
〽️ ሐዋ 1፤ 9-11፦
<<ይህንም ከተናገረ በኋላ እነርሱ እያዩት ከፍ ከፍ አለ፤ ደመናም ከዓይናቸው ሰውራ ተቀበለችው። እርሱም ሲሄድ ወደ ሰማይ ትኵር ብለው ሲመለከቱ ሳሉ፥ እነሆ፥ ነጫጭ ልብስ የለበሱ ሁለት ሰዎች በአጠገባቸው ቆሙ፤ ደግሞም። የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደሰማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል አሉአቸው።>>
⁉️ #ኢየሱስ ወደ #ሰማይ ሲያርግ ሁሉም #ደቀመዛሙርትና #ሴቶች #ማርያምም ጭምር #በደብረ ዘይት ተራራ #ዕርገቱን ሲመለከቱ ሁለቱ #መላእክት በአጠገባቸው #ቆመው < #ለማርያም ብቻ> ወይም < #በማርያም #በኩል> ሳይሆን የተናገሩት ለሁሉም #በእኩል አይን <<የገሊላ ሰዎች ሆይ...>> በማለት ነበር።
〽️ ሐዋ 1፤ 12-14፦
<<በዚያን ጊዜ ደብረ ዘይት ከሚባለው ተራራ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፥ እርሱም ከኢየሩሳሌም የሰንበት መንገድ ያህል የራቀ ነው። በገቡም ጊዜ ወደሚኖሩበት ሰገነት ወጡ፥ ጴጥሮስና ዮሐንስም፥ ያዕቆብም፥ እንድርያስም፥ ፊልጶስም፥ ቶማስም፥ በርተሎሜዎስም፥ ማቴዎስም፥ የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብም፥ ቀናተኛ የሚባለው ስምዖንም፥ የያዕቆብ ልጅ ይሁዳም። እነዚህ ሁሉ ከሴቶችና ከኢየሱስ እናት ከማርያም ከወንድሞቹም ጋር በአንድ ልብ ሆነው ለጸሎት ይተጉ ነበር።>>
⁉️ #ከክርስቶስ #እርገት ቡሀላ ወደ #ኢየሩሳሌም ሲመለሱ #ማርያም #ከሐዋሪያቶቹ ጋር ሌሎችም #በርካታ #ሴቶች ያለምንም #ልዩነት ለአንድነት #ለጸሎት #ይተጉ ነበር። ይህ ደግሞ #ማርያም #ከፍጡራን #የተለየች ወይም #ወጣ ያለች እንዳልነበረች አንብቦ #መረዳት አያቅትም።
〽️ ሐዋ 1፥15፦
<<በዚህም ወራት ጴጥሮስ መቶ ሀያ በሚያህል በሰዎች ማኅበር አብረው በነበሩ በወንድሞቹ መካከል ተነሥቶ አለ።>>
⁉️ የጸሎቱም #መሪ ሐዋሪያው #ጴጥሮስ ነበር እንጂ #ማርያም #ከጉባኤው ጋር #ምእመን ከመሆን ውጪ #የአምልኮው #መሪ እንኳን አልነበረችም። ይህ #ከፍጡራን #የተለየች ናት እንድንል አያደርገንም።
〽️ ሐዋ 1፥16፦
<<ወንድሞች ሆይ፥ ኢየሱስን ለያዙት መሪ ስለሆናቸው ስለ ይሁዳ መንፈስ ቅዱስ አስቀድሞ በዳዊት አፍ የተናገረው የመጽሐፍ ቃል ይፈጸም ዘንድ ይገባ ነበር፤>>
⁉️ ማርያም ባለችበት #ጉባኤ ተነስቶ <<ወንድሞች ሆይ>> በማለት #በቀጥታ #ንግግሩን ጀመረ እንጂ #በመካከላቸው ለነበረችው #ማርያም #ስግደት ወይም የተለየ #አክብሮት አላቀረበም። ይህም ከእነሱ #የተለየች እንዳልነበረች ያስረዳል።
〽️ ሐዋ 1፤ 21-22፦
<<ስለዚህ ከዮሐንስ ጥምቀት ጀምሮ ከእኛ ዘንድ እስካረገበት ቀን ድረስ፥ ጌታ ኢየሱስ በእኛ መካከል በገባበትና በወጣበት ዘመን ሁሉ ከእኛ ጋር አብረው ከነበሩት ሰዎች፥ ከእነዚህ አንዱ ከእኛ ጋር የትንሣኤው ምስክር ይሆን ዘንድ ይገባል።>>
⁉️ አሁንም ሐዋሪያው #ጴጥሮስ #ማርያም ባለችበት በዚህ #ጉባዔ #በይሁዳ ምትክ ሌላ #ሐዋሪያ እንዲተካ #ሃሳብ ሲያቀርብ <<ከእነዚህ አንዱ ከእኛ ጋር #የትንሳኤው ምስክር ይሆን ዘንድ ይገባል>> አለ እንጂ ስለ #ማርያም #ምስክር የሚሆን አለማለቱ በአሁኑ #ዘመን ለእኛ #ምስክርነታችን መሆን የሚገባው #ስለክርስቶስ እንጂ #ስለማርያም #መመስከር #የሐዋሪያት #ትምህርት እንዳልሆነ #የሚያስረዳ ነው።
〽️ ሐዋ 1፥25፦
<<ሲጸልዩም። የሁሉን ልብ የምታውቅ አንተ ጌታ ሆይ፥ ይሁዳ ወደ ገዛ ራሱ ስፍራ ይሄድ ዘንድ በተዋት በዚህች አገልግሎትና ሐዋርያነት ስፍራን እንዲቀበል የመረጥኸውን ከእነዚህ ከሁለቱ አንዱን ሹመው አሉ።>>
⁉️ ይሄው ጉባዔ #ማርያም ባለችበት <<ሲጸልዩም የሁሉንም ልብ የምታውቅ አንተ ጌታ ሆይ>> ብለው #ቀጥታ ወደ #ጌታ ጸለዩ እንጂ እሷ #ከፍጡራን #በላይ ነች ብለው ወደ #ማርያም ወይም #በማርያም #ስም #አልጸለዩም። ይህም በግልጽ #ማርያም #ከሰው #የተለየች እንዳልሆነች ያሳያል።
〽️ ሐዋ 2፤ 1-4፦
<<በዓለ ኀምሳ የተባለውም ቀን በደረሰ ጊዜ፥ ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው አብረው ሳሉ፥ ድንገት እንደሚነጥቅ ዓውሎ ነፋስ ከሰማይ ድምፅ መጣ፥ ተቀምጠው የነበሩበትንም ቤት ሁሉ ሞላው። እንደ እሳትም የተከፋፈሉ ልሳኖች ታዩአቸው፤ በያንዳንዳቸውም ላይ ተቀመጡባቸው። በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፥ መንፈስም ይናገሩ ዘንድ እንደ ሰጣቸው>>
⁉️ በዓለ #ሀምሳ የተባለውም #ቀን በደረሰ ጊዜ ሁሉም #በአንድ #ልብ ሆነው አብረው ሳሉ #መንፈስቅዱስ #በጉባዔው መካከል ከነበረችው #ከማርያም ወይም #በማርያም #በኩል ሳይሆን #ከሰማይ #መምጣቱ አንዳንዶች እንደሚሉት #ማርያም #መለኮታዊ መነሻ ወይም #ምንጭ ወይም #ሰጪ እንዳልሆነችም ያስረዳናል።
〽️ ሐዋ 2፤ 3-4፦
<<እንደ እሳትም የተከፋፈሉ ልሳኖች ታዩአቸው፤ በያንዳንዳቸውም ላይ ተቀመጡባቸው። በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፥ መንፈስም ይናገሩ ዘንድ እንደ ሰጣቸው በሌላ ልሳኖች ይናገሩ ጀመር።>>
⁉️ #መንፈስቅዱስም ሲወርድ ሁሉም ላይ #እኩል ወረደ እንጂ #ለማርያም የተለየ #ጸጋ(መንፈስ) አለመሰጠቱ #በእግዚአብሄር ፊት ያው እንደማንኛውም #ክርስቲያን #እኩል እንደሆነች #እንጂ የተለየች ወይም #ከፍጡራን #የምትበልጥ እንደሆነች አያሳይም።
〽️ ሐዋ 2፤ 5-10፦
<<ከሰማይም በታች ካሉ ሕዝብ ሁሉ በጸሎት የተጉ አይሁድ በኢየሩሳሌም ይኖሩ ነበር፤ ይህም ድምፅ በሆነ ጊዜ ሕዝብ ሁሉ ተሰበሰቡ፥ እያንዳንዱም በገዛ ቋንቋው ሲናገሩ ይሰማ ስለ ነበር የሚሉትን አጡ። ተገርመውም ተደንቀውም እንዲህ አሉ። እነሆ፥ እነዚህ የሚናገሩት ሁሉ የገሊላ ሰዎች አይደሉምን?...>>
⁉️ #በኢየሩሳሌም ይኖሩ የነበሩት #አይሁዶች በሁሉም ላይ #ከወረደው #ከመንፈስ ቅዱስ የተነሳ በገዛ #ቋንቋዎቻቸው ሲናገሩ እየሰሙ በሁሉም ተገረሙ እንጂ #ለማርያም የተለየ #አትኩሮት አልሰጡም። ይህም #ማርያም እንደነሱ #እኩል #ማንነትና #ጸጋ እንደነበራት ያሳያል።
〽️ ሐዋ 2፤ 9-12፦
<<የጳርቴና የሜድ የኢላሜጤም ሰዎች፥ በሁለት ወንዝም መካከል በይሁዳም በቀጰዶቅያም በጳንጦስም በእስያም፥ በፍርግያም በጵንፍልያም በግብፅም በቀሬናም በኩል ባሉት በሊቢያ ወረዳዎች የምንኖር፥ በሮሜም የምንቀመጥ፥ አይሁድም ወደ ይሁዲነትም የገባን፥ የቀርጤስና የዓረብ ሰዎች፥ የእግዚአብሔርን ታላቅ ሥራ በልሳኖቻችን ሲናገሩ እንሰማቸዋለን።...>>
⁉️ እነዚህ #የኢየሩሳሌምና #የአረብ ሰዎች <<የእግዚአብሄርን ታላቅ ስራ በልሳኖቻችን ሲናገሩ እንሰማቸዋለን>> አሉ እንጂ አንዳንዶች እንደሚሉት #የማርያምን #ታላቅ #ስራ ሲናገሩ #ሰማን ስላላሉ እንደ ሐዋሪያት #ምስክርነታችን <<የእግዚአብሔርን ታላቅ ስራ>> እንጂ #ስለማርያም #መስበክ #የሀዋሪያት #ፈለግ እንዳልነበረ ያስተምረናል።
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
▶️ እስቲ እነዚህን ጥቅሶች ይመልከቷቸው። 〽️ ሐዋ 1፤ 9-11፦ <<ይህንም ከተናገረ በኋላ እነርሱ እያዩት ከፍ ከፍ አለ፤ ደመናም ከዓይናቸው ሰውራ ተቀበለችው። እርሱም ሲሄድ ወደ ሰማይ ትኵር ብለው ሲመለከቱ ሳሉ፥ እነሆ፥ ነጫጭ ልብስ የለበሱ ሁለት ሰዎች በአጠገባቸው ቆሙ፤ ደግሞም። የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደሰማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ…
〽️ ሐዋ 2፤ 14-18፣ 17-20፦
<<ነገር ግን ጴጥሮስ ከአሥራ አንዱ ጋር ቆመ፥ ድምፁንም ከፍ አድርጎ እንዲህ ሲል ተናገራቸው። አይሁድ በኢየሩሳሌምም የምትኖሩ ሁላችሁ፥ ይህ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን፥ ቃሎቼንም አድምጡ። ለእናንተ እንደ መሰላችሁ እነዚህ የሰከሩ አይደሉም፥ ከቀኑ ሦስተኛ ሰዓት ነውና፤ ነገር ግን ይህ በነቢዩ በኢዩኤል የተባለው ነው። እግዚአብሔር ይላል። በመጨረሻው ቀን እንዲህ ይሆናል፤ ሥጋ በለበሰ ሁሉ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ፥ ጎበዞቻችሁም ራእይ ያያሉ፥ ሽማግሌዎቻችሁም ሕልም ያልማሉ. . .>>
⁉️ መንፈስቅዱስም የመጣው #ማርያም ስላለች ሳይሆን በነብዩ #በኢዩኤል #የተተነበየው #ይፈጸም ዘንድ ነበር። ስለዚህ #የማርያም #በአካል መኖር የተለየ ነገር አልነበረውም። #ማርያምም እዛ #ትንቢት ውስጥ መካተቷ <<ስጋ በለበሰ ሁሉ ላይ>> እንደተባለው #ማርያምን ጨምሮ ሳያበላልጥ #እኩል #በወንዶችና #በሴቶች ላይ ማደሩ፤ እሷም #ስጋ ከለበሱት ጋር #እኩል #መቆጠሯ ፈጽሞ ከሌላው #የተለየች እንዳልሆነች ያሳያል።
〽️ ሐዋ 2፤ 22-35፦
<<የእስራኤል ሰዎች ሆይ፥ ይህን ቃል ስሙ፤ ራሳችሁ እንደምታውቁ፥ የናዝሬቱ ኢየሱስ እግዚአብሔር በመካከላችሁ በእርሱ በኩል ባደረገው ተአምራትና በድንቆች በምልክቶችም ከእግዚአብሔር ዘንድ ለእናንተ የተገለጠ ሰው ነበረ፤ እርሱንም በእግዚአብሔር በተወሰነው አሳቡና በቀደመው እውቀቱ ተሰጥቶ በዓመፀኞች እጅ ሰቅላችሁ ገደላችሁት። እግዚአብሔር ግን የሞትን ጣር አጥፍቶ አስነሣው፥ ሞት ይይዘው ዘንድ አልቻለምና። . . . ስለ ክርስቶስ ትንሣኤ አስቀድሞ አይቶ፥ ነፍሱ በሲኦል እንዳልቀረች ሥጋውም መበስበስን እንዳላየ ተናገረ። ይህን ኢየሱስን እግዚአብሔር አስነሣው ለዚህም ነገር እኛ ሁላችን ምስክሮች ነን፤. .>>
⁉️ #ሐዋርያት #በመንፈስ ቅዱስ ሆነው #በመካከላቸው #ማርያም ብትኖርም <<የናዝሬቱን ኢየሱስ እግዚአብሔር በመካከላችሁ በእርሱ በኩል ባደረገው ተአምራትና በድንቆች በምልክቶችም ከእግዚአብሄር ዘንድ ለእናንተ የተገለጠ ሰው ነበር>> በሚል ቃል #ክርስቶስን ብቻ #ማዕከል ያደረገ #ስብከት #ሰጡ እንጂ #ስለማርያም ያሉት ነገር አልነበረም።
〽️ ሐዋ 2፤ 37-38፦
<<ይህንም በሰሙ ጊዜ ልባቸው ተነካ፥ ጴጥሮስንና ሌሎችንም ሐዋርያት። ወንድሞች ሆይ፥ ምን እናድርግ? አሉአቸው። ጴጥሮስም። ንስሐ ግቡ፥ ኃጢአታችሁም ይሰረይ ዘንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፤ የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ።>>
⁉️ #የሐዋርያትን #ስብከት የሰሙት ህዝቦች #ሐዋርያትን ምን እናድርግ ብለው #ሲጠይቋቸው በመካከላችን እናቱ #ማርያም ስላለች #በእርሷ #አማላጅነት #እመኑ ወደ እርሷ ወይም #በእርሷ በኩል ቅረቡ ሳይሆን ያሉት #ንስሃ ገብታችሁ #በኢየሱስ ስም ተጠመቁ #የመንፈስ ቅዱስ #ስጦታ #ትቀበላላችሁ የሚል #ክርስቶስን #ብቻ የገለጸ #መልስ ነበር የሰጡት።
〽️ ሐዋ 2፥47፦
<<እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ በሕዝብ ሁሉ ፊት ሞገስ ነበራቸው። ጌታም የሚድኑትን ዕለት ዕለት በእነርሱ ላይ ይጨምር ነበር።>>
⁉️ ሁሉም #በአንድነት #እግዚአብሔርን #በቀጥታ #ያመሰግኑ ነበር እንጂ ወደ #ማርያምም ሲጸልዩም ሆነ #ምስጋና ሲያቀርቡ አላየንም። በዚህም #ምክንያት የማርያም #በመካከላቸው #መኖርና #አለመኖር የተለየ ምንም #ጥቅም እንደሌለው የተረዱ ሲሆን #ጌታም #አብሮአቸው በመስራት #ዕለት #ዕለት #ቁጥራቸው ይጨምር ነበር።
▶️ ደግሞም #በብሉይም ይሁን #በአዲስ ኪዳን #እጹብ ድንቅ #በእግዚአብሄር ኃይል #ተአምራትን ካደረጉ #ሴቶች ይልቅ #ማርያም ከፍ ብላ የምትታይበት #አንድም #ተአምር #በመጽሀፍ ቅዱስ እንዳደረገች እንኳ #አልተጻፈም። #በወንዶችም ቢሆን የተደረገው #ተአምር #ምድርን ሁሉ ቢያስገርምም ማንም <ከፍጡራን በላይ> የተባለ ግን የለም። ምክንያቱም #የተአምራቱ ባለቤት #እግዚአብሔር እንጂ #ሰዎች አይደሉምና። ስለዚህም እዚህ ላይ ልንገነዘበው የሚገባን #እውነት ቢኖር #ማርያም ከተባረኩ #በርካታ #ሴቶች #መካከል #የተባረከች #አንዷ #ሴት መሆኗን ነው {ሉቃ 1፥28 ፣ ሉቃ 1፥42}። #ቃሉም እንደ እርሱ ነው የሚለውና #ቃሉን #ብቻ እንመን።
✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/
🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆
"ማጣቀሻዎች - References"
_______________
[1] 📚፤ አባ መልከ ጻድቅ (ሊቀ ጳጳስ) <ኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክ እምነትና ትምህርት> ገጽ 217፥ ንግድ ማተሚያ ድርጅት፡ አ.አ 1994 ዓ.ም።
📚፤ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፤
<መጽሐፈ ሚስጥር> ገጽ 97፤
<መጽሀፈ ደጓ> ገጽ 380 እና 386።
📚፤ አባ ጎርጎሪዮስ (የሸዋ ሊቀ ጳጳስ)፡ የኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክ ታሪክ፡ ገጽ 133፤ አ.አ ፡1994 ዓ.ም።
[2] 📚፤ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
<መጽሀፈ ሚስጥር> ገጽ 97፥
"አርጋኖን ዘዓርብ" ገጽ 296፥ 3፤ 3-4። ተስፋ ገብረ ሥላሴ ማተሚያ ቤት፤ 1989 ዓ.ም።
[3] 📚፤ የዘውትር ጸሎት፡ ውዳሴ ማርያም በአማርኛ፤ ገጽ 5-8፡ ተስፋ ገብረ ሥላሴ ማተሚያ ቤት፤ አ.አ 1986 ዓ.ም።
📚፤ አንዱ ዓለም ዳግማዊ (መምህር)፤ <ወላዲተ አምላክ በነገረ ድኅነት> ገጽ 257፤ ብራና ማተሚያ ድርጅት፤ አ.አ፥ ሚያዚያ 1998 ዓ.ም።
(6.1▶️ጥያቄ) ይቀጥላል...
@gedlatnadersanat
<<ነገር ግን ጴጥሮስ ከአሥራ አንዱ ጋር ቆመ፥ ድምፁንም ከፍ አድርጎ እንዲህ ሲል ተናገራቸው። አይሁድ በኢየሩሳሌምም የምትኖሩ ሁላችሁ፥ ይህ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን፥ ቃሎቼንም አድምጡ። ለእናንተ እንደ መሰላችሁ እነዚህ የሰከሩ አይደሉም፥ ከቀኑ ሦስተኛ ሰዓት ነውና፤ ነገር ግን ይህ በነቢዩ በኢዩኤል የተባለው ነው። እግዚአብሔር ይላል። በመጨረሻው ቀን እንዲህ ይሆናል፤ ሥጋ በለበሰ ሁሉ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ፥ ጎበዞቻችሁም ራእይ ያያሉ፥ ሽማግሌዎቻችሁም ሕልም ያልማሉ. . .>>
⁉️ መንፈስቅዱስም የመጣው #ማርያም ስላለች ሳይሆን በነብዩ #በኢዩኤል #የተተነበየው #ይፈጸም ዘንድ ነበር። ስለዚህ #የማርያም #በአካል መኖር የተለየ ነገር አልነበረውም። #ማርያምም እዛ #ትንቢት ውስጥ መካተቷ <<ስጋ በለበሰ ሁሉ ላይ>> እንደተባለው #ማርያምን ጨምሮ ሳያበላልጥ #እኩል #በወንዶችና #በሴቶች ላይ ማደሩ፤ እሷም #ስጋ ከለበሱት ጋር #እኩል #መቆጠሯ ፈጽሞ ከሌላው #የተለየች እንዳልሆነች ያሳያል።
〽️ ሐዋ 2፤ 22-35፦
<<የእስራኤል ሰዎች ሆይ፥ ይህን ቃል ስሙ፤ ራሳችሁ እንደምታውቁ፥ የናዝሬቱ ኢየሱስ እግዚአብሔር በመካከላችሁ በእርሱ በኩል ባደረገው ተአምራትና በድንቆች በምልክቶችም ከእግዚአብሔር ዘንድ ለእናንተ የተገለጠ ሰው ነበረ፤ እርሱንም በእግዚአብሔር በተወሰነው አሳቡና በቀደመው እውቀቱ ተሰጥቶ በዓመፀኞች እጅ ሰቅላችሁ ገደላችሁት። እግዚአብሔር ግን የሞትን ጣር አጥፍቶ አስነሣው፥ ሞት ይይዘው ዘንድ አልቻለምና። . . . ስለ ክርስቶስ ትንሣኤ አስቀድሞ አይቶ፥ ነፍሱ በሲኦል እንዳልቀረች ሥጋውም መበስበስን እንዳላየ ተናገረ። ይህን ኢየሱስን እግዚአብሔር አስነሣው ለዚህም ነገር እኛ ሁላችን ምስክሮች ነን፤. .>>
⁉️ #ሐዋርያት #በመንፈስ ቅዱስ ሆነው #በመካከላቸው #ማርያም ብትኖርም <<የናዝሬቱን ኢየሱስ እግዚአብሔር በመካከላችሁ በእርሱ በኩል ባደረገው ተአምራትና በድንቆች በምልክቶችም ከእግዚአብሄር ዘንድ ለእናንተ የተገለጠ ሰው ነበር>> በሚል ቃል #ክርስቶስን ብቻ #ማዕከል ያደረገ #ስብከት #ሰጡ እንጂ #ስለማርያም ያሉት ነገር አልነበረም።
〽️ ሐዋ 2፤ 37-38፦
<<ይህንም በሰሙ ጊዜ ልባቸው ተነካ፥ ጴጥሮስንና ሌሎችንም ሐዋርያት። ወንድሞች ሆይ፥ ምን እናድርግ? አሉአቸው። ጴጥሮስም። ንስሐ ግቡ፥ ኃጢአታችሁም ይሰረይ ዘንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፤ የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ።>>
⁉️ #የሐዋርያትን #ስብከት የሰሙት ህዝቦች #ሐዋርያትን ምን እናድርግ ብለው #ሲጠይቋቸው በመካከላችን እናቱ #ማርያም ስላለች #በእርሷ #አማላጅነት #እመኑ ወደ እርሷ ወይም #በእርሷ በኩል ቅረቡ ሳይሆን ያሉት #ንስሃ ገብታችሁ #በኢየሱስ ስም ተጠመቁ #የመንፈስ ቅዱስ #ስጦታ #ትቀበላላችሁ የሚል #ክርስቶስን #ብቻ የገለጸ #መልስ ነበር የሰጡት።
〽️ ሐዋ 2፥47፦
<<እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ በሕዝብ ሁሉ ፊት ሞገስ ነበራቸው። ጌታም የሚድኑትን ዕለት ዕለት በእነርሱ ላይ ይጨምር ነበር።>>
⁉️ ሁሉም #በአንድነት #እግዚአብሔርን #በቀጥታ #ያመሰግኑ ነበር እንጂ ወደ #ማርያምም ሲጸልዩም ሆነ #ምስጋና ሲያቀርቡ አላየንም። በዚህም #ምክንያት የማርያም #በመካከላቸው #መኖርና #አለመኖር የተለየ ምንም #ጥቅም እንደሌለው የተረዱ ሲሆን #ጌታም #አብሮአቸው በመስራት #ዕለት #ዕለት #ቁጥራቸው ይጨምር ነበር።
▶️ ደግሞም #በብሉይም ይሁን #በአዲስ ኪዳን #እጹብ ድንቅ #በእግዚአብሄር ኃይል #ተአምራትን ካደረጉ #ሴቶች ይልቅ #ማርያም ከፍ ብላ የምትታይበት #አንድም #ተአምር #በመጽሀፍ ቅዱስ እንዳደረገች እንኳ #አልተጻፈም። #በወንዶችም ቢሆን የተደረገው #ተአምር #ምድርን ሁሉ ቢያስገርምም ማንም <ከፍጡራን በላይ> የተባለ ግን የለም። ምክንያቱም #የተአምራቱ ባለቤት #እግዚአብሔር እንጂ #ሰዎች አይደሉምና። ስለዚህም እዚህ ላይ ልንገነዘበው የሚገባን #እውነት ቢኖር #ማርያም ከተባረኩ #በርካታ #ሴቶች #መካከል #የተባረከች #አንዷ #ሴት መሆኗን ነው {ሉቃ 1፥28 ፣ ሉቃ 1፥42}። #ቃሉም እንደ እርሱ ነው የሚለውና #ቃሉን #ብቻ እንመን።
✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/
🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆
"ማጣቀሻዎች - References"
_______________
[1] 📚፤ አባ መልከ ጻድቅ (ሊቀ ጳጳስ) <ኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክ እምነትና ትምህርት> ገጽ 217፥ ንግድ ማተሚያ ድርጅት፡ አ.አ 1994 ዓ.ም።
📚፤ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፤
<መጽሐፈ ሚስጥር> ገጽ 97፤
<መጽሀፈ ደጓ> ገጽ 380 እና 386።
📚፤ አባ ጎርጎሪዮስ (የሸዋ ሊቀ ጳጳስ)፡ የኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክ ታሪክ፡ ገጽ 133፤ አ.አ ፡1994 ዓ.ም።
[2] 📚፤ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
<መጽሀፈ ሚስጥር> ገጽ 97፥
"አርጋኖን ዘዓርብ" ገጽ 296፥ 3፤ 3-4። ተስፋ ገብረ ሥላሴ ማተሚያ ቤት፤ 1989 ዓ.ም።
[3] 📚፤ የዘውትር ጸሎት፡ ውዳሴ ማርያም በአማርኛ፤ ገጽ 5-8፡ ተስፋ ገብረ ሥላሴ ማተሚያ ቤት፤ አ.አ 1986 ዓ.ም።
📚፤ አንዱ ዓለም ዳግማዊ (መምህር)፤ <ወላዲተ አምላክ በነገረ ድኅነት> ገጽ 257፤ ብራና ማተሚያ ድርጅት፤ አ.አ፥ ሚያዚያ 1998 ዓ.ም።
(6.1▶️ጥያቄ) ይቀጥላል...
@gedlatnadersanat